በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት) @kegedilatandebet27217 Channel on Telegram

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት)

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት)
ይኽ ለ3ኛ ጊዜ የተከፈተ አዲስ ቻናል ነው። በየቀኑ ገድለ ቅዱሳንና የተለያዩ አገልግሎቶች በጽሑፍና በድምፅ ይተላለፉበታል።
12,139 Subscribers
1,422 Photos
32 Videos
Last Updated 02.03.2025 15:22

የቅዱሳን ኅሩያን፣ ከገድላት አንደበት ወቅታዊ መረጃ

ቅዱሳን ኅሩያን የአማርኛ ድምፅ ቻናል አዲስ ይዘው እንደሚገኙ የሚያዘዙ ሀይማኖታዊነትና የእምነት ጸጋ ይበልጣል። ይህ ቻናል ለዚህ ወቅት የወሰነ አዲስ ዝርዝር በሚኖርበት ጊዜ ገድለ ቅዱሳንን በጽሑፍና በድምፅ ይተላለፉበታል። በየቀኑ የሚኖሩ ትዕዛዞች እና መረጃዎች ይታወቃሉ። ቅዱሳን ኅሩያን እንዲሁም የፍትሕ እና የአስተዋል ብሄርን ይዮው የሚሰጣል ነው።

ቅዱሳን ኅሩያን ቻናል ምን ይዟል?

ቅዱሳን ኅሩያን ቻናል ከእምነት እና በመንፈሳዊ ዓይነት ጋር የተያያዘ ድምፅ እና ገለጻ ላይ ይገኛል። የቻናሉ ዋነኛ ጊዜ ለውህድ በሚገኘው ዕንቅስቃሴ የአማርኛ እና ሐዘን መሰረታዊ እንደዚህ ያለው አይነት ድምፅ ይሰጣል።

ይኽ ለ3ኛ ጊዜ የተከፈተ የውይይት እና የፍትሕ መሀይል መረጃዎች ተጨማሪ ተመልካት ይሰጣል። እነዚህ ገንቢዎች የከንቱ እና የዝማኔ ገድለ ሃይማኖታትን ይወዳድሩ ይችላሉ።

ቅዱሳን ኅሩያን አንድ የሚሰጣቸው አገልግሎት ምንድን ነው?

ቅዱሳን ኅሩያን ለመጠቀም የዝርዝር አገልግሎት አብሮትን ይሰጣል። አንዱ ዝርዝር በገድለ ቅዱሳን መሠረት የሚኖሩ እና በእምነታቸው የተነሱ የምርት ማዕከላዊ ጋር ይታወቃሉ።

እንዲሁም ዘርዝር አገልግሎታት በጽሑፍ ገበሬ ይቀርባሉ። የሚኖሩ ቅዱሳን ገድለ አይነት ዕውነታቸው ይወዳድሩ ይችላሉ።

የቅዱሳን ኅሩያን ምን የሚተላለፊ ይዘት አለው?

የቅዱሳን ኅሩያን ይዘት እንደዚህ ይሰጣል። ይህ በውይይት እና በክፍል ያሉበት ሀይማኖታቸውን ግንቦት ይወዳድሩ ይችላሉ።

ይህ ዘመናዊ ይዘት ይወዳድሩን ይብዛል እና እርግብ የብዙ ተጽእኖን ያለው ይሆን። ይገኝተህ እንደ ሀይማኖት ሞልክን የቀደም ጨዋታ ይወዳድሩ ይሆን።

ቅዱሳን ኅሩያን ምንድን ዓይነት ዝርዝር አገልግሎት አለ?

ቅዱሳን ኅሩያን ይዚህ ዓይነት ዝርዝር ይሰጣል። ይኸው ተረጃን ወደ ቅዱሳን ዙሪያ እና ዘርዝር እንደ ዘይውን በሚገኝ የወጣበትን ይወዳድሩ ይችላሉ።

ይህ ቅዱሳን ላይ ያቀርባቸው ያለው ዝርዝር አገልግሎት ኀኪም ይልቅ ይሆን። የእምነት አይነት የሚገኘው ዝርዝር ይሰጣል።

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት) Telegram Channel

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት) የታሪኩን ስነስርዓት የተማሪዎችን ማስታወቂያዎችን እና ጽሑፍን ከአፈቃላይ መልእክት ማወቅ ይችላሉ ። እስካሁንም ገድላት የኅሩያን ወንድሞችን እና ሴትሞችን ለመመልከት መረጃዎች ይሰጡበታል። ብቁ ከገዳብ ልብ ውስጥ የሚደረጉትን ውይይት ሰልቦና በኮንትራቨኝ መናገር ይችላሉ።

