የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC @egbcc Channel on Telegram

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

@egbcc


ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።

"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC (Amharic)

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC የቴሌግራም ቻናል ነው። ይህ ባለምንም ክስደት ወንጌላዊ ለማስተማርም እና በወንጌላዊነት በእንግሊዝ ግንባታ ለማዋልና ለምን አነሳስነው ብሄራዊ ችግርን ለመጠቀም ዋጋውን ማስኬትና የሚመልከት መገኛው ቴሌግራም ምንጮቻችንን እንቀበል። ለወንጌል አማኞች ጸጋን በማስቀመጥ ሰኞ እሁድ አሉታዊ ማህበሩን በመመልከት ዋጋውን እና መረጃውን ማራዘም መክፈት ነን። ስለሆነ ለወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ያልዘወትር የቴሌግራም ቻናላችንን ትክክለኛ መረጃለሽ።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

14 Feb, 08:53


#ቤዛ_ኢንተርናሽናል_ቸርች_የ2017_ዓ_ም_የአፍሪካ_ተነሺ_ኮንፍረንስ_ተጀመረ።

የቤዛ ኢንተርናሽናል ቸርች ከ16 ዓመታት ቆይታ በኋላ አዲስ የአምልኮ አዳራሽ ወይም የአፍሪካ አምልኮ ማዕከል በይፋ ተጀምሮዋል።

የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ቤተ መንግስቱ ይህ የአካባቢ ለውጥ ብቻ አይደለም የእግዚአብሔር ታማኝነት ሙላት እና ለቤተ ክርስቲያናችን አዲስ ወቅት ነው።ወደዚህ አዲስ ጅምር ስንገባ፣ ከየት እንደመጣን እናስታውሳለን ጉዞው በትንሽ የቤት ውስጥ መሰባሰብ የጀመረው እና አሁን ወደዚህ አስደናቂ ጊዜ መርቶናል። በነገር ሁሉ የረዳንን እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ ታሪካችን የእምነት፣ የመለወጥ እና የማይካድ የእግዚአብሔር በህይወታችን የመገኘት ማስረጃ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ በመገኘት በዚህ ሁሉ አመታት ውስጥ በነገር ሁሉ የረዳቸውን እግዚአብሔርን በማመስገንና “ከፊተኛው ይልቅ የዚህ የሁለተኛው ቤት ክብር ይበልጣል፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ በዚህም ስፍራ ሰላምን እሰጣለሁ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።”ሐጌ 2፥9 የለውን የእግዚአብሔርን ቃል በማንበብ ጸሎት አደርገዋል።

በተገነባው የአምልኮ አደራሽ ውስጥ ከየካቲት 2/2017 ዓ.ም የተጀመረው ተነሺ አፍሪካ እስከ የካቲት 6/2017 ዓ.ም የሚቀጥል እንደሆነና የአብያተክርስቲያናት መሪዎች ፣ ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች እና አብረዉ በስራ ሲደክሙ የነበሩ የቤተክርስቲያን አባላት በተገኙበት የአምልኮ አዳራሽ በድምቀት ይመረቃል።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

14 Feb, 08:49


#ኑ_የአምልኮ_ኪዳናችንን_እናድስ

ዘማሪት ቃልኪዳን ጥላሁን (ሊሊ) መጋቢት 6 ቀን 2017 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ኑ የአምልኮ ኪዳናችንን እናድስ በሚል መሪ ቃል እንደምታገለግል በሐርመኒ ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰቷል።

የክርስቶስ ተልዕኮ ቤተክርስቲያን መጋቢ የሆኑት ዶክተር ተስፋሁን ቤተ ክርስቲያን ያለፉትን 17 ዓመታት በኢትዮጵያ ምድር እንዲሁም በክርስቶስ ተልዕኮ አገልግሎት አማካኝነት በአሜሪካ ስታገለግል መቆየቷን በመግለፅ ይኼንን ልዩ መርሃ ግብር በማዘጋጀት እንደምትጠብቅ ተናግረዋል።

የመርሃ ግብሩ አጋር የሆኑት አርት ሚኒስትሪ ኢትዮጵያን ወክለው የተገኙ መጋቢ፣ አርቲስት ደበሽ ተመስገን እንዲሁም የኢልቬዜት ኢቨንት ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሩት ሃይሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

"የአምልኮ ቃልኪዳናችንን እናድስ" የተሰኘው መርሃ ግብር የወንጌል ስርጭት ሳምንት፣ የፆም እና ፀሎት አዋጅ እንዲሁም ትምህርታዊ ጉባኤዎች እንደሚኖሩት የሚጠበቅ ሲሆን ቅዳሜ መጋቢት 6 ቀን 2017ዓም የመዝጊያ መርሃ ግብሩ ላይ በዘማሪት ቃልኪዳን ጥላሁን (ሊሊ) የተፃፈ "የቃልኪዳን ፍቅር" የተሰኘ መፅሐፍ ይመረቃል።

በዕለቱ ዘማሪት ቤተልሔም ወልዴ እና ዘማሪት አዜብ ሐይሉ የሚያገለግሉ ሲሆን ለረጅም ዓመታት በዝማሬ ያገለገለችንን እህታችንን በፕሮግራሙ ላይ ሁላችንም በመገኘት ፍቅራችንን እንድንገልፅ አደራ አሳስበዋል።
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://t.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

12 Feb, 05:47


https://youtu.be/1FTKcq6gKxo

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

11 Feb, 06:16


https://youtu.be/ILIDKFC4Zw4

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

10 Feb, 13:48


የካቲት 3፣ 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊግርሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን ጋር በመተባበር የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባ ለሚደረገው ታላቅ የስብከተ ወንጌል አስመልክቶ የካውንስል ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ።

ጋዜጣዊ መግለጫ


የእግዚአብሔር የተስፋና የፍቅር መልዕክት ለአዲስ አበባና አካባቢው

አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያ፡ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም - የቢሊ ግራሃም የወንጌል ማኅበር በ1952 ዓ.ም ወንጌላዊ ቢሊግራሃም በአዲስ አበባ ስቴዲየም ወንጌል ከሰበኩና በንጉሠ ነገሥት ኃይለ ሥላሴ በቤተ መንግስታቸው በክብር ተጋበዘው ከተሸለሙ ከ65 ዓመታት በዃላ የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባይ ለሚያደርገው ታሪካዊ የሁለት ቀናት መርሐ ግብር ወደ አዲስ አበባ እየተመለሰ ይገኛል።

h1.600 በላይ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት የወንጌላዊ ቢሊ ግርሃም ልጅ የሆኑትን ሬቨረንድ ፍራንክሊን ግርሃምን በአዲስ አበባ እንዲሰብኩ በመጋበዝ ከቢሊ ግራሃም የወንጌል ማኅበር /ቢሊግርሃም ኢቫንጀሊስቲክኣሶሊሽን ጋር በመተባበር ላይ ይገኛሉ። ልከ እንደ አባታቸው ፍራንከሊን ግራሃም ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥልቅ እና ታላቅ አክብሮት ያላቸው ሲሆን ላለፉት 40 አመታትም ወደዚህች ሀገር በተደጋጋሚ መጥተዋል።

"ኢትዮጵያ ውብና ጠንካራ አገር ነች። ከዚህ ታላቅ አገር ህዝብ ጋር ለማሳለፍ ሁል ጊዜ እጓጓለሁ "ሲሉ የቢሊ ግርሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን (BGEA) ፐሬዝዳንት እና በኢትዮጵያ ውስጥ ለአስርት አመታት በበጎ አድራጎት ሥራ ተሰማርቶ ሲሰራ የቆየው የአለም አቀፍ የከርስቲያን እርዳታ ድርጅት የሆነው የሳማሪታን ፐርስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሬቨረንድ ፍራንክሊን ግራሃም ተናግረዋል።

