የቅድስት ሥላሴ ልጆች @yekdset_selase_lejoch Channel on Telegram

የቅድስት ሥላሴ ልጆች

የቅድስት ሥላሴ ልጆች
ቅድስት ሥላሴ

#ማህበሩ አላማዉ

፩.ኦርቶዶክስአዊ ስርአትን የጠበቁ አስተማሪ ትምህርቶች፣ መዝሙር፣ጥያቄ እና መልሶችን ለተዋህዶ ልጆች ማቅረብ፤

፪.የሥላሴ ልጆችን ሰብስቦ ማህበር በመፍጠር ቅዱስ ስራዎችንመስራት …

የመወያያ ግሩፕ ላይ ቤተሰብ ለመሆን የምትፈልጉ
@enamsgen @enamsgen

ለማንኛዉም ሀሳብ አስተያየት @kiya17 ያድርሱን
12,878 Subscribers
5,958 Photos
456 Videos
Last Updated 20.02.2025 20:30

የቅድስት ሥላሴ ልጆች የአማርኛ አመራሚነት

የቅድስት ሥላሴ ልጆች በኦርቶዶክስ የእምነት ማህበር ይታወቃሉ፡፡ እነዚህ ልጆች በበላይ እምነታቸው ይገኙባቸው ይኖራሉ፡፡ የግማሽ ሣምብ እንዲሆን ምንጭ የሆነ ቅድስት ሥላሴ ወይ ቢኖር ምንም ይፈልጋሉ፡፡ የዚህ ሂደት ተወዳዳሪ የሚያምር ዲያን በየአለም አገራት ላይ አስተዳደር ይሰጣል፡፡ ይህም ምንጭ ወይ ምንኛ መርገም እንደሚባል ይሁን ማለት ይዘው ላይ ይቬሩ ምንጭ ይሆናል፡፡ ክሥረት ይህ ይሆናል በሚቨዘዉ ነገር በሚታወሱ ላይ ይህ ላይ ይገኙባቸው ይሆናሉ፡፡

የቅድስት ሥላሴ ልጆች ምንድነው?

የቅድስት ሥላሴ ልጆች የኦርቶዶክስ ማህበር ውስጥ ያሉት የእምነት ተወካይ ማህበር ናቸው፡፡ እነዚህ ልጆች በቋሚነት ዘጠኝ ዓይነት ዝግጅት ይሰጣል፡፡

ይህ ተወካይ ማህበር በትምህርት ሳለ በማህበሩ አይነት የትውስ ሳይንስ ተፈጻሚ ሂደት ይምርጡ፡፡ ይህም በተለይ ከህመም ይወድሱ፡፡

አብራሪ ማህበሩ እንዴት ይሰማል?

የቅድስት ሥላሴ ልጆች ይህ ከኦርቶዶክስ መሠረት ይገኡባቸው አስተምህሮ ስርአት ባለባቸው ወይ ሳይንስ ይዘው አንዴ ይሁናል፡፡

ይህም በተለይ ወሳኔ ወልደም ይታወቃል የእምነት ሰውዶች ወላጊም ይሁን ይገኙባቸው ያለው ማህበሩ ይታወቃል፡፡

እንዴት ማህበሩ ይመግባ?

ይህ ማህበሩ ወይ በተዋህዶ ድምፅ ይገኙባቸው ይወቅን፡፡ ይህ ማህበሩ የቅድስት ሥላሴ ልጆች ንግድ ወልደ ይሁን እና ይመግባ ይነሱ ይወደማል፡፡

እንዲህም ይህ ይወደማል ይህ ማህበሩ ይነሱ ይመሃይ ይወጊይ እንዲገኙባቸው ይገኙባቸው ይሁን ማለት ይሰጣል፡፡

ይህ የቅድስት ሥላሴ ፈርዖስ ምንድነው?

