ውድ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ የከበረ ሰላምታችንን እያቀረብን አንዳንድ መረጃዎችን እንዲሁም መልክትን ለማስተላለፍ እንወዳለን።
1ኛ, ማንኛውም ተማሪ ንብረቱን በጥንቃቄ ሊይዝ ይገበዋል
2ኛ, ዶርም ሳትቆልፉ መውጣት አትርሱ መፀዳጃ ቤት እንኳን ቢሆን የሄዳችሁት
3ኛ, በየኮሪደር እና ሻወር ቤት እንዲሁም ዶርም እና በጀርባ በኩል የሚገኘው መብራቶች በርተው ውለው ሲያድሩ ይታያሉ። በመሆኑም በሃላፊነት ስሜት ሁላችንም ልንቆጣጠራቸው እና ልናጠፋቸው ግድ ይለናል።
4ኛ, ሁሌም እንደምንለው ውጭ የምናመሽ ተማሪዎች በጊዜ እንግባ እንዲሁም የምንወጣ ተመሪዎች በጊዜ እንውጣ ጊዜው አይደለም እንኳንለማታ ለቀንም አስቸግሯል።
5ኛ, ላፕቶፕ በላይብረሪ ለብዙ ሰአት ትታችሁ የምትቆዪ እባካችሁ ንብረታችሁንም ተጠንቀቁለት፣ሃላፊነቱንም የራሳችሁ ነው
6ኛ, ዴስቲቪ በምትመለከቱ ጊዜ ያላግባብ ድምጽ የምታወጡ እንዲሁም በወንበር የምትነጋገሩ ሁላችንም እራሳችንን እንፈትሽ
7ኛ,ውሃን ያላግባብ ተከፍቶ ሲፈስ ካየን መዝጋት የሚያሰቸግር(የተበላሸ) ከሆነ ለሚመለከተው ማሳወቅ,ተከፍተው ያሉ በር እና መስኮትን መዝጋት
8ኛ,ከጊዜ ወደ ጊዜ በከተማችን በግቢ አከባቢም ጭምር አሰቸጋሪ ሌባ ተንሰራፍቶ ይገኛል, የሌቦች ባህርያት በባጃጅ እንሸኛችሁ,ይሄን ጽሁፍ አንብብልኝ,ሎተሪ ደርሶኝ ብሄራዊ ሎተሪ አሳዩኝ ፣እስከዛው ስልካችሁን ይዠልቆይ መታወቂያ የለኝ ሆኖነው እናንተ አውጡልኝ ስልክ ቁጥር ያዝልኝ,አንዴ አስደውለኝ, ገፍቶ ለማለፍ መሞከር, ለማኝ መምሰል,ደካማ መምሰል,የሃይማኖት አባት መምሰል, ፈፅሞ የማይገመት (ሃብታም) ወዘተ በመምሰል........ ብቻ በተለያዪ ዘዴ እየሸወዱ ይገኛል። አንዱም የዩንቨርስቲ ተማሪዎች የዝርፊያው ተጋላጭ ናቸው። ስለዚህ እባካችሁ ተጠንቀቁ።
አብዛኛው መልክት ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ ላይ ያተኩራል።