Ethiopian Electric Utility @eeuethiopia Channel on Telegram

Ethiopian Electric Utility

@eeuethiopia


EEU Official Telegram Channel
Web: www.eeu.gov.et

Ethiopian Electric Utility (English)

Are you interested in staying updated with the latest news and information from the Ethiopian Electric Utility (EEU)? Look no further than the EEU Official Telegram Channel! As the official channel of EEU, you can expect to receive timely updates, announcements, and important information regarding the electric utility sector in Ethiopia. From new projects and initiatives to service disruptions and outage notifications, this channel will keep you informed and in the know. Stay connected with the EEU Official Telegram Channel to stay ahead of the curve and be well-informed about everything related to the Ethiopian Electric Utility. Join us today by visiting our website at www.eeu.gov.et and become a part of our growing community of subscribers!

Ethiopian Electric Utility

19 Feb, 08:44


አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመስጠት እየተሠራ ነው

አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ የኃይል መቆራረጥ ችግር የሚታይባቸዉ መስመሮችን በመለየት የመልሶ ግንባታ ስራ እያከናወነ እንደሚገኝ የደብረ-ብርሃን ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ደሳለኝ ገለጹ፡፡

ሀገረ ማርያም 33 ኬ.ቪ፣ እነዋሪ 33 ኬ.ቪ፣ አጣዬ 15 ኬ.ቪ እና አረርቲ 33 ኬ.ቪ መስመሮች የኃይል መቆራረጥ የሚስተዋልባቸው ከፍተኛ መስመሮች መሆናቸውን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ የእንዋሪ 33 ኬ.ቪ መስመር 42 ሳታላይቶችን እና የእንዋሪ ከተማ መጋቢ መስመር በሸክላ ሲኒ የተዘረጋ በመሆኑ ችግሩን ለመፍታት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ ሪጅኑ ባከናወነው መስመር ፍተሻ ስራ ከደብረ ብርሃን እስከ እንዋ ሪ የተዘረጋው 67 ኪ.ሜ መስመር፤ ከደነባ-አንጭቆረር 12.5 ኪ.ሜ እና ከደነባ - ሲያ ደብር 16 ኪ.ሜ በአጠቃላይ 95.5 ኪ.ሜ መስመር ላይ ያሉት 6000 የሸክላ ሲኒዎች ሙሉ በሙሉ የማያገለግሉ መሆናቸውን ማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ሪጅኑና ማዕከላቱ በጋራ ባከናወኑት ሥራ ከደብረ ብርሃን እስከ እንዋሪ አና ከደነባ እስከ አንጭቆረር የተዘረጉ 3,300 ሸክላ ሲኒዎችን ወደ ፕላስቲክ ሲኒ የመቀየር ስራ እንዲሁም የረገቡ መስመሮችን የመወጠር ስራ መከናወኑን አብራርተዋል፡፡

በመጨረሻም ዳይሬክተሩ በ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ሪጅኑ በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚታዩ ጉድለቶችን የመለየት እና የቅድመ ጥገና ሥራዎችን በስፋት ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል፡፡

በግማሽ ዓመቱ 1365.4 ኪ.ሜ መካከለኛ መስመር ላይ ያሉ ችግሮችን የመለየት ሥራ በማከናወን 251.5 ኪ.ሜ የቅድመ ጥገና እና 1785 ቁጥር ያለው አስቸኳይ ጥገና ስራ መሠራቱን ገልጸዋል፡፡

Ethiopian Electric Utility

19 Feb, 06:51


ኤሌክትሪክ እና የመስኖ ልማት!!

Ethiopian Electric Utility

19 Feb, 06:21


በአዲስ አበባ እና ሐረር ከተሞች የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎችለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1208?lang=am

Ethiopian Electric Utility

18 Feb, 11:52


በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ታወር ላይ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት የሃይል አቅርቦት ተቋርጧል

ከላሊበላ - አላማጣ በተዘረጋ 66 ኪ.ቮልት ትራንስሚሽን መስመር ታወር ላይ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት ከላሊበላ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በሽምሽሀ ፣ በብልባላ፣ በላልኪው፣ በአዲስ አምባ፣ በገለሶት፣ በገ/ማሪያምና ነአኩቶለአብ ሳተላይት ጣቢያዎች፤ ከአይና አገልግሎት መስጫ ማዕከል በብርኮ፣ በቅዱስ ሀርቤ፣ በአይና ሚካኤል እና ዳሪያ ሳተላይት ጣቢያዎች፤ ከሙጃ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በኩልመስክ፣ በወንዳች፣ በደንሳና ጠረወንዝና ሳተላይት ጣቢያዎች የሃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ የተፈጠረው ችግር በወልድያ ሪጅን በኩል ተፈትቶ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁ በአክብሮት እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

18 Feb, 07:29


ለመልሶ ግንባታና አቅም ማሰደግ ሥራ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው

ለመካከለኛ መስመር መልሶ ግንባታ እና አቅም ማሳደግ ሥራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የወላይታ ሪጅን የኔትወርክና ኢንፍራስትራክችር ኃላፊ አቶ ገረሱ ቴጋ ገልፀዋል፡፡

የመልሶ ግባታ ስራው እየተከናወነ የሚገኘው በስድስቱ ከተሞች ያልተካተቱ እና የኃይል መቆራረጥ በሚስተዋልባቸው የገሡባ፣ የበቁሎሠኞ፣ የቦዲቲ፣ ሻንቶ እና የኮሙቡጠበላ ወረዳዎችን ያቀፈ መሆኑን ኃላፊው አስታውቀዋል፡፡

በመልሶ ግንባታ ስራው 420 ምሰሶዎች ተከላ እና 49 ነጥብ 5 ኪ.ሜ መካከለኛ መስመር ዝርጋታ መከናወኑን የገለፁት አቶ ገረሱ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የመልሶ ግንባታ ስራው 95 በመቶ መጠናቀቁን አስታውቀዋል፡፡

የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቱን ለመገንባት ከ63 ሚሊየን 621 ሺህ ብር በላይ በጀት ተመድቦለት ወደሥራ መገባቱን ጨምረው ገልጿል፡፡

በተጨማሪም ኃላፊው ለጨለለቅቱ አንድ ባለ 1250 ኪ.ቮ.አ፣ ለቦረዳ ባለ 630 ኪ.ቮ.አ አዲስ ትራንስፎርመር የተከለ ሲሆን ቦምቤ፣ ቦዲቲ እና ወናጎ ላይ የተተከሉ ትራንስፎርመሮች አቅም ከ100 ኪ.ቮ.አ ወደ 200 ኪ.ቮ.አ እንዲያድጉ ተደርጓል ብለዋል፡፡

የመካከለኛ መስመር አቅም ግንባታ ስራ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው በዝቅተኛ መስመሮች ላይ ደግሞ የቅደመ መከላከል ሥራ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የመልሶ ግንባታ እና አቅም ማሰደግ ሥራዎች አዲስ የኃይል ተጠቀሚን ለማፍራት፣ ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ የሚያግዝ ነው፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

18 Feb, 06:06


የገጠር ከተሞችን በአማራጭ የሃይል ምንጭ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተከናወኑ ለሚገኙ እንቅስቃሴዎች ማሳያ !!

Ethiopian Electric Utility

17 Feb, 17:34


በኃይል አስተላለፊያ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የኃይል አቅረቦት

ከኮሶበር -ቻግኒ በተዘረጋው 66 ኪ.ቮልት ኃይል አስተላለፊያ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት ቻግኒን ጨምሮ በመተከል ዞን፣ በግ/በለስ ከተማ፣ በማንዱራ፣ በፖዌ፣ በዲባጠ፣ በቡለን፣ በደ/ዘይት፣ በዳንጉርና አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ የተፈጠረው ብልሽት ተጠግኖ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁ በአክብሮት እንጠይቃለን።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

17 Feb, 14:32


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተሳለጠና የተቀናጀ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በመስጠት 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 46ኛው የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው አስተዋፆ በመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት እውቅና ተሰጥቶታል፡፡

Ethiopian Electric Utility

17 Feb, 10:09


በቂ የትራንስፎርመር አቅርቦት ያለ በመሆኑ አዲስ ኃይል ጠያቂ ደንበኞች ከተቋሙ መውሰድ ይችላሉ

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቂ የትራንስፎርመር አቅርቦት ያለ በመሆኑ ደንበኞች ከተቋሙ በመውሰድ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ የተቋሙ ኢንጂነሪንግ ዳይሬክተር አቶ ተፈራ ደርቤ ገለፁ፡፡

ኃይል ለማቅረብ የሚያስፈልገው የትራንስፎርመር ግብዓት በተቋሙ ውስጥ የሚገኝ ከሆነ ደንበኞች ማቅረብ እንደማይጠበቅባቸው የጠቀሱት ዳይሬክተሩ በአንፃሩ የሚፈለገው ግብዓት በተቋሙ አለመኖሩ ሲረጋገጥ ደንበኞች እንዲያቀርቡ እየተደረገ አገልግሎቱን እንዲያገኙ ሲደረግ እንደነበር ጠቅሰዋል፡፡

በተለይ ከአሁን በፊት የትራንስፎርመር አቅርቦት ችግር ስለነበር ደንበኞች በራሳቸው ትራንስፎርመር እንዲያቀርቡ ፍቃድ ተሰጥቷቸው በተቋሙ ፍተሻ ከተደረገ በኋላ የጠየቁት ኃይል ባቀረቡት ትራንስፎርመር እንዲገናኝላቸው ይደረግ እንደነበር አስረድተዋል፡፡

ይህ አሠራር ደንበኞች እንዲጉላሉ እና ላላስፈላጊ ወጪ እንዲዳረጉ ከማድረጉም ባሻገር አንዳንድ የትራንስፎርመር አምራቾች የጥራት ችግር ሲገኝባቸው በግል ጥራት የሌለው ትራንስፎርመር ለደንበኞች በመሸጥ ዙሮ ወደ ተቋሙ መሰረተ ልማት እንዲገባ በማድረጋቸው ለሃይል መቆራረጥ መንስኤ እየሆነ በመምጣቱ ለጊዜው ደንበኞች ከአምራቾች መግዛት እንዲያቆሙ መደረጉን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ተቋሙ በአገር ውስጥ ካሉና በስታንዳርዱ መሠረት ማምረት ከሚችሉ አምራቾች ጋር ውል በመያዝ ትራንስፎርመሮችን እየተረከበ እንደሆነ ተናግረው በሌላ በኩል አምርቼ ተቋሙ ሳይገዛኝ ቀረ ወይም ለመግዛት ፍቃደኛ አይደለም የሚል አምራች ካለ ጥያቄውን በግልፅ ማቅረብ ይችላል ብለዋል፡፡

ተቋሙ ከአብዛኞቹ የሃገር ውስጥ የትራንስፎርመር አምራቾች ጋር በቅርበት እየሠራና እያበረታታ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው አምራቾች ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም ዳይሬክተሩ ለአገልግሎት አሰጣጡ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን ከሃገር ውስጥም ሆነ ከውጪ ሃገር አምራቾች እንደሚገዛና በሃገር ውስጥ የማይመረቱ ትራንስፎርመሮችን ከውጪ የሚያስገባ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በዚህ አጋጣሚ ተቋሙ የሃገር ውስጥ አምራቾችን ላለማበረታታ ከሃገር ውስጥ የትራንስፎርመር አምራቾች ግዥ አልፈፅምም እንዳለ ተደርጎ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ተቋማት የቀረበው መረጃ ስህተት መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

17 Feb, 07:27


425 ኪ.ዋ የኤሌክትሪክ ሃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው ፕሮጀክቶች ተመረቁ

425 ኪ.ዋ የኤሌክትሪክ ሃይል የማመንጨት አቅም ያላቸው የካራ ዱስ እና የካራ ቆርጮ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በዛሬው ዕለት ተመርቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል፡፡

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክት ፖርትፎሊዮ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክንፈ ነጋሽ ፕሮጀክቶቹ ለአካባቢው ማህበረሰብ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ትልቅ ፋይዳ ያላቸው መሆኑን ጠቁመው ማህበረቡ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን እንደራሱ ንብረት አድርጎ ሊጠብቅ ይገባል ብለዋል፡፡

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ የተከበሩ ዶ/ር ሱልጣን ወሊን በበኩላቸው የኤሌክትሪክ አገልግሎት በገጠር ቀበሌዎች ተደራሽ መሆን የግብርና ምርቶችን ወደ ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይም የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማረግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡

ፕሮጀክቶቹ የተገነቡት በደቡብ ኦሞ ዞን በሃመር ወረዳ ሥር በሚገኙት የካራ ዱስ እና የካራ ቆርጮ ቀበሌዎች ሲሆን ለ5 ሺሕ 828 ዜጎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው፡፡

በፕሮጀክት ግንባታው በካራ ዱስ 1 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መካከለኛ መስመር፣ 5.5 ኪ.ሜ ዝቅተኛ መስመር ዝርጋታ እና ባለ315 ኪ.ቮ.አ. እና አንድ ባለ100 ኪ.ቮ.አ. ትራንስፎርመር ተከላ ስራ ተከናውኗል፡፡

በተመሳሳይ ለካራ ቆርጮ ቀበሌ ደግሞ 1 ነጥብ 5 ኪ.ሜ የመካከለኛ፣ 3 ኪ.ሜ ዝቅተኛ መስመር ዝርጋታ፣ አንድ ባለ 315 ኪ.ቮ.አ እና አንድ ባለ50 ኪ.ቮ.አ ትራንስፎርመር ተከላ ተከናውኗል ብለዋል፡፡

የካራ ዱስ እና የካራ ቆርጮ 15ኛ እና 16ኛ የፀሃይ ኃይል የኤሌክትሪክ ማመንጫዎች ሲሆኑ የ25ቱ የፀሃይ ኃይል ፕሮጀክት አካል ናቸው፡፡

እሰከአሁን በማዕቀፍ ከተገነቡት የ12 ከፀሃይ ኃይል የኤሌክትሪክ ማመንጫዎች 11 የተጠናቀቁ ሲሆን በዚህም 6 ሺሕ 252 ደንበኞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እያገኙ ናቸው፡፡

ፕሮጀክቱ የተገነባው ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ሲሆን ግንበታውን ለማከናወንም 955 ሺሕ 748 ዶላር እና 13 ሚሊየን 496 ሺሕ 455 ብር ወጪ ተደርጎበታል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 65 ከዋናው የኤሌክትሪክ ቋት ቀሪውን ደግሞ በርቀት ላይ የሚገኙ የገጠር ከተሞችንና መንደሮችን የጸሀይ ኃይል ማመንጫ በመገንባት ኤሌክትሪክ ለሁሉም ዜጋ ለማዳረስ እየሠራ ይገኛል፡፡

በምረቃው ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ የተከበሩ ዶ/ር ሱልጣን ወሊን፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጅክት ፖርትፎሊዮ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክንፈ ነጋሽ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚን ጨምሮ የዱስ እና ቆርጮ የሐገር ሽማግሌዎች እና የወረዳው አመራር ተገኝተዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

14 Feb, 09:07


1 ሺህ 650 ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ሆኑ

የሶዶ ቁጥር 2 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ሲከናወን ከመኖሪያ ቀያቸው የተነሱ 1 ሺህ 650 ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ መደረጋቸውን የወላይታ ሪጅን ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተዘራ ታደሠ ገለፁ፡፡

ነዋሪዎቹን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ 61 ኪ.ሜ ዝቅተኛ እና 21 ነጥብ 23 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም 27 ባለ 15 ኪ.ቮ.አ. ትራንስፎርመሮች መተከላቸውን ጠቅሰው ቀሪ አራት ትራንስፎርመሮች ለመትከል እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ሥራ አስኪያጁ አያይዘውም ነዋሪዎቹን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ 200 ሚሊየን ብር ወጪ መደረጉን ጠቅሰው የወጪው 40 በመቶ በተቋሙ የተሸፈነ ነው ብለዋል፡፡

ኤሌክትሪክ ተጠቃሚየሆኑት የዋጃ ሾያ፣ የወራዣ ላሾ ሱታ፣ የጉርታንጆ፣ የቁጦ፣ የሻምባ ቅሌ፣የላሾ ከተማ፣ የጉርሞ ወይዴ፣ የዋጃ ቄሮ ቀጠና 1፣ 2 እና 3 እንዲሁም የዳሞት ዋጃ ቀጠና 1 እና 2 ቀበሌ ነዋሪዎች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ዝርጋታውን በስድስት ወራት ለማጠናቀቅ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በትራንስፎርመር ግብዓት እጥረት ምክንያት ዝርጋታው ከተያዘው ግዜ በላይ መውሰዱን ጠቅሰዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

14 Feb, 06:17


የመልሶ ግንባታ ስራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

ዛሬ የካቲት 7 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 11:00 ድረስ በኮምቦልቻ ከተማ የመልሶ ግንባታ ስራ ለማከናወን ሲባል በሚጢ ቆሎ (ኮምቦልቻ ከተማ ሳተላይት ጣቢያ እና በባቲ ከተማ ሙሉ በሙሉ) የሃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡

በተመሳሳይ የካቲት 7 እና 8 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 10፡00 ድረስ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 20፣ አዘዞ፣ አባ ሳሙኤል፣ ቀበሌ 18፣ ኢምባሲ፣ ቀበሌ1፣ ቀበሌ13፣ ብልኮ፣ ቀበሌ17፣ አውቶፓርክ፣ ቀበሌ18፣ ቀበሌ7፣ ቀበሌ9፣ አራዳ፣ አዲስ ዓለም፣ ቤዛዊት ማርያም፣ ቀበሌ18፣ ሸዋ ዳቦ፣ ሳንጃ ከተማ የመልሶ ግንባታ ስራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡

ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

14 Feb, 05:59


የወላይታ መልሶ ግንባታ ፕሮጀክት እና በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ያመጣው ለውጥ በደንበኞች እይታ !!

