ፈረስ ግልቢያን ቻሉ፡፡ ፋሲለደስም ልጆቹ ይባረኩ ዘንድ ወደ ሊቀ ጳጳሱ ዘንድ ወሰዳቸው፡፡ ሊቀ ጳጳሱም የልጆቹን እጅ ይዞ ‹‹ልጆቼ እናንተም ባርኩኝ፣ ልዩ የሆነ ያማረ የዕጣን መዓዛ ከእናንተ ይወጣልና›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ለሰባት ቀን ታላቅ ግብዣ አዘጋጅቶ መኳንንት መሳፍንቱን ሁሉ ጠርቶ ዮስጦስን፣ አውሳብዮስንና ፋሲለደስን ሾማቸው፡፡ ንጉሡ የመንግሥቱን ዘውድ አንስቶ በቅዱስ ፋሲለደስ ራስ ላይ ጫነና አንሥቶ በቀኙ አስቀመጠው፡፡ የወርቅ ዝናርም አንሥቶ ልጁን ዮስጦስን አስታጠቀውና የእርሱ ተከታይ ሹም አደረገው፡፡ ከንጉሡ በታች 3ኛ አድርጎ በፋሲለደስ ቀኝ አስቀመጠው፡፡ አውሳብዮስንም እንዲሁ ዝናር አስታጥቆ የወታደሮች የአለቆች አለቃና ከመኳንንትና መከሳፍንት በላይ ከንጉሡ ቀጥሎ 4ኛ አድጎ ሾመው፡፡
ቅዱስ ፋሲለደስ የቤተ መንግሥት ሥራን በተመለከተ ከሁሉ የበላይ አዛዥ አለቃ ከሆነ በኋላ ሕዝቡን በጥበብና በፍቅር ያስተዳድራቸው ስለነበር ሁሉም ይወዱት ነበር፡፡ ድኆችና ጦም አዳሪዎችን ይረዳቸዋል፡፡ ከዚህም በኋላ በምዕራብ በኩል ሮሳኒኮስ የተባሉ አሕዛብ በእነ ፋሲለደስ ላይ ጦርነት አነሡና ሮም ደርሰው ሮምን አፈረሱ፡፡ ንጉሡ ኑማርያኖስም ስለእነዚህ አሕዛብ ወረራ ከፋሲለደስ ጋር ተማከረ፡፡ ፋሲለደስም ለንጉሡ ‹‹ልጄ አውሳብዮስ ከሠራዊት ጋር ወደ እነዚህ ወራሪዎች ይሂድ›› አለው፡፡ ነገር ግን ንጉሡ ‹‹ልጄ ዮስጦስ ከእሱ ጋር ካልሄደ ያንተ ልጅ ብቻ አይሄድም›› ብሎ ማለ፡፡ ፋሲለደስም የንጉሡን ማሀላ ባየ ጊዜ የእኅቱን ልጆች አባድርንና ምሥራቃዊ ቴዎድሮስን ጠርቶ እነርሱ ፊት አውራሪ ሆነው ጦሩን ይመሩ ዘንድ ከ270,000 ሠራዊት ጋር ዮስጦስንና አውሳብዮስን የበላይ ጠባቂ አድርጓቸው ወደ ጦርነቱ እንዲሄዱ አዘዛቸው፡፡ ንጉሡ ኑማርያኖስም ዮስጦስንና አውሳብዮስን ጦርነቱን ድል አድርገው ሲመጡ ሚስት እንደሚያጋባቸው ቃል ገብቶ በክብር ሸኛቸው፡፡
የገንዘብ ፍቅር ባደረበት በሊቀ ጳጳሱ በዮሐናዳኬዎስ ምክንያት ዲዮቅልጥያኖስ ጨርሶ ጌታችንን ከካደ በኋላ ወዲያው እርሱ በሚገዛበት አውራጃ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ በምትካቸውም የጣዖታት ቤቶች እንዲከፈቱ አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የአብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮችም በሙሉ ለጣዖታቱ እንዲሠው ያልሠዋ ቢኖር ግን እንዲገደል አዘዘ፡፡ የትእዛዙንም ደብዳቤ በግዛቶቹ ሁሉ ላከ፡፡ መልአክቱም በመላ ዓለም ተሠራጨ፡፡ ሊቀ ጳጳሱም በጉቦ የተቀበለውን ወርቅ አቅልጦ 35 የወንድና 35 የሴት ጣዖታትን አሠርቶ ሰው በሚመላለስበት አደባባይ አቆማቸውና ሁሉም ለእነርሱ እንዲሰግድ አዘዘ፡፡ ንጉሡ ላቆማቸው ለእነዚህ ጣዖታት