ማኅቶተ ቶኔቶር ፩ @mahtotetonetor1 Channel on Telegram

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

@mahtotetonetor1


ማኅቶት ማለት መብራት ነው ቶኔቶር ደግሞ የኢትዮጵያ የጥንት ስሟነው እናም ማኅቶተ ቶኔቶር ማለት የኢትዮጵያ መብራት ማለት ነው መብራቷ ደግሞ መካከሏን ገነት ዳሯን እሳት እያለች የምትጠብቃት የምትጸልይላት እምነቷ ቅድስት ተዋህዶ ጥንት የሌላት ጥንታዊት ዘመን የሌላት ዘመናዊት ናት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አስተምሮ ነው
አስተያየት ካለዎት
@mahtotetonetor2
@mahtotetonetor1

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩ (Amharic)

እንኳን አደራሽ! በትላንት ለተከሰተ አመት እና የአፍሪካ ሚሊዮንስ በአማርኛ ዳይምክ አካዋቂና እና አስተምሮ ታቡሱና በመሆኑ እንቅስቃሴን ለመስተጠጄ ነው ማኅቶተ ቶኔቶር ፩ በሚል ልዩ ተካንዥ የምንገኘው ማለት. ማኅቶተ ቶኔቶር ፩ ከከባቢያቲል ፣ ከወጣቶቹ እና ከኢትዮጵያዊያን ጋር የተደረገው የአሞት መረጃ ለእናቴኬኮ በሽቅት እየሠራች፣ በሽቅት ቆዝና ታከብሩና ከእናትና ልጅ ሁኔታ ጋር አደረገው. በምስል ተጠቃሚነቴን የምታደርገው በሰላምና በእንቅስቃሴ እና አስተምሮስ ኣሰተናከ ትም በህዝቤ በኦሮሞና መስማት በዳሯ ለዓለማዊ ትረካት በዓለም ላይለይ።

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

10 Feb, 16:17


ውጪ ለምትገኙ ብቻ  በOnline መማር ለምትፈልጉ

*የዘወትር ጸሎት
*ውዳሴ ማርያም
*አንቀጸ ብርሃን
*መልክአ ማርያም
*መልክአ ኢየሱስ
*ንባብ
*ዳዊት
*ውዳሴ ማርያም ዜማ
••••
@mahtot2 ላይ  ይፃፉልን

ይደውሉልን
+15092943369
+15095058383
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

10 Feb, 14:48


አልድን ያለ የሀገራችን በሽታ
፩) ዘረኝነት
፪) ድኅነት(ኅ ጠብቆ ይነበብ)
፫) ኃጢአት


ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

09 Feb, 18:49


አንተ ትፆማለህ ሰይጣን ግን አይበላም. አንተ በብርቱ ትደክማለህ ሰይጣን ግን አይተኛም ሰይጣንን ልትበልጠው የምትችለው ብቸኛ መንገድ ትህትና ሲኖርህ ነው, ሰይጣን ምንም አይነት ትህትና የለውምና.

ቅዱስ ሙሴ ጸሊም

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

09 Feb, 11:45


አንብበው በሀሳቡ ከተስማሙ እና አብረውን ሊያገለግሉ ፈቃደኛ ከሆኑ ከታች ባለው የቴሌግራም ሊንክ ወደ ግሩፑ ይቀላቀሉ ያግዙን አብረን እናገልግል


፩) እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳም የምሕረት የይቅርታ የድኅነት የፈውስ ቦታ መሆኑን ለዓለም ማሳወቅ የገዳሙን ታሪክ ለህትመት ማብቃት እና ለህዝብ እንዲደርስ ማድረግ
፪) በዓለም የሚገኙ ክርስቲያኖች ከተያዙበት የነፍስ የሥጋ ህመም እንዲድኑ ማድረግ
፫) ይህን ቅዱስ ሥፍራ ለህሙማን ምቹ ማድረግ ምሳሌ :-እንግዳ መቀበያ አዳራሽ መስራት፣ፀበል ቦታውን ሰፋ አድርጎ መስራት ፣ዋሻዎቹን ለጸበለተኞች ምቹ ማድረግ ፣መጸዳጃ ቤት ማሰራት  ፣ወዘተ
፬) የቅዳሴ ፣የቅኔ ፣የድጓ ፣የአቋቋም ፣የመጽሐፍት መምህራን በቦታው መቅጠር

ሕንጻውን የሚሰራው ብር እና ሰው ነው።
ህንፃ ሰብእን(ሰውን)የሚሠራው ግን ክርስቶሳዊ ትምህርት ነው።
በኦርቶዶክሳዊ አስተሳስብ የተቀረጸ ሰው በድንኳንም ቢሆን መቁረቡ ማስቀደሱ አይቀርም።
በኦርቶዶክሳዊ አስተሳስብ ያልተቀረጸ ሰው ግን በትልልቅ ካቴድራሎችም ቢሆን ስንኳን ሊቆርብበት አያስቀድስበትም።
የሚበዛው ሰው እየደከመ ያለው የቱ ላይ ነው?
ብዙዎች መዋዕለ ንዋይ እየፈሰሰ ያለው የቱ ላይ ነው?
፭) ከገዳሙ የወጡትን መነኮሳት መመለስ የተግባር ሥራ  እንዲሰሩ ማድረግ ለምሳሌ:-ሻማ ፣ጧፍ ማምረት ፣የእደጥበብ ሥራ ማስፋፋት(ሽመና ፣ሹራብ ፣ፎጣ )ወዘተ እንዲሰሩ ማድረግ
፭)በአቅራቢያው በሚገኘው የወረዳ ከተማ የተገዛውን የገዳሙ ቦታ ግንባታ ማስጀመር እና ከፍጻሜ ማድረስ
፮) አጠቃላይ በዚህ ግሩፕ የሚገኝ የመድኃኔዓለም ማኅበረተኛ አባል ሆኖ በስሙ በወር አንድ ቀን በOnline ስብሰባ ማድረግ
፯) ለገዳሙ የአገልግሎት ጊዜያት  በጎደለው ሁሉ በሚችለው አቅም አፋጣኝ ምላሽ መስጠት ሀሳብ ማካፈል፣ለዚህ ታላቅ አገልግሎት ሌሎችም በረከቱን እንዲወስዱ መጋበዝ
፰) የራሱ የገዳሙ ጉዞ ማኅበር እንዲኖር ማስቻል
፱) በገዳሙ የሚገኙ ህሙማንን ማልበስ ፣መመገብ በሚያስፈልጋቸው ሁሉ እገዛ ማድረግ
🚶‍♂ሕንጻ ቤተ ክረስቲያን መሥራት ጥሩ ቢሆንም ሰው ከመሥራት ግን አይበልጥም።
፲) ገዳሙ በጎርፍ ምክንያት ያጣቸውን አፀዶች ወይም እጸዋቶች መልሶ መተካት
፲፩)የገዳሙ ማንኛውም ገቢ ከዚህ ግሩፕ ሀሳብና እውቅና ውጪ እንዳይንቀሳቀስ ማድረግ ወጪ ገቢውን በምን ዓለማ ላይ እንደዋለ ቁጥጥር ማድረግ
፲፪)ማንኛውም ወደ ገዳሙ ጉዞ ማስጓዝ የፈለገ ከዚህ ማኅበር እውቅና ውጪ እንዳይሆን ማድረግ
፲፫)አንድ ምዕመን ለአንድ ካህን በማለት በገዳሙ የሚገኙ ካህናት ደመወዝ እንዳይቸገሩ   አገልግሎታቸውን ያለምንም ጥያቄ እንዲያገለግሉ ማስቻል።
፲፬) የአብነት ት/ቤቱን ማጠናከር
፲፭)ወደ ገዳሙ መውረጃ መንገዱን ማሰራት
፲፮)  ለዚህ ቅንነት በጎነትና መንፈሳዊ ዓላማ ያላቸውን በፈቃደኝነት ወደ ግሩፑ መጋበዝ እና የዓላማችን ተካፋይ እንዲሆኑ ማድረግ።
ሰው ዘመኑ ገብቶታል ሊባል የሚችል ሰው አቅሙ በፈቀደው ሁሉ ተተኪ ሰው ላይ እና ከትውልድ አደራ ላይ እየሠራ ከሆነ ነው።ሃይማኖቱን ከጠበቀ ነፍሱን ከጠበቀ ነው
ግሩፓችን ይህ  platform የሚሰራባቸው የዓለም ሀገራት የሚገኙ የተዋህዶ ልጆች ሁሉ ነው
https://t.me/EguaMedhanialem

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

09 Feb, 11:13


ገጠር ያለችው ቤተክርስቲያንም ከተማ ያለችውም ከተማያለውም በሳር የተሰራውም በእብነበረድ የታነጸውም በጭቃ የተገነባውም አንድ ነው ።ሁሉም የክርስቶስ ሥጋና ደም ይፈተትበታል
ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

09 Feb, 09:59


እዮብ እንዴት አደርክ ቢሉት
°በጤናም በሕመምም እያለ
°በማግኘትም በማጣትም ሆኖ
°ሚስቱ ከድታው ልጆቹ ሞተውበትም
°ዘመዶቹ ትተውት ሰውነቱ ተልቶና ቆስሎ
°በገል እያከከ መልሱ ግን••••••
እግዚአብሔር ይመስገን ነበር።

ዲያቆን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

08 Feb, 21:21


አንድ የመድኃኔዓለም ወዳጅ 5500 ብር በአቢሲንያ አካውንት  በማስገባት555638 .43 ብር  አድርሶታል እድሜ ከጤና ጋር ያድልልን ።
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን

ማስታወሻ = በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነበረው ብር ወደ አብሲንያ ስላዛወርነው በዚህ ያለው ሲቀንስ ቅር እንዳትሰኙ ለማለት እንወዳለን ( እንዳይሰማችሁ የትም አልሄደም አለ) ።

ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

08 Feb, 18:16


ይመስለናል እንጂ ሁሉም ጊዜያዊ ነው።

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

07 Feb, 15:26


አንዲት የመድኃኔዓለም ወዳጅ 100 ብር በአቢሲንያ አካውንት በማስገባት538,738 .43 ብር አድርሳዋለች እድሜ ከጤና ጋር ያድልልን መድኃኔዓለም ትምህርትሽን ይግለጽልሽ ።
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን

ማስታወሻ = በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነበረው ብር ወደ አብሲንያ ስላዛወርነው በዚህ ያለው ሲቀንስ ቅር እንዳትሰኙ ለማለት እንወዳለን ( እንዳይሰማችሁ የትም አልሄደም አለ) ።

ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

07 Feb, 11:11


በሕይወታችሁ ከባዱ ነገር አስመሳይ ሰውን ማወቅ ።
እኔ የምላችሁ መድኃኔዓለም ለፀሐይ እና ለኦክስጅን ቢያስከፍለን የምንከፍልበት ቢል ቢኖር ማን ይኖር ነበር ?ቸርነቱን ተመልከቱት ስለጤንነታችሁ አመስግኑት እስኪ ሆስፒታል ገብታችሁ የታመሙትን ጎብኟቸው ያን ጊዜ ለተንኮል ሳይሆን ለጤንነት ምን ያህል ዋጋ መክፈል እንዳለባችሁ ትረዳላችሁ።እውነት እላችኋለሁ የጤንነት ምስጢሩ ተመስገን ማለት ነው።የሰላም ምስጢሩ መጸለይ ብቻ ነው።
ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

07 Feb, 07:16


አንብበው በሀሳቡ ከተስማሙ እና አብረውን ሊያገለግሉ ፈቃደኛ ከሆኑ ከታች ባለው የቴሌግራም ሊንክ ወደ ግሩፑ ይቀላቀሉ ያግዙን አብረን እናገልግል


፩) እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳም የምሕረት የይቅርታ የድኅነት የፈውስ ቦታ መሆኑን ለዓለም ማሳወቅ የገዳሙን ታሪክ ለህትመት ማብቃት እና ለህዝብ እንዲደርስ ማድረግ
፪) በዓለም የሚገኙ ክርስቲያኖች ከተያዙበት የነፍስ የሥጋ ህመም እንዲድኑ ማድረግ
፫) ይህን ቅዱስ ሥፍራ ለህሙማን ምቹ ማድረግ ምሳሌ :-እንግዳ መቀበያ አዳራሽ መስራት፣ፀበል ቦታውን ሰፋ አድርጎ መስራት ፣ዋሻዎቹን ለጸበለተኞች ምቹ ማድረግ ፣መጸዳጃ ቤት ማሰራት  ፣ወዘተ
፬) የቅዳሴ ፣የቅኔ ፣የድጓ ፣የአቋቋም ፣የመጽሐፍት መምህራን በቦታው መቅጠር

ሕንጻውን የሚሰራው ብር እና ሰው ነው።
ህንፃ ሰብእን(ሰውን)የሚሠራው ግን ክርስቶሳዊ ትምህርት ነው።
በኦርቶዶክሳዊ አስተሳስብ የተቀረጸ ሰው በድንኳንም ቢሆን መቁረቡ ማስቀደሱ አይቀርም።
በኦርቶዶክሳዊ አስተሳስብ ያልተቀረጸ ሰው ግን በትልልቅ ካቴድራሎችም ቢሆን ስንኳን ሊቆርብበት አያስቀድስበትም።
የሚበዛው ሰው እየደከመ ያለው የቱ ላይ ነው?
ብዙዎች መዋዕለ ንዋይ እየፈሰሰ ያለው የቱ ላይ ነው?
፭) ከገዳሙ የወጡትን መነኮሳት መመለስ የተግባር ሥራ  እንዲሰሩ ማድረግ ለምሳሌ:-ሻማ ፣ጧፍ ማምረት ፣የእደጥበብ ሥራ ማስፋፋት(ሽመና ፣ሹራብ ፣ፎጣ )ወዘተ እንዲሰሩ ማድረግ
፭)በአቅራቢያው በሚገኘው የወረዳ ከተማ የተገዛውን የገዳሙ ቦታ ግንባታ ማስጀመር እና ከፍጻሜ ማድረስ
፮) አጠቃላይ በዚህ ግሩፕ የሚገኝ የመድኃኔዓለም ማኅበረተኛ አባል ሆኖ በስሙ በወር አንድ ቀን በOnline ስብሰባ ማድረግ
፯) ለገዳሙ የአገልግሎት ጊዜያት  በጎደለው ሁሉ በሚችለው አቅም አፋጣኝ ምላሽ መስጠት ሀሳብ ማካፈል፣ለዚህ ታላቅ አገልግሎት ሌሎችም በረከቱን እንዲወስዱ መጋበዝ
፰) የራሱ የገዳሙ ጉዞ ማኅበር እንዲኖር ማስቻል
፱) በገዳሙ የሚገኙ ህሙማንን ማልበስ ፣መመገብ በሚያስፈልጋቸው ሁሉ እገዛ ማድረግ
🚶‍♂ሕንጻ ቤተ ክረስቲያን መሥራት ጥሩ ቢሆንም ሰው ከመሥራት ግን አይበልጥም።
፲) ገዳሙ በጎርፍ ምክንያት ያጣቸውን አፀዶች ወይም እጸዋቶች መልሶ መተካት
፲፩)የገዳሙ ማንኛውም ገቢ ከዚህ ግሩፕ ሀሳብና እውቅና ውጪ እንዳይንቀሳቀስ ማድረግ ወጪ ገቢውን በምን ዓለማ ላይ እንደዋለ ቁጥጥር ማድረግ
፲፪)ማንኛውም ወደ ገዳሙ ጉዞ ማስጓዝ የፈለገ ከዚህ ማኅበር እውቅና ውጪ እንዳይሆን ማድረግ
፲፫)አንድ ምዕመን ለአንድ ካህን በማለት በገዳሙ የሚገኙ ካህናት ደመወዝ እንዳይቸገሩ   አገልግሎታቸውን ያለምንም ጥያቄ እንዲያገለግሉ ማስቻል።
፲፬) የአብነት ት/ቤቱን ማጠናከር
፲፭)ወደ ገዳሙ መውረጃ መንገዱን ማሰራት
፲፮)  ለዚህ ቅንነት በጎነትና መንፈሳዊ ዓላማ ያላቸውን በፈቃደኝነት ወደ ግሩፑ መጋበዝ እና የዓላማችን ተካፋይ እንዲሆኑ ማድረግ።
ሰው ዘመኑ ገብቶታል ሊባል የሚችለው ሰው አቅሙ በፈቀደው ሁሉ ተተኪ ሰው ላይ እና ከትውልድ አደራ ላይ እየሠራ ከሆነ ነው።ሃይማኖቱን ከጠበቀ ነፍሱን ከጠበቀ ነው
ግሩፓችን ይህ  platform የሚሰራባቸው የዓለም ሀገራት የሚገኙ የተዋህዶ ልጆች ሁሉ ነው
https://t.me/EguaMedhanialem

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Feb, 17:25


100 እና3000 ብር  አስገብተዋል ።
እድሜ ይስጥልን እግዚአብሔር በረከትን ያድልልን
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን

ማስታወሻ = በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነበረው ብር ወደ አብሲንያ ስላዛወርነው በዚህ ያለው ሲቀንስ ቅር እንዳትሰኙ ለማለት እንወዳለን ( እንዳይሰማችሁ የትም አልሄደም አለ) ።

ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Feb, 15:53


የኔታ አክሊሉ የዘብር ገብርኤል ስማቸው በእመጓ መጽሐፍ ላይ የተጠቀሰው እኒህ ነበሩ። ለ107 ዓመታት በትጋት በትልቁ ዩንቨርስቲ በዘብር ቅዱስ ገብርኤል ወንበር ዘርግተው የአቋቋሙ የድጓው ሊቅ በዚህ ሲያስተምሩ ነበር።

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Feb, 08:56


~Some practices that may help you find inner peace include: Meditation, Practicing self-care, Cultivating a positive mindset, Developing love for yourself, and Living in the present. 

~"You cannot find peace by avoiding life". 
"Peace is not something you wish for, it is something you make". 
~"You find peace not by rearranging the circumstances of your life, but by realizing who you are at the deepest level". 
~"Peace is its own reward". 
"Do not let the behavior of others destroy your inner peace". 
~"You will find peace not by trying to escape your problems, but by confronting them courageously
.

ውስጣዊ ሰላም እንድታገኝ ሊረዱህ የሚችሉ አንዳንድ ልምምዶች፦ ማሰላሰል፣ ራስን መቻልን መለማመድ፣ አዎንታዊ አስተሳሰብን ማዳበር፣ ለራስህ ፍቅርን ማዳበር እና በአሁኑ ጊዜ መኖር።  "ህይወትን በማስወገድ ሰላም ማግኘት አይቻልም"  "ሰላም የምትመኘው ሳይሆን የምትሰራው ነው።"  "ሰላም የምታገኘው የህይወትህን ሁኔታዎች በማስተካከል ሳይሆን በጥልቅ ደረጃ ላይ ያለህ ማንነትህን በመገንዘብ ነው።"  "ሰላም የራሱ ሽልማት ነው"  "የሌሎች ባህሪ ውስጣዊ ሰላምህን እንዲያጠፋ አትፍቀድ"  "ሰላም ታገኛላችሁ ከችግራችሁ ለማምለጥ በመሞከር ሳይሆን በድፍረት በመጋፈጥ ነው።

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

05 Feb, 16:02


ውጪ ለምትገኙ ብቻ  በOnline መማር ለምትፈልጉ

*የዘወትር ጸሎት
*ውዳሴ ማርያም
*አንቀጸ ብርሃን
*መልክአ ማርያም
*መልክአ ኢየሱስ
*ንባብ
*ዳዊት
*ውዳሴ ማርያም ዜማ
••••
@mahtot2 ላይ  ይፃፉልን

ይደውሉልን
+15092943369
+15095058383
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

05 Feb, 04:10


እኒህ ወንድሞቻችን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳን መላእክትና ሰዎችን ታመልካለች የሚለውን ፕሮቴስታንታዊ የድር ምሽግ እንዲሁ ደግሞ በእስልምናም በኩል የነበሩ ስህተታዊ አስተምህሮዎችን ሲበጣጥሱ እየተመለከትን ነው ።ቀርበን ብናግዛቸው የተሻለ ይሆናል ።ብናወግዛቸው ግን ሌሎች ክርስቲያኖችን እንዳያነቡ እያበረታታን ነው ።
ወንድሞች በጎ ሲሠሩ እናበርታ፡፡ሲስቱ እንክርዳድ ከስንዴ እየለየን በፍቅር እናርም፡፡አልታረምም የሚል ካለ ደግሞ በቤክርስቲያን በአግባቡ ይዳኛል ።እንደ ግለሰብእ እኔ ነኝ መምህሩ ማለት ግን የስሕተት ስሕተት ነው፡፡

ሌሎች ጥሩ መምህራን ሊቃውንት ወንድሞችም አሉ፡፡ እነሱን ለማምጣት እነዚህን መደገፍ መልካም ነው
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Feb, 16:03


እነዚህ ወሮበላዎች ኦርቶዶክስ መስለዋችሁ የምትከተሏቸው ወይም ቁጭ ብላችሁ የምታደምጧቸው ኦርቶዶክስ አይደሉም ተጠንቀቁ የበግ ለምድ የለበሱ ቀበሮዎች ናቸው።
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Feb, 03:11


በፓኪስታን ሀገር " እስልምና ላይ ተሳልቀዋል " በሚል የተከሰሱ  4 ሰዎች የሞት ፍርድ ተላለፈባቸው።
4ቱ ሰዎች " ቅዱስ ቁርዓንን ጨምሮ የእስልምናን ዕምነት እሴቶችን ጎድተዋል " በሚል ነው የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው።

መረጃው የአል አይን ኒውስ / አል አረቢያ ነው።


በእኛ ሃገርስ ጥምቀት ላይ በታቦት በመስቀል እና በድንግል ማርያም የተሳለቁትስ ይሙቱ ባንልም ከሞት የተለየ ተመጣጣኝ ቅጣት እንዴት አይፈጸምባቸውም ??

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

02 Feb, 15:26


ጎንደር አዘዞ ሎዛ ማርያም በጣም ብዙ አስተያየቶች እየደረሱኝ ነው።
የዚህ ዘመን ወጣቶች ወደ ቤተክርስቲያን እየመጡ ነው ?አዎ እውነት ነው ግን እየተማሩ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን እያወቁ ትህትናን እየተለማመዱ ቢሆን መልካም ነው ።በጎነት ከመንፈሳዊ ቅናት የተነሳ ሥርዓት ለማስከበር ውርውር የሚሉ ወጣቶች እነሱም ስርዓት ማክበር አለባቸው አሐዱ አብ ሲባል የሚያወሩ ቅዳሴ ሲቀደስ የሚሯሯጡ በየአድባራቱ እያየን ነው።አንዳንዶቹም ሲነገራቸው ምን ችግር አለው የሚሉ አሉ ችግርማ በደንብ አለው። ጥንቸል ከመሬት ጋር ማኅበር ገባች አሉ ጥንቸል መሬትን አንቺ መጀመሪያ ደግሽ እኔ ደግሞ በቀጣይ ጊዜ እደግሳለሁ አለች መሬት የደገሰችውን ከበላች በኋላ አመልጣለሁ ብላ አስባ መሆኑ ነው ሮጣ ከመሬት የት እንደምትደርስ ባይታወቅም ምን ለማለት ፈልጌ ነው እኛ ከአባቶቻችን አንበልጥም ይህ ጊዜ በቅድስና እነሱ ከነበሩበት በጭራሽ አይበልጥም አንድ ጊዜ ተሰንዳ የተሰራች የራሷ መሰረትም ሥርዓትም ያላት ቤተ ክርስቲያን እኛ ለማፍረስ ብንሞክር መሐል አናታችን ነው የሚፈርሰው ነገሮች በስርዓት ቢከወኑ መልካም ነው ።በሥርዓት ማስከበር ስም የሚመጡ ዘፈን መሰል መዝሙር ዝላይ መሰል ከበሮ አመታት ቢቀር የተሻለ ነው ጎንደር አዘዞ ማርያም እጅግ የምታምር ብዙ ታላላቅ አባቶች ያሉባት የአርምሞ የጸጥታ ቅዱስ ስፍራ ናት ።ለአስተርእዮ ማርያም የተደረገው ግን ለሚመጣው ዓመት በዚህ ሁኔታ ባታደርጉት ሥርዓት ቢኖር መልካም ነው ባይ ነኝ።ስርዓት ማክበር በረከቱ ለእኛ ነው። የሚጠቅመን እኛን ነው ።
ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

02 Feb, 07:15


ከሁለት ዓመት በኋላ ከባለቤቷ አስተዋወቀችኝ ባለቤቷም  ከአንድ ወንዝ ሆነና ትሁት አይገልጸውም ስልክ ደውሎ ባይመቸኝ ባልመልስ እንኳን ይቅርታ የሚጠይቀው እሱ ነው በእውነት የሚያስቀና ትዳር እግዚአብሔር ፍጻሚያችሁን ያሳምረው በዛሬው ዕለት ለዓመታዊ ክብረ በዓሉ እንዲደርስ ከወዲሁ ለገዳሙ  ለአገልግሎት የሚሆን ሶላር ከእነ ሙሉ የአገልግሎት  እቃው ሳውንድ ሲስተም ከእነ ማይክራፎን በመግዛት ገጥመው ሊያስረክቡ በዛውም በረከትን ሊቀበሉ ወደ ገዳሙ እየተጓዙ ነው በሰላም ግቡ  በሉልኝ እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ያድርጋችሁ በሞገስ በክብር ያኑራችሁ ያላሰባችሁትን በረከት ያድላችሁ።
ከልብ አመሰግናለሁ ።🙏🙏

ዲ/ን ኤርምያስ
0912494703
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

02 Feb, 06:49


የማያውቁኝ የማላውቃቸው ባለትዳሮች

መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ተፈጠርን ኤፌ ፪÷፲
አንተ ሰው በወጣትነትህ ዘመን ፈጣሪህን አስብ ።በመልካም ምግባርና በሙያ ብልሃት የምትተጋ ከሆንክ፣ ኑሮህ ይደላል፣ ሕይወትህ ይጣፍጣል፤ ያስደስታል። “ ፈጣሪ ያዘዘውን ምሳሌም ትሆናለህ”።ሰው፣ በሁለቱ አማራጮች፣ ወደ ከፍታው ወይም ወደ ዝቅታው፣ በተቃናው ወይም በጠመመው መንገድ መሄድ እንደሚችል፣  ባለ ብዙ ገፅ ፍጥረት ነው።  አእምሮው፣ አካሉ፣ መንፈሱ፣…. ሃሳቡ፣ ተግባሩ፣ ስሜቱ….የሰው ማንነት፣ ማለት አላማው ብቻ ሳይሆን ጥረቱም ነው። የስራ ውጤቱ ብቻ ሳይሆን፣ የሙያ ብቃቱም ነው። የእውቀቱና የስነምግባር መርሁ ብቻ ሳይሆን፣ የሰብዕና ንፅህናውና ፅናቱም ነው።ዛሬ የማስተዋውቃችሁ የማያውቁኝ የማላውቃቸው ባለትዳሮች ለሃይማኖታቸው በጎ አድራጊ ለእምነታቸው ታዛዥ በአጠቃላይ ከእነቤተሰቡ የንግግር ምልልሳችን እንኳን ፍጹም ትህትና የተመላበት ያልተፃፈ መጽሐፍ የሆኑ አንድ ቤተሰብ ነው።ሰይፈ ገብርኤል ይባላል በስልክ ነው የማውቀው በእርግጥ በስልክም ቢሆን ለመጀመሪያ ወደ ስልኬ የመጣው የባለቤቱ ስልክ ጥሪ ነበር እኅተገብርኤል ትባላለች ከአንድ ወንዝ ይቀዳል ብቻ ሳይሆን ከተግባርና ከትህትና ቤት እግዚአብሔር መርጦ ያገናኛል ማለት ይቀላል እኅተ ገብርኤል እኔን ሳታውቀኝ ያውም በሚዲያ እንዲህ እና እንደዛ ነኝ እየተባለ ሰው በሚዘረፍበት አጭበርባሪ በበዛበት በዚህ ዘመን የስልክ ጥሪዋን ስቀበል ጤና ይስጥልኝ ከበረከት እንድሳተፍ ይፈቀድልኝ የሚል ጥያቄ ነበር ያቀረበችልኝ ተገኝቶ ነው የሚል ምላሽ ከሰጠሁ በኋላ ለእጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳም ትላልቅ የአገልግሎት መጽሐፍትን ገዝታ በሞተር ሳይክል ላከችልኝ

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

01 Feb, 18:36


የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ለእጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳም ይህን መሳይ ድንኳን የሚያሰፋልን ወይም የሚገዛልን እንፈልጋለን ።እግዚአብሔር የፈቀደላችሁ
በረከቱን ይኸው ይድረሳችሁ ብለናል ።
@mahtot2
0912494703
ሼር ሼር ሼር
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

01 Feb, 17:56


ሠሪውን አክብሩት

ሰው ከንቱነቱን አይዘንጋ የሚከረፋ ጭቃ ነው።ከሞተ ከትንሽ ደቂቃዎች በኋላ ሽታው አላስቀምጥ ስለሚል ይታጠባል ይቀበራል። ።ትንሽ በበላ እና ስፖርት በሰራ ጊዜ ክንዱን ቢያሳብጥ ፣የተቅለሰለሰ ፀጉሯን በተተኮሰች ጊዜ ከእሷ በላይ ውብ የሌለ እስኪመስላት መሬት አትንካኝ የምትል  100ኪሎ ቢሆን/ብትሆን 100ኪሎ አፈር ነው/ነች።ኢሳይያስም እንዲህ አለ። “እስትንፋሱ በአፍንጫው ውስጥ ያለበትን ሰው ተዉት፤ እርሱ ስለ ምን ይቈጠራል?”ኢሳ2፥22
"ጥበብ ይሉሃል እውቀት ይሉሃል እግዚአብሔርን መፍራት ነው"እኛ የሠሪው ዕቃ ነን።
ለእርቃን ሩብ ጉዳይ የሆናችሁ ተመለሱ።

ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

01 Feb, 16:23


100 እና 2000 ብር አስገብተዋል ።
እድሜ ይስጥልን እግዚአብሔር በረከትን ያድልልን
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን

ማስታወሻ = በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነበረው ብር ወደ አብሲንያ ስላዛወርነው በዚህ ያለው ሲቀንስ ቅር እንዳትሰኙ ለማለት እንወዳለን ( እንዳይሰማችሁ) ።

ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

31 Jan, 08:39


ስምህን የሚያወድሱ ሁሉ በአንተ ይመካሉ መዝ ፭÷፲፩

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

31 Jan, 07:13


ሰው በሃይማኖት ውስጥ የራሱና የሚያነበው መጽሐፍ ድምር ነው

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

31 Jan, 02:56


ውጪ ለምትገኙ ብቻ  በOnline መማር ለምትፈልጉ

*የዘወትር ጸሎት
*ውዳሴ ማርያም
*አንቀጸ ብርሃን
*መልክአ ማርያም
*መልክአ ኢየሱስ
*ንባብ
*ዳዊት
*ውዳሴ ማርያም ዜማ
••••
@mahtot2 ላይ  ይፃፉልን

ይደውሉልን
+15092943369
+15095058383
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

29 Jan, 14:38


(3ኛ) በየትኛውም መመገቢያ ስፍራ እና መጠጥ ቤት የምትጠጡትን በብርጭቆም ይሁን በጠርሙስ ያለ መጠጥ ክፍት ጥላችሁ አትሂዱ፡፡ የተከፈተ መጠጥ ከሚያቀርብላችሁ ወየም ከሚጋብዛችሁ እንግዳ ሰው ራሳችሁን ጠብቁ፡፡ይህ ዱቄት የተነሰነሰበት ፈሳሽ መጠጣት በተለይ ዶዙ ከፍ ያለ ከሆነ እስከሞት ሊያደርሳችሁ ይችላል፡፡ አለያም ለረጅም ሰዓት(እስከ24 ሰዓት) አፍዝዞ ስለሚያስተኛ እናንተ የምትነቁት ሁሉ ነገር ካለቀና ከደቀቀ በኋላ ይሆናል ማለት ነው፡፡

በተለይ አዘውትራችሁ ናይት ክለብ የምትወጡ ሰዎች በጣም ተጠንቀቁ፡፡ ብቻችሁን መኪና ከያዛችሁ የሚከተላችሁ ይኖራል፡፡ በአነድ መኪና ሆናችሁ ብትወጡ ይመረጣልሸ፡ ምክንያቱም የመኪናችሁ በር እጀታ በዚህ ዱቄት ከተነካ በሩን ስትከፍቱ ንጥረነገሩ በቆዳችሁ ይገባና ወዲያው ወንጀለኞቹ ከናንተ ጋር ተሳፍረው እናንተ እየነዳችሁ የትም ይዘዋችሁ ሊሄዱ ወይም ወደራሳችሁ ቤት ወይም ሱቅ ራሳችሁ እየነዳችሁ ወስዳችኋቸው የፈለጉትን ዘርፈው ለመሰወር ያስችላቸዋል፡፡

እዚህ ሃገር ብዙ ጊዜ ወንጀሉ የሚፈጸመው አብያተ ክርስቲያናት አካባቢ መሆኑን ከአቤቱታዎች ተገንዝቤያለሁ፡፡ እህቴ ቦሌ መድሃኔአለም ተሳልማ ስትመለስ ነጠላ እንደለበሰች ነው ሁሉ ነገሯን አጥታ ራሷን መስቀል ፍላወር ያገኘቸው፡፡ እናቴም ከእስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ስትመለስ ነበር በታክሲ ወስደው የዘረፏት፡፡ ቅድም አንዲት ወጣት ቲክቶክ ላይ ከኪዳነምህረት ስመለስ ሚሊኒየም አካባቢ አግኝተውኝ 28ሺህ በር ከባንክ አስወጥተው ዘረፉኝ ስትል ሰምቻታለሁ፡፡ ብዙ ጉዳት ደረሰብን የሚሉ ሰዎች ከመንፈሳዊ ሰፍራ ሲመለሱ በነዚህ ሰይጣኖች እየተጠመዱ ነው መሰለኝ ፡፡

ቀናችንን ለእግዚአብሄር ሰጥተን መውጣት ዋናው ነገር ነው፡፡ ያም ሆኖ የራስን ጥንቃቄ ማድረግ ደግሞ አምላክን “ምን በደልኩህ” ብሎ ከመሟገት ያድነናል፡፡ እናንተም ማንነታቸውን ስለማታስታውሷቸው፣ ፖሊስም ዳናውን ማግኘት ስለሚቸግረው ወንጀል ፈጻሚዎችን መያዝ አስቸጋሪ ነው፡፡ “ጥንቃቄ ይጠብቃል፣ ማስተዋልም ይጋርዳል” እንዲል ቅዱስ መጽሃፉ! በነገር ሁሉ እየተጠነቀቅን ፣ በጉዟችንም እያስተዋልን ይሁን ፡፡

ማሳሰቢያ! …ስለዚህ ዱቄት አውቃለሁ የሚል ማንም ሰው እዚህ ፖስት ስር የንጥረነገሩን ስምና ተያያዠ መረጃዎች ቢጽፍ ወንጀል እያስተማረ መሆኑን ፣ ለዚህም ተጠያቂ እንደሚሆን አስቀድሞ ይወቀው፡፡

መላኩ ብርሃኑ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

29 Jan, 14:38


“አፍዝ አደንግዝ ወንጀል” አለ?

