ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ @binibook Channel on Telegram

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

@binibook


👉 ሰሞነኛ ትኩስ መፅሐፍት ከነድስቱ እንገጮታለን።
👉 ዘርፈ ብዙ የሆነውን የኪነት ወሬ እስከነቃጭሉ ዱብ እናረጋለን።
👉 ነባርና አዳዲስ መፅሐፍትን መጠነኛ ዳሰሳ አድርገን እንጠቁሞታለን።

ወሬ ጥሩ ስለሆነ በዚህ ቦይ ላኩልኝማ @a3b2ysm

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ (Amharic)

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ በእኛ ላይ ነው። እዚህ ቦይ ለትኩስ መፅሐፍት እንገጮታለን። ብዙ የሆነውን የኪነት ወሬ እስከነቃጭሉ ዱብ እናረጋለን። እናንት ከሆነ ክፉ የሆነውን መፅሐፍት ለመጠነኛ ዳሰሳ አድርገን እንጠቁሞታለን። ወሬ ጥሩ ነው እናንት ለማን ይጠቅማል ብትችል ማንበብ @a3b2ysm ላኩልኝ።

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

18 Nov, 14:18


በአንድ ዓይነት ሙያ ውስጥ በሕይወትህ እንዴት ገብተህበት እንደምትሣተፍ አታውቀውም፡፡ ዜና ዘግቤ አላውቅም:: ጋዜጣ ላይ በመጻፍ ሃሳቤን እንድዘራ በበዓሉ ግርማ ታጨሁ:: በኋላ ነው “እ! ለካስ ጀምሬዋለሁ የምትለው፡፡ በአንድ ወቅት በትምህርት ሚኒስቴር በስኮላርሺፕ ክፍል እየሰራሁ እያለ አንዱን ቀን በአሉ ግርማ “እዚህ ዝም ብለህ ከቢሮክራሲ ሥራ ጋር ጊዜህን አታባክን፡፡ አሁን በስኮላርሺፕ ለምትሠራው ሥራ አገሪቱ በርካታ ሰዎች አሉዋት፡፡ ለአንተ ተፈጥሮ የእኛ ሙያ ነው የሚስማማህ” አለኝ፡፡

“እሺ እውነትክን ነው” አልኩና መልቀቂያ እንዲሰጠኝ ላለሁበት ትምህርት ሚኒስቴር ማመልከቻዬን ጻፍኩ፡፡ እዚህ ላይ

አንድ Interesting ነገር ልጨምርልህ፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ምክትል ሚኒስትር ማመልከቻዬን አይቶት “ለምን ትሔዳለህ? እኛ እንፈልግሃለን፣ እድገትም አስበንልሀል''

አለኝ፡፡ ከዚህ ሰውዬ ጋር ጥሩ የሥራ ጊዜ አሣልፌያለሁ፡፡ በባህሪው እዚህ'ጋ ብቻ አበሽነቱን አየሁበት፡፡ በውሳኔዬ እንደፀናሁ ሲያይ ጊዜ፣ በፃፈልኝ የመሸኛ ደብዳቤ ላይ “ያሰብንለት እድገት የሌለ መሆኑን እናስታውቃለን” ይላል፡፡ አየህልኝ? ማስታወቂያ ሚኒስቴር ሄጄ እድገት ታስቦልኛል ጨምሩልኝ ብዬ እንዳልወተውት መሆኑ ነው፡፡ በሄደበት ይቆርቁረው፣ የታባቱን! ዓይነት ነገር ናት የክቡር ሚኒስትሩ ደብዳቤ፡፡

እኔ ግን እየታዘብኩት ከበአሉ ግርማ ጋር ሥራ ጀመርኩ፡፡ ከበአሉ ጋር መሥራት ማራኪ ነው፡፡ የመጀመሪያ ሥራዬ እንዲሆን አፈወርቅ ተክሌን አነጋግርና ጻፍ አለኝ፡፡ እኔ እንዲህ ዓይነት ዝነኛ ሰው አነጋግሬ አላውቅም፡፡ ስለምፈራ ተወኝ፣ አንተው እንደ ለመድከው ሂድ አናግረው አልኩት፡፡ “እኔም አብሬህ እሄዳለሁ" አለኝ፡፡ ተስማማሁ፤ ሄድን፡፡ አፈወርቅን ሳየው እንደገመትኩት

#ማስታወሻ
#ስብሃት_ገ/እግዚአብሔር
#ዘነበ ወላ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

17 Nov, 05:33


የገቢ ንግድን ለመቀነስና የወጪ-ንግድን ለማበረታታት መወሰድ ያለባቸው ፖሊሲዎች የዋጋ ንረትን ሊያመጡ ይችላሉ፡፡ በአጠቃላይ የገቢ ዕቃ ከቀነሰ ወይም የወጪ ዕቃ ከጨመረ በተያያዥ ወይ ገቢ ይጨምራል ወይ ፍጀታ ይቀንሳል፤ ይሀም አጠቃላዩ የመዋዕለ-ንዋይ መጠን አይቀንስም ብለን ታሳቢ ካደረግን ነው:: ነገር ግን የገቢ ዕቃዎች ውድ በሆኑ የአገር ውስጥ ዕቃዎች ስለሚተኩና አዲሱ የወጪ ንግድም በድጎማ የሚመረት በመሆኑ የሚመረተው ምርት ዋጋው ከሚያፈራው ገቢ በታች ስለሆነ፣ የዋጋ ንረቱ ጫና ከገቢ-ዕቃ ቅነሳው በላይ ነው የሚሆነው፡፡ ይህ ደግሞ በስተመጨረሻ በበጀት ጭማሪ መልክ (በድጎማና የወጪ-ንግድ ማበረታቻ መልክ) የመንግስት በጀት ላይ ይታያል፡፡