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት) Latest Posts

Post image

ፈረስ ግልቢያን ቻሉ፡፡ ፋሲለደስም ልጆቹ ይባረኩ ዘንድ ወደ ሊቀ ጳጳሱ ዘንድ ወሰዳቸው፡፡ ሊቀ ጳጳሱም የልጆቹን እጅ ይዞ ‹‹ልጆቼ እናንተም ባርኩኝ፣ ልዩ የሆነ ያማረ የዕጣን መዓዛ ከእናንተ ይወጣልና›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ለሰባት ቀን ታላቅ ግብዣ አዘጋጅቶ መኳንንት መሳፍንቱን ሁሉ ጠርቶ ዮስጦስን፣ አውሳብዮስንና ፋሲለደስን ሾማቸው፡፡ ንጉሡ የመንግሥቱን ዘውድ አንስቶ በቅዱስ ፋሲለደስ ራስ ላይ ጫነና አንሥቶ በቀኙ አስቀመጠው፡፡ የወርቅ ዝናርም አንሥቶ ልጁን ዮስጦስን አስታጠቀውና የእርሱ ተከታይ ሹም አደረገው፡፡ ከንጉሡ በታች 3ኛ አድርጎ በፋሲለደስ ቀኝ አስቀመጠው፡፡ አውሳብዮስንም እንዲሁ ዝናር አስታጥቆ የወታደሮች የአለቆች አለቃና ከመኳንንትና መከሳፍንት በላይ ከንጉሡ ቀጥሎ 4ኛ አድጎ ሾመው፡፡
ቅዱስ ፋሲለደስ የቤተ መንግሥት ሥራን በተመለከተ ከሁሉ የበላይ አዛዥ አለቃ ከሆነ በኋላ ሕዝቡን በጥበብና በፍቅር ያስተዳድራቸው ስለነበር ሁሉም ይወዱት ነበር፡፡ ድኆችና ጦም አዳሪዎችን ይረዳቸዋል፡፡ ከዚህም በኋላ በምዕራብ በኩል ሮሳኒኮስ የተባሉ አሕዛብ በእነ ፋሲለደስ ላይ ጦርነት አነሡና ሮም ደርሰው ሮምን አፈረሱ፡፡ ንጉሡ ኑማርያኖስም ስለእነዚህ አሕዛብ ወረራ ከፋሲለደስ ጋር ተማከረ፡፡ ፋሲለደስም ለንጉሡ ‹‹ልጄ አውሳብዮስ ከሠራዊት ጋር ወደ እነዚህ ወራሪዎች ይሂድ›› አለው፡፡ ነገር ግን ንጉሡ ‹‹ልጄ ዮስጦስ ከእሱ ጋር ካልሄደ ያንተ ልጅ ብቻ አይሄድም›› ብሎ ማለ፡፡ ፋሲለደስም የንጉሡን ማሀላ ባየ ጊዜ የእኅቱን ልጆች አባድርንና ምሥራቃዊ ቴዎድሮስን ጠርቶ እነርሱ ፊት አውራሪ ሆነው ጦሩን ይመሩ ዘንድ ከ270,000 ሠራዊት ጋር ዮስጦስንና አውሳብዮስን የበላይ ጠባቂ አድርጓቸው ወደ ጦርነቱ እንዲሄዱ አዘዛቸው፡፡ ንጉሡ ኑማርያኖስም ዮስጦስንና አውሳብዮስን ጦርነቱን ድል አድርገው ሲመጡ ሚስት እንደሚያጋባቸው ቃል ገብቶ በክብር ሸኛቸው፡፡
የገንዘብ ፍቅር ባደረበት በሊቀ ጳጳሱ በዮሐናዳኬዎስ ምክንያት ዲዮቅልጥያኖስ ጨርሶ ጌታችንን ከካደ በኋላ ወዲያው እርሱ በሚገዛበት አውራጃ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ በምትካቸውም የጣዖታት ቤቶች እንዲከፈቱ አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የአብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮችም በሙሉ ለጣዖታቱ እንዲሠው ያልሠዋ ቢኖር ግን እንዲገደል አዘዘ፡፡ የትእዛዙንም ደብዳቤ በግዛቶቹ ሁሉ ላከ፡፡ መልአክቱም በመላ ዓለም ተሠራጨ፡፡ ሊቀ ጳጳሱም በጉቦ የተቀበለውን ወርቅ አቅልጦ 35 የወንድና 35 የሴት ጣዖታትን አሠርቶ ሰው በሚመላለስበት አደባባይ አቆማቸውና ሁሉም ለእነርሱ እንዲሰግድ አዘዘ፡፡ ንጉሡ ላቆማቸው ለእነዚህ ጣዖታት ያልሰገደ ቢኖር ግን ‹‹ይገደል ንብረቱም ይዘረፍ›› አለ፡፡ ሕዝቡንም ሁሉ ሰብስቦ እርሱ ለጣዖታቱ ሰገደላቸው፡፡ ከንጉሡ ቀጥሎ የወታደሮቹ አለቃ ህርማኖስም ሰገደ፡፡ 900 ባለሥልጣናትና 40 ሺህ ወታደሮችም እንዲሁ በየተራ ሰገዱ፡፡ ሕዝቡም ሁሉ እንዲሁ ሰገዱ፡፡ ንጉሡም በልቡ ከእርሱ ቀጥሎ ቅዱስ ፋሲለደስ ለጣዖታቱ የሚሰግድላቸው መስሎት ነበር፡፡ ቅዱስ ፋሲለደስ ግን ከሕዝቡ ተለይቶ ወደኋላው ተመልሶ ተቀመጠ፡፡
