ሆሳዕና ጥር 27 ቀን 2017 (ማ.ኢ.ፖ.ኮ)
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል በተቀናጀ አኳሀን የተፋሰስ ስራ እየተሰራ ነዉ።
ይህንን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ፖሊስ የወንጀልና የትራፊክ አደጋን በህብረተሰቡ እገዛ አሰቀድሞ መከላከል ይችል ዘንድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ መሆኑንና የፖሊስ አባላትም በልማት ስራዉ ለይ ተሳትፎ እያደረጉ ይገኛሉ።
የሀላባ ዞን ፖሊስ መምሪያ፣ የ3ቱም ወረዳ እና የቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አመራርና አበላት ተሳታፊ መሆናቸዉ ተነግሯል።
የሀላባ ዞን ፖሊስ የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነትን ለመጠበቅና ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው ከፀጥታ አካለት ጋር ተቀናጅቶ እየሰራ መሆኑን ከዞኑ ፖሊስ የደረሰን መረጃ አመላክቷል።
##ሰላም