ከውጪ የሚገቡትን ዕቃዎች በአገር ውስጥ ምርት የመተካቱና የወጪ-ንግዱን የማጠናከር ስራዎች አስቸኳይ ያልሆነ የመንግስት ሥራ ላይ የተሰማራውን የሠው ሃይልና ሃብት ወደነዚህ ስራዎች በማዛወር የተከወነ ከሆነ፣ በበጀት በኩል ይመጣ የነበረውን የዋጋ ንረት ጫና መቋቋም ይቻላል፡፡ ... የመንግስት ሥራዎችን ለወጪ-ንግድ ማጠናከርና የገቢ-ዕቃዎችን በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ለሚደረገው ስራ ሲባል የማቆሙ ፖሊሲ ሊተገበር የሚገባው፣ አዲሶቹ የሥራ መስኮች የሚፈጥሩት የሥራ ዕድል የሥራ አጥነቱን ችግርም አብረው የሚፈቱ ከሆነ ነው፡፡

#የታዳጊ አገሮች ኢኮኖሚ
#ሚካኤል ካልስኪ
#ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገዳ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

14 Nov, 15:08


እኮኢዝም፡ በብዙ የሃሳብ ልውውጦችና ጉሥዐተልብ (discourse) ጋጋታዎች ላይ “እኮ የተባለ ቃል ደጋግሜ እሰማለሁ:: የዚህ ቃል ትርጉሙ ለብቻው ምን እንደሆነ ባላውቅም በጆሮዬ ሲገባ ግን አፌን ዳባ ዳባ ይለኛል፡፡ ያልወለዱት ልጅ “አባባ' ሲልዎ ወይም “እማማ' ሲልዎ ዐይነት:: አይጥመኝም ማለቴ ነው:: እስኪሰለቸኝ ሰምቼው ምንም ትርፍ ትርጉም ሊያመጣ ስላልቻለ፣ ወይም፣ ብዙ ጊዜ የምሰማው ረቂቅ የመሰለ ውይይት ላይ የሆነ መደዴ ሃሳብ የደካማነት ጠባሳውን ሊጋርድ እንደ ካባ የሚለብሰው ቃል ስለሆነ ይሆናል፡፡ በ “እኮ” የታጀቡ አንዳንድ ሂሳዊ ስልቶች እውነታን እናስጨብጣለን ብለው ይነቃነቁና ሳይሳካላቸው በሄዱበት ወጥተው ይቀራሉ፣ ተመልሰው ከመጡም ፈንጠዝያ ያስታቅፉናል፡፡ በተከዳው ልቦናችንም ውስጥ ተስፋ መቁረጥ ዘውድ ትጭናለች፡፡ ምክንያቱም በ “እኮ‛ የተጀመረው ነገር ምክንያት መሰለ እንጂ ምክንያት አይደለም፡፡ “እኮ' አፍ ውስጥ ቦታ ትይዛለች፣ የአዳማጭ ጆሮ ታጣብባለች እንጂ ምክንያት የማትሰጥ ምክንያት ናት፡፡ ድልድይ መስላ ተዘርግታ እናያታለን እንጂ እወዲያ ሄዳ የምትቆምበት ደረቅ ወደብ የሌላት ለአንድ እግረኛ ብቻ የምትበቃ የአንድ አቅጣጫ መንገድ ናት፡፡ አውስጥዋ የተቀመጠው ዐይነአፋር ነው፨ ጡንቻ ያለው የመሰለ ቀጫጫ ነው፡፡ የተማረ የመሰለ መሃይም ነው፡፡ ያወቀ የመሰለ አላዋቂ ነው፡፡

#የስንብት ቀለማት
#አዳም ረታ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

14 Oct, 14:41


ሁለተኛ፡-
መካከለኛው የፊልም ዘመን በኢትዮጵያ እና የተከታታይ ድራማ አጀማመር በኢትዮጵያ ላይ የነበረ የአሠራር መንገድ፣ ተግዳሮት እና ዕድሎች ማጥናት ለሚሻ ሰው ትልቅ ፋይዳን የሚሰጥ መጽሐፍ ነው። ስለ መንትያ፥ የንዋይ ሰለቦች፥ ትዝታ፥ ፊርማ፥ ምርጫ፥ ይቅርታ፥ አጋጣሚ፥ መላ ... የተሰኙ ሥራዎቹን ከቅድመ-ቀረጻ እስከ ድኅረ-ቀረጻ የነበረውን በማተቱ በኩል የኢትዮጵያ የፊልም፣ የድራማ ታሪኮችን ለሚሰንድ የጥናት ባለሙያ አንዱ ዋቢ የሚሆን ቅምጥ ጽሑፍ ማዘጋጀቱ ትልቅ አበርክቶት ነው። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅት ለወደፊቱ ታሪኩን ሲሰንድ ኹነኛ ማጣቀሻ የሚኾን መጽሐፍም ነው።

ሦስተኛ፡-
የጋሽ ተስፋዬ የማስታወቂያ ሥራ አጀማመሩ፣ አካሄዱ እና ዕድገቱን በማካተቱ ወደዚህ ሥራ ለሚገቡ ሰዎች ቀላል የማይባል ጥቁምታ ሰጪ ነው። ባለታሪኩ ከምንም ተነስቶ እዚህ መድረሱ በራሱ፣ በቀቢጸ-ተስፋ ለሚናውዘው የሀገራችን ወጣት “ዝሆንም በልጅነቱ ትንሽ ነበር!” ብሎ እንዲነሳሳ የማድረግ አቅሙ ላቅ ያለ ነው።

አራተኛ፡-
በሀገራችን ያለው የግለሰብ ታሪክ አጻጻፍ የረጋ ሐይቅም አይደል? ልክ እንደ ሰዋሰው ባለቤት፥ ተሳቢና ግስ። ተወለደ፥ አደገና ሞተ የግለሰብ ታሪክ የአጻጻፍ ቀኖና መስሎ ነበር። ጋሽ ተስፋዬ ዐዲስ በኾነ የአጻጻፍ መንገድ መከሰቱ ለሀገራችን ሥነጽሑፍ አንድ ትልቅ ዕምርታ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ጥናትና ውይይትን ይሻል።

