መልህቅ @zanchor Channel on Telegram

መልህቅ

@zanchor


"ይህም ተስፋ እንደነፍስ መልሕቅ አለን!" ዕብ 6:19

▣ በግል ሊያገኙኝ ከፈለጉ ➾ @agyap101
▣ የቻነሉ ግሩፕ➾ @LOVE_Of_WISDOM

Tiktok :

https://www.tiktok.com/@zanchorr

ቻነሉና ግሩፑ የሚመሩባቸውን የአዲስኪዳን መርሆች ከቀጣዮቹ ክፍሎች ማግኘት ትችላላችሁ።

Titus 2 : 2, 6 - 8
1 Peter 3: 8 - 12
James 3: 13 - 18

መልህቅ (Amharic)

መልህቅ - እናቴን፣ ህላዊ እና አስትዮይስ መዝገብ ላይ መነሻን አስመልሷል። ይህም ተስፋ እንደነፍስ መልሕቅ አለን! በእጅጉ የሚያሳይ ታሪክ ፋን ፖርኖውማን ዘርፍ መልእክተኞች እንዳበረታቸው ዋና ቪንቷስ ሚድያ እሳት አካሂዳቸው። ከእናቴን ሚድያዎች እንዳልነበሩባችሁ ስሜትን መልእክት ጥሰዉን። እሳት አካሂዳቸው።

መልህቅ

13 Feb, 08:29


'አትናቲዎስ vs እዩ ጩፋ'

የትላንትናው የቃሌና የልደተቃል ውይይት እውነት ለመናገር ምንም ጥርጥር በሌለው መልኩ በቃሌ አቸናፊነት በድል የተጠናቀቀ ነው። 😁 ይህ ከዛ ሳይድም ያለ ሚዛናዊ የሆነ ሰው ድምዳሜ እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ! It was just a Banger. 💥

እንደምታውቁት ብዙ ጊዜ ውይይቶች ሲደረጉ ሰፋ ያለ ሪቪው እሰጥ ነበር። ይሄ ግን ምንም አያስፈልገውም። ከዛ ሳይድ ያለውን ምን ያህል ድኩም ሙግትና ከታሪክ የተጣሉ መሆን ተመልክተንበታል።

እራሱ ቃሌ እንዳለው ውይይቱ 'አትናቲዎስ vs እዩ ጩፋ' ነበር ብለን ብንቋጨው በቂ ነው። 💀😅

መልህቅ

11 Feb, 17:43


ላይቭ ገብተናል ተቀላቀሉ!

https://t.me/LOVE_Of_WISDOM?videochat=8b186a5df30d922863

መልህቅ

11 Feb, 04:32


ጋይስ እንዴት እየከረማችሁ ነው ? ትንሽ የተጠፋፋን አይመስላችሁም ? 😁

መጨረሻ ላይ በለቀቅኩት ቪድዮ ላይ በተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄ ዙሪያ ዛሬ ማታ 2:30 ላይ ከአንድ ጥሩ ኦርቶዶክስ ወንድም ጋር እዚሁ ግሩፓችን ውስጥ ውይይት (Open-Discussion) ይኖረናል።

ምናልባት ከቻልን ሌሎች ወንድሞችም ተጨምረው የሆነ ያህል ጥያቄዎቻችሁን ልንቀበልም እንችላለን።

ማታ እንገናኝ! መልካም ቀን!

መልህቅ

09 Feb, 07:58


ከጥምቀት በኋላ 3ተኛ እሁድ
የወንጌልና የመልዕክት ክፍል
ኢየሱስ እምነታችንን ያፀናል!


ማቴዎስ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ከተራራም በወረደ ጊዜ ብዙ ሕዝብ ተከተሉት።
² እነሆም፥ ለምጻም ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ ብትወድስ ልታነጻኝ ትችላለህ እያለ ሰገደለት።
³ እጁንም ዘርግቶ ዳሰሰውና፦ እወዳለሁ፥ ንጻ አለው። ወዲያውም ለምጹ ነጻ።
⁴ ኢየሱስም፦ ለማንም እንዳትናገር ተጠንቀቅ፥ ነገር ግን ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ፥ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ሙሴ ያዘዘውን መባ አቅርብ አለው።
⁵ ወደ ቅፍርናሆምም በገባ ጊዜ የመቶ አለቃ ወደ እርሱ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥
⁶ ብላቴናዬ ሽባ ሆኖ እጅግ እየተሣቀየ በቤት ተኝቶአል ብሎ ለመነው።
⁷ ኢየሱስም፦ እኔ መጥቼ እፈውሰዋለሁ አለው።
⁸ የመቶ አለቃውም መልሶ፦ ጌታ ሆይ፥ በቤቴ ጣራ ከታች ልትገባ አይገባኝም፤ ነገር ግን ቃል ብቻ ተናገር፥ ብላቴናዬም ይፈወሳል።
⁹ እኔ ደግሞ ለሌሎች ተገዥ ነኝና፥ ከእኔም በታች ጭፍራ አለኝ፤ አንዱንም፦ ሂድ ብለው ይሄዳል፥ ሌላውንም፦ ና ብለው ይመጣል፥ ባሪያዬንም፦ ይህን አድርግ ብለው ያደርጋል አለው።
¹⁰ ኢየሱስም ሰምቶ ተደነቀና ለተከተሉት እንዲህ አለ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ በእስራኤል እንኳ እንዲህ ያለ ትልቅ እምነት አላገኘሁም።
¹¹ እላችኋለሁም፥ ብዙዎች ከምሥራቅና ከምዕራብ ይመጣሉ ከአብርሃምና ከይስሐቅ ከያዕቆብም ጋር በመንግሥተ ሰማያት ይቀመጣሉ፤
¹² የመንግሥት ልጆች ግን በውጭ ወደ አለው ጨለማ ይጣላሉ፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።
¹³ ኢየሱስም ለመቶ አለቃ፦ ሂድና እንዳመንህ ይሁንልህ አለው። ብላቴናውም በዚያች ሰዓት ተፈወሰ።


ገላትያ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁹ እኔ ለእግዚአብሔር ሕያው ሆኜ እኖር ዘንድ በሕግ በኩል ለሕግ ሞቼ ነበርና።
²⁰ ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።
²¹ የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።

መልህቅ

07 Feb, 10:22


በነገራቹ ላይ በዚህ በለቀቅኩት ቪድዮ መጀመሪያ የምታዩት ጥያቄ ብቻውን ራሱ ስህተቶች አሉበት። እንደምታስታውሱት ጥያቄው ከቃሌ ጋር በነበረው ውይይት የጠየቀው ነው።

ጥያቄው እንዲህ ነው :

መፅሐፈ ጥበብ መፅሐፍ ቅዱስ ላለመሆኑ ሊሳሳት የማይችል ማስረጃ አለህ ?

መልስ :

በጥያቄው አሲውም ያደረገው ሊሳሳት የማይችል ማስረጃ ግዴታ ነው የሚለው Flawed Assumption ነው። ይህን አሲውም ካላደረገ የለም ለሚለው መልስ አንዳች አይጠቅመውም የኛን ለመውቀስ የራሱን ደግሞ ለማስረገጥ ሊጠቀምበት አይችልም። ማን ነው ግዴታ ያስፈልጋል ያለው ?!

ሊሳሳት የማይችልም ይሁን ሊሳሳት የሚችል አንድን አካል እውነት መሆኑን ለማወቅና ለመቀበል የሚያስፈልገው መስፈርት በቂ ማስረጃና መረጃ (Sufficient Evidence) ነው።

በሰራሁት ቪድዮ ላይ ለተሰጡትና ለሚሰጡት ምላሾች መልስ መስጠቴ አይቀርምና ጠብቁ!

@zanchor
@zanchor

መልህቅ

05 Feb, 08:30


በአዲስ ቪድዮ ከተፍ ብለናል 🙌

ኦርቶዶክስ ወንድሞቻችን ቅዱሳት መፅሐፍትን ልትሳሳት በማትችለዋ (ወይም Infallible በሆነችዋ) ቤተክርስቲያን አውቀናል ይሉናል። ለጥቀውም ደግሞ እናንተ ግን ቤተክስቲያን ልትሳሳት ትችላለች ስለምትሉ ልታውቁአቸው አትችሉም ምክንያቱም ሊሳሳት የሚችል ነገር ሊሳሳት ለማይችል ነገር ማስረጃ ሊሆን አይችልምና ብለው ይሉናል።

ይህን የሙግት አካሄድ አንድ እርምጃ ገፋ እናድረገውና ግልፅና ቀጥተኛ ጥያቄ እናቅርብላቹ።

46 ጊዜ ኮፒ ሊንክ ፣ ሼር ፣ ላይክ ፣ ኮመንት ምናምንንንን ማድረግ እንዳይረሳ! 😁

https://www.tiktok.com/@abesus09/video/7467845732976856326

መልህቅ

02 Feb, 08:21


ከጥምቀት በኋላ 2ኛ እሁድ
የወንጌልና የመልእክት ንባባት
ኢየሱስ ኑሮአችንን ይቀድሳል!


ማርቆስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ደግሞም በባሕር አጠገብ ወጣ፤ ሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ መጡና አስተማራቸው።
¹⁴ ሲያልፍም በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረውን የእልፍዮስን ልጅ ሌዊን አየና፦ ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው።
¹⁵ በቤቱም በማዕድ ተቀምጦ ሳለ፥ ብዙ ቀራጮችና ኃጢአተኞች ከኢየሱስና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጡ፤ ብዙ ነበሩ ይከተሉትም ነበር።
¹⁶ ጻፎችና ፈሪሳውያንም ከቀራጮችና ከኃጢአተኞች ጋር ሲበላ አይተው ለደቀ መዛሙርቱ፦ ከቀራጮችና ከኃጢአተኞች ጋር የሚበላና የሚጠጣ ስለ ምንድር ነው? አሉ።
¹⁷ ኢየሱስም ሰምቶ፦ ሕመምተኞች እንጂ ብርቱዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም ኃጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም አላቸው።

ሮሜ 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁹ ፍቅራችሁ ያለ ግብዝነት ይሁን። ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ፤
¹⁰ በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤
¹¹ ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ፤
¹² በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ፤
¹³ ቅዱሳንን በሚያስፈልጋቸው እርዱ፤ እንግዶችን ለመቀበል ትጉ።
¹⁴ የሚያሳድዱአችሁን መርቁ፥ መርቁ እንጂ አትርገሙ።
¹⁵ ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ።
¹⁶ እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ፤ የትዕቢትን ነገር አታስቡ፥ ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ። ልባሞች የሆናችሁ አይምሰላችሁ።
¹⁷ ለማንም ስለ ክፉ ፈንታ ክፉን አትመልሱ፤ በሰው ሁሉ ፊት መልካም የሆነውን አስቡ።
¹⁸ ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ።
¹⁹ ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና።
²⁰ ጠላትህ ግን ቢራብ አብላው፤ ቢጠማ አጠጣው፤ ይህን በማድረግህ በራሱ ላይ የእሳት ፍም ትከምራለህና።
²¹ ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ።

መልህቅ

31 Jan, 08:43


ፕሮማክስ ከጥንቷ ቤተክርስቲያን የራቀ ነውን? 😁😁 እስቲ እየገባችሁ ቪዲዮዋን አየት አድርጓት https://vm.tiktok.com/ZMk4GDrbe/

መልህቅ

31 Jan, 08:13


ቲዎሎጂ ያደርቃል ሲባል ሰምታቹ ታውቃላቹአ ? 😁 ከሚሉትስ መሀከል ናቹህ ? 🙈

በነገራቹ ላይ በጥንቃቄ ካልተያዘና ባላንስ ለማድረግ ካልተሞከረ በቀር እውነት ነው ያደርቃል ፤ ችግር ያመጣል። ብዙ ጊዜ ይህ ሩም የሚያተኩረው እቅበተ-እምነት ላይ ነውና ይህንን ማስታወስ ያለብኝ እንደሆነ እየተሰማኝ ነው።

ሁለት ጥጎች አሉ! ጨርሶ ስነመለኮት ጠል መሆንና ሙሉ ለሙሉ ዲቮሽናል ህይወት ላይ ብቻ ማተኮር (ምንምኳ ምንም አይነት ዲቮሽን የሆነ አይነት ቲዎሎጂ ላይ ቢመሰረትም) ፤ በተቃራኒው ደግሞ በቲዎሎጂው ጨርሶ ተወስዶ በሳምንት አራት አምስት መፅሐፍ እየጨረሱ ለ30 ደቂቃኳ የምትሆን የእለት የፀሎት ጊዜን ማጣት።

ሁለቱም ትክክል አይደሉም። በተለይ እንደወጣት ለእኛ ደግሞ ለሁለቱም ምንም ልንሰጠው የምንችለው ኤክስኪውዝ የለንምና በጣም ትክክል አይደሉም።

በጣም ማንበብ አለብን!
በጣም መፀለይ አለብን!
በጣም ህብረት ማድረግ አለብን!

እንዲህ ለማስኬድ የሚከብዳቹ ከሆነና ንባቡ ዲቮሾናቹን የሚጋፋቹ ከሆነ ቀንሱት!

የሆነ ቦታ እንዲህ ብዬ ፅፌ ነበር :

➾ ከመመናፈስ የራቀ ቲዎሎጂ ያደርቃል!
➾ ከቲዎሎጂ የራቀ መመናፈስ ያስታል ከዛም አልፎ ያመነፍቃል!

ስለዚህ ጌታ ከሁለቱም አዳቅሎ አሪፍ ባላንሱን የጠበቀ መናፍስት ቲዎሎጂያን ያድርገን! 😁 ይብዛም ይነስ በቀን ውስጥ ጌታ ፊት ከመገኘት አንጉደል።

____

መመናፈስ ተብሎ የገባው ቃል ትርጉሙ የዲቮሽን ህይወት በአራድኛ አፍ ተገልብጦ መሆኑን ልብ ይሏል።

መልህቅ

28 Jan, 11:30


ብዙ ልጆች ብዙ ቢሉበትም እኔም ልጨመርና ልበል ...

መድሎተ ፅድቅ ማለት እቅበተ እምነታዊ መፅሐፍ እንዴት መፃፍ እንደሌለበት ሰቅሎ ያሳየን መፅሐፍ ነው።

ዲያቆን ያረጋልን በጣም የምወዳቸውና የማከብራቸው የቤተ/ክኒቷ አገልጋይ ቢሆኑም እዚህ ላይ ግን ምን ሆነው እንደሆነ አላውቅም ፍፁም የማይሰሩና የሚያሳፍሩ ሙግቶችን አቅርበው ይኸው ላንመለስ ፕሮማክስ ሆነን እንድንቀር አድርገውናል።

ሚገርማቹ እኔ እንደውም አስተምህሯችን ምን ማለት እንዳልሆነ ለሰው ለማሳየት ስፈልግ በምሳሌነት የምጠቅሰው መፅሐፍ ነው። 😅

ይታያቹስኪ! ኮሜንታሪ አላቸው ከሚል ፕሬሚስ ተነስቶ ሶላ-ስክሪፕቱራ ስህተት ነው ተብሎ የተሞገተበት መፅሐፍኮ ነው። 💀🙈 ይህ ለአብነት የተጠቀሰ ነው! ተከታዮቹ ደግሞ እሱን ይዘው መተው እኛን ያዝጉናል! 😅

እሱን መፅሐፍ አንብበህ ኦርቶዶክስ አደረገኝ አልያ ደግሞ ፕሮማክሱን እጨምቃለሁ ብለህ የምታስብ ከሆነ እውነት እልሀለው ፀሀፊው የፈጠረልህን ፕሮቴስታንቲዝምንጂ በታሪክ የነበረውን ፕሮቴስታንት ጨርሰህ አታውቀውም። ስለዚህ መለስ ብለህ ራስህን ፈትሽ! ደህና ነገር ከፈለግህ ደግሞ ናና እኔን ጠይቀኝ! ፕሮቴስታንቱን አሪፍ አድርገው የሚሞግቱና የሚጨምቁ የማከብራቸውን ፀዴ ፀዴ የካቶሊክ ሊቃውንት አሳቅፍሀለው!

ምናልባት የዚህ አገልጋይ ሙግቶች ምን ያህል ድክም የሚያረጉ እንደሆኑ ይበልጥ ለመረዳት ቀጣዩን ሊንክ ተጠቀሙና እስኪ የሚጠይቃቸውን ጥያቄዎች ተመልከቱ! 😁

https://t.me/ZANCHOR/753

መልህቅ

27 Jan, 21:07


ትንሹን የሰው ፍቅር አይኔ አይቶ ሲደነቅ
የፍቅር መጀመሪያው አንተማ እንዴት ትልቅ
ጥቂቱን የሰው መውደድ አይኔ አይቶ ሲደነቅ
የመውደድ ጅማሬ አንተማ እንዴት ትልቅ

ከባህር ይጠልቃል መውደድህ ጥልቀቱ
ራስህን አሳንሰህ ገብተሀል ከእየቤቱ
ከባህር ይጠልቃል መውደድህ ጥልቀቱ
በኢየሱስ በኩል መጥተህ ተገኘህ በእየቤቱ

አቤት ፍቅርህ አቤት ፍቅርህ ..
አቤት መውደድህ አቤት መውደድህ ..
አቤት ትዕግስትህ አቤት ትዕግስትህ ..

🙏🙏🙌

https://youtu.be/0-TO7poisMo?si=TfM6TqSEZUx0UwKS

መልህቅ

26 Jan, 07:29


ከጥምቀት በኋላ 1ኛ እሁድ
የወንጌልና የመልእክት ንባባት


ማቴዎስ 24
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤
¹² ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች።
¹³ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።
¹⁴ ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።


2ኛ ቆሮ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ ስለዚህ እኛ ከአሁን ጀምሮ ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም።
¹⁷ ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።
¹⁸ ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤
¹⁹ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ።
²⁰ እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን።
²¹ እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።

መልህቅ

21 Jan, 13:53


"... Salmeron was unwilling to be content with these five. In Comm. (vol. 15, p. 25), he attributes twenty discrepant positions on justication to Luther. However, our discussion will be with Bellarmine, to whom we respond as follows. He cannot attribute the third and fifth of these positions to us for, as far as the error of Osiander is concerned, Osiander was crushed and put to bed by the writings of our theologians before Bellarmine moved his hand to writing."