በዚህም ጊዜ እነ አውሳብዮስ ከአረማውያን ከፋርስ ሰዎች ጋር እየተዋጉ ነበር፡፡ የንጉሥ ልጅ ዮስጦስ ከሠራዊቱ ጋር በፋርስ ንጉሥ ተማርኮ በእስር ቤት ተጥሎ ሳለ እነርሱም ለጣዖታቸው እስከሚሠዋ ይጠብቁ ነበር፡፡ እርሱ ግን ‹‹ለጣዖት አልሰዋም›› ብሎ እምቢ አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ተልኮ መጥቶ ለቅዱስ ፋሲለደስ ልጅ ለአውሳብዮስ ተገልጠለትና ‹‹ጌታህ ኢየሱስ ክርስቶስ ከምርኮ ያድንህ ዘንድ አለውና የፋርስን ሰዎችና ሠራዊታቸውንም ሁሉ በእጅህ አሳልፎ ይሰጥሃል፣ አንተም ታማኝ አገልጋዩ ሆነህ ስለ ቅዱስ ስሙ ሰማዕትነትን ትቀበላለህ›› አለው፡፡ መልአኩ ዳግመኛም ‹‹የአባትህን የፋሲለደስን ልመናና ጸሎት ሰምቼ ነው የመጣሁ›› አለው፡፡ ዳግመኛም መልአኩ የፋርስን ንጉሥ በእጁ አሳልፎ እንደሚሰጠውና ዮስጦስንም እንደሚያድነው ነግሮት በጦር እንዲገባባቸው አዘዘው፡፡ መልአኩ ለቅዱስ ዮስጦስም ተገልጦለት እንዲሁ ወንድሙ አውሳብዮስ መጥቶ እንደሚወስደውና በጣላቶቻቸው ላይ እንሚያሰለጥናቸውና በመጨረሻም በክርስቶስ ስም ሰማዕት እንደሚሆኑ ነገረው፡፡ ቅዱስ አውሳብዮስም የመልአኩን ትእዛዝ ተቀብሎ ገላውዴዎስንና አባድርን ጠርቶ መልአኩ የነገረውን ነገራቸው፡፡ እነርሱም ያን ጊዜ ‹‹የፋርስን ሰዎች አሳልፎ ከሰጠን እኛም ስለስሙ ሰማዕት እንሆናለን›› ተባባሉ፡፡ ቅዱስ አውሳብዮስም እየጸለየ ወደ ጦርነቱ ሄደ፡፡ የፋርስ ሰዎችም እጅግ ብዙ ቢሆኑም አስቀድሞ የታየው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በእጁ የተሳለ ሰይፍ ይዞ የፋርስን ሠራዊት ሲፈጃቸው ተመለከተ፡፡ ቅዱስ አውሳብዮስም በፈረሱ ላይ ተቀምጦ ወደ ጦርነቱ ገባና ብዙዎችን ገደለ፡፡ ገዳውዴዎስና አባድርም ብዙ ሠራዊትን ጨረሱ፡፡ የፋርስም ንጉሥ ሲሸሽ ከፈረሱ ላይ ወድቆ ሳለ አውሳብዮስ ማርኮ ያዘው፡፡ አውሳብዮስም ዮስጦስን ከእሥር ቤት አወጣውና በፋርስ አደባባይ ድንኳኖቻቸውን ተክለው እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ሁለት ዓመትም በዚያ ቆይተው ምርኮን ወደ አንጾኪያ ላኩ፡፡ ሌሎቹንም ጠላቶቻቸውን ሁሉ ድል እየነሱ ለሮም አስገዟቸው፡፡ የዲዮቅልጥያኖስ ዓመተ መንግሥቱ 5 ዓመት በሆነ ጊዜ በሰባተኛው ወር የንጉሥ ኑማርያኖስ ልጅ ዮስጦስ የፋሲለደስ ልጅ አውሳብዮስ፣ የታላላቅ ወታደሮች አለቆች የሆኑ ገላውዲዮስና አባድር በታላቅ ደስታ ወደ አገራቸው በተመለሱ ጊዜ በአንጾኪያ ታላቅ ደስታ ተደርጎ ሕዝቡም ወጥቶ በክብር ተቀበላቸው፡፡ ነገር ግን ዲዮቅልጥያኖስ ይህንን ሲያይ እጅግ ደነገጠ መንግሥቱ የንጉሡ ልጅ የዮስጦስ መሆኑን ያውቃልና፡፡
ሁሉም የመንግሥት ልጆች ጠላቶቻቸውን ድል ነሥተው ወደ ሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ በመጀመሪያ ወጥቶ በደስታና በታላቅ ክብር ከተቀበላቸው በኋላ የቅዱስ ፊቅጦር አባት የሆነው ከሃዲው መኰንኑ ህርማኖስ ለጣዖት እንዲግዱና ምስጋና እንዲያቀርቡ ለንጉሡ መከረው፡፡ ንጉሡም እንደተመከረው ለአጵሎን ሰግደው ዳግመኛ ደስ እንደዲያሰኙት ሲጠይቃቸው ቅዱሳኑ እጅግ ተቆጡት፡፡ የፋሲለደስ ልጅ ቅዱስ አውሳብዮስም ንጉሡን ለመግደል ሰይፉን ሲመዘዝ አባቱ ቅዱስ ፋሲለደስ ከለከለው፡፡ በንዴትም ከንጉሡ ጭፍሮች ብዙዎችን ገደለ፡፡ የከበረ ፋሲለደስም ባይከለክላቸው ኖሮ ከንጉሡ ቤት ምንም ሰው ባልቀራቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ህርማኖስ ቅዱስ አውሳብዮስን ወደ ግብፅ እንዲልከው መከረው፡፡ ይህም የንጉሡ መኰንን ህርማኖስ የገዛ ልጁን ቅዱስ ፊቅጦርንም እንዲሁ ወደ ግብፅ በማስላክ አሠቃይቶ ያስገደለ አረመኔ ነው፡፡
ከዚህም በኋላ ዲዮቅልጥያኖስ በሚገዛበት አገር ሁሉ ክርስቶስን ያልካዱትን ምእመናን ማስገደልና ማሳደድ ጀመረ፡፡ ብዙ ሰማዕታትም ወደ ንጉሡ የሰማዕትነት አዳባባይ እየመጡ በጌታችን ስም ደማቸውን አፈሰሱ፡፡ ንጉሡም እንደተመከረው ቅዱስ አውሳብዮስን ወደ ግብፅ ላከውና በዚያም ጽኑ ሥቃይን አሠቃዩት፡፡ ሥጋውን ቆራርጠው በብረት ምጣድ አድርገው ከሥር እሳት አንድደው አበሰሉት፡፡ ጌታችንም መልአኩን ልኮ ከመከራው ሁሉ አድኖት ያለ ምንም ጉዳት አስነሣው፡፡ ነፍሱንም ወደ ገነት ወስዶ ለእርሱና ለጻድቃን ሰማዕታቱ ሁሉ ያዘጋጀላቸውን የገነት ቦታዎች ሁሉ አሳይቶታል፡፡ ዳግመኛም የግብፁ መኰንን ቅዱስ አውሳብዮስን በእሳት ምድጃ ውስጥ ሲጨምረው የታዘዘ መልአክ እሳቱን እንደ ጠል አቀዝቅዞ አዳነው፡፡ ከዚህም በኋላ መኳንንቱ መኰንኑን ‹‹እንዲህ ከመታገል አንገቱን በሰይፍ ብንቆርጠው ይሻላል›› ብለው መከሩትና