አምስተኛ፡-
ይህ መጽሐፍ በጋሽ ተስፋዬ ዘመን ለነበሩ ጉምቱ የዘመን ጓዶች የራሳቸውን ታሪክ እንዲጽፉ ተነሳሽነትን የሚፈጥር ነው ብዬ አምናለሁ። ጉምቱ ሰዎቻችንን ባጣን ቁጥር ለቀብር ቀን የሚነበብ የሟች የሕይወት ታሪክ ጽሑፍ እስከማጣት መድረስ እንደ ዓመት በዓል በየዓመቱ የምንደጋግመው የሲሲሰፈስ እርግማን ኾኖብናል። ታላላቆቻችንን ባጣን ቁጥር እዝራ እጅጉ ወደ ሚያዘጋጀው “መዝገበ አእምሮ” እና ወደ ማዕዛ ብሩ “የጨዋታ እንግዳ” መርሐግብር" የምናማትረው በዚህ ምክንያትም አይደል? ይህ መጽሐፍ ጉምቱ ሰዎቻችን በተለይም የጋሽ ተስፋዬ የዘመን ጓዶች እንዲጽፉ የሚያነሳሳ ነው። ሁሉም የራሱን መልክ በጽሑፍ ከገበረ ደግሞ የዘመን ምስል እና የሀገር ቁመና ይከስትልናል። ጋሽ ተስፋዬ የራሱን ፊት እስከነቡጉሩ በማሳየት “ኑ አብረን የዘመን እና የሀገርን መልክ ለዚህኛውና ለሚመጣው ትውልድ እናሳይ” የሚል ትልቅ ቀጨምታን (inspiration) ገብሯል፤ ለዘመን ጓዶቹ።

ስድስተኛ፡-
ከዚህ በኋላ ለሚጻፉ የግለሰሰብ ታሪኮች በእነዚህ ምክንያት ደንበኛ ማጣቀሻ የመኾን ዕድል ያለው ይመስለኛል። እጅጉን ግላዊ የሚባለው ነገር ለሰዎች ትምህርት ይኾን ዘንድ ሊሰዋ እንደሚገባ፥ ከታሪኮች መሃል የተሻለውን መርጦ መከተብ የመጽሐፉን አቅም እንደ ሚወስን፥ የራስ ታሪክ የሚደምቀው በሌሎች ታሪክ መሃል መኾኑን፣ የሌሎችን ታሪክ ስናስገባ ዐውዱን በጠበቀ መልኩ እና በልክ መኾን እንዳለበት መጽሐፉ በጉልህ ይናገራል።

ሥነ ጽሑፋዊ ውበት፥ ቋንቋ፥ ሥርዓተ ነጥብ፥ ሰዋሰው እጅግ ውብ በመኾኑ ከዚያ ውስጥ ሕጸጽ ለማውጣት መሞከር “ከቁንጫ ሌጦ” ማውጣትን የሚጠይቅ አድርጎብኛል።

የመጽሐፉ ርዕስ - ከማዕበል ማዶ

ደራሲ - ተስፋዬ ማሞ

ዘውግ - ኢ-ልቦለድ (ቅይጥ ወይም የተስፋዬ መንገድ)

የገጽ ብዛት - 364

የኅትመት ዘመን - 2017

የዳሰሳው አቅራቢ - ቢኒያም አቡራ (የባለቅኔዋ ሶሪት እና ወደ ፍቅር ጉዞ መጻሕፍት ጸሐፊ) [email protected]

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

14 Oct, 14:41


የተስፋዬ ቤት - ከማዕበል ማዶ
ከቢኒያም አቡራ

ቅይጥ ወይስ የተስፋዬ ቤት
የጋሽ ተስፋዬ ማሞ “ከማዕበል ማዶ” የተሰኘው መጽሐፍ፥ በስፍን ቅንብብ ለመታጠር ያልፈቀደ “አመጸኛ ጅረት” ነው። አሃዱ ብለን፥ "የአንድ ዕብድ ቀን ውሎ" ጋር ስንፋጠጥ፥ “ይሄ ነገር በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ ግለ ሕይወት ታሪክ (auto-fiction) ነው እንዴ?” ያሰኘናል።

ጥቂት ፈቀቅ እንዳልን ግን ጥንቅቅ ያለ የግለ ሕይወት ታሪክ (autobiography) ቅርጽ ይመጣል። በራሱ ላይ ትኩረት ከመስጠቱ እና በራሱ ብዕር ከመተረኩ ባሻገር፥ በየዘመናቱ የደረሰበትን አስተሳሰብን እንደ ብር ጻሕል ዘርግቶ፥ ሥነ-ልቦናዊና ፍልስፍናዊ ቀለማትን እንደ ወርቅ እንኮይ ያቀርባቸዋልና፥ “ይሄማ ደንበኛ ግለ ሕይወት ታሪክ (autobiography) ነው!” እንድንል ይገፋፋናል። ለአብነትም ያህል ከመጽሐፉ ውስጥ ይሄን መመልከት እንችላለን፡- “… ከሰዎች ጋር ለመግባባት ምንም ያህል ጊዜ አይፈጅብኝም። ግልጽነቴም ለአንድ የፖለቲካ ሠራተኛ ከሚያስፈልገው ቁጥብነት የሚያልፍም ይመስለኛል። ችኩልነትም አያጣኝም። አንድን ነገር ለማድረግ ካሰብኩ ይዋል ይደርን አላውቅም፤ አደርገዋለሁ። ቡቡ ነገርም ነኝ። ለደስታም ለኀዘንም ትንሽ ይበቃኛል። ይህ ባሕርዬ የከፋ ጉዳት ባያደርስብኝም አልፎ አልፎ የሰው የሆኑ ጥቃቅንም፣ ትልልቅም ስህተቶችን ያሠራኛል። በአጠቃላይ እነዚህ ባሕርይዎቼ ተደማምረው ብዙ ጊዜ ለጥቃት አጋልጠውኛል።” (ገጽ 122)