ያልሰገደ ቢኖር ግን ‹‹ይገደል ንብረቱም ይዘረፍ›› አለ፡፡ ሕዝቡንም ሁሉ ሰብስቦ እርሱ ለጣዖታቱ ሰገደላቸው፡፡ ከንጉሡ ቀጥሎ የወታደሮቹ አለቃ ህርማኖስም ሰገደ፡፡ 900 ባለሥልጣናትና 40 ሺህ ወታደሮችም እንዲሁ በየተራ ሰገዱ፡፡ ሕዝቡም ሁሉ እንዲሁ ሰገዱ፡፡ ንጉሡም በልቡ ከእርሱ ቀጥሎ ቅዱስ ፋሲለደስ ለጣዖታቱ የሚሰግድላቸው መስሎት ነበር፡፡ ቅዱስ ፋሲለደስ ግን ከሕዝቡ ተለይቶ ወደኋላው ተመልሶ ተቀመጠ፡፡
በዚህም ጊዜ እነ አውሳብዮስ ከአረማውያን ከፋርስ ሰዎች ጋር እየተዋጉ ነበር፡፡ የንጉሥ ልጅ ዮስጦስ ከሠራዊቱ ጋር በፋርስ ንጉሥ ተማርኮ በእስር ቤት ተጥሎ ሳለ እነርሱም ለጣዖታቸው እስከሚሠዋ ይጠብቁ ነበር፡፡ እርሱ ግን ‹‹ለጣዖት አልሰዋም›› ብሎ እምቢ አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ተልኮ መጥቶ ለቅዱስ ፋሲለደስ ልጅ ለአውሳብዮስ ተገልጠለትና ‹‹ጌታህ ኢየሱስ ክርስቶስ ከምርኮ ያድንህ ዘንድ አለውና የፋርስን ሰዎችና ሠራዊታቸውንም ሁሉ በእጅህ አሳልፎ ይሰጥሃል፣ አንተም ታማኝ አገልጋዩ ሆነህ ስለ ቅዱስ ስሙ ሰማዕትነትን ትቀበላለህ›› አለው፡፡ መልአኩ ዳግመኛም ‹‹የአባትህን የፋሲለደስን ልመናና ጸሎት ሰምቼ ነው የመጣሁ›› አለው፡፡ ዳግመኛም መልአኩ የፋርስን ንጉሥ በእጁ አሳልፎ እንደሚሰጠውና ዮስጦስንም እንደሚያድነው ነግሮት በጦር እንዲገባባቸው አዘዘው፡፡ መልአኩ ለቅዱስ ዮስጦስም ተገልጦለት እንዲሁ ወንድሙ አውሳብዮስ መጥቶ እንደሚወስደውና በጣላቶቻቸው ላይ እንሚያሰለጥናቸውና በመጨረሻም በክርስቶስ ስም ሰማዕት እንደሚሆኑ ነገረው፡፡ ቅዱስ አውሳብዮስም የመልአኩን ትእዛዝ ተቀብሎ ገላውዴዎስንና አባድርን ጠርቶ መልአኩ የነገረውን ነገራቸው፡፡ እነርሱም ያን ጊዜ ‹‹የፋርስን ሰዎች አሳልፎ ከሰጠን እኛም ስለስሙ ሰማዕት እንሆናለን›› ተባባሉ፡፡ ቅዱስ አውሳብዮስም እየጸለየ ወደ ጦርነቱ ሄደ፡፡ የፋርስ ሰዎችም እጅግ ብዙ ቢሆኑም አስቀድሞ የታየው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በእጁ የተሳለ ሰይፍ ይዞ የፋርስን ሠራዊት ሲፈጃቸው ተመለከተ፡፡ ቅዱስ አውሳብዮስም በፈረሱ ላይ ተቀምጦ ወደ ጦርነቱ ገባና ብዙዎችን ገደለ፡፡ ገዳውዴዎስና አባድርም ብዙ ሠራዊትን ጨረሱ፡፡ የፋርስም ንጉሥ ሲሸሽ ከፈረሱ ላይ ወድቆ ሳለ አውሳብዮስ ማርኮ ያዘው፡፡ አውሳብዮስም ዮስጦስን ከእሥር ቤት አወጣውና በፋርስ አደባባይ ድንኳኖቻቸውን ተክለው እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ሁለት ዓመትም በዚያ ቆይተው ምርኮን ወደ አንጾኪያ ላኩ፡፡ ሌሎቹንም ጠላቶቻቸውን ሁሉ ድል እየነሱ ለሮም አስገዟቸው፡፡ የዲዮቅልጥያኖስ ዓመተ መንግሥቱ 5 ዓመት በሆነ ጊዜ በሰባተኛው ወር የንጉሥ ኑማርያኖስ ልጅ ዮስጦስ የፋሲለደስ ልጅ አውሳብዮስ፣ የታላላቅ ወታደሮች አለቆች የሆኑ ገላውዲዮስና አባድር በታላቅ ደስታ ወደ አገራቸው በተመለሱ ጊዜ በአንጾኪያ ታላቅ ደስታ ተደርጎ ሕዝቡም ወጥቶ በክብር ተቀበላቸው፡፡ ነገር ግን ዲዮቅልጥያኖስ ይህንን ሲያይ እጅግ ደነገጠ መንግሥቱ የንጉሡ ልጅ የዮስጦስ መሆኑን ያውቃልና፡፡