02 Mar, 05:31
607
Post image

የቅዱስ አውሳብዮስን ራስ የካቲት 23 ቀን በሰይፍ ቆርጠውት የሰማዕትነቱ ፍጻሜ ሆኖ የክብርን አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀብሏል፡፡ የቅዱስ አውሳብዮስ ወንድሙ ቅዱስ መቃርስም እንዲሁ በከሃድያኑ ነገሥታት እጅግ ተሠቃይቶ ነው በሰማዕት ያረፈው፡፡ አባቱ ቅዱስ ፋሲለደስም ከብዙ ሥቃይማ መከራ በኋላ መስከረም 11 ቀን ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡ የቅዱስ አውሳብዮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ዳግመኛም በዚህች ዕለት ሐዋርያውና ሰማዕቱ ቅዱስ ፖሊካርፐስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ይኽም ቅዱስ ሐዋርያና ሰማዕት የሆነው ፖሊካርፐስ ከ70 ዓ.ም እስከ 156 ዓ.ም የነበረ ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእዩ ከመሰከረላቸው ከ7ቱ አብያተ ክርስቲያናት የአንዱ ይኸውም የሰርምኔስ ዻዻስ የነበረ ነው፡፡ ይኽም ቅዱስ ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ቃል በቃል የተማረና ደቀ መዝሙሩ የነበረ ነው፡፡ አቡነ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ የቅዱስ ፖሊካርፐስ ባልንጀራው ነበር፡፡ ቅዱስ ፖሊካርፐስ ከ46 ዓመታት በላይ በፍጹም ትጋት ቤተ ክርስቲያንን አገልግሎ አረማውያን በ86 ዓመቱ በአደባባይ በእሳት አቃጥለው በሰማዕትነት ገድለውታል፡፡
የቅዱስ ፖሊካርፐስ የሰማዕትነቱ ዜና የተገኘው የራሱ የሆነችው የሰምርኔስ ቤተ ክርስቲያን ሰማዕትነቱን በአካል በተከታተሉ ወንድሞች አማካኝነት ጽፋ ለሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ከበተነችው መልእክት ነው:: በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት የሰማዕትነታቸው ሁኔታ፣ ሳይፈሩ ሰውነታቸውን ለሰይፍ ለስለት እንዴት እንደሰጡ፣ ስለ ክርስቶስ ለመመስከር እንዴት ይጨክኑ እንደነበር በሙሉ ዜና ገድላቸው እየተጻፈ በየአብያተ ክርስቲያናቱ ይሰራጭነበር:: እንደ አግናጥዮስ ሁሉ (በሮም) ፖሊካርፐስ ሰማዕት በሆነበት ጊዜም በሰምርኔስ ከተማ የሕዝብ በዓል ተደርጎ ነበር:: እንደልማዳቸው በዓሉ በሚከበርበት በእስታድየማቸው የአራዊት ትርኢት ነበር:: አሬኒከስ የተባለ አንድ ክርስቲያንም የአሕዛብ ጣዖታትን ካላመለክህ ለአራዊት እንሰጥሃለን ብለውት አሻፈረኝ ብሎ በመፅናቱ በዚያ በአራዊት ተበልቶ ሰማዕት ሆነ:: በዚህ ጊዜም ሕዝቡ ክርስቲያኖች እንዲህ እንዲፀኑ የሚያስተምራቸው ዋነኛው ፖሊካርፐስ ነው እርሱ ተይዞ ይምጣ እያሉ ጮሁ::
ቅዱስ ፖሊካርፐስ የሞት ፍርድ ሲፈረድበት ፀንቶ በከተማዋ ቢቆይም ምእመናን እንዲሸሽ እያለቀሱ ስለለመኑት ባጠገብ ወዳለች መንደር ሸሸ።በዚያ ሳለ ሰማዕት እንደሚሆን በራእይ ተረድቶ እንደሚሞት ለወንድሞችና እህቶች ነገራቸው:: ወዲያው በጥቆማ ተይዞ ወደ ሰምርኔስ ከተማ እያንገላቱ ወስደው ሕዝብ በተሰበሰበበት በበዓሉ አደባባይ አቆሙት:: እርሱም ክርስቶስ በሕዝብ አደባባይ ቆሞ የተቀበለውን መከራ እያሰበ የመከራው ተካፋይ ስላደረገው በፍጹም ደስታ መከራውን ይቀበል ነበር:: በሕዝቡ ፊት አቁሞ የሚያናዝዘው ሹም ክርስቶስን እንዲክድ ብዙ ማግባቢያዎችንና ማስፈራሪያዎችን ቢያቀርብለትም ያለፍርሃት ፀንቶ ክርስቲያንነቱን ስለመሰከረ በእሳት እንዲቃጠል ተፈረደበት:: ወታደሮቹ እሳቱ ውስጥ ከገባ በኋላ የሚያመልጠን መስሏቸው ለማጠር ሲዘጋጁ አይቶ “ወደ እሳቱ እንድገባ ያበረታኝ ጌታዬ በእሳቱ ውስጥም ፀንቼ እንድቆይ ያስችለኛል” አላቸው:: ወታደሮቹ እጅና እግሩን አስረው ወደ እሳቱ ሲያቀርቡት አይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ እንዲህ በማለት የመጨረሻ ጸሎት አደረገ:- “አቤቱ ልዑል እግዚአብሔር የተወደደው ልጅህ የኢየሱስ ክርስቶስ አባት ሆይ በልጅህ አንተን እንድናውቅ ሆነናል:: የመላእክትና የኀይላት እንዲሁም የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ አንተ ነህ፤ ፍጥረታትም ሁሉ የሚኖሩት ባንተ ነው በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ለዘላለማዊ ሕይወት ትንሣኤ ያለፍርሃት ከክርስቶስ መከራ ተካፋይ ከሆኑት ከሰማዕታት ወገን እንድቆጠር ስላደረግኸኝ እና በዚህች ቀንና ሰዓት በሚገባ ስላስተማርኸኝ አመሰግንሃለሁ ።እንደ እነርሱ ዛሬ በፊትህ ተቀብያለሁና እንደ መልካምና የተወደደ መሥዋዕት አድርገህ ተቀበልልኝ።አንተ አስቀድመህ እንዳሳየኸኝ እና እንዳዘጋጀኸኝ አንተ እውነተኛና ታማኝ አምላክ ነህና ስለሁሉ ነገር አመሰግንሃለሁ፣ አከብርሃለሁ፣ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ:: ከሰማያዊው ዘላለማዊ ሊቀ ካህናት ከተወደደው ልጅህ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሱ ጋር ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክብርና ምስጋና ለአንተ ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን!”
የጸሎቱ ይዘት ዛሬ ቤተ ክርስቲያናችን ከምታስተምረው ምሥጢረ ሥላሴ ጋር አንድ አይነት ሲሆን ይህንኑም የመሰለ ጸሎት አላት።በዚህም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጥንታዊና ከምንጮቹ ከሐዋርያት የተረከበችው ለመሆኑ ታላቅ ማስረጃ ነው:: ቅዱሱ ጸሎቱን ሲጨርስ በእሳቱ ውስጥ ወረወሩት:: በቅዱሳኑ ላይ አድሮ ተአምር የሚሠራ እግዚአብሔር ለምእመናን መጽናኛ የሚሆን ድንቅ ተአምርን አደረገ:: እሳቱ የቅዱሱን ሰውነት ዙሪያውን እንደግድግዳ ከቦ የማያቃጥለው ሆነ;: ሕዝቡም እሳቱ እንዳላቃጠለው ባዩ ጊዜ በጦር ተወግቶ ይሙት እያሉ ጮሁ፤ ወታደሮቹም በጦር ወጉትና በዚህ ሰማዕትነቱን ፈጸመ:: ክርስቲያኖች እንዳያመልኩት በሚል የከበረ ሥጋውን አቃጠሉ፤ በዚህ ጊዜ ደስ የሚያሰኝ የእጣንና የሽቶ መአዛ ሸተተ:: ክርስቲያኖችም ተረፈ አፅሙን በክብር ወሰደው ቀበሩት: ቤተ ክርስቲያንም በስሙሠሩለት::
የቅዱስ ፖሊካርፐስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!