ግና … ቅደም-ተከተላዊ (chronological) ተረክ ጥሶ፥ ከገጠመኞቹ መካከል ሊያስተምሩ ይገባል ያላቸውን ብቻ መርጦ፥ ከድርጊቱ ይልቅ ለድርጊቱ ያለው አተያይ አድልቶ ወደ ግለ ማስታወሻ (memoir) የአጻጻፍ ምኩራብ ላይ ተሰይሞ እናገኘዋለን። ለምሳሌ፡- 2006 ላይ ሲቆዝም ያስነብበን እና 15 ዓመት ወደ ኋላ ይወስደናል፥ ከዚያ በድጋሚ ወደ 2006 ያመጣንና ከመቅጽበት ወደ 1949 ዓ.ም የኋላ ሽምጥ ያስጋልበናል። በተጨማሪም ከገጠመኞች መካከል ሊያስተምሩ ይገባል ያላቸውን መርጦ በማስፈር ረገድ፥ ወደ ግለ ማስታወሻ (memoir) አጻጻፍ ያደላበትን ለአብነት ያህል እንጥቀስ። የማክሲም ካፌን እና የእያሱ በርኼን ተረክ ካወጋን በኋላ፥ ከዚህ ዘመን ኩነት ጋር ነጽሮ ትዝብቱን እንዲህ በማለት ያጋራል፡- “ሁልጊዜ ከሚያስቆጩኝ ነገሮች መካከል አዲስ አበባ ይህንን ጥሩ ባሕል ማጥፋቷና ማምከኗ ነው። ሊበረታታ፣ ሊያድግ፣ ሊስፋፋ፣ የሚገባው ነገር በፖለቲካዊ ተጽዕኖዎችና ፍላጎቶች ምክንያት ከስሞ ወጣቶች ከአርአያዎቻቸው ጋር በቅርብ የሚተያዩበትና ተምሳሌት የሚፈጥሩበትን ዐውድ ማጣቷ የሚያስቆጭ ነው። አዲስ አበባ ዐዳዲስ ወጣቶችን በማፍራትና የኪነጥበብ ሰዎች እንደየዝንባሌያቸው በነጻነት የሚገናኙበት ቦታ የሌላት መሆኑ ያሳዝናል። ዛሬም ከሠራቻቸውና ከምትኩራራባቸው በርካታ ሜጋ ፕሮጄክቶች ፓርኮች፣ አደባባዮች መናፈሻዎችና ጊዜ ማሳለፊያዎች ባለፈ እንዲህ ዓይነት ጥበባዊ ልምምዶች በነጻነት የሚካሄዱባቸውን ቦታዎች አለመሥራቷ ኪሳራዋ ይመስለኛል።” ገጽ 269

የተስፋዬ ብዕር አመጸኛ ጅረት ነውና በዚህ አያከትምም። ወደ ትዝታ (reminiscence) ጎሬ ውስጥም ጎራ ይላል። ነባር የተሰነዱ የሕይወት ዘገባዎችን ግልጋሎት ላይ ሳያውል፥ በትዝታ ብቻ ወደ ኋላ ሽምጥ ጋልቦ፥ በአሁናዊ ኹኔታ የሚታወስን ድርጊት በሌሎች ላይ አተኩሮ ይጫጭራልና።

የጋሽ ተስፋዬ ብዕር በሕግ እና በደንብ መቀንበብን ያልፈለገች ነጻ ልሳን ናት። ሕግን የምታውቅ ግን ለዛ ባለው መንገድ የደንቡን ኮረብታ የምትነድል ብዕር። የስፍን መጋረጃን ለመቅደድ የፍንገጣ መቀስ የሰደደች ብዕር። የዚህን መጽሐፍ ስፍን፥ “ቅይጥ” ከማለት ይልቅ “የተስፋዬ ቤት” ወይም “የተስፋዬ መንገድ” ልንለው እንችል ይሆን? ከማዕበል ማዶ ለግለ ሕይወት ታሪክነት (autobiography) ያደላ አጻጻፍ መኾኑን አለማመን ግን እብለት መኾኑን ልብ ይሏል።