ይህ ጽሁፍ ረዘም ቢልም በጣም ይጠቅማችኋል፡፡

ነገርየው በተለምዶ “አፍዝ አደንግዝ” ተብሎ ይጠራል፡፡ ሰዎች በገዛ ፍቃዳቸው በእጃቸው ያለ ወርቅ ይሁን ሞባይል፣ ብር ይሁን መን ሳይቀራቸው ያለ የሌለ ንብረታቸውንና ያም ሳይበቃ በባንክ ያለ ገንዘባቸውን በኤቲኤም አውጥተው ለሌቦች ያስረክቡና ጥቂት ቆይተው ሲነቁ ራሳቸውን ያልጠበቁበት ስፍራ ላይ ያገኙታል፡፡ ፖሊስ ጋር ሄደው ያመለክታሉ፡፡ ወይም ቲክቶክና ዩቲቱብ ላይ መጥተው "እንዲህ እንዲህ ሆኖ ይህ ወንጀል ተፈጸመብኝ" ይላሉ፡፡ ወንጀል የተፈጸመባቸው መሆኑ ባያጠራጥርም ‘ገና ሲነካኝ ፈዘዝኩ ፣ደነዘዝኩ፣ ከዚያ በኋላ የሆነውን አላስታውስም’ የሚሉትን ነገር ግን ብዙም ሰው አያምናቸውም፡፡

እኔም አንድ ወቅት የገዛ እህቴ እና እናቴ በተለያየ ጊዜ የዚህ ወንጀል ሰለባ ሲሆኑ ያሉትን ማመን ቸግሮኝ ነበር፡፡ እናቴ 'የልጄ ማስታወሻ' የምትለውን የወርቅ ቀለበትና ቦርሳዋ ውስጥ የነበረ ገንዘቧን ፣ እህቴ ደግሞ ሞባይልና ባንክ የነበረ ብሯን በተለያየ ጊዜ ለሌቦች አስረክበው ‘ያደረግነውን ሁሉ አናውቅም ነበር፣ ስንነቃ ራሳችንን ያልጠበቅነው ቦታ አገኘነው’ ብለው የነገሩኝን ታሪክ በሙሉ ልቤ ለመቀበል ተቸግሬ ነበር፡፡

በቅርብ እስከማውቀው ድረስ ፖሊስም በርካታ ይህንን መሰል አቤቱታዎች የቀረቡለት ቢሆንም በዚህ መንገድ የተፈጸመንና ፈጻሚውን ለማወቅ የሚያስቸግርን ወንጀል ለማጣራት አዳጋች ይሆንበታል፡፡ ማስረጃና ማረጋገጫ ስለማያገኝም አንዳንዴ ‘በዚህ ሁኔታ የሚፈጸም ወንጀል አለ’ ብሎ ለመቀበል ይቸገራል፡፡ ወንጀሉን “ማታለልና ማጭበርበር” በሚለው ርዕስ ላይ ብቻ መዝግቦ ያልፈዋል፡፡ በዚህ ሳቢያ ወንጀለኞቹ አይያዙም፡፡ተጎጂዎችም ሁሌም ስጉ ሆነው ይቀራሉ፡፡ አንዳንዶች ስለማይተማመኑ ተዘረፍን ባሉት ንብረት ሳቢያ ከትዳር አጋራቸውና ከቤተሰባቸው ተጣልተው ቀርተዋል፡፡ በዚህ መሃል ሌሎች ዜጎች በተራ በተራ የወንጀል ሰለባ እየሆኑ ይመጣሉ፡፡ በቀላል አማርኛ ከተማችን ውስጥ እየሆነ ያለው ነገር ይኸው ነው፡፡

እውን ግን “አፍዝ አደንግዝ" አለ?

ዛሬ የምነግራችሁ ብዙዎች “ሃሳብ የፈጠረው ቅዠት” ስለሚሉትና መኖሩን ስለማይቀበሉት (መሪጌታ ነን ባይ ሃሳዊዎችን ጥንቆላ ተዉትና) በተለምዶ ‘አፍዝ አደንግዝ’ ተብሎ ስለሚጠራው ንጥረ ነገር ነው፡፡ ‘አፍዝ አደንግዝን’ ብዙዎች ለወንጀል ተግባር መገልገያነት እያዋሉት መሆኑን ከበርካታ አቤቱታዎች ማረጋገጥ ችያለሁ፡፡ ይህንን ነገር ስጽፍ ዝርዝር ጉዳይ ውስጥ ገብቼ መረጃውን አንዳንድ ዋልጌዎች ለመጥፎ ተግባር እንዳይጠቀሙበትና ለጥፋት እንዳያውሉት እየተጠነቀቅኩ በመሆኑ ፣ እየሸፋፈንኩ ባለፍኳቸው ነገሮች ቅር እንዳትሰኙ፡፡ ለጥንቃቄ የሚሆናችሁን ብቻ እነግራችኋለሁ፡፡ The devil is in the detail እንዲል ፈረንጅ ዝርዝሩ የሚያስከትለው ውጤት በጣም አደገኛ ነውና እለፉት፡፡


ነገርየው ዱቄት ነው፡፡ የሚገኘው ከአንድ ተክል ነው፡፡ ይህ ተክል በሃገራችን በበርካታ አካባቢዎች ፣ በከተማችንም ብዙ ቦታ በተለይ ወንዝ ዳር አካባቢ በቅሎ ይገኛል፡፡ በልጅነታችን እቃቃ ስንጫወትበት ስላደግን ፣ እናቶቻችንም ለአንዳንድ የቆዳ ችግሮች እንደመድሃኒት ስለሚጠቀሙበት እኔ በደንብ አውቀዋለሁ፡፡ አሁንም ብዙ ሰፈሮች ውስጥ አየዋለሁ፡፡

ሳይንስ “የምድራችን እጅግ አስፈሪው ተክል” ብሎ ይጠራዋል፡፡ በብዙ ሃገራት “የዲያቢሎስ ትንፋሽ” የሚል ስም ተሰጥቶታል፡፡ እግዚአብሄር ጠብቆን እንጂ በልጅነታችን ፍሬውንና አበባውን እየተጫወትንበት አድገን ምንም ሳንሆን መትረፋችን ተዐምር ነው፡፡ (ስሙ ይቅር)

ከዚህ ተክል የሚመረትና በዱቄት መልክ የሚዘጋጅ 'xxxx' የሚባል ንጥረነገር አለ፡፡ ይህ xxxx ንጥረነገር በጣም በጥቂት ግራም ጆሮ ግንድ አካባቢ ቆዳ ላይ እንዲቀባ ተደርጎ ይዘጋጅና በትራንስፖርት ሲጓዙ ለሚያጥወለውላቸውና ለሚያስመልሳቸው ሰዎች በየፋርማሲው ይሸጣል፡፡ ከፍ ላለ ህመም ማስታገሻነት ደግሞ በሚቀባ እና በሚዋጥ መልኩም ይዘጋጃል፡፡ ከቀዶ ጥገና በኋላ የሚከሰት ማቅለሽለሽና ማስታወክን ለማስወገድም ይሰጣል፡፡ አደገኛ ማደንዘም ይሰራበታል፡፡ በሌላ በኩልም በማይድን በሽታ ተይዘው መሞት ለሚፈልጉ ሰዎች እንደየሃገሩ ህግ በሃኪም ለሚታገዝ የሞት ውሳኔ ማስፈጸሚያ መጠኑ ከፍ ተደርጎ ይዘጋጅና ይሰጣል፡፡ (አወሳሰዱ አሁንም ይቆየን)

በአጠቃላይ ይህ ዱቄት በቆዳ በመስረግ፣ በትንፋሽ በመሳብ እና በመጠጥና በምግብ ውስጥ በመግባት የሰውን ልጅ የማሰብ፣ የማሰላሰል እና የማመዛዘን አቅም ያሳጣል፡፡ዋናው አላማ ማደንዘዝና ምንም ነገር እንዳይሰማን ማድረግ ነው፡፡

የሃገራቱ ስም ይቅርና በአንዳንድ የሩቅ ምስራቅ እና የአውሮፓ ሃገራት በፋርማሲ ውስጥ ያለሃኪም ትዕዛዝ ይሸጣል፡፡ ስለዚህ በቀላሉ ይገኛል ማለት ነው፡፡ እስካሁን ብዙዎች ቢወተውቱም በዓለምአቀፍ ደረጃ ቁጥጥር ከማይደረግባቸው ድራጎች ተርታ እስካሁን አልወጣም፡፡ አሁን ዋናው ነገር “ይህንን ዱቄት ወንጀለኞች እንዴት ይጠቀሙበታል?” የሚለው ጥያቄ ነው፡፡ እሱን እንየው፡፡

ይህንን ንጥረነገር በመጠቀም በተለያዩ ሃገራት ወንጀል ይፈጸማል፡፡ ቀደም ባለው ጊዜ ልክ እንደኛ ሃገር ሁሉ አሜሪካ ጭምር እንዲህ ያለ ወንጀል ተፈጽሞ ተበዳይ አቤቱታ ሲያቀርብ ፖሊሶች “የከተማ ተረት ተረት ” ብለው ይቀልዱበት ነበር፡፡ የሚያሳዝነው ነገር ልክ እንደኔ እናትና እህት ተበዳዮች ወይ ሰው አያምናቸው፣ ወይ ንብረታቸው አይመለስላቸው ወይ ወንጀለኛው አይያዝላቸው ከሁሉ ያጡ ሆነው ስለሚቀሩ ፖሊስ ጋር መሄድም ለሰው ማውራትም ያቆማሉ፡፡

ሌላው ጥልቅ መረጃ ይቅርብንና እናንተ ብቻ ከዚህ በታች ከምዘረዝራቸው ሰዎች ራሳችሁን ጠብቁ!!

(1ኛ) በሆነ አጋጣሚ ካገኛችሁትና ያለምንም ምክንያት ከቀረባችሁ ዘናጭ ‘ጀንትል ማን’ ነኝ ባይ ሰው ቢዝነስ ካርድ አትቀበሉ፡፡ ይህንን አንብቡልኝ ብለው ብጣሽ ወረቀት ከሚሰጧችሁ አዛውንት መሳይ ወይም የገጠር ሰው መሳይ ሰዎች ወረቀቱን አትቀበሉ፡፡ “ሎተሪ ደርሶኛል እዩልኝ” ብለው ሎተሪውን ከሚያቀርቡላችሁ ሰዎችም እንዲሁ ሎተሪውን እንዳትቀበሉ፡፡ ምክንያቱም ይህ ዱቄት የተነሰነሰበት ማንኛውንም ወረቀት በእጃችሁ በነካችሁ በጥቂት ሰከንዶች ውስጥ በትንሹ ለ4 ሰዓት በሚቆይ ‘መነሁለል’ ውስጥ ትገባላችሁ፡፡ ነጻ ፍቃዳችሁን መቆጣጠር አትችሉም፡፡ የሚጠይቋችሁን ቀርቶ ያልተጠየቃችሁትን ሁሉ ታደርጋላችሁ፡፡ የወሰዷችሁ ቦታ ሁሉ ትሄዳላችሁ፡፡ በዚህ የተነሳ በእጅ ላለ ንብረት መወሰድ ወይም ቤት ድረስ በመሄድ ለከባድና ውድ ንብረቶች መዘረፍ፣ ለባንክ አካውንት መመዝበር፣ ሲከፋም ለመደፈርና ለአካል ብልቶች ዘረፋ ወንጀሎች ትጋለጣላችሁ፡፡ (እኛ ሃገር እስካሁን የተመዘገበው ሞባይል፣ወርቅና የባንክ ገንዘብ ስርቆት ነው )

(2ኛ) ከጸጉራችሁ ላይ ቆሻሻ ነገር ለማንሳት በሚል ሰበብ መሃረብ ወይም ሌላ ነገር ይዘው እጃቸውን ወደፊታችሁ ከሚያቀርቡ ሰዎች ፣ ወይም ፎቶግራፍ ወይም ስዕል መሳይ ነገር በእጃቸው ይዘው ወደፊታችሁ በማስጠጋት ከሚያሳዩዋችሁ ሰዎች ራሳችሁን ጠብቁ፡፡ ምክንያቱም የያዙት ነገር ላይ ያለውን ዱቄት በትንፋሻቸው ፊታችሁ ላይ ‘እፍፍ’ ሲሉት እናንተ ወደውስጥ ትስቡትና በቅጽበት ከላይ በተገለጸው መልክ ፈዝዛችሁና ደንግዛችሁ ራሳችሁን ትስታላችሁ፡፡ ያኔ የፈለጉትን ነገር እሺ ብላችሁ መፈጸም፣ አለያም ወደፈለጉት ቦታ መነዳት እጣችሁ ይሆናል፡፡

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

29 Jan, 10:07


@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

28 Jan, 18:14


   ጥር 21  በዓለ  አስተርእዮ 

       《የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት》
      

       እንኳን ለዚህች ታላቅ በዓሏ አደረሰን፡፡

      ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በስድሳ አራት አመቷ ከሞት ወደ ሕይወት ከመከራ ወደ ደስታ የተሸጋገረችበት ዕለት ነው፡፡

      ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ ያሬድም “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ” ትርጉሙ ሞት ለማናኛቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል፡፡ በማለት አደነቀ፡፡

     በመሆኑም በዓሉ የወላዲተ አምላክ በዓለ ዕረፍት ከመሆኑ የተነሳ ታላቅ በረከት የሚያስገኝ ስለሆነ በየዓመቱ ይከበራል፡፡

     ... የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉስድሳ አራት ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ ጥር 21 እሁድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላዕክቱን አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት፡፡

      ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁミ አለችው፡፡

      በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት፡፡ እኚህን ከማርክልኝስ ይሁን አለችው፡፡ ቅድስት ሥጋዋን ከቅስስት ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በዝማሬ መላእክት አሳረጋት፡፡

      ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት በደመና ጠቅሶ ካለችበት አድርሶ እመቤታችሁን ቅበሩ አላቸው፡፡ ባባ ይዘወት ወደ ጌሰማኒ ሲስደት አይተው ልጇን ተነሳ አረገ እያሉ ሲውኩን ይኖራሉ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች አረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለም ብሎ ኑ እናቃጥላት ተባባሉ፡፡

       ከመካከላቸው አንዱ ታውፋንያ ዘሎ ያልጋውን ሸንኮር ያዘ፡፡ የታዘዘው መላእክት መጥቶ በሰይፍ ሁለት እጁን ቀጣው፡፡ በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት ድኖለታል፡፡ ከዚህ ቦሃላ ዮሐንስን ጨምሮ ከመካከላቸው ነጥቆ በእጸ ሕይወት ሥር አኑሯታል፡፡

       አንድም በዓሉ-፡ እግዚአብሔር ወልድ በሰውነት ተወልዶና ማንነቱ በይፋ ታውቆ በተገለጠበት በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር የ#አስተርእዮ__ማርያም ተብሏል፡፡

      አስቀድመው አሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል ወደ ዓለም ሁሉ ተበትነው ነበርና በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ሁሉም ደመናን ጠቅሰው ወደ ኢየሩሳሌም መጡ፡፡ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ መርቶ አመጣቸው እንጂ ለምን እንደመጡ አያውቁም ነበር፡፡ እመቤታችንም ለምን እንደመጡ ጠየቀቻቸው፡፡

      ቅዱስ ጴጥሮስም፡- “ጸጋን የተመላሽ ቅድስት ሆይ! የመምጣታችን ምሥጢርማ እኛ አንቺን እንጠይቅ እንጂ አንቺም እኛን ትጠይቃለሽን? ሁላችንም ለምን እንደመጣን አናውቅም፡፡

     💟ለምሳሌ እኔ አስቀድሜ በአንጾክያ ነበርኩኝ አሁን ግን እነሆ እዚህ ነኝ፡፡ ለምን እንደመጣሁኝ ግን አላውቅም” አላት፡፡ እርሷም ሁሉም በአጠገቧ በተሰበሰቡ ጊዜ የሚሆነውን ነገር አስቀድማ ከልጇ ከወዳጇ አውቃ ተዘጋጅታ ነበርና ለምን እንደመጡ 《ዕረፍተ ሥጋዋን ለማየት እንደሆነ》ነገረቻቸው፡፡

     💟ሌሊቱንም በሙሉ በጸሎትና በማኅሌት ደግሞም በዝማሬ ሲያመሰግኑ አደሩ፡፡ ከዚህ በኋላ የተወደደችው እናት በረከቷን አሳድራባቸው በሰላም አንቀላፋች፡፡ ነፍሷም በዐብይ ዕልልታና በታላቅ ምስጋና በመላእክት እጅ ወደ አምላኳ ሄደች፡፡

     ኋላ ሐዋርያቱ ዮሐንስን ሲያገኙት፡- “እመቤታችን እንደምን ሆነች?” አሉት፡፡ እርሱም “በገነት በዕጸ ሕይወት ሥር ዐርፋለች” አላቸው፡፡

      የቀሩት ሐዋርያት “ዮሐንስ ያን ድንቅ የእግዚአብሔርን ሥራ አይቶ እኛስ ሳናይ እንዴት እንቀራለን?! አቤቱ ለእኛም ቸርነትህን አድርግልን” ብለው በነሐሴ መባቻ በአንድነት ሆነው ወደ ፈጣሪያቸው የሚቀርብ የአንድ ሳምንት ጾምና ጸሎት ጀመሩ፡፡

       በሁለተኛው ሱባዔ ማብቂያ ዕለት ነሐሴ 14 ቀን እሑድ የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ መልአኩ ከገነት አምጥቶ ለሐዋርያቱ ሰጣቸው፡፡

     እነርሱም ልመናቸው ስለ ተፈጸመላቸው ፈጣሪያቸውን በጸሎት አመስግነው በዚያችው ዕለተ እሑድ ቅዱስ ሥጋዋን ወስደው ቀብረውታል፡፡ እርሷም በሦስተኛው ቀን ነሐሴ 16 ቀን ማክሰኞ ተነሥታለች፡፡

     ትንሣኤዋ “ከመ ትንሣኤ ወልዳ- እንደ ልጇ ትንሣኤ” ያሰኘው ይህ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይታ የመነሣቷ እውነታ ነው፡፡

የአዛኚቱ ድንግል አማለጅነትና በረከት አይለየን አሜን ።

ወስብሓት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር አሜን
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

28 Jan, 13:42


https://youtu.be/MMvv5RvS3yU?si=Ehws0uQ5aRmmqyYi

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

27 Jan, 11:19


ሰውዬው ይህ ነው መረጃ በደንብ ላኩልኝ ቤተክርስቲያንንማ ማንም አይቀልድባትም


@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

27 Jan, 11:14


ይህን ስለጻፍኩ እንዴት እንደሚሳደብ ተመልከቱ ምስጢሩ ስለታወቀበት ከቤተክርስቲያን ራስ እስካልወረደ ድረስ ማን ይለቀዋል
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

27 Jan, 09:12


እርግማን ሲደርስ በቀጸላ አየን

ይህ ሰው መርጌታ ቀጸላ ይባላል :የቀሲስ መንግሥቱ ልጅ ፣የዚያ የቅኔ አዋቂው ሊቅ ወንድም ነው ፣በእርግጥ ቅኔው ላይ እሱ ብዙም ስላልነበረ ድሮም ከበሮ ብቻ ስለነበረ መጽሐፍትን አያውቅም አይመረምርም ፣የዚህ ሰው የእውነት ጴንጢ መሆን ብዙ አያስደንቅም ይሰክር ነበር መርጌቶችን ይደባደብ የነበረ ለጥር ጊዮርጊስ ከእሱ ውጪ ከበሮ ከተያዘ አልመታችሁትም ብሎ የሚበጠብጥ ፣እድሜ ልኩን ሰንበት ተማሪዎችን ወረብ አሰልጣኝ የነበረ ፈጽሞ ማንበብ የሚጠላ በስካሩ ምክንያት የክህነት ሚስቱን የፈታ እና የአንድ ወንድ ልጅና የብዙ ሴቶች ባል የሆነ ከጓጃም ከወጣ በኋላ ሐዋሳ ሲያጭበረብር የነበረ።የብዙ መምህራን እርግማን ያለበት፣አሁን ሻሹንም ካባውንም ሳያወልቅ ርትዕት ሃይማኖት የሚል ticktok ከፍቶ ሰውን የሚያጭበረብር ።ካባና የቤተክርስቲያን መገለጫዎችን ያስቀምጥልን ዘንድ እንጠይቃለን።
ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

26 Jan, 20:18


የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስድስተኛው ፓትርያርክ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ የሹመት በዓል ዛሬ ረፋድ ላይ በአሥመራ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተካሄዷል።

የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት እና እህትማማች ከሆኑ ከግብፅ፣ ከሩሲያ፣ ከግሪክ፣ ከአርመን፣ ከሶሪያ እና ከህንድ የተውጣጡ የውጭ ሀገር ልዑካን ተሳትፈዋል።

በተጨማሪም ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ፣ የመንግሥት ሚኒስትሮች፣ የዲፕሎማቲክ ቡድን አባላት፣ የሁሉም አህጉረ ስብከትና የዋና ዋና ገዳማት ተወካዮችና ምእመናን ተገኝተዋል።
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

11 Jan, 15:08


በዛሬው ዕለት 1800 ኢአማንያን ወደ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተመልሱ።
እግዚአብሔር ይመስገን።
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

11 Jan, 14:55


100ብር አስገብተዋል ።
እድሜ ይስጥልን እግዚአብሔር በረከትን ያድልልን
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

11 Jan, 03:02


በጣም መልካም ነው ሼር ይደረግ ከዚህ የበለጠ ጠንከር ያለ መልዕክትም እንጠብቃለን
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

09 Jan, 14:01


የምስራች ወደ እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳም ጉዞ ተዘጋጅቷል

ዙር አንድ
🗣መነሻ ጥር  25(እሁድ)
🗣መመለሻ 28(ረቡዕ)
ዙር ሁለት
መነሻ= ጥር 26(ሰኞ)
መመለሻ =ጥር 28(ረቡዕ)

🚃ርቀት 285 ኪሜ 
🚶‍♂የእግር መንገድ =የለም
🌥ዓየር ንብረት = ወይናደጋ
መነሻ  ቦታ=አዲስ አበባ
የትራንስፖርት ዋጋ ምግብን ጨምሮ 2,500ብር
በጉዟችን የምንሳለማቸው ሌሎች ገዳማት
    ጻድቃኔ ማርያም ፣ዘብር ገብርኤል ------
የምዝገባ ጊዜ=  ከዛሬ ጀምሮ

በዚህ ጉዞ እገዛ ማድረግ  የምትፈልጉ
   ለገዳሙ:-
፩) ገዳሙ በጎርፍ ምክንያት ያጣቸውን ዕፀዋት ለመመለስ ቅጠላቸው መስፋት የሚችሉ ዕጸዋት
፪) ምንጣፍ
፫) ጧፍ ፣እጣን ፣ሻማ
፬) ድንኳን ( ከተቻለ በግሩፕ በማኅበር ሆናችሁም ቢሆን ለቃል ኪዳን ታቦት ማደሪያ)
፭) የቤተ መቅደስ አልባሳትን  ለማጠብ የሚያገለግል ላርጎ (ሳሙና)
፮) ሙሉ ግቢውን ዲዛይን ለማሰራት የዲዛይን ባለሙያዎች እንፈልጋለን
፯) ሥዕለ አድኅኖ ማሳል ስለምንፈልግ መንፈሳዊ ሠዓሊያን የቦታውን ግምት ለማወቅ
፰)መንፈሳዊ የኮርስ መጽሐፎችን ለማስተማሪያ የሚሆኑ ለምሳሌ  አምስቱ አዕማደ ምስጢር ፣ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ፣ሰባቱ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን ፣ዓምደ ሃይማኖት ፣የቤተክርስቲያን ታሪክ ፣ነገረ ቅዱሳን ፣ክብረ ክህነት ፣የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ቁጥር ፩ &፪  ወዘተ
ለጸበለተኛ
፩)  የሚሆን አልባሳት
፪) ተንከባካቢ እና የሚመገቡት ለሌላቸው በሶ ፣ስኳር   ፣ ወዘተ

ማሳሰቢያ :- ማንኛውም የጤና እክል(ህመም) ያለባቸው ተጓዦች ጸበል 3 ቀን እንዲሞላቸው የእሁዱን ጉዞ ቢመርጡ መልካም ነው ።
ከተጓዥ የሚጠበቁ( የሚያስፈልጉ )  = የቀበሌ መታወቂያ ፣የፀበል ዕቃ ፣ንስሐ መግባት

መረጃ ከፈለጉ እና ለመመዝገብ  :
+251938947632
+251912494703
በቴሌግራም መልዕክት  @mahtot2 ይጻፉልን ።

ሼር ያድርጉ ለጓደኛዎት ይጋብዙ


በራሳቸው  መሄድ ለማይችሉ  ህመም ላይ ላሉ ከገዳሙ በረከት እንዲቀበሉ የትራንስፖርት በመሸፈን  አንዲት እህታችን ለአንድ ሰው እችላለሁ ብላለች ሌሎችም ካላችሁ በስልክ  አሳውቁን።

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

09 Jan, 03:38


ዛሬ ጥር ፩ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ልደቱና እረፍቱ ነው እንኳን አደረሳችሁ ።
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

07 Jan, 07:39


እመቤቴ ሆይ ሌሎች ሴቶች በወለዱ ጊዜ እንኳን ማርያም ማረቻችሁ እንላለን ሰማይ እና ምድርን የፈጠረውን የወለድሽ አንቺን ምን እንበልሽ🤔
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ፡፡
መልካም በዓል
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

07 Jan, 05:13


የአእላፋት ዝማሬ በኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለ ሥልጣን የቅጂና ተዛማጅ መብቶች ተመዘገበ።
ከዚህ በኋላ በዚህ ዓይነት ሲስተም ሌላ ቤተ እምነት መኮረጅም ማስመሰልም አከተመለት።
ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

07 Jan, 04:07


በተደጋጋሚ መልዕክት ለላካችሁልኝ  በአጭሩ :-
ምን እንዲሆን ነው የምትፈልጉት ?
እንዴት የአዕላፋት ዝማሬ ሰው እንደ ጎመን እየታጨደ ባለበት በዚህ ሰዓት ይህ ይሆናል ?።እሺ ምን ይሁን ?ከቤተክርስቲያንም እንቅር ማኅሌቱም ሰብሐተ እግዚአብሔርም ይቅር ይህ ሁሉ ሰው ዘፈን ዳንኪራ ጭፈራ መጠጥ ቤት ያምሽ? ትክክለኛ መሆን የሚገባው ይህ ነው የሀገራችን ችግር ከአዕላፍ ዝማሬ በመቅረት አብዝተን በመጠጣት አብዝተን በመብላት አልባሌ ቦታ በማደር በመዋል አንፈታውም ትልቁ ቁልፍ እንደዚህ እግዚአብሔርን ማመስገን ነው።ይህ ዝማሬ  በንጹህ ልብ ከሆነ እንኳን ጦርነት እንኳን ችግር  የእስር ቤት ቁልፍ ሰብሮ በግፍ የታሰሩትን  የሚያስፈታ ይመስለኛል።102  የምትደርሱ ወንድም እህቶች መልእክት የፃፋችሁልኝ መልሴ ጸልዩ ንስሐ ግቡ ሥጋወደሙን ተቀበሉ እንደዚህ እንደ መላእክት ስዘምሩ ዋሉ እደሩ ነው የምላችሁ ።
እንዲያውም ለሚቀጥለው ዓመት ሁሉም የአቋቋም የድጓ  መምህራን ከእነ ደቀመዝሙራቸው የቅዱስ ያሬድ ጥበብ በዜማ የሚያሳዩበት ቢሆን ብዬ እመኛለሁ።

~~ዲ/ን ኤርምያስ ~`

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Jan, 18:30


አንዲት ቤዛ የምትባል እህታችን 3000ብር አስገብታለች
እድሜ ይስጥልን እግዚአብሔር በረከትን ያድልሽ
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Jan, 15:08


https://youtu.be/ekED88bbBh8?si=a8BDvgTB1T57wbvM

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Jan, 15:01


አባትና ልጅ በአንድ ላይ ተጠመቁ ከፕሮታስታንት ወደ ኦርቶዶክስ የተመለሰው አባት በዛሬው ዕለት ከልጁ ጋር የሥላሴን ልጅነት አግኝቷል እግዚአብሔር ይመስገን።
~~ዲ/ን ኤርምያስ~~
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Jan, 11:57


አስቸኳይ መረጃ :-
ውድ ኦርቶዶክሳውያን ይህ ሰው መናፍቅ ነው በትክክል ተጠንቀቁ የንስሐ አባት ልሁናችሁ እያለ እህቶቻችን ወደማይገባ መስመር እየወሰደ፣ ከክብራቸውም እያስነወረ የሚገኝ ሰው ነው በተለይ ሐዋሳ የምትገኙ ተጠንቀቁ በተደደጋጋሚ video ሲላክልኝ ነበር ዛሬ ግን በትክክል አጣርቼ ነው ።"ሁሉን ትቼ ተከተልኩህ "የሚል የticktock አካውንት አለው።

የተለየ መረጃ ያላችሁ ላኩልኝ

ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Jan, 10:37


ፍቅርተ ማርያም የምትባል እህታችን ለእጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም 300ብር አስገብታለች
እድሜ ይስጥልን እግዚአብሔር በረከትን ያድልሽ
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Jan, 06:06


በዓለ ጥምቀት ወይም ልደት ረቡዕና ዓርብ ሳይውል ገሃድ አለ ይጾማል ወይ?

ገሃድ ምትክ ፣መገለጥ ማለት ነው በሰባት ዓመት አንድ ጊዜ ነው ረቡዕ ወይም ዓርብ የሚውለው ይሁን እንጂ እንዳይረሳ ሁልጊዜ እንጾመዋለን ።
ደግሞስ አንድ ቀን ስለጾምህ ምን ትሆናለህ አትሟሟ በየዓመቱ ጥያቄ።
~ዲ/ን ኤርምያስ ~
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Jan, 04:41


ኃጢአት የሚሸት ቢሆን አብረን አንኖርም አብረን አንመገብም አብረን በአንድ ትራንስፖርት አንቀሳቀስም ነበር እግዚአብሔር ምሮን እንጂ መርምሮን ቢሆን ማን ከፊቱ ይቆም ነበር
*ለሀገራችን ሰላም ያውርድልን።
*እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ።

~ዲ/ን ኤርምያስ~
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

05 Jan, 18:18


ሌላ አንድ ሰው 100 ሌላ አንዲት እህታችን 200 ብር አስገብተዋል እግዚአብሔር ይስጥልን በረከተ አበው ያድልልን መድኃኔዓለም እድሜ ይስጥልን

EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

05 Jan, 13:23


ውጪ ለምትገኙ ብቻ  በOnline መማር ለምትፈልጉ

*የዘወትር ጸሎት
*ውዳሴ ማርያም
*አንቀጸ ብርሃን
*መልክአ ማርያም
*መልክአ ኢየሱስ
*ንባብ
*ዳዊት
*ውዳሴ ማርያም ዜማ
••••
@mahtot2 ላይ  ይፃፉልን

ይደውሉልን
+15092943369
+15095058383
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

04 Jan, 01:16


የዛሬ ከሌሊቱ 9:52 የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ አልተለየባችሁም?


የመድኃኔዓለም ያለህ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Jan, 17:56


ነጩን ወፍ ከራድዮንን
ከራድዮን ነጭ ወፍ ሲሆን በሊቃውንቱም ዘንድ የታወቀ ነው። ጠቢባን በድካም ፈልገው አድነው ይይዙታል፤ የታመመ ሰው ቢኖር ያቀርቡታል፤ እርሱም በሽተኛውን ትኩር ብሎ ያየዋል፤ የማይድን ለሞት የቀረበ ከሆነ ፊቱን አዙሮ ይመለሳል፤ ቀኑ ገና ከሆነ ግን አፉን ከፍቶ ከበሽተኛው አፍ እስትንፋሱን ይወስዳል፤ በልዑል እግዚአብሔር ኃይል የሰውየው ደዌ ሙሉ ለሙሉ ወደ ወፉ በእስትንፋሱ ይተላለፋል። ሰውየው ይድናል፤ ወፉ ይታመማል። ፊት ነጭ የነበረው እንደ ከሰል ይጠቁራል ሕመም ሲሰማው ወደ አየር ይነጠቃል ሲብስበት ወደ ባሕር ራሱን ይወረወራል በባሕር ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት ቆይቶ ጠጉሩን መልጦ በዐዲስ ተክቶ፣ ድኖ፣ታድሶ፣ ኃያል ሆኖ ይወጣል። ይህ ፍጥረት በዕለተ ሐሙስ የተፈጠረ ፍጥረታት ነው፡፡ ስለምን ፈጠረው? ቢሉ የወልደ እግዚአብሔር ክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ ለማያምኑ ትምህርት ምሳሌ አብነት ይሆን ዘንድ ይህን ወፍ የማዳን ኃይል ሰጥቶ ፈጥሮታል። ምሳሌነቱ ምንድነው?
ከራድዮን ወፍ የክርስቶስ ምሳሌ
የታመመው ሰው ፡ የአዳም ዘር ምሳሌ ሲሆን
ወፉ በዐይኑ መመልከቱ ፡- ክርስቶስ የሰው ልጆችን በሙሉ ለማዳን በምሕረትና በቸርነት ዓይኑ ለመመልከቱ ምሳሌ
ወፉ መታመሙ ፡- ክርስቶስ ስለ እኛ በደል መታመሙ ምሳሌ
መጥቆሩ ፡- ጌታችን ለእኛ ቤዛ ሊሆነን ከኃጢአተኞች ጋር ለመቆጠሩ ምሳሌ
ወፉ ወደ ላይ መውጣቱ ፡- ክርስቶስ ከፍ ብሎ በመስቀል የመሰቀሉ ምሳሌ
ወፉ በባሕር ሦሰት ቀን ሦስት ሌሊት መኖሩ ፡- ክርስቶስ በከርሰ መቃብር ሦሰት ቀንና ሦሰት ሌሊት ለማደሩ ምሳሌ ከራድዮን ወፍ ታድሶ ኃያል ሆኖ ከባሕር መውጣቱ ፡- ክርስቶስ በሲኦል የነበሩ ነፍሳትን አድሶ፣ አንጽቶ ገነት አስገብቶ፤ እርሱም ወደ ቀደመ ክብሩ ለማረጉ ምሳሌ ነው፡፡                       @mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Jan, 17:51


መድኀኔዓለም ክርስቶስም ረኃበ ነፍስ ረኃበ ሥጋ ጸንቶ ለኖረብን ለእኛ የሕይወት ምግብና መጠጥ ኾኖ ተሰጥቶናል ዮሐ ምዕ 6:56::
ጳልቃ፥ ልጆቿ ሲያቆስሏት በጥፍሯ እንደምትቀጣቸውና እንደሚሞቱ ኹሉ፥
የሰው ልጅም አትብላ የተባለውን ዕፀበለስ በልቶ አምላክነትን ሽቶ ፈጣሪውን አሳዝኗል፤ ስለዚኽም ሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ ተፈርዶበታል። ጳልቃ፥ ከሦስት ቀን በኋላ ደም ቀብታ ልጆቿን ከሞት አድና እሷ እንደምትሞት ኹሉ አምላካችን ክርስቶስም ከሦስት ክፍለ ዘመን ማለትም ከዘመነ አበው፣ ከዘመነ መሳፍንት፣ ከዘመነ ነገሥት በኋላ፡ ዛሬ በዕለተ አርብ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ዕርቃኑን ተሰቅሎ ሞታችንን ሞቶ፡ ሞትን ገድሎ እኛን አድኖናል። ሆሴዕ ምዕ 6:2።

የጳልቃ ልጆች ለእናታቸው ያላቸውን ፍቅር የሚገልጡት እናታቸውን በማድማት ነው።
በእናት ሀገራቸው ላይ ስሑት ፍቅር ያላቸው ሰዎችም እንዲኹ ናቸው።
መድኃኔዓለም ኾይ
ስቅለትኽ ከኀጢኣት ፍዳ ብቻ ያይደለ ከተሳሳተ ፍቅርም ያድነን።
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Jan, 17:50


ልጆቿን ለማዳን የምትሞተው ወፍ~
(repost)

ይኽች ወፍ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት "ጳልቃ" በሌሎቹ
(pelican ~ፐሊካን) ተብላ ትታወቃለች
ለልጆቿ ባላት ልዩና ጽኑ ፍቅር ምክንያት የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ናት።
ጳልቃ፥ የጠኔ ጊዜ መጥቶ የሚጫር የሚቀመስ በየብስና በባሕር አንዳች ምግብ ካጣች፣ ከራሷ አካል በጥፍሯ ደሟን አፍስሳ ሥጋዋን መንትፋ ለልጆቿ ሰጥታ ክፉውን ቀን ታሻግራለች።
ይኽችን ዕፅብት ወፍ፥ ልጆቿ ፍቅር መስሏቸው በጥፍራቸው እየወጉ ያቆስሏታል፤ እሷም ቁስሉ ይሰማትና በጥፍሯ ትወጋቸዋለች፤ ልጆቿም ይሞታሉ፤ ለልጆቿ ያላት ፍቅር ፍጹም ነውና ታዝናለች፤ ድምጻቸው ይናፍቃታል፤ ጠረናቸው ያባባታል። በሦስተኛው ቀን ሕመሟን ችላ በጥፍሯ ደረቷን ወግታ ደሟን ታፈስባቸዋለች፤ ይነሳሉ። እሷግን ብዙ ደም ሲፈሳት ትወድቃለች፤ ትሞታለች። በሀገራችን ወደ ግእዝ ከተተረጎመው ፊሳሎጎስ ጋር በተመሳሳይ
ልሳነ-እንግልጣሩም እንዲኽ አለ"…… in time of famine, the mother pelican wounded herself, striking her breast with the beak to feed her young with her blood to prevent starvation. Another version……that the mother fed her dying young with her blood to revive them from death, but in turn lost her own life"
ዛሬ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ጳልቃ እኛም እንደ ልጆቿ ኾነን የታየንበት ዕለት ነው።
ጳልቃ በረኃብ ጊዜ ራሷን ለልጆቿ እንደምትመግብ ኹሉ፥
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

