አሐዱ ባንክ የአንድ ወር ዘመቻ ጀመረ
አሐዱ ባንክ ከግንቦት ፳፩ (21) እስከ ሰኔ ፳፩ (21) ቀን ፳፻፲፭ (2015) ዓ.ም ለአንድ ወር የሚቆይ የደንበኞች ወር መርሐ ግብር ሊጀምር ነው።
አሐዱ ባንክ ለአንድ ወር በሚቆየው በዚህ የደንበኝነት ወር መርሐ ግብር ላይ ከአንድ ሚሊዮን ቤተሰብእ ያላነሰ ለማፍራት አቅዶ በመስራት ላይ ይገኛል።
ባንኩ ከብዙዎች ለብዙዎች በሆነ መርሕ በመላው አገሪቱ በሚገኙ ከ፷፭ (65) በላይ በደረሱ ቅርንጫፎቹ የኢትዮጵያዊንን ባህልና እሴት አቀናጅቶ ዘመኑን የዋጀ የባንክ አገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆን የሞባይል ባንኪንግ፣ የኢንተርኔት ባንኪንግ፣ የካርድ ባንኪንግ እንዲሁም ከከተማ እስከ ገጠር ታሳቢ ያደረጉ የብድር አገልግሎቶች፣ የወጪና ገቢ ንግድ በአጠቃላይ ሙሉ የባንክ አገልግሎቶችን አቅርቧል።
በአቅራቢያዎ በሚገኙ የባንኩ ቅርንጫፎች በመሄድ ደንበኛ እንዲሆኑ በክብር ተጋብዘዋል።