ከማዕበል ማዶ vs የአንጋፋዎቹ ግለሰቦች ታሪክ
ከማዕበል ማዶ ከታሪክ ሰነድነት አኳያ፥ የየካቲት 66 የፖለቲካ ትምህርት ቤት ቁመና ኾነ፥ የፓዊ-መተከል ሠፈራ ጣቢያ ውስጥ ያለው ሐተታ ከየኔታ ተመስገን ገብሬ (ሕይወቴ) የፋሺስት ጭፍጨፋ የዓይን እማኝነት ጋር አይጋጠምምን? … የባለታሪኩን ሙያ በማተት ረገድ የሕክምና፥ የፊልም እና የድራማን እንዲሁም የማስታወቂያን ሙያን ከፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ (አንዳፍታ ላውጋችሁ) የካታሎግ አሠራርን፥ የአተረጓጎም ሥልት ሐቲትን አይተዝትምን? …እንደ ትዳር ያለ እጅጉን ግላዊ ነገር አደባባይ ላይ በግልጸኝነት በማውጋት በኩል፥ ከጋሽ በቀለ ወልደ ኪዳን (ጣልቃ እየገባ) ያንስ ይኾን? … ልጅነትን፥ የቅርብ ዘመድን ቤተሰብን በመተረክ ረገድ ከአብዬ መንግሥቱ ለማ (ደማሙ ብዕረኛ) የተዋሰ ይኾንን? … ወቅትን፥ ዘመንን ከራስ ተረክ ጋር ገምዶ ወሽኔ በኾነ ሥነ ጽሑፍ በመከተብ በኩል፥ ከብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ (ትዝታዬ ስለራሴ የማስታውሰው) መጽሐፍ ጋር ትከሻ ለትከሻ ለመለካካት ይንደረደር ይኾን? … በሀብተ-ቋንቋ ረገድ፥ ከዮሐንስ አድማሱ (ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ) ጋር አይቀራረብምን? … እንደ ኤርትራዊቷ አደይ ያሉ የግለሰቦችን ዘዬ በመከሰት ረገድ፥ መጽሐፈ ትዝታ ዘ አለቃ ለማ ኃይሉን አያስተዝትምን? … በአንድ ጉዳይ ላይ አድምቶ በመጻፍ ረገድ እንደ ፊታውራሪ ተክለሐዋርያት (ኦቶባዮግራፊ) ያለ ልፋት አይታይምን? … ኢ-ቅደም-ተከተላዊ አሰዳደር በማንበር በኩል፥ የፍቅረ ማርቆስ ደስታ (የሚሳም ተራራ) ጥላ የረበበ አይመስልምን? … የራስን የአጻጻፍ ዘይቤ ለማሥረጽ፥ እንደ አሰፋ ጫቦ (የትዝታ ፈለግ፣ 2008) ያለ ጥረት አይታይምን? … በታሪክ አጋጣሚ በሕይወት ሰርጥ ውስጥ ስላገኛቸው ጉምቱ ሰዎች ሲያወጋ የእነ-ጋሽ ተክለጻዲቅ መኩሪያ (የሕይወቴ ታሪክ) ቀለም አይታይምን?

የ”ከማዕበል ማዶ ፋይዳ”
አንደኛ፡-
ፒየር ማሻሪ "ሥነ ጽሑፍ ለተጻፈበት ዘመን ጥበባዊ አንደበት ነው!” ይላል። የግለሰብ ታሪክ ሲሆን ደግሞ ይብሱን ልሳንነቱ ይተባል። በዚህ ረገድ ጋሽ ተስፋዬ ዘመናቸውን "በፊደላት ስዕል" አንብረውታል። ከማዕበል ማዶ ዐዲስ የአጻጻፍ ይትባሕል ለመፍጠር በመታተር ሂደት ውስጥ ቢኾንም እንኳ የዘመን መስታየትነቱን አልነፈገም። ዘመንን በማኅበራዊ፥ በኢኮኖሚያዊ፥ በፖለቲካዊ እንዲሁም በታሪካዊ ሁኔታዎች በመዳሰስ በኩል ለምሉዕነት ቀርቧል። ስለጓድ ደበላ ዲንሳ ብንል ስለእትየ ዓመለ-ወርቅ (የፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያም እህት)፥ ስለባለቅኔው ሙልጌታ ተስፋዬ ብንል ስለሁለገቧ አርቲስት አዳነች ወልደገብርኤል፥ ስለኢንጂነር ካሳ ገብሬ ብንል ስለኢያሱ በርኼ፥ ስለጋሽ ሥዩም ተፈራ ብንል ስለሎሬት ጸጋዬ ገ/መድኅን … በስም ወጭት የግብር እና የሰነድ ወጣወጥ በዓይነት በዓይነቱ የቀረበ የታሪክ ብፌ ነው ብል ማጋነን አይኾንብኝም። የአዲስ አበባን ልብና ኩላሊቷን መርምሮ፥ በየዘመኑ የነበራትን መልክ ከትቧል። አሥመራን የበዓሉ ገጸሰብ እንደ ነበረው ጸጋዬ ኃይለማርያም በብዕሩ ስሏታል። ባሕርዳር፥ መተከል፥ ፓዌ፥ መንዱራ፥ ጣና በለስ፥ ሠፈራ ጣቢያዎችን ጅማትና ቅልጥማቸውን ለያይቶ ጽፏል። የመጽሐፉ ቁልፍ ቃላት ናቸው ብዬ ባልፍ ይሻለኛል። በአጭሩ ሠፈራ ጣቢያን በሚመለከት እንደ መጀመሪያ የታሪክ ምንጭ የሚጠቀስ ሰነድ በመኾን የዘመን መስታወትነቱን ያንጸባርቃል። በታሪካዊ አንደበትነት ረገድ እጅግ ብዙ አበርክቶት የሰነቀ ጥራዝ በመኾኑ ምክንያት የመጽሐፉ ፋይዳ ንሯል።

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

02 Oct, 14:01


አንድ ወደ ፍቅር ጉዞ መጽሐፍን በ500 ብር በመግዛት የሊዱን ሕይወት እንታደግ 🙏

ተማሪ ሊዲያ ሥዩም፣ በውስጠኛው የአእምሮዋ ክፍል ውስጥ የደም ሥር መወሳሰብ በፈጠረው መድማት ሳቢያ እንደ ስትሮክ እየሆነባት ትገኛለች። ለሕክምናም ከ2 ሚልየን ብር በላይ ያስፈልጋታል። እኔ የአቅሜን 50 መጻሕፍትን በ500 ብር አበርክቻለሁ። ከታች ባስቀመጥኩላችሁ የቤተሰቦቿ አካውንት 500 ብር በማስገባት ከቢኒያም አቡራ ዘንድ 1 መጽሐፍ ይውሰዱ።

እባካችሁ 🙏🙏🙏

ንግድ ባንክ - 1000027428162 - ሥዩም ዘውዴ - (አባቷ)

አዋሽ ባንክ - 01336511809500 - አቤኔዘር ሥዩም (ወንድም )

አቢሲኒያ ባንክ - 44516721- አቤኔዘር ሥዩም (ወንድም )