02 Jan, 19:19


ሌላ አንድ ሰው 30ብር አስገብተዋል እግዚአብሔር ይስጥልን በረከተ አበው ያድልልን መድኃኔዓለም እድሜ ይስጥልን

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

02 Jan, 17:25


አንዲት እህታችን 500ብር በማስገባት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለውን የገንዘብ መጠን 137,289 ብር አድርሳዋለች መድኃኔዓለም በእድሜ በጤና ይጠብቅልን ።

ለእጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳም:-
፩) አስራታችንን
፪) ከታክሲ ከቁርስ ቀንሰን በወር 10ብር ብቻ
፫) በማኅበር በቤተሰብ ሰብስበን

ማሳሰቢያ :ሱባኤ ለመያዝም ይሁን ጸሎት ለማስያዝ ተብሎ የሚከፈል ምንም አይነት ክፍያ የለም ቤተክርስቲያን የአንተ የአንቺ የእኔም የሁላችንም እናት  ናት ።ሰው  ለእናቱ አስቦ ያደርጋል እንጂ እናት አታስከፍልም ።በእርግጥም ቤተክርስቲያን ከእኛ ምንም አትፈልግም ይሁን እንጂ ጥቅሙ ለራሳችን ነው።


EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

01 Jan, 03:15


https://t.me/mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

01 Jan, 03:13


ለእጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳም:-
፩) አስራታችንን
፪) ከታክሲ ከቁርስ ቀንሰን በወር 10ብር ብቻ
፫) በማኅበር በቤተሰብ ሰብስበን

ማሳሰቢያ :ሱባኤ ለመያዝም ይሁን ጸሎት ለማስያዝ ተብሎ የሚከፈል ምንም አይነት ክፍያ የለም ቤተክርስቲያን የአንተ የአንቺ የእኔም የሁላችንም እናት  ናት ።ሰው  ለእናቱ አስቦ ያደርጋል እንጂ እናት አታስከፍልም ።በእርግጥም ቤተክርስቲያን ከእኛ ምንም አትፈልግም ይሁን እንጂ ጥቅሙ ለራሳችን ነው።


EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

30 Dec, 18:05


ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ በግንባሩ ተደፍቶ ልዑል እግዚአብሔርን
‹ጌታ ሆይ! የምትነግረኝ ይደረግ ዘንድ እንደምን ይሆናል?› አለው፡፡ ጌታም ‹የጀመርኩትን ቸርነት ፈጸምኩ፣ የወይን ግንድ ይቆረጣል (ወልደ እግዚአብሔር ይሞታል)፣ ወይራም ከበለስ ጋር ይተከላል (መስቀል ይተከላል)፣ ቅጽሮችም ይቀጸራሉ (ምግባር ከሃይማኖት ጋር ይሠራል)፣ የኤልፍና የሌሚ ወገን ይነሣል፡፡ ገብርኤል ሆይ! ሄደህ ለዳዊት ልጅ ‹እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ› ብለህ አብሥራት› አለው፡፡ ‹ለዘለዓለም ነግሦ የሚኖረውን እነሆ ትፀንሳለሽ በላት› አለው፡፡
መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ሰገደ፡፡  ልብሱንም በላዩ ይዞ በመስቀል ቀኝ ይወርድ ዘንድ ወደደ፡፡
 ጌታም ‹መግባትህና መውጣትህ በፍቅር አንድነት ይሁን› አለው፡፡ ‹ዘካርያስን ረግመህ አንደበቱን እንዳሰርህ እርሷን እንዳታሳዝናት ይልቁንም አብዝተህ ደስ አሰኛት አንጂ አለው፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ፈጽሞ ደስ እያለው ሊባኖስ ከሚባል ተራራ እስኪሰማ ድረስ ክንፉን እያማታ ወረደ፡፡ በዚህም ጊዜ በዙሪያው ያሉ ሁሉ ‹ይህ የምንሰማው ምንድነው?› ይሉ ነበር፡፡ የተደረገበትንም ቦታ አላወቁትም ነበር፡፡››


እመቤታችንን በ3 ዓመቷ እናትና አባቷ ብፅዓት አድርገው ለእግዚአብሔር ሰጥተዋታልና ካህናትም በቤተ መቅደስ ከመካነ ደናግል አስገብተዋት በመልአኩ በቅዱስ ፋኑኤል አማካኝነት ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ሰማያዊ እየመጣላት ያንን እየተመገበች ቅዱሳን መላእክት እየጎበኟት 12 ዓመት ኖራለች፡፡ በ15 ዓመቷ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን ጌታችንን እንደምትወልድ በዚህች ዕለት አብሥሯታል፡፡

 በመጀመሪያ እመቤታችን ውኃ ቀድታ ስትመለስ የጠተማ ውሻ እያለከለከ ሲመጣ ብታየው ለፍጥረት ሁሉ የምትራራ ናትና በወርቅ ጫማዋ ለዛ ለተጠማው ውሻ ውኃ ስታጠጣ አብሯት የነበሩ ሴቶች ‹‹ማድጋሽን አጎደልሺው፣ ቀድቼ እሞለዋለሁ እንዳትይ ጉድጓዱ ጥልቅ ነው መቅጃም የለሽም›› አሏት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ‹‹ውሃ የሚገኘው ከወደላይ ነው እንጂ ከወደታች ነውን? ፍጥረቱን ያጠጣ ጌታ ይሞላልኛል›› አለቻቸው፡፡

ማድጋዋም በተአምራት ሞልቶ ተገኘ፡፡ ሴቶቹም ዳግመኛ ‹‹በዚህ ዘመን አምላክ ከድንግል ይወለዳል ይላሉ ካንቺ ይሆን?›› እያሉ ሲዘብቱባት ወዲያው ከወደኋላዋ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ‹‹እነሆ ትጸንሻለሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ዞር ብትል የተናገራትን አጣችው፡፡ በዚህም ጊዜ ‹‹አባቴን አዳምን እናቴን ሔዋንን ያሳተ ጠላት ይሆናል›› ብላ ሄደች፡፡
ዳግመኛም እመቤታችን ከቤት ደርሳ ማድጋዋን ስታስቀምጥ መልአኩ አሁንም በድምፅ ‹‹እነሆ ትጸንሻለሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ይህን ጊዜ ‹‹ምነው ይህስ ነገር ደጋገመኝ እንዲህ ያለውን ነገር ቤተ መቅደስ ሄደው ሊረዱት ይገባል›› ብላ ወደ ቤተ መቅደስ ሄዳ ወርቅና ሐር እያስማማች ስትፈት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እሁድ ቀን በ3 ሰዓት በገሃድ ተገለጸላትና እጅ እየነሳ እየሰገደ አበሠራት፡፡
‹‹የዕውነተኛ ንጉሥ እናቱ እመቤታችን ላንቺ ፍቅር አንድነት ይገባል›› አላት፡፡ ዳግመኛም ‹‹አንቺ ከሴቶች ይልቅ ተለይተሸ ንዕድ ክብርት ነሽ›› አላት፡፡ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናቸ ክብርት እመቤታችንም የብርሃናዊውን መአልክ የቅዱስ ገብርኤልን ቃል በሰማች ጊዜ
‹‹እንዲህ ያለውን ሰላምታ እንደምን ይቀበሏል/ እንዴትስ መቀበል ይቻላል? እንጃ›› አለችው፡፡                                           መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ‹‹ማርያም ሆይ! መንፈስ ቅዱስ ያድርብሻል፣ ኃይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ይለብሳልና አይዞሽ አትፍሪ›› አላት፡፡ ዳግመኛም ‹‹ይህ ካንቺ የሚወለደው ጽኑ ከሃሊ ነው፡፡ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ፣ እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፣ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፣ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፣ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም›› አላት፡፡

 እመቤታችንም መልአኩን ‹‹ምድር ያለ ዘር ፍሬን አትሰጥምና እኔ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል?›› አለችው፡፡ መልአኩም መልሶ ‹‹መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፣ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል። እነሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ እርሷ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፡፡ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው፣ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና›› አላት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ይህን ጊዜ ‹‹እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ›› አለችው፡፡
መልአኩም ከእርሷ ዘንድ ሄዶ ተሠወረ፡፡ አካላዊ ቃልም በማኅፀኗ አደረ፡፡ በዚያችም ቅጽበት የእመቤታችን የፊቷ መልክ ተለወጠ፣ እንደፀሐይም አሸበረቀ፡፡ ልመነዋ ክብሯ እኛ ለዘለዓለም በዕውነት ይደርብን፡፡

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

30 Dec, 18:05


ብስራተ ገብርኤል
       ታኅሣሥ 22 ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን አምላክን እንደምትወልድ ያበሰረበት መታሰቢያ በዓል፡፡
ልመናዋ ክብሯ በእኛ ለዘላለም በእውነት ይደርብንና አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ያደረገችው ተአምር ይህ ነው፡- ‹‹ልዑል እግዚአብሔር ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ‹ሂድና ለጽዮን ልጅ ለድንግል የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ ወደአንቺ መጥቶ ኃይለ ልዑል ወልድ ሥጋሽን ለብሶ ሰው ይሆናል፤ ይኸውም ካንቺ የሚወለደው ጽኑዕ ነው ብለህ ንገራት› አለው፡፡

‹ደንቆሮዎች የሚሰሙበት፣ ድዳዎቸ የሚናገሩበት፣ ዕውራንም የሚያዩበት፣ ሙታን የሚነሡበት፣ ለምጻሞች የሚነጹበት፣ ሐንካሳዎች የሚሄዱበት፣ በጨለማ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ብርሃን የሚያዩበት ጊዜ እነሆ ደረሰ ብለህ ንገራት› አለው፡፡
     

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

30 Dec, 15:07


አንድ ሊቅ እንዲህ አሉ ንብ እና ዝንብ እየተወያዩ ነው አጀንዳው ከእኔ እና ከአንቺ ጭራ የሚነሳው ለማነው ?ዝንብ ንብን አትዋሺኝ እውነቱን ንገሪኝ ለእኔ ወይስ ለአንቺ አለቻት ንብም እኔ ከአበቦች ንግስት ጋር እየዋልኩ አበባ መስዬ እየዋልኩ ለአንቺ እንጂ ለእኔማ እንዴት ሆኖ ጭራ ቢነሳ ነበር የሚገርመው አለች ።ዝምብም አዋዋሌ ነው ከቆሻሻ ጋር እየዋልኩ ተኝቼ እንኳን እንዳላርፍ ያደረገኝ ያገኘኝ ሁሉ የሚያባርረኝ አለች አሉ።
ወንድሜ አዋዋልህ ወይዝንብ ወይ ንብ ያደርግሃልና ውሎህን አስተካክል።

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

29 Dec, 15:11


የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እነዚህን ነዋዬ ቅድሳት እንፈልጋለን ልታግዙን የምትችሉ።በሚከተሉት አካውንት አግዙን

፩) ፃህል ፣ጽዋ
፪) ማይክ
፫) ድንኳን (ለቃል ኪዳን ታቦታት ማደሪያ)



ብሩን ስታስገቡ ይህ ለዚህኛው ነዋዬ ቅድሳት ነው እያላችሁ ላኩልን  @mahtot2  ላይ ይፃፉልን  ወይም 0912494703 ላይ ይድውሉልን
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

29 Dec, 04:22


ኢቫንጀሊስት ሄኖክ የሚባለው የፕሮቴስታንት ቸርች መሪ ለብዙ ዘመናት ቅድስት ቤተክርስቲያንን ሲያሳድድ የነበረ በፍጹም ይቅርታ እና ንስሐ ወደ ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተመልሷል ።እግዚአብሔር ለሌሎችም ልቦና ይስጥልን ።

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

28 Dec, 12:17


ለእጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳም:-
፩) አስራታችንን
፪) ከታክሲ ከቁርስ ቀንሰን በወር 10ብር ብቻ
፫) በማኅበር በቤተሰብ ሰብስበን

ማሳሰቢያ :ሱባኤ ለመያዝም ይሁን ጸሎት ለማስያዝ ተብሎ የሚከፈል ምንም አይነት ክፍያ የለም ቤተክርስቲያን የአንተ የአንቺ የእኔም የሁላችንም እናት  ናት ።ሰው  ለእናቱ አስቦ ያደርጋል እንጂ እናት አታስከፍልም ።በእርግጥም ቤተክርስቲያን ከእኛ ምንም አትፈልግም ይሁን እንጂ ጥቅሙ ለራሳችን ነው።


EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

28 Dec, 09:35


በነፃ ማስታወቂያ እንሰራላችኋለን
የሚመጣው የፊታችን ጥር 26ለ27 ወደ መንዝ እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳም ጉዞ ማስጓዝ ለምትፈልጉ ህጋዊ መንፈሳዊ የጉዞ ማኅበራት በነፃ ማስታወቂያ እንሰራላችኋለን ከበረከቱ ተሳታፊ አብረን እንሁን።። ይደውሉ
0912494703 ወይም @mahtot2 ይፃፉልን
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

28 Dec, 04:15


ቅዱስ ገብርኤል እና ክብሩ

ቅዱስ ሉቃስ እንደጻፈው መልአኩ #ቅዱስ_ገብርኤል ሁል ጊዜም ለደስታና ለምሥራች የሚላክ መልአክ ነው፤ በተለይም ስለ ልደተ ክርስቶስ ለድንግል ማርያም ለመጀመሪያ ጊዜ የምስጋና እና  የክብር ሰላምታ ያበሠረ በመሆኑ ‹‹አብሳሬ ትስብእት (መልአከ ብሥራት) መጋቤ ሐዲስ›› ተብሎ ይጠራል፡፡
#ቅዱስ_ገብርኤል ከሌሎች መላእክት ተለይቶ መላእክት ከተፈጠሩ በኋላ አምላካቸውን ለማወቅ ‹‹መኑ ፈጠረነ›› እያሉ ሲባዝኑ ሳጥናኤል ‹‹እኔ ፈጠርኳችሁ›› ሲል ቅዱስ ገብርኤል ግን የፈጠረንን አምላክ እስክናውቅ ድረስ በያለንበት እንቁም እንጽና፤ ንቁም በበህላዌነ እስከ ንረክቦ አምላክነ›› በማለት መላእክትን ያረጋጋ መልአክ ነው፡፡ (አክሲማሮስ. ገጽ.፴፭) በዚህም አባቶቻችን እንደሚሉት መልአኩን የመጀመሪያው የተዋሕዶ ሰባኪ ነው፡፡ ምክንያቱም ከፍጥረታት አስቀድሞ አምላኩን ዐውቆ ስብከት የጀመረ መልአክ ነውና፡፡ በዚህም ምክንያት ጌታ ‹‹ወበእንተዝ ይደልዎ ከመ ይጹር ዜናሃ ለማርያም፤ድንግል ማርያምን ያበስር ዘንድ የተገባው ሆነ›› እንዲል፤ ነገረ ሥጋዌውን ለድንግል እንዲያበሥር አድሎታል፤ ከዚህ በኋላም ደጋግ ሰዎችን ለመርዳት የሚወጣ የሚወርድ ሆኗል፡፡
#ቅዱስ_ገብርኤል ከሌሎች መላእክት ተለይቶ ዘወትር በምንጸልያቸው ጸሎቶች ስሙ የሚጠራ መልአክ ነው፡፡ ይኸውም በዘወትር ጸሎቶች በአቡነ ዘበሰማያት፣ በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል፣ በውዳሴ ማርያም፣ በይዌድስዋ መላእክት እና በመሳሰሉት ጸሎቶች ዘወትር ስሙ የሚጠራ መልአክ ነው፡፡
#ቅዱስ_ገብርኤል ካህናት አባቶች እንደሚሉት ስእለት ሰሚ እንዲሁም ፈጥኖ ደራሽ መልአክ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት በክርስቲያኖችም ዘንድ እጅግ ተወዳጅ መልአክ ነው፡፡ ስለዚህም ፈጥኖ ደራሹ መልአክ፣ ስእለት ሰሚው መልአክ ይባላል፡፡ በሀገራችንም ክብረ በዓሉ በቁልቢ ገብርኤል እና በተለያዩ ቦታዎች እጅግ በርካታ ሕዝበ ክርስቲያን በተገኙበት ይከበራል፡፡
የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከሌሎች መላእክት ሁሉ በይበልጥ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን እንደ ምትወደው በድርሳነ ገብርኤል ላይ ተጽፏል፤ ‹‹ርእዩኬ አኃዊነ ዘከመ ታፈቅሮ እግዝእትነ ማርያም ለቅዱስ ገብርኤል እምኲሎሙ መላእክት እስመ አብሠራ ልደተ ወልድ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ ወውእቱ ከመ ያፈቅራ ወይረድኣ በጊዜ ምንዳቤሃ ለነኒ ይርድአነ በጊዜ ምንዳቤነ፣ ወንድሞቻችን ሆይ፥ እመቤታችን ድንግል ማርያም ከመላእክት ሁሉ ይልቅ ቅዱስ ገብርኤልን በይበልጥ እንደምትወደው ተመልከቱ፤ የልጅዋን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ከእርሷ መወለድ ያበሠራት እርሱ ነውና›› እንዲል፡፡ (ድርሳነ ገብርኤል ዘኅዳር ምዕራፍ ፪፥ ቁጥር ፲፫)
#ቅዱስ_ገብርኤል ብርሃናዊ መልአክ ነው፤ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ በራእዩ እንዲህ በማለት ተናግሯል፤ ‹‹ከዚህ በኋላ ታላቅ ሥልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች፡፡›› (ራእ.፲፰፥፩)
ነቢዩ ዳዊት ‹‹መላእክቱን የእሳት ነበልባል የሚያደርግ›› እንዳለው ቅዱስ ገብርኤል ነበልባላዊ መልአክ ነው፡፡ (መዝ.፻፫፥፬)
ቅዱስ ገብርኤል ኃያል መልአክ ነው፤ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ ‹‹ብርቱ መልአክ ደመና ተጎናጽፎ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ በራሱም ላይ ቀስተ ደመና ነበረ፤ ፊቱም እንደ ፀሐይ እግሮቹም እንደ እሳት ዐምዶች ነበሩ፤ የተከፈተችንም ታናሽ መጽሐፍ በእጁ ያዘ፤ ቀኝ እግሩንም በባሕር ላይ ግራውንም በምድር ላይ አኖረ፤ እንደሚያገሳም አንበሳ በታላቅ ድምጽ ጮኸ›› በማለት መስክሯል፡፡ (ራእ.፲፥፩)
#ቅዱስ_ገብርኤል የመላእክት አለቃ ነው፤ በራማ በሠፈሩት ዐሥሩ የነገድ ሠራዊት ላይ የአርባብ አለቃ ነው፡፡ ነቢዩ ሄኖክም ‹‹በሠራዊት ሁሉ ላይ የተሾመ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው››  ይላል፡፡ በዚህም ምክንያት የራማው መልአክ ተብሎ ይጠራል፡፡ (ሄኖክ.፲፥፲፬)
#ቅዱስ_ገብርኤል ፈጣን መልአክ ነው፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚሉት በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሥነ ስቅለት ጊዜ በመስቀል ላይ የደረሰበትን መከራ አይቶ አላስችለው ቢል ሰይፍ ወርውሯል፤ ‹‹ዓለምም የሚያልፈው #ቅዱስ_ገብርኤል የወረወረው ሰይፍ ሲያርፍ ነው›› ይላሉ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ መልኩም ሰይፍ እንደወረወረ ከዚህ በታች በተጻፈው መልኩ እንገነዘባለን ይኸውም፡-
ሰላም ለሰኰናከ ወለመከየድከ ክልኤ
ታሕተ ዐውደ መስቀል ዘቆማ በዕለተ ድልቅልቅ መውዋዔ
ሰይፈ ቁጥዓ ገብርኤል ዘመላኅከ ቅድመ ጉባኤ
አንስትሰ ሶበ ሰምዓ ቃለ ዚኣከ በቋዔ
ኀበ ሐዋርያት ሖራ ይንግራ ትንሣኤ
ትርጉም፡- ገብርኤል ሆይ፥ በዚያ ድብቅልቅና ሽብር በሆነበት ዕለት ከጌታ እግረ መስቀል ሥር ለቆሙት ተረከዞችህና ጫማዎችህ ሰላም እላለሁ፤ ገብርኤል ሆይ የጌታን ትዕግሥት የአይሁድን ግፍ ተመልክተህ በታላቅ ዐደባባይ ላይ ሰይፈ ቁጣህን አምዘገዘግኸው ቅዱሳት አንስት ግን ክርስቶስ ተነሥቷል ስላልካቸው የትንሣኤውን ምሥራች ይነግሩ ዘንድ ወደ ሐዋርያት ሄዱ›› እንዲል፡፡ ስለዚህ ቅዱስ ገብርኤል ከዓለም በፊት አምላኩን ያወቀ ዓለም ልታልፍ ስትልም የወረወረው ሰይፍ እንደሚያርፍ ሊቃውንቱ ያስረዳሉ፡፡
በሀገራችን በተለምዶም ‹‹ሚካኤል እንደአየህ ገብርኤል እንዳያይህ›› የሚባል አባባል አለ፤ ይኸውም የመልአኩ ተራዳኢነት እንዳለ ሁኖ ተነግሮ ለማይሰማ አካል ግን መልአኩ ፈጣን እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡ በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችም የቅዱስ ገብርኤልን ቁጣ የምንሰማ እና የምናይ ሲሆን ለምሳሌም ካህኑ ዘካርያስ የመልአኩን ቃል ባለመስማቱ (ባለመቀበሉ) ዲዳ ሁኗል፡፡በተጨማሪም በኢ-አማንያንም ዘንድ ሳይቀር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ይፈራል፡፡ (ሉቃ.፩፥፲፩)


በረከቱ ረድኤቱ ይደርብን
እንኳን አደረሳችሁ።
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

28 Dec, 04:10


‹‹እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ›› (ሉቃ.፩፥፲፱)

የሊቀ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል በዓል  (ታህሳስ 19)
ይህን ቀን የምናከብረው አምላካችን፣ ጌታችናን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰለስቱ ደቂቅን ከሚነደው ከእሳቱ እቶን ውስጥ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ ያዳነበትን በማሰብ ነው።
አባቶቻችን እንዳስተማሩን፣ ቅዱስ መጽሐፍም እንደሚነግረን በዚያን ዘመን ጣኦት የሚመለክበት ዘመን ነበር።
እግዚአብሔርን በፍጹም ልባቸው ያምኑ የነበሩ ሶሥቱ ወጣቶች፤ አናንያ(ሲድራቅ)፣ አዛርያ (ሚሳቅ)፣ ሚሳኤል(አብድናጎ) ይባሉ ነበር።በትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ 3 ከቁጥር 1 እስከ መጨረሻው እንደተጻፈው ታሪኩ በአጭሩ እንዲህ ነበር።
ንጉሡ የጣኦት  ምስል አሰራ፣ በገሊላ አውራጃ ያለወን ሕዝብ ጠርቶ ለጣኦቴ ያልሰገደ ወደ እሳት ውስጥ ይጣላል ብሎ አወጀ። በዚያን ወቅት እኒያ ሰልስቱ ደቂቅ ነበሩ። የንጉሥ ትእዛዝ ነውና ሕዝብ ሁሉ ለጣኦቱ ሲንበረከክ እነዚያ በእግዚአብሔር አዳኝነት የተማመኑ ሶሥት ወጣቶች ግን ቆመው ያዩ ነበር። የእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምንም ነገር አያስፈራውምና ናቡከደናፆር እርሱ ላስቆመው ጣኦት አለመስገዳቸውን ሲሰማ እጅጉን ተናደደ። ከመበሳጨቱም የተነሳ የሚነደውን እሳት ሰባት እጥፍ እንዲነድ አስደረገ። ሦስቱንም ወጣቶች አስሮ እሳቱን እያሳየ ለእኔ ጣኦት መስገድ ይሻላችኋል ወይስ ከዚህ ከሚነደው እሳት መጣልና መቃጠል አላቸው። እነርሱ ግን የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶን ያድነናል ባያድነንም እንኳ አንተ ለሰራኸውና ለምታምልከው ጣኦት አንሰግድም አሉት። ወዲያውም ንጉሡ ሦስቱን ወጣቶች አስረው ወደ እሳቱ እንዲጥሏቸው ወታደሮችን አዘዘ። ወጣቶቹን አስረው የጣሏቸው ወታደሮች  የእሳቱ ወላፈን ሲያቃጥላቸው ሠለስቱ ደቂቅን ግን መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ እሳቱን አጠፋላቸው። ንጉሡም ናቡከደናጾር በዚያን ጊዜ እንዲህ አለ “ታስረው የተጣሉት ሦስት ነበሩ አሁን ግን አራተኛ ሰው በእሳቱ መካከል ሲመላለስ ይታየኛል” አለ። “ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን? ብሎ ተናገራቸው። እነርሱም። ንጉሥ ሆይ፥ እውነት ነው ብለው ለንጉሡ መለሱለት። እርሱም። እነሆ፥ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል ብሎ መለሰ። የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ። እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች፥ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም፥ ኑ ውጡ ብሎ ተናገራቸው። ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ። መሳፍንቱና ሹማምቶቹም አዛዦቹና የንጉሡ አማካሪዎች ተሰብስበው እሳቱ በእነዚያ ሰዎች አካል ላይ ኃይል እንዳልነበረው፥ የራሳቸውም ጠጕር እንዳልተቃጠለች፥ ሰናፊላቸውም እንዳልተለወጠ፥ የእሳቱም ሽታ እንዳልደረሰባቸው አዩ። ናቡከደነፆርም መልሶ። መልአኩን የላከ፥ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፥ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ። እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም አምላክ ላይ የስድብን ነገር የሚናገር ወገንና ሕዝብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ይቈረጣሉ፥ ቤቶቻቸውም የጕድፍ መጣያ ይደረጋሉ ብዬ አዝዣለሁ አለ።  የዚያን ጊዜም ንጉሡ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም በባቢሎን አውራጃ ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋቸው። (ዳን.3

የእግዚአብሔር መልአክ #ቅዱስ_ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ ‹‹እግዚእ ወገብር፤ አምላክ ሰው ሆነ ሰው አምላክ ሆነ›› ማለት ነው፤ ‹‹ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘኢይተረጐም ምሥጢር ባሕቱ ይመስል ብሂለ እግዚእ ወገብር፤ ገብርኤል ሆይ ተመራምሮ ለማይደረስበት ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ፤ ነገር ግን አምላክ ሰው ሆነ ሰው አምላክ ሆነ ማለት ይመስላል›› እንዲል፡፡ (መልክዐ ቅዱስ ገብርኤል)
#ቅዱስ_ገብርኤል የጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መምጣት እና ሰው መሆን ለመናገር ተልኮ የምሥራች ዜናን ያበሠረ፤ በዲያቢሎስ የተንኮል ወጥመድ ገብተው ለተሰናከሉት ፈጥኖ ለርዳታ የሚደርስ፣ በጨለማ እና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩት ሁሉ የብርሃን ፋና ያበራ፣ ሰብአ ሰገልን የመራ መልአክ ነው፡፡ ከቀድሞ ጀምሮ ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር ተልከው መንፈስ ቅዱስ እንዳናገራቸው ዓለምን ስለማዳን ከጽዮን የሚወጣ ከያዕቆብ በደልን የሚያርቅ ጌታ ‹‹ይወርዳል ይወለዳል›› በማለት በየወገናቸው እና በየዘመናቸው የተናገሩትን የነቢያትን ትንቢት ያስፈጸመና የምሥራችን ቃል የተናገር፣ የጨለማ አበጋዝ በሆነ በሰይጣን ተንኮል ከእፉኝት መርዝ የከፋ በሰው ልቦና ውስጥ አድሮ የነበረውን የኀዘን ስሜት ያጠፋ የእግዚአብሔር መልአክ #ቅዱስ_ገብርኤል ነው፡፡

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

27 Dec, 18:51


"ከድግሪ ያገኘኸው ፍልስፍና ከሃይማኖትህ የሚበልጥብህ ከሆነ ሞተሃል"ቤተመንግስት አድገው ኖረው ንጉሥ ላቆመው ጣኦት አንሰግድም አሉ።በእምነታቸው ጸኑ ስለሆነም መልአኩን ላከላቸው።ቤተመንግሥት የመግባት እድሉን ስታገኝ አድር ባይና ስግብግብ ፍጥረተ እግዚአብሔርን ለመበደል እንጂ ለማንሳት የማትፋጠን ከሆነ ሞትህ ቅርብ ነው።

ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

27 Dec, 03:07


የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እነዚህን ነዋዬ ቅድሳት እንፈልጋለን ልታግዙን የምትችሉ።በሚከተሉት አካውንት አግዙን

፩) ፃህል ፣ጽዋ
፪) ማይክ
፫) ድንኳን (ለቃል ኪዳን ታቦታት ማደሪያ)



ብሩን ስታስገቡ ይህ ለዚህኛው ነዋዬ ቅድሳት ነው እያላችሁ ላኩልን  @mahtot2  ላይ ይፃፉልን  ወይም 0912494703 ላይ ይድውሉልን
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

24 Dec, 16:34


ውጪ ለምትገኙ ብቻ በOnline መማር ለምትፈልጉ

*የዘወትር ጸሎት
*ውዳሴ ማርያም
*አንቀጸ ብርሃን
*መልክአ ማርያም
*መልክአ ኢየሱስ
*ንባብ
*ዳዊት
*ውዳሴ ማርያም ዜማ
••••
@mahtot2 ላይ  ይፃፉልን

ይደውሉልን
+15092943369
+15095058383

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

20 Dec, 12:34


እግዚአብሔር ይስጥልን መድኃኔዓለም በረከትን ያድልልን።
በገዳሙ አካውንት ብቻ ያስገቡ

EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

18 Dec, 17:00


እግዚአብሔር ይስጥልን መድኃኔዓለም በረከትን ያድልልን።
በገዳሙ አካውንት ብቻ ያስገቡ

EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

17 Dec, 13:01


ቅዱስ ጳውሎስ ስለ መዳን በተናገረባቸው ከሃያ በላይ ቦታዎች ድኅነትን ሥላሴያዊ አድርጎ መናገሩን ልብ ይሏል። ታዲያ "ኢየሱስ ብቻ" የሚለው ትምህርት ከየት የመጣ 'መቀነስ' ነው? ኢየሱስ ክርስቶስ አብዝቶ ይናገር የነበረው ስለ እርሱ ሥራ ብቻ ሳይሆን ስለ አባቱ እና ስለ መንፈስ ቅዱስ መሆኑ እየታወቀ "አይሆንም፤ ስለ እርሱ ብቻ ነው የምንናገረው!" ማለት ትልቅ ማጣመም ነው። አንዳንዶች ስለ አብ ሲናገሩ እንኳ ቁጡ እና በመዓት የተሞላ አድርገው ይስሉታል፤ ወልድን ደግሞ ከአብ ቁጣ የሚያድን ቸር አድርገው ይስሉታል። ወልድ ከኃጢኣት፣ ሞት እና ዲያብሎስ ብቻ ሳይሆን ከአባቱ የሚያድነን ያስመስሉታል። በዚህም በአባትና በልጅ መካከል የግብር ልዩነትን ያመላክታሉ። ይህ ግን ክርስቶስ በጠፋው ልጅ ምሳሌ ውስጥ የጠፋ ልጁን ከሩቅ ሲያየው በፍቅር ከተቀበለው እና በዓልን ካደረገው ቸር አባት ጋር ይገጥማል? በፍጹም!

በአብ ዘንድ የማንወደድ ስለሆንን የምንወደድ ለማድረግ አይደለም ክርስቶስ የሞተው፤ ምንም ኃጢኣተኞች ብንሆን በአብ ዘንድ የምንወደድ ስለሆንን ልጁን ልኮ አዳነን እንጂ። የወልድ ሞት እግዚአብሔርን አልቀየረም፤ እኛን እንጂ!

ማዳን ሥላሴያዊ ነው። በልጁ ሞት ያዳነን አብ ነው! የሚቀድሰን እና ሕይወትን የሚሰጠን መንፈስ ቅዱስ ነው! አዳኝነት የሦስቱም አካላት የአንድነት ግብር ነው።


@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

17 Dec, 10:48


እንግሊዛዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ካህን፤

“እንግሊዛዊ ነው፤”ብትባሉ ታምናላችሁ?
ይህ ካህን እንግሊዛዊ ነው፥”በግዕዝ ይቀድሳሉ፤”ያልናችሁ ዝም ብለን አይደለም።ዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ገብቶ መዝገብ ቅዳሴ ጥንቅቅ አድርጎ ተምሯል። አሁን የለንደን ጽዮን ማርያም ቄሰ ገበዝና የቅዳሴ መምህር ነው።እያስተማረ ጥሩ ጥሩ ዲያቆናትን አፍርቷል። እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን።


ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስና አቶ ኃይለ ሚካኤል ከእንግሊዛዊው ካህን ታንሱ ዘንድ ሰይጣን እንዴት አጠመዳችሁ??
ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

17 Dec, 10:46


ጊዜ የሰጠው ቅል......

