ሀሁ መጻሕፍት ( Hahu books )

@fanab123


የሚፈልጉትን ማንኛውንም መፅሐፍት ካሉበት ቦታ እናመጣልዎታለን
በ 0911006705 ደዉለዉ ይዘዙን
አድራሻ፦ቁ.1 ሜክሲኮ ደብረ ወርቅ ህንፃ
ቁ.2 አራት ኪሎ አብርሆት ቤተ መጻህፍት

ሀሁ መጻሕፍት ( Hahu books )

09 Oct, 08:14


ተወልዶ ያደገው ጎንደር ነው፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪውን በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ስነ ጽሑፍ (B.A) አግኝቷል፡፡ በዲላ ዩኒቨርሲቲ post Graduate Diploma in teaching (PGDT) ሁለተኛ ዲግሪውን (M.A) ይዟል፡፡ በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በሰነ መለኮት በዲግሪ (B.th ) ተመርቋል፡፡ በአልፋ ዩኒቨርሲቲ በ management ዲግሪውን ተከታትሏል፡፡ ወደቆ የተገኘው መጽሐፍ ደራሲ እና መምህር ነው፡

ምሁራን እና አገልጋዮች ስለ መጽሐፉ የሰጡትን አስተያየቶች ሙሉውን በመጽሐፉ መጨረሻ ያገኙታል፡፡ ጥቂቶቹን ቀንጭብን አነሆ ብለናል፡

መምህር የማርያምወርቅ ተሻገር ያሳተመው መጽሐፍ ለግንዛቤና ለትምህርት እንዲሆነን በተለይም ጥልቅ የሀገር ፍቅር እንዲኖረን በሃይማኖታዊ ዝማሬዎች ሀገራዊ ፍቅር፣ አብሮነትንና ሰላማዊ መስተጋብርን እንድንመለከት አድርጎናል፡፡ - እኛ እና እነሱ ከመሰባል ወጥተን በሚያቀራርበን እንዲሁም በሚያግባቡን፣ አንድ በሚያደርጉን ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አተኩረን ብንሠራ የሚል መልእክት ያዘለ ጽሑፍ ሆኖ አግኝቸዋለሁ።

ለቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ (የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፉ)

በፈተና ስለኖረችውና በመከራ ውስጥ ስላለችው ኢትዮጵያና ሕዝቦችዋ በተለይ ዛሬ እንደ ሀገር በከባዱ እየተናወጥን ባለንበት ጊዜ ላይ ይህን መጽሐፍ ማዘጋጀት ተስፋ ሳይቆርጡ ህልውናዋ ላይ የተጋረጡ ቸግሮችዋን እየጠረጉ ቀጣይነቷን ለማረጋገጥ የሚጥሩ ልጆች ያላት መኾኑን ያሳያል፡፡ ሊነበብ የሚገባው መጽሐፍ።
ቀሲስ መዝገቡ ካሳ ፈለቀ (ዶ/ር) (በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ከ የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ)

መጽሐፉ የቆሰለውን አብሮነታችንን ለማከም ሀገራዊ ስናፍጭ፤ የተሰበረውን ማኅበራዊ እሴት ለመጠገን ብሔራዊ ከርቤ ሆኖ ያገለግላል የሚል እምነትና ተስፋ አለኝ። ኢትዮጵያዊነት እንዲያንሰራራ፣ ሀገራዊ ፍቅር እንዲቀጣጠል፣ ሃይማኖታዊ መከባበር እንዱሰፍን፣ የጋራና የትስስር ታሪክ እንዲስፋፋ፣ ግፍንና በደልን የመቃወም ባህል እንዲዳብር የሚወድ ሁሉ ሊያነበውና ሊያስነብበው የሚገባ ጥናታዊ መጽሐፍ ነው።
ዲያቆን ታደሰ ወርቁ (ጸሐፊ እና አርታዒ)

ወገንተኛ ሳይሆን ከብዙ ልፋትና መንከራተት በኋላ ይህን የመሰለ ድንቅ ስራውን አቅርቦልናል። ሥራው ምን ያህል ከባድ እንደነበረ ይህን መጽሐፍ የሚያነበው ይረዳዋል። በግምት እና በመሰለኝ ሳይሆን በላይንሳዊ ዘዴ በስልት እና በስሌት የተሰራ ነው። ሀገሬን በአራቱ ሀይማኖቶች መነፅር ማየት እፈልጋለሁ። በተለይ ባለፉት 20 ዓመታት የሃይማኖቶቹ የጥበብ ሰዎች በመዝሙር፣ በመንዙማና በነሺዳ እንዴት እንዳገለገሉዋት ልወቅ ባይ ከእዚህ የተሻለ መጽሐፍ ሊያገኝ አያገኝም። የማርያምወርቅ እጅግ ቅን ትሁት ፀሐፊ መሆኑን ስራውን በማየት መመስከር ይቻላል። ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነት በአራቱም ሃይማኖቶች እንዴት ተገለፁ? ለምንድነው ዘማሪዎች እና ሙንሺዶቹ ትናንትን ናፍቀው ያ ቀን እንዲመለስ የሚጠይቁት? መጽሐፉን እያነበብን ከራሳችን ጋር ቆም ብለን እንድናወራ ይጋብዘናል።
ሁሴን ከድር (ጋዜጠኛ፣ ደራሲ እና አርታኢ )

