የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር(PSSSA)

@publicpsssa


Public servants social security administration official Telegram channel

የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር(PSSSA)

18 Oct, 16:09


አስተዳደሩ የተለያዩ ሠነዶችን ለሚያዘጋጁ አመራሮች እና ሠራተኞች ተግባር ተኮር ስልጠና መስጠት ጀመረ
============//===========
የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ስድስት የተለያዩ ሠነዶችን ለሚያዘጋጁ አመራሮች እና ሠራተኞች ከጥቅምት 05 ቀን 2017 ጀምሮ በቢሾፍቱ ከተማ ተግባር ተኮር ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል።
ተግባር ተኮር ስልጠናው የተለያዩ ስትራቴጂዎች እና መመሪያዎችን ለማዘጋጀት የሚያግዙ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን በስልጠናዉ ጎን ለጎን አስተዳደሩ ወደ ኢንቨስትመንት ዉስጥ በስፋት እንዲሳተፍ የሚያግዝ የኢንቨስትመንት ስትራቴጂ፣ የአስተዳደሩን ገጽታ የሚገነባ እና ተቋማዊ ሚናውን አጉልቶ የሚያሳይ የኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ፣ የአዋጭነት ዳሰሳ ጥናት፣ የሥራ አፈጻጸም ምዘና መመሪያ፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ መመሪያ እንዲሁም የዜጎች ቻርተር እየተዘጋጀ ይገኛል።
በዚህ ተግበራ ተኮር ስልጠና እና ስትራቴጂ እና መመሪያ ዝግጅት ስራ ላይ 35 የአስተዳደሩ አመራሮች፣ የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
//****
ጥቅምት 8 / 2017
ቢሾፍቱ

የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር(PSSSA)

14 Oct, 08:49


17ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በድምቀት ተከበረ
=========//=======
የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር አመራሮችና ሠራተኞች 17ኛውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!”  በሚል መሪ ቃል ጥቅምት 4/2017 በድምቀት አከበሩ።

በበዓሉ አከባበር ላይ የአስተዳደሩ የኮርፖሬት ሪሶርስ ማኔጅመንት ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አምባሳደር ምስጋና አድማሱ፣ ሠንደቅ ዓላማ የብሔራዊ አንድነት መገለጫ፤ ዜጎች አገራዊ ፍቅርና ብሔራዊ ስሜታቸውን የሚገልፁበት፤ ታሪካዊ ትስስርና ስነ-ልቦናዊ አንድነት የሚንፀባረቅበት የአንድነትና ህብረት ዓርማና ምልክት ነው ያሉ ሲሆን፣ ሀገራችን ክብሯን እና ነጻነቷን ጠብቃ፣ አሁን የተጋረጡባትን ፈተናዎች ሁሉ አልፋ፣ የብልጽግና ጉዞዋን ለማስቀጠል፣ ለበርካታ ሀገራትም የነጻነት ተምሳሌት የሆነውን የሠንደቅ ዓላማችንን ክብር በማስጠበቅ ለብሔራዊ አንድነታችንና ሉዓላዊነታችን ያለንን ቁርጠኝነት የምናድስበትና ከምን ጊዜውም በላይ ኃላፊነታችንን የምንወጣበት ወሳኝ ወቅት ላይ እንገኛለን ብለዋል። አምባሳደሩ አክለውም የሀገራችንን ልማት እና ዕድገት የማይፈልጉ የውስጥና የውጭ ጠላቶቻችን በነጻነታችን እና በሉዓላዊነታችን ላይ የጋረጡብንን ፈተና ለመመከትና ለመቀልበስ ሁላችንም በመናበብና በመደራጀት በተባበረ ክንድ በጋራ ልንቆም ይገባል ብለዋል፡፡

17ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዋናው መ/ቤት፣ በሪጅኖች እና በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችም ጭምር በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት የተከበረ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል።

//****
ጥቅምት 4 / 2017
አዲስ አበባ

የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር(PSSSA)

07 Oct, 14:15


ለተተኪ ህጻናት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ
============//===========
የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተደዳር የምዕራብ ሪጅን ጽ/ቤት ሠራተኞች ድጋፍ ለሌላቸዉ 22 ተተኪ ህጻናት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል፡፡

//***

የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር(PSSSA)

04 Oct, 10:06


እንኳን ለኢሬቻ  በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
=========//===========
የመንግስት ሠራተኞች ማኀበራዊ ዋስትና አስተዳደር እንኳን ለኢሬቻ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡

ኢሬቻ በኦሮሞ ዘንድ ፆታ፣ እድሜ፣ ኃይማኖት እና መሰል ልዩነቶች ሳይገድቡት ይቅር በመባባል፣ በአብሮነት እንዲሁም ከክረምት ወደ በጋ፣ ከጨለማ ወደ ብርሀን፣ በወንዝ ሙላት ከመለያየት ወደ አንድነት፣ ከዘመን ወደ ዘመን ያሸጋገረውን ፈጣሪዉን የሚያመሰግንበት ታላቅ በዓል ነዉ።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የበረከት እንዲሆን እንመኛለን!

