ቅዱሳት መጻሕፍት @holy_scriptures Channel on Telegram

ቅዱሳት መጻሕፍት

@holy_scriptures


በዚህ ቻናል

👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ::
👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ::
👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ።

⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️

@Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት (Amharic)

ቅዱሳት መጻሕፍት እንዴት ነህ? እና ምን ነው? ይህ በተጨማሪ እናት እና ሰው ላይ እንዲሂድ የሚያስችል ድምፅ ነው። መጻሕፍት ቅዱሳትን ለማየት የሚከተለውን መቆየታዊ ሥራዎች ላይ ተከታተው። ለዚህ መጻሕፍትን እርስዎ ይቀርቧል። በተጨማሪ ወንድም ማህበር እስከ አገር አለቆች ከተገኘ አድንጀት አቅርቦ ከማድረግ በፊቴ ነው። ይህ ሶስተኛ እናት ለተመሰገን መጻሕፍትን ስትከተለውን በድምፅ ያሳውቃሉ። የብእስትንና መንፈስን የሚለጥ እና በድምፅ እንዴት ማየት እና በእንግሊዝኛ ለውጥ። እዚህ እርሶ የቅዱሳት መጻሕፍት ሶስተኛ እናትን ይከባበራል። በተጨማሪ በምትከበሩ መጻሕፍትን ይቀርባሉ።

ቅዱሳት መጻሕፍት

16 Feb, 18:35


የቀጠለ...

⏱️ቢዚ - ቢዚ፤ ለሁሉ ጊዜ አለው ወይስ አለን?



                    በጋሽ ንጉሤ ቡልቻ


ይረዳን እንደ ሆነ እስቲ መላ ልምታ፡፡ በጎ ትብብራችሁን ስጡኝና ይህን ጥያቄ በጥሞና መልሱልኝ “ለመሞት አንድ ወር ቀርቶሃል የምትሠራውን ሁሉ በነዚህ ሠላሳ ቀናት ጨርስ” ብትባሉ ቀኖቹንና ሌሊቶቹን ምን ታደርጉባቸው ነበር?
 
ብጣሽ ወረቀት አውጡና የምታደርጓቸውን ነገሮች በቅደም ተከተል ጻፉዋቸው፡፡ ልምምዱ ምናልባት ዋና የምትሉትን ዋና ካልሆኑት ለመለየት ይረዳችሁ ይሆናል፡፡
 
የሕይወታችሁ ዋና ዓላማ ምንድን ነው? የደም ግፊታችሁን እየጨመረ፣ ናላችሁን እያዞረ፣ ትንፋሽ አሳጥቶ የሚያስሮጣችሁን ነገር ሁሉ ከዚህ ዋና ዓላማ አንጻር ፈትሹት፡፡ ወደ ዓላማው የሚፈስ ነባር ወንዝ ነው ወይስ በየመስኩ የፈነዳ መድረሻው ያልታወቀ የውሃ ምንጭ? የክርስቶስ ተከታይ ዋና ዓላማ ምንድን ነው የተባለ እንደሆነ ሐዋርያው ጳውሎስ ባጭሩና በግልጽ ከተናገረው ከዚህ ጥቅስ የተሻለ መግለጫ አላገኘሁም፡፡ “አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፣ እንግዲያውስ ሁሉ ሞቱ በሕይወትም ያሉትም ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ፡፡” 2ኛ ቆሮ 5፡13
 
የክርስቶስ ተከታይ ግለ ሰብም ሆነ ማኅበረ ሰብ የሕይወት ዓላማው ንድፍ ተሠርቶለት አልቋል፡፡ የምንሠራው ሁሉ የምናስበው ሁሉ የዚህ ዋና ንድፍ (Master Plan) አካል ካልሆነ ሕገ ወጥ ግንባታ ነው፤ ለፍቶ መና ነው፡፡ እያንዳንዱዋ የእንቅስቃሴ ቅንጣት መፈተሸ ዋጋዋም መተመን አለባት፡፡ መሮጥ ብቻውን ዋጋ ቢስ ነው፤ ሕይወት መሮጫ ግብ ይሻል፤ ግቡም በአንጻሩ የመገስገሻ መስመር አለው፡፡ ሐዋርያው ትንፋሽ ሊሰበስብ ሲቃረብ ሩጫ ጨረስኩ ሳይሆን ‹‹ሩጫውን ጨረስኩ›› ማለቱ የተሰመረ መንገድ፣ የሚደረስበት ግብ መኖሩን  ሲያመለክተን ነው፡፡
 
የቢዚነት ጉዳይ ግን ከዓላማ አንጻር ብቻ ሳይሆን በጊዜ አስተዳደር አንጻርም ሊታይ ይገባል፡፡ ጊዜ ከፈጣሪ የተሰጠን ሀብት ነው፡፡ ጊዜ ሀብት ከሆነ እንግዲያው እያንዳንዳችን “መጋቤ ጊዜያት” ሆነን በዚህ ሀብት ላይ ተሹመናል፡፡ የጊዜ መጋቢነት እንዴት ይከወን ስንል ባለ ሙያዎች ከሚመክሩን መካከል ሦስቱን ብቻ ልጥቀስ፡-
 
ጊዜዬ የት ጠፋ? ምን አደረግሁት? እያልክ የምትጠይቅ ከሆነ ሥራዬ ብለህ የዕለት ዕለት እንቅስቃሴህን ለተከታታይ ሰባት ቀናት ያደረግከውን ነገር ስም እየሰጠህ ልትጽፈው ትችላለህ፡፡ ከሳምንቱ በኋላ የጊዜ አጠቃቀምህን በዐይነቱ ስትሰድረው ጊዜህ ምን ላይ እንደዋለ የጊዜ ምጋቤ ባህርይህን ትረዳዋለህ፡፡ ያኔ ያላግባብ የባከነ ወይም በቂ ጊዜ ያልተሰጠው ምን እንደሆነ ግልጽ ይሆናል፡፡
 
ይህ የጊዜ ውሎ ግምጋሜ ወደ ሁለተኛው ዋና ነገር ይመራሃል ይህም ጊዜህን የሚሰርቁ የጊዜ መንታፊዎቸን ለይቶ ማወቅ ነው፡፡ ከታወቁት የጊዜ መንታፊዎች መካከል፡-

👉መወላወል (የቱን ላንሳ የቱን ልጣል)
👉ዝርክርክነት (ካርዱን የት ነበር ያደረግኩት)
👉መግቻ የሌላቸው የስልክ ጥሪዎች
👉ነገ ይደርሳል እያሉ መሳነፍ
👉ተራ/ወረፋ ጥበቃ
👉ጥድፊያ (ጥድፊያ ሲበዛ ፍጥነት ይቀንሳል ይባላል)
👉ድንገት የሚከሰቱ መስተጓጉሎች ይገኙበታል፡፡

እነዚህን የጊዜ ሌቦች እንዴት ነቅተህ እንደምትጠብቅ ከራስህ ጋር ተመካከር፡፡
 
ሦስተኛው ርምጃ ለሕይወትህ ዓላማ መሳካት የሚረዳ ከአንተ ባህርይና ሁናቴ ጋር የሚጣጣም የጊዜ ሰሌዳ መንደፍ ነው፡፡ የጊዜ መርሃ ግብር እንደሚያወጡት ቀላልነት ሳያዛንፉ መከተሉ ቀላል አይደለም፡፡ ላወጣኸው የጊዜ ሰሌዳ መገዛት ቢያቅትህ እንደገና መከለስና ማሻሻል ምንም ነውር የለበትም፡፡
 
ይህን ሁሉ ስታደርግ ልብ ማለት የሚገባህ ሕይወት ሥራ ብቻ÷ የግል ኑሮ ብቻ እንዳይደለ መገንዘብ ነው፡፡ የሥራና የዕረፍትን ሚዛን፣ የግልና የማኅበር ኑሮን ሚዛን፣ የዕለቱንና የዘላለሙን ሚዛን የሚጠብቅ የሕይወት ስልት መቀየስ ሁሉ ጎናዊ ስምረት እንዲኖረን ይረዳል፡፡
 
ወገኖቼ ጤናችን እስኪዛባ ደስታችን እስኪጠፋ ቢዚ ከሆንን እየቆየ ወደ ክስመት (burn out) ልንሄድ እንችላለን፡፡ በእምነት እጦት ሰበብ ሩጫ ያበዙትን ሕዝበ እስራኤል እግዚአብሔር እንደገሰጻቸውና እንደመከራቸው እኛንም ያስጠነቅቀናል፡፡
 
“የእስራኤል ቅዱስ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና በመመለስና በማረፍ ትድናላችሁ፣ በፀጥታና በመታመን ኃይል ይሆንላችኋል፡፡”
(ኢሳ 30፡15)

ቁምላቸው ፈንታሁን ወደ አማርኛ ተርጉሞት በቃለ እግዚአብሔር አንባቢዎች ማኅበር በኩል ከታተመው መጽሐፍ ይህን አስተዋይ ጸሎት ልብ እንድንለው አብረንም እንድንጸልየው እጋብዛለሁ፡፡
 
ሰከን አርገኝ ጌታ!
ለአእምሮዬ ፀጥታ ለግሰህ፣ የልቤን ድውድውታ ቀንሰው፡፡
በጊዜ ውስጥ የዘላለምን አፅናፍ ራእይ ስጠኝና ጥድፊያዬ ልጓም ይበጅለት፡፡
በቀናት ዑደት ቱማታና ግርግር መካከል፣
የዘላለም ዓለም ኮረብቶች ግርማዊ አርምሞ በኔ ላይ ያርብብ፡፡
የሠራ አካላቴ ውጥረት በትውስታዬ በሚኖሩ
ዘማሪ ጅረቶች የሚያሳርፍ ሙዚቃ ይርገብ፡፡
የእንቅልፍን አስማታዊ አዳሽ ኃይል እንድገነዘብ እርዳኝ፡፡
ጥበብን አካፍለኝና የደቂቃ እርፍቶች በየመካከሉ እየወሰድኩ፡-
አበቦችን ልመልከት፣ ከወዳጅ ጋር ልጫወት፣
በጫካው መካከል ልመላለስ፣ ሸረሪት ድሯን ስትሸምን ልያት
ህፃኗን በፈገግታ ልቀበላት፣ እንባዎቿንም ላብስላት፡፡
ሩጫ ሁልጊዜ ለፈጣኖች እንዳይደለ፣
የኑሮ ሁለንተና ፍጥነት እየጨመሩ መኖጥ እንዳይደለ በየዕለቱ አስታውሰኝ፡፡
ቀና ብዬ ደመኖቹንና ሰማዩን
እንዲሁም ያዘመመን ዛፍ ልመልከታቸው፣
ዛፉ ዛሬ ይህን አክሎ ያደረገው፣ የበረታው በሕይወት ሰጪ ፀሐይህ ሙቀት
በዝግታ በማደጉ መሆኑን ልገንዘብ፡፡
ሰከን አርገኝ ጌታ ከአንተ ጋር ኅብረት በማድረግ በጥልቅ እኔነቴ የሚያሹኝን ሰላምና እረፍት ልጎናጸፍ፡፡


ምንጭ :- semayawithought.com




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

16 Feb, 14:03


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 5 (ሕይወትን ከእግዚአብሔር ዕይታ አንጻር መልእክት)


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

16 Feb, 11:39


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ለባሪያህ ከሠራኸው ከምሕረትህና ከእውነትህም ሁሉ ትንሽ ስንኳ የማይገባኝ ነኝ፤ በትሬን ብቻ ይዤ ይህን ዮርዳኖስን ተሻግሬ ነበርና፥ አሁን ግን የሁለት ክፍል ሠራዊት ሆንሁ።”
ዘፍጥረት 32፥10



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

16 Feb, 05:48


#እራሳችንን_እንመርምር



"ሰው" መሆን ማለት ምን ማለት ነው? ሁለት እግር ያለው የሚንቀሳቀስ፣ የሚያስብ፣ የሚበላ፣ የሚጠጣ ወይስ ሌላ? ሰው አለመሆንስ ይቻላል?


“በርታ ሰውም ሁን፤ የምታደርገውንና የምትሄድበትን ሁሉ ታከናውን ዘንድ፥ በሙሴ ሕግ እንደ ተጻፈ ሥርዓቱንና ትእዛዛቱን ፍርዱንና ምስክሩንም ትጠብቅ ዘንድ፥ በመንገዱም ትሄድ ዘንድ፥ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ጠብቅ።”
1ኛ ነገሥት 2፥3



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

15 Feb, 18:35


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 4 (ለዘላለም ሕይወት ተፈጥረሃል)


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

15 Feb, 10:32


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ጥቂት ጊዜ ተውሁሽ፥ በታላቅም ምሕረት እሰበስብሻለሁ።”
ኢሳይያስ 54፥7



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

14 Feb, 19:21


ቢዚ - ቢዚ፤ ለሁሉ ጊዜ አለው ወይስ አለን?



በጋሽ ንጉሤ ቡልቻ


ጓዙን ጠቅልሎ ወደ ውጪ አገር የሚሄድ ጓደኛውን ለመሸኘት ከተሰበሰቡት መካከል የሽኝት ፕሮግራሙን ማጠቃለያ ጸሎት የሚጸልየው ሰው እንዲህ ብሎ ጸልዮአል አሉ፡፡
 
“ጌታ ሆይ ይህ ወንድማችን በሚሄድበት አገር ቢዚ ከሚባል ጋኔን እንድትጠብቀው እንለምንሃለሁ፡፡”
 
“ቢዚ” የሚባል ጋኔን መኖር አለመኖሩን መመራመራችንን ትተን ባተሌነት “ቢዚነት” የውጪ አገር አበሳ መሆኑ ቀርቶ ውስጥ አገርም የሚያስጨንቀን ጉዳይ እንደ ሆነ እንቀበል፡፡
 
በቀጠሮ ብዛት፣ በእንቅስቃሴ ብዛት፣ በጉዳይ ብዛት፣ በሥራ ብዛት፣ በሥራ ውጣ ውረድ፣ በማኅበራዊ ግንኙነት ብዛት፣ በሽቅብ ቁልቁል ብዛት፣ የአካላችን አውታር እስኪነዝሩ ተወጣጥረናል፤ ነፍሳችን ብን ትን እስክትል እንማስናለን፡፡ ትንፋሽ አጥሮን ስናለከልክ የሚያየን የሌላ ዓለም ፍጡር ቢኖር “ምን ሥራሥር በጥብጠው ቢጠጡ ነው እንዲህ የሚያዛብታቸው፣ የሚያሽከረክራቸው” ብሎ በጠየቀ፡፡ ለመሆኑ ምን እንዲህ ያባትለናል?
 
የየዕለቱ ውጣ ውረድ ነዋ! የጉረሮ መድፈን ጥሪ፣ የማኅበረ ሰብ ቦታችንን የማስጠበቅ ጥሪ፣ የነገ ምን ይሆናል ጭንቀት፣ ሌሎችም ይህን የመሳሰሉ ሁሉ፡፡ የሰው ልጅ የሚሠራውንና የሚውልበትን ሁነኛ ጉዳይ አግኝቶ በሥራ መጠመዱ በረከት እንጂ ርግማን አይደለም፡፡ ጊዜ እንደ ጅረት በሚንፎለፎልበት ልማዱ ቢነጉድ የሥራ ቦይ እየቀደዱ ጥቅም ላይ የሚያውሉት የታደሉ ናቸው “ዘመኑን ዋጁ” በሚለው ምክር አብነት፡፡ እንዲህ የሚያደርጉ በሥራው ከሚገኘው ጥቃሞት በላይ ስብእናቸው ይለማል፣ ርካታና ደስታም ያገኛሉ፡፡
 
አሁን ያነሣነው “ጋኔኑ ቢዚነት” ግን ከሚያለማው የሚያጠፋው የበለጠ፣ ከሚያረካው የሚያቅበዘብዘው የበዛ፣ ደስታችንን ቦጥቡጦ የሚበላ መልቲ ነው፡፡
 
ሮጠን ሮጠን ልባችን ሊፈነዳ ሲል ስንቆም የትም እንዳልደረስን ስንረዳ፣ ከበሬታ ፍለጋ ብዙ የአንቱታ ካባ ደርበን ድንገት ካባው የወደቀ ቀን የነፍሳችን ክሳት ሲጋለጥ የዚህ ዐይነት ቢዚነት ፍሬ ይታወቅ ይሆናል፡፡
 
መድኃኒታችን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ “በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ ወደዚህ ምድር ስለመጣ ልክ እንደ እኛ በቀን ውስጥ 24 ሰዓት ብቻ ነበረው፡፡ ያደረገውን ሁሉ ያደረገው በዚሁ በባለ 24 ሰዓት ቀን ነበር፡፡ የምድር እድሜው ጥቂት ነበረ፤ የይፋ አገልግሎቱ ደግሞ ከሦስት ዓመታት እጅግም ያልዘለለ አጭር ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ሆኖ ወደ አባቱ መሄጃው ጊዜ ሲደርስ የጸለየው ጸሎት የተዋከበ፣ የተጨነቀ አልነበረም፤ “ምነው አንድ ዐሥር ዓመት ብትጨምርልኝና የጀመርሁትን በጨረስሁ” የሚል የጊዜ ልመና አልነበረበትም፡፡ “የሰጠኸኝን ሥራ በምድር ላይ ፈጽሜ አከበርሁህ” የሚል ደልዳላ ዘገባ ነበር፡፡
 
እንዴት እንደዚህ ስክን ያለ ሕይወትና አገልግሎት አገኘ? እጅግ ብዙ የእርሱን ርዳታ የሚሹ ፍጡራን ባሉበት ዓለም ውስጥ በቀኝና በግራ ሊያዋክቡት የሚችሉ አስባታሊ ተግባራት በነበሩበት ሁኔታ እንደምን ርጋታ አገኘ? መጽሐፉ ላይ እንደ ተጠቆምን ከሆነ መልሱ ውስብስብ አይደለም፡፡ ጌታችን ዋናውን ጉዳይ ከአስቸኳዩ የለየ፣ የሕይወት ጥሪውን አሳምሮ ያወቀ፣ ቆፍጣና የዓላማ ሰው ስለነበረ ነው፡፡ “የሰጠኸኝን ሥራ” አለ እንጂ በሜዳ ያለውን ተግባር ሁሉ አላለም፤ ወይም ዘመድ ወዳጅ የጠየቀኝን ኀላፊነት ሁሉ ወይም የተገኘውን ሥራ ሁሉ ፈጸምሁ አላለም፡፡ የአባቱ ፈቃድ የሕይወት ጥሪው ነበረና ያንኑ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ፈጸመው፡፡ በጸሎቱ ዘገባ በዝርዝር እንዳሰፈረው እያንዳንዱን ቅንጣት ተግባር ከነውጤቱ እንደተከናወነ ርግጠኛ ነበር፡፡ በምድር አገልግሎቱ የነካቸው ሰዎች ሁሉ ሕይወታቸው በጥልቅ ተነክቷል፤ የይድረስ ይድረስ በሽታ ሳይጠናወተው የሚሠራውን ሁሉ ወደ ተገቢው ፍጻሜ አደረሰ፡፡ በዓላማ ጽናት፣ በርግጠኛ ርምጃ፣ በታላቅ ማስተዋል ተራመደ፡፡ ስለዚህ ሞቱ የጸጸት አልነበረም የድልና የስኬት እንጂ፡፡ ሕይወቱ አልተጨናገፈም፤ ውጥኑ ባጭር አልቀረም፤ የሰማይ አባቱን ያስከበረ ወርቃማ ፍጻሜ አገኘ፡፡ የሕይወትን ዋና ጥሪ ለመፈጸም ጊዜን በጥበቡ የመጠቀም ጉልህ አርኣያ ሆነ፡፡ ስሙ ይክበር፡፡ ቻርልስ ሁሜል የተባለ አስተዋይ ጸሐፊ “The Tyranny of the Urgent” ብሎ የጻፈውና ቁምላቸው ፈንታሁን የተረጎመው አንድ ጽሑፍ እንዲህ ይላል፦
 
/ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንመለከት፣ያልተጠናቀቁ ሥራዎች፣ ምላሽ ያልተሰጣቸው ደብዳቤዎች፣ ያልተጎበኙ ወዳጆች ያልተጻፉ መጣጥፎችና ያልተነበቡ መጻሕፍት ይታዩናል፡፡ በሥራ እየባተልን ቢሆንም የምናገኝበት ደስታ እያደር የመነመነ ነው፡፡ ሆኖም ችግር የሚፈጥርብን ተግቶ መሥራት ሳይሆን ጥርጣሬና መወላወል ናቸው፡፡ ትልቁ አደጋ ለአስቸኳዩ ጉዳይ መላ ለመፈለግ ስንጣደፍ ዋነኛውን ጉዳይ መዘንጋቱ ነው፡፡ ችግሩ ደግሞ ዋነናው ጉዳይ ዛሬ ወይም በዚህ ሳምንት ይሠራ የሚያሰኝ አጣዳፊነት የሌለው መሆኑ ነው፡፡ ፈጣን ርምጃ የሚጠይቁን አጣዳፊ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በጊዜው በጣም አስፈላጊና ወደ ጎን የማይባሉ ስለሚመስሉን ጉልበታችንን ይመጡታል፡፡ ክርስቲያን ፋታ ወስዶ መንፈሳዊ ሁኔታውን በመፈተሸ፣ የሥራ ኀላፊነት ለመቀበል እንዳይችል ሆኖ በሥራ ከተጠመደ፣ ለአስቸኳዩ ጉዳይ ምላሽ ለመስጠት ሎሌ ያድራል፡፡ በራሱና በሌሎች ዐይን ዋጋ የሚሰጠው የሚመስል ነገር፣ ሌት ተቀን ሠርቶ ማከናወን ቢችልም፣ እግዚአብሔር ያቀደለትን ሥራ ግን ሳያጠናቅቅ ይቀራል/
 
እንግዲያው በባርነት ቀፍድዶ የያዘን “አስቸኳይ” የሚባል አምባ ገነን የፍዳችን አንዱ ዋና ምክንያት መሆኑ ነው፡፡ አስቸኳዩን ከዋናው ጉዳይ እንዴት እንለያለን? የሚለው ጥያቄ ብርቱ ጥያቄ ነው፡፡ ለዚህ መልስ ካገኘን የፍልሚያው እምብርት ታወቀ ማለት ነው፡፡

 
ይቀጥላል ...


ምንጭ :- semayawithought.com



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

14 Feb, 17:46


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 3 (ሕይወትህ የሚመራው በምንድነው?)


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

14 Feb, 10:27


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።”
ገላትያ 5፥22



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

13 Feb, 21:27


👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጄሊካል ቲዎሎጂካል ኮሌጅ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

13 Feb, 21:26


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

13 Feb, 13:25


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 2 (አጋጣሚ አይደለህም)


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

13 Feb, 11:13


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“መድኃኒታችንም ከዓመፅ ሁሉ እንዲቤዠን፥ መልካሙንም ለማድረግ የሚቀናውን ገንዘቡም የሚሆነውን ሕዝብ ለራሱ እንዲያነጻ፥ ስለ እኛ ነፍሱን ሰጥቶአል።”
ቲቶ 2፥14



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

12 Feb, 17:48


#የሮሜ_መልእክት_ጥናት


ሮሜ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ሙሴ ከሕግ የሆነውን ጽድቅ የሚያደርገው ሰው በእርሱ በሕይወት እንዲኖር ጽፎአልና።
⁶ ከእምነት የሆነ ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል፦ በልብህ፦ ማን ወደ ሰማይ ይወጣል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
⁷ ወይም፦ በልብህ፦ ወደ ጥልቁ ማን ይወርዳል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
⁸ ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።
⁹ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
¹⁰ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
¹¹ መጽሐፍ፦ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
¹² በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
¹³ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።


ሮሜ 10 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ሙሴ በሕግ በኩል የሆነውን ጽድቅ ሲገልጽ፣ “እነዚህን የሚፈጽም ሰው በእነርሱ ይኖራል” ይላል።
⁶ ከእምነት የሆነው ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል፤ “ ‘በልብህ ማን ወደ ሰማይ ይወጣል?’ አትበል”፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
⁷ “ወይም ‘ወደ ጥልቁስ ማን ይወርዳል?’ አትበል”፤ ይህም ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
⁸ ነገር ግን ምን ይላል? “ቃሉ በአጠገብህ ነው፤ በአፍህና በልብህም ውስጥ ነው፤” የምንሰብከውም የእምነት ቃል ይህ ነው፤
⁹ “ኢየሱስ ጌታ ነው” ብለህ በአፍህ ብትመሰክር፣ እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን፣ ትድናለህ።
¹⁰ የምትጸድቀው በልብህ አምነህ ነው፤ የምትድነውም በአፍህ መስክረህ ነውና።
¹¹ መጽሐፍ እንደሚለው፣ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም።”
¹² በአይሁድና በአሕዛብ መካከል ልዩነት የለም፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፤ የሚለምኑትንም አብዝቶ ይባርካል፤
¹³ “የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።”


ሮሜ 10 (ሕያው ቃል)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ሕግን በመጠበቅ ስለ መጽደቅ ሙሴ፥ «አንድ ሰው ሕግ የሚያዘውን ሁሉ መጠበቅ ከቻለ ፥ ሕግ ራሱ ሕይወት ይሰጠዋል» ሲል ጽፎአል።
⁶ በእምነት የሚገኘው ጽድቅ ግን፥ «ክርስቶስን ወደ ምድር ለማውረድ ወደ ሰማይ መውጣት አያስፈልግህም።
⁷ ወይም ወደ ሲኦል ወርደህ ክርስቶስን ከሙታን መካከል ማስነሣት የለብህም» ይላል።
⁸ ነገር ግን መጽደቅ ስለሚቻልበት መንገድ እንዲህ ይላል። «የእግዚአብሔር ቃል በአጠገብህ ይገኛል ፤ በአፍህና በልብህም ውስጥ ነው።» ይህም የእግዚአብሔር ቃል እኛ የምናስተምራችሁ የእምነት ቃል ነው።
⁹ ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ በአፋችሁ ብትመሰክሩ፥ እግዚአብሔርም ከሞት እንዳስነሣው በልባችሁ ብታምኑ ትድናላችሁ።
¹⁰ ምክንያቱም ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃል። ስለ እምነቱም በመመስከሩ ይድናል።
¹¹ ይህ እውነት መሆኑን ለማረጋገጥ እንዲህ የሚል ቃል በመጽሐፍ ተጽፎ ይገኛል ፤ «በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም።»
¹² ይህ ቃል የተጻፈው በአይሁድና በአሕዛብ መካከል ምንም ልዩነት ሳይደረግ ለሁሉ ነው። የሁሉም ጌታ የሆነው ኢየሱስ፥ ለሚለምኑት ሁሉ በረከቱን የሚሰጥ ባለጸጋ አምላክ ነው።
¹³ በቅዱሳት መጻሕፍት ፥ «የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል» ተብሏል።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

12 Feb, 13:41


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🗒ክፍል፦ 1


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

12 Feb, 10:30


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።”
ይሁዳ 1፥21




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

11 Feb, 21:50


ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሕይወት ቅድሚያ ሊያገኙና ሊከተሉ ስለሚያስፈልጉ ነገሮች ምን አለ?


ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር ስንኖር "life priority order" ወይንም በሕይወት ቅድሚያ ስለሚያስፈልጉ እና ስለሚከተሉ ነገሮች በማቴዎስ 6፥25-34 አብራርቶልናል።

1. እግዚአብሔር ወይንም የእግዚአብሔር መንግሥት (ቁ. 33)
2. ነፍስ (ቁ. 25)
3. ምግብ (ቁ. 25)
4. ሰውነት (ቁ. 25)
5. ልብስ (ቁ. 25)

ከላይ በቅደም ተከተል የተጠቀሱት ቦታቸው የሚዛነፍ ከሆነ ሕይወት ሚዛኗን ስታ አማኝን ለጭንቀት ይዳርጉታል። ይባስ ካለ ደግሞ ዓለሙን አትርፎ ነፍሱን ወደ ማጉደል አዘቅት ይከተዋል።

“ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት፥ ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ አይበልጥምን?”
ማቴዎስ 6፥25


“ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።”
ማቴዎስ 6፥33



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

11 Feb, 15:35


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ ዓላማ መር ሕይወት
✍️ጸሐፊ፦ ሪክ ዋረን
🗣ትርጉም፦ ኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ
🚪 መግቢያ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

11 Feb, 15:32


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

11 Feb, 10:03


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በነጻነት ሕግ ፍርድን ይቀበሉ ዘንድ እንዳላቸው ሰዎች እንዲህ ተናገሩ፥ እንዲህም አድርጉ።”
ያዕቆብ 2፥12



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

10 Feb, 18:51


#እንወያይ

ጥምቀት በእናንተ አባል በሆናችሁበት አጥቢያ ወይንም ቤተ እምነት እንዴት ይታያል? እናንተስ እንዴት ታያላችሁ? የተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ያለው የጥምቀት አስተምህሮ ልዩነት ወደ አንድ ሊመጣ ይችላል ብላችሁ ታምናላችሁ? ወደ አንድ ለመምጣት የማይችል ከሆነ ለምን?


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

10 Feb, 17:48


#ጥምቀት


                    ክፍል-፱
           (የመጨረሻ ክፍል)


በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ጥምቀት ያድናል” ሲባል ምን ማለት ነው?

“ጥምቀት ያድናል” የሚለው ሐረግ በዋነኝነት የተወሰደው ከ1ኛ ጴጥሮስ 3፡21 ሲሆን እሱም እንዲህ ይላል።

“ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፥ የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፥ ለእግዚአብሔር የበጎ ሕሊና ልመና ነው እንጂ፥ ይህም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው፤”
      1ኛ ጴጥሮስ 3፥21

ይህ ቁጥር የሚያመለክተው ጥምቀት አካላዊ ብቻ ሳይሆን ከደህንነት ጋር በተያያዘ መንፈሳዊ ጠቀሜታ እንዳለው ነው። ሆኖም፣ የተለያዩ ክርስቲያናዊ ወጎች ይህንን ጽንሰ ሐሳብ በተለያየ መንገድ ይተረጉማሉ።

የ"ጥምቀት ያድናል" የቤተክርስቲያን የተለያዩ ትርጓሜዎች

1. የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን

የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጥምቀት ለመዳን አስፈላጊ እንደሆነ ታስተምራለች ምክንያቱም የመጀመሪያውን ኃጢአት አስወግዶ ሰውን ወደ ቤተክርስቲያን ስለሚያመጣ። ይህ እምነት በዮሐንስ 3፥5 ላይ የተመሰረተ ሲሆን ኢየሱስ “... እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም።”

2. የምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን

ከካቶሊክ እምነት ጋር በሚመሳሰል መልኩ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጥምቀትን ለድነት አስፈላጊ እንደሆነ አድርገው ይመለከታሉ። ይህም ሂደት ሰውን ወደ ክርስቶስ አካል ይጨምራል።

3. የሉተራን ቤተ ክርስቲያን

ሉተራውያን በጥምቀት እንደገና መወለድን ያምናሉ። ማለትም ጥምቀት የእግዚአብሔርን ጸጋ እና ይቅርታ ያስተላልፋል። የሐዋርያት ሥራ 2፥38ን በመጥቀስ ጴጥሮስ “...ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።” ሲል ተናግሯል። ነገር ግን፣ እምነት ለመዳን አስፈላጊ መሆኑንም አፅንዖት ይሰጣሉ።

4. የተሐድሶ እና የፕሪስባይቴሪያን አብያተ ክርስቲያናት

የተሐድሶ ወጎች ጥምቀትን እንደ እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ምልክት እና ማኅተም ይመለከቱታል፣ ልክ እንደ ብሉይ ኪዳን መገረዝ። ጥምቀት እራሱ እንደሚያድን አያምኑም ይልቁንም አስቀድሞ በእምነት የተቀበለውን የድነት ውስጣዊ ጸጋ ያሳያል።

5. ባፕቲስት እና ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት

ባፕቲስት እና ብዙ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ጥምቀት እራሱ ያድናል የሚለውን ሃሳብ አይቀበሉም። መዳን በእምነት ብቻ እንደሆነ ያምናሉ (ኤፌሶን 2፥8-9) እና ጥምቀት የውስጣዊ እምነት ውጫዊ መግለጫ እንደሆነ ያምናሉ። የመታዘዝ ተግባር ነው ነገር ግን ለመዳን አስፈላጊ አይደለም (ሮሜ 10፥9)።



ምንጭ፦ Catechism of the Catholic Church. (1994). Libreria Editrice Vaticana.
Calvin, J. (1559). Institutes of the Christian religion.
Holy Bible, New International Version. (2011). Zondervan.
Luther, M. (1529). Luther’s Small Catechism.
Ware, T. (1993). The Orthodox Church. Penguin Books.



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

10 Feb, 10:55


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“የእስራኤል ልጆች ማኅበር ሁሉ በሴሎ ተሰበሰቡ፥ በዚያም የመገናኛውን ድንኳን ተከሉ፤ ምድሩም ጸጥ ብሎ ተገዛላቸው።”
ኢያሱ 18፥1



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

09 Feb, 21:53


#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?


2ኛ ነገሥት 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ ኤልሳዕም ወደ ደማስቆ መጣ፤ የሶርያም ንጉሥ ወልደ አዴር ታምሞ ነበር፤ ወሬኞችም፦ የእግዚአብሔር ሰው ወደዚህ መጥቶአል ብለው ነገሩት።
⁸ ንጉሡም አዛሄልን፦ ገጸ በረከት በእጅህ ወስደህ የእግዚአብሔርን ሰው ልትገናኝ ሂድ፤ በእርሱም አፍ፦ ከዚህ በሽታ እድናለሁን? ብለህ እግዚአብሔርን ጠይቅ አለው።
⁹ አዛሄልም ሊገናኘው ሄደ፥ ከእርሱም ጋር ከደማስቆ መልካሙን ነገር ሁሉ የአርባ ግመል ጭነት ገጸ በረከት ወሰደ፤ መጥቶም በፊቱ ቆመና፦ ልጅህ የሶርያ ንጉሥ ወልደ አዴር፦ ከዚህ በሽታ እድናለሁን? ሲል ወደ አንተ ልኮኛል አለ።
¹⁰ ኤልሳዕም፦ ሂድ፥ መዳንስ ትድናለህ በለው፤ ነገር ግን እንዲሞት እግዚአብሔር አሳይቶኛል አለው።
¹¹ እስኪያፍርም ድረስ ትኵር ብሎ ተመለከተው፤ የእግዚአብሔርም ሰው አነባ።
¹² አዛሄልም፦ ጌታዬ ለምን ያነባል? አለ። እርሱም፦ በእስራኤል ልጆች ላይ የምታደርገውን ክፋት ስለማውቅ ነው፤ ምሽጎቻቸውን በእሳት ታቃጥላለህ፥ ጕልማሶቻቸውንም በሰይፍ ትገድላለህ፥ ሕፃናቶቻቸውንም ትፈጠፍጣለህ፥ እርጉዞቻቸውንም ትቀድዳለህ አለው።
¹³ አዛሄልም፦ ይህን ታላቅ ነገር አደርግ ዘንድ እኔ ውሻ ባሪያህ ምንድር ነኝ? አለ። ኤልሳዕም፦ አንተ በሶርያ ላይ ንጉሥ እንድትሆን እግዚአብሔር አሳይቶኛል አለው።
¹⁴ ከኤልሳዕም ርቆ ወደ ጌታው መጣ፤ እርሱም፦ ኤልሳዕ ምን አለህ? አለው።
¹⁵ እርሱም፦ እንድትፈወስ ነገረኝ አለው። በነጋውም ለሐፍ ወስዶ በውኃ ነከረው በፊቱም ላይ ሸፈነው፥ ሞተም። አዛሄልም በፋንታው ነገሠ።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

09 Feb, 10:26


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እኔም በልቤ፦ በዚያ ለነገር ሁሉና ለሥራ ሁሉ ጊዜ አለውና በጻድቅና በኃጢአተኛ ላይ እግዚአብሔር ይፈርዳል አልሁ።”
መክብብ 3፥17



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

09 Feb, 04:31


#እራሳችንን_እንመርምር


እኔምለው ግን እግዚአብሔር አንድ በአንድ ነገሮችን መቼም ቢሆን የትም የተሰሩትን፣ በማንም ይሁን በየትኛው ሁኔታ፣ መልካም ቢሆን ክፉ ለፍርድ እንደሚያመጣ በእርግጥ አስበን እናውቃለን? የእግዚአብሔር ዝምታ ፍርድ አልባ ነው ብለን እንድናስበው አድርጎን እንዳይሆን እፈራለሁ። የክፉ ምክር ሰምተን እና የዓለምን መለኪያ ተውሰን ፍርድ እያከማቸን ይሆን ወይስ እግዚአብሔርን በመፍራት ላይ እንገኛለን?

"የነገሩን ሁሉ ፍጻሜ እንስማ፤ ይህ የሰው ሁለንተናው ነውና፤ እግዚአብሔርን ፍራ፥ ትእዛዙንም ጠብቅ። እግዚአብሔር ሥራን ሁሉ የተሰወረውንም ነገር ሁሉ፥ መልካምም ቢሆን ክፉም ቢሆን፥ ወደ ፍርድ ያመጣዋልና።"
መክብብ 12፥13-14



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

08 Feb, 12:19


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“የደመና ዓምድ በቀን፥ የእሳት ዓምድ በሌሊት ከሕዝቡ ፊት ከቶ ፈቀቅ አላለም።”
ዘጸአት 13፥22



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

07 Feb, 22:31


ቅዱሳት መጽሐፍት እንዴት ተመረጡ?


1. ከታወቁ ሐዋሪያት ወይም ነብያት የተጻፈ ከሆነ
2. ከታወቁ ሐዋሪያት ወይም ነብያት ጋር ግንኙነት ባለው  የተጻፈ ከሆነ(ምሣሌ:- ሀኪሙ ሉቃስ)
3. እውነተኝነት(ዘዳ 18:20-22)
4. ከሌላው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ጋር የማይጣረስ መሆን ይገባዋል::
5. በ ኢየሱስ ክርስቶስ, በነብያት ወይንም  በሐዋሪያት የተረጋገጡ ሲሆኑ(ሉቃ 24:44, 2ኛ ጴጥ 3:16)
6. በቤተክርስቲያን አባቶች ጥቅም ላይ የዋለና የተረጋገጠ::
ለዚህ ጥሩ ምሣሌ በ397 ዓ.ም በሰሜን አፍሪካ በካርታጎ (በካርቴጅ ቱንዚያ) በተደረገው ጉባኤ ነው::


መጽሐፍ ቅዱስ እና ቤተ ክርስቲያን

👉በመጀመሪያ ቤ.ክ. አይሁድ ያወቁአቸውን የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ተቀበለች::

👉ቅዱስ አትናቴዎስ በ367 ዓ.ም. በጻፈው በፋሲካ ዕለት ቃለ በረከት የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት 27 መሆናቸውን ተናግረዋል::

👉በ397 ዓ.ም በሰሜን አፍሪካ በካርታጎ (በካርቴጅ ቱንዚያ) በተደረገው ሲኖዶስ 27 መጻሕፍት አጸደቀ::

👉በ1228 ዓ.ም መጽሐፍ ቅዱስ ምዕራፍ ተከፈለ::

👉በ1551 ዓ.ም መጽሐፍ ቅዱስ በቍጥር ተከፈለ::
            


ምንጭ:-biblicaltraining.com ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

07 Feb, 18:56


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 31


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

07 Feb, 12:56


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ዳዊትም በእስራኤል ሁሉ ላይ ነገሠ፤ ለሕዝቡም ሁሉ ፍርድንና ጽድቅም አደረገላቸው።”
1 ዜና 18፥14




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

06 Feb, 17:11


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 30


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

06 Feb, 11:18


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አሁን እኔ ጐሽ ለመባል የምሻው በሰዎች ዘንድ ነው ወይስ በእግዚአብሔር ዘንድ? ወይስ ሰዎችን ደስ ለማሰኘት እየተጣጣርሁ ነው? ሰዎችን ደስ ለማሰኘት የምጥር ብሆን ኖሮ፣ የክርስቶስ አገልጋይ ባልሆንሁ ነበር።”
ገላትያ 1፥10 (አዲሱ መ.ት)



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

06 Feb, 06:01


#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?


ፊልጵስዩስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁹ ነገር ግን ኑሮአችሁን ሳውቅ እኔ ደግሞ ደስ እንዲለኝ ፈጥኜ ጢሞቴዎስን ልልክላችሁ በጌታ በኢየሱስ ተስፋ አደርጋለሁ።
²⁰ እንደ እርሱ ያለ፥ ስለ ኑሮአችሁ በቅንነት የሚጨነቅ፥ ማንም የለኝምና፤
²¹ ሁሉ የራሳቸውን ይፈልጋሉና፥ የክርስቶስ ኢየሱስን አይደለም።
²² ነገር ግን ልጅ ለአባቱ እንደሚያገለግል ከእኔ ጋር ሆኖ ለወንጌል እንደ አገለገለ መፈተኑን ታውቃላችሁ።


ፊልጵስዩስ 2 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁹ ስለ እናንተ ሰምቼ ደስ እንዲለኝ፣ ጢሞቴዎስን ቶሎ ወደ እናንተ ልልክላችሁ በጌታ ኢየሱስ ተስፋ አደርጋለሁ።
²⁰ ስለ እናንተ ደኅንነት ከልቡ የሚገደው እንደ እርሱ ያለ ማንም የለኝም፤
²¹ ሁሉም የኢየሱስ ክርስቶስን ሳይሆን የራሳቸውን ፍላጎት ለማሟላት ይሯሯ ጣሉና።
²² ነገር ግን እንደምታውቁት ጢሞቴዎስ ማንነቱን አስመስክሮአል፤ ልጅ ከአባቱ ጋር እንደሚያገለግል፣ ከእኔ ጋር በወንጌል ሥራ አገልግሎአልና።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

05 Feb, 22:08


👉ርዕስ፦ መስቀል-አልባ ክርስትና
ጸሐፊ፦ ዶክተር መለሰ ወጉ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

05 Feb, 22:02


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

05 Feb, 18:31


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 29


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

05 Feb, 11:07


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ከእናንተ የሆነ የክርስቶስ ባሪያ ኤጳፍራ ሰላምታ ያቀርብላችኋል፤ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሁሉ ተረድታችሁና ፍጹማን ሆናችሁ እንድትቆሙ፥ ሁልጊዜ ስለ እናንተ በጸሎቱ ይጋደላል።”
ቆላስይስ 4፥12




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

04 Feb, 20:36


#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት


#ቴቁሔ


ቴቁሔ፤ ከቤተ ልሔም በስተደቡብ 8 ኪ.ሜ.
ርቆ የሚገኝ ከተማ። ቴቁሔ የሚገኘው የይሁዳ ምድረ በዳ ክፍል በሆነው ወጣ ገባና ኮረብታማ አካባቢ ነው። ከተማዋ በመልክአ ምድራዊ አቀማመጥ ምክንያት ብዙ ጊዜ ከእረኝነት እና ከግብርና ጋር ትገናኛለች።

የቴቁሔ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማጣቀሻዎች

ቴቁሔ እንደ አሞጽ ቤት፡- ከቴቁሔ ጋር የተያያዘው በጣም ታዋቂው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሰው ነቢዩ አሞጽ ነው። አሞጽ 1፥1 በ8ኛው መቶ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት ለሰሜናዊው የእስራኤል መንግሥት ትንቢት እንዲናገር ከመጠራቱ በፊት ነቢዩ ከቴቁሔ እረኞች አንዱ እንደሆነ ይናገራል።

ቴቁሔ በጦርነት  አውድ፡- ቴቁሔ በ2ኛ ዜና 11፥5-6 ላይ የይሁዳ ንጉሥ ሮብዓም ሊደርስበት ከሚችለው ጥቃት ለመከላከል ከተመሸጉ ከተሞች አንዷ ነች። ይህም በክልሉ ያለውን ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ ያሳያል።

ቴቁሔ እና ጥበበኛዋ ሴት፡- በ2ኛ ሳሙኤል 14 ላይ፣ የቴቁሔ ጠቢብ ሴት፣ የዳዊት የጦር አዛዥ በሆነው በኢዮአብ፣ ንጉሥ ዳዊት ከልጁ ከአቤሴሎም ጋር እንዲታረቅ ለማሳመን ተልካለች። ምሳሌዋ እና ጥበቧ በትረካው ውስጥ ጉልህ ሚና ይጫወታሉ።

ቴቁሔ በትውልድ ሐረግ፡- በነህምያ 3፥5 እና 3፥27፣ ቴቁሔ የተጠቀሰው ከባቢሎን ግዞት በኋላ የኢየሩሳሌምን ግንቦች እንደገና በመገንባቱ ሁኔታ ውስጥ ነው። የቴቁሔ ሰዎች ለዚህ ጥረት ባደረጉት አስተዋጽዖ ይታወቃሉ፣ ምንም እንኳን አንዳንድ መኳንንት ለመሳተፍ ፈቃደኛ ባይሆኑም (ነህምያ 3፥5)።



ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 130፣
Aharoni, Y. (1979). The Land of the Bible: A Historical Geography. Philadelphia, PA: Westminster Press.
Mazar, B. (1975). The Mountain of the Lord: Excavating in Jerusalem. Garden City, NY: Doubleday.




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

04 Feb, 16:18


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 28


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

04 Feb, 11:17


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔር ክፍሌ ነው፤ ሕግህን እጠብቃለሁ አልሁ።”
መዝሙር 119፥57



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

03 Feb, 18:45


#ጥምቀት


                    ክፍል-፰



ፕሮቴስታንት

ፕሮቴስታንት ስለ ጥምቀት ያለው አመለካከት በሰፊው ይለያያል፡-

ሉተራኒዝም፦ ሉተራውያን ጥምቀት የጸጋ መቀበያ መንገድ እንደሆነ ያምናሉ እናም ለድነት አስፈላጊ ነው፣ ነገር ግን እምነትን የእግዚአብሔርን ጸጋ የመቀበያ ዋና መሳሪያ እንደሆነም ያምናሉ።

ካልቪኒዝም፦ ጥምቀት እንደ እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ምልክት እና ማኅተም ነው የሚታየው ነገር ግን ለመዳን በፍጹም አስፈላጊ አይደለም። መዳን በእምነት ብቻ በጸጋ ነው።

ባፕቲስት፦ ባፕቲስቶች በአጠቃላይ ጥምቀትን እንደ ሥርዓተ ቁርባን ይመለከቱታል። የእምነት እና የመታዘዝ ይፋዊ መግለጫ ነው ነገር ግን ለመዳን መስፈርት አይደለም ይህም በእምነት ብቻ ነው።

ጴንጤቆስጣዊ፡- ብዙ ጴንጤቆስጤዎች የጥምቀትን አስፈላጊነት ያጎላሉ፣ ብዙ ጊዜ ከመንፈስ ቅዱስ መቀበል ጋር ያገናኙታል። አንዳንድ ቡድኖች፣ ልክ እንደ አንድነት ጴንጤቆስጤዎች፣ በኢየሱስ ስም መጠመቅ ለመዳን አስፈላጊ እንደሆነ ያስተምራሉ።


ይቀጥላል...


ምንጭ፦ Luther, M. (1529). The Small Catechism.
Calvin, J. (1536). Institutes of the Christian Religion.
Erickson, M. J. (2013). Christian Theology. Baker Academic.
Horton, S. M. (2005). Systematic Theology: A Pentecostal Perspective. Logion Press.




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

03 Feb, 17:40


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 27


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

03 Feb, 11:44


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።”
ኤፌሶን 4፥24



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

22 Jan, 19:59


👉ርዕስ:- እፎይታ
✍️ጸሐፊ:- ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

22 Jan, 19:54


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

22 Jan, 18:16


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 15


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

22 Jan, 13:30


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አሁን ግን ከኃጢአት አርነት ወጥታችሁ ለእግዚአብሔርም ተገዝታችሁ፥ ልትቀደሱ ፍሬ አላችሁ፤ መጨረሻውም የዘላለም ሕይወት ነው።”
ሮሜ 6፥22



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

21 Jan, 20:08


#ጥምቀት


                                     ክፍል-፫


ጥምቀት በማን ስም?


ሰዎች ኢየሱስን ለመቀበል እንዲዘጋጁ መጥምቁ ዮሐንስ የንስሐ ጥምቀትን ይሰብክ ነበር። ኢየሱስ አማኞችን በመንፈስ ቅዱስና በእሳት አጥምቋል (ማቴ. 3፥11፤ ማር. 1፥8)። በአዲስ ኪዳን ጥምቀት በአብ፥ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም፤ በውኃ መርጨት፥ ማፍሰስና ማጥለቅ የሚደረግ ነው። በሐ.ሥ. «በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ» የሚለው፥ ሉቃስ የጴጥሮስን ትእዛዝ በሙሉ ሳይሆን በአጭሩ የጻፈው መሆኑን ያመለክታል። ሐዋርያት፥ አማኙ ከሥላሴ አካላት ጋር ግንኙነት እንዳለው ስለሚያውቁ የክርስቶስን ትእዛዝ አሟልተው የፈጸሙ መሆናቸውንም መረዳት አያስቸግርም፤ ሐ.ሥ. 2፥38። ሰው በኢየሱስ ከርስቶስ ስም ሲያምንም ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክና ፍጹም ሰው ሆኖ የአብ አንድያ ልጅ፥ እንደዚሁም መንፈስ ቅዱስን ሰጭ መሆኑን ያምናል። ይህም በጴጥሮስ ስብከት ግልጥ ሆኗል፤ ሐ.ሥ. 2፥33:36። ይህን እውነት የማይቀበል መንፈስ ቅዱስን መሳደብ እንዳይሆንበት መጠንቀቅ አለበት፤ ማቴ. 12፥31:32። እንግዲህ «በክርስቶስ ስም መጠመቅ» ሥላሴን (ሦስቱን አካላት) እና ግብራቸውን ያጠቃልላል።

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት በበዓለ ኀምሳ ዕለት በቤተክርስቲያን ተደረገ (ሐ.ሥ. 1፥5፤ 2፥1-4)፥ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ምእመናን ሁሉ በክርስቶስ ሥራ ከክርስቶስ አካል (ቤተክርስቲያን) ጋር አንድ በመሆን በቤተክርስቲያን ላይ የወረደውን መንፈስ ቅዱስ አብረው ይካፈላሉ፤ 1ቆሮ. 12፥13፤ ቲቶ 3፥3-5። ክርስቶስ ሲጠመቅ የውሃና የመንፈስ ጥምቀት የተያያዘ ነበር፥ ይህም ለእኛ ምሳሌ ነው፤ ሉቃ. 3፥21:22፤ ሐ.ሥ. 2፥38፤ ቲቶ 3፥5። የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት የውሃን ጥምቀት ሊከተል ወይም ሊቀድም ይችላል፤ ሐ.ሥ.8፥4-17፤ 10፥44-48።
ጥምቀት ከክርስቶስ ጋር አንድ ያደርገናልና በዚህ መሠረት ከኃጢአት እንደተለየን ቁጥረን በአዲስ ሕይወት እንኖራለን፤ ሮም 6፥1-11።

ጥምቀት በሊቃውንቶች ዘንድ

በቤተክርስቲያን ሊቃውንት የማይስማሙባቸው ነገሮች አሉ። ከእነዚህም ጥቂቶችን በአጭሩ እንገልጣለን።

1. አንዳንዶች ጥምቀት የሚለው ቃል በውሃ ውስጥ ማጥለቅን ያሳያል ሲሉ፥ ሌሎች ደግሞ «ማፍሰስ» የሚለው ቃል የጥምቀትን ምሥጢር ያመለክታል ይላሉ፤ ሐሥ.2፥33።

2. አንዳንዶች ማር. 16፥16 ና ሌላም ክፍልን ጠቅሰው ሰው ሳያምን ሊጠመቅ አይገባም ይላሉ። እንደዚሁም ሌሎች በብሉይ ኪዳን ዘመን ሕፃናት ተገረዙ፤ ስለዚህ ልጆች እንደ እግዚአብሔር ሕዝብ ተቈጥረው እግዚአብሔር የቃል ኪዳን አባሎች አድርጓቸዋልና (ዘፍ. 17፥7፤ ሮሜ 4፥11፤ ገላ. 3፥29፤ ቆላ. 2፥11-12፤ 1ቆሮ. 7፥14) ሊጠመቁ ይገባቸዋል ይላሉ፤ ሐ.ሥ.2÷39፤ 16፥15:33።

3. በዚያም ሆነ በዚህ ጥምቀት አስፈላጊ ነው፤ በረከቱ በክርስቶስ ከመንፈስ ቅዱስ ነውና። ተጠማቂው በረከትን የሚያገኘው ፦
(ሀ) በተለይ በሥርዓቱ፥
(ለ) በተለይ በእምነቱ፥
(ሐ) ጥምቀት
በተለይ የቃል ኪዳን ተስፋ ስለታተመበት ነው በማለት ሊቃውንት በአሳብ ይለያያሉ።


ይቀጥላል...


ምንጭ፦  የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 256፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 3




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

21 Jan, 15:19


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 14


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

21 Jan, 13:30


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እርሱም የላከውን እናንተ አታምኑምና በእናንተ ዘንድ የሚኖር ቃሉ የላችሁም።”
ዮሐንስ 5፥38



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

21 Jan, 04:23


#ሄኖን


#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት


ሄኖን፤ ምንጮች ማለት ነው። ከዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ ከስካይቶፖሊስ (ቤተ ሳን) በስተ ደቡብ በኩል ዐሥራ ሦስት ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ የሚገኝ ስፍራ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ወንዝ አቅራቢያ ከቤትሳን ወደ ደቡብ ያለ ቦታ።  መጥምቁ ዮሐንስ ብዙ ገሊላውያንን በዚህ ቦታ አጥምቋል፤ ዮሐ. 3፥23።



ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 13፣ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጽሑፍ ጋር፤ ገጽ 1593



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

20 Jan, 18:55


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 13


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

20 Jan, 16:38


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እንዲሁ ዳግመኛ ለኢየሩሳሌምና ለይሁዳ ቤት በዚህ ወራት በጎነትን አደርግ ዘንድ አስቤአለሁ አትፍሩ።”
ዘካርያስ 8፥15



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

19 Jan, 19:02


👉ርዕስ፦ ምስጢረ ጥምቀት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

19 Jan, 18:56


👉ርዕስ፦ የውኃ ጥምቀት
ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎስ
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ
📝እርማት፦ ይግረም ረታ



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

19 Jan, 18:46


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

19 Jan, 17:25


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 12


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

19 Jan, 14:57


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ፈሪሳውያንና ሕግ ዐዋቂዎች ግን በዮሐንስ እጅ ባለ መጠመቃቸው፣ እግዚአብሔር ለእነርሱ ያለውን ዐላማ አቃለሉ።”
ሉቃስ 7፥30 (አዲሱ መ.ት)



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

18 Jan, 18:31


#ጥምቀት



              ክፍል-፪


የጥምቀት ዓይነቶች


1.የአካል ጥምቀት

"…እኛ ሁላችን በአንድ መንፈስ አንድ አካል እንድንሆን ተጠምቀናልና…" (1ኛ ቆሮ.1፥13)፡፡ አጥማቂ መንፈስ ቅዱስ ሲሆን መጠመቂያው የክርስቶስ አካል ነው፡፡ "…ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን …" (ሮሜ.6፥2) ሲል ይህንን ጥምቀት ያመለክታል፡፡ ለመዳን ብቸኛው አስፈላጊ ጥመምቀት ነው ይህ ጥምቀት፡፡ ባመንን ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ ወደ ክርስቶስ አካል ይጨምረናል፤ ኤፌ.1፥13

2.የውሃ ጥምቀት

"በመንገድም ሲሄዱ ወደ ውኃ ደረሱ፤ ጃንደረባውም። እነሆ ውኃ፤ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድር ነው? አለው። ፊልጶስም በፍጹም ልብህ ብታምን፥ ተፈቅዶአል አለው። መልሶም ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ አለ። ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም።" (የሐዋ.8፥36-38)

3. የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት

"ዮሐንስ በውኃ አጥምቆ ነበርና፥ እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኋላ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ አለ" (የሐዋ.1፥5)
"ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ" (የሐዋ.1፡8)
"እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል" (ማቴ.3፡11)
አጥማቂው ኢየሱስ ሲሆን መጠመቂያው መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ አስፈላጊነቱ ለአገልግሎት ኀይልና የተለያዩ ፀጋ ስጦታዎችን ለመቀበል ነው፡፡ በበዓለኀምሳ ቀንም የሆነው አስረጂ ነው፡፡

4. የእሳት ጥምቀት

"እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል" (ዮሐ.3፥11)፡፡
ሁለት የተለያዩ ጥምቀቶች ናቸው የተጠቀሱት፡፡ የመንፈስ ጥምቀትን ተነጋግረንበታል፡፡ አብሮ የተጠቀሰው የእሳት ጥምቀት ነው፡፡ አጥማቂው ጌታ ነው፤ መጠመቂያው ደግሞ መንፈሳዊ እሳት፡፡ አስፈላጊነቱን በተመለከተ ቀጥር 12 ላይ መንሹም በእጁ ነው፥ አውድማውንም ፈጽሞ ያጠራል፥ ስንዴውንም በጎተራው ይከታል፥ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል ይለናል፡፡ ህይወትን የሚያጠራ እሳት ነው፡፡ በሚልክያስ መጽሐፍ 3፥1-4 ላይ ጥሩ ትንቢታዊ ማስረጃ አለን።

5. የመከራ ጥምቀት

"ኢየሱስም እኔ የምጠጣውን ጽዋ ትጠጣላችሁ፥ እኔ የምጠመቀውንም ጥምቀት ትጠመቃላችሁ ሲል ለዘብዴዎስ ለጆች የተናገረው ነው" (ማር.10፥39)፡፡

አጥማቂ አልተጠቀሰም፡፡ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው፡፡ መጠመቂያው መከራ ነው፡፡ አስፈላጊነቱ ለብስለት (ያዕ.1፥2-4) ወይም በጥበብ ለማደግ እና መታዘዝን ለመማር (ያዕ.1፥5፤ ዕብ.5፥8-9፤ ሉቃ.2፥52) እንዲሁም ለባህሪ መታነጽ ነው(ሮሜ.5፥3-4)፡፡

6. የንስሐ ጥምቀት

“እኔ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ ...ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ግን በእሳት ያጠምቃችኋል.." ማር 1፥8፤ ማቴ 3፥11፤ ሐዋ 19፥4

7. የሙሴ ጥምቀት

ይህ ጥምቀት እስራኤላውያን በቀይ ባህር አድርገው ከግብጽ ነፃ መውጣታቸውን የሚያመለክት ነው። (1ኛ ቆሮ. 10፥2)


ይቀጥላል...


ምንጭ፦ 1biblee.blogspot.com



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

18 Jan, 12:10


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 11


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

18 Jan, 10:34


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔርም በጃንደረቦቹ አለቃ ፊት ለዳንኤል ሞገስንና ምሕረትን ሰጠው።”
ዳንኤል 1፥9




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

17 Jan, 17:30


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 10


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

17 Jan, 13:21


👉ርዕስ፦ የመንግሥቱ ወንጌል
በባይብል ፕሮጀክት፣ በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

17 Jan, 13:20


https://youtu.be/i7A2KVfX6nM?si=2h5TEylpJZcKhthO



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

17 Jan, 10:34


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን፦ አንሄድባትም አሉ።”
ኤርምያስ 6፥16




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

16 Jan, 18:39


#ጥምቀት



ክፍል-፩


ጥምቀት ምንድነው?

ጥምቀት የሚለው ቃል βάπτισμα (baptisma) ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ስርወ-ቃሉ βαπτίζω (baptizo) ነው። ባፕቲዞ ማለት "ማጥለቅ ወይም መንከር" ማለት ነው። በመጀመሪያ አጠቃቀሙ፣ አንድን ነገር በውሃ ውስጥ በማጥለቅ የመታጠብ ወይም የማጽዳት ሂደትን ያመለክታል።

ጥምቀት በብሉይ ኪዳን መታጠብ ወይም መንጻት ማለት ነው (ዘጸ. 30፥17–21፤ ዘሌ. 11፥25)።

ጥምቀት የተለያየ ነው። በውሃ፥
በመንፈስ ቅዱስ፥ በሥቃይም መጠመቅ አለ፤ ሉቃ 3፥16፤ 12፥50። ጥምቀት የሚከተሉትን አሳቦች ይይዛል።

1. መንጻት፤ ማር. 1፥1-4፤ ዮሐ 3፥22-25፤ ሐ.ሥ. 22፥16፤ ቲቶ 3፥5።

2. መለወጥ፤ ማር. 1፥4-8፤ ሉቃ. 3፥7-14፤ 1ጴጥ. 3፥18-22።

3. መተባበር፤ 1ቆሮ. 1፥13፤ 10፥2፤ ገላ. 3፥27፤ ሮሜ 6፥3:4።

በአዲስ ኪዳን ጥምቀት በአብ፥ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም፤ በውኃ መርጨት፥ ማፍሰስና ማጥለቅ የሚደረግ ነው። ጥምቀት የአማኞችን ንስሐ መግባት፥ የኃጢአት ይቅርታ ማግኘትና ከኃጢአት መንጻትን የሚያሳይ ምልክት ነው (የሐዋ. 2፥38)። በተጨማሪም ጥምቀት አማኙ ከክርስቶስ ጋር በኅብረት ተካፋይ መሆኑን ያመለክታል (ገላ. 3፥26-27)። አማኝ ሲጠመቅ የክርስቶስ ሞት ተካፋይ ሆነ ማለት ነው። ለኃጢአትና ለአሮጌው ኃጢአተኛ ተፈጥሮው ይሞታል። የዚያኑ ጊዜ ደግሞ የኢየሱስ ትንሣኤ ተካፋይ ይሆናል፤ በእምነት አዲስ ሕይወትን ይቀበላል (ሮሜ 6፥38)።

ይቀጥላል...


ምንጭ፦ Carson, D. A. (1984). Matthew: Chapters 1-12. Zondervan.
This book explains the Great Commission and the significance of baptism as a command from Christ.፣ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 255-256፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 3



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

16 Jan, 13:54


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 9


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

16 Jan, 10:03


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ወንድሞች ሆይ፥ በአእምሮ ሕፃናት አትሁኑ፤ ለክፋት ነገር ሕፃናት ሁኑ እንጂ በአእምሮ የበሰሉ ሁኑ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 14፥20



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

15 Jan, 18:03


ጌታ ቸር እንደሆነ የቀመሰ ሰው በድነቱ ለመጽናት እና ለመቀጠል የእግዚአብሔር ቃል ፍቅር እና ጉጉት (appetite) እንዲኖረው የግድ ነው። ስለሆነም አንድ ክርስቲያን ይህን የጋለ ለቃሉ ያለውን ፍላጎትና ጥማት ማስቀጠል የእድሜ ዘመኑ ሁሉ ኃላፊነት አልፎ ተርፎም ተጋድሎው ነው። ይህ የመንፈሣዊ ሕይወት የጤናማነት ጠረን ከአማኝ ከተወሰደ ወደ ውድቀት መንደር መንጎድ እንደጀመረ አልያም እንደወደቀ ትልቅ ማሳያ ነው። የሚያሳዝነው ነገር ግን ይህን ግለት በቸልተኝነት እና በለብታ እንዲጠቃ የሚያደርጉ በሽታዎች አሉ። ሐዋርያው ጴጥሮስ እንዲህ ይዘረዝራቸዋል፦
👉ክፋት
👉ተንኰል
👉ግብዝነት
👉ቅንዓት
👉ሐሜት
ከዚህ ጹሑፍ አንባቢ መካከል "እንዴ እውነት ነው እኔ ጋም የቃሉ ጥማት ጠፍቷል" የሚል አይጠፋም። ታዲያ ወንድሜ/እህቴ ምን ትጠብቃለህ/ቂያለሽ ከላይ ከተጠቀሱት ደዌዎች በአንዱ ተጠቅተሃል/ሻልና ነፍስህን/ሺን አድን/ኚ!

"እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።"
1ኛ ጴጥሮስ 2፥1-3



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

15 Jan, 17:31


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 8


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

15 Jan, 13:35


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ነፍሴን ደግሞ አነሣት ዘንድ አኖራለሁና ስለዚህ አብ ይወደኛል።”
ዮሐንስ 10፥17



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

15 Jan, 01:23


#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?


ኤርምያስ 45
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም በአራተኛው ዓመት የኔርያ ልጅ ባሮክ እነዚህን ቃሎች ከኤርምያስ አፍ በመጽሐፍ በጻፋቸው ጊዜ፥ ነቢዩ ኤርምያስ የተናገረው ቃል ይህ ነው።
² ባሮክ ሆይ፥ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይልሃል፦
³ አንተ፦ እግዚአብሔር በሕመሜ ላይ ኀዘንን ጨምሮብኛልና ወዮልኝ! በልቅሶዬ ጩኸት ደክሜአለሁ፥ ዕረፍትንም አላገኘሁም ብለሃል።
⁴ እንዲህ በለው፦ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ የሠራሁትን አፈርሳለሁ፥ የተከልሁትንም እነቅላለሁ፤ ይኸውም በምድር ሁሉ ነው።
⁵ ለራስህ ታላቅን ነገር ትፈልጋለህን? በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ፥ እነሆ፥ ክፉ ነገርን አመጣለሁና አትፈልገው፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን በሄድህበት ስፍራ ሁሉ ነፍስህን እንደ ምርኮ አድርጌ እሰጥሃለሁ።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

14 Jan, 18:03


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 7


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

14 Jan, 10:46


የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ በዚህ ሳምንት ስለጥምቀት እናወራለን። ጥምቀት ምንድነው? ስንት ዓይነት ጥምቀት አለ? እነማን ይጠመቁ? የጥንት ቤተክርስቲያን እና የቤተክርስቲያን አባቶች ስለጥምቀት ምን አሉ? እነዚህ የመሳሰሉትን ጥያቄዎች እያነሳን እናወጋለን። በተጨማሪም እናንተ በምትገኙበት ቤተክርስቲያን የቅዱስ ጥምቀት ሥርዓት እንዴት ነው? መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው ብላችሁ ታምናላችሁ? እንዴት?



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

14 Jan, 10:09


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አቤቱ፥ ምሕረትህን እንዴት አበዛህ! የሰው ልጆች በክንፎችህ ጥላ ይታመናሉ።”
መዝሙር 36፥7



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

11 Jan, 14:42


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ወደ ዘለፋዬ ተመለሱ፤ እነሆ፥ መንፈሴን አፈስስላችኋለሁ፤ ቃሌን አስተምራችኋለሁ።”
               ምሳሌ 1፥23




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

10 Jan, 20:34


#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት


#ጊልቦዓ

ጊልቦዓ፤ ኃይለኛ ምንጭ ማለት ነው። በይሳኮር ርስት ያለ ተራራማ አገር። ሳኦልና ዮናታን በጊልቦዓ ተገደሉ፤ 1ሳሙ. 31፤ 2ሳሙ. 1፥21።



ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 242



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

10 Jan, 19:26


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
✍️ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 3


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

10 Jan, 11:29


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ንቂ፥ ንቂ፥ ዲቦራ ሆይ፤ ንቂ፥ ንቂ፥ ቅኔውን ተቀኚ፤ ባርቅ ሆይ፥ ተነሣ፤ የአቢኒኤም ልጅ ሆይ፥ ምርