ውብ ታሪኮች®

@wubtarikoch


👋የረበና ሰላም በናንተ ላይ ይሁን👋

“ማወቅ መልካም ነው ያወቁት ማሳወቅ ይበልጥ መልካምነት ነው።”

ውብ ታሪኮች 𝐎𝐅𝐅𝐈𝐂𝐈𝐀𝐋 𝐏𝐀𝐆𝐄®

ለሃሳብ አስተያየታችሁ👉 @Jemseidbot

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:28


ዉሸት  እንደሆነች  እያወቅኩ  ግን  በዉሸቷ  የሸነገለችኝ   ዱንያ  ብቻ  ነች!

እንደማይቀርልኝ  እያወቅኩኝ   ቀኑ በገፋ ቁጥር ወደ እኔ እየመጣ እንደሆነ  እርግጠኛ ሆኜ  ያልተዘጋጀሁለት  ነገር  ቢኖር  ሞት''  ነዉ!

@wubtarikoch

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:27


ውብ ታሪኮች® pinned «የኢስላም አርበኞች ምዕራፍ ሁለት ክፍል አንድ ረያን እና ሪና ሁዳ . . ጀምበር ከተሰየመች ረፈድፈድ ብሏል። ቢሮው ውስጥ ካለው ተሽከርካሪ ወንበር ላይ ቀና ብሎ ተቀመጠና የእጅ ሰዓቱን ተመለከተ። 4፡00 ሁኗል። በፍጥነት ከጠረጴዛው ላይ የመኪናውን ቁልፍ አንስቶ ክፍሉን ለቅቆ ወጣ! የቸኮለ ይመስላል። መኪና አነዳዱ መቸኮሉን በደምብ ያሳብቃል። ከደቂቃዎች ሹፍርና በኋላ መኪናዋ ቦሌ ኤርፖርት ማሳረጊያዋን…»

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:27


አንዳንዴ እኮ ያለን እየመሰለን የለንም ከአላህ እና ከሰላታችን ከመራቃችን የተነሳ ጎዶሎነት ሁሌ ይሰማናል ለነገሮች ምስጋና ለማቅረብ አልሀምዱሊላህ ካልን እንኳን እንደነግጣለን በትንሹም ቢሆን ልባችን ከአይምሯችን ጋር እንደሚጣመር ይገባናል ...... ይሄ ጎዶሎ መች ይሆን ሚሞላዉ

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:26


ማናችን እንሆን...ከወንጀል የጠራነው በየትኛው መንገድ ይሆን መልካም ሰሪ ብቻ የሆነው በይፋም ሆነ በድብቅ ስንት ወንጀሎችን እንሰራለን...ነገር ግን የኛ ሩህሩና አዛኝ የሆነው አላህ ወደ እሱ በቀረብን ቁጥር ሁሉንም ወንጀላችንን ይምረናል እንደ ሰው ድጋሚ ሳያነሳ ወንጀላችንን ሁሉንም በምህረቱ ያልፍልናል ታዲያ ይሄን የመሰለ ጌታችንን ማመፅ እንዴት ቀላል ሆነ...?
.
.
@wubtarikoch
@wubtarikoch

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:25


<<Am for it! አንድ ወር ሲበዛ ነው!>>
<<አይ አይ.. አይበዛም! ለሁሉም ነገር Effect አለው ሲባል አልሰማሺም?>>
<<ማለት?>> አሁን ሀያት ብቻ ሳትሆን እነ ሱደይስም ጆሯቸውን አቆሙ።
<<አንዳንድ ሰዎች <የአንድ ነገር መፈጠር ሌላ ነገር መኖሩን ለማረጋገጥ ያግዛል። ለምሳሌ የውሃ መኖርን የምናምነው በአይን የሚታይና የሚዳሰስ ስለሆነ ነው። ግን የማይታዩትን ነገሮች ላይ ለማመን ግዴታ ጀርባውን ማጥናት ግድ ይላል!> ይላሉ!>> 
<<I don't get ya!>> ግንባሯን አጨማደደች።
<<ለምሳሌ አላህ (ሱ.ወ) አናየውም ግን እናመልከዋለን። እሱን ለማምለክ ግዴታ በአይን ማዬት አልተጠበቀብንም! የመልዕክተኞች መላክ፣ የቁርዓን መውረድ፣ ፍጡራኖቹ፣ ወንዙ፣ ተራራው፣ ከዋክብት፣ ስርዓተ መሬት... ስናይ የሰው ልጅ ሊፈጥራቸው የማይችላቸው፤ እነሱን የፈጠረው ታላቅ ሀይል እንዳለ ትጠረጥሪያለሽ። እነዚያ አያቶች ወይንም ምልክቶች ደግሞ የሚያዳርሱን ወደ አላህ ብቻ ሲሆን ደግሞ ታመልኪዋለሽ!>> አማንና ሱደይስ እርስ በእርስ ተያዩ!
<<Okay ገባኝ! ለኔ ጊዜ መስጠታቹ ከጀርባው አሪፍና የተጠና ስራ እንደሚኖረው ስለምታምኑ ነው!>> ሀያት ፈገግ አለች።              
<<ይሄ ነው የሚፍታሁል ቀልብ ተማሪዎችን ለየት የሚያደርጋቸው። አመስግኑ!>> 
<<አልሀምዱሊላህ!>> በአንድ ድምፅ።
*
አሚር ሶስቱን ልጆች ወደ ክፍላቸው አድርሷቸው ሲመለስ ኢምራን ትክዝዝዝ ብሎ ተቀምጧል። ፈገግ ብሎ ትካሻውን መታ አድርጎት ተቀመጠና <<ብዙም አትጨናነቅ! የተቻለንን እናደርጋለን!>> አለው።
<<ሀያት ያለችውን በደምብ አስተውለኸዋል?>> ኢምራን ሙሉ ለሙሉ ወደ አሚር ዞረ። አሚር ለመናገር ጉሮሮውን ሲጠራርግ ኢምራን <<ሙሉውን ልትደግምልኝ ባልሆነ>> አለው።
<<ነበር...>> ፀጉሩን እያሻሸ ተነስቶ ከስቱዲዮ ፒሲ አምጥቶ ተቀመጠ።
<<ተስዕጦ!>> ኢምራን ተቆጥቷል።
<<ጥቅም የለውም ነው?>>
<<አላልኩም! የሚጠቅሙ ተስዕጦዎች እንዳሉ ሁሉ... ኡማ ለማገልገል ነው በሚል ስም ልክ እንደ ሀያት ስንቱ ተበላሽቶ ይሆን? ሙስሊም ተዋናይት? ለሀሳብ እንኳ የማይመች ግብ እኮ ነው!>>
<<እሱስ ልክ ነህ! አንዳንዱ ላዩን እንጂ ውስጡን ሳይፈትሹ ነው የሚገቡበት። አላህ ይምራቸው!>> ረጅጅጅጅጅም ፀጥታ ሰፈነ።
.
.
ይቀጥላል!

@wubtarikoch

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:25


የኢስላም አርበኞች
ምዕራፍ ሁለት
ክፍል ሰባት
(ረያን እና ሪና ሁዳ)
.
ኢምራን መኪናውን ወደ ቤቱ በሚወስደው ቅያስ እያሽከረከራት ነው። ውስጡ በሀሳብ ሰጥሟል። <ፊርዱን ስለ በፊቱ ማንነቷ ባነሳባት ምን ትለኝ ይሆን?> ያስባል።
<ግንኮ ለህፃኗ የሚያግዛት ከሆነ እንዴት ትከፋለች?> ራሱ ለሚያመጣው ጥያቄ በጥያቄ መልክ ምላሹን አዕምሮው ያስቀምጥለታል።
<ያ አላህ! አግዘኝ!> አለ ቤቱ በር ላይ እንደደረሰ። ፊርደውስ የመኪናውን ድምፅ ስትሰማ ሩጣ በሩን ከፈተችለት። ኢምራን ከመኪናው ወርዶ ውብ ሆና የጠበቀችውን ባለቤቱን ሲያይ <መጠየቅ የለብኝም!> ሲል አሰበ። ተጠመጠመችበት።
<<አንተ ግን ትገርማለህ!>> ከእቅፉ ወጥታ ወደ ቤት እየገቡ አሸሞረችው። ኢምራን ግንባሩን ሲያጨማድድ <<አዋ! ለኔ ጊዜ ሲሆን ነው ስራ የሚበዛብህ!>> ሳቀች። ሳሎን ገብተው መጅሊሱ ላይ አረፍ አሉ።
<<ኦህ! ፊርዱ ደግሞ..... እንደዛኮ አይደለም! አንቺም ፍሪ ሁነሽ እንድታጠኒ እድል ይፈጥርልሻልኮ!>>
<<ቲሽ! አሁን አንተ ሳትኖር እንዴት ይጠናኛል?>> አኮረፈች።.
<<እናሳ! መፅሀፉን ገልጠሽ የምታይው እኮ ኢምራንን ነው! ነው እኔን ነው አጥኚ የተባልሺው>> ጠቀሳት። ፊርደውስ ይበልጥ እያኮረፈች <<ከዛሬ በኋላ ግን ከቤት ውጪ ማደር የለም!>> አለችው።
<<ፊርዱ.. ሰዓቱን ሳላዬው እየመሸብኝ እኮ ነው!>>
<<እኮ በጊዜ ና! እኔም አግዝሀለሁ እንደውም!>> ኩርፊያዋ በአንድ ጊዜ ለቀቃት። ኢምራን ዝም ሲል በሰማያዊ ብሌን የተዋበ የአይኗን ጨረር ለቀቀችበት። ደካማ ጎኑ የሚቅለሰለሰው አይኗ ነው። የብሌኗ ሰማያዊነት ደግሞ ይበልጥ እንዲወደው አድርጎታል።
<<ድመት!>> አላት እያቀፋት። ሁሌ <አይኖችሽን ሳያቸው ትንሽዬ ድመት ትመስይኛለሽ> ይላታል። እሷ ደግሞ <አንተ ከወደድክልኝ ድመት መሆን ያስደስተኛል!> ትለዋለች። ፊርደውስ እቅዷ በመሳካቱ ደስ አላት። እዛው እቅፉ ውስጥ እያለች <<ድመትህን መቋቋም እንደማትችል አውቅ ነበር!>> አለችው።
<<ልክ ብለሻል! ማንም ይህን አስተያየትሽን ሊቋቋመው አይችልም.... ግን.... ከእኔ ፊት ድመት የሆነችዋ ፊርዱ ከሌላው ፊት ነብር መሆኗን አላውቅም ነበር!>> ፈገግ አለ። ፊርደውስ ግራ በመጋባት ስሜት ውስጥ ሁና <<እንዴት?>> አለችው።
<<እኔ አንቺን ወደ ቀጥተኛው መንገድ ለማምጣት ስጥር ወደድኩሽ! ግን ስሜቴን አፍኜ ግቤ እስኪሰምር ጠበቅኩ! ከዛም አገባሁሽ አይደል?>>
<<አዎ!>>
<<የኔዋ ድመት ግን.... ጓደኛዋን ለመመለስ ባገኘቻት ጊዜ ንዴቷ ከእርጋታዋ በልጦ ነበር!>> ፊርደውስ አቀረቀረች።
<<ኢምሩዬ ስለምወዳት እኮ ነው!>>
<<እሱን ማን ካደ! በመውደድ የሚወዳደርሽ አለ እንዴ?>> ሳቀ።
<<እንዴት መሰለህ.... አህሉዬን ሳያት... ያኔ ገና እናንተን ሳናገኝ በፊት የኖርኩት ሀያት ትዝ ይለኛል! እኔ ምን ያክል ጥፋት ውስጥ እንደነበርኩ እያወቅኩ እሷ ስትዘፈቅበት ማዬት. ከበደኝ..>> ኢምራን ከአሚር ጋ ያወሩበትን ሀሳብ ከፊርደውስ ጋ ለመወያየት አጋጣሚ የፈጠረለት መሰለው። ደስ አለው።
<<ፊርዱዬ ግን አንድ ጥያቄ ብጠይቅሽ ደስ ይለኛል! ማለቴ... የማትከፊብኝ ከሆነ!>>
<<ትችላለህ!>>
<<እምም... ሀያት... አንቺ እኛን ከማግኘትሽ በፊት የነበርሺበት ማንነት ውስጥ ናት። ምናልባትም የባሰ ሊሆን ይችላል.... ፊርዱዬ... ብታግዢን ምን ይመስልሻል?>> አይን አይኗን ይመለከታት ጀመር። ፊርደውስ ከራሷ ጋ ስትመላለስ ቆይታ እንባ ያቀረሩ አይኖቿን እየጠረገች <<እሺ!>> አለችው።
*
ንጋት ላይ - ሚፍታሁል ቀልብ
ፋሪስ በዝግታ እየተራመደ ወደ ህፃናት መማሪያ ክፍሎች ቅያስ ተቀለበሰ። ዛሬ ማስተማር የእርሱ ተራ ነው። እቅዳቸው ነፍስ ያወቁ ልጆች ላይ ሳይሆን ገና መጥፎና ጥሩን ባልለዩት ህፃናት ላይ ነው የሚያተኩረው። ንፁህ አዕምሯቸውን ከዛ እድሜያቸው ጀምረው በአላህ ውዴታ መክተብ ነው ፍላጎታቸው። ፋሪስ የክፍሉን በር ከፍቶ ሲገባ በጩኸት ሲታመሱ የነበሩት ህፃናት በአንዴ ፀጥ አሉ።
<<አሰላሙ ዓለይኩም ልጆች!>> አላቸው እንደገባ።
<<ወዓለይኩም ሰላላላም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ!>> ህፃናቱ በተለመደው ዜማቸው ለሰላምታው ምላሽ ሰጡ።
<<እንዴት ናችሁ?>>
<<አልሀምዱሊላሂ ረቢል ዓለሚን! እኛ ደህና በጣም ደህና ነን!>> ፋሪስ ፈገግ አለ። ሁሌ ይሄ አነጋገራቸው ያስቀዋል።
<<ዛሬ ስለምን ይመስላችኋል የምንማረው?>> ሁሉም ፀጥ!
<<እሺ! አሁን ሁላችሁም በሰልፍ ወደ ውጭ ትወጣላችሁ!>> አላቸው። ህፃናቱ በኮልታፋ አንደበታቸው እየተንሾካሾኩ መማሪያ ክፍሉን ለቀው ወጡ። ፋሪስ ከፊት ሆኖ እየመራቸው ሰፊው ሜዳ ደረሱ።
*
<<ብዬህ ነበርኮ!>> አሚር ነበር። ኢምራን ፊርደውስ በሀያት ዙሪያ አሪፍ ሀሳብ እንዳመጣች ነግሮት ነው እንዲህ የጮኸው።
<<እኔስ መች ካድኩ!>> ኢምራን እየሳቀ አጠገቡ ተቀመጠ።
<<አሁን ጊዜ ሳናጠፋ ተግባራዊ እናድርገው! እምም... ሶስቱን ልጆች ይዘህልኝ ና!>> አዘዘው። አሚር በፍጥነት የታዘዘውን አደረገ። ሰፊው ጠረጴዛ ዙሪያ አምስቱም ተደረደሩ። አማን ከደረቱ ለጥፎ ያቀፈውን መፅሀፍ ጠረዝጴዛው ላይ አስቀመጠው። ሱደይስ ወፍራም ክብ መነፅሩን መስታወት በሶፍት ይወለውላል። ሀያት ደግሞ ስልኳን ትጎረጉራለች። ኢምራን ጉሮሮውን ሲጠራርግ ሁሉም የሚሰሩትን ስራ ትተው ትኩረታቸውን ወደሱ አደረጉ።
<<እስኪ.... ወደፊት ምን መሆን እንደምትፈልጉ ንገሩኝ!>> ኢምራን ጠረጴዛውን በዜማ እየመታ አፈጠጠባቸው።
አማን፡- <<የነርቭ ሀኪም!>>
ሱደይስ፡- <<ሳይንቲስት!>>
ሀያት፡- <<In this time ማወቅ ብቻ ነው አላማዬ! whether it helps me or not -ለወደፊቱ ዓላማዬ፤ እውቀትን አሳድጄ ነው የማድነው!>>
<<ወደፊትስ?>>
<<ሙስሊም ተዋናይትና ፋሽን ዲዛይነር>>
<<አብራሪው!>>
<<ፍላጎቴ በተሰጥኦዬ ኢስላምን ማገልገል ነው! እኔ ዲዛይን በማደርጋቸው ልብሶች ኢስላምን ማስተዋወቅ እፈልጋለሁ!>>
<<ጥሩ! የትኛው ልብስ ነው ኢስላምን ሊያስተዋውቀው የሚችለው?>>
<<አሁን ላይ አለ ማለት አልችልም! ኢስላም Fashion industry ላይ ጠልቆ አልገባበትም።>> ኢምራን እንባው መጣው። አስተሳሰቧ አመመው። ልጆቹን እየገደልናቸው ነው! ሲል ወዶ አልነበረም። ከየትኛውም ትምህርትቤት የተሻለ እውቀት ያገኛሉ፤ ከየትኛውም መድረሳ በተሻለና በፈጠነ መልኩ በሀይማኖት ዕውቀት ይመላሉ፤ ግን በምን መልኩ ተግባራዊ እንደሚያደርጉ ስለማይነግሯቸው በራሳቸው መንገድ መፍጠር ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሀያት! አሁን ወደፊቴ ብላ ያመነችው ነገዋ፤ ለነገዋ የነቀሰችው ንድፍ የተንጋደደ እንደሆነ ማን ነገራት? የተሳሳተና መጨረሻውም እሳት እንደሆነ ማን ነገራት? ኢምራን እንባውን ጠረገና <<እምም.... ፋሽን ላንቺ ምንድን ነው?>>                                            
<<Freedom!>>
<<ጥያቄዎቼን ጨርሻለሁ! ላንቺ እንደ ወንዶቹ ብዙ ጥያቄዎች አይሰጡሽም። አንድ እንድትሰሪበት የፈለግነው ርዕስ አለ ኡስታዝ አሚር በደምብ ያስረዳሻል። የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ነው የምንሰጥሽ! በአንድ ወር ውስጥ ሁሉም ነገር አልቆ ማግኘት እንፈልጋለን።>>

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:24


✒️አንብባችሁ አስተያየት መጀመሪያ ራሳችሁን ፈትሹ ሲቀጥል አስተያየት ስጡ

ርዕሱ ፦
ልቤን ስለምፈልገው!!

ለምንድነው ጥያቄዬን ያልተቀበልሸኝ? አለኝ በለሰለሰ ድምፅ

የቱን ጥያቄህን? አልኩ አንገቴን አቀርቅሬ ያልገባኝ ለመምሰል እየሞከርኩ

እንደረሳሽው አትሁኚ ቆይ ግን ጎበዝ እና አርቆ አሳቢ እንደሆንኩ የምትነግሪኝ ሁሉ ውሸት ነበር አይደል? ለነገሩ ምን ጥያቄ አለው ከልብሽ ቢሆንማ አላንስብሽም ነበር አለኝ። ድምፁ ውስጥ ያለመፈለግ እና የሚፈልገውን የማጣት ህመም ይሰማኛል።

አይደለም! ሁሉንም ያልኩህ ከልቤ ነው አንሰህብኝም አይደለም ግን....

ግን ምን? አለ ቀጣይ የማወጣቸውን ቃላት በጉጉት እየጠበቀ

ግን ደግሞ አላህ ጋር የሚያጣላኝ የሀራም ግንኙነት ውስጥ በጭራሽ መግባት አልፈልግም።

እንዴ እኔ መች ሀራም አልኩ አለኝ ምክንያትሽ ይሄ ብቻ ነው በሚል የተስፋ አስተያየት እያየኝ።

አላልክም ግን በቅርብ ቀን ሽማግሌ መላክ ትችላለህ? አልኩት ተስፋውን ላለማጨለም እየተጠነቀቅኩ

ታውቂያለሽ አሁን ላይ ትዳር ለመመስረት የሚጎድሉኝ ነገሮች አሉ ግን ትንሽ አመት ብቻ ነው። አንቺ ከጎኔ ከሆንሽ ደግሞ ነገሮች ካሰብኩት በላይ ይፈጥናሉ እርግጠኛ ነኝ አለኝ እሺታዬን በጉጉት እየጠበቀ!

ይቅርታ ግን አይሆንም! ከትዳር ውጭ በሚሄድ ፍቅር ላይ ተጉዤ ልቤን ማጣት አልፈልግም በቃ! አይሆንም።

እውነት ይሄ ብቻ ነው ምክንያትሽ? ወይስ ይሄን ማድረግ ስለማልችል ይሄን ሰበብ አድርገሽ ለመሸሽ እየሞከርሽ ነው?..

እውነቱን ንገሪኝ ካልከኝ አሁን ላይ አንተ አለኝ የምትለው አይነት ስሜት (የፍቅር ስሜት) ያለኝ አይመስለኝም ማለቴ ባሌ ቢሆን ብዬ አስቤህ አላውቅም። ያላሰብኩህ ግን ስለማትገባኝ ወይ ደግሞ አንሰህብኝ ሳይሆን ልቤ ፍቅር የሚባለውን ነገር እንዲሞክር በጭራሽ ስላልፈቀድኩለት ነው።ምን አልባት እኔ የምፈልገው አይነት የትዳር አጋር ለመሆን ብዙ አይጎልህ ይሆናል ግን ከ ወንድምነት በዘለለ አስቤህ አላውቅም።

እሺ.. አውቃለሁ እንደዛ እንደማታስቢኝ ግን ለራስሽ ብትፈቅጂለት የምትወጂኝ ይመስልሻል?

አዎ!

እሺ እንደዛ ከሆነ አሁን ላይ እንድታገቢኝ ቢሆን ኑሮ እየጠየኩሽ ያለሁት ትቀበይኝ ነበር?

እርግጠኛ አይደለሁም ግን ልቀበልህ የምችልበት እድል ሰፊ ነው።

ታዲያ እንደዛ ከሆነ ለምን በዚህ ደረጃ ነገሮችን እንደማይሆኑ ታስቢያቸዋለሽ ቢበዛ 3 ወይ 4 አመት እኮ ነው። እስከዛ አንችም ትመረቂያለሽ ከዛ በኋላ ነገሮችን ቶሎ አስተካክለን እንጋባለን።

አይሆንም! በጭራሽ ሊሆን የማይችል ነገር ነው እያሰብክ ያለኸው imagine 4 አመት ሙሉ በሀራም ፍቅር ውስጥ ሀላልን እየጠበቅኩ ነፍሴን ሳቆሽሽ እና ከአላህዬ ጋር ስጣላ። አይደለም እርግጠኛ የሆንኩበት ስሜት ሳይኖረኝ ይቅር እና ካንተ ክንፍ ያለ ፍቅር ቢይዘኝ እንኮን ያንን አስቀያሚ መንገድ ተጉዤ አላህ የወደደውን የሀላል ሂወት እኖራለሁ ብዬ የማምን ሞኝ አይደለሁም። በጭራሽ ያንተ አልሆንም ብዬ መናገር አልችልም ምክንያቱም አላህ ፅፎት ሊሆን ይችላል.. ግን ደግም በእርግጠኝነት የምነግርህ በጭራሽ እንደዚህ አይነት መስመር ውስጥ እንደማልገባ ነው ምክንያቱም ልቤን እፈልገዋለሁ..... ያለኝን አቆም ሊያስቀይረኝ እንደማይችል እንዲገባው ተኮሳትሬ እና ከልቤ ነበር የመለስኩለት።

ልቤን እፈልገዋለሁ ማለት? ልብሽን በክህደት የምሰብረው ነው የሚመስልሽ? እንደዛ አይነት ተራ ዱርዬ ነኝ እንዴ እኔ? እንደዛ ነው የምታስቢው አኢሻ?... አለኝ ግራ በተጋባ ፊት አኢሻ ሲለኝ የመጀመሪያው ነው እንደጓደኞቼ ማቆላመጥ ይቀለው ነበር።

አይደለም እንደዛ አይነት ማንነት እንደሌለህ አውቃለሁ። ግን የኔ ልብ ውስጥ ትልቅ ጌታ አለ የሚፈቀር እና የሚፈራ ጌታ። ጌታዬን ያፈቀርኩበት ልብ ላይ የሀራም ፍቅርን ልሸከምበት አልችልም። እዚህ ልቤ ላይ የአንተን ፍቅር በሀራም ከተሸከምኩ ጌታዬን አጣዋለሁ እሱ የሌለበትን በድን ልብ ደግሞ ፆታዊ ፍቅር ሊያሞቀው አይችልም!

እሺ ከዚህ በላይ አልጫንሽም... ግን ነገሮችን አስተካክዬ ከአመታት በኋላ ብመጣ እና የዛን ግዜ አንቺ ነፃ  ብትሆኚ ትቀበይኛለሽ?... አለኝ አራቱን አመት ጨርሶት ሊመጣ በሚመስል ጥድፊያ።

ልቀበላቸው የማልችላቸውን ባህሪወች ሳትይዝ በዚሁ ስብዕናህ ላይ ካገኘሁህ አዎ!

ጥሩ እሺ አላህ ከኔ ሌላ ለማንም ሁነሽ እንዳያሳየኝ የሁል ጊዜ ዱአዬ ነው። ትንሽ እንኮን ካዘንሽልኝ ግን በዱአ አግዢኝ። ብሎኝ በእምባ የተሞሉ አይኖቹን ወደመሬት እንደተከለ ጀርባውን አዙሮ ሄደ።

እኔንም እሱንም ከጌታችን ቁጣ እና ቅጣት  የታደኩ ያህል ተሰማኝ። በተመሳሳይ ሰአት  ደግሞ ሁኔታው አሳዘነኝ ለአመታት ጠብቄው ዛሬ ተሰብሮ የሄደ ልቡ ሲጠገን ባይ ተመኘሁ ግን ያን ያህል ግዜ ለመጠበቅ የሚያስችል ፍቅር እና ሶብር መኖሬን እንጃ.......

rehima hussen

ይህ ፅሁፍ በእንደዚህ አይነት ጥያወቄወች ውስጥ ለምታልፉ እና እያለፋችሁ ላላችሁ እህቶች(ወንድሞች) ነው። ሁሌም የምወስነው  ውሳኔ አላህን የሚያስደስት ነው ወይስ የሚያስቆጣ ብላችሁ አስቡ! አላህን የሚያስደስት ከሆነ መቼም በውሳኒያችሁ እንደማትፀፀቱ እርግጣኛ ሁኑ ጌታችሁን የሚያስቆጣ ሁሳኔ እንደሆነ እያወቃችሁ ከወሰናችሁ ግን በሂወታችሁ የሚቆጫችሁን ነገር እያደረጋችሁ እንደሆነ አትርሱ!

@kheyruluswa

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:21


አሰላሙ ዓለይኩም ውድ የዚህ ቻናል ቤተሰቦች👋

ሰሞኑን ላልኖር ስለምችል ክፍል 4 ፣5፣ 6 ተለቋል አንብቡ።
ይህ ቻናል የሁላችንም ነው ቻናሉን ሼር በማድረግ አግዙን። 💕

ውብ ታሪኮች® የሁላችንም

@wubtarikoch

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:21


ውብ ታሪኮች® pinned «የኢስላም አርበኞች ምዕራፍ ሁለት ክፍል አራት (ረያን እና ሪና ሁዳ) . . <<ወላሂ እያደረግን ያለው ነገር ምንም ጥቅሙ አልታየኝም>> ከሴቶቹ ክፍል የኢምራን ድምፅ በስፒከሩ ውስጥ ያቃጭላል፡፡ የአርበኞቹ ስብሰባ ጀምሯል። ነባት፣ ፊርደውስና ኢኽላስ ከሴቶቹ ምሽግ ሁነው ወንዶቹ ምሽግ ውስጥ የሚደረገውን ስብሰባ በድምፅ እየታደሙ ነው። እያንዳንዳንዷን ቃላቱን በትኩረት ያዳምጡታል፡፡ <<እያደረግን ያለነው…»

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:21


<<ሀያት! ስለሷ ምን ማድረግ እንዳለብን ከሀሩኔ ጋ ሁላ አልተወያየንበትም። ልነግረው በነበረበት ሰዓት የረውዳ አባት ደውለው ጠሩት። እምም... እስካሁን ግን ሀሳብ አልመጣልኝም!>>
<<ምንድን ነበር የሷ ኬዝ?>>
<<ፉክክር!>>
<<ፉክክር?>>
<<እንዴት መሰለህ! ልጂቱ ገና ህፃን ብትሆንም.... ከዚህ በፊት ትማርበት የነበረው ትምህርት ቤት ውስጥ በአመት or ሁለት አመት ከሚበልጧት ጓደኞቿ ጋ ፉክክር ፈጥራ
ነበር። ማን ከማን ያንሳል? አይነት ነገር! ግሩፓቸው ሀሳቡ የትምህርት ቤቱ ቆንጆ ማን ነው?፣ ስንት ወንዶችን አንበረከክሽ.. የሚሉትን ብቻ ነው የሚያስቡት! በዚያ ላይ ደግሞ ፋሽን ተከታዮች ናቸው። ከህፃን አዕምሯቸው ብዙ የማትጠብቃቸው ነገሮች አሉ። በዚያ ላይ በፊልሞች የተተበተበ ማንነትን ነው የገነቡት!>>
<<ሱብሀነላህ!>> አለ አሚር ተገርሞ። ከአመታት በፊት መሰናዶ ሲማር ያስተዋለውን የሴቶችን ሁኔታ አስታውሶም ይሆናል። ለማስታወስ ምን ገዶት?
<<ግን ኢምሩ... እንዴት ነው የምናስተካክላት?>>
<<ወላሂ.... እንጃ! በጣም እያሰብኩበት ነው። መሬት የሚወርድ ሀሳብ ግን አልመጣልኝም!>> አሚር አሰብ እንደማድረግ አለና <<ፊርዱን ጠይቃት!>> አለው። ኢምራን ሲፅፍበት የነበረውን እስክርቢቶ ዘመም አድርጎ ቀና አለ።
<<ፊርዱ?>>
<<አዎ! ፊርዱኮ... ከኛ ግሩፕ ውስጥ በፋሽን ሱስ የተጠመቀች እና በፊልሞች የተሸበበች ነበረች አታስታውስም?>>
<<ልክ ነህ ግን..?>>
<<ምንም ግን የለውም... እሷ እንደውም አሪፍ ዘዴ ልትነግረን ትችላለች! ራሷን ካሳመነችበት አንፃር!>> ኢምራን ፊቱ በፈገግታ ተመላ።
<<በጣም ጥሩ ሀሳብ ነው! ልደውልላት!>> እየተፍለቀለቀ ስልኩን ሲያወጣ ቀድማ ደወለችለት። ሳቀና አነሳው።
<<ወዓለይኪ ሰላም ወራህመቱላህ ሀቢብቲ!>> ለሰላምታዋ አፀፋ ሰጠ።
<<ኢምሩዬ.... ዛሬም ቤት አትመጣም?>> ተቅለሰለሰች።
<<ዛሬ እንኳን እመጣለው! ግን.. ችግር አለ እንዴ?>>
<<አይ... ስትናፍቀኝ ጊዜኮ ነው!>>
<<እንዲ ናፍቄሽማ ካልመጣሁ ምኑን ባል ሆንኩት! ኢንሻአላህ በጊዜ እመጣለሁ!>>
<<እሺ እጠብቅሃለው>> ልቧ ሀሴት አደረገች
.
.
.ይቀጥላል!...

#ቻናሉን_ይቀላቀሉ👇
@wubtarikoch
@wubtarikoch

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:21


የኢስላም አርበኞች
ምዕራፍ ሁለት
ክፍል ስድስት
.
.
አሚርና ኢምራን ሚስጥራዊው ዋሻ ከሚገኘው የምስል ስቱዲዮ ውስጥ አዲስ ቪዲዮ ይቀርፃሉ። ኢምራን የባለፈውን ቪዲዮ ክፍል ሁለት በተጠናቀረ መልኩ ይተነትናል፤ አሚር ይቀርፃል።
<<ሀሳቤን ስጠቀልለው!.ዛሬ በሁለተኛው ክፍላችን ብዙ ነገሮችን አይተናል፡፡ እንደተባባልነው ፍልስፍና የመጠየቅና ለመረዳት የመፈለግ ያህል አስፈላጊ ነው፡፡ ፍልስፍና ለጥያቄዎቻችን ተገቢውን መልስ እስከሰጠን ድረስ መጥላቱ ተገቢ አይመስለኝም፡፡ አንዳንዴ ግን ፍልስፍና ሰውን ለፍፅምና ያቀርባል፡፡ አልደርስበትም አላውቅም ብሎ ነገር አያውቅም፡፡ ይህ ነው የችግሩ ሁሉ ጥንስስ፡፡ ብዙዎቹ ፈላስፋዎች ኢአማንያን ናቸው፡፡ ያ ማለት ግን አማኝ ፈላስፋዎች የሉም ማለት አይደለም፡፡ በቀጣይ መርሃግብሮቻችን በኢአማንያኑ ለሚጠየቁ ጥያቄዎች መልሶችን እንሰጣለን፡፡ ይኽ አቂዳችንን ለማጠንከርም ዋጋ ይኖረዋል፡፡ ኢአማንያኖች ከምትጠይቁን አንዱ ለስዕል ሰዓሊ፣ ለቅርጻቅርፅ ቀራጺ ወዘተ እንዳለው ሁሉ ይህንን ዩኒቨርስ የፈጠረ ፈጣሪ አለ ትላላችሁ ትሉና በእናንተው አመክንዮ የፈጣሪስ ፈጣሪ ማነው ብላችሁ ትጠይቁናላችሁ፡፡ ይኽ ምን ማለት ነው?>> ኢምራን ከብርጭቆው ውኃ ተጎነጨ፡፡ <<ፈጣሪም ፍጡርም መሆን ማለት ምን ማለት ነው? ፈጣሪንስ ራሱ ፈልጎ የፈጠራቸው ህግጋት የሚገዙት አድርጎ ማሰብ ምን ማለት ነው? ይህ <ነገሮች ሁሉ ፈጣሪ አላቸው ህግ> የሚሰራው በጊዜና ቦታ ተወስነን ለምንኖረው እኛ እንጅ ጊዜና ቦታን ለፈጠረው ፈጣሪ አይደለም፡፡ ይህ እኮ በስፕሪንግ የምትንቀሳቀስን አሻንጉሊት የፈጠረ ኢንጅነር እንደአሻንጉሊቷ ይንቀሳቀሳል ማለት ነው፡፡ በቀጣዩ ፕሮግራሞቻችን ከምናያቸው ጉዳዮች ሁለተኛው ደግሞ ፈጣሪ የምሰራውን ሁሉ ቀድሞ ከቀደረው እኔ የምዳኝበት ምክንያት ምንድን ነው? የሚለውን ይሆናል! ኢንሻአላህ በቀጣይ ክፍሎች እንመለስባቸዋለን። የዛሬውን ቪዲዮ በዚሁ እቋጨዋለሁ። ያ ማለት ርዕሱ ቀላልና በአጭሩ የሚፈታ እንዳልሆነ ልብ ይሏል። ውድ የሚፍታሁል ቀልብ ገፅ ተከታታዮች ቪዲዮውን ከወደዳችሁት ላይክና ሼር በማድረግ ይተባበሩን። ቤታችንን ያልተቀላቀላችሁ ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ። እንዲሁም አዳዲስ ቪዲዮዎች እንዲደርሷችሁ የደውል ምልክቷን ይጫኑ! በቀጣዩ ክፍል እስከምንገናኝ ወሰላሙ ዓለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ!>> አሚር ቀረፃውን አቆመ።
<<ማሻ አላህ! ተከራካሪዎችህ ከአንተ የተሻለ ማስረጃ የሚያመጡ አይመስለኝም!>> አሚር ከኢምራን ኳሌታ ላይ የተሰካውን ድምፅ መቅጃ እያነሳ።
<<ተሳሳትክ!>>
<<የቱ ላይ?>> አሚር ግራ ተጋባ።
<<እየተከራከርኩ ሳይሆን እየተወያየሁ ነበር!>>
<<ምን ልዩነት አለው!>> በፌዝ ፈገግታ ፈገግ አለ።
*
<<አየህ! ተነጋግሮ ከመተማመን ይልቅ የኔ ብቻ መሰማት አለበት ከሚል ማህበረሰብ መሀል መፈጠራችን ምን ያህል ተፅዕኖ እንደፈጠረብን? እኔ ከኤቲስቶች ጋ ክርክር እየገጠምኩ አልነበረም። እነሱ ግን ፍልሚያ እንደሆነ ነው የሚያስቡት! ምናልባት አነጋገሬን በደምብ አድምጠኸው ከሆነ... የክርክር እንዳልሆነ በደምብ ያስታውቃል! እነሱ አስተሳሰባቸውን በአንዴ መለወጥ እንደማይችሉት ሁሉ የፈለገ ብረጋጋ ውይይት እንደማይመስላቸው የታወቀ ነው። እውነቱን እስከሚረዱት ድረስ ግን እነሱ ፍልሚያ ባደረጉት መወያየት እቀጥላለሁ!>>
<<ልክ ነህ... ግን ይሄን ለማድረግ ምን አነሳሳህ? ማለቴ... በደፈናው ሀይማኖት የለም ከሚሉ ሰዎች ጋ ለመወያየት..!>>
<<ብዙ ሰው... ኢስላማዊ ትምህርት የሚሰጠው ወይ ሙስሊም ሆኖ የማያውቀውን ለማሳወቅ ነው፤ ወይ ደግሞ የሚያውቁትን ለማነቃቃት ነው። በእርግጥ ካፊሩንም ወደ እስልምና ለመጥራትም ያሰበ አይጠፋም። ማሰባቸው ጥሩ ሆኖ የሚሰሩበት መንገድ ግን ያን ያህል አመርቂ አይደለም>>
<<ማለት?>> በንግግራቸው ከስቱዲዮ ወጥተው ባለ ሰፊው ጠረጴዛ ክፍል ደረሱ።
<<አሁን ላይ ብዙ ኢስላማዊ ሚዲያዎች ተስፋፍተዋል። ኢስላማዊ አስተምህሮት የሚተላለፍባቸው፤ መረጃና አዳዲስ ነገሮች የሚያገኙባቸው እንዲሁም ለእስልምና መብት ተሟጋች የሆኑ ከቴሌቪዥን ጣቢያ እስከ ሶሻል ሚዲያ ተሰራጭተዋል። በእርግጥ እንደ ግብ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ትላልቅ አገልግሎቶችን እየሰጡ ቢሆኑም.. ከእስልምና ውጭ ያሉ ሀይማኖቶችን ለሚከተሉት ግን በአግባቡ አልደረሱላቸውም! በአጭሩ ክርስቲያኖች ወይም ሌላ ሀይማኖት ተከታዮች ኢስላማዊ ቲቪ የመክፈታቸው እና ኢስላማዊ ዩትዩብ ቻናሎችን ለመከታተላቸው ምንም መረጃ የለንም። በፐርሰንት ብናስቀምጠው ከመቶ አስር ፐርሰንት አይሞላም።>>
<<እና እኛስ የተለየ ነገር እየሰራን ነው?>>
<<of course!... እኛ የምንሰጣቸውን የመወያያ ነጥቦች እንዲያደምጡትና ትኩረት እንዲሰጡት መጀመሪያ ላይ ከሀሩኔ ጋ እርምጃ ወስደንበታል። በኮሜንት እና በተለያዩ ሀገር አቀፍ ሚዲያዎች ላይ እንዲለቀቁ ፍቃድ ጠይቀን አግኝተናል። አሁን ላይ ሙስሊም ያልሆኑ ወደ ሰላሳ ሺህ የሚጠጉ ተከታታዮች አሉን። ከሙስሊሙ በግማሽ የሚያንሱ ቢሆንም እንደ መጀመሪያ እቅድ በጣም አሪፍ ነበር። ወደፊትም እንቀጥላለን ኢንሻአላህ!>>
<<ኢንሻአላህ!>> አሚር ጠረጴዛው ላይ ፒሲውን ከፍቶ ተቀመጠና ቅድም የቀረፀውን ቪዲዮ ኢዲት ማድረግ ጀመረ።
*
የዓሱር ሰላት እየደረሰ ነው። ኢኽላስ ዊልቸር ላይ ሆነው የግቢውን አበቦች ውሃ ለማጠጣት የሚሞክሩትን አያቷን በረንዳው ላይ ቆማ ታያቸዋለች። <<ለምንም ነገር እጅ የማይሰጥ ሰው!>> አለች በውስጧ እጇን እያደራረበች። ወዲያው ማሂ ከቤት ወጣና ፊዳን አቅፏት ቆመ።
<<ምን እያሰብሽ ነው?>> አላት ኡስታዝ አብዱሰላምን አተኩራ ስታይ ተመልክቷት።
<<እንጃ! ደስታ ልበልህ? በፍጥነት እየተሻለው መሆኑ አስደስቶኛል!>> አለች አይኗን ከአያቷ ላይ ሳትነቅል። ማሂ ፈገግ ብሎ ሲመለከታቸው የውሃ መሳቢያ ቱቦ ረዝሞ አስቸግሯቸው ይንደፋደፋሉ።
<<ሳይቸገር አልቀረም ላግዘው መሰል!>> አለና ሊሄድ ሲል ኢኽላስ እጁን ያዘችው።
<<ማሂዬ.... አሁን ላይ ብዙ ነገሩን የምናደርግለት እኛ ነን። አንዳንድ ቦታዎች ላይ ግን እገዛችንን ካልገታን.. በራሱ ምንም ነገር ማድረግ እንደማይችል ራሱን ያሳምነዋል። ያ ደግሞ ቶሎ እንዳያገግም ያደርገዋል.... አንዳንድ ጊዜ በራሱም መስራት እንደሚችል... እኛ ባናምን እንኳ እሱ ራሱን እንዲያሳምነው እናድርግ!>> አለችው። ማሂ ንግግሯ አሰብ አድርጎ አንገቱን በአወንታ ነቀነቀና ወደ ውስጥ ገባ። ልብሱን ቀያይሮ ሲወጣ <<ወዴት ነህ?>> አለችው።
<<ሚፍታሁል ቀልብ! አዲሱ ፕሮግራም ይወጣል ማዬት አለብኝ!>> ግንባሯን ስሟት ወደ አያቱ ተንደረደረ።
<<ፋሪስ አይነግርህም እንዴ በስልክ?>>
<<አይ... ምናልባት ከክላስ ጋ የሚጋጭ ምደባ ካለ እዛው እንዳስቀይረው ነው..>> የአያቱንም ግንባር ስሞ ተሰናብቷቸው ወጣ።
*
<<እኔ የምልህ ኢምሩ?>> አሚር ምስሎቹን አርትዕ ማድረጉን ለአፍታ ገታ አድርጎ ወደ ኢምራን ዞረ።
<<የሱደይስና የአማንን እቅድ ስትነግረኝኮ የሴቷን አልነገርከኝም!>> አለ።

