AMN - ጥር 22/2017 ዓ.ም
18ኛው የራስ አልካይማህ ግማሽ ማራቶን ቅዳሜ ማለዳ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ራስ አልካይማህ ከተማ ይካሄዳል፡፡ በሴቶች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የማሸነፍ ግምት አግኝተዋል፡፡
እጅጋየሁ ታዬ ደግሞ ቀዳሚዋ ናት፡፡ በትራክ ውድድር ኢትዮጵያን በኦሊምፒክና ዓለም ሻምፒዮና የወከለችው እጅጋየሁ ለማሸነፍ ቀዳሚ ግምት ያገኘች አትሌት ናት፡፡
የቡዳፔስት ዓለም ሻምፒዮና የ10 ሺ ሜትር ነሀስ ሜዳሊያ አሸናፊዋ እጅጋየሁ በራስ አልካይማህ የምትጠበቅ አትሌት ናት፡፡ ከሶስት ወራት በፊት የቫሌንሲያ ግማሽ ማራቶንን በአራተኛነት ስታጠናቅቅ ያስመዘገበችው አንድ ሰዓት ከ04 ደቂቃ ከ14 ሰከንድ የራሷ የርቀቱ የምንጊዜውም ፈጣን ሰዓት ሆኗል፡፡
የባለፈው ዓመት የራስ አልካይማህ ግማሽ ማራቶን አሸናፊዋን ጽጌ ገብረ ሰላማን አስከትላ ቫሌንሲያ ላይ የደመቀችው እጅጋየሁ፣ የራስ አልካይማህ ግማሽ ማራቶን ሪከርድን የተተስተካከለ ፈጣን ሰዓት ይዛ ትሮጣለች፡፡
ሙሉ መረጃውን ለማንበብ
👇
https://web.facebook.com/permalink.php?story_fbid=pfbid02GEaL14rsBrGg7cKQxSyxPm15FE2JbvW2r9qucXdZXedjUnFpx61RoiNaaYkkWrwJl&id=61557351622843