✍️..አሁን ላይ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መከፋፈልና ለንጹሐን የተዋሕዶ ልጆች ጭፍጨፋ ዋናዎቹ አባ ሳዊሮስና አቶ ኃይለሚካኤል ታደሰ ከፈኒ ናቸው።ቤተክርስቲያኗንና አማኞቿን ጊዜ ሰጠን ብለው ያልፈጸሙባቸው የግፍ አይነት የለም!! በእነዚህ ሁለት ሰዎች አጋፋሪነት ክርስቲያኖች በቅጽረ ቤተክርስቲያን ውስጥ በክላሽና በስናይፐር ተጨፍጭፈዋል።ቤተ ክርስቲያን በመናፍቅና በዋቢያዎች አውደ ምሕረቷና ቤተ መቅደሷ በጫማ ተረግጧል።

✍️ የቤተ ክርስቲያኗ አምላክ በደንብ አድርጎ ዋጋቸውን እንደሚከፍላቸው እናምን ነበር!! ይኸው ዓመታት ሳይቆጠሩ እሳቸው ያጠመዱት ቦንብ ራሳቸው ላይ መፈንዳት ጀምሯል።እመኑኝ ሲያቀጣጥሏት የነበረችውና አዳፍነው ያስቀመጧት እሳት በልታ ትፈጅዎታለች ።ይኸው እርስ በርሳቸው መናከስ ጀምረዋል ።
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

17 Dec, 05:40


የገና ገሃድ ስንት ሰዓት ይጾማል??
ከበዓለ ሃምሳ ከገና እና ጥምቀት ውጪ ጾመ ድኅነት ጾም ነው።
ለምሳሌ በነቢያት ጾም ላይ ያለ ጾመ ድኅነት(ዓርብ እና ረቡዕ)ከዚህ ሰዓት እስከዚህ ሰዓት ጾመ ድኅነት እስከዚህ እና እስከዚያ ደግሞ ጾመ ነብያት(የገና ጾም)ሳንል ተደርቦ ይጾማል ልደተ ክርስቶስ (ገና)ረቡዕ ቢውል ማክሰኞ የረቡዕ ለውጥ (ገሃድ)ተደርቦ ይጾማል ምክንያቱም የነቢያትም
ጾም ስላላለቀ ።ቅዳሴ እንደ ትንሣኤ እንደ ጥምቀት ሌሊት ስለሆነ 18ሰዓት ይጾማል።

ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

15 Dec, 09:57


አንድ ወንድማችን 2000 ብር አስገብቷል ።እግዚአብሔር ያክብርልን መድኃኔዓለም እድሜ ይስጥልን በረከትን ያድላችሁ

አጠቃላይ = በአቢሲንያ ባንክ 431,261.56 ብር
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ = 130,312.45 ብር
ደርሰናል በእውነቱ ደስ የሚል አገልግሎት ነው።
በገዳሙ አካውንት ብቻ ያስገቡ

EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Dec, 09:19


የገጠር ዐብያተ ክርስቲያናትን እናግዝ እንደግፍ የምላችሁ በእውነት በጣም ችግር ውስጥ ስላሉ ነው እዚህ ከተማ ተቀያሪ ልብስ ወይም የገቢ ምንጭ የሚሆን ህንፃ ለመስራት አንድም የቅንጦት ውድ አልባሳትን ለመግዛት ነው ።አስተውሉ ክርስቲያኖች ሥጋ ወደሙ ገጠርም እዚህም አንድ ነው እባካችሁ የገጠሪቷን ምዕመናን አስቧቸው።

@mahtot2 ላይ  ይፃፉልን

ይደውሉልን
+15092943369 አሜሪካ
+15095058383
+251912494703..ኢትዮጵያ

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

02 Dec, 10:04


የካህን መናፍቅ


ቅዱስ ጴጥሮስ ክዶ ሲመለስ መቼ ክህነቱን አጣ በማለት አንድ ካህን መናፍቅ (ከፍሎ አማኝ )ሆኖ ቆይቶ ሲመለስ ክህነቱን አያጣም ብሎ አንድ ሰው ተከራከረኝ ይሁን እንጂ ያልተፃፈ የምታነቡ ሆይ


✓ በታወቀ ምክንያት የተሻረ ቄስ ወይም ዲያቆን ቢኖርና ከተሻረ በኋላ የክህነት ሥራ ቢሠራ ከምዕመናን ፈጽሞ ይለይ፤ መሻሩን እያወቀ ከእርሱ ጋር አንድ የሚሆንም ይለይ።
የከሃድያን ጥምቀት የተጠመቀ ወይም ከቁርባናቸው የቆረበ ኤጲስ ቆጶስ ወይም ቄስ ወይም ዲያቆን ቢኖሩ ከሹመታቸው ይሻሩ። አብጥሊስ 41:-

"በታወቀ ኃጢአት በትክክል የተሻረ ኤጲስ ቆጶስም ቢሆን ቄስም ቢሆን ዲያቆንም ቢሆን ከተደፋፈረና ሥልጣን ባለው ጊዜ ይሠራው የነበረውን መሥራት ከጀመረ ፈጽሞ ከቤተክርስቲያን ይራቅ" ( ቀኖና ዘኒቅያ (ዘሠለስቱ ምእት) ትእዛዝ 19)።

" ባደረገው በደል ከቤተክርስቲያን ያስወጡት ኤጲስ ቆጶስ፣ በግድም ያለ ፍርሀት የቤተክርስቲያንን አገልግሎት ቢፈጽም እስከመጨረሻው ከቤተክርስቲያን ይሰናበት" (አብጥሊስ 27)።

"በታወቀ በደል በትክክል የተሻረ ኤጲስ ቆጶስ ቢኖርና ቀድሞ በተሰጠው ሥልጣን ለመሥራት ቢደፋፈር እስከዘለዓለሙ ድረስ ከቤተክርስቲያን ይሻር።" (ሥርዓተ ጽዮን 27)

በዝንጉዎች የተጻፈን የውሸት መጽሐፍ እንደ ተቀደሰ መጽሐፍ አስመስሎ ሕዝብን ለጥፋትና ለችግር ለማጋለጥ ወደ ቤተ ክርስቲያን ያስገባ ቢኖር ከክህነቱ ይሻር (ሥርዓተ ጽዮን 56)።

"ባደረሰው በደል ምክንያት ሥልጣኑ ተይዞ ከቤተክርስቲያን የተባረረ ኤጲስ ቆጶስ ከተወገዘ በኋላ ውግዘቱን አቃሎ በክህነት ሲያገልግ የተገኘ እስከመጨረሻው ከቤተክርስቲያን ይሰናበት።" (ቀሌምጦስ 27)


@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

30 Nov, 18:44


ወደ ሥልጣን ማማ ላይ ከወጣ ጀምሮ ብዙ በዓይን የሚታዩ ስህተቶችን እንደፈጠረ እሙን ነው እኔ በግሌ ይህን ሁኔታውን አድርባይነቱን አልስማማበትም ይሁን እንጂ የዛሬው በአንድ የመጽሐፍ ምረቃ መርሐ ግብር ላይ ተገኝቶ በዚያ መርሐ ግብር ላይ የፕሮቴስታንት ቤተ እምነት ዘማርያን ሲዘምሩ እሱ ቆሞ ሲመለከት እናያለን። ሆኖም ግን አንዳንድ ሰዎች በሚዲያ እንደሚያራግቡት አይደለም ።በእርግጥ ለምን በዚያ ቦታ ተገኘ እሱን እሱ ራሱ ሙሉ ሰው ስለሆነ የሚናገር ይመስለኛል ይሁን እንጂ ምክንያቱን ሳናውቅ ባንፈርድ መልካም ነው። በዘማሪ ሐዋዝ ወደ ቅድስት ተዋህዶ መመለስ በዚያኛው ቤት የለቅሶ ድንኳን ተጥሏል ለዚያ ሐሳብ ያስቀየሱ መስሏቸው ነው።

ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

30 Nov, 13:02


ውጪ ለምትገኙ እና በOnline መማር ለምትፈልጉ

*የዘወትር ጸሎት
*ውዳሴ ማርያም
*አንቀጸ ብርሃን
*መልክአ ማርያም
*መልክአ ኢየሱስ
*ንባብ
*ዳዊት
*ውዳሴ ማርያም ዜማ
@mahtot2 ላይ  ይፃፉልን

ይደውሉልን
+15092943369
+15095058383

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

30 Nov, 12:16


ሳዊሮስ ዘገብሎን የእባቡን ምስል አስመልክቶ ሙሴን እንዲህ ሲል ይጠይቀዋል፡፡ ‘የተረገመ ሥዕል በመከራ ለተናወጠ ሕዝብ እንዴት ድኅነትን ሊያመጣ ይችላል? የተነደፋችሁ ሁላችሁ አንጋጥጣችሁ ወደ ሰማይ ወደ እግዝዚአብሔር ተመልከቱ ወይም ወደ መገናኛው ድንኳን ተመልከቱና ትድናላችሁ’ ቢል አይሻለውም ነበር? ከምድርም ፣ ከሰማይም የተቀረጸ ምስል አታድርግ ያለ ሙሴ ስለምን ይህንን አደረገ? እጅግ የታመንከው የእግዚአብሔር አገልጋይ ሙሴ ሆይ የከለከልከውን ነገር ራስህ እየሠራህ ነውን? ‘የተቀረጸ ነገር አታድርግ’ ያልህ አንተ ፣ የጥጃ ምስል የሰባበርህ አንተ የናስ እባብን እንዴት ሠራህ? ያውም በምሥጢር ሳይሆን በገሐድ ነበረ!’ (Severian Bishop of Gabala , Homily on the Serpent pg 56)

ነገሩ ወዲህ ነው ፤ በመጀመሪያ ወደ ማብራሪያው ሳንሔድ ‘የተቀረጸ ምስል ለአንተ አታድርግ’ የሚለው ትእዛዝ ራሱ የተጻፈው በተቀረጸ ምስል ላይ መሆኑን በማስተዋል እንጀምር፡፡ ትእዛዛቱ የተጻፉት ከድንጋይ በተቀረጸ ጽላት ላይ ሲሆን የሚቀመጡት ደግሞ ከግራር እንጨት ተሠርቶ በወርቅ በተለበጠና ከወርቅ ተቀጥቅጠው የተሠሩ ኪሩቤል ያሉበት ታቦት ውስጥ ነበር፡፡ ስለዚህ የተቀረጸ ምስል ለአንተ አታድርግ የሚለውን ቃል እያነበብን ያለነው ከተቀረጸ ምስል ውስጥ ባገኘው በተቀረጸ ሰሌዳ ላይ የመሆኑን ምፀት (irony) እንደ ዋዛ አናልፈውም፡፡ ቃሉ የተጻፈበት ፊደልም ቢሆን ሌላው በጣት የተቀረጸ ነገር መሆኑም የሚዘነጋ ነገር አይደለም፡፡

       እግዚአብሔር ‘የተቀረጽ ምስል ለአንተ አታድርግ’ ብሎ ያዘዘውን ትእዛዝ ግን ብዙዎች ከምስሉ ጀምረው አነበቡት እንጂ ቃሉ የሚጀምረው ‘ከእኔ በቀር ሌላ አማልክት አይሁኑልህ’ በሚል ነው፡፡ ይህም ማለት ‘ሌላ አምላክ አለ ብለህ አትመን ፤ ይህንን አምነህም የተቀረጸ ምስል ለአንተ አታድርግ ፣ አትስገድላቸው አታምልካቸውም’ ብሎ ከጣዖት አምልኮ እንድንርቅ ያዘዘው ትእዛዝ ነው፡፡ በራሱ ፈቃድ እንዲሠሩ ያዘዛቸው ሁለቱ ኪሩቤልም ‘በእግዚአብሔር ሥዕል የተሣሉ’ (ይሣሉ ብሎ ያሣላቸው) ሲሆኑ አምላክ ናቸው ተብለው ሊመለኩ አይደለምና የላይኛው ትእዛዝ እነርሱን አይመለከትም፡፡ የናሱን እባብም ኃይሉን ሊገልጥበት ወድዶ አሠራው እንጂ ይመለክ ብሎ አላሠራውም፡፡ በኋላ ዘመን የናሱን እባብ እንደ አምላክ ቆጥረው ከሐውልቶች መካከል አቁመው ያመለኩትን ደግሞ ራሱ እንዲሰባበርባቸው አድርጓል፡፡ (2 ነገሥ. 18፡4)

ይህ ሁሉ የሚያሳየን የተቀረጸ ምስል ሁሉ ጣዖት እንዳልሆነ ፤ በተመሳሳይ እንጨት ፣ በተመሳሳይ ወርቅ ቢሠራ እንኳን የተሠራበት ዓላማ እንደሚለየው ፣ እግዚአብሔርን ለማምለክ የተሠራ ታቦት እግዚአብሔርን ለመተካት ከተሠራ ጣዖት ጋር ልዩነት እንዳለው ነው፡፡     

       የታቦትንና የጣዖትን ልዩነት በተመለከተ የፍልስጤም ሰዎችን ያህል ግን እውቀት ያለው ያለ አይመስልም፡፡ ፍዳቸውን አይተው ታቦትን ከጣዖት የለዩ እነሱ ናቸው፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው ፦     

       በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በእግዚአብሔር ታቦት ፊት ብዙዎች በግንባራቸው ተደፍተው ስለመስገዳቸውተጽፎአል:: መስፍኑ ኢያሱ በእግዚአብሔር ታቦት ፊትሰግዶአል:: የእስራኤል ሽማግሌዎችም ሙሉ ቀን በታቦቱፊት ወድቀው ምሕረት ለምነዋል:: (ኢያ. 7:6) በታቦት ፊት ከሰገዱ ሁሉ ግን  እጅግ በጣም የሚያስደንቀውከፍልስጤማውያን ዘንድ የታየው ሰጋጅ ብቻ ነው::
ዳጎን ይባላል:: ዳጎን ሰው አይደለም:: ደህና አናጢ እጅ የገባ የፍልስጤማውያን ዛፍ ነው፡፡ ፍልስጤማውያን ከእንጨት ጠርበው ያቆሙት ሰው ሠራሽ አምላክ ነው::አይሰማም አይለማም:: አይበላም አይጠጣም::። ለክብሩ መቅደስ ተሠርቶለት ሰዎች በስሙ እየተሰየሙለት (አብደናጎ ገብረ ዳጎን ማለት ነው እንዲል) ይኖራል::

       ዳጎን ተንቀሳቅሶ ባያውቅም ታቦተ ጽዮን ተማርካ አጠገቡ ስትመጣ ግን ተንቀሳቀሰ:: ፍልስጤማውያን ዳጎንን ከታቦተ ጽዮን ጋር እኩል አድርገው አስቀመጡት::በማግሥቱ ሲመጡ ግን ሌላ ነገር ጠበቃቸው::  ‘እነሆም፥ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በምድር ላይ በግምባሩ ወድቆ ነበር ፤ ዳጎንንም አንሥተው ወደ ስፍራው መለሱት" 1ኛ ሳሙ.5:3

       አይሰሜ አይለሜው ዳጎን በታሪኩ ቁምነገር ሠርቶ አያውቅም ነበር:: በታቦተ ጽዮን ፊት ሰግዶ ማደሩ ግን ብቸኛው ቁምነገሩ ነው:: ታቦትን ከጣዖት እኩል አድርገው ለሚያስቡ እና ጎን ለጎን ላስቀመጡት የአዛጦን ሰዎች"የእግዚአብሔር ታቦት ይኼ ነው እኔ ግን ጣዖት ነኝ" ብሎበተግባር አሳያቸው:: ለእርሱ ሲሰግዱ ለነበሩት ሰዎች ስግደት የሚገባው በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እንደሆነ ሰግዶ አሳያቸው::  በእውነት ዓይን እያለው የማያየው ፣ ጆሮ እያለውየማይሰማው ጣዖት እንኩዋን የገባው እውነት ከብዙዎች ተሰውሮ ታቦትን ጣዖት ሲሉ ማየት ያሳዝናል::

"ታቦትን ጣዖት ስትሉ እኛ እንደሰማን ፍልስጤማውያን እንዳይሰሙ፣ ዳጎን እንዳይሰማችሁ” ያሰኛል::  የአዛጦን መቅደስ ታቦት ገብቶበት እንኳን አልተቀደሰም:: የእግዚአብሔር ታቦት ደግሞ ጣዖት ቤት ገብቶ አልረከሰም:: ታቦት ቢማረክ ቢሸጥ ቢለወጥ ታቦትነቱን አያስቀረውም:: እግዚአብሔርም ኃይል የለውም አይባልም:: ልብ አድርጉ ይህ ሁሉ ታሪክ የሚሆነው የእንስሳ ደም ይረጭበት በነበረው በኦሪት ታቦት ላይ ነው::የክርስቶስ ደም የሚፈስስበት ሥጋው የሚፈተትበት አልፋና ኦሜጋ የሚል ስሙ የሚጻፍበት የሐዲስ ኪዳኑ የመሠዊያ ታቦትማ ምንኛ እጥፍ ክብር ይገባው ይሆን? ዳጎን ለዚያኛው ታቦት ከወደቀ ለዚህኛው የቁርባን ጠረጴዛ እንዴት ይሰባበር ይሆን?

       ታቦትን ከጣዖት አጠገብ የማስቀመጥ “ፍልስጤማዊ አባዜ” ያለበት ሰው ግን ይህን ለመረዳት ይቸገራል:: "ዳጎንም እንጨት ታቦተ ጽዮንም እንጨት" ይልሃል:: ሁለቱም እንጨት ነው ነገር ግን ታቦተ ጽዮን እግዚአብሔር ያደረባት ስትሆን ዳጎን ሰይጣን የሰፈረበት ነው:: "የአሕዛብ አማልክት ሁሉ አጋንንት ናቸውና" መዝ. 96:5

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

30 Nov, 12:16


ሙሴ የያዘውን በትር የግብፅ ጠንቋዮች ይዘውት ነበር::ሁለቱም እባብ ሆነ ልዩነቱን ግን የሙሴ በትር የአስማተኞቹን ዕባብ ውጣ አሳየች:: "ያም በትር ነው ይሄም በትር ነው" ካልከኝ ፈርዖን ይታዘብሃል:: ጌታ የለበሰውም ቀሚስ ነው ፤ ሕዝቡ የለበሱትም ቀሚስ ነው:: በሕዝብ መካከል እንደ እባብ እየተሳበች በብዙ ቀሚሶች እየተዳሰሰች መጥታ የመሲሑን ቀሚስ ስትነካ ደምዋ ቀጥ ላለላት ሴት "ቀሚስ ቀሚስ ነው" በላትና ትመልስልህ::

አዎ ዳጎንም ታቦተ ጽዮንም የተቀረጸ ምስል ናቸው:: ነገር ግን ታቦት የእግዚአብሔር ዙፋን ሲሆን ጣዖት ግን በእሳታዊ ዙፋኑ ፊት እንድ ማገዶ የሚሰባበር  እንጨት ነው፡፡ ታቦትን ከጣዖት ጋር ከመመደብ ይሠውረን:: አንድም ታቦት ሰውነታችንን ከዳጎን ኃጢአት ጋር ከማስቀመጥ ይሠውረን::

‘ብርሃን ከጨለማ ምን ኅብረት አለው? ክርስቶስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስም ከጣዖት ጋር ምን መጋጠም አለው’ 2ቆሮ. 6፡14-16

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

30 Nov, 12:16


+ ታቦትን ከጣዖት ጋር አታስቀምጡ +

.እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ አለው ፦ በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ። አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም››(ዘጸ. 20፡4)

ይህንን ትእዛዝ በእሳት ቀለም የጻፈበት ድንጋይ ሳይደርቅ እግዚአብሔር ለሙሴ ሌላ ትእዛዝ አዘዘው ፦ ‘ሁለት ኪሩቤል ከተቀጠቀጠ ወርቅ ሥራ’ (ዘጸ. 25፡18) እግዚአብሔር ለሙሴ ምን እያለው ነው? ‘የተቀረጸ ምስል ለአንተ አታድርግ’ ካለው መልሶ የሁለት ኪሩቤል ‘የተቀረጸ ምስል ማሠራቱ ለምንድን ነው?’ መርቅያን የተባለው ጸረ ብሉይ ኪዳን የነበረ ውጉዝ ይህንን ተቃርኖ በመጥቀስ የብሉይ ኪዳኑ እግዚአብሔርን ክብር ይግባውና ‘በሃሳቡ እንደሚወላውል’ አድርጎ ሐሰትን ተናግሯል፡፡ እውን እግዚአብሔር ‘የተቀረጸ ምስል አታድርግ’ ያለውን የራሱን ቃል ‘ታቦት ሥራ ፣ ኪሩቤልን ቅረጽ’ ሲል እየጣሰው ይሆን?  

ታሪኩ በዚህ አላበቃም ፤ እስራኤላውያን ‘የወርቅ ጥጃ ምስል’ ሰርተው ሲያመልኩ እግዚአብሔር አይቶ ቁጣው ነደደ ፤ ቀሠፋቸውም፡፡ (ዘጸ. 32፡4) ቆይቶ ደግሞ ‘እግዚአብሔርም ሙሴን፦ እባብን ሠርተህ በዓላማ ላይ ስቀል የተነደፈውም ሁሉ ሲያያት በሕይወት ይኖራል አለው’ (ዘኁ. 21፡8) ነገሩ እንዴት ነው? ከወርቅ ጥጃ መሥራት ጥፋት ከሆነ ከነሐስ እባብ መሥራት እንዴት ልክ ሊሆን ይችላል?

      

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

30 Nov, 10:12


እንኳን ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
✍️ኅዳር 21 ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል ነው ብለን በተለየ መልኩ የምናከብርበት ምክንያት፡-

➩ በብሉይ ኪዳን ታቦተ ጽዮን የፈጸመችውን ልዩ ልዩ ገቢረ ተአምራትን ለማሰብ፤

➩ ቀዳማዊ ምኒልክ ከዐሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል የበኲር ልጆች ጋር ሊቀ ካህናቱን አዛርያስንና ታቦተ ጽዮንን ይዞ አክሱም የደረሰበት ዕለት በመሆኑ፤

➩በሦስት መቶ ሠላሳ ዓመተ ምሕረት በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግሥት ክርስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ይሁን ተብሎ ዐዋጅ የታወጀበት፣

➩ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ ምሳሌ ራእይ ያየበት፤

➩ነቢዩ ሕዝቅኤል በተቆለፈች ቤተ መቅደስ
ዕዝራ በቅድስት ሀገር ምሳሌ ራእይ ያየበት፤

➩ አብርሃና አጽብሃ በወርቅና በዕንቁ ያሠሩት ባለ አሥራ ሁለት ክፍል ቤተመቅደስ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዮዲት ጉዲት አብያተ ክርስቲያናትን ስታቃጥል ታቦተ ጸዮንን ይዘው ወደ ዝዋይ ሐይቅ ከተሰደዱ በኋላ ዘመነ ሰላም ሲጀመር አክሱም በነበሩ ካህናት አስታዋሽነት ከዝዋይ ወደ አክሱም የገባችበት ዕለት በመሆኑ በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ከፍ ባለ መንፈሳዊ በዓል እናከብራለን፡፡

✍️የወላዲተ አምላክ አማላጅነት የቅዱሳን ተራዳኢነት ከእኛ አይለየን፡፡
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

29 Nov, 17:55


ውጪ ለምትገኙ እና በOnline መማር ለምትፈልጉ

*የዘወትር ጸሎት
*ውዳሴ ማርያም
*አንቀጸ ብርሃን
*መልክአ ማርያም
*መልክአ ኢየሱስ
*ንባብ
*ዳዊት
*ውዳሴ ማርያም ዜማ
@mahtot2 ላይ  ይፃፉልን

ይደውሉልን
+15092943369
+15095058383

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

29 Nov, 17:51


እግዚአብሔር አምላክ ይጠብቃችሁ በእውነት ክብር ያድልልን ሰው አስራቱን መባአውን ሲሰጥ የጎደለበት የሚመስለው አለ ይህ ግን ስህተት በጭራሽ መድኃኔዓለም አትርፎ ይሰጣል እንጂ አጉድሎ አያውቅም።
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

28 Nov, 17:28


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ መታሰቢያ ሐውልት ሊቆምላቸው ነው።

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

28 Nov, 07:52


ጥንቃቄ
ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች በትናንትናው ዕለት አንድ ሁለት የስልክ ጥሪዎችን ተቀብዬ አውርቼ ነበር።ለቤተክርስቲያን እንደዚህ ዓይነት ነዋየ ቅዳሳት፣ገንዘብ ልከን ነበር አልደረሰም ወይ የሚል ነበር የጠየቁኝ ወደ እኔ የመጣም የለም ወደ ገዳሙም የደረሰ የለም ።ከአሁን በፊት ገንዘብ በካሽ በፍጹም አትስጡ ብዬ ነበር ።መርዳት የሚያስፈልግ ከሆነ

፩ኛ) የገዳሙን አካውንት አስቀምጣለሁ
፪ኛ)ለአገልግሎት የሚያስፈልግ ዕቃ ነዋየ ቅድሳት ካለ በዝርዝር በዚህ ገጽ እልካለሁ።
ከዚህ ውጭ ለሚሆን ማንኛውም ነገር ለራሳችሁ ጥንቃቄ ታደርጉ ዘንድ በመድኃኔዓለም ስም አደራ እላለሁ።በማንም ወጠምሻ በቤተክርስቲያን ስም እንዳትበሉ ።
@mahtot2 ላይ ይፃፉልን
ዲ/ን ኤርምያስ
0912494703
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

25 Nov, 18:51


ጾመ ነቢያት 40 ቀን ሆኖ ሳለ ለምን አሁን 44ቀን እንጾማለን??????
40 ነቢያት የጾሙት
3 ጾመ አብርሃም ሶርያዊ (ጾመ አስቴር )
1 የገሃድ ጾም
40+3+1=44


ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

25 Nov, 15:20


ዘማሪ ሐዋዝ ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን መመለሱን በቆየባቸው ዓመታት መጸጸቱን ንስሐ መግባቱን ስንሰማ ደስ አለን ።በጋሻውንም የተጸበልክበት ጠበል ቦታ ብትነግረው አንዲት የባዘነች ነፍስን መለስክ ማለት ነበር በርታ።

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

23 Nov, 15:30


እሑድ ጾም ነው!

ጾመ ነቢያት የሚገባው እሑድ ህዳር 15 ሲሆን: የጾም ማሰሪያ ቅዳሜ ነው:እሑድ ከጥሉላት ምግቦች እንጾማለን።

እንደ ቀኖናም ጾም ሁሉ ሰኞ ይገባል የሚል አዋጅ የለም። ግዴታ ሰኞን ጠብቀው የሚገቡ አጽዋማት ነነዌ: ሁዳዴ(ዓቢይ ጾም): ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) ብቻ ናቸው። ሌሎች አጽዋማት በሰኞ ሊገቡም ላይገቡም ይችላሉ።ይህ ጾም ደግሞ ያለ ተውሳክ የሚወጣ ስለሆነ ቀንን እንጂ ዕለትን አይጠብቅም።

ይህ ጾም የአጽዋማት ሁሉ መሠረት ነው። የተስፋ: የሱባኤ ጾም ነው: ከአዳም እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ያሉ ቅዱሳን የጮሁት ጩኸትም ነው። የሌሎች አጽዋማት መወለድ በዚህ ጾም ምክንያት ነው።

ነቢያት የአምላክን በሥጋ መገለጥ: የንጉሡን ከድንግሊቱ መወለድ ተስፋ በማድረግ ጾመውታል: በርግጥም ተስፋቸው ተፈጽሞ ጌታችን ስለእኛ ከድንግል ማርያም ተወልዷል: በጨለማ ለምንኖር የማይጠፋ ብርሃን በራልን:ወንጌል ወይም የምስራች መባሉም ዋነኛ ምክንያት ይህ ነው።

ታዲያ ለምን እንጾመዋለን? ጌታ አንዴ ተወልዶ የለም ወይ? የሚል ጥያቄ ሊነሣ ይችል ይሆናል:መልሳችን ጌታ ኢየሱስ በልባችን ገና ስላልተወለደ ነው! የሚል ይሆናል።

ባዶ ሆድ ከመሆን እንዲሁ ከመራብ ከፍ ያለ ጾም ያርግልን :ልባችንም ቤተልሔም ይሆን ዘንድ ፈቃዱ ይሁን!

ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

23 Nov, 13:08


እንኳን አደረሳችሁ ጾመ ነቢያት ነገ ይጀምራል ።

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

22 Nov, 16:53


አንዲት እህታችን አስራቷን ለእጓ ደብረ ምሕረት ይሁንልኝ በማለት በየወሩ ከሰጣት በመስጠት ታስባርካለች እግዚአብሔር ይለመንሽ ፣ሰላምና ጤናን ይስጥሽ።ውድ ማኅበረ ምዕመናን የጾመ ነቢያት የቁርስ ግምት ዋጋ ለእጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ይሁንላችሁ።

EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን  +15095058383 =አሜሪካ ለምትገኙ
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @mahtot2 ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

21 Nov, 19:17


በገንዘብ ለምትበጣበጡ በአገልግሎት ለምትመስሉኝ ካህናት ይቺን video ትደርሳችሁ ዘንድ ጋበዝኳችሁ ።

https://youtu.be/WngGtWEeINw?si=ZsYiu6RXgsQHk1ME

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

21 Nov, 07:16


ከላይ ስትሆን(ገንዘብ ሲኖርህ) ሁሉም ሰው ወዳጅህ ነው ልጠፍጠፍልህ ልነጠፍልህ ነወር ነወር ና ተቀመጥ ብሎ የሚነሳልህ ብዙ ነው የሰው ልክ ማለት እሱ አይደለም የወዳጅነትህ ልክ መሰረቱ ከታች ሆነህ  ነው  ።አዋርዶ ከፍ የሚያደርግህ ሌላ ውርደት ስላጣልህ ነው ።ዝቅ ከአልንበት ዝቅ ብሎ የሚያነሳ ምንኛ ክቡር ነው።

ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

21 Nov, 03:40


ቅዱስ ሚካኤል የሚከብርበት ፫  ምክንያቶች

፩) በዓለ ሲመቱ(የተሾመበት)፣

፪) በእነ ዱራታኦስ እና ቴዎብስታ ቤት የተገለጠበት እና ቤታቸውን የባረከበት ፣

፫) ህዝበ ፳ኤልን ከግብጽ እየመራ ወደ ፳ኤል ያስገባበት።


ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

20 Nov, 18:49


በድካም ውስጥ ብትሆንም ተስፋ አትቁረጥ፤ ተስፋ መቁረጥ ወደከፋ ደረጃ ከሚያስገባህ ባለህበት ብትቆይ ይሻልሃልና።

ብጹዕ አቡነ ሺኖዳ
ሳልሳዊ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

20 Nov, 09:47


ይህ ፎቶ ሾብ አይደለም እውነት ነው !!
✍️..የሮማ ካቶሊክ ያልተገባ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን መፍቀዷ ብቻ አይደለም የሴት ካህናትና ጳጳሳትም እያለማመደች ነው። የሮማ ፓፕ ድፍረት ወደ ሌሎች አህጉር እየተስፋፋ ሴቶች ካህንና ጳጳስ መሆን አለብን ጥያቄ ተስፋፍቷል። ይህ ጉዳይ እኛን ይጠብቀን


Dn Ermias

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

19 Nov, 21:33


እመቤቴ ማርያም ጠጅ እያማረሽ
ማር አትይውም ወይ ሲቆርጥ ልጅሽ

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

19 Nov, 20:25


▶️፲፩. ወራት የባሰባት ሴት ማለት ምን ለማለት ነው? እንዲሁም መካኗ ሰባት ወልዳለች ይላልና ሐና የወለደቻቸው ስንት ናቸው?

✔️መልስ፦ ወራት የባሰባት ሴት ማለት መከራ የተደራረበባትና በዚህም ምክንያት ያዘነች ሴት ማለት ነው። ሐና ከሳሙኤል በኋላ ሦስት ወንዶች ልጆችንና ሁለት ሴቶች ልጆችን ወልዳለች። ሳሙኤል ምስፍናን ከክህነት አንድ አድርጎ ይኖር ስለነበር ስለሁለት ተቆጥሮ ነው መካኗ ሐና ሰባት ወልዳለች የተባለው። በሌላ አገላለጽ ሰባት በዕብራውያን ፍጹም ተብሎ ይተረጎማል። ስለዚህ ፍጹም ደግ ልጅ ሳሙኤልን ወለድኩ ስትል ሐና መካኗ ሰባት ወልዳለች ብላ ስለራሷ ተናግራለች።


መጋቤ ብሉይ በትረ ማርያም አበባው


@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

19 Nov, 20:25


▶️፩. "ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ" ይላል። በዚህ አገባብ ቀንድ የተባለ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ የሳሙኤል እናት የሐና እንደ በሬ እንደ ላም ቀንድ ነበራት ለማለት አይደለም። በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ጊዜ ቀንድ እየተባለ የሚጠራ ሥልጣን ነው። ስለዚህ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ ማለቷ ሥልጣኔ ከፍ ከፍ አለ ለማለት ነው።

▶️፪. "ስለዚህም የዔሊ ቤት ኃጢአት በመሥዋዕትና በቍርባን ለዘላለም እንዳይሠረይለት ለዔሊ ቤት ምያለሁ" ይላል (1ኛ ሳሙ.3፥14)። ይህ ነገር ከእግዚአብሔር መሓሪነትና ይቅር ባይነትጋ አብሮ ይሄዳል ወይ ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ የእግዚአብሔር መሓሪነት አያጠያይቅም። በባሕርይው ቸር መሓሪ እግዚአብሔር ብቻ ነው። የዔሊ ወገኖች ከበደላቸው ቢመለሱ እግዚአብሔር ይቅር ይላቸዋል። ነገር ግን እንደማይመለሱ አውቆ አይሠረይላቸውም አለ።

▶️፫. "የእግዚአብሔርም ታቦት ተማረከች፥ ሁለቱም የዔሊ ልጆች አፍኒንና ፊንሐስ ሞቱ" ይላል (1ኛ ሳሙ.4፥11)። በዚህ ዘመን ብዙ አብያተ ክርስቲያናት በአክራሪ ኃይሎች ይቃጠላሉ፤ ታቦታትና ንዋየ ቅድሳት ይዘረፋሉ፤ አገልጋይ ካህናት ይገደላሉ። አንዳንድ ሰዎች እንዴት ታቦት ካህን ባልሆነ ያውም በማያምን ሰው እጅ ይያዛል? እውነት የምትሰግዱለት ታቦት የሆነ ኃይል ካለው ለምን አይቀሥፍም? ወይስ  ለምን ሌላ ተአምር ሠርቶ አያጠፋቸውም? ይላሉና ከዚህ ጥቅስ ተነሥተው ቢያብራሩልኝ።

✔️መልስ፦ እግዚአብሔር ፈታሒ (ፈራጅ) ብቻ ሳይሆን መሓሪም ነው። አንድ ሰው አጥፍቶ ሳለ እንኳ ወዲያው አያጠፋውም በንስሓ ይመለስ ዘንድ በድሎም ዝም ይለዋል። የእርሱ ማደሪያ የሆነው ታቦት ብቻ ሳይሆን እርሱን ራሱን ኢየሱስ ክርስቶስን ይሁዳ ስሞ ሲሸጠው ሲሰቅሉት እንደሚታረድ በግ ዝም እንዳለ ተገልጿል። ይህ ሁሉ የእግዚአብሔርን መሓሪነት ሰው እንዲረዳ ነው። ታቦተ ጽዮን መማረኳ ስለሁለት ነገር ነው። አንደኛ እስራኤላውያን ስለበደሉ በእርሷ መማረክ አዝነው ንስሓ እንዲገቡ ነው። ሁለተኛ ተማርካ የአሕዛብን አማልክት እነዳጎንን እንድትሰባብርና አሕዛብ የሚያመልኳቸው አማልክት የእጅ ሥራዎች መሆናቸውን አሕዛብ እንዲረዱ ነው። ስለዚህ ታቦት የሚሰርቅ ሰው ያልተቀሠፈ እግዚአብሔር መሓሪ ስለሆነ የንስሓ እድሜ እየሰጠው እንጂ ወዲያው ማጥፋት አቅቶት እንዳልሆነ ሊረዳው ይገባል።

▶️፬. "የእግዚአብሔርም ሰው ወደ ዔሊ መጥቶ አለው። እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። በግብጽ በፈርዖን ቤት ባሪያ ሳለ ለአባትህ ቤት ተገለጥሁ" ይላል (1ኛ ሳሙ.2፥27)። የእግዚአብሔር ሰው የተባለው ነቢይ ነው ወይስ ማነው?

✔️መልስ፦ ስሙ ከዚህ ያልተጻፈ ነቢይ ነው። መተርጉማን በሰው አምሳል ስለታየ ነው እንጂ መልአክ ነው ብለዋል።

▶️፭. "እነሆ፥ ለቤትህ ሽማግሌ እንዳይገኝ፥ ክንድህን የአባትህንም ቤት ክንድ የምሰብርበት ዘመን ይመጣል። በእስራኤል በረከት ሁሉ፥ በማደሪያዬ ጠላትህን ታያለህ በቤትህም ለዘላለም ሽማግሌ አይገኝም። ከመሠዊያዬ ያልተቈረጠ ልጅህ ቢገኝ ዓይንህን ያፈዝዘዋል፥ ነፍስህንም ያሳዝናል ከቤትህም የሚወለዱ ሰዎች ሁሉ በጎልማስነት ይሞታሉ" ይላል (1ኛ ሳሙ.2፥31-33)። ክንድ የተባለ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ክንድ የተባሉ ወገኖች ናቸው። ክንድህን ማለት ወገንህን ማለት ነው፣ የአባትህንም ቤት ክንድ ማለት ደግሞ የአባትህን ወገኖች ማለት ነው። ዘርህን ወገንህን የማጠፋበት ቀን ይመጣል ለማለት የተነገረ ቃል ነው።

▶️፮. "ዔሊም በስፍራው ተኝቶ ሳለ፥ የእግዚአብሔር መብራት ገና ሳይጠፋ፥ ሳሙኤልም የእግዚአብሔር ታቦት ባለበት በእግዚአብሔር መቅደስ ተኝቶ ሳለ" ይላል
(1ኛ ሳሙ.3፥3)። ታቦት ባለበት መቅደስ ውስጥ መተኛት በዛን ዘመን ሥርዓት ነበር? አሁን በዚህ ዘመን ላለን ሰዎችስ በሕንፃ ቤተ ክርስቲያን (በቅኔ ማኅሌት፣ በቅድስት) ውስጥ መተኛት ይፈቀዳል ወይ? አንዳንድ ካህናት ታቦቱ ባለበት መቅደስ ወስጥ ሳይቀር ገብተው የሚተኙ (የሚያንቀላፉ) አሉና ከዚህ ጥቅሰ አንፃር ሥርዓቱን ቢነግሩኝ።

✔️መልስ፦ ሳሙኤል የእግዚአብሔር ታቦት ባለበት በእግዚአብሔር መቅደስ ተኝቶ ነበር መባሉ ከቅጽሩ ውስጥ ሆኖ በዙሪያው ተኝቶ ነበር ለማለት ነው እንጂ በደብተራ ኦሪት ውስጥ ተኝቶ እንደነበረ የሚገልጽ አይደለም። በሕንፃ ቤተክርስቲያን ውስጥ መተኛት ፈጽሞ አይገባም። በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 1 ላይ እንደተገለጸው ቤተክርስቲያን የጸሎት ቤት ናት እንጂ የመኝታ ቤት አይደለችም። በቤተክርስቲያን ውስጥ ሁሉም ንቁሕ ሆኖ ቃለ እግዚአብሔርን በንቃት መከታተል፣ በንቃት መጸለይ ይገባዋል እንጂ መተኛት ፈጽሞ አልተፈቀደም። መቅደስ ውስጥ ገብተው የሚተኙ ካሉም ስሕተት ነው መታረም አለበት።

▶️፯. "የውስጥ አካላቸውን በእባጭ መታ"
ይላልና ትርጓሜው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ የውስጥ አካላቸውን በእባጭ መታ ማለት ብልታቸውን (መሽኛቸውን) በእባጭ መታ ማለት ነው።

▶️፰. "በዚያንም ዘመን የእግዚአብሔር ቃል ክቡር ነበር፤ ራእይም አይገለጥም ነበር" ይላል። ራእይ አይገለጥም ሲል ምን ማለቱ ነው እግዚአብሔር ስዎችን እንዴት ነበር የሚያናግራቸው?