".... ሳልሜሮን በእነዚህ በአምስቱ ረክቶ ለመስማማት አልፈቀደም። በመፅሐፉም ሉተር በፅድቅ አስተምህሮው ላይ 20 እርስ በእርሳቸው የማይስማሙ አቋሞች እንዳሉት ይናገራል። ነገር ግን አሁን የእኛ ውይይት ከቤላርሚን ጋር ነው። እንደዚህም እንመልስለታለን! ሶስተኛውንና አምስተኛውን ነጥብ የእኛ አቋም ሊያረጋቸው አይችልም። በእነሱ ላይ ኦሲያንደር የተሳሳተውን ስህተት በተመለከተ ቤላርሚንኳ የክታብ ብዕሩን ሳያነሳ የስነመለኮት ሊቃውንቶቻችን በፅሁፎቻቸው ኦሲያንደርን ሰባብረው አልጋ ላይ አጋድመውታል!"

Gerhard, On Justification


😅😅

መልህቅ

17 Jan, 11:29


የሰሞኑን የበጋሻው ትምህርት ላይ ግራ ለተጋባችሁ

በመጀመሪያ ይህን ሰው በዶክትሪናል ጉዳዮች ላይ አትስሙት ብዬ ከዚህ በፊት መክሬ ነበር። ምንምኳ ይቅርታ ቢጠይቅም ከዚህ በፊትም በስላሴ ላይ እጅግ ከባድ ስህተት ሲናገር ስለነበር። ይህም ከእርሱ ጋር ምንም ፐርሰናል ነገር ኖሮኝ ሳይሆን ለእናንተ በሚጠንቀቅ ልብ የተናገርኩት ነው።

እንዴት ከእግዚአብሄር ጋር ታረቅን የሚለውን ጥያቄ መፅሐፍ ቅዱስ ሲመልስልን የተለያዩ ማብራሪያዎችን (Theories of Atonements) ይሰጠናል። ከእነዛ መሀከል መሀከለኛውና ዋነኛው ይህ የምትካዊ ቅጣት ማብራሪያ (Penal Substitutionary Atonement (PSA)) ነው። ብዙ ሰዎች በዚህ አስተምህሮ ላይ እጅግ ብዙ ስሁት መረዳት አላቸው።

በአጭሩ ሲቀመጥ PSA እንዲህ የሚል ማብራሪያ ነው :

እኛ ሰዎች ሀጥያተኞች በመሆናችን በእግዜር ፍርድ ፊት ኩነኔ አለብንና ስለዚህም የሞት ፍርድ (ቅጣት) የተገባን ነን። ኢየሱስ ክርስቶስ የእኛን ሀጥያት በመሸከም ለእኛ ይገባ የነበረውን ፍርድ (ቅጣት) ተቀብሎልናል።

PSAን ለመቀበል ይህ በቂ ኮንዲሽኑ ነው። ትልቁ ቁምነገር በፍርድቤትና በሕግ አውድ ውስጥ የሚተረጎም መሆኑ ነው። ይህንን በቀላሉ ለመረዳት የብሉይኪዳን የመስዋእትን ስርአት መመልከት ከበቂ በላይ ነው። ሀጥያተኛው በሀጥያቱ ምክንያት የሞት ፍርድ ይገባዋል። ነገር ግን በእርሱ ፈንታ የሚሰዋው በግ ይዞ ይመጣና እጁንም ጭኖበት ይናዘዛል ከዛ የሰውየው የተገባውን ፍርድ በጉ በመታረድና በመሞት ይቀበላል። ካህኑም ደሙን ወደ ቅድስት ይዞ በመግባት ይረጫል። ሰውየውም ይቅር ተብሎ (ፀድቆ) በነፃነት ይመለሳል! That is all you need to affirm PSA!

'ጌተሰማኔ ላይ ተንበርክኮ ፅዋውን ሲጠጣ ጠፋበት' ፤ 'ከአባቱ አይን ጠፋ' ፤ 'ሙሉ ለሙሉ ሀጥያተኛ' ፤ 'ተኩሶ መታው ልጁ እስኪጠፋ ድረስ' ...

እነዚህ ሁሉ አገላለፆች እጅግ ስህተት ያለባቸውና መፅሐፍ ቅዱሳዊም ያልሆኑ ናቸው። ምናልባት ትክክል የሆነበትን ነጥቦች ከስህተቱ ለይተን ካወጣንም በጣም ሰነጣጥቅን መሆን አለበት። ጉዳዩን ጠንቅቆ የማያውቅ በበዛበት በጉባኤ ደረጃ እየተሰበከ ከመሆኑ አንፃር ደግሞ ስህተቱ ይከፋል ብዬ አስባለሁ።

ይህንን አገላለፆች ከPSA ጋር አንድ አድርገው የሚወቅሱና የባሰባቸው ደግሞ ይህ የጠቅላላ የፕሮቴስታንቱ አስተምህሮ (ወይም አገላለፅ) እንደሆነ አድርገው ለገዛ ጥቅማቸው ሲሉ ህዝቡን የሚያስቱ አንዳንዶችን ደግሞ እያየሁ ነው። አስተምህሮውን ጠንቅቀው የማያውቁትን ይህ ምን ያህል እንደሚጎዳ ሳውቅ አዝናለሁ።

ይህ የ PSA አስተምህሮ በስላሴ ውስጥ የፍቃድንም ሆነ የማንነት መለያየትንና መነጣጠልን በጭራሽ የሚሰብክ አይደለም። ይህ የምንፀየፈው ነውና ከእኛ ይራቅ! የስላሴ ግንኙነት በጭራሽ በሆነ ነጥብ ላይ ሊቋረጥ የሚችል አይደለም።

ሲቀጥል ደግሞ አብን እንደቀጪ ወልድን እንደተቀጪ ማድረግም የPSA Necessary Condition አይደለም። እንደውም ይህንን አገላለፅ የሚቃወሙ ሊቃውንትም አሉ። ምናልባትም እርሱን አገላለፅ ከተጠቀምንም መፅሐፍቅዱስ አብንና እኛን በሁለት ጎራ ያሉ እንደሚታረቁ አካላት ወልድን እንደመሀከለኛ አስታራቂ አካል አድርጎ ከሚገልፀው አገላለፁ የሚመዘዝና በዚህ አጥር ውስጥ ብቻ የሚብራራ መሆኑን ልብ ይሏል። ይህ ግን አንዱ የተሰጠን መገለጫው ነው እየተባለንጂ ብቸኛውና ሙሉ ማብራሪያው ነው እየተባለ አለመሆኑን መረዳት አስፈላጊ ነው። በሌላ አቅጣጫ ወልድ ራሱ የታመፀበት አካል ነውና ፤ ከራሱም ጋር አስታርቆናልና! በተረፈ ብዙ ሰዎች በስህተት ለመረዳት ቅርብ ከመሆናቸው አንፃር ይህንን አገላለፅ ጨርሶ አለመጠቀሙን ወይም ቦታ መርጦ መጠቀሙን እመክራለሁ። 


ምናልባት በPSA ውስጥ ልንረዳቸው የሚገቡን ተርሞች :

▣ የእግዚአብሄር ቁጣ (the Wrath of God) :

በሀጥያተኛው ላይ ያለን የእግዚአብሄርን ፍርድ የሚወክል ነው። ምንም አይነት Emotional Baggage አትጨምሩበት።

▣ ቅጣት (Penal Punishment) :

በሕግ መሰረት ላይ የቆመ ለጥፋት የሚሰጥ ተመጣጣኝ ክፍያን ይመለከታል። A legal infliction of God's justice for a capital offense.


@zaNchor
@zaNchor

መልህቅ

15 Jan, 10:50


..

የትላንቱ ላይ ወንድማችን አክሊል ቀጥሎ ምላሽ ቢጤ ተሰቶ አየሁና ልሂድበትስኪ ..

እሱ :

"Infallible canon አለ ብለን መች ተናገርን..?? እንደ አካባቢው ሁኔታ እና እንደ አቀባበላቸው አብያተ ክርስቲያናቱ እነርሱ ጋር የደረሱትን መጽሐፍት ይይዛሉ.. ስለዚህም የቀኖና ጉዳይ ልክ እንደ ሃይማኖት ዶግማ ምናምን አይደለም.. ይሄ ከጥንትም አለ በአይሁዳውያንም ዘንድ አለ.. አንዳንድ የአይሁድ ማህበረሰብ የሚቀበሉት የመጽሐፍት ብዛት ከሌላኛው የአይሁድ ማህበረሰብ ይለያይ ነበር ጥንት ላይ.. ይሄንን በብዙ የአይሁድና የፕሮቴስታንት እንዲሁም የዘርፉ ባለሙያዎች ማሳየት ይቻላል.. ከዚህ በፊትም የተወሰነ አሳይቼ ነበር..''

እኛ :

➾ አሀ Infallible Canon የላችሁም ? ስለዚህ Fallible list(Canon) of Infallible Books ነው ያለን እያልከን ነው ? ና ግባለት! 👊😅
➾ እንደ ሀይማኖት ወይም እንደ ዶግማ ምናምን ካይደለ ቤተ/ክኗ ሊሳሳት በማይችል ስልጣኗ አልሰጠችህም ማለት ነው ?!
➾ የአይሁድ ማህበረሰብ እንደማህበረሰብ የሚቀበሉት ይለያይ ነበር የሚልውን ከየት አመጣኸው ? እንደለመደብህ ፈሪሳዊና ሰዱቃዊ ምናምን ብለህ ልትሰክስ ነው ? አያዋጣም እሱ!

እሱ :

"ራሱ እጅህ ላይ ያለው የዮሐንስ ወንጌል infallible መሆኑን infallible በሆነ ደረጃ ታውቃለህ ወይ ነው..?? ማለትም ፍጹም በማትሳሳትበት ደረጃ እርግጠኛ ነህ..?? እኔ አዎ ነኝ ምክንያቱም ከቸርች ነው የተቀበልኩት.. ሌላው ግን አንዱ ጋር የሆነ መጽሐፍ ኖሮ ሌላው ጋር ድንገት ባይኖር ራሱ አያሳስበንም ከላይ ባልኩት ምክንያት.."

እኛ :

➾ ቤተ/ክንህ ሊሳሳት በማይችል ስልጣኗ ስትሰጥህ አይደልንዴ ኢንፋለብል በሆነ ደረጃ የምታውቀው ? ራስሁ ነህ ይህንንም ክራይቴሪያ የሰጠኸንኮ! ወይስ ሀሳብ ቀይረህ አያይ ሊሳሳት በሚችል ስልጣኗ ብትሰጠኝም ሊሳሳት የማይችል እርግጠኝነት አለኝ ነው እያልከን ያለኸው ? እንዲያ ከሆነ አንተ በርቀት ያለኸው ፕሮማክስ ና በድጋሜ ያዝ! 👊 ዌልካም ብለንሀል ! እርሱን አይደልንዴ የምንፈልገው!

➾ ግን የባሰው ነው ይሄ! Fallible የሆነች ማይንድ ይዘህ እንዴት Infallible የሆነ እርግጠኝኘት ኖረህ ባክህ ? 😝 በህይወት መኖርህን ራሱ Infallibly እንደማታውቅ ብነግርህስ አንበሳው!

እሱ :

"ሲቀጥል ቤተ ክርስቲያን infallible ናት ያልነው ሃይማኖት ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ልትሳሳት አትችልምና ነው.. ይሄንን በተደጋጋሚ ተናገርን እኮ😁😁"

እኛ :

እንዲያ ከሆነ የራስህን ክራይቴሪያ ኮንሲስተንት ሁነህ ተቀበልና ቀኖናውን Infallibly አልነገረችንም ስለዚህም Infallible እርግጠኝነት የለኝም ብለህ እረፈውኮ ነው እያልንህ ያለነው! You realy want to have your cake and eat it too. ችግሩ It doesn't work that way!

እሱ :

"ከኢትዮጵያ ጋር በተያያዘ ለተነሳው.. autocephalous church ከሆነች ገና 60 አመቷ ነው ከዛ አንጻር የመጽሐፍትን ጉዳይ በደንብ በራሷ ትውፊት መሠረት በጉባኤ ደረጃ ቀኖናውን ማወጅ ይኖርባታል ነው.. በዘመናት ውስጥ ይህንን ስላላደረገች የሷን መጠበቅ ይኖርብናል እስከዛው ግን ይኸው ባለው እንቀጥላለን.. ልክ እንደ ጥንቱ ማለት ነው"

እኛ :

ቆይ ግን ቁጥር 2 ላይ ከቸርች ነው የተቀበልኩት ፤ ሁላ ሊሳሳት በማይችል መልኩ እርግጠኛ ነኝ ብለኸን አልነበርንዴ? ምነው ታድያ ቁጥር 4 ላይ ገና ቀኖናውን ማወጅ ይኖርባታል ፤ ገና መጠበቅ ይኖርብናል.. ብለህ አፈረስከው ? ጭራሽ በአዋጅ ያልተቀበልከውን ነው እንደዛ እርግጠኛ የሆንከው ?🙈

ምናልባት ግን የተወሰኑትን ወስና አውጃ ሰታኛለች ፤ የተወሰኑትን ግን ገና ወስና አልሰጠችኝም ከሆነ ይህንን ክፍፍል በራሱ ከየት አመጣህ ? ውሳኔ አልተላለፈላቸውም ያልካቸውን መፅሐፍት ሳታካትት እነዚህ እነዚህን ሰጥቼሀለው ብላ የወነችበት ቦታ አለ ? ምንአስለፋቹ በአጭሩ የለም!

ብቻ ግን በቃ አውጃ እስክትሰጥህ ድረስ ሰታኛለች እኔም ተቀብያለሁ ፤ ሊሳሳት በማይችል መልኩ እርግጠኛ ነኝ ምናምን እያልክ አትሰክሰን!

ኧረ እሱም ብቻ አይደለም! ቆይ እሺ ነገ ወስና ሰጠችህ እንበል! በእርሱንም ላይ infallible እርግጠኝነት አለኝ ልትለን ነው ? ቤተ/ክ ደግሞ ልትሳሳት የማትችለው በዶግማ ላይ ብቻ ነው ፤ ቀኖና ግን ዶግማ አይደለም ብለህ ራስሁ ነግረኸን መልሰህ ደግሞ እንደዛ ለማለት ትደፍራለህ ? ያው እንግዲ Inconsistency ከcontradiction ጋር ተጣምሮ Bleed ሲያረግ!


እንደሁኔታው ዙሪያ ገባውን እያየን እንቀጥላለን ... 😁

@zaNchor
@zaNchor

መልህቅ

14 Jan, 19:11


...

መፅሐፍ ቅዱስ Infallible የሚሆነው Infallible የሆነችው ቤተ/ክን ስለሰጠችን ነው ሲለን የከረመው ሰውዬ ያኔ ስትሰጠው ተሳስታለች መሠል ይኸው አሁን ደግሞ ሪቪዥን እየጠየቀ ነው። በእርግጥም ስህተት እንዳለ ተረድቷል ማለት አይደል ታድያ ?!

ቆይ እሱን ተውትና እንደው ከሰጠችው ራሱ የትኛዋ ቤተ/ክን ነች የምትሰጠው ?

የኢትዮጲያ ቤተ/ክ ነች ካለ እሷ ልትሳሳት ትችላለች። ስለዚህ 81ዱን ብትሰጠውኳ ልትሳሳት የሚችል አካል ነው የሰጠው ማለት ነው። ስለዚህ በራሱ ክራይቴሪያ ወድቆ Infallible የሆነ መፅሐፍቅዱስ ጨርሶውኑ ሊኖራቸው አይችልም ማለት ነው። ሊሳሳት የሚችል አካል ሊሳሳት የማይችለውን ልትሰጥ አትችልም ብሎናልና! በእርግጥ ልትሳሳት ትችላለች ብሎ የነገረንም እራሱ ነው። 💀

ስለዚህ Eccumenical Council ነው እየጠበቀ ያለው ? ካልሆነስ ከእኛ ምን ለየው ?

ዘይገርም ነውኮ ዘንድሮ ...