ስልክ: 0932588260 Abenezer Seyoum

እናመሰግናለን 🙏🙏🙏

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

25 Sep, 16:35


የሐዋሳ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ ዓመት ጎበዝ ተማሪ የነበረችው ሊዲያ ሥዩም፣ ተመርቃ ለቤተሰቦቿ መከታ የመሆን ሕልሟ ላይ brainsteam cavernoma  የተሰኘ የጭንቅላት ሕመም ጋሬጣ ሆኖባት፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ትገኛለች።

ይህች ምስኪን ልጅ በውስጠኛው የአእምሮ ክፍል ውስጥ የደም ሥር መወሳሰብ በፈጠረው መድማት ሳቢያ እንደ ስትሮክ እየሆነባት ትገኛለች።

ሕመሙ በሀገር ውስጥ ሕክምና ሊገታ ስላልተቻለ በሀገረ ሕንድ ሄዳ እንድትታከም የጥቁር አንበሳ ቦርድ ወስኗል። ለአጠቃላይ ወጪም እስከ ሁለት ነጥብ ሦስት ሚልየን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን በጸሎታችሁ እንድታስቡ እንዲሁም ከታች በተጠቀሰው አካውንት የአቅማችሁን በማበርከት ከጎናችን እንድትሆኑ ሲሉ ቤተሰቦቿ በእግዚአብሔር ስም ይማጸናሉ።

ከዚህ በኋላ የውስጠኛው የአእምሮ ክፍል ውስጥ የሚደማ ከሆነ፣ እጅግ ለከፋ ችግር ስለምትጋለጥ፣ እርዳታችሁን በአፋጣኝ እንሻለን።
Gofundme: https://gofund.me/063f71fb

1000027428162 Commercial bank
Seyoum Zewdie (አባቷ)

01336511809500  Abenezer Seyoum(ወንድም ) Awash

44516721
Abenezer Seyoum(ወንድም )Abysinia

ስልክ: 0932588260 Abenezer Seyoum

እናመሰግናለን 🙏🙏🙏

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

21 Sep, 13:03


ደበበ ለመጽሐፉ መጠሪያ የመረጠው የብርሃን ፍቅር የአንድ ነጠላ ግጥም ርዕስ አይደለምና ስብስቡን ይወክልለታል። በደልና ቀርነት ጨለማ ናቸው፤ ድልና ነፃነት ብርሃን ይሆኑታል። “ጥቁር አፈር አቅፎን / ጥቁር ብርሃን ውጦን” በማለት እሳቦቱን ያሰፈዋል።

ከበባው ሲበዛ
ብዝበዛው ሲንዛዛ
ከጨለማ ጥጋት በውስጤ የበቀለች ያቺን ዘሃ ብርሃን አራግቤያታለሁ
ዙሪያዬን ጨለማ ቀጥቼባታለሁ
የፋኖ ፋናዬም ሁና አይቻታለሁ።

የጨለማን ገበና በብርሃን ነው የተረተረው። የባለቅኔ ምጥ ብርሃንን መገላገል መሆኑን ያተኩርበታል፤ “አይደለም” በሚለው ግጥሙ ለኪነጥበብ ማደሩ ምርጫው ስቃይም ደስታም እያከለ ብርሃንን ለመገላገል ሲል የዘልማድ ጉዞ አልመረጠም። ተጨማሪ ብርሃን፥ ወንድና ሴት በፍቅር ሲቀልጡ የሚፈካው ቦግታም ነው። ደበበ ለፍልስፍና ለዕውቀት ተቀኝቷል። ለልጅነት ትዝታው፥ ለቦረቀበት መንደርና ባህል በግጥሞቹ ተመስጧል። የሀገር የጭቁን ወገን ዕጣ ፈንታ በሰው እንጂ በሆነ መለኮታዊ ሃይል እንደ ማይቃና እንደ ማይጐብጥ ተገንዝቧል።

አብደላ ዕዝራ የደበበ ሰይፉ ስንኞች ላይ ከሰጠው ፍካሬ የተቆነጠረ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

18 Sep, 13:31


ዘመን ተሻጋሪ መጻሕፍቶቻችን ወደ ሕጻናት መጻሕፍትነት ቢቀየሩ የንባብ ባሕላችን ምናልባት እየተስተካከለ ይሄድ ይሆን?

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

17 Sep, 15:10


ከአስራ አንድ ዓመት በኋላ ለቴአትር ትምህርት ወደ እንግሊዝ ሀገር ስሄድ የሁለቱን የግሪክ ወንድማማቾች ግጭት ከአቤልና ከቃየል ግጭት ጋር፤ እንደዚሁም ከዚያ በፊት የጥር ካም ግብጽ ታሪክ ሴትና የኦስራ ግጭት ጋር እንደዚሁም በኢትዮጵያ ኦሮሞ ባህል ውስጥ ከሳቦና ከጉና፣ ከቦረናና ከከረዮ (ከሜጫና ቱለማ) ወንድማማቾች የሚቶሎጅ ግጭትና እርቅ ጋር እያነጻጸርኩ የፈተና ወረቀት የሮያል ኮርት ቴአትር አስተማሪዬን ጆርጅ ዴቪንን እጅግ ባስቆጣቸው ጊዜ ነበር። ‹እንዴት ብትደፍር ነው የታላቋን ግሪክ ስልጣኔ ታሪክ ከአፍሪካ ተረትና እንቆቅልሽ ጋር የምታነጻጽረው? _ በሚል ነበር እጅግ የተቆጡኝ፤ ነገሩን ለማሳጠር በዚህ አፍራሽ ተጽዕኖ ምልክት ሰጭነት የተነሣ የአፍሪካን አንትሮፖሎጅ ጥናት በጣም በበለጠ ቁም ነገር ማጥናትና ማጠናከር ቀጠልኩ።

#ሎሬት_ጸጋዬ ገ/መድኅን
(ጦቢያ፣ ቅጽ 5፣ ቁ.11፣ 1990 ዓ.ም)