Ethiopian Electric Utility

13 Feb, 12:41


የጨረታ ማስታወቂያ

Ethiopian Electric Utility

13 Feb, 12:14


አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመስጠት እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት

Ethiopian Electric Utility

13 Feb, 06:43


የመስኖ አልሚዎችን የሃይል ጥያቄ ለመመለስ እየተሰራ ነው

የመስኖ አልሚዎችን የሃይል ጥያቄ ለመመለስ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ማሻሻያ ስራ እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአርባ ምንጭ ሪጅን ቁጥር 2 የአገልግሎት መስጫ ማዕከል ስራ አስኪያጅ አቶ ምንአለ አበበ ገለፁ፡፡

ለግብርናው ዘርፍ አስተማማኝና ጥራት ያለው የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን የገለፁት የማዕከሉ ስራ አስኪያጅ በአንድ ግዜ እስከ 689 ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቅመው በመስኖ ለሚያለሙ አርሶ አድሮች ኃይል እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ስራ አስኪያጁ አክለውም በማዕከሉ ሥር ካሉ አራት ትላልቅ የእርሻ አልሚዎች ውስጥ ለሁለቱ አልሚዎችን የትራንስፎርመር አቅም ማሳደግ ስራ በማከናወን ጥራት ያለውና አስተማማኝ የሃይል አቅርቦት እንዲኖር መደረጉን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በግብርናው ዘርፍ ለመሰማራት ጥያቄ ላቀረበ ሌሎች አርሶ አደሮች የ1 ነጥብ 2 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ እና 20 ምሰሶ ተከላ ስራ መከናወኑን የገለፁት አቶ ምንአለ በአንድ ጊዜ እስከ 891 ኪ.ዋ.ሰ የኃይል ጥያቄ ላቀረቡ ደንበኞች ምላሽ ለመስጠት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡

የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቅመው መስኖ የሚያለሙት አቶ ምንተስኖት መኮንን በበኩላቸው በኃይል አቅርቦቱ መደሰታቸውን ተናግረው ኤሌክትሪክን ተጠቅመው በማልማታቸው በገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን እንዳስቻላቸው አመላክተዋል፡፡

አቶ ምንተስኖት አክለውም ከነዳጅ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የኃይል አቅርቦቱን ብቸኛና አዋጭ የኃይል ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ጠቁመው፤እየጨመረ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማርካት ይበልጥ ሊሠራ እንደሚገባው ጠቁመዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

13 Feb, 06:25


በሐረር ክልል የመስመር ዝርጋታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1190?lang=am

Ethiopian Electric Utility

12 Feb, 08:23


ከ6ሺህ 3 መቶ በላይ አዳዲስ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአምቦ ሪጅን ባለፉት 6 ወራት ውሰጥ 6 ሺህ 3 መቶ ዘጠና ዘጠኝ አዳዲስ ደንበኞችን የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል፡፡

ሪጅኑ አዳዲስ ደንበኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ 21 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር እና  60.78 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ዝርጋታ እና 44 ዲስትሪቢዩሽን ትራንስፎርመር ተከላ ስራ ማከናወን ችሏል፡፡

በተያያዘ ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን በመስመር ውስጥ የገቡ ዛፎች የማፅዳት፣ የረገቡ የመካከለኛ እና የዝቅተኛ መስመሮችን ማስተካከል፣ትራንስፎርመሮችን የመጠገን  እና ያረጁ ምሰሶዎች የመቀየር ስራ የሚጠቀሱት ናቸው፡፡  

በተጨማሪም ሪጅኑ 36 ኪ.ሜ እና 54 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር መልሶ ግንባታ ስራ ያከናወነ ሲሆን የ28 የዲስትሪቢዩሽን ትራንስፎርመሮች አቅም ማሳደግ  ስራ በማጠናቀቅ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

12 Feb, 06:08


በሐረር ክልል የመልሶ ግንባታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡- http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1188?lang=am

Ethiopian Electric Utility

12 Feb, 06:04


በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ወቅት የኃይል መቆራረጥ ችግር እንዳይፈጠር የተደረገ ቅድመ ዝግጅት !!

Ethiopian Electric Utility

11 Feb, 13:45


የኤሌክትሪክ ኬብል ግዢ ለመፈፀም የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኬብል ግዢ ለመፈፀም የሚያስችለውን ስምምነት ዛሬ የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ተፈራርሟል፡፡

የኬብል ግዢ ስምምነቱ የተፈረመው ቲቢኤ ዲያንግ ኬብል ካምፓኒ ከተሰኘ የቻይና ኩባንያ ጋር ሲሆን በስምምነቱ መሠረት የኬብል አቅርቦቱ በ9 ወራት ተጠናቆ የሚቀርብ ይሆናል፡፡

የኬብል ግዢው የተፈፀመው በዋናነት በገጠር እና በከተማ ያለውን የአዲስ ኃይል ጥያቄ ለማስተናገድ እንዲሁም የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ዝርጋታ ለማከናወን ነው፡፡

ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ክቡር ኢንጂነር ሽፈራው ተሊላ እና የቲቢኤ ዲያንግ ኬብል ካምፓኒ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ጅልበርት ዛዎ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ክቡር ኢንጂነር ሽፈራው ተሊላ በፊርማ ስነ ስርዓቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት የኬብል ግዢ ስምምነቱ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ አዲስ ኃይል ጠያቂ ደንበኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ አቅርቢ ድርጅቱ በጥራትና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ እንዲያቀርብ ጠይቀዋል፡፡

የቲቢኤ ዲያንግ ኬብል ካምፓኒ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ጅልበርት ዛዎ በበኩላቸው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ለመስራት ዕድሉን በማግኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው ቃላቸውን ጠብቀው የሚያቀርቡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ለኬብል ግዢ ስምምነቱ 66 ሚሊየን 123 ሺህ 842 የአሜሪካን ዶላር እና 37 ሚሊዮን 233 ሺህ 62 ብር ወጪ የሚደረግ ሲሆን ወጪው ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የሚሸፈን ይሆናል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

11 Feb, 07:06


የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በስኬት እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ተደርጓል

38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 46ኛው የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ ከጅምሩ እስከ ፍፃሜው ያለምንም የኃይል መቆራረጥ ችግር እንዲጠናቀቅ የቅድመ-ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤክትሪክ መሰረተ ልማት ማኔጅመንት ሥራ አስፈጻሚ ገበየሁ ሊካሳ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

ስራ አስፈጻሚው አክለውም በጉባዔው ወቅት የሃይል መቆራረጥ ችግር እንዳይፈጠር የሚያስችሉ የቅድመ ጥገና ስራዎች መከናወናቸውን እና ከዚህ ጎን ለጎን ድንገት መቆራረጥ ቢከሰት ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ ራሱን የቻለ ግብረ ኃይል ተዋቅሮ ወደ ሥራ መግባቱን ተናገረዋል፡፡

በጉባኤው ወቅት ሊከሰት የሚችለውን የኃይል መቆራረጥ ለመቀነስ በርካታ የቅድመ መከላክልና ማሻሻያ ስራዎቸ መሰራታቸውን የገለፁት ዶክተር ገበየሁ በአዲስ አበባ 92 የመካከለኛ ቮልቴጅ መስመሮች ላይ ከፍተኛ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡

ከተከናወኑ የቅድመ መከላከል ስራዎች መካከል የኤሌክትሪክ መስመሮችን ከዛፎች የማፅዳት፣ የረገቡ መስመሮችን መወጠር፣ የላሉ ሲኒዎችን ማስተካከል እና ያረጁ ምሰሶዎችን የመቀየር ሥራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ 14 ዋና ዋና ቦታዎችን የሚመግቡ መስመሮችን እንደ አደዋ መታሰቢያ ሙዚየም፣ የአፍሪካ ኮንቬንሽን፣ የአፍሪካ ህብረት፣ ብሔራዊ ባንክ፣ ወዳጅነት አደባባይ፣ ሸራተን ሆቴል እና ሌሎችም የተመረጡ ቦታዎች ተጨማሪ መስመር እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል፡፡

ከነዚህ በተጨማሪ 15 የሚጠጉ ሰብስቴሽኖች ላይ ኃይል የማቀናነስ ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን ከባለድርሻ አካላት ጋር መሠራት ያለባቸው ሥራዎችም በጋራ መሠራቱ ተጠቅሷል::

Ethiopian Electric Utility

11 Feb, 06:19


በሐረር ከተማ የመልሶ ግንባታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1185?lang=am

Ethiopian Electric Utility

08 Feb, 07:16


የጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

Ethiopian Electric Utility

08 Feb, 06:02


በአዲስ አበባ ከተማ የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1182?lang=am

Ethiopian Electric Utility

07 Feb, 07:50


የጨረታ ማስታወቂያ

Ethiopian Electric Utility

07 Feb, 07:38


በ222 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር ወጪ የትራንስፎርመር ዘይት ግዢ ተፈጸመ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ222 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር ወጪ 3 ሺህ 900 በርሜል የትራንስፎርመር ዘይት ግዥ መፈፀሙን የተቋሙ ዕቃ ግምጃ ቤት ኃላፊ አቶ ቢኒያም ገ/ እግዚሕአብሔር አስታወቁ፡፡

ኃላፊው አክለውም የተገዛው የትራንስፎርመር ዘይት ትራንሰፎርመሮች እንዳይቃጠሉ ከማድረጉ ባሻገር ጥራት ያለውና አስተማማኝ ኤሌክትሪክ አገልገሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የተገዛው የትራንስፎርመር ዘይት ለተያዘው በጀት ዓመት እና ለቀጣይ ዓመት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

የትራንስፎርመር ዘይት መግባቱ በጥገና ክፍል የዘይት መምጣት እየተጠባበቁ ላሉ እና ዘይት ጨርሰው ለመቃጠል ጫፍ የደረሱ ትራንስፎርመሮችን ይታደጋል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም ኃላፊው የትራንስፎርመር ዘይት በሚፈለገው መጠን መቅረብ ወጥ የሆነ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ እንዲሁም ውድ የሆነው የተቋሙን ንብረት ለረጅም ጊዜ እንዲያገለግል ያደርጋል ብለዋል፡፡

አንድ ትራንስፎርመር አዲስ ከሆነ ከ2 እስከ 4 በርሜል ዘይት የሚሞላ ሲሆን አገልግሎት ላይ ያለ ከሆነ ከሃያ እስከ አርባ ሊትር ይሞላለታል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

07 Feb, 07:16


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብዎን በቀላሉ፣ የትም ሳይሄዱ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ካሻዎ በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕሮ ወይም በኤም ፔሳ በኩል ይፈፅሙ፡፡

ፍጆታዎ በስልክዎ! ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ በመምረጥ ኑሮዎን ያቅሉ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

07 Feb, 06:10


በአዲስ አበባ እና ሐረር ከተሞች የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1179?lang=am

Ethiopian Electric Utility

06 Feb, 16:44


የቅጥር ማስታወቂያ

Ethiopian Electric Utility

06 Feb, 16:42


ኃይል ስርቆት በፈፀሙ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል ስርቆት በፈፀሙ 157 የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ወስዷል፡፡ እርምጃ ከተወሰደባቸው የንግድ ተቋማት ውስጥ 120 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን፣15 በደቡብ አዲስ አበባ፣ 13 በሸገር ከተማ፣ 9 ምዕራብ አዲስ አበባ  እና  አንዱ በጭሮ ሪጅን የሚገኝ ነው፡፡

የሰሜን አዲስ አበባ 10 ሚሊየን፣ ደቡብ አዲስ አበባ 4 ሚሊየን ፣ ሸገር 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር እንዲሁም ምዕራብ አዲስ አበባ 2 ነጥብ 4  የፍጆታ ሂሳብ ማስከፈላቸው ታውቋል፡፡  የኃይል ስርቆት የፈፀሙት በአንድ ሼድ ውስጥ የሚገኙ እንጀራ የሚጋግሩ ማኅበራት፣ ወፍጮ ቤቶች እና የብሎኬት ማምረቻዎች ናቸው፡፡   

የኃይል ስርቆቱ  መፈፀሙ የተረጋገጠው  በተቋሙ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ መመርመሪያ  ቤተ-ሙከራ  ሲሆን  ስርቆት የፈፀሙት ግለሰቦች ላይ የወንጀል ክስ ተመስርቶ ክትትል እየተደረገ ይገኛል፡፡

ከተፈቀደለት የኤሌክትረክ ኃይል ውጭ ሲጠቀም የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ በሃገሪቱ የኢነርጂ አዋጅ ቁጥር 810/2006 መሰረት በህግ ተጠያቂ የሚሆን ሲሆን አዋጁን ተላልፎ የስርቆት ተግባር ሲፈፅም የተገኘ ማንኛውም አካል በሕግ ከመጠየቁም በተጨማሪ ይጠቀምበት የነበረው አገልግሎት እንደሚቋረጥና ያላግባብ ለተጠቀመው የፍጆታ ሂሳብ በታሪፉ መሰረት ተሰልቶ ከዳግም ማስቀጠያ ክፍያ እና ከተጨማሪ ቅጣት ጋር እንዲከፈል ይደረጋል፡፡

በኢነርጂ አዋጁ አንቀፅ 28  የኤሌክትሪክ ኃይል የሰረቀ፣ በሕገ-ወጥ መንገድ ከሌላ ጋር ያገናኘ፣ መስመር ያሰናከለ   ወይም መስመሩ እንዲሰናከል ያደረገ፣ ወይም መስመሩ የተሰረቀ፣ በሕገ-ወጥ መንገድ ከሌላ መስመር ጋር የተገናኘ ወይም የተሰናከለ መሆኑ እያወቀ  የኤሌክትሪክ ኃይል ለፍጆታ ያዋለ ወይም የተገለገለ በኃይል ስርቆት ወንጀል ተከሶ እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እና እስከ 50 ሺህ ብር በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡፡   

ከዚህ በተጨማሪ የኃይል ስርቆት መፈፀም በሃገሪቱ የፍትሃ-ብሔር እና የወንጀል ህግ መሰረት ተጠያቂነት የሚያስከትል ከመሆኑም ባሻገር ለትራንስፎረመር መቃጠል፣ ለሃይል መቆራረጥ እና ለከፍተኛ የኤሌክትሪክ አደጋ መንስኤ ስለሆነ ማንኛውም አካል ይህን መሰል እኩይ ተግባር  ከመፈፀም ሊቆጠብ ይገባል፡፡ 
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

06 Feb, 06:25


በአዲስ አበባ ከተማ የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption?lang=am

Ethiopian Electric Utility

05 Feb, 08:44


አዲስ ሃይል ፈላጊ ደንበኞች ማሟላት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች

ውድ ደንበኛችን አዲስ ቆጣሪ ለማግኘት ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላችን ሲመጡ ከዚህ በታች የተገለፁትን ቅድመ ሁኔታዎች እንዲያሟሉ እንጠይቃለን፡፡

የነጠላ ፌዝ ቆጣሪ /Single Phase Meter/ ለማግኘት፡-

• የአመልካቹ የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት ወይም መንጃ ፈቃድ፣
• አንድ ጉርድ ፎቶ /3 በ 4 የሆነ/፣
• የኪራይ ቤት ከሆነ ከባለቤቱ የተሰጠ የስምምነት ደብዳቤ፣
• ለኃይል ማሻሻያ ወይም ለተጨማሪ ቆጣሪ ከሆነ የኤሌክትሪክ ፍጆታ የመጨረሻ ክፍያ ደረሰኝ፣
• ጥያቄው ለሽርክና ማህበር ከሆነ በተራ ቁጥር 1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የሽርክና ማረጋገጫ ሰነድ ኮፒ፤

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ሙሉ መረጃውን ለማግኝት ይህን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ያንብቡ: -
http://www.ethiopianelectricutility.gov.et/contents/getting-electricity?lang=am

Ethiopian Electric Utility

05 Feb, 07:28


ከ21 ሺህ በላይ አዳዲስ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ
*****
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአገር አቀፍ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም 21 ሺህ 104 አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድርግ ችሏል፡፡

በፕሮግራሙ በተጠናቀቀው የመጀመሪያ ስድስት ወራት ውስጥ ተጠቃሚ ከሆኑ አዳዲስ ደንበኞች ውስጥ 6 ሺህ 455 በኦሮሚያ፣ 6 ሺህ 306 በአማራ፣ 2 ሺህ 374 በትግራይ፣ 288 በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ 64 በጋምቤላ ክልል እና ሌሎች ደግሞ በሌሎች ክልሎች የሚገኙ ናቸው፡፡

ደንበኞችን ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ 639 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር፣1 ሺህ 61 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር እና 245 ትራንስፎርመር ተከላ ስራ ተከናውኗል፡፡

በተመሳሳይ በዋናው የኃይል ቋት እና በፀሐይ ኃይል ምንጭ የገጠር ከተሞችን በማገናኘት አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡

ተቋሙ ከዋናው የኤሌክትሪክ መረብ ርቀው በገጠሩ የሃገራችን ክፍል የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን አማራጭ የሃይል ምንጮችን በመጠቀም ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

05 Feb, 06:24


በአዲስ አበባ እና ጋምቤላ የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption?lang=am

Ethiopian Electric Utility

04 Feb, 11:09


ተግባራዊ እየተደረገ ሚገኘው የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ እና ለደንበኞች የሚኖረው ጠቀሜታ !!