(ምንጭ፡- የተስፋ ገብረሥላሴ እትም ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ስንክሳር ዘወርሃ የካቲት)

02 Mar, 05:31
820
Post image

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
የካቲት 23-የልዳው ፀሐይ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በጦርነት ላይ ሳለ ሣህለ ማርያምን (ዐፄ ሚኒልክን) በመርዳት ጠላትን ድል እንዳደረገ የሚናገር ተአምር ይህ ነው፡- ‹‹ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት 1854 ዓመት በኋላ የኢትዮጵያ ነጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ምኒልክ በነገሠ በ26ኛ ዓመት የምኒልክ የጦር አለቃ ገበየሁ ድል ካደረጋቸው በኋላ እንደገና ምኒልክን ወግተው ኢትዮጵያን በቅኝ አገዛዝ ሊገዙ የሮም ሰዎች መጡ፡፡ ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ‹አገሬ ኢትዮጵያን እወዳለሁ የሚል ኢትዮጵያዊ ሁሉ በአስቸኳይ ይነሣ፣ መስቀለ ሞቱንም ተሸክሞ ይከተለኝ፡፡ እግዚአብሔር የወሰነልንን የባሕር ወሰን አልፎ አገር የሚያጠፋ፣ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት መጥቷልና› ሲል አዋጅ አስነገረ፡፡ ዳግመኛም በፈረሶቻቸው መጣብር ላይ በጦራቸው ላይ በጋሻቸው ላይ የመስቀል ምልክት እንዲያደርጉ ወታደሮቹን አዘዛቸው፡፡ መስቀል ጠላትን ድል አድራጊ እንደሆነ አስቀድሞ ያውቅ ነበርና፡፡ ከዚያም ተነሥቶ ወደ ትግራይ ክፍለ ሀገር ዘመተና ከትግራይ አውራጃዎች አንዷ የምትሆን አድዋ ከምትባል አገር ደረሰ፡፡
የሣህለ ማርያም (ዐፄ ሚኒልክ) ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) በንጉሡ ትእዛዝ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሲዛ ከሊቀ ጳጳሱ ከአባ ማቴዎስ እንዲሁም ከቀሳውስቱና ከመነኮሳቱ ጭምር ከንጉሡ ጋር ወደ ጦርነቱ ተጓዘች፡፡ በዚያም ጊዜ የአክሱም ጽዮን መነኮሳትና ካህናት የእመቤታችንን ሥዕል ይዘው ወደ ንጉሡ ወደ ምኒልክ መጥተው ከሊቀ ጳጳሱ ከእነ አቡነ ማቴዎስ ጋር ተቀላቀሉ፡፡ ከዚያም ሌሊቱን ሙሉ ጸሎተ ምሕላ ሲያደርሱ አደሩ፡፡ ቅዳሜ ማታ ለእሑድ አጥቢያ ይኸውም የካቲት 22 ቀን ነው ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ዐፄ ሚኒልክ) የጦር ልብሱን ለብሶ ከሠራዊቱ ጋር ወደ ጦር ግንባር ሄደ፡፡ ከዚያም ከሮማውያን የጠላት ጦር ጋራ ተገናኝቶ ከሌሊቱ በዓሥራ አንድ ሰዓት ጦርነቱን ጀመረ፡፡
የንጉሥ ሣህለ ማርያምን ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) ሌሊት በታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስና በእመቤታችን ሥዕል ፊት በጸሎትና በስግደት እያደረች ሲነጋ ወደ ጦርነቱ ቦታ በመሄድ እጅግ በሚያስደንቅ የአነጋገሯ ኃይለ ቃል በጦርነቱ መካከል እየተገኘች ለንጉሡ ወታደሮች የሞራልና የብርታት ድጋፍ ትሰጣቸው ነበር፡፡ በዕውነትም ለተመለከታት ሁሉ እንደኃይለኛ ተጋዳይ አርበኛ ትመስል ነበረ እንጂ የሴቶች የተፈጥሮ ባሕርይ በእርሷ ላይ አይታይባትም ነበር፡፡ የንጉሡም ወታደሮች የንግሥቲቱን የጀግንነት አነጋገር በሰሙ ጊዜ በእሳት ላይ እንደተጣደ የብረት ምጣድ ልባቸው ጋለ፡፡ ይልቁንም ላም እንዳየ አንበሳና ፍየል እንዳየ ነብር እየተወረወሩ በጦርነቱ መካከል በመግባት የጠላትን ጦር በሰይፍ ይጨፈጭፉት ነበር፡፡ መጽሐፍ ‹ሹመቱን ሽልማቱን ያየ አርበኛ ከጦርነት ከሰልፍ ወደኋላ አያፈገፍግም› ብሎ ተናግሯልና፡፡
በዚያንም ጊዜ ንጉሡ ሣህለ ማርያም በጦርነቱ መካከል ሳለ ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ እንዲሁም የአክሱም መነኮሳት ሌሎቹ ካህናት በሙሉ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስንና ሥዕለ ማርያምን ይዘው ከንጉሡ በስተኋላ በደጀንነት ቆመው ጸሎተ ምሕላ ያደርሱ ነበር፡፡ ንግሥቲቱ ወለተ ሚካኤል በጸሎት ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም ከእነርሱ አትለይም ነበር፡፡ የጽዮን አገልጋዮችም በእግዚአብሔር በሕጉ ታቦት ፊት መለከት ይነፉ ነበር፡፡ በዚህም ዕለት ይኸውም የካቲት 23 ቀን በሮማውያንና በኢትዮጵያውያን መካከል ከፍተኛ ጦርነት ሆነ፡፡ ወዲያውም በሰማይ ታላቅ ተአምር ተደረገ፡፡ ይኸውም የቀስተ ደመና ምልክት