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

13 Jul, 06:24


ነገ ሐምሌ 7 የቴዲ አፍሮ ልደትም አይደል? ልደቱን በማስመልከት ገቢው ለተስፋ አዲስ የሕጻናት የካንሰር ሕሙማን ማዕከል የሚውል 30 ኮፒ "ወደ ፍቅር ጉዞ" መጽሐፍ ለመስጠት አስበናል። 30ው በ300 ብር ቢሸጥ 9 ሺህ ብር ይመጣል። አንድ ሺህ ብር እኛ በግላችን እንጨምርና 10 ሺህ አድርገን እናስገባለን።

ልትተባበሩን የምትሹ ሰዎች ካላችሁ "ኢንቦክስ" ማድረግ ትችላላችሁ።

እናመሰግናለን 🙏

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

26 Jun, 15:02


አሁን ያሉት የ60ዎቹ ትውልድ ጽሑፍ ከዘመን ጓዶቻቸው ጋር የነበረውን መጠባጠብ ከመዘገብ ፈቅ ብለው በተማሩበት መስክ ያከማቹትን ዕውቀት በቋንቋችን በመጻፍ ሳይንስን ማኸዘብ ለምን ቅድሚያ የሚሰጡት ጉዳይ አልሆነም? ለዚህኛው ትውልድ ከያ ትውልድ ፍጭት ይልቅ ያ ትውልድ ከነበረው ዕውቀት ቆርሶ ቢሰጠው አይሻልምን?

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

23 Jun, 04:04


ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ፥ የደጋ ሰው አልበም ላይ የውይይት ሐሳብ ይቀርባል።

መነሻ ጽሑፍ አቅራቢ፦
ቢኒያም አቡራ እና
ትሬዛ ዮሴፍ

አዘጋጅ፦ ዐውደ ፋጎስ የውይይት ክበብ

ቀን፦ እሑድ / ሰኔ 16

ሰዓት፦ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ

ቦታ፦ በወመዘክር አዳራሽ (ብሔራዊ አከባቢ ከሚገኘው ከድሮ ኢቲቪ ሕንጻ ጀርባ)

መግቢያ፦ በነጻ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

04 May, 04:45


አምላክ ለእኛ ብሎ ቢያፈሰው ደሙን
ለምን ከለከለች ፀሐይ ብርሃኗን?

ረቡኒ፣ በጎልጎታ ሲሰቀል ፀሐይ አሻፈረኝ ብላ ብርሃኗን ከልክላለች። ፀሐይ እምቢኝ እንዳለች ከአራቱ ወንጌላት ሦስቱ ዘግበውታል። በዚህ ቀን ሊፈጠር የሚችል የፀሐይ ግርዶሽ እንደሌለ ሳይንቲስቶች አረጋግጠዋል። ለደቂቃዎች እንጂ ለሰዓታት የሚቆይ የጨረቃ ግርዶሽም እንደሌለ እሙን ነው። ፀሐይ ብርሃኗን የነፈገችው በደመና ጉያ ተሸሽጋ አይደለም። ታዲያ ለሦስት ሰዓታት የቆየው የፀሐይ ዝምታ ለምንድነው? ደሙን ያፈሰሰው ለእኛ ሆኖ ሳለ ፀሐይ ምን ይሁን ብላ ነው የሸሸችው? ይኼ ምርምር የሚጠይቅ ሚስጥር ነው።

ጨለማ የእግዚአብሔር ሕልውና ያለመኖር ውክል ነው። ክርስቶስ የሰው ልጆችን ኃጢዓት በሙሉ የመሸከሙ የማረጋገጫ ሰነድም ጭምር ነው። በዚህም የክርስቶስን የሰቆቃውን ክብደት እናያለን። የእግዚአብሔር አብ አጠቃላይ ፍርድም ይንፀባረቃል።

የፀሐይ ግብዓቱ ከፈርዖን አገዛዝ ነፃ ለመውጣት የተደረገውን ተዓምር ያስታውሰናል። እስራኤላዊያን ከግብፅ ባርነት ከመላቀቃቸው በፊት ሦስት ቀን በግብፅ ጨለማ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱሳችን ያወሳል። እስራኤላውያን ከሦስቱ የጨለማ ቀናት በኋላ ከግብፅ ባርነት ነፃ እንደሆኑ ሁሉ፣ በዕለተ ስቅለት ከረበበው ጽልመት ማግስት የሰው ዘር በሙሉ ከኃጢአት ባርነት ነፃ ወጥቷል። በሥራ ከሚመጣ የጽድቅ ባርነት በፀጋ ወደ ሚገባበት የጽድቅ ነፃነት መልሶናል። በግብፅ ምድር የጨለመችው ፀሐይ ሙሴ እጁን አንስቶባት ሲሆን በዕለተ ስቅለት የጠለቀችው ፀሐይ ግን በገዛ ፍቃዷ ይመስላል።

የከበረው ስጋ የከበረው ደም
በመስቀል ላይ ዋለ ኢየሩሳሌም

የሰው ልጅ ራሱን ወደ መንፈሳዊ ረቂቅነት መቀየር ስለማይችል፥ ፈጣሪ ራሱን ወደ ተጨባጭ አካል መቀየር ነበረበት። "የከበረው ስጋ የከበረው ደም" በማለት መለኮት  ራሱን ወደ ተጨባጭ አካልነት መቀየሩን ጥቁምታ ንሰጠናል። ወልድ መለኮታዊ ክብሩን ትቶ ስጋ መልበሱ ለፍጥረቱ ያለውን ጥልቅ ፍቅር ያመለክታል። ስለ ሰው ልጆች ኃጢአት ሲል መስቀል ላይ የዋለበትን የፍቅር ውሃ ልክ የሚተካከል አይገኝም።