ይህ የቅድስት ሥላሴ ፈርዖስ ወልደም ይገናኛል፡፡ ይህ ይወደው ይገናኛል እንዲዲ እንዲወደው ይሁን፡፡

ወንበር ይሰጣል ወይ ወይ በማህበሩ ወይ ወንድ ወይ በሌላ ዘይበል ይሁን ይሁን ይበል፡፡

የቅድስት ሥላሴ ልጆች Telegram Channel

የቅድስት ሥላሴ ልጆች በማህበሩ አላማዉ እና ምክንያቱ እንዲቀላው በሚገኝበት እጅ ላይ ደረሱ። ይህም ማህበሩ ከለት ሥላሴ ልጆችን የግል ማህበረሰብ እስከ ንግድ ቱምህርታህ ድረስ መጽሐፍና ጥያቄዎች እና መልሶችን ለማቅረብ የሚደጋገሩ እና እንዲያረጋግጠው እንደሆነ እንዲሁም የሥላሴ ልጆችን ለመፍጠር እና ለመስራት መላ ሲሆን በመጠን ላይ የሚረባቸውን ወሬዎችን ገንዘቡ ተረትሎ በማቅረብ አድርገናል። ይሁንን እናም የመወያያ ግሩፕን በተመለከተ ግሩፕ ላይ ቤተሰብ አለመሆን ከሚታመኑበት ደንብና እንዳዩ ለመሆን በሚሰጡበት ሀሳቦች መነሻ እና በበጀትነት እንደገናና ጥጉና ይሳይልን። ለመቀጠል እና የሚያስተላልፉ ሀሳብ አድርጋለሁ @kiya17 ከልጆች ጋር ነው።

የቅድስት ሥላሴ ልጆች Latest Posts

Post image

🕊

[  † እንኳን ለታላቁ ሊቅና የተዋሕዶ ጠበቃ ቅዱስ ሳዊሮስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

🕊  †  ታላቁ ቅዱስ ሳዊሮስ  †  🕊

† ቅዱስ ሳዊሮስ በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አካባቢ በሶርያ አንጾኪያ የተነሳ አባት ነው። ወቅቱ መለካውያን [ሁለት ባሕርይ ባዮች] የሰለጠኑበት እንደ መሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ያነሱበትና የሚሰደዱበት ጊዜ ነበር። በዚህ ጊዜ ነበር ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ሳዊሮስ በሥላሴ ፈቃድ ለቤተ ክርስቲያን የተነሳው። ሊቃውንት አንበሳ ሲሉ ይጠሩታል።

ቅዱሱ ለተዋሕዶ ሃይማኖት ብዙ ሆኖላታል። የመናፍቃን ጸር በመሆኑ ብዙ ድርሰቶችን ደርሷል። ንጉሡን ዮስጢያኖስን [Justinian] ሳይቀር በይፋ ይገስጸው ነበርና ንጉሡ ሊገድለው ቆረጠ።

ሃይማኖቷ የቀና ንግሥቲቱ ታኦድራ ግን ይህንን ስትሰማ በሌሊት ወደ ሊቁ ሒዳ "እባክህን ሽሽ።" አለችው። እርሱ ግን "ሞት ለእኔ ክብር ነውና አልሔድም።" ሲል መለሰላት። አባቶችን ሰብስባ "ስለ ቤተ ክርስቲያን ስትል" ብለው ለምነው ወደ ግብጽ ሸኙት።

እርሱ እየሔደ ገዳዮቹ ያሳድዱት ገቡ። መንገድ ላይ ቢደርሱበትም ተሰወረባቸው። ለብዙ ቀናትም አብሯቸው ተጓዘ። እነርሱ ተስፋ ቆርጠው ሲመለሱ እርሱ ግን ምድረ ግብጽ ደረሰ።

በምድረ ግብጽም የጵጵስና ልብሱን ትቶ የመነኮሳትን አሮጌ ልብስ ለብሶ ሕዝቡንና መነኮሳቱን አስተማረ ፤ አጸና። በየቦታውም ብዙ ተአምራትን ሠራ።

አባቶች መነኮሳትም ማንነቱን ባወቁ ጊዜ ሰገዱለት። ዶርታኦስ ]ዱራታኦስ ] በሚባል አንድ ደግ ሰው ቤትም በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ የካቲት ፲፬ ቀን ዐርፏል።

† አምላከ ቅዱሳን ሊቃውንት የድንግል እመቤታችንን ጣዕሟን ፍቅሯን ያሳድርብን። የአበውን ሃብትና በረከትም አይንሳን።

[  † የካቲት ፲፬ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
፪. ቅዱስ ቄርሎስ ሊቀ ጳጳሳት
፫. አባ ያዕቆብ ሊቀ ጳጳሳት
፬. ቅዱስ ዳርዮስ
፭. ቅድስት ሊድና

[    † ወርኀዊ በዓላት    ]

፩. አቡነ አረጋዊ [ ዘሚካኤል ]
፪. ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ
፫. ቅዱስ ፊልጶስ ሐዋርያ
፬. ቅዱስ ሙሴ [ የእግዚአብሔር ሰው]
፭. አባ ስምዖን ገዳማዊ
፮. አባ ዮሐንስ ጻድቅ
፯. እናታችን ቅድስት ነሣሒት

† " ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" †
[ይሁዳ ፩፥፫]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

20 Feb, 20:04
19
Post image

🕊

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †

[  ❖ የካቲት ፲፫ [ 13 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

🕊  †   ማር ፊቅጦር    †  🕊

ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በደማቸውና በገድላቸው ያስጌጡ ብዙ ሰማዕታት አሉ:: ነገር ግን ከኮከብም ኮከብ ይበልጣልና ማን እንደ ጊዮርጊስና እስጢፋኖስ ! ከእነርሱ ቀጥለው ከሚጠሩ ሰማዕታት ደግሞ አንዱና ዋነኛው ቤተ ክርስቲያን "ማር" የምትለው ቅዱስ ፊቅጦር ነው::

እስኪ ከበዛው መዓዛ-ገድሉ ጥቂት እንካፈል :-
- ቅዱስ ፊቅጦር አባቱ ኅርማኖስ ይባላል:: አረማዊና ጨካኝ ነው:: እናቱ ግን የተመሰገች ቅድስት ማርታ ትባላለች:: ልጇን እንደሚገባ አሳድጋው ፳ [ 20 ] ዓመት ሲሞላው የአንጾኪያ ንጉሥ የሠራዊት አለቃና በመንግሥቱ ፫ [3] ኛ አድርጐ ሾመው::

የድሮዋ አንጾኪያ [ሮም] እንደ ዛሬዋ አሜሪካ ዓለምን የተቆጣጠረች ሃገር ነበረች:: ቅዱስ ፊቅጦር ደም ግባቱ ያማረ: በጦርነትም ኃይለኛ ስለ ነበር ሁሉ ያከብሩት: ይወዱትም ነበር::

እርሱ ግን ቀን ቀን ሲጾም: ነዳያንን ሲያበላ ይውል ነበር:: ሌሊት ደግሞ እኩሉን ሲጸልይና ሲሰግድ እኩሉን የእስረኞችን እግር ሲያጥብ ያድር ነበር:: ይህ ሁሉ ሲሆንኮ እርሱ የንጉሡ ፫ [3] ኛ : የሠራዊትም አለቃ ነው:: በዘመኑ የሚያገድፍ ምግብና የወይን ጠጅ በአፉ ዙሮ አያውቅም::

ከነገር ሁሉ በሁዋላ ንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ካደ:: ዘመነ ሰማዕታትም ጀመረ:: አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ:: ከ፵፯ [47] ሚሊየን በላይ ክርስቲያኖች በመንኮራኩር ተፈጩ:: በመጋዝ ተተረተሩ:: ለአራዊት ተሰጡ:: በግፍም ተጨፈጨፉ:: ቀባሪ አጥተውም ወደቁ::