ታየ፡፡ ከዚያም ቀስተ ደመና ውስጥ መልኩ አረንጓዴ የሚመስል ጢስ ይወጣ ነበር፡፡ ከዚያም ጢስ ውስጥ እንደክረምት ነጎድጓድ ያለ ድምፅ ተሰማ፡፡ ከዚያም የነጎድጓድ ድምፅ የተነሣ በሮማውያን ወታደሮች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና ሽብር ሆነ፡፡ ለመዋጋትም አልቻሉም፡፡ ይልቁንም ኃያሉ ገባሬ ተአምር ቅዱስ ጊዮርጊስ በአምባ ላይ ፈረስ ተቀምጦ ከነፋስ ሩጫ ይልቅ እየተፋጠነ በአየር ላይ በተገለጠ ጊዜ በግንባራቸው ፍግም እያሉ ወደቁ፡፡ ‹የኢትዮጵያ ሕዝብ አምላካቸው ሊረዳቸው መጣ፡፡ እንግዲህ ማን ያድነናል› አሉ፡፡ ምድር ጠበበቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ የአትዮጵያ ሠራዊት የሮምን የጦር ሠራዊት ፈጁዋቸው፡፡ የተረፉትንም ማረኳቸው፡፡ ፈጽመውም እስኪያጠፏቸው ድረስ በሮማውያን ላይ በእግዚአብሔር ሥልጣን የኢትዮጵያውያን እጅ እየበረታች ሄደች፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ሣህለ ማርያም በእግዚአብሔር ኃይልና በተአምራት አድራጊው በቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት የሮማውያንን የጦር ሠራዊት በጦርነት ድል አድርጎ የድል አክሊል ተቀዳጀ፡፡
ስለዚህም ‹በዳዊት የምስጋና ቃል የድል ዘውድ ያቀዳጀኝን እግዚአብሔርን ባለ ዘመኔ ሁሉ አመሰግነዋለሁ፡፡ ለፈጣሪዬም እዘምራለሁ› አለ፡፡ ሕዝቡም ሁሉ ‹በክብር ከፍ ከፍ ያለ እግዚአብሔርን በፍጹም ምስጋና እናመሰግነዋለን የሮማውያንን ኃይል ቀጥቅጦ አጥፍቷልና፣ ሠረገሎቻቸውንም ሰባብሯልና፣ ሠራዊቱንም ሁሉ በምድር ላይበትኗቸዋልና…› እያሉ አመሰገኑ፡፡ በፈጣሪው በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል በጦርነቱ መካከል የረዳቸውን ቅዱስ ጊዮርጊስንም በፍጹም ማድነቅ እያደነቁ አመሰገኑት፡፡ የሮማም የጦር ሠራዊት በኢትዮጵያውያን ፊት ተዋረዱ፡፡ ዳግመኛም በኢትዮጵያ ላይ እጃቸውን ከፍ ከፍ አላደረጉም፡፡ በምኒልክም ዘመነ መንግሥት ኢትዮጵያ ከጦርነት ለ40 ዓመት ያህል አረፈች፡፡ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ምኒልክም ከአድዋ ጦርነት ከተመለሰ በኋላ አዲስ አበባ በምትባለው ከተማው መካከል በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም የተዋበች ቤተ ክርስቲያን አሠራ፡፡ ስሟንም ‹ገነተ ጽጌ›› ብሎ ሰየማት፡፡ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ በጦርነቱ ሁሉ ይረዳው ነበርና፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስ ጥበቃው ዛሬም አይለየን! ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ዳግመኛም በዚህች ዕለት ክቡር የሆነ የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ ፋሲለደስ ልጅ ቅዱስ አውሳብዮስ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ ይኽም ታላቅ ሰማዕት ቅዱስ አውሳብዮስ የቅዱስ ፋሲለደስ ልጅ ሲሆን በአንጾኪያ ከንጉሡ ቀጥሎ 4ኛ ሆኖ የተሾመ ነበር፡፡ ታላቁ የአንጾኪያ ንጉሥ አውማንዮስ በሞት ባረፈ ጊዜ ኑማርያኖስ በእርሱ ተተክቶ ነገሠ፡፡ ይኸውም ኑማርያኖስ የቅዱስ ፋሲለደስን እኅት ታኦድራን አግብቶ ቅዱስ ዮስጦስን ወለደ፡፡ ቅዱስ ፋሲለደስም የፊቅጦርን የእናቱ እኅት ሶፍያን አግብቶ አራት ልጆችን ወለደ፡፡ እነርሱም ወንዶቹ ቅዱስ አውሳብዮስና ቅዱስ መቃርስ ሲሆኑ ሌሎቹ ዮና እና ሮድስ የተባሉ ሴቶች ናቸው፡፡ ቅዱስ ፋሲለደስ አውዶክስያ፣ ታኦብስታ እና ታኦድራ የተባሉ ሦስት እኅቶች አሉት፡፡ ታላቋ አውዶክስያ ምሥራቃዊውን ቴዎድሮስን ወለደች፡፡ ታኦብስታም የንጉሥ ኑማርያኖስን ወንድም አብጥልማዎስን አግብታ ቅዱስ ገላውዴዎስን ወለደች፡፡
ታናሹዋ ታኦድራም ንጉሡን ኑማርያኖስን አግብታ ቅዱስ ዮስጦስን ወለደች፡፡ የንጉሡ ልጅ ቅዱስ ዮስጦስና የፋሲለደስ ልጅ ቅዱስ አውሳብዮስ የጥበብንና የተግሣጽን ትምህርት እየተባሩ አብረው አደጉ፡፡ ቅዱስ ፋሲለደስም ነገሥታትን የሚመክርና በቤተ መንግሥት በሚሠራ ሥራ ሁሉ አለቃ ሆነ፡፡ ንጉሡ ኑማርያኖስ ፋሲለደስን ሳያማክር ምንም ነገር አያደርግም፣ ምንም ትእዛዝ አያዝም ነበር፡፡ በማዕድም አብረው በተቀመጡ ጊዜ የሁለቱም ልጆቻቸው ዮስጦስና አውሳብዮስ የተማሩትን በፊታቸው አነበቡ፡፡ ንጉሡም የልጁን ትምህርትና ጥበብ መማሩን ባየ ጊዜ ደስ ብሎት ሁለቱም ፈረስ ግልቢያ እንዲማሩ አዘዘ፡፡ ዮስጦስና አውሳብዮስም