Ethiopian Electric Utility

04 Feb, 06:39


የሀላላ ኬላ ሎጅ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆነ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ዳውሮ ዞን በሎማ ቦሣ ወረዳ የሚገኘው ሃላላ ኬላ ሎጅ በ140 ሚሊየን ብር ወጪ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እንዲሆን መደረጉን የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ገብረ ገለፁ፡፡

የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነዉን የቱሪስት መዳረሻ ተጠቃሚ ለማድረግ የ36 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ፣አንድ ባለ 800 ኪ.ቮ.አ ኮምፓክት ትራንስፎርመር ተከላ እንዲሁም አንድ የኤ.ኤም.አይ ስማርት ቆጣሪ መገጠሙን ተናግረዋል፡፡

የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታውን በ6 ወራት በማጠናቀቅ ከጥር አጋማሽ ጀምሮ የቱሪስት መዳረሻው የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡

የሀላላ ኬላ የቱሪስት መዳረሻ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ዝርጋታ ወጪ የተሸፈነዉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

11 Jan, 07:32


ለጥገና ሥራ ሲባል በእቅድ የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

እሑድ ጥር 4 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:00 እስከ 8:00 ድረስ በቃሊቲ ጂ አይ ኤስ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመሮች ላይ የጥገና ሥራ ስለሚከናወን የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል።

ስለሆነም በሀይሌ ጋርመንት፣ በአፍሪካ ህብረት የምርምር ማእከል፣ በሰፈራ፣ በቡልቡላ ፣ በአቦ ኮንዶሚኒየሞች፣ በኦሮሚያ ውሃ ሥራዎች፣ በቃሊቲ ኢንዱስትሪ መንደር፣ በወርቁ ሰፈር፣ በገላን ጎሮ፣ በቃሊቲ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ የሚቆይ ስለሆነ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን ።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

11 Jan, 06:51


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በወቅቱ አለመፈፀም ለተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብና ቅጣት የሚዳርግ መሆኑን ያውቃሉ? እንግዲያውስ እንንገርዎ!! ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በወቅቱ አለመፈፀም ለተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብና ቅጣት ይዳርጋል፡፡ ስለሆነም ውድ የድህረ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባችሁን በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በወቅቱ እንድትፈፅሙ እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

11 Jan, 06:42


የቢሾፍቱ ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከል 901 አዳዲስ ደንበኞችን ተጠቃሚ አደረገ

በፊንፊኔ ዙሪያ የቢሾፍቱ ቁጥር 2 አገልግሎት ማእከል በያዝነው 2017 በጀት ዓመት 9 መቶ አንድ የሚሆኑ አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል፡፡

ለአዳዲስ ደንበኞች ቅድሚያ እየሰጠ በመሥራት ላይ የሚገኘው ማዕከሉ በበጀት ዓመቱ በፕሮጀክት እና በራስ ኃይል የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ማስፋፊያ ሥራዎችን ያከናወነ ሲሆን 2.88 ኪሎ ሜትር ዝቅተኛ መስመር፣ 2.5 ኪሎ ሜትር የመካከለኛ መስመር እና 8 አዳዲስ ትራንስፎርመሮችን መትከል ችሏል፡፡

ባሳለፍነው ሩብ ዓመት በማዕከሉ 212 የሚሆኑ ስማርት ቆጣሪዎች የተገጠሙ ሲሆን ከነዚህ መካከልም ትልልቅ ኢንዱስትሪዎች ዋነኞቹ ሲሆኑ ለአብነት ያህል የብረት ማቅለጫ፣ የአበባ ልማት፤ የምግብ እና የፕላስቲክ ፋብሪካ፤አግሮ ኢንዱስትሪና መሰል ትላልቅ ተቋማትን ያካተተ ነው፡፡

ስማርት ቆጣሪ ከተቀየረ በኋላ የማዕከሉ ገቢ በእጥፍ ያደገ ሲሆን በየዕለቱ ንባብ ስለሚያደርግ ተቋሙ ማግኘት የሚገባውን ገቢ በአግባቡ ማግኘት ችሏል፤ በዚህም ማዕከሉ በአራት ወራት ውስጥ ከታቀደው 96.91 በመቶ አፈጻጸም ከእጥፍ በላይ በማሳካት 278.02 በመቶ አስመዝግቧል ችሏል፡፡

ማዕከሉ አጠቃላይ 25 ሺ 823 ደንበኞች ያሉት ሲሆን 15 ሺ 26 ያህሉ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚዎች ሲሆኑ ቀሪዎቹ 10 ሺ 850 የቅድመ ክፍያ ደንበኞች ናቸው፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

11 Jan, 05:57


በአዲስ አበባ ከተማ የመስመር ዝርጋታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1124?lang=am

Ethiopian Electric Utility

10 Jan, 08:21


ከፍለው ትራንስፎርመር ሲጠብቁ የነበሩ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ

የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለመሆን ከፍለው ትራንስፎርመር ሲጠብቁ ሲጠባበቁ የነበሩ የኢንዲስትሪ፣ ኮሜርሻል እና የአጠቃላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ፈላጊ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡

ትራንስፎርመር የቀረበላቸው ደንበኞች በአዲስ አበባ ባሉ አራቱም ሪጅኖች እና ለሸገር ሪጅን መሰመር እና ሌሎች መሰረተ-ልማት ተሟልቶላቸው ወረፋ ሲጠባበቁ የነበሩ ናቸው፡፡

በአጠቃላይ ከቀረቡት 210 ትራንስፎርመሮች ውስጥ 90 በምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን፣ 43 ሸገር ከተማ፣ 34 ደቡብ አዲስ አበባ፣ 23 ምዕራብ አዲስ አበባ ሪጅን፣ 20 ሰሜን አዲስ አበባ ለሚገኙ ደንበኞች የተሰራጩ ትራንስፎርመሮች ናቸው፡፡

የትራንስፎርመሮቹ መገዛት ከፍለው ሲጠባበቁ የነበሩ ደንበኞች ቅሬታ ሙሉ በሙሉ እንደሚፈታ እና የተቋሙን የኃይል ፍጆታ ገቢ የሚጨምር ነው፡፡

ትራንስፎርመሮቹን ለመግዛት 300 ሚሊየን ብር አጠቃላይ ወጪ የተደረገባቸው ሲሆን የትራንስፎርመር ተከላው በአዲስ አበባ ከተማ በአስር ቀን ውስጥ በሸገር ከተማ ደግሞ እስከ ጥር ወር መጨረሻ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

10 Jan, 05:20


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎት ተመልሷል

ከግንቢ- ነጆ እና አሶሳ በተዘረጋው 132 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ታወር በመውደቁ ምክንያት ከግንቢ፣ ነጆ፣ መንዲ፣ ግዳሚ እና አሶሳ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኤሌክትሪክ ሃይል ሲያገኙ በነበሩ አካባቢዎች ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል፡፡

የጥገና ስራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን ።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

09 Jan, 16:21


ሁለቱ ተቋማት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለደንበኞች ለማቅረብ ውይይት አደረጉ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ዛሬ ባደረጉት ውይይት አስተማማኝ የሆነ የኃይል አቅርቦት ለደንበኞች ለማድረስ እንደሚሠሩ ገልጿዋል።

በተደረገዉ የጋራ ውይይት የተለያዩ ሃሳቦች የተነሱ ሲሆን በተለይም ከኃይል አቅርቦት ጋር እና ከሃይል መቆራረጥ ጋር በተያያዘ እንዲሁም ለቅድመ መከላከል ጥገናም ሆነ ለማሻሻያና መልሶ ግንባታ ስራ የሚቋረጥ የሃይል መቋረጥ ላይ ሁለቱ ተቋማት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ መግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡

በውይይቱ በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የሃይል ፍላጎት ለማሟላት እና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለደንበኞች ለመስጠት በየደረጃው ያሉ ሃላፊዎች በቅንጅት መሥራትና ከደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን መፍታት እንደሚገባ ተጠቅሷል።

ተቋማቱ እየሠጡት ያለው አገልግሎ ለሃገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት መሠረት በመሆኑ ያልተቆራረጠና ጥራ ያለው የኃይል አቅርቦት ለመስጠት መደረግ ስለሚገባቸው ተግባራት ዙሪያ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

መሠል የምክክር መድረክ በሁለቱ ተቋማት መካከል በየጊዜው የሚደረግ ሲሆን ያለውን ቅንጅታዊ አሰራር ለማሻሻል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተመላክቷል።

ውይይቱ በሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች መካከል የተካደ ነበር።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

09 Jan, 11:32


በአዲስ አበባ እና ሐረር ከተሞች የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-

http://www.eeu.gov.et/power-interruption?lang=am

Ethiopian Electric Utility

09 Jan, 08:48


ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ የኤሌክትሪክ አቅርቦት

ከደሴ ወልዲያ 66 ኪሎ ቮልት እና ከኮምቦልቻ አለማጣ በተዘረጋ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ላይ የጥገና ስራ ስለሚከናወን ከጥር 03 ቀን እስከ ጥር 06 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ወልዲያ ከተማ ውሃ በከፊል፣ ሳንቃና አካባቢው የሀይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል።

ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

09 Jan, 08:29


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በቀላሉ፣ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕሮ ወይም በኤም ፔሳ በኩል ይፈፅሙ፡፡ፍጆታዎ በስልክዎ! ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ በመምረጥ ኑሮዎን ያቅሉ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

09 Jan, 06:39


ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት እየተካሄደ ነው

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት በ14 ከተሞች ላይ የኤሌክትክ መሰረተ-ልማት የማዛወር እና መልሶ ግንባታ ስራ እያከናወነ ነው፡፡

በኮሪደር ልማቱ የሚዛወሩ መስረተ-ልማቶች በአራት ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ የታቀደ ሲሆን እስከ ጥር 30 ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ተቋሙ እስከ ህዳር 30 ቀን ብቻ 3 ሺህ 275 የምሰሶ እና 96 የማሰራጫ ትራንስፎርመሮች ማዛወር ስራ የተከናወነ ሲሆን በአዲስ አበባ፣ በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማና በድሬዳዋ 13 ነጥብ 4 ኪ.ሜ የመሬት ውስጥ ተቀባሪ መስመር እና አምስት ስዊቺንግ ስቴሽኖችን የማዛወር ሥራ ተከናውኗል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ 24 ሺህ 964 ፒቢሲ እና 23 ሺህ 100 ሜትር የመሬት ውስጥ ተቀባሪ የዩቲሊቲ መስመር ዝርጋታ ስራ
የምሰሶ መንቀያ ክሬን እንደልብ አለመኖር ለሥራው ፍጥነት እክል እየፈጠረ መሆኑን የዝግጅት ክፍሉ መረጋገጥ ችሏል፡፡

የኮሪደር ልማት በአዲስ አበባ፣ ጎንደር፣ በህርዳር፣ ደሴ፣ ድሬደዋ፣ በሐረሪ፣ ሰመራ፣ ሻሸመኔ፣ ቢሾፍቱ፣ ጅማ፣ አምቦ፣ አዋሳ፣ አርባምንጭ እና በሸገር ከተሞች እየተደረገ ይገኛል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አጠቃላይ የኮሪደር ልማቱ ሽፋን 132 ኪ.ሜ ርዝመትና 2817 ሄክታር የሚገመት ስፋት አለው፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

08 Jan, 11:25


የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ታወር በመውደቁ ምክንያት የተቋረጠ የኃይል አቅርቦት

ከግንቢ ወደ ነጆ እና አሶሳ በተዘረጋው 132 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ታወር በመውደቁ ምክንያት ከግንቢ፣ ነጆ፣ መንዲ፣ ግዳሚ እና አሶሳ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኤሌክትሪክ ሃይል ሲያገኙ በነበሩ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም የወደቀው ታወር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል በኩል ተጠግኖ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትግዕስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

08 Jan, 07:28


የኃይል መቆራረጥና ችግሮችን ለመቀነስ የሚያስችል ሥራ እየተሠራ ነው

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል መቆራረጥና መዋዠቅ ችግሮችን ለመቀነስ የሚያስችሉ የቅድመ-ጥገና፣የመልሶ ግንባታ እና የማስፋፊያ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡

ተቋሙ ባላፉት አምስት ወራት ውስጥ በኤሌክትሪክ እና በዛፎች መነካካት፣ በገመዶች መርገብ፣ በፖሎች መዛመም ምክንያት ሊፈጥር የሚችለውን የኃይል መቆራረጥ ችግር ለማስቀረት 20 ሺህ 291 ኪሎ ሜትር የቅድመ-መከላከል፣ 1 ሺህ 572 ኪሎ ሜትር መልሶ ግንባታ ሥራ ማከናወን ችሏል፡፡

በተጨማሪም እንደ ሃገር 544 የትራንስፎርመር መልሶ ግንባታ እና 1 ሺህ 261 የአዲስ ትራንስፎርመሮች ተከላ ሥራ ማከናወን ችሏል፡፡

በተመሳሳይ 2 ሺሕ 925 ኪሎ ሜትር አዲስ የኤሌክትሪክ መስመር ማስፋፊያ ሥራ ተከናወኗል፡፡

በተከናወኑ የመሰረተ-ልማት አቅም ማሳደግ፣ ማስፋፋት እና የቅድመ-ጥገና ስራዎች ላይ የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ ነበር፡፡

የመሠረተ-ልማት መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ፣ የአዲስ የኤሌክትሪክ ማስፋፊያ መደረጉ አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እንዲሁም የኃይል መዋዠቅን ለመቀነስ አስችሏል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

07 Jan, 14:11


በአሶሳና አካባቢው ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷ

ከመንዲ - አሶሳ በተዘረጋው 132 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በደረሰ የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በአሶሳና አካባቢው ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል።

የጥገና ስራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን ።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

06 Jan, 14:12


መልካም የገና በዓል !! በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን !!
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

06 Jan, 13:18


ተቋማችን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብረሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ ይመኛል!!
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

06 Jan, 10:59


የተቋማችን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሽፈራው ተሊላ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!!
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

06 Jan, 09:27


በሰሜን አዲስ አበባ ቁጥር 1 ፣ በደቡብ አዲስ አበባ ቁጥር 5 እና በተቋሙ ጥሪ ማዕከል የተደረገ የበዓል ቅድመ ዝግጅት!!
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

06 Jan, 09:10


ለቅድመ-ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በሙሉ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የገና በዓልን አስምልቶ ለቅድመ-ክፍያ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በበዓሉ ዕለት በመላው አገሪቱ በተመረጡ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ካርድ መሙላት እንዲችሉ ሁኔታዎችን አመቻችቷል፡፡ በዚህ መሰረት በበዓሉ ዕለት

⚠️ ከሽረ ሪጅን፡- የዓደዋ፣ አክሱም፣ ሽረ አገልግሎት መስጫ ማዕከት ለግማሽ ቀን፣
⚠️ ከመቐለ ሪጅን፡- የመቐለ ቁጥር 1፣ ቁጥር 2 እና ቁጥር 4 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ከጠዋት 2፡00 ጀምሮ ለግማሽ ቀን፣
⚠️ከሰሜን አዲስ አበባ ሪጀን ፡-ቁ:2 : አራት ኪሎ የሚገኘው ማዕከል ሙሉ ቀን
⚠️ ከምስራቅ አዲስ አበባ ሪጀን ፡- በ7ቱም አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሙሉ ቀን፣
⚠️ ከደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን፡- ቁጥር 9 እና ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሙ ቀን፣
⚠️ ከምዕራብ አዲስ አበባ ሪጅን፡- ቁ 1 ልደታ ሻርፕ ህንፃና ቁ 2 አየር ጤና ቴሌ አካባቢ የሚገኘው ማዕከል
⚠️ ከጎንደር ሪጅን ፡- የጎንደር ቁጥር 1 እና ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሙሉ ቀን፣
⚠️ከደብረማርቆስ ሪጅን፡- የደብረ ማርቆስ ቁጥር 1 እና 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለግማሽ ቀን፣
⚠️ ከባህር ሪጅን፡- የባህር ዳር ቁጥር 1 እና ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ መዕከላት ለግማሽ ቀን፣
⚠️ ከሻሸመኔ ሪጅን፡- ሻሸመኔ ቁጥር 1 እና ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ መዕከላት ለሙሉ ቀን፣
⚠️ ከጅማ ሪጅን፡- የጅማ ቁጥር 1 እና ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሙሉ ቀን፣
⚠️ ከነቀምት ሪጅን፡- ነቀምት ቁጥር 1 እና 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በፈረቃ ጠዋትና ከሰዓት፣
⚠️ ከመቱ ሪጅን፡- የመቱ፣ የበደሌ እና የያዩ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለግማሽ ቀን፣
⚠️ ከአምቦ ሪጅን፡- የአምቦ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ለሙሉ ቀን፣
⚠️ ከአዳማ ሪጅን፡-ቁጥር 1 እና 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሙሉ ቀን፣
⚠️ ከሸገር ሪጅን፡- የቢሾፍቱ ቁጥር 1 እና 2፣ የለገጣፎ፣ የቡራዩ፣ የጫንጮ፣ የሆለታ፣ የሱልልታ፣ የታጠቅ (አሸዋ ሜዳ)፣የዱከም፣ የገላን፣ የጨፌ ዶንስ፣ የአዱላላ፣ የሰባታ፣ የአልም ገና፣ የፉሪ (ወለቴ)፣ የአንፎ ሜዳ እና የኦሮሚያ ኮንዶሚኒየም አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሙሉ ቀን፣
⚠️ ከሐረሪ ሪጀን፡- የሐረሪ ቁጥር 1 እና 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሙሉ ቀን፣
⚠️ከድሬዳዋ ሪጀን፡-ቁጥር 1 (ኮኔል) እና ቁጥር (ቁጥር 2) ግማሽ ቀን፣
⚠️ ከሱማሌ ሪጀን፡- ጅግጅጋ ቁጥር 1 እና 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሙሉ ቀን፣
⚠️ከአፋር ሪጅን ሁሉም የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት አገልግሎት ይሰጣሉ ፣
⚠️ከሆሳና ሪጅ፡- ቡታጅራ ወራቤ ሆሳና ቁጥር ቁጥር 2፣ ወልቂጤ፣ ዱራሜ፣ እምድብር አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሙሉ ቀን፣
⚠️ ከደቡብ ምዕራብ ሪጅን፡- ቦንጋ ፣ ቴፒ እና ሚዛን ማዕከላት ለሙሉ ቀን፣
⚠️ከወላይታ ሪጅን፡- የሶዶ ቁጥር 1 እና 2፣ የአለባእና ዲላ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሙሉ ቀን የካርድ መሙላት አገልግሎት የሚሰጡ መሆናቸው አውቃችሁ አገልግሎቱን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

04 Jan, 09:22


መጪውን የገና በዓል አስመልክቶ የተደረገ ቅድመ ዝግጅት

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት በቅድሚያ መልካም ምኞቱን ይገለፃል፡፡

ተቋሙ በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ ሊያጋጥም የሚችለውን የኃይል መቆራረጥና መዋዥቅ ችግር ለመቀነስ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡

በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ የኃይል መቆራረጥና መዋዥቅ ችግር ሳይፈጠር ለተጠቃሚው ለማቅረብ ከተከሰተም በአፋጣኝ የአስቸኳይ ጥገና ስራ ለመስራት በየደረጃው ግብረ-ሃይል በማዋቀርና አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን በማዘጋጀት ወደ ስራ ገብቷል፡፡

ግብረ-ሃይሉም በተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥና መዋዠቅ ችግር የሚስተዋልባቸውን መስመሮች በመለየት የቅድመ መከላከል ጥገና ስራዎች እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በመቀናጀትና የጋራ ግብረ ሀይል በማዋቀር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በጋራ እየተከናወኑ ነው፡፡

የቅድመ-ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ደግሞ በዓሉ ሲደርስ የሚኖረውን አላስፈላጊ እንግልት ለማስቀረት ከወዲሁ የኤሌክትሪክ ኃይል አስቀድመው እንዲገዙ /ካርድ እንዲሞሉ/ እየጠየቅን፤ በዋዜማውና በዕለቱ ካርድ ማስሞላት ለሚፈልጉ ደንበኞችም የተለዩ ማዕከላት ይህንን አገልግሎት እንደሚሰጡ እንገልፃለን፡፡

ደንበኞች የኃይል አጠቃቀም ለአደጋ ተጋላጭ እንዳያደርጋቸው አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እየጠየቅን፣ የኃይል ጭነት በማይበዛባቸው ሰዓታት በተለይ ከምሽቱ 3፡00 እስከ ንጋቱ 11፡00 ባሉት ጊዚያት መጠቀም የተሻለ የኤሌክትሪክ ኃይል ከማግኘት ባለፈ ሊኖር የሚችለውን የኃይል መቆራረጥ ችግር ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

የታደሰ የተቋሙ መታወቂያና የስራ ትእዛዝ ደብዳቤ የያዙ የቴክኒክ ባለሞያዎቻችን በተለያዩ አካባቢዎች ለስራ ጉዳይ እንደሚንቀሳቀሱ እያሳወቅን፤ ሆኖም የተቋሙ ሠራተኞች በመምሰል መሠረተ ልማቱ ላይ ስርቆትና ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ አካላት ሊኖሩ ስለሚችሉ፤ህብረተሰቡ ይህንን ከወዲሁ ተገንዝቦ የኤሌክትሪክ መሰረት ልማቶችን እንዲጠበቅና አጠራጣሪ ነገር ካጋጠመው ለፀጥታ አስከባሪ አካላት ወይም ለተቋማችን ጥቆማ እንዲሰጠን በዚህ አጋጣሚ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

በመጨረሻም ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ተያይዞ ማንኛውም ቅሬታ፣ ጥቆማና አስተያየት በ905 ወይም 904 ነፃ የጥሪ ማዕከል በመደወል፣ በአቅራቢያዎ በሚገኝ የአገልግሎት ማዕከላችን በቀጥታ ስልክ በመደወል ወይም በአካል ማቅረብ እንደሚችሉ እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

04 Jan, 06:50


በበዓል ወቅት ሊኖር የሚችለውን የሃይል መቆራረጥ ችግር ለመቀነስ እየተከናወኑ የሚገኙ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

03 Jan, 06:59


በአዲስ አበባ ከተማ የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1120?lang=am

Ethiopian Electric Utility

03 Jan, 06:47


ከጃክሮስ- ጎሮ-የረር-ሰሚት አካባቢዎች ለሚስተዋለው የሃይል መቆራረጥ መንስኤ እና በአካባቢው ላጋጠመው ችግር እየተወሰደ የሚገኘው የመፍትሄ እርምጃ !!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

03 Jan, 06:32


የኃይል ፍጆታ ቆጣሪ ከየት ወደ የት?