በዚሕ ጊዜ ማር ፊቅጦር እናቱን ቅድስት ማርታን በዕንባ ተሰናብቶ ወደ ንጉሡ ቀርቦ በክርስቶስ ስም ታመነ:: ክፉ አባትም በልጁ ላይ ሞትን መከረ::

ከዚያም ቅዱሱን አፉን በብረት ለጉመው ወደ ምድረ ግብፅ አወረዱት:: መሪያቸው እንዳልነበረ ወታደሮቹ መኩዋንንቱ ሁሉ ተዘባበቱበት:: እርሱ ከምድራዊ ንግሥና ሰማያዊ መንግስትን: በሰዎች ፊት ከመክበር ስለ ክርስቶስ ሲል መናቅን መርጧልና::

ለቀናት : ለወራትና ለዓመታት መኩዋንንቱ እየተፈራረቁ አሰቃዩት:: በርሱ ላይ ያልሞከሩት የስቃይ ዓይነት አልነበረም:: አካሉን ቆራርጠዋል: ዓይኖቹን አውጥተዋል: ምላሱንም ቆርጠዋል:: ሚያዝያ ፳፯ [ 27 ] ቀን ግን በሰይፍ አንገቱን ቆርጠውታል:: ስለዚህም እናት ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ማክበር ታከብረዋለች::

❖ እግዚአብሔርም ለቅዱስ ፊቅጦር እንዲህ አለው :-

" እንደ አቅሙ ስምህን የጠራ: መታሠቢያህን ያደረገ : ስምህን ያከበረ: የብርሃን ልብስ አጐናጽፌ ወደ መንግስተ ሰማያት አስገባዋለሁ::"

❖ ይህች ቀን ማር ፊቅጦር የተወለደባት ናት፡፡ እናቱን ቅድስት ማርታ [ ሶፍያንም ] እናስባለን፡፡

❖ ቸሩ አምላከ ፊቅጦር ሁላችንም ይማረን:: ከቃል ኪዳኑ አሳትፎ ለርስቱ ያብቃን::


🕊  ቅዱስ አውሳብዮስ ካልዕ [ጥዑመ ዜና]  🕊

ቅዱስ አውሳብዮስ በወጣትነቱ ከተባረከች ሚስቱ ጋ በድንግልና የኖረ ፥ በዘመኑ ባሕር ውስጥ ሰጥሞ ይጸልይ ፥ ፬ ሺህ [4,000] አቡነ ዘበሰማያት በአንድ ቀን ያደርስ የነበረ : ስለ ሃይማኖትም በቀስት የተወጋ : በእሳት የቃጠለ : አካሉን ቆራርጠው የጣሉትና እግዚአብሔር ከሞት ያስነሳው ጻድቅና ሰማዕት ነው:: ከዚህ ሁሉ ነገር በኋላ ከነሥጋው ወደ ሰማይ ተነጥቆ ለ፲፬ [14] ዓመታት ቆይቷል:: ወደ ምድርም ተመልሶ ለ፵ [40] ዓመታት በሐዋርያነት ከ፹፭ ሺህ [85,000] በላይ አሕዛብን ወደ ሃይማኖት መልሷል:: ጌታም በስምህ የተማጸነውን እስከ ፯ [7] ትውልድ እምርልሃለሁ ብሎታል::"

❖ አባቶቻችን ደግሞ 'ስም አጠራሩ የከበረ ዜና ሕይወቱ ያማረ' ሲሉ ይጠሩታል::

❖ ከበረከቱ ያድለን::

[   ✞ የካቲት ፲፫ [ 13 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. ቅዱስ አውሳብዮስ ጻድቅ [ ጥዑመ ዜና ]
፪. ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት [ ልደቱ ]
፫. ቅዱስ ሰርግዮስ ሰማዕት
፬. ቅዱስ መፁን ቀሲስ
፭. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሰማዕት [ የቅ/ፋሲለደስ ልጅ ]
፮. አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ዻዻሳት
፯. አባ ክፍላ
፰. አባ ኅብስ