02 Mar, 05:31
940
Post image

5ኛው ዙር ሽያጭ ተጀምሯል!
ይኽ መልክዐ ጉባኤ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የሚገኙ ከ40 በላይ የሚሆኑ የታላላቅ ገዳማትን የብራና መልክዐ ጉባኤዎችን በማስተያየት ከአንዱ ላይ የሌለውን ከሌላው ላይ በመውሰድ ከኹሉም የተውጣጡ ከ380 በላይ የተለያዩ መልክዐ መልኮችን ለማካተት እጅግ ከፍተኛ ጥረት የተደረገበት ነው፡፡

መዝሙረ ዳዊቱን በተመለከተ በአሁኑ ጊዜ በገበያ ላይ የሚሸጡት በተለይም የአማርኛ ትርጒም የአላቸው ዳዊቶች በርካታ ስሕተት ያለባቸው በመኾኑ ይኽንን ችግር ለመቅረፍና ምእመናንን ለመርዳት በማሰብ በመጀመሪያ በ1978 ዓ.ም በአሥመራ ኮከበ ጽባሕ ማ/ቤት የታተመውን ዳዊት ግዕዝና አማርኛውን እንደ መነሻ በመውሰድ እርሱ ላይ የተለያዩ የአርትዖት ሥራዎችን በመሥራትና በተለያዩ ገዳማት ከሚገኙ የብራና ዳዊቶች ጋር ቃል በቃል በማስተያየት አስፈላጊውን እርማት በመስጠት ከዚያም በዐፄ ኀይለ ሥላሴ ዘመን በ1952 ዓ.ም በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ በአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት ከታተመው ጥራት ከአለው ዳዊት እንዲሁም በ1941 ዓ.ም በተስፋ ገብረ ሥላሴ አዘጋጅነት በአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት ከታተመው ጥራት ከአለው ዳዊት ጋር ቃል በቃል በማመሳከርና አስፈላጊውን እርማት በማድረግ በመጨረሻም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲያዩት በማድረግ በከፍተኛ ጥንቃቄ ለማዘጋጀት ተችሏል፡፡

ሌላው ይኽንን የጸሎት መጽሐፍ ለየት የሚያደርገው ነገር ሊቃውንት አባቶች በሰጡኝ ጥቆማና መመሪያ መሠረት ዳዊቱ ላይ መዝሙረ ክርስቶስና መዝሙረ ድንግል መካተቱ ሲሆን የጥንት ዳዊቶች ላይ በግዕዝ ብቻ ይገኙ የነበሩትን እነዚኽን ኹለት መዝሙራት ወደ አማርኛ ቋንቋ አስተርጒሜና አርትዖቱን በከፍተኛ ጥንቃቄ ሠርቼ ከዳዊቱ ጋር አብሬ የአካተትሁ ሲሆን ይኽም መዝሙረ ዳዊቱን የበለጠ እጅግ ከፍተኛ ጥቅም እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ በማሕልየ መሓልይውም ላይ ቢሆን ከተለመደውና ከምናውቀው ማሕልየ መሓልይ በተለየ ሁኔታ ተጨማሪ የሰሎሞን ምስጋናዎችን የአካተትሁበት ሲሆን ይኽም በገዳማት ከሚገኙ ከጥንት ብራናዎች ጋር ቃል በቃል በማመሳከር እስከአሁን በታተሙት ቅጂዎች ላይ የሌሉትን ልዩ የኾኑ አንቀጾች ከብራናዎቹ ቅጂዎች ላይ በመውሰድና ወደ አማርኛ በማስተርጐም የተሟላና ትክክለኛ ትርጒም ያለው ማሕልየ መሓልይ እንዲሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ ተደርጎበታል፡፡ ልዩነቱንም ለማሳየት ጭማሪዎቹን አንቀጾች በቅንፍ () ምልክት ውስጥ አስቀምጫለሁ፡፡