"አገሪቷን ስጎበኝ ይህ ለ11ኛ ጊዜ ይሆናል፤ በዚህ ጊዜ ከዚህ ቀደም እዚህ ሰርቼው የማላውቀውን ነገር አደርጋለሁ። በአብያተ ከርስቲያናት ግብዣ በአገሪቱ ትልቁ አደባባይ በመገኘት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚሆን መልእክት አቀርባለሁ። እሱም ሕይወት ለዋጭ የሆነው እግዚአብሔር እንደሚወደን፣ እንደምንከባከበንና ለሕይወታችን ዓላማ እንዳለው የሚያሳይ የምሥራች መልዕከት ነው። "

መለኮታዊ ጉብኝት ደስታ በዋና ከተማው እና በመቶዎች በሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮች ርቀው ባሉ ማህበረሰቦች ውስጥ ሕይወታቸውን እየገነባ እንዳለ እየታየ ነው። በዚህ ዝግጅት ላይ ለወንጌል መልዕከት ምላሽ የሚሰጡትን ጨምሮ፣ አማኞች የክርስቶስን ፍቅር ከሌሎች ጋር በብቃት እንዲካፈሉ ለማገዝ በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን የስልጠና ክፍለ ጊዜዎች በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የአጥቢያ ቤተከርስቲያን አባላት ተሳትፈዋል። በዝግጅቱ ላይ የመጓጓዣ ትራንስፖርት በማጣት ለመሳተፍ የሚቸገሩ ሰዎችን ወደ መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ መርሐ ግብር ለማምጣት በመቶዎች የሚቆጠሩ ነጻ አውተቡሶች ለስምሪት ተይዘዋል። በከተማውና በዙሪያዋ በርካታ የጸሎት ቡድኖች በእያንዳንዱ ቀን ለዝግጅቱ የማያቋርጥ ጸሎት በመጸለይ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ከርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቁስ ደረጀ ጀምበሩ፡ "ብዙ የተለያዩ ፈተናዎች እና ትግሎች አሉብን - ለዚህም ድህነት እና ግጭት የመሳስሉትን መጥቀሰ ይቻላል። በአሁን ጊዜው የተሐድሶና የመኒቃቃት ወቅት ነው ብለን እናምናለን። ለዚህም የሚያስፈልገን የእየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ነው። በአሁኑ ወቅት ለምድራችን ፈውስ ሊየመጣ የሚችለው ልብንና አእምሮን ሊለውጥ የሚችለው ወንጌል ብቻ ነው። "በማለት ተናግረዋል። በማስከተልም፡ እንደቃሉ " እጆቻችንን ወደ እግዚአብሔር እንዘረጋለን። “በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።” (2ዜና 7፥14) እርስን ስናዳምጠው የእያንዳንዳችን ሕይወትን ይለውጣል፣ ሀገርንም ይለውጣል። ስለሆነም የእግዚአብሔር ፊት ለተሐድሶ እንፈልጋለን። በዚህች ምድር እግዚአብሔር የሚያደርገውን ለማየት በጉጉት እንጠብቅ ለአብያተ ክርስቲያናት ብቻ ስይሆን በሀገራችን ጭምር አዲስ ነገር ይሆን ዘንድ ፊቱን መፈለግ አለብን ብለዋል።

መለኮታዊ ጉብኝት ሁሉም ሰው እንዲካፈለው የተጋበዘበት መርሐ ግብር ነው። የዝማሬ አገልግሎት ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ ከአሜሪካን ሀገር በመጡ መዘምራንና በዚ ባሉ ኢትዮጵያዊያን የሶሎ መዘምራን ይቀርባል፣ መጋቢ ዘማሪ አገኘሁ ይደግ ፣ዘማሪ አቤኔዘር ለገሰ ፣ዘማሪ ሃና ተክሌ፣ ዘማሪ ጉቱ ሽፈራውና የጎብረት መዘምራን ዝማሬ ያቀርባሉ።

እስከዚያው ድረስ በጸሎት እንትጋ አግዚአብሔር እንዲያስበን ሀገራችንን ከክፉ ሁሉ እንዲጠብቅ በበረከቱም እንዲጎበኝ በትጋት እንጸልይ ጌታም ድንቅ ነገር በምድራችን እንደሚያደርግ በማመን አግዚአብሔር ሕዝባችንን ሀገራችንን ኢትዮጵያ በድንቅ አሠራሩ ይባረክ። አሜን

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

10 Feb, 09:37


"ኢትዮጵያ ውብና ጠንካራ አገር ነች። ከዚህ ታላቅ አገር ህዝብ ጋር ለማሳለፍ ሁል ጊዜ እጓጓለሁ "ሲሉ የቢሊ ግርሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን (BGEA) ፐሬዝዳንት እና በኢትዮጵያ ውስጥ ለአስርት አመታት በበጎ አድራጎት ሥራ ተሰማርቶ ሲሰራ የቆየው የአለም አቀፍ የከርስቲያን እርዳታ ድርጅት የሆነው የሳማሪታን ፐርስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሬቨረንድ ፍራንክሊን ግራሃም ተናግረዋል።"አገሪቷን ስጎበኝ ይህ ለ11ኛ ጊዜ ይሆናል፤ በዚህ ጊዜ ከዚህ ቀደም እዚህ ሰርቼው የማላውቀውን ነገር አደርጋለሁ። በአብያተ ከርስቲያናት ግብዣ በአገሪቱ ትልቁ አደባባይ በመገኘት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚሆን መልእክት አቀርባለሁ። እሱም ሕይወት ለዋጭ የሆነው እግዚአብሔር እንደሚወደን፣ እንደምንከባከበንና ለሕይወታችን ዓላማ እንዳለው የሚያሳይ የምሥራች መልዕከት ነው። "

መለኮታዊ ጉብኝት ደስታ በዋና ከተማው እና በመቶዎች በሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮች ርቀው ባሉ ማህበረሰቦች ውስጥ ሕይወታቸውን እየገነባ እንዳለ እየታየ ነው። በዚህ ዝግጅት ላይ ለወንጌል መልዕከት ምላሽ የሚሰጡትን ጨምሮ፣ አማኞች የክርስቶስን ፍቅር ከሌሎች ጋር በብቃት እንዲካፈሉ ለማገዝ በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን የስልጠና ክፍለ ጊዜዎች በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የአጥቢያ ቤተከርስቲያን አባላት ተሳትፈዋል። በዝግጅቱ ላይ የመጓጓዣ ትራንስፖርት በማጣት ለመሳተፍ የሚቸገሩ ሰዎችን ወደ መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ መርሐ ግብር ለማምጣት በመቶዎች የሚቆጠሩ ነጻ አውተቡሶች ለስምሪት ተይዘዋል። በከተማውና በዙሪያዋ በርካታ የጸሎት ቡድኖች በእያንዳንዱ ቀን ለዝግጅቱ የማያቋርጥ ጸሎት በመጸለይ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ከርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቁስ ደረጀ ጀምበሩ፡ "ብዙ የተለያዩ ፈተናዎች እና ትግሎች አሉብን - ድህነት እና ግጭት የበዛ ነው። አሁን ጊዜው የተሐድሶና የመኒቃቃት ነው። የሚያስፈልገን የእየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ነው። ለምድራችን ፈውስ ለየመጣ የሚችለው ልብንና አእምሮን ሊለውጥ የሚችለው ይህ ብቻ ነው። "በማለት ተናግረዋል።

በማስከተልም፡ " እጆቻችንን ወደ እግዚአብሔርእንዘረጋለን። እርሱን ስናዳምጠው ሕይወትን ይለውጣል፣ ሀገርንም ይለውጣል። ፊት ለተሐድሶ እንፈልጋለን፡ በዚህች ምድር እግዚአብሔር የሚያደርገውን ለማየት እጓጓለሁነ ለቤተከርስቲ ስቲያናት ብቻ ስይሆን ለሀገራችን ጭምር ፊቱን እንፈልጋለን" ብለዋል።

መለኮታዊ ጉብኝት ሁሉም ሰው እንዲካፈለው የተጋበዘበት መርሐ ግብር ነው። የዝማሬ አገልግሎት ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ ከአሜሪካን ሀገር በመጡ መዘምራንና በዚ ባሉ ኢትዮጵያዊያን የሶሎ መዘምራን ይቀርባል፣ መጋቢ ዘማሪ አገኘሁ ይደግ ፣ዘማሪ አቤኔዘር ለገሰ ፣ዘማሪ ሃና ተክሌ፣ ዘማሪ ጉቱ ሽፈራውና የጎብረት መዘምራን ዝማሬ ያቀርባሉ።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

10 Feb, 09:36


#የካቲት_3_2017_ዓ_ም_የኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተ_ክርስቲያናት_ካውንስል_ከቢሊግርሃም_ኢቫንጀሊስቲክ_አሶሴሽን_ጋር በመተባበር የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባ ለሚደረገው ታላቅ የስብከተ ወንጌል አስመልክቶ የካውንስል ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ።

የእግዚአብሔር የተስፋና የፍቅር መልዕክት ለአዲስ አበባና አካባቢው

አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያ፡ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም - የቢሊ ግራሃም የወንጌል ማኅበር በ1952 ዓ.ም ወንጌላዊ ቢሊግራሃም በአዲስ አበባ ስቴዲየም ወንጌል ከሰበኩና በንጉሠ ነገሥት ኃይለ ሥላሴ በቤተ መንግስታቸው በክብር ተጋበዘው ከተሸለሙ ከ65 ዓመታት በዃላ የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባይ ለሚያደርገው ታሪካዊ የሁለት ቀናት መርሐ ግብር ወደ አዲስ አበባ እየተመለሰ ይገኛል።

h1.600 በላይ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት የወንጌላዊ ቢሊ ግርሃም ልጅ የሆኑትን ሬቨረንድ ፍራንክሊን ግርሃምን በአዲስ አበባ እንዲሰብኩ በመጋበዝ ከቢሊ ግራሃም የወንጌል ማኅበር /ቢሊግርሃም ኢቫንጀሊስቲክኣሶሊሽን ጋር በመተባበር ላይ ይገኛሉ። ልከ እንደ አባታቸው ፍራንከሊን ግራሃም ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥልቅ እና ታላቅ አክብሮት ያላቸው ሲሆን ላለፉት 40 አመታትም ወደዚህች ሀገር በተደጋጋሚ መጥተዋል።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

10 Feb, 06:31


https://youtu.be/b5tCx0YRNy4

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

07 Feb, 09:08


የሀይማኖት መገናኛ ብዙኃን የሰላም እሴት ግንባታ ላይ በመስራት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲወጡ ተጠየቀ፡፡ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የሰላም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ጋር በመተባበር “የሀይማኖት መገናኛ ብዙኃን ለሰላም ግንባታ” በሚል መሪ ሀሳብ የግንዛቤ ማስጨበጫና የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሂዷል፡፡በመድረኩ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ የሀይማኖት መገናኛ ብዙኃን ሀይማኖታዊ አስተምህሮቶችን ለተከታዮቻቸው ከማስተማር ባለፈ መልካም ስነምግባርን በማስረጽ፣ መተሳሰብና አብሮነትን በማጎልበት በሰላም እሴት ግንባታ ላይ ያተኮረ ቋሚ ፕሮግራም በማዘጋጀት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሊወጡ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ክቡር አቶ መሀመድ የሀይማኖት ተቋማት ሀገርን በመጠበቅና በመገንባት ወደፊትም ከፍ በማድረግ ከፍተኛ ሚና ያላቸው በመሆኑ በሚያስተዳድሯቸው የመገናኛ ብዙኃን ትውልድ ግንባታ ላይ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸውም ተናግረዋል፡፡
የመገናኛ_ብዙኃን_ባለስልጣን_ምክትል_ዋና_ዳይሬክተር_አቶ_ዮናታን_ተስፋዬ_በበኩላቸው_መድረኩ_ለሀገር_ሰላምና_አንድነት_መጎልበት_በጋራ_ለመስራት_በሚያስችሉ_ጉዳዮች_ላይ_ግንዛቤ_የሚፈጠርበት_መሆኑንም_ገልጸዋል በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) "የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን ለትውልድ ግንባታና ለአገር ሰላም መጠናከር ተጨማሪ አቅም የሚፈጥሩ እድሎች መሆናቸውን ጠቅሰው ተቋማቱ በመከባበርና በትብብር በመስራት ለአገራዊ አንድነትና ለሰላም አርአያ ሊሆኑ ይገባል" ብለዋል፡፡
በመድረኩ የሰላም ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፣ የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አመራሮች፣ የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

07 Feb, 08:11


#የቢሊግርሃም_ኢቫንጀሊስቲክ_አሶሴሽን_ከኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተ_ክርስቲያናት_ካውንስል_ጋር_በመተባበር_በየካቲት_29_እና_30_ቀን_2017 ዓ.ም ለሚደረገው ታላቅ የስብከተ ወንጌል አስመልክቶ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋዜጣዊ መግለጫ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሰታወቀ።

የቢሊግርሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ጋር በመተባበር በየካቲት 29 እና 30 ቀን 2017 ዓ.ም በመስቀል አደበባባይ ለሚካሄደው ታላቅ ስብከተ ወንጌል በርካታ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል። እኔ እንድሪያስ ነኝ በሚል ርዕሰ በሚዘጋጀው ፕሮግራምና ስለ እንድሪያስ አገልግሎት ማብራሪያ እንዲሁም በአዲስ አበባና በሸገር ከተሞች በሚገኙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ስልጠናዎችም ሲሰጥ መቆየቱ የታወሳል።

ለእነዚህ ስራዎችና ለታቀደው ፕሮግራም መሳካት የእናንተ የቅዱሳን ጸሎት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን እየገለጽን ብዙዎች ከጨለማው መንግስት እንዲያመልጡ እና መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ እንዲሆን ሁላችንም በጌታ ፊት እንጸልይ የኢቫንጀሊካል ቴሌቬዥን መልክት ነው።
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://t.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

06 Feb, 14:28


የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ ጀንበሩና የካውንስሉ ጽፈት ቤት የስራ ሐላፊዎች የኢትዮጵያ ሲቪል እና የሙያ ማህበራት ምክር ቤት ባዘጋጀው የሐይማኖት አባቶች የፀሎትና የሰላም ጥሪ መድረክ በመገኘት ፀሎትና የሰላም መልእክት አስተላልፈዋል::

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙ አባቶች ለኢትዬጵያ ህዝብ አስፈላጊ የሆነው ሰላም ነውና ሁሉም ለሰላም ዘብ ይቁም ፈጣሪ ሰላምን እንዲሰጠን እንለምን በማለት ጥሪ ያደረጉ ሲሆን የኢትዬጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ ጀንበሩም በአንድ ላይ ስንቆም ለሰላም ስንመካከር ተግባራዊ ለውጥ ይመጣል:: መሳያዎችን ቁጭ እድርገን እንወያይ:: ጦርነት ይብቃ ጥላቻ ይብቃ ሞት ይብቃ የሚያስፈልገን ሰላምና ሰላም ስለሆነ ሁላችንም ለዚህ ሰላም እንስራ በማለት የሰላም ጥሪ መልእክት አስተላልፈዋል::

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

06 Feb, 12:49


#የኢትዮጵያ_ሙሉ_ወንጌል_አማኞች_ቤተክርስቲያን_በአዲስ_አበባ_እና_አከባቢው_የሚገኙ_ሶስት_ክልሎች_ውስጥ_ሚገኙ_አጥቢያዎች_የስልጠናና_የምክክር_ፕሮግራም_በአዳማ_ከተማ_መካሄድ_ጀመረ፡፡
በፕሮግራሙ የቤተ እምነቱ የቦርድ አባላት፣ የክልሎች የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት እና ከአጥቢያ የተወከሉ አገልጋዮች በመካፈል ላይ ይገኛሉ፡፡
በመጀመርያው ክፍለ ጊዜ መጋቢ አዕምሮ መልካሙ በጸሎት ፣ መጋቢ በረከት ዝማሬ ያገለገሉ ሲሆን በመቀጠልም የቤተ ዕምነቷ ፕሬዝዳንት መጋቢ ላኮ በዳሶ የእንኳን ደህና መጣችሁና የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።እንዲሁም በመጋቢ ጻድቁ አብዶ ቃል አካፍለዋል፡፡
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://t.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

06 Feb, 12:48


#በመሠረተ_ክርስቶስ_ቤተክርስቲያን_የደቡብ_ኢትዮጵያ_ቀጠና_የመጀመሪያውን_ዋና_ጸሐፊ_ሾመ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ቀጠና ከምዕራብ ኢትዮጵያ በመቀጠል የቤተክርስቲያኒቱ ሁለተኛው ቀጠና ሆኖ በይፋ የጸደቀው ባለፈው ነሀሴ ወር በተካሄደው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን መሪዎች ጠቅላላ ጉባኤ ሲሆን ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የሐዋሳ ክልል ዋና ጸሐፊ የሆኑትን መጋቢ ደነቀ ሁሴንን የቀጠናው ዋና ጸሐፊ አድርጎ መርጧል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ዋና ቢሮን በመወከል በጠቅላላ ጉባኤውን የተገኙት የቤተክርስቲያኒቱ እረኝነት መምሪያ ዳይሬክተር መጋቢ ሰብረላ ከድር የሹመት ስነስርዓቱን ሲያካሂዱ መጋቢ ደነቀ ሁሴን ለቀጣዮቹ አራት አመታት 13 የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ክልሎችና 375 አጥቢያዎችን ያቀፈውን የደቡብ ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ቀጠናን በዋና ጸሐፊነት የሚመሩ ይሆናል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በነደፈችው የአምስት ስልታዊ እቅድ መሠረት በቀጣዮቹ አመታት የቀጠናዎች ቁጥር ወደ አምስት እንደሚያድግ ይጠበቃል።
መረጃዉ በመሠረተ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው።
#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://t.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

30 Jan, 13:08


https://youtu.be/-SsJo-jk6do

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

29 Jan, 13:27


https://youtu.be/kWJZlVxlCLY

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

29 Jan, 12:01


#የኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተክርስቲያናት_ካውንስል_ከኢትዮጵያ_መጸሐፍ_ቅዱስ_ማህበር_ጋር_በመተባበር_በኢትዮጵያ_ዘላቂ_ሰላም_ጉደይ_ላይ_የተዘጋጀ_አውደ_ጥናት_ተካሄደ

ጥር 16 ቀን 2017/ ዓ.ም የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ከኢትዮጵያ መጸሐፍ ቅዱስ ማህበር ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ጉደይ ላይ የተዘጋጀ አውደ ጥናት በስካይላይት ሆቴል የተካሄደ ሲሆን የካውንስሉ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እስኪ መጣ ድረስ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ስራውን ይቀጥላል ሲሉ ገልፀው በሀገር ደረጃ የኢትዮጵያ መጸሐፍ ቅዱስ ማህበር እየሰራ ያለውን ስራ አድንቀው ልባዊ ምስጋናቸውን ገልጸዋል ።


ቀሲስ ሊቅ ትጉዋን ይልማ ጌታሁን የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማህበር በሀገር ደረጃ በሰላም ዙሪያ ምን አይነት ተጽእኖ እየፈጠረን ነው ብለን ልንጠይቅ ይገባል ሲሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል ።በዚህ መርሐግብር ላይ ከተለያዩ አብያተክርስቲያናት የተወከሉ መሪዎች በሰላም ዙሪያ ላይ እየሰራው የሚገኙት የልምድ ማካፈል ጊዜ አከናውነዋል።
በዶ/ር ሳምሶን እስጢፋኖስና በቄስ ዶ/ር ገለታ ሲሜሶ ቀጣይ አካሄዶችና እርምጃዎች ላይ ጠቃሚ አሳቦችን በማቅረብና ውይይት በማድረግ መርሐግብሩ በጸሎት ተጠናቋል ።



#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

29 Jan, 11:15


https://youtu.be/MLu4NbYuSqM

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

17 Jan, 17:31


https://youtu.be/BMUiDdYvky0

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

17 Jan, 15:53


https://youtu.be/rG-yhhnEjyA

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

17 Jan, 11:26


“በአንድነት ቆመን ለሀገራችን ሰላም እና የጋራ ጠላት የሆነውን ድህንነትን ለማሸነፍ በጋራ እንሰራለን” ቄስ ደረጀ ጀምበሩ

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ደረጀ ጀበሩ ይህንን ያሉት "የጥምቀት በዓልን በጽዱ አዲስ አበባ! " በሚል መሪ ቃል የጥምቀት በዓልን ምክንያት በማድረግ በጃን ሜዳ የታቦታት ማደሪያ የጽዳት መርሐግብር በተካሄደበት ወቅት ነው።


በጽዳት መረሃ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የካውንስሉ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ “በአንድነት ቆመን ለሀገራችን ሰላም እና የጋራ ጠላት የሆነውን ድህንነትን ለማሸነፍ በጋራ እንሰራለን” በዛሬው እለትም እዚህ የተገኘነው የጥምቀት በዓል የመላው ኢትዮጵያውያን እና የአለም አቀፍ ማህበረሰብ በዓል መሆኑን በማስመልከት አንድነታችንን ለመግለጽ ነው በማለት ለመላው ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ መልካም በዓል እንዲሆን ተመኝተዋል።

በመርሐግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ፀሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ ሃይማኖታዊ በዓላት ሁሉም ህብረተሰብ አንድነቱንና ትብብሩን የሚያጠናክርባቸው መልካም እሴቶቻችን ናቸው ብለዋል።

ይህም በዓላቱ ደምቀውና አምረው እንዲከበሩ በማድረግ የሀገር ገፅታ እየገነባ መሆኑን የተናገሩት ዋና ጽሐፊው በዛሬው ዕለትም የሁሉም ሃይማኖት ተከታዮች አንድነታቸውን ለማሳየት በጥምቀት በዓል የታቦታት ማደሪያ የፅዳት ዘመቻ ላይ በመሣተፋቸው ምስጋናቸው አቅርበው አንዳችን የአንዳችን በዓል ደስታችን መሆኑን እና አክብሮታችንን ለመግለጽ ተገኝተናል ብለዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ በበኩላቸው ከተማ አስተዳደሩ ለበዓሉ ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠርና በስኬት እንዲከበር የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲሰሩ መቆየቱን አስታውሰው በዓሉን ለማክበር ወደ ከተራና ጥምቀት ለሚጓዙ እግረኞችና ለተሽከርካሪዎች መንገዶችን የማስተካከል ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።

