Harun Media - ሀሩን ሚዲያ @harunmedia Channel on Telegram

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

@harunmedia


Harun Media - ሀሩን ሚዲያ (Amharic)

ሀሩን ሚዲያ ለማግኘት እና ለማሳሰብ ለችግር ፍቃድ ደርሷን! ሀሩን ሚዲያ የኢንተርኔት መረጃ፣ ከፍተኛ ዜናዎች እና ስፖርት ዜናዎችን የተለያዩ መረጃዎችን በመዝገብ አልፏል። ሀሩን ሚዲያ ከፍተኛ ሀይልንና ችግር ፍቃድን የመረጃ ዜናዎችንና የቅምሻል አለቃውን እና ሁኔታዊ መረጃዎችን ለመጠቀም ፔጅን ይዘረብ። ሀሩን ሚዲያ ለማገኘት እና ለማሳሰብ ምንም ባለማለት ከሆምንና ምንም ብቻ አይመረጥም። ለመተግበር እና ለበደላ ምልክት ለሚጠቀስ ዜናዎችን ለማስረበር ከሚወሰድ ምንረተም እና ዜናዎች እንዲለያዩ በነሐሴ ፲፱ ወስጌ ይታወቅ ።

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

22 Jan, 09:11


የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአፋር ክልል በርዕደ መሬት የተጎዱ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም እየተደረገ ያለው ጥረት በቂ አለመሆኑን ገለጸ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 14/2017

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በአፋር ክልል በርዕደ መሬት የተጓዱ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም እየተደረገ ያለው ጥረት በቂ አለመሆኑን ገልጿል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት እንዲሁም ከውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች የተውጣጣ ቡድን ይህን ያለው በአፋር ክልል በርዕደ መሬት የተጎዱ ዜጎች ያሉበትን ሁኔታ መመልከቱን ተከትሎ ነው።

የምክር ቤቱ አባላቱ ከሰብአዊ እርዳታ ጋር በተያያዘ የመጠለያ፣ የምግብና ውሃ አቅርቦት እንዲሁም የጤና አገልግሎት አሰጣጥ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ከተመለከቱ በኋላ፤ በቀጣይ መሻሻል ያለባቸውን ጉዳዮች አመላክተዋል ተብሏል።

ለዜጎች የሚደረገው ድጋፍ መጠናከር እንዳለበትና በየደረጃው ያሉ የክልሉ አመራር ለጉዳዮ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው የቡድኑ አባላት ማስገንዘባቸውን ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች በበኩላቸው፤ ጉዳቱ ቅፅበታዊ ድርጊት ቢሆንም በአደጋው የተጎዱ ዜጎችን ለማገዝ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

በአፋር ክልል በተደጋጋሚ እየተከሰተ ባለው የመሬት መንቀጥቀጥ ከ58 ሺህ በላይ ዜጎች መፈናቀላቸው ይታወቃል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

22 Jan, 08:33


የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በሻሸመኔ ከተማ ከተለያዩ መዋቅር ለተውጣጡ ወጣቶች ስልጠና መስጠቱ ገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 14/2017

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በጠቅላይ ም/ቤቱ የሴቶችና ወጣቶች ዘርፍ አዘጋጅነትና በካውንስሉ አስተባባሪነት የሚካሄደውን ሀገር አቀፍ የወጣቶች የስራ አመራርና ስራ ፈጠራ ስልጠናን የመክፈቻ ፕሮግራም በኦሮሚያ ክልል፥  በሻሸመኔ ከተማ በትላትናው ዕለት ማካሄዱን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመዘዋወር ከተለያዩ መዋቅር ውስጥ ከተውጣጡ ወጣቶች ጋር የውይይት እና ስልጠና መርሃግብር ለማካሄድ እቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከዚህ ቀደም በወራቤ ከተማ በትላንትናው ዕለት ደግሞ በሻሸመኔ ከተማ የውይይት እና የስልጠና መርኅ ግብር ማካሄዱ ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

22 Jan, 06:18


የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት የፍልስጤምን አምባሳደር በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸው ተገለፀ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ጥር 14፥ 2017 ዓ.ል አዲስ አበባ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ አምባሳደር ፋሬስ አልቁብን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

በኢትዮጵያ የፍልስጤም አምባሳደር ፋሬስ አልቁብ እና የአምባሳደሩ ዋና ጸሐፊ ዲያዲን አል-ናሙራህ በጠቅላይ ምክር ቤቱ ተገኝተው ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት እና ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ስራ አስፈጻሚ አባላት ጋር በፍልስጤም ሰላም ዙሪያ ተዋይተዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም የሃይማኖታችን መለያ እና የተቋሙ ተልዕኮ ሰላም በመሆኑ የፍልስጤምን እና የኢስራኤልን የተኩስ አቁም ስምምነት አላህ የዘላቂ ሰላም ምክንያት እንዲያደርገው ዱዓችን ነው ብለዋል።

ፍልስጤማዊያን ጸንቶ የመታገል ተምሳሌት፣ በአላህ የመወከል ከፍታንና ትዕግስትን ለዓለም በተግባር ያሳዩ መሆናቸውንም ፕሬዝደንቱ በውይይቱ አንስተዋል።

ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም አያይዘውም በተኩስ አቁም ሰምምነቱ ጦርነት እንዲቆምና ሰላም እንዲሰፍንም ያለመታከት ያደራደሩት አካላትን አመስግነዋል።

የፍልስጤም በኢትዮጵያ አምባሳደር ፋሬስ አልቁብን በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት የፍልስጤም ታሪክ ከነፃነት ትግል ጋር የተያያዘ መሆኑ ለዓለም ሕዝብ ሁሉ ግልፅ ነው ብለዋል።

አምባሳደሩ አያይዘውም በጦርነቱ መቆም መደሰታቸውን ገልፀው አሁን ያለው ሰላም ዘላቂ እንዲሆን ሙስሊሞች ዱዓ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ የስራ አሰፈጻሚ አባላትም ፍልስጤም በሁሉም ዘርፍ ተረጋግታ ማየት እንደሚመኙ ገልጸው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍንም ዘወትር ዱዓ እንደሚያደርጉ መናገራቸው ተገልጿል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

21 Jan, 18:56


ሂጃባችንን ለብሰን እንማራለን! ልዩ ቆይታ ከሰልፉ ተሳታፊዎች ጋር| ታሪካዊ ሰልፍ በመቐለ ከተማHarunMedia#ethiomuslim #habesha #Axum
https://youtu.be/_Sv9vXcb3CM

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

21 Jan, 11:52


የሁለተኛው አለም አቀፍ የቁርኣን እና የአዛን ውድድር ዳኞች አዲስ አበባ መግባት መጀመራቸው ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 13/2017

ከአስራ ሁለት ቀናት በኋላ ጥር 25/2017 ዓ.ል በአዲስአበባ ስቴዲየም ለሚካሄደው ሁለተኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር በኢትዮጵያ ዳኞች አዲስአበባ መግባት መጀመራቸው ተገልጿል።

የአለም አቀፍ የቁርአን ዳኛ ሳዲቅ ሙሀመድ (ዶ/ር) ትላንት ምሽት አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ተወካይ ሸይኽ ኢድሪስ ሁሴን አሊ (ደጋን)፣ የዘይድ ኢብን ሳቢት የቁርኣን ማህበር መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ የአለም አቀፍ የቁርአን ዳኛ ኑረዲን ቃሲም (ዶ/ር)፣ የአለም አቀፍ የቁርአን ውድድር አቢይ አስተባባሪ ኮሚቴ አመራሮችና ሌሎች ወንድሞች በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቪአይፒ ሳሎን አቀባበል እንዳደረጉላቸው ተገልጿል።

በቀጣይ ቀናትም ውድድሩን ለመምራት የአለም አቀፍ ዳኞችና ተወዳዳሪዎች፣ የክብር እንግዶች አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

21 Jan, 09:27


የሒጃብን ጉዳይ አስቸኳይ እልባት ለመስጠት እንደሚሰሩ የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ መናገራቸው ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 13/2017

በአክሱም ከተማ በሚገኙ 5 ትምሕርት ቤቶች ከሒጃባቸው አሊያም ከትምህርታቸው አንዱን እንዲመርጡ ለተፈረደባቸው ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ድምጽ ለመሆን በዛሬው ዕለት በመቐለ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ መካሄዱ ይታወቃል።

ከሰላማዊ ሰልፉ መገባደድ በኋላ የትግራይ 20 የሚሆኑ የሙስሊም ማህበረሰብ ተወካዮች ከጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል።

ከሰልፉ በኃላ ተወክለው ለሄዱ 20 የሙስሊሙ ተወካዮች በጽ/ቤታቸው በሰጡት ምላሽም «የሒጃብ ጉዳይ ፍጹም አጀንዳ መሆን የማይገባው ሆን ተብሎ አጀንዳ እንዲሆን የተደረገ ነው፤ በፍጥነት እልባት እንዲሰጠው እናደርጋለን» ሲሉ መናገራቸው ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

21 Jan, 08:39


https://www.facebook.com/share/v/18sYHfryvz/

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

21 Jan, 08:38


የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ በመቀሌ ከተማ ተካሄደ!

-ሀሩን ሚድያ ጥር 13/2017

ሂጃቧንም ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች፣(ሒጃባ ክትገብር እያ፤ ትምህርታ ውን ክትማሃር እያ) በሚል መሪ ቃል በመቐለ ከተማ በአክሱም በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት የተገለሉ ሙስሊም ተማሪዎች ወደትምህርት ገበታ እንዲመለሱ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂጿል።

በሰልፉ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ የመቐለ ከተማ ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን በአክሱም የሀገሪቱ ህገ መንግስት፣ የትምህርት ሚኒስትር መመሪያና ደምብ በአጠቃላይ ሀገራዊና ዓለማቀፋዊ የሰብአዊ መብት ህጎችና ድንጋጌዎች በመጣስ በ159 ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ እየተፈጸመ ያለን የመብት ጥሰት በመቃወም በርካቶች አደባባይ በመውጣት ሂጃብ እንዲከበር፣ ትምህርታቸውን እንዲማሩ ሰብዓዊነትና የእኩልነት መርሆች እንዲጠበቁ የሚገልፁ መፈክሮችን አሰምተዋል።

ሰላማዊ ሰልፍፉ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትና ከክልሉ ሸሪዓ ፍርድ ቤት ዋና ፅህፈት ቤት መነሻውን በማድረግ እስከ ሮማናት አደባባይ ድረስ የተካሄደ ሲሆን 3 ኪሎሜትር መሸፈኑም ተገልጿል።የሰልፉ ተሳታፊዎችም፤ ሂጃብ እንዲከበር፣ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ እንዲሁም የፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲከበር የሚጠይቁ በርካታ መፈክሮችን ይዘው ተስተውለዋል፡፡

የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼይኽ አደም አብዱልቃድር እና ዋና ፀሀፊ ሀጂ መሀመድ ካህሳይ; "ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ሁለት ወይም ሶስት ጊዜ ለትምህርት ቢሮ እና ለአክሱም ትምህርት ጽህፈት ቤት ደብዳቤ ጻፍን ነገር ግን ምንም ለውጥ ስላላመጣ በዛሬው ዕለት ሰላማዊ ሠልፍ መካሄዱን ተናግረዋል።

የትግራይ መጅሊስ ዋና ፀሀፊ ሀጂ መሀመድ ካህሳይ አክለውም የአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ፍትህ እንዲያገኙ ለማስቻል 11 ሰዎች መመረጣቸውንም ገልፀዋል።

ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ኡለማዎች፣ ኢማሞች እና የሀገር ሽማግሌዎች ከፊት ሆነው የመሩት ሲሆን በርካታ የከተማዋ ማህበረሰብ በመገኘት በአክሱም በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው በደል እንዲቆም ድምፅ አሰምተዋል።

-ሀሩን ሚድያ በሰልፉ ዙሪያ ያጠናቀርነውን ዘገባ በአላህ ፍቃድ ወደናንተ ምናደርስ ይሆናል።

©ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

21 Jan, 06:10


ትምህርቷንም ትማራለች፣ ሂጃቧንም ትለብሳለች (ሒጃባ ክትገብር እያ፤ ትምህርታ ውን ክትማሃር እያ) በሚል መሪ ቃል በመቐለ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል!

ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 13/2017

የትግራይ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት በተጠራው የመብት መከበር ሰላማዊ ሰልፍ በአክሱም የሀገሪቱ ህገ መንግስት፣ የትምህርት ሚኒስትር መመሪያና ደምብ በአጠቃላይ ሀገራዊና ዓለማቀፋዊ የሰብአዊ መብት ህጎችና ድንጋጌዎች በመጣስ በ159 ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ እየተፈጸመ ያለን የመብት ጥሰት ለመቃወም በጠራው ሰልፍ በርካቶች አደባባይ በመውጣት ሂጃብ እንዲከበር፣ ትምህርታቸውን እንዲማሩ ሰብዓዊነትና የእኩልነት መርሆች እንዲጠበቁ እየገለጹ ይገኛሉ።

ሰላማዊ ሰልፉን ኡለማዎች፣ ኢማሞች እና ሽማግሌዎች ከፊት ሆነው እየመሩት ሲሆን በርካታ የከተማዋ ማህበረሰብ ተገኝቷል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

13 Jan, 18:08


https://youtu.be/vRAQODu0mzg?si=qM0Qz9tJZPMbfG1f

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

13 Jan, 10:38


የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት መጭውን የሐጂ ጉዞ በተመለከተ ከሳውዲ አረቢያ ሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራረሙ!

-ሀሩን ሚዲያ፣ጥር 5/2017

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትና የሳውዲ አረቢያ ሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር የ1446 ዓ.ሒ የሐጅ ጉዞን የተመለከተ የሁለትዮሽ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።

የመግባቢያ ሰነድ ስምምነቱ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንትና የሐጅና ዑምራ ዘርፍ ተጠሪ በሆኑት ሸይኽ አብዱልአዚዝ ሼይኽ አብዱልወሊና እና በሳውዲ አረቢያ በሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ተውፊቅ ራቢዓ እንደተፈረመ ከቦታው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

በምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝደንትና የሐጅና ዑምራ ዘርፍ ተጠሪ ሼይኽ አብዱልአዚዝ ሼይኽ አብዱልወሊ የተመራው ልዑክ በሳውዲ አረቢያ በተዘጋጀው የ1446 ዓ.ሒ/2017 ዓ.ል ዓመታዊው የሐጅ ማስጀመሪያ አውደርዕይ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ በአውደ ርዕዩ የሚቀርቡ ልምዶችን ከመቅሰም ጎን ለጎን ከአገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ጋርም ተጨማሪ ስምምነቶች ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል ሲሉ የዘገበው የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ነው።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Jan, 19:22


ባቡል ኸይር የበጎ አድራጎት ድርጅት "አምስት አመታት በሰብአዊነት" በሚል መሪ ሀሳብ የአምስተኛ አመቱን ልዩ ዝግጅት በድርጅቱ የምገባ እና የአረጋውያን መጠለያ ማዕከል በዛሬው እለት በድምቀት አካሄደ!

-ሀሩን ሚዲያ፣ጥር 4/2017

ባቡል ኸይር ላለፋት አምስት አመታት የሰራቸው የሰብዓዊነት ዘርፈ ብዙ ስራዎች በድርጅቱ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሀናን ማህሙድ አማካኝነት ለመድረኩ ታዳሚዎች ገለፃ የተደረገ ሲሆን አምስት ዓመታቱ በተስፋ ፣ በማግኘት ፣ በማጣት የተመላለሰ ድርጅቱም በየጊዜው ህዝባዊነቱ እያደገና የሚሰጠው አገልግሎት እየሰፋ መሆን ገልጻ የማዕከል ግንባታውን ሁሉም ርብርብ በማድረግ የግሉን አሻራ እንዲያስቀመጥ መናገሯ ተገልጿል።

የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢፌዴሪ የሴቶችና ማሀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክብርት ሁሩያ አሊ ፣የሀይማኖት አባቶች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው የባቡል ኸይር የደግነት ቤተሰቦች የድርጅታችን ተጠቃሚ እናቶች እና አባቶች በዚህ ታሪካዊ መድረክ ላይ ታድመዋል።

በመድረኩ የሮዳስ ቲ ሮቶ ባለቤት አቶ ፀጋዬ በመድረኩ በመገኘት የተሰማቸውን ደስታ ሲገልጹ “ ልሰጥ አልመጣሁም ፣ ልቀበል እንጂ “ በማለት የተሰማቸውን ሀሴት በመግለጽ በመካከላችሁ ስለመገኘታቸው የጋበዛቸውን እና አምላካቸውን አመስግነዋል ባለሀብቱ 50 ሺ ሊትር የሚይዝ ሮቶም አበርክተዋል።

ወጣቱ ባለሀብት ምህረትአብ ሙሉጌታ በበኩሉ ከድርጅቱ ድጋፍ አንጻር ምንም አላደረግንም ደስታውው የተሰጠንን ጊዜ ገንዘብ ለአባቶችና እናቶች ድጋፍ ማድረግ ደስታው ለኛ በማለት ተናግረዋል ። መድረኩ በአባቶች ዱኣ የተዘጋ ሲሆን ባቡል ኸይር በመድረኩ ላይ አቶ ፀጋዬን እና ምህረትአብን የክብር ጋቢ በማልበስ አመሰግኗል ሲል ድርጅት በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባጋራው መረጃ አስታውቋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Jan, 18:35


በሀረር ከተማ በኢማሙ አህመድ ስቴድየም ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ተካሄደ!

-ሀሩን ሚድያ ጥር 4/2017

በሐረሪ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አዘጋጅነት በሐረር ከተማ ኢማም አህመድ ስታዲየም የታላቁ የረመዳን ወር መቃረብን አስመልክቶ የሙሃደራ ፕሮግራም እና ከ18 ትምህርት ቤት የተወጣጡ የተማሪዎች ምርቃት መርኅግብር ተካሂጿል።

የሐረር ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼይኽ አብዱልሰላም ጅብሪል የፕሮግራሙ አላማ በክልሉ በሚገኙ የእውቀት ትምህርት ቤቶች መካከል ፍቅርና አንድነት ለመፍጠር ያለመ መሆኑን አንስተዋል።

ሼይኽ አብዱልሰላም አክለውም ክልሉ ማህበረሰቡ በፍቅርና በአንድነት አብሮ በመኖር የሚታወቅ በመሆኑ የክልላችን ፀጥታ በሁሉም አካላት ሚና ይጠበቃል ብለዋል።

መርሃ ግብሩ የረመዳን ወር ዝግጅት አካል ሲሆን ማህበረሰባችን የረመዳንን ወር በጋራ ለመቀበል ዝግጅት በማድረግ ላይ ነው ብለዋል።

ዝግጅቱ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና ለተጫወቱትን የጸጥታ አካላትና የህብረተሰብ ክፍሎችን በራሴና በክልሉ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በዝግጅቱ ላይ በተለያዩ ምሁራንና የሀይማኖት አባቶች በህብረተሰቡ መካከል አብሮ የመኖር፣የፍቅር እና የአንድነት መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ በክልሉ የሚገኙ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ኡለማዎች፣የእስልምና ሀይማኖት ትምህርት ቤቶች አመራሮች እና ተማሪዎች መገኘታቸውን ሀሩን ሚድያ ከክልሉ መጅሊስ ያገኘው መረጃ ያመላክታል።

©ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Jan, 17:31


በሸገር ሲቲ የፉሪ ክ/ከተማ እ/ጉ/ም/ቤት 2ኛ መደበኛ ጠቅላለ ጉባኤውን ማካሄዱን ገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 4/2017

ም/ቤቱ ጠቅላለ ጉባኤውን የሸገር ሲቲ እ/ጉ/ከ/ም/ቤት ም/ፕሬዚዳንት ኡስታዝ አድናን ጀእፈር፣ የመስጅድና አውቃፍ ዘርፍ ኃላፊ ሼ/ሙሀመድ አሊ ፣የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዚዳንት ኡስታዝ ሀይደር ኸዲር፣ የክ/ከተማ መጅሊስ ሥራ አስፈጻሚ አባላት፣ የወረዳ መጅሊስና የመስጅዶች አስተዳደር ኮሚቴ አባላት፣ ኢማሞች፣ ሙአዝኖች፣ የወጣት ተወካይዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ያለፈው አመት እቅድ አፈጻጸምና የ2017 ዓ.ል የስራ ዘመን እቅድ ቀርቦ ውይይት እንደተደረገበት ተገልጿል።

የ2017 ዓ.ል የስራ ዘመን እቅድ ሰፋ ያለ ሀይማኖታዊና ማህበራዊ ጉዳዮችን የዳሰሰ ሲሆን ለእቅዱ ውጤታማነት የም/ቤቱ መዋቅር ሁሉ ድርሻውን እንዲወስድ ጥሪው ቀርቧል።

በመድረኩ በክ/ከተማው መጅሊስ የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው የተገመገሙ ሲሆን በመስጅዶች ደረጃ በህዝበ ሙስሊሙ አንድነት፣ ወንድማማችነትና የሀገር ልማት ላይ ኢማሞች ከመስጅድ አስተዳደር ኮሚቴና ከወጣቱ ጋር ጠንክረው በአንድነት መስራት እንዳለባቸው ተጠቁሟል።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ ያገኘውን እድል በአግባቡ በመጠቀም በሀገር ግንባታ፣ በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ የልማትና በየእርከኑ የአመራር ተሳትፎውን በሚመጥነው ልክ ከፍ ማድረግ እንዳለበት መልእክቶች ተላልፈዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Jan, 14:44


የ12ተኛ ክፍል ፈተና ምዝገባ ከነገ በስቲያ ማክሰኞ ጥር 6/2017 ዓ/ል ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ ይጠናቀቃል ተባለ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 4/2017

የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የ2ዐ17 ዓ.ል ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (የ12 ኛ ክፍል) ፈተና ምዝገባ መጪው ማክሰኞ ጥር 6/2017 ዓ/ል ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ እና በተለያየ ምክንያት ያልተመዘገባችሁ ካላችሁ በነዚህ ቀሪ ሁለት ቀናት ላይ ብቻ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፣ ያልተመዘገበ አይፈተንም” ሲል ማሳሰቢያ ለጥፏል።

እንደሚታወቀው በአክሱም ከተማ የ12ተኛ ክፍል ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሒጃባቸው ምክንያት የብሄራዊ ፈተና መመዝገቢያ ፎርም እንዳይሞሉ ተከልክለዋል።

በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር እና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ጣልቃ በመግባት የአክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች ፎርም የሚሞሉበትን መንገድ እንዲያመቻቹ ተጠይቋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Jan, 13:37


ሙስሊም ተማሪዎች በተለይም ከታች ባለው መዋቅር ተደጋጋሚ የሆኑ የመብት ጥሰቶች እየተፈፀመባቸው ስለሆነ ያለምንም ስጋት ይማሩ ዘንድ የትምህርት ሚኒስቴር ቋሚ የሆነ ድንጋጌ እንዲያስገባ ተጠየቀ!

- ሀሩን ሚድያ ጥር 4/2017

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሱ ያሉ በደሎችን አስመልክቶ ወቅታዊ መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫውም ሙስሊም ተማሪዎች በተለይም ከታች ባለው መዋቅር ተደጋጋሚ የሆኑ የመብት ጥሰቶች እየተፈፀመባቸው ስለሆነ ያለምንም ስጋት ይማሩ ዘንድ የትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ ማሻሻያ እያደረገባቸው ባሉ አዋጆችና መመሪያዎች ውስጥ ለመብቱ ከለላ የሚሆንና መብቱን የሚጥሱ አካላትን ተጠያቂ የሚያደርግ ድንጋጌ እንዲያስገባ ጠይቀዋል።

ሙስሊም ተማሪዎች በአክሱም ትምህርት ቤቶች፣ በጉንቸሬ፣ በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ፣ በሰላሌ ዩንቨርስቲ፣ በዲላ ዩንቨርስቲ፣ በመቱ ዩንቨርስቲ በሂጃብና በሰላት ምክንያት ተደጋጋሚ በደሎች እየተፈፀመባቸው እንደሚገኝም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት አስታውቋል።

በመሆኑም የሚመለከተው አካል በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል በዘላቂነት እንዲያስቆም ቋሚ መፍትሄ እንዲያወጣ በመግለጫው ላይ ተነስቷል።

- የመግለጫውን ሙሉ ይዘት ከታች አያይዘናል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Jan, 12:03


በጋምቤላ ከተማ የተገነባው ዘመናዊ መስጅድ ተመረቀ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ጥር 4/2017

በጋምቤላ ከተማ 03 ቀበሌ በኡስታዝ ሹአይብ ሸምሱ አስተባባሪነት ግንባታው የተጠናቀቀው ደረጃውን የጠበቀ የአል-አቅሳ መስጂድ መመረቁ ተገልጿል።

መስጂዱንም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ እና የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ መርቀው ከፍተውታል።

የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ እንደገለፁት በጋምቤላ ከተማ ዘመናዊ መስጂድ እንዲገነባ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በዝግጅቱ ላይ የፌደራል መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ የኦሮሚያ መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአዲስ አበባ መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች፤ኡለማዎች፣ ኡስታዞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች፣ በርካታ የጋምቤላ ከተማ ነዋሪዎች መገኘታቸው ተገልጿል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Jan, 11:39


የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተቋማት እና ማህበራት በአክሱም ተማሪዎች ጉዳይ ያላቸውን አቋም እንዲያሳውቁ ጠየቀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 4/2017

የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተቋማት እና ማህበራት በአክሱም ተማሪዎች ጉዳይ ያላቸውን አቋም እንዲያሳውቁ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ጠይቋል።

የክልሉ መጅሊስ ለትግራይ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ ትግራይ ህዝብ ግንኙነት ጉባኤ፣ ትግራይ ሲቪክ ማህበራት ህብረት፣ ትግራይ ሴቶች ቢሮ፣ ህወሓት ጽ/ቤት፣ ባይቶና ፓርቲ ጽህፈት ቤት፣ ሳልሳይ ወያነ ፓርቲ ጽ/ቤት፣ ዓሲምባ ፓርቲ ፅህፈት ቤት፣ ውናት ፓርቲ ፅሕፈት ቤት፣ ለ አክሱማዊ ዋዐሰላ ፓርቲ ፅሕፈት ቤት እና ለ ሁሉም የትግራይ ብሔራዊ ፓርቲዎች አቋማቸውን በጽሁፍ እንዲገልጹ ጠይቀዋል።

- ሙሉ መግለጫው ከታች ተያይዟል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Jan, 18:00


ሴኩላሪዝም እና የሃይማኖት ነፃነት በኢትዮጵያ የትምህርት መስተጋብር ተግዳሮቶችና ተስፋዎች በሚል የምርምር አውደ ጥናት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ጥር 3/2017 አዲስ አበባ

ኢማን ኢስላማዊ ማህበር ለ1 ዓመት ኢስላሚክ ሪሰርች እና ካልቸራል ሴንተር (IRCC) በተባለ ተቋም ሴኩላሪዝም እና የሃይማኖት ነፃነት በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት መስተጋብር፣ ተግዳሮቶች እና ተስፋዎች" በሚል ጥናት ሲያስጠና መቆየቱ ተገልጿል።

በዛሬው ዕለትም የፌደራል መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ ኡለማዎች፣ ኡስታዞች፣ ምሁራኖች እና ሌሎች ባለድረሻ አካላት በተገኙበት የጥናቱ ውጤት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

ጥናታዊ ፅሁፉን ያቀረቡት ሚ/ር ቃሲም ሱልጣን እና ሚ/ር ኦርጂ ቢሶ ናቸው። በጥናታዊ ፅሁፉ ላይ የሃይማኖት ነፃነት በኢትዮጵያ የትምህርት ተቋማት አረዳድና አተገባበር ምን እንደሚመስል፣ የሴኩላሪዝም ምንነት፣ የሴኩላሪዝም አተገባበር በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ተሞክሮዎችን በመውሰድ መካተታቸው ተገልጿል።

ሴኩላሪዝምን በተመለከተ እስከታች ድረስ ግልፅ አሰራር አለመኖሩን፣ የሴኩላሪዝም አረዳድ ላይም ክፍተት መኖሩን እንዲሁም መንግስት የሚያስተዳድረውን ማኅበረሠብን የሚመሰል የህግ ማዕቀፍ እንዲኖረውም ምክረ ሀሳብ ቀርቧል።

በውይይቱ ላይ ከተሳታፊዎች ጥናቱን ለማዳበር ሙያዊ ሃሳቦችዎን ያጋሩ ሲሆን የጥናቱ ውጤት ለሃገር ፋይዳ በሚጠቅም መልኩ እና ጥናቱ እንዲተገበር ገንቢ አስተያየቶችን በመስጠት ውይይቱ ተጠናቋል።

- ሀሩን ሚድያም በዝግጅቱ ላይ በመገኘት ያሰናዳነውን የቪድዮ ዝግጅት በአላህ ፍቃድ ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Jan, 15:44


በኢትዮጵያ የመጀመሪያ አለም አቀፍ ከወለድ - ነጻ የፋይናስ ኮንፍረንስ እና ሽልማት ስነ-ስርአት ሊካሄድ መሆኑ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 3/2017

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ከወለድ- ነፃ ፋይናንስ ኮንፍረንስ እና ሽልማት "ጠንካራ የፋይናንስ አገልግሎት ለህብረተሰብ ዘላቂ ጥቅም" በሚል መሪ ሀሳብ በመጭው የካቲት ወር እንደሚካሄድ ተገልጿል።

ሳዲያ መልቲ ሚዲያ እና አል ማቲን ኮንሰልታንሲ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጋር በመተባበር ኮንፍረንስ እና ሽልማቱን የሚያዘጋጁ መሆናቸውን በዛሬው ዕለት አዘጋጆቹ በአዲስ አበባ አያ ሆቴል በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

የአልማቲን አማካሪ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የዓለም አቀፍ ከወለድ-ነጻ የፋይናንስ ኮንፈረንስ እና ሽልማት 2025 አዘጋጆች መካከል የሆነው ከማል አብደላ እንደገለፀው የኮንፈረንሱ ዋና አላማ በሀገራችን ያሉ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ ተቋማትን ተቀራርበው እንዲሰሩ የትብብር መድረክ ማዘጋጀት፣ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎቱን አስመልክቶ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር እንዲሁም በዘርፉ ያሉ ማነቆዎች ላይ መፍትሔ ለማበጀት መሆኑ ተገልጿል።

ይህ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ከወለድ- ነፃ ፋይናንስ ኮንፍረንስ እና ሽልማት የፌዴራል እና የአዲስአበባ መጅሊስ አመራሮች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የዘርፉ ምሁራን፣ ነጋዴዎች፣ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ ተቋማት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በመጭው የካቲት ወር በአዲስአበባ ስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Jan, 15:06


2ኛው አለም አቀፍ የቁርኣንና የአዛን ውድድር በኢትዮጵያ አዘጋጆች ከአዲስአበባ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ጋር ውይይት አካሂዱ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 3/2017

በዘይድ ኢብኑ ሳቢት የቁርአን ማህበር አዘጋጅነት በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነት በመጭው ጥር 25/2017 በአዲስአበባ ስታዲየም የሚካሄደውን 2ኛው አለም አቀፉ የቁርአንና የአዛን ውድድር አስመልክቶ ውድድሩን በኻዲምነት ከሚመሩት የአዲስአበባ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ጋር ውይይት ተደርጓል።

በውይይቱ ላይ ውድድሩን በተሻለ መልኩ ለማዘጋጀት የኢትዮጵያን ኢስላማዊ ታሪኮች አጉልቶ ለማሳየት በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ እንዲሁም የማህበረሰቡን የእንግዳ ተቀባይነት ባህል በሚገልጽ መልኩ እንግዶችን ለመቀበል የተደረጉ ዝግጅቶች ላይ ውይይት ተደርጓል።

የአዲስአበባ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ 2ኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር በኢትዮጵያን አስመልክቶ በመስጅዶች በጀማአና በተለያዩ መንገዶች ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየሰራ መሆኑ ተገልጿል።

ፍልስጤም እና ሶሪያን ጨምሮ ከ60 ሀገራት በላይ እንደሚሳተፉበት የሚጠበቀው 2ኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር በኢትዮጵያ ከጥር 10/2017 ጀምሮ እንግዶች ወደ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሏል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Jan, 14:12


በአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት በቀላሉ የሚታይ አይደለም ሲል ቅድሚያ ለሰብኣዊ መብቶች የተሰኘ ድረጅት የሒጃብ ክልከላውን አወገዘ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 3/2017

ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች (Human Rights First) በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1234/2 አንቀጽ 11(4) የተቋቋመ ድርጅት መሆኑ ተገልጿል።

ድርጅቱ በአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት በቀላሉ የሚታይ አይደለም ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫው አስታወቋል። ይህ ጥሰት የትግራይን ሕገ መንግሥት የሚጻረር፣ የተማሪዎችን የአለባበስ ሥርዓት የሚጻረር እና በአጠቃላይ ከሕግ እና ከነባሩ የትግራይ ተወላጆች ባህል ጋር የሚጋጭ ነው ብሏል።

በትግራይ ሂጃብ መልበስ ህጋዊ እና ለብዙ ሺህ አመታት ሃይማኖታዊ ተግባር ሆኖ ቆይቷል ያለ ሲሆን ትምህርት ቤቶች በማንኛውም መልኩ ከስቴት ወይም ከክልል ሕገ መንግሥት ጋር የሚቃረኑ ሕጎችን እንዲያወጡ ወይም እንዲተገበሩ አይፈቀድላቸውም ብሏል ድርጅቱ።

ህገ መንግስቱን በግልፅ በመጣስ የተማሪዎችን የትምህርት እድል መነፈግ በጣም አሳሳቢ ጉዳይ ነው ያለ ሲሆን ጉዳዩ ወደ ህግ መምራት አለበት ሲል አክሏል።

በፌዴራል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1234/2 አንቀጽ 11(4) እነዚህን ጥሰቶች በፈጸሙት የመንግስት ተቋማት እና ግለሰቦች ላይ በከፈቱት ክስ (የትግራይ እስልምና ጉዳዮች) ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች አስፈላጊው እርዳታ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል

ሰብአዊ መብቶች በቋንቋ፣ በጎሳ፣ በሀይማኖት፣ በሀብት እና በቀለም አይለያዩም። ሁሉም ሰው በተፈጥሮው ብቻ በሕግ ፊት እኩል ነው። የኛ ውግንና ለሰብአዊ መብት ብቻ ነው ሲል መግለጫውን አጠቃሏል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Jan, 13:44


"...ሂጃባችሁን ካላወለቃችሁ ፎርም አትሞሉም በመባላችን የ12 አመት ልፋታችንን መና ሊቀር ነው።"

-የአክሱም ከተማ የ12ኛ ክፍል ሙስሊም ተማሪዎች!