ከ1948 ዓ.ም በፊት የነበሩ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ ሒሳብ የሚከፍሉት ከተቋሙ ጋር በሚዋዋሉት የቁርጥ ሒሳብ ዋጋ ነበር፡፡ማለትም ይሄን ያክል ሻማ አምፖል ለሚፈልግ የዚህን ያክል “ሳንቲም” በወር ይከፍላል በሚል ስምምነት ነበር፡፡ ከዚያም ወሩን ጠብቆ ደንበኛው በሚጠቀመው የአምፖል መጠንና በውል ስምምነቱ መሰረት ይከፍል ነበር፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ!
http://www.eeu.gov.et/publication/detail/1117?lang=am

Ethiopian Electric Utility

02 Jan, 07:34


በኤሌክትሪክ በአንድ ቀን ንቅናቄ የገጠር ከተሞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት “በኤሌክትሪክ በአንድ ቀን ንቅናቄ” ኤሌክትሪክ አገኝተው የማያውቁ የገጠር ከተሞች ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ማድርግ ተችሏል፡፡

በሃዲያ ዞን አመካ ወረዳ የጌጃ ሳተላይት ጣቢያ በትልንትናው እለት ብቻ 130 አዳዲስ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡

ቀድሞ የጌጃ አካባቢ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ቢኖርም ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እንዳልሆኑ ታውቋል፡፡ ነዋሪዎቹ አገልግሎቱን ለማግኘት በማህበር ተደራጅተው በመምጣት ኤሌክትሪክ ለማግኘት 7 ሚሊየን ብር ወጪ አድርገዋል፡፡

በተመሳሳይ በሆሳና ሪጅንን በዶዮገና አገልግሎት መስጫ ማዕከል የዋግብታ ሳተላይት ጣቢያ በበኩሉ ታሕሳስ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ ለ66 አዳዲስ ደንበኞች ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ አድርጓል፡፡

በባሌ ሮቤ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በታሕሳስ 21 ቀን 2017 ዓ.ም 75 አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትክ ኃይል ተጠቃሚ ማድረጉን አስታውቋል፡፡

የማዕከሉ ሰራተኞች ደንበኛችን ኤሌክትሪክ በአንድ ቀን መስጠት ለማስተናገድ እስከ ምሽት 4 ሰዓት ድረስ ሲያስተናግዱ አምሽተዋል፡፡

“ኤሌክትሪክ በአንድ ቀን” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የማድረግ ንቅናቄ በመላ ሃገሪቱ በሚገኙ ሪጅኖችም ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

02 Jan, 07:13


ወርሃዊ የቆጣሪ ንባብ እየተወሰደ መሆኑን ያረጋግጡ! ከተጨማሪ ውዝፍ እዳ ይዳኑ!!

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከተጠቀሙበት ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ውጪ የተጋነነ ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ እየተጠየቀ አይደለም፡፡ ይሁን እንጂ ደንበኞች የቆጣሪ ንባብ በወቅቱ ካልተወሰደ ለተጨማሪ ውዝፍ እዳ ሊዳረጉ ይችላል፡፡

ውድ #የድህረ_ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኛችን ከፍጆታ ሂሳብ ጋርም ሆነ ተቋሙ ከሚሰጣቸው አገልግሎት ጋር ተያይዞ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት በርካታ የቅሬታ ማስተናገጃ ስርዓቶችን የዘረጋ ሲሆን ከተዘረጉ የቅሬታ ማስተናጋጃ ስርዓቶች መካከል ዲጅታል የቅሬታ ማቅረቢያ ስርዓቶችን ጨምሮ በየደረጃው በሚገኝ የተቋሙ ቢሮዎች ከደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ዝግጁ ናቸው፡፡

አብዛኛውን ጊዜ ከፍጆታ ሂሳብ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎች ምንጫቸው የቆጣሪ ንባብ በወቅት አለመወሰድ ሊሆን ስለሚችል ውድ ደንበኞቻችን ቆጣሪ አንበቢዎች ንባብ ለመውሰድ ወደ ቤታችሁ ሲመጡ በር ዘግቶ አለመጥፋት፣ ቆጣሪያችሁ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት መነበብና አለመነበቡን ማረጋገጥ እና ቆጣሪው አለመነበቡን እረግጠኛ ከሆኑ በቅራቢያዎ ለሚገኝ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል ማሳወቅ ይገባል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ከተቋሙ እውቅና ውጪ ቆጣሪን መነካካት በህግ ተጠያቂ ከማድረጉም በላይ ለኤሌክትሪክ አደጋ ስለሚያጋልጥ ተገቢውን ጥንቀቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

በዚህ አጋጣሚ የተቋሙን ሰራተኞች በመምሰል በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ ስርቆት የሚፈፅሙ አጭበርባሪዎች ስለሚኖር የጥገና ስራም ሆነ መሰል አገልገሎቶችን ለመስጠት ወደ አካባቢያችሁ የሚመጡ ሰራተኞች የተቋሙን መታወቂያ መያዛቸውን እንድታረጋግጡ እናሳስባልን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

02 Jan, 06:44


በአዲስአበባ ፣ ሐረር፣ ድሬደዋ እና አሶሳ  ከተማ ለመስመር ዝርጋታ እና የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየትድረ-ገፃችንንይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1119?lang=am

Ethiopian Electric Utility

01 Jan, 14:47


እራስዎን ከኤሌክትሪክ አደጋ ይጠብቁ!!

Ethiopian Electric Utility

01 Jan, 06:51


82 በመቶ የሚሆኑ አዲስ ኃይል ፈላጊ ደንበኞች በስታንዳርዱ መሰረት እየተስተናገዱ ነው

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በህዳር ወር ብቻ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ካደረጋቸው አዳዲስ ደንበኞች ውስጥ 82 በመቶ የሚሆኑት በስታንዳርዱ መሰረት የተስተናገዱ ናቸው፡፡

ተቋሙ በ2017 ዓ.ም ህዳር ወር ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ካደረጋቸው 42 ሺህ 314 ደንበኞች ውስጥ 34 ሺህ 721 ደንበኞች በተቀመጠው የአስር ስታንዳርድ ውስጥ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡

በህዳር ወር በስታንዳርዱ መሰረት የተስተናገዱ ደንበኞች አፈጻፀሙ በሪጅን ደረጃ ሲታይ አዳማ ሪጅን 3 ሺህ 156፣ ሸገር 3 ሺህ 179፣ ሻሸመኔ 2 ሺህ 486፣ ደሴ 1ሺህ 790፣ አምቦ 1ሺህ 259፣ ጎንደር 1 ሺህ 100፣ ደብረ-ብርሃን 1 ሺህ 29 ደንበኞችን በስታንዳርዱ መሰረት የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል፡፡

ደንበኞች በፈጥነት የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ‹‹የኤሌክትሪክ በአንድ ቀን›› ንቅናቄ አስተዋፅዖ ያበረከተ ሲሆን በሕዳር ወር ኤሌክትሪክ ካገኙት 42 ሺሕ 314 ደንበኞች ውስጥ 9 ሺህ 942 አዲስ ደንበኞችን በአንድ ቀን ውስጥ ኤሌክትሪክ ያገኙ ናቸው፡፡

በበጀት አመቱ በስታንዳርዱ መሰረት የተስተናገዱ ደንበኞች ቁጥር ከፍተኛ መሻሻል ያሳየ ሲሆን በሐምሌ ወር 46 በመቶ፣ በነሐሴና በመስከረም 66 በመቶ፣ በጥቅምት ደግሞ 77 በመቶ የሚሆኑ ደንበኞች በተቀመጠው ቀነ ገደብ መሰረት ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የሆኑ ናቸው፡፡

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተገልጋዮች ቻርተር መሰረት አንድ ደንበኛ ኤሌክትሪክ በጠየቀ በአማካይ በ10 ቀን ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ሊያገኝ እንደሚገባ ይደነግጋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

31 Dec, 11:24


የሥነ-ምግባር ጥሰት በፈፀሙ አመራርና ሠራተኞች ላይ እርምጃ ተወሰደ

የሥነ-ምግባር በፈፀሙ አመራርና ሠራተኞች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን በተቋሙ የሥነ-ምግባር እና ፀረ ሙስና ክፍል ዳይሬክተር አቶ ህብረወርቅ ይመኑ ገልፀዋል፡፡

እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ተቋሙ ከደንበኞቹ የመጡ ቅሬታዎችን መሰረት አድርጎ ባደረገው ማጣርት በ20 የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ላይ ከፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እስከ ደመወዝ ቅጣት የሚደርስ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አክለውም እርምጃ የተወሰደባቸው አመራርና ሠራተኞች ከትራንስፎርመር አቅም በላይ በመጫን እንዲቃጠል ያደረጉ፣ አዳዲስ ደንበኞችን በሕገ-ወጥ መንገድ ያስተናገዱ እና አገልግሎቱ ለሚሰጣቸው አገልግሎት ሂሳብ ቀንሰው ተቋሙ ላይ ጉዳት ያደረሱ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

የስነ-ምግባር ጥሰት እንዳይፈፀም የአሠራር ሥርዓቱን የማዘመን፣ የሥነ-ምግባር መመሪያዎችን የማሻሻል እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው የደንበኞች ቅሬታ አቀራረብ በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን የሞባይል መተግበሪያ እና የድረ-ገፅ ማበልፀግ ሥራ ተጠናቆ የሙከራ ሥራ ላይ ይገኛል ብለዋል ዳይሬክተሩ፡፡

ክቡራን ደንበኞቻችን አብዛኛው የተቋሙ አመራርና ሰራተኛ በህዝብ የተጣለበትን ሃላፊነት ለመወጣት ደፋ ቀና የሚል ቢሆንም ጥቂት የሚባሉ አመራርና ሰራተኞች በስነ-ምግባር ጥሰት ከተቋሙ ከተባረሩ ሰራተኞች እና ደላሎች ጋር በመተባበር መሰል እኩይ ተግባር ሊፈፅሙ ስለሚችሉ የጥገና ስራ ለማከናወን ሆነ ሌላ አገልግሎት ለመስጠት ወደ አካባቢያችሁ የሚመጡ ሰራተኞች የተቋሙ መታወቂያ የያዙ መሆናቸውን ማረጋገጥና አጠራጣሪ ነገር ስትመለከቱ በተቋሙ ነጻ የጥሪ ማዕከል በመደወል እንዲያሳውቁን እንጠይቃለን፡፡

Ethiopian Electric Utility

31 Dec, 07:40


ደንበኞች ካሉበት ሆነው ኃይል መግዛት የሚችሉበትን የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት እየተከናወኑ የሚገኙ ዋና ዋና ተግባራት !!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

31 Dec, 06:52


በአዲስአበባ እና ኦሮሚያ ከተማ ቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየትድረ-ገፃችንንይጎብኙ፡- http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1115?lang=am

Ethiopian Electric Utility

31 Dec, 06:17


የሥነ-ምግባር ጥሰት በፈፀሙ አመራርና ሠራተኞች ላይ እርምጃ ተወሰደ

የሥነ-ምግባር በፈፀሙ አመራርና ሠራተኞች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን በተቋሙ የሥነ-ምግባር እና ፀረ ሙስና ክፍል ዳይሬክተር አቶ ህብረወርቅ ይመኑ ገልፀዋል፡፡

እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ተቋሙ ከደንበኞቹ የመጡ ቅሬታዎችን መሰረት አድርጎ ባደረገው ማጣርት በ20 የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ላይ ከፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እስከ ደመወዝ ቅጣት የሚደርስ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አክለውም እርምጃ የተወሰደባቸው አመራርና ሠራተኞች ከትራንስፎርመር አቅም በላይ በመጫን እንዲቃጠል ያደረጉ፣ አዳዲስ ደንበኞችን በሕገ-ወጥ መንገድ ያስተናገዱ እና አገልግሎቱ ለሚሰጣቸው አገልግሎት ሂሳብ ቀንሰው ተቋሙ ላይ ጉዳት ያደረሱ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

የስነ-ምግባር ጥሰት እንዳይፈፀም የአሠራር ሥርዓቱን የማዘመን፣ የሥነ-ምግባር መመሪያዎችን የማሻሻል እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው የደንበኞች ቅሬታ አቀራረብ በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን የሞባይል መተግበሪያ እና የድረ-ገፅ ማበልፀግ ሥራ ተጠናቆ የሙከራ ሥራ ላይ ይገኛል ብለዋል ዳይሬክተሩ፡፡

ክቡራን ደንበኞቻችን አብዛኛው የተቋሙ አመራርና ሰራተኛ በህዝብ የተጣለበትን ሃላፊነት ለመወጣት ደፋ ቀና የሚል ቢሆንም ጥቂት የሚባሉ አመራርና ሰራተኞች በስነ-ምግባር ጥሰት ከተቋሙ ከተባረሩ ሰራተኞች እና ደላሎች ጋር በመተባበር መሰል እኩይ ተግባር ሊፈፅሙ ስለሚችሉ የጥገና ስራ ለማከናወን ሆነ ሌላ አገልግሎት ለመስጠት ወደ አካባቢያችሁ የሚመጡ ሰራተኞች የተቋሙ መታወቂያ የያዙ መሆናቸውን ማረጋገጥና አጠራጣሪ ነገር ስትመለከቱ በተቋሙ ነጻ የጥሪ ማዕከል በመደወል እንዲያሳውቁን እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

30 Dec, 07:16


የስድስቱ ከተሞች ዲስትሪቢዩሽን መስመር መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት አፈጻፀም 96 በመቶ ደረሰ

በኤሌክትሪክ ኃይል ማሰራጫ መስመሮች እርጅና ምክንያት በከተሞች አካባቢ እያጋጠመ ያለውን የኃይል መቆራረጥና መዋዠቅ ችግር ለመቅረፍ እየተሰራ የሚገኘው የስድስቱ ከተሞች የኃይል ማሰራጫ መስመር የመልሶ ግንባታ እና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈፃፀም 96 በመቶ ደርሷል፡፡

የፕሮጀክቱ ዋና አላማ በተመረጡት ስድስት ከተሞች ያለውን የመካከለኛ እና ዝቅተኛ የኃይል ማሰራጫ መስመሮች አቅም በማሳደግ በከተሞቹና በዙሪያቸው ያለውን የኃይል አቅርቦት ጥራት አስተማማኝ ለማድረግ እንዲሁም በቀጣይ አዲስ ኃይል የሚጠይቁ ደንበኞችን ለማስተናገድ እንዲያስችል ነው፡፡

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ከስር የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ !!
http://www.eeu.gov.et/press-releases/detail/1113?lang=am

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

30 Dec, 06:24


በአዲስአበባ፣ ደብረማርቆስ ከተማ እና ድሬዳዋ ቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየትድረ-ገፃችንንይጎብኙ፡- http://www.eeu.gov.et/power-interruption?lang=am

Ethiopian Electric Utility

30 Dec, 06:12


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በቀላሉ፣ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕሮ ወይም በኤም ፔሳ በኩል ይፈፅሙ፡፡ፍጆታዎ በስልክዎ! ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ በመምረጥ ኑሮዎን ያቅሉ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

29 Dec, 16:08


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅረቦት ወደ አገልግሎት ተመልሷል

ከአላማጣ-ሰቆጣ በተዘረጋው 66 ኪ.ቮልት መስመር 2 የትራንስሚሽን ፌዝ በመበጠሱ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የሃይል አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ወደ አገልግሎት ተመልሷል።

በዚህም ስቆጣ ከተማ፣ ሰቆጣ ዙሪያ ወረዳ፣ አምድ ወርቅ ከተማ አስተዳደር፣ ደሃና ወረዳ፣ ጋዝጊብላ ወረዳ፣ ዝቆላ ወረዳ ፣ሰሃላ ወረዳ ፃግብጅ ወረዳ በከፊል አበርገሌ፣ ወረዳ በከፊል የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል።

በተመሳሳይ ከኮምበልቻ -ደሴ በተዘረጋው 66 ኪ.ቮልት መስመር ታወር ላይ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት በፈረቃ እየተሰጠ የሚገኘውን የሃይል አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ስለሆነ ክቡራን ደንበኞቻችን በትግዕስት እንድትጠብቁን እናሳስባለን።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