መልካም በዓል!

የመንግስት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አስተዳደር

://***

የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር(PSSSA)

27 Sep, 02:28


እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ!
===========//===============
የመንግስት ሠራተኞች ማኀበራዊ ዋስትና አስተዳደር እንኳን ለ2017 መስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የበረከት እንዲሆን እንመኛለን!

መልካም በዓል!

የመንግስት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አስተዳደር

://***

የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር(PSSSA)

20 Sep, 05:22


የመንግስት ሠራተኞች ማኀበራዊ ዋስትና አስተዳደር የሥራ ውል ስምምነት ተፈራረመ
=============//===========
አዲስ አበባ፡ መስከረም 3/2017 ዓ.ም፡ የመንግስት ሠራተኞች ማኀበራዊ ዋስትና አስተዳደር  ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር  ጋር የሥራ ውል ስምምነት ተፈራረሙ።

ስምምነቱ ዌብ ላይ መሰረት ያደረግ የተቀናጀ ብሔራዊ የማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል ሲሆን ስራዉ በውስጡ-7 ንዑስ ሲስተሞች የያዘ መሆኑን ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ድህረገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ትግበራዉ ሲጠናቀቅ የጡረታ ምዝገባን፣ የጡረታ መዋጮ ክፍያን፣ የጡረታ ተጠቃሚነትን እና ሌሎች ስርዓቶችን በማቀናጀት እና በቴክኖሎጂ በማዘመን ሥራን የሚያቀላጥፍ ይሆናል ተብሎ ይገመታል።

ከሶስት አመት በፊት ጀምሮ አስተዳደሩን ብቃት ባለዉ የሰዉ ሀይል ለማደራጀትና አሰራሮችን በቴክኖሎጂ ለማዘመን ሰፊ የሪፎርም ሥራዎች ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑ ይታወቃል ።

://***

የመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር(PSSSA)

09 Sep, 13:57


የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ከመንግስት አሠሪ መስሪያ ቤቶች ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ
=========//==============
የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ከማስረጃ አያያዝ እና ከጡረታ መዋጮ ገቢ አሰባሰብ ጋር በተያያዘ ከመንግስት አሠሪ መስሪያ ቤቶች የስራ ኃላፊዎች ጋር ጳጉሜ 4 ቀን 2016 የምክክር መድረክ አካሄደ።

በመድረኩ ላይ የተገኙት በአስተዳደሩ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን በቀለ እንዳሉት ተቋሙ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎችን በማከናወን አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን በርካታ ጥረቶችን በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ የዚህ መድረክ አላማም በተቋሙ የሪፎርም ስራዎችና በማስረጃ አያያዝ ላይ ግንዛቤ መፍጠር ነው ብለዋል። የአዋጅ ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ ከጡረታ መዋጮ ገቢ አሰባሰብ ጋር በተያያዘ የአስተዳደሩ አፈጻጸም መሻሻል የታየበት ሲሆን፣ በቀጣይም ከተለያዩ ተቋማት ጋር ስራዎችን በጋራ ለመስራት ዕቅድ የተያዘ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚዉ እንደገለፁት ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና ከማዕከላዊ ስታትስቲክስ አገልግሎት ጋር በጋራ በመሆን የመንግስት ሠራተኞችን ቆጠራ ለማካሄድ የታቀደ ሲሆን፣ አሠሪ መስሪያ ቤቶችም ትክክለኛ መረጃ በመስጠት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

በምክክር መድረኩ ላይ በጡረታ አዋጅ ማስፈጸሚያ መመሪያዎች፣ በምዝገባና የጡረታ አበል ውሳኔ የመረጃ አቀራረብ ላይ እንዲሁም በጡረታ መዋጮ ገቢ አሠባሰብ ላይ ትኩረት ያደረጉ ገለጻዎች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል።

በዋናው መስሪያ ቤት በተካሄደው በዚህ የውይይት መድረክ ላይ ከ72 የፌዴራል አሠሪ መስሪያ ቤቶች የተገኙ 144 የሰው ሃብት እና የፋይናንስ የስራ ኃላፊዎች ተካፍለዋል።
://***
ጳጉሜ 4/2016 ዓ/ም
አዲስ አበባ