✔️መልስ፦ በዚያን ዘመን እግዚአብሔር ማንንም እንዳላናገረ የሚገልጽ ቃል ነው። በራእይም በሌላም መንገድ ለሕዝቡ አልተገለጠም አልተናገረም ነበር። ስለዚህ በዚያን ወቅት ያናገረው ሰው አልነበረም ማለት ነው።

▶️፱. "ከተሸከሙትም በኋላ የእግዚአብሔር እጅ በታላቅ ድንጋጤ በከተማዪቱ ላይ ኾነች። ከታናሹም እስከ ታላቁ ድረስ የከተማዪቱን ሰዎች መታ ዕባጭም መጣባቸው" ይላል። ማን ነበር ታቦቱን የሚሸከመው?

✔️መልስ፦ ታቦቷን በሠረገላ ስለነበር የሚያደርጓት በሠረገላ አድርገው በላሞች ነበር የሚያስጎትቷት እንጂ በተለየ ታቦተ እግዚአብሔርን የሚሸከም አልነበረም። ወደእስራኤል ስትመጣ ግን ሌዋውያን ይሸከሟት ነበር።

▶️፲. "እግዚአብሔርም ማሕፀኗን ዘግቶ ነበርና ጣውንቷ ታስቈጣት ታበሳጫትም ነበር" ይላል። ጣውንቷ ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ጣውንት ማለት ጎባን ማለት ነው። ለምሳሌ አንዲት ሴት ያገባችውን ባል ሌላ ሴት ብታገባው አንዷ ለአንዷ ጎባን ናቸው ይባላል። የወንድም እንዲሁ ነው። አንዱ ያገባት የነበረችን ሴት ሌላ ሲያገባት ጎባን ሆኑ ይባላል።

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

19 Nov, 16:30


ዛሬ ታክሲ ውስጥ እያለሁ ከአጠገቤ ያለ ሰው ብዙ ያወራል እኔን ስላልመሰለኝ አሐቲ ድንግልን እያነበብኩ ነበርና ዝም አልኩት አንድ ቃል ግን እንዲህ አለኝ ከአንድ ታዋቂ ሰው የተዋስኩትን ሀሳብ ብሎ ነው የጀመረልኝ One best book is equal to hundred good friends but one good friend is equal to library አለኝ ያው የፈረጅኛ አፍ ብዙም አይደለሁም ግን ማንበብ ጥሩ ነው ለማለት የፈለገ መሰለኝና ልክ ነው አልኩት ።

ማንበብ ማንበብ ነገም ዛሬም ማንበብ መልካም ነው እላችኋለሁ።

ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

19 Nov, 07:36


የዋህነት ልበለው አለማወቅ ?
አንቺ ዓለም አንቺ ዓለም የማይልሽ የለም አለ ሰውዬው ጉድ እኮ ነው!
የካህናት ሩጫ ግን ይዘጋጅልን 😂እኔ አንደኛ የምወጣ ይመስለኛል!
ለወንጌል አልፋጠን ካልን ይህ የሚሻል አይመስላችሁም ?
ፖሊስም ከነ ሙሉ ትጥቁ እንደማይሮጥ ኹሉ ፥ ካህንም ከነ ቆቡ አይሮጥም፤
እውቅና ለማግኘት ሲባል ራስን ማጣትም አለ !
ኅሊናዎ ግን እንዴት እሺ አለዎት ??
አይ የዋህነት .!!!

ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

19 Nov, 07:05


No friend no problem
No girlfriend no boyfriend no problem
No cash big problem አለ ትረምፕ አለኝ አንድ ጓደኛዬ እንዴ ትክክል አይደል እንዴ ታዲያ አልኩት እየውልህ የችግሮች ሁሉ ችግር No health ,ነው አለኝ እና ጓደኛዬ አሜሪካን ቢመራ ብዬ ለማሾፍ አስቤ እውነትም ገንዘብ ሆስፒታል ሊገነባ ይችላል ጤና ማለት ታሞ ሆስፒታል መግባት አይደለም ጤና ማለት ከጭንቀት ፣ከአካላዊ እክል ፣ከሁሉም ነገር ጤናማ መሆን ነው ፣ጤናማ ከሆንክ ሁሉም በጊዜው ይኖርሃል ።ጓደኛዬ አንተ ትክክል ነህ ።


ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

16 Nov, 01:31


'የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና ተጠንቀቁ፥ ከመጎምጀትም ሁሉ ተጠበቁ '

በ40 ዓመቷ በጨጓራ ካንሰር ከመሞቷ በፊት በዓለም ታዋቂው ዲዛይነር እና ደራሲ “ክሪስዳ ሮድሪጌዝ” እንዲህ ስትል ፅፋለች።
1. ጋራዥ ውስጥ የአለማችን ውድ መኪና ነበረኝ፣ አሁን ግን በዊልቸር መንቀሳቀስ አለብኝ።
2. ቤቴ ሁሉንም አይነት ብራንድ ያላቸው ልብሶች፣ ጫማዎች እና ውድ እቃዎች ይሸጣል፣ አሁን ግን ሰውነቴ በሆስፒታሉ በተዘጋጀ ትንሽ ጨርቅ ተጠቅልሏል።
3. በባንክ ውስጥ ብዙ ገንዘብ አለኝ። አሁን ግን ከዚህ መጠን ምንም አልጠቀመኝም።
4. ቤቴ እንደ ቤተ መንግስት ነበር አሁን ግን በሆስፒታል ውስጥ በሁለት አልጋዎች ተኝቻለሁ።
5. ከባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ወደ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል. አሁን ግን በሆስፒታል ውስጥ ከአንድ ላብራቶሪ ወደ ሌላ በመንቀሳቀስ ጊዜዬን አሳልፋለሁ
6. በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ፊርማ ሰጥቻለሁ ነገርግን በዚህ ጊዜ የሕክምና መዝገቦች የእኔ ፊርማ ናቸው።
7. ፀጉሬን ለመስራት ሰባት ፀጉር አስተካካዮች ነበሩኝ ፣ አሁን ግን - በራሴ ላይ አንድ ፀጉር የለኝም።
8 .በግል ጄት ላይ፣ የትኛውም ቦታ መብረር እችላለሁ፣ አሁን ግን ወደ ሆስፒታል በር ለመራመድ ሁለት እርዳታዎች ያስፈልጉኛል።
9. ምንም እንኳን ብዙ ምግቦች ቢኖሩም, አሁን የእኔ አመጋገብ በቀን ሁለት ክኒን እና ምሽት ላይ ጥቂት የጨው ውሃ ጠብታዎች ናቸው::
10. ይህ ቤት፣ ይህ መኪና፣ ይህ አውሮፕላን፣ ይህ የቤት ዕቃ፣ ይህ ባንክ፣ ብዙ ዝናና ዝና፣ አንዳቸውም አይመጥኑኝምነበር። አሁን ግን ከእነዚህ ውስጥ አንዳቸውም ሊደርሱልኝ እና ሊጠቅሙኝ አልቻሉም፡፡
“የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና ተጠንቀቁ፥ ከመጐምጀትም ሁሉ ተጠበቁ ..🤔
ምንጭ :-ጋዜጠኛ ጌጡ እንደፃፈው
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

14 Nov, 18:15


#ኅዳር_6
#ደብረ_ቁስቋም

ኅዳር ስድስት በዚህች ዕለት ክብርት እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር ከስደት በሚመለሱበት ጊዜ ደብረ ቁስቋም ገብተው ካገኛቸው ድካም ዐረፉ፡፡

አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ከስደት በተመለሰች ጊዜ እንዲህ ሆነ፡- የብርሃን እናቱ ክብርት እመቤታችን ልጇን ይዛ ከእነ ዮሴፍ ጋር ወደ ምድረ ግብፅ ስትሰደድ ግብፅ ደርሰው በዚያ ቢቀመጡም ነገርን ግብፅ አልተመቸቻውም፡፡ ሕዝቡም በሰላም አልተቀበላቸውም፡፡ እንዲያውም በምድረ ግብፅ ብዙ ተሠቃይተዋል፡፡ ከግብፅም ተነሥተው ወደ ኢትዮጵያ በመጡ ጊዜ ግን ኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ በሰላምና በፍቅር ተቀበላቸው፡፡ ከመንገዱና ከርሃብ ጥሙ ጽናት የተነሣ እጅግ ደክማለችና የኢትዮጵያ ሰዎች እመቤታችንን አይተው እጅግ አዘኑላት፡፡ ‹‹ይህችስ የነገሥታት ዘር ትመሥላለች ነገር ግን አንዳች ችግር አጋጥሟት ተሰዳ ወደ ሀገራችን መጥታለች..›› ብለው እንክብካቤን አደረጉላት፡፡ እግራቸውን አጥበው በክብር ማረፊያዎች ላይ አሳረፏቸው፡፡ መልካም መስተንግዶም አደረጉላቸው፡፡ እመቤታችንም ከድካሟ ካረፈች በኋላ ሀገሪቱን በእጅጉ ወደደቻትና የተወደደ ልጇን ‹‹ይህን ሀገርና ሕዝቧን በመላ ወድጃቸዋልሁና በዚህ እስከ መጨረሻው እንኑር›› አለችው፡፡ ጌታችንም ክብርት እናቱን ‹‹ይህች ቅድስት ሀገር ናት፣ በኋለኛው ዘመን የቅዱሳን መነኮሳት ቦታ ትሆናለች፡፡ በውስጧም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እመሰገንባታለሁ፤ የአንቺም ስም ሳይጠራ አይውልባትም›› አላት፡፡

ከዚህም በኋላ ጌታችን ደመና ጠቅሶ በእርሷ ላይ ተቀመጡ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤልም መጣና እየመራቸው መላ ኢትዮጵያን ጎበኟት፡፡ እመቤታችንም ሀገሪቱንና ሕዝቦቿን ወዳቸዋለች ደስም ተሰኝታባቸዋለችና ጌታችን ለክብርት እናቱ ‹‹ይህችን ቅድስት ሀገር አሥራት አድርጌ ሰጠሁሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም እጅግ ተደስታ ‹‹ልጄ አምላኬ›› ብላ አመሰገነችው፡፡ ከዚህም በኋላ ከአንዱ ቦታ ወደ አንዱ ቦታ እየተዘዋወሩ መላዋ ኢትዮጵያን በኪደተ እግራቸው ባረኳት፡፡ ጌታችንም ‹‹በዚህ ቦታ እንዲህ ዓይነት ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል፤ እከሌ የሚባል እንዲህ ዓይነት ቅዱስ ይነሣል…›› እያለ ብዙ ምሥጢራትን ለክብርት እናቱ ነገራት፡፡ ከዚህም በኋላ የስደቱ ዘመን ሲያልፍ ሄሮድስም በመጨረሻ ክፉ አሟሟትን ሲሞት መልአኩ ወደ ገሊላ አውራጃ እንዲመለሱ ነገራቸው፡፡ እመቤታችንም ‹‹ከዚህች ሀገርስ ባንሄድ እመርጣለሁ›› ስትለው የተወደደ ልጇ ግን ‹‹እናቴ ሆይ ጽድቅንና ፈቃድን ሁሉ ልንፈጽም ይገባናል›› ብሎ አጽናናትና ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ሄዱ፡፡

ተመልሰውም ሊሄዱ ሲነሡ የኢትዮጵያ ሰዎች ልዩ ልዩ አምሐ እጅ መንሻ ሰጧቸው፡፡ ልዩ ልዩ ልብሶች፣ ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤ፣ ሽቱ እና ሥንቀቸውን በግመሎች ላይ ጭነው እመቤታችንንና የተወደደ ልጇንም በበቅሎ ላይ አስቀምጠው በክብር ሸኟቸው፡፡ እመቤታችንም ልጇን ታቅፋ በበቅሎ ተቀምጣ በበረሃው በመጓዝ ወደ መጣችበት አገር ሄደች፡፡ ኢትዮጵያንም የሰጧትን ብዙ እጅ መንሻዎች በግመሎች ጭና ይዛ ወደ አገሯ በተመለሰች ጊዜ ከአንድ ባሕር ዳር ደረሰች፡፡ ከዚያም የጀልባውን ባለቤት ‹‹እግዚአብሔርን ስለመውደድ አሻግረኝ›› ብላ ለመነችው፡፡ ባለጀልባውም ‹‹እነሆ ዕቃ የተጫኑ አምስት ግመሎችና ከአንቺ ጋር ከዚህም ሕፃን ጭምር አምስት ሰዎች እመለከታለሁ፣ አንቺ የተቀመጥሽባት በቅሎም አለች፡፡ ጀልባዋም ታናሽ ናት፣ የመቀመጫ ክፍሏም በውስጧ የተሳፈሩት ሰዎችም ተጨናንቀው ነው ያሉት፡፡ ስለዚህ እንዴት ላሻግርሽ እችላለሁ? ነገር ግን እመቤቴ ሆይ! ይቅርታ አድርጊልኝ ይህን በክፋት አላደረግሁትምና›› አላት፡፡

ክብርት እመቤታችንም የጀልባው ባለቤት ሊያሻግራት እንዳልቻለ በተረዳች ጊዜ ‹‹ልጄ ሆይ የእግዚአብሔር ልጅ እንደመሆንህ ይህን ትልቅ ወንዝ ለመሻገር የአምላክነትህን ሥራ ትሠራ ዘንድ እለምንሃለሁ›› ስትል ማለደችው፡፡ ያንጊዜም ጌታችን ክብርት እናቱን ‹‹የወለደሽኝ እናቴ ሆይ! አትዘኝ›› ብሎ አረጋጋት፡፡ ዳግመኛም ‹‹በእኔ ፈቃድ በአባቴ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ካንቺ ሰው ሆኛለሁና ሰው መሆኔንም ከአባቴ በቀር መስተፍሥሒ ከሚሆን ከመንፈስ ቅዱስም በቀር ያወቀ የለም፡፡ ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ ለሁሉም እንደየሥራው እከፍለው ዘንድ እመጣለሁ፡፡ ያችንም ሰዓት የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ የአዳም ልጆችም ቢሆኑም ከእኔና ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስም በቀር የሚያውቃት የለም፡፡ ያንጊዜ ‹ዐመፅን የሚናገር አንደበት ሁሉ ይዘጋል› ብሎ አባትሽ ዳዊት እንደተናገረ እከራከራለሁ የሚል አንደበት እንደድዳ ምላሽ ያጣል›› አላት፡፡

ክብርት እመቤታችን ማርያምም ይህንን ሁሉ ምሥጢር የተወደደ ልጇ የነገራትን ታስተውለው በልቧም ትጠብቀው ነበር፡፡ ጌታችንም አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለክብርት እናቱ ይህንን ከነገራት በኋላ ቀኝ እጁን ዘርግቶ ከወንዙ ማዶ ጢር በሚባል ተራራ ያሉትን ድንጋዮች ጠቀሳቸው፡፡ ያንጊዜም እነዚህ ድንጋዮች እየተገለባበጡ መጥተው እንደ ጀልባ ሆነው በወራጁ ወንዝ ላይ ተንሳፈፉ፡፡ ከዚያም እመቤታችንን ከሕፃኑ ጋር ከነቤተሰቧና ከነጓዟ አሻገረሯት፡፡

እነዚህንም ድንጋዮች ያዩ ሰዎች ሁሉ እጅግ አድንቀው ‹‹ብቻውን ድንቅ ተአምራት ያደረገ፣ እስራኤልን የፈጠረ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን የጌትነቱም ስም የተመሰገነ ነው›› እያሉ አመሰገኑ፡፡ እነዚህም የተባረኩ ሰዎች ወንዙን ከተሻገሩ በኋላ በዚህች አገር ለስምንት ቀን ተቀመጡ፡፡ ከዚህም በኋላ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ስለደረገላት መልካም ሥራ ሁሉ እግዚአብሔርን ፈጽማ እያመሰገነች ወደ አባቷ ወደ ዳዊት አገር ተመለሰች፡፡

ዳግመኛም በኋለኛው ዘመን ጌታችን በዚህ በደብረ ቍስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቶቹን ሰበሰባቸውና ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንን አክብሮ የቍርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወገኖቹ ሰጣቸው፡፡ ለዚህም ነገር የእስክንድርያ አገር ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱሳን አባቶቻችን ቄርሎስና ቴዎፍሎስ ምስክሮቹ ሆኑ፡፡

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን ።

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

13 Nov, 19:35


"ክፉ ዘመን ቢመጣና በቤተክርስቲያን መገልገል ባንችል ቀድሰን የምናቆርበዉ እናንተ ቤት ስለሆነ ክርስቲያኖች ሆይ የምትኖሩበትን ቤት በቅድስና ና በክብር ያዙት፤ ጠብቁት" (ሊቀ ሊቃዉንት ስምዐኮነ መልአክ)
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

13 Nov, 15:33


ውጪ ለምትገኙ እና በOnline መማር ለምትፈልጉ

*የዘወትር ጸሎት
*ውዳሴ ማርያም
*አንቀጸ ብርሃን
*መልክአ ማርያም
*መልክአ ኢየሱስ
*ንባብ
*ዳዊት
*ውዳሴ ማርያም ዜማ
@mahtot2 ላይ ያናግሩን ይፃፉልን

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

13 Nov, 15:29


መታረም ያለባቸው ብሒሎች፦

➽ "እርጉዝ ሴት ቅዱስ ቍርባን መቀበል አትችልም" ማለቱ ልክ አይደለም። ከእርግዝናዋ ጋር ተያይዘው የሚመጡ እንደ ማቅለሽለሽ ፣ ቶሎ ቶሎ ምራቅ መትፋትና ፣ ፈሳሽ ነገር የማያስቸግራቸው ካላኾነ በቀር ።

➽ "ወጣቶች የፈቲው ጾር ስላለባቸው ትዳር ካልያዙ በቀር ቅዱስ ቍርባን መቀበል አይችሉም" ማለትም ስህተት ነው። የፈቲው ጾሩን የሚቋቋሙት በቅዱስ ቍርባን መስሎን።

➽ "ቀን በቀን መቍረብ አይቻልም" ማለትም አይቻልም። ግለሰቡ ቅዱስ ቍርባን እንዳይቀበል የሚያደርግ እንቅፋት ካልገጠመው በቀር ይችላል። ተገኝቶ።

➽ "ካህናት ከኾኑ ካልቀደሱ በቀር ቅዱስ ቍርባን መቀበል አይችሉም" ማለት ስሕተት ነው። ቀዳሽ ኾኖ ከገባ እሰየው። ካልኾነ ግን አይከለከልም።

➽ "ባልና ሚስት ቅዱስ ቍርባን መቀበል ያለባቸው በተመሳሳይ ቀን ብቻ ነው፤ ካልኾነ አይችሉም" ማለትም አይቻልም። አብረው ቢቀበሉ ጥሩ። ኹኔታዎች ካልተመቻቹ ግን {ለምሳሌ አንዱ አካል የሥራ ጫና ውስጥ ከወደቀ} አንዳቸው ሊቀበሉ ይችላሉ። ያልተቀበሉት ደግሞ ሌላ ጊዜ ይቀበላሉ።

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

10 Nov, 10:26


This is our reality

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

10 Nov, 01:59


እግዚአብሔር አምላክ ይጠብቃችሁ በእውነት ክብር ያድልልን ሰው አስራቱን መባአውን ሲሰጥ የጎደለበት የሚመስለው አለ ይህ ግን ስህተት በጭራሽ መድኃኔዓለም አትርፎ ይሰጣል እንጂ አጉድሎ አያውቅም።
EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @sekokaw ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

09 Nov, 21:21


ከአውሬ የተረፈ ፣ታንቆ የሞተ ፣ለጣኦት የተሰዋውን ፣መርዝ ያላቸውን ፣ከእነደሙ የሆነን ፣ በፍጹም እንዳንበላ ተከልክሏል ። አንድ ሰው ከሌላ ባህልና እምነት ቢመጣ ከተጠመቀ ከአመነ ሥጋወደሙን ከተቀበለ ለመዳን የሚያስፈልገው ዋናው ይህ ነው። ይህን ብላ ይህን አትብላ ተብሎ አይገደድም እንደባህሉ እየተመገበ ይኖራል እንጂ
ከዛ ውጪ በኦሪት የነበረ በክርስቶስ ተሽሯል ግዝረት በጥምቀት ፣መስዋዕት በክርስቶስ ተተክቷል ። ይሁን እንጂ ኦርቶዶክሳውያን ሚዲያዎች ስለምታቀርቡት ብትጠነቀቁ ግን መልካም ነው። ምክንያቱም እናንተ በምትጠይቁት ልክ ሳይሆን ሀሳቡ ተቆራርጦ ( ሙሉ ሀሳብ ያልሆነ) ያልጸኑት ጋር ይደርስና ህዝበ ክርስቲያንን ይበትናል።

ዲ/ን ኤርምያስ

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

09 Nov, 20:07


እኒህ ሊቀ ጳጳስ ሲናገሩ ብቻ ነው እንዴ ??እነ ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ፣እነ መምህር ኃይለማርያም (ዘቦሩ ሜዳ ጉባኤ መምህር )ሲያስተምሩ ቃለሕይወት ያሰማልን ሲል የነበር https://www.facebook.com/share/v/17dGVK8Mp1/?mibextid=5SVze0

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

09 Nov, 12:54


የእኒህ ሊቀ ጳጳስ ስህተት ምንድነው በየሚዲያው እንዲህ መነጋገሪያ የሆኑበት ።ኧረ ኦርቶዶክሳዊያን እንረጋጋ በእግረኛው ሚዲያ ከተናገሩት ስህተት የሆነው የትኛው ነው??? የቱ ጋር ይህን ብሉ ይህን አትብሉ ብለው ተናገሩ??እኔ አልገባኝም ።እውነትን በሚደፍሩ አባቶች እውነት እየመጣች ነው ይህን ባሕል እና እምነት የቀላቀለ ሕዝብ ለማንቃት ብዙ ድካም ይጠይቃል ግን የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መምህራን ድምጻችሁን አሰሙን።

@mahtotetonetor2

ዲ/ን ኤርምያስ

@sekokaw

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

09 Nov, 12:31


ዘሳድስ ሣምንት ጽጌ
ሥርዐተ ማኅሌት መጀመሪያ)
ለማንኛውም ወርኃዊ እና አመታዊ ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ
.....................................................
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።

@mahtotetonetor2
መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለአፉክሙ ዘማዕፆሁ ሰላም፤ጽጌያቲሁ ሥላሴ ለተዋሕዶ ገዳም፤መንገለ አሐዱ አምላክ ንዋየ መጻኢ ዓለም፤ወልጡ አምልኮትየ በጸጋክሙ ፍጹም፤እምአምልኮ ጣዖት ግሉፍ አሐዱ ድርህም።
@mahtotetonetor2
ዚቅ፦
አሠርገወ ገዳማት ስን በመንክር ኪን አርአያሁ ዘገብረ ሰሎሞን ጥቀ ኢለብሰ በኩሉ ክብሩ ከመ አሎን ጽጌያት ኢቀደምት ወኢያኃርት :ዓራዛተ ሰርጎ ነሢኦሙ ኢክህሉ ከመ ክርስቶስ መዊሃ
@mahtotetonetor2
ወቦ መልክዓ ሥላሴ(ሌላ)፦
ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወፀ ለሣህል፤እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል፡፡
@mahtotetonetor2
ዚቅ፦
እምሥርወ ዕሤይ ሠሪፃ ዘእምዘርዓ ዳዊት ተወሊዳ ተዓብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር ትቤ ድንግል ሳይዳ ከመ ፍህሶ ቀይህ ከናፍሪሃ ተዓብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር ትቤ ድንግል ሳይዳ ወከመ ሮማን መላትሒሃ ተዓብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር ትቤ ድንግል ሳይዳ ኅብስተ ሕይወት በየማና ተዓብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር ትቤ ድንግል ሳይዳ ወጽዋዓ ወይን በጸጋማ ተዓብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር ትቤ ድንግል ሳይዳ ጸሎታ ወበረከታ ይኩነነ ወልታ
@mahtotetonetor2
ማኅሌተ ጽጌ
ኢየኃፍር ቀዊመ ቅድመ ስእልኪ ወርኃ ጽጌረዳ አመ ኃልቀ፤ዘኢየኃልቅ ስብሐተኪ እንዘ እሴብሐኪ ጥቀ፤ተአምርኪ ማርያም ከመ አጠየቀ፤ጸውዖ ስምኪ ያነሥእ ዘወድቀ፤ኃጥአኒ ይሬሲ ጻድቀ፡፡
@mahtotetonetor2
ወረብ
ኢየኃፍር ቀዊመ ቅድመ ስእልኪ ወርኃ ጽጌ ረዳ አመ ኃለቀ/፪/
ዘኢየኃልቅ ስብሐተ ስብሐተ እንዘ እሴብሐኪ/፪/
@mahtotetonetor2
ዚቅ
እለትነብሩ ተንሥኡ ወእለ ታረምሙ አውሥኡ፤ማርያምሃ በቃለ ስብሐት ጸውዑ፤ቁሙ ወአጽምዑ ተአምረ ድንግል ከመ ትስምዑ፤ጸልዩ ቅድመ ስዕላ ለቅድስት ድንግል ፤መርዓተ አብ ወእመ በግዑ፡፡
@mahtotetonetor2
ወረብ
እለ ትነብሩ ተንስኡ ወእለ ተረምሙ አውስዑ ማርያምሀ በቃለ ስብሐት ፀውኡ/፪/
ጸልዩ ቅድመ ስዕል ለቅድስት ድንግል እመ በግ ወመርዓተ አብ/፪/
@mahtotetonetor2
ማኅሌተ ጽጌ
ለንጉሠ ነገሥት ሰሎሞን ከመ ተፈሥሐ ልቡ፤በዕለተ ወፃእኪ መርዓት ለአንበሳ ትንቢት እምግቡ፤ማዕከለ ማኅበር ፍሡሓን ተአምረኪ ዘይነቡ፤እዜምር ለኪ ጽጌ ሐና ወፍኖተ ነፈርዓፅ እሌቡ፤ከመ ጣዕዋ ሐሊበ ዘይጠቡ።
@mahtotetonetor2
ወረብ፦
እዜምር ለኪ ጽጌ ሐና ወፍኖተ ነፈርዓፅ እሌቡ ፍኖተ ነፈርዓፅ/፪/
ማዕከለ ማኅበር እዜምር ማዕከለ ማኅበር/፪/
@mahtotetonetor2
ዚቅ
ሰሎሞን ይቤላ ለማርያም፤ወለተ ሐና ወኢያቄም፤ ጽጌ ደመና ዘብርሃን።
@mahtotetonetor2
ዓዲ ዚቅ፦
ወትወፅእ እምግበበ አናብስት ፤ እምታዕካ ዘነገሥት እምቅድመ ሃይማኖት ፤ንዒ ርግብ ሠናይት፤ኵለንታኪ ሠናይት አልብኪ ነውር ፤ወኢምንትኒ ላዕሌኪ፤ንዒ ርግብ ሠናይት፤ንዒ ርግብየ።
@mahtotetonetor2
ማኅሌተ ጽጌ
እንዘ  ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ ፣አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣ንዒ  ርግብየ  ትናዝዝኒ  እምላህ፣ወንዒ  ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ
@mahtotetonetor2
ወረብ፦
እንዘ  ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ/፪/
ንዒ ርግብየ ምስለ ገብርኤል ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ሚካኤል/፪/
@mahtotetonetor2
ዚቅ
ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል ምስለ ወልድኪ ፍቁርኪ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ትባርኪ ላዕሌነ
@mahtotetonetor2
ማኅሌተ ጽጌ
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ  ዘየኃቱ፤ዘተጽሕፈ ብኪ  ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤አክሊለ ጽጌ ማርያም  ለጊዮርጊስ ቀጸላ  መንግሥቱ፤አንቲ  ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡
@mahtotetonetor2
ወረብ
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ክበበ ጌራ ወርቅ  ጽሩይ ዘየኃቱ እምዕንቈ ባሕርይ/፪/ 
አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ መንግሥቱ ለጊዮርጊስ መንግሥቱ ለመፍቀሬ አምላክ/፪/
@mahtotetonetor2
ዚቅ፦
አክሊል ዘእምጳዝዮን ተደለወ :ጌራ ባሕሪይ ወቀጸላ ወርቅ ጽሩይ በቤተልሔም ተወልደ እምድንግል በብስራትክሙ መሐይምናን እምአፈ ዮሐንስ ሥርግው ተቀሰመ አፈው ሰባኬ ወንጌል ነዋ በማዕከለ አኃው
@mahtotetonetor2
ማኅሌተ ጽጌ፦
ኅብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወፀዓድዒድ
አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር፤ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር፤ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ ሥሙር፤አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት ወምድር፤ከመ በሕጽንኪ ያሰምክ ፍቁር፡፡
@mahtotetonetor2
ወረብ
ናሁ ተፈጸመ ተፈጸመ ናሁ ማኀሌተ ጽጌ ሥሙር ተፈጸመ ናሁ/፪/
አስምኪ ቦቱ አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት/፪/
@mahtotetonetor2
ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ጥቀ አዳም መላትሕኪ ከመ ማዕነቅ ይግበሩ ለኪ
ኰሰኰሰ ወርቅ፡፡
@mahtotetonetor2
ሰቆቃወ ድንግል
ተመየጢ እግዝእትየ ማርያም ሀገረኪ ናዝሬተ፤ወኢትጎንድዪ በግብጽ ከመ ዘአልብኪ ቤተ፤በላዕሌኪ አልቦ እንተ ያመጽእ ሁከተ፤ለወልድኪ ዘየኃሥሦ ይእዜሰ ሞተ፤በከመ ነገሮ መልአክ ለዮሴፍ ብሥራተ፡፡
@mahtotetonetor2
ወረብ
ተመየጢ ተመየጢ እግዝእትየ ማርያም ሀገረኪ/፪/
ወኢትጎንድዪ በግብፅ በግብፅ ከመ ዘአልብኪ ቤተ/፪/
@mahtotetonetor2
ዚቅ
ተመየጢ ተመየጢ ሰላመ ሰጣዊት
ወንርአይ ብኪ ሰላመ፤ምንተኑ ትኔጽሩ በእንተ ሰላመ ሰጣዊት፤እንተ ትሔውጽ እምርኁቅ ከመ መድበለ ማኅበር፤ሑረታቲሃ ዘበስን ለወለተ አሚናዳብ።
@mahtotetonetor2

መዝሙር ፦
በ፮ ሃሌታ-
ክርስቶስ ሠረዓ ሰንበት፤ክርስቶስ ሠረዓ ሰንበት ወጸገወነ ዕረፍት ከመ ንትፌሳሕ ኅቡረ።አዕፃዳተ ወይን ጸገዩ ቀንሞስ ፈረይ፤ማ- ሰሎሞን ጥቀ ኢለብሰ፤ከመ አሐዱ እምእሉ
@mahtotetonetor2
አመላለስ፦
ሰሎሞን ጥቀ ኢለብሰ/፪/
ከመ አሐዱ እምእሉ/፬/

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

08 Nov, 15:14


ጥያቄ እና መልስ

▶️፩. "በቤተ ፌጎርም አቅራቢያ በናባው ምድር ቀበሩት" ይላል (ዘዳ.34፥6)። ሙሴን የቀበሩት እነማን ናቸው? ከዚያ "እስከዛሬ ድረስ መቃብሩን የሚያውቅ የለም" ይላል (ዘዳ.34፥7)።

✔️መልስ፦ ሙሴን የቀበሩት መላእክት ናቸው። እስከ ዛሬ ድረስ መቃብሩን የሚያውቅ የለም የተባለው ከሰው የሚያውቅ የለም ማለቱ ነው እንጂ የቀበሩት መላእክትስ ያውቁታል። መቃብሩ ያልታወቀውም እስራኤላውያን በዐፅሙ እንዳያመልኩ ነው።

▶️፪. “ከሞትሁ በኋላ ፈጽማችሁ እንድትረክሱ፥ ካዘዝኋችሁም መንገድ ፈቀቅ እንድትሉ አውቃለሁና። በእጃችሁም ሥራ ታስቈጡት ዘንድ በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ስላደረጋችሁ በኋለኛው ዘመን ክፉ ነገር ያገኛችኋል” ይላል (ዘዳ.31፥29)። በኋለኛው ዘመን ክፉ ነገር ያገኛችኋል የተባለውስ መቼ ነው?

✔️መልስ፦ ሙሴ ሊሞት ሲል ለእስራኤላውያን የተናገረው ቃል ነው። በኋለኛው ዘመን ያላቸው እርሱ ከሞተ በኋላ ስለሚመጣው ዘመን ነው። ክፉ ቢያደርጉ የተለያዩ መከራዎች እንደሚደርስባቸው ነው የነገራቸው። ለጊዜው በእርሱ ዘመን ያሉ ሰዎች እግዚአብሔርን ቢበድሉ የሚደርስባቸውን ሲያሳውቅ ፍጻሜው ግን ለሁሉም ሰው የተነገረ ነው። ማለትም ማንኛውም ሕዝብ ክፉ ቢሠራ መከራ እንደሚደርስበት የተነገረ ነው። በዚያን ዘመን ይህን የነገራቸው ስለትንሣኤ ሙታን ሳይሆን በዘመናቸው ስለሚገጥማቸው ነገር ነው።

▶️፫. “በእስራኤል ልጆች መካከል በጺን ምድረ በዳ በቃዴስ ባለው በመሪባ ውኃ ስለ በደላችሁኝ፥ በእስራኤልም ልጆች መካከል ስላልቀደሳችሁኝ” ይላል (ዘዳ.32፥51)። ይህ አንቀጽ ሙሴ ከንዓን እንዳይገባ ያደረገው በደል ነው። ታዲያ እኔ ግልጽ የማይሆንልኝ ለምን ምሕረት አልተደረገለትም? እሽ እግዚአብሔር ባወቀ ካልን አሁን ላይ መምህራን ጭምር የሰው ልጅ በምድር የበደለው ነገር ቢኖር  የዛችን ቅጣት ወይም መከራ በምድር ሳይሞት በፊት ያገኘዋል ይላሉ ይህን እንዴት ያዩታል? ንስሓ ስንገባስ ለነፍሳችን ብቻ ነው በሥጋችንስ መከራ እንዳያገኘን አያደርግም?