ሁሉም የመንግሥት ልጆች ጠላቶቻቸውን ድል ነሥተው ወደ ሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ በመጀመሪያ ወጥቶ በደስታና በታላቅ ክብር ከተቀበላቸው በኋላ የቅዱስ ፊቅጦር አባት የሆነው ከሃዲው መኰንኑ ህርማኖስ ለጣዖት እንዲግዱና ምስጋና እንዲያቀርቡ ለንጉሡ መከረው፡፡ ንጉሡም እንደተመከረው ለአጵሎን ሰግደው ዳግመኛ ደስ እንደዲያሰኙት ሲጠይቃቸው ቅዱሳኑ እጅግ ተቆጡት፡፡ የፋሲለደስ ልጅ ቅዱስ አውሳብዮስም ንጉሡን ለመግደል ሰይፉን ሲመዘዝ አባቱ ቅዱስ ፋሲለደስ ከለከለው፡፡ በንዴትም ከንጉሡ ጭፍሮች ብዙዎችን ገደለ፡፡ የከበረ ፋሲለደስም ባይከለክላቸው ኖሮ ከንጉሡ ቤት ምንም ሰው ባልቀራቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ህርማኖስ ቅዱስ አውሳብዮስን ወደ ግብፅ እንዲልከው መከረው፡፡ ይህም የንጉሡ መኰንን ህርማኖስ የገዛ ልጁን ቅዱስ ፊቅጦርንም እንዲሁ ወደ ግብፅ በማስላክ አሠቃይቶ ያስገደለ አረመኔ ነው፡፡
ከዚህም በኋላ ዲዮቅልጥያኖስ በሚገዛበት አገር ሁሉ ክርስቶስን ያልካዱትን ምእመናን ማስገደልና ማሳደድ ጀመረ፡፡ ብዙ ሰማዕታትም ወደ ንጉሡ የሰማዕትነት አዳባባይ እየመጡ በጌታችን ስም ደማቸውን አፈሰሱ፡፡ ንጉሡም እንደተመከረው ቅዱስ አውሳብዮስን ወደ ግብፅ ላከውና በዚያም ጽኑ ሥቃይን አሠቃዩት፡፡ ሥጋውን ቆራርጠው በብረት ምጣድ አድርገው ከሥር እሳት አንድደው አበሰሉት፡፡ ጌታችንም መልአኩን ልኮ ከመከራው ሁሉ አድኖት ያለ ምንም ጉዳት አስነሣው፡፡ ነፍሱንም ወደ ገነት ወስዶ ለእርሱና ለጻድቃን ሰማዕታቱ ሁሉ ያዘጋጀላቸውን የገነት ቦታዎች ሁሉ አሳይቶታል፡፡ ዳግመኛም የግብፁ መኰንን ቅዱስ አውሳብዮስን በእሳት ምድጃ ውስጥ ሲጨምረው የታዘዘ መልአክ እሳቱን እንደ ጠል አቀዝቅዞ አዳነው፡፡ ከዚህም በኋላ መኳንንቱ መኰንኑን ‹‹እንዲህ ከመታገል አንገቱን በሰይፍ ብንቆርጠው ይሻላል›› ብለው መከሩትና
በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት)

Similar Channels



የቅዱሳን ኅሩያን፣ ከገድላት አንደበት ወቅታዊ መረጃ
ቅዱሳን ኅሩያን የአማርኛ ድምፅ ቻናል አዲስ ይዘው እንደሚገኙ የሚያዘዙ ሀይማኖታዊነትና የእምነት ጸጋ ይበልጣል። ይህ ቻናል ለዚህ ወቅት የወሰነ አዲስ ዝርዝር በሚኖርበት ጊዜ ገድለ ቅዱሳንን በጽሑፍና በድምፅ ይተላለፉበታል። በየቀኑ የሚኖሩ ትዕዛዞች እና መረጃዎች ይታወቃሉ። ቅዱሳን ኅሩያን እንዲሁም የፍትሕ እና የአስተዋል ብሄርን ይዮው የሚሰጣል ነው።
ቅዱሳን ኅሩያን ቻናል ምን ይዟል?