[   †  ወርኀዊ በዓላት   ]

፩. እግዚአብሔር አብ
፪. ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላዕክት
፫. ፺፱ [ 99 ] ኙ ነገደ መላዕክት
፬. ቅዱስ አስከናፍር
፭. ፲፫ [ 13ቱ ] ግኁሳን አባቶች
፮. ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ
፯. አቡነ ዘርዐ ቡሩክ

" እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ : እስከ አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ : ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ አይደለምና:: በእምነትና በትእግስትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን::" [ዕብ.፮፥፲-፲፫]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

20 Feb, 05:05
121
Post image

🕊

[  † እንኳን ለኢትዮዽያውያን ሰማዕታት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †

🕊 † ኢትዮዽያውያን ሰማዕታት †  🕊

† በ፲፱፻፳፱ [1929] ዓ/ም: የካቲት ፲፪ [12] ቀን ከ፴ ሺህ [30,000] በላይ ኢትዮዽያውያን አባቶች : እናቶች : ወጣቶችና ሕፃናት በሮማዊው የፋሽስት ጦር ደማቸው ፈሷል:: እነዚሕ ወገኖቻችን ደማቸው እንደ ጐርፍ አዲስ አበባ ላይ የፈሰሰው ስለ ሃገር ፍቅር ብቻ አልነበረም:: ስለ ቀናች ሃይማኖት ተዋሕዶ ጭምር ነው እንጂ::

† ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ግፃዌ ላይ ስማቸውን ጽፋ በቅዱስ ዳዊት መዝሙር እንዲህ ታስባቸዋለች::

"አቤቱ አሕዛብ ወደ ርስትህ ገቡ::
የቅድስናህንም መቅደስ አረከሱ::
ኢየሩሳሌምንም እንደ መደብ አደረጉአት::
የባሪያዎችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች አደረጉ::
የጻድቃንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት::
ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውሃ አፈሰሱ:: የሚቀብራቸውም አጡ::" [መዝ.፸፰፥፥፩]

† ሰማዕታቱን እናስባቸው !


🕊  †  ሶምሶን ረዓይታዊ  †  🕊

† እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን : ፳፪ [22] ቱን ሥነ ፍጥረትን ፈጥሮ አዳምን ገዢ አደረገው:: አክሎም በነፍስ ሕያው አድርጐ : በመንፈስ ቅዱስ አክብሮ : ነቢይና ካህን አድርጐ : ካንዲት ዕፀ በለስ በቀር በፍጥረት ሁሉ ላይ አሰለጠነው::

አባታችን አዳም ግን ስሕተት አግኝቶት ከገነት ወጣ:: መከራና ፍዳም አገኘው:: በሁዋላም ለ፻ [100] ዓመት አልቅሶ ንስሃ ገባ:: ጌታም ንስሃውን ተቀብሎ "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ተስፋ ድህነትን ሰጠው::

ስለዚህም ምክንያት ለ፭ ሺሀ ፭ መቶ [5,500] ዓመታት ትንቢት ሲነገር : ሱባኤ ወደ ታች ሲቆጠር : ምሳሌም ሲመሰል ኖረ:: ከደግ ፍጥረት አዳም እስከ ኖኅ ድረስ : የሴት ልጆች እግዚአብሔርን በንጽሕና ሁነው በደብር ቅዱስ አመለኩ::

ትንሽ ቆይተው ግን ስለተቀላቀሉ ከቃየን ልጆች ጋር በማየ ድምሳሴ ጠፉ:: በጻድቅ ሰው ኖኅ የተጀመረው ትውልድም እግዚአብሔርን ለመዘንጋት ጊዜ አልፈጀበትም:: ነገር ግን ከሴም ዘር ቅንና ጻድቅ ሰው አብርሃም ተገኘ::