ይህ መድረክ አንድነታችንን ይበልጥ አጉልተን የምናሳይበት መድረክ ነው እኛም ይህንን አንድነታችንን ለመግለጽ እዚህ ተገኝተናል ያሉት ደግሞ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሐዋርያዊ ጽ/ቤት ሐላፊ አባ ጴጥሮስ በረጋ ናቸው።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የፕሮጀክት መምሪያ ኃላፊ የሆኑት መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ወልደኢየሱስ ሰይፉ የጥምቀት በዓል ፍቅርንና አብሮነትን የሚያስተምር በዓል ነው በማለት በዓሉ የሚከበርበትን ስፍራ በአብሮነት በማጽዳት የተባበሩትን የሁሉንም ሃይማኖት ተወካዮችና የህብረተሰብ ክፍሎች በቤተክርስቲያኗ ስም አመስግነዋል።

በመረሃ ግብሩ የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባል ቤተዕምነት መሪዎች ፤ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች እና የጽዳት አምባሳደሮች ፤ የአዲስ አበባ እና የፌደራል ፖሊስ አባላትን ጨምሮ የከተማዋ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

10 Jan, 14:57


https://youtu.be/F9GwjujsczI

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

10 Jan, 13:29


#ጥር_4_የእኔ_እንድሪያስ_ነኝ_ቀን

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል: ከቢሊግርሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን ጋር በመተባበር ጥር 4 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባና በሸገር ከተሞች በሚገኙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት "የእኔ እንድሪያስ ነኝ" የፀሎትና የወንጌል ስርጭት እንደሚያካሄድ ታወቀ::

በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሐፊ በቄስ ደረጀ ጀምበሩ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደታወቀው የወንጌል ምስክርነቱ ካለፈው ህዳር 8 ቀን 2017 ዓ.ም በ400 አጥቢያዎች ከተካሄደው ተመሳሳይ የወንጌል ስርጭት ቀጣይ እንደሆነ ታውቋል::

በዚሁ የቢሊግርሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን ኃላፊዎች በተገኙበት በዚሁ መግለጫ በወንጌል አገልግሎቱ ከ26ሺ በላይ አገልጋዮች የክርስቲያን ህይወትና ምስክርነት ስልጠና የተሰጣቸው ሲሆን ከ200ሺ በላይ "የእኔ እንድሪያስ ነኝ" የፀሎት ካርድ ተበትኖ ክርስቶስን ለማያውቁ ወገኖች ወንጌል የደረሰ መሆኑ በመግለጫው ተብራርቷል::

ጥር 4 ቀን 2017 ዓ.ም ለሚደረገው የፀሎትና የምስክርነት መርሐግብርም ምዕመናን መለኮታዊው የእግዚአብሔር ጉብኝት በምድሪቱ ላይ እንዲገለጥ እንዲፀልዩና ለዚሁ ሥራ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጠቅላይ ጸሐፊው ጥሪ አቅርበዋል::



#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

08 Jan, 16:46


https://youtu.be/MeZsYgPBVVA

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

08 Jan, 13:37


https://youtu.be/uenQv1qKc_w

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

08 Jan, 12:49


https://youtu.be/icLeNkBT56Q

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

07 Jan, 17:32


https://youtu.be/aa6ScM4LEGA

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

07 Jan, 14:47


https://youtu.be/A3Xy3k6zGOw

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

07 Jan, 09:22


https://youtu.be/Jk9wUpegaFQ

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

31 Dec, 15:04


#የመድሐኒታችን_የኢየሱስ_ክርስቶስ_የልደት_መታሰቢያ_በአል
#በዘጸአት_አፖስቶሊክ_ሪፎርሜሽን_ቤተክርስቲያን_ሳርቤት

#አዘጋጅ_የኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተክርስቲያናት_ካውንስል


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

26 Dec, 13:21


https://youtu.be/LNSr2cvwHNY

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

26 Dec, 11:59


#የመድሐኒታችን_የኢየሱስ_ክርስቶስ_የልደት_መታሰቢያ_በአል
#በዘጸአት_አፖስቶሊክ_ሪፎርሜሽን_ቤተክርስቲያን_ሳርቤት

#አዘጋጅ_የኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተክርስቲያናት_ካውንስል


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

26 Dec, 07:38


https://youtu.be/Ge75CDnA-54

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

23 Dec, 15:15


https://youtu.be/WMwc3Nkz_tA

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

20 Dec, 15:46


https://youtu.be/h6_vF34V9M0

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

20 Dec, 14:05


https://youtu.be/FGTRe68_nps

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

20 Dec, 13:48


#የኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተክርስቲያናት_ካውንስል
#ከdynamic church planting international (DCPI) ጋር በመተባበር በሀዋሳ እና አዳማ ከተማ ስልጠና ተሰጠ።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ከDCPI ጋር በመተባበር በሀዋሳ እና አዳማ ከተማ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን የስልጠናው አላማ ቤተክርስቲያን በተሰጣት ብርቱ አላፊነት ላይ ትኩረት እንድትአደርግ የሚረዳ ስልጠና እንደሆነ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የዓለም አቀፍ ግኑኝነት ዳይሬክተር ፓስተር አሸብር ከተማ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የዓለም አቀፍ ግኑኝነት ዳይሬክተር ፓስተር አሸብር ከተማ የመጨረሻው ስልጠና በአምቦ ከተማ የሚደረግ መሆኑንና በ2025 በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በስፋት ስልጠናው የሚሰጥ መሆኑን አክለው ገልፀዋል።


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

15 Dec, 13:32


#ኢየሱስ_ሰውን_ሁሉ_ይወዳል_የኢትዮጵያ_ሙሉ_ወንጌል_አማኞች
ቤተክርስቲያንታላቅ የወንጌል ጀማ ስብከት ወንጌል በአዲስ አበባ ስታዲየም l ቀን 3



#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

29 Nov, 14:30


https://youtu.be/Wb6rrbxFZ0w

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

29 Nov, 12:37


#የኢትዮዽያ_ሙሉ_ወንጌል_አማኞች_ቤተክርስቲያ_ኢየሱስ_ሰዉን_ሁሉ_ይወዳል_በሚል_መሪ_ቃል_በአዲስ_አበባ_ስታዲየሚ_የሚካሄደዉን_ኮንፍራስ_በማስመልከት_ህዳር_20_ቀን_2017_ዓ/ም_ጋዜጣዊ_መግለጫ_ሰጠች።

በመግለጫዉ ከታህሳስ 4 እስከ ታህሳስ 6 ቀን 2017ዓ/ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት ኢየሱስ ሰዉን ሁሉ ይወዳል በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ስታዲየም ኮንፍራንሱ እንደሚካሄድ የተገለፀ ሲሆን ከአዲስ አበባ እና ከሸገር ከተማ የተሰባሰቡ 206 የሚሆኑ የሙሉ ወንጌል አጥቢያ አብያተክርስቲያናት ኮንፍራንሱን በጋራ እንዳዘጋጁት ተገልፃል።

ከኮንፍራንሱ በማስቀደም ለ10 ተከታታይ ወራት የወንጌል ስርጭት ስራ ሲሰራ መቆየቱ እና በቀጣይ 10 ቀናት በተለያዩ ማህበራዊ ሚድያዎች የወንጌል ስርጭት እንቅስቃሴ እንደሚደረግ አስታዉቀዋል።
እንዲሁም በልዩ ልዩ በጎ ተግባራት ማለትም ነፃ የህክምና አገልግሎት በቂርቆስ ጤና ጣቢያ ታህሳስ 2 እና 3 እንደሚሰጥ እና በቂሊንጦ፣በዳለቲ እና በቃሊቲ ማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች ልዩ ልዩ ድጋፍ እንደሚደረግ ተገልፃል።

ቤተክርስቲያኒቱ በሀገር ዉስጥ እና ከሀገር ዉጪ በደቡብ አፍሪካ፣በሶማሊያ፣በደቡብ ሱዳን እና በጅቡቲ ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስራዎችን ስትሰራ እንደቆየች በመግለጫዉ ተካቷል።