ቅዱሳን ኅሩያን ቻናል ከእምነት እና በመንፈሳዊ ዓይነት ጋር የተያያዘ ድምፅ እና ገለጻ ላይ ይገኛል። የቻናሉ ዋነኛ ጊዜ ለውህድ በሚገኘው ዕንቅስቃሴ የአማርኛ እና ሐዘን መሰረታዊ እንደዚህ ያለው አይነት ድምፅ ይሰጣል።
ይኽ ለ3ኛ ጊዜ የተከፈተ የውይይት እና የፍትሕ መሀይል መረጃዎች ተጨማሪ ተመልካት ይሰጣል። እነዚህ ገንቢዎች የከንቱ እና የዝማኔ ገድለ ሃይማኖታትን ይወዳድሩ ይችላሉ።
ቅዱሳን ኅሩያን አንድ የሚሰጣቸው አገልግሎት ምንድን ነው?
ቅዱሳን ኅሩያን ለመጠቀም የዝርዝር አገልግሎት አብሮትን ይሰጣል። አንዱ ዝርዝር በገድለ ቅዱሳን መሠረት የሚኖሩ እና በእምነታቸው የተነሱ የምርት ማዕከላዊ ጋር ይታወቃሉ።
እንዲሁም ዘርዝር አገልግሎታት በጽሑፍ ገበሬ ይቀርባሉ። የሚኖሩ ቅዱሳን ገድለ አይነት ዕውነታቸው ይወዳድሩ ይችላሉ።
የቅዱሳን ኅሩያን ምን የሚተላለፊ ይዘት አለው?
የቅዱሳን ኅሩያን ይዘት እንደዚህ ይሰጣል። ይህ በውይይት እና በክፍል ያሉበት ሀይማኖታቸውን ግንቦት ይወዳድሩ ይችላሉ።
ይህ ዘመናዊ ይዘት ይወዳድሩን ይብዛል እና እርግብ የብዙ ተጽእኖን ያለው ይሆን። ይገኝተህ እንደ ሀይማኖት ሞልክን የቀደም ጨዋታ ይወዳድሩ ይሆን።
ቅዱሳን ኅሩያን ምንድን ዓይነት ዝርዝር አገልግሎት አለ?
ቅዱሳን ኅሩያን ይዚህ ዓይነት ዝርዝር ይሰጣል። ይኸው ተረጃን ወደ ቅዱሳን ዙሪያ እና ዘርዝር እንደ ዘይውን በሚገኝ የወጣበትን ይወዳድሩ ይችላሉ።
ይህ ቅዱሳን ላይ ያቀርባቸው ያለው ዝርዝር አገልግሎት ኀኪም ይልቅ ይሆን። የእምነት አይነት የሚገኘው ዝርዝር ይሰጣል።
በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት) Telegram Channel
በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት) የታሪኩን ስነስርዓት የተማሪዎችን ማስታወቂያዎችን እና ጽሑፍን ከአፈቃላይ መልእክት ማወቅ ይችላሉ ። እስካሁንም ገድላት የኅሩያን ወንድሞችን እና ሴትሞችን ለመመልከት መረጃዎች ይሰጡበታል። ብቁ ከገዳብ ልብ ውስጥ የሚደረጉትን ውይይት ሰልቦና በኮንትራቨኝ መናገር ይችላሉ።