ደራሲ የማርያምወርቅ ተሻገር የተማረበትንና የተመራመረበትን፣ ያጠናውንና ያሰላሰለውን፤ የተደነቀበትንና የተመረቀበትን ጽሑፍ በመጽሐፍ አዘጋጅቶ አቅርቦልናል፡፡ መዝሙርንም ይሁን መንዙማን ስንሰማ ልብ ያላልናቸው የኢትዮጵያዊነትን ከቡር ሐሳቦች እንድናስተውል እያደረገን ለወደፊትም ሰሚዎች ብቻ ሳንሆን አድማጮች፣ አስተዋዮች፣ አሳላሳዮች እንድንሆን የሚያበረታታን ድንቅ መጽሐፍ አቅርቦልነናል፡፡ መልካም ንባብ እመኛለሁ!
ዶክተር ወዳጄነህ መሐረነ (የህከምና፥ የስነልቦና ፣ የስነ መለኮት ምሁር)

በዚህ መጽሐፍ የቀረበው የጥናት ውጤት ለከፍተኛ ትምህርት ማጠቃለያ የምርምር ሥራ ሆኖ አዘጋጁን "ጥቁር ካባ ደርቦ እንዲመረቅ ያበቃው የድካሙ ፍሬ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ አድካሚ የምርምር ሥራው በዩኒቨርስቲ ሼልፍ ላይ ብቻ ተቆልፎበት እንዳይቀር በማሰብ ለእኛ ለተራ አንባቢዎች በሚገባን ዐውድ ልክ ተመጥኖ እንዲቀርብልን መደረጉ የአዘጋጁን የሩቅ ርዕይ "ባለጠግነት” የሚያረጋግጥ ምሥከር ነው፡፡
ጌታቸው በለጠ (የቀድሞ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ፕሬዚዳንት)

የማርያምወርቅ የሠራው ይኸ መጽሐፍ ጥናት ላይ የተመሠረተ ነው:: በተቻለው አቅም ሁሉን ያማከለ ነው:: ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በአራቱ ሃይማኖቶች መዝሙር፣ ነሽዳ እና መንዙማወችን አጠናቅሮ የተሰራ ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያዊና እንደ ሃይማኖተኛ ያሉትን መልካም ነገር መዝኖ በማሳየቱ ሊደነቅ የሚገባው ነው። በመጀመሪያ ደረጃ የሀገሪቱን ስታስቲክስ ተከትሎ አራቱን ሃይማኖቶች በማሳያነት መምረጡ፤ እንድ ሀይማኖትን ብቻ አለማለቱ፣ ከየእኔ ብቻ አመለካከት መውጣቱ፤ በራሱ ብዙዎች የሌላቸው እና ሊደነቅ የሚገባው ጉዳይ ነው፡፡ በተለይም ብዙ ጊዜ በኢትዮጵያ ውጨኛው ማኅበራዊ ሚዲያ ችላ የምትባለውን የኢትዮጵያ ካቶለካዊት ቤተከርስቲያንን የቃኘ መሆኑ ይበል የሚያሰ ሚዛናዊነት ያለበት መሆኑን ያሳያል። ...

ራእይ ሳሙኤል (በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተከርስቲያን የካፑቹን ፍራንቼስካዉያን የነገረ መለኮት ተቋም ተማሪ እና የጽሞና ቅጥር የተሰኘ የግል የመዝሙር አልበም ዘማሪ፤ ገጣሚና የዜማ ደራሲ።

ዋና አከፋፋይ ፦ ሀሁ መጻሕፍት መደብር

**************

በመደብራችን ሁሉም አይነት መጻህፍት ይገኛሉ። የትምህርት መርጃ መጻህፍት፣ የልብወለድና የታሪክ መጻህፍት፣ መንፈሳዊና አለማዊ መጻህፍት፣ የግጥምና የወግ መጻህፍት፣ የፖለቲካና ኢኮኖሚ እሳቤ መጻህፍት፣ የፍልስፍና እና የስነልቦና መጻህፍት ሁሉም አሉ። ሀሁ መጥታችሁ የፈለጋችሁትን ብቻ ሳይሆን የረሳችሁትንም መጻህፍት ታገኛላችሁ። ከእናንተ የሚጠበቀው ግዜ ወስናችሁ መምጣት ብቻ ነው።