@zaNchor
@zaNchor

መልህቅ

12 Jan, 08:27


ከልደት በኋላ አንደኛ እሁድ
የወንጌልና የመልእክት ክፍል


ማቴዎስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ እነርሱም ከሄዱ በኋላ እነሆ፥ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍ ታይቶ፦ ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልገዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ፥ እስክነግርህም ድረስ በዚያ ተቀመጥ አለው።
¹⁴-¹⁵ እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊት ያዘና ከጌታ ዘንድ በነቢይ፦ ልጄን ከግብፅ ጠራሁት የተባለው እንዲፈጸም ወደ ግብፅ ሄደ፥ ሄሮድስም እስኪሞት ድረስ በዚያ ኖረ።
¹⁶ ከዚህ በኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገል እንደ ተሣለቁበት ባየ ጊዜ እጅግ ተቆጣና ልኮ ከሰብአ ሰገል እንደ ተረዳው ዘመን በቤተ ልሔምና በአውራጃዋ የነበሩትን፥ ሁለት ዓመት የሆናቸውን ከዚያም የሚያንሱትን ሕፃናት ሁሉ አስገደለ።
¹⁷-¹⁸ ያን ጊዜ በነቢዩ በኤርምያስ፥ ድምፅ በራማ ተሰማ፥ ልቅሶና ብዙ ዋይታ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች፥ መጽናናትም አልወደደችም፥ የሉምና የተባለው ተፈጸመ።
¹⁹ ሄሮድስም ከሞተ በኋላ፥ እነሆ፥ የጌታ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ፦
²⁰ የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ አለ።
²¹ እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ያዘና ወደ እስራኤል አገር ገባ።
²² በአባቱም በሄሮድስ ፈንታ አርኬላዎስ በይሁዳ እንደ ነገሠ በሰማ ጊዜ፥ ወደዚያ መሄድን ፈራ፤ በሕልምም ተረድቶ ወደ ገሊላ አገር ሄደ፤
²³ በነቢያት፦ ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጸም ዘንድ፥ ናዝሬት ወደምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ።


ገላትያ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤
⁵ እንደ ልጆች እንሆን ዘንድ፥ ከሕግ በታች ያሉትን ይዋጅ ዘንድ።
⁶ ልጆችም ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባት ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ውስጥ ላከ።
⁷ ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ልጅ ነህ እንጂ ባሪያ አይደለህም፤ ልጅም ከሆንህ ደግሞ በክርስቶስ የእግዚአብሔር ወራሽ ነህ።

መልህቅ

11 Jan, 15:28


Is to be deep in history to cease to be Protestant? When it comes to the venerating of icons, to be deep in history is, emphatically to the contrary, to cease to be Roman Catholic or Eastern Orthodox. For the witness of the early church is unanimously and thunderingly opposed to the practice, in consistency with the witness of Scripture.

Yet the seventh ecumenical council, which both the Roman Catholic and Eastern Orthodox traditions regard as infallible, casts anathemas widely and liberally at all who abstain from the practice (or “knowingly communicate” with those who do!).

This is not a case of doctrinal development, but doctrinal U-turn: The seventh ecumenical council reversed the view of the early church on the veneration of icons. Unfortunately, traditions that consider Nicaea II to represent infallible teaching cannot reform its teaching. It is, by definition, irreformable. The Protestant tradition, by contrast, offers us a pathway of meaningful return to the practice and theology of the early church, as well as to that of later contexts like the Council of Frankfurt. It also allows us to obey the second commandment.

Further, it obligates no anathemas. Therefore, it is the Protestant position on icon veneration that is not only deep in history, but biblical and catholic.

Gavin Ortlund, What it means to be Protestant , p 192

መልህቅ

10 Jan, 18:03


የመዳን ቀንዴ ጌታዬ
አምላኬ ያስነሳው ለእኔ
ከአብ ጋር ያስተራረቀኝ
ዘወትር የሚማልድልኝ
ውዴ የመዳን ቀንዴ
ውዴ የመዳን ቀንዴ
...

ሊቀካህን ሆኖልኛል ሊቀካህን
ሊቀካህን ሆኖልኛል ሊቀካህን


https://youtu.be/a4VifIxvskc?si=NbEKwH72UC9y166q

መልህቅ

09 Jan, 19:57


...

ሰዎችዬ ቅድም የለቀቅኩት ከኦሪጅናሉ ጥራቱ ቀንሶብኝ ለእናንተ ስል ይኸው አሪፍ አድርጌ ደግሜ ፖስቼዋለሁ!

ያው ብዙዎች ጋር እንዲደርስ ደግማችሁ በደንብ ኢንጌጅ አድርጉበት! ሼር ፣ ላይክ ፣ ኮመንት ፣ ኮፒ ሊንክ .... 😁👊


https://www.tiktok.com/@abesus09/video/7458004418387070214

መልህቅ

09 Jan, 18:13


እናንተ ፕሮቴስታንቶች ቤተክርስቲያን 2ተኛው ወይ 3ተኛው ክፍለዘመን ላይ ጠፍታ 16ተኛው ክፍለዘመን ላይ ጌታ ታደጋት ብላችሁ እንዴት ታምናላችሁ ... ?

ብላችሁ የምትወቅሱን ኦርቶዶክስ ወንድሞቻችን ይኸው መልሳችንን ተመልከቱስኪ እንዲህ አቅርቤላቹሀለው ... 😁

.... 👇👇👇👇

መልህቅ

07 Jan, 10:20


እንኳን ለጌታችን ልደት የመታሰቢያ በአል አደረሳችሁ!

ይህ የአምላክ ሰው ሆኖ መወለድ ፍጥረታዊ ሰው ሊረዳው የማይችለው ፤ በመንፈስቅዱስ ብርሀን ብቻ ልንታመነው የምንችለው ፤ ከአምላክ መገለጦች ሁሉ የመጨረሻውና የመሰጠረው መገለጥ ነው።

▣ ለምን ቃል ስጋ ሆነ ?

ሀጥያታችንን ሊሸከምና ለእኛ ይገባ የነበረውን የሞት ቅጣት(ደሞዝ) ከፍሎ ከዘላለም ፍርድ ነፃ ሊያወጣን በዚህም ደግሞ የዘላለምን ህይወት የመውረስ መብት ሊቸረን ነው! ይህም በእኛ በፕሮቴስታንቱ ስነመለኮቶ ወስጥ ፅድቅ | Justification ብለን የምንጠራው ነው። ስጋዌን ያስገደደው (Necessitate ያደረገው) ስለዚህም ዋናውና ቀዳሚው አላማ (Cause) የሆነው ይህ የፅድቅ ጉዳይ ነው!

▣ እግዚአብሄርን ለዚህ ውሳኔ ምን ምክንያት ሆነው ?

እግዚአብሄር አምላክ ሰው እንዲሆን ግድ ያሰኘው ብቸኛ ምክንያት በሀጥያታችን ሙታንና ፍርድ የተገባን ሆነን ላለነው ለሰው ልጆች ያለው ፍቅር ብቻና ብቻ ነው!

▣ ግን ስጋዌ ከዚህ የዘለለ ምስጢር አለው ?

ይህ ምስጢር በመስቀል የመሞቱንና እኛን ከማዳኑ አንፃር ብቻ የሚተረጎም አይደለም። ከላይ የስጋዌ አላማና ግብ ሆኖ የተገለፀው ፅድቅ ምንምኳ የስጋዌው ትልቁና ዋነኛው ግብ ቢሆንም ነገር ግን ፅድቁን የመስራቱና ለእኛም የመስጠቱ የመጨረሻ አላማና ግብ (Telos) የእግዚአብሄርን ባህሪ ወይም የእግዚአብሄርን ህይወት ተካፋይ ለመሆን ነው! ስለዚህ በድህነት አስተምህሮ ውስጥ ፅድቅ በራሱ የመጨረሻው ነጥብ አይደለም። እርሱ ራሱ ግብ አለው!

ስለዚህ ይህ ማለት :

➾ የፅድቅ (Justification) ግቡ በእግዚአብሄር ህይወት ውስጥ ያለ ተካፋይነት ነው!

➾ The end Goal of Justification is participation in the life of God.

ይህንን የፅድቅ የመጨረሻ ግብ አባቶች Theosis እንዲሁም Divinization ብለው ይጠሩታል። ይህም በእዚህ በምድር ባለን ህይወትም ሆነ ከመጨረሻው ፍርድ በኋላ ከጌታ ጋር ባለን ህይወት ጨርሰን የምንሆነው ወይም የምናጠናቅቀው ነገር ባይሆንም ነገር ግን በዚህ በምድር በቅድስና ጉዞ (Sanctification) እለት እለት እየተላበስን የምንመጣውና ከከበርንም በኋላ (After Glorification) በሙላት የእግዚአብሄርን ህይወት የምንካፈልበት እንዲሁም ያለማቋረጥ እየጠለቀ በሚሄድ መልኩ Experiance የምናደርግበትም ነው።

ታድያ ቃል በዚህ በስጋዌው ይህን ለእኛ የመጨረሻ ግብ የሆነውን ያንን ሰው ፕሮቶታይፕ ሆኖ በአካልና በስጋ የገለጠበት ነው። ጳውሎስም በሮሜ 8: 29 ላይ ስለዚህ ሲናገር የእግዚአብሄር የማዳኑ የመጨረሻው ግብና አላማ የልጁን መልክ መምሰል ነው ይለናል። ይህንንም በመጥራት ፤ በማፅደቅና በማክበር በኩል ፈፀመው!

በውድቀት ምክንያት ባህሪው ደቆ ለሀጥያትም ባሪያ ሆኖ የተገዛው የሰው ልጅ ከዚህ ፍፁም የሚገላግለው መድሀኒት የእራሱ የእግዚአብሄር ህይወት ነው! ስለዚህ ስጋዌው ይህንን መድሀኒት ለራሳችን Appropriate (Apply) የምናደርግበትን መብት (አስተውሉ! ስለመብት (Title) ነው እያወራሁ ያለሁት!) የምናገኝብን ስራ ለመስራት የተገለጠበት ብቻ ሳይሆን ፤ ያ ሙሉ ለሙሉ አለምን ሀጥያትንና ሞትን አሸንፎ እግዚአብሄርን የመሰለውና ባህሪውንም የሚያንፀባርቀውን የእርሱን ማንነት ለእኛ በቅርበት የገለጠበትም ጭምር ነው። እኛም በእርሱ በኩል (In participating in his Status) ከዛም ደግሞ በእርሱ ውስጥ (In an Onthological Participation in his Nature) አለምን ሀጥያትንና ሞትን እናሸንፋለን!

መልካም በአል!


@zanchor
@zanchor

መልህቅ

02 Jan, 15:47


ስገምት ስገምት አብዛኞች ኦርቶዶክስ ወንድሞቻችን Apostolic Succession (AS) ማለት ማንኛውም አይነት ቅብብሎች ይመስላቸዋል መሠል። ማለትም ለምሳሌ ክርስቶስ ሐዋርያቱን ሾመ ፤ ሐዋርያቱ ኤጲስቆጶሳትን ሾሙ ፤ የተሾሙትም ታማኝ የሆኑ ተከታይ ኤጲስቆጶሳትን ሾሙ ፤ እያለ እያለ ሄደ ..  ታድያ ይህንን በማሳየት ብቻ Apostolic Succestionን ጨርሰው ያስረገጡ የሚመስላቸው ሰዎች አሉ።

ያው ግን ይህ ስለ AS ጨርሶ አለማወቅ ነው። ይህንንማ በየትም የፕሮቴስታንት ቤተእምነት ውስጥ ሆነህ መቀበል ትችላለህ ፣ ትቀበላለህም። ቀይ መስመር ሆኖ የሚለያየንን ፕሮፐር የሆነ የሐዋርያት ቅብብሎሽ (AP) አስተምህሮ ትርጉም ከዚህ በፊት አብራርቼ አስቀምጫለሁ። አራት መሠረታዊ ነጥቦች አሉት። ቀጣዩን ሊንክ ተጠቀሙና ተመልከቱት!

➾ https://t.me/ZANCHOR/990


ሌላው ደግሞ እንደው በOrdinary የቤተ/ክን ህይወት ውስጥ ማንም ብድግ ብሎ ራሱን መሾምና ሳክራመንትን Administer ማድርግ ይችላል ብለንም እንደምናምን እና በቃ ምንም መስፈርት የሌላቸው አድርገውን የሚስሉንም አሉ። ይህም ስህተት ነው። ጌታ ይርዳቸው!


Side Note :

እንደው ምናልባት ትክክል ከሆነኳ በተወሰኑ ሉተራንና በአንግሊካን ዘንድ AP የሚታመን መሆኑን አትዘንጉት! 'ወይ ዜሮ ወይ መቶ , ምረጥ!' በሚል የሚሰሩት ፋልስ ዳይኮቶሚ ለማያውቁቱ ካልሆነ በቀር በእኛ ዘንድ አያዋጣቸውም!

መልህቅ

31 Dec, 09:26


ጋይስ እንዴት ናችሁሳ ? ያው እንደምታዩት በአጭር ጊዜ ውስጥ 3k ገብተናል። እንኳን ደስ አለን። 👊 ገና ደግሞ እንበዛለን። 😁

እስከዛሬ ለሰዎች ሼር እያደረጋችሁ ጀማችንን እንዲቀላቀሉን ላደረጋችሁና እያደረጋችሁ ላላችሁ ወንድም እህቶች ፤ ለተቀላቀላችሁንም ጭምር ፈጣሪ ያክብርልኝ።

ይህ አገልግሎት እንዲሰፋ የሁላችንንም መረባረብ የሚጠይቅ መሆኑ ምንም ጥያቄ የለውምና አሁንም በተቻለን አቅም በዙሪያችን ላሉ ለሰዎች በማሳወቅ ፣ በመጋበዝ ፤ ሼር በማድረግ እንድናሰፋው አደራ እላለሁ።

ምናልባት ደግሞ ይህን አስመልክቶ ከዚህ በፊት እንዳደረግነው ሰብሰብ እንበልና እነዚህ እነዚህ ላይ እናውጋ የሚል ሀሳብ ካላችሁ እስኪ አሳውቁኝ እናደርገዋለን።😁

መልህቅ

28 Dec, 13:28


ድኛለሁ፣ እየዳንሁ ነው፣ ወደፊትም እድናለሁ በሚለው ሰሞናዊ የሶሻል ሚዲያ ትምህርታችሁ ላይ ግን ፓትሪስቲካዊ ማስረጃ እያየን አይደለም😁😁 እስቲ እርዱን እባካችሁን ስራችንንም አቅልሉልን😄
ከመጸሃፍ ቅዱስ በ16ኛ ክፍለ ዘመን መነጽር ከምታስተምሩን እባካችሁን ከአበው እያመሳጠራችሁ፣ በጉባኤ ውሳኔዎች እያስደገፋችሁ፣ በቤተ እምነታችሁ የእምነት ድንጋጌ እያመሳከራችሁ እባካችሁን እኛ የጠፋን በጎቹን ተጣሩን😀
ከመጸሃፍ ቅዱስ ብቻ እያስተማራችሁ ከመሰረታዊ መርሆቻችሁ ፈቀቅ አትበሉ። ደግሞ ድኛለሁ፣ እየዳንሁ ነው ያልከው ግለሰብ ናና እስቲ በና ሶላ ፊዴን የማትቀበልበት ሰማያዊ ምስጥርህን ንገረኝ😁

መልህቅ

27 Dec, 15:29


ሰዎችዬ ይህችን ነገር እስኪ ቼክ አድርጓት። አሰራሩን ለመልመድና እንደሁኔታው በዚህም ለማገልገል ቼካፕ ላይ ነኝ። 😁

በዛውም ሼርና ፎሎው ማድረግ እንዳይረሳ! 😅🙈

https://www.tiktok.com/@abesus09/video/7453109731885042950

መልህቅ

23 Dec, 10:22


ተጠምተናል | Tetemtenal
By AASTU ECSF Worship Team

https://www.youtube.com/watch?v=Cqo87LSFfzg

መልህቅ

22 Dec, 08:43


የመምጣቱ (የምፅአቱ) ሁለተኛ እሁድ
የወንጌልና የመልእክት ክፍል


ማቴዎስ 24
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁹ ከዚያች ወራትም መከራ በኋላ ወዲያው ፀሐይ ይጨልማል፥ ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፥ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፥
³⁰ የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ። በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል፥ በዚያን ጊዜም የምድር ወገኖች ሁሉ ዋይ ዋይ ይላሉ፥ የሰው ልጅንም በኃይልና በብዙ ክብር በሰማይ ደመና ሲመጣ ያዩታል፤
³¹ መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፥ ከሰማያትም ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከአራቱ ነፋሳት ለእርሱ የተመረጡትን ይሰበስባሉ።
³² ምሳሌውንም ከበለስ ተማሩ፤ ጫፍዋ ሲለሰልስ ቅጠልዋም ሲያቈጠቍጥ፥ ያን ጊዜ በጋ እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ፤
³³ እንዲሁ እናንተ ደግሞ ይህን ሁሉ ስታዩ በደጅ እንደ ቀረበ እወቁ።
³⁴ እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም።
³⁵ ሰማይና ምድር ያልፋሉ፥ ቃሌ ግን አያልፍም።


1ኛ ቆሮንቶስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንዲሁ ሰው እኛን እንደ ክርስቶስ ሎሌዎችና እንደ እግዚአብሔር ምሥጢር መጋቢዎች ይቍጠረን።
² እንደዚህም ሲሆን፥ በመጋቢዎች ዘንድ የታመነ ሆኖ መገኘት ይፈለጋል።
³ ነገር ግን በእናንተ ዘንድ ወይም በሌላ ሰው ዘንድ ብፈረድ ለእኔ ምንም አይደለም፤ እኔም በራሴ እንኳ አልፈርድም፤
⁴ በራሴ ላይ ምንም አላውቅምና፥ ነገር ግን በዚህ አልጸድቅም፤ እኔን የሚፈርድ ግን ጌታ ነው።
⁵ ስለዚህም በጨለማ የተሰወረውን ደግሞ ወደ ብርሃን የሚያወጣ የልብንም ምክር የሚገልጥ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ጊዜው ሳይደርስ አንዳች አትፍረዱ፤ በዚያን ጊዜም ለእያንዳንዱ ምስጋናው ከእግዚአብሔር ዘንድ ይሆናል።

መልህቅ

20 Dec, 18:27


A nice punch 👊😁 check it out

https://vm.tiktok.com/ZMk6qvQEe/

መልህቅ

20 Dec, 13:17


ነብይና ሐዋርያ ነኝ በሚሉ ግለሰቦች የሚመሩ የዘመናችን ስመ 'ቤተክርስቲያኖች' እውነተኛ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ናቸው ብሎ መጥራትም ሆነ በእነርሱ የጌታን አካል መወከል ትክክል ነው ብዬ አላስብም።

ይህ ማለት ግን የዳኑ ሆነው ከእውቀት ማጣት የተነሳ በእዛ የሚኖሩም ሆነ የሚንከራተቱ ብዙ ሰዎች መኖራቸውን አላስተውልም ማለት አይደለም።

እንደው በጥቂቱ ሶስት መሠረታዊ ምክንያቶችን ብቻ ላቅርብ!