መግለጫዉን የሰጡት የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዝዳንት ፓስተር ላኮ በዳሶ፣ ምክትል ፕሬዝዳንት ፓስተር ለወየው ስንሻው እና የፕሮግራሙ አስተባባሪ ፓስተር አበራ አብዋሬ ሁሉም የወንጌል አማኝ በኮንፍራንሱ ላይ ሰዎችን በመጋበዝ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

26 Nov, 09:15


#የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊግረሃም አሶሴሽን ጋር በመተባበር የአገልጋይ ሴቶች ስልጠና ሁለተኛ ዙር ህዳር 17 ቀን 2017ዓ/ም በናዛሪን ቤተክርስቲያን አካሄደ::

አላማው አገልጋይ ሴቶች ውጤታማ የወንጌል መስካሪዎችና ለታላቁ ተልእኮ አገልግሎት ብቁ እንዲሆኑ ለማስታጠቅ ነው።
ስልጠናው ለ200 አገልጋይ ሴቶች የተሰጠ ሲሆን በህይወታቸውና በአገልግሎታቸው የጌታ ኢየሱስን አዳኝነት የሚመሰክሩ ለሌሎች የጌታን ብቸኛ አዳኝነት የሚናገሩና የሚያሳዩ ሴቶች እንዲሆኑ የሚያበቃ ነው:: የኢትዬጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የሴቶች አገልግሎት ክፍል ሴት አገልጋዬች የወንጌልን ተልእኮ በመወጣት የእግዚአብሔርን መንግስት በማስፋት ብቁ እንዲሆኑና እንዲተጉ ልዩ ልዩ ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሆነ ተገልጿል።


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

25 Nov, 08:30


https://youtu.be/8kj14ljTKNg

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

23 Nov, 08:31


https://youtu.be/3TSz8oXgZwo

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

22 Nov, 16:34


https://youtu.be/QRjZCdO1VM0

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

22 Nov, 16:00


https://youtu.be/riVRprWTTyU

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

22 Nov, 09:27


#የኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተክርስቲያናት_ካውንስል_ከቢሊግረሃም_አሶሴሽን_ጋር_በመተባበር_ለአገልጋይ_ሴቶች_ስልጠና_ተሰጠ

ህዳር 12 ቀን 2017ዓ/ም በዩጎ ቤተክርስቲያን በተሰጠዉ ስልጠና ከልዩ ልዩ ቤተ-ዕምነት እና ህብረቶች የተወጣጡ 260 የሚሆኑ ሴት አገልጋዮች በስልጠናዉ ተካፍለዋል።

የካዉንስሉ መንፈሳዊ ዘርፍ ዳይሬክተር ፓስተር ስንሻት ተካ እንደገለፁት የስልጠናዉ አላማ አገልጋይ ሴቶች ውጤታማ የወንጌል መስካሪዎች እንዲሆኑ ለማስታጠቅ መሆኑን በመግለፅ ይህ ፕሮግራም በተመሳሳይ ማክሰኞ ህዳር 17 ቀን 2017ዓ.ም. ከ2:30 ጀምሮ ልደታ ባልቻ ሆስፒታል ጀርባ በሚገኘው በናዛሪን ቤ/ክ የሚሰጥ መሆኑን አክለዉ ተናግረዋል።

ከቢሊግርሃም ኢቫንጀልስቲክ አሶሴሽን ስልጠናዉን የሰጡት ቄስ ፀጋነሽ በበኩላቸዉ እኔ እንድሪያስ ነኝ በሚል መሪ ሃሳብ በስልጠናዉ የተሳተፋ ሴት አገልጋዮች ወደመጡበት ሲመለሱ ወንጌልን በአካባቢያቸዉ መመስከር እንዲችሉ የሚያበቃ ስልጠና መሆኑን ገልፀዋል።

ከስልጠናዉ በኋላ የጋራ የዉይይት እና የምክክር እንዲሁም የትዉዉቅ ጊዜ ተከናዉኖ ስልጠናዉ ተጠናቋል።


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

20 Nov, 06:45


https://youtu.be/5wKJ8LfGHOU

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

19 Nov, 14:25


https://youtu.be/I-QyXNcypSE

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

19 Nov, 13:13


#የሮሆቦት_አብያተክርስቲያናት_ህብረት_2ተኛ_መደበኛ_ጠቅላላ_ጉባኤዉን_አካሄደ

በጉዲና ቱምሳ ፋዉንዴሽን አዳራሽ በተካሄደዉ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የኢትዮዽያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል ጠቅላይ ፀሃፊ ቄስ ደረጀ ጀንበሩ እና የኢትዮዽያ ወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ፕሬዝዳንት ፓ/ር ፃዲቁ አብዶ እንዲሁም የሌሎች ኀብረት መሪዎች በክብር እንግድነት ተገኝተዋል።

የሮሆቦት አብያተክርስቲያናት ህብረት ፕሬዝዳንት መጋቢ ካሳሁን እምሩ ለጉባኤዉ የእንኳን ደህና መጣቹ ንግግ ያደረጉ ሲሆን የህብረቱ የቦርድ ሰብሳቢ መጋቢ አየለ ወርቁ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል እንዲሁም ም/ፀሃፊ እና የፅ/ቤቱ ሃላፊ ፓ/ር አዲስ አዳነ ፀሎት በማድረግ ፕሮግራሙን አስጀምረዋል ዘማሪ ፀሀይ ዘለቀ በዝማሬ ስታገለግል የገሊላ ኢንተርናሽናል ባይብል ሰሚነሪ ም/ፕረዚዳንት  ዶ/ር ብርሃኑ ያደታ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል።

በጉባኤዉ የካዉንስሉ ጠቅላይ ፀሃፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ ከቀድሞ ይልቅ ተያይዘን አብረን መስራት አለብን በማለት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ፕሬዝዳንት ፓ/ር ፃዲቁ አብዶ ትኩረታችንን በቃሉ ላይ የተመሰረተ አስተምህሮ አድርገን ወንጌል እንስራ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የሮሆቦት አብያተክርስቲያናት ህብረትን በገንዘብ እና በልዩ ልዩ አስተወፅኦ ለደገፉ ለህብረቱ መስራች እና አስፈፃሚዎች የእዉቅና እና የሰርተፍኬት ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።

በ2ተኛ መደበኛ ጉባኤ ህብረቱ በተለያየ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ በዋናነት ቀድሞ የነበረዉን መተዳደሪያ ደንብ የበለጠ በስፋት ለመንቀሳቀስ ያመች ዘንድ አሻሽሎ ልዩ ልዩ ዉሳኔዎች አስተላልፏል።

በመጨረሻም ለጉባኤ መሳካት የበኩላቸዉን ላደረጉና ሲያስተባብሩ ለነበሩ የአዲስ አበባ ፅ/ቤት ሰብሳቢ ነብይት ሮዛ አድማሱ እንዲሁም ዋና ፀሃፊ ነብይ ኤልያስ እና ከዋናዉ ፅ/ቤት ፓ/ር አዲስ አዳነን ኅብረቱ አመስግኗቸው የጉባኤ ፍጻሜ ሆኗል።


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

18 Nov, 14:28


https://youtu.be/6TS6ZXswSFE

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

18 Nov, 13:43


#የኢትዮዽያ ቲር ፈንድ ቢሮ ቤተክርስቲያን እና የማህበረሰብ ለዉጥ ላይ አተኩሮ የሚሰራ ቦርድ አቋቋመ። በኢትዮዽያ የቦርዱ ሰብሳቢ የካዉንስሉ ተወካይ የሆኑት ፓስተር አሸብር ከተማ ሆነዉ ተመርጠዋል።