ሌላው በመደብራችን ከ20—50% ቅናሽ አለ። አስር መጽሀፍ ለሚገዙ ደንበኞቻችን ደግሞ አንድ መጽሀፍ በነጻ እናበረክታለን። ስትጎበኙን በደስታ፣ በቅልጥፍና እናስተናግዳችኋለን። ባላችሁበት ሆናችሁ መረጃ ለመጠየቅ ካሻችሁም ስልኩን አንስታችሁ ሀሎ በሉን።

በመደብራችን ሀሁ መጻህፍት ሁሉንም አይነት መጽሀፍ ያገኛሉ፦

የቆዩ እና አዲስ
መንፈሳዊም ሆነ አለማዊ
ክላሲክም ሆነ ዘመናዊ
የታሪክ፣ የፍልስፍና፣ ልብወለድ፣ የትምህርት፣ የስነልቦና፣ የሃይማኖት፣ ግለታሪክ ወዘተ

ሀሁ መጻህፍት መደብርን
በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@fantahunabie?_t=8mYzg7vMRJ0&_r=1
በቴሌግራም https://t.me/fanab123
እንዲሁም በራሱ የፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/hahubook?mibextid=ZbWKwL
ማግኘት ይቻላል።

የፈለጋችሁትን መጽሀፍ እዘዙን፣ ጠይቁን። በቅልጥፍና፣ ከ20-50% በሚደርስ ቅናሽ፣ በደስታ እናቀርብላችኋለን።

አስታውሱ! በመደብራችን 10 መጻህፍት ለሚገዛ 1 መጽሀፍ በነጻ እንሰጣለን።

#የሀሁ_መጽሐፍት_መደብር

አድራሻ ቁ.1 አራት ኪሎ አብርሆት ጎን

ስ.ቁ 0911006705/0924408461

ሀሁ መጻሕፍት ( Hahu books )

04 Oct, 11:04


ስነ ፍጥረት ይመረመርበታል። ረቂቁ ዓለም ይተነተንበታል። ፍጥረት በየ ፈርጅ ፈርጁ ይቀመጥበታል። ሊቃውንት ባሕረ ሀሳብን እንደ ማሳያ ውስደው ዘመን እና ወቅትን ይቀምሩበታል።
ማን ነው? ትሉ እንደሆን መጽሐፈ አቡሻክር ድርሻውን ይወስዳል።
አስተውሎትን፣ ትጋትን፣ ትዕግስትን እና ጥበብን የሚሻ እውቀትን የያዘ ነው መጽሐፈ አቡሻክር። ከጥቂት ሊቃውንት በቀር የደፈረው የለም።
ከጎንደር መንበረ መንግሥት መድኃኔዓለም ሊቃውንት በአንዳቸው በኩል ይህንኑ እውቀት በሚገባን ቋንቋ ሊያደርሱን ከተፍ ብለዋል። እጅ ከምን ባንላቸውም የዓለም መቃኛ የሆነውን እውቀት የያዘ መጽሐፍ በገበያ ላይ አውለዋል።
የዓለምን ምስጢር ለማወቅ እና ለመፈለግ የምትኳትኑ ፈረሱም ሜዳውም ይኸው..........
©Taodokos Nat Enatie
ዋና አከፋፋይ ፦ሀሁ መጻሕፍት መደብር

**************

በመደብራችን ሁሉም አይነት መጻህፍት ይገኛሉ። የትምህርት መርጃ መጻህፍት፣ የልብወለድና የታሪክ መጻህፍት፣ መንፈሳዊና አለማዊ መጻህፍት፣ የግጥምና የወግ መጻህፍት፣ የፖለቲካና ኢኮኖሚ እሳቤ መጻህፍት፣ የፍልስፍና እና የስነልቦና መጻህፍት ሁሉም አሉ። ሀሁ መጥታችሁ የፈለጋችሁትን ብቻ ሳይሆን የረሳችሁትንም መጻህፍት ታገኛላችሁ። ከእናንተ የሚጠበቀው ግዜ ወስናችሁ መምጣት ብቻ ነው።

ሌላው በመደብራችን ከ20—50% ቅናሽ አለ። አስር መጽሀፍ ለሚገዙ ደንበኞቻችን ደግሞ አንድ መጽሀፍ በነጻ እናበረክታለን። ስትጎበኙን በደስታ፣ በቅልጥፍና እናስተናግዳችኋለን። ባላችሁበት ሆናችሁ መረጃ ለመጠየቅ ካሻችሁም ስልኩን አንስታችሁ ሀሎ በሉን።