28 Dec, 06:22


በአዲስአበባ እና ሐረር ከተማ ቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየትድረ-ገፃችንንይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1111?lang=am

Ethiopian Electric Utility

28 Dec, 05:56


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በወቅቱ አለመፈፀም ለተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብና ቅጣት የሚዳርግ መሆኑን ያውቃሉ? እንግዲያውስ እንንገርዎ!! ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በወቅቱ አለመፈፀም ለተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብና ቅጣት ይዳርጋል፡፡ ስለሆነም ውድ የድህረ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባችሁን በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በወቅቱ እንድትፈፅሙ እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

27 Dec, 19:29


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅረቦት ወደ አገልግሎት ተመልሷል

ከጅማ-ቦንጋ በተዘረጋው 132 ኪሎ ቮሎት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅረቦት ወደ አገልግሎት ተመልሷል።

በዚህም የኃይል አቅረቦቱ ተቋርጦባቸው የነበሩት የከፋ፣ ቤንች፣ ሸኮ ዞን እና ምዕራብ ኦሞ ዞን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል።

የተቋርጠው የኃይል አቅረቦት እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት የጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

27 Dec, 15:37


በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ታወር ላይ በተፈፀመ ዝርፊያ ምክንያት በተወሰኑ አካባቢዎች የሃይል አቅርቦት ተቋርጧል

ከደሴ- ኮምቦልቻ በተዘረጋ 66 ኪ.ቮልት ትራንስሚሽን መስመር ታወር ላይ በተፈፀመ ዝርፊያ ምክንያት ከታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የሃይል አቅርቦቱ በፈረቃ እየተሰጠ ይገኛል።

በዚህም በደሴ ከተማ፣ በወረባቦ፣ በአልቡኮ፣ በኩታበር፣በደሴ ዙሪያ፣ ወልዲያና በአካባቢው የሃይል አቅርቦቱ በፈረቃ እየተሰጠ ይገኛል ።

ስለሆነም በኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ በተፈፀመው ዝርፊያ ምክንያት የተፈጠረው ችግር ተፈትቶ አገልግሎቱ ሙሉ በሙሉ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁ በአክብሮት እንጠይቃለን።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

27 Dec, 06:48


በአዲስአበባ  ከተማ ቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየትድረ-ገፃችንንይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1110?lang=am

Ethiopian Electric Utility

27 Dec, 05:52


ደንበኞች ካሉበት ሆነው ኃይል ለመግዛት የሚያስችሉ ስማርት ቆጣሪዎች እየተገጠሙ ነው

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቅድመ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ካሉበት ሆነው የኤሌክትሪክ ሃይል መግዛት የሚችሉበትን የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል ፕሮጀክት ነድፎ ነባር ቆጣሪዎችን በስማርት ሜትር በመቀየር ላይ ይገኛል፡፡

ፕሮጀክቱ በሁለት ምዕራፍ የሚተገበር ሲሆን በመጀመሪያው ዙር 25 ሺህ ነባር ቆጣሪዎችን በአዲስ አበባ ለመቀየር ታቅዶ እስካሁን በባልደራስ ኮንዶሚኒየም እና በመካኒሳ ባቱ አንድ ኮንዶሚኒየም ከ1 ሺህ 6 መቶ በላይ ነባር ሲንግል ፌዝ ቆጣሪዎች በኤስ.ቲ.ኤስ ቆጣሪዎችን መቀየር ተችሏል፡፡

እየተቀየሩ የሚገኙት የኤስ.ቲ.ኤስ ስማርት ቆጣሪዎች ደንበኞች ወደ ማዕከል መምጣት ሳይጠበቅባቸው ካሉበት ቦታ ሆነው በእጅ ስልካቸው በመጠቀም ብቻ ኃይል መግዛት እንዲሁም የኃይል አጠቃቀማቸውን መከታተል የሚያስችሉ ናቸው፡፡

በተጨማሪም የኤስ.ቲ.ኤስ ስማርት ቆጣሪዎች ደንበኞች ኃይል ገዝቶ ለመጠቀም የሚያጠፉትን ጊዜና ጉልበት ለመቀነስ ብሎም ከቢል ጋር በተያያዘ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት የሚያግዙ ይሆናል፡፡

በፕሮጀክቱ ሁለተኛ ዙር ትግበራ 125 ሺህ ነባር ባለ ሶስት ፌዝ ቆጣሪዎች በመላ ሃገሪቱ ለሚገኙ ደንበኞች በአዲስ ኤስ.ቲ.ኤስ ስማርት ቆጣሪዎች የሚቀየሩ ይሆናል፡፡

በአጠቃላይ በዚህ ፕሮጀክት የ500 ሺህ ደንበኞች ነባር ቆጣሪዎች የሚቀየሩ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የቆጣሪዎቹ ግዢ ተፈጽሞ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡

ለፕሮጀክቱ ትግበራ ከ48 ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ የሚደረግ ሲሆን ወጪው በዓለም ባንክ የሚሸፈን ነው፡፡

ፕሮጀክቱ ኢንሄሜትር በተሰኘ የቻይና ኩባንያ እና ኮለን ኢንጂነሪንግ በተሰኘ ሃገር በቀል ተቋራጭ በጋራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

20 Nov, 07:42


ደህንነታቸው የተጠበቀ ትራንስፎርመር እንዲኖር እየተሰራ ነው

የትራንስፎርመር ወቅታዊ መረጃ መከታተል የሚያስችል ቴክኖሎጂ እየተተገበረ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኔትወርክ ኢንፈራስትራክቸር ኦፕሬሽን ኤክሰለንስ ዳይሬክተር አቶ ፈሪድ አብዱልሰላም አስታወቁ፡፡

ዳይሬክተሩ በትራንስፎርመሮች ላይ በተገጠሙ “የኤ.ኤም.አይ” ቆጣሪዎች በመጠቀም ወቅታዊ የትራንስፎርመር መረጃ እየተከታተለ ነው ብለዋል፡፡

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ከዚህ በታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ያንብቡ !!
http://www.eeu.gov.et/news/detail/1032?lang=am

Ethiopian Electric Utility

19 Nov, 15:50


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል

ከመንዲ -አሶሳ የተዘረጋው ከፍተኛ የኃይል አስተላላፊ መስመር በመውደቁ ምክንያት በአሶሳና አካባቢው ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል

በዚህም አሶሳ ከተማ ፣ ባምባሲ፣ ኡራ፣ አብራሃሞ፣ ሸርቆሌ፣ መንጌ፣ ኩርሙክ፣ ሆሞሻ፣ ቶንጎ ፣ ኡንዱሉ፣ብልድግሉ ወረዳዎችና አካባቢዎቻቸው አገልግሎት ማግኘት ጀምረዋል፡፡

የጥገና ስራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁ ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን ፡፡

#በኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

19 Nov, 06:53


በሐረር፤ ደብረማርቆስ እና ጎንደር ከተማ የመልሶ ግንባታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የሃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1031?lang=am

Ethiopian Electric Utility

19 Nov, 05:36


ውድ የመኖሪያ ቤት ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ደንበኛችን፤ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳቦትን በቀላሉ ለማስላት ያመችዎት ዘንድ ይህንን #የታሪፍ መረጃ ይጠቀሙ፡፡ ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብዎትንም በወቅቱ ይፈፅሙ!

ተቋማችንን የሚመለከቱ ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et

Ethiopian Electric Utility

18 Nov, 10:59


ተቋርጦ የነበረው አገልግሎት ተመልሷል

ከህዳር 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በሲስተም ማሻሻያ ስራ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የድህረ ክፍያ አገልግሎት፣ የ905 እና 904 የጥሪ ማዕከላት አገልግሎት ወደ ነበረበት ተመልሷል፡፡

የማሻሻያ ስራው እስኪጠናቀቅ ድረስ በትግዕስት ለጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን ምስጋና እያቀረብን ከዛሬ ጀምሮ ማንኛውም አገልግሎትና መረጃ ማግኘት እንደምትችሉ በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

በዚህ አጋጣሚ በተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

18 Nov, 08:35


በአዲስ አበባ ከተማ የመልሶ ግንባታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የሃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1027?lang=am

Ethiopian Electric Utility

18 Nov, 06:22


በአዶላ ከተማ ለማሠራጫ መስመር ማሻሻያ ስራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው

በአዶላ ከተማ የሚስተዋለውን የሃይል መቆራረጥ ለመቀነስ የኤሌክትሪክ መስመር አቅም መሻሻል ቅድሚያ ሰጥተን እየሠራን ነው ሲሉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሻሸመኔ ሪጅን የአዶላ ወዩ አገልግሎት መስጫ ሥራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ መንግሥተሩ ተናገሩ፡፡

ባለፉት ወራት ሦስት ወራት የ19 ኪሜ ርቀት ያለው ባለ15 ሺህ ኬቪኤ የመልሶ ግንባታ ሥራ የራስ አቅም መሰራቱን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ከተሠሩት የመልሶ ግንባታ ሥራዎች ውስጥ የአረጁ መስመር መቀየር፣ የተሰነጠቁ ሲኒ መተካት እና ፖል እንደ አዲስ የመቀየር ሥራ ይገኙበታል ብለዋል፡፡

አቶ ያሬድ አክለውም በቀጣይ በከተማዋ ባሉ አራት ቦታዎች 250 ኪሜ የዝቅተኛ መስመር የመልሶ ግንባታ ሥራ ለመጀመር የግብዓት አቅርቦት እየጠበቁ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ኃላፊው የኃይል ማሻሻያ ሲጠናቀቅ በወር ውስጥ በአንድ መጋቢ መስመር ያለውን የኃይል መቆራረጥ ከ33 ወደ 10 ለማድረስ እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡

የማሠራጫ መስመር የሚገነባው በያዝነው በጀት ዓመት አዲስ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሚያገኙ 950 አዲስ ደንበኞች ውጤታማ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡

በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የአዶላ ወዩ አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ከኃይል ሽያጭ 3 ነጥብ 6 ሚለየን ብር፣ ከቆረጣ ቅጠላ፣ ከአዲስ ደንበኛ ማገኛት፣ ከቆሙ ቆጣሪዎች 2 ነጥብ 7 ሚለየን ብር ገቢ ሰብስቧል፡፡
#በኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

17 Nov, 14:34


ከፍተኛ ኃይል አስተላላፊ መስመር በመውደቁ የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል

ከመንዲ -አሶሳ የተዘረጋው ከፍተኛ የኃይል አስተላላፊ መስመር በዳቡስ አካባቢ በመውደቁ ምክንያት በአሶሳ ከተማ ፣ ባምባሲ፣ ኡራ፣ አብራሃሞ፣ ሸርቆሌ፣ መንጌ፣ ኩርሙክ፣ ሆሞሻ፣ ቶንጎ ፣ ኡንዱሉ፣ብልድግሉ ወረዳዎችና አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡

የወደቀው መስመር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል በኩል ተጠግኖ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#በኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

16 Nov, 11:02


የጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

እሑድ ህዳር 8 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ድረስ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሰመራ ሰብሰቴሽን ላይ በሚያደርገው ጥገና ስራ ምክንያት በሠመራ ዋና ከተማ፣ ሎግያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሃ፣ ዱብቲ፣ አይሳኢታ፣ ዲጂኦቶ፣ ጋላፊ፣ ሰርዶ፣ ኤሊዳር፣ አፍዴራ ዋና ዋና ከተሞች እና አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጦ ይቆያል፡፡

ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

ተቋማችንን የሚመለከቱ ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et

Ethiopian Electric Utility

16 Nov, 08:33


በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል

በሆሳዕና 132/33/15 ኪ.ቮ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በሆሳዕና እና አካባቢው ከትናንት 11፡00 ጀምሮ የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል።

በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን ጥገና ተከናውኖ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትግዕስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

ተቋማችንን የሚመለከቱ ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et

Ethiopian Electric Utility

16 Nov, 08:18


የተቀናጀ የመሰረተ-ልማት ዝርጋታ እንዲኖር እየተሰራ ነው

የተቀናጀ የመሰረተ-ልማት ዝርጋታ እውን እንዲሆንና በቅንጅት ማነስ ምክንያት የሚደርሰውን የሃብት ብክነት ለመቀነስ እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ማኔጅመንት ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ገበየሁ ሊካሳ ገልፀዋል፡፡

ተቋሙ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚዘረጋቸውን የመካከለኛና ዝቅተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች፣ አቅማቸውን ለማሻሻልና ለማዛወር ከመንገዶች ባለስልጣን፣ከኢትዮ-ቴሌኮምና መሰል-ተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት ላይ መሆኑን ስራ አስፈጻሚው ገልፀዋል፡፡

ከዚህ ቀደም ተቋማቱ በተናጠል በሚሰሩበት ወቅት አንድ ተቋም የሌላኛውን ተቋም መሰረተ ልማት የማበላሸትና የማጥፋት ሁኔታ ይከሰቱ እንደነበር የገለጹት ዶ/ር ገበየሁ ይህም ለስራ ድግግሞሽና ለኪሳራ ይደረግ እንደነበር አንስተዋል፡፡

በአንፃሩ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በኮሪደር ልማት የኤሌክትሪክ፣ የውኃ፣ የስልክ፣ የመንገድ ወዘተ መሰረተ-ልማቶች ሲዘረጉ ተቋማት በቅንጅት በመስራታቸው አላስፈላጊ እና ተደጋጋሚ የሆኑ ወጪዎችን እንዲቀንስ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡

ተቋሙ የኃይል መቆራረጥን ለማስቀረት በርካታ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች መልሶ ግንባታ እያከናወነ እንደሆነ የጠቀሱት ስራ አስፈፃሚው የተቋማት መቀናጀት ሥራዎች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ፣ደንበኞችም የኃይል አቅርቦት እንዲያገኙ እንዲሁም ግብዓቶች እንዳይጎዱ ማድረግ አስችሏል ብለዋል፡፡

የተጀመሩ የጋራ ስራዎች ለማጠናከርና ቀጣይነት እንዲኖራቸው ለማድረግ የፌደራል የተቀናጀ መሰረተ-ልማት ማስተባበሪያ ኤጀንሲ አስገዳጅ ደረጃዎችን (ስታንዳርዶችን) አዘጋጅቶ ወደ ስራ ማስገባቱ ይታወሳል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

15 Nov, 13:24


እንድታውቁት

ከዛሬ ህዳር 6 ቀን 2017 ዓ.ም ቀኑ 11፡00 እስከ እሁድ ህዳር 8 ምሽቱ 1፡00 ድረስ የሲስተም ማሻሻያ ስራ ስለምናከናውን፤ የድህረ ክፍያ አገልግሎት፣ የ905 እና 904 የጥሪ ማዕከላት አገልግሎት አይሰጡም፡፡

ስለሆነም የድህረ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ የሆናችሁ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

15 Nov, 11:03


የጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

እሑድ ህዳር 8 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በንፋስ ስልክ ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመሮች ላይ የጥገና ስራ ስለሚያከናውን በቄራ፣ በገነት ሆቴል፣በደንበል ሲቲ፣ በመስቀል ፍላወር፣ በወሎ ሰፈር፣ በቦሌ መድኃኒዓለም፣ በዮሴፍ እና አደይ አበባ አካባቢ የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጦ ይቆያል፡፡

ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

15 Nov, 09:45


የአዲስ አበባ መሠረተ-ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከአዲስ አበባ ሪጅን ማስተባበሪያ ቢሮ ጋር ውይይት አደረገ

የአዲስ አበባ መሠረተ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሪጅን ማስተባበሪያ ቢሮ ጋር በትላንትናው እለት ውይይት አደርጓል።

በውይይቱ የአራቱም ሪጅኖች የ2017 በጀት አመት የመጀመሪያ ሩብ አመት ዕቅድ አፈጻፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ተቋሙ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ የተገኙ ተሞክሮዎችን እና መሻሻል ያለባቸውን ነገሮች ተነስተዋል።

በተጨማሪም የቋሚ ኮሚቴው አባላት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንቦች እና አሠራር ላይ ግንዛቤ ማስጨበጫ እንዲሰጣቸው ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል፡፡

በመጨረሻም የቋሚ ኮሚቴው አባላት በአገልግሎት አሰጣጥ በተለይ በኃይል መቆራረጥና በስነ-ምግባር ችግሮች ዙሪያ ጥያቄዎችን አንስተው ምላሽ ከተሰጣቸው በኋላ የቀጣይ የመፍትሔ አቅጣጫዎች አስቀምጠው ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

ተቋማችንን የሚመለከቱ ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et

Ethiopian Electric Utility

15 Nov, 05:43


የኃይል ብክነትን መከላከያ መንገዶች

• የምጠቀምባቸው ማሽነሪዎች ማለትም ሞቶሮች፣ ኮምፕሮሰሮች፣ ቦይሎርችና የመሳሰሉት ረጅም ጊዜ ያገለገሉ አገልግሎው ያረጁ ከሆኑ በአዳዲስ የሚቀየሩበት መንገድ መፈለግ፣

• የእያንዳንዱ ማሽን የኢነርጂ ፍጆታ ዳታ በመያዝ እና በመተንተን ማሰተካከያ የሚያሰፈልገው ከሆነ የማስተካከያ እርምጃ መውሰድ፣

• የኢነርጂ ማሽነሪዎች ሲገዙ የኢነርጂ ብቃታቸውን ግምት ውስጥ ማስገባት፣

• የፓወር ፋክተር ማሻሻያ ማድረግ፣

• የማሽነሪዎች የጥገና ጊዜያቸውን ጠብቀው በዕቅድ እንዲጠገኑ ማድረግ፣

• በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ጫና በማይበዛበት ሰዓት ኤሌክትሪክ ቢጠቀሙ፣

• የማሽነሪዎችን ሎድ ፋክተር ማሻሻል እና ማሽኖቹ ዲዛይን በተደረጉበት የመሸከም አቅም ላይ እንዲሰሩ ማድረግ ወይም ካለአቅማቸው አለማሰራት፣

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ተቋማችንን የሚመለከቱ ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et

Ethiopian Electric Utility

14 Nov, 12:01


በአዲስ አበባ ከተማ የመልሶ ግንባታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የሃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1025?lang=am