ከህዳር 3 እስከ ህዳር 6 ቀን 2017ዓ/ም በኬኒያ በተካሄደዉ ስብሰባ የኢትዮዽያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል የአለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር ፓ/ር አሸብር ከተማ ጨምሮ አራት ተወካዮች በስብሰባዉ ተካፍለዋል።

በስብሰባዉ ከሯንዳ፣ቡርንዲ፣ከዲሞክራቲክ ሪፐፕሊክ ኦፍ ኮንጎ፣ከደቡብ ሱዳን እና ኢትዮዽያን ጨምሮ ከስድስት ሀገራት የተወጣጡ ወደ 30 የሚሆኑ ተወካዮች ተገኝተዋል።

ስብሰባዉ የትኩረት አቅጣጫዉን ያደረገዉ ቤተክርስቲያን ማህበረሰቡን መለወጥ እንደምትችል እና በሰላም፣ተስፋ በማደስ እነዚህን እና በመሳሰሉ ጉዳዮች የለዉጥ ሐዋሪያ ሆና ማገልገል እንደምትችል በዋነኝነት ተወያይተዋል። ከዉይይቱ ባሻገር የስልጠና ጊዜ እና በሌሎች ሀገራት የተሰሩ ስራዎች የግምገማ ጊዜ ተከናዉኗል።

በመጨረሻም በኢስት አፍሪካና በሴንትራል አፍሪካ ሪጅን ምርጫ ተካሂዶ የካዉንስሉ አለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር ፓስተር አሸብር ከተማ የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ሆነዉ ተመርጠዉ ስብሰባዉ ተጠናቋል።


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ -
https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦
https://t.me/EGBCC
tiktok :-
https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

15 Nov, 12:57


https://youtu.be/o6RyZ4hYHic

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

12 Nov, 07:08


https://youtu.be/z68cPY4_OuQ

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

08 Nov, 15:42


https://youtu.be/AoAL1UtJg5M

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

07 Nov, 13:38


https://youtu.be/-DDpIFuI_uM

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

07 Nov, 09:02


https://youtu.be/l35PRB_2bIw

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

06 Nov, 12:19


https://youtu.be/VnmwFMvmiYE

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

06 Nov, 12:13


#በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የደራይታ #አዲስ ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስ በጊዶሌ ከተማ በድምቀት ተመረቀ።

የትርጉም ሥራው ከ1996-2012 ዓ.ም በድምሩ 16 ዓመታት የወሰደው የደራይታ አዲስ ኪዳን የህትመት ሥራው ተጠናቆ በጋርዱላ ዞን ጊዶሌ ከተማ በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።

የደራሼ ማህበረሰብ ወንጌልን ካገኘ 75 ዓመታት ቢቆጠሩም መጽሐፍ ቅዱስን በአፍ መፍቻ ቋንቋው አላገኘም ነበር። የደራይታ አዲስ ኪዳን ተመርቆ ለምዕመናን መድረሱ አማኞች ያለ ምንም ችግር በልብ ቋንቋቸው የእግዚአብሔርን ቃል ማንበብ እና መስማት እንዲችሉ ያስችላል።

የትጉሙም ሂደቱ ብዙ አመታትን ከመፍጀቱ ባሻገር በቡዙ ፈተናዎች ውስጥ ማለፉን እና ለዚህ ውጤት በመድረሱ እግዚአብሔርን እንደሚያመሰግኑ የደራይታ መጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ቡድን መሪ ቄስ ሐታኖ ሐይቶሳ ገልፀዋል።

በምረቃ መርሃ ግብሩም የቤተ ክርስቲያኒቱ የሚስዮን እና ቲኦሎጂ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል፣ የደቡብ ምዕራብ ሲኖዶስ ፕሬዚደንት እና ማኔጅመንት፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ የትርጉም አገልግሎት ብሄራዊና የክልል ማስተባበሪያ ቢሮ ባለሙያዎች፣ በፕሮጀክቱ በአጋርነት ሲሰሩ የነበሩ ተቋማት፣ የዞኑ የመግሥት ቢሮ ተወካዮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
መረጃዉን ከኢትዮዽያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማህበራዊ ትስስር ገፅ ላይ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።

#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://t.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

05 Nov, 15:43


https://youtu.be/MCEUMis_6xY

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

05 Nov, 15:38


#ቤሪያ_ሊደርሺፕ_ኢንስቲቲዮት_በማስተርስ_እን_በዲግሪ_መርሃ_ግብር_በአዲስ_አበባ_በድሬዳዋ_እና_በጅማ_ካምፓስ_ያስተማራቸዉን_ተማሪዎች_በታላቅ_ድምቀት_አስመረቀ

ጥቅምት 23 ቀን 2017ዓ/ም በብሔራዊ ቲያትር አዳራሽ በተከናወነዉ የምረቃ መርሃ ግብር የካዉንስሉ ምክትል ፕሬዝዳንት ፓ/ር ዶ/ር ቤተ መንግስቱ፣የካዉንስሉ ጠቅላይ ፀሃፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ፣የአብያተክርስቲያናት ህብረት ምክትል ፕሬዝዳንት ፓ/ር ሰንበቶ በሼ ፣የመሰረተ ክርስቶስ ቤ/ክ ፕሬዝዳንት ፓ/ር ደሳለኝ አበበ፣ዶ/ር ወዳጄነህ ማህረነ ጨምሮ የልዩ ልዩ አብያተክርስቲያን መሪዎች የክብር እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

የቤሪያ ሊደርሽፕ ኢንስቲቲዩት ፕሬዝዳንት ፓ/ር ሚካኤል ተፈራ ከዛሬ 21 አመት በፊት ይህን ራዕይ ተቀብለዉ ዛሬ ላይ እዉን ሆኖ በማየታቸዉ የተሰማቸዉን ደስታ በመግለፅ ለተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላቹ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።ቤሪያ እዚህ እንዲደርስ ከጎናቸዉ የቆሙትን በሙሉ በመባረክ አመስግነዋል።

በመጨረሻም ከቤራያ ጎን ለቆሙት የእዉቅና ሰርተፍኬት በመስጠት እና ተሸላሚ ተማሪዎችን በመሸለም የምርቃት መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።

ቤሪያ ሊደርሺፕ ኢንስቲቲዩት ለተለያዩ አብያተክርስቲያን መሪ አገልጋዩች እና ተቋማት ስልጠናዎችን እንደሰጠ መዘገባችን ይታወሳል።


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://t.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

01 Nov, 16:40


https://youtu.be/4iVWjooBGXE

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

31 Oct, 14:23


https://youtu.be/dBHCkMA0uVc

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

30 Oct, 14:18


https://youtu.be/DGhJ4RU-qVE

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

30 Oct, 09:36


#የኢትዮጵያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተክርስቲያናት_ካውንስል_ከውሃና_ኢነርጂ_ሚንስትር_ጋር_የመግባቢያ_ስምምነት_ተፈራረሙ

ጥቅምት 19/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ከውሃና ኢነርጂ ሚንስትር ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። በቀጣይ በማንኛቸውም በሚሰሩ ስራዎችን በመደገፍ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጋር በርካታ ስራዎችን በጋራ እንደሚሰሩ የውሃና ኢነርጂ ሚንስትር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገልጸዋል ።የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሃፈ ቄስ ደረጃ ጀምበሩ የውሃና ኢነርጂ ሚንስትር በማመስገን በመያያዝና በመከባበር በአንድነት ብንሰራ በሀገር ደረጀ በርካታ ስራዎች ላይ ውጤታማ መሆን እንችላለን ብለዋል።


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://t.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

29 Oct, 14:10


https://youtu.be/_GsHisNA0Tc

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

29 Oct, 12:31


#የኢትዮዽያ_ወንጌል_አማኞች_አብያተክርስቲያናት_ካውንስል_በአዲሰ_አበባ_ከተማ_የሚገኙ_የካውንስሉን_አባል_ቤተ_አምነቶቸን_በራ_እንዲሰሩ_አደራጀ