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:21


<<የት ልትሄጂ ነው?>> ፊርደውስ ነበረች።
<<የማልቀርበት ቀጠሮ አለኝ!>>
<<ኻሊድ ጋ?>> አህላም ምላሽ ሳትሰጣት ትታቸው ሄደች። ፊርደውስ በአህላም ሁኔታ እየተናደደች <<አየሽ አይደል?... ቆይ ከዚህ በላይ ምን እናድርግ እሺ! Why she isn't listening us? Why?>> ተናዳ ግንባሯን በመዳፏ ጠበችው።
<<ፊርዱ! በዚሁ ስሜትሽ የምትቀጥይ ከሆነ.. ልጂቱ እንዲብስባት እንጂ እንድትተወው ማድረግ አንችልም። ተረጋጊ! ተረጋግተሽ ስታስቢው ነው ቀላል የሚሆነው! ደግሞ እኔ ፕላን <ኤ>ን አሳክቻለሁ!>> ፈገግ አለች።
<<እንዴት?>>
<<ራሷን እንድትጠይቅ ስነግራት ተቆጥታለች! ብቻዋን ስትሆን ግን አስታውሳ ማውጠንጠኗ አይቀርም!>>
<<በጣም ጥሩ!>> ፊርደውስ አሻግራ ወደ ውጭ ተመለከተች።



ይቀጥላል....


#ቻናሉን_ይቀላቀሉ 👇
@wubtarikoch
@wubtarikoch

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:21


የኢስላም አርበኞች
ምዕራፍ ሁለት
ክፍል አምስት
(ረያን እና ሪና ሁዳ)
.
.
ሱደይስ የአማን ዝምታ ሲረዝምበት ስልኩን ከእጁ መነተፈው። ደጋግሞ ካነበበው በኋላ እየተበሳጨ <<ምን አይነት ጥያቄ ነው አሙ? እንደዚህ አይነት ነገር አላሰብኩም ነበር፡፡>> አለ።
<<እኔም የሆነ ውስብስብ ቀመር፤ ወይም የሆነ ሀዲስ፣ የቁርአን አያ ምናምን የሚጠይቁን መስሎኝ ነበር>> አማን ወንድሙ ላይ አፍጥጧል፡፡
<<የሚገርም ነው!>> ሱደይስ መነጽሩን አድርጎ ድጋሚ የአማንን ሞባይል ተመለከተ፡፡ የተለወጠ ነገር የለም! <<"ንፋስ መኖሩን በምን ማስረጃ አረጋገጣችሁ?">> ነበር ጥያቄያቸው፡፡
<<እውነታቸውን ነው እኮ ሁሉንም ነገር የምናምነው በማስረጃ አረጋግጠን መሆን አለበት እንል የለ? ንፋስ መኖሩን በምን አረጋገጥን?>> አለ አማን ለደቂቃዎች አስቦ።
<<እሰብ አሙ በደንብ እሰብ! አሁን ስላልመጣልን ይሆናል እንጂ የሆነ ማስረጃማ ይኖረናል፡፡>> አለ ሱደይስ፡፡ አማን ትንሽ ካሰላሰለ በኋላ <<ምናልባት የአቧራ መነሳት፣ የዛፎች መገነዳደስ፣ የሳሮች መተኛት፣ ሱናሜ፣ ሀሪኬን ምናምነን የሆነ ኃይል እንዳለ እንድናምን አድርገውን ይሆን?>>
<<Bravo!! ከዚህ በላይ ምን ማስረጃ አለ? Hi Five!>> ሱደይስ የቀኝ እጁን መዳፍ ከፍ አድርጎ ዘረጋ፡፡
<<Makes Ten!>> አማን የሱደይስን መዳፍ ከራሱ መዳፍ ጋር አጋጨ፡፡
<<እና መልሱን እንላክላቸው ሱዲ?>> አለ ዓይኖቹን ወንድሙ ላይ እያቁለጨለጨ፡፡
<<ተረጋጋ! በደንብ እንሰብ፡፡ የምንልክበትን ጊዜ አልነገሩንም፡፡>> አለ ሱደይስ በጥልቀት እያሰበ፡፡
*
ከዩኒቨርስቲው አካበቢ ካለች አነስተኛ ካፌ ውስጥ ኢኽላስና ፊርደውስ ተቀምጠዋል፡፡ ከአህላም ጋር ተቀጣጥረው ነበር፡፡ አህላም ግን አሁንም አልደረሰችም፡፡
<<ዛሬ ግን ዝም አልላትም፤ ልናገራት ይገባል!>> አለች ፊርደውስ ሞባይሏን በመዳፏ እየጠበጠበች፡፡
<<ለምን ፊርዱ? ቀስ ብለን ልንመልሳት ተነጋግረን!?>> አለች ፊዳ በፊርደውስ ኃሣብ ተገርማ፡፡ <<አያቴንም ነግሬው ዳዕዋ ብልሀትን ይጠይቃል ብሎኛል>>
<<ልክ ነበርሽ እኮ... አንቺ ቴሌግራሟ ላይ ፕሮፋይል ያደረገቻቸውን ፎቶዎች ስላላየሽ ነው፡፡ እኔም ሀሳቤን የቀየርኩት ድጋሚ ፎቶዎቹን ሳይ ነው>> አለች ፊርደውስ። ቀጠለችና <<ከኻሊድ ጋር አብረው ሲያጠኑ፣ መዝናኛ ቦታ፣ ሲበሉ፣ ተቃቅፈው...>> ዓይኖቿን ጨፍና ተኮሳተረች <<...ሲሳሳሙም!>> መልሳ ገለጠቻቸው፡፡ <<አየሽ ፊዱ በጓደኝነት እናቀርባለን ስንል ልንዘገይም እንችላለን!>>
<<እሱን ትክክል ነሽ! የልጅቷ ፍላጎት ግን ምንም እየገባኝ አይደለም፡፡ ልታስተካክለው አይደል እንዴ የምትፈልገው?>>
<<ትወደዋለችም!>> አለች ፊርደውስ
<<እኔ ግን አይመስለኝም! ብትወደው ኖሮ ባህሪውን እንዲለወጥ አትፈልግም ነበር!>>
<<ኧረ አታስቂኝ ፊዱ! የሚወደደው ባህሪ ብቻ ነው ያለሽ ማን ነው?>> ቀና ስትል ከሩቅ አህላምን ወደእነርሱ ስትመጣ ተመለከተቻት፡፡
<<አልሀምዱሊላህ መጣች!>> አለቻት ለፊዳ፡፡
*
<<ኢምሩ ልጆቹ እስካሁን መልስ አላኩም እኮ>> አለ ሀሩን እያነበበ የነበረውን መጽሐፍ ወደቦታው እየመለሰ፡፡ የፍልስፍና ስለነበር ምኑም አልጣመውም፡፡
<<እኛም መልሳቸውን አንፈልግም ሀሩኔ! ሌላ ጥያቄ እንልክላቸዋለን፡፡>>
<<ምን እያደረግን ነው ያለነው? ምኑም አልገባኝም>> ሀሩን ግራ በተጋባ ፊቱ ኢምራንን ተመለከተው፡፡
<<ልክ ፈላስፋዎቹ እንዳደረጉዋቸው፡፡ አምነውበት የነበረውን ሁሉ በጥቂት ጥያቄዎች እንዲጠራጠሩ እናደርጋቸዋለን፡፡ ህጻናት ስለሆኑ አእምሯቸው ሊበጠበጥ ይችላል፡፡ ያኔ እንደረስላቸዋለን፤ ሰበብ እንሆናቸዋለን፡፡ እውነታውን እንዲያዩት እንረዳቸዋለን፡፡>>
<<ኢንሻአላህ! አላህ ያሳካልን!>> አለ ሀሩን፡፡ ወዲያው ስልኩ ጠራ፡፡
<<ኢምሩ...!>> ባለማመን ስሜት ውስጥ እየተንከባለለ ስልኩ ላይ አፍጥጧል።
<<ወዬ!>>
<<ጋሼ ደወሉ! የራውዲ አባት!>> አለ ሀሩን ፍንድቅድቅ ብሎ፡፡
*
አህላም እየተፍለቀለቀች ፊርደውስና ኢኽላስ ወደተቀመጡበት ቦታ ተንደረደረች። <<ብዙ አስጠበቅኳችሁ እንዴ?>> አለች እነፊዳ ለኢስላማዊ ሰላምታዋ ምላሽ ሲሰጧት፡፡
<<ብዙ አልቆየሽም፡፡ ተቀመጭ፡፡>> ፊርደውስ በምርመራ ዓይን እያየቻት <<የት ቆይተሽ ነው?>>
<<እምም ከጓደኞቼ ጋር ነበርኩ፡፡ ብታዪ አልላቀቅ ብለውኝ...>> አህላም ቀጠፈች።
ፊርደውስ አቋርጣት <<ኻሊድ ነዋ?>> አለቻት፡፡
የአህላም ፊት ተለዋወጠ፡፡ <<አዎ ከእሱ ጋር ነበርኩ! ምነው?>> አለቻት፡፡ ኢኽላስ የፊርደውስ ስሜታዊነት፤ ከአህላም ንዴት ጋ ተደምሮ እንዳያጣላቸው ስለሰጋች ጣልቃ ገባች።
<<ለምንድን ነው ከኻሊድ ጋር ይኽንን ያህል የምትቀራረቡት?>>
<<ሌላ ምን ምክንያት ይኖረዋል? ስለምንዋደድ ነዋ!>>
<<ትወጅዋለሽ?>> ትኩር ብላ ተመለከተቻት።
<<በጣም!>>
<<እሱስ?>> አህላም ደነገጠች። እጆቿን እያፋተገች <<ይወደኛል ግን...>> ምላሽ አጣች። ፊርደውስ ትንፋሿን ሰብስባ <<ያኔ ከቤተ መፅሀፍት ስትወጪ አስቁሜሽ ያልሽኚን ታስታውሺዋለሽ?>> በእርጋታ ጠየቀቻት። ከእርሷ ምላሽ አልጠበቀችም።
<<ለኻሊድ መለወጫ ሰበብ መሆን እፈልጋለው! ተሳሳትኩ?>>
<<አልተሳሳትሺም..! ወዶ ሳይሆን በጓደኛ ግፊት መጥፎ ሰው እንደመሰለ አውቃለሁ! ለኔ ግን በጣም ጥሩና የዋህ ነው። ታውቃላችሁ?.... ብዙ ጊዜ ይደውልልኝና... ሰላት እንደሰገድኩ፣.. ዚክር እንዳደረግኩ ይጠይቀኛል! አይ ያልኩት እንድሆነ... ይቆጣኛል።>>
<<ይሄ እኮ ሲስተማቸው ነው don't u get it? በጣም አስተዋይ እንደሆንሽ ነበርኮ የማውቀው አህሉ!>> ፊርደውስ በንዴት ጮኸች። ኢኽላስ ቶሎ ብላ በእግሯ ረገጥ አድርጋ አስቆመቻት። የፊርደውስ ንዴት ሲጨምር የአህላምም ፊት በእልህ ይንቦገቦጋል።
<<አህሉዬ...... እንዴት ነው ልትለውጪው ያሰብሽው... የተጠና ነገር አለሽ?>> ኢኽላስ ተረጋግታ አረጋጋቻት።
<<አሁን የወሰድኩት step... በጣም ቀርቤው የፈለገውን እየሰጠሁት እምነት እና ተሰሚነትን ማግኘት ነው>>
<<የፈለገውን እየሰጠሁት ማለት?>> ፊርደውስ አሁንም ተናዳለች።
<<ወንድ አይደል?... አንዳንዴ ሸይጧን ሲፈታተነው ስሜቱን እንድጠብቅለት የሚያስፈልጉበት ቀናቶች አሉ። በእርግጥ እሱ እንደሌሎቹ ወንዶች <እንተኛ> አላለኝም። እንደማይለኝም እርግጠኛ ነኝ። ስሜቱ አናቱ ላይ ቢወጣ እንኳ ከመሳም ያለፈ ነገር አያደርግም.. even አጉል ቦታ አይነካኝም!>> ፊርደውስ እንደ እብድ ከትትት ብላ ሳቀች።
<<አጉል ቦታ አይነካሽም?>> አሁንም ረጅም ሳቅ ሳቀች።
<<ይኸውልሽ አህሉ.... ለመቀየር መፈለግሽ ጥሩ ሆኖ... የመረጥሽው መንገድ ግን መጥፎነቱ እንዲበዛ አድርጎታል። ከቻልሽ ደግመሽ አስቢበት እስኪ! ሌላ የተሻለ ዘዴ ልታገኝም ትችዪ ይሆናል!... እኛም ከጎንሽ ነን!>> ኢኽላስ የፊርደውስን ሳቅ ችላ ብላ አህላምን ልታረጋጋት ሞከረች።
<<እገዛ አያስፈልገኝም! የምወደው እኔ እንጂ እናንተ አይደላችሁም! ደግሞ አላህም ዱዓዬን ስለሚሰማኝ.. ብዙም አትጨነቁ! የጠራችሁኝ ለዚሁ ከሆነ... የጨረስን መሰለኝ! መሄድ አለብኝ!>> ከተቀመጠችበት ተነሳች።