ሀሩን ሚዲያ፣ጥር 3/2017

በትግራይ ክልል የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች "ወይ ሂጃባችሁን አውጣችሁ ፎርሙ ሙሉ አሊያ ከፈተና ውጪ ትሆናላችሁ" በመባላቸው የአስራ ሁለት አመት ድካማችን ሜዳ ላይ ሊቀር ነው ሲሉ ለሀሩን ሚዲያ ገልጸዋል።

የዘንድሮው አመት የትምህርት ዘመን የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፎርም የሚሞላበት ቀን በመጭው ሰኞ ጥር 5/2017 ዓ.ል የሚጠናቀቅ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን 159 የሚሆኑ የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ፎርሙን አለመሙላታቸውን ገልጸዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ሁለት አመት ወደኋላ መቅረታቸውን የሚናገሩት ተማሪዎቹ አሁን ደግሞ በሂጃባችን ምክንያት ከፈተና ውጪ ልንሆን ነው ሲሉ ተናግረዋል።

"ትምህርታችሁን ወይም ሂጃባችሁን"አንዱን ምረጡ ተብለን ሰብዓዊ ክብራችን ሀይማኖታዊ ማንነታችን ተገፎ ከጓደኞቻችን በታች እንድንሆን እየተደረግን ነው ሲሉ ተማሪዎቹ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

በከተማዋ 159 የሚሆኑ ሙስሊም ሴት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ጨምሮ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሙስሊሞች ተማሪዎች በተመሳሳይ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ ከሆኑ ከወር በላይ ሆኗቸዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ በሴቶች እና ህፃናት ላይ የሚሰሩ ተቋማት እንዲሁም የሰብዓዊ መብትን በተመለከተ የሚሰሩ ተቋማት አስካሁን ያሉት ነገር የለም።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Jan, 09:09


ሴኩላሪዝም እና የሃይማኖት ነፃነት በኢትዮጵያ የትምህርት መስተጋብር ተግዳሮቶችና ተስፋዎች በሚል የምርምር አውደ ጥናት ቀርቦ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል!

- ሀሩን ሚድያ ጥር 3/2017፤ አዲስ አበባ

ኢማን ኢስላማዊ ማህበር ለ1 ዓመት ኢስላሚክ ሪሰርች እና ካልቸራል ሴንተር (IRCC) በተባለ ተቋም ሴኩላሪዝም እና የሃይማኖት ነፃነት በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት መስተጋብር፣ ተግዳሮቶች እና ተስፋዎች" በሚል ጥናት ሲያስጠና መቆየቱ ተገልጿል።

በዛሬው ዕለትም የፌደራል መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ ኡለማዎች፣ ኡስታዞች፣ ምሁራኖች እና ሌሎች ባልድረሻ አካላት በተገኙበት የጥናቱ ውጤት ቀርቦ ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል።

- ሀሩን ሚድያም በዝግጅቱ ላይ የተገኘ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን የሚያደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

10 Jan, 19:30


https://youtu.be/CF3WB8zd17Q?si=hoKhcTl44KiXVBSF

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

10 Jan, 18:33


በአፋር በተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ከ54 ሺ በላይ ወገኖች ከቀያቸው መፈናቀላቸው ተገለፀ።

- ሀሩን ሚድያ፣ ጥር 2/2017 ዓ.ል

በአፋር ክልል በተደጋጋሚ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የካልዋሌና አጎራባች ቀበሌዎች የአደጋ ተጋላጭ በመሆናቸው ምክንያት ከ54 ሺህ በላይ ሰዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸው የተገለፀው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የልዑካን ቡድን በአፋር ክልል ምልከታ ባደረገበት በዛሬው ዕለት ነው።

በክልሉ የገቢረሱ ዞን አስተዳደሪ አቶ ዓሊ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤቱ ልዑክ በሰጡት ማብራሪያ የመሬት መንቀጥቀጡ የአደጋ ስጋት በፈጠረባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ኮማንድ ፖስት ታውጇል ብለዋል።

አስተዳዳሪው እንዳሉት ከአዋሽ ፈንታሌ የ4 ቀበሌ እና ከድሉቻ ደግሞ የ2 ቀበሌ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለቀው አስቦሌ ቦራ እና ዳኢዶ በሚባል አካባቢ ሰፍረዋል። መንግስት ለተፈናቃዮች ድጋፍ እያደረገ እንደሆነ የገለፁት አስተዳዳሪው ከችግሩ ስፋት አንፃር የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል።

የጥናት ባለሙያዎች ከፈንታሌ እስከ ደፋን ባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ወገኖች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ቢጠየቁም አሁንም በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች አካባቢውን ለቀው ለመውጣት ፈቃደኛ ሊሆኑ እንዳልቻሉም አስተዳዳሪው ጠቅሰዋል።

በኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሥራ አስፈጻሚ አባልና የፈትዋና ምርምር ዘርፍ ተጠሪ በሆኑት ሼይኽ ኢድሪስ አሊ ሑሴን የተመራው የምክር ቤቱ ልዑክ በመሬት መንቀጥቀጡ ሳቢያ በነዋሪዎች ላይ የደረሰውን ጉዳት ተመልክቷል።

ሼይኽ ኢድሪስ አሊ ሑሴን የመሬት መንቀጥቀጡ በዜጎች ላይ ያደረሰውን ችግር አስከፊነት በአካል ተገኝተን መመልከታችን በችግሩ ስፋት ልክ መፍትሄ ለማፈላለግ ይረዳናል ብለዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ልዑክ በመሬት መንቀጥቀጡ ከፍተኛ ወድመት የደረሰበትን የከሰም ስኳር ፋብሪካም የጎበኘ ሲሆን ጉዳቱን የፋብሪካው የሲቪል ስራዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ አሰመላሽ ፍሳሃዬ ለልዑካኑ ገለፃ አድረገዋል።

የአፋር ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት እና የክልሉ ሸሪዓ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ሸይህ ሙሳ ሙሐመድ ዑመር በበኩላቸው በስኳር ፋብሪካው አካባቢ በነበረ መስጅድ ላይ ከደረሰው ውድመት በስተቀር እስከ አሁን በሰዎች ላይ የደረሰ የሞት እና የአካል ጉዳት የለም ብለዋል።

የኢትዮጵያን እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ልዑክ ከተፈናቃዮች ጋር የጁምዓ ሰላትን የሰገደ ሲሆን የጠቅላይ ምከር ቤቱ የመስጂድና አውቃፍ ዘርፍ ተጠሪ ሸይኽ መሐመድ አህመድ አውስዮ እና የምክር ቤቱ የሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ተጠሪ ሸይህ ሁሴን ሀሰን በተፈጥሮ አደጋው ምክንያት ከቀያቸው ተፈናቅለው ለከፋ ማህበራዊ ቀውስ ለተጋለጡ ወገኖች የአብሮነት መልዕክት አስተላልፈዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ የልዑክ ቡድኑ በቀጣይ ህዝቡን በማስተባበር አስፈላጊ የሆኑ ሰብዓዊ እርዳታዎችን እንደሚያደርግም ቃል መግባታቸውን ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

10 Jan, 17:46


በአክሱም ከተማ በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ የታገዱ ተማሪዎችን አስመልክቶ ስብሰባ የተደረገ ቢሆንም ያለስምምነት መጠናቀቁ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 2/2017

በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ የታገዱ ተማሪዎችን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት በከተማዋ ስብሰባ መካሄዱ ተገልጿል።

ስብሰባውን የመሩት አዲስ የተሾሙት የአክሱም ከተማ ከንቲባ አቶ ትኩ እንዲሁም የአርሚ 35 አዛዥ ወድ ራያ መሆናቸው ተገልጿል።

በስብሰባው ላይ ከ500 የሚበልጡ የከተማዋ ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን ከእነዚያ ውስጥ ሙስሊሞቹ የወረዳውን እና የዞን መጅሊስ አመራሮችን ጨምሮ ከ20 እንደማይበልጡ ተገልጿል።

የስብሰባው ዋና አጀንዳ ሂጃብ እነደነበር የተገለፀ ሲሆን ሂጃብን በተመለከተ ሙስሊሙ ማህበረሰብ የሚያነሳው ጥያቄ አግባብ አይደለም መባሉ ተሰምቷል። አክሱም በፌደራልም ሆነ በክልል ሳይሆን በራሷ መመሪያ ነው የምትመራው ሲሉ የከተማዋ ከንቲባ መናገራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በዚህም ምክንያት ስብሰባው ያለ ስምምነት መበተኑ ተሰምቷል። የዛሬው ስብሳማ ዋና አላማ ችግሩን በራሳችን ፈተነዋል በሚል መግለጫ ለመስጠት የነበረ ቢሆንም በስብሰባው ላይ የተገኙት የወረዳ እና የዞን መጅሊስ አመራሮች ጥያቄዎችን ክልል ይዞታል ከክልል በሚመጣ መመሪያ መሰረት እንቀጥላለን በሚል የዛሬውን የአክሱም ከተማ ከንቲባ ሀሳብ ሳይቀበሉ መውጣታቸው ተገልጿል።

የዛሬው ስብሰባ ሙስሊሙ ማህበረሰብ አንድነቱን በተግባር ያሳየበት ነበር የተባለ ሲሆን በሰሜኑ ጦርነት አንድ ልጃቸውን ያጡ ወ/ሮ ኬሪያ የተባሉ የስብሰባው ተሳታፊ "የታገልነው ለዚህ አልነበረም የታገልነው ልጆቻችን ሀይማኖታዊ ማንነታቸው ሳይነካ በክብር ቀና ብለው እንዲሄዱ እንዲማሩ ነበር እየሆነብን ያለው ግን እጅግ አሳዛኝ እና አሳፋሪ ተግባር ነው" ሲሉ መናገራቸው ተገልጿል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሀገር አቀፍ ዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ፎርም የሚሞላበት የመጨረሻ ቀን ጥር 5/2017 ዓ.ል ቢሆንም 159 የሚሆኑ የአክሱም ሴት ሙስሊም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሂጃብ ምክንያት ፎርሙን እስካሁን  እንዳልሞሉ ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

10 Jan, 15:50


በመሀል ጎንደር የሚገኘውን የቀኝ ቤት መስጂድ (መስጂደል የሚን) ግንባታ ለማጠናቀቅ ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኅግብር እየተካሄደ እንደሚገኝ ተገለፀ!

-ሀሩን ሚድያ፣ ጥር 2/2017፤አዲስ አበባ

በመሃል ጎንደር ከተማ ከአፄ ፋሲል ቤተ- መንግስት አቅራቢያ የሚገኘውን የቀኝ ቤት መስጂድ (መስጂደል የሚን) የመስጅድና የመድረሳ ፕሮጀክት ግንባታ ለማጠናቀቅ ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኅግብር በአዲስ አበባ በተለያዩ መስጂዶች እየተካሄደ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የመስጂዱ ግንባታን ለማጠናቀቅ በአዲስ አበባ በታላቁ አንዋር መስጂድ፤በፒያሳ ኑር መስጂድ፤በቤተል ተቅዋ መስጂድ እና ሸጎሌ መስጂድ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኅግብር መካሄዳቸውን አስተባባሪ ኮሚቴው ለሀሩን ሚድያ ተናግረዋል።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ የዚህ ታሪካዊ መስጂድና መድረሳ ግንባታ እንዲጠናቀቅ ድጋፍ በማድረግ እንዲተባበር የመስጂዱ ኮሚቴዎች ጥሪ አቅርበዋል።

ለመስጂዱ ግንባታ ድጋፍ ለማድረግ፦

የአካውንት ስም
የቀኝ ቤት መስጂድ አሰሪ ኮሚቴ

ኢትዮጵያዊ ንግድ ባንክ
1000549197373

አቢሲንያ ባንክ
177943177

ሂጅራ ባንክ
1000036300001

ዘምዘም ባንክ
0038133510301

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

10 Jan, 07:46


ለመስጂድ መሄጃ መንገዱ እንዲመች ፍርድ ቤት ድረስ በመሄድ ኮብልስቶን እንዲሰራ ያደረገው ጀማል ማነው?

ጀማል አህመድ በጅማ የተወለደ በጅማ የሚኖር ወጣት ነው። ጀማልን ታታሪ ሰራተኛ ፤ ለተቸገረ ደራሽ ፤ ቤተሰቡን በላቡ ደስተኛ አድርጎ ለማኖር የሚለፋ ሰው በማለት ይገልፁታል።

ለብዙዎች ከችግር ለመውጣት እና ለብዙዎች መሻሻልም አላህ ሰበብ አድርጎታል።

ሰዎች እንዳይቸገሩ ካደረጋቸው ነገሮች ለየት ባለ መልኩ የሚገለፅለት በጅማ ወደ ራህማ መስጂድ የሚወስደውን የኮብልስቶን መንገድ እንዲሰራ ማድረጉ አንዱ ነው። ያንን ኮብልስቶንም ፍርድ ቤት ድረስ በመታገል ነበር እንዲሰራ ማስደረግ የቻለው።

ትላንት ብዙዎችን በማገዝ ፤ በመስጂድ ከጀመአዎች ጋር በመኻደም ፤ ባለቤቱን እና ልጆቹን ለመንከባከብ በመልፋት የሚታወቀው ነበር።

አንድ ቀን አዲስ የሚሰራን ቤት ጓደኛው ሊያሳየው ሄዱ። ከመስጂድ አዛን በመሰማቱ ጀማል ውዱእ አድርጎ ወደ መስጂድ ሊሄድ ሲል ጀርባው ላይ የሆነ ነገር ሲወድቅ ይሰማዋል። ለመሮጥም ሞከረ የነበረበት ቦታ ጠባብ በመሆኑ አልቻለም። አዲስ ከሚሰራው ቤት የነበረ ግንብ ነበር ላዩ ላይ የወደቀው።

ከአደጋው በኋላ ያለውን ገንዘብ በሙሉ በህክምና ቢጨርስም በቂ ህክምና እና ለበሽታው መድሀኒት እንኳን ማግኘት አልቻለም። ከስቃዩ በማስታገሻ ተንፈስ እያለ ለመኖር ቢሞክርም ስቃዩን መቋቋም ከሚችለው በላይ እየሆነበት ይገኛል። ሰውነቱም ከማስታገሻ መርፌዎች ብዛት መርፌዎቹን መቋቋም አልችል እያለ ነው።

ትላንት ብዙዎችን ያበላው እጅ ዛሬ ለተማፅኖ ተዘርግቷል!

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000670775635 ጀማል አህመድ
COOP - 1041900006097 ጀማል አህመድ
CBE - 1000571390543 ኡሚ አህመድ (ባለቤት)

ስልክ - +251913793005

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

10 Jan, 07:33


https://youtu.be/NFRDxTrcaro?si=xGX1jyQXVdipvskW

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Jan, 17:58


የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የልማት ኤጀንሲ የዋና መስሪያ ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ መርኅግብር ተካሄደ!

- ሀሩን ሚድያ ጥር 1፣ 2017 ዓ.ል

በአራት ወራት እንዲሚጠናቀቅ የተገለፀው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የልማት ኤጀንሲ ዋና መስሪያ ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ መርኅግብር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለከተማ ሪቼ አካባቢ በሚገኘው የድርጅቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ተካሂዷል።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የልማት ኤጀንሲ ዋና መስሪያ ቤት ግንባታን ያስጀመሩት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የልማት ኤጀንሲው የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና የልማት ክንፍ እንደሚሆን ገልፀው የማኀበረሰቡን ችግር ከመቅረፍ ባሸገር የምክር ቤቱ የኢኮኖሚ መሰረት ይሆናልም ብለዋል።

ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም አክለውም ግንባታው በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ የታለመለትን አገልግሎት ለመስጠት ብቁ እንድታደርጉት ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሀጅ ከማል ሀሩን በግንባታ ማስጀመሪያ ዝግጅቱ ላይ እንደተናገሩት ጠቅላይ ምክር ቤቱ እራሱን ማስተዳደርና ለህዝበ ሙስሊሙ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት አቅቶት እንደቆየ አስታውሰው በተሰሩ ተከታታይ ስራዎች ነባር ችግሮችን በመፍታት ውጤት ማስመዝገብ መጀመሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የልማት ኤጀንሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጁደዲን ሰይድ በበኩላቸው የጠቅላይ ምክር ቤቱ ድጋፍ ካልተለየን የልማት ኤጀንሲው ሃይማኖታችን በሚያዘው መሰረት እንደ ሀገር የማህበረሰቡን ችግር ለመቅረፍ በሚያስችል ሁኔታ በትጋትና በታማኝነት እንሰራለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የልማት ኤጀንሲ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አህመድ ሁሴን የልማት ኤጀንሲው ሪፎርም እውን አንዲሆን በቅርበትና በትጋት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የልማት ኤጀንሲ ዋና መስሪያ ቤት ፕሮጀክት ከዲዛይን እስከ ግንባታ ያለውን ሂደት የሚያሳይ ገለፃ በምክር ቤቱ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ባለሙያ ኢንጅነር ሰኢድ ዲልተታ አብራርተዋል።

- ሀሩን ሚድያ በዝግጅቱ በመገኘት ያጠናቀርነውን የቪድዮ ዝግጅት በአላህ ፍቃድ ወደናንተ ሚያደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Jan, 16:15


2ኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና አዛን ውድድር በኢትዮጵያ አዘጋጅ አብይ ኮሚቴ ከኦሮሚያ መጅሊስ ጋር አብሮ ለመስራት ከስምምነት መድረሳቸው ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ጥር 1/2017

ከሳምንታት በኋላ ጥር 25/2017 ዓ.ል በአዲስአበባ ስታዲየም ለማካሄድ ቀነ ቀጠሮ የተያዘለት ሁለተኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር በኢትዮጵያ ውድድሩን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወን የተለያዩ ስራዎች እየተካሄዱ እደሆነ ተገልጿል።

የውድድሩ አዘጋጅ አብይ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት ከኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት አብሮ መስራት በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ውይይት በማድረግ ከስምምነት መድረሳቸውን ገልፀዋል።

በኦሮሚያ መጅሊስ ዋና ቢሮ በተካሄደው ውይይት የኦሮሚያ መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች እና የውድድሩ አብይ ኮሚቴ አባላት ተገኝተው ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ገልፀዋል።

የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሁለተኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር በኢትዮጵያ ውድድሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጿል።

ከ24 ቀናት በኋላ በአዲስአበባ ስታዲየም የሚካሄደው ሁለተኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር በኢትዮጵያ ከ60 ሀገራት በላይ ይሳተፉበታል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ህዝበ ሙስሊም የመግቢያ ትኬት በመግዛት እንዲሁም ውድድሩን በተለያዩ መንገዶች በማገዝ የበኩሉን ድርሻ እንድወጣ ጥሪ ቀርቧል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Jan, 13:39


አቡ ሁረይራህ መስጅድ የተካሄደው ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራምHarunMedia
https://youtu.be/-xVUvNPn8uA

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Jan, 12:02


በአሜሪካ በተከሰተው የሰደድ እሳት በርካታ ህንጻዎች እና ከተሞች መጎዳታቸው ተገለፀ።

- ሀሩን ሚዲያ ጥር፣1/2017

በአሜሪካ ከተሞች በተለይም በሎስአንጀለስ ከተማ ከፍተኛ የሆነ የሰደድ እሳት የተነሳ ሲሆን በርካታ ነዋሪዎች አካባቢውን ለቀው እየወጡ ይገኛሉ።

የአሜሪካ መንግስት የሰደድ እሳቱን ለመቆጣጠር የተለያዩ ሙከራዎችን እያደረገ ቢሆንም የሰደድ እሳቱ ለመቆጣጠር ከባድ እንደሆነ ተነግሯል።

የሰደድ እሳቱ በ4 አቅጣጫ በሎስአንጀለስ የሚገኙ መኖሪያ ቤቶችን፣ ህንጻዎችን እና የተለያዩ ፋብሪካዎችን ወደ አመድነት የቀየረ ሲሆን የጉዳት መጠኑም ከ85 ቢሊየን በላይ የአሜሪካ ዶላር እንደሚገመት ተነግሯል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Jan, 08:30


ጆንጎ የልማት በጎ አድራጎት ማህበር ለበድር ኢትዮጵያ ሽልማት አበረከተ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ጥር 1/2017

በስልጤ ዞን ባሉ የተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ የሚንቀሳቀሰው ጆንጎ የልማት ማህበር መቀመጫውን አሜሪካን ሀገር ላደረገው በድር የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች አለም አቀፍ ድርጅት በዞኑ ለሚከናወኑ ስራዎች ላደረጉት አስተዋጽኦ ሽልማት አበርክቷል።

አሜሪካን ሀገር ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የሀሩን ሚዲያ ስቱዲዮ በተካሄደው የሽልማት ስነስርዓት ላይ የበድር ኢትዮጵያ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው ሽልማቱን ተቀብለዋል።

በድር ኢትዮጵያ አለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ድርጅት በተለያዩ የልማት እና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ከጆንጎ የልማትና በጎ አድራጎት ማህበር ጋር በጋራ ለመስራት ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

08 Jan, 18:12


የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የአክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች የሂጃብ ክልከላ ጉዳይ ወደህግ መውሰዱን ገለፀ!

-ሀሩን ሚዲያ፣ታህሳስ 30/2017

በአክሱም ትምህርት ቤቶች ሂጃብ የለበሱ ተማሪዎች ትምህርት ቤት እንዳይገቡ መከልከላቸው ይታወቃል።ይህ ደግሞ ከሃይማኖታዊም ከሰብዓዊ መብት አያያዝ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ አማራጮችን የሚጥስ አሰራር መሆኑን የክልሉ መጅሊስ ገልጿል።

የትግራይ ትምህርት ቢሮ ተግባራዊ የማይሆን ደብዳቤ ከመጻፍ በስተቀር ምንም አይነት ለውጥ ማምጣት አልቻለም ያለው መጅሊሱ የልጆቻችን ጥያቄ ሁሉንም ሀይማኖቶች የምታስከብር ትግራይን ማየት ነው ብሏል።

አንዳንድ ወገኖች በተለይም የትምህርት ቤቱ አስተዳደር እነዚህን ልጆች በራሳቸው ሀይማኖታዊ ፍላጎት የመማር መብታቸውን በመርገጥ ወደ ትምህርት ቤት እንዳይገቡ እያስገደዷቸው እንደሚገኙ ተገልጿል።

ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርገው ደግሞ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ክልከላው መደረጉ ነው ሲል አክሏል።

ከዚህ ቀደም ምን አይነት ህጋዊ መሠረት የሌላቸው የሂጃብ ክልከላዎች በቅርቡ መፍትሔ ካልተገኘላቸው በህግ ክስ እንደምንመሰርት በጽሁፍ አስታውቀን ያለው የክልሉ መጅሊስ እየተደረገ ያለው የሙስሊም ተማሪዎችን ብቻ ሳይሆን የሴቶችን የመማር መብት የሚጥስ ተግባር በመሆኑ ጉዳዩን ወደህግ ወስደነዋል ሲሉ የትግራይ ክልል መጅሊስ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

08 Jan, 15:53


ሂክማ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲን ለማጠናከር  በነገው ዕለት በሪያድ ከተማ ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም እንደሚካሄድ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 30/2017

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን ርዕሰ መዲና በሆነችው ወራቤ ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የሒክማ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ ግንባታ ለማገዝ በሳውዲ አረቢያ ሪያድ ከተማ በነገው ዕለት ጥር 1/2017 (ጃንዋሪ 9/2025) ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ይካሄዳል ተብሏል።

በመርኀ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ መጅሊስ አመራሮች ታላላቅ ኡለማኦች የስልጤ ዞን ተወላጆች እና ወዳጆች እንዲሁም በሪያድ እና አካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሙስሊም ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ሒክማ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ይህ ለሀገራችን የኢልም ሽግግር ጉልህ ሚና የሚያሳርፍ በመሆኑ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በመረባረብ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

08 Jan, 13:11


https://youtu.be/67sDTxMik88?si=1le-4ZvAAXIYMgYT

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Jan, 19:15


በግፍ የተገደሉት የበድር መስጅድ ኢማም ሼይኽ አብዱ ያሲን ምንም አይነት ፍትህ ሳያገኙ አንድ አመት ሆናቸው!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 29/2017

ሸይክ አብዱ ያሲን ከአንድ አመት በፊት ነበር የኢሻዕ ሰላት አሰግደው ሲመለሱ ከጀርባ በተተኮሰባቸው ጥይት የተገደሉት።

በግፍ የተገደሉት ሸይኽ አብዱ ምንም ፍትህ ሳያገኙ ገዳይም ሳይያዝ በዛሬው ዕለት ድፍን አንድ አመት ሞልቷቸዋል።

በወቅቱ ተጠርጣሪውን አፋልጉኝ በሚል በማህበራዊ ሚዲያ ጥሪ አቅርቦ የነበረው የአዲስ አበባ ፖሊስ ከዛ በኋላ ስለጉዳዩ ያለው ነገር አለመኖሩ ተገልጿል።

በተጨማሪም የእሳቸውን ጉዳይ  ለማስፈፀም ሀላፊነት የወሰዱ አካላት አስካሁን ያሉት ነገር አለመኖሩን የአካባቢው ሰዎች ገልጸዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Jan, 18:32


አዲስ አበባ በሚገኘው የአል ሒዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚካሄዴው የጉብኝትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም እንደቀጠለ መሆኑ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 29/2017

"የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ሳምንት" በሚል መሪ ሀሳብ ካሳለፍነው ቅዳሜ ታህሳስ 26 ጀምሮ እስከ መጭው ቅዳሜ ጥር 3/2017 አዲስ አበባ አለም ባንክ ኢማሙ አህመድ መስጅድ ጀርባ የሚገኘውን የዩኒቨርስቲው ፕሮጀክት ቢሮ በመጎብኘት ስለፕሮጀክቱ፣ ስለ አልሂዳያ ታሪክ እና አጠቃላይ እቅድ በአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ አመራሮች ገለፃ እየተደረገ ይገኛል።

የጉብኝቱ አላማ ስለፕሮጀክቱ ግንዛቤ መፍጠር እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ስለ አልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሮጀክት ለመወያየት መሆኑ የተገለ ሲሆን በዛሬው ዕለትም የተለያዩ ወንድሞች በዩኒቪርስቲው ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።

በተጨማሪም ስለ አል ሒዳያ ዩኒቨርስቲ የማህበረሰቡን ግንዛቤ ለማስፋት ጁመአ እና እሁድ በተለያዩ መስጅዶች የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃግብር እንደሚካሄድ ተገልጿል።

የዚሁ አካል የሆነ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም አለም ባንክ በሚገኘው ኢማም አህመድ መስጅድ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፈው የአል ሒዳያ ዩኒቨርስቲ የቦርድ አባል ኡስታዝ አዩብ ደርባቸው አል ሒዲያ ዩኒቨርስቲ የሚገነባው በጉራጌ ዞን ቢሆንም ጥቅሙ ግን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሙስሊም አልፎም ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ የእውቀት ምንጭ የሚሆን በመሆኑ ሁሉም ወገን ተረባርቦ ግንባታው እውን በማድረግ አሻራውን እንዲያሳርፍ ጥሪ አቅርቧል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Jan, 17:27


ሙስሊሙ ወደመሪነት መምጣት አለበት''
|ኡስታዝ ሀይደር ኸድር Harunmedia
https://youtu.be/IuD7JYMJPAY?si=oaKU00y6RxeQV36r

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Jan, 14:40


"ሪፖርት የተሰራዉን ሥራ ለመከታተልና ለመገምገም እንድንችል ይረዳናል"

-የኮልፌ ክፍለከተማ መጅሊስ ምክትል ስራ አስፈፃሚ ኡስታዝ አህመድ አልይ

ሀሩን ሚድያ ታህሳስ 29/2017፤አዲስ አበባ

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የክፍለከተማውን፤የአስራ አንዱም ወረዳ መጅሊሶች፤ እንዲሁም የክፍለከተማው የሙስሊም ወጣቶችና የሴት ሊግ የግማሽ ዓመት የስራ አፈፃፀምና የፋይናንስ ሪፖርት አቅርበዋል።

በሪፖርቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምክትል ስራ አስፈፃሚ ኡስታዝ አህመድ አልይ እንደገለፁት የሥራ አፈፃፀምና የፋይናንስ ሪፖርት ማቅረብ የዕቅድ አንዱ አካል መሆኑን በማንሳት ሪፖርት ቀደም ሲል ያስቀመጥነዉ ዕቅድ ምን ያህል ግቡን እንደመታ ከምንመዝንባቸዉ መንገዶች አንዱና ዋነኛ ሥልት መሆኑን ተናግረዋል።