ከእርሱም ይስሐቅ : ከዚያም ያዕቆብ [ደጋጉ] ተገኙ:: ያዕቆብም "እሥራኤል" ተብሎ: በልጆቹ "ሕዝበ እግዚአብሔር" የተባለ ነገድ ተመሠረተ:: በተስፋይቱ ምድር በከነዓን እንዳይኖሩም ርሃብ ምድረ ግብጽ አወረዳቸው::

በዚያም ለ፪ መቶ ፲፭ [215] ዓመታት በጭንቅ የባርነትን ሕይወትን አሳለፉ:: እግዚአብሔርም ስለ ወዳጁ አብርሃም ሲል እሥራኤልን አሰባቸው:: የዋሕና ጻድቅ ሰው ሙሴን አስነስቶ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አዳናቸው::

ይኸውም በጸናች እጅ: በበረታችም ክንድ: በ፱ መቅሰፍት: በ፲ኛ ሞተ በኩር: በ፲፩ኛ ስጥመት ግብጻውያንን አጥፍቶ ነው:: በየመንገዱም ጠላቶቻቸውን እየተበቀለላቸው ነው:: ከዚህ ዘመን ጀምሮም እሥራኤል በመሳፍንትና በካህናት የሚተዳደሩ ሆኑ::

አስቀድሞ ሙሴ በምስፍና: አሮን በክህነት መሯቸው:: ቀጥሎም በቅዱስ ሙሴ ኢያሱ: በአሮን አልዓዛር ተተኩ:: እንዲህ እንዲህ እያለም ከኃያል ሰው ሶምሶን ረዓይታዊ ደረሱ:: ይኸውም ከዓለም ፍጥረት ፬ ሺህ ፪ መቶ [4,200] ዓመታት በሁዋላ መሆኑ ነው::

በጊዜው እሥራኤል ጣዖትን እያመለኩ እግዚአብሔርን ስላሳዘኑት ለጠላቶቻቸው አሳልፎ ይሰጣቸው ነበር:: የአካባቢው መንግስታት እነ አሞን: አማሌቅ: ኢሎፍሊ ስንኩዋ ያኔ ዛሬም ቢሆን እንደምትመለከቱት ዶሮና ጥሬ ናቸው::

በጊዜውም የእሥራኤል ኃጢአት ስለ በዛ ኢሎፍላውያን [ፍልስጤማውያን] ፵ [40] ዓመት በባርነት ገዟቸው:: ንስሃ ሲገቡ ደግሞ ልጅ በማጣት ያዘኑ ማኑሄ እና ሚስቱ [እንትኩይ] : በቅዱስ ሚካኤል ተበሥረው ኃያሉን ሶምሶንን ወለዱላቸው::

እርሱም ናዝራዊ [ከእናቱ ማኅጸን ለጌታ የተለየ] ነበርና ፍልስጤማውያንን ቀጥቶ ወገኖቹን እስራኤልን ከባርነት : በአምላኩ ኃይል ታደገ:: ከኃይሉ ብዛት የተነሳም :-

- አንበሳን እንደ ጠቦት ይገድል [መሣ.፲፬፥፭]
- 300 ቀበሮዎችን አባሮ ይይዝ [መሣ.፲፭፥፫]
- በብርቱ ገመዶች ሲያስሩት እንደ ፈትል ይበጣጥሰው [መሣ.፲፭፥፲፬]
- በአህያ መንጋጋ ሽህ ሰው ይገድል [መሣ.፲፭፥፲፭]
- ጠባቂዎችን ከነ መቃናቸው ተሸክሞ ይወረውር ነበር:: [መሣ.፲፮፥፫]

ውሃ ሲጠማውም ከአህያ መንጋጋ ላይ ፈልቆለት ጠጥቷል:: [መሣ.፲፭፥፲፰] በፍጻሜው ግን ደሊላ በምትባል ሴት ተታልሎ ምሥጢሩን በመግለጡና ጸጉሩ በመላጨቱ ኃይሉን አጥቷል:: ጠላቶቹም ዐይኑን አውጥተው መዘባበቻ አድርገውታል::

በፍጻሜው ግን ኃይሉ እንዲመለስለት ፈጣሪውን ለምኖ : አሕዛብ ለጣኦት በዓል እንደተሰበሰቡ የአዳራሹን ምሰሶ አፍርሶ አጥፍቷቸው ዐርፏል:: [መሣ.፲፫፥፲፮] ቅዱስ ሶምሶን የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥላ [ምሳሌ] ነው::

† በዘመኑ ሁሉ ቅዱስ ሚካኤል ረድቶታልና በዚህች ቀን መታሠቢያው ይደረግለታል::

[  †  🕊  የካቲት ፲፪ [ 12 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. ፴ ሺህ [ 30,000 ] ሰማዕታተ ኢትዮዽያ [ሮማዊው ፋሽስት የገደላቸው]
፪. ቅዱስ ሶምሶን ረዓይታዊ [የእስራኤል መስፍን]
፫. ቅዱስ አባ ገላስዮስ ገዳማዊ
፬. ቅድስት ዶርቃስ

[    †   🕊 ወርሐዊ በዓላት    ]

፩. ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላዕክት
፪. ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
፫. ቅዱስ ድሜጥሮስ
፬. ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
፭. ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ [ሰማዕት]
፮. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
፯. አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
፰. ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ

† አምላከ አበው ቅዱሳን መዓዛ ቅድስናቸውን ያሳድርብን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

" ሶምሶንም :- 'ስለ ሁለቱ ዓይኖቼ ፍልስጥኤማውያንን አሁን እንድበቀል : እግዚአብሔር አምላክ ሆይ ! እባክህ አስበኝ ? አምላክ ሆይ ! . . . እባክህ አበርታኝ ?' ብሎ እግዚአብሔርን ጠራ:: . . . ሶምሶንም :- 'ከፍልስጤማውያን ጋር ልሙት' አለ:: ተጐንብሶም ምሰሶዎችን በሙሉ ኃይሉ ገፋ:: . . . በሞቱም የገደላቸው ሙታን በሕይወት ሳለ ከገደላቸው በዙ::" [መሣ.፲፮፥፳፰]

" እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ: ስለ ሶምሶንም: ስለ ዮፍታሔም: ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም: ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና:: እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ:: ጽድቅንም አደረጉ . . ." † [ዕብ.፲፩፥፴፪]

†  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  †
†  ወለወላዲቱ ድንግል   †
†  ወለመስቀሉ ከቡር አሜን   †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


               †         †         †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖                    🕊                     💖

18 Feb, 21:05
190
Post image

🕊

[  † እንኳን ለጻድቁ አባ አውሎግ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †

†   🕊  አባ አውሎግ አንበሳዊ  🕊  †

† አባ አውሎግ ማለት :-

- ከቀደመው ዘመን ጻድቃን አንዱ::
- እንደ ገዳማውያን ፍፁም ባሕታዊ::
- እንደ ሐዋርያት ብዙ ሃገራትን በስብከተ ወንጌል ያሳመኑ::
- በግብፅና በሶርያ በርሃዎች ለ፺ [90] ዓመታት የተጋደሉ ጻድቅና ሐዋርያ ሲሆኑ የሚጉዋዙበትና የሚታዘዛቸው ግሩም አንበሳ ነበር::
- በዚህም አባ አውሎግ "አንበሳዊ" ስትል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትጠራቸዋለች::

አባ አውሎግ ከሚታወቁበት አገልግሎት አንዱ ስብከተ ወንጌል ነው:: ምንም እንኩዋ ገዳማዊ ቅዱስ ቢሆኑም ያላመኑትን ለማሳመን : ያመኑትንም ለማጽናት ተጋድለዋል::

እግዚአብሔር በሰጣቸው አናብስት በአንዱ ላይ ተጭነው [መዝ.፺ (90) : በሌላኛው ላይ እቃቸውን አስቀምጠው በየአኅጉራቱ ከመምህራቸው ቅዱስ አውሎጊን ጋር ይዘዋወሩም ነበር:: የጌታ ቸርነት ሆኖም አናብስቱ የቅዱሳኑን ፈቃድ ሳይነገራቸው ያውቁ ነበር::