✔️መልስ፦ እግዚአብሔር መሓሪ ነው። ፈታሒም ነው። ስለዚህ መሓሪነቱንና ፈታሒነቱን አስማምቶ እርሱ ባወቀ ለሙሴ የሚገባውን አድርጓል። ሰው ሁሉ በምድር ስለሠራው ኃጢአት በምድር ይከፈለዋል የሚለው ግን የተሳሳተ አስተምህሮ ነው። እንዲያ ከሆነ ነዌ ለምን በምድር ሳይከፈለው ቀረ?። ለሌሎች ትምህርትና ተግሣጽ እንዲሆን በምድር የሚከፈለው ሊኖር ይችላል፣ ሙሉ ቅጣቱን በሰማይ ያገኝ ዘንድ በምድር ምንም የማይቀጣ ሊኖር ይችላል። ምንም ሳይበድል በዚህ ምድር ሥጋዊ መከራ የሚያጋጥመው ሊኖር ይችላል። ኃጢአት ሠርቶ በምድር የተቀጣ ሰው በሰማይ ፍርዱ ሊቀንስለት ይችላል። በምድር ያልተቀጣ በሰማይ ጽኑ ቅጣት ሊጠብቀው ይችላል። ሁሉንም የሚያውቀው እግዚአብሔር ነው። ንስሓ መግባት ከሥጋም ከነፍስም መከራ ያድናል።

▶️፬. "እግዚአብሔር ከሲና መጣ በሴይርም ተገለጠ። ከፋራን ተራራ አበራላቸው ከአእላፋትም ቅዱሳኑ መጣ። በስተቀኙም የእሳት ሕግ ነበረላቸው" ይላል። የእሳት ሕግ ምንድን ነበረ?

✔️መልስ፦ የእሳት ሕግ ያለው ምኑን እንደሆነ አላወቅሁትም። በትርጓሜ ትምህርትም የእሳት ሕግ አይልም። መላእክት ወእለ ምስሌሁ ነው የሚል። ምናልባት መላእክትን እሳት ብሏቸው እንደሆነ የአማርኛው ትርጉም አላወቅሁም።

▶️፭. "የላሙንም ቅቤ የመንጋውም ወተት ከጠቦት ስብ ጋራ የባሳንንም አውራ በግ ፍየሉንም ከስንዴ እሸት ጋራ በላህ። ከወይኑም ደም ያለውን ጠጅ ጠጣህ።  ደም ያለውን ጠጅ ጠጣህ ሲባል ምን ለማለት ነው?

✔️መልስ፦ የወይኑን ዘለላ ሲጨምቁት የሚገኘውን ፈሳሽ ለመግለጽ ነው።

▶️፮. "በዚያም ቀን ቍጣዬ ይነድድባቸዋል እተዋቸውማለሁ ፊቴንም እሰውርባቸዋለሁ። ለአሕዛብ መብል ይሆናሉ። በዚያም ቀን በእውነት እግዚአብሔር በእኛ መካከል የለምና ይህ ክፉ ነገር ሁሉ አገኘን እስኪሉ ድረስ ብዙ ክፉ ነገርና ጭንቀት ይደርስባቸዋል" ይላል (ዘዳ.31፥17)። ለአሕዛብ መብል ይሆናሉ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ለጠላቶቻቸው ምግብ ይሆናሉ ማለት ምግብ በእጅ እንደሚበላ በጠላቶቻቸው እጅ አሳልፌ እሰጣቸዋለሁ ማለት ነው።

▶️፯. ዘዳ.32፥8 "ልዑል ለአሕዛብ ርስታቸውን ባወረሰ ጊዜ፥ የአዳምን ልጆች በለየ ጊዜ፥ እንደ እግዚአብሔር መላእክት ቍጥር፥ የአሕዛብን ድንበር አቆመ። የአሕዛብ ድንበር እንደ መላእክት ቁጥር አደረገ ሲል ምን ለማለት ነው? ማለቴ የመላእክት ቁጥር ስለማይታወቅ።

✔️መልስ፦ መላእክት ብዙ እንደሆኑ ሁሉ ሰዎችንም አበዛኋቸው ማለት ነው።

▶️፰. በኦሪት የበግ ወተት ይጠጣል እንዴ? ስብስ ይበላል እንዴ? ዘዳ.32፥14 ላይ የበግ ወተት እና ስብ መገብኋችሁ ስለሚል።

✔️መልስ፦ ስብ አይበላም። የጠቦት ስብ ያለው ሥጋውን ነው። የበግ ወተትን ግን እንደሚጠጣ ከዚህ ተናግሮታል።

▶️፱. ዘዳ.33፥6 "ሮቤል በሕይወት ይኑር፥ አይሙት፤ ቍጥሩም  ብዙ ይሁን" ይላል። ሮቤል ሲጀመር አልሞተም ወይ? እንዴትስ ይበዛል?

✔️መልስ፦ ሮቤል ሞቶ ነበረ። ነገር ግን በሕይወት ሳለ ከአባቱ ዕቅብት ደርሶ ስለነበረ ጌታ ሆይ ዕዳ አታድርግበት ሲል ነው (ይህ የፍትሐት ምሳሌ ነው)። በተጨማሪ ግን ከዚህ ሮቤል የተባለው ከእርሱ የሚወለደውን ሕዝብ (ነገድ) ነው።

▶️፲. ዘዳ.33፥22 "ስለ ዳንም እንዲህ አለ፦ ዳን የአንበሳ ደቦል ነው፤ ከባሳን ዘልሎ ይወጣል" ይላል። የአንበሳ ደቦል ይሁዳ አይደለም ወይ (ዘፍ.49፥9)።

✔️መልስ፦ ይሁዳን የአንበሳ ደቦል ብሎ የመረቀው ያዕቆብ ነው። ከዚህ ደግሞ ዳንን የአንበሳ ደቦል ብሎ የመረቀው ሙሴ ነው። ሁሉም ምሳሌያዊ አነጋገር ነው። አንድ ቃል ለብዙ ነገሮች ምሳሌ መሆን ስለሚችል ምንም ችግር የለውም።

▶️፲፩. የእስራኤል ትምክህት ሰይፍ ነው ሲል ምን ማለት ነው (ዘዳ.33፥29)።

✔️መልስ፦ይህ ማለት በሰይፋቸው አሕዛብን ወግተው በረድኤተ እግዚአብሔር ተጠብቀው ይኖራሉ ማለት ነው።

▶️፲፪. ዘዳ.34፥10 "እግዚአብሔርን ፊት ለፊት እንዳወቀው እንደ ሙሴ ያለ ነቢይ ከዚያ ወዲህ በእስራኤል ዘንድ አልተነሣም" ይላል። እግዚአብሔር ለሙሴ እንዳንተ ያለ ነቢይ ከወገኖቻቸው አስነሣለሁ ብሎ የለምን (ዘዳ.18፥18)። የሚነሣው ነብይ ፍጻሜው ክርስቶስ ቢሆንም ለጊዜው ግን የሚነሣው ማን ነው?

✔️መልስ፦ ሙሴ ሊቀ ነቢያት ነው። ከነቢያት ሁሉ ታላቅ ስለነበረ እንደእርሱ ያለ አልተነሣም ተብሏል። እንደሙሴ ያለ ነቢይ ያስነሣላችኋል የተባለ ኢያሱ ነው። ከዚህ እንደአንተ የሚለው በጥቂት መመሳሰል ስላለ ነው። በጥቂት መመሳሰልን በእንደ መግለጽ ደግሞ ልማደ መጻሕፍት ነው።


መ/ር በትረ ማርያም አበባው

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

07 Nov, 13:09


ሁለት ሰዎች በአንድ ጉዳይ አብረው ይፀልያሉ አንደኛው ፀሎቱ ተመለሰለት አንደኛው ሳይመለስለት ቀረ። በዚህ ጊዜ ፀሎቱ ያልተመለሰለት ሰው "ጌታ ሆይ ሁለታችንም እኩል ፀልየን ለእርሱ ሰጥተኸው ለእኔ ከለከልኝ ለምንድ ነው?" አለው። እግዚዘብሔርም "ለእርሱ ባልሰጠው ይጠፋል፣ ላንተ ከሰጠሁህ ደግሞ ትጠፋለህ" አለው ይባላል።

እግዚአብሔር ከራሳችን በላይ እኛን ያውቀናል። ለአንዳችን በመስጠት፣ አንዳችንን በመከልከል ዕድሜያችንን ያረዝመዋል። መስጠቱም መንሳቱም ሁለቱም በፍቅር ነውና በልመናችን በፀሎታችን የአንተ ፈቃድ ይሁንልን ማለት ተገቢ ነው።

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

07 Nov, 13:00


እግዚአብሔር ከሚታይም ከማይታየውም ፈተና ይጠብቅልን ።


በሚሞት ሥጋችን አንመካ በገንዘባችን ባለን የኃብት መጠን አንመዛዘን።
ገንዘባችሁ አያጸድቃችሁም መቶ ሺ ብር ሰርቃችሁ ሃያ ሺ ብር ብትሰጡ አትጸድቁም ገንዘባችሁ ከንጽሕና ጋር ሲሆን እንጂ ።እግዚአብሔርን በአስራታችን አንስረቀው እግዚአብሔር ከአስር ብር ውስጥ አንድ ብር የሚጠይቀን ዘጠኙን ሲጠብቅ ነው ሲያበዛልን የበረከት ሲያደርግልን ነው

EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @sekokaw ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

07 Nov, 10:55


https://youtu.be/8Nxr9nqdbXk?si=OPPGs4X7LIQTgjSv

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

06 Nov, 15:23


እንኳን ለቸሩ መድኃኔዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

05 Nov, 18:38


ተጠቃሚው ማን ነበር?  

ሁልጊዜ የምበግንበት የከተማ አስተዳደራችን ክብርት/ክቡር /ተቀዳሚ ፣የባህልና ቱሪዝም ሚንስተር ሚኒስትር እገሌ ካላቸው ጊዜ አጣበው በዛሬ እለት በመካከላችን ተገኝተዋል ቢገኙ ባይገኙ አውደ ምሕረት ላይ ቆመው የምሕረት ወንጌል አያስተላልፉልን ስልጣናቸውን ለማቆየት ለሪፖርት የሚያግዛቸውን ቤተክርስቲያን በሰበሰበችላቸው ህዝብ ላይ ሊያፏጩብን ካልሆነ በቀር ለቤተክርስቲያን ምን ይጠቅማሉ ? ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ •••• ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት እያለ ይቀጥላል ብጹዕ አባታችን የዚህ ሀገረ ስብከት በብፁዕ ወቅዱስ መልካም ፈቃድ እያለ እ••ያ••ለ በእከከኝ ልከክልህ የተሾመ የቤተክርስቲያን አለቃውንም ውስጡ እያወቀ ምንም ትምህርት ሳይማር እንደተቀመጠ እያወቀ የተከበሩ መጋቤ ሐዲስ ፣መጋቤ ምስጢር የወንጌል ገብሬ በየትኛውም ቦታ ብንጠምዳቸው ሰለቸኝ ደከመኝ የማይሉ በመካከላችን ስለተገኙልን እልል በሉ እረ የመድኃኔዓለም ያለህ ይህ ሁሉ ገመድ ጉተታ ሳንባ ቆጠራ ቢቀር ለቤተክርስቲያን ምን ይጎዳታል ? እግዚአብሔር ከመካከላችን እሳቸውን እንደመሳሪያ አድርጎ ፣ እነሱን አንደበት አድርጎ ያስተምረናል የአባቶቻችን አምላክ ከሁላችን ጋር ይሁን አስተምረው ሲጨርሱ ቃለ ህይወት ያሰማልን ወደ ቀጣዩ መርሃ ግብር እንሄዳለን ቅድስት ቤተክርስቲያን ለምታለማው ልማት መደገፍ የምትፈልጉ በየሙዳይ ምጽዋት አስገቡ ብቻ ቢባል ብዙን ጊዜ ወንጌል ለመስበክ ትውልዱን ለመጠበቅ ቢሰራ ተጠቃሚው ማን ነበር?  መሞጋገስ ቢቀር ምን አለበት !!


ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

04 Nov, 06:50


https://vm.tiktok.com/ZMhXWbaTP/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Nov, 23:02


መልስ፦ እግዚአብሔር እስራኤላውያን የተገዙበትን ዋጋ ተውሰው በዚያው እንዲወስዱ
እየነገራቸው ነው።
፯. “እኔ ግን ልቡን አጸናዋለሁ፥ ሕዝቡንም አይለቅም” ይላል (ዘፀ.4፥21)። የፈርዖንን ልብ
ያፀናው እግዚአብሔር ነውን?

መልስ፦ እግዚአብሔር ሰውን ክፉ አያደርግም። ነገር ግን ሰው ክፉ ሲሆን ረድኤቱን
ይነሣል። ስለዚህ ረድኤት መንሣቱን ለመግለጽ ልቡን አጸናዋለሁ አለ። በእርሱ
አላድርበትም ለማለት ነው። በተጨማሪም ሁሉንም ክፋት ፈርዖን ሲሠራ እስከ
ሚሰጥም ድረስ አላጠፋውም ማለቱ ነው።
፰. “እንዲህም ሆነ፤ በመንገድ ላይ ባደረበት ስፍራ እግዚአብሔር ተገናኘው፥ ሊገድለውም ፈለገ”
ይላል (ዘፀ.4፥24)። ይህ ቃል ስለማን ተነገረ? ለምንስ ሊገለው ፈለገ?

መልስ፦ ስለሙሴ የተነገረ ነው። ሙሴ ልጆቹን ባለመግዘሩ እግዚአብሔር ሊቀጣው
እንደነበረ የሚገልጽ ነው። ሚስቱ ሲፓራ ልጇን በፍጥነት ስትገዝረው ቅጣቱ
ቀርቶለታል።
፱. "የግብፅ ንጉሥም፦ አንተ ሙሴ አንተም አሮን፥ ሕዝቡን ለምን ሥራቸውን ታስተዋላችሁ?
ወደ ተግባራችሁ ሂዱ አላቸው። ፈርዖንም፦ እነሆ የምድሩ ሕዝብ አሁን በዝቷል፥ እናንተም
ሥራቸውን ታስፈቷቸዋላችሁ አለ" ይላል (ዘፀ.5፣4-5)። የግብፅ ንጉሥ እና ፈርዖን ይለያያሉ
እንዴ ንባቡ አልገባኝም።
መልስ፦ አይለያዩም። የግብፅ ንጉሥ የተባለው ራሱ ፈርዖን ነው።
፲. የግብፅ ሰዎች እስራኤላውያን ግፍ ያደረሱባቸው እና ወንድ ሲወለድ እንዲገደል ያደረጉት
በምን ምክንያት ነው?

መልስ፦ እስራኤላውያን በግብፅ ምድር እየበዙ ስለመጡ ሀገራችንን ይወርሱናል ብለው
ፈርተው ነው።
፲፩. የሙሴ አማት ዮቶር ኢትዮጵያዊ ነው የሚባለው የሰነድ ማሰረጃ አለው?
መልስ፦ አዎ ካህኑ ዮቶር ኢትዮጵያዊ ነበረ። ከዚሁ ከመጽሐፍ ቅዱስ ሙሴ
ኢትዮጵያዊትን እንዳገባ ይገልጻልና (ዘኍ.12፣1)። ሙሴ ያገባት ሲፓራ ደግሞ የዮቶር
ልጅ ናት።
፲፪. የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች ናትና ጫማህን ከእግርህ አውጣ ማለቱ ትርጉሙ ምንድን
ነው?

መልስ፦ ለጊዜው ወደቅዱስ ቦታ ስንገባ ጫማችንን አውልቀን እንድንገባ ለማሳሰብ
ሙሴም ጫማውን እንዲያወልቅ ታዝዟል። ሌላኛው ምክንያት ግን ሙሴ ፋል የሚባል
ጥንቆላ ተምሮ ነበረና እርሱን ትተህ እኔን እግዚአብሔርን አምልከኝ ማለት ነው።
፫. ዘፀ.2÷16 "የአባታቸውን የዮቶርን በጎች ይልና እልፍ ብሎ ወደ አባታቸው ወደ ራጉኤል
መጡ" ይላል። ዮቶር ማን ነው? ራጉኤልስ?

መልስ፦ የአንድ አንድ ሰው ሁለትና ከዚያ በላይ ስም ሊኖረው ይችላል። ስለዚህም
ዮቶርም ራጉኤል እየተባለ ይጠራ ስለነበረ ነው።
፲፬. የምድያም ምድር የት ነው? አሁናዊ መገኛውስ?
መልስ፦ በቀድሞው ኢትዮጵያ ይገኝ የነበረ ነው። አሁን ግን ሱዳን ነው። (ቀድሞ
የኢትዮጵያ ግዛት እስከ ሱዳን የዘለቀ ስለነበረ) ነው።
፲፭. ዮቶር ኢትዮጵያዊ ነው?
መልስ፦ አዎ።
፲፮. “እናንተ የዕብራውያትን ሴቶች ስታዋልዱ፥ ለመውለድ እንደደረሱ ባያችሁ ጊዜ፥ ወንድ
ቢሆን ግደሉት ሴት ብትሆን ግን በሕይወት ትኑር” ይላል (ዘፀ.1፥16)። ዘር እንዳይበዛ ከሆነ
ለምን ወንዶች እንዲገደሉ አዘዘ?

መልስ፦ ግብጻውያን የእስራኤላውያንን ወንዶች በዝተው በርትተው ወደፊት ሀገራችንን
ይገዟታል ብለው ሰግተው ነው። ወንድ ከሴት ይልቅ ብርቱ ነውና።
፲፯. ዕብራውያን በግብፅ እንደ እስራኤል ስደተኞች ናቸው?
መልስ፦ ዕብራውያን እየተባሉ የሚጠሩት ራሳቸው እስራኤላውያን ናቸው። በዔቦር
ዕብራውያን በያዕቆብ እስራኤል ተብለዋልና። ስለዚህ የተለያዩ ስላልሆኑ ስደተኞች ነበሩ።
፲፰. የሙሴ አማት የራጉኤል ክህነት ከማነው? (ካህኑ ዮቶር ሲባል እንሰማለንና)። ማስረጃም
ካለ ቢጠቁሙን።

መልስ፦ ዮቶር የእግዚአብሔር ካህን አልነበረም። የጣዖት ካህን ነበረ። ሙሴ ጫማህን
አውልቅ መባሉ አንደኛው ምክንያት ልማደ ዮቶሮን የዮቶርን አምልኮ ተው ሲል ነውና።
፲፱. በሰዎች ዘንድ ክህነት መች ተጀመረ?
መልስ፦ በመጀመሪያው ሰው በአዳም ተጀምሯል። እግዚአብሔር ለአዳም ሰባት ሀብታት
ሰጥቶታል። ከሰባቱ አንዱ ሀብተ ክህነት ነው።



መ/ር በትረ ማርያም አበባው
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Nov, 22:58


ኦሪት ዘፀአት ላይ የተነሡ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
፩. ሙሴ የክርስቶስ ምሳሌ መሆን ይችላል ወይ? ከሆነ የሙሴ ሕይውትን ከክርስቶስ ጋር
አነፃፅረው ቢነግሩን (ነገረ ክርስቶስ) ማለቴ ነው
?
መልስ፦ አዎ ሙሴ የክርስቶስ ምሳሌ ነው። ሙሴ እስራኤላውያንን ከግብፅ ባርነት
አውጥቶ ወደ ከነዓን ምድር እንዳስገባቸው ሁሉ ክርስቶስም በሲዖል ይሰቃዩ የነበሩ
ነፍሳትን በመልዕልተ መስቀል ተሰቅሎ ወደገነት መልሷቸዋልና። ሙሴ በበትሩ ባሕረ
ኤርትራን ከፍሎ እስራኤላውያንን እንዳሻገረ ክርስቶስም በመስቀል ተሰቅሎ ከሲኦል ወደ
ገነት አሸጋግሮናልና።
፪. “እንዲህም ሆነ አዋላጆች እግዚአብሔርን ስለ ፈሩ ቤቶችን አደረገላቸው” ይላል (ዘፀ.1፥21)።
ይህ ቃል ስለ እግዚአብሔር ነው? "ቤቶችን አደረገላቸው” ሲል ምን ማለቱ ነው?

መልስ፦ አዋላጆች እግዚአብሔርን ስለፈሩ እግዚአብሔር ቤት ንብረት ሰጣቸው ማለት
ነው።
፫. “በከፈተችውም ጊዜ ሕፃኑን አየች፥ እነሆም ሕፃኑ ያለቅስ ነበር፤ አዘነችለትም፦ ይህ
ከዕብራውያን ልጆች አንዱ ነው አለች” ይላል (ዘፀ.2፥6)። እንደ አዋጁ ለምን ወንዝ ውስጥ
አልጣለችውም? ፈርዖንስ እንዳለመታዘዝ አልቆጠረውም ወይ?

መልስ፦ የፈርዖን ልጅ ልጅ ስላልነበራት ሙሴን የእርሷ ልጅ አድርጋ አሳድገዋለች።
ስለዚህ የፈርዖን የልጅ ልጅ እየተባለ ስለሚያድግ ፈርዖን አልተቆጣም።
፬. “ሕፃኑም አደገ፥ ወደ ፈርዖንም ልጅ ዘንድ አመጣችው፥ ለእርሷም ልጅ ሆነላት። እኔ ከውኃ
አውጥቼዋለሁና ስትልም ስሙን ሙሴ ብላ ጠራችው” ይላል (ዘፀ.2፥10)። ስሙ ካደገ በኋላ
ለምን ወጣላት?

መልስ፦ ስሙ የወጣለት ከአደገ በኋላ አይደለም። ለእርሷ ልጅ እንደሆነ አንሥታ
ከወሰደችው ጀምራ ነው ያወጣችለት። ከዚህ ላይም ሙሴ ከውሃ ስለተገኘ ሙሴ
እንደተባለ ለመግለጥ እንጂ ከአደገ በኋላ ስም እንደወጣለት ለመግለጥ አይደለም።
፭. “እግዚአብሔርም በእነርሱ ያለውን ነገር አወቀ” ይላል (ዘፀ.2፥25)። ይህ ጥቅስ ረበሸኝ
እስከሚያለቅሱ ድረስ አላወቀም ወይ?

መልስ፦ እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር ቀድሞ ያውቃል። ከዚህ ላይ አወቀ ማለት
ረድኤትን ለመስጠት ጊዜው መድረሱን መግለጥ ነው። እንጂ እግዚአብሔር በዘመን
ብዛት እንደ አዲስ ዕውቀትን ያውቃል ለማለት አይደለም።
፮. “ነገር ግን እያንዳንዲቱ ሴት ከጎረቤቷ በቤቷም ካለችው ሴት የብር ዕቃ የወርቅ እቃ ልብስም
ትለምናለች፤ በወንዶችና በሴቶች ልጆቻችሁ ላይ ታደርጉታላችሁ፤ ግብፃውያንንም
ትበዘብዛላችሁ” ይላል (ዘፀ.3፥22)። ይህ ንባብ አልገባኝም?

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Nov, 11:51


እግዚአብሔር ከሚታይም ከማይታየውም ፈተና ይጠብቅልን ።


በሚሞት ሥጋችን አንመካ በገንዘባችን ባለን የኃብት መጠን አንመዛዘን።
ገንዘባችሁ አያጸድቃችሁም መቶ ሺ ብር ሰርቃችሁ ሃያ ሺ ብር ብትሰጡ አትጸድቁም ገንዘባችሁ ከንጽሕና ጋር ሲሆን እንጂ ።እግዚአብሔርን በአስራታችን አንስረቀው እግዚአብሔር ከአስር ብር ውስጥ አንድ ብር የሚጠይቀን ዘጠኙን ሲጠብቅ ነው ሲያበዛልን የበረከት ሲያደርግልን ነው

EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ
+15095058383
+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @sekokaw ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Nov, 04:59


‹‹እስከ ማእዜኑ እግዝእትየ ማርያም ውስተ ምድረ ነኪር ትሄልዊ
ሀገረኪናሁ ገሊላ እትዊ
ለወልድኪ ሕፃን ዘስሙ ናዝራዊ
ለክብረ ቅዱሳን በከመ ይቤ ዖዝያን ዜናዊ
እምግብፅ ይጼውዖ አቡሁ ራማዊ፡፡››

ትርጉም፡-
እመቤቴ ማርያም ሆይ! ስሙ ናዝራዊ የሚባል ልጅሽን ለአዳምና ለሔዋን ክብር የባሕርይ አባቱ አብ ከግብጽ ይጠራዋል፣ማለት በግብጽ ስደት አይሞትም ኋላ በቀራንዮ ተሰቅሎ ዓለምን ያድናል ብሎ ነቢዩ ዖዝያን (ሆሴዕ) ትንቢት እንደተናገረ እስከ መቼ ባድዕ አገር ትኖሪያለሽ? እነሆ ወደ አገርሽ ናዝሬት ተመለሽ፡፡

(ሰቆቃወ ድንግል)

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

03 Nov, 04:37


መድኃኔዓለም በእድሜ ይጠብቅልን

በእውነት እግዚአብሔር አምላክ በጎደለ ይሙላላችሁ መድኃኔዓለም ያላሰባችሁትን ይስጣችሁ።
  አስራታቸውን ስዕለታቸውን እንዲያስገቡ በረከቱን እያበዛላቸው እየባረካቸው ለምሕረት የማይታጠፉ እጆቹ እንደማይጎድል ውሃ  እያፈሰሰላቸው ነው ።
እግዚአብሔር ይቀበልላችሁ እም ብርሃን አትለያችሁ የሰላም አምላክ ሰላምን ይስጣችሁ።



በሚሞት ሥጋችን አንመካ በገንዘባችን ባለን የኃብት መጠን አንመዛዘን።
ገንዘባችሁ አያጸድቃችሁም መቶ ሺ ብር ሰርቃችሁ ሃያ ሺ ብር ብትሰጡ አትጸድቁም ገንዘባችሁ ከንጽሕና ጋር ሲሆን እንጂ ።እግዚአብሔርን በአስራታችን አንስረቀው እግዚአብሔር ከአስር ብር ውስጥ አንድ ብር የሚጠይቀን ዘጠኙን ሲጠብቅ ነው ሲያበዛልን የበረከት ሲያደርግልን ነው

EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @sekokaw ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

02 Nov, 14:04


በቤተመንግስት ተገኘ ስለተባለው 400 ኪ/ግ ወርቅ

ጠ/ሚር አብይ አህመድ ፓርላማ ላይ "ባደረግነው የቤተመንግስት ዕድሳት ተቆልፎበት የተቀመጠ 400 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ አስገብተናል" ማለታቸው ይታወሳል።

"ይህ ወርቅ ምን ይሆን ብዬ?" አንዳንድ ማጣራቶችን ለማድረግ ሞክሬ ነበር። ያገኘሁት መረጃ አስደንጋጭም፣ አሳሳቢም ሆኖ አግኝቼዋለሁ።

ይህ ወደ ብሄራዊ ባንክ ተላከ የተባለ ወርቅ በኢትዮጵያ የንጉሳዊ ስርዐት ወቅት ለበርካታ መቶ አመታት ነገስታት ሲገለገሉባቸው የነበሩ በወርቅ እና በሌሎች የከበሩ ማዕድናት የተሰሩ ቁሳቁሶች፣ ከሌሎች ሀገራት በስጦታ የተሰጡ ቅርሶች እንዲሁም በርካታ በነገስታቱ ታዘው የተሰሩ እና የተገዙ ናቸው።

"ታድያ እነዚህ ወደ ሙዚየም እንጂ ለሽያጭ ወይም ለወርቅ ክምችት ወደ ባንክ እንዴት ሊላክ ይችላል?" ብዬ ጥያቄ ያቀረብኩላቸው ጉዳዩን የሚያውቁ ግለሰቦች ምላሻቸው "ማን ሰምቶን?" ነው።

ቅርስ ጥበቃ፣ ብሄራዊ ባንክ፣ የጠ/ሚር ፅ/ቤት እንዲሁም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በዚህ ዙርያ መክሮ እነዚህን የኢትዮጵያ ታሪክ የሆኑ ንብረቶች ወደነበሩበት ቦታ ወይም ወደ ሙዚየም እንዲመለሱ ማድረግ አለባቸው።

እጅግ አሳሳቢ ጉዳይ ነው!
ምንጭ :ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

02 Nov, 13:45


Are these orthodox brothers ???

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

29 Oct, 06:00


+++ የምፈልገውን ሳይሆን ፤ የሚያስፈልገኝን ስጠኝ+++

በአንድ ወቅት አንድ መነኩሴ የወይራ ዘይት ዛፍ ተከለና ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል መጸለይ ጀመረ ፤ "ጌታ ሆይ ለዛፌ ይጠቅም ዘንድ ዝናብን አዝንብልኝ" አለ። እግዚአብሔርም ጸሎቱን ተቀብሎ ዝናቡን አዘነበለት ፤ ዛፉም ውኃን በጣም ጠግቦ አፈሩ ረሰረሰ። ለዛፉ ይጠቅም ዘንድ ግን ከመጠን በላይ የረሰረሰው አፈር መድረቅ ያስፈልገው ነበር። ስለሆነም መነኩሴው ወደ እግዚአብሔር ጸለየ "ጌታ ሆይ ብዙ ፀሐይ በዛፉ ላይ እንድታወጣ እለምንሃለሁ" አለ። እግዚአብሔርም በለመነው መሠረት ፀሐይ አወጣለት ፤ ዛፉም አደገለት። መነኩሴው ልመናውን ቀጠለ "ጌታ ሆይ የዛፉ ሥር እና ቅርንጫፍ ይጠነክር ዘንድ ጥቂት ውርጭ ላክልኝ" አለ። እግዚአብሔርም በጠየቀው መሠረት ውርጩን ላከለት ፤ ከዚያም ዛፉ ከውርጩ የተነሣ ጠወለገ ሞተም።

መነኩሴው በኹኔታው በጣም ተናድዶ ወደ አንድ መነኩሴ ሔዶ የገጠመውን ታሪክ እና ቅሬታውን ያለማጉደል አጫወተው ኀዘኑን አካፈለው። ሁለተኛው መነኩሴ ታሪኩን ከሰማ በኋላ "እኔም እንደ አንተ የወይራ ዘይት ዛፍ አለኝ ተመልከት" አለው ፤ የእርሱ ዛፍ በመልካም ኹኔታ አድጋለች። ሁለተኛው መነኩሴም ቀጥሎ "እኔ ግን ከአንተ በተለየ መልኩ እጸልያለሁ ፤ ይህን ዛፍ የፈጠረው እርሱ ነውና ፤ ከእኔ የተሻለ የሚያስፈልገውን እንደሚያውቅ ለእግዚአብሔር ነገርኹት ፤ እግዚአብሔርም እንዲንከባከበው በጸሎት ጠየቅኹት ፤ እርሱም ጸሎቴ ሰምቶ ተንከባከበው" በማለት አስረዳው።

በእኛም ሕይወት እንዲህ ነው ፤ የሚያስፈልገንን በትክክል የምናውቅ መስሎን እንለምናለን ፤ ነገር ግን ለእኛ የሚያስፈልገንን ያለማጓደል የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ስለዚህ "፥በሙሉ ልብ እንመነው! "የምፈልገውን ሳይሆን የሚያስፈልገኝን ስጠኝ" እንበለው።

                                 +++

" ኢየሱስ ግን፦ የምትለምኑትን አታውቁም። እኔ የምጠጣውን ጽዋ ልትጠጡ፥ እኔ የምጠመቀውንስ ጥምቀት ልትጠመቁ ትችላላችሁን? አላቸው።"
(የማርቆስ ወንጌል 10: 38)

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

28 Oct, 10:57


ደግ_ደጉን_ብናስብ
በአርባዕቱ_ግብራት_ይጸልም_ልብ

#በአራት ነገሮች ልብ ይጨልማል (አእምሮ ይጠቁራል)

1. #በጸሊአ_ቢጽ ፦ ባለንጀራን በመጥላት

" ወንድሙን የሚጠላ ግን በጨለማ አለ፥ በጨለማም ይመላለሳል፥ የሚሄድበትንም አያውቅም፥ ጨለማው ዓይኖቹን አሳውሮታልና" 1ኛ ዮሐ 2 : 11።

2. #በአስተሐቅሮ፦ ሰውን በመናቅ/በማቃለል

" እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል፤ ወንድሙንም ጨርቃም የሚለው ሁሉ የሸንጎ ፍርድ ይገባዋል፤ ደንቆሮ የሚለውም ሁሉ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይገባዋል" ማቴ5 : 22።

3. #በቅንዓት፦ በክፉ ቅንዓት/ምቀኝነት "ቅንዓት አጥንትን ያነቅዛል" ምሳ 14፡30።

4. #በአስተአክዮ፦ ሰውን በማክፋፋት/የሰው ስም በማጥፋት "ክፉ ሰውም ከክፉ መዝገብ ክፉ ነገርን ያወጣል" ማቴ 12 : 35።

የእኛን ልብ ያጠቆረው ፤ አእምሯችንን ያጨለመው የትኛው ይሆን?

ጸሎታችን እንዳይሰማ
እንዳንተያይ ፤ እንዳንግባባ የጋረደን ጨለማ
ብርሃናችን በሰው ፊት እንዳይበራ የከለከለን የልብ ጨለማ የአእምሮ ጽልመት የትኛው ይሆን???

ሀገራችን ውስጥ ብዙዎች የአእምሮ (የልብ) ጨለምተኞች አሉ ፤ ሀገር የምትታወከው ሰላም የሚታጣው በነዚህ የአእምሮ ጨለማ ውስጥ በሚኖሩ ሰዎች ነው።

አምላካችን ሁላችንንም ከልብ ጨለማ በብርሃኑ ያውጣን!

ንዑ ናንሶሱ በብርሃኑ
ከጨለማ ወጥተን ኑ በትንሣኤው ብርሃን እንመላለስ!

ጌታ መድኃኔ ዓለም ሆይ! በመስቀልህ ትርክዛ እየቀዘፍክ ወደሚደነቀው ብርሃንህ አሻግረን!

አሜን!!!