ሪፖርት የተሰራዉን ሥራ ለመከታተልና ለመገምገም እንድንችል ይረዳናል ያሉ ሲሆን ሪፖርት-አንድ ተቋም በጀትን፣ ጊዜን፣ የሰዉ ኃይልን፣ ዕዉቀትን፣ ልምድንና ተሞክረሮን እንዲሁም ቁሳቁስንና ቴክኖሎጂን ምን ያህል እንደተጠቀመ በግልጽ እንደሚያሳይም አክለዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የክፍለከተማው መጅሊስን ጨምሮ አስራ አንድ ወረዳዎች፤የክፍለከተማው ሙስሊም ወጣት ሊግ እና ሴቶች ሊግ የግማሽ ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርታቸውን አቅርበዋል።

ዑስታዝ አብዱረሂም ነስረዲን የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ-ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ፀኃፊ በበኩላቸው በክፍለከተማው የዑለማዎችን የዳሰሳ ጥናት ከማቅረብ ጀምሮ፤ የመስጂድ ዝያራዎችን በማድረግ የአቅመ ደካማ ቤቶችን በማደስ እንዲሁም ሌሎች ዘረፈ ብዙ ተግባራትን መከናወናቸውን ተናግረዋል።

ለቀሪ ስድስት ወራትም የክፍለ ከተማውና የወረዳው መጅሊስ ሥራ አስፈፃሚዎች እንዲሁም የወጣቶችና የሴቶች ሊግ አመራሮች ክፍተቶችን በመሙላትና ድክመቶችን በማጠናከር የላቀ የሥራ ክንውን ማስመዝገብ እንደሚገባ የኮልፌ ክፍለ ከተማ መጅሊስ ምክትል ስራ አስፈፃሚው ኡስታዝ አህመድ አልይ መልዕክት አስተላልፈዋል።

©ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Jan, 14:06


የእስራኤል መንግስትን በማስገደድ የታገቱ ዜጎችን በፍጥነት እንዲያሰለቅቅ የሚጠይቅ ኮንፈረንስ እያዘጋጁ መሆኑን የታጋች ቤተሰቦች ተናገሩ።

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 29/2017

በእስራኤል የታጋች ቤተሰቦች የቢኒያሚን ኔታንያሁን መንግስት በማስገደድ ታጋቾችን እንዲያስለቅቅ የሚጠይቅ ኮንፈረንስ እያዘጋጁ መሆኑን የታጋች ቤተሰቦች ተናግረዋል።

የእስራኤል እስረኛ ቤተሰቦች ማህበር ልጆቻቸውን ለማስፈታት የቢኒያሚን ኔታንያሁ መንግሥት በፍጥነት ወደ ድርድር እንዲመለስ የሚያደርግ ኮንፈረንስ እያዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል።

በእስራኤል የእስረኛ ቤተሰቦች በእስራኤል መንግስት ላይ ተደጋጋሚ ተቃውሞዎችን የሚያሰሙ ሲሆን በጠቅላይ ሚኒስቴር ቢኒያሚን ኔታንያሁ መኖሪያ ቤት አካባቢም ጭምር በመገኘት የእስራኤል መንግስት ተደራድሮ እስረኞች እንዲያስለቅቅ ተቃውሟቸውን እንደሚያሰሙ ይታወሳል።

በተለይም የፍልስጤሙ ሀማስ ከሰሞኑ ሀይሉን እያደራጀ ሮኬቶችን እና ሚሳኤሎችን ጭምር ወደ እስራኤል ግዛት መተኮስ መጀመሩ እስራኤል በሀይል ታጋቾችን የማስለቀቋ ጉዳይ አዋጭ እንደማይሆን ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።

▣ መረጃው የአልጀዚራ ነው

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Jan, 12:02


የታሪክ ባለሙያ ለሆኑት ሸይኽ አደም ካሚል (ረ/ፕሮፌሰር) ለማኅበረሰብ ላበረከቱት አስተዋጽኦ የመኪና ሥጦታ ተበረከተላቸው!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 29/2017

ረጅሙን የእድሜያቸውን ክፍል በታሪክ አጥኚነት ላሳለፉት ሼይኽ አደም ካሚል (ረ/ፕሮፌሰር) በዛሬው እለት በየሲር ለና የበጎ አድራጎት ድርጅት በተካሄደው መርሐ ግብር ላይ ለታሪክ አጥኚው ሥጦታ የተበረከተው ለማኅበረሰብ ላበረከቱት አስተዋጽኦ መሆኑ ተገልጿል፡፡ሥጦታውን ያበረከቱት አካላት ሥማቸው አልተገለጸም ተብሏል፡፡

በሰሜን ወሎ ዞን ገፍራ ወርሳ ሜንሳ ተብሎ በሚጠራ ቦታ በ1948 ገደማ የተወለዱት ሼንህ አደም ካሚል (ረ/ፕሮፌሰር)፤ በአሁኑ ሰዓት ዕድሜያቸው 69 ደርሷል፡፡

ሼይኽ አደም ካሚል በኢትዮጵያ ከቀሰሙት የእስልምና ትምሕርት በኋላ የከፍተኛ ትምሕርታቸውን በቀዳሚነት የተከታተሉት በሳዑዲ ዐረቢያ ኪንግ ሮያል ዩኒቨርሲቲ ነው።

ሼይኽ አደም ካሚል በኢትዮጵያ ሙስሊሞ ሰላማዊ የመብት ትግል ውስጥ ጉልፍ ሥፍራ በሚሰጠው የ“ድምጻችን ይሰማ” እንቅስቃሴ ውስጥ በሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ውስጥ ከነበሩ 17 ግለሰቦች ውስጥ አንደኛው አባል ነበሩ፡፡ ከመጻሕፍት ዝግጅት፣ ከጥናታዊ ጽሑፎች፣ ከአደባባይ ንግግሮች ውጪ የመጽሔት አዘጋጅ ሆነው ሠርተዋል፡፡

ባለፉት በርካታ ዐስርት ዓመታት በተለይ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን የተመለከቱ ጉዳዮችን የሚዳስሱ መጻሕፍትን ማበርከትም ችለዋል፡፡ ለኅትመት ከበቁት መካከል “ኢትዮጵያ መካከለኛው ምሥራቅ እና ነጃሺ”፣ “እስልምና እና ዓለማችን”፣ “ሀበሾች እና የሀበሻ ክብር በእስልምና”፣ “ሀበሾች በነቢዩ (ሰ.ዓ.ወ) ዙርያ”፣ የሀበሾች አሻራ በእስልምና እንዲሁም ቱሪዝም እና ኢንቨስትመንትን የተመለከቱት ተጠቃሽ ናቸው፡፡

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Jan, 19:38


የአክሱም ከተማ ትምህርት ቢሮ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሀይማኖት፣ የእምነትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየፈፀመ መሆኑን የአፋር ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ገለፀ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 28/2017

በአክሱም ሙስሊም ተማሪዎችና ማህበረሰብ ላይ እየደረሰ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥስት በተመለከተ ከአፋር ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት መግለጫ ሰጥቷል።

ከፍተኛ ምክር ቤቱ በመግለጫው ሀገራችን ከነጃሺ ዘመን ጀምሮ ብዝሀ ሀይማኖትና ብዝሀ ብሄሮች በአንድ ላይ ተሰባስበዉ ተከባብረዉ የሚኖሩባት የጋራ ቤታችን መሆኗ ሁላችንም የሚያኮራ እና በባለቤትነት ስሜት የምንኖረዉ ጸጋችን ነዉ ብሏል፡፡

በትግራይ ክልላዊ መስተዳደር የአክሱም ከተማ ትምህርት ቢሮ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሙስሊም ሴት ተማሪዎችን የእምነት አለባበስ (ሂጃብ) አስመልክቶ ትምህርታቸውን በሚጐዳ መልኩ ከአንድ ወር ባላነሰ ጊዜ ከትምህርት ገበታቸው እንዲስተጓጐሉ በማድረግ ተማሪዎች ላይ የሀይማኖት፣ የእምነትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጽሟል ሲል የአፋር ክልል መጅሊስ ገልጿል፡፡

ይህ ተግባር ለዘመናት የዘለቀ የህዝባችን አብሮነትና ተቻችሎ የመኖር መልካም ባህላችን የሚያደፈርስና በህዝባችን መካከል መቃቃር የሚፈጥር ተግባር በመሆኑ የተስተዋለዉ የእምነትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት በፅኑ እንቃወማለን ብሏል። የሙስሊም ማህበረሰብ ሀይማኖታዊ መብቶቻቸው በነፃነት እንዲተገብሩ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ተገቢዉን ትኩረት እንዲሰጡ ጠይቋል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Jan, 17:18


ሙስሊም ሴቶች ሂጃባቸውን እንደለበሱ ይማራሉ!HarunMedia
https://youtu.be/13HQWxdbR-Y?si=_HRfSWnOqizePA_A

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Jan, 13:06


የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአክሱም በሙስሊም ተማሪዎች  ላይ እየደረሰ ያለውን በደል አስመልክቶ ምን እርምጃ ወሰደ?

ከጠቅላይ ምክር ቤቱስ በቀጣይ ምን ይጠበቃል?

▣ሀሩን ሚድያ እነዚህንና ሌሎች ጉዳዮችን አስመልክቶ ከኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ቆይታ አድርገናል ዛሬ ምሽት 1:05 ይጠብቁን።

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Jan, 08:06


የአክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች በሒጃባቸው ምክንያት እየደረሰባቸው ያለውን ጫና አስመልክቶ ለአክሱም ከተማ እስልምና ጉዳዮች የቅሬታ ደብዳቤ አስገብተው እንደነበር ተገለፀ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 27/2017

በደብዳቤው ላይ እንደተገለፀው 64 የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ እና ወርዒ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርትቤት ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሕዳር ወር በየትምህርት ቤቶቻቸው በሒጃባቸው ምክንያት እየደረሰባቸው ባለው ጫና ትምህርታቸውን በአግባቡ እየተማሩ እንዳልሆነ ለአክሱም ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ቅሬታ ማቅረባቸው ሀሩን ሚድያ የደረሰው መረጃ ያመላክታል።

የአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በየትምህርት ቤቶቻችን ሒጃቦቻችንን እንድናወልቅ ከባድ ጫና እየደረሰብን ነው ያሉ ሲሆን እኛ ሙስሊም ሴቶች ሒጃባችንን አውልቀን (ፀጉራችንን ሳንሸፈን) ሸሪዓው (ሃይማኖታችን) አይፈቅድልንም ሲሉ ገልጸዋል። በመሆኑም እውቀት ከምንቀስምበት ትምህርት ቤት ሒጃባችሁን ጣሉ ወይም መማር አትችሉም በሚል እየደረሰብን ባለው ጫና እና ዛቻ ትምህርታችንን መከታተል አልቻልንም ሲሉ ለከተማው መጅሊስ አስታውቀዋል።

በሒጃባችንን ምክንያት እየደረሰብን ያለው ችግር በአስቸኳይ እና ባፋጣኝ ከሚመለከታቸው አካላት ተነጋግራችሁ መፍትሔ ስጡን ሲሉ ለአክሱም ከተማ መጅሊስ ጥያቄ አቅርበዋል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

05 Jan, 19:22


የቂርቆስ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ለወረዳ መጅሊስ ኃላፊዎች፣ ለወጣት እና ለሴት ሊግ አመራሮች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠቱ ተገለፀ!

ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 27/2017

የስልጠና መድረክ በንግግር የከፈቱት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ስራ አስፈጻሚ ወንድም ሙከሚል አሕመድ በስልጠናው ለስራ የሚጠቅሙ ግንዛቤዎችን ከማሳደግ በዘለለ አንድነታችንን ያጠነክራል ብለዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ሙከሚል አሕመድ የክፍለ ከተማው መጅሊስ ባለፉት ሁለት ዓመታት የተጓዘበትን ዋና ዋና ሂደቶች አብራርተዋል።

የክፍለ ከተማው መጅሊስ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በማዋቀር ተደራሽ ለመሆን እየተንቀሳቀሰ መቆየቱን የገለፁት ዋና ስራ አስፈጻሚው የመደበኛ ግንኙነት ክፍተት ባለፈው የስራ ጊዜ የገጠመ ችግር መሆኑን ተናግረዋል። ይህንን ችግር በቀጣይ ለማረም መዋቅራችንን እንጠቀማለን ያሉ ሲሆን የዛሬው ዓይነት ስልጠናም አስፈላጊና አጋዥ መሆኑን በመልዕክታቸው ላይ አስፍረዋል።

ችግሮችን መለየት፣ መረዳትና መፍትሔ የመስጠት አቅምን ለማጎልበት፤ በአመራርነት ወቅት ከባቢን መረዳትና ሌሎች ጉዳዮችን የተመለከቱ የግንዛቤ መፍጠሪያ ርዕሶች በአሰልጣኙ ኡስታዝ አሕመድ ሙስጠፋ ቀርበው በተግባር በታገዘ መልኩ ግንዛቤ መፈጠሩም ተገልጿል።

ስልጠናው በተግባራዊ ጥያቄና መልስ፤ በቡድን ውይይት እና የቡድኖችን የጋራ ሐሳብ ለሌላው በማጋራት የተደገፈና ሰፊ የልምድ ልውውጥ እንዲሁም የንድፈ ሀሳብ ማብራሪያ እንደነበረውም ተነስቷል።

በቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ በተካሄደው በዛሬው ስልጠና ላይ ከሁሉም ወረዳዎች የተውጣጡ የመጅሊስ አመራሮች፤ የወጣት ሊግ አደረጃጀት አመራሮችና የሴት ሊግ አመራሮች መሳተፋቸውን ከአዲስ አበባ መጅሊስ ህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

05 Jan, 16:21


"አክሱም ላይ የተከለከለው ሂጃብ ብቻ አይደለም እስልምናም ጭምር ነው"

▣ በፌደራል መጅሊስ የትግራይ ክልል ተወካይ እንዲሁም የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ኢንጅነር አንዋር ሙስጠፋ ለሀሩን ሚድያ ከገለፁት

- ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 27/2017

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ኢንጅነር አንዋር ሙስጠፋ እንዳሉት ሂጃብ እና እስልምና የማይነጣጠሉ መሆናቸውን አንስተው በአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ይህን ያደረጉት አካላት የእስልምና ጥላቻ ያለባቸው መሆኑን ለሀሩን ሚድያ ተናግረዋል።

በአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ መገለላቸውን አስመልክቶ ፌደራል መጅሊሱ ምን እየሰራ ነው ብለን ለጠየቅናቸው ጥያቄም ከትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጋር በጋራ በመሆን ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ እየሰራን ነው ብለዋል።

ሙስሊም ተማሪዎች ላይ በየጊዜው የሚፈፀሙ የመብት ጥሰቶችን ለማስቆም የጠቅላይ ምክር ቤቱ የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል።

- ሀሩን ሚድያ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ከሆኑት ከኢንጅነር አንዋር ሙስጠፋ ጋር ያደረግነውን ቆይታ በቀጣይ ወደ እናንተ ምናደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Jan, 18:58


- የፕሮግራም ጥቆማ

ነገ እሁድ ታህሳስ 27 በአዲስ አበባ ቦሌ ወሎ ሰፈር አካባቢ በሚገኘው አቡ ሁረይራህ መስጅድ ከተማ አቀፍ የዳዕዋ ፕሮግራም በአ/አ/ከ/ እስልምና ጉዳዮች ሙስሊም ወጣቶች ሊግ አማካኝነት ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ተዘጋጅቷል።

በፕሮግራሙ፦

①) ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ዘህረዲን: «አርአያችን ማን ነው?» በሚል ርዕስ፣

②) ሸይኽ ኢልያስ አሕመድ: «ወጣትነት እና ጊዜ አጠቃቀም» በሚል ርዕስ፣

③) ኡስታዝ ሐይደር ኸድር፦ «(የወጣቶች መሪ) ተቋምን ማጠናከር» በሚል ርዕስ ዳዕዋ ያደርጋሉና ሁላችሁም ትሳተፉ ዘንድ የሙስሊም ወጣቶች ሊግ ጥሪ አቅርቧል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Jan, 18:11


ለሀሩን ሚዲያ እና ሀሚልተን ቲቪ አባላት በሳጃ ከተማ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 26/2017

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በየም ዞን ርዕሰ ከተማ በሆነችው ሳጃ ከተማ በነገው ዕለት እሁድ ደማቅ የዳዕዋ ዝግጅት ይካሄዳል።

ዝግጅቱን ለመዘገብ ወደቦታው ያቀኑት የሀሩን ሚዲያ እና ሀሚልተን ቲቪ አባላት አመሻሹን ቦታው ላይ ሲደርሱ በርካታ የከተማዋ ሙስሊም ማህበረሰብ ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል።

በአቀባበል ዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረገው የሀሩን ሚዲያ ጋዜጠኛ ከማል ኑርዬ "ሀሩን ሚዲያ ለሁሉም ሙስሊም ማህበረሰብ እንደሚያደርገው የየም ሙስሊም ማህበረሰብ ሚዲያ በሚያስፈልገው ሰአት ሁሉ ከጎናችሁ አለን" ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።

የሀሚልቲን ቲቪ ማናጀር የሆኑት ሀጂ ሙሳ በበኩላቸው ስለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው ሰደቃን በተመለከተ ዳዕዋ አድርገዋል።

በነገው ዕለት በሚካሄደው ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ላይ ታላቁን አሊም ዶ/ር ጀይላን ኸድር ጨምሮ የፌዴራል እና የክልል መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች እና ታላላቅ ኡስታዞች ይገኛሉ ተብሏል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Jan, 17:13


"ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ሕጋዊ መፍትኄ እንዲያገኙ የሚመለከታቸውን አካላት በሮች እያንኳኳን ነው"

- የፌደራል መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ

ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 26/2017

የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ እንደገለፁት "ሴት ልጆቻችን ዲናቸውን እንደጠበቁ ይማራሉ፤ ሕግና ሕግን መሠረት አድርገን ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ሕጋዊ መፍትኄ እንዲያገኙ የሚመለከታቸውን አካላት በሮች እያንኳኳን ነው" ብለዋል።

ፕሬዚደንቱ ይህን የተናገሩት፣ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የትምህርትና ማኀበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት "የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትምህርት ተሳትፎ" በሚል ርዕስ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ነው።

ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር በኢትዮጵያ ከትምህርት አጀማመር ታሪክ አንስቶ ሙስሊሞች መዋቅራዊ በኾነ መልኩ ከትምህርቱ ዓለም የተገለሉ እንደነበረ አስታውሰዋል።

ፕሬዚደንቱ አያይዘውም መስሊሞች የሁሉም ነገር መነሻ እውቀት መሆኑን ሳይዘነጉ፣ ያገኙትን ዕድል ተጠቅመው በቁጭት ልጆቻቸውን ሊያስተምሩ ይገባል" ብለዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ኢንጂነር አንዋር ሙስጠፋ፣ ትምህርት ማኅበረሰባዊም ሆነ ሀገራዊ ፈይዳው የላቀ እንደኾነ ጠቅሰው፣ ዳይሬክቶሬቱ የትምህርት ዘርፍ መመሪያ አጸድቆ እየሠራ መሆኑን እና የዛሬው የምክክር መድረክ የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል።
የትምህርት ምንነት እና ትምህርት ለሀገር ዕድገት ያለው ፋይዳ" በሚል ርዕስ ጽሑፍ ያቀረቡት አቶ ባህሩ ሽኩር፣ 'የትምህርት ምንነትን'፣ 'የትምህርት ታሪካዊ እድገት'ን፣ 'የትምህርት አይነቶች'ን እና 'ትምህርት ያለውን ፋይዳ' በጽሑፋቸው ዳስሰዋል።

በትምህርት ዙሪያ የረጅም ጊዜ ተሳትፎ ያላቸውና በእስላማዊ የምርምር ማዕከል የቦርድ አባል የሆኑት ኢንጅነር ቢንመሊክ አብዶ "ትምህርት በእስልምና ዕይታ" በሚል ርዕስ ትምህርትና ዕወቀት በእስልምና ያለውን ቦታ የተመለከተ ጽንሰ ሐሳባዊ ማብራሪያ አቅርበዋል።

የመድረኩ አወያይ ወይዘሮ ዘቢባ መልኪ የፓናል ውይይት ተሳታፊዎች በቡድን ተከፍለው በቀረቡላቸው ጥያቄዎች ላይ ተወያይተው ለቀጣዩ ቀን ሪፖርት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

መድረኩ ነገ እሑድ ሕዳር 27/2017 በሀገራችን የሕዝበ ሙስሊሙ የትምህርት ተሳትፎ በምን ደረጃ ላይ ነው? በሚለው እና መሰል የመወያያ ሪፖርቶችን በመስማት እንደሚቀጥል ተነግሯል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Jan, 14:38


የዜጎች የእምነት ነጻነት እና የመማር መብት ይከበር!!

የአክሱም ከተማ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው እንዳይማሩ የጣሉትን ክልከላ አስመልክቶ ከነእፓ የተሰጠ መግለጫ!!

በአክሱም ከተማ የሚገኙ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው ወደ ትምህርት ቤት እንዳይገቡ የጣሉት ክልከላ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በሀገራችን ትልቅ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል። ትምህርት ቤቶቹ በወሰዱት እርምጃ ምክንያት በርካታ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ከትምህርት ቤት መባረራቸው ታውቋል። ተማሪዎቹ ከትምህርት ገበታቸው መባረራቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች፣ በተለይም በአመቱ ለብሄራዊ ፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎች የፈተና ዝግጅታቸው እንዲስተጓጎል አድርጓል።

ችግሩን ለመፍታት የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን ጨምሮ በክልሉ የሚገኙ የኃይማኖት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህበራት፣ ታዋቂ ግለሰቦች ወዘተ  የተለያየ ሙከራ ቢያደርጉም፣ ትምህርት ቤቶቹ ባሳዩት ኃላፊነት የጎደለው እምቢተኝነት ችግሩ ሊፈታ አልቻለም። ነእፓ ትግራይ ክልል ቅርንጫፍን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎችም ውሳኔውን በጽኑ አውግዘዋል።

የትምህርት ቤቶቹ የሂጃብ ክልከላ ውሳኔ ዜጎችን ከማሳዘን እና ከማስቆጣት ባሻገር፣ በክልሉም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ በበርካታ የመብት ተሟጋቾች ከፍተኛ ውግዘትን አስተናግዷል። ትምህርት ቤቶቹ በሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ የጣሉት የሂጃብ ክልከላ   የትግራይ ክልል ህዝብ እና መንግስት በክልሉ ውስጥ ለሁለት አመት የተካሄደው አስከፊ ጦርነት ካደረሰባቸው ከፍተኛ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና የስነ ልቦና ጉዳት ለማገገም ጥረት እያደረጉ ባሉበት ወቅቱ መሆኑ ይበልጥ አሳዛኝ አድርጎታል። 

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ትምህርት የአንድን ሀገር ሁለተናዊ እድገት የሚወስን መሰረታዊ ጉዳይ ነው ብሎ የሚያምን ሲሆን፣ የክልል እና የፌዴራል መንግስት አካላት ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች ለማዳረስ ከየትኛውም ዘርፍ በበለጠ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል የሚል ጽኑ እምነት አለው። የሀገራችንን የትምህርት ሽፋን ለማሳደግ የመንግስት ተቋማት ዜጎችን ወደ ትምህርት ሊስቡ የሚችሉ ሁሉንም አይነት ማበረታቻዎች ማድረግ የሚጠበቅባቸው ሲሆን፣ በተቃራኒው ዜጎችን ከትምህርት ገበታቸው ሊያርቁ የሚችሉ ማናቸውንም አሉታዊ ተግባራት ከመፈጸም የመቆጠብ ህጋዊ፣ ሞራላዊ እና ፖለቲካዊ ግዴታ አለባቸው። 

ከዚህ መሰረታዊ እምነት በመነሳት፣ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በአክሱም ከተማ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች በሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ የጣሉትን የሂጃብ ክልከላ በጽኑ ያወግዛል። ነእፓ ትምህርት ቤቶቹ በሴት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ያደረጉት ክልከላ፣ በሴኩላሪዝም ስም የክልሉንም ሆነ የሀገሪቱን ህጎች የሚጻረር፣ የዜጎችን የእምነት ነጻነት እና እኩልነት የሚቃረን፣ የዜጎችን የመማር መብት የሚሸራርፍ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው ብሎ ያምናል። በመሆኑም፣

1. ትምህርት ቤቶቹ በተማሪዎች ላይ ያደረጉትን የሂጃብ ክልከላ በአስቸኳይ እንዲያነሱ እና ተማሪዎች ትምህርታቸውን በነጻነት እና በተረጋጋ መንፈስ እንዲከታተሉ እንዲያደርጉ፤ ትምህርት ቤቶቹ የዜጎችን የእምነት ነጻነት እና እኩልነት እንዲያከብሩ፣

2. የሚመለከታቸው የክልሉ የትምህር ተቋማት ትምህርት ቤቶቹ በተማሪዎች ላያ ያደረሱት ጉዳት የሀገራችንን የትምህርት ህጎች የሚጻረር፣ የክልሉን ህጻናት የመማር መብት የሚጋፋ እና በአጠቃላይ የክልሉ የትምህርት ዘርፍ እና የመማር ማስተማር ሂደትን የሚያውክ በመሆኑ፣ ክልከላው በአስቸኳይ ተነስቶ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ አስፈላጊውን እንዲያደርጉ፣   

3. የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሂጃብ ክልከላ የፈጸሙ ትምህርት ቤቶች፣ ከአስከፊ የእርስ በእርስ ጦርነት ለማገገም ጥረት በማድረግ ላይ በሚገኘው የትግራይ ክልል ሰላም እና መረጋገት ላይ ሊያደርስ የሚችለውን አሉታዊ ጉዳት ከግምት ውስጥ በማስገባት የሚጠበቅበትን ሁሉ እንዲያደርግ፣

4. በተለያየ ጊዜ እና ቦታ አንዳንድ የትምህር ቤት አመራሮች ሴኩላሪዝምን በተሳሳተ መንገድ በመተርጎም ከሀገሪቱ የትምህርት ፖሊሲ ባፈነገጠ ሁኔታ፣ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ መከልከል ባለፉት አመታት በሀገራችን ተከስቷል። ይህን ችግር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት ለመስጠት የፌዴራል ትምህርት ሚኒስቴር ግልጽ እና የማያሻማ መመሪያ ለክልል መንግስታት እና ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲያስተላልፍ ነእፓ በአጽንኦት ይጠይቃል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ታህሳት  26፣ 2017
አዲስ አበባ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Jan, 13:40


ባቡል ኸይር የበጎ አድርጎት ድርጅት «አምስት አመታትን በሰብአዊነት» በሚል መሪ ቃል አምስተኛ አመቱን አስቦ ሊውል መሆኑን ገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 25/2017

ባለፉት አምስት ዓመታት ማህበራዊ ሀላፊነቱን ለመወጣት በተለይም ዜጎች ቢያንስ በቀን ሁለት ጊዜ ጤናማ የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡ ለማስቻል በቀን ሁለት ጊዜ የተዘጋጀ ምሳ እና እራት እንደ ቤተሰባቸው ብዛት እየመገበ ዛሬ ላይ ከ5000 በላይ የሚሆኑ ቤተሰቦችን የምግብ ዋስትና እና የጤና መድህናቸውን ማረጋገጥ መቻሉን ድርጅቱ አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪም ባቡል ኸይር በአበበ ቢቂላ የመመገቢያ ማዕከልና የሙያ ስልጠና ማሳያ ስፍራ ጨምሮ ፣ በአቃቂ ቃሊቲ የስልጠና ማዕከል እና የህፃናት ማቋያ፣ በኦሎንኮሚ ለወጣቶች የስራ እድልን እየፈጠረ የሚገኝ የብሎሌት ማምረቻ፣ በቤተል አለም ባንክ (አሁን የምንገኝበት ቦታ) የባቡል ኸይር የምገባና የአረጋዊያን መጠለያ ሁለገብ ማዕከል ፕሮጀክት ዋና መስሪያ ቤት ለመገንባት የከርሰ ምድር የንጹህ መጠጥ ውሃ በራስ ሙሉ ወጪ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ አስመርቀናል።

የመብራት ዝርጋታም በተመሳሳይ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ ለፕሮጀክቱ ግንባታ አቅም እንዲሆን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

የፊታችን ጥር 4 ቀን 20፞17 ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ «አምስት አመታትን በሰብአዊነት» በሚል መሪ ቃል የደረጅቱን አምስተኛ አመት አስቦ ለማዋል ቅድመ ዝግጅቱን መጨረሱ ተገልጿል።

በመሆኑም በዕለቱ ከቤተል ወደ አለም ባንክ በሚወስደው መንገድ ባቡል ኸይር የምገባና የአረጓዊያን መጠለያ ማዕከል እንዲገኙና በእለቱ በሚኖረው ዝግጅት ላይ ከባቡል ኸይር ቤተሰብና ከአረጋዊያን ጋር አብረን እንድናሳልፍ ሲል ድርጅቱ ጥሪ አቅርቧል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Jan, 11:40


ከሀጥያቶቻችን መመለስ ባለመቻላችን የተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች እየተከሰቱ ነው ሲል የኢትዮጵያ ኡለሞች ጉባኤ አስታወቀ።

▣ የኢትዮጵያ ኡለማ ጉባኤ ጽህፈት ቤት በመላው ሀገሪቱ ቁኑት እና ዱአ እንዲደረግ መልእክቱን አስተላልፏል።

- ሀሩን ሚዲያ ታህሳስ 26/2017

የኢትዮጵያ ኡለሞች ጉባኤ ጽህፈት ቤት ከሰሞኑ በሀገራችን በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለውን የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት አስመልክቶ ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ መልእክት አስተላልፏል። የመልዕክቱ ሙሉ ቃል ከዚህ በታች እንደሚከተለው ቀርቧል፦

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዩች ኡለማ ምክርቤት ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ የተላለፈ መልእክት።፦

አላሁ (ሱ.ወ) በተከበረው በቁርኣን በ17ኛው ምዕራፍ በ59ኛው አንቀጽ እንዲህ ይላል›

"ተዓምራትንም ለማስፈራራት እንጂ አንልክም"

እንደሚታወቀው ሃገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ሰው ሰራሽና በተፈጥሮ ችግሮች ምክንቶች እየታመሰች ትገኛለች። ለዚህም ዋና ምክንያቱ የሰው ልጆች የርስበርስ ፍቅር መጥፋት፤ ጥላቻ መስፋፋት፤ የእርስ በርስ መገዳደል መበራከትና የሰው ልጅ ነብስ ከምን ጊዜውም በላይ ርካሽ የሆነበትና በቀላሉ ሀይወት እየተቀጠፈ የሚገኝበት ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከጥፋቶቻችንና ከስህተቶቻችን ለመመለስ ባለመቻላችን ምክንያት የተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች በመከሰት ላይ ይገኛሉ፡፡ ለአብነት ያህልም ባለፈው ክረምት በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማ፣ እንዲሁም በአማራ ክልሎች በተከሰተው የመሬት መንሸራተት በርካታ ሰዎች መሞታቸውና ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ደግሞ የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ በሃገራችን እየተከስተ ይገኛል:: ይህ ሁሉ ክስተት እኛ የሰው ልጆች በምንሰራቸው ወንጀሎች ሳቢያ የሚመጡ ክስተቶች በመሆናችው አላህ ይታረቀን ዘንድ ከስህተታችን በመታቀብ ወደርሱ በመጸጸትና ተውበት በመግባት መመለስና እርሱን መማጸን ይኖርብናል ፡፡

ለዚህም ሲባል ከፊታችን እሁድ ታህሳስ 27/2017 ጀምሮ እስከ ጥር 2/2017 ድረስ የሚቆይ ልዩ የሆነ ወደ አላህ የመመለስና መልካም ስራዎች እየስሩ ለሃገር ሰላምና ደህንነት ዱዓ የማድረግ ቀን ተግባራዊ እንዲደረግ የኡለማ ጉባዔ ጽ/ቤት ለመላው ህዝበ-ሙስሊም የሚከተሉትን መልእክቶች ያስተላልፋል፡፡

በዚሁ መሰረት

1. ህዝበ-ሙስሊሙ በአጠቃላይ ተውበት በማድረግ ወደ አላህ እንዲመለስ !

2. ሁላችንም እርስ በርስ ይቅርታ እንድንባባል፣

3. ለተቸገሩትና ረዳት ለሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሶደቃ (ምጽዋት) መስጠት፣

4. በሃገሪቱ ውስጥ በሚገኙ አጠቃላይ መስጂዶች በየአምስት አውቃት ሶላቶች ላይ ቁኑት እንዲደረግ፣

5. የቀጣዩ ጁሙኣ ቀን በሁሉም መስጂዶች የሚደረጉ ኹጥባዎች በዚህ ዙሪያ እንዲሆኑና አጠቃላይ ዱዓ እንዲደረግ በአላህ ሱብሃነሁ ወተኣላ ስም እናሳስባለን፡፡

ሲል የኢትዮጵያ ዑለማእ ጉባኤ ጽ/ቤት ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ መልእክቱን አስተላልፏል።


© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Jan, 10:22


የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትምህርት ተሳትፎን አስመልክቶ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል!

- ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 26/2017

በኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አዘጋጅነት የኢትዮጲያ ሙስሊሞች የትምህርት ተሳትፎን የሚያስቃኝ ለሁለት ቀናት የሚቆይ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።

ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በትምህርት ተሳትፎ ላይ ያላቸው ሚናን አስመልክቶ በተለያዩ ምሁራን ጥናታዊ ፅሁፎች የቀረቡ ሲሆን ውይይት እንደሚደረግበትም ተገልጿል።

በውይይቱ መድረኩ ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ እንዳሉት ኢትዮጲያውያን ሙስሊሞች ከትምህርት እንዲገለሉ የተለያዩ በደሎች ሲደርስባቸው እንደቆየ አንስተው አሁንም ችግሩ እንዳልተፈታ ተናግረዋል።

በዝግጅቱ ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ከፍተኛአመራሮች፣ ኡለማዎች፣ ኡስታዞች፣ ምሁራኖች ተገኝተዋል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Jan, 09:59


በኢትዮጵያ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶችን መንግስት በዘርፉ ባለሙያዎች በቅርበት እየተከታተለ ነው።

▣ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

- ሀሩን ሚዲያ ታህሳስ፣ 26/2017

የመንግስት ኮምኒኬሽን አገልግሎት ከሰሞኑ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ባለው የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት ጉዳዩን አስመልክቶ ወቅታዊ መግለጫ አውጥቷል።

በአፋር፣ ኦሮሚያ እና አማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ማዕከላቸውን አድርገው የተለያየ መጠን ያላቸው የርዕደ መሬት ክስተቶች በተደጋጋሚ መከሰታቸው ይታወቃል።

ክስተቶቹ ከጊዜ ወደ ጊዜ በመጠን እና በድግግሞሽ እያደጉ ይገኛሉ። በተለይም በዚህ ሳምንት በርዕደ መሬት መለኪያ እስከ 5.8 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ መንቀጥቀጥ መከሰቱን መረጃዎች ያሳያሉ።

መንግሥት ክስተቶቹን በዘርፉ ባለሙያዎች በቅርብ እየተከታተለ ደገኛል። በተጨማሪም በተለይ የርዕደ መሬቱ ማዕከል (epicenter) የሆኑት አካባቢዎችን በመለየት በ12 ቀበሌዎች ላይ መንግሥት ከተለያዩ የሙያ ዘርፎች የተውጣጡ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞችን በቦታው በማሰማራት የጉዳቱን መጠን አሰሳ እያደረገ ይገኛል።

በእነዚህ ቀበሌዎች ከሚኖሩ 80 ሺህ ዜጎች ቅድሚያ የሚሰጣቸውን በመለየት ነዋሪዎችን ከአካባቢው በማራቅ ለማስፈር ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ ነው፡፡

በተጨማሪም ርዕደቱ በማኅበራዊ አግልግሎት ሰጭ ተቋማት፣ በኢኮኖሚ ተቋማት እና በመሠረተ ልማት ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተጽዕኖ በመከታተል ላይ ነው፡፡

እስካሁን ባለው ሁኔታ በዋና ዋና ከተሞች የጎላ ተጽዕኖ ያላደረሰ ቢሆንም ዜጎች በባለሙያዎች የሚሰጡ የጥንቃቄ መልዕክቶችን እንዲከታተሉ እና በጥብቅ እንዲተገብሩ ለማሳሰብ እንወዳስን።

በቀጣይም ጉዳዩን በቅርበት በመከታተል አስፈላጊ መረጃዎችን በሚመለከታቸው ተቋማት አማካኝነት የሚያደርስ መሆኑን መንግሥት ያስታውቃል።

▣ መረጃው የመንግሥት ኮምኒኬሽን አገልግሎት ነው።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

03 Jan, 19:44


በየትኛውም ቦታ ሂጃብ ሊከለከል አይገባም!

የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሀፊ በሙስሊም ተማሪዎች ጉዳይ ለሀሩን ሚድያ የሰጠው ምላሽHarunMedia
https://youtu.be/dn-9BXXS4Z0

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

03 Jan, 19:33


በአፋር ክልል አዋሽ አካባቢ በተደጋጋሚ የሚከሰተው የርዕደ መሬት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለፀ።

እስካሁን ከአራት ሺህ የሚልቁ ነዋሪዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸው ተገልጿል።

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 25/2017

በአፋር ክልል አዋሽ አካባቢ ዛሬ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ገደማ ከፍተኛ የሆነ በሬክተር ስኬል 5.5 የተመዘገበ ርዕደ መሬት ዛሬ አርብ ምሽት መከሰቱን የአሜሪካ እና የአውሮፓ ተቋማት አስታውቀዋል።

ይህ ርዕደ መሬት ከአዋሽ ከተማ 44 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለ ስፍራ የደረሰ መሆኑን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት አስታውቋል።

የጀርመን የጂኦሳይንስ የምርምር ማዕከል በበኩሉ ምሽቱን የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 5.0 የሚለካ እንደሆነ በመረጃ ቋቱ ላይ አስፍሯል። ይህ የምርምር ማዕከል ከሁለቱ ተቋማት በተለየ፤ ትላንት ሐሙስ ለሊት በአፋር አካባቢ በሬክተር ስኬል 5.3 የደረሰ ርዕደ መሬት መከሰቱን አስታውቆ ነበር።

በክልሉ አዋሽ አካባቢ በተደጋጋሚ እየተከሰተ የሚገኙ ርዕደ መሬት አሳሳቢ ደረጃ የደረሰ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ነገር ግን ተገቢውን ትኩረት አላገኘም ተብሏል።

እስካሁን በአካባቢው እየተከሰተ ባለው አደጋ ከአራት ሺህ በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ቀያቸውን ጥለው ወደተለያዩ አካባቢዎች በመፈናቀላቸው አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

03 Jan, 19:19


ከጥቂት ደቂቃዎች ቡሀላ በዩትዩብ ቻናላችን ይጠብቁን !

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

01 Jan, 15:26


ከአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ጋር በተያያዘ ችግሩ ከነገ ዛሬ ይሻሻላል ብለን በትእግስት ብንጠብቅም እልባት ሊያገኝ አልቻለም ሲል የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠ/ምክር ቤት ገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 23/2017

በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ በሂጃባቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታ የተፈናቀሉ ተማሪዎችን አስመልክቶ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መግለጫ አውጥቷል።

የመግለጫው ሙሉ ይዘት እንደሚከተለው ቀርቧል።

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የሚፈፀሙትን የመብትና የሃይማኖት ጥሰቶችን በሚመለከት የተሰጠ ወቅታዊ መገለጫ

አገራችን ኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን ከፍተኛ ርብርብና በሃይማኖት አባቶች ዱአ በምናደርግበት በአሁኑ ወቅት በተፃራሪው አንዳንድ ቦታዎች ላይ የሚከሰቱ ሃይማኖታዊ ተንኮሳዎች የመንግስት አካላትን ጨምሮ የስጋት ምንጭ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡

ከዚህ አንፃር በትግራይ ክልላዊ መስተዳደር የአክሱም ከተማ ትምህርት ቢሮ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሙስሊም ሴት ተማሪዎችን የእምነት አለባበስ አስመልክቶ ትምህርታቸውን በሚጐዳ መልኩ ከአንድ ወር ባላነሰ ጊዜ ከትምህርት ገበታቸው እንዲስተጓጐሉ ከማድረጉም ባሻገር አንዳንድ ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው በእስር ያቆዩ _ በመሆኑ ጉዳዩ ከትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ጋር እየተነጋገርን የቆየንና ከአሁን አሁን ሁነኛ መፍትሄ እስኪገኝ በትዕግስት እየጠበቅን ያለ ቢሆንም ምንም እልባት አለመኖሩን በተግባር መረዳት ችለናል፡፡

ስለዚህ የአክሱም ከተማ ሙስሊም ነዋሪዎች ለዘመናት የነበረባቸውን የእምነት ነፃነት፣ የመስገጃ ቦታ ችግርና የቀብር ቦታ ችግር እልባት ያልተሰጠበትና ወደ ባሰ ሁኔታ እየሄደ ነው፡፡

የክልሉና የፌዴራል መንግስት የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጽ/ቤቶች በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ህግጋትና በህገ መንግስቱ አንቀጽ 27 መሠረት በዚህ ዘመን በጋራ እምነቶች ተከባብረው

በሚኖሩበት አገር እሴቱን የሚሸረሽር ተግባር መፈፀሙን በጥብቅ እናወግዛለን፡፡

በመሆኑም የሙስሊም ማህበረሰብ መብቶች ሳይሸራርፉ በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲደገግና የሚመለከታቸው የመንግስት አካላትም ይህንኑ እንዲያስፈጽሙ እየጠየቅን፤ ይህንን ድርጊት በፈፀሙ ግለሰቦች ላይ ህጋዊ እርምጃ እዲወሰድ እንጠይቃለን፡፡

የህግ ክፍላችንም አስፈላጊውን ክትትል የሚያደርግ ሲሆን መላው የሙስሊም ማህበረሰብና ሌሎች የእምነት ተቋማትና ተከታዮች ጉዳዩን እንዲያወግዙና ከአክሱም ሙስሊም ማህበረሰብ ጐን እንዲቆሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን ሲሉ መጅሊሱ በመግለጫው አስታውቋል፡፡

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

01 Jan, 13:10


የአል ሒዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ የስራ አስፈፃሚ ቦርድ አዲስ አበባ በሚገኘው የዩኒቨርስቲው ፅ/ቤት የጉብኝት ፕሮግራም ማዘጋጀታቸውን ገለፁ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 23/2017

"የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ሳምንት" በሚል መሪ ሀሳብ ከመጪው ቅዳሜ እስከ ሳምንቱ ቅዳሜ አዲስ አበባ አለም ባንክ ኢማሙ አህመድ መስጅድ ጀርባ የሚገኘውን የዩኒቨርስቲው ፕሮጀክት ቢሮ በመጎብኘት ስለፕሮጀክቱ፣ ስለ አልሂዳያ ታሪክ እና አጠቃላይ እቅድ በአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ አመራሮች ገለፃ እንደሚደገረግ ለማወቅ ተችሏል።

የጉብኝቱ አላማ ስለፕሮጀክቱ ግንዛቤ መፍጠር እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ስለ አልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሮጀክት ለመወያየት መሆኑ ተገልጿል።

በመሆኑ በአዲስ አበባ እና አካባቢው የሚገኙ ሙስሊሞች በጉበኝቱ ተሳታፊ በመሆን ለፕሮጀክቱ አፈፃፀም ግብዓት የሚሆኑ ገንቢ ሀሳቦችን ለአመራሮቹ እንዲያካፍሉ ጥሪ ቀርቧል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

01 Jan, 08:11


የአክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች የትግራይ ክልል ት/ት ቢሮ በፃፈው ደብዳቤ መሰረት ወደ ትምህርት ቤት ያቀኑ ቢሆንም በአድማ ብተና ፖሊስ እንዲመለሱ መደረጉ ተገለፀ!

- አንድ ታዳጊ ተማሪ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሶባታል፣ በጉልበት ሂጃባቸውን ለመንጠቅም ተሞክሯል።

ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 23/2017

በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ በሂጃባቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው የተፈናቀሉ ተማሪዎችን አስመልክቶ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ትላንት በፃፈው ደብዳቤ አዲስ የወጣ መመሪያ ባለመኖሩ ተማሪዎች በቀደመው አለባበሳቸው ይማራሉ ማለቱ ይታወሳል።

በዚህ መሰረት ተማሪዎቹ በዛሬው ዕለት ወደ ትምህርት ቤቱ ያቀኑ ቢሆንም በፀጥታ ሀይሎች እንዲበተኑ መደረጉን ከስፍራው ለሀሩን ሚዲያ የደረሰው መረጃ ያመላክታል።

የፀጥታ ሀይሎች በተማሪዎች ላይ ድብደባ መፈፀማቸው የተገለፀ ሲሆን አንድ ታዳጊ ሙስሊም ሴት ተማሪ ላይ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባት ተሰምቷል።

የከተማው ትምህርት ቢሮ እና ከንቲባ ከክልል የተፃፈው ደብዳቤ እንደማይቀበሉት በመግለፅ ተማሪዎቹን በፀጥታ ኋይሎች እንዲበተኑ እና ተማሪዎቹን ሒጃቦቻቸውን ለመቀማት እንደሞከሩ ለማረጋገጥ ተችሏል።

የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በትምህርት ቢሮ የተፃፈው ደብዳቤ በሶስት ቀናት ውስጥ ተተግብሮ የሂጃብ ክልከላው በአዎንታዊ መልኩ ካልተፈታ በቀጣይ እንደ እስልምና ጉዳዮች ከህዝቡ ጋር በመመካከር የሚወሰዱ ሰላማዊ እርምጃዎች እንደሚያሳውቁ መግለፃቸው ይታወሳል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

31 Dec, 17:12


የአዲስአበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሙስሊም ወጣቶች ሊግ ያዘጋጀው ከተማ አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር ተካሄዴ!

ሀሩን ሚዲያ፣ታህሳስ 22/2017

በአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሙስሊም ወጣቶች ሊግ በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች ሲያካሂደው የነበረውን ልዩ ልዩ የዲን ተግባራት ማጠቃለያ እያካሄደ ነው።

በዛሬው ዕለትም የቁርአንና አዛን የስድስት ወሩን የማጠቃለያ መርሃ ግብር አድርጓል።በዚህም በቁርአን ዘርፍ ከሁሉም ክፍለ ከተማ የተውጣጡ 22 ተወዳዳሪዎችን ያሳተፈ ሲሆን በአዛን ደግሞ 11 ተፎካካሪዎች ቀርበው ተወዳድረዋል።

በዛሬው የቁርአን ውድድር ላይ ሴቶችም ተሳታፊ የነበሩ ሲሆን ለብቻ በተዘጋጀላቸው የፉክክር መድረክ ተወዳድረዋል።የሁለቱንም ዘርፎች ውድድር ታላላቅ እና ታዋቂ የከተማችን የቁርአን ዳኞች የመሩት ሲሆን ተወዳዳሪዎችም አስደማሚ ውድድር ሲያደርጉ ውለዋል።

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ከዓመታት ወዲህ የተዘነጋውን የጀመዓ ግንኙነትና የዳዕዋ መድረኮችን ለመመለስ ያለመ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ሲሆን የዛሬው መድረክም የዚሁ ዓላማ አንዱ አካል መሆኑን የሊጉ ሰብሳቢና የከፍተኛ ምክር ቤቱ የስራ አስፈጻሚ አባል ወንድም መሐመድ አሕመድ ተናግሯል።

የሙስሊም ወጣቶች ሊግ ከዲን ስራዎች በተጨማሪ በማሕበራዊ ስራዎች ላይ የተለያዩ ተግባራትን እየሰራ ሲሆን እስከ 16 ሺህ ለሚደርሱ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖችና ለተማሪዎች የምገባ መርሃ ግብር ሲያከናውን ቆይቷል።

ከመጀመሪያው የስድስት ወራት ማጠቃለያ ዝግጅት በኋላ የዲንና የማሕበራዊ አገልግሎት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ሊጉ አሳውቋል።

እነዚህ ተግባራት የተዘነጋውን የጀመዓ ስብስብ ከማጠናከራቸው በተጨማሪ መልካምና ብቁ ዜጋ በማፍራት ረገድ የሚኖራቸው ሚና የላቀ መሆኑን ወንድም መሐመድ ጨምሮ ገልጿል።

ከዚህ ባለፈም ወጣቶች የእርስ በርስ የዕውቀትና የልምድ ልውውጥ ለማድረግ መሠል መድረኮች የላቀ ጠቀሜታ እንዳላቸው በመረዳት የተጠናከረ ስራ እንደሚሠራ ተጠቁሟል።

መድረኩን በንግግር የከፈቱት የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ ሼህ ሁሴን በሽር ቁርአን ትውልድ እየገነባ፣ ዓይን እየከፈተ፣ መንገድ የሚጠርግ፣ የትኛውም ዓይነት ጉልበትና ሕሊና ያለው ኃይል የማይገዳደረው በአላህ ጥበቃ ውስጥ የሚኖር እንዲሁም ለማጠልሸት የሞከሩትን ሁሉ እያደባየ የዘለቀ፤ ሰዎችንን ከድቅድቅ ጨለማ እያወጣ የኖረና የሚኖር ነው ብለዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሼህ ሱልጣን አማን ኤባ መድረኩን ያዘጋጀው የሙስሊም ወጣት ሊግ፤ ተሳታፊዎችንና ዳኞችን ያመሠገኑ ሲሆን ቁርአንን ያከበረ ይከበራል ሲሉ ተናግረዋል።

ከቁርአን ባለፈ የተከናወነው የአዛን ውድድር መልካም መሆኑን ተናግረው አዛን የኛ የኢትዮጵያውያን ድርሻ መሆኑንም አብራርተዋል።

ከማጠቃለያ መድረኮች አንዱ የሆነና ታላቅ ከተማ አቀፍ የሙሃደራ ዝግጅት የተሰናዳ ሲሆን በመጪው ዕሁድ ታህሳስ 27/2017 በወሎ ሰፈሩ አቡኹረይራ መስጂድ እንደሚደረግ ተገልጿል።

በመድረኩ ጠቃሚ ርዕሰ ጉዳዮች የሚነሱ ሲሆን በታታላቅ ዓሊሞች እንደሚቀርብ ይጠበቃል።የዛሬ አሸናፊዎች በመጪው ዕሁድ ዝግጅት ላይ የሚታወቁና የሚሸለሙ መሆኑን የአዲስ አበባ መጅሊስ ገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

31 Dec, 14:19


"...በደብዳቤው መሠረት በዚህ ሶስት ቀን ውስጥ ተማሪዎች ተመልሰው ችግሩ ካልተፈታ ከህዝባችን ጋር በመመካከር የምንወስዳቸውን ሰላማዊ የትግል እርምጃዎች እናሳውቃለን.."

- የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት

ሀሩን ሚዲያ፥ ታህሳስ 22/2017

የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ አደም አብዱልቃድር እና የምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ ሐጂ ሙሓመድ-ካሕሳይ ከተበዳዮች ጎን ለቆሙት ሁሉ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ይህ በትምህርት ቢሮ የተፃፈው ደብዳቤ በሶስት ቀናት ውስጥ ተተግብሮ የሂጃብ ክልከላው በአዎንታዊ መልኩ ካልተፈታ በቀጣይ እንደ እስልምና ጉዳዮች ከህዝቡ ጋር በመመካከር የሚወሰዱ ሰላማዊ እርምጃዎች እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል።

የትምህርት ቢሮ ችግሩ ይፈታ በማለቱ መግለጫ መስጠታችን አሁን ላይ ትርጉም የለውም ያለው ከፍተኛ ም/ቤቱ እስካሁን በትግል እና ትዕግስት እንደመጠበቃችን መጠን ይህ ደብዳቤ ከተፃፈ ጋዜጣዊ መግለጫው አስፈላጊ አለመሆኑን ገልጸዋል። ነገር ግን በዚህ ሶስት ቀን ተማሪዎቹ ወደ ትምህርት ገበታቸው ካልተመለሱ ከህዝባችን ጋር በመመካከር የምንወስዳቸው ሰላማዊ እርምጃወች እናሳውቃለን ሲሉ ገልጸዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

31 Dec, 13:45


መግለጫው ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል

ሀሩን ሚዲያ፥ ታሕሳስ 22/2017

የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአክሱም ከተማ የሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ክልከላን አስመልክቶ ሊያደርገው የነበረውን ጋዜጣዊ መግለጫ ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘሙን አስታውቋል።

በዛሬው እለት የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ በሂጃብ ጉዳይ ላይ ለአክሱም ከተማ ትምህርት ቢሮ ይፋዊ የእርምት ደብዳቤ መጻፉን ተከትሎ መግለጫው መራዘሙን ለማወቅ ተችሏል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

31 Dec, 11:13


የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ በአክሱም ትምህርት ቤቶች የተጣለው የሂጃብ እገዳ አዲስ መመሪያ ያልወጣበት በመሆኑ በነበረው የአለባበስ ሥርዓት እንዲቀጥል አሳስቧል!

- ካለምንም መመሪያ ይህን የህግ ጥሰት በፈፀሙ አካላት ላይ ግን ቢሮው ምንም ያለው ነገር የለም

ሀሩን ሚድያ ታህሳስ 22/2017

የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ እንደገለፀው በትምህርት ቤቶች ውስጥ ያሉ የተማሪዎች የአለባበስ ሥርዓት መመሪያና አሰራር እንዳለ ጠቅሷል። በዚህም በአክሱም ውስጥ የሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች በተለመደው አሰራር መሰረት እየሰሩ ባሉበት ወቅት በአክሱም አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሂጃብ መከልከሉን እና ይህ እንዲስተካከል ጥያቄ ቀርቦላቸው እንደነበር ማወቁን ገልጿል።

ይህንን ችግር ለመፍታት ከትግራይ ትምህርት ቢሮ ከተላኩት ባለሙያዎች ጋር ስምምነት ላይ ቢደረስም የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በ17/04/2017 በደብዳቤ ቁጥር ኢ1/060/03/17 በፃፈው መሰረት በአክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች ችግር እንዳልተፈታ ቅሬታ መቅረቡን ገልጿል

ስለዚህ በዚህ ጊዜ የተለየ አዲስ መመሪያ እስካልወጣ ድረስ አዲስ እገዳም ሆነ አዲስ ጥያቄ (Demand) ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ በነበረው የአለባበስ ስርዓት እንዲቀጥል ሲል በደብዳቤ አሳውቋል።

የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ በአክሱም ትምህርት ቤቶች ያለምንም መመሪያ የሂጃብ ክልከላና መጉላላት በፈጸሙ አካላት ላይ ግን ምንም ያለው ነገር የለም።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

31 Dec, 08:19


የአዲስአበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሙስሊም ወጣቶች ሊግ ከተማ አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር እያካሄደ ይገኛል!

-ሀሩን ሚዲያ ፣ ታህሳስ 22/2017

የአዲስአበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሙስሊም ወጣቶች ሊግ ያዘጋጀው ከተማ አቀፍ የቁርአን እና የአዛን የፍፃሜ ውድድር ጦር ሀይሎች በሚገኘው የከፍተኛ ምክር ቤቱ አዳራሽ እያካሄደ ይገኛል!

የቁርአን እና የአዛን ውድድሩ በከፍተኛ ምክር ቤቱ ዋና ፀሀፊ ሼይኽ ሁሴን በሽር የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በማድረግ ተከፍቷል።

በዛሬው ዕለት የሚካሄደው የቁርአን እና የአዛን ውድድር እስካሁን በመስጅዶችና በክፍል ከተማ ደረጃ ሲካሄዱ የነበሩ ውድድሮች የማጠቃለያ (የፍፃሜ) ውድድር መሆኑ ተገልጿል።

-ሀሩን ሚዲያ በቦታው በመገኘት ውድድሩን እየተከታተለ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን በተከታታይ ወደናንተ ያደርሳል!

©ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

31 Dec, 07:52


በአክሱም ከተማ ከትምህርት ገበታቸው የታገዱ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች እና ወላጆቻቸው ስብሰባ መጠራታቸው ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 22/2017

ዛሬ ጠዋት ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ል በአክሱም ከትምህርት ገበታቸው የተከለከሉ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች እና ወላጆቻቸው ዛሬ ከጠዋቱ 4 ሰአት ላይ በባህልና ቱሪዝም እንዲገኙ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪ ማድረጉ ተሰምቷል።

በትላንትናው ዕለት 159 የአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ሒጃብ ለብሰው መማር እንደማይችሉ በመግለጽ፣ ይህንን ተቃውመው ጥያቄ ለማቅረብ መምጣታቸውንም "ለመረበሽ ነው" በሚል ሰብስበው ማሰራቸው ይታወሳል።

በተመሳሳይ የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ተማሪዎቹ ሒጃባቸውን ለብሰው እንዲማሩ ያደረገው ተደጋጋሚ ሙከራ ባለመሳካቱ በጉዳዩ ዙሪያ ዛሬ ከሰአት በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት ጥሪ አድርጓል።

በዛሬው ዕለት የተጠራው ስብሰባም የወረዳውን ጨምሮ የክልሉም መጅሊስ ይፋዊ በሆነ መልኩ የማያውቁት መሆኑን ሀሩን ሚዲያ ከመረጃ ምንጮቹ ለማረጋገጥ ችሏል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

30 Dec, 18:35


"ጠንካራ የስራ ባህል ያለውና ሀገሩን የሚወድ ወጣት ለመገንባት መስጂዶች ወሳኝ ስፍራ ናቸው"

- የአዲስ አበባ መጅሊስ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይህ ፈቱዲን ሀጅ ዘይኑ

ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 21/2017

የአዲስ አበባ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ቢሮ በጋራ ለመስራት የመግባብያ ስምምነት መፈራረማቸው ተገልጿል።

በዚህ ወቅት የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይህ ፈቱዲን ሀጅ ዘይኑ እንደገለፁት ወጣቱን በመልካም ስነምግባር ለማነፅ የሀይማኖት ተቋማት ወሳኝ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ የወጣቶችን አቅም ለመጠቀም የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በጋራ መስራታቸው ጥሩ ጅምር መሆኑን የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን፣ በቀጣይ የሚከበሩ የአደባባይ በአላት በሰላም እንዲከበሩ ወጣቶች ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ አንስተዋል።

ቢሮው ከሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በጋራ መስራቱ የሃይማኖት ተቋማቱ በውስጣቸው የያዟቸውን ወጣቶች አቅም ለሀገር ግንባታ ለመጠቀም እድል እንደሚፈጥር በመድረኩ ተነስቷል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

30 Dec, 15:53


https://youtu.be/3bdiHWW_tMw?si=McUXShos5FXQHcph

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

30 Dec, 15:21


የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም የሂጃብ እገዳን አስመልክቶ በነገው ዕለት መግለጫ እንደሚሰጥ ገለፀ!

-ሀሩን ሚድያ ታህሳስ 21/2017

የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በነገው ዕለት ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በአክሱም ከተማ ከትምህርት መታገዳቸውን አስመልክቶ መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል።

-ሀሩን ሚድያም መግለጫውን ተከታትለን እንደምናቀርብ ለመግለፅ እንወዳለን።

©ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

30 Dec, 14:08


በአክሱም ከተማ በሒጃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ የታገዱ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ከ150 በላይ መሆናቸው ተገለፀ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 21/2017

በዛሬው ዕለት ሰኞ ታሕሳስ 21/2017 አዲስ ነገር ይኖራል ብለው የጠበቁ 159 የ12ኛ ክፍል ማትሪክ ተፈታኝ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሒጃባቸውን ለብሰው ወደ የትምህርት ቤቶቻቸውን ሄደው የነበረ ቢሆንም ዛሬም ሒጃባችሁን አውልቃችሁ ካልሆነ መግባት አትችሉም ተብለው እንደተመለሱ ተማሪዎቹ ለሀሩን ሚድያ ገልፀዋል።

የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና የፈተናዎች ኤጀንሲ በበላ ሀገሪቱ ከ499 ሺህ በላይ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመውሰድ ተመዝግበዋል ያለ ቢሆንም በአክሱም ከተማ ግን አንድም ሙስሊም ሴት ተማሪ ምዝገባ አለማድረጉን ተማሪዎች ተናግረዋል።

የ12ኛ ክፍል የዩንቨርስቲ መግቢያ ፈተና ፎርም መሙያ የቀሩት ቀናት ጥቂት በመሆናቸው የሚመለከተው አካል አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

30 Dec, 11:51


በአክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የተለያዩ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው መሆኑን ገለፁ!

▣ የታሰሩ ሴት ታዳጊ ተማሪዎችም አሉ።

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 21/2017

በትግራይ ክልል ማዕከላዊ ዞን የአክሱም ከተማ በሂጃባቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎች እስከዛሬዋ ዕለት ድረስ ምንም አይነት መፍትሔ አለማግኘታቸውን ገልፀዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በተማሪዎች እና ወላጆቻቸው ላይ በፀጥታ ሀይሎች እና በትምህርት ቤቶቹ ዳይሬክተሮች የተለያዩ ማስፈራሪያ እና ዛቻ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ የገለፁ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ የታሰሩ ተማሪዎችም እንደነበሩ ተገልጿል።

ስሟ እንዳይጠቀስ የፈለገች አንድ ተማሪ ለሀሩን ሚዲያ እንደገለፀችው "እኛ የቻልነው ታግለናል ነገር ግን ምንም ለውጥ ልናመጣ አልቻልንም" ብላለች።

ሂጃብ ለብሰው ወደ ትምህርት ቤት የሄዱ ተማሪዎች ላይ የተለያዩ ድብደባ እና ማዋከብ እንደተፈፀመባቸው ተማሪዎቹ ገልፀዋል።

ሌላኛዋ ስሟ እንዳይጠቀስ የፈለገች የከተማዋ ተማሪ "ለምን ሂጃብ ለብሰን እንማር አላችሁ?" በሚል ለ17 ሰኣት ታስረው እንደነበር ገልፃ ከዚህ በኋላ መሰል ጥያቄ እንዳያነሱ ማስፈራሪያ እና ዛቻ እንደተፈፀመባቸው ገልፃለች።

የጠየቅነው በሀገሪቱ ህገመንግስት የተፈቀደ ሀይማኖታዊ ግዴታችን የሆነውን ሂጃብ ለብሰን ትምህርታችንን እንማር ቢሆንም ምላሽ ግን እስከ ቤተሰቦቻችን ማስፈራሪያ ዛቻ ማዋከብ እና ድብደባ ነው ሲሉ ተማሪዎቹ ገልፀዋል።

የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና የፈተናዎች ኤጀንሲ በበላ ሀገሪቱ ከ499 ሺህ በላይ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመውሰድ ተመዝግበዋል ያለ ቢሆንም በአክሱም ከተማ ግን አንድም ሙስሊም ሴት ተማሪ ምዝገባ አለማድረጉን ተማሪዎች ገልጸዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

30 Dec, 09:23


የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚያሳትመው ''ሰላምታ'' መጽሔት ሙስሊሙን ያማከለ አለመሆኑ ተገለጸ።

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 21/2017

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚያሳትመው ''ሰላምታ'' መጽሔት እና አየር መንገዱ የሚጠቀማቸው ማስታወቂያዎች ሙስሊሙን ያማከለ እንዲሆን ተጠይቋል።

''ሰላምታ'' መጽሔት በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚታተም ሲሆን የሚያወጣውቸው ማስታወቂያዎች የሙስሊሞችን ባህላዊ እና ሀይማኖታዊ ቅርሶችን እንዲሁም አጠቃላይ የሙስሊሞችን ማህበራዊ መስተጋብሮች እና መልካም ጎኖች ታሳቢ ያላደረገ መሆኑ ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በርካታ ባህላዊ እና ሀይማኖታዊ ቅርሶች እንዲሁም በተለያዩ ዘመናት የራሳቸውን በጎ አሻራ ለሀገራችን ያስተላለፉና በሀገረ መንግስት ግንባታ ላይ ከጦር ሜዳ ውሎ እስከ ሀገራት ዲፕሎማሲ በመስራት ሀገራችንን ከፍ ያደረጉ በርካታ ጀግኖች ቢኖሩም አየር መንገዱ በሚያሳትመው ''ሰላምታ'' መጽሔት ግን ይህ እንደማይገለጽ ተነግሯል።

ለሀገራችን በጎ አሻራዎችን ያስተላለፉ በርካታ የኢትዮጵያ ሙስሊም ታሪኮች ቢነገሩ ለማህበረሰቡ መልካም እሴት ግንባታ ላይ በጎ ተጽዕኖዎችን እንደሚያመጡ እና መጪው ትውልድ ለሀገሩ የራሱን መልካም ታሪክ በመስራት ሀገርን መገንባት እንደሚቻል የተገለጸ ሲሆን የኢትዮጵያ አየርመንገድ የሚያሳትመው ''ሰላምታ'' የተባለው መጽሔትን ጨምሮ አየር መንገዱ የሚጠቀማቸው ማስታወቂያዎች ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ያካተተ መሆን እንዳለበት ለሀሩን ሚዲያ አስተያየታቸውን የሰጡ ግለሰቦች ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚታተመው ''ሰላምታ'' መጽሔት እና አየርመንገዱ የሚጠቀማቸው ማስታወቂያዎች ሁሉንም እምነቶች፣ ብሄርብሄረሰቦችና ቅርሶችን ባካተተ መልኩ እንዲስተካከል ጥያቄ ያቀረበ ቢሆንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ አሁን ተገቢውን ምላሽና መፍትሔ ማምጣት እንዳልቻለ ለማወቅ ተችሏል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

30 Dec, 09:05


በአዋሽ ፈንታሌ እየተከሰተ ባለዉ ተደጋጋሚ ርዕደ መሬት ሳብያ ከ2,500 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸዉ ተነገረ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 21/2017

ትናንት ምሽት ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ በሬክተር ስኬል 5 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

በአፋር ክልል በአዋሽ ፈንታሌ አከባቢ በሚከሰት ተደጋጋሚ ርዕደ መሬት ከ100 በላይ ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸዉ ሲሆን፤ 2 ሺሕ 560 ሰዎች መፈናቀላቸውን እና እንሰሳት መሞታቸውን የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ አስተዳደር አቶ አደም ባሂ ተናግረዋል።

አስተዳደሩ አክለውም ይህ ክስተት በሚድያ እንደሚባለዉ በቀን ሦስቴ እና ሁለቴ የሚከሰት ሳይሆን ከዚያም በላይ አስጊ እየሆነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በተጨማሪም በአካባቢው ያለዉ ተፈናቃይ ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ መሆኑን ያነሱት አቶ አደም፤ መጠለያ፣ ምግብ እና መሰረታዊ ግብአቶች እንደሚያስፈልጉ ተናግረዋል። የክልሉ የአደጋ ስጋት ድጋፍ እንዲያደርግም እንደጠየቁ ገልጸዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

29 Dec, 17:44


ከተጀመረ ስምንት ዓመታት ያስቆጠረው ሙሀጅር መስጂድ ግንባታን ለማጠናቀቅ ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃግብር ተካሄደ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 20/2017፤ ሸገር

በሸገር ከተማ የኩሪ ጅዳ ክፍለከተማ ወልገዋ ለገበሪ ወረዳ የሚገኘውና ግንባታው 8 ዓመታትን ያስቆጠረው የሙሀጅር መስጂድ ግንባታን ለማጠናቀቅ ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃግብር በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

በአካባቢው በርካታ ሙስሊም ማኅበረሰብ ቢገኝም በአቅም እጦት ምክንያት የመስጂዱን ግንባታ ማጠናቀቅ እንዳልተቻለ የመስጂዱ ኮሚቴዎች ለሀሩን ሚድያ ገልፀዋል።

በዛሬው የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ ሸይኽ ባህሩ ኡመር እና ኡስታዝ ጀማል በሽር የተገኙ ሲሆን የመስጂዱን ግንባታ ለማጠናቀቅ መላው ሙስሊም ማህበረሰብ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የሙሀጀር መስጂድ ግንባታን ለማገዝ የሚከተሉትን አካውንቶች ይጠቀሙ፦

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000592607135

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000620314181

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

29 Dec, 16:54


የአል ሒዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ የስራ አስፈፃሚ ቦርድ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የውይይት መድረክ አካሄደ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ታህሳስ 20/2017፣ ወልቂጤ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን በጉመር ወረዳ በግንባታ ላይ የሚገኘው የአል ሒዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ ያለበትን የግንባታ ሂደት እንዲሁም የወደፊት ሁኔታዎችን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ዩኒቨርስቲው እስካሁን የነበረው ሂደት እንዲሁም የወደፊት እቅዶችን አስመልክቶ በዩኒቨርሲቲው ስራ አስፈፃሚ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ዛኪር ሚፍታህ ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።

አል ሒዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ አሁን ላይ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን በዚህም የመማሪያ ክፍሎች እና የተማሪዎች ዶርም ይሆናሉ የተባሉ ሁለት ብሎኮች ግንባታ ተጀምሯል።

ኢልም ለአንድ ማህበረሰብ ከፍታ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ የሚገልፅ ዳዕዋ በኡስታዝ ሰልሀዲን አማካኝነት ለታዳሚው ቀርቧል።

ዛሬ በነበረው የግንዛቤ ማስጨበጫ መርኅ ግብር ላይ የአል ሒዳያ ዩኒቨርስቲ የቦርድ አመራሮች፣ የጉራጌ ዞን መጅሊስ አመራሮች፣ ኡለማኦች እና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የውይይት ፕሮግራሙ በወልቂጤ ባህላዊ አዳራሽ፣ ረቢዕ መስጅድ እና በድረዲን መስጅድ ተካሄዷል።

የአል ሒዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ መገንባት ለአካባቢው ማህበረሰብ ከሚሰጠው የተለያዩ አገልግሎት በተጨማሪ በሀገራችን ኢልም ፍለጋ ወደተለያዩ ሀገራት ለሚሄዱ ሙስሊሞች መፍትሔ ይሆናል የተባለ ሲሆን ሁሉም ሙስሊም ማህበረሰብ ዩኒቨርስቲው ለመገንባት እንዲረባረብ ጥሪ ቀርቧል።

- ሀሩን ሚዲያ በቦታው በመገኘት ያጠናቀረውን የቪዲዮ ዘገባ ወደናንተ ያደርሳል!

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

29 Dec, 16:15


በጅግጅጋ ለከተማው የመጀመሪያው የሆነ ኢስላማዊ ዩንቨርስቲ ምርቃት ተካሄደ!

-ሀሩን ሚድያ ታህሳስ 20/2017

በሱማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ለከተማው የመጀመሪያው የሆነው ኢስላማዊ ዩንቨርስቲ በዛሬው ዕለት ለምርቃት በመብቃት መከፈቱ ተገልጿል።

በጅግጅጋ ከተማ ዛሬ በተከናወነው የምርቃት ስነስርዓት ላይ የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይህ አብዱላዚዝ ሼይኽ አብዱል ወሊ፤ዶክተር ጄይላን ኽድር ተገኝተው በኢስላማዊ በዩንቨርስቲው ምርቃት የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።

በኢስላማዊ ዩንቨርስቲው የምርቃት ስነስርዓቱ ላይ የፌደራል መጅሊሱ ከፍተኛ አመራሮች፤የጅግጅጋ ከተማ የመንግስት አመራሮች፤ኡለማዎች፤ኡስታዞች፤የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች መገኘታቸው ተገልጿል።

©ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

29 Dec, 12:04


የኸይር ውሀ ፕሮጀክት የሆነው 600 ሜትር ድረስ መቆፈር የሚያስችል የውሀ ጉድጓድ መቆፈሪያ ማሽን ተመረቀ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 20/2017

ከተመሠረተ 11 ዓመታት ያስቆጠረው ኸይር ፈላጊ የበጎ አድራጎት ድርጅት በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የበጎ አድራጎት ተግባራትን የሚያከናውን ሲሆን በዛሬው ዕለት “የኸይር ውሃ” የጉድጓድ መቆፈሪያ ማሽን በድምቀት አስመርቋል።

ንፁህ የመጠጥ ውሃ ለሁሉም የሀገራችን ክፍሎች በሚል መሪ ሀሳብ 600 ሜትር ጥልቀት ድረስ የሚቆፍር ማሽን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በፉልውሃ ተወፊቅ መስጂድ የምርቃት ስነ-ስርዓቱ ተካሂጿል።

የኸይር ፈላጊ "የኸይር ውሀ" ፕሮጀክት የውሀ ጉድጓድ መቆፈርያ ማሽን የምርቃት ስነስርዓት ላይ የኢ/እ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ የኢ/እ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ም/ፕሬዝዳንት ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን፣ የኢ/እ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ፅ/ቤት ኃላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ፣ የአ/አ/እ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ እና ሌሎች የክብር እንግዶች ተገኝተዋል::

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Dec, 17:58


በኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ አቅራቢያ የሚገነባው የባምዛ አል-ረህማን መስጂድ ግንባታ መጀመሩ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ሕዳር 30/2017

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን፣ ጉባ ወረዳ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አቅራቢያ በተመሰረተችው ባምዛ ከተማ ላይ 'አል-ረህማን' በሚል ስያሜ መስጅድ ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ መቀመጡ የሚታወስ ሲሆን የመስጂዱ ግንባታ መጀመሩም ተገልጿል።

የፊታችን ጁመአ በአዲስ አበባ በቂርቆስ ክፍለከተማ በሚገኙት ፍልውሃ ተውፊቅ መስጂድ እና ወሎ ሰፈር አቡሁረይራ መስጂድ ላይ ለታሪካዊው መስጂድ ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር እንዲሚካሄድ አስተባባሪ ኮሚቴ ለሀሩን ሚድያ ተናግረዋል።

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ኘሬዝዳንት ሸይኽ ኢብራሂም ሲራጅ በመስጂዱ የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሀግብር ላይ ባስተላለፉት መልዕክት አካባቢው ላይ ያለው ማህበረሰብ የመስጂድ እጦት የተቸገረና አካባቢው የመዝናኝ ከተማ እየሆነ ስለሆነ መስጂዱን በአፋጣኝ እንዲሰራ መጠየቃቸው ይታወሳል።

ሙስሊሙ ማህበረሰብም ለዚህ ታሪካዊ መስጂድ ግንባታ ማሰባሰቢያ መርሀግብር ላይ በፍልውሀ ተውፊቅ መስጂድ እና ወሎ ሰፈር አካባቢ በሚገኘው በአቡሁረይራ መስጂድ የጁመአ ሰላትን በመስገድ ለመስጂዱ ግንባታ የበኩላችንን እንድንወጣ አስተባባሪ ኮሚቴው ጥሪ አቅርቧል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Dec, 16:26


https://youtu.be/jPuPWXrcccE?si=EMNHd5isTkbpfBVr

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Dec, 16:03


የሶማሌ (ዒሳ) ማህበረሰብ የሚመራበት ''ሄር ሂሴ'' የተባለው ህግ በዩኔስኮ ተመዘገበ።

- ሀሩን ሚዲያ፣ ህዳር 30/2017

በሶማሌ ህዝብ ዘንድ ጥንታዊና ባህላዊ ህግ እንደሆነ የሚነገርለት ''ሂር ሂሴ'' የተባለ ማ/ሰቡ የሚጠቀምበት ባህላዊ ህግ የተመዘገበው ከቀናት በፊት ዩኔስኮ በኡራጓይ ባካሄደው ጉባኤ ላይ ነው።

''ሂር ሂሴ'' የተባለው የማህበረሰቡ ህግ ጂቡቲ፣ እና ሶማሊያ በኢትዮጵያ አስተባባሪነት በዓለም ዓቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ተቋም በሆነው ዩኔስኮ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ መሳተፋቸው የተገለፀ ሲሆን ''ሂር ሂሴ'' ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በጂቡቲ እና ሶማሊያም የሚተገበር ባህላዊ ህግ ነው።

የሂሳ ዑጋዛዊ ምክር ቤት ቃል አቀባይ አቶ ሙሀመድ ሙሴ የቅርሱ በአለምአቀፍ ቅርስነት መመዝገብ በብሄረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ደስታን እንደፈጠረ ገልጸዋል።

የሶማሌ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን ቅርሱ በአለማቀፍ ቅርስነት እንዲመዘገብ በርካታ ጥረቶችን እንዳደረጉ አውስተው ሌሎች የሶማሌ ማ/ሰብ ባህላዊ እና ሀይማኖታዊ ቅርሶችም በዩኔስኮ እንዲመዘገቡ እየሰራን ነው ሲሉ ለዶቼ ቬሌ ገልጸዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Dec, 15:07


በዩኒቨርሲቲዎች የምግብ ሜኑ ዋጋ ተመሳሳይ እንዲሆን መወሰኑ ተገለፀ።

- ሀሩን ሚዲያ ህዳር 30/2017

የትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ የምግብ ሜኑ ዋጋ ተመሳሳይ እንዲሆን መወሰኑን የገለጸ ሲሆን ለተማሪዎች የቁርስ የምሳ እና የእራት በጀት ላይም ማሻሻያ እንዳደረገ ገልጿል።

ሚኒስቴሩ ባደረገው ጥናት መሠረት የምግብ ዋጋ ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ያሳወቀ ሲሆን ከዚህ ቀደም ለተማሪዎች ይደረግ የነበረው የምግብ በጀት ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ገልጿል።

በዚህም ለ1 ተማሪ የቁርስ፣የምሳ እና የእራት ወጪ 22 ብር የነበረ ሲሆን አሁን በተደረገው ማሻሻያ ወደ 100 ብር ከፍ እንዲል መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Dec, 15:07


በኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ የሚመራው የሲርለና የበጎ አድራጎት ድርጅት ያስቆፍራቸው የንፁህ መጠጥ ውሃ ጉድጓዶች እና ምንጮች ብዛት 340 ማድረሱ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ህዳር 30/2017

የሲርለና በጎ አድራጎት ድርጅት ያስቆፈራቸውን የንፁህ መጠጥ ውሃ ጉድጓዶች እና ምንጮች ብዛት 340 መድረሳቸውን የድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ ገልፀዋል።

የሲር ለና ለሁሉ ደራሽ ሁሉን አጉራሽ ሁሉን አልባሽ የተቸገሩ ዜጎችን ቀጥታ በመደገፍ የልማት ስራዎች ላይ በመሳተፍ እና የሰው ሀብት ልማት ላይ በማተኮር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ የሚገኝ ድርጅት መሆኑንም ተናግረዋል።

የሲርለና በጎ አድራጎት ድርጅት በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በስልጤና በጉራጌ ዞኖች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ በማይገኝባቸው ቦታዎች ጉድጓዶችን እያስቆፈረ የንፁህ መጠጥ ውሃ እያቀረበ ይገኛል ብለዋል።

በየትኛውም አካባቢ የውሃ እና ልዩ ልዩ ችግሮች ያለባቸው አካባቢዎችን እና ሰዎችን መደገፍ በአኼራም በዱኒያም ወደር የሌለው እርካታን ያጎናፅፋል በማለት ማህበረሰቡም ከየሲር ለና በጎ አድራጎት ድርጅት በመቆም የኸይር ስራ ተከፋይ እንዲሆን ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪም በየሲርለና በጎ አድራጎት ድርጅት በሚሰበስበው የልብስ ባንክ አማካኝነት ለበርካታ ልጆች፣ እናቶች እና አባቶች የልብስ ስጦታ እያበረከተ እንደሚገኝም ተገልጿል። በዚህ ኸይር ስር ላይ መሳተፍ ለምትፈልጉ አህለል ኽይሮች አዲስ አበባ ከሳባ መስጅድ ከፍ ብሎ ኢትዮ ፓረንት ት/ቤት አጠገብ በሚገኘው የድርጅቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት የሲርለናን በመጎብኘት የልብስ ድጋፍ ማድረግ ይችላሉ ተብሏል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

09 Dec, 09:36


የሐማስ/አል-ቀሳም ብርጌድ አዛዥ የነበረው አቡ ጁዳት አል-ጃሉዲ ከደማስቆ ሰድናያ እስር ቤት ተፈታ።

ሀሩን ሚዲያ፥ ሕዳር 30/2017

የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ አልቀሳም ብርጌድ ኮማንደር የነበረው አቡ ጁዳት አል-ጃሉዲ ከደማስቆ ሰድናያ እስር ቤት መፈታቱ ተገልጿል።

በድምሩ ከ630 በላይ ፍልስጤማውያን 67 የአልቀሳም ብርጌድ አባላትን ጨምሮ ከደማስቆ ወጣ ብሎ ከሚታወቀው ከአሰቃቂው ሴድናያ እስር ቤት ተፈተዋል። በበሽር አል አሳድ አገዛዝ የታሰሩት እነዚህ እስረኞች ብዙዎቹ እንደሞቱ ይታመን ነበር።

- መረጃው የዶም ነው።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

08 Dec, 21:43


https://youtu.be/6Q-RsLYxvcA?si=tgjBSnNp9vN7IYXC

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

08 Dec, 18:20


በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ በአብጀት አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ላይ ድጋፍ ላደረጉ አካላት የምስጋና እና የእውቅና ፕሮግራም ተካሄደ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ህዳር 29/2017 አዲስ አበባ

በስልጤ ዞን የአልቾ ውሪሮ ወረዳ በአዲስ አበባ ከተማ በልደታ ክፍለከተማ አዳራሽ በአብጀት አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ላይ ድጋፍ ላደረጉ አካላት የወረዳው አስተዳደር የምስጋና እና የእውቅና ፕሮግራም አካሄደ።

ፕሮግራሙ "ባደከ የካደመ ባድ ያሾክረያን" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ከተማ በዛሬው እለት ተካሄዷል።

በምስጋና ፕሮግራሙ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ዶ/ር መሀመድ ሽኩር የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ ማህዲያ ሀሰን፣ ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን ሙሐመድን ጨምሮ ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ በርካታ የልማት ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ በማለት የተናገሩት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የእለቱ የክብር እንግዳ የተከበሩ ዶክተር መሀመድ ሽኩር በወረዳው እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ስራዎች በማህበረሰባችን ትጋት መሆኑ ለየት ያደርገዋል ሲሉ ገልፀዋል።

የወረዳው አስተዳደር መሰል የምስጋና ፕሮግራሞችን ማዘጋጀቱ ለልማቱ መሳካት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል በማለት የገለጹት ዶክተር መሀመድ የአብጀት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ላይ ተሳትፎ ያደረጋችሁ አባላት ከልማቶች ሁሉ በላጩ የትምህርት ልማት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

በመድረኩ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ ማህዲያ ሀሰን በወረዳው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እጥረት በተደረገው ከፍተኛ ርብርብ ባለፋት አመታት የተገነቡት አዲስ አራት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ ቁጥራቸውን ስምንት ማድረስ መቻሉን አንስተዋል።

የአብጀት አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በወረዳው ከተገነቡ አዳዲስ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ መሆኑን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪዋ በግንባታ ሂደቱ ላይ የአካባቢው ተወላጆችና ባለሀብቶች በገንዘብ በአይነትና አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ሁሉ ላደረጋችሁት አስተዋጽኦ የወረዳው አስተዳደር ምስጋናው የላቀ ነው ብለዋል።

የትምህርት ቤቱን የግንባታ ሂደቱን አጠናቅቆ ለምርቃት ለማብቃት በአዲስአበባና በሌሎችም አካባቢዎች የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆች እንደየአቅማቸው ድጋፍ ሲያደርጉ በመቆየታቸው በግንባታው አስተባባሪ ስም አመስግነዋል።

በምስጋና መርሀግብሩ ላይ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ላይ ህብረተሰቡን በማስተባበር እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዋች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ ቀርቧል።

በመድረኩ በስልጤ ዞን ፓርቲ ጽ/ቤት የሲቪክ ተቋማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አማን ከድርና ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙባሪክ አሊ የአዲስአበባ ከተማ አስተዳዳር ግብርና ኮሚሽን አቶ ፋሩቅ ጀማል የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙባሪክ አብደላና የከተማ ባለሀብቶችና የአካባቢው ተወላጆች፣ የኮሚቴ አባላትና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

- ሀሩን ሚድያ በዝግጅቱ በመገኘት ያጠናቀርነውን የቪድዮ ዝግጅት በአላህ ፍቃድ ወደናንተ የሚያደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

08 Dec, 15:34


በሀላባ ዞን ለተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የሽኝት ፕሮግራም አካሄደ!

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፣ ህዳር 29/2017 ዓ.ል

የሀላባ ዞን ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ወደ ዩንቨርሲቲ ለሚገቡ ተማሪዎችና በተጨማሪም ወደ ሀይስኩል ለሚገቡ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የሽኝት ፕሮግራም አካሄደ!

የሀላባ ዞን ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በዞኑ የሚገኙ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለሚሄዱ ተማሪዎች የሽኝትና እና ወደ ሀይስኩል ለሚገቡ ተማሪዎች ደግሞ የእንኳን ደህና መጣችሁ መርኅ ግብር አካሒደዋል። በተጨማሪም አሚሮችንም በክብር ሸኝተዋል።

በሀላባ ዞን ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በተማሪዎች ሰብሳቢ አ/ጀባር ሸኽ ጀማል ሪፖርት የቀረበ ሲሆን መረኅ ግብሩ ላይ የሀላባ ዞን እስልምና ጉዳዮች ዋና ፀኃፊ ሸይኽ ሁሴን መሀመድ ቃበቶ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል። በተጨማሪም የሀለባ ቁሊቶ እስልምና ጉዳዮች ሰብሳቢ ሸይኽ አህመድ ሀሰንም መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ኡስታዝ ካሚል ጣሃ ተገኝተው ዳዕዋ አድርገዋል።

መድረኩ ላይ ኡስታዝ አብዱልመሊክ ሃጂ አህመዲን የሀላባ ዞን እሰለምና ጉዳዮች ምክር ቤት ም/ሰብሳቢ፣ የሀላባ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ፀኃፊ ሸይኽ ሁሴን መሀመድ ቃበቶ ፣ የሀላባ ቁሊቶ እስልምና ጉዳዮች ሰብሳቢ ሸይኽ አህመድ ሀሰን፣ ኡመር አርሲ፣ ወንድም መሀመድ ጋሹ የሂራ ሙስሊም ተማሪዎች ማኅበር ም/ሰብሳቢ፣ መሻይኮች፣ ኡለማኦች፣ ተማሪዎችና የተማሪ ቤተሰቦች ታድመዋል።

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ ስፍራው ተገኝቶ ያጠናቀረው የቪዲዮ ዘገባ በቀጣይ ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

08 Dec, 14:54


-የዳዕዋ ፕሮግራም ጥቆማ

“ሪዝቃችን” በሚል ርዕስ በኡስታዝ ካሚል ጣሃ በሀላባ ከተማ በታላቁ ኑር መስጂድ ዛሬ እሁድ ከመግሪብ ሶላት በኋላ ዳዕዋ ይቀርባል።ሀላባ እና አካባቢው የምትኖሩ ሁላችሁም የዳዕዋ ፕሮግራሙ ተካፋይ እንዲትሆኑ ተጋብዛችሃል።

©ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

08 Dec, 14:44


ዋህደቱል ኡማ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት ስድስተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ህዳር 29/2017፣ አዲስአበባ

ዋህደቱል ኡማ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት ስድስተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ እፎይታ አዳራሽ አካሂዷል።

ዋህደቱል ኡማ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት ትኩረት አድርጎ የሚሰራው ለሙስሊሙ ማህበረሰብ እምብዛም ትኩረት ባላገኘበት የወለጋ እና የሸዋ ዞኖች መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከዚህ ጋር በተገናኘ ድርጅቱ በርካታ ተግባራትን ማከናወኑ ተገልጿል።

ድርጅቱ እስካሁን በሁለቱ አካባቢዎች ትኩረት በማድረግ ከሰራቸው ስራዎች መካከል በወለጋ እና አካባቢ በድርቅ እና በወባ በሽታ ጉዳት ለደረሰባቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ አድርጓል። ከአራት ጊዜ በላይ ከተለያዩ አካባቢዎች ለተውጣጡ ኡለማኦች ስልጠናዎችን መስጠቱ ተገልጿል።

በተጨማሪ ሴቶች እና አቅም ለሌላቸው ወገኖች ድጋፍ ማድረጉ የተገለፀ ሲሆን ነገር ግን በሁለቱ አካባቢዎች ይበልጥ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት ተነስቷል።

በዛሬው ዕለት በተካሄደው የድርጅቱ ስድስተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የኦሮሚያ መጅሊስ አመራሮች የአዲስአበባ ከተማ መጅሊስ አመራሮች የሸገር ከተማ መጅሊስ አመራሮች የድርጅቱ አመራሮች እና ደጋፊዎች ኡለማኦችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ በድርጅቱ ስልጠና ሲወሰዱ ለነበሩ ኡለማኦችና ድርጅቱን በተለያዩ መንገዶች ሲያግዙ ለነበሩ አካላት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ እምብዛም ትኩረት ባላገገኙት የወለጋ እና የሸዋ ዞኖች ያሉ ሙስሊሞች ትኩረት እንዲሰጥ ዋህደቱል ኡማ የበጎ አድራጎትና የልማት ድርጅት ጥሪ አቅርቧል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Dec, 16:26


የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገለፀ!

-ሀሩን ሚድያ ህዳር 28/2017

በቅርቡ በኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተቋቋመው የኢትዮጲያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ትኩረቱን በሙስሊም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሁለንተናዊ ችግር እና መፍትሔዎቻቸው ዙሪያ አድርጎ ከሚሰራው ከኢትዮጲያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል።

በውይይቱ የተለያዩ ነጥቦች የተነሱ ሲሆን በዋናነትም ከሙስሊም ተማሪዎች የመብት ትግል እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች መነሳቱም ተነግሯል::

የኢትዮጲያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከሙስሊም ተቋማት ጋር በመተባበር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ዙሪያ እየደረሱ ያሉ መግፋቶችንና በደሎችን ለመፍታት እንደሚሰራም ከህብረቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

-ፎቶ ከፋይል

©ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Dec, 15:53


ማዕሀድ አባ ጅፋር ኮሌጅ በርቀት የትምህርት ፕሮግራም ሲያስተምራቸው የቆዩ ተማሪዎችን አስመረቀ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ህዳር 28/2017

ማዕሀድ አባ ጅፋር ኮሌጅ በሸሪዓ ትምህርት እና አረብኛ ቋንቋ በርቀት ትምህርት ፕሮግራም ለአራተኛው ዙር ሲያስተምራቸው የቆዩ 65 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት ማስመረቁ ተገልጿል።

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የጅማ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ሰብሳቢ ሼህ ሙሀመድ ተማምን ጨምሮ ኡለማዎች፣ ኡስታዞች፣ የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

የማዕሀድ አባ ጅፋር ዳይሬክተር ሼህ ሀምዛ ሼህ ሙሀመድኑር ለተመራቂዎች እና ለቤተሰቦቻቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Dec, 14:59


የሸገር ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ባለ አምስት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን አጠናቀቀ!

-ሀሩን ሚዲያ፣ህዳር 28/2017

ከተቋቋመ የአንድ አመት እድሜ ያስቆጠረው የሸገር ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት መደበኛ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት በአዲስአበባ ኡማ ሆቴል አካሂዷል።

በጉባኤው ላይ የከተማዋ የመጅሊስ አመራሮች ፣የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ፣የኦሮሚያ እና የአዲስአበባ መጅሊስ አመራሮች እንዲሁም በሸገር ከተማ የሚገኙ የክፍለ ከተማ መጅሊስ አመራሮች ተገኝተዋል።

ጉባኤው ዶ/ር ሙሀመድ ሳሊህ ጀማልን የሸገር ከተማ መጅሊስ ፕሬዚዳንት አድርጎ የሾመ ሲሆን ባሳለፍነው የበጀት አመት የተከናወኑ ተግባራት በዋና ፀሀፊው ያህያ ኢብኑ ጀበል ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የ2017 ዓ.ል የስራ ዘመን የሸገር ከተማ መጅሊስ የስራ እቅዶች እንዲሁም አጠቃላይ በከተማዋ መጅሊስ ያሉ ክፍተቶች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል። ባሳለፍነው የበጀት አመት ጥሩ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ መጅሊሶች የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

ጉባኤው በመጨረሻም ባለ አምስት አቋም መግለጫ በማውጣት ጉባኤውን ያጠናቀቀ ሲሆን የአቋም መግለጫው ከታች እንደሚከተለው ቀርቧል።

የሸገር ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተሰጠ የአቋም መግለጫ ።

1ኛ የሸገር ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከተቋቋመ አጭር ግዜ ቢሆንም ሸገር ከተማ መቋቋም አዲስ በመሆኑ መጅሊሱም እንደ አዲስ የተቋቋመ ሲሆን መጅሊሱን የከተማውን ሙስሊም በሚመጥን መልኩ ለመገንባት የሁሉንም ማህበረሰብ ድጋፍና ትብብር ይፈልጋል ።

2ኛ የሸገር ከተማ ሙስሊሞች ያሏቸውን በርካታ ጥያቄዎች ለመለስ መንግስታችን ቀና ትብብር እንዲያደርግ እንጠይቃለን ።

3 ኛ በክልላችን መንግስት እና በከተማ አስተዳደራችን በኩል ቃል የተገቡ ነጥቦች
3.1. የፈረሱ መስጅዶቻችኝ ጉዳይ

3.2. በሁሉም ክፍለ ከተሞች ያለውን የመስጅድ እና የመቃብር ቦታ ከፍተኛ እጥረት
3.3.የመሳጂዶቻችን እና የመቃብር ቦታ ህጋዊ ሰነድ እንዲኖራቸው

3.4. ትልቅ መስጂድ እና መድረሳ ለመስራት የሚሆን ቦታ እና መሰል ጥያዎቻችን ቃል በተገባው መሰረት እንዲፈፀሙልን ስንል በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን ።

4. የፌድራል እና የኦሮሚያ መጅሊሶች የሸገር ሙስሊሞችን ጥያቄ ማስመለስ የሚቻለው አንዱ ጠንካራ ተቋም ሲኖር በመሆኑ የሸገር መጅሊስን ልዩ ቱኩረት ሰጥታቹሁ እንድታቋቁሙት እና ከጎናችን እንድትቆሙ  ስንል እንጠይቃለን።

5. የከተማችን ሙስሊም ነዋሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ የክልል መጅሊሶች፣ በከተማችን እና ከከተማችን ውጪ  የምትገኙ  የሙስሊም ማህበራት ድርጅቶች፣ ባጠቃላይ በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጪ ያለችሁ ሙስሊሞች የሸገር መጅሊስን በማቋቋም ረገድ ሀላፊነታችሁን እንድትወጡ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ።"

-የሸገር ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት

©ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Dec, 12:30


"ጫኝ እና አውራጅ የሚባል አደረጃጀት አናውቅም" - የድሬዳዋ ፖሊስ

- ሀሩን ሚዲያ ህዳር 27/2017

ማህበረሰቡ በተደጋጋሚ ቅሬታ ከሚያቀርብባቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የሆነው ጫኝ እና አውራጅ ነን የሚሉ ሰዎች የተጋነነ ዋጋ እና በማህበረሰቡ ላይ የሚፈጥሩት እንግልት እንደሆነ ተደጋግሞ ይጠቀሳል።

ይህንን በማስመልከት የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር መግራ በድሬዳዋ ጫኝ እና አውራጅ ነን እያሉ ማህበረሰቡን እያማረሩ የሚገኙ ህገ ወጦች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ገልጸዋል።

ማህበረሰቡ የፈለገውን እቃ ሲያሻው በራሱ ካልፈለገም በፈለገው አካል ዋጋ ተደራድሮ ንብረቱን ማስወረድ እና ማስጫን ይችላል ሲሉ ተናግረዋል።

አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች ጫኝ እና አውራጅ ነን በሚሉ ሰዎች ከፍተኛ ገንዘብ እየተጠየቁ ንብረታቸውን እንደሚያስጭኑና እንደሚያስወርዱ በርካታ ሰዎች ቅሬታ እንደሚያነሱ ይታወቃል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Dec, 12:17


የሶርያ ተቃዋሚ ኃይሎች ግስጋሴያቸውን ቀጥለው ከደማስቆ 10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በከተማው ዙሪያ መድረሳቸው ተገለጸ

ሀሩን ሚዲያ፥ ሕዳር 28/2017

የሶርያ ተቃዋሚ ኃይሎች ግስጋሴያቸውን ቀጥለው ከደማስቆ 10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል። ባለፉት አስር ቀናት ድንገተኛ የተባለውን የተቀናጀ ጥቃት በሶርያው የበሽር አል አሳድ ሰራዊት ላይ የፈጸሙት ተቃዋሚዎቹ ፈጣን የሚባል ግስጋሴ በማድረግ የሶርያ ግዙፍ ከተሞችን ሲቆጣጠሩ ቆይተዋል።

በዛሬው እለት ስትራቴጂያዊ ከተማ ተደርጋ የምትታመነውን ሆምስን ለመቆጣጠር ውጊያ ላይ የሚገኙ ሲሆን አብዛኛው የመንግስቱ ሰራዊት የከተማ ይዞታዎችን በመተው ወደ ደማስቆ እየሸሸ መሆኑን አለም አቀፍ ሚዲያዎች በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።

ደማስቆን በተለያየ አቅጣጫ የከበበው የተቃዋሚ ሀይል በዙሪያው የሚገኙት ካናከር፣ ፓሊሜራንና ከእስራኤል ጋር የሚያዋስነውን የሶርያ ድንበርን መቆጣጠራቸው ተገልጿል። የሆምስ ከተማ በተቃዋሚዎች እጅ ከወደቀ ከዚህ በኃላ የአሳድ ኃይል የሚቀረው ዋና ከተማዋ ደማስቆ ብቻ ይሆናል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Dec, 11:07


📌 እንድታውቁት...

በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ላለባቸው ሕጻናት እና አዋቂዎች ነፃ የቀዶ ሕክምና አገልግሎት በመደበኛነት እየተሰጠ እንደሚገኝ ተገልጿል።

- ሀሩን ሚድያ ህዳር 28/2017

በአዲስ አበባ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለከተማ ዘነበ ወርቅ አካባቢ በሚገኘው በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ላለባቸው ሕጻናት እና አዋቂዎች ነፃ የቀዶ ሕክምና አገልግሎት በመደበኛነት ሳምንቱን ሙሉ እየተሰጠ እንደሚገኝ ሆስፒታሉ አስታውቋል።

የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከስማይል ትሬን ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ላለባቸው ሕጻናት እና አዋቂዎች ነፃ የቀዶ ሕክምና አገልግሎት በመደበኛነት ሳምንቱን ሙሉ እየሰጠ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ችግር Cleft lip እና Cleft palate ያለባችሁ በመሉ በ0948898284 በመደወል ወይም ወደ አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመሔድ መመዝገብ እንደሚችሉም ተመላክቷል።

ከአዲስ አበባ ውጭ ለሚመጡ ታካሚዎች የትራንስፖርት እና የምግብ አገልግሎት እንዲሁም ለሚያድሩት የአልጋ (መኝታ) ወጪ እንደሚሸፈን ከሆስፒታሉ ማህበራዊ ትስስር ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Dec, 08:34


ኢስላም በሀገር ልማትና በሰላም ግንባታ ላይ የንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ መጅሊስ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ HarunMedia
https://youtu.be/A4he_Wl7aJg

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

07 Dec, 08:29


ዶ/ር ሙሀመድ ሳሊህ ጀማል የሸገር ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ሕዳር 28/2017፣ አዲስአበባ

የሸገር ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት በዛሬው ዕለት መደበኛ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስአበባ ኡማ ሆቴል እያካሄደ ይገኛል።

በጉባኤው ዶ/ር ሙሀመድ ሳሊህ ጀማልን የሸገር ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ዋና ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።

የቀድሞ የሸገር ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ፕረዚዳንት የሆኑት ሼይኽ ጣሂር አብዱልቃድር በቅርቡ የኦሮሚያ መጅሊስ ምክትል ፕረዚዳንት መሆናቸው ይታወሳል።

የሸገከ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት እያከሄደ የሚገኘው መደበኛ ሁለተኛ ጉባኤው የተለያዩ ጉዳዮችን በማንሳት የሚቀጥል ሲሆን ሀሩን ሚዲያ ተከታታይ መረጃዎችን ወደናንተ ያደርሳል!

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Dec, 18:07


አላማቸው የበሽር አላሳድን መንግስት መገርሰስ መሆኑን የሶሪያ ተቃዋሚ ሀይሎች መሪ ገለፀ!

- ሀሩን ሚድያ ህዳር 27/2017

በሶሪያ በበሽር አላሳድ መንግስት ላይ መጠነሰፊ ጥቃት እየፈፀሙ የሚገኙት ተቃዋሚ ሀይሎቹ አላማቸው የፕሬዚዳንት ባሻር አል-አሳድን አገዛዝ መገርሰስ መሆኑን የቡድኑ መሪ አቡ መሐመድ አል-ጆላኒ ተናግረዋል።

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ረሲብ ጠይብ ኤርዶጋን በበኩላቸው ዛሬ ከጁምአ ሶላት በኋላ ባስተላለፉት መልዕክት ኢድሊብ፣ ሆምስና፣ ሀማ ከተሞች በሶሪያ ተቃዋሚ ሀይሎች ነጻ መውጣታቸው ገልፀዋል።

ኤርዶጋን አክለውም ከእነዚህ ግዙፍ ከተሞች በተጨማሪ ተቃዋሚ ሀይሎች ወደ ደማስቆ ግስጋሴያቸውን መቀጠላቸውን አንስተዋል።

የበሽር አል አሳድ መንግስት ከህዝቡ እና ተቃዋሚ ሀይሎች ጋር ንግግር እንዲያደርግ በተደጋጋሚ ቢጠየቅም ለመነጋገር ፈቃደኛ ባለመሆኑ ይህ ጦርነት እንደተከሰተና ለጦርነቱ መጀመር የበሽር አል አሳድ መንግስት ተጠያቂ መሆኑን ኤርዶጋን ተናግረዋል።

ጦርነቱ ንጹሀንን እንዳያጠቃና የሶሪያ ህዝብ ላይ የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝና በሶሪያ የተረጋጋና ህዝብ የሚቀበለው መንግስት ይመሠረት ዘንድ የበኩላችን እንወጣለን ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ከጁምአ በኋላ መልዕክታቸውን ማስተላለፋቸውን አልጀዚራ እና የተለያዩ ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሀን ዘገባ ያመለክታል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Dec, 17:51


https://youtu.be/rMPkc65vXec?si=Dqq57cg53xWkHUbw

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Dec, 15:34


ኢማሙ ናፊዕ መርከዝ 46 የቁርኣን ኺፍዝ ተማሪዎችን አስመረቀ!

- ሀሩን ሚድያ ሕዳር 27/2017

በሱማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው ኢማሙ ናፊዕ የቁርኣን ንባብ እና ጥናት ማዕከል በመጀመሪያ ዙር ያስተማራቸውን 46 ተማሪዎች ማስመረቁ ተገልጿል።

በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ ኡለማዎች፣ ኡስታዞች፣ የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦች የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች መገኘታቸውም ታውቋል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Dec, 12:35


የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተደጋጋሚ የሚያወጣቸው የስራ ማስታወቂያዎች አሁንም ሙስሊሙን ያገለሉ መሆናቸው ተገለጸ።

ሀሩን ሚዲያ፣ ህዳር 26/2017

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሙስሊም ማህበረሰብ እሴት፣ እምነት እና ስርዓትን ያላማከለ የስራ ማስታወቂያዎች ማውጣቱን አሁንም መቀጠሉ ተገልጿል።

አየር መንገዱ በሚያወጣቸው የስራ ማስታወቂያዎች እንደ መወዳደሪያ ህግ ከተቀመጡ ጉዳዮች መካከል ሚኒስከርት (አጭር ጉርድ) መልበስ እና ጸጉራቸውን መልቀቅ ወይም ጸጉራቸውን አለመሸፈን እንደሆነ በተደጋጋሚ ከሚያወጣቸው የስራ ማስታወቂያዎች ላይ በግልጽ ያስቀምጣል።

በዚህም የሀገሪቱን ግማሽ ህዝብ ቁጥር የሚሸፍነው ህዝበ ሙስሊም ከተቋሙ እንዲገለል ምክንያት ሁኗል። ዩናይትድ ኪንግድምን ጨምሮ የሙስሊሙ ቁጥር አናሳ በሆነባቸው የዓለም ሀገራት አየር መንገዶች ሂጃብ ለብሰው የሚሰሩ አስተናጋጆች እንዳሏቸው ይታወቃል።

የሀገሪቱን ግማሽ ያህል ህዝቧ ሙስሊም በሆነባት ኢትዮጵያ ግን ሙስሊሞች ከእምነታቸው ጋር የሚቃረን ህግ በማውጣት አየርመንገዱ የሙስሊሞችን ሀይማኖታዊ መብት ያላማከለ ተደጋጋሚ የስራ ማስታወቂያዎችን ማውጣቱ አሳዛኝ መሆኑን ማስታወቂያውን የተመለከቱ ሙስሊሞች አስተያየታቸውን ለሀሩን ሚዲያ ገልጸዋል።

በመሆኑም የኢ/እስ/ጉ/ጠ/ም/ቤትን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚያወጣቸውን ሙስሊሙን ያገለሉ እና ኢፍትሀዊ ህጎች እንዲስተካከል ይታገል ዘንድ ተጠይቋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Dec, 11:55


በየካ ክፍለ ከተማ የሙስሊሙ ቅርስ የሆነው የወሌ ሙሀመድ የመስጂድ አካል የሆነ ቤት በአፍራሽ ግብረ ሀይል እየፈረሰ መሆኑ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ሕዳር 27/2017

አዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ አቧሬ አካባቢ ወይም ቤተ መንግስት ጀርባ ላይ በአድዋ ጦርነት ጀብድ ለሰሩት ወሌ ሙሀመድ በአፄ ሚኒሊክ በሽልማት መልክ መኖሪያ ቤትና መስጅድ ተበርክቶላቸው ነበር።

በዚህም በአዲስ አበባ የመጀመሪያ መስጅድ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ቤቱና መስጅዱ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ሀብት ከሙስሊም ውጭ ለሆነውም የጋራ ቅርስ በመሆን መመዝገቡ ተገልጿል።

ከዚህ ቀደም ቤቱ ይታደስልን የሚል ጥያቄ መጅሊሱ በተደጋጋሚ ማቅረቡ የተገለፀ ሲሆን እስካሁን ምላሽ አለማግኘቱ ተነግሯል። ዛሬ በጠዋት አፍራሽ ግብረ-ሀይል የቤቱን ከፊል ማፍረሱን የክፍለ ከተማው መጅሊስ ለሀሩን ሚዲያ ገልጿል።

ይህ ታሪካዊ ቅርስ የክፍለ ከተማው መጅሊስም ሆነ ሌላ የሚመለከተው ተቋም በማያውቀው ሁኔታ እንዲፈርስ መደረጉ አግባብ ያልሆነ አካሄድ መሆኑን የክፍለ ከተማው መጅሊስ ገልጿል።

በመሆኑም የሚመለከተው አካል አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጠው ተጠይቋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Dec, 09:24


በወልድያ እና አካባቢው ትኩረት አድርጎ የሚሰራ "አማና ኢስላማዊ ማህበር" የተሰኘ የበጎ አድራጎት ማህበር ተመሰረተ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ሕዳር 27/2017

በወልዲያ አጠቃላይ በሰሜን ወሎ ዞን ባሉ ኢስላማዊ ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ ለመስራት ያለመ "አማና ኢስላማዊ ማህበር" የተሰኘ የበጎ አድራጎት ማህበር መመስረቱ ተገልጿል።

"አማና ኢስላማዊ ማህበር" በሚል መጠሪያ በወልድያ እና አካባቢዋ ልጆች የበጎ አድራጎት ማህበር የተመሰረተ ሲሆን ህዳር 24/2017 ዓ.ል ከፌደራል መጅሊስ ሙሉ የእውቅና ፈቃድ (ሰርተፊኬት) ተሰጥቶታል።

በመሆኑም ማህበሩ ከዚህ በሗላ በዲን እና ተያያዥ ጉዳዮች ዘርፈ-ብዙ ስራዎችን ለመስራት አልሞ የተመሰረተ በመሆኑ ፈቃድ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በይፋ ወደ ስራ ይገባል የተባለ ሲሆን ሁሉም ሙስሊም ማህበረሰብ ከማህበሩ ጎን በመቆም ማህበሩን እንዲያግዝ ጥሪ ቀርቧል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

06 Dec, 06:49


በስልጤ ዞን አሊቾ ዊሪሮ ወረዳ ቃዋቆቶ ከተማ የኢብኑ አባስ መስጂድ ግንባታን በተመለከተ የአባቶች መልዕክት

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፣ ህዳር 26/2017 ዓ.ል

በስልጤ ዞን አሊቾ ዊሪሮ ወረዳ ቃዋቆቶ ከተማ ኢብኑ አባስ መስጂድ ግንባታን በተመለከተ አባቶች መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በመልዕክታቸውም በ1,400 ካሬ ያረፈው G+1 መስጂድ ለሴቶች 700ካሬ እንዲሁም ለውዱዕ ማድረጊያ 200 ካሬ የሸፈነ ግዙፍ ግንባታ መሆኑን ጠቅሰው
ግንባታውን ኡስታዝ መሀመድ ፈረጅ አስተባባሪነት በአሜን ሆስፒታል ባለቤት አቶ መሀመድ ሹኩር መሰረቱ የወጣ ሲሆን
የአካባቢው ሙስሊም ማኅበረሰብ 250 ሲኖትራክ ድንጋይ በጉልበቱ ፈልጦ በማቅረብና በገንዘብም መዋጮ አድርጎ ግንባታው 55% ማድረሳቸውን አስረድተውናል።

እስከ አሁን ባለው ወደ 25 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደወጣና ቀሪ ግንባታውን ከነ ሚናራውና ቁባው ለመጨረስ ከ25 እስከ 30 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግም የመስጂዱን ግንባታ የሚከታተለው መሀንዲስ የገለፀልን ሲሆን ይህ ገንዘብ ደግሞ ከአቅማችን በላይ ስለሆነብንና እንደሚታወቀው አካባቢው ደጋ ከመሆኑም አንፃር ውጭ ላይ መስገድ በጣም አስቸጋሪ በመሆኑ በመላው አለም የምትገኙ ሙስሊም ወንድም እህቶች አግዙን በማለት አባቶቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

እንዲሁም ኡስታዝ መሀመድ ፈረጅ፣ ሼኽ አ/ሰላም አንዋር እና ኡስታዝ ባህሩ ኡመር የመስጅዱን ግንባታ ሂደት ያለበትን ደረጃ የጎበኙ ሲሆን እነሱም ሙስሊሙ ኡማ ለዚህ መስጂድ ግንባታ የአቅሙን በማዋጣት ግንባታው እንዲጠናቀቅ እንዲያግዝ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

ማገዝ ለምትፈልጉ።፦
የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000437833145

ዳሽን - 2945525546811

ስልክ
+251911804747 +251902040746
+251902040746
+251902040746
መጠቀም ይችላሉ።

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ በስፍራው ተገኝቶ ያጠናቀረው የቪዲዮ ዘገባ በተከታይ ወደናንተ ይደርሳል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

03 Dec, 18:53


አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ዓውደ ርዕይ ብዙ የቴክኖሎጂ እውቀቶች ልምድ የተጋሩበት እንደነበረ ዶ/ር ፎዚያ አሚን ገለፁ፡፡

- ሀሩን ሚድያ ሕዳር 24/2017

በኢትዮጵያ የተዘጋጀው የተለያዩ ሀገራትን ያሳተፈው አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ዓውደ ርዕይ ንቃት የተሞላበትና ብዙ የቴክኖሎጂ እውቀቶች ልምድ የተጋሩበት እንደነበረ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ፎዚያ አሚን ገለፀዋል፡፡

ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዝየም ሲካሄድ የቆየው ከ14 ሀገራት በላይ የተሳተፉበት 41 ቴክኖሎጂዎች ለእይታ የቀረቡበት አለም አቀፍ ዓውደ ርዕይ በሀካቶን ውድድር አሸናፊዎች ሽልማት ተጠናቋል፡፡

በፕሮግራሙ መዝጊያ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ፎዚያ አሚን ኢትዮጵያ የደቡብ ትብብር አባል ሀገራትን ያሳተፈ የመጀመሪያውን አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ዓውደ ርዕይ በዘርፉ ላይ ለተሰማሩት የቴክኖሎጂ ተዋናዮች ትልቅ አቅም መፍጠሩን ገልፀዋል፡፡

የቴክኖሎጂ ልማት የተናጠል ስራ አይደለም ያሉት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አባል ሀገራቱ ዘርፉን ለማሳደግ የፈጠሩት ምቹ የትብብር ስነምህዳር ለሁሉም ሀገራት ከስራ ፈጠራና ከቴክኖሎጂ ማበልፀግ ባሻገር የትብብርና የኢኮኖሚ እድገት ላይ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ያደርጋል ብለዋል፡፡

እንዲህ ያሉ ዓውደ ርዕዮች ተጠናክረውና ተናበው በሄዱ ቁጥር አባል ሀገራቱ የቴክኖሎጂ አብዮት ፈጣሪዎችና ተጠቃሚዎች መሆን እንደሚችሉ ካየናቸው ውጤቶች ማረጋገጥ እንደሚቻል አንስተዋል፡፡

የደቡባዊ ትብብር ድርጅት (OSC) ዋና ጸሃፊው መንሱር ቢን ሙሳላም በትምህርትና ክህሎት፣ በፋይናንስ ቴክኖሎጂ፣ በዘላቂ ትራንስፖርት፣ በንጹህና ተመጣጣኝ ኃይል፣ በዘላቂ ግብርና እና በተቀናጀ ጤና አገልግሎት ዘርፍ ላይ የተካሄደው ዓውደ ርዕይ ላይ የተፈጠረው የቴክኖሎጂ እውቀት ሽግግርና የነበረው ሁነት ሰኬታማ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የተካሄደው ዓውደ ርዕይ በሁለት አመት አንድ ጊዜ የሚካሄድ በመሆኑ በጋራና በትብብር የምንሰራቸው ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሁሉም የቴክኖሎጂ ተዋናዮች የመፍጠር አቅማቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡

በደቡብ ትብብር ድርጅት የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዘርፍ ሃላፊ ዶ/ር ሹመቴ ግዛው ዓውደ ርዕዩን በትብብር አባል ሀገራቱ የተገኙ የቴክኖሎጂ እውቀቶችን በማጋራት በቀጣይ አብሮ መስራት የሚቻልበትን ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል፡፡

በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዝየም ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የቴክኖሎጂ ዓውደ ርዕይ ከፍተኛ አመራሮችና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት የሀካቶን ወድድር አሸናፊዎች ሽልማት በመስጠት የመዝጊያ ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

03 Dec, 18:03


ህጋዊ ካርታ ያለው ሱመያ መስጂድ በፍርድ ቤት እንዲነሳ ያለአግባብ ውሳኔ ለምን ተሰጠበት?
https://youtu.be/d5MgooqBajc?si=Ej3qbSDlZs6vxoa1

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

03 Dec, 17:58


የወራቤ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የኩላሊት እጥበት (ዲያሌሲስ) አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ ፣ሕዳር 24/2017፣ደቡብ ስቱዲዮ

የወራቤ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የኩላሊት እጥበት (ዲያሌሲስ) አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገልጿል።

የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር ካሊድ ሸረፋ እንደገለፁት አገልግሎቱን ለማስጀመር ከማሽን ግዢ፣ ማሽን ተከላና የዘርፉን ሰብ-እስፔሻሊስት ሀኪም ማፈላለግ እንዲሁም ሌሎች ባለሙያዎችን ማሰልጠንን ጨምሮ ቅድመ ዝግጅቱ ጊዜ መውሰዱን አስታውሰዋል፡፡

የኩላሊት እጥበት አገልግሎት በቀላሉ እንደማይገኝ በመግለጽ የአገልግሎቱ መጀመር የበርካቶችን እንግልት የሚቀንስና እፎይታን የሚሰጥ መሆኑን አንስተዋል፡፡

አገልግሎቱ በአግባቡ እንዲሰጥና ቀጣይነቱ እንዲረጋገጥም ተቋሙ የተቻለውን ሁሉ እንደሚያደርግ ገልፀው የክፍሉ ባለሙያዎች በትጋት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ  ማሳሰባቸውን ሆስፒታሉ አስታውቋል።

አገልግሎቱን በዘላቂነት ለማቅረብ የሕክምና ቁሳቁስ ስለሚያስፈልግ የህብረተሰቡ፣ የባለሀብቱ፣ የዳያስፖራው እና የባለድርሻ አካላት ድጋፍ  እንደሚያስፈልግም ሆስፒታሉ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባሰራጨው መረጃ አመላክቷል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

03 Dec, 15:49


የሶርያ ታጣቂዎች ከአመታት በኃላ ድንገተኛና መጠነ ሰፊ ነው በተባለው ጥቃታቸው በርካታ አካባቢዎችን ከሶርያው የበሻር አል አሳድ መንግስት መንጠቃቸው ተገልጿል

"በሶሪያ ድጋሚ የተከሰተውን ጦርነት ለማስቆም ከአጋሮቻችን ጋር እየሰራን ነው"

- የኳታር ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

ሀሩን ሚዲያ፣ ህዳር 24/2017

ባለፈው ረቡዕ የሶሪያ ተቃዋሚ ሀይሎች በፈጸሙት ያልተጠበቀ እና መጠነ ሰፊ ጥቃት የሶርያ ሁለተኛ ግዙፍ ከተማ የሆነችውን አሌፖ ከተማን ጨምሮ በርካታ ቦታዎችን እየተቆጣጠሩ ይገኛሉ።

በቱርክ እንደሚደገፉ የሚነገርላቸው ተቃዋሚ ሀይሎች ከበሽር አልአሳድ ጦር ጋር ከፍተኛ ውጊያ እያደረጉ ይገኛሉ። በመጀመሪያ የድንገተኛ ጥቃታቸው የአሌፖን በርካታ ክፍሎች በሶስት ሰአት ብቻ እንዳስለቀቁ ተነግሯል። በአሁኑ ሰአት ስትራቴጂ ከተማ የሆነቸው ሀማን ለመያዝ ውጊያ በማድረግ ይገኛሉ።

በዚህም ከ2020 በኋላ ረገብ ብሎ የነበረው የሶሪያ ጦርነት ድጋሚ ያገረሸ ሲሆን ሀገራት የተኩስ አቁም እንዲደረግና ታጣቂ ሀይሎች ወደ ሰላም እንዲመለሱ እየጠየቁ ይገኛሉ።

የኳታር ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሶሪያ የተቀሰቀሰውን ውጊያ ለማስቆም በቀጠናው ከሚገኙ አጋሮቻችን ጋር መፍትሔ በማፈላለግ እየሰራን ነው ብለዋል።

የበሻር አል አሳድ አጋር የሆኑት ራሺያና ኢራን በቅርቡ በገጠሟቸው ጦርነቶች ማለትም በዩክሬንና በእስራኤል ጦርነቶች መጠመዳቸው የበሻር አል አሳድ ጦር ያለ አጋዥ እንዲቀር እንዳደረገው ተነግሯል። እንዲያም ሁኖ የሁለቱ ሀገራት የአየር ኃይል ድጋፍ የታጣቂዎችን የይዞታ ከተሞች የደበደበ ሲሆን የበርካታ ሰላማዊ ህይወትም ተነጥቋል።

ጦርነቱ አሁንም የቀጠለ ሲሆን ሀገራት የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ እየወተወቱ ይገኛሉ።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

03 Dec, 12:24


https://youtu.be/r58JUrIv4Hc?si=0CG9rUemwE1-0nZi

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

03 Dec, 12:03


ህጋዊ ካርታ ያለው ሱመያ መስጂድ በፍርድ ቤት እንዲነሳ ያለአግባብ ውሳኔ ለምን ተሰጠበት?

በሸገር ከተማ በለገጣፎ ለገዳዲ ክፍለ ከተማ በደንበል ጣፎ ወረዳ ሮዚታ ሪል ስቴት አካባቢ የሚገኘውና በ2014 ዓ.ል ህጋዊ  ካርታ የተሰጠው ሱመያ መስጂድ በተለያዩ ምክንያቶች የመስጂዱ ካርታው እንዲመክን ያለአግባብ በፍርድ ቤት ውሳኔ ተሰጥቶበታል።

- ሀሩን ሚድያ በለገጣፎ ለገዳዲ በመገኘት ከመስጂዱ ኮሚቴዎች እና ከለገጣፎ ለገዳዲ ክፍለከተማ መጅሊስ እና ከክርስትና እምነት ተከታዮች ጋር መስጂዱን  በተመለከተ ያደርግነው ልዩ ቆይታ ዛሬ ምሽት ይጠብቁን።

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

02 Dec, 19:41


https://youtu.be/FKLv0tImQfc?si=U8gC7_XMoXeZt5Lb

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

02 Dec, 18:23


"ለዚህ ደረጃ ያበቃኝ የወላጆቼ በተለይ የእናቴ ዱአ ነው"

ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሳቦም ኤልያስ ኩመል

ሀሩን ሚድያ፣ ሕዳር 23/2017

በሀገረ አሜሪካ በተካሄደ ኢንተርናሽናል የማርሻል አርት ፌስቲቫል ውድድር 1 ወርቅ 2 ብር በማምጣት የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ከፍ ካደረገው ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሳቦም ኤልያስ ኩመል ጋር የሀሩን ሚድያ ባልደረባ ሲራጅ ሙሰማ ስለውድድሩ እና ስለማርሻል አርት ምንነት አጠቃላይ ቆይታ አድርጎል።

ሀሩን ሚድያ፦ ሳቦም ወደ ማርሻል አርት ስፖርት እንዴት ገባክ?

ሳቦም ኤልያስ ኩመል፦ ወደ ማርሻል አርት ስፖርት የገባሁት በልጅነቴ ነው ድብድብ እወድ ነበር ወደ ማርሻል አርት ከገባሁ ጀምሮ ግን ስነምግባርን አስተምሮኛል።

ሀሩን ሚድያ፦ ማርሻል አርት ስፖርት ላይ ሙስሊም መሆንክ የጠቀመክ ነገር?

ማርሻል አርት ስፖርት ከሚያስተምራቸው ዋና ነገሮች ውስጥ ስነ ምግባርን እና ጠንካራ ሰው መሆን ነው ኢስላም ውስጥ የሰው ልጅ ስነምግባር እንዲኖረው እና ሙእሚን ጠንካራ እንዲሆን ይመክራል ያ በጣም ትልቅ ትምህርት ሰጥቶኛል።

ወደ ማርሻል አርት አሰልጣኝነት እንዴት ልትገባ ቻልክ?

ጭራሽ አሰልጣኝ መሆንን አስቤ አላውቅም ነበር 1996 አስተማሪያችን የነበረው ሳቦም ሀያቱ ሀሰን ከሀገር ውጭ በመውጣቱ ምክንያት ማሰልጠን ጀመረኩኝ ከዛም ከ1999 ጀምሮ በአሰልጣኝነት ህይወት ውስጥ አለሁ። የኔ ክለብ ከዛን ጊዜ ጀምሮ 22 ጊዜ ሻምፒዮን መሆን ችለናል።

ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሳቦም ኤልያስ ኩመል የጥበብ መንገድ የሚል ማርሻል አርት ስፖርት ላይ የሚያጠነጥን መፅሀፍ ፅፈሀል፣ ለመጻፍ ምን አነሳሳህ?

ባለህበት ዘርፍ ላይ የሆነ ነገር ማብርከት አለብህ፣ ለዛም ነው መፅሀፉን የፃፍኩት መፅሀፉን ስፅፍ ፓለቲካ የፃፍኩኝ እስኪመስል ድረስ ዘርፉ ላይ ካሉ ሰዎች ግጭት አጋጥሞኛል። በመጨረሻም አልሀምዱሊላህ በ2015 ዓ.ል ለምርቃት በቅቷል። መፅሀፉንም ስለማርሻል አርት ማወቅ የሚፈልግ ሰው እንዲያነብ እመክራለው።

ስለኢንተርናሽናል ውድድሮች እንመጣ እንዴት ገባህ?

እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ2015 አካባቢ በሀገር ውስጥ ስወዳደር የተመለከተኝ ሰው ሄጄ እንድወዳደር ግብዣ አቀረብልኝ ከዛም በ2018 የመጀመሪያ የውጭ ውድድርን በማድረግ ሁለት የብር ሜዳሊያዎችን ማግኘት ችያለው፣ ከዛም በኮሮና ምክንያት ስላልተካሄደ በ2022 በተካሄደ ውድድርም ሜዳሊያ ውስጥ መግባት ችያለው።

የዘንድሮውን ውድድር እንዴት ነበር?

የተካፈልኩት በ3 ውድድሮች ላይ ነው በመጀሪያ ደረጃ የፖተርን ውድድር የወርቅ ሜዳልያ፤በነፃ ፍልሚያ ውድድር የብር ሜዳልያ፤ በሁለተኛ ደረጃ የፖተርን ውድድር የብር ሜዳልያ በማስመዝገብ የሀገሬ ስም ከፍ ብሎ እንዲታይ አድርጌያለው አልሀምዱሊላህ።

ከኢንተርናሽናል መድረኮች ምን ትምህርት አገኘህ?

ሀገራችን ላይ ያለው አሰራር በልምድ ነው ያለነው እና ወደሲስተም መግባት እንዳለብን ትልቅ ትምህርት ሰጥቶኛል የኛ ሀገር ባለሙያዎች፣ የመንግስት አካላት ሄደው ውድድሮችን በመመልከት ልምድ እንዲወስዱ እመክራለው።

ማስተላለፍ ምትፈልገው መልዕክት ካለ እድል እንስጥህ?

በመጀመሪያ አላህን አመሰግናለው በመቀጠል እዚህ ደረጃ እንድደርስ ያደረገኝ የወላጆቼ ዱአ ነው በተለይ የእናቴ ዱአ ነው። አቀባበል ላደረጉልኝ የሙያ አጋሮቼ ምስጋና ማቅረብ እፈልጋለው ይሄ ስራ የፌደሬሽን መሆን ነበረበት። ለሀሉም ለኔ እዚህ መድረስ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት በተለይ ለዲኖ አሊ ምስጋና አቀርባለው። ሀሩን ሚድያም እንግዳ አድርጋችሁ ስለጋበዛችሁኝ አመሰግናለው።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

02 Dec, 16:44


የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ጠቅላላ ጉባዔውን አካሄደ!

- ሀሩን ሚድያ ሕዳር 23/2017

ከተመሠረተ 3 አመታትን ያስቆጠረውና በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሙስሊም ተማሪዎችን የጋራ ችግሮች ጀመዓዎችን በህብረት በማቆም እንዲፈቱ እያደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የዩኒቨርሲቲ ጀመዓ አሚሮች በተሰባሰቡበት ከህዳር 20/2017 ዓ.ል እስከ ህዳር 22/2017 ዓ.ል የጠቅላላ ጉባዔውን በአዲስ አበባ ማካሄዱ ተገልጿል::

ህብረቱ ከፌደራል መጅሊስ እውቅና ያገኘ ሲሆን በጉባዔው ባለፉት 3 አመታት የሰራቸውን ስራዎች ገምግሞ የወደፊት አቅጣጫውን መቀመጡ ተገልጿል። በጠቅላላ ጉባዔው ላይ በተለይም ከመብት ትግል እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ የተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎች ቀርበው የመፍትሔ አቅጣጫም ተቀምጧል::

በመጨረሻም ጉባዔው የተለያዩ አመራሮችን መርጦ መጠናቀቁን
ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

02 Dec, 16:10


https://youtu.be/Cl91efdBtOU?si=gTlDdsQ072DUQGyw

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

02 Dec, 13:31


በኢማሙ አህመድ መስጅድ የነፃ ህክምና አገልግሎት መሰጠቱ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ሕዳር 23/2017

የኢትዮጵያ ሙስሊም ጤና ባለሙያዎች ማህበር 7ተኛ ዙር ነፃ የህክምና አገልግሎት በአዲስ አበባ አለም ባንክ አካባቢ በሚገኘው በኢማሙ አህመድ መስጂድ ውስጥ በትላንትናው ዕለት ያካሄደ ሲሆን ከ400 በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል።

በአገልግሎት ላይ 29 የጤና ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ስፔሻሊስቶች፣ ነርሶች፣ ጠቅላላ ሀኪሞች እና ፋርማሲስቶች ተገኝተዋል። የኢማሙ አህመድ መስጂድ ስራ አስኪያጅ እና ኻዲሞች ላደረጉት አስተዋፅኦ እና በነፃ ህክምናው ላይ ለተሳተፉ የጤና ባለሙያዎች ማህበሩ ምስጋናውን አቅርቧል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

02 Dec, 12:38


ጋዜጠኛ ሰዒድ ኪያር የሀሩን ሚዲያ ሶስቱንም ስቱዲዮዎች የጎበኘ የመጀመሪያው ሰው ሁኗል። ከዚህ በፊት የአሜሪካውን እና የአዲስ አበባውን ስቱዲዮ የጎበኘ ሲሆን አሁን ደግሞ የሀላባውን ስቱዲዮ ጎብኝቷል።

የመጨረሻ ጉብኝቱ በነበረው በሀላባ ስቲዲዮ ከባልደረባችን አብዱልመጅድ አሕመድ ጋር ልዩ ቆይታ አድርጓል።

''ሶስቱንም የሀሩን ሚዲያ ስቲዲዮ በመጎብኘቴ እድለኛ ነኝ'' ይላል ሰዒድ ኪያር

ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ይጠብቁን !

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

02 Dec, 08:03


ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጅዑን

ታላቁ አሊም ሼይኽ አብዱረሂም አቡበከር ወደ አኼራ መሻገራቸው ተሰማ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ሕዳር 23/2017

በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ኢልምን በማስተማር ረጅም ዓመት ያገለገሉት ታላቁ አሊም ሸይኽ አብዱረሂም አቡበከር በትላንትናው ዕለት ወደ አኼራ መሻገራቸው ተሰምቷል።

ታላቁ አሊም ሸይኽ አብዱራሂም አቡበከር በሳዑዲ አረቢያ በመዲና ዩንቨርስቲ ትምህርታቸውን በማጠናቀቅ በባሌ መድረሳ በማቋቋም በርካታ አሊሞችን ማፍራታቸው ታውቋል። የታላቁ አሊም የቀብር ስነስርዓት በትላንትናው ዕለት በሺዎች የሚቆጠሩ የባሌ ከተማ ነዋሪዎች በተገኙበት መፈፀሙን ከኑር ቲቪ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

- ሀሩን ሚድያ ለእሳቸው አላህ ጀነተል ፊርዶስን እንዲወፍቃቸውና ለመላው ህዝበ ሙስሊም ለወዳጆቻቸው እና ለዘመዶቻቸው መፅናናትን ይመኛል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

01 Dec, 18:44


የአዳማ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት 6ተኛ የስራ ዘመን 5ተኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት አካሄደ።

- ሀሩን ሚድያ ሕዳር 22/2017

ሀሩን ሚድያ በጉባኤው ላይ ምን ምን ሀሳቦች ተነሱ ሚለውን የአዳማ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ፀሀፊ የሆኑትን ሼይኽ አብዱራሂምን ጠይቀን ተከታዩን ምላሽ ሰጥተውናል።

በጉባኤው ላይ የ2016 የስራ አፈፃፀም እና የ2017 እቅድ ቀርቦ ውይይት መደረጉን ገልፀውልናል።

የከተማው መጅሊስ ህንፃ ግንባታ ማካሄድ፣ በአዳማ ከተማ ከተማ የሚገኙ የክፍለከተማ የወረዳ መጅሊሶች እና መስጂድ ኮሚቴዎችን የማጠናከር ስራ፣ ቁርኣን ለሰላም በሚል ትልቅ ኮንፈረንስ መካሄዱ፣ ሌሎችም ስራዋችም በ2016 የተሰሩ ዋና ዋና ተግባራት መሆናቸውን ተናግረዋል።

በ2017 ምን ለመስራት አቀዳችሁ ብለን ለጠየቅናቸውን ጥያቄም ከከተማው አዲስ ፕላን ጋር በተያያዘ ሚነሱ መስጂዶች እንዳይነሱ ከሚመለከተው አካል ጋር ውይይት ለማድረግ መታቀዱን፣ ህብረተሰቡ የህገ መጅሊሱን አስፈላጊነት እንዲረዳ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን ለመስራት ማሰባቸውን ከሎጀሲቲክ እና ከበጀት ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶች እንደሚደረጉና ሙስሊሙ ማህበረሰብ በሸሪዓዊ እውቀት እና በአካዳሚክ እውቅት የበቃ ለማድረግ ስራዎች እንደሚሰሩም ገልፀዋል።

በጉባኤው ላይ የኦሮሚያ መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ ኡለማዎች፣ ኡስታዞች፣ የጠቅላላ ጉባኤው አባላት መገኘታቸውን ከአዳማ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

01 Dec, 18:13


በፉሪ ክፍለከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በሙስሊም መካነ መቃብር ችግሮችና የመፍትሄ ሀሳቦች ላይ ውይይት ተካሄደ

- ሀሩን ሚድያ ሕዳር 22/2017

በሸገር ሲቲ ፋሪ ክ/ከተማ እ/ጉ/ም/ቤት በሙስሊም መካነ መቃብር ችግሮችና የመፍትሄ ሀሳቦች ዙሪያ ጥናት ቀርቦ ከባላድርሻ አካላት ጋር ውይይት መካሄዱ ተገልጿል።

የውይይት መድረኩን የክ/ከተማ እ/ጉ/ም/ቤት ዋና ሰብሳቢ ዶ/ር ሙሀመድሳኒ ቲጃኒ በእንኳን ደህና መጣችሁ መክፈቻ ንግግር የከፈቱ ሲሆን በመድረኩ ላይ የሸገር ሲቲ እ/ጉ/ከፍተኛ ም/ቤት ዋና ጸሓፊ ኡስታዝ የህያ አባ ጀበል የፉሪ ክ/ከተማ መጅሊስ ሥራ አስፈጻሚ አባላት የወረዳና መስጅድ መዋቅሮች፣ በክ/ከተማ ውስጥ የሚገኙ እድር አመራሮችና ሚዲያ ተሳታፊ ሆኑዋል።

በመካነ መቃብር ችግሮችና ቀጣይ የልማት አቅጣጫ ዙሪያ የክ/ከተማው እስልምና ጉዳዮች ዋና ጸሓፊ ኡስታዝ ስልጣን ኡስማን ጥናቱ ያቀረቡ ሲሆን፣ ሥፍራዎቹ ካለባቸው መሰረታዊ ተግዳራቶች መካከል:-

የጽዳት፣ የመካነ መቃብር ሥፍራዎች ጥበት፣ በክረምት ወቅት ሟቾችን ለመቅበር ውሃማና አመቺ አለመሆን፣ የአይካ መካነ መቃብር ድንጋያማና ለመቆፈር አስቸጋሪ የመሆን፣ የቦታ አጠቃቀም፣ ተቋማዊ የአስተዳደርና አሰራር ሰፊ ክፍተቶች፣ በውል የሚታወቅ የይዞታ ክልል አለመኖር፣ በመቃብር ቦታዎች ዙሪያ ባሉ ባለሃብቶችና ግለሰቦች የቀብር ይዞታ መጋፋት፣ ሥፍራዎቹ ድንበር ባለፈ ደን መሸፈንና ጅቦችና ሌሎች አራዊቶች ለሙታኑ ስጋት እስከ መሆን መደረሱ በጥናቱ ቀርቦ በስፋት ውይይት ተደርጎበታል።

በመድረኩ የተገኙት ኡስታዝ የህያ አባ ጀበል ባስተላለፉት መልእክት ሙስሊሙ ማህበረሰብ ለዘመናት ታግሎ ያቆያቸውን የቀብር ሥፍራዎች በጋራ ማልማት፣ መንከባከብና መጠበቅ አለበት ያሉ ሲሆን፣ ይህንን የማህበረሰቡን ትልቅ አጀንዳ በጥናት መልክ መፍትሄ ጭምር ላቀረበው የፉሪ ክ/ከተማ እስልምና ጉዳዮችን ምስጋና አቅርበዋል።

በተመሳሳይ መልኩ የፓናል ውይይቱን የክ/ከተማው እ/ጉ/ም/ቤት ም/ሰብሳቢ ኡስታዝ አዩብ ሙሀመድ የመሩ ሲሆን ከተሳታፊዎች በርካታ ሀሳቦች ተነስቶ ስፍራዎቹን በጋራ እቅድና ስትራቴጂ ለመጠበቅ፣ ለመንከባከብና ለማልማት ከስምምነት የተደረሰ ሲሆን ለአተገባበርና አፈጻጸም የብዙ ባላድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ስለሚጠይቅ ሙስሊሙ ማህበረሰብና የሚመለከተው አካል ሁሉ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የፉሪ ክ/ከተማ እ/ጉ/ም/ቤት ዋና ሰብሳቢ ዶ/ር ሙሀመድሳኒ ቲጃኒ በኩል ጥሪ ቀርቧል።

መጅሊሱ ለአንድ አመት ከሸገር መጅሊስ ጋር በመሆን ባደረገው ብርቱ ጥረት ለአመታት የጠፉ የበርካታ መስጅዶችና ወቅፍ ቦታዎች ኦርጅናል ካርታ ማግኘቱን በመድረኩ ለተሳታፊዎች አብስሮ የፓናል ውይይቱ መጠናቀቁን የፉሪ ክፍለከተማ መጅሊስ ያደረሰን መረጃ ያመላክታል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

13 Nov, 05:34


በደቡብ አፍሪካ ጁሀንስበርግ ከተማና አከባባዋ የሚኖሩ የሀላባ ተወላጆችና ወዳጆች ለሀላባ ኢንተርናሽናል ስቴዲየም ግንባታ ገቢ ማሰበሰብ ጀመሩ !

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፣ ህዳር 4/2017

በጆሃንስበርግ ከተማ እና አካባቢ የሚኖሩ እንዲሁም ከተለያዩ ሰፍራ የመጡ የሀላባ  ዞን ተወለጆችና እንዲሁም የከምባታ ዞን ተወላጆች በጋር ለሀላባ ኢንተርናሽናል ስቴዲየም ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አካሂደዋል::

ተሳታፊዎቹ የፕሮጀክቱ ፋይዳና ጠቀሜታ ዘርፈ ብዙ መሆኑን አንስተውም የተወያዩ ሲሆን ከኢትዮጲያ ወደ ደቡብ አፍሪካ የሚመጣውን የሀላባ ዞን ስቴዲየም ግንባታ ገቢ አሰባሰብ ኮሚቴን እንዴት እንደሚቀበሉም ተወያይተዋል።

የገቢ አሰበሰቡ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ቃል በመግባት መርኃ ግብሩን አጠናቀዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Nov, 18:51


''ደሜን በመስጠቴ ደሜ አይጎልም''ጥቅምትን ለየሲር ለናHarunmedia
https://youtu.be/ujrBxfTCZV0?si=8TvArU0UVciryaWK

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Nov, 18:45


እስራኤል ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባልነት እንድትሰናበት የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መጠየቁ ተገለፀ!

-በባለፈው ወር መጨረሻ ማሌዢያ እስራኤል በፍልስጤሞች ላይ
እያደረሰች በምትገኘው በደል ከተመድ እንድትሰናበት የሚጠይቅ ረቂቅ ሰነድ ለጠቅላላ ጉባኤው አቅርባ እንደነበር ይታወሳል፡፡

_ሀሩን ሚድያ ህዳር 3/2017

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋሂ አለም አቀፋዊ ህጎችን በተለያዩ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት እየጣሰች የምትገኘው ቴል አቪቭ ከአለም አቀፉ ተቋም መገለል አለባት ብለዋል፡፡

በተጨማሪም በመካከለኛው ምስራቅ የሚፈጸሙ የጦር ወንጀሎች እና የዘር ማጥፋቶች እንደጨመሩ በመግለጽ፥ አለም አቀፉ ማህበረሰብ የእስራኤልን ህገወጥ ተግባራት አይቶ እንዳላየ ከማለፍ ሊቆጠብ እንደሚገባ ነው ያስጠነቀቁት፡፡

ቃል አቀባዩ ይህን ያሉት ባሳለፍነው እሁድ እስራኤል በሶሪያ ዋና ከተማ ደማስቆ በፈጸመችው የአየር ጥቃት ንጹሀን መገደላቸውን ተከትሎ ነው፡፡

የአውሮፓ እና የአሜሪካ ያልተገደበ ድጋፍ እስራኤል በህገወጥ ተግባሯ እንድትገፋ አረንጓዴ መብራት ሰጥቷል ያሉት ቃል አቀባዩ፤ በፍልስጤም፣ ሊባኖስ እና ሶሪያ የሚደርሰው ያልተገባ የንጹሀን ግድያ እንዲቆም ጠይቀዋል፡፡

“በጽዮናዊው አገዛዝ ላይ ተግባራዊ እና ውጤታማ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባል፤ ይህም የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መጣልን፣ አገዛዙን ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ማባረርን ጨምሮ መሪዎቹን መከሰስ እና መቀጣትን ማካተት አለበት” ሲሉ ጥሪ አድርገዋል።

እስራኤል ከተቆጣጠረቻቸው የጎላን ኮርብቶች የተነሱ ናቸው የተባሉ የጦር አውሮፕላኖች በደማስቆ “ሳይዳ ዛይናብ” በተባለ አካባቢ በመኖርያ ህንጻ ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን የሶርያ መገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል፡፡

የእስራኤል ጦር እስካሁን ለጥቃቱ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡

በባለፈው ወር መጨረሻ ማሌዢያ እስራኤል በፍልስጤሞች ላይ እያደረሰች በምትገኘው በደል ከተመድ እንድትሰናበት የሚጠይቅ ረቂቅ ሰነድ ለጠቅላላ ጉባኤው አቅርባ እንደነበር ይታወሳል፡፡

በጋዛ እና ሊባኖስ ጦርነት አለፍ ሲልም በመካከለኛው ምስራቅ እያየለ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ እስራኤል ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጋር ያላት ግንኙነት ከጊዜ ወደጊዜ እየሻከረ መጥቷል፡፡

በጥቅምት ወር መጀመሪያ ኢራን በእስራኤል ላይ የፈጸመችውን ጥቃት አላወገዙም የተባሉት የተመድ ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ወደ እስራኤል እንዳይገቡ ታግደው ነበር፡፡

ይህን ተከትሎ ጉቴሬዝ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ “በመላው መካከለኛው ምስራቅ እየተስፋፋ የመጣውን ግጭት እቃወማለሁ” ማለታቸው ይታወሳል፡፡

በወቅቱ ከ100 በላይ ሀገራት ይህን የእስራኤል ውሳኔ በመቃወም ባወጡት መግለጫ እርምጃው ተመድ የሚጠበቅበትን ሃላፊነት በነጻነት ተንቀሳቅሶ እንዳያከናውን የሚያግድ ነው ማለታቸው የሚታወስ ነው፡፡

ኢራን አሁን ባቀረበችው ጥያቄ ጉዳዮን ይፋዊ በሆነ መንገድ ለመንግስታቱ ድርጅት ልታቀርበው እንደምትችል የታወቀ ነገር ባይኖርም እስራኤል ከድርጅቱ እንድትታገድ በመጠየቅ ከማሌዥያ ቀጥላ ሁለተኛዋ ሀገር ሁናለች ሲል የዘገበው አል አይን አማርኛ ነው፡፡

©ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Nov, 17:54


በ3 አመት ውስጥ ከ17ሺ በላይ የኢትዮ ኮደርስ ሰልጣኞችን ብቁ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የደሴ ከተማ ስራና ስልጠና መምሪያ ገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ሕዳር 3/2017

በበይነ መረብ የሚሰጠውና አለም አቀፍ ይዘት ያለው በተለያዩ የቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ ስልጠና የሚሰጥበት የኢትዮ ኮደርስ መርሀ ግብር በደሴ ከተማ መጀመሩ ተነግሯል።

የከተማዋ ስራና ስልጠና መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ጥላሁን ከበደ ለደሴ ፋና ሬዲዮ እንደተናገሩት ስልጠናው በቴክኖሎጂ ብቁ ከማድረግ ባሻገር አለም አቀፍ ተወዳዳሪም የሚያደርግ ነው ብለዋል።

በመሆኑም በከተማ አስተዳደር ደረጃ በ3 አመት ውስጥ ከ17 ሺህ በላይ ሰልጣኞችን ለማሳተፍ የታቀደ ሲሆን 4 ሺህ የሚደርሱት በዚህ አመት ስልጠናውን የሚወስዱ ናቸው ተብሏል።

አስከ አሁን ከ1 ሺህ በላይ ተመዝጋቢዎች ያሉ ሲሆን 260 የሚሆኑት ስልጠናውን አጠናቀው መመረቃቸው ተነግሯል።

ሰልጣኞች በግል ስልካቸውም ስልጠናውን መውሰድ ይችላሉ የተባለ ሲሆን ከተማ አስተዳደሩ ማእከሎችን ቢያዘጋጅም ጉዳዩን ተገንዝቦ ወደ ስልጠና የሚገባው ቁጥር አነስተኛ መሆኑ ተገልጿል።

ስልጠናው በርካታ ጥቅሞች ያሉት በመሆኑ ሀሉም ሊሳተፍበት እንደሚገባም ተጠቁሟል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Nov, 16:24


የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠ/ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሼይኽ ሀጂ ኢብራሂም የሱዳን ዓለምአቀፍ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚደንትን ተቀብለው ማነጋገራቸው ተገለፀ!

-ሀሩን ሚዲያ፣ሕዳር 3/2017፣አዲስአበባ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ የሱዳን ዓለምአቀፍ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚደንት የኾኑትን ፕሮፈሰር ጧሃ አብዲ ጧሃን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት (Education) ባለሙያ የኾኑት ፕሮፈሰር ጧሃ አብዲ በኢትዮጵያ የዓረብኛ ትምህርትን ለማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት እና ሌሎች የጠቅላይ ምክር ቤቱ አመራሮች ጋር ሰፋ ያለ የሐሳብ ልውውጥ አድርገዋል።

የፌዴራል መጅሊሱ ፕሬዚደንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ጠቅላይ ምክር ቤቱ የአረብኛ ትምህርትን ለማሳደግ ተግቶ እንደሚሠራ በውይይቱ ላይ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የሦስት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙት ፕሮፌሰር ጧሃ አብዲ ከአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ቀጥሎ በትምህርት ሚኒስቴር ዓረብኛን ለማስተማር እውቅና የተሰጠውን አወልያ የዓረብኛ ኮሌጅን መጎብኘታቸውን ለማወቅ ተችሏል።

በጉብኝታቸው ወቅትም፣ በኮሌጁ ስለሚሰጠው የዓረብኛ ትምህርት ይዘቶች እና በሥርዓተ ትምህርቱ ዙሪያ ሰፋ ያለ ገለጻ እንደተደረገላቸው ታውቋል።

ፕሮፌሰር ጧሃ አብዲ ጧሃ ከክቡር ሸይኽ ሐጂ ጋር በተወያዩበት ወቅት የአወልያ የዓረብኛ ኮሌጅ መምህራንን አቅም በመገንባት ኮሌጁን ወደ ዩኒቨርሲቲ ማሳደግ በሚቻልበት መንገድ ዙሪያ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር አብሮ ለመሥራት ፍላጎት ያላቸው መኾኑን ተናግረዋል። ሲል የዘገበው የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ነዉ!

©ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Nov, 15:28


https://youtu.be/EE7zpvBf-Ok?si=M6P9ilmji2ThNSNh

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Nov, 14:26


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መስራች ከነበሩ ሰዎች መካከል የነበሩት የክልሉ የመጀመሪያው ርዕሰ መሥተዳድር የተከበሩ አቶም ሙስጠፋ መሞታቸው ተሰማ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ሕዳር 3/2017

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመጀመሪያው ርዕሰ መሥተዳድርና የነፃነት ትግል ዓርበኛ የነበሩት አቶም ሙስጦፋ ሙሀመድ መሞታቸውን ተሰምቷል።

አቶ አቶም ሙስጠፋ ሙሀመድ በክልሉ ሕዝቦች የነፃነት ትግል ውስጥ እጅግ ውድ የሆነ ዋጋ ከከፈሉ የነፃነት አርበኞች መካከል በቀዳሚነት የሚጠቀሱ መሆናቸው ተገልጿል።

የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ርዕሰ መስተዳዳር  አቶ አሻድሊ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ መልዕክት "አቶ አቶም ዕድሜ ዘመናቸውን ለክልሉ ሠላምና ልማት ሲታትሩ የኖሩ ባለ ራዕይ መሪ ነበሩ" ብለዋል፡፡

ሠላምና መረጋጋትን ለመፍጠር ያበረከቱት አስተዋፅዖ በክልሉ ሕዝብ ታሪክ ውስጥ የላቀ ስፍራ የሚሰጠውና  ሲወሳ የሚኖር መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Nov, 13:31


በኢትዮጵያዊው ወጣት ሙሳ ከድር የተሰራ ድሮን!

- ሀሩን ሚድያ ህዳር 3/2017

ሙሳ ከድር ይባላል። ነፍሱ ለቴክኖሎጂ ፈጠራዎች በተለይ ደግሞ ለስፔስ ሳይንስ እጅግ የቀረበች ናት።

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪው ሙሳ ከድር ይበል የሚያሰኝ በርካታ የድሮን ቴክኖሎጂ ሥራዎች እየሰራም ይገኛል።

በልጅነቱ ስፔስ ሳይንስ ነክ ዶክመንታሪዎችን እያየ ማደጉ ወደዚሁ ሳይንስ እንዲሳብ እንዳደረገው ይናገራል። በአሁኑ ወቅት ለተለያየ ዓላማ የሚውሉ ድሮኖችን አምርቷል።

ከጓደኛው ጋር በመሆንም የእሳት ማጥፊያ እና የሕንጻ መስታወት ማጽጃ ድሮን በመስራት ወደ ገበያ ለማቅረብ በሥራ ላይ ናቸው።

የእሳት አደጋ ሲነሳ ለማጥፋት የሚያስችል እና ለማጽዳት አደገኛ የሆኑ ረጃጅም ሕንጻዎችን፣ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መስኮቶችን ለማጽዳት አገልግሎት ላይ የሚውል ድሮን በስፋት ለማምረት ነው እቅዳቸው።

የሚሰራቸው ድሮኖች አንድን እቃ የተፈለገበት ቦታ ላይ አድርሶ (ጥሎ) የመመለስ አቅም እንዳላቸው የሚናገረው ሙሳ የህክምና እና የተለያዩ እቃዎችን ለማድረስ እንደሚያግዙም ይገልጻል።

ታዳጊው ሙሳ ከድር በ2019 በነበረው የጎላ አስተዋጽኦ እና ባሳየው ድንቅ ብቃት የኢትዮጵያ ወጣት የአስትሮኖሚ አምባሳደርነትን አግኝቷል።

በአሁኑ ወቅት ከድሮን በተጨማሪ ራሱን መንዳት የሚችል መኪና መፍጠር እንደቻለም ይናገራል።

ሙሳ ከእነዚህ ሥራዎቹ በተጨማሪም ሌሎች የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች በመስራት ላይ ይገኛል። ወደ ፊትም በዘርፉ የተሻሉ ሥራዎችን የመስራት እቅድ ሰንቋል።

- ዘገባው የአዲስ ዋልታ ነው

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

12 Nov, 11:33


የሳዑዲ አረብያ ልዑል አልጋ ወራሽ መሐመድ ቢን ሰልማን እስራኤል በጋዛ ‘የዘር ጭፍጨፋ’ እየፈጸመች መሆኑን ገለፁ!

- ሀሩን ሚድያ ህዳር 3/2017

ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ በአደባባይ እስራኤል ላይ የሰላ ትችት ያሰሙት ልዑል አልጋ ወራሹ የእስራኤልን ድርጊት ኮንነዋል። የሙስሊምና አረብ አገራት መሪዎች ጉባዔ ላይ እስራኤል በሊባኖስና በኢራን የፈጸመችውንም ጥቃት አውግዘዋል።

ይህ የተገለፀው የሙስሊም ሀገራት መሪዎች በጋዛ እና በሊባኖስ ጉዳይ በሪያድ ባካሄዱት ስብሰባ ወቅት ነው።

በሪያድና ቴህራን መካከል ያለው ግንኙነት እየተሻሻለ መሆኑን በሚጠቁም ሁኔታ ኢራን ላይ እስራኤል የምታደርሰውን ጥቃት በተመለከተም ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።

ሌሎችም በጉባዔው የታደሙ መሪዎች እስራኤል ከዌስት ባንክና ከጋዛ ሙሉ በሙሉ ለቃ እንድትወጣ ጠይቀዋል።

የሳዑዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑል ፈይሰል ቢን ፋርሀን አል-ሱአድ የጋዛ ጦርነት እስካሁን ያልቆመው “በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ውድቀት ምክንያት ነው” ብለዋል። እስራኤል በቀጠናው ረሃብ አስከትላለች ሲሉም ኮንነዋል።

“የእስራኤልን ጥቃት ለማስቆምና ግጭቱን ለማስቆም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ተስኖታል” ሲሉም አክለዋል። እስራኤል በጋዛ ላይ በከፈተችው ጥቃት ከ43,400 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገልጿል።

የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ቢሮ ባለፉት ስድስት ወራት ከተገደሉት መካከል 70 በመቶ የሚሆኑን ሴቶችና ሕጻናት ናቸው ብሏል።

የሙስሊምና አረብ አገራት ጉባዔ ተሳታፊዎች እስራኤል በተባበሩት መንግሥታት ሠራተኞችና በጋዛ መሠረተ ልማት እያደረሰች ያለውን “ተከታታይ ጥቃት” አውግዘዋል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Nov, 18:35


የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር በሙስና ወንጀል እና እምነት በመጣስ በተከሰሰበት ክስ ፍርድ ቤት ቀርቦ ቃሉን ለመስጠት የ80 ቀን ጊዜ ይሰጠኝ ሲል ጠየቀ!

- ሀሩን ሚድያ ሕዳር 2 ፣2017 ዓ.ል

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በጋዛ እና ሊባኖስ በተከሰቱ ግጭቶች መጨናነቁን በመጥቀስ የሙስና ክስ ጉዳዩ አካል የሆነው ምስክርነት ወደ 80 ቀናት ገደማ እንዲራዘም ጠይቀዋል።

እንደ እስራኤላዊው የህዝብ ማሰራጫ ካን ገለጻ የኔታንያሁ የህግ ቡድን ምስክርነቱን እንዲዘገይ በኢየሩሳሌም አውራጃ ፍርድ ቤት ጥያቄ አቅርቧል።

ኔታንያሁ የእስራኤል የጦርነት ጊዜ የደህንነት ፕሮቶኮሎች አካል በመሆን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ምድር ቤት ውስጥ በተጠናከረ ክፍል ውስጥ ተግባሩን ሲያከናውን ቆይቷል።

ፍርድ ቤቱ ምስክርነቱን እስከ መጋቢት 2025 እንዲዘገይ ከዚህ ቀደም የቀረበለትን ጥያቄ ውድቅ ማደረጉ የተገለፀ ሲሆን በምትኩ ለታህሳስ ወር 2024 ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል።

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የተከሰሰው በሁለት ክሶች በማጭበርበር እና እምነትን በመጣስ፣ መሆኑም ተገልጿል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Nov, 18:04


https://www.facebook.com/100044193861273/posts/1311541886995594/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Nov, 16:15


https://youtu.be/DZNY2GNS6WQ?si=NtZLV0jVYJ19_vdR

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Nov, 15:28


በፌደራል የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች በሚታዩ ችግሮችና መፍትኄዎቻቸው ላይ ያተኮረ ጥናታዊ ሰነድ ለኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መሰጠቱ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚድያ ሕዳር 2 ፣2017 ዓ.ል

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በፌዴራል የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች በሚታዩ ችግሮች እና በመፍትኄዎቻቸው ላይ ያተኮረ ጥናታዊ ሰነድ ከአጥኚው ኮሚቴ መረከባቸው ተገልጿል።

ሚያዚያ 30፣ 2016 ዓ.ል የተመሠረተውና አምስት አባላት ያሉት ይህ አጥኚ ኮሚቴ፣ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ የዓሊሞች ጉባዔ ጽሕፈት ቤት የተመረጡ ዓሊሞችና የሕግ ባለሙያዎች የተካተቱበት ነው።

በፌደራል የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አደረጃጀት፣ በሰው ኃይል አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጥ፣ እንዲሁም በሕጉ ማዕቀፍ ላይ የሚታዩ ችግሮችን በመለየት የመፍትኄ ሐሳብ ያቀረበውን ሰነድ፣ የጥናት ኮሚቴው አባላት ዶ/ር ሼይኽ ሙሐመድ ሐሚዲን እና የሕግ ባለሙያው አብዱልሐኪም ጀማል ለጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ለሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ አስረክበዋል።

በሰነዱ ርክክብ ወቅት ፕሬዚደንቱ ሲናገሩ የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥና መፍትኄው ላይ ያተኮረውን ይህን ጥናት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ላከናወኑት የጥናት ቡድኑ አባላት በራሳቸውና በጠቅላይ ምክር ቤቱ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ፕሬዚደንቱ ይህን ሰነድ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ የዓሊሞች ጉባዔ ምክትል ሰብሳቢና የፈትዋ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከኾኑት ከዶክተር ጀይላን ኸድር ጋር አብረው መቀበላቸውን ጠቅሰው ጥናቱን ወደ ሥራ ለመተርጎም ከሚመለከተው አካል ጋር በመኾን እንሠራለን ማለታቸውን የዘገበው የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ነው።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

11 Nov, 14:29


"ዘመናችን" በሚል ሀሳብ የዳዕዋ መድረክ በአዋሽ መልካሳ ከተማ ተካሄደ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ህዳር 2/2017

በአዋሽ መልካሳ ከተማ በአል ኑር ወጣቶች ጀመዓ የተዘጋጀ "ዘመናችን በሚል መሪ ሀሳብ የዳዕዋ የመድረክ ዝግጅት በትላትናው ዕለት በድምቀት ተካሂዷል።

በመድረኩ ኡስታዝ ሳዲቅ ሙሀመድ (አቡ ሀይደርን) ጨምሮ ሌሎች ኡስታዞች በተለያዩ ርዕሶች የዳዕዋ ስራዎችን ያቀረቡ ሲሆን መነባንብ እና መሰል ስራዎች በመድረኩ ለታዳሚው ቀርበዋል።

ዘመናችን በሚል ሀሳብ በተዘጋጀው በዚህ የዳዕዋ መድረክ የአዋሽ መልካሳ አካባቢ ሙስሊም ማህበረሰብ፣ ታላላቅ አሊሞች፣ ዳኢዎች፣ የአዳም አካባቢ ጀመአዎች፣ እንድሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

- ሀሩን ሚዲያ በአዋሽ መልካሳ ከተማ በመገኘት ይህን ዝግጅት ያጠናቀረ ሲሆን በቅርብ ቀን ወደናንተ ያደርሳል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

05 Nov, 18:47


እሷስ ማን አላት? ጥቅምትን ለየሲር ለናልዩ ዝግጅትHarunmedia||
https://youtu.be/2sYwc7L27HE?si=818qYHmEF3uZRU-L

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

05 Nov, 18:15


ሰበር ዜና | የእስራኤል ቻናል 12 እንደዘገበው፦

ቤንጃሚን ኔታንያሁ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር የሆኑትን ዮአቭ ጋላንትን በዛሬው እለት ከስልጣን አባረዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

05 Nov, 14:37


"እሷስ ማን አላት?"
በየሲር ለና ከ500 በላይ አቅም ለሌላቸው እናቶች እና አረጋውያን የነፃ ህክምና አገልግሎት የተሰጠበትን ልዩ ዝግጅት ዛሬ ምሽት 02:45 ይጠብቁን።

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

05 Nov, 13:31


በመሃል አዲስ አበባ እምብርት ፒያሳ ላይ  የሚገኘው ጥንታዊው የሙስሊም ት/ቤት የመጀመሪያው አወሊያ ሊፈርስ መሆኑ ተሰማ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥቅምት 26/2017

ጥቅምት 24/2017 ዓ.ል በአወሊያ አዳራሽ በነበረው የወላጆች ስብሰባ ስለ አወሊያ የፒያሳው ቅርንጫፍ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ወቅታዊ ሁኔታ በትምህርት ዙሪያ በተጠራ ስብሰባ በበርካታ ወላጆች ጠንከር ያሉ ጥያቄዎች ሲነሱ እንደነበር ተሰምቷል።

ወላጆቹ ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከልም ልጆቸው የት/ቤታቸው የመፍረስ አደጋ ስጋት እንደፈጠረባቸው አንስተው ስለጥንታዊ ተቋማቸው ወቅታዊ ሁኔታ ዘርዘር ያሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ለተቋሙ አስተዳደር ጥያቄ አቅርበዋል። 

በጉዳዩ ላይ ለወላጆች ማብራሪያ የሰጡት የአወሊያ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰይድ አስማረም ጉዳዩ እውነት እንደሆነ አረጋግጠው በሂደቱ ላይ ግን ጉዳዩን የሚከታተል በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ስር አምስት አባላት ያሉት በኡስታዝ አቡበከር አህመድ ሰብሳቢነትና በኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ም/ሰብሳቢነት የሚመራ ኮሚቴ ክትትል እየተደረገበት እንደሆነ ስራ አስኪያጁ ለሬዲዮ ነጃሺ ገልጸዋል።

ኮሚቴው ከተዋቀረ ከ2 ወራት በላይ እንዳስቆጠረ ያወሱት ስራ አስኪያጁ ከመንግስት አካላት ጋር የቅርብ ጊዜ ስብሰባውን ያለፈው አርብ ጥቅምት 22/2017 እንዳደረገ አብራርተዋል። ስራ አስኪያጁ ``ሙስሊሙ የመንግስትና የልማት ደጋፊ`` መሆኑን ገልጸው ኮሚቴው ተለዋጭ ቦታ ለመረከብ አማራጭ ቦታዎችን እያማተረና የስምምነት ጫፍ ላይ እንደደረሰ`` አውስተዋል።

ስራ አስኪያጁ በገለጻቸው ት/ቤቱ በ2016 የት/ት ዘመን ክልላዊ ፈትና 100% የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎችን በማሳለፍ ውጤታማ የሆነ ት/ቤት ሲሆን በክ/ከተማ ደረጃም የዋንጫ ሽልማት እንዳገኘ ገልጸዋል።

ይህ ቦታ በዓለም አቀፍ የሙስሊም ሊግ ዋና ጸሃፊና በአዲስ አበባ ከንቲባ የጠ/ም/ቤቱ ባሉበት የዛሬ ዓመት ገደማ በአዲስ መልክ እንዲገነባ የ900,0000,000 /የዘጠኝ መቶ ሚሊዮን/ ብር የ19 ወለል (ፎቅ) ግንባታ ሊሰራበት የመሰረተ-ድንጋይ እንደተጣለበት በበርካታ ሚዲያዎች መዘገቡን በዛሬው ዕለት በነበረው ገለጻ ተወስቷል።

ለዚሁ አዲሱ ግንባታ ከሚያስፈልገው ተጨማሪ 5ሺ ካሬ ገደማም የአዲስ አበባ መሬት ማኔጅመንት በስሩ ከሚያስተዳድራቸው ቦታዎች ከ3ሺህ ካሬ በላይ የሚሆነውን ቦታ መስጠቱን የመሰረት ድንጋዩ በጣለበት ዕለት ከንቲባዋ ይፋ ማድረጋቸው አይዘነጋም።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

05 Nov, 12:39


በትላንትናው ዕለት "ዛሬ ፍርድ ቤት እንደሚቀርብ" ገልፀን የነበረው አሚር አብዱልከሪም በ5 ሺህ ብር ዋስ መፈታቱ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚድያ፥ ጥቅምት 26/2017

በኒቃብ ጉዳይ ታስረው የነበሩ ሙስሊም ተማሪዎችን አስመልክቶ ትላንት ከህግ ባለሙያ ጠበቃ ሙስጠፋ ሽፋ ጋር በነበረን ቆይታ ዛሬ ፍርድ ቤት እንደሚቀርብ ገልፆልን የነበረው ተማሪ አሚር አብዱልከሪም በአምስት ሺህ ብር መፈታቱን ለሀሩን ሚድያ ተናግሯል።

ዛሬ ጥቅምት 26 ቀን 2017 በአዲስ ከተማ አዲስ ከተማ ምድብ ከተማ ነክ ፍርድ ቤት ተማሪ አሚር አብዱልከሪም በነበረው የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ወገን ክርክር ከሰማ በኋላ ተጨማሪ ጊዜ መስጠት ሳያስፈልገው በብር አምስት ሺህ ዋስትና እንዲለቀቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

የህግ ባለሙያው ጠበቃ ሙስጠፋ ሽፋ በዛሬው ችሎት በነፃ የህግ ድጋፍ ላደረገው ጠበቃ ሁሴን ዑስማን ምስጋናውን አቅርቧል።

ጥቅምት 28 ቀን 2017 ተማሪ ሰሚር መሀመድ፣ ነቢል መሀመድ፣ ሚኪያስ እና ብሩክ ከላይ በጠቀስኩት ምድብ ችሎት ጊዜ ቀጠሮ ችሎት እንደሚቀርቡም ከህግ ባለሙያው ጠበቃ ሙስጠፋ ሽፋ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Nov, 19:33


በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በግፍ ስለተገደሉት የመስጂድ ኢማም ጉዳይ የኦሮሚያ መጅሊስ እና የፌዴራል መጅሊስ ምላሽ ሰጡ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥቅምት 25/2017

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ገንዳ አረቦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አብረዋቸው ከታገቱ 12 ከሚሆኑ የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ጋር በግፍ የተገደሉትን የሃጂ አህመድ መጅሊስ ኢማም ሼይኽ ሙሀመድ መኪን ሼይኽ ሙሀመድ አሪፍን ጉዳይ አስመልክቶ ሀሩን ሚዲያ የኦሮሚያ መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሼይኽ ጀማል ሙሳን እና የፌዴራል መጅሊስ ዋና ፀሀፊ ሼይኽ ሀሚድ ሙሳን አነጋግሯል።

የኦሮሚያ መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሼይኽ ጀማል ሙሳ በህመም ምክንያት እረፍት ላይ በመሆኔ የኢማሙን ሞት አልሰማሁም ነበር ያሉ ሲሆን ነገር ግን በደራ ወረዳ ከአራት ወራት በፊት ጀምሮ ሰላም እንደሌለ የአካባቢው ሰዎችም በሰላም እጦት ችግር ውስጥ እንደነበሩ ሰምተናል ብለዋል።

በኢማሙ ሞት ማዘናቸውን ገልፀው በአካባቢው የኔትወርክ አልመስራት ጉዳዩን ለማጣራት እንከን ሆኖብናል ብለዋል። ቢሆንም ግን ችግሩን መንግስት በሰላም አስከባሪ የሚያስከብር ከሆነ እንጂ ጉዳዩ ከእኛ አቅም በላይ ነው ብለዋል።

የፌዴራል መጅሊሱ ዋና ፀሀፊ ሼይኽ ሀሚድ ሙሳ በበኩላቸው ይህንን ጉዳይ "ህዝብ ግንኙነታችን ምላሽ ይሰጥበታል" የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Nov, 19:26


https://youtu.be/JrjS27qXlHk?si=ocOfLDOrp8LxRQqd

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Nov, 18:24


በኒቃብ ምክንያት የታሰሩ ተማሪዎችን የታሰሩበት ጣቢያ ድረስ በመገኘት አናጋግሪያቸዋለሁ - የህግ ባለሙያው ጠበቃ ሙስጠፋ ሽፋ

- ሀሩን ሚድያ ጥቅምት 25/2017

በኒቃብ ጉዳይ የታሰሩ ተማሪዎችን አስመልክቶ ትላንት በሰራነው ዘገባ አማካኝነት በሙያው ለማግለግል ፍቃደኛ የነበረው የህግ ባለሙያው ጠበቃ ሙስጠፋ ሽፋ በዛሬው ዕለት ተማሪዎቹ የታሰሩበት እህል በረንዳ ወረዳ 7 ፖሊስ ጣቢያ በመገኘት ማነጋገሩን ለሀሩን ሚድያ ገልጿል።

በትላንትናው ዕለት ወላጆቻቸውን በማነገገር የታሰሩ ተማሪዎችን መረጃ ካሰባሰብኩኝ በኋላ በዛሬው ዕለት ጣቢያ በመገኘት ተማሪ ነቢል፣ ተማሪ አሚር እና ተማሪ ሰሚርን በማናገር ተማሪ አሚር በነገው ዕለት ፍርድ ቤት እንደሚቀርብ ተማሪ ነቢልና ተማሪ ሰሚር ሀሙስ ጥቅምት 28/2017 ዓ.ል ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ማረጋገጥ መቻሉን ለሀሩን ሚድያ ተናግሯል።

በተጨማሪም ተይዞ የነበረው ተማሪ አብደላ ቅዳሜ እለት ከእስር መፈታቱም ተገልጿል።

በኒቃብ ጉዳይ የታሰሩ ሴት ተማሪዎች መፈታታቸው የተገለፀ ሲሆን አሁንም የታሰሩ ሙስሊም ተማሪዎች ከእስር እንዲለቀቁ ሁሉም ሀላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Nov, 17:30


በኒቃብ ምክንያት የታሰሩት ሙስሊም ተማሪዎችHarunmedia
https://youtu.be/vHtWejBqJ40?si=3ARhKdzruHWKKQm4

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Nov, 14:45


ሰለምቴው መምህር ፂሙን በማሳደጉ ለዲሲፕሊን ቅጣት መዳረጉ ተገለፀ።

▣ ጺሙን ካልተቆረጠ በስራው ላይ መቀጠል እንደማይችል ተነግሮታል።

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ሰቱዲዮ ጥቅምት 25/2017

ሰለምቴው መምህር አሸናፊ ትርፋ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ገዋታ ወረዳ የገዋታ ትምህርት ቤት 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት መምህር ሲሆን መደበኛ ስራውን እየከወነ ቢሆንም ከጺሙ ጋር በተያያዘ የዲስፒሊን ቅጣት ተጥሎበታል። ጺሙን ካልተቆረጠ ወደ ማስተማር እንደማይመለስም ተገልጾለታል።

ለጺም ማሳደጉ ምክንያት ተደርገው የቀረቡ ክሶችም፦

1/ የተማሪዎችን ስነ-ልቦና የሚሰርቅ መሆኑ

2/ ትም/ት ከፖለቲካና ሃይማኖት ነፃ ነዉ የሚለዉን መርህ መጣሱ

3/ በየደረጃ ካሉ አመራሮች ወይም በህግ ስልጣን ከተሰጣቸዉ አካላት ለሚሰጡ ህጋዊ ትዕዛዞቸ አፋጣኝ ምላሽ ያለመስጠትና አለመፈፀም

4/ በማኅበራዊ ምድያ የዉሸት መረጃ በማሰራጨት በትም/ቤቱ ር/መ/ራን ላይ ሌሎችን መቀስቀስና ማነሳሳት ጥፋት የሚሉ ሲሆን በእነዚህ አራት ክሶች ምክንያት የ3 ወር ደመወዝ ቅጣት እና ፂሙን እንዲያስቆርጥ መወሰኑን ከውሳኔ ደብዳቤው መረዳት ችለናል።

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ የወረዳውን ትምህርት ጽ/ቤት አመራሮችን ለማግኘት ጥረት እያደረግን ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን የምናደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

04 Nov, 14:24


ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፈተ!

- የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ጽሑፍ ማቅረባቸው ተገልጿል።

- ሀሩን ሚድያ ጥቅምት 25/2017፣ አዲስ አበባ

የሰላም ሚኒስቴር በዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ከሚገኘው ከመሐመድ ቢን ዛይድ ፎር ሁማኒቲ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ዓለም አቀፍ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በአዲስ አበባ ዛሬ በተከፈተው ዓለም ዓቀፍ የሃይማኖት ጉባዔ ላይ ጽሑፍ ማቅረባቸው ተገልጿል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት  ያቀረቡት ጽሑፍ "የመከባበርና የመቻቻል ባህልን ለማዳበር የሃይማኖት ተቋማት የሚያደርጉት አስተዋጽዖ" የሚል ርዕስ ያለው ሲኾን፣ ሸይኽ ሐጂ ከ1440 ዓመታት በፊት እስልምና ወደ ኢትዮጵያ በገባበት ጊዜ በሐበሻው ንጉሥ አስሐመተል ነጃሺ እና ወደ ሐበሻ በስደት የመጡት የነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) ባልደረቦች መሪ በነበረው ታላቁ ሶሃባ ጃዕፈር ቢን አቡ ጧሊብ መካከል እምነትን አስመልክቶ የተካሄደውን ውይይትና መተማመን የመቻቻል አብነት እንደኾነ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ነብያችን ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) "ከእናቴ ቀጥላ ሁለተኛ እናቴ " ያሏት የዑሙ አይመን አገር መሆኗን የጠቀሱት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም፣ ታላቁ ነብይ (ሰ.ዐ.ወ) ቀደምት ተከታዮቻቸው በመካ የቁረይሽ ባላባቶች ግፍ እና መከራ በደረሰባቸው ጊዜ፣ "ወደ ሐበሻ ሂዱ፤ እርሷ እርሱ ዘንድ አንድም ሰው የማይበደልበት እውነተኛ መሪ ያለባት የፍትኅ አገር ናት" ማለታቸው በጽሑፋቸው ጠቅሰዋል።

ሼይኽ ሐጂ አክለውም አገራችን ኢትዮጵያ የነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ሙአዚን የቢላል ኢብኑ ረባህ አገር እንደኾነችና የታላቁ ነቢይ (ሶ.ዐ.ወ) ቀደምት ባልደረቦች ቀብር የሚገኝባት ታላቅ አገር መሆኗን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ልዩነትን የማስተናገድ ከአስሐመተል ነጃሺ የተወረሰ የረጅም ዘመን ታሪክ ያላት አገር መሆኗን የጠቀሱት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም፣ ዓለም ይህንን ልምድ ከኢትዮጵያ  ሊወስድ ይገባዋል ብለዋል።

ዛሬ በተጀመረው ዓለምአቀፍ የሃይማኖት ጉባዔ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ አባል ቤተ እምነት አባቶች፣ አሜሪካ፣ አውሮጳ እና ኤዥያን ጨምሮ ከአሥራ ሦስት ሀገራት የመጡ የሃይማኖት ሊቃውንት፣ አሥራ አምስት ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ከሦስት መቶ በላይ ሰዎች በጉባዔው ላይ ተሳታፊ ሆነዋል።

ለሁለት ቀናት በሚካሄደው በዚህ ዓለም አቀፍ ጉባዔ ላይ በምሁራን የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎች መቅረባቸው እንደሚቀጥል ከኢት/እ/ጉ/ጠቅላይ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

30 Oct, 08:45


https://youtu.be/1FKs6JKnvEo?si=6Dr6KUEfVvfypxbE

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

30 Oct, 07:08


በአሜሪካ በአለም አቀፍ ማርሻል አርት ፌስቲቫል በሦስት ውድድሮች በመሳተፍ 1 ወርቅ እና 2 የብር ሜዳልያ በማግኘት ኢትዮጲያ ከፍ ብላ እንድትታይ ያደረገው ኤሊያስ ኩመል

- ሀሩን ሚድያ ጥቅምት 20/2017

በሀገረ አሜሪካ ፍሎሪዳ ከተማ በአለም አቀፍ ማርሻል አርት ፌስቲቫል ውድድር ከአፍሪካ ብቸኛ ተወዳዳሪ የነበረው ኤልያስ ኩመል በሦስት ውድድሮች በመሳተፍ አንድ ወርቅና ሁለት የብር ሜዳሊያ በማግኘት የኢትዮጲያን ሰንደቅ አላማ ከፍ ብሎ እንዲታይ አድርጎል።

ኤልያስ ኩመል በመጀሪያ ደረጃ የፖተርን ውድድር የወርቅ ሜዳልያ
፣በነፃ ፍልሚያ ውድድር የብር ሜዳልያ፣ በሁለተኛ ደረጃ የፖተርን ውድድር የብር ሜዳልያ ማግኘቱን ለሀሩን ሚድያ ተናግረዋል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

30 Oct, 05:30


የሐራ ከተማ የቲሞች እና ህሙማን መርጃ ማህበር <<በትምህርት ቁሳቁስ ችግር ምክንያት አንድም ተማሪ ከትምህርት አይቀርም>> በሚል መሪ ቃል ወላጆቻቸውን በሞት ላጡ ህፃናትና አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የት/ት ዩኒፎርም ልገሳ ማከናወኑ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ ፣ጥቅምት 20/2017

በሐራ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ለሚማሩ 87 ተማሪዎችና በሐራ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ለሚማሩ 30 ተማሪዎች በድምሩ 117 ተማሪዎች ዩኒፎርም ማበረከቱን የማህበሩ ሰብሳቢ አቶ አብዱ ሰኢድ ገልፀዋል።

ዛሬ ዩኒፎርም የተበረከተላቸው ተማሪዎች መስከረም 8 እና 9 ለአንድ አመት የሚሆን የትምህርት ቁሳቁስ የተበረከተላቸው ተማሪዎች መሆናቸውን ሰብሳቢው አቶ አብዱ ሰኢድ ገልፀዋል።

አቶ አብዱ አያይዘውም እነዚህ ተማሪዎች ከደብተርና እስኪቢርቶ በተጨማሪ የትምህርት ቤት ዩኒፎርም ለማማሏት የማይችሉ በመሆናቸወ ተቋሙ ይሄንን ችግራቸውን በመረዳት ለዩኒፎርም የሚሆን ብትን ጨርቅ ከደሴ በማስመጣት በከተማው ካሉ ልብስ ሰፊዎች በጨረታ በማወዳደር በዝቅተኛ ዋጋ አሸናፊ ለሆነው ልብሰ ሰፊ ለ117 ተማሪዎች ዩኒፎርም ማሰፋቱን ገልፀዋል።

በዛሬው እለት ዩኒፎርም የተበረከተላቸው ተማሪዎች ለተደረገላቸው ልገሳ ከልብ አመስግነው መስከረም 8፣ 9 እና በዛሬው እለት የተከናወነው የዩኒፎርም ልገሳ የዓመቱን ትምህርት በደንብ እንዲማሩ የሚያስችላቸው በመሆኑ ትምህርታቸውን እንዳይማሩ እንቅፋት የሆነባቸው ችግር በመቀረፉ ትምህርታቸውን ያለ ችግር እንድከታተሉ እንደሚያስችላቸው ገልፀዋል።

በተመሳሳይ የዩኒፎርም ልገሳ የተደረገላቸው ትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን ለተደረገላቸው ልገሳ በትምህርት ቤቱና በተማሪዎቹ ስም የሐራ የቲሞችና ህሙማን መርጃ ማህበርን ከልብ አመስግነው እንደዚህ አይነት መልካም ተግባር ለሌሎች መሰል ተቋማትም ምሳሌ ስለሚሆን ድጋፋቸውን አጠናክረው እንድቀጥሉ ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

29 Oct, 17:58


በሰሜን ጋዛ እየተካሄደ በሚገኘው ጦርነት አራት የእስራኤል ወታደሮች መገደላቸው ተገለፀ!

- ሀሩን ሚድያ ጥቅምት 19፣ 2017 

በሰሜን ጋዛ እየተካሄደ በሚገኘው ጦርነት አራት የእስራኤል ወታደሮች መገደላቸውን የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት አስታውቋል፡፡

ከተገደሉት ወታደሮች በተጨማሪ አንድ የእስራኤል ኦፊሰር ከባድ ጉዳት እንደደረሰበት አልጀዚራ በዘገባው አስፍሯል፡፡

ወታደሮቹ በአካባቢው ከባድ ውጊያ ሲያደርጉ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን የሟቾቹ ማንነት ለቤተሰቦቻቸው ይፋ መደረጉም ተመላክቷል፡፡

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

29 Oct, 16:18


https://youtu.be/GYr-KU1OSbM?si=16Wf5LA7kZlPFJfa

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

21 Oct, 13:10


ከፍተኛ ምክር ቤቱ ከኢምፓክት ሜከርስ ፋውንዴሽን ጋር በተለያዩ ጉዳዮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ!

- ሀሩን ሚድያ፥ ጥቅምት 11/2017 ዓ.ል. አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከኢምፓክት ሜከርስ ፋውንዴሽን ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አብሮ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈራርመዋል።

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሱልጣን አማን ኤባ እንዳሉት የአዲስ አበባ መጅሊስ በአዲስ መልክ ከተቋቋመ ወዲህ እስከ መስጂድ የደረሰ የመዋቅር ዝርጋታ ሰርቷል ያሉ ሲሆን ይህ ስምምነት ተቋሙና ማሕበረሰቡ የሚፈልገው ብቁ አመራርና ባለሙያ እንዲፈጠር ያደርጋል ብለዋል።

የኢስላማዊ ተቋማት ዘርፍ ተጠሪና የስራ አስፈጻሚ አባል ኡስታዝ መሐመድ አባተ በበኩላቸው የአዲስ አበባ መጅሊስ የሚያከናውናቸውን ተግብራቶች የበለጠ ቀልጠፋና ውጤታማ ማድረግ እንደሚፈልግ ገልፀው ይህንን ለመከወን የሰለጠነ የሰው ኃይል አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል። በመሆኑም ኢምፓክት ሜከርስ ፋውንዴሽን በዚህ ረገድ ምክር ቤቱ የሚሠራውን ስራ ለማገዝ የሚያስችለውን ስምምነት ማድረጉ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል።

የፋውንዴሽኑ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል በስምምነቱ ወቅት እንዳሉት ፋውንዴሽኑ ከተቋቋመ ሁለት ዓመት ገደማ ያስቆጠረ ሲሆን በዚህ ጊዜ አመርቂ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ስራ ሲያከናውን እንደቆየ ተናግረዋል።

ፋውንዴሽኑ ብቁ፣ ተምሳሌታዊ ዜጋ ለማፍራት በማለም የተቋቋመ መሆኑን ያስታወሱት ኡስታዝ አሕመዲን መጅሊሱ የከተማውን ማሕበረሰብ በላቀ ደረጃ ለማገልገል የያዘው ቁርጠኝነት በመረዳት የራሱን ሚና እንደሚወጣ ገልፀዋል።

ከአዲስ አበባ መጅሊስ ጋር ለመሥራት መስማማታችን ለሀገራዊ ግንባታ ተሳትፏችን የምናደርገውን አስተዋፅኦ ያሳድገዋል ያሉት ኡስታዝ አሕመዲን የዛሬውን ስምነነት በቀጣይ እየመነዘርን እና እያሰፋን ወደ ስራ እንገባለን በማለት ተናግረዋል።

ስምምነቱን በም/ቤቱ በኩል የፈረሙት አቶ አደም ተማም እንዳሉት የተቋማችንን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ከኢምፓክት ሜከርስ ፋውንዴሽን ዓይነት ተቋም ጋር በጋራ መሥራት መልካም ነው ብለዋል። ስምምነቱ የመጅሊሱን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ገልፀዋል።

በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ የከፍተኛ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ሼህ ሱልጣን አማን ኤባ፣የአዲስ አበባ መጅሊስ የስራ አስፈፃሚ አባላት በኢምፓክት ሜከርስ ፋውንዴሽን በኩል የፋውንዴሽኑ መሥራችና የቦርድ ሰብሳቢ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል እና የፋውንዴሽኑ ዋና ዳይሬክተር ሺሃቡዲን ሼህ ኑራ ተገኝተዋል።

▣ ሀሩን ሚዲያ በቦታው የተገኘ ሲሆን ሙሉ መሰናዶውን ወደ እናንተ የሚያደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

20 Oct, 19:49


የእስራኤል ጦር የ401'ኛው ብርጌድ አዛዥ በጋዛ መገደሉ ተገለፀ!

-ሀሩን ሚድያ ጥቅምት10/2017

የእስራኤል ቻናል 12 እንዳስታወቀው የ401'ኛው ብርጌድ አዛዥ በጃባሊያ በጋዛ ሰርጥ በስተሰሜን በተደረገ ጦርነት መገደሉን ገልጿል።

©ሀሩን ሚድያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

20 Oct, 18:16


በሲዳማ ክልል የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ኢስላማዊ አንድነት ለተቋማት ግንባታና ለከተማ ልማት በሚል መሪ ቃል ህዝባዊ ውይይት አካሄደ !

ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ ጥቅምት 11/2017

በሲዳማ ክልል የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ኢስላማዊ አንድነት ለተቋማት ግንባታና ለከተማ ልማት በሚል መሪ ቃል ህዝባዊ ውይይት በሲዳማ ባህል አዳራሽ አካሒዷል።

በውይይት መድረኩ ላይ ከመስጂድ ኢማሞች፣ ሙዓዚኖች፣ ኢስላማዊ ዕድሮች፣ መሻይኮች፣ ኡለማኦች ፣ ዱዓቶች፣ ወጣቶችና ሴቶች እና ሌሎች ባለድርሻ አላካላት ተሳትፈዋል።

መድረኩን ኡስታዝ አልተሞ ቱምሲሳ የሀዋሳ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ዋና ሰብሳቢ፣ ሩሽዲ ሁሴን በድሩ የሀዋሳ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክትል ሰብሳቢና ሙሃባ ሁሴን የሀዋሳ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ዋና ጸኃፊ በጋራ መርተውታል።

ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን የመጅሊስ አመራሮቹም የህዝበ ሙስሊሙን ችግር ለመፍታት እንዲህ አይነት መድረክ ማዘጋጀታቸውንም ተሳታፊዎች አድናቆታቸውን በመግለጽ ይህም ለመጀመሪያ ጊዜ ነው እንዲህ ባለ መልክ የተሰበሰብነው ለቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥል ብለዋል።

መድረኩ ላይ የሲዳማ ክልል እስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ሃጂ አ/ሹኩር አ/ቃድርም ተገኝተው መልዕክት በማስተላለፍ ከታዳሚዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን በመቀበል የመጅሊስ አመራሮቹ ችግሩን ለመፍታት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

በመጨረሻም በሀዋሳ ከተማ ለህዝበ ሙስሊሙ አያሌ አመታትን ላገለገሉ መሻይኮችና ግለሰቦች የምስጋናና እውቅና በመስጠት መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ ስፍራው ተገኝቶ ያጠናቀረውን ዘገባ በተከታይ ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚዲያ

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

20 Oct, 14:41


ኢማሙ ሻፊዕይ /ሰለፊያ/ መስጅድና መድረሳ ግንባታ እንዲጠናቀቅ ሙስሊሙ ማኀብረሰብ ርብርብ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ!

- ሀሩን ሚድያ ጥቅምት 10/2017፥ አዲስ አበባ

በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ወረዳ 3 የሚገኘው ኢማሙ ሻፊዕይ /ሰለፊያ/ መስጅድና መድረሳ ግንባታ ከተጀመረ 4ተኛ ዓመት ያስቆጠረ ሲሆን በዛሬው ዕለትሞ በመስጂዱ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሰደቃ፣ የዱዓና የጉብኝት መርኃግብር ተካሂዷል።

በዛሬው የሰደቃና የጉብኝት መርሀግብር ኢማሙ ሻፊዕይ መስጂድ ግንባታ እንዲጠናቀቅ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር የተካሄደ ሲሆን ህዝበ ሙስሊሙም የመስጂዱ ግንባታ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያደርግ የአዲስ አበባ መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች ገልፀዋል።

በዝግጅቱ ላይ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባን ጨምሮ፣ የአ/አ መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ ኡለማዎች፣ ኡስታዞች እንዲሁም በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

ኢማሙ ሻፊዕይ /ስለፊያ/ መስጅድና መድረሳ ግንባታን ድጋፍ ለማድረግ
ንግድ ባንክ 1000630665527
ሂጅራ ባንክ 1005989890001
ዘምዘም ባንክ 0034988810301 ኢማሙ ሻፊዕ መስጂድ

- ሀሩን ሚድያ በዝግጅቱ በመገኘት ያጠናቀርነውን የቪድዮ ዝግጅት በአላህ ፍቃድ ወደናንተ ምናደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚድያ

23,828

subscribers

7,818

photos

52

videos