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:21


<<ያ አላህ!>> ኡስታዙ ጥቂት አቀርቅረው ከቆዩ በኋላ <<ዳዕዋ ሶብርን ይጠይቃል ልጆቼ፡፡ ግልፍተኛ አትሁኑ! ዳዒ ብልህም ጭምር መሆን አለበት፡፡ ልጅቷን በስድብ፣ በጩኸት አይደለም መመለስ የሚቻለው በብልሃት እንጂ!>> አሁንም አንጋጠው ሁለቱንም ተመለከቱ፡፡
<<እታዘዛለሁ አላልክም!? በል ወደግቢ ውሰደኝ!>> አሉ ወደማሂ እየተመለከቱ ፈገግ ብለው፡፡
<<እሺ ባባ>> ማሂና ፊዳ የኡስታዝ አብዱሰላምን ዊልቸር ለመግፋት ተሽቀዳደሙ፡፡
*
ቤት ውስጥ ከሁለቱና ከቤት ሰራተኛቸው ውጭ ማንም የለም፡፡ መግሪብ አልፎ የኢሻ ሰዓት እየተቃረበ ነው፡፡ አባትና እናታቸው ግን አሁንም ድረስ ስራ ቦታ ናቸው፡፡ ቴሌቪዥኑ <<Nat Geo Kids>> ላይ ተከፍቶ ብቻውን ይለፈልፋል፡፡ በዩቲዩብ የተከፈተው የኦሾ ንግግር ከአማን ሞባይል ውስጥ ይሰማል፡፡ የስቴፈን ሀውኪንግ <ኤ ብሪፍ ሂስትሪ ኦፍ ታይም>፣ የአልበርት አንስታይን <ዘ ወርልድ አዝ አይ ሲ ኢት> እና የኒቼ <ቢዮንድ ጉድ ኤንድ ኢቭል> መጽሀፎች እንደተገልጡ ጠረጴዛው ላይ ተቀምጠዋል፡፡ በሱደይስ ሞባይል ላይም የኦሾ ንግግሮችን አሰባስቦ በአርባ ሺህ ገጾች የተዋቀረው ፒ-ዲ-ኤፍ ተከፍቷል፡፡
ሱደይስ ክብ ወፍራም መነፅሩን ሽቅብ እየገፋ <<አሙ! እነኡስታዝ ጥያቄዎቹን ልከውልናል እንዴ?>> አለ።
<<እስኪ ቼክ ላድርግ!>> አማን ዩቲዩቡን አቋርጦ ፌስቡኩ ውስጥ ገባ <<አዎ ልከውልናል!>> አለው ወደሱደይስ ዞሮ!
<<ምን ይላል?>> አለ ሱደይስ ፊቱን ከባለአርባ ሺህ ገጹ መጽሐፍ ሳይነቅል፡፡ አማን በዝግታ ጥያቄውን ደጋግሞ አነበበው።
<<ዘጋህ እኮ! ምን ይላል?>> ሱደይስ ድጋሜ ጠየቀው። አማን በመደናገር ስሜት ግንባሩን ጨፈገገው።
.
.
ይቀጥላል!


Join us👇👇
@wubtarikoch

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:21


የኢስላም አርበኞች
ምዕራፍ ሁለት
ክፍል አራት
(ረያን እና ሪና ሁዳ)
.
.
<<ወላሂ እያደረግን ያለው ነገር ምንም ጥቅሙ አልታየኝም>> ከሴቶቹ ክፍል የኢምራን ድምፅ በስፒከሩ ውስጥ ያቃጭላል፡፡ የአርበኞቹ ስብሰባ ጀምሯል። ነባት፣ ፊርደውስና ኢኽላስ ከሴቶቹ ምሽግ ሁነው ወንዶቹ ምሽግ ውስጥ የሚደረገውን ስብሰባ በድምፅ እየታደሙ ነው። እያንዳንዳንዷን ቃላቱን በትኩረት ያዳምጡታል፡፡
<<እያደረግን ያለነው ለተማሪዎቹ እውቀት መስጠት ነው፡፡ የቀለምም የዲንም አውቀት! አይደል እንዴ? ከዚያ እኛ የተናገርነውን የደገመልንን ጎበዝ ብለን አጨብጭበን እንሸልማለን፡፡ ችግራችን እኮ እዚህ ላይ ነው፡፡ የህጻናቱ ግብ የፊዚክስ ቀመሮችን መሸምደድ፣ ቁርዓን መሐፈዝ፣ ያልቀሩትን ኪታብ ፈልጎ መቅራት፣ ሀዲሶችን በቃል መያዝ ነው፡፡ ይህ ሁሉ ከተሳካላቸው እጃቸውን አጣጥፈው ቁጭ ይላሉ፡፡ ግባቸው ማወቅ ነበራ! ማወቅ እኮ ግብ አይደለም መሳሪያ እንጅ! የውመል ቂያማ ያወቀ እና ያላወቀ አይደለም ደረጃው የሚበላለጠው፡፡ ደረጃችን የሚበላለጠው "ባወቅነው ልክ ሰርተናል ወይ?" በሚለው መመዘኛ ነው፡፡ ወላጆቻቸውም የልጆቻቸውን እውቀት ብቻ ነው ግድ የሚሰጣቸው፡፡ ህጻናቱ ምን እንዳወቁ ግን የሚያገባቸው ነገር የለም፡፡ አሁን ለሰባት አመት ልጅ ስልክ መስጠት ምን ማለት ነው? የፈለገውን መጽሐፍ ያንብብ ማለትስ ምንድር ነው? ሁሉም ነገሬ እኮ ለመጥፎ ከተጠቀምንበት መጥፎ ይሆናል፡፡ በሀፊዝነታቸው፣ በሙጃሂድነታቸው፣ በለጋስነታቸው የሚቀጡ ሰዎች እኮ አሉ፡፡ ምን ጥሩ ስራ ቢሰሩ ለዝና፤ ለመታየት ብለው ስለሰሩት አስቀጣቸው፡፡ መጸሀፍትም ስልክም ለመጥፎ ነገር ከተጠቀምናቸው መጥፎዎች ናቸው፡፡ ያንን መምረጥ የወላጅ ስራ ነው፤ ህጻናቱ ጥሩና መጥፎዉን መለየት አይችሉማ፡፡ እኛም እንዲያውቁ ብቻ ሳይሆን እንዲተገብሩም ልናስተምራቸው ይገባል፡፡>> ኢምራን ተናግሮ ሲጨርስ በረዥሙ ተንፍሶ ወንበሩ ላይ ተመቻቸ፤ ንዴቱ በንግግሩ ሳቢያ ረገብ ብሎለታል፡፡

*
   <<በጣም ጥሩ ሀሳብ ነው፡፡>> የነባት ድምፅ ከሌላኛው ስፒከር በኩል አስተጋባ፡፡ <<ዋነኛው ጥያቄ ግን እንዴት እንተግብረው የሚለው ይመስለኛል፡፡ ህጻናቱን በምን መንገድ እንዲተገብሩ ማግባባት እንችላለን፡፡ ወላጆችንስ የህጻናቱን ስልክ እንዲቀሙ የሚያነቡትንም እንዲገመግሙ ማድረግ የምንችለው እንዴት ነው? የሚለውን ብናስብበት ጥሩ ይመስለኛል፡፡>>
<<ትክክል! እስካሁን በጥሞና እያደመጥኩ ነበር፡፡>> አለ ፋሪስ ወደ ድምፅ ማጉያው ተጠግቶ <<እምም ሁላችንም አስበንበት ብንገናኝ ጥሩ ነው፡፡ እምም እንደሚታየኝ ከሆነ ግን ስራዎች እየተደራረቡብን ነው፡፡ ስራ ብንከፋፈል ጥሩ ይመስለኛል፡፡>>
<<wait! before that አንድ ተጨማሪ ስራ አለኝ፡፡ ለነነባት ነግሪያቸዋለሁ፡፡ I think ለእናንተም ኢምራን ነግሯቹሀል፡፡ ስለአህላም ጉዳይ>> አለች ፊርደውስ፡፡
<<አዎ ነግሮናል፤ እንደሰማሁት ከሆነ ልጅቱ መካሪ ጠልታለች፡፡>> አለ አሚር፡፡ <<አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ ስሜታዊ የሆኑትን ሙሳን እና ወንድማቸውን ሀሩንን እኔ ጌታችሁ ነኝ ወዳለው ፊርዐውን ሲልካቸው እኮ ይገሰጽ ዘንድ ልዝብ ቃል ተናገሩት ብሎ ነው፡፡ የእኛ ቃላትን ማጠንከር ከማቃናት ይልቅ ምን ያህል ሰዎችን ሊያጠም እንደሚችል አህላም ማሳያ ናት፡፡ ሁልጊዜ ለማስተካከል የምናስበውን ሰው ወደዚህ ህይወት ያስገባውን ምክንያት ልናጣራ ይገባል፡፡ ፊርዲ... ያንቺን አካሄድ ግን ወድጀዋለሁ፡፡ እንደጓደኛ ማቅረቡ ጥሩ መፍትሄ ነው፡፡ ብቻሽን ግን ይከብዳል፡፡ ስራ ስንመዳደብ የሚያግዙሽን ልናካትት ይገባል፡፡ በዚያ ላይ ልጁም... ኢምሩ ስሙን ማን ነበር ያልከን?... አዎ ኻሊድ እሱም ሊስተካከል ይገበዋል፡፡>> ሁሉንም አፈራርቆ አያቸው።
ኢኽላስ ለመናገር ጉሮሮዋን ስታፀዳ በስፒከሩ ውስጥ ተሰማ፡፡ <<ህ! ህ! እምም ቅድም ጀምሬ ሳስበው ነበር፡፡ ኢምራንና ሀሩን ዳዕዋዎቹን መልቀቁና አዳዲሶቹን ህጻናት መከታተል ላይ ብትሰሩ ጥሩ ይመስለኛል፡፡ አሚርና ፋሪስ ቅድም የተወያየንበትን እንዴት መተግበር እንደምንችል እቅድ አውጡ፡፡ አዲሱን የማስተማር ዘዴ ለመምህራን ማስረዳት ሊኖርባችሁ ይችላል፡፡ በትርፍ ጊዜያችሁ እናንተም በማስተማር ብታግዟቸው ጥሩ ይመስለኛል፡፡ እኔና ማሂ ፊርዲን እንረዳታለን፡፡ ነባት እንደበፊቱ እኛን coordinate ታድርግ፡፡>>
<<እኔ ግን...>> ፊርደውስ ነበረች።
<<በአህሉ ጉዳይ ላይ ፊዱ ብቻ ታግዘኝ ነው የምለው። ሀሩኔ... ትንሽ ፍሪ መሆን ያለበት ጊዜ ይመስለኛል። so አሚር ኢምሩዬን በህፃናቱ case ላይ አግዘው። ሀሩኔ ቪዲዮዎቹን መልቀቅና ኢዲት ማድረግ ላይ ስራ። ያው... ቤትህ ሆነህ ልታደርገው የምትችለው ነገር ስለሆነ ከረውዲም ጋ ትስማሙበታላችሁ። አዲሱን የማስተማር ዘዴ ደግሞ.... ሀሳብ አፍላቂው ማሂ ስለሆነ ከፋሪስ ጋ እሱ ቢመራው የተሻለ ነው -ወንዶቹን። ነቡ ደግሞ እነማሂን በሴቶቹ በኩል ከሌሎች ሴት የሚፍታሁል ቀልብ መምህራን ጋ ትደግፍ። አይመስላችሁም?>>
<<ተስማምተናል!>>
<<ጥሩ ሀሳብ ይመስላል!>>
<<እኔም ወድጄዋለሁ!>>
ሁሉም ተስማሙላት፡፡
*
<<ሄሎ አህሉ እንዴት ነሽልኝ?>> የኻሊድ ድምፅ በአህላም ስልክ ውስጥ ይሰማል፡፡
<<አለሁልህ! ጠፋህኮ የት ሆነህ ነው?>> ከአስፋልቱ ባሻገር የቆሙትን ሁለት ጥንዶች እየተመለከተች ነው፡፡ ኻሊድና ግቢ ውስጥ በመልክ ብቻ የምታውቃት ሌላ ልጅ ናቸው፡፡ ተቃቅፈዋል፡፡ ይህንን ስታይ ነበር የደወለችለት፡፡ ወዲያው ከልጅቱ ገንጠል ብሎ ሲያነጋግራት ታዘበችው
<<ኧ! እምም ቤተ-መጻህፍት፣ መጸዳጃ ማነው ስሙ... ጓደኞቼ ጋር ነኝ!>>
<<በቃ ስትመለስ ደውልልኝ እንገናኛለን!>>
<<እሺ እደውላለሁ፡፡>> ስልኩን ዘግቶ ወደልጅቱ ሲከንፍ ተመለከተችው፡፡
<<ያ አላህ ይህንን ልጅ የማስተካክለው ሰበብ አድርገኝ፡፡>> ዱዓ አደረገች፡፡ ምን ያህል ብትከንፍለት ነው በጥፋትና ክህደት መሀል እያገኘችው አንደበቷ ከስድብ ይልቅ ዱዓን የሚያፈልቀው? አጂብ!
*
<<ኢኽላስ ቢንቲ! ለምን ስለእኔ ትጨነቃላችሁ! አልሀምዱሊላህ እኔ እኮ ደህና ነኝ፡፡>> ኡስታዝ አብዱሰላም ህመማቸውን ደብቀው ከአልጋቸው ተነስተው ዊልቸራቸው ላይ ለማረፍ ይጥራሉ።           
<<ባባ! ራስህንም አታታልል እንጅ እኛ እኮ ልጆችህ ነን አይደል እንዴ እንደፈለግክ ልታዘን ይገባል!>> ማሂ ዊልቸራቸውን ወደአልጋው አስጠግቶ እንዲቀመጡበት አገዛቸው፡፡
<<ትምህርታችሁስ? የኢስላም አርበኞችንም ሚፍታህ አል-ቀልብንም ለእናንተ እኮ ነው አማና የሰጠሁት!>>
<<አታስብ ባባ የሚጠበቅብንን ሁሉ እያደረግን ነው!>> አለች ፊዳ፡፡
<<ባለፈው የነገራችሁኝ ልጆች ጉዳይ እንዴት ሆነ?>>
<<ኢምራንና ሀሩን እየተከታተሉዋቸው ነው! እኛ ሌላ ስራ ይዘናል፡፡>> አለ ማሂ፡፡
<<የምን ስራ?>> ኡስታዙ አንገታቸውን ሽቅብ ቀልብሰው ሁለቱንም እያፈራረቁ ተመለከቷቸው፡፡
<<አህላም የምትባል የፊርደውስ ጓደኛ ናት፡፡ ሀራም የሆነ ግንኙነት ውስጥ ነው ያለችው፡፡>> አለች ፊዳ፡፡