ምንጭ፦ ሕንጻ መነኰሳት

መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

28 Oct, 04:11


ጉየተ ሕፃን አጉየዮ ለሰይጣን
" የሕፃኑ ስደት ሰይጣንን ከሰው ልቦና አሰድዶ (አስወጥቶ) ሰደደው።"
ቅዱስ ቄርሎስ

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

27 Oct, 10:58


ክህነት ተንበላሸ

‹ክህነት›፣ ‹‹ተክህነ – አገለገለ›› ከሚል የግእዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጓሜውም ‹‹አገልግሎት፣ መላላክ፣ ለሌሎች መኖር፣ መጥዎተ ርእስ (ራስን መስጠት) መላ ሕይወትን ለእግዚአብሔር ማስረከብ›› ማለት ነው፡፡ ክህነት ካለ ካህናት ይኖራሉ፤ ክህነት አገልግሎቱ፣ ሹመቱ፤ ካህናት ደግሞ አገልጋዮቹ፣ ተሿሚዎቹ ናቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ካህናት መላእክት ናቸው፡፡ የመጀመሪያ የእግዚአብሔር እና የሰው ልጆች አገልጋዮች፡፡ ‹‹በዙፋኑ ዙሪያ ሃያ አራት ወንበሮች ነበሩ፡፡ በእነዚያ ወንበሮችም ሃያ አራት አለቆች (ካህናተ ሰማይ) ተቀምጠዋል፡፡ ነጭ ልብስም ለብሰዋል፡፡ በራሶቻቸው ላይ የወርቅ አክሊሎች ደፍተው ነበር … በዂለንተናቸው ዓይኖችን የተመሉ ናቸው፡፡ ‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የነበረውና ያለው፣ የሚመጣውም፤ ዂሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ› እያሉ›› ቀንና ሌሊት አያርፉም፡፡  እነዚህ በዙፋን ላይ ለተቀመጠው ከዘለዓለም እስከዘለዓለም በሕይወት ለሚኖረው ለእርሱ አክሊላቸውን በዙፋኑ ፊት አውርደው ይሰግዳሉ፡፡ እንዲህም ይላሉ፤ ‹ጌታችን እና አምላካችን ሆይ፣ አንተ ዂሉን ፈጥረሃልና በፈቃድህም ኾነዋልና ተፈጥረውማልና ክብርና ውዳሴ ኀይልም ለአንተ ይገባል፤››› ተብሎ እንደ ተጻፈ (ራእ. ፬፥፬)፡፡ሥልጣነ ክህነት በጳጳሳት እጅ የሚሰጥ ሥልጣን ነውና ማቃለል አይገባም፡፡ ካህናት የእግዚአብሔር ዓይኖች ናቸውና፡፡ እግዚአብሔር ኀጢአተኛውን የሚያየው፣ የሚጐበኘውና ኀጢአቱን ይቅር የሚለው በእነርሱ በኩል ነው፡፡ ‹‹ሒድ ራስህን ለካህን አሳይ›› (ማቴ. ፰፥፬) ተብሎ እንደ ተጻፈ ካህን አየን ማለት እግዚአብሔር አየን ማለት ነው፡፡ ካህን የእግዚአብሔር ዓይን ነውና፡፡ 
ይሁን እንጂ በትግራይ የሚገኙት አባቶቻችን ውግዘቱ ሳያግዳቸው አሁንም ጳጳስ ነን እንዲያውም ሲኖዶስ መስርተን እናሳያችሁ እያሉ ነው ።ይህ ብቻ አይደለም በኦሮምያም የነበሩት ጥቂቶቹ በራሳቸው መንገድ ጳጳስ ነን ይላሉ።
በጣም የሚገርመው ግን በሁለቱም በኩል የተሾሙ ድቁናም ቅስናም የተቀበሉ እየተቀበሉ ያሉም አሉ በአሜሪካና አውሮፓ እየገቡ ይህን ድርጊትም እየፈጸሙ ነው ፣በእነዚያ ዲያቆናትና ቀሳውስትም ክርስትና ሥርዓተ ተክሊል እየተቀበሉ ያሉ ምእመናን አሉ ባልተገባ ክህነት በተበላሸ ካህንነት(አገልግሎት)የሚገኘው የሚፈጸመው ነገር ለሚደገሙና ለማይደገሙ የአገልግሎት ክፍሎች ለምሳሌ ምሥጢረ ክህነት እንዴት ይሆናል ይህ ነገር ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኝ ፈታኝ ነገር ነው።
በምዕመናን ቤተክርስቲያን ብትታመስ ከእውቀት ማነስ ነው ብለን በተገረምን በካህናት እንዲህ ስትሆን ማየት ግን ያሳዝናል።

ካህናት በትረ ክህነት የጨበጡ፣ በእግዚአብሔር የተመረጡ፣ አጋንንትን የሚቀጡ፣ ኃጢአትን እንደ ሰም አቅልጠው የሚያጠፉ ናቸው፡፡ ሰውን ወደ እግዚአብሔር ያቀርባሉ፤ የእግዚአብሔርን መንጋ ምእመናንን ይጠብቃሉ፡፡ በለመለመ መስክ በጠራ ውኃ ያሠማራሉ፡፡ ደጋግ ንጹሓን አባቶችን ያምጣልን።

ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

27 Oct, 08:08


ከዚህም በኋላ በሐሰት ምስክር ‹‹ይህን ሰው በሙሴና በእግዚአብሔር ላይ የስድብን ቃል ሲናገር ሰምተነዋል›› በማለት ወነጀሉት፤ እርሱ ግን ስለ እውነት መሰከረ እንጂ በጀ አላላቸውም፤ ሊቀ ካህናቱም በጠየቁት ጊዜ ስለ እግዚአብሔር አምላኩ መሰከረ፤ በመጨረሻም እንዲህ አላቸው፤ ‹‹እናንተ አንገታችሁ የደነደነ፥ ልባችሁም የተደፈነ፥ ጆሮአችሁም የደነቈረ፥ እንደ አባቶቻችሁ መንፈስ ቅዱስን ዘወትር ትቃወማላችሁ፡፡ አባቶቻችሁ ከነቢያት ያሳደዱት ማን አለ? ዛሬም እናንተ አሳልፋችሁ የሰጣችሁትንና የገደላችሁትን የጻድቁን መምጣት አስቀድመው የተናገሩትን ገደሉአቸው፡፡ በመላእክትም ሥርዐት ኦሪትን ተቀብላችሁ አልጠበቃችሁም፡፡›› በዚህም ተበሳጭተው በድንጋይ ወግረው ገደሉት፡፡ በዚህም ምስክሩን ፈጽሞ የሰማዕታት አክሊልን በጥር ፩ ቀን ተቀዳጅቷል፤ በዚህም ቀዳሜ ሰማዕታት ይባላል፡፡(የሐዋ. ፯፥፶፩-፶፫)
አይሁድ ቅዱስ እስጢፋኖስን ለማጥፋት ቀንተው ሲገድሉት ጠላት ዲያብሎስ ደግሞ ክርስትናን ለማጥፋት እነርሱን ሰበብ አድርጎ ለሞቱም ተጠያቂ እንዲሆኑ አድርጎአቸዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜም ክርስትናን ለማጥፋት ጠላት በሰዎች ላይ እያደረ ክርስቲያኖችን ያስገድላል፤ ያስጨፈጭፋል፤ እንዲሁም ያሳድዳል፡፡ በየጊዜውም በተለያዩ ክፍለ ሀገራት በጅምላ የሚጨፈጨፉት ሕፃናት፣ አረጋዊያን እንዲሁም ወጣቶች ምንም በማያውቁት ምክንያት፣ በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በመናገራቸው ሳቢያ፣ ቤተ ክርስቲያን ሄደው በዓላትን በማክበራቸውና ባህላቸውን ለማስጠበቅ በመፈለጋው ብቻ ነው፡፡ እነዚህ እርኩስ መንፈስ ያደረባቸው ሰዎች የጠላት ተገዢ ከመሆናቸው ባሻገር ለራሳቸውና ለሌሎች ጥፋት መንሥኤ በመሆናቸው እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሐሰተኞችን በመቃወም ለእውነት መመስከር ይገባናል፡፡ ለዚህም በሃይማኖት ጸንቶ መኖር ይጠበቃልና እንጽና!
የቅዱስ እስጢፋኖስ አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን፡፡
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

27 Oct, 08:08


ሲመቱ ለሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕታት ቅዱስ እስጢፋኖስ

የስሙ ትርጓሜ ‹አክሊል› የሆነው በሕገ ወንጌል የመጀመሪያ ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳማዊ ሰማዕት የተባለ ቅዱስ እስጢፋኖስ ‹‹ሊቀ ዲያቆናት›› ከመባሉ በፊትም በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነበር፤ ከዚያም ዲያቆን ሆኖ ተሾሟል፤ ይህም ጥቅምት ፲፯ ቀን ነው፡፡
በሐዋርያት ሥራ ላይ እንደተጠቀሰው ይህ ቅዱስ በመጀመሪያ ገማልያል በተባለ መምህር ትውፊትን፣ ኦሪትንና ነቢያቱን ተምሯል፡፡ በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መዋዕለ ስብከት ወቅትም እርሱ በዋለበት እየዋለ ባደረበት እያደረ ወንጌልን ተማረ፤ ደቀ መዝሙሩም ሆነ፤ ጌታችንም ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ አደረገው፤ አጋንንትም ተገዙለት፡፡ (የሐዋ.፭፥፴፬፣፮፥፭-፲)
በበዓለ ሃምሳም መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከሰባ ሁለቱ አርድእት መካከል የእርሱን ያህል ልሳን የበዛለት ምሥጢርም የተገለጠለት አልነበረም፡፡ በመንፈስ ቅዱስ መሪነትም ወንግልን ሰብኳል፡፡ በቤተ ክርስቲያንም ፈተና ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ሰባት ዲያቆናት ሲመርጡ አንዱ እርሱ ነበር፡፡ የስድስቱ ዲያቆናት አለቃና የስምንት ሺህ ማኅበር መሪ ሆኗል፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በኋላ ለአንድ ዓመት ያህል ስምንት ሺህውን ማኅበረ እየመራ ወንጌልን እየሰበከ ቢጋደል ኦሪት እየጠፋች ወንጌል ደግሞ እየሰፋች ሄደች፡፡ (የሐዋ.፮፥፬)
ቅዱስ እስጢፋኖስም የእግዚአብሔር ጸጋና ኃይል ያደረበትና ታላቅ እንዲሁም ድንቅ ታምራትን የሚያደርግ ሰው ስለነበር በዚያን ጊዜ አይሁድ በምቀኝነት ተነሡበት፤ ከእርሱ ጋርም ክርክር ገጠሙ፤ ነገር ግን ሊያሸንፉት አልቻሉም፤ የእግዚአብሔር መንፈስ አድሮበታልና በፈጣሪ ኃይል አሸነፋቸው፡፡

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

26 Oct, 14:53


የአራተኛ ሳምንት ማኅሌተ ጽጌ
🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀🌺🥀

ነግሥ (የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዐተ ማኅሌት መጀመሪያ)
........................................................................
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።

መልክዓ ሥላሴ
ሰላም ለአፉክሙ ዘማዕፆሁ ሰላም ፣
ጽጌያቲሁ ሥላሴ ለተዋሕዶ ገዳም፡፡
መንገለ አሐዱ አምላክ ንዋየ መጻኢት ዓለም ፣
መልጡ አምልኮትየ በጸጋክሙ ፍጹም ፣
እም አምልኮ ጣዖት ግሉፍ አሐዱ ድርህም፡፡

ዚቅ:
ፈጠርካሆሙ ለመላእክት ከመ ይትለአኩከ ፣
ግብረ እደዊከ አዳም አሠርጎከ ለሰማይ በከዋክብት ፣
ወለምድርኒ በስነ ጽጌያት ፣
ግብረ እደዊከ አዳም ፣
እግዚኦ ፈድፋደ ቃልከ ጥዑም ፡፡

ማኅሌተ ጽጌ:
ናሁ ጸገየ ወወሀበ መዓዛ ፣
ተአምርኪ ናርዶስ ለቤተክርስቲያን ዘይውሕዛ ፡፡
እንዘ ታረውጽኒ ቦቱ ማርያም ፍኖተ ቤዛ ፣
አጉይዪኒ ከመ ወይጠል ወከመ ኃየል ወሬዛ ፣
እምገጸ ኃጢአት አጎተ አርዌ ዘይቀትል ኀምዛ፡፡
ትርጉም፦ ቤተክርስቲያንን የሚያስጌጣት ናርዶስ የተባለ ተዓምርሽ እነሆ አብቦ መዓዛን ሰጠ ማርያም ሆይ በድኅነት ጎዳና እያስሮጥሽኝ እንደ ፌቆና እንደ ዋልያ አውራ አሽሺኝ፡፡

ወረብ:
ናሁ ጸገየ ወወሀበ መዓዛ ተአምርኪ ናርዶስ (2) ይሐውዛ ለቤተክርስቲያን (2)
እንዘ ታረውጽኒ ቦቱ ፍኖተ ቤዛ (2) ማርያም ፍኖተ ቤዛ (2)

ዚቅ:
ነፍሳተ ጻድቃን እውያን አመ ይሁቡ መዓዛ ፣
ለዘምግባረ ጽድቅ አልብነ ይኩነነ ቤዛ ፣
ንግደትኪ ማርያም እስከ ደብረ ቁስቋም እምሎዛ፡፡

ማኅሌተ ጽጌ:
እእሚርየ ማርያም ከመ ዘልፊ ታፈቅሪ ፣
ሰላም መልአከ ለኪ አንተ ጽጌረዳ ትፈሪ፡፡
ለለአማኅኩኪ ባቲ ከመ ገብርኤል አብሣሪ ፣
አፈዋተ ጽጌ እምልሳንየ ትፀርሪ ፣
ትእምርቶ ለሠናይትኪ ምስሌየ ግበሪ ፡፡

ወረብ:
እእሚርየ ማርያም (ከመ) ዘልፊ ታፈቅሪ ሰላመ መልአክ (2)
አንተ ጽጌረዳ ትፈሪ ሰላመ (2) መልአክ (2)
(ለለአማኅኩኪ ከመ ገብርኤል አብሣሪ አፈዋተ ጽጌ (2)  )

ዚቅ:
ሃሌ ሉያ ጸረሐ ገብርኤል ልዑለ ቃል ወይቤ ፣
ጽገዩ ገዳም ተፈሥሒ ገዳም ፣
እስመ ናሁ ናርዶስ ወሀቦ መዓዛሁ ፡፡

ማኅሌተ ጽጌ:
ትመስል እምኪ ማርያም ዕለተ ሣልስት ወራብዕተ ፣
ዘወለደት ጽጌ ወፀሐየ ዓለም ብርህተ ፣
ካዕበ ትመስል ሰብእተ ዕለተ ፣
እስመ ፈረየት ኪያኪ ተአምረ ግዕዛን ሰንበተ ፣
ለእለ በሰማይ ወምድር ዘኮንኩ ዕረፍተ ፡፡
ትርጉም፦ ማርያም እናትሽ አበባን ያስገኘች ሦስተኛይቱ ቀን ማክሰኞን ትመስላለች ዳግመኛም ሰባተኛይቱ ቀን ቀዳሚትን ትመስላለች በሰማይና በምድር ላሉ ፍጥረታት ዕረፍት የሆንሽ የነፃነት ምልክት አንቺን አፍርታለችና አስገኝታለችና፡፡

ወረብ:
ትመስል እምኪ ማርያም ዕለተ ሣልስተ ወራብዕተ ትመስል እምኪ (2)
ዘወለደት ጽጌ (2) ወፀሐየ ዓለም (2)

ዚቅ:
እምኩሉ ዕለት ሰንበተ አክበረ ፣
ወእምኩሎን አንስት ማርያምሃ አፍቀረ ፣
ከመ ትኩኖ ማሕደረ ለመንፈስ ቅዱስ ፣
ወምስጋድ ለኩሉ ዓለም፡፡

ወረብ:
እምኩሉ ዕለት ሰንበተ አክበረ (2)
ወእምኩሎን አንስት ማርያምሃ አፍቀረ ከመ ትኩኖ ማኅደረ ለመንፈስ ቅዱስ (2)

ማኅሌተ ጽጌ:
እንዘ  ተሐቅፊዮ  ለሕጻንኪ  ጽጌ ፀዓዳ  ወቀይሕ ፣
አመ  ቤተ  መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣
ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ እምላህ፣
ወንዒ ሠናይትየ  ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣
ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ ፡፡
ትርጉም፦ ነጭና ቀይ መልክ ያለው አበባ ልጅሽን ታቅፈሽ ወደ ቤተ መቅደስ በገባሽ ጊዜ  ርግቤ ከሐዘን ታረጋጊኝ ዘንድ ነይ የእኔ አዛኝ ደስ ካለው ከገብርኤል እንደ አንቺ ሩኅሩኅ ከሚኾን ከሚካኤል ጋር ነይ፡፡

ወረብ:
እንዘ  ተሐቅፊዮ  ለሕጻንኪ  ጽጌ ፀዓዳ  ወቀይሕ (2)
አመ  ቤተ  መቅደስ ቦእኪ ሠናይትየ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ (2)

ዚቅ:
ዕፀ ጳጦስ ይእቲ እንተ በአማን ፣
ይብልዋ ቅድስተ ቅዱሳን ፣
ንዒ ርግብየ ሠናይት ፣
ወይቤላ መልአክ ተፈሥሒ ፍሥሕት ፣
ቡርክት አንቲ እም አንስት ፣
ንዒ ርግብየ ሠናይት፡፡

ወረብ:
ንዒ ርግብየ (2) ምስለ ሚካኤል (2)
ወንዒ ሠናይትየ (2) ምስለ ገብርኤል ፍሱሕ (2)

ማኅሌት
ክበበ ጌራ ወርቅ  ጽሩይ  እምዕንቈ ባሕርይ ዘየኃቱ፣
ዘተጽሕፈ  ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ  ሞቱ፣
አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ  ቀጸላ መንግሥቱ፣
አንቲ ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፣
ወለኪኒ  ይሰግድ  ውእቱ፡፡
ትርጉም፦ በስሙ ምልክትና የሞቱ መታሰቢያ የታነፀብሽ ከሚያበራ ወርቅ ይልቅ እንደ ዕንቁ የጠራ ንጽህና ያለሽ የጊዮርጊስ የመንግሥቱ ሽልማት የአበባ አክሊል ማርያም ሆይ አንቺ ኹሉን ለእርሱ ታሰግጂለታለሽ እርሱም ለአንቺ ይሰግዳል፡፡

ወረብ:
ክበበ ጌራ ወርቅ ዘየኀቱ እምዕንቁ ባሕርይ (2)
ማርያም አክሊለ ጽጌ ለጊዮርጊስ ቀፀላ መንግሥቱ (2)

ዚቅ:
ይእቲ ተዓቢ እም አንስት ፣
አሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት ፣
መድኃኒቶሙ ለነገሥት አክሊል ንፁህ ለካህናት ፣
ብርሃኖሙ ለከዋክብት፡፡

ወረብ:
ይእቲ ተዓቢ እም አንስት እሞሙ ለሰማዕት ተዓቢ (2)
መድኃኒቶሙ ለነገሥት ፋሲለደስ ወኢያሱ መድኃኒቶሙ (2)

ሰቆቃወ ድንግል:
አይቴኑ መልአክ ዘአብሠረኒ ፣
ብካይየ ይርአይ ወይርድአኒ ፣
ወአልብየ ሰብእ ዘየአምረኒ ፣
እንዘ ትብሊ ድንግል እራኅራኅከኒ ፣
በገዳም አመ ነሥኡኪ ልብሰ ወልድኪ ረቡኒ ፣
ጸላኢ ወተቃራኒ ፈያታይ ማኅዘኒ ፡፡

ወረብ:
አይቴኑ መልአክ ዘአብሰረኒ (2) ገብርኤል ወይርድአኒ (2)
እንዘ ትብሊ ድንግል እራኅርከኒ አልብየ ሰብእ ዘየአምረኒ (2)

ዚቅ:
አመ ወጽአት በፍርሃት እም ሀገረ ዳዊት ዘይሁዳ ፣
በብሥራተ መልአከ እንግዳ ፣
ኢረከበት ማየ በፍኖት ዘታሰቅዮ ለወልዳ፡፡

መልክአ ውዳሴ:
ለኪ ይደሉ ውዳሴ ወስባሔ ፣
በአፈ መላእክት ወሰብእ እለ ይነብሩ ውስተ ኩለሄ ፣
ማርያም ድንግል ማርያም አመ ኤሎሄ ፣
ከመ ሰብሐዊ ፍቁርኪ አቀረብኩ እማኄ ፣
ለዝክረ ስምኪ ዘይምዕዝ እምርኄ፡፡
 
ዚቅ:
ለኪ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወስግደት ፣
እምኀበ ሰብእ ወመላእክት ፡፡

መዝሙር:
ሠርዓ ሰንበተ ለዕረፍት ፣
ኩሉ ነባሪ ወቀናዪ ያዕርፉ ባቲ ፣
ግብረ እደዊከ አዳም ፣
ለሐኮ ለሰብእ በአርአያከ ወበአምሳሊከ ፣
ግብረ አደዊከ አዳም ፣
ፈጠርካሆሙ ለመላእክት ከመ ይትለአኩከ ፣
ግብረ እደዊከ አዳም ፣
አሠርጎከ ለሰማይ ወለከዋክብት ፣
ወለምድርኒ በስነ ጽጌያት ፣
ግብረ እደዊከ አዳም ፣
እግዚኦ ፈድፋደ ቃልከ ጥዑም፡፡

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

26 Oct, 03:41


ፕሮቴስታንት ወንድም እኅቶቼ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ሌላ መጽሐፍት አያስፈልግም ለምትሉ ኢያሱ የጠቀሰውን መጽሐፍ ወዲህ በሉ?እኛ ከተሳሳትን ከኢያሱ ጋር ነው ።እናንተ ግን ከኢያሱ ከበለጣችሁ ፀሐይን በገባኦን ሰማይ አቁሙና አሳዩን።


ኢያሱ 10÷13
13: ሕዝቡም ጠላቶቻቸውን እስኪበቀሉ ድረስ ፀሐይ ቆመ፥ ጨረቃም ዘገየ። ይህስ በያሻር መጽሐፍ የተጻፈ አይደለምን? ፀሐይም በሰማይ መካከል ዘገየ፥ አንድ ቀንም ሙሉ ያህል ለመግባት አልቸኮለም።

ሌላ የሰራቸው ተአምራት በሌላ መፅሐፍ ቢመጣላችሁ አታምኑም አይደል?


ዮሐንስ 20÷30
³⁰ ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤
³¹ ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።


ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

25 Oct, 15:16


በየሚዲያው ስለሚዘዋወረው ይህ ዓይነት ነገር ቤተክርስቲያን አስተምህሮዋ ምንድነው እያላችሁ በውስጥ ለምትጠይቁኝ
ጠቅለል ያለው ምላሼ ቤተክርስቲያን እንደዚህ ሁኑ አትልም ።
በየቦታው የማር ጸበል የምን እምነት እየተባለ ያለውን ነገር ለራሳችሁና ለህሊናችሁ ተጠንቀቁ።መዳን ከፈለግህ ንስሐ ግባ ሥጋወደሙን ተቀበል መልካም ነገር አድርግ ከትዕቢት ራስህን ጠብቅ አበቃ ቤተክርስቲያን በውሳጣዊ የማታውቀው የመንደር መማክርትና ወጠምሻ እየመጣ ሲበዘብዛት ማየት ግን ያሳምማል ።


ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

24 Oct, 20:07


Peace is the original state of this universe. It was also the
original state before the world was created. Since the beginning
of time, God alone has been in perfect peace. Millions of years
have passed or millions of millions of years, more than that
even; in fact before time existed and before its dimensions were
known, the original state was peace.
God began to work in peace and His first work was the
Creation. In perfect peace God created everything... "Then
God said, "Let there be light"; and there was light. And God
saw the light, that it was good;" (Gen. 1:3-4

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

24 Oct, 19:49


የእኛ ናቸውና እናግዛቸው
እኛም ነገ ምን እንደምንሆን አናውቀውም ምን እንደሚገጥመን እሱ መድኃኔዓለም ብቻ ነው የሚያውቀው ።
በትናንትናው ዕለት የገዳሙ አበምኔት ደውለው በሰላም እጦት(ጦርነት ) ምክንያት ጸበለተኞች ስንቅ አመላልሰው ራሳቸውን እየመገቡ ሱባኤያቸውንና ጸበል መከታተል አልቻሉም እባካችሁ የምትችሉ ከሆነ ለጸበለተኞች ገብስ ገዝተን አስፈጭተን በሶ ለመስጠት ፣ስኳር እና ሌሎች ነገሮችን መደጎም እንችል ዘንድ አሳስብልን አሉኝ
የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ከአሁን በፊት ለኮቪድ ጊዜ እንዳደረግነው ለገዳሙ ቅርብ የሆናችሁ ገብሱን ወይም ሽንብራውን ገዝታችሁ ማቅረብ ብትችሉላቸው በሩቅ ያለን ደግሞ የምንችለውን ከታክሲ ከቁርስ ከአስራታችን ቀንሰን ይህን ብናደርግ

ዲ/ን ኤርምያስ


0912494703

@sekokaw
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

23 Oct, 17:45


ስሜ ናፈቀኝ


ዕቃ ለማውጣት ቦሌ ወደሚገኘው የካርጎ ተርሚናል ሄጃለሁ፡፡ መቼም ዘመድ ውጭ ሀገርያለው ሰው ደጋግሞ የሚሄደው አንድም ለወዳጁ እድሜ ከጤና ለመለመን ቤተ ክርስቲያን፣ አንድም የተላከለትን ዕቃ ለመውሰድ ካርጎተርሚናል፣ አንድም የዓመት በዓል ብር ለመቀበል ባንክ ቤት ነው፡፡

ወረፋውን ጠብቄ መስኮቱ ጋ ደረስኩና ስሜን አስመዘገብኩ፡፡ እስክትጠራ ጠብቅ ተብዬምወንበር ፈልጌ ተቀመጥኩ፡፡ ከጎኔ አንድ ጎልማሳ ተቀምጦ ይቁነጠነጣል፡፡ አንዴ ፀጉሩን አንዴ ዓይኑን ያሻል፡፡ ኩኩሉ እንደሚልአውራ ዶሮ አንገቱን ከወዘወዘ በኋላ ወደ እኔ ዞር አለና ‹‹ስምህ ናፍቆህ ያውቃል›› አለኝ፡፡

ገረመኝና ‹‹ስሜማ አብሮኝ ነው የሚኖረው፤ ምን ብሎ ይናፍቀኛል›› አልኩት፡፡

‹‹ስምህን ሰጥተህ አታውቅም፤ አሁን ስምህን አልሰጠህም እንዴ›› አለኝ፡፡

ይበልጥ ግራ ገባኝና ‹‹እና ወሰዱት ማለት ነው›› አልኩት ሳቅ እያፈነኝ፡፡

‹‹ታድያስ፤ አሁንኮ ወሳኙ እነርሱ ጋር ያስመዘገብከው ስምህ እንጂ አንተ ጋ ያለውስምህ አይደለም፡፡ አንተ እገሌ መሆንህ ቁም ነገር የለውም፡፡ እነርሱ ‹እ-ገ-ሌ› ብለው ሲጠሩህ ነው ሕይወትህየሚንቀሳቀሰው፡፡ እኔ አሁን ስሜ ናፍቆኛል፡፡ ስሜ ሲጠራ መስማት፣ ስሜ ሲጠራ አቤት ማለት ናፈቀኝ፡፡››

የእርሱን ስሰማ እኔም ስሜ ይናፍቀኝ ጀመር፡፡ ‹‹ትጠራላችሁ›› አይደል ያሉን፤እውነትም ስማችንን ወስደውታል ማለትኮ ነው፡፡ ካልጠሩን ቁጭ ብለን መቅረታችን ነው፡፡ የተጠሩት ደግሞ እየተፍነከነኩ ወደመስኮቱ እየተጠጉ ነው፡፡ ሰልፉ ሲረዝም፣ ጊዜው ሲሄድ፣ መቀመጥም ሲሰለቻችሁ ደግሞ ስማችሁ ይበልጥ ይናፍቃችኋል፡፡

‹‹እዚህ ብቻ ነው ወይስ ሌላውም ቦታ ወረፋ አለው›› አልኩት፡፡

‹‹ምን እዚህ ብቻ ኑሮህኮ እንደዚሁ ነው፡፡ ስም ትሰጣለህ፣ ትጠብቃለህ፣ ስምህንትናፍቃለህ፣ እድለኛ ከሆንክ ትጠራለህ፣ አቤት ትላለህ፣ ወደ ሌላው ምእራፍ ትሻገራለህ፡፡ እዚያም ስም ትሰጣለህ፣ ስምትናፍቃለህ፣ ትጠራለህ፣ አቤት ትላለህ፣ እንዲህ እያልክ ትኖራለህ፡፡ አቤት ካላልክ ደግሞ ችግር ነው፡፡ ያልፍሃል፡፡ አሁን ያሰውዬ ስልክ እያወራ አለፈው፡፡ ‹አቤት› ማለት ነበረበት፡፡ አሁን እንደገና ስሙ እየናፈቀው ነው፡፡ ያኛው ደግሞ ስሙቢናፍቀው፣ ቢናፍቀው የሚጠራው አጥቷል፡፡እየደጋገመ ‹ጥሩኝ እንጂ› ይላል፡፡‹ቆይ እንጠራሃለን› ይሉታል፡፡ አሁን አንተንበስልክ ጠርተውህ ነው አይደል የመጣኸው? አሁን ይኼ ጋቢ ነገርየለበሰው ሰው ለምን አትጠሩኝም ብሎ ነው ከክፍለ ሀገር የመጣው፡፡ ስሙ ናፍቆት፡፡ ልጁ ደውላ ዕቃ ልኬልሃለሁ አለቺው፡፡ እርሱካሁን አሁን ስሜ በስልክ ይጠራል ብሎ ቢጠብቅ ቀረበት፡፡ ስሙ ሲናፍቀው መጣና ‹እባካችሁ ጥሩኝ› አለ፡፡ እነርሱ ደግሞ‹ሀገርህ ተመለስና ስንጠራህ ትመጣለህ› ይሉታል፡፡ ስሙ የናፈቀው ሰው መች እንዲህ በቀላሉ ይመለሳል፡፡››

‹‹እውነትምኮ ስም የሚያስናፍቁ አሠራሮች ሞልተዋል›› አልኩት ለመጎትጎት

‹‹ቤት ለማግኘት ትመዘገባለህ፣ ስምህ ይናፍቅሃል፡፡ ጋዜጣ ላይ ወጣ፣ ተለጠፈ፣በሬዲዮ ተነገረ በተባለ ቁጥር ስምህን ማየት ትናፍቃለህ፡፡ እዚያ ዝርዝር ውስጥ ስታጣው ቅር ይልሃል፡፡ ስኳር ለማግኘትትመዘገባለህ፣ ከሻሂው ሱስ ይልቅ ስምህን የመስማት ሱስ ይይዝሃል፡፡ ሥራ ለማግኘት ትመዘገባለህ፣ እንጠራሃለን ስትባልትጠብቃለህ፤ ከዚያ ስልክ ባቃጨለ ቁጥር እመር ብለህ ትነሣለህ፤ የሆነ ሰው ስምህን ሲጠራው፣ አንተም አቤት ስትል ለመስማትትናፍቃለህ፡፡ ጓደኛህ ደውሎ በቅጽል ስምህ ከጠራህ ትናደዳለህ፡፡ አንተ የምትጠብቀው ‹አቶ እንትና ነዎት› ተብሎ ሲጠራ መስማትነዋ፡፡ ››

‹‹ቆይ ግን ለምን ይመስልሃል ስማችን እስኪናፍቀን የምንደርሰው››

‹‹አንደኛ ለምዶብናል፡፡ ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ ስም ጠሪ መምህር ተመድቦ ስም መጥራትተለምዷል፡፡ ዕድር ላይ ይጠራል፤ ፍታት ላይ ይጠራል፤ ዕቁብ ላይ ይጠራል፤ ቡና ለመጠጣት ይጠራል፤ እሥረኛ ለመጠየቅ ይጠራል፤ቪዛ ለመጠየቅ ይጠራል፤ ስም መጥራት ባህላችን ሆኗል፡፡ ሁለተኛ ደግሞ ስማቸው የሚጠራና የማይጠራ ስላሉ ነው፡፡ ስማቸውሊጠራ የሚችል፣ ስማቸው የማይጠራና ስማቸው ሳይጠራ እንደተጠራ የሚቆጠሩ አሉ፡፡ ስማቸው ሊጠራ የሚችለው እንደእኔና አንተ ያሉት ናቸው፡፡ ዕድል ካለህ ስምህ ይጠራል፡፡ ስማቸው የማይጠራው ደግሞ አንዳች ምክንያት የሚኖራቸው ናቸው፡፡ ስማቸውመጠራት የማያስፈልጋቸው ደግሞ ጉዳያቸው በውስጥ የሚያልቅላቸው ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ስማቸው የወርቅ ቁልፍ ነው፤ ብዙቢሮዎችን ይከፍታል፤ ወይም ደግሞ የወርቅ ቁልፍ ያንጠለጠለ ስም የሚያውቁ ናቸው፡፡ አንዳንዴኮ ስምን መናፈቅ ይሻላል፡፡ ጭራሽስምህ ይጠፋልኮ››

‹‹አንተ ዋናው ክፉ አትሥራ እንጂ ስምህ ቢጠፋ ምን ችግር አለው? ከባሰ በሕግ መጠየቅ ነው››

‹‹ኖ ኖ ኖ ኖ ኖ እንደዚያ አይደለም፤ ስምህ ከነ ጭራሹ ከመዝገብ ላይ ይጠፋልእንጂ፤ ስምህ አልተመዘገበም፤ ‹ዳታ› ውስጥ የለም፡፡ ኮምፒውተር ውስጥ አልገባም፤ መዝገብ ላይ አልተገኘም፤ ፋይሉ ጠፍቷል፤ትባላለህ፡፡ አንዳንዱ ስምማ ይገርምሃል እንደ ቁልፍ ማንጠልጠያ ወልቆ የሚጠፋ ነውኮ የሚመስለው፤ በተመዘገበበት ቦታአታገኘውም፡፡ አሁን የእኔ ስም ዕድር ልከፍል ከሄድኩ አንደኛ ነው የሚጠራው፤ ስኳር ልወስድ ከሄድኩ ግን ጭራሽ ሳይጠራ ሊቀርይችላል፡፡ ለክፍያና ለመዋጮ ብቻ የታደሉ ስሞች አሉ፡፡ ለመቀበል ብቻ የታደሉ ስሞችም አሉ፡፡ ሁለቱንም ስሞች በየመዝገባቸውነው የምታገኛቸው፡፡ አንተ አንዴ እንኳን ስምህ አልጠራ ብሎህ እየናፈቀህ አንዳንድ ሰዎች ሁለትና ሦስት ጊዜ ስማቸው ሲጠራ ስታይ፣ስም የሌለህ ሁሉ ይመስልሃል፡፡››

‹‹ግን ለሥራና ለስም የታደሉ ሰዎች የሉም››

‹‹ሞልተው፤ አሁን እኛ ሀገር ሊቅ፣ ሳይንቲስት፣ እውነተኛ ነጋዴ፣ ባለሞያ፣ ሥራፈጣሪ፣ ገበሬ፣ ምናምን ለስም ያልታደሉ ናቸው፡፡ ስማቸውን የደመወዝ መክፈያና ግብር ሰብሳቢ ብቻ የሚያውቀው፤ አርቲስት፣ዘፋኝ፣ ቀልደኛ፣ ደግሞ ለስም የታደሉ፡፡ እስኪ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የአንድ ሳይንቲስት ቤት ዓመት በዓል ሲያከብር አይተህ ታውቃለህ? የአንድ የረዥም ርቀት አሽከርካሪ ቤት ገብቶ ኑሮውን ሲያስቃኝ አይተህ ታውቃለህ? እነዚህ ለስም ያልታደሉ ናቸው፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ሥራውን የሠሩት፣ የደከሙት፣ የለፉትስማቸው ሳይጠራ መጨረሻ ላይ የሚጨመሩ ቅመሞች ስማቸው ሲጠራ ትሰማለህ፡፡››

ይህንን እያወራልኝ በድምጽ ማጉያ ስም መጥራት ተጀመረ፡፡ አምስት ሰዎች ተጠሩ፡፡አብሮኝ የነበረው ሰው ግን አልተጠራም፡፡ በድምጽ ማጉያው ‹መሐሪ ተሾመ› የሚል ስም ሲጠራ ከእኛ ፊት ለፊት ባለው ወንበር ላይየተቀመጠው ሰው ‹ወንድ ከሆንሽ መሐሪ አስቻለው ብለሽ አትጣሪም›› አለ፡፡

‹‹መሐሪ አስቻለው ብሎ መጣራት የወንድነት መለኪያ ሆነ እንዴ›› አልኩት

‹‹መሐሪ አስቻለው እኔ ነኛ››


@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

23 Oct, 14:38


WHAT IS FAITH?
In the name of the Father and of the Son
and of the Holy Spirit One God. Amen.
Faith is not merely adopting a set of beliefs that you may say in the “Creed”, but a way of life or adherence to that which leads to life.
To what benefit is believing in God without having a relationship with him, obeying and loving Him?
In addition, what is the benefit of believing in eternity and in life after death if one does not prepare for it by repentance, spiritual vigil, and loving God? And to what benefit is believing in virtues if one does not live them? Therefore there is a big difference between theoretical faith which does not save the soul, and practical faith, the fruits of which are evident in one's life..
St. Paul wrote, “Examine yourselves as to whether you are in the faith. Test yourselves.
Do you not know yourselves” (2 Cor.13÷5)

Dn Ermias
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

21 Oct, 07:02


ሴትየዋ ችግሯን ልታማክር ወደ ዶክተር ሄደች።
"ዶክተር እባክህ አንድ ችግር ገጥሞኛል።"
"ምን ገጠመሽ?"
".…ከወለድኩ ገና አንድ አመት አልሞላኝም። ሆኖም ሌላ ልጅ አርግዣለሁ። እኔ ደግሞ ተጨማሪ ልጅ በዚህ ወቅት እንዲኖረኝ አልፈልግም።"
"እና ምን ልርዳሽ?""
"ሆዴ ውስጥ ያለውን ልጅ ማስወረድ እፈልጋለሁ!"
ዶክተሩ ትንሽ አሰብ አደረገና “ለምን ከዚህ የተሻለ ሀሳብ አላቀርብልሽም?” ሲል ጠየቃት።
“ምን አይነት ሀሳብ?”
“አየሽ ይሄን ልጅ ከሆድሽ ለማስወረድ ብዙ ችግር ውስጥ ትገቢያለሽ፣ ደም ይፈስሻል ልትሞቺ ወይም በቀጣይ ላትወልጂ የምትችይበት አጋጣሚም ሊፈጠር ይችላል። ስለዚህ ይሄን ሁሉ ችግር ከምታይ ለምን በእጅሽ ያቀፍሽውን ልጅ አንገድለውም?” አላት
ሴትየው ደነገጠች። ዶክተሩ ንግግግሩን ቀጠለ።
“አዎ! ለእናት እንደሆነ ሁሉም ልጅ እኩል ነው። ስለዚህ አንዱ መሞት ካለበት ሆድሽ ውስጥ ያለው ከሚሞት ይሄኛው የተወለደው ቢሞት ምንም ችግር ሳይገጥምሽ ሀሳብሽን ታሳኪያለች…” እያለ ምክረ ሀሳቡን መተንተን ጀመረ።
ሴትየዋ ግን በጆሮዋ የሚንቆረቆረው የዶክተሩ ሀሳብ ሳይሆን የአምላክ ማሳሰቢያ መሆኑን እያሰበች ለማስወርድ የዘረጋቻቸውን ሁለት እግሮቿን ሰብስባ ብድግ ብላ ክፍሉን ለቃ መውጣት ጀመረች።..…ልጆቿን አንዱን በክንዷ ሌላውን በሆዷ እንዳቀፈች ወደ ቤቷ ተመለሰች። አዎ! የተወለደም በሆድ ውስጥ ያለም ቢሆን ለእናት ልጆቿ ሁሉ እኩል ናቸው!

