የካቲት ፫/፳፻፲፯ ዓ.ም
በወላይታ ሶዶ ከተማ በሚገኙት በግልና በመንግሥት ትምህርት ቤቶች የቅድመ ግቢ ጉባኤ ሥልጠና የሚከታተሉ ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች መንፈሳዊ የእግር ጉዞ ወደ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም የካቲት 1/ 2017 ዓ.ም አከናውነዋል፡፡
በጉዞም የሊቃ ፣የቆንቶ ልጃገረድ እና ጮራ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡
በዕለቱ ከወላይታ ማእከል የተመደቡ የኦቶና ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ሰበካ ጉባኤ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን አቤነዘር መስፍን “ልባም ሰው” ማቴ 7፡24 በሚል ርዕስ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲሆን በተጨማሪም ከገዳማዊያን አባቶች ምክር እና ቡራኬ ተሰጥቷል፡፡
መረጃው የማኅበረ ቅዱሳን ወላይታ ማእከል ሕ/ግ እና ሚዲያ ክፍል ነው