➾ 99.9 %ቱ ቅዱሳት ምስጢራት የሀጥያት ይቅርታንና ሌሎችንም ፀጋዎችን እንደሚሰጡ የሚክዱ ናቸው።

➾ ከሐዋርያት ቀጥታ ከተሰጠ ስርአትና ከቤተ/ክ 2000 አመት ህይወት ያፈነገጡ ናቸው። መስራችና ባለራዕይ ግለሰብ የሆነላት ፤ ግለሰቡ ከላይ ተቀምጦ በእርሱ የምትመራም ሆነ የምትጠራ ቤተ/ክንን ክርስቶስ አልመሠረትም ፣ አልሰጠንምም!

➾ በብዙ ጉዳዮች ከመፅሐፍ ቅዱስም ፣ ከታሪክም የተጋጩ ናቸው። እንዲሁም የHeresy እና የHetrodoxy መፈልፈያ ቀንደኛ ቦታዎች ናቸው።

@zanchor
@zanchor

መልህቅ

19 Dec, 08:50


°°°

የእኔን ሁላችሁም ታውቁታላችሁ 😁

እስኪ የእናንተን እንስማ!

መልህቅ

16 Dec, 11:19


ነገ ማለትም ማክሰኞ 8 ሰአት እስከ 10 ሰአት በንጥቀት ላይ በተጠቀሰው ቦታ ሴሚናር ይኖራል። ጥያቄና መልስ ምናምንም ሳይኖር አይቀርም!

የምትችሉ ሁሉ ተጋብዛቹሀል!

በተለይ ከመከራው በፊት ባለ ንጥቀት (Pre-Tribulation Rapture) የምታምኑ ወንድሞች እንደው እንደምንም ጨክናቹ ብትገኙ ጌታም ጨክኖ ከዚህ ትምህርት ይነጥቃቹ ይሆናል ማን ያውቃል ? 😅

(እወዳቹሀለው ለማንኛውም! 😁)

...

መልህቅ

15 Dec, 11:45


°°°

ሉተራዊነት ይለምልም! አሜን በሉ!

ቤታችን ውስጥ እናት አንግሊካዊነትን ለመስበክ የሚጥሩ አንዳንድ ተቀናቃኝ ወንድሞች ሾልከው ገብተዋልና እየተጠነቀቅን! 😅

የልጥፉ ቀንደኛ ተደራሲ እነርሱ ናቸው! 😁

መልህቅ

15 Dec, 09:52


የመምጣቱ አንደኛ እሁድ

የወንጌልና የመልእክት ክፍል

ማቴዎስ 21
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወደ ኢየሩሳሌምም ቀርበው ወደ ደብረ ዘይት ወደ ቤተ ፋጌ ሲደርሱ፥ ያንጊዜ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለት ላከ፥
² እንዲህም አላቸው፦ በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ፥ በዚያን ጊዜም የታሰረችን አህያ ውርንጫም ከእርስዋ ጋር ታገኛላችሁ፤ ፈትታችሁ አምጡልኝ።
³ ማንም አንዳች ቢላችሁ፦ ለጌታ ያስፈልጉታል በሉ፤ ወዲያውም ይሰዳቸዋል።
⁴-⁵ ለጽዮን ልጅ፦ እነሆ፥ ንጉሥሽ የዋህ ሆኖ በአህያ ላይና በአህያይቱ ግልገል በውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል በሉአት ተብሎ በነቢይ የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆነ።
⁶ ደቀ መዛሙርቱም ሄደው ኢየሱስ እንዳዘዛቸው አደረጉ፥
⁷ አህያይቱንና ውርንጫዋንም አመጡለት፥ ልብሳቸውንም በእነርሱ ላይ ጫኑ፥ ተቀመጠባቸውም።
⁸ ከሕዝቡም እጅግ ብዙዎች ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉ፥ ሌሎችም ከዛፍ ጫፍ ጫፉን እየቈረጡ በመንገድ ላይ ያነጥፉ ነበር።
⁹ የሚቀድሙትም ሕዝብ የሚከተሉትም፦ ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።
¹⁰ ወደ ኢየሩሳሌምም በገባ ጊዜ መላው ከተማ፦ ይህ ማን ነው? ብሎ ተናወጠ።
¹¹ ሕዝቡም፦ ይህ ከገሊላ ናዝሬት የመጣ ነቢዩ ኢየሱስ ነው አሉ።


ሮሜ 13
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።
¹² ሌሊቱ አልፎአል፥ ቀኑም ቀርቦአል። እንግዲህ የጨለማውን ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ።
¹³ በቀን እንደምንሆን በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን፤
¹⁴ ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም ለሥጋ አታስቡ።

መልህቅ

11 Dec, 11:40


የህፃናት ጥምቀት በታሪካዊ ፕሮቴስታንት ዘንድ

በነገራችሁ ላይ ከትላንትናው ክታብ ጋር በተያያዘ በታሪካዊ ፕሮቴስታንት ውስጥ የህፃናትን ጥምቀት የማይቀበለው ቤተእምነት ባፕቲስት (Reformed Baptist) ብቻ ነው። ይህ ማለት በጠቅላላው የምታገኟቸው የቱኛውም ኮንፌሽንስ እና ካቴኪዝምስ ከእነርሱ ውጪ አፅዳቂውና ተቀባይ ናቸው።

ማውቃቸውን ብቻ ልጥቀስላቹ! 😁

➾ All Lutheran Confessions and Catechisms
➾ Westminister Confession
➾ 39 Article of Religion
➾ Scots Confession
➾ 1 and 2 Helvetic Confession
➾ The Heidelberg Catechism
➾ Belgic Confession
➾ Canons of Dort
➾ The Geneva Confession
➾ The French Confession
➾ First Confession of Basel
➾ Calvin’s Catechisms

እንድታስተውሉ የምፈልገው ከመጀመሪያው ውጪ የተጠቀሱት በአጠቃላይ ሪፎርምድ መሆናቸውን ነው። ማለትም 5 (or 4) Point Calvinist ናቸው። ይሄ መልእክቱ ለማ እንደሆነ የሚያውቅ ያውቀዋል።😁

በአጭሩ የህፃናትን ጥምቀት የሚቃወም ሰው በጥንታዊው ማህበረሰብ ዘንድ ያለውን ኮንሴንሰስ ብቻ ሳይሆን ከዛም አልፎ በክላሲካል ፕሮቴስታንቱ ውስጥ ያለውን ወጥ የሆነ የአቋም አንድነት ጭምር የሚቃወም ነው። እርሱን ሰው እኛ ሳንሆን ራሱ አንድዬ ነው ሊረዳው የሚገባው!

ከዚህ የምንረዳው ቁምነገር የህፃናትን ጥምቀት መቀበል ለእኛ ዲፎልት ፖዚሽናችን መሆኑን ነው!

ታድያ ይህንን የቲክታክ ኦርቶዶክስ አቃቢያን ዘመዶቻችን ቢያውቁ ሙግታቸውን የተሻለ የሚያጠራላቸው ይመስለኛል። ያው እዛ ላሉት ለአብዛኞቹ ፕሮቴስታንቲዝም በጣም ከተሻለ ከኢትዮጲያ ፤ ከከፋ ደግሞ ከነብይ እንትና ስለማያልፍ። 💀😁 አሳውቋቸው ለማለት ነው!

@zanchor
@zanchor

መልህቅ

10 Dec, 10:41


የህፃናት ጥምቀት | Infant Baptism

ብዙ ሰዎች የህፃናት ጥምቀትን አስተምህሮ ለመቀበል የሚከብዳቸውና በተደጋጋሚም የሚጠይቁት ነገር ቢኖር እንዴት ህፃናት ማመን ይችላሉ ? የሚለው ነው። በእርግጥ በጠቅላላ ይህንን አስተምህሮ የማያምኑ ሁሉ ቀንደኛው ምክንያታቸው 'ህፃናት ማመን አይችሉም' የሚል ነው።

መቼም ሁላችንም እንደምንስማማው ሰው ለመዳን የእግዜርን ቃል ሰምቶ ማመን አለበት። መፅሐፍቅዱስ ሰው ለመዳን ማመን እንዳለበት መሀከለኛ አስተምህሮው አድርጎ የሚያስቀምጠው ነገር ነው። ነገር ግን አንድ የምናውቀው ነገር ህፃናት ወንጌልን ብንሰብክላቸው ሰምተው ከዛም አሰላስለው የተነገራቸውን ተረድተውት ፤ በተገለጠም መልኩ እምነታቸውን አያሳዩም ወይም አይናገሩም። ስለዚህም ብዙዎች ከዚህ ተነስተው ህፃናት ሊያምኑ አይችሉም ብለው በማመን እነሱን ማጥመቅን ይከለክላሉ።

በአጭሩ የዚህ አይነቱ አስተሳሰብ ስህተት የሚጀምረው ራሳቸው ጥያቄ አድርገው ከሚያቀርቡት ከእምነት ምንነት ነው። እምነትን በትክክል በመረዳት ብቻ ይህን አረዳድ ማስካከል ይቻላል።

እንግዲህ እምነት ማለት ሰዎች ከእግዚአብሄር በነፃ የቀረበላቸውን የተጨረሰና የተጠናቀቀ ድህነት የሚቀበሉበት እጅ ነው። ይህንን ከቀናት በፊት በተለቀቅኩት የእምነት ብቻ አስተምህሮና የሳክራመንት አስተምህሮ ንፅፅር በስፋት አብራርቼ አስቀምጫለሁ። በታሪካዊው ፕሮቴስታንቱ አስተምህሮ መሠረት እውነተኛ አዳኝ እምነት በሶስት መሠረታዊ ነገሮች ላይ የሚመሠረት ወይም በእነርሱ የሚተረጎም ነው። እነርሱም እውቀት ፣ ፍቅር እና መደገፍ (Trust) ናቸው። አንድ ሰው ለማመን የሚታመንበት ነገር ሊቀርብለት እርሱንም በሆነ መልኩ ሊያውቅ ፤ ሊረዳ ወይም ሊያስተውል ይገባል። ሲቀጥል ይህ አዳኝ እምነት በፍቅር የሚሰራ ነው። ማለትም ከፍቅር ባህሪ ጋር የተጋመደና የፍቅር ድርጊቶችንም የሚያፈልቅ ነው። ሶስተኛውና ትልቅ ዋጋ ያለው ደግሞ የአዳኝ እምነት Definitional Aspect Trust ነው። ይህም ማለት እምነት በአማኙ ደካማነት ፣ አለመቻልና ባዶነት ላይ ተመስርቶ የሚታመነው አካል ባለው ጥንካሬ ፣ ችሎታ ፣ አቅምና ብርታት ላይ ራስን መጣልና መደገፍ ነው። ከዚህ የTrust ትርጉሙ አንፃር እምነት ሙሉ ለሙሉ ተቀባይ ነው እንጂ ሰጪ አይደለም ማለት ነው። እምነት የሚያድነውም በዚህ በተቀባይ ባህሪው ብቻ ነው። ይህንን Fides Directa ብለን እንጠራዋለን።

እምነትን በዚህ መልኩ ከተረጎምነው ሌላው መረዳት ያለብን አንድ Distiniction አለ። እርሱም Councious Faith እና Uncouncious Faith ናቸው። እንተርጉማቸው።

#Councious_Faith [CF] - This refers to faith that is actively known and understood by the believer. It involves an intellectual and rational comprehension of the faith one has.

#Uncouncious_Faith [UF]- This refers to a faith that is present but not yet actively or Intelectually realized by the individual. It doesn't involve an intellectual and rational comprehension of the faith one has.

እነዚህን ሁለት Distinictions ህፃናቱ ጋር ሳንሄድ ከትላልቅ ሰዎች በመነሳት መረዳት እንችላለን። ለመጀመሪያው የእምነት አይነት ምንም የራቀ ማስረጃም አያስፈልግም። ይህን የምታነቡ እናንተው አንዴ ወደራሳችሁ ዞር ብላችሁ ስለእምነታችሁ Reflect ካደረጋችሁ እርሱ በቂ ማስረገጫ ነው። ሁለተኛውን የእምነት አይነት ግን አቅርበንም ፣ አርቀንም በተለያዩ መንገዶች ልንመለከተው እንችላለን። ከቅርቡ ለመነሳት ያህል ለምሳሌ በቀን ውሏችን ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ትኩረታችንን በሚወስዱ ስራና የተለያዩ ድርጊቶች በተወጠርንበት ሰአት Councious የሆነ Self-Reflective Faith የለንም። በዚህ ውስጥ የትኛውም ከራሳችን ውጪ ሙሉ ትኩረታችንን የሚወስዱ ድርጊቶች ሙሉ ለሙሉ ሊካተቱ ይችላሉ። ይህ በቀን ለቀን ህይወታችን ውስጥ ያለ ከመሆኑ አንፃር ቀላሉና ቅርቡ ምሳሌ ይሆናል። ምናልባት ካራቅነው ደግሞ እውነተኛ እምነት የነበራቸውና የዳኑ ነገር ግን በአደጋ ምክንያት ራሳቸውን የሳቱ ወይም ሲብስ ኮማ ውስጥ የገቡ ሰዎችን መጥቀስ እንችላለን። በእርግጥ እዛም ሳይደርስ ሁላችንንም የሚያካትት ሙሉ ለሙሉ የWillም ሆነ የIntellect Conciousnessን የምናጣበት እጅግ ቅርብ የሆነውን የሌሊት እንቅልፍ በምሳሌነት ማንሳትም እንችላለን። በእነዚህ ሁሉ ውስጥ ግን እምነት አይጠፋም።

እነዚህ ሁሉ በአጭሩ ሰው የፍቃዱም ሆነ የመረዳቱ Facultyዎች ሙሉ ለሙሉ ተግባራቸውን Counciously በማይሰሩበት በዛ ሁኔታ ውስጥ Still እውነተኛ እምነት መኖርና መቀጠል መቻሉን የሚያስረግጡ ናቸው።

ወደመጀመሪያው ጥያቄ ስንመለስ መረዳት ያለብን ነገር 'ህፃናት ማመን አይችሉም!' የሚሉ ወንድሞች በዚህ አገላለፃቸው በጭራሽ ህፃናት የማመን አቅምና ችሎታ የላቸውም (Capacity to Believe) እያሉን አይደለም። ምክንያቱም Potentialኡ በሰው Intrinsic Property ውስጥ የሚቀመጥ ነውና። ስለዚህ በብቸኝነት ለእውነተኛ እምነት Neccessary Condition አድርገው የሚያስገቡት ከላይ የተቀመጠውን Councious Faithን ነው። እርሱም Counciously ያለንበትን State Analyse ማድረግ እና Rationallyም በንቃት Comprehend ማድረግ።

ነገር ግን ከላይ ከተቀመጡት ሁለቱ Distiniction የምንረዳው ለእውነተኛ እምነት (Fides Directa) CF በጭራሽ Necessary Condition ሊሆን እንደማይችል ነው። ካለበለዚያ በUF ስር በተዘረዘሩት ምሳሌዎች ስር ያሉ አማኝ ሰዎችን በጠቅላላ አስሬ ወደ ኢ-አማኒነት እየገለበጥን ልንኖር ነው። ያው Neccessary Condition ካደረግው እርሱ ከወጣ ሙሉ ለሙሉ እምነትም Collaps ስለሚያደርግ።

ከዚህ ቀጥሎ መጨመር የሚያስፈልገን ነጥብ በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት ያለውን አንድ መፅሀፍ ቅዱሳዊ እውነት ነው። እርሱም እምነት ራሱ የእግዚአብሄር ስጦታ መሆኑ ነው። መፅሐፍ ቅዱስ መንፈስቅዱስ በሚሰጠው የቃሉ ብርሀን እና እርሱም ይዞት በሚመጣ ፀጋ እምነትን በነፍሳችን ውስጥ እንደሚፈጥር ያስተምረናል። እዚህ ላይ መሳሳት የሌለብን ይህ ማለት እግዜር ነው የሚያምንልን ማለት አይደለም። አማኞቹ እኛ ነን። ነገር ግን የምናምንበትን ልብ እንዲያምን የሚቀርፀውም ሆነ የምናምንበትን ያንን Object of Faith የሚያቀርብልን መንፈስቅዱስ ነው ማለት ነው።

መንፈስቅዱስ ይህንን ስራ እንዳይሰራ በብቸኝነት የሚከለክለው ነገር ደግሞ ተቃውሞና እምቢታ ብቻና ብቻ ነው (Willfull Rejection)። ህፃናት ግን መንግስተ ሰማይ የተወከለባቸው ፤ እኛ ትላልቆቹንኳ ሰማይን ለመቀላቀል ተመልሰን እነርሱን እንድንመስላቸው የተነገረላቸው ናቸው። መቼም ምሰሉ የተባልነው ቁመታቸውን አይደለም። ራሳቸውን አዋርደው የተሰጣቸውን ሁሉ ያለተቃውሞ የሚቀበሉ መሆናቸውን እርሱም እምነታቸውን (Fides Directa) እንጂ! ስለዚህ መንፈስቅዱስ ልክ በእኛ ውስጥ እምነትን እንደሚሰራ በእነርሱም ውስጥ ሊሰራ የማይችልበት ምንም ምክንያት የለም ማለት ነው።

@zanchor
@zanchor

መልህቅ

09 Dec, 20:05


መልህቅ   {https://t.me/ZANCHOR}


ሶስተኛ ማውጫ ገፅ

በመልህቅ ቻነል በተለያዩ ርዕሶች ላይ የተለቀቁ አጫጭርና ረዣዥም ፅሁፎችን ፤ እንዲሁም ተከታታይ ትምህርቶችንና ጥናቶችን በቀላሉ ለማግኘት እንዲረዳ የተዘጋጀ የማስፈንጠሪያ ማውጫ ገፅ!