እዩት ኢየሱስን መስቀሉ ማማሩ
ለተመራመረው ብዙ ነው ሚስጥሩ

መስቀልና የመስቀል ውበት እርስ በራስ የሚቃረኑ ሐረጎች ናቸው። መስቀል በሰቀቀን የታጨቀ የሰቆቃ ጥቅል እንጅ አንዳች የውበት ዘለላን ያነገበ ነዶ አይደለም። መቸም መስቀል ስንል እንጨቱን አለመሆኑን ልብ ይሏል። በተለየ ሁኔታ የኢየሱስ መስቀልን እንዲያምር የሚያደርግ የስዕል ባለሙያ እንጅ የመጽሐፍ ቅዱስ ተረክ የለም። እንደውም እንደውም የመሲሕው መስቀል በየትኛውም ሰፊ ትከሻ የሚሸከሙት ሆኖ አናገኘውም። መስቀሉ ከገዛ ወገኖቹ  ዘንድ ቅቡልነት ከማጣት የሚጀምር እንጅ ሰያፉን እንጨት ተሸክሞ ተራራ ከመውጣት ብቻ አይደለም። ሌላው ሌላው ይቅርና ሐዋርያቱ እንኳን ብቻውን ትተውታል። ቁንጫ እንኳን ከፍራሹ ጋር አብሮ ይቃጠላል። ፎካሪው ጴጥሮስ እንኳን ከመስቀሉ ግዝፈት የተነሳ በአንድ የክህደት መለዮ ሦስቴ ቃለ-አባይ ሆኗል። ታዲያ ምኑ ጋር ነው የኢየሱስ መስቀል ማማሩ? የመስቀሉን ውበት ሚስጥር እሱው ይግለጥልን!

ቢመቱት ቢሰቅሉት ቢያላግጡበትም
ምንም አላገኙም ከሱ ዘንድ ስህተት
ፈጣሪ መሆኑን ሚስጥሩ ገብቷት
ጌታ ላይ ዝም አለች ግዑዟ መሬት

ትዕቢተኛ በቆሎ ከጤፍ ማኅፀን ዱቄት የሚወጣ አይመስላትም። ግዑዟ መሬት የገባትን እውነት፣ ሕያው ነኝ ባዮቹ የሰው ልጆች ሊያስተውሉ ዘንድ አልተቻላቸውም። ልሳነ-ሰቡ፣ ፈጣሪው ላይ እያላገጠ ሲያዋርደው፣ ምድር ግን በልሳነ-ተፈጥሯዊ አርምሞ፣ ፈጣሪዋን አከበረችው።

የአለማችን አብዛኛው ጦርነቶች የተካሄዱት በተራራዎችና በኮረብቶች ላይ ነው። ጦርነቱን ያሸነፈው ሀገር በኮረብታው አናት ላይ ትልቅ እንጨት በመትከል ባንድራውን ያውለበልባል። ኢየሱስ በቀራኒዮ ኮረብታ የተውለበለበ የእግዚአብሔር መንግሥት ሰንደቅአላማ ነው።

በመጨረሻም

ይኼ ታላቅ ንጉስ ሲገለጥ በሰማይ
የናቁት የወጉት ይሉለታል ዋይ ዋይ
ምድርና ሰማይ ከፊቱ ሲሸሹ
ወዴት ልግባ ይላል ትልቁ ትንሹ

መልካም በዓል 🙏

ከቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

14 Apr, 09:13


የሚሳም ተራራን ካነበብኩ በኋላ የተሰማኝን በመጽሐፍ ዳሰሳ መልክ አቅርቤያለሁ። 

ሊንኩን በመጠቀም ዳሰሳውን ማግኘት ይችላሉ።

https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=32452:%E1%8B%A8%E1%88%9A%E1%88%B3%E1%88%9D-%E1%89%81%E1%88%B5%E1%88%8D&Itemid=211

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

06 Apr, 08:08


"አዝማሪው ልቤን የት አገኛለሁ?" እያላችሁ፥ ልቤን ውልቅ ስታደርጉ የነበራችሁ እስኪ እንያችሁ። ሁለተኛ ዕትም በገበያ ላይ ውሏል🙏

ዋና አከፋፋይ -
ሜክሲኮ ደብረ ወርቅ ህንፃ ጎን
በ ሀሁ የመፃህፍት መደብር ያገኙታል፡፡

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

06 Apr, 03:37


ዓለማየሁ ገላጋይ፣ በወሪሳ አውድማ ላይ በምጸታዊ መንሽ ማኅበራዊ አዝዕርትን ንፋስ ላይ አበጥሯል። በታለ ማሰሮ ጦማራዊ ልቦለድን ንጧል። በኢህአዴግን እከስሳለሁ ሙቀጫ የጋዜጠኝነትን ዘነዘና ይዞ ምኩራብ ወጥቷል። በቅበላ ብራና የድህረ ዘመናዊ ልቦለድን ከትቧል። በመልክአ ስብሃት ሰፌድ ላይ ሰበዝም፣ አለላም፣ አክርማም ሆነ ስንደዶ ለመሆን የሚመች፥ የደቦ ከያኔ መሆኑን ተመልክተናል። በየፍልስፍና አጽናፍ ተርጓሚነቱን፣ በስብሃት ገ/እግዚአብሔር ሕይወትና ክሕሎት - ኀያሲነቱን አስመስክሯል። በየተጠላው እንዳልተጠላው አይነኬ ዕሳቤዎችን በመጠይቅ ወንፊት አንገዋሏል። በአጥቢያ የንስር ዓይናማነቱን፣ በመለያየት ሞት ነው ሊቀ-መጣጥፍነቱን፣ በፍቅር ስም ላይ ደግሞ experimental novelist-ነቱን ተመልክተናል። በኩርቢት መም ላይ የስሜት ጂምናስቲክ አሠርቶናል። በ18ኛው ደሞ 24 እንዳልሞላው ሊያስታውቀን ተከስቷል። እኔ በበኩሌ በጋሽ ወንድዬ ዓሊ ብሂል "የሥነ-ጽሑፍ ወዛደር" ብዬዋለሁ። what a ትጋት?!?!

ቢኒያም አቡራ