ይኽንንም ቤተ ክርስቲያን እንደ ተቋም ልትሠራው የሚገባ ትልቅ ሥራ ቢሆንም እኔ ደካማውና ኃጥኡ ሰው 13 ተርጓምያንና 7 አርታዕያን ሊቃውንትን ይዤ ይኽንን ትልቅ ሥራ በመሥራቴ ትልቅ የመንፈስ እርካታ ከማግኘቴም በላይ ምን ያህል ዕድለኛ እንደኾንሁ እንድረዳ አድርጎኛል፡፡ ለዚኽ ያበቃኝን አምላኬን ኹልጊዜ አመሰግነዋለሁ፡፡

በመኾኑም ይኽን በከፍተኛ ጥራት የተዘጋጀውን ዳዊት እና ከ380 በላይ የሚኾኑ መልክዐ መልኮችን በትጋት የሚጸልይ ሰው ራሱን ከእግዚአብሔርና ከቅዱሳኑ ጋር በቀጥታ ማገናኘት እንደሚችል፤ በነፍስ በሥጋ በእጅጉ እንደሚከብርበትና ሰይጣንን ድል እንደሚነሣበት አዘጋጁ በጽኑ ያምናል፤ ምእመናንም ወደፊት ለዚኽ ምስክር እንደሚሆኑ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡ ምክንያቱም ቅዱሳን አባቶቻችን ዳዊትንና መልክዐ ቅዱሳንን ደግመው ለቅድስና እንደበቁ ኹሉ ምእመናንም ሳያቋርጡ በየጊዜው ዳዊትንና መልክዐ ቅዱሳንን በመድገም ከሰይጣን ፈተና ራሳቸውን መጠበቅና አጋንንትን ድል ማድረግ ይችላሉ፤ በቅድስና የሕይወት መንገድ ራሳቸውን ማኖር ይችላሉ፤ ሰማያዊ ጸጋንና ምድራዊ በረከትን ያገኛሉ፡፡
ይኽ መልክዐ ጉባኤም ይኽንን ዓላማ ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ነውና ለጸሎት ያመች ዘንድ መዝሙረ ዳዊቱን በሳምንት ወይም በ30 ቀናት ውስጥ እንዲጸለይ ተደርጎ የተለየ ማውጫ ተዘጋጅቶለታል፡፡ (ማውጫውን የመጽሐፉ የመጨረሻ ገጾች ላይ ይመለከቷል፡፡)

የመልክዐ ቅዱሳኑንም አቀማመጥ ምቹ እንዲኾን በማሰብ በመጀመሪያ 24 መልክዐ ሥላሴንና ሥሉስ ቅዱስን የሚያመሰግኑ ጸሎቶችን በማስቀመጥ ቀጥሎ የጌታችንን 21 የተለያዩ መልኮችን ከዚያም የእመቤታችንን 31 መልኮችንና ምስጋናዎችን በቅደም ተከተል እንዲቀመጡ ተደርጓል፡፡ የቅዱሳኑን መልክዕ በተመለከተ የመጀመሪያው ማውጫ በስማቸው ቅደም ተከተል መሠረት የተዘጋጀ ሲሆን ኹለተኛው አቀማመጥ በወሩ ውስጥ ከ1-30 በአሉት ቀናት ውስጥ የየቀኑን ለየብቻ በማዘጋጀት ምቹ በኾነ መልኩ ማውጫው ተዘጋጅቷል፡፡

የገጹ ብዛት---> 3181 ገጽ (በ 'A4' size) በጣም ትልቅ ስለኾነ በኹለት ቅጽ ተከፍሏል።
380 መልክዐ መልኮችንና ምስጋናዎችን ከመዝሙረ ዳዊት፣ ከመዝሙረ ክርስቶስና ከመዝሙረ ድንግል ጋር አንድ ላይ አጠቃልሎ የያዘ (በግዕዝና በአማርኛ)
ዋጋ---> በፊት ይሸጥ የነበረው 25,000 (ኻያ አምስት ሺህ) ሲኾን ይኽም አጠቃላይ የኅትመትና የአርትዖት ወጪው ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ ስለነበረና በዱቤም የታተመ ስለነበረ ዕዳውን ለመክፈል ነበር። አሁን ላይ ግን ዕዳው ስለተከፈለ ለገዳማትና ለጉባኤ ቤቶች በነጻ እየተሰጠ ስለኾነ ምእመናንም በሚችሉት ዋጋ አቅማቸው በፈቀደው መጠን በመክፈል መውሰድ እንዲችሉ ኹኔታዎች ተመቻችተዋል።

ገዳማውያን አባቶች ብዙ ተኣምራት እያደረጉበት ያለው ከምንም በላይ ቤተ ክርስቲያንንና ሀገርን እየጠበቁበት ያለው
ይኽ መልክዐ ጉባኤው የትኛውም ነጋዴ እጅ ስለማይገኝ መጽፉን የምትፈልጉ ምእመናን በስልክ እየደወላችሁና መልእክት እያስቀመጣችሁ ተመዝግባችሁ ማግኘት ትችላላችሁ።

ስልክ፦ 0912063211 (ለቴሌግራም) በተለይም በውጭ ሀገር የምትኖሩ ምእመናን ሪከርድ በማስቀመጥና የጽሑፍ መልእክት በመላክ መገናኘት ይቻላል።

ገብረ ሥላሴ

01 Mar, 02:51
1,850