ህጻናትን በውርጃ መግደል ወንጀልም ኃጢዓትም ነው!
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

20 Oct, 17:12


መድኃኔዓለም በእድሜ ይጠብቅልን

በእውነት እግዚአብሔር አምላክ በጎደለ ይሙላላችሁ መድኃኔዓለም ያላሰባችሁትን ይስጣችሁ።
  አስራታቸውን ስዕለታቸውን እንዲያስገቡ በረከቱን እያበዛላቸው እየባረካቸው ለምሕረት የማይታጠፉ እጆቹ እንደማይጎድል ውሃ  እያፈሰሰላቸው ነው ።
እግዚአብሔር ይቀበልላችሁ እም ብርሃን አትለያችሁ የሰላም አምላክ ሰላምን ይስጣችሁ።



በሚሞት ሥጋችን አንመካ በገንዘባችን ባለን የኃብት መጠን አንመዛዘን።
ገንዘባችሁ አያጸድቃችሁም መቶ ሺ ብር ሰርቃችሁ ሃያ ሺ ብር ብትሰጡ አትጸድቁም ገንዘባችሁ ከንጽሕና ጋር ሲሆን እንጂ ።እግዚአብሔርን በአስራታችን አንስረቀው እግዚአብሔር ከአስር ብር ውስጥ አንድ ብር የሚጠይቀን ዘጠኙን ሲጠብቅ ነው ሲያበዛልን የበረከት ሲያደርግልን ነው

EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @sekokaw ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

20 Oct, 16:44


👌አኑረን እንዳንል ኑረን ምን አፈራን፣
ግደለን እንዳንል እሳትህን ፈራን፣
ጸሎቱ ጠፍቶናል በፈለግኸው ምራን።
🙏

ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ይህ ቀረሽ የማትባል ዘመን የሌላት ዘመናዊት ናት ይሁን እንጂ በዓመት አንድ ጊዜ በሚከወነው የዓለም አቀፍ የሰበካ ጉባኤ ትዝብቴን ላካፍላችሁ እንዲያው የእናንተንም አስተያየት ወዲህ በሉኝ።
፩) ከንቱ መሞጋገስ መንቆለጳጰስ እገሌ ይቀየማል እገሌ ቅር ይለዋል ብለው መሰለኝ 😂

፪)የአንድ ሊቀ ጳጳስ ሥራው ምንድነው ?ወደ ሀገረ ስብከቱ ሲመጣ አቀባበል አደረግንለት፣አንድ ጳጳስ አስቀደሱ ፣ባረኩ ፣ክህነት ሰጡ ብሎ ሪፖርት ማድረግ ይህን ማኅበረ ምዕመናን መናቅ አይመስልም ወይ? እና ሥራቸው ምንድነው ድሮስ ? በዚህ ዓመት ክህነት ሰጡ ቀደሱ ተብሎ ሪፖርት ቀረበ ወትሮስ ምንድነው ሥራቸው ክህነት ያልሰጡበት ጊዜ አለ??
፫)በስልክ በሰጡት መመሪያ እንዲህ አደረግን ምን ማለት ነው አዲስ አበባ ተቀምጦ ቤተክርስቲያንን ማስተዳደር ወጀብ ለበዛባት መርከብ መልካም ነው ወይ?

አስተያየት :-ቤተክርስቲያን ውስጥ መሸላለም ቢቀር ያልተሸለመ አድፍጦና እእእኽ እያለ ከሚሄድ አርአያ የሚሆን አንድ ሀገረ ስብከት ሥራን በተግባርና በVideo በታገዘ ቢያሳይ ሪፖርት ቢያቀርብ ።
ደብቆት የኖረው
ለራስ እውነት ያለው
ሁሉም ውሸት አለው!



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

19 Oct, 20:52


ማኅሌተ ጽጌ በሰዓሊተ ምሕረት አዲስ አበባ
https://youtube.com/live/RJ9ZcjNpeAE?feature=sharedhttps://youtube.com/live/RJ9ZcjNpeAE?feature=shared

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

18 Oct, 18:44


ዚቅ፦
====
በትረ አሮን እንተ ሠረፀት ወባቲ ይገብሩ ተአምረ
በውስተ አህዛብ እስመ አርአያ መስቀል ይዕቲ
ማኅሌተ ጽጌ፦
==+++====
ትመስል እምኪ ማርያም ዕለተ ሣልስተ ወራብዕተ፤
ዘወለደት ጽጌ ወፀሐየ ዓለም ብርህተ፤ካዕበ
(ወካዕበ) ትመስል ሳብዕተ ዕለተ፤እስመ ፈረየት
ኪያኪ ተአምረ ግዕዛን ሰንበተ፤ ለእለ በሰማይ
ወምድር ዘኮንኪ ዕረፍተ።
ወረብ፦
=====
ትመስል እምኪ ማርያም ዕለተ ሣልስተ ወራብዕተ
ትመስል እም/፪/
ዘወለደት ጽጌ ጽጌ ጽጌ ወፀሐየ ዓለም/፪

ዚቅ፦
===
እምኲሉ ዕለት ሰንበተ አክበረ ወእምኲሎን
አንስት ማርያምሃ አፍቀረ ከመ ትኩኖ ማኅደረ
ለመንፈስ ቅዱስ ወምስጋድ ለኲሉ ዓለመ።
ማኅሌተ ጽጌ፦
===+=====
እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ ፣
አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣
ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ እምላህ፣ወንዒ ሠናይትየ
ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ።

ወረብ፦
====
እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ/፪/
ንዒ ርግብየ ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል
ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ/፪/

ዚቅ፦
===
ንዒ ርግብየ ሰላማዊት፤ ተመየጢ ወንርአይ ብኪ
ሰላመ፤ በአምሳለ ወርቅ ይግበሩ ለኪ ኮሰኮሰ
ዘብሩር፤ አመ ወለደቶ አርአያ ወሰደቶ፤
በትእምርተ መስቀል፤ ትፍሥሕትኪ ውእቱ፤
ብርሃንኪ ውእቱ ሰላምኪ።

ዚቅ(ዓዲ)፦
=======
ወይቤላ ንዒ ንሑር፤ኀበ ደብረ ከርቤ ውስተ
አውግረ ስኂን፤ እኅትየ መርዓት ርግብየ ሠናይት።

ማኅሌተ ጽጌ፦
=====+++
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘየኃቱ፤
ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤
አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ
ቀጸላ መንግሥቱ፤አንቲ ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤
ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡
ሰቆቃወ ድንግል፦
===========
ብክዩ ኅዙናን ኀልየክሙ ስደታ፤ወላህዉ ፍሡሐን
ተዘኪረክሙ ብዙኃ ሠናይታ፤ማርያም ተዓይል
ከመ ዖፍ ውስተ አድባረ ግብጽ ባሕቲታ፤ተአወዩ
በኃጢኦታ ሀገረ አቡሃ ኤፍራታ፤ወደመ ሕፃናት
ይውኅዝ በኵሉ ፍኖታ።

ወረብ፦
ብክዩ ኅዙናን ኀልየክሙ ስደታ ለማርያም/፪/
ማርያም ተዓይል ከመ ዖፍ ባሕቲታ ውስተ አድባረ
ግብጽ ተዓይል/፪/
ዚቅ፦
አመ አጒየይኪ እምሰይፍ ዕጓለኪ በሐቂፍ፤
0አድባራተ ኤልኪ ከመ ዖፍ፤ እንዘ ከመ ዝናም
ያንደፈድፍ፤እምአዕይንትኪ አንብዕ ወእመላትሕኪ ሐፍ።
ወረብ፦
አመ አመ አጒየይኪ ዕጓለኪ በሐቂፍ/፪/
እንዘ ከመ ዝናም ያንደፈድፍ እምአዕይንትኪ
አንብዕ ወእመላትሕኪ ሐፍ/፪/

ሰቆቃወ ድንግል ዓዲ
====+++===++
ኀበ አዕረፍኪ እግዝዕትየ ማርያም ታሕተ ጽላሎተ
ዕፅ እምፃማ፤ፈያት ክልኤቱ ሶበ በጽሑኪ በግርማ፤
እምትሕዝብተ ሞቱ ማሕየዊ ለወልድኪ ንጉሠ
ራማ፤እፎኑ አዕይንትኪ ማያተ አንብዕ አዝንማ፤
አዕይትየ ለገብርኪ ክልኤሆን ይጽለማ።
ዚቅ፦
=+=
ሐፃቤ ርስሐትየ ይኩን አንብዕኪ ዘአንፀፍፀፈ ዲበ ምድር አመ ወልድኪ ይፄዓር በመልዕልተ

መዝሙር፦
====+==
ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፣ወመኑ መሐሪ ዘከማከ
ምስለ ኖኅ ኪዳነ ዘዓቀምከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ ምስለ ኖኅ ኪዳነ ዘአቀምከ ለደቂቀ
እስራኤል መና ዘአውረድከ ወበጽጌያት ምድረ
አሠርጎከ፤ወመኑ መሐሪ ዘከማከ ወበጽጌያት ምድረ
አሠርጎከ ወስነ ገዳምኒ ምስለ ቅዱሳኒከ ፤ ወመኑ
መሐሪ ዘከማከ ወከመ ወሬዛ ኀይል መላትሒሁ፤
ጉርዔሁ መዓርዒር አምሳሉ ዘወይጠል፤ ወመኑ
መሐሪ ዘከማከ ሰማይ ወምድረ ዘአንተ ፈጠርከ
ፀሐየ ወወርኃ ዘአስተዋደድከ፤ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ በከዋክብት ሠማይ ዘከለልከ ወበጽጌያት
ምድረ አሠርጎከ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ ቀደሳ
ወአክበራ አዕበያ ለሰንበት ወአልዓላ እምኩሉ
ዕለት፤ማ፦ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፥ ወኩሉ ይሴፎ
ኪያከ።

አመላለስ፦

ወመኑ መሐሪ ዘከማከ/፪/
ወኩሉ ይሴፎ ኪያከ ወኩሉ ይሴፎ ኪያከ/፪/

መልካም ማኅሌት !!
ጥቅምት 09/2017

         @mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

18 Oct, 18:44


ሥርዓተ ማኅሌት ዘጽጌ፣ አንደኛ ዓመት ሦስተኛ ሳምንት
============+++==================
መልክዓ ሥላሴ፦
========++
ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤
ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወፀ ለሣህል፤እምኔክሙ
አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ተፈጸመ ተስፋ አበው
በማርያም ድንግል፤ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት
መስቀል፡፡
ዚቅ፦
==++
ዝኬ ዘተዘርዓ ቃለ ጽድቅ በትውክልተ መስቀል፤
ወፍሬሁኒ ኮነ መንፈሰ ህይወት፤ ተስፋሆሙ ለእለ
ድኅኑ፤ ወበጽጌሁ አርዓየ ገሃደ አምሳለ ልብሰተ
መለኮት፤ ዕቊረ ማየ ልብን፤ ጽጌ ወይን
ተስፋሆሙ ለጻድቃን
ማኅሌተ ጽጌ፦
==+++====
በትረ አሮን ማርያም ዘሠረጽኪ እንበለ ተክል፤
ወጸገይኪ ጽጌ በኢተሰቅዮ ማይ ወጠል፤
ወበእንተዝ ያሬድ መዓርዒረ ቃል፤ ምስለ ሱራፌል
ይዌድሰኪ ወይብል፤ ሐጹር የዓውዳ ወጽጌረዳ
በትእምርተ መስቀል።

ወረብ፦
=====
በትረ አሮን ማርያም ዘሠረጽኪ እንበለ ተክል/፪/
ምስለ ሱራፌል ይዌድሰኪ ያሬድ ወይብል ሐጹር
የዓውዳ ወጽጌረዳ በትእምርተ መስቀል/፪/

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

18 Oct, 04:17


የእኛ ናቸውና እናግዛቸው
እኛም ነገ ምን እንደምንሆን አናውቀውም ምን እንደሚገጥመን እሱ መድኃኔዓለም ብቻ ነው የሚያውቀው ።
በትናንትናው ዕለት የገዳሙ አበምኔት ደውለው በሰላም እጦት(ጦርነት ) ምክንያት ጸበለተኞች ስንቅ አመላልሰው ራሳቸውን እየመገቡ ሱባኤያቸውንና ጸበል መከታተል አልቻሉም እባካችሁ የምትችሉ ከሆነ ለጸበለተኞች ገብስ ገዝተን አስፈጭተን በሶ ለመስጠት ፣ስኳር እና ሌሎች ነገሮችን መደጎም እንችል ዘንድ አሳስብልን አሉኝ
የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ከአሁን በፊት ለኮቪድ ጊዜ እንዳደረግነው ለገዳሙ ቅርብ የሆናችሁ ገብሱን ወይም ሽንብራውን ገዝታችሁ ማቅረብ ብትችሉላቸው በሩቅ ያለን ደግሞ የምንችለውን ከታክሲ ከቁርስ ከአስራታችን ቀንሰን ይህን ብናደርግ

ዲ/ን ኤርምያስ


0912494703

@sekokaw
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

17 Oct, 10:06


ይህ የእኛ ግሩፕ አይደለም ይጠንቀቁ ፕሮፋይልም ስምም አንድ አይነት በማድረግ በቴሌግራምም በቲክቶክ በእንስታግራም የሚንቀሳቀሱ አሉ
የእኛ ብቸኛ ፔጅ
@mahtotetonetor2
እና @mahtotetonetor1 ነው

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

17 Oct, 09:42


ክርስቲያኑም ሙስሊሙም በአንድ ቃል"አባ" የሚላቸው የፍቅር ሰው የዘመናችን ጻድቅ አባ መፍቀሬ ሰብእ አረፉ።
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

15 Oct, 20:20


በሚሞት ሥጋችን አንመካ በገንዘባችን ባለን የኃብት መጠን አንመዛዘን።
ገንዘባችሁ አያጸድቃችሁም መቶ ሺ ብር ሰርቃችሁ ሃያ ሺ ብር ብትሰጡ አትጸድቁም ገንዘባችሁ ከንጽሕና ጋር ሲሆን እንጂ ።እግዚአብሔርን በአስራታችን አንስረቀው እግዚአብሔር ከአስር ብር ውስጥ አንድ ብር የሚጠይቀን ዘጠኙን ሲጠብቅ ነው ሲያበዛልን የበረከት ሲያደርግልን ነው

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

15 Oct, 17:45


ምክራችሁን እንሻለን

ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንኳን ለአባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ በዓለ ክብር አደረሳችሁ።የእጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ገዳምን በዘላቂነት ራሱን ችሎ እንዲቆም ብዙ ስንረባረብ እንደሆነ ሁላችሁም የምታውቁት ሐቅ ነው ።
፩) ማለትም በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኝ የወረዳ ከተማ ላይ 300ካሬ የሚሆን ቦታ በዚሁ ግሩፕ በተሰበሰበ ገንዘብ እንደገዛን ታስታውሳላችሁ ግንባታውን እንዳንጀምር በአካባቢው ባለው ሰላም እጦት ምክንያት ሲምንቶ ፣ብረት ፣ብሎኬት ሎሎችም ማስገባት አልቻልንም ስም ለማዛወር ቢያንስ ኮለን ማቆም እንዳለብን በጊዜው ተገልጾልን ነበር ።
፪) መሬት ከገዛንበት ገንዘብ ውጪ አሁን ላይ በዚሁ ግሩፕ እየተሰበሰበ ያለ 547,000ብር አካባቢ ደርሰናል ።ገንዘቡ ባንክ ተቀምጦ ዋጋ እያጣ እንዳይሄድብን ማሰባሰባችን እንዳለ ሆኖ
ምን እንስራበት ሀሳብ አስተያየታችሁን በ @sekokaw ላይ ጻፉልን ወይም 0912494703 ላይ ይደውሉልን

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

14 Oct, 18:31


ይህቺኛዋ ደግሞ ተማሪ ኤልዳና መስፍን ትባላለች እጅግ ትሁትና እያንዳንዱ እንቅስቃሴዎቿ ሁሉ እግዚአብሔር ያዝልቅልሽ የምትሏት ዓይነት ልጅ ናት እመ ብርሃን አትለይሽ በርቺ እግዚአብሔር ፍጻሜሽን ያሳምረው ።


0912494703
ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

14 Oct, 10:40


መንፈሳዊ እኅታችን ማርታ ኃይሉ ትባላለች በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ ናት የምትስላቸውን መንፈሳዊ ሥዕላት ስትመለከቱ በጣም ትደመማላችሁ ይህ ከላይ ከመድኃኔዓለም ካልሆነ በቀር እንዴትም ሊቻል አይችልም ስዕል ለጸሎት ቤታችሁ እንዲሁ ለገጠር አድባራትና ገዳማት ማሳል የምትፈልጉ ደውሉላት ውድ እህቴ እጆችሽን ይባርክልሽ ።+251943804311 Marta Hailu


0912494703
ዲ/ን ኤርምያስ

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

13 Oct, 09:05


አንድ  ካህን  ለሁለት  ምዕመን 
ውድ  የተዋህዶ  ልጆች  በእጓ  ደብረ  ምሕረት  መድኃኔዓለም  ገዳም   ካህናት  ከሚገባው  መጠን  በላይ  በጣም  ችግር  ላይ  ናቸው      የሚያገለግሉት  በነፃ  ነው   መነኮሳትስ  ሚስትም  ድስትም  ልጆችም  የላቸውም  የባለትዳር  ካህናቶች  ጉዳይ  ግን  በጣም  አሳዘኑኝ   በየጊዜው  በአገኘኋቸው  ቁጥር  እኛስ  እንደምታየን  ክረምት  ከበጋ  ያለመሰልቸት  ግርማ  አራዊቱን  ቅዝቃዜውን  ሙቀቱን  ታግሰን  እናገለግላለን  የልጆቻችንን  ጥያቄ  ግን  መመለስ  አልቻልንም  ልጆቻችን  ተምረው  ካህን  እንዳይሆኑ  በእኛ  ክህነትን  እያስጠላናቸው  ነው  ብለው  አሉኝ  እኔም  አንድ  ካህን  ለሁለት  ምዕመን  መልዕክቱን  አደርሳለሁ  ብዬ  አልኳቸው  ።ይህን  በምን  መንገድ  ይሆናል  ሰበካ  ጉባኤ  ለካህናት  ደመወዝ  ብሎ  አካውንት  ይከፍታል  በዚያ  በማስገባት  ብናግዛቸው  ።ፈቃደኛ  የሆናችሁ  በሀገር  ውስጥም  በውጭም  ያላችሁ  ፈቃደኛነታችሁን  አሳዩኝ  ከዚያ  አካውንቱን  እንዲከፍቱላቸው  እነግራለሁ  ።  በጽዋ ማኅበር ፣አስራታችንን ሰብስበንም ቢሆን በወር  5000  ብር   ለአንድ  ካህን  ።

0912494703   whats up ,telegram   ,IMO ስልኬ ነው   ደውሉልኝ 
ወይም  ቴሌግራም  @sekokaw  ብለው  ይፃፉልኝ


ዲ/ን  ኤርምያስ 

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

12 Oct, 21:03


እግዚአብሔር ከአስር ብር አንድ ብር የሚጠይቀን ዘጠኙን ለመጠበቅ ነው ።




ስርዓተ ማህሌት ዘካልዕ ጽጌ በዓለ በዓታ ለማርያም
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
ነግሥ (የማንኛውም ወርኃ  በዓልና ክብረ በዓል ሥርዐተ ማኅሌት መጀመሪያ)
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
@mahtotetonetor2
መልክዓ ሥላሴ
ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወፀ ለሣህል፤እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል፡፡

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሐረገ ወይን፤እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ አዕፁቂሃ ሐረገ ወይን፤እንተ በሥሉስ ትትገመድ ወታፈሪ ለነ አስካለ በረከተ፤ሐረገ ወይን፤ሲሳዮሙ ለቅዱሳን፤ሐረገ ወይን፤ሠርዓ ሰንበተ በቃሉ ወጸገወ ሰላመ ለኩሉ።

ማኅሌተ ጽጌ
በከመ ይቤ መጽሐፍ ማዕከለ ፈጣሪ ወፍጡራን፤ለዕረፍት ዘኮንኪ ትእምርተ(ጽላተ) ኪዳን፤ሰንበተ ሰንበታት ማርያም ዕለተ ብርሃን፤ብኪ ይትፌስሑ ዘገነተ ጽጌ ጻድቃን፤ወብኪ ይወጽኡ ኃጥአን እምደይን፡፡

ወረብ
በከመ ይቤ መጽሐፍ ማዕከለ ፈጣሪ ወፍጡራን ዘኮንኪ ለዕረፍት ትእምርተ ኪዳን/፪/
ብኪ ይትፌስሑ ዘገነተ ጽጌ ጻድቃን ብርሃን ዕለተ ብርሃን/፪/

ዚቅ
ሰንበቶሙ ይእቲ ለጻድቃን ትፍሥሕት፤ሰንበቶሙ ይእቲ ለኃጥአን ዕረፍት፤ኅቡረ ንትፈሳሕ ዮም በዛቲ ዕለት፡፡
@mahtotetonetor2

ማኅሌተ ፅጌ፦
ከመ ታቦት ሥርጉት በወርቀ ዓረብ ወተርሴስ፤በድንግልና ማርያም ሥርጉተ ሥጋ ወነፍስ፤ ተአምረ ነቢር አርአይኪ በቤተ መቅደስ፤ኢያቄም ወሐና ቀንሞስ ቀናንሞስ፤ እምዘ ጸገዩኪ ለጳጦስ በዓመት ሠላስ


ወረብ፦
እምዘ ጸገዩኪ ለጳጦስ በዓመት ሠላስ  ኢያቄም ወሐና ቀንሞስ ቀናንሞስ/፪/
ተአምረ ነቢር አርአይኪ ተአምረ ነቢር አርአይኪ በቤተ መቅደስ/፪/
@mahtotetonetor2
ዚቅ
አንቲ ውእቱ ንጽሕት እምንጹሐን ድንግል ኅሪት ዘነበረኪ ውስተ ቤተ መቅደስ ከመ ታቦት ዘግቡር እምዕፅ ዘኢይነቅዝ ሥርግው በወርቅ ንጡፍ ወልቡጥ በዕንቍ ባሕርይ ዘየኃቱ ዘብዙኅ ሤጡ ከመዝ ነበርኪ በቤተ መቅደስ ወመላእክት ያመጽሑ ወትረ ሲሳየኪ ከመዝ ነበርኪ አሠርተ ወክልኤተ ዓመተ እንዘ ትትናዘዚ እምኀበ መላእክት ስቴኪኒ ስቴ ሕይወት ውእቱ ወመብልዕኪኒ ኅብስት ሰማያዊ

ማኅሌተ ጽጌ
እንዘ  ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ ፣አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣ንዒ  ርግብየ  ትናዝዝኒ  እምላህ፣ወንዒ  ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ

ወረብ፦
ንዒ ርግብየ ንዒ ርግብየ ምስለ ሚካኤል/፪/
ወንዒ ሰናይትየ ወንዒ ሰናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ/፪/

ዚቅ፦
ንዒ ርግብየ አግዓዚት ከመ ጎሕ ሠናይት ታቦተ መቅደስ ቅድስተ ቅዱሳን ዕፀ ጳጣስ ደብተራ ፍጽምት ማኅደረ መለኮት

ዓዲ ዚቅ
ንዒ ርግብየ ኲለንታኪ ሠናይት ፀምር ፀዓዳ እንተ አልባቲ ርስሐት መሶበ ወርቅ እንተ መና በትረ አሮን እንተ ሠረፀት።

ወቦ ዘይቤ ዚቅ
ይዌድስዋ ትጉሃን፤ይቄድስዋ ቅዱሳን፤ሰሎሞን ይቤላ ርግብየ ሠናይት፤ጳውሎስኒ ይቤላ ደብተራ ፍጽምት፤ዳዊትኒ ይቤላ ስምዒ ወለትየ ወርይዪ ወአጽምዒ ዕዝንኪ

ማኅሌተ ጽጌ
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ  ዘየኃቱ፤ዘተጽሕፈ ብኪ  ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤አክሊለ ጽጌ ማርያም  ለጊዮርጊስ ቀጸላ  መንግሥቱ፤አንቲ  ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡

ወረብ፦
ክበበ ጌራ ወርቅ ዘየሐቱ እምዕንቈ ባሕርይ/፪/
ማርያም አክሊለ ጽጌ ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ/፪/

ዚቅ
ከርካዕ ዘተተክለት በቤተ መቅደስ፤መራኁቱ ለጴጥሮስ፤አንቲ ውእቱ ደብተራ ስምዕ ዘጳውሎስ፤አማን አክሊሉ ለጊዮርጊስ
@mahtotetonetor2
ሰቆቃወ ድንግል
በቤተ መቅደስ ዘልሕቀት ወለተ ካህናት እንዘ ትሴሰይ ሥሩዓ፣ ኅብስተ ኅቡዓ ወጽዋዓ ወይን ምሉዓ፤እፎ ከመ ነዳይ ሲሳየ ዕለት ዘኃጥአ፤ተአገሠት በብሔረ ግብጽ ረኃበ ወጽምዓ፤አልቦ ከማሃ ዘረከበ ግፍዓ

ወረብ፦
እፎ ከመ ነዳይ ዘኃጥአ ሲሳየ ዕለት/፪/
በቤተ መቅደስ ዘልሕቀት ወለተ ካህናት እንዘ ትሴሰይ ኅብስተ መና ኅቡዓ/፪/

ዚቅ
እሴብሕ ጸጋኪ ኦ ዑጽፍተ ልብሰ ወርቅ እግዝዕትየ ወለተ ዳዊት ንጉሥ ዘተሐፀንኪ በቤተ መቅደስ ወተዓንገድኪ በፈሊስ እምሀገር ለሀገር እንዘ ተዓውዲ በተፅናስ

መዝሙር፦
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ
ኪነ ጥበቡ መንክር ወእፁብ፤ኪነ ጥበቡ መንክር ወእፁብ ለዘሀሎ መልእልተ አርያም።አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ።ዘከለሎ ለሰማይ በከዋክብት ብሩህ። አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ ወለምድርኒ አሠርገዋ በጽጌያት ንፁህ። አርአየ ምሕረቶ በላዕሌነ ወሠርዓ ሰንበተ ለነባረ ያዕርፉ ባቲ። አርአየ ምሕረቶ በላዕሌ:ማ- መዓዛሆሙ ለቅዱሳን ከመ ፅጌ ደንጎላት ዘውስተ ቆላት። ጸገዩ ቀንሞስ ምስለ ናርዶስ።
@mahtotetonetor2
አመላለስ፦
መዓዛሆሙ ለቅዱሳን ከመ ፅጌ ደንጎላት ዘውስተ ቆላት/፪/
ጸገዩ ቀንሞስ ምስለ ናርዶስ/፬/

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

12 Oct, 17:51


“ቤተ ክርስቲያን መነገጃ አይደለችም! ሌቦች ይውጡ! ጉበኞች ይውጡ! ሠርተው ይብሉ! በቤተ ክርስቲያን አውደልዳይ አይብዛ፤ ቦታ ይሰጠው፤”“በጎጥ እና በቋንቋ የምንመራው እስከ መቼ ድረስ ነው?”ቢሮው የማን ነው? በጉቦ የገባ ማን ነው? ወንጌሉ የሚሰበከው ለማን ነው?

ሕዝቡ ተሰብኮ፣ ተሰብኮ ዐውቆታል፤ ከቢሮ ውስጥ ነው ችግሩ፤ ጥያቄው ሲጎርፍ አለመመለስ ነው ችግሩ፤ በዚኽ ዓለም ያልታመነ በእግዚአብሔር መንግሥትስ ቦታ አለው እንዴ? ትምህርቱ የጆሮ ቀለብ ኾኗል፤ ውስጥ ገብተው ሲያዩት ያስለቅሳል፡፡”

“ምርጫ በሞያ ይኹን፤ በጎጥ አይደለም፤ ሲጠየቅ መልስ የሚሰጥ ቤተክርስቲያንን የሚያውቅ የሕዝብ አባት ይኹን፤ ድኻ ተበደለ፤ ፍርድ ተጓደለ የሚል አባት ከሌለ ትርጉሙ ምንድን ነው መሰብሰባችንም ምንም በቈዔት የለውም፤”
“አእምሯችን ሳይገራ፣ ለሕጉ ተገዥ ሳንኾን ከየትም ከየትም መጥተን እግዚአብሔርን የምናስቀይም ነው የምንኾነው፤ ያልተቀጣ ልጅ ኹልጊዜ እንደሰረቀ ይኖራል፤ ልቡናው በእግዚአብሔር ቃል እና ምስጢር ያልተቀጣ ሰውም ኹልጊዜ እንደበጠበጠ ይኖራል፤

- ፖለቲካ ከቤተ ክርስቲያን ይውጣ፤ እውነት ይገለጥ ቅዱስ አባታችን፤ ስለእውነት እንቁም፤ በአራቱ ማዕዝን ጥያቄ ተቀስሯል፤ ስለ ሃይማኖት ጥያቄ እየተነሣ ነው፤ ጥያቄውን የሚመልሰው ማን ነው? ብዙ ችግሮች ቀርበዋል፤ የሚፈታቸው ማን ነው? አእምሮ ያስባል፤ ጆሮ ይሰማል፤ ድኻ ተበደለ፤ ፍርድ ተጓደለ፤ የሚል አባት ከሌለ ትርጉሙ ምንድን ነው? ዙሪያውን ሰይፍ ተመዞ እየተብለጨለጨ የደነዘዘውን አእምሮ እናስወግደው፤ ቃሉን እንጠይቀው፡፡

ሕጉ ይከበር፤ ስም ብቻ አንያዝ፤ ሕጉን ወደ ኋላ አሽቀንጥረን ትተን እንዴት መምራት እንችላለን? ተንኰል ይቅር፤ በውሸት አንመን፤ በዝባዥ ይጋለጥ፤ ጨርሻለኹ፡፡

ብፁዕ አቡነ እንድርያስ 2008 ዓ. ም የተናገሩት ነው።
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

12 Oct, 16:47


መድኃኔዓለም በእድሜ ይጠብቅልን

በእውነት እግዚአብሔር አምላክ በጎደለ ይሙላላችሁ መድኃኔዓለም ያላሰባችሁትን ይስጣችሁ።
  አስራታቸውን ስዕለታቸውን እንዲያስገቡ በረከቱን እያበዛላቸው እየባረካቸው ለምሕረት የማይታጠፉ እጆቹ እንደማይጎድል ውሃ  እያፈሰሰላቸው ነው ።
እግዚአብሔር ይቀበልላችሁ እም ብርሃን አትለያችሁ የሰላም አምላክ ሰላምን ይስጣችሁ።


EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @sekokaw ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

12 Oct, 08:19


እግዚአብሔር በጎደለ ይሙላልህ ሰላመ እግዚአብሔር አይለህ።
በእውነት እግዚአብሔር አምላክ በጎደለ ይሙላላችሁ መድኃኔዓለም ያላሰባችሁትን ይስጣችሁ።
  አስራታቸውን ስዕለታቸውን እንዲያስገቡ በረከቱን እያበዛላቸው እየባረካቸው ለምሕረት የማይታጠፉ እጆቹ እንደማይጎድል ውሃ  እያፈሰሰላቸው ነው ።
እግዚአብሔር ይቀበልላችሁ እም ብርሃን አትለያችሁ የሰላም አምላክ ሰላምን ይስጣችሁ።


EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @sekokaw ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

11 Oct, 16:05


ታጥባችሁ ብሉን
አንድ ሰው በቤቱ የተዘጋጀለትን ምግብ ንጽህናውን የጠበቀ ቢቀርብለትና ተመግቦም እንዲስማማው ከፈለገ በክብር በስነ ሥርዓት ህጉን አክብሮ ሊመገበው ይገባል ከእሱ ንጽሕና ጉድለት የተነሳ ሊሰጠው ከነበረው ጥቅም ይልቅ መርዝ ሊሆንበት ይችላል።
~የቤተክርስቲያን ልዕልና እኔ ወይም ሌላው የሚደፍራት አልነበረችም ምክንያቱም መሰረቷ ይታወቃል።የማይኖረውን የማያምነውን የሚሰብክ የሃይማኖት አባት  መናፍቅ  ነው ለራሱ ያልሆነ የሌሎችን ነፍስ ሊታደግ አይችልም ለይምሰል መኖር ለእምነቱ ይቅርና ለህሊናው እረፍት አልባ ኑሮ  ነው።
ጥቂት ህዝብ ሲሰበሰብ የማይመጣ ለኪዳን ለማኅሌት ለሰዓታት በአጠቃላይ ለጸሎት የማይተጋ ሌሎች ጉድጓድ ገብተው ትቢያ ነስንሰው አመድ መስለው ሰርተው ካላቸው ከፍለው በሙዳይ ከአስቀመጡት ገንዘብ የቅቤ ቅል መስሎ መታየት እንዴት ያስጠላል ።የንጹሐን እምባ የቅዱሳን አውደ ምሕረት የህሙማን ጸሎት አፈር ያስቅማል ይህ ደግሞ ቢዘገይ እንኳን የሚቀድመው የለም ።
እግዚአብሔር ወርቅ ሊሸልም ሲል አያያዝን በመዳብ ይፈትናል ።
~አዛዥ ናዛዥ መሆናችሁ በራሱ ምን አጉድሎባችሁ ነው ሳትታጠቡ የምትበሉን ቢያንስ ድጋሚ ለራሳችሁ መርዝ ሳንሆንባችሁ ታጥባችሁ እንኳን ብሉን።

ዲ/ን ኤርምያስ
@mahtotetonetor2

ማኅቶተ ቶኔቶር ፩

11 Oct, 14:54


እግዚአብሔር በጎደለ ይሙላልህ ሰላመ እግዚአብሔር አይለህ።
በእውነት እግዚአብሔር አምላክ በጎደለ ይሙላላችሁ መድኃኔዓለም ያላሰባችሁትን ይስጣችሁ።
  አስራታቸውን ስዕለታቸውን እንዲያስገቡ በረከቱን እያበዛላቸው እየባረካቸው ለምሕረት የማይታጠፉ እጆቹ እንደማይጎድል ውሃ  እያፈሰሰላቸው ነው ።
እግዚአብሔር ይቀበልላችሁ እም ብርሃን አትለያችሁ የሰላም አምላክ ሰላምን ይስጣችሁ።


EGUA D/MIHRET MEDIHANIALEM
እጓ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን
🫴🫴አቢሲኒያ ባንክ 182395657

🫴🫴በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000273479744
  
በምንም ጉዳይ ለምትፈልጉት መረጃ ስልክ:-የእጅ ስልኮቻችን 

+15092943369 አሜሪካ ለምትገኙ

+251912494703  =ኢትዮጵያ ለምትገኙ
ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም @sekokaw ላይ ይጻፉልን



ዲ/ን ኤርምያስ

@mahtotetonetor2

1,388

subscribers

2,564

photos

30

videos