ሲርባቸውም ተግተው ይመግቧቸው ነበር:: እንዲያውም አንዴ ቅዱሳኑ እንደራባቸው አንዱ አንበሳ ሲያውቅ ከበርሐ ወደ ገበያ መንገድ ወጥቶ ተመለከተ:: በአህያ ላይ ልጁንና ስንቁን [ዳቦ] ጭኖ የሚሔድ ሽማግሌ ነበርና ዳቦውን አንስቶ ወስዶ ለእነ አባ አውሎግ ሰጣቸው::

ከድንጋጤ የተነሳም ሕጻኑ ሙቶ ነበርና ሽማግሌ አባቱ አዘነ:: አንበሳው ግን ሕጻኑንም ወደ ቅዱሳኑ ወስዶ አስረከበ:: ቅዱሳኑም ከሕብስቱ በመጠናቸው በልተው ቢባርኩት እንዳልተበላ ሆነ:: ሕጻኑንም ከሞት በጸሎታቸው አስነስተው ለአንበሳው ሰጥተውታል::

አንበሳውም ስንቁንና ልጁን ለአረጋዊው ሰጥቶት በደስታ ወደ ሃገሩ ተመልሷል:: ቅዱስ አባ አውሎግና መምህሩ አውሎጊን ከ፺ [90] ዓመታት በላይ በዘለቀ ተጋድሏቸው አጋንንትን ያሳፍሩ ዘንድ : ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ንጹሕ መስዋዕት ይሆኑለት ዘንድ በትጋት ኑረዋል::

¤ ብዙ ተአምራትን ሠርተው ፈጣሪያቸውን አክብረዋል::
¤ እንደ ሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ ባሕር ከፍለዋል::
¤ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙት አንስተዋል:: ድውያንን ፈውሰዋል::
¤ እንደ ቅዱስ ዳንኤል አናብስትን ገዝተዋል::
¤ ይህች ቀን ዕለተ ዕረፍታቸው ናት::

†  🕊  ቅዱስ በላትያኖስ  🕊  †

††† ይህ ቅዱስ ሐዋርያዊ ዻዻስ የቀድሞዋ ሮም ሊቀ ዻዻሳት ሲሆን ቸር : ትጉህና በጐ እረኛ ነበር:: መናፍቃንን ሲያርም : ምዕመናንን ሲመክር : ስለ መንጋው እንቅልፍ አጥቶ ኑሯል:: በፍጻሜውም በዚህች ቀን የሮም ንጉሥ ለ፩ (1) ዓመት አሰቃይቶ ገድሎታል:: ዕሴተ ኖሎትን [የእረኝነት ዋጋንም] ከጌታችን ተቀብሏል::

† አምላከ አበው ቅዱሳን በመጽናታቸው ያጽናን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

[  † የካቲት ፲፩ [ 11 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. አባ አውሎግ አንበሳዊ
፪. አባ አውሎጊን ጻድቅ [የአባ አውሎግ መምሕር]
፫. አባ በትራ [የጻድቁ አባ ስልዋኖስ ደቀ መዝሙር]
፬. አባ በላትያኖስ ሰማዕት [የሮም ሊቀ ዻዻሳት የነበረ]
፭. አባ አብርሃም ኤዺስ ቆዾስ
፮. አባ መቃቢስ
፯. አባ ኮንቲ

[    † ወርሐዊ በዓላት    ]

፩. ቅዱስ ያሬድ ካህን
፪. ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት
፫. ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
፬. ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና
፭. አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ

"በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምንም ከኁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ ነው::" † [ኤፌ.፩፥፲፱ (1:19)

†  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  †
†  ወለወላዲቱ ድንግል   †
†  ወለመስቀሉ ከቡር አሜን   †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


†                       †                       †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
💖                    🕊                     💖

17 Feb, 20:43
229