በመደብራችን ሀሁ መጻህፍት ሁሉንም አይነት መጽሀፍ ያገኛሉ፦

የቆዩ እና አዲስ
መንፈሳዊም ሆነ አለማዊ
ክላሲክም ሆነ ዘመናዊ
የታሪክ፣ የፍልስፍና፣ ልብወለድ፣ የትምህርት፣ የስነልቦና፣ የሃይማኖት፣ ግለታሪክ ወዘተ

ሀሁ መጻህፍት መደብርን
በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@fantahunabie?_t=8mYzg7vMRJ0&_r=1
በቴሌግራም https://t.me/fanab123
እንዲሁም በራሱ የፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/hahubook?mibextid=ZbWKwL
ማግኘት ይቻላል።

የፈለጋችሁትን መጽሀፍ እዘዙን፣ ጠይቁን። በቅልጥፍና፣ ከ20-50% በሚደርስ ቅናሽ፣ በደስታ እናቀርብላችኋለን።

አስታውሱ! በመደብራችን 10 መጻህፍት ለሚገዛ 1 መጽሀፍ በነጻ እንሰጣለን።

#የሀሁ_መጽሐፍት_መደብር

አድራሻ ቁ.1 አራት ኪሎ አብርሆት ጎን

ስ.ቁ 0911006705/0924408461

ሀሁ መጻሕፍት ( Hahu books )

30 Sep, 17:09


በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው መጽሐፍ #ጥቅምት_2 ሊመረቅ ነው።

ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ በፀያሔ ፍኖት ቀጣይ ክፍሉ #ስለ_ድንግል_ማርያም መሆኑ ጠቁመውን ነበር።እንሆ ጊዜው ደርሶ መጽሐፉ ታትሞ ጥቅምት ፪ ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ሊመረቅ ነው። መርሐግብራችን እናስተካክል እንዘጋጅ።

**************

በመደብራችን ሁሉም አይነት መጻህፍት ይገኛሉ። የትምህርት መርጃ መጻህፍት፣ የልብወለድና የታሪክ መጻህፍት፣ መንፈሳዊና አለማዊ መጻህፍት፣ የግጥምና የወግ መጻህፍት፣ የፖለቲካና ኢኮኖሚ እሳቤ መጻህፍት፣ የፍልስፍና እና የስነልቦና መጻህፍት ሁሉም አሉ። ሀሁ መጥታችሁ የፈለጋችሁትን ብቻ ሳይሆን የረሳችሁትንም መጻህፍት ታገኛላችሁ። ከእናንተ የሚጠበቀው ግዜ ወስናችሁ መምጣት ብቻ ነው።

ሌላው በመደብራችን ከ20—50% ቅናሽ አለ። አስር መጽሀፍ ለሚገዙ ደንበኞቻችን ደግሞ አንድ መጽሀፍ በነጻ እናበረክታለን። ስትጎበኙን በደስታ፣ በቅልጥፍና እናስተናግዳችኋለን። ባላችሁበት ሆናችሁ መረጃ ለመጠየቅ ካሻችሁም ስልኩን አንስታችሁ ሀሎ በሉን።

በመደብራችን ሀሁ መጻህፍት ሁሉንም አይነት መጽሀፍ ያገኛሉ፦

የቆዩ እና አዲስ
መንፈሳዊም ሆነ አለማዊ
ክላሲክም ሆነ ዘመናዊ
የታሪክ፣ የፍልስፍና፣ ልብወለድ፣ የትምህርት፣ የስነልቦና፣ የሃይማኖት፣ ግለታሪክ ወዘተ

ሀሁ መጻህፍት መደብርን
በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@fantahunabie?_t=8mYzg7vMRJ0&_r=1
በቴሌግራም https://t.me/fanab123
እንዲሁም በራሱ የፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/hahubook?mibextid=ZbWKwL
ማግኘት ይቻላል።

የፈለጋችሁትን መጽሀፍ እዘዙን፣ ጠይቁን። በቅልጥፍና፣ ከ20-50% በሚደርስ ቅናሽ፣ በደስታ እናቀርብላችኋለን።

አስታውሱ! በመደብራችን 10 መጻህፍት ለሚገዛ 1 መጽሀፍ በነጻ እንሰጣለን።

#የሀሁ_መጽሐፍት_መደብር

አድራሻ ቁ.1 አራት ኪሎ አብርሆት ጎን

ስ.ቁ 0911006705/0924408461