ቀዳማይ ማውጫ ገፅ ➺  https://t.me/ZANCHOR/449}
ሁለተኛ ማውጫ ገፅ ➺ https://t.me/ZANCHOR/662}




▣ 'በእምነት ብቻ ሳይሆን በስራም'

▷ https://t.me/ZANCHOR/889

▣ ስለፕሮቴስታንት የድህነት አስተምህሮ መታወቅ ያለባቸው ነጥቦች

▷ https://t.me/ZANCHOR/882

▣ ጳውሎስና ፅድቅ

▷ https://t.me/ZANCHOR/893

▣ Useful thought on the use of the term Infallibility

▷ https://t.me/ZANCHOR/908

▣ 'የገሃነም ደጆችም አይችሏትም'

▷ https://t.me/ZANCHOR/911

▣ በቀኖና ጉዳይ ከክርስቶስ በፊትም ይሁን በኋላ ያለው የአይሁድ ማህበረሰብ አቋም ዋጋ የለውምን ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/925

▣ CONFESSIONS AND CATECHISMS of Mainline Denominations in Classical Protestantism

▷ https://t.me/ZANCHOR/926

▣ Initial Salvation ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/929

▣ ድጋሜ ስለጳውሎስ የፅድቅ አስተምህሮ

▷ https://t.me/ZANCHOR/939

▣ ኦርቶዶክስ ወንድም እህቶች የእኛን መዝሙር መስማት አይችሉምን ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/940

▣ በመዳን አስተምህሮ ኦርቶዶክስና ካቶሊክ ከፕሮቴስታንቱ ጋር ያላቸው መሠረታዊ ልዩነት - እያጠራን እንሂድ!

▷ https://t.me/ZANCHOR/942

▣ Can protestans say 'the Church wrote the scriptures'  ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/944

▣ የጌታ እራት በፕሮቴስታንት ዘንዳ

Part 1 ▷ https://t.me/ZANCHOR/943
Part 2 ▷ https://t.me/ZANCHOR/945
Part 3 ▷ https://t.me/ZANCHOR/949

▣ 'እንዴት ይህን ሁሉ ክፍፍል ይዛችሁ እውነተኛ ነን ትላላችሁ ?'

https://t.me/ZANCHOR/955

▣ Unconditional Election ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/957

▣ ኢሬኒየስ እና መፅሐፍ ቅዱስ ብቻ

1 ▷ https://t.me/ZANCHOR/958
2 ▷ https://t.me/ZANCHOR/961

▣ ነገረ ክርስቶስ - Enhyplostsis & Anhypostasis

▷ https://t.me/ZANCHOR/970

▣ የማያድነው የሕግ ስራ ምንን የሚያጠቃልል ነው ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/973

▣ ከቤተ-እምነታችሁ ለተነጠለና ለተለየ ሀሳብ ላይ ብቻ ላለ ፕሮቴስታንቲዝም አትቁሙ!

▷ https://t.me/ZANCHOR/979

▣ መሠረታውያኑን በምን መስፈርት አወቃችሁ ?

Part 1 ▷ https://t.me/ZANCHOR/978
Part 2 ▷ https://t.me/ZANCHOR/980
Part 3 ▷ https://t.me/ZANCHOR/982

▣ The principle of Sola Scriptura from Historical Instantiations

▷ https://t.me/ZANCHOR/986

▣ የሐዋርያዊ ቅብብሎሽ አስተምህሮ ምንድን ነው ? ማንስ ነው የሚያምነው ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/990

▣ ዮሐንስ 15 : 1- 8 በእውነተኛ እምነት ክርስቶስን የታመነ ሰው ፍፁም ፍሬን ሳያፈራ ሊኖር እንደሚችል ያስተምራልን ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/995

▣ Martin Chemnitz - Explanation of what justifying faith is and what faith alone realy mean.

Part 1 ▷ https://t.me/ZANCHOR/1004
Part 2 ▷ https://t.me/ZANCHOR/1004
Part 3 ▷ https://t.me/ZANCHOR/1008
Part 4 ▷ https://t.me/ZANCHOR/1012

▣ ስነመለኮታዊ-ክፍፍሎሽ (Theological Triage) መፅሐፍ ቅዱሳዊ ነው ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/1007

▣ ሉተራን (እንዲሁም አብዛኛው አንግሊካንና ሜተዲስት) ጥምቀት ያድናል (Baptism Regenerates) ብለው ሲሉ ምን እያሉ አይደለም ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/1015

▣ እምነት እና ስራ በያዕቆብ መፅሀፍ ውስጥ

▷ https://t.me/ZANCHOR/1023

▣ ግን 'ፕሮቴስታንቶች' ክርስቶስን ያምኑታልን ? 😁

▷ https://t.me/ZANCHOR/1024

▣ የወንድም አክሊል የማቲዎስ 18 ንባብ ስህተቶች

▷ https://t.me/ZANCHOR/1028

▣ ታሪካዊ ፕሮቴስታንት (Classical Protestant) ወይስ ጥንታዊ አብያተ-ክርስቲያናት ? የእውነት ሙላት በየትኛው ቤተእምነት ይገኛል ? ምን ልሁን ?  | Road Map

▷ https://t.me/ZANCHOR/1031

▣ ሉተር ክርስቶስን ተሳድቧል ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/1037

እምነት እና ፍቅር በመዳን አስተምህሮ ውስጥ

▷ https://t.me/ZANCHOR/1040

▣ የመዳን አስተምህሮ -  Atonment, Saving Faith and Justification by Faith Alone (Audio)

▷ https://t.me/ZANCHOR/1041
▷ https://t.me/ZANCHOR/1042

▣ Answer - Material Sufficiency - POD VS SOD

▷ https://t.me/ZANCHOR/1051

ጥምቀት - ሐዋርያት ስራ 2:38

Part 1 ▷ https://t.me/ZANCHOR/1052
Part 2 ▷ https://t.me/ZANCHOR/1062

▣ የኬልቄዶን ጉባኤ በቂ በሆነ ልኬት ራሱን አላብራራም ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/1073

▣ እውነት ድንግል ማርያም በስጋ አርጋለችን ? 😁

▷ https://t.me/ZANCHOR/1080

▣ Justifiction by faith Alone | Live Sessions

▷ https://t.me/ZANCHOR/1085
▷ https://t.me/ZANCHOR/1090

▣ የጥበብ እና የተረፈ ኤርምያስ መፅሐፍት ከክርስቶስ ልደት በፊት የተፃፉ መፅሐፍ ሆነው ሳለ ስለክርስቶስ ህይወት በጣም ጥልቅ በሆነ መልኩ መናገራቸውን እንዴት ነው የምትረዱት ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/1091

▣ ቃሌ vs አክሊል | Sola Scriptura | የውይይት ዳሰሳ

▷ https://t.me/ZANCHOR/1094

▣ ሁለት አይነት አበላሎች | Sacrament and Jon 6

▷ https://t.me/ZANCHOR/1117

▣ የሉተራኑ ጠንከር ያሉ አነጋገሮች

▷ https://t.me/ZANCHOR/1133

▣ የምትታየዋ vs የማትታየዋ ?

▷ https://t.me/ZANCHOR/1140

▣ ስምምነቱ ይዞት የሚመጣው ጣጣ - EO vs OO

▷ https://t.me/ZANCHOR/1144

▣ ፅድቅ በእምነት ብቻ vs ቅዱሳት ምስጢራት

▷ https://t.me/ZANCHOR/1153



በብዙ ይጠቀማሉና ይቀላቀሉን!

JOIN👇 and SHARE !!

@zaNchor
@zaNchor
@love_of_wisdom

መልህቅ

08 Dec, 14:07


Kyrie Eleison
Lord have mercy
ጌታ ማረን

መልህቅ

03 Dec, 20:19


The Colloquy of Montbeliard

Andreae: Paul writes, I Corinthians 10:16, “The bread which we break is a communication of the body of Christ.” He does not say, it is a communication of the remission of sins, but rather it is a communication of the body of Christ.

Beza: Prove it with a syllogism.

Andreae: Sayings of Holy Scripture do not need to be proven with a syllogism; they are rather believed on account of divine authority.

Beza: Make a syllogism.

Andreae: This is a novelty unheard of in any school, that testimonies of Scripture are proved with a syllogism.

Beza: Make a syllogism.

Andreae: The genuine meaning of the saying of Scripture should not be proved with a syllogism, but should rather be demonstrated from Scripture (152).


ቤዛ የካልቪን ሰክሰሰር የነበረ ሪፎርምድ ነው። አንድሬስ ደግሞ ሉተራን ነው። በምስራቋ ፍራንስ በሞንትቤላርድ ከተማ ተገናኙ። በቅዱስ ቁርባን ላይ ነበር ውይይታቸው። በእርግጥ ተወያይቶ መስማማትንና ወደአንድነት መምጣትን አቅደውና ተመኝተው ነበር የተሰባሰቡት።

ነገር ግን አንድኛው 'ዝም ብለህ አትጥቀስ! በል ሎጂኩን ሰርተህ አሳየኛ' ይላል ፤ ሌላኛው ደግሞ 'ያው መፅሐፍ ቅዱሴ ከዚህ በላይ ምን ፈለክ ?' ይለዋል። 😁

እናንተስ ምን ትላላችሁ ? ምንስ ትረዳላችሁ ? 😅

መልህቅ

01 Dec, 13:26


ፖፑ ኢንፋለብል ነው ወይስ አይደለም የሚለው በካቶሊክ እና በኦርቶዶክስ መሀከል ያለው ልዩነት ጥምቀት ፀጋን ያስተላልፋል በሚለው አስተምህሯቸው እንደሚለያዩ ያስረግጣል። አንዳችሁ ጥምቀት ፀጋን ያስተላልፋል ስትሉ እዛው ላይ ፖፑ ኢንፋለብል አይደለም የሚል ክሌም በመጨመር ነው ሌላችሁ ግን አያይ ነውንጂ በማለት ነው።

ቅዱሳት ምስጢራት ፀጋን ያስተላልፋሉ አያስላልፉም የሚለው ልዩነታችሁ በእምነት ብቻ አስተምህሯቹ እንደምትለያዩ ያስረግጣል። ምክንያቱም አንዳቹ እምነት ብቻ ስትሉ ጥምቀት ፀጋን አይሰጥም የሚል ክሌም በመጨመር ነው ሌላችሁ ግን አያይ ይሰጣልንጂ በማለት ነው።  🤦‍♂

እንዲህ ብሎ እኛን መውቀስ ወደ እነርሱ ስንገብጠው ከላይ መጀመሪያ ላይ ካለው ሙግት ጋር ፍፁም ተመሳሳይ ነው።

መቼ ነው ከዚህ አይነት የደከመ ሙግት ምትላቀቁት ? ughh


@zanchor
@zanchor

መልህቅ

28 Nov, 16:27


ብዙ ጊዜ ተደጋግሞ የሚነሳ አንድ አመለካከት ከተዋህዶ ወዳጆቻችን የሚነሳ አለ። ሉተራዊያን ከወንጌላዊያን ቤተ እምነቶች ይልቅ ለኦርቶዶክሳዊያን ይቀርባሉ የሚል። በርግጥ እንዲህ አይነት ጥያቄ ወይም አመለካከት የሚይዙ ሰዎች ግልብ እውቀት ያላቸው ወይም የሶሻል ሚዲያ ፖለቲካ የሚሰሩ መሰሪ ሃይማኖተኞች ናቸው። እነዚህ ሰዎች በቅዱስ ጥምቀትና በጌታ እራት ላይ ሉተራዊያን ያላቸው አቋም ከወንጌላዊያን የተለየ ስለሆነ ሉተራዊያን ከወንጌላዊያን ይልቅ ለኦርቶዶክሶች ይቀርባሉ የሚል ሙግት ነው። ያው የሉተራዊያን ነገረ መለኮትና የ ቤተ እምነቱ ኮንፌሽኖችን፣ ካታኪዝሞችና ክሪዶቹን በትክክል ያነበበ ሰው ቅዱስ ቁርባንና ቅዱስ ጥምቀት ብቻ ሳይሆን በሌሎች አስተምህሮ የበለጠገ ቤተ እምነት እንደሆነ ይረዳል።
ሌላ ጊዜ በስፋት የምናወራ ቢሆንም የሉተራዊያንና የተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን በቅዱስ ጥምቀትና በጌታ እራት ላይ ያላቸው አስተምህሮ አንድነት እንዳለው ሁሉ የተለያዩ አስተምህሮ በመካከላቸው አለ። ለዚህም ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ለፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ እንጂ የሉተራዊያንን የቅዱስ ጥምቀትና የጌታ እራት validity የምትቀበል ሆና አይደለችም።
ኮንፌሽናል ሉተራዊያን ለ ጤናማ ለሆኑ ወንጌላዊያን ትቀርባለች ወይስ ለተዋህዶ ትቀርባለች? የሚለውን ጥያቄ አንድ ባለ አእምሮ እንዲያመዛዝን የተወሰኑ ነጥቦችን ላቅርብ 😁

1. ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን ጽድቅ በእምነት ብቻ እንደሆነና አስተምህሮውም የቤተክርስቲያንን ህልውና የሚወስን ነው ብለው ያምናሉ።

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ጽድቅ በእምነት ብቻ ሳይሆን በመልካም ስራም ይጸደቃል ብለው ያምናሉ።

2. ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን ደኅንነት በጸጋው ብቻ ነው ብሎ ያምናሉ።

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ደኅንነት በጸጋ ብቻ ሳይሆን በሰዎች መልካም ስራ ጭምር ነው ብለው ያምናሉ።

3. ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን በቅዱሳት መጸሃፍት የበላይና የመጨረሻ ባለስልጣንነት መርህ ያምናሉ።

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን መጸሃፍ ቅዱስን በብቸኝነት መሳሳት አለመቻልና የበላይ ስልጣን መሆን አያምኑም። ይልቁኑ ከመፅሐፍቅዱሱ እኩል ስልጣን ያላት ልትሳሳት በማትችል ቤተክርስቲያን ያምናሉ።

4. ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን በ66ቱ ብቻ የቅዱሳት መጸሃፍት ቀኖና ይመራሉ ፤ እርሱንም ብቻ የአምላክ እስትንፋስ አድርገው ይቀበላሉ።

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን በየትኛውም ትውፊት ፈፅሞ የማይታወቀውን 81 የሆኑ የቅዱሳት መጸሃፍትን ቀኖና ይቀበላሉ።

5. ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን በ Ecclesiological Exclusivism አያምኑም።

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ከኛ በረት ውጪ ላሉት በጎች የመዳን መንገድ የላቸውም ብለው ያምናሉ።

6. ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን ወደ ሞቱ ቅዱሳን መጸለይ ፣ መዘመር ፣ በስማቸው ታቦት አሰርቶ መስገድን ከጣኦት አምልኮ ለይቶ አያዩም።

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ወደ ሞቱ ቅዱሳን መጸለይ ፣ መዘመር ፣ በስማቸው ታቦት አሰርቶ መስገድን የአምልኮአቸው ዋናው ማእከል አድርገው ያምናሉ።

7. ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን ስእል ሰርቶ በፊቱ መስገድ ፣ ስእሉ እንዲረዳቸው ወደ ስእሉ መጸለይ ፣ በስእሉ በኩል ለአምላክ ጸሎት ፣ ቅዳሴ ፣ ምስጋና ማቅረብ ይጠየፋሉ።

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ስእል ሰርቶ በፊቱ መስገድ ፣ ስእሉ እንዲረዳቸው ወደ ስእሉ መጸለይ ፣ በስእሉ በኩል ቅዳሴ ፣ ምስጋና ፣ ለአንዱ አምላክ እጣን ማጠን የአምልኮአቸው መካከለኛ አስተምህሮ ነው።

8. ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን ማርያም እንደማንኛውም ሰው እንደሞተች ፣ ወደፊትም እንደሌሎቹ በትንሳኤ ዘጉባኤ ካረፈችበት ትነሳለች ብለው ያምናሉ።

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ማርያም አስቀድማ ከሙታን መካከል የተነሳች ፣ ስጋዋም ከመበስበስ ተጠብቆ ትንሳኤ ሆኖላት ወደ ሰማይ እንደተወሰደች ያምናሉ።

9. ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን ቅድስት ማርያም የአዳም የሃጢአት ውርስ እንደነበራት ፣ በልጇ ደም እንደሌሎች ሰዎች ሁሉ እንደነጻች ያምናሉ።

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ማርያም የአዳም የውርስ ሃጢአት የለባትም ብለው ያምናሉ።

10. ወንጌላዊያንና ሉተራኖች በነገረ ክርስቶስ አንድ አካል ሁለት ባህርይ ብለው ኬልቄዶናዊ የነገረ ክርስቶስ አስተምህሮ ያምናሉ።

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ከሃዋሪያዊ የነገረ ክርስቶስ አንድ አካል ሁለት ባህርይ ከሚለው አስተምህሮ የተቆረጡ ናቸው።

11 ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን ማርያም ከሌሎች ፍጡራን የተለየች፣ በሰማይ በእግዚአብሄር ቀኝ የቆመች የሰማይና የምድር ንግስት፣ አስታራቂ አማላጅ፣ የምህረት ኪዳን የተገባላት የሚል አስተምህሮ ሰው ሰራሽ፣ አጋንንታዊ ጠያፍ ትምህርት እንደሆነ ያምናሉ፤

ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ማርያም ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ የሆነች፣ የሰማይና የምድር ንግስት፣ በእግዚአብሄር ቀኝ ቆማ ሰዎችን የምታማልድ፣ የምህረት ኪዳን ከልጇ የተቀበለች ናት ብለው ያምናሉ።


12 ወንጌላዊያንና ሉተራዊያን ክብርና ስግደት ለ እግዚአብሄር ብቻ እንደሆነ ያምናሉ፤
ተዋህዶ ኦርቶዶክሳዊያን ክብርና ስግደት ለእግዚአብሄር፣ ለማርያም፣ ለመላእክት፣ ለጻድቃን ለሰማእታት፣ ለመስቀሉ፣ ለታቦት፣ ለተቀደሱ ስፍራዎች፣ ለቤተመቅደስ እቃዎች ሁሉ ይገባል ብለው ያምናሉ።
እንዲህ እያልን ብዙ ነጥቦችን ማንሳት ይቻላል። ይህን በጥሩ ልቡና ላነበበ አንባቢ በቂ መልስ ይመስለናል! አስፈላጊ ከሆነ በጥልቀት ማውራት እንችላለን! 😁😁

መልህቅ

25 Nov, 15:17


ሀዋዝ ተገኝ ወደ ኦርቶዶክስ መመለሱ እውነት ሆኖ ተገኘ ማለት ነው። እውነት ለመናገር አዝኛለሁ! ቢያንስ ቢያንስ ምክንያቱ የዛኛውን ቤተእምነት አቋም መርምሮ ከዛም አሳምኖት እንደሆነና ሌላ ነገር እንሌለ ልገምት። ያም የሆነ ይህ በዝማሬዎቹ እጅግ በጣም ከተጠቀሙ ሰዎች መሀከል አንዱ ነኝ።

እዚሁ ቻነል ላይ ከለቀቅኳቸው በጣም ከምወዳቸው ሁለቱ መዝሙሮቹ ተጋበዙ! ቀጣዮቹን ሊንኮች ተጠቀሙ!


https://t.me/ZANCHOR/705
https://t.me/ZANCHOR/757

መልህቅ

24 Nov, 08:25


ከሥላሴ በኋላ 19ኛው እሁድ

የወንጌልና የመልእክት ክፍል ምንባባ


ማቴዎስ 25
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤
¹⁵ ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ፥ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ።
¹⁶ አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤
¹⁷ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ።
¹⁸ አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ።
¹⁹ ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው።
²⁰ አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ፦ ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ።
²¹ ጌታውም፦ መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።
²² ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ።
²³ ጌታውም፦ መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።
²⁴ አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤
²⁵ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ።
²⁶ ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፦ አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ፥ ካልዘራሁባት እንዳጭድ ካልበተንሁባትም እንድሰበስብ ታውቃለህን?
²⁷ ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፥ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር።
²⁸ ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤
²⁹ ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል።
³⁰ የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።

ሐዋርያት 18
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ከዚህም በኋላ ጳውሎስ ከአቴና ወጥቶ ወደ ቆሮንቶስ መጣ።
² በወገኑም የጳንጦስ ሰው የሚሆን አቂላ የሚሉትን አንድ አይሁዳዊ አገኘ፤ እርሱም ከጥቂት ጊዜ በፊት ከሚስቱ ከጵርስቅላ ጋር ከኢጣልያ መጥቶ ነበር፥ አይሁድ ከሮሜ ይወጡ ዘንድ ቀላውዴዎስ አዞ ነበርና፤ ወደ እነርሱ ቀረበ፥
³ ሥራቸውም አንድ ስለ ነበረ በእነርሱ ዘንድ ተቀምጦ በአንድ ላይ ሠሩ፤ ሥራቸው ድንኳን መስፋት ነበረና።
⁴ በየሰንበቱም ሁሉ በምኵራብ ይነጋገር ነበር፥ አይሁድንና የግሪክንም ሰዎች ያስረዳ ነበር።

መልህቅ

20 Nov, 18:29


ሰዎች #ሸልፈኛው ላይቭ ላይ ነው።

ከተፍ በሉና እንማር!

https://vm.tiktok.com/ZMhW51sM7/

መልህቅ

17 Nov, 08:58


ከሥላሴ በኋላ 18ኛው እሁድ

የእለቱ የወንጌልና የመልእክት ክፍል

ማቴዎስ 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ ኢየሱስም ከዚያ ወጥቶ ወደ ጢሮስና ወደ ሲዶና አገር ሄደ።
²² እነሆም፥ ከነናዊት ሴት ከዚያ አገር ወጥታ፦ ጌታ ሆይ፥ የዳዊት ልጅ፥ ማረኝ፤ ልጄን ጋኔን ክፉኛ ይዞአታል ብላ ጮኸች።
²³ እርሱ ግን አንዳች አልመለሰላትም። ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው፦ በኋላችን ትጮኻለችና አሰናብታት እያሉ ለመኑት።
²⁴ እርሱም መልሶ፦ ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ።
²⁵ እርስዋ ግን መጥታ፦ ጌታ ሆይ፥ እርዳኝ እያለች ሰገደችለት።
²⁶ እርሱ ግን መልሶ፦ የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም አለ።
²⁷ እርስዋም፦ አዎን ጌታ ሆይ፤ ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ አለች።
²⁸ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ፦ አንቺ ሴት፥ እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች።

1ኛ ዮሐንስ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ክርስቶስ ነው ብሎ በኢየሱስ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዶአል፥ ወላጁንም የሚወድ ሁሉ ከእርሱ የተወለደውን ደግሞ ይወዳል።
² እግዚአብሔርን ስንወድ ትእዛዛቱንም ስናደርግ የእግዚአብሔርን ልጆች እንድንወድ በዚህ እናውቃለን።
³ ትእዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነውና፤ ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም።
⁴ ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው።
⁵ ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማን ነው?

መልህቅ

16 Nov, 09:54


ስምምነቱ ይዞት የሚመጣው ጣጣ - EO vs OO

የሆነ ጊዜ ላይ ኦርየንታል እና ኢስተርን ኦርቶዶክስ ተስማሙ ማለት ይህ ግዴታ ፕሮማክስ መሆንን የሚያስገድድ ነው ብያቹ ነበር። ምክንያቴን እስኪ በተዋቀረ መልኩ ላስቀምጥ። ቀጣዩን አመክንዮ ተከተሉ!

P1 ➾ ኢስተርን ኦርቶዶክስ ኦርየንታል ኦርቶዶክስን በነገረ-ክርስቶስ ላይ ተሳስታለች በማለት አናቴማታይዝ በማድረግ ከክርስቶስ አካል የተለየች መናፍቅ አድርጋ ትቀበላለች። በዚህም አቋሟ ከ1000 አመታት በላይ ኖራለች ፤ ዛሬም ድረስ አለች።

P2 ➾ ኦርየንታል ኦርቶዶክስ ኢስተርን ኦርቶዶክስን በነገረ-ክርስቶስ ላይ ተሳስታለች በማለት አናቴማታይዝ በማድረግ ከክርስቶስ አካል የተለየች መናፍቅ አድርጋ ትቀበላለች። በዚህም አቋሟ ከ1000 አመታት በላይ ኖራለች ፤ ዛሬም ድረስ አለች።

P3 ➾ ከጥቂት አመታት ጀምሮ በሁለቱ ቤተእምነቶች መሀከል በተደረጉ ውይይቶች አማካኝነት የደረሱበት ስምምነት ልዩነቶቻቸው የቃላትና የአገላለፅ እንጂ የእምነት አቋም ልዩነት (on the Substance of the Faith) እንዳልሆነና በዚሁሉ አመታት ውስጥ ሁለቱም አንድና ተመሳሳይን አቋም ያምኑ እንደነበር ነው።

P4 ➾ ይህ ስምምነት የመጣው በጭራሽ አንድኛው አካል ተሳስቶ የነበረ መሆኑን አምኖ ከዛ ተቃራኒውን አቋም ለመቀበል ፍቃደኛ ሆኖ አይደለም። ይልቁኑ ሁለቱም ጎራ ሙሉ ለሙሉ ትክክለኛነታቸውን አጥብቀው ይዘው ነው ስምምነቱ ላይ የደረሱት።

C1 ➾ ሁለቱም ቤተእምነቶች አንድ አቋምና እምነት የነበራቸው ከሆኑና ልዩነታቸው የአገላለፅና የቃላት ብቻ ከነበሩ ከ1000 አመታት በላይ አንዳቸው አንዳቸውን በከፋ ምንፍቅና እንደተሳሳቱ አድርገው ማየታቸው ስህተት ነበር ማለት ነው።

C2 ➾ ሁለቱም ቤተእምነቶች አንዳቸው አንዳቸውን እንደተሳሳቱ አድርገው ማየታቸው ብቻ ሳይሆን በዚህ ላይ ቆመው አንዳቸው አንዳቸውን አናቴማታይዝ ማድረጋቸው ስህተት ነበር ማለት ነው። አናቴማው የወጣው አንዱ ሌላውን ተሳስቷል ብሎ ስለተቀበለና ስላመነ ብቻ ስለሆነ።

C3 ➾ ስለዚህ እነዚህ ቤተእምነቶች ወደአንድነት ከመጡ ከ1000 አመት በላይ አንዳቸው አንዳቸውን በከፋ ምንፍቅና እንደወደቁና እንደተሳሳቱ አድርገው ማየታቸውና በዛም ላይ ቆመው በቤተእምነት ደረጃ ማውገዛቸው ስህተት እንደነበር ሁለቱም ቤተእምነት መቀበል ግድ ይላቸዋል።

(አስተውሉ! በዚህ ሁሉ ዘመን ውስጥ አንዳቸው አንዳቸውን ሲያወግዙ አንዲቷ ፣ ቅድስት ፣ ሐዋርያዊት እና ኩላዊት ቤተ/ክ እያወገዘች እንደሆነ አድርገው ነው ራሳቸውን ይመለከቱ የነበረው።)

C4 ➾ ከ C3 በመነሳት አንዲት ፣ ቅድስት ፣ ሐዋርያዊት እና ኩላዊት የሚሏት ቤተ/ክናቸው እንደተሳሳተች ማመን ግድ ይላቸዋል።

__________________

እንዲያ ከሆነ ቀጥለን ሌላ ለእኛ ጠቃሚ የሆነ ሙግት ላቅርብ :

P1 ➾ የኦርየንታልም ሆነ የ
ኢስተርን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አንዲቷ ፣ ቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ/ክ ልትሳሳት እንደማትችል ያምናሉ ፣ ያስተምራሉ። ከፕሮቴስታንቱም የሚለያቸው መሠረታዊ አስተምህሯቸው ነው።

P2 ➾ ኦርየንታል እና ኢስተርን ኦርቶዶክስ ተስማሙ ማለት አንዲት ፣ ቅድስት ፣ ሐዋርያዊትና ኩላዊት ቤተ/ክን ናት የሚሏት ቤተ/ክናቸው ለ1000 አመታት ተሳስታ እንደነበር መቀበል ግድ ይላቸዋል። (C4)

C ➾ ኦርየንታል እና ኢስተርን ኦርቶዶክስ ተስማሙ ማለት ኢስተርንም ሆነ ኦርየንታል ኦርቶዶክስ ግዴታ መሆን አይቻልም።

__________________

እንግዲህ ያሉት አማራጮች ካቶሊክ ፣ የአሲሪያ ቤተ/ክ እና ታሪካዊ ፕሮቴስታንት ብቻ ናቸው። ያው
ችግሩ ግን ካቶሊኩንም ፕሮውንም.. ሁሉንም አውግዘው ስላሉ ባዶ ሜዳ እንደመቅረት አይደል ?

ብቸኛው መፍትሄ ታሪካዊው ፕሮቴስታንቲዝም ነው የሚሆነው። አለበለዚያ ሽሽታቸው ወደ ሮም ይሆንና በፊሎኩዌ ፣ በፓፓል ኢንፋለቢሊቲ ፣ በኢማኩሌት ኮንሰፕሽን ፣ በትራንሰብስታንሼሽን እና በሌሎችም ጭራሽ በማይቀበሏቸውና በሚያወግዟቸው አስተምህሮዎች ስር ራሳቸውን አስገዝተው ለመኖር ይገደዳሉ ማለት ነው። በአጭሩ ኮስቱ እጅግ ከባድ ነው።

ለዚህም ነው ሁለቱ ቤተእምነቶች ወደአንድነት መጡ ማለት ምንምኳ እኛ በዚህ ደስ ቢለንም ነገር ግን ሊሸሹት የማይችሉት መራር እውነት በጭራሽ ከዚያ ወዲያ ኦርቶዶክሳውያን ሆነው መቀጠል አለመቻላቸው ነው።

@zanchor
@zanchor

መልህቅ

14 Nov, 19:55


👆👆

እየተማርን ሰዎች 😁 ለዘመዶቻችን (ሸልፌክስ ጎረቤት ብሏቸዋል) አድርሱላቸው!

...

መልህቅ

14 Nov, 19:54


ሶሻል ሚዲያ ላይ ለሚሰሩ ጎረቤቶቻችን መረጃ ለመስጠት ያህል…ያው አብዛኛው የማንበብ ልምድ የለውም የሆነ ጊዜ ከሰማ እሱን እያመነዠገ፣ በየ ሶሻል ሚዲያው እንደ አዋቂ የሰማውን እያስተጋባ ከሚኖር የእውቀት አድማሳቸውን መረጃ በመስጠት ላስፋ ብዬ ነው 😁😁
1 የህጻናት ጥምቀት የሚቀበሉ የፕሮማክስ ቤተ እምነቶች ሉተራን፣ ፕሬስባይተሪያን፣ አንግሊካን/ኤፒስኮጳል፣ ሜቶዲስት፣ ፒውሪታንስ….
ስለዚህ ሁሌ አንዴ የሰማቹትን ከምታስተጋቡ ከሉተራን ውጪ እነዚህ ቤተ እምነቶች የህጻናት ጥምቀትና በጥምቀት በኩል ጸጋዎች እንደሚተላለፍ እንደሚያምኑ ከዛሬ ጀምሮ እወቁ😀
2 አፖስቶሊክ ሰክሴሽን የሚቀበሉ የፕሮማክስ ቤተ እምነቶች..።
አንግሊካን/ኤፒስቆጳል፣ የተወሰኑ ሜቶዲስቶችና የተወሰኑ ሉተራኖች።
በፕሮማክሱ አፖስቶሊክ ሰክሴሽን ያላቸው ቤተ እምነቶች የሉም ስትሉ እንዳልሰማችሁ ቀድሜ ነገርኳችሁ😁
3 ካልቪኒዝምን የሚቀበሉ የፕሮማክስ ቤተ እምነቶች….
ፕሬስባይቴሪያን፣ ኮንቲነንታል ሪፎርምድ፣ አንግሊካን/ኤፒስቆጳል በኮንፌሽን፣ የተወሰኑ ሜቶዲስቶች፣ ፓርቲኩላር ባፕቲስቶች
በየ ሶሻል ሚዲያ ያገኛችኋትን እውቀት ከሪፎርምድ ባፕቲስቶች ውጪ ያሉትን ሌሎችን እንግዳውስ ከዛሬ ጀምራችሁ እወቁ 😁

4 በሴቶች አገልግሎት፣ በነቢያትና በሃዋሪያት፣ በሌሎችም የጸጋ ስጦታ ላይ በኮንፌሽኖቻቸው መሰረት strict የሆኑ የፕሮማክስ ቤተ እምነቶች…..
ኮንፌሽናል ፕሬስባይቴሪያን፣ ኮንፌሽናል ሉተራን፣ ኮንፌሽናል ባፕቲስቶች፣ ኮንፌሽናል ኤፒስቆጳል፣ ኮንፌሽናል ኮንቲነንታል ሪፎርምድ ቤተ እምነቶች
ስለዚህ ከላይ የነገርኳችሁን ቤተ እምነቶች ከፔንቲኮስታል፣ ኢቫንጄሊካል በብዛት፣ ነን ዲኖሚኔሽናል ቤተ እምነቶች ጋር ለያይተህ ውዳሴህንና ነቀፋህን በተነሳው ርእስ ላይ አቅርብ ውዱ ጎረቤታችን 😀
5 ኮንሰርቫቲቭ ሉተራን ነህ ተብሎ አይጠየቅም ይልቁን ኮንፌሽናል ሉተራን ነህ? ነው የሚባለው😁
ማሳሰቢያ፤ ከላይ የጻፍከው እኛን ምን ይመለከተናል? ትለኝ ይሆናል ሎል አይጠቅምህም አንብበህ ማውራት ስለማትችል መንገዱን እያቃለልሁልህ ነው 😁
ደግሞ እቀበተ እምነት ስሰራ በእውቀት ማድረግ እፈልጋለሁ ለምትል አስተዋይ ጎረቤታችን እባክህን ኮንፌሽኖቻችንን አንብብልን😄

ከሉተራንና ከሉተር ያለፈ እውቀት ስለ ፕሮማክሱ እንዳስጨበጥኳችሁ ተስፋ አለኝ 😙

መልህቅ

13 Nov, 10:09


ከላይ ለለቀቅኩት ርዕሰ ጉዳይ ተጨማሪ ማጥሪያ ሀሳቦች

ከላይ ትላንት በለቀቅኩት ክታብ ውስጥ 'ልጁ ስለሚያወራው ነገር አያውቅም' ብዬ ስደመድም 'አልተረዳኸውም' ወይም 'በስህተት ነው የተረዳኸው' ለምትሉኝ በእርግጥም እንተደረዳሁት የሚያስረግጥልን በቪድዮው ውስጥ የተናገራቸውን አራት መሠረታዊ ነገሮችን ናቸው።

#አንደኛ ➾ ሉተር እና ሉተራኑ በ Invisible Church እሳቤ አያምኑም ፤ ከእነርሱም በኋላ ነው የመጣው ማለቱ። #ስህተት!

#ሁለተኛ ➾ የ Invisible Church እሳቤን የተቀበልነው እንደው በሶላ ስክራፕቱራ አማካኝነት የተለያየ አስተምህሮ እዚም እዛም በዝቶብን ሁሉም ቤተ/ክን ነኝ እያለ ሲያስቸግረን ሁሉንም ለማካተት ስንል የፈጠርነው እንደሆነ አድርጎ ስላስቀመጠው። #በጣም_ስህተት!

#ሶስተኛ ➾ ሉተርም ሆነ ሉተራኑ ልክ እንደሱ በ Ecclessiological Exclusivism እንደምታምን አድርጎ ማስቀመጡ (ከላይ በሶስተኛ ነጥብ ላይ የተቀመጠው ማለት ነው) #ይህም_ስህተት

#አራተኛ ➾ የInvisible Church ን እሳቤ ለመቃወምና ስህተት ለማድረግ ብሎ ቤተ/ክ የምትታይ እንደሆነች መሞገቱ #ይሄ_ደግሞ_የባሰበት_ስህተት

አራቱም ነጥቦች ጉዳዩን ፈፆሞ አለማወቁን እጅግ ጮኸው ይናገራሉ። እኔ ከላይ የ Visible እና Invisible Churchን ምንነት ተርጉሜ ከዛም Distiniction ኡም ምን ላይ እንደቆመ ያብራራሁትን ማብራሪያ ተመልክታችሁ እርሱ ደግሞ እንዴት ተረድቶት እንዳስቀመጠው ጎን ለጎን አስቀምጣችሁ ተመልከቱ። ጨርሶ አይገናኙም።

ታድያ ግን አንዲቷ ቅድስት የሐዋርያት ቤተ/ክርስቲያን የቷ ነች ? በአጭሩ መልሱስኪ ? ለምትሉን ..

አንዲቷ ቅድስት የሐዋርያት ቤተ/ክ (in the strictest sense) በእርግጥም የማትታየዋ ቤተ/ክ ነች። ይህች የማትታየዋ ቤተክርስቲያን ግን በሚታዩ ሰዎች ህብረት መሀከል በሚሰበከው ወንጌልና በቅዱሳት ምስጢራት አገልግሎት ምልክትነት በተለያዩ ቦታዎች Instantiate ተደርጋለችና በዚህ በእርግጥም የምትታይ ሆና ትታወቃለች። ስለዚህ እነዚህ ሁለቱ Marks of the Church ባሉበት ሁሉ እውነተኛዋ ያቺ አንዲቷ የጌታ ቤተ/ክ በዛ እንዳለች እርግጠኛ መሆን እንችላለን።

የምንቃወመው መሠረታዊ ነገር አንዲትን የምትታይ ህብረት ጠቁመን አንዲቷን ቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ/ክን በዛች ህብረት ብቻ አጥረንና ገድበን ማስቀመጥን እና በተጨማሪም በዛች ባለንባት በምትታየዋ ህብረት ብቻ ገድበን ባጠርነው አጥር ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሁሉ ጠቅልሎ የዳኑ የእግዚአብሄር ህዝቦች አድርጎ ማሰብን ነው።

@zaNchor
@zaNchor

መልህቅ

10 Nov, 09:29


የዕለተ እሁድ የወንጌል እና የመልዕክት ክፍል


ማቴዎስ 13
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴⁴ ደግሞ መንግሥተ ሰማያት በእርሻ ውስጥ የተሰወረውን መዝገብ ትመስላለች፤ ሰውም አግኝቶ ሰወረው፥ ከደስታውም የተነሣ ሄዶ ያለውን ሁሉ ሸጠና ያን እርሻ ገዛ።
⁴⁵ ደግሞ መንግሥተ ሰማያት መልካምን ዕንቁ የሚሻ ነጋዴን ትመስላለች፤
⁴⁶ ዋጋዋም እጅግ የበዛ አንዲት ዕንቁ በአገኘ ጊዜ ሄዶ ያለውን ሁሉ ሸጠና ገዛት።


1ኛ ቆሮንቶስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በእግዚአብሔር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ሊሆን የተጠራ ጳውሎስ ወንድሙም ሶስቴንስ፥
² በቆሮንቶስ ላለች ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን፥ በክርስቶስ ኢየሱስ ለተቀደሱት፥ የእነርሱና የእኛ ጌታ የሆነውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በየስፍራው ከሚጠሩት ሁሉ ጋር ቅዱሳን ለመሆን ለተጠሩት፤
³ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።
⁴ በክርስቶስ ኢየሱስ ስላመናችሁ በተሰጣችሁ በእግዚአብሔር ጸጋ ምክንያት ሁልጊዜ ስለ እናንተ አምላክን አመሰግናለሁ፤
⁵-⁶ ለክርስቶስ መመስከሬ በእናንተ ዘንድ እንደ ጸና፥ በነገር ሁሉ በቃልም ሁሉ በእውቀትም ሁሉ በእርሱ ባለ ጠጎች እንድትሆኑ ተደርጋችኋልና።
⁷ እንደዚህ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መገለጥ ስትጠባበቁ አንድ የጸጋ ስጦታ እንኳ አይጎድልባችሁም፤
⁸ እርሱም ደግሞ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትሆኑ እስከ ፍጻሜ ድረስ ያጸናችኋል።
⁹ ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው።

መልህቅ

10 Nov, 07:10


Recommendation

#የየሹዋ_አፖለጀቲክስ_ሚኒስትሪ ከክርስትና እምነት አንጻር ደርዛቸውን የጠበቁ ስነ-መለኮታዊ ፍልስፍናዊ ፤ አመክንዮአዊና ታሪካዊ ጽሑፎችን የሚያቀርብ ፤ በክርስትና ላይ የሚነሱ የተቃውሞ ሀሳቦችንና የኑፋቄ ትምህርቶችን የሚመክት ፤ የሌላውን እምነተ መርህ ከሎጂክና ከታሪካዊ ዳራዎች አንጻር የሚመረምር ሚንስትሪ ነው።


ትጠቀሙበታላችሁና ቴሌግራሙንም ዩቱዩቡንም ተቀላቀሉት።

➾ @Yeshua_Apologetics_Ministry
➾ https://youtube.com/@yeshuaapologetics?si=10wK_60IZloSe-ZI

...

መልህቅ

04 Nov, 15:31


...

እስኪ እቺን 👆 ቮይስ አድምጧት። ከሰባት ወር ምናምን በፊት ነበር የለቀቅኩት። ከዛ ደግሞ በስፋት ለመረዳት ከታች ያለችውን ሊንክ በመጫን ለማንበብ ሞክሩ።

ከሰሞኑን ጉዳዮች አንፃር ጥሩ ነገር ይሰጣቹሀል። በዚህም መንገድ መሞገት የጀመርነው ዛሬ እንዳልሆነም እንድትረዱ ይረዳቹሀል።

https://t.me/ZANCHOR/955

...

መልህቅ

04 Nov, 15:29


ከቤተ-እምነታችሁ ለተነጠለ እና ሀሳብ ላይ ብቻ ላለ ፕሮቴስታንቲዝም አትቁሙ! እርሱ የለምና!

ከዚህ በፊት በፅሁፍ ባቀርበውም በዚህ መልኩ ደግሞ ማስቀመጡ ለብዙዎቻችሁ ሊጠቅም የሚችል ይሆናል በማለት ነው!

#share
@zanchor
@zanchor

መልህቅ

02 Nov, 12:28


የሉተራኑ ጠንከር ያሉ አነጋገሮች

ብዙ ጊዜ ኦርቶዶክስ ወንድሞቻችን እነዚህ ክፍሎች ላይ መሠረት በማድረግ ሙግት ሲያዋቅሩ ይሰማል። ሙግታቸውም ክፍሎቹ ላይ ሉተራኑ በቅዱሳት ምስጢራት ላይ  ከእነርሱ የተለየ አቋም ያላቸውን በጠነከሩ አገላለፆችን በመጠቀም የሚያወግዝ ስለሆነ እዛ ላይ መሠረት በማድረግ ከዛም እነዚህን ወደሪፎርምድ ካምፕም ቤተእምነቶች ፕሮጀክት በማድረግ እነርሱንም የሚመለከት በማድረግ በመሀከላችን በዚህ ልኬት ልዩነት እንዳለና አንድነትን ክሌም ልናረግ እንደማንችል ለማስረገጥ ነው።

ከላይ ላለው ሙግታቸው ግን አራት ነጥቦችን መረዳት ከበቂ በላይ መልስ ይሆናል።

1 ➾ እነዚህን የጠነከሩ ንግግሮች ሙሉ ለሙሉ መረዳትም ሆነ መፍታት ያለብን ፀሀፊዎቹ ከፃፉበት ከዛ ታሪካዊ አውድ አንፃር ብቻና ብቻ ነው።

እነዚህ ፅሁፎች የተፃፉት ሪፎርሜሽኑ ከፈነዳ በኋላ ሉተር በዛ ጊዜ ለነበሩ ተቃዋሚዎቹ ነው። በአጭሩ በታሪኩ ውስጥ ሶስት አካላት አሉ። ሮማ ካቶሊክ ፤ ማጄስቴሪያል ሪፎሮመርስ ርና ራዲካል ሪፎርመርስ። እነዚህን ሶስቱን መቀላቀል የለብንም። እንደሚታወቀው በዚህ ጊዜ የሉተርና የእርሱ ፈለግ ተከታይ የሆኑት ሀዳስያን (Magesterial1 Reformers) ተቃዋሚዎች ካቶሊኮች ብቻ ሳይሆኑ በሌላ ጥግ ደግሞ ራዲካል ሪፎርመርስ ጭምር ናቸው። ራዲካል ሪፎርሜሽኑ በጠቅላላው በአናባፕቲስቶች ሊወከል ይችላል። የአናባፕቲስት እንቅስቃሴ Monolitic ሳይሆን በContinental Europe የተነሳና የተለያዩ አቋምና እምነት ያላቸውን አካላት የሚመለከት ነው። እነዚህም በ Ecclesaiological, Eschatological እንዲሁም Political ጉዳዮች ላይ ከሮም ጋር ብቻ ሳይሆን ከMagesterial Reformers ጋር የተጣሉና የተጣበዩ ነበሩ። ከተጠቀሱት ጉዳዮች በዘለለና ባለፈ መልኩ ደግሞ የዚህም ምክንያቱ በአስተምህሮ መለያየታቸው ብቻ ሳይሆን ገና ከጅምሩም እነርሱ ካሰቡት የተሀድሶ እሳቤ ጋር ፍፁም የሚቃረኑና የሚያሰናክሉ ናቸው ብለው ስለሚያስቡ ነበር። ሉተር Anabaptists, Schwenckfeldians, New Arians, and Anti-Trinitarians ብሎ በዝርዝር ያስቀምጣቸዋል።

ስለዚህ የመጀመሪያው ነጥብ እነዚህን ክፍሎች ስንተረጉም ከሞላ ጎደል ያን ሁሉ ውግዘትና ቅዋሜ የደረሰባቸው እነማን ናቸው የሚለውን ባሉበት ታሪካዊ አውዱ ስንመለከት ከላይ የተጠቀሱት ራዲካል ሪፎርመርስ ሆነው እናገኛለኝ። እነርሱን ደግሞ ሉተርና ሉተራኖች ብቻ ሳይሆኑ የሪፎርምድ ካምፕ ቤተእምነት አምድ የሆኑት Mageterial Reformers ራሳቸው ጭምር ናቸው።

ይህ ማለት በሉተራኑ እና በሪፎርምዱ መሀከል ልዩነት የለም ማለት አይደለም። እንዲሁም እንደዚህም አይነት ጠንካራ አገላለፆቾች ለእነርሱም አይጠቀሙምም ማለት አይደለም። ነገር ግን ሁሉን በየአውዱ መፍታት አስፈላጊ መሆኑን ለማስቀመጥ ነው።

2 ➾ የፀሀፊዎቹ ባህሪ ከግምት መግባት አለበት። በተለይ በኮንኮርዱ የካተቱ 98 - 99 % የሚሆኑትን እነዚህን አገላለፆች ከሉተር እንደማግኘታችን ከሉተር ማንነትና አፕሮች አንፃር እነዚህን መመልከት እጅጉን አስፈላጊ ነው። ሉተር እጅግ ፕለሚካል አፕሮች የነበረውና በጊዜው ከሚቃወማቸው ሰዎች አንፃር ከነበረው ከስነመለኮታዊና ፖለቲካዊ ልዩነት የተነሳ Theological Rhetorics አብዝቶ የሚጠቀምና በዚህም ምክንያት ጠንካራ አገላለፆችን ያሉት ሰው ነው። ይህንን እሱ ላይ ከተሰሩ ባዮግራፊዎች መረዳት እንችላለን።

ከዚህ በዘለለ ሌላው ሉተር በስነመለኮቱ አለም ሲስተማቲሺያን እንዳልነበርም መረዳት አለብን። ይህም ማለት ምንምኳ ስነመለኮት ተማረና በዩኒቨርሲቲም የተከበረ አስተማሪ የነበረ ቢሆንም ግን ብዙ ሊቃውንት እንደሚያስቀምጡት በአካዳሚክ ዘርፉ More of Mystical Theology ላይ የሚያዘነብል እንደሆነ ይነገርለታል። ለዛም ነው ከሉተርና በሱ ጊዜ ከነበሩ አንዳንዶች ሰዎች ይልቅ የሉተራኑን አቋም ከሱ የተቀበሉ ወይም ቀጥለው በመጡ ሉተራን ሊቃውንት (እንዲሁም ስኮላስቲክስ) እጅጉን በጠነከረና በተብራራ መልኩ ንፅፅራዊ በመሆነ መንገድ ያስቀመጡት። ለዚህ እንደ Martin Chemitz, Johan Gerhard ... ያሉትን Divines መጥቀስ እንችላለን። ይህ ማለት ምንምኳ ሉተር አስፈላጊ ጉዳዮች ላይ መሠረትን ቢጥልም ነገር ግን እርሱ በደንብ ቆይቶ ሳያስብባቸውና ሳያጠራቸው ያለፋቸው ጉዳዮች ቀጥለው በመጡ ሊቃውንት በጥልቀት ተሰርቶባቸው እናገኛለን። ከዚህ ከአንፃር እነዚህን አገላለፆች ከነበራቸው ታሪካዊ አውድ አንፃር ከመርጎም በዘለለ እነርሱ ላይ ብቻ ቆመን ኦርቶዶክስ ወንድሞቻችን ወደደረሱበት ድምዳሜ መድረስ በጭራሽ አለመቻላችንን መረዳት አለብን። Non-Sequiter Fallacy ይሆንብናል።

ይህም ወደ ቀጣዩ ሶስተኛ ነጥብ ያመራናል።

3 ➾ ከላይ እንዳልኩት ሉተርን የተኩ ሉተራን ሊቃውንት ከሉተርና ከእርሱ ጋር ከነበሩ ሊቃውንት ላይ ቆመው ከእነርሱም ደግሞ ይልቁን በጠለቀና በጠነከረ መልኩ አቋማችንን ያስቀመጡ ናቸው። ከእነዚህም አልፈን ደግሞ የ 17ተኛ ክፍለዘመን ሉተራን ስኮላስቲኮችንም መመልከት ግድ ይለናል። በእነዚህ ሊቃዎንት መሀከል የምመለከተው ነገር ምንምኳ ለአናባፕቲስቱ እንቅስቃሴ ልክ እንደነሉተር አብረው የሚያወግዟቸውና የሚቃወሟቸው ቢሆኑም ነገር ግን በሪፎርምድ ካምፕ ውስጥ ያሉትን ቤተእምነቶች በጭራሽ ከራዲካል ሪፎርመርስ ጋር በአንድ ጫማ ውስጥ አያስቀምጧቸውም። ይልቁኑ ምንምኳ በመሀከላችን ልዩነቶች ቢኖሩም እንዲሁም ደግሞ ልዩነቶቹም ዳውን ፕሌይ መደረግ የሌለባቸውና እጅግም ጠጣር መሆናቸውን አጥብቀው ቢቀበሉም ነገር እነዚህ ልዩነቶች ከእግዜር መንግስት አውጥቶ አልዳኑም የሚያስብሉ አድርገው አይመለከቷቸውም። በአጭሩ የሚያለያዩንን ጉዳዮች Theological Triage ሲሰሩላቸው በጭራሽ 1st Order አያደርጓቸውም። ይልቁኑ ለእነርሱ እጅግ ከባድ Hetrodoxy ናቸው። ስለዚህ እነዛ አገላለፆች ካላቸው ታሪካዊ አውድ አንፃር ብቻ የሚመለከቷቸው ናቸው እንጂ የቤተእምነት አቋም አድርገው የሚያስቀምጧቸው አይደሉም። ይህን መረዳት እጅጉን አስፈላጊ ነው።

ስለዚህ ሶስተኛው ነጥቦ በአጭሩ ኮንኮርዱ ራሱ ሲተረጎም እንደፈለጉ ከየትም እየመጡና ወደፈለጉት እያዞሩ የሚተረጎም ሳይሆን ኮንኮርዱን የእምነት መግለጫቸው አድርገው በተቀበሉና ባብራሩት ማህበረሰብ ውስጥ ባለው አቀባበልና በዛም የትርጓሜ አጥር በኩል ብቻ የሚተረጎም መሆን አለበት። ስለዚህ የኦርቶዶክሱ ወቀሳና የሙግት አካሄድ ይህን ያላማከለ ነውና ተቀባይነት አይኖረውም።

4 ➾ የመጨረሻው ነጥብ በቅዱሳት ምስጢራት ላይ ከተቀመጡት እነዚህ አገላለፆች ውስጥ ቅዱስ ቁርባንን በሚመለከት የተቀመጠው ጭራሹኑ የሪፎርምድን ካምፕ ቤተእምነት አቋም የሚመለከት አለመሆኑ ነው። በአቋም ደረጃ ራሱ ኮንኮርዱ ስህተት ነው ከሚለው አቋም ፍፁም የተለዩ ናቸውና። ይህንንም ከግምት እናስገባ። ይህ ማለት ግን አሁንም በሁለቱ መሀከል ልዩነት የለም ፤ ልዩነታቸውም ተራ ነው ማለት አይደለም። በእርግጥም ጠጣርና የለያያቸው ልዩነት አለ። ነገር ግን ስለዚህ ስፔሲፊክ ክፍል ስናወራ ሪፎርምዶችን አልመለከትም።

በአጭሩ ኦርቶዶክስ ወንድሞቻችን ልዩነቶችን በማሳየት እኛን ስህተት ለማድረግ የሚሄዱት ሩቅ መንገድ እንደው ልፉ ሲላቸውንጂ እኛ ላይ የጠጠርን ውርወራ ያህልኳ አቅም የሌለው የሾቀ የሙግት አካሄድ ነው። በዚህ በጭራሽ ልባችሁ አይውረድ።

@zanchor
@zanchor

መልህቅ

02 Nov, 12:27


ተመልከቷቸውስኪ 😁

ከዛ ከታች ያለውን ያንብቡ!

መልህቅ

01 Nov, 11:57


እቺን ተጋበዙልኝስኪ! ወሳኝ ውይይት ነች! 😁

https://vm.tiktok.com/ZMhCNQNo6/

መልህቅ

30 Oct, 09:04


ወርሀ ሪፎርሜሽኑ እንዲህ እንዲያ እያለ ተገባዶ ይኸው ሊያልቅ አንድ ቀን ብቻ ቀረው። 😁

በሚያሳዝን ሁኔታ በዚህኛው አመት ምንም አላልኩበትም። ያው ስለሪፎርሜሽኑ ስናነሳ የምናወሳቸው ብዙ ነገሮች አሉ። የተሀድሶው Formal Cause እና Material Cause ተደርገው የሚቆጠሩት ቀንደኞቹ ጉዳዮች ሶላ ስክሪፕቱራ እና ሶላ ፊዴ ቢሆኑም እነርሱ ላይ ቆሞ ለተሀድሶው መከሰት ምክንያት የሆኑ ሌሎች ብዙ ጉዳዮችም አሉ።

ተሀድሶው ወደኋላ የምንመለከተው ብቻም ሳይሆን አሁን ላይም የሚያስፈልገንም ጭምር ነው።

ስለዚህ ምን አሰብኩ መሰላችሁ ነገ Oct 31 ሰብሰብ ብለን ከሁለቱ መሰረታውያን ጀምረን ሌሎቹንም በምንችለው እያነሳን እያወጋን እናከብራለን። አሁን ላይ ካለንበትም ሁኔታ አንፃር እንዴት መቀጠል እንዳለበትም እንመካከራለን።

3 ሰአት እንጀምራለን! በተቻለ አቅም ለመገኘት እና ሌሎችም ስንዲገኙ ሼር ለማድረግ ሞክሩ። ያው ጥያቄዎችንም ለመቀበል ክፍት ስለሆነ ስፔሻሊ ኦርቶዶክስ ወንድሞች በአክብሮት ተጋብዛቹሀል። 😁

መልህቅ

25 Oct, 10:33


መልህቅ pinned «»

መልህቅ

23 Oct, 13:52


ሁለት አይነት አበላሎች - Two kinds of Eating

ትላንት የለቀቅኩትን ጥያቄ ያነሳሁት በመሠረታዊነት የዮሐንስ ምዕራፍ 6 ክፍል ብዙ ጊዜ ከቅዱስ ቁርባን ጋር በተያያዘ በሪፎርምድ ካምፕ ባሉ ቤተእምነቶች የሚነሳ ክፍል ስለሆነ ነው። ወይም Spiritual Presence ን የሚቀበሉ ቤተእምነቶች (Anglican, Presbiterian and Traditional Baptist) ከሉተራውያንና ከጥንታዊ ቤተ/ክናት ጋር በምስረታው ቃል ላይ በሚያደርጉት ውይይት ውስጥ ብዙ ጊዜ የሚነሳ ክፍል ነው።

ዮሐንስ 6 ላይ ኢየሱስ 'ስጋዬን (እንጀራውን) የበላ የዘላለም ህይወት አለው' ሲል ሉተራኖች ከሪፎርምድ ቤተእምነቶች ጋር በመስማማት ይህንን Spiritual Eating ይሉታል። ይህም መብላት እምነትን በግዴታነት ከግምት ያስገባ ነው። ወይም በእምነት አፍ መብላትን የሚናገርና ጥቅሙንም የሚያስቀምጥ ነው።

ወደ ቅዱስ ቁርባን ስንመጣ የሪፎርምድ ካምፑ አቋም ህብስቱ በእምነት ካልተበላ በስተቀር የጌታ ስጋ እንዳልተበላ እና ይልቁኑ ሳይኑ ብቻ እንደተወሰደ ነው። ስለዚህ የምስረታው ቃል ላይ 'ውሰዱና ብሉ' ተብሎ የታዘዘው የአበላል አይነት በራሱ በእነርሱ አረዳድ በዮሐንስ 6 ላይ ካለው የብሉ ትእዛዝና አበላልም ጋር ተመሳሳይ ነው።

ነገር ግን ቀጥዬ የጠቀስኩት የ1 ቆሮ 11 ክፍል እንደሚለው ከሆነ ሳይገባቸው የጌታን እንጀራ የሚበሉትን ይወቅስና ፍርድም እንደሚመጣባቸው ያስጠነቅቃል። አስተውሉ! በዚህ ክፍል ውስጥ ጳውሎስ የጌታን ስጋ (እንጀራ) ባለመብላታቸው ምክንያት ፍርድ እንደሚመጣባቸው አይደለም እየተናገረ ያለው። ይልቁኑ የጌታን ስጋ ሳይገባቸው በመብላታቸው ፍርድ እንደሚመጣባቸው እንጂ። እንዲሁም ህብስቱን ብቻ (ወይም ሳይኑን ብቻ) ያለእምነት መብላት ፍርድን እንደሚያመጣም አይደለም እያወራ ያለው።

ስለዚህ ከተጠቀሱት ሁለቱ ክፍሎች ግዴታ የምንደመድመው ነገር ሁለት አይነት አበላሎች እንዳሉ ነው። እነርሱንም በዮሐንስ 6 ላይ ያለው አበላል በእምነት አፍ በልቶ ፤ ጥቅሙንም (The Efficacy) መቋደስ ነው። ይህም ከላይ እንዳልኩት Spiritual Eating ይባላል። ሁለተኛው ደግሞ በ1 ቆሮ 11 ላይ እንዳለው ያለ አበላል ሲሆን ፣ እርሱም የጌታን ስጋ (እንጀራ) ያለአግባብ መብላት ነው። ልክ እንደ ዮሐ 6ቱ ይህም መብላት አለው። ነገር ግን ያኛው የዘላለምን ህይወት የግድ ሲያመጣ ፤ ይኸኛው ግን ያለአግባብ ነውና ፍርድን የሚያመጣ መብላት ነው። ይህንን ደግሞ እኛ Sacramental Eating ብለን እንሰይመዋለን። በምስረታው ቃል መሠረት ይህ የክርስቶስን ስጋ በአፍ ከቶ መብላትን (Oral Eating or Eating by mouth) የሚመለከት ነው። ጥያቄው ይህን እንድታወጡና እንድትረዱ በማሰብ የተጠየቀ ነበር።

ከቅዱስ ቁርባን አንፃር ህብስቱ በእምነት ሲበላ እንደሚገባ ተበልቷልና ወይም የሚገባው በልቶታልና የዮሐንስ 6ቱ Spiritual Eating አብሮ እንደሚካሄድ ወይም እንዳለ ሪፎርምድ ቤተእምነቶችም ፣ ሉተራኑም የሚስማማበት ነጥብ ነው። በአፍ ተበልቶል ወይስ አልተበላም የሚለው ግን ይለያያቸዋል።

ይህን ያህል ካልኳቹ እስኪ የሆነ ቀን ደግሞ በሉተራኑ እና በሪፎርምዱ የጌታ ራት አንድነት እና ልዩነት ላይ ላይቭ ገብተን እንማማራለን።

መልህቅ

17 Oct, 10:09


ለጥንቃቄ ያህል ..

አይደለም ኦርቶዶክሶችና ታሪካዊ ፕሮቴስታንቶች ቅሩና ጴንጤዎች የሆናችሁንኳ ሳትቀሩ ኤፍሬም ባለጊዜ የተባለውን ወንድም እንደው ጭራሹኑ ባትሰሙት የሚል ወንድማዊ ምክር አለኝ .. በተለይ የሰሞኑን የፍቃድ ምናምን ጉዳይ ላይ ላሽ በሉት በቃ ..

ምንም ፐርሰናል የሆነ ነገር ኖሮኝ ሳይሆን እውቀቱም ሆነ አቀራረቡ የማይመጥናችሁ እና ያልተገባ ስለሆነ ብቻ ነው።

በሉ ሰላም ሰንብቱ! 😁

መልህቅ

12 Oct, 18:45


ተመልከቷት እስኪ ላመለጣችሁም ላላመለጣችሁም ክሽን ያለች አሪፍ መልስ ነች 😁

https://vm.tiktok.com/ZMhU9Ygu6/

መልህቅ

08 Oct, 12:35


ሁለት ግብዣ .. 😁

➭ The Worst argument against Sola Scriptura

ብዙ ሙግት ከ possible / imposible ወደ የ Probability ሙግት መውረዱ ራሱ ትልቅ ነገር ነው። ኦርቶዶክስ ወንድሞች እስኪ መጥፎ የሚባሉትን ሙግቶች ከትሬንት አድምጡ።

https://youtu.be/1fkbJYcLRyY?si=KPa0FerOCbDYpA1T

➭ Translation and Sola Scriptura

ጋቪንና ትሬንት በቅዱሳት መፅሐፍት ትርጓሜ ላይ ወንድም አክሊል ያነሳውን ተመሳሳይ ጥያቄ ተጠይቀው የመለሱትን መልስ ተጋበዙ። በተለይ የትሬንትን መልስ ሙሉውን ደጋግማችሁ አድምጡት። የአክሊልን የትርጓሜ ሙግት እኛ ብቻ ሳንሆን ካቶሊኩም የሚቃወመው ነው።

https://youtube.com/clip/UgkxxvKGxWnb1nYF0Y_VIKsdCQYklCvdCxsb?si=NvLPpOaAEDWOujeB

..

መልህቅ

02 Oct, 13:42


ሁላችንም ባለንበት ልንቀበለው እና ልንሰራበት የሚገባን ይመስለኛል። ዙሪያ ገባውን ስንመለከት የሚከብድና የማይሆን ይመስላል። ግን ከእግዚአብሄር ጋር አሁን ላይ በወንጌላውያን መሀከል ያለችው ቤተ/ክ ወደኋላ (ቢቻል ወደጥንቷ ቤተ/ክ ፤ ቢያንስ ወደታሪካዊ ፕሮቴስታንት) በመመለስ በራሷ ላይ መስራት ያለባት አንዱ ትልቁ ስራዋ ነው ብዬ አስባለው።

Semper Reformanda !


https://www.youtube.com/watch?v=EeM5u4A6KTY

መልህቅ

29 Sep, 22:24


“We affirm that inspiration, strictly speaking, applies only to the authographic text of Scripture, which in the providence of God can be ascertained from available manuscripts with great accuracy. We further affirm that copies and translations of Scripture are the Word of God to the extent that they faithfully represent the original.
We deny that any essential element of the Christian faith is affected by the absence of the autographs. We further deny that this absence renders the assertion of Biblical inerrancy invalid or irrelevant.”
Article X of The Chicago Statement on Biblical Inerrancy

መልህቅ

27 Sep, 22:35


Discussion on Sola Scriptura with Dr Naol and others

መልህቅ

26 Sep, 11:53


እነሆኝ የእምነት ድንጋጌው። አንቀጽ 1 ላይ ያለውን እያነበባችሁ audioውን ብትሰሙ አሪፍ ይመስለኛል ሎል

መልህቅ

26 Sep, 11:53


የመጨረሻው ክፍል ይህ ነው። ብዙም ደቂቃ ስለማይወስዱ በአንዴ ጭጭ ብታደርጓት ብዬ ነው በአንዴ ሁሉንም መልቀቄ ሎል

መልህቅ

26 Sep, 11:53


ቀጣዩ ማለትም ሶስተኛው ክፍል 😁

መልህቅ

26 Sep, 11:53


ሁለተኛው ክፍል ይህ ነው @christiandogmatics

መልህቅ

26 Sep, 11:53


ሰላም ወዳጆች
ሰሞኑን በሶሻል ሚዲያ በብዛት ስሙ ሲነሳ የነበረው የዌስትሚኒስቴር እምነት ድንጋጌ ላይ በ አንቀጽ 1 ላይ ማብራሪያ ነገር ሰርተንላችኋል። እስቲ audio መስማት ለምትወዱ 4ክፍል ብቻ ናት ስሟት lol
በክፍል አንድ necicity of scripture እና inspiration of scripture ላይ፤ በክፍል 2 authority of scripture እና sufficiency of scripture ላይ፤ በክፍል 3 ደግሞ perspecuity of scripture, translation of scripture, interpretation of scripture፣ finality of scripture ላይና በመጨረሻው ክፍል ደግሞ የዌስትሚኒስቴር doctrine of scripture ን ከአጠቃላይ sola scripture አስተምህሮ አንጻር ለማየት ጥረት አድርጌአለሁ። ይህ የመጀመሪያው ክፍል ነው

መልህቅ

22 Sep, 11:57


' 'Let him be anathema' Proofs the infallibility of Church. '

እሺ አሁን ይሄ ምንድን ነው የሚባለው ?
እውነት እኔ ለእርሱ ጨነቀኝ! ወንድማችን ያለውን ደጋግሞ በደንብ ሊያስብበት ይገባል እላለሁ!

ጌታ ወደ እውነት ሁሉ ይምራው!

መልህቅ

21 Sep, 12:07


...

ስለዚህ ዲቤት ምን ታስባላችሁ ? ክሬግ ወይስ ሂጃብ ?

መልህቅ

20 Sep, 03:47


...

የትላንትናው ዲቤት አበሳጭቶን መጥተን ይኸው Straight 6 ሰአት በላይቭ ተወተነዋል ... እኛስ ወጣልን እንጃ ላመለጠው 😭

ምን ያልተወራ አለ እድሜ ለዘመዶቻችን 😁😂

...

መልህቅ

18 Sep, 15:58


የሚገርማቹ አጅሬ የጠቀሰው ዳንኤል ዋላስ ከላይ ከተጠቀሰው ግሩደም በባሰ መልኩ ስላሉት Variants ሲያነሳ 'ቢያንስ ቢያንስ 99.8% ምንንም የማይነካ ነው' ፤ 'በእነዚህም ልዩነቶች አደጋ የሚደርስበት ምንም ዶክትሪን የለም' ብሎ ያስቀምጠዋል። ከራሱ አፍ ለማድመጥ ከታች ያለውን ሊንክ ተጠቀሙ!

ምናልባት ይህ ምን ማለት እንደሆነ ለማትረዱ በጣም አማርኛ ለማድረግ ባጭሩ ይህ ማለት የሐዋርያቱ የራሳቸው Original Text በእጃችን ላይ ነው ያለው ማለት ነው።

ስለዚህ Inerrancy ማለት ሐዋርያቱ ያስተላለፉት መልእክት ውስጥ አንዳች የእውነት መዛባት የለም ፤ ስህተት አልባ ነው ማለት ከሆነና መታወቅና ከግምት መግባት ያለባቸው አጠቃላይ Corollaries ከጎኑ አስቀምጠን በእጃችን ላይ የያዝነው ትርጓሜ በእርግጥም የሐዋርያቱ የራሳቸውን Text ነውና ስህተት አልባ ነው ማለት እንችላለን።

ይህን በጥንቃቄ መረዳት ብቻውን ያለ አንዳች ተጨማሪ ሙግት ያቀረበውን አጠቃላይ ሙግት ይመልሳል።

https://www.youtube.com/watch?v=NikVdhp0YFs

@zanchor
@zanchor

መልህቅ

18 Sep, 15:54


Challenge : We Have No Inerrant Manuscripts; Therefore, Talk About an Inerrant Bible Is Misleading.

Those who make this objection point to the fact that inerrancy has always been claimed for the first or original copies of the biblical documents.

Yet none of these survive: we have only copies of copies of what Moses or Paul or Peter wrote. What is the use, then, of placing so great importance on a doctrine that applies only to manuscripts that no one has ?

In reply to this objection, it may first be stated that for over 99 percent of the words of the Bible, we know what the original manuscript said. Even for many of the verses where there are textual variants (that is, different words in different ancient copies of the same verse), the correct decision is often quite clear, and there are really very few places where the textual variant is both difficult to evaluate and significant in determining the meaning. In the small percentage of cases where there is significant uncertainty about what the original text said, the general sense of the sentence is usually quite clear from the context. (One does not have to be a Hebrew or Greek scholar to know where these variants are, because all modern English translations indicate them in marginal notes with words such as “some ancient manuscripts read . . .” or “other ancient authorities add. . . .”) This is not to say that the study of textual variants is unimportant, but it is to say that the study of textual variants has not left us in confusion about what the original manuscripts said.

It has rather brought us extremely close to the content of those original manuscripts. For most practical purposes, then, the current published scholarly texts of the Hebrew Old Testament and Greek New Testament are the same as the original manuscripts. Thus, when we say that the original manuscripts were inerrant, we are also implying that over 99 percent of the words in our present manuscripts are also inerrant, for they are exact copies of the originals. Furthermore, we know where the uncertain readings are (for where there are no textual variants we have no reason to expect faulty copying of the original).

Thus, our present manuscripts are for most purposes the same as the original manuscripts, and the doctrine of inerrancy therefore directly concerns our present manuscripts as well.

Wayne Grudem, Systematic Theology