ፕሮግራሙ ጥቅምት16-2017/ዓ.ም በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ዋና ጽ/ቤት ስብሰባ አዳራሽ ውስጥ የተካሄደ ሲሆን የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዘዳንት ፓስተር ፃድቁ አብዶ የእግዚአብሔርን ቃል ያካፈሉ ሲሆን እግዚአብሔር ትሁት ነውና በትህትና እና በአንድ ልብ ተያይዘን እናገልግል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የኢትዮዽያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል ጽ/ቤ ሃላፊ ፖስተር ጌቱ ለማ ስለ ካዉንስሉ አደረጃጀት ገለፃ በማድረግ እንዲሁም ለህብረት ሲባል ብዙ መሰዋዕትነት መክፈል ይገባል በተለይም በአዲስ አበባ ያላችሁ መዋቅሮች ምሳሌ ልንሆን ይገባል ብለዋል። 
በአዲሰ አበባ ከተማ የካዉንስሉን ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በማቋቋም የካዉንስሉን ስራ እንዲያስፈፅሙ የኮሚቴ ምርጫ ተደርጎ ቦርድ ተቋቁሟል።


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://t.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

25 Oct, 14:02


#የገርጂ አማኑኤል ህብረት ቤ/ክ፡ የጋሽ ብሉጽ ወዳጆችና የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ጋር በመሆን የምረቃ ፕሮግራምን በተመለከተ ጥቅምት 15ቀን 2017ዓ/ም በስካይላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥተዋል።

መዝገበ ቃላቱ 5600 በላይ የግሪክ ቃላትን የያዘ ሲሆን፡ ለእያንዳንዱ የቃል ትርጉም ተዛማጅ የአዲስ ኪዳን ክፍሎችን ይጠቅሳል። ጋሽ ብሉጽ ፍትዊ የመዝገበ ቃላቱን አዘጋጅተው አጠናቀው፡ የህትመት አደራውን ለገርጂ አማኑኤል ህብረት ቤ/ክ ሰጥተው ወደ ጌታ የሄዱ ሲሆን፡ መዝገበ ቃላቱን ስራውን የገርጂ አማኑኤል ህብረት ቤ/ክ አሳትማዋለች። መዝገበ ቃላቱ አደራ በሚል መሪ ቃል ጥቅምት 25 ቀን 2017ዓ/ም በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል እንደሚመረቅ ነዉ የተገለፀዉ።ይህ ታሪካዊ ሥራ “ዐደራ” የሚል ስያሜ በተሰጠው ልዩ የምረቃ መርሓ ግብር በይፋ ለአንባቢያን ይቀርባል።

የጋሽ ብሉጽ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ ደስታ"እኔ ወደ አባቴ ስሄድ ምን ሰራህ ቢለኝ ምን እመልሳለው ይል ነበረ።" የገርጂ አማኑኤል ህብረት ቤ/ክ የባለቤቴን አደራ ተቀብላ፡ እዚህ ስላደረሰች፡ ቤተ ክርስቲያኗን እግዚአብሔር ይባርካት ብለዋል።
የገርጂ አማኑኤል ቤ/ክ ዋና መጋቢ ዘሪሁን ኋ/ሚካኤል ጋሽ ብሉጽ ለቤተ ክርስቲያን እና ለትውልዱ ላበረከቱት ትልቅ አስተዋጾ እግዚአብሔር ይባርካቸው ብለዋል። የእርማት ስራውን ከኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤ/ክ አባ ዳንኤል ለሁለት አመታት በትጋት እንደተሰራ ተገልፃል ጋሽ ብሉጽ በአዲስ አበባ መጽሃፍ ቅዱስ ኮሌጅና ሙሉ ወንጌል ሴሚናርየሞች አስተምረዋል። መዝገበ ቃላቱ ለኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት፡ ለመጽሃፍ ቅዱስ ኮሌጆችና ተመራማሪዎች ትልቅ አስተዋጾ አለው ተብሏል።


#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://t.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

25 Oct, 07:12


https://youtu.be/a8h8YsVrsUk

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

24 Oct, 11:43


የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት የሰላም እና አድቮኬሲ መምሪያ ጂስራ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር “የሐይማኖት ተቋማት ምክክር እና ወይይት ለሰላም እና አብሮነት ያለው ፋይዳ” በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ተካሄደ።
በመረሃ ግብሩ “የሐይማኖት ተቋማት ምክክር (ወይይት) ለሰላም እና አብሮነት ያለው ፋይዳ” ከክርስትና እና ከእስልምና አስተምሮ አንጻር እንዴት ይታያል? የሚለውን የመነሻ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።


በመረሃ ግብሩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት መጋቢ ታምራት አበጋዝ በሃይማኖት ተቋማት የሚደረግ ምክክር ፈጣሪን ከመፍራት፣ በስነምግባርና ሞራል እሴት የሚመራና አንፃራዊ ተዓማኒነት ያለው በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ያሉ ሲሆን ሃይማኖት ተቋማት በውስጣቸውና ከሌሎች ጋር የሚያደርጉት ምክክር ውስጥ ጥንካሬን፣ለርስ በርስ መተማመን እና ለጋራ ረዕይ በጋራ መስራትን ሲያጎለብት በሃይማኖቶች መካከልም መከባበርን ፣ መተባበርን እና አብሮነትን በማሳደግ ጥርጣሬንና ስጋትን ይቀርፋል ሲሉ ተናግረዋል።

ሃይማኖቶች ሁሉ የሰላም ምንጭ ናቸው የሚፈጠሩ ችግሮችንም በምክክር በመፍታት ለሀገር የተሻለ ስራ መስራት ይገባል ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት ፓስተር ጻዲቁ አብዶ ናቸው።

መጋቢ ጻዲቁ አብዶ አክለው የሁሉም ሃይማኖት ቅዱሳት መጽሀፍ እንደሚያዝዙን አንዱ በሌላው ክፉ ባለመስራት ለሰላም መቆም፣ አንዱ የሌላውን ሀይማኖት ማክበር ይገባልም ብለዋል።

በመረሃ ግብሩ ላይ “የሐይማኖት ተቋማት ምክክር (ወይይት) ለሰላም እና አብሮነት ያለው ፋይዳ” ከክርስትና እና ከእስልምና አስተምሮ አንጻር እንዴት ይታያል? በሚል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙሃን ስርጭት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ ቀሲስ ዶ/ር መዝገቡ ካሳ እና የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሪያድ ጀማል የመነሻ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።

ምክክር በእስልምና ምክክር በክርስትና ፤ በጋራ ጉዳዮች ላይ እንዴት ተባበር ለሀገራችን የራሳችንን ድርሻ መወጣት እንችላለን ? የሃይማኖት ተቋማት ሚዲያዎች ፤ አማኙስ ማህበረሰብ ድርሻው ምንድነው? ወንድማማችነት እንዲጠነክር ምን እናድርግ ? የሚሉ ሃሳቦችን በውይይቱ በስፋት የተነሳ ሲሆን ጽሁፍ አቅራቢዎች ለተነሱ ጥያቄዎች እና ሃሳቦች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥጠዋል።

ተመሳሳይነት ያላቸው ውይይቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥል የተገለጸ ሲሆን በተካሄደዉ መረሃ ግብር የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባል ቤተዕምነት መሪዎች እና የሴቶች ተወካዮችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል።

#ለበለጠ_መረጃ
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EGBCC/
ዩትዩብ፡ - https://www.youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
ቴሌግራም፦ https://t.me/EGBCC
tiktok :- https://www.tiktok.com/@evangelical_tv
ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!!!!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

24 Oct, 06:49


https://youtu.be/X8gC3C2jlAs