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:20


የዐጧእ ብኑ የሳር እና የቆንጆዋ ገጠሬ ታሪክ

ኢብኑ አቢ ዱኒያ እንዲህ ያወሳል፦

ዐጧእ ብኑ የሳር እና ሱለይማን ብኑ የሳር ከባልደረቦቻቸው ጋር ለሐጅ ጉዞ ከመዲና ወጡ። አብዋእ ላይ ሲደርሱ እረፍት አደረጉ።

ሱለይማን እና ባልደረቦቻቸው ለከፊል ጉዳዮቻቸው ሄዱ። ዐጧእ ከቤት ቀረና ቁሞ መስገድ ጀመረ። ከዚያም አንዲት ውብ የገጠር ሴት ወደ እርሱ ገባች፣ እየሰገደ እያለ ከፊት ለፊት ቁጭ አለች። ጉዳይ ያላ፞ት መሰለውና ሶላቱን አሳጥሮ ጨረሰና ፡— “ጉዳይ አለሽን?” አላት።

እሷ፡— “አዎ”

እርሱ፡— “ምንድን ነው?”

እሷ፡—  “ተነስ! ከእኔ ላይ ጉዳይን ፈፅም፣ ወንድ አስፈልጎኛል፣ እኔ ባል የለኝም።” አለችው። ወደሷም ተመለከተ፣ ወጣት ... እጅግ በጣም ውብ ...

እርሱ፡— “ዘወር በይልኝ! እኔንም እራስሽንም በእሳት አታቃጥይ” አላት። ከነፍሱም ማባበል ጀመረች፣ የፈለገችው ካልሆነ ብላ ችክ አለች።

ዐጧእ እያለቀሰ፡— “ወዮልሽ! ዘወር በይልኝ! ዘወር በይልኝ!” ይል ጀመር። ለቅሶውም በረታ፣ ሴቲቱ ለቅሶውንና ጭንቀቱን ስትመለከት ጊዜ እሷም አለቀሰች!!

  በዚህ ሁኔታ ላይ እያለ ሱለይማን ብኑ የሳር ከሀጃው ሲመለስ ዐጧእን እያለቀሰ ሲመለከት፣ ሴቲቱም በቤቱ ጥግ ላይ ሁና ስታለቅስ ሲያይ ምን እንዳስለቀሳቸው ሳያውቅ እነሱ ስላለቀሱ አለቀሰ።

   ባልንጀሮቻቸውም ተራ በተራ መጡ። አንድ ሰው መጥቶ ሲያለቅሱ ሲያቸው ጊዜ ስለጉዳዩ ምንም ሳይጠይቅ እሱም እያለቀሰ ይቀመጣል። ለቅሶው በረታ፣ ድምፆችም ከፍ አሉ።

ገጠሬዋ ሴት ይህን ስታይ ተነስታ ወጣች። እሱም ተነሳ፣ ሰዎቹም ገቡ።

  ሱለይማን ለወንድሙ ዐጧእ ካለ፞ው ክብርና ፍራቻ የተነሳ ስለሴትዮዋ ታሪክ ሳይጠይቀው የተወሰነ ጊዜ ቆየ። ዐጧእ ለሱለይማን ትልቅ ወንድሙ ነው። 

  ከዚያም ለሆነ ጉዳያቸው ወደ ግብፅ ምድር ሄዱና አላህ የሻውን ያህል ቆዩ። ዐጧእ በአንድ ሌሊት ተኝቶ ሳለ እያለቀሰ ተነሳ።

ሱለይማን፡— “ወንድሜ ሆይ! ምን ያስለቅስሃል?”

ዐጧእ፡— “ዛሬ ሌሊት ያየሁት ህልም!”

ሱለይማን፡— “ምንድን ነው?”

ዐጧእ ፡— “እኔ በህይወት እስካለሁ ድረስ ለማንም እንዳትናገር መስፈርት አርጌ ነው የምነግርህ”

ሱለይማን፡— “መስፈርት ያደረከው አለልህ”

ዐጧእ እንዲህ አለ፡— “ነቢ ዩሱፍን ዐለይሂሰ፞ላም በህልሜ አየሁት፡ ወደሱ ከሚመለከቱት ጋር እመለከተው ጀመር። ውበቱን ሳይ ግዜ አለቀስኩ፣ ከሰዎች መካከል ነጥሎ ተመለከተኝ።

“አንተ ሰው ሆይ! ምን ያስለቅስሃል?” አለኝ።

እኔም፡— “አባቴ እና እናቴ ይሰውልህ የአላህ ነብይ ሆይ! አንተን፣ የንጉሱን ሚስት፣ በእሷ ምክንያት የደረሰብህን ፈተና፣ በእስር ቤት የገጠመህን ነገር እና ከሽማግሌው አባትህ የዕቁብ መለየትህን አስታወስኩ” አልኩት።

ዩሱፍም (ዐለይሂሰ፞ላም) ፡— “በአብዋእ የገጠሯ ሴት ባለቤት አትገረምምን?” አለኝ።  ምን ማለት እንደፈለገ አወቅሁ፣ አለቀስኩ፣ እያለቀስኩ ተነሳሁ።

ሱለይማን፡— “ወንድሜ! የዛች ሴት ነገር ምን ነበር?”

  ዐጧእ ታሪኩን ነገረው፤ ሱለይማንም ዐጧእ እስኪሞት ድረስ ለማንም አልተናገረም፤ ዐጧእ ከሞተ በኋላ ከቤተሰቡ ለሆነች ለአንዷ ሴት ስለ ጉዳዩ ነገራት።  [አሪ፞ቃ ወል ቡካእ: 199]

በቤት ውስጥ ብቻቸውን፣ መንገደኛ፣ ለአገሩ እንግዳ ፣ እሷ እየለመነችው፣ እሱ ግን “እራቂኝ! እራቂኝ! እራቂኝ!” ይላታል። #ሰለፎቻችን_እንዲህ_ነበሩ
• እኛንም እነሱንም አላህ ይማር።

#ሼር_አድርጉ_የሚገርም_ታሪክ_ነው
#ሼር_ማድረግ_አትርሱ

https://t.me/wubtarikoch

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:18


°°~🇵🇸~°°

   •ፉደይል ኢብኑ ዒያድ ዘራፊ(ሌባ) ነበረ። በአንዲት ሴት ፍቅርም ወደቀ። ከዕለታት በአንዱ ቀን ያፈቀራትን ሴት ለማየት በሌሊት ሄደ። በቤቱ አጥር ተንጠላጥሎ ለማየት በሚሞክርበት ወቅት አንድ በዕድሜ የገፉ ሽማግሌ ተከታዩን የቁርኣን አንቀፅ ሲያነቡ አደመጠ:–

أَلَمْ يَأْنِ لِلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ أَن تَخْشَعَ قُلُوبُهُمْ لِذِكْرِ ٱللَّهِ وَمَا نَزَلَ مِنَ ٱلْحَقِّ وَلَا يَكُونُوا۟ كَٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ مِن قَبْلُ فَطَالَ عَلَيْهِمُ ٱلْأَمَدُ فَقَسَتْ قُلُوبُهُمْ وَكَثِيرٌ مِّنْهُمْ فَٰسِقُونَ

ለነዚያ ለአመኑት ለአላህ ተግሳጽና ከቁርኣንም ለወረደው ልቦቻቸው ሊፈሩ እንደእነዚያም በፊት መጽሐፍን እንደ ተሰጡትና በእነርሱ ላይ ጊዜ እንደረዘመባቸው ልቦቻቸውም እንደ ደረቁት ላይኾኑ (ጊዜው) አልቀረበምን? ከእነርሱም ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፡፡
                                   ሀዲድ:  16
🇵🇸 በተንጠላጠለበት እያለቀሰ  እንዲህ አለ:–

‏"قد آن، قد آن!"
በርግጥ ደርሷል፣ በርግጥ ደርሷል!

   🇵🇸 ፉደይል ኢብኑ ዒያድ ከዚህ ክስተት በኋላ ወደ አላህ ተመለሱ፤ ተውበትም አደረጉ ከትላልቅ መሻኢኾችም ለመሆን በቁ።

   🇵🇸 የአረብ ሀገራትንና የሻም ገዢ የነበረው ሀሩን አረሺድ ከፉደይል ኢብኑ ዒያድ የበለጠ የሚያምነው ሰው አልነበረም።ይህም የሆነው ዱኒያን ችላ ያሉና "ወሪዕ"(ሀራም ላይ ላለመውደቅ በጣም ጠንቃቃ)  ስለነበሩ ነው።


======================
ሚፍታሑል ቀልብ የቁርአን ማዕከል
======================

🛑 በኦን ላይን ቁርአን መቅራት ለምትፈልጉ
ምዝገባ ጀምረናል።
👇👇👇 ተመዝገቡ
@miftahulQelbBot


ቻናሉን ለመቀላቀል👇
T.me/miftahulQelb

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:18


የኢስላም አርበኞች
ምዕራፍ ሁለት
ክፍል ሶስት
(ረያን ና ሪና ሁዳ)
.
.
ከደቂቃዎች በፊት እሷ ላይ በሹክሹክታ ሲወረወርባት የነበሩት ቃላት ረገብ ብለዋል። ምናልባት ከፀባዬ ሰናዩዋ እና ባለ ትዳሯ ፊርደውስ ጋ ስለተቀመጠች ይሆናል። አህላም ፊቷ ላይ አግራሞት ይነበባል። አንደበቷ ሊላቀቅ ይልና መልሶ ይቆለፋል። ከገለጠችው መፅሀፍ ይበልጥ የምታየው ፊርደውስን ነው።
<<ፊርዱ...>> አህላም የምታነበውን መፅሐፍ አጥፋ ወደፊርደውስ ዞረች።
<<ለምንድን ነው ግን ዶርም ውስጥ ማደር ያቆምሽው?>>
<<አግብቼ! አሁን ቤቴ ነው የምኖረው!>> ፊርደውስ አይንዋን ከመጸሀፉ ላይ ሳትነቅል መለሰችላት፡፡
<<ማሻ አላህ! ወላሂ በጣም ደስ ይላል፡፡ ግን...>> አህላም የምትናገረው ጠፋባት <<እንዴት ተገናኛችሁ? ማለቴ በፊት እኮ ከእነፋሪስ ጋር ነበር የምትውይው፤ አሁን ግን ሁላችሁም ተቀይራቹኃል፡፡ ማለት እምም...>>
"ከኢምሩ ጋር ባጋጣሚ ነበር የተገናኘነው፡፡ ሁላችንም መጥፎ ህይወት ውስጥ ነበርን፤ አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ እነሱን ሰበብ አድርጎልን እንደምታይው ተለወጥን፡፡ አልሀምዱሊላህ፡፡>>
<<አየሽ እኔም የኻሊድ መለወጫ ሰበብ ነው መሆን የምፈልገው፡፡>> አንሾካሾከች።
ፊርደውስ መፅሀፏን አጥፋ ከኢምራን በወረሰቻቸው የሳይኮሎጂ እውቀቶች ከመረመረቻት በኋላ <<ኢምሩ እኮ!... እኔን ለመለወጥ ሲጥር...... አንድ ቀን ቀና ብሎ እንኳ አይቶኝ አያውቅም!>> አለቻት፡፡
አህላም ቀና ብላ ስታያት <<አዎ!>> አለች.
*
ኢምራን የሱደይስና አማን አባት፤ ዶክተር ኢብራሂም ከሚሰሩበት ሆስፒታል ፊትለፊት ከምትገኘው ካፌ ውስጥ ተቀምጧል፡፡ ዶክተሩ ሚፍታህ አል-ቀልብ ድረስ ለመምጣት ሲቸገሩ ነው  እስከሆስፒታላቸው በር ድረስ ቀርቦ ሊያናግራቸው ከካፌዋ መሰየሙ!
<<አሰላሙአለይኩም! ኢምራን አንተ ነህ?>> ከልጆቻቸው ፋይል ላይ ፎቷቸውን የተመለከተው አባት ከፊቱ ወንበር ስበው ተቀመጡ፡፡
<<አዎ ኢምራን ነኝ! ከስራዎ ስላቋረጥኩዎት በጣም ይቅርታ ዶክተር!>> አለ ኢምራን ለሰላምታቸው ምላሽ ሰጥቶ፡፡
<<ኧረ ችግር የለውም! ጥቂት ጊዜ አይጠፋም>> ወንበሩ ላይ ተመቻቹ፡፡
<<ኦውውውው ምን የሚል መፅሀፍ ነው?>> አሉ ከኢምራን እጅ ላይ ወደአዩት መፅሐፍ እየጠቆሙ፡፡
<<የኦሾ <ሪበቤሊዬስ ስፕሪት> ነው፡፡ አንብበውታል?>>
<<እንዴ? በሚገባ!>> ፈገግ አሉ፡፡
<<ምን አገኙበት?>>
<<ከጠባብዋ ጊዜዬ ላይ ቀንሰህ የጠራኸኝ ስለመፅሀፍ እንድናወራ ነው እንዴ?>> ሣቁ፤ ኢምራንም ላለማሳፈር ፈገግ አለላቸው፡፡ <<እምም ያው መፅሀፉ ስለብዙ ነገሮች ያወራል፡፡ ራስን ስለመመልከት፣ አዲስ ኃይማኖትን ስለመፍጠር፣ ጭንቅላትን ስርአት ስለማስያዝ ስለብዙ ነገሮች ያነሳል፡፡ ብዙዎቹ ኃሳቦች ግን አሳማኝ አይደሉም፡፡>> አሉ ዶክተሩ በሰላት ምክንያት የበለዘ የሚመስለውን ግምባራቸውን እያሻሹ፡፡
<<ጥሩ አሳማኝ የሆኑትንና ያልሆኑትን ሀሳቦች በምን ለዩዋቸው?>>
<<ምን አይነት ጥያቄ ነው? አመዛዝኜ ነዋ! ይልቅ ስለጠራህብኝ ጉዳይ እንነጋገር!>>
<<ልጆችዎ ይህንን መፅሐፍ ሲያነቡ አገኘሁዋቸው>>
<<እና...?>> አሉ ዶክተሩ፡፡ ኢምራን የጠበቀው ምላሽ አልነበረም፡፡ <<መፅሀፉ ውስጥ እኮ ጥሩ ያልሆኑ ሀሳቦች አሉ፡፡ በዚያ ላይ...>>
ዶክተሩ አላስጨረሱትም <<መጸሀፍትን ማንበብ ምሉዕ ሰው ያደርጋል እንጅ ምንም ጉዳት አያመጣም፡፡ በዚያ ላይ የሚነበብ ነገር አይመረጥም፤ የምትወስደውን ሀሳብ ብቻ ነው መምረጥ ያለብህ! ገባህ አይደል?>>
<<ልጆቹ እኮ ገና ህጻናት ናቸው? የሚወሰድና የሚጣለውን ሀሳብ በምን ይለያሉ?>> የኢምራን ድምፅ ከወትሮው ይበልጥ ጨምሮ ነበር፡፡
<<ልጆችህ ጎበዞች ናቸው ብላችሁ የሸለመችሁዋቸው ራሳችሁ ናችሁ፡፡ ስለዚህ በልጆቼ ጭንቅላት አትጠራጠር፡፡ ይቅርታ! ትንሽ ስራ አለችብኝ! አፍወን!>> ዶክተሩ ካፌዋን ለቅቀው ወጡ፡፡ ኢምራንም የጠጣውን የማኪያቶ ሂሳብ ከፍሎ መኪናው ውስጥ ገባ፡፡ መኪናዉን ወደሚፍታህ አል ቀልብ አስወነጨፋት፡፡ ሀሩን ቢኖር ኖሮ በንዴቱ ላይ ይነጫነጭ ነበር፡፡
*
ፊርደውስ የተሳፈረችበት ታክሲ የጋሪ ያህል ተጓተተባት፡፡ የህጻናቱን መድረክ ትወደዋለች፡፡ በሚኮላተፍ አፋቸው ግጥም፣ መነባንብ፣ ጭውውት ሲያቀርቡ፤ የሀፈዙትን ቁርዓን ሲቀሩ መስማት ያስደስታታል፡፡ ዛሬ ግን ከአህላም ጋር
ቤተመጻህፍቱ ውስጥ ስለቆየች ለስብሰባው ካልሆነ የህጻናቱ መድረክ ጋር መድረስ አትችልም፡፡ ጉዞዋ ሲረዝምባት በኢኒስታግራምዋ የተለቀቁት ቪዲዮች ምን ያህል ተመልካች እንዳላቸው ለማየት የበይነመረብ ግንኙነትዋን ከፈተች፡፡ ከመቅጽበት ራሷን ከአህላም የቴሌግራም አካውንት ላይ ፕሮፋይል የተደረጉ ፎቶዎችን ሲመለከት አገኘችው፡፡ ፎቶዎቹን ጥራታቸው ተስተካክሎ እንደተመለከተቻቸው በድንጋጤ አይኖቿን ጨፈነች፡፡
*
ሁለት ህጻናት ከመድረኩ ላይ ቆመዋል፡፡ ከታዳሚያኑ መሀከል ኢምራንና አሚር ጎንለጎን ተቀምጠው ፕሮግራሞቹን ይከታተላሉ፡፡
<<የመጀመሊያው ፕሎግላማችንን ከማቅለባችን እ.. እእ በፊት አማንና ሱጀይስ መድለኩን በቁርዓን ይከፍቱልናል፡፡>> አለ ከህጻናቱ አንዱ፡፡ ወዲያው አማንና ሱደይስ ከመድረኩ ላይ ተሰይመው በአስገራሚ ድምጽ ሁለት አጫጭር ሱራዎችን ቀርተው ወረዱ፡፡
<<ማሻ አላህ! የሚገርም ጭንቅላት ነው ያላቸው ኣ ኢምሩ? በጥቂት ጊዜ ውስጥ እኮ ነው ሀፊዝ የሆኑት፡፡>> አለ አሚር ወደኢምራን ተጠግቶ፡፡ ኢምራን ግን አልመለሰለትም፡፡ ዙሪያውን የከበቡትን ተማሪዎች እየቃኘ አላደመጠውም ነበር፡፡
<<ኢምራን ምን እያሰብክ ነው?>> አለው አሚር፡፡
<<እነዚህን ልጆች እየጠቀምናቸው አይደለም፡፡ ወላሂ እየገደልናቸው እንደሆነ ነው የሚሰማኝ!>>
<<ኧረ እንደሱ አትሰብ አኺ! እኛ እኮ ከሌሎች ትምህርት ቤቶች በተሻለ ጥሩ አካዳሚክ እውቀት እንዲኖራቸው እያደረግን ነው፡፡ በዚያ ላይ ስለዲናቸው እውቀት እንዲኖራቸው እየለፋን ነው፡፡>>
<<እኔም እየገደልናቸው ነው ያልኩህ ለዚህ ነው!>>
<<ማለት አልገባኝም?>> አሚር ፊቱን ሙሉበሙሉ ወደኢምራን አዞረ፡፡
<<በኋላ ስብሰባው ላይ እንወያይበታለን>> አለ ኢምራን አሁንም አይኖቹን በህጻናቱ ላይ እያንከራተተ፡፡
.
.
.
.
.
ይቀጥላል!


@wubtarikoch

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:17


ፊርደውስ እጆቿንዘርግታ እያቀፈቻት <<አብረን እንድናጠና ፈልጌ ነበር፤ የሚመችሽ ከሆነ!>> አለቻት በፈገግታ ተሞልታ።
*
ሱደይስ፣ አማንና ሀያት ሀሩንን ተከትለው ቤተመጸሀፍቱ ውስጥ ገቡ፡፡ ቤተመጸሀፍቱ ለጊዜው ጭር ብሏል፡፡ ኸድር መፀሀፍቶቹን ይደረድራል፡፡
ሀሩን ኸድርን <<መጥተናል፤ ንገረው!>> ካለው በኋላ አረንጓዴ ምልክት ካለው የመጸሀፍት መደርደሪያ ፊት ቆመ፡፡ እነሀያተም ተከተሉት፡፡ መደርደሪያው ወደቀኝ ተንሸራቶ ተከፈተ፡፡
<<OMG! What is happening? የሆነ fantasy ፊልም ነው እኮ የሚመስለው!>> ሀያት በአግራሞት ጮኸች፡፡
አማን መዳፉን በሰፊው የተከፈተ አፉ ላይ አስቀመጠ፡፡ የሱደይስ አይኖችም በመነጽሩ ውስጥ ይበልጥ ጎልተው ታዩ፡፡ ገፋ ገፋ አደረገው ክብ ወፍራም መነጽሩን፡፡ ትላልቅ ስክሪኖች ያሉበትን ክፍል አልፈው የቀረጻና ኤዲቲንግ መሳሪያዎችን የያዘው ነጭ ክፍል ውስጥ ገቡ፡፡ አማካይ ቦታ ላይ ከተገተረው ትልቅ ጠረጴዛ ዙሪያ ከተደረደሩት አምስት ወንበሮች መሀከል በአንደኛው ላይ ኢምራን ተቀምጧል፡፡
ኢምራን፡- <<አሰላሙዓለይኩም፤ እንዴት ናችሁ?>> ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደእነርሱ ቀረበ፡፡
<<ወዓለይኩም አስሠላም ኡስታዝ!>> በአንድነት መለሱ፡፡
<<ይህ የምታዩት የኢስላም አርበኞች የተሰኘ ቡድን መስሪያ ቤት ነው፡፡ እዚህ የምታዩን ሁላችንም የቡድኑ አባላት ነን፡፡ እናንተም ወደፊት የቡድኑ አባላት እንድትሆኑ ተመርጣችሁዋል!>>
<<Wow it is incredible!!>> ሀያት በደስታ ዘለለች፡፡
የአማን መዳፎች አሁንም ከተከፈተው አፉ ላይ አልወረዱም፡፡ ሱደይስ ወፍራም ክብ መነጽሩን ገፋ ገፋ አደረገ፡፡
<<በመጀመሪያ ግን ጥቂት ጥያቄዎችን እጠይቃችሁዋለሁ፤ እሰኪ <ሮል ሞዴላችሁ> ማን እንደሆነ ንገሩኝ!>>
ሀያት ፈጠን ብላ <<ካት ውማን፣ ሲንደሬላ፣ ፀጉረ ረዥሟ ራምፑንዘል፣ ዘንድሮ ሚስ ዩኒቨርስን ያሸነፈችው፣ እምም...>>
<<ይበቃል!>> በዝምታ ሲያደምጥ የነበረው ሀሩን አቋረጣት <<አማንና ሱደይስስ?>>
ሁለቱም ፀጥ አሉ፤ ፀጥጥጥጥ! ለረዥም ጊዜ፡፡ ኢምራንና ሀሩንም ሊጫንዋቸው አልፈለጉም፡፡ የአንድ ፈላስፋ ስም ለመጥራት ተቸግረው እንደሆነ ጠርጥረዋል፡፡
<<ጥሩ! በቃ ተውት! ለዛሬ ይበቃል! ካሁን በኋላ የሚኖሩን ጥያቄዎች በፖስታ ታሽገው በእጆቻችሁ ይደርሷቹሃል!>>
ሱደይስ፡- <<ለምን በሶሻል ሚዲያ አትልኩልንም? ማለቴ...>> ክብ መነጽሩን ገፋ ገፋ አደረገ፡፡ <<ለሁላችንም እንዲቀል!>>
<<ሞባይል ትይዛላችሁ እንዴ?>> ሀሩን በመገረም ጠየቀ። አማን የስድስተኛ፣ ሱደይስ ና ሀያት ደግም የሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች ስለሆኑ ሞባይል ይኖራቸዋል ብሎ አልጠረጠረም ነበር፡፡
ሶስቱም ሳቁበት፤ ረዥዥዥም ሳቅ!
<<ጥሩ! ስልክ ቁጥራችሁን እዚህ ላይ ፃፉ፤ ከጎን ስማችሁንም ጨምሩበት!>> ኢምራን ሌጣ ወረቀት ለአማን አቀበለው፡፡
*
ሀሩን ልጆቹን ስትጠብቃቸው ወደነበረችው ኮስተር ሸኝቷቸው ተመለሰ፡፡ ኢምራን የልጆቹን ፋይል እያገለበጠ ነበር፡፡ <<ምን እያደረግክ ነው?>> አለው ሀሩን፡፡
<<ወላጆቻቸውን ማነጋገር ሳይኖርብን አይቀርም!>>
ሀሩን <<ጥሩ! እኔም በልጆቹ ስልክ ቁጥር የተከፈቱ አካውንቶችን ልፈልግ>> ብሎ ከአንደኛው ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡ ለጥቂት ደቂቃዎች ሞባይሉን ሲጎረጉር ቆይቶ <<ኢምራን!>> ብሎ ተጣራ፡፡ ድምፁ ድንጋጤውን ያሳብቃል፡፡
<<ምነው?>> አለ ኢምራን ድንገት የተለወጠው ፊቱ አስገርሞት፡፡
<<ባለፈው በተለቀቁት ቪዲዮዎች ዙሪያ መወያየት የሚፈልጉ ሰዎች አሉ፡፡ ስማቸው ለየት ያለ ነው፤ በኢንቦክስም አናግረውኛል ያልኩህን አስታወስክ?>>
<<አዎ! አዎ! አስታወስኩ!>> አለ ኢምራን ጭንቅላቱን እያወዛወዘ፡፡
<<ልጆቹ.....>> ተንተባተበ።
<<ተናገራ..>>
<<አማንና ሱደይስ ናቸው>> ኢምራን ድንጋጤ፣ አግራሞት፣ ፍርሃት በቅፅበት ተፈራረቁበት። ምናልባት ልጆቹ በእጃቸው ስለሆኑም ደስታም ተሰምቶት ይሆናል።
<<ሱብሃነላህ!>> አለ በመዳፉ ፂሙን እያፍተለተለ።
.
.
.ይቀጥላል!..

@wubtarikoch @wubtarikoch

ውብ ታሪኮች®

21 Jan, 00:17


የኢስላም አርበኞች
ምዕራፍ ሁለት
ክፍል ሁለት
(ረያን እና ሪና ሁዳ)
.
.
አማን፡- <<<ኒቼ> እንደዚህ አይፃፍም! ለምንድነው የማትሰማኝ!? <ዜድ> መጨመር አለባት!>>
ሱደይስ፡- <<አንተ ነህ ልትሰማኝ የሚገባው ታላቅህ እኮ ነኝ!>>
አማን፡- <<ታላቄስ ብትሆን!? ከተሳሳትክ አርምሀለሁ!>>
ሱደይስ፡- <<አሙ!..አንተ እኮ ሰው ያለውን ሁሉ ስለምትከተል ነው፡፡ ኦሾ <ራሳችሁን ሁኑ> ይል የለ? ሌሎች ቢጨምሯትም እኔ ግን ኒቼ ውስጥ የ<ዜድ> ድምፅ ስለሌለ አወጣሁዋት!>> ሁለቱ ብላቴና ወንድማማቾች እርስ በእርስ ይከራከራሉ።
ከፊታቸው ወንበር ስቦ በዝምታ ክርክራቸውን ሲያደምጥ የነበረው ኢምራን ጉሮሮውን ጠራረገ፡፡ ሁለቱም በድንጋጤ በድን ሆኑ፡፡ በመጀመሪያ ኢምራን ላይ አፈጠጡ ከዚያም ርስበርስ ተፋጠጡ፡፡ አማን ባይሳካለትም ከጎኑ የተደረደሩትን የመፅሀፍት አርእስት በመዳፎቹ ለመሸፈን ተጣጣረ፡፡

<<እያነበባችሁ ነው?>> ኢምራን ፈገግ እንዳለ ጠየቃቸው፡፡
<<አዎ ኡስታዝ!>> ሱደይስ መለሰለት፡፡
<<ምንድነው የምታነቡት?>> ኢምራን አይኑን ወደመጸሀፍቱ ወረወረ፡፡ አማን ተስፋ ቆርጦ እጆቹን መለሳቸው፡፡
<<የኦሾ እና የኒቼ መጻህፍት ናቸው!>> ሱደይስ ወፍራም ክብ መነጽሩን ሽቅብ እየገፋ መለሰ፡፡
<<ሲደብረን እያነበብናቸው ነው፡፡>> አማን አገዘው፡፡
<<ጥሩ! ምን አገኛችሁባቸው?>> ኢምራን በእንቅስቃሴያቸው የሚያስቡትን ለመገመት ይጥራል፤ ሳይኮሎጂስትነቱ ደግሞ ጠቅሞታል፡፡
<<ዝምብለው ነው የሚቀባጥሩት፤ ምንም አላመንናቸውም!>> አማን መለሰ፡፡ ይህንን ሲናገር ብቻ በእጁ አፍንጫውን ሶስት ጊዜ ሞዥቋል፡፡ ዓይኖቹም ከኢምራን ላይ ተነቅለው መፃህፍቱ ላይ አርፈዋል፡፡ ኢምራን ሁሉንም እያስተዋለ ነው፡፡
<<ጥሩ ትምህርታችሁን እንደጨረሳችሁ ቢሮ እፈልጋችሁዋለሁ፡፡ ቲቸር ሀሩን ይወስዳቹሇል፡፡>> አተኩሮ ተመለከታቸው፡፡
<<እሺ ኡስታዝ>> በአንድነት መለሱ!

*
ፊርደውስ የዩኒቨርስቲው ቤተመጽሀፍ ውስጥ ናት፡፡ የገለጠችውን ባለብዙ ገጽ መፅሐፍ እንዳታነብ ከፊቷ የሚንሾካሸኩት ሁለት ተማሪዎች ሀሳቧን ሰርቀዋታል፡፡ ጠየም ያለችው ጥቁር ሂጃብና ቡኒ ጅልባብ ለብሳለች፡፡ ቀይዋ ተመሳሳይ ቡኒ ጅልባብ እና ነጭ ሂጃብ ነው ያደረገችው፡፡
<<ደግሞ እኮ አታፍርም! ደኅና ነገር እንደሰራ ሰው ትኮፈሳለች፡፡>> አለች ጠይሟ ልጅ በእጇ ከፊርደውስ ጀርባ እየጠቆመች፤ ፊርደውስ ለመዞር ቃጥቷት ነበር፡፡
<<የዲን እውቀት ባይኖራት እንኳ ምን አለ? በእሷ ላይፈረድ ይችላል! ለስሙ ቀርታለች እንጅ...>>
<<አሁን እኮ አዋቂው ነው የሚያጠፋው! አላህ እኛንም ይጠብቀን እንጅ! እሷማ መስማት አቁማለች፡፡ <አይጠቅምሽም የብዙ ሴቶችን ህይወት ያበላሸ ነው፤ ግንኙነታችሁም ሀላል አይደለም!> ብትባል እምቢኝ አለች፡፡ ምን ይደረጋል?>>
ፊርደውስ መታገስ አቅቷት ፊቷን አዞረች፡፡ ከላይብረሪው በር ላይ ጥቁር ረዥም ቀሚስና ጥቁር ሂጃብ የለበሰች ረዥም ወጣት ተመለከተች፡፡ አወቀቻት፤ አህላም ናት፡፡ ላይብረሪው ውስጥ የተሰበሰቡት ተማሪ በመላ አፍጥጠውባታል፡፡ ገሚሶቹ ያንሾካሽካሉ፤ ገሚሶቹ በዝምታ ያዩዋታል፡፡ አህላም ሁሉንም ካስተዋለች በኋላ በንዴት እጇን አወናጭፋ በመጣችበት ተመለሰች፡፡ ፊርደውስም ተከተለቻት፡፡

*
የኢምራን ቢሮ ምስቅልቅሏ ወጥቷል። ጠረጴዛው በቀለም ባሸበረቁ ፋይሎች ተሞልቷል። ኢምራን የጠፋውን ፋይል ፍለጋ መደርደሪያውን ሲያምቦረቋቁስ ሀሩን የእንግዳ ማስተናገጃ ወንበሩ ላይ ተቀምጦ ያየዋል።
<<ሳሊም ምን ያህል እንደናፈቀህ አታውቅም!?>> አለ ሀሩን ዝምታውን ለመስበር።
<<ከሰው ጋር እንዳታጣላኝ፡፡ ሁልጊዜ እየጠየቅኩት!?>> ኢምራን የጠፋውን ፋይል አገኘው መሰል ተሽከርካሪው ወንበር ላይ ተቀምጦ አንዳች ነገር መሞነጫጨር ጀመረ።
<<ራሱ ነው <አጎቴ ኢምራን ናፍቆኛል> ያለው!>>
<<አፉን ፈትቶ?>> ኢምራን የሚፅፍበትን እስክርቢቶ አስቀመጠው።
<<ይህንንም ሳታውቅ ነው በየቀኑ እጠይቀዋለሁ የምትለው?>> ሳቀበት፡፡
<<ሀሩኔ.......ከራውዲ ጋር ልትስማሙ አልቻላችሁም?>> ኢምራን ወሬ ለመቀየር ሞከረ፤ ተሳካለት፡፡
<<ምንም መፍትሄ የለውም!>> አቀረቀረ፡፡
ኢምራን ከወንበሩ ተነስቶ ትከሻውን ያዝ አደረገውና <<አብሽር!>> አለው።
ሀሩን ና ራውዳ ተጋብተው ሶስት አመት ኖረዋል፡፡ ሳሊምንም ወልደዋል፡፡ ሀሩን ግን ለቤተሰቡ የሚሆን ጊዜ አልነበረውም፡፡ በስራ ደክሞ ቤት ይገባል፤ ይተኛል፡፡ አንዳንዴም ሚስጥራዊው ዋሻ ውስጥ ተኝቶ ያድራል፡፡ ህይወቱ ከመድረሳው ጋር ተቆራኘች፡፡ ኡስታዝ አብዱሰላም ይህንን ፈርተው ነበር ሚስጥራዊው ዋሻ ውስጥ ተልዕኮ የተሰጣቸው በመላ አምስት አመታትን ብቻ እንዲሰሩ የወሰኑት፡፡ የሀሩን ጉዳይ ግን አስጨንቋቸው ብዙ ጊዜ ከሚጠይቀው የቤተመጻሕፍት ሀላፊነቱ አንስተው በተማረበት የኮምፒውተር ሙያ ቡድኑን እንዲያገለግል አደረጉት፡፡ ለውጥ ግን የለም፤ የተቀረፁ ዳዕዋዎችን በየማህበራዊ ድረገጹ ሲለጥፍ፣ የተበላሹ ኮምፒውተሮችን ሲጠግንና ሲያስተምር ይውላል፤ ያድራል፡፡ ከራውዳ ጋር ሲጣሉ መልሰው በሽምግልና ሲታረቁ ኖሩ፡፡ የሀሩን ባህሪ ግን አልተለወጠም፡፡ ራውዳ መታገስ ሲያቅታት እንዲፈታት ጠየቀችው፤ ሀቋን መጠበቅ አቅቶታል፤ ግን ሊፈታት አልደፈረም። በጣም ይወዳታል። ለልጁም አሰበ። ራውዳ የሀሩንን የማፈግፈግ ምክንያት ብታውቅም፤ መፍትሄ ማስቀመጥ ስለነበረባት ውሳኔ ላይ እስከሚደርስ ቤተሰቦቿ ጋ ሄዳለች።
<<ልጆቹን የፍልስፍና መፅሐፍ ሲያነቡ አላገኛቸውም መሰለህ?>> አለ ኢምራን ድጋሚ ርዕስ ቀይሮ ሀሩንን ከገባበት መጥፎ ስሜት ለማውጣት፡፡
<<እነማንን?>> ሀሩን እንደመባነን አለ፡፡
<<ሱደይስና አማንን!፤ ከኸድር እንደተረዳሁት ከሆነ ሁልጊዜ የፍልስፍና መጽሐፍትን ነው የሚያነቡት፡፡>>
<<ይገርማል!! እና በሌሎች ልጆች ልንቀይራቸው ይገባል? ወይስ..ምን አሰብክ?>>
<<አይ! አይ! ልናስተካክላቸው ነው የሚገባው!>>
<<በምን መንገድ?>>
<<በመጀመሪያ ወላጆቻቸውን እናናግራለን፡፡ ከዚያ ፈተናዎችን እንሰጣቸዋለን!>>
<<ልክ እንደነአሚር ነው?>>
<<በፍፁም! ለእነሱደይስ ጥያቄ ብቻ ነው የምንጠይቃቸው መልስ ማምጣትም አይጠበቅባቸውም!>>
<<እስኪ እናያለን አሁን ሁሉንም ይዣቸው ልምጣና እናናግራቸው!>>
<<እሺ ጥሩ!>>
*
አህላም ቤተ-መፅሀፍቱን ለቅቃ እየተካለበች ስትወጣ ፊርደውስ ተከተለቻት። በልጆቹ ንግግር በጣም ተንገብግባለች። አረማመዷ ራሱ የተስተካከለ አይደለም። ስትወላከፍ በእጇ የያዘችው መፅሀፍ ወደቀባት።
<<አህሉ!፤ አህሉ!፤ አህሉ!!....አንዴ ጠብቂኝ!>> ፊርደውስ መፅሀፏን ሰብስባ ለመራመድ ወደምትቸኩለው አህላም እየከነፈች።
<<አቤት!>> አህላም አይኗ በቁጣ እንደተንቀለቀለ ፊቷን አዞረች፡፡
<<አንዴ ላናግርሽ ነበር!>>
<<ስለምን? አንቺም እንደሌሎቹ ልትጮሂብኝ ነው? ራስሽን ንፁህ አድርገሽ <የአላህን ትእዛዝ የተላለፍሽ ከንቱ!> ብለሽ ልትዘልፊኝ? ሲጀመር እዚህ ውስጥ ማን አስገባኝና!? እናንተ አይደላችሁም!? አናግሬው እንኳ ከማላውቀው ልጅ ጋር <አብራችሁ ናችሁ!> እያላችሁ አልጮሀችሁብኝም!? ያኔ <ውሸት ነው!> ስላችሁ አምናችሁኛል እንዴ? በፍፁም! ለእናንተ እልህ ግን አብሬው ሆንኩ! ምን ይዘጋሻል!? ተሳድበሽ አትሄጂም ነበር? ደግሞ እንደምትሉት አይደለም፡፡ ለሌሎች ሴቶች መጥፎ ሊሆን ይችላል፡፡ እኔን ግን ይወደኛል፡፡ ወደአላህ ያቃርበኛል እንጅ አያራርቀኝም! እናንተ ምን ታውቃላችሁ? ችግር ካለበትም እኔ አስተካክለዋለሁ!>> እየተንሰቀሰቀች አነባች፡፡