Ethiopian Electric Utility

14 Nov, 08:46


በቦረና ከተማ የሚስተዋለውን የኃይል መቆራረጥ ለመቀነስ ጥረት እየተደረገ ነው

በቦረና ከተማ የሚስተዋለውን የኃይል መቆራረጥ ለመቀነስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሻሸመኔ ሪጅን ስር የሚገኘው የነጌሌ ቦረና አገልግሎት መስጫ ማዕከል ዲስትሪቢዩሽን ቡድን መሪ አቶ ሙሳ ሁሴን አስታውቋል፡፡

በከተማዋ የተለያዩ መንደሮች የኤሌክትሪክ መስረተ-ልማት ማስፋፊያ በማድረግ በከተማዋ የሚሰተዋለውን የኃይል መቆራረጥ ለመቀነስና አዳዲስ ደንበኞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጨምረው ገልፀዋል፡፡

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ከዚህ በታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ያንብቡ !!
http://www.eeu.gov.et/news/detail/1023?lang=am

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

14 Nov, 07:15


በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ላይ ስርቆት የፈፀሙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ካዛንቺስ አካባቢ 550 ሺ ብር የሚገመት የኤሌክትሪክ መስመር ላይ ስርቆት ያደረሱ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች በኮሪደር ልማት ሥራ ምክንያት ተቆፍረው የተቀመጡ 200 ሜትር የሚደርስ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ቆራርጠው ለግል ጥቅማቸው ያዋሉ ሲሆን ተቋሙ ከአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ጋር ባደረገው ከፍተኛ ርብርብ መያዛቸው ተጠቅሷል፡፡

በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ ስርቆት መፈፀም በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት አውታሮች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 464/97 መሰረት ከ5 ዓመት እስከ 20 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት የሚቀጣ ያስጠይቃል፡፡

በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማቶች ላይ የሚፈፀምን የስርቆት ወንጀል መከላከል የሁሉም ሃላፊነት በመሆኑ መሰል እኩይ ተግባራትን የሚፈፅሙ አከላትን ሲመለከቱ በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ማሳወቅና ጥበቃ ማድረግ ይገባል።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ አመት ብቻ ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የስርቆት ወንጀል መፈፀሙ የሚታወስ ነው፡፡

ተቋማችንን የሚመለከቱ ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et

Ethiopian Electric Utility

13 Nov, 12:47


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በቀላሉ፣ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕሮ ወይም በኤም ፔሳ በኩል ይፈፅሙ፡፡ፍጆታዎ በስልክዎ! ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ በመምረጥ ኑሮዎን ያቅሉ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ተቋማችንን የሚመለከቱ ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et

Ethiopian Electric Utility

13 Nov, 06:59


የኤሌክትሪክ አገልግሎት በመጀመሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እንደሚያሻሻል የቦቆልማዮ ነዋሪዎች ተናገሩ

የኤሌክትሪክ አገልግሎት በመጀመሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እንደሚሻሻል የቦቆልማዮ ነዋሪዎች እና የከተማዋ ሊቀመንበር ተናግረዋል፡፡

ዝግጅት ክፍሉ ጋር ቃለ-መጠይቅ ያደርጉ የቦቆል ማዩ ከተማ ነዋሪዎች ቀድሞ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚያገኙት ከግለሰብ ቀጥለው እስከ ምሽቱ 4 ሰዓት ድረስ ብቻ ይጠቀሙ እንደነበር ጠቅሰው፤ አሁን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ በመሆናቸው ለንግድ ሥራና ለከተማዋ እድገት አዎንታዊ አስተዋፅዖ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ከዚህ በታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ያንብቡ !!
http://www.eeu.gov.et/news/detail/1022?lang=am

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

13 Nov, 05:53


ወድ ደንበኞቻችን የእርሶን ጥቆማ፣ ቅሬታና አስተያየት የምንቀበልበት አዲሰ የከፈትነው የቴሌግራም ግሩብ (EEU Customers Digital Support) 👉 https://t.me/EEUCustomersupport ተቀላቅለዋል? ካልሆነ እንግዲያውስ ይፈጠኑ! እርሶም ቤተሰብ በመሆን ሌሎችም እንዲቀላቀሉ #share ያድርጉ!

በየትኛውም ቦታ ሆነው ከአገልግሎት አሰጣጣችን ጋር በተያያዘ የሚቀረቡ ማንኛውም ጥቆማና ቅሬታዎችን በፍጥነት ለመፍታት ዝግጁ መሆናችንን እንገልፃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

12 Nov, 13:12


በአዲስ አበባ ከተማ የቅድመ መከላከል ስራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1021?lang=am

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

12 Nov, 10:12


የበቆልማዮ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመረቀ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሶማሌ ክልል፣ በሊበን ዞን፣ በበቆልማዮ ወረዳ ያሰገናበውን የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አስመረቀ፡፡

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢ/ር ሽፈራው ተሊላ ይህ በከፍተኛ ወጪ የተገነባ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የከተማዋን ማህበረሰብ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚዊ እንቅስቃሴ የሚያሻሻል በመሆኑ ነዋሪው እንደራሱ ንብረት አድርጎ ሊጠብቅ ይገባል ብለዋል፡፡

ዋና ሥራ አስፈፃሚው አክለውም ፕሮጀክቱ የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል በከተማዋ ለሚኖሩ 43 ሺህ 542 ነዋሪዎች፣ ትምሕርት ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ የንግድ ተቋማት እና የመንግሥት አስተዳደር ቢሮዎች አገልግሎት ላይ እንደሚውል ተናግረዋል፡፡

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ከዚህ በታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ያንብቡ !!
http://www.eeu.gov.et/news/detail/1020?lang=am

ተቋማችንን የሚመለከቱ ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et

Ethiopian Electric Utility

12 Nov, 05:36


ለአዲስ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ጠያቂ ደንበኞቻችን በሙሉ!

ተቋማችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ሲሆን፤ በተያዘው በጀት ዓመትም አዳዲስ ደንበኞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለማድረግ በሰፊው እየሰራ ይገኛል፡፡

ስለሆነም የነጠላ ፌዝ ቆጣሪ ለማስገባት ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከሎቻችን የምትመጡ አዲስ ደንበኞች፤ የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት ወይም መንጃ ፈቃድ እንዲሁም አንድ 3 በ 4 የሆነ ጉርድ ፎቶግራፍ በመያዝ ያለምንም ውጣ ውረድ በቀላሉ መስተናገድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን፤ ነገር ግን አመልካቹ

የኪራይ ቤት ተጠቃሚ ከሆነ ከባለቤቱ የተሰጠ የስምምነት ደብዳቤ
ተጨማሪ ቆጣሪ ለማስገባት ከሆነ የኤሌክትሪክ ፍጆታ የተከፈለበት የመጨረሻ ደረሰኝ
ጥያቄው ለሽርክና ማህበር ከሆነ የሽርክና ማረጋገጫ ሰነድ ኮፒ በመያዝ ይኖርበታል፡፡

በሌላ በኩል የቆጣሪ ጥያቄው ያቀረበው ቤቱን በመንግስት ስም የተዋዋለ ተከራይ ከሆነ ከሚመለከተው የመንግስት አካል የተሰጠ ፈቃድ፣ የኪራይ ውል እና ማንነቱን የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

በዚህ አጋጣሚ በአገልግሎት መስጫ ማዕከላችን ላገኙት ማንኛውም የአገልግሎት ክፍያ ህጋዊ ደረሰኝ እንዲቀበሉ እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

11 Nov, 08:57


በአዲስ አበባና በጎንደር ከተሞች የጥገናና የመልሶ ግንባታ ስራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1011?lang=am
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

11 Nov, 07:21


የሲዳማ ሪጅን 3ሺህ 360 አዳዲስ ደንበኞች የኃይል ተጠቃሚ ማድረጉን አስታወቀ

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሲዳማ ሪጅን በ2017 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት 3ሺህ 360 አዳዲስ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረጉን የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ አስታውቀዋል፡፡

እንደ አቶ አበበ ገለጻ አዲስ ኃይል ካገኙ አዳዲስ ደንበኞች ውስጥ 85 በመቶ የሚሆኑት የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ኮሜርሻል እና የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ናቸው፡፡

በዚህም 95 በመቶ የሚሆኑት አዳዲስ ደንበኞች በአማካይ በ11 ቀን እንዲያገኙ ማድረግ የተቻለ ሲሆን በአንድ መካካለኛ መስመር ላይ የነበረውን የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽና የቆይታ ጊዜ መቀነስ ተችሏል ብለዋል፡፡

ሪጅኑ በ2017 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት 255 ሚሊየን የኃይል ፍጆታ ለመሰብሰብ አቅዶ መቶ በመቶ ማሳካት የቻለ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ የሪጅኑን ገቢ ለማሳደግ ለ1 ሺህ 23 የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ስማርት ቆጣሪ መግጠም፣ በንባብ ግደፈት፣ በቆጣሪ ብልሽት እና በቁጥጥር ማነስ ያልተሰበሰበ ገቢን መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አክልለውም ሪጅኑ የስማርት ቆጣሪ በመግጠሙ 181 ሚሊየን ብር በፊት ያልተሰበሰበን ገቢ እንዲሰበሰብ ማድረግ ተችሏል፡፡

ሪጅኑ ደንበኞቹን ውጤታማ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ከመስጠት ባሻገር አቅም የሌላቸውን የኃይል ፈላጊ ደንበኞች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ዘዴ ቀይሶ ለማዳረስ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በበጀት አመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አዲስ ደንበኛን የኃይል ተጠቃሚ በማድረግ፣ የፍጆታ ሒሳብ ገቢ በሙሉ በመስብሰበ እና ኃይል አቅርቦቱን ውጤታ በማደረግ ስኬታማ ስራ መስራቱን አስታውቋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

09 Nov, 07:55


የምስራች ለክቡራን ደንበኞቻችን በሙሉ

የተቋማችን የደንበኞች ኮንታክት ሴንተር ከ905 እና 904 ነፃ ጥሪ መስመሮች በተጨማሪ በዲጅታል አማራጭ አገልግሎት መሰጠት ጀመረ፡፡

ከክቡራን ደንበኞቻችን ከአገልግሎት አሰጣጣችን ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ ቅሬታዎችና ጥቆማዎችን ለመቀበልና ለመፍታት ነፃ የጥሪ ማዕከል መዘረጋታችን ይታወቃል፡፡ በአሁን ወቅት ይህ የጥሪ ማዕከል ይበልጥ ለእናንተ ተደራሽ ለማድረግና አገልግሎቱንም ለማስፋት የዲጅታል አማራጭ በመጨመር ወደ ደንበኞች ኮንታክት ሴንትር አድጓል፡፡

በዚህም ማንኛውም ቅሬታዎችና ጥቆማዎችን በተቋማችን የፌስቡክ ገፅ 👉 https://web.facebook.com/EEUOfficial ቴሌግራም ገፅ 👉 https://t.me/eeuethiopia እንዲሁም አሁን ይበልጥ ተደራሽ ለመሆን በከፈትነው ቴሌግራም ግሩፕ 👉 https://t.me/EEUCustomersupport አማካኝት ቦታና ጊዜ ሳይገድባችሁ በቀላሉ ተደራሽ ማድረግ እንደምትችሉ ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው፡፡

👉 የፌስቡክ ገፃችንን https://web.facebook.com/EEUOfficial
👉 እንዲሁም አዲሰ የከፈትነው የቴሌግራም ግሩብ (EEU Customers Digital Support) https://t.me/EEUCustomersupport

ሁላችሁም እንድትቀላቀሉና ሌሎችንም እንዲቀላቀሉ #share እንድታደርጉ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

09 Nov, 06:45


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በወቅቱ አለመፈፀም ለተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብና ቅጣት የሚዳርግ መሆኑን ያውቃሉ? እንግዲያውስ እንንገርዎ!! ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በወቅቱ አለመፈፀም ለተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብና ቅጣት ይዳርጋል፡፡ ስለሆነም ውድ የድህረ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባችሁን በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በወቅቱ እንድትፈፅሙ እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

08 Nov, 09:06


በኦሮሚያ ክልል የቅድመ መከላከል ስራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1008?lang=am
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

08 Nov, 07:44


በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የስርቆት ወንጀል የፈፀመዉ ግለሰብ እጅ ከፍንጅ ተያዘ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዳዉሮ ዞን ዲሳ ወረዳ ጋቶ ጉፎ ቀበሌ ከጎራ እስከ ዲሳ እየተዘረጋ በሚገኘዉ የኤሌክትሪክ ማስፋፊያ መስመር ላይ ጨለማን ተገን በማድረግ የስርቆት ወንጀል የፈፀመው ግለስብ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

ግለሰቡ በቁጥጥር ስር የዋለው በዉድ ዋጋ ወደ ሃገር የገቡ የኤሌክትሪክ የመስመር ሽቦችን በመስረቅ በእንሰት ቅጠል ስር ሲደበቅ የተመለከቱ የህብረተሰብ ክፍሎች ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ ነው፡፡

ተጠርጣሪዉ ላይ የተጀመረው ምርመራ የቀጠለ ሲሆን ምርመራው ሲጠናቀቅ ለዓቃቤ ህግ ተልኮ ክስ የሚመሰረትበት ይሆናል፡፡

በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማቶች ላይ የሚፈፀምን የስርቆት ወንጀል መከላከል የሁሉም ሃላፊነት በመሆኑ መሰል እኩይ ተግባራትን የሚፈፅሙ አከላትን ሲመለከቱ በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ማሳወቅና ጥበቃ ማድረግ ይገባል።

መረጃው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ፓሊስ ኮሚሽን ነው!!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

08 Nov, 05:33


በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል

በሻሸመኔ ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በሻሸመኔ ከተማና በአካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል።

በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን በኃይል ማከፋፊያ ጣቢያው ላይ የተፈጠረው ችግር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ተጠግኖ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትግዕስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

08 Nov, 05:32


የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመሮችን የዘረፉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

ከማኅበረሰቡ ጋር በመተባበር ሦስት የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመሮችን ዘርፈው ለመሸጥ በእንቅስቃሴ ላይ የነበሩ ሌቦችን ከነ ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራው በመጣራት ላይ መሆኑን የሰቆጣ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት አስታውቋል።

የዋግኸምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ደጀን ወዳጅ እንደገለፁት ካለፉት 3 ዓመታት ወዲህ በብሄረሰብ አስተዳደር ዞኑ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ዘረፋ እየተበራከተ መምጣቱን ገልፀው ፤ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም በማኅበረሰቡ ጥቆማ ከነ ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር አውሎ የሰውና የሰነድ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ኮማንደሩ አክለውም ካሁን በፊትም አበርገሌና ሰቆጣ ወረዳ ወለህ አካባቢ ተመሣሣይ የትራንስፈርመር ሥርቆት የፈፀሙ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ለህግ አቅርቦ ውሳኔ መሠጠቱን ገልፀዋል።

በወንጀሉ የተጠረጠሩ 5 ዘራፊዎች ጋር በመቀናጀት ሦስት የኤሌክትሪክ ትራንስፈርመሮችን ዘርፈው ለመሸጥ በመዋዋል ላይ እያሉ መያዛቸውንም የብሄረሰብ አስተዳደር ዞኑ ፖሊስ መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር ደጀን ጨምረው አስረድተዋል።

ዘረፋና ሥርቆትን ለመከላከል ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ወልድያ ሪጅን ሰቆጣ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩም ተናግረዋል።

በመሠረተ ልማቶች ላይ የሚደርስ የዘረፋና ሥርቆት ወንጀሎችን የመከላከሉ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና ህብረተሰቡም የራሱን መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ የጸጥታ አካሉ ተባባሪ እንዲሆን ኮማንደር ደጀን አሳስበዋል።

መረጃው፦የብሄረሰብ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ ነው።

Ethiopian Electric Utility

07 Nov, 11:40


የቅጥር ማስታወቂያ
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

07 Nov, 10:35


የቡሬ አገልግሎትመስጫማዕከል ኤሌክትሪክ በአንድ ቀን የስራ ዘመቻ ተቀላቀለ

በደብረ ማርቆስ ሪጅን የቡሬ አገልግሎትመስጫማዕከል "ኤሌክትሪክ በአንድ ቀን" በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ በሚገኘውን ስራ ዘመቻ ተቀላቅሏል፡፡

ማዕከሉ ዛሬ ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም ባከናወነው የስራ ዘመቻ 80 አዳዲስ ደንበኞችን በአንድ ቀን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል፡፡

ተቋሙ በተያዘው የ2017 በጀት አመት የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ያልሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን "ኤሌክትሪክ በአንድ ቀን" በሚል መሪ ቃል በሃገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ አካባቢዎች እየተከናወነ ይገኛል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

07 Nov, 06:40


የኃይል መቋረጥ መረጃን የሚያደርሱ የቴክኖሎጂ አማራጮች እየተተገበሩ ነው

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል መቋረጥ መረጃዎችን በፍጥነት የሚያደርሱ ቴክኖሎጂዎችን እየተገበረ መሆኑ ተገለፀ፡፡

የኃይል መቋረጥ መረጃ የሚሰጡ ቴክኖሎጂዎች ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ መተግበራቸውን የጠቀሱት የአገልግሎቱ የዲስትሪቢዩሽን ቴክኒካል ሳፖርት ማኔጀር አቶ አቢዮት አብርሃም ቴክኖሎጂዎቹ “9223”፣ “ሳውዝ ክላውድ” እና ”ኤ.ኤም.አይ.” የተሰኙ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት፡-
http://www.eeu.gov.et/news/detail/1004?lang=am

Ethiopian Electric Utility

06 Nov, 13:11


በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል

በላሊበላ 66 ኪ.ቪ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በአይናቡግና፣ በሙጃ፣ በብልባላ ፣ በድብቆ ፣ በሽምሸሀ ፣ በነአኩቶለአብ እና በአካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል።

በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን በኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ የተፈጠረው ብልሽት ተጠግኖ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትግዕስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

06 Nov, 10:45


ለኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በሙሉ

ተቋማችን የደንበኞቹን መረጃ ወቅታዊ ለማድረግና ለማዘመን የአገልግሎት ተጠቃሚነት ውል ስምምነት ከፈረሙ አምስት ዓመት ያለፋቸው ደንበኞችን የውል እድሳት እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል። እስካሁንም በርካታ ደንበኞች የውል እድሳት አከናውነው መረጃቸውን ወቅታዊ አድርገዋል፡፡ ሆኖም ሥራው ውጤታማ በሆነ መንገድና ለደንበኞቻችን በሚያመች መልኩ መከናወን እንዳለበት በመታመኑ፤ ጊዜው እስከ ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ተራዝሟል፡፡ ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ በየአገልግሎት መስጫ ማዕከላቱ በሚወጣው መርሀግብር መሰረት ከህዳር 01 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ያለምንም ክፍያ፡-

የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ፣ ብሄራዊ መታወቂያ፣ ታደሰ መንጃ ፍቃድ ወይም ፓስፖርት
አንድ ጉርድ ፎቶግራፍ
የቀድሞው ውል ወይም የወርሀዊ ፍጆታ ክፍያ ሰነድ ወይም የደንበኝነት መለያ ቁጥር
የስም ዝውውር የተደረገ ከሆነ የተዛወረበትን ህጋዊ ሰነድ፤
የቆጣሪ ባለቤትነቱ በውክልና ከሆነ ህጋዊ የውክልና ሰነድ፣

እንዲሁም የቅድመ ክፍያ ቆጣሪ ተጠቃሚ ከሆኑ ከተጠቀሱት ቅድመ ሁኔታዎች በተጨማሪ ካርድ የተሞላበትን ደረሰኝ በመያዝ የውል እድሳት ማከናወን የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

06 Nov, 07:44


ውድ #የድህረ_ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኛችን የተጠቀሙበትን ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳብ ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተቋሙ በዘረጋቸው ዘመናዊ የክፍያ አማራጮች ይፈፅሙ! ከዚህ በተጨማሪም ወርሃዊ የቆጣሪ ንባብ እየተወሰደ መሆኑን ያረጋግጡ! የቆጣሪ ንባብ ካልተወሰደ ለተጨማሪ ውዝፍ እዳ የሚዳርግ በመሆኑ ወቅቱን የጠበቀ ንባብ መወሰዱን ያረጋግጡ፤አለመነበቡን እርግጠኛ ከሆኑ በአቅራቢዎ ለሚገኙ የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመሄድ ያሳውቁ፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

06 Nov, 07:02


የተቋሙ የፋይናንስ አፈፃፀም በ2017 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት

👉 ከተለያዩ ገቢዎች የተሰበሰበ ጠቅላላ ገቢ ብር 11.16 ቢሊዮን ብር፣

👉ለኢነረጂ ሽያጭ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የተከፈለ 4 ቢሊዮን 422 ሚሊዮን 321 ሽህ 417 ብር ፣
👉ጠቅላላ ወጪ ብር 16 ቢሊዮን ተመዝግቧል፣

በሩብ ዓመቱ በስራ ላይ የዋለ የካፕታል በጀት(ሚሊዮን ብር)

👉ለመልሶ ግንባታ ፕሮጀክቶች 429.71 ሚሊዮን ብር፣
👉ለአዲስ የዲስትሪቢዩሽን ኔትወርክ ግንባታ (ለአዲስ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች) 4,499.1 ሚሊዮን ብር፣
👉ለልህቀት ማዕከልና ሌሎች ቢሮዎች ግንባታ 322.57 ሚሊዮን ብር፣
👉ለገጠር ከተሞችና መንደሮች ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም 466.04 ሚሊዮን ብር በስራ ላይ ውሏል፡፡

Ethiopian Electric Utility

05 Nov, 08:13


ከ90 ሺህ በላይ አዳዲስ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት 90 ሺህ 573 አዳዲስ ደንበኞን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ በማድረግ የዕቅዱን 75 በመቶ ማሳካት ችሏል፡፡

ይህ አፈጻጸም ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 28 ነጥብ 2 በመቶ ጭማሪ አለው፡፡

የአዲስ ደንበኞች ዕድገት ከባለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ2015 በ 46 ሺህ 713 ደንበኞች ወይም 54.5 በመቶ እና ከ2016 በ15 ሺህ 63 ደንበኞች ወይም 17.6 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡

በተጨማሪም በሩብ ዓመቱ 30 የገጠር ቀበሌዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ 26 የሚሆኑ የገጠር ቀበሌዎች ተጠቃሚ በማድረግ የእቅዱ 83.9 በመቶ ተሳክቷል።

የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽን ለማሳጠር በተሠራው ሥራ በሩብ ዓመቱ መሻሻል ማሳየቱ ተመላክቷል፡፡

አገልግሎቱ በሩብ ዓመቱ ባከናወናቸው አንኳር ተግባራት ዙሪያ በዛሬው እለት ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡

የመግለጫውን ሙሉ ይዘት ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ:-
http://www.eeu.gov.et/news/detail/1002?lang=am

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

05 Nov, 06:31


በቤት ውስጥ የሚኖረን የኤሌክትሪክ አጠቃቀም እና ልናደርጋቸው የሚገቡ ቅድመ ጥንቃቄዎች 👇

👉የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለአንድ ሃገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት የሚያበረክተው አስተዋጾ እጅግ ከፍተኛ ቢሆንም በአጠቃቀምና ጥንቃቄ ጉድለት ምክንያት በአካል እና በንብረት ላይ ጉዳት ብሎም ሞት ሲያስከትል ይስተዋላል፡፡

👉ተቋሙ አዲስ ደንበኞቹን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ የመስመር ዝርጋታ የሚያከናውነው እስከ ቆጣሪ ድረስ ያለውን በመሆኑ ከቆጣሪ በኋላ በቤት ውስጥ የሚከናወኑ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታዎች በቂ ልምድ ባለው ባለሞያና ደረጃቸውን በጠበቁ የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶች መሆን ይኖርበታል፡፡

👉ደንበኞች በቤት ውስጥ ሆነ ከቤት ውጪ የሚጠቀሙባቸው ማንኛውም የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶች ከህፃናት ዕይታ ማራቅ እንደሚያስፈልግና ለጊዜው የማይጠቀሙባቸውን የኤሌክትሪክ መገልገያ ቁሳቁሶችን ከሶኬት ላይ ነቅሎ ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል ፡፡

👉ከዚህ በተጨማሪም ለኤሌክትሪክ አደጋ ስጋት የሚሆኑ ቁሳቁሶችን ማስወገድ፤ እርጥበት እና እርጥበት አዘል ሁኔታዎችን ከኤሌክትሪክ አካባቢ ማስወገድ፣ ትክክለኛ እና ደረጃቸውን የጠበቁ የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶችን መጠቀም አስፈላጊ ነው፡፡

👉የቤት ውስጥ የመስመር ዝርጋታ የሚያከናውን አካል ቅድሚያ ከቆጣሪ ኤሌክትሪክ በማቋረጥ ሁሌም በጥንቃቄ እና ሀሳቡን ሰብስቦ ስራውን በትኩረት ሊያከናውን ይገባል፡፡

Ethiopian Electric Utility

04 Nov, 13:56


በአዲስአበባ ከተማና በሐረሪ ሪጅን የመልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ስራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡፡
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1000?lang=am
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

04 Nov, 11:59


ሁለተኛው ምዕራፍ የሬዲዮ ኮሙኒኬሽን ተግባራዊ ተደረገ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሁለተኛ ምዕራፍ የሬዲዮ ኮሙኒኬሽን በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ተግባራዊ ተደርጓል።

የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ምዕራፍ ትግበራ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ስር በሚገኙ 13 ሳይቶች ሲሆን አቃቂ ቃሊቲ፣ አለምገና፣ አዳማ፣ ሃዋሳ፣ ድሬደዋ፣ ጅማ፣ ባህርዳር፣ ሐረር፣ መቀሌ፣ ወላይታ ሶዶ፣ አርባ ምንጭ እና ጅግጅጋ ከተሞች ይገኙበታል፡፡

ተቋሙ ተግባራዊ ያደረገው የሬዲዮ ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ በየደረጃው በሚገኙ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች መካከል ፈጣን የመረጃ ልውውጥ እንዲኖር በማድረግ ቀልጣፋና ጥራት ያለው የአስቸኳይ ጥገና አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው፡፡

በሁለተኛው ምዕራፍ የሬዲዮ ኮሙኒኬሽን ማስፋፊያ ሥራ 160 የእጅ፣ 64 የጠረጴዛ /ቤዝ ፣ 74 እና 64 የመኪና በአጠቃይ 298 ሬድዮዎች ተሰራጭተዋል።

የመጀመሪያው ምእራፍ የሬዲዮ ኮሙኒኬሽን በአዲስ አበባ በሁለት ሪፒተር ሳይቶች ተግባራዊ መደረጉ የሚታወስ ነው።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

04 Nov, 06:34


የጋዜጣዊ መግለጫ ጥሪ (ለሁሉም መገናኛ ብዙሃን)

ተቋማችን በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈፃፀም ላይ ነገ ማክሰኞ ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም ጠዋት 3፡30 ለሁሉም መገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል፡፡

ጋዜጣዊ መግለጫው ሜክሲኮ አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ንግድ ሥራ ት/ቤት ፊት ለፊት በሚገኘው ንብ ባንክ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ 17ኛ ፎቅ ላይ ስለሚሰጥ፤ ሁሉም መገናኛ ብዙሃን በቦታው ተገኝታችሁ እንድትሳተፉና መረጃውንም ተደራሽ እንድታደርጉልን በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

04 Nov, 06:13


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያን በቀላሉ፣ የትም ሳይሄዱ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ካሻዎ በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕሮ ወይም በኤም ፔሳ በኩል ይፈፅሙ፡፡

ፍጆታዎ በስልክዎ!
ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ በመምረጥ ኑሮዎን ያቅሉ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

04 Nov, 05:56


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል

በሁርሶ ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በምስራቁ የሃገራችን ክፍል በሚገኙ የድሬ ዳዋ፣ የሀረረ፣ የጅግጅጋ ከተሞች እና አካባቢያቸው ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል፡፡

የጥገና ስራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁ ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

03 Nov, 08:22


የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል

በሁርሶ ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በምስራቁ የሃገራችን ክፍል በሚገኙ የድሬ ዳዋ፣ የሀረረ ፣ የጅግጅጋ ከተሞች እና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል።

በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን በኃይል ማከፋፊያ ጣቢያው ላይ የተፈጠረው ችግር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ተጠግኖ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትግዕስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

02 Nov, 08:27


በአድዋ፣ በድሬዳዋ እና በጎንደር ከተሞች ከጥቅምት 23 ጀምሮ 2017 ዓ.ም ለመልሶ ግንባታ፣ ለአዲስ ኃይል ማገናኘት እና ለቅድመ-ጥገና ሥራ በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/999?lang=am

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

02 Nov, 08:23


የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል
**
በጎንድር 01 ቁጥር ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት ፋሲል፣ አራዳ፣ ትክል ድንጋይ እና አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡

በተመሳሳይ በድሬ ዳዋ ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በድሬ ዳዋ ከተማ በከፊል የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡

በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን በሁለቱ ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ላይ የተፈጠረውን ችግሩን ለመፍታት ርብርብ እየተደረገ ስለሆነ በትግዕስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

02 Nov, 07:37


ከ3 ሚሊየን በላይ ቆጣሪዎች ወቅታዊ መረጃ ተሰበሰበ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከ3 ነጥብ 2 ሚለየን በላይ ቆጣሪዎች ወቅታዊ መረጃ መሰብሰብ ችሏል፡፡

የቆጣሪ መረጃ መሰብሰብ ከተጀመረበት 2014 ዓ.ም እስከ 2017 በጀት ዓመት መስከረም ወር መጨረሻ ድረስ የ3 ሚለየን 211 ሺህ 782 ቆጣሪዎች መረጃ ተሰብስቧል፡፡

በኦሮሚያ ከ1 ሚሊየን በላይ ቆጣሪ መረጃ፣ በአማራ ከ7 መቶ ሺህ በላይ፣ በአዲስ አበባ ከ6መቶ ሺህ በላይ እንዲሁም በደቡብ ከ400 ሺህ በላይ ቆጣሪ መረጃ ተሰብስቧል፡፡

የቆጣሪ መረጃ መሰብሰቡ ደንበኞች በተበላሸ ቆጣሪ ምክንያት ላልተገባ ወጪ እንዳይዳረጉ፣ አገልግሎቱም ትክክለኛ የፍጆታ ሂሳብ እንዲሰበስብ የሚያግዝ ይሆናል፡፡

ወቅታዊ የቆጣሪ መረጃ ለማሰባሰብ 74.7 ሚሊየን ብር በጀት የተመደበ ሲሆን አፈፃፀሙም 78 በመቶ ደርሷል፡፡


#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

02 Nov, 06:56


ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

ዛሬ ጥቅምት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 8፡00 ድረስ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአዲስ ሴንተር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የጥገና ሥራ ስለሚከናወን በአዲስ አበባ ሜክሲኮ ደብረወርቅ ህንጻ፣ ኤግዚቢሽን ማዕከል፣ ኦሎምፒያ፣ ገነት ሆቴል፣ አይናለም ቨዜ ሕንፃ፣ ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ኢቢሲ፣ ሂልተን ሆቴል፣ መቻሬ፣ ልደታ ፀበል፣ መብራት ኃይል ክበብ ጀርባ፣ አፍሪካ ህብረት እና በአካባቢያቸው፤

በተመሳሳይ ጥቅምት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 9፡00 ድረስ በመካኒሳ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የጥገና ሥራ ስለሚከናዎን በጀሞና አካባቢው፣ በአርሴማ እና አካባቢው፣ በጀረመን አደባባይ እና አካባቢው፣ በካፒታል ሲሚንቶ፣በመስታውት ፋብሪካ ፣ በላፍቶና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡

ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ስራው ተጠናቆ ወደ አገልግሎት እስኪመለስ ድረስ በትግዕስት እንድትጠብቁ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

01 Nov, 15:27


በሐረሪ ሪጅን ጥቅምት 23 ቀን 2017 ዓ.ም የመልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ስራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡፡
http://www.eeu.gov.et/power-interruption?lang=am
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

01 Nov, 15:26


በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል

በጎንደር ቁጥር 1 ልደታ ኃይል ማከፋፈያ ፓወር ትራንስፎርመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት ዛሬ ከጠዋቱ 1 ሰዓት ጀምሮ ለፋሲል፣ለአራዳና ለትክል ድንጋይ ኃይል የሚያቀርበው መስመር እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡

በዚህም ምክንያት በጎንደር ከተማ ፒያሳ፣አውቶፓርኮ እና ዩሐንስ ቀበሌ 10 የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ጥገናው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

01 Nov, 06:36


የሃይል ብክነትን እንዴት መከላከል እንችላለን?

ኤሌክትሪክ ለአንድ ሃገር ሁለንተናዊ የልማት እንቅስቃሴ ሚናው የጎላ ቢሆንም ቴክኒካል እና ቴክኒካል ባልሆኑ ምክንያቶች ሲባክን ይስተዋላል፡፡

በሃይል አጠቃቀም ችግርና ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን የሃይል ብክነት ለመቀነስ ኃይል ቆጣቢ የሆኑ የኤሌክትሪክ መገልገያ ዕቃዎችን መጠቀምና የኤሌክትሪክ መጠቀሚያ ዕቃዎችን ኃይል ቆጣቢ መሆናቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ለረዥም ጊዜ ያገለገሉ የኤሌክትሪክ ምጣድ፣ ምድጃ፣ ማሽን እና ሌሎች የኤሌክትሪክ መገልገያ ዕቃዎችን በአዳዲስ መቀየር እና የኃይል ጭነት በማይበዛበት ጊዜ ማለትም ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 11፡00 መጠቀም የሃይል ብክነትን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል፡፡

እርስዎ ከላይ የተጠቀሱትን ዘዴዎች በስራ ላይ ሲያውሉ የሃይል መቆራረጡን ለመቀነስ በሚደረገው ጥረት የበኩልዎን አስተዋፆ ከማበርከት በተጨማሪ የፍጆታ ወጪ ይቀንሳሉ፡፡

የኤሌክትሪክ ኃይልን መቆጠብ መልካም ዕሴታችን እናድርገው!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

31 Oct, 08:32


በጋምቤላ ክልል የቅድመ መከላከል ስራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ:-http://www.eeu.gov.et/power-interruption?lang=am

Ethiopian Electric Utility

24 Oct, 11:45


የዲጂታል የክፍያ አማራጮች ምንነት እና ያላቸው ጠቀሜታ

የዲጅታል ክፍያ መፈፀሚያ ሥርዓቶች ለተገልጋዩ ማህበረሰብ ብሎም ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ካላቸው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ መካከል ባህላዊ ጥሬ ገንዘብን በመተካት ወይም ግብይቶችን ወደ ዲጂታል በመቀየር የትኛውንም የአገልግሎት ክፍያ በቀላሉ መፈፀም ያስችላሉ፡፡

ተቋማችን ከጊዜ ወደ ጊዜ አሰራሩን በማዘመን የደንበኞቹን የአገልግሎት ዕርካታ ለመጨመር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ከሚገኝባቸው ዘርፎች አንዱ የዲጅታል ክፍያ ስርዓት ይጠቀሳል፡፡

በዚህም ለድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባቸውን ለመፈፀም እንዲችሉ ከተዘረጉ ዘመናዊ አማራጮች መካከል ቴሌ ብር፣ ሲቢኢ ብር፣ ሲቢኢ ሞባይል ባንኪንግ፣ ሲቢኢ ኢንተርኔት ባንኪንግ፣ አዋሽ ብር ፕሮ እና በቅርቡ ስራ ላይ ያዋለው ሳፋሪኮም ኤምፔሳ ይገኙበታል፡፡

በተመሳሳይ ለቅድመ ክፍያ ቆጣሪ ተጠቃሚ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ኃይል የሚገዙበት አሰራር ወደ ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ ለማስገባት ነባር የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን በስማርት ቆጣሪዎች ለመቀየር ተቋማችን በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡

ሙሉ ትንታኔውን ለማንበብ፡ 👉 http://www.eeu.gov.et/news/detail/959?lang=am

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

24 Oct, 06:42


የተቋማችን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢ/ር ሺፈራው ተሊላ በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከዋልታ ቴሌቪዥን ነጻ ሃሳብ ፕሮግራም ጋር ያደረጉት ቆይታ ክፍል 1 !!

Ethiopian Electric Utility

23 Oct, 11:22


ከግልገል በለስ ድባጤ ያለው መካከለኛ ቮልቴጅ የሃይል አስተላላፊ መስመር የመልሶ ግንባታ ስራ ተጀመረ

የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ የኢንሱሌተር ቅየራ ሥራ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌትሪክ አገልግሎት የቤኒሻንጉል ሪጅን የቡለን ደንበኞች አገልግሎት መሥጫ ማዕከል ስራ አስኪያጅ አቶ ያደታ ቢራቱ ገልፀዋል።

የመልሶ ግንባታ ሥራው ሲጠናቀቅም የቡለን፣ ድባጤና ወንበራ ወረዳዎች በተደጋጋሚ የሚከሰተውን የኃይል መቆራረጥ ለመቀነስ ያግዛል።

የቴክኒክ ሠራተኞች በሚደርሱበት ቦታ ማህበረሰቡን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት ለሥራው ቀና ትብብር እንዲያደርጉ ሥራ አስኪያጁ አሳስበዋል።

በመልሶ ግንባታ ስራው ሪጅኑን ጨምሮ የቡለን እና የደብረዘይት የአገልግሎት መስጫ ማዕከል የቴክኒክ ቡድን በጋራ እየሠራ ይገኛል ፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

23 Oct, 08:01


በአዲስ አበባ ከተማ አንዳንድ አካባቢዎች የቅድመ ጥገና የመልሶ ግንባታ ስራ ለማከናዎን ሲባል በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎችን ለማየት ይህ ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ:-http://www.eeu.gov.et/power-interruption?lang=am

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

23 Oct, 05:55


በህገ ወጥ መንገድ ቆጣሪ በማስገባት የሃይል ስርቆት እንዲፈፀም ባደረገ ግለሰብ ላይ የፍርድ ውሳኔ ተላለፈ!!

Ethiopian Electric Utility

23 Oct, 05:36


⚠️ከአጭበርባሪዎችና ከደላሎች እራስዎን ይጠብቁ!⚠️

ውድ ደንበኞቻችን ተቋማችን በአገልግሎት አሰጣጡ ፍትሃዊነትና ተጠያቂነት ከማስፈን ባሻገር ህጋዊነቱንም ጭምር ለማረጋገጥ ለደንበኞቹ የትኛውንም አይነት አገልግሎት ሲሰጥ የራሱ የሆነ የአሰራር ስርዓት እንዲሁም ህግና ደንብን ተከትሎ ነው፡፡

ተቋማችን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኤሌክትሪክ ኃይልን በጅምላ በመግዛት ለህብረተሰቡ ለማድረስ በአዋጅ የተቀመጠ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ ይህንኑ ኃላፊነት ተከትሎ ተቋሙ የኤሌክትሪክ ኃይልን ፍትኃዊነትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎቱን ለተጠቃሚው ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመተግበር ደንበኞቹን እያገለገለ ይገኛል፡፡

ተቋማችን ከሚሰጣቸው መሰረታዊ አገልግሎቶች መካከል በዋናነት የመካከለኛ እና ዝቅተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመሮችን መዘርጋት፣ አዲስ ደንበኛን ማገናኘት፣ የዲስትሪቡዩሽን ትራንስፎርመሮችን መግጠም በዋናነት ተጠቃሽ ናቸው፡፡

በመሆኑም አንድ ደንበኛ ከላይ የተጠቀሱትንና ተያያዥ አገልግሎቶች ለማግኘት ወደ አገልግሎት ማዕከላችን ሲመጣ፤ ደንበኞችን ለማስተናገድ ተቋሙ ባስቀመጣቸው የአሰራር ስርዓቶች እንዲሁም ህግና ደንቦችን በመከተል በየደረጃው ያሉ ሰራተኞች እና የስራ ኃላፊዎች ተፈፃሚ እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡

በተጨማሪም ደንበኞች ለእያንዳንዱ ለተገለገሉበት የአገልግሎት ክፍያ ተቋማችን ህጋዊ የአገልግሎት ክፍያ ደረሰኝ ይሰጣል፡፡

⛔️ ሆኖም አሁን ላይ አንዳንድ አጭበርባሪዎችና ደላሎች ጉዳይ እናስፈፅማለን፣ የኤሌክትሪክ መስመር እንዘረጋለን፣ ቆጣሪ እና ትራንስፎርመር እንገጥማለን፣ ስም እናዛውራለን በማለት ደንበኞችን ያለ አግባብ እየበዘበዙና ለህገ-ወጥ ተግባር እየዳረጉ ይገኛሉ፡፡

ተቋማችን መሰል የህገ-ወጥ ተግባር የሚፈፅሙ ደላሎች እና ተባባሪ የህብረተሰብ ክፍሎችን ከፀጥታ ኃይሎችና ከህግ አካላት ጋር በመተባበር በህግ ተጠያቂ እያደረገ ሲሆን፤ ይህን ጥረቱንም በቀጣይ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

በመሆኑም ውድ ደንበኞቻችን ስለ ተቋማችን የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም ሌሎች መረጃዎችን በተቋሙ ይፋዊ ድህረ-ገፅ እንዲሁም የፌስቡክ እና ቴሌግራም ገፅ፣ በ905 እና 904 ነፃ የስልክ ጥሪ፣ ተቋሙ በቅርቡ ስራ ላይ ያዋለውን የሞባይል መተግበሪያ ብሎም በየደረጃው የሚገኙ የተቋሙ ቢሮዎች አማካኝነት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን፤ አገልግሎታችንን ህጋዊነቱን በተከተለ መልኩ እንድትጠይቁ፣ ነገር ግን ከአጭበርባሪዎችና ከህገ-ወጥ ደላሎች ደግሞ ራሳችሁን እንድትጠበቁ እንዲሁም መሰል ድርጊት ስትመለከቱም ለፀጥታ አካላትና በአቅራቢያ ለሚገኝ አገልግሎት መሰጫ ማዕከላችን ጥቆማ በማቅረብ እንዲተባበሩ እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

22 Oct, 17:35


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል

በመሬት ውስጥ ተቀባሪ የኤሌክትሪክ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በየካ አባዶ ኮንዶሚኒየም ብሎክ 440 እና 447፣ አርሴማ አካባቢ፣ ወጋገን ባንክ ጀርባ፣ ሸገር ዳቦ መሸጫ፣ አባዶ መስቀለኛ እና ፒያሳ አካባቢዎች ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት በተደረገ ከፍተኛ ርብርብ ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል ፡፡

የጥገና ስራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁ ደንበኞቻችን ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

22 Oct, 12:46


በመሬት ውስጥ ተቀባሪ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል

በመሬት ውስጥ ተቀባሪ የኤሌክትሪክ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የካ አባዶ ኮንዶሚኒየም ብሎክ 440 እና 447፣ አርሴማ አካባቢ፣ ወጋገን ባንክ ጀርባ፣ ሸገር ዳቦ መሸጫ፣ አባዶ መስቀለኛ እና ፒያሳ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል ፡፡

ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ያጋጠመውን ብልሽት ጠግኖ ወደ አገልግሎት ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አውቃችሁ በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

22 Oct, 09:03


715 አዳዲስ ደንበኞች በአንድ ቀን የኤሌክትሪከ ተጠቃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ወልዲያ ሪጅን "ኤሌክትሪክ በአንድ ቀን" በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ በሚገኘው የስራ ዘመቻ 715 አዳዲስ ደንበኞች በአንድ ቀን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል፡፡

በሪጅኑ እየተከናወነ በሚገኘው የስራ ዘመቻ ከተስተናገዱ አዳዲስ ደንበኞች ውስጥ 266 የሚሆኑት በሐምሌና በነሐሴ ወራት ሃይል በጠየቁ በ24 ስዓት ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል የገባላቸው ሲሆኑ 314 የሚሆኑ ደግሞ በመስከረም ወር ብቻ የሃይል ተጠቃሚ የሆኑ ናቸው፡፡

በመስከረም ወር ኤሌክተሪክ ከገባላቸው አዳዲስ ደንበኞች ውስጥ 147 የሚሆኑት በመስከረም 27 ቀን የተገናኘላቸው ሲሆኑ 136 የሚሆኑት ደግሞ በአንድ አገልግሎት መስጫ ማዕከል የተገናኙ ናቸው፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ሪጅኑ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ያልሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ በጀመረው የስራ ዘመቻ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ.ም 135 አዳዲስ ደንበኞችን የሃይል ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል፡፡

በሪጅኑ የሚገኙ አዲስ ሃይል ፈላጊ ደንበኞችን በአንድ ቀን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ያደረገው በጋሸና፣ በመርሳ፣ በወልድያና በሰቆጣ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ሲሆን አሁን የጀመረውን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የማድረግ ተግባር በማጠናከር የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ደንበኞችን ቁጥር ለማሳድግ እየሰራ ነው፡፡

ተቋሙ በተያዘው የ2017 በጀት አመት የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ያልሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን "ኤሌክትሪክ በአንድ ቀን" በሚል መሪ ቃል በሃገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ አካባቢዎች እየተከናወነ ይገኛል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

22 Oct, 08:24


በአዲስ አበባ ከተማ አንዳንድ አካባቢዎች የቅድመ ጥገና የመልሶ ግንባታ ስራ ለማከናዎን ሲባል በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎችን ለማየት ይህ ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ:-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/987?lang=am
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

22 Oct, 07:37


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያን በቀላሉ፣ የትም ሳይሄዱ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ካሻዎ በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕሮ ወይም በኤም ፔሳ በኩል ይፈፅሙ፡፡

ፍጆታዎ በስልክዎ!
ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ በመምረጥ ኑሮዎን ያቅሉ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

21 Oct, 16:26


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ሽፈራው ተሊላ ከአዲስ ዋልታ ቴሌቪዥን #ነፃ_ሐሳብ ጋር ያደረጉትን ቆይታ ረቡዕ ምሽት 3፡00 ይጠብቁ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

21 Oct, 13:24


ለክቡራን ደንበኞቻችን በሙሉ

ከአገልግሎት አሰጣጣችን ጋር በተያያዘ የሚቀርቡ ቅሬታዎችና ጥቆማዎችን ለመቀበልና ለመፍታት ነፃ የጥሪ ማዕከል መዘረጋታችን ይታወቃል፡፡ በአሁን ወቅት ይህ የጥሪ ማዕከል ይበልጥ ለደንበኞቻችን ተደራሽ ለማድረግና አገልግሎቱንም ለማስፋት የዲጅታል አማራጭ በመጨመር ወደ ደንበኞች ኮንታክት ሴንትር ለማሳደግ እየሰራን እንገኛለን፡፡

ለዚህም እንዲያግዝ 905 እና 904 ነፃ ስልክ መስመሮች የምናስተናግድበት የጥሪ ማእከላችን አሁን ከሚገኝበት አድራሻ ወደ ሌላ የተሻለ ቢሮ ከትላንት ጥቅምት 10 ቀን 2017 ጀምሮ የማዛወር ሥራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ሥራው ዛሬም ባለመጠናቀቁ በአዲስ አበባ የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን በአቅራቢያችሁ የሚገኝ አገልግሎት መስጫ ማዕከላችን ቀጥታ ስልክ ቁጥር በመደወል በጊዜያዊነት መገልገል የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

ለተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል ይቅርታ እየጠየቅን፤ የጥሪ ማዕከሉ ወደ መደበኛ አገልግሎት እንደተመለሰ ወዲያው የምናሳውቅ መሆኑንም እንገልፃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

21 Oct, 12:00


ተቋርጦ የቆየው የኃይል አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ተመልሷል

በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በትላንትናው ዕለት የኃይል አቅርቦቱ ያልተመለሰላቸው የለገጣፎ ከተማ፣ 44 እና ኢንዱስትሪ መንደር እንዲሁም አባዶ ኮንድምኒየም አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ የኃይል አቅርቦቱ ተመልሶላቸዋል፡፡

ስለሆነም የጥገና ስራው ሙሉ በሙለ ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁ ደንበኞቻችን ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

21 Oct, 07:42


ተቋርጦ የቆየው የኃይል አቅርቦት በከፊል ተመልሷል

በለገጣፎ ከፍተኛ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት አምባሳደር ሪል ስቴት፣ አያት ዞን 1፣ ዞን 2 እና ዞን 8፣ መሪ 40/60 ኮንድምኒየም፣ ሰባ ሁለት፣ ከሸገር ዳቦ ወደ ጥሩ መናፈሻ፣ ሳራ አምፖል ፋብሪካ፣ ካራ ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ወደ አገልግሎት የተመለሰ ሲሆን፤ በቀሪዎቹ አካባቢዎች ማለትም በለገጣፎ ከተማ፣ 44 ማዞሪያ፣ ኢንዱስትሪ መንደር፣ ገዋሳ እንዲሁም የካ አባዶ ኮንዶሚኒየም በከፊል ኃይል ለማገናኘት ጥረት እየተደረገ ነው፡፡

ኤሌክትሪክ ለተመለሰላችሁ ደንበኞቻችን በትዕግስት ስለጠበቃችሁ ምስጋና እያቀረብን፤ አሁንም የኃይል አቅርቦቱ ባልተመለሰባቸው አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ጥገናው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ አቅርቦቱ ወደቦታው እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠባበቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

21 Oct, 07:05


ሪጅኑ ለ6ሺህ 96 አዳዲስ ደንበኞች ኃይል አገናኘ

የአዳማ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2017 በጀት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ለ6 ሺህ 96 አዳዲስ ደንበኞች ኃይል የማገኛኘት ሥራ አከናውኗል፡፡

ሪጅኑ በሩብ ዓመቱ 7 ሺህ 384 ለሚሆኑ ደንበኞች አዲስ ኃይል ለማገናኘት አቅዶ 6ሺህ 96 ለሚሆኑ ደንበኞች በማገናኘት የእቅዱን 83 በመቶ ማሳካት ችሏል።

አዲስ ኃይል ከተገናኘላቸው ደንበኞች መካከል በ በቆጂ፣ አሰላ፣ መተሀራ፣ ዝዋይ፣ ሞጆ፣ መቂ እና ሌሎች ከተሞች ይገኙበታል፡፡

የአዲስ ኃይል አቅርቦቱ ተጠቃሚ ከሆኑት ደንበኞች መካከል 4ሺህ 548 የሚሆኑት በተቀመጠው የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ መሰረት ማለትም በ10 ቀናት ውስጥ የተስተናገዱ ናቸው።

በተጨማሪም ሪጅኑ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት መልሶ ግንባታና ማሻሻያ ሥራ 39 ነጥብ 22 ኪሎ ሜትር ሥራ በማከናወን የእቅዱን 94 በመቶ ማሳካት ችሏል።

በመልሶ ግንባታ ሥራው ከተከናወኑ ተግባራት መካከል 784 የኮንክሪት እና የእንጨት ምሰሶ ተከላ ስራ የተሰራ ሲሆን፤ የመልሶ ግንባታ ሥራው የተከናወነው በአዳማ ሪጅን ዴክሲስ፣ ዴራ እና መተሀራ አካባቢዎች ነው።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

19 Oct, 14:34


የጥሪ ማዕከል ቦታ ማዛወር ስራ ስለሚከናወን ማዕከሎቻችን አገልግሎት አይሰጡም

ነገ እሁድ ጥቅምት 10 ቀን 2017 ዓ.ም እና ሰኞ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ሙሉ ቀን የጥሪ ማዕከል ቦታ ማዛወር ስራ ስለሚከናወን የ905 እና 904 ነጻ የጥሪ ማዕከሎቻችን አገልግሎት አይሰጡም፡፡

ስለሆነም የቦታ ማዛወር ስራው ተከናውኖ የጥሪ ማዕከሎቻችን ወደ አገልግሎት እስኪመለሱ ድረስ በአዲስ አበባ የምትገኙ ደንበኞቻችን ከስር ባያያዝነው ስልክ ቁጥር በመደወል ወይም በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በአካል በመሄድ አገልግሎት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

19 Oct, 11:34


በአዲስ አበባ ከተማ አንዳንድ አካባቢዎች የቅድመ ጥገና የመልሶ ግንባታ ስራ ለማከናዎን ሲባል በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎችን ለማየት ይህ ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ http://www.eeu.gov.et/power-interruption?lang=am

Ethiopian Electric Utility

19 Oct, 06:15


የኤሌክትሪክ መስመር ጥገና ሥራ እጅግ ፈታኝና ህይወትን አደጋ ላይ የሚጥል ነው፡፡ ባለሞያዎቻችን የኤሌክትሪክ ኃይል ሲቋረጥ መልሶ ለማገናኘት በሚያደርጉት ጥረት አካላቸውን አልፎም ህይወታቸውን ሊያጡ ይችላሉ፡፡ ሆኖም ህዝብን ማገልገል ቀዳሚው ሥራችን በመሆኑ፤ በብዙ መስዋቶች ውስጥም ሆነን እናንተን ውድ ደንበኞቻችን ለማገልግል ሁሌም ተግተን እንሰራለን፡፡ ያሉብንን ክፍተቶች በማረም ከእናንተ ጋር በጋራ በመስራት የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት በቀርጠኝነት እንተጋለን፡፡

በዚህ አጋጣሚ ዋልታ ቴሌቪዥን ከኤሌክትሪክ መስመር ጥገና ጀረባ ያሉ እውነቶችን አስመልክቶ የሰራውን ፕሮግራም እንዲመለከቱ እንጋብዛለን፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=NsmxJlQ1xsg

Ethiopian Electric Utility

18 Oct, 13:47


በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የኃይል አቅርቦት

በለገጣፎ የኃይል ማከፋያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በለገጣፎ ከተማ፣ ለገጣፎ አዲሱ መንገድ፣ አምባሳደር ሪል ስቴት፣ አያት ዞን 1፣ ዞን 2፣ እና ዞን 8፣ መሪ 40/60 ኮንድምኒየም፣ ሰባ ሁለት፣ ከሸገር ዳቦ ወደ ጥሩ መናፈሻ፣ ሳራ አምፖል ፋብሪካ፣ ካራ እና አባዶ ኮንድምኒየም ሙሉ በሙሉና በከፊል የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ብልሽቱን ለመጠገን ርብርብ እያደረገ መሆኑን በመገንዘብ ጥገናው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ በትዕግስት እንድትጠባበቁን እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Ethiopian Electric Utility

18 Oct, 08:16


በአዲስ አበባ ከተማ ከጥቅምት 9 እስከ 30 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ ኃይል ለማገናኘትና በመልሶ ግንባታ ምክንያት በዕቅድ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸውን አካባቢዎችን ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption?lang=am

Ethiopian Electric Utility

18 Oct, 06:56


በክልሉ 11 የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው

ተቋሙ ግንባታቸው የተጠናቀቁት ማዕከላት በ ደ/ታቦር፣ ተንታ እና ወራታ እንዲሁም በዳንግላ አንድ የሰብስቴሽን መቆጣጠሪያን ጨምሮ አሁን ላይ ግንባታቸው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራቱን እና የደንበኞቹን ዕርካታ ለመጨመር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት፡-http://www.eeu.gov.et/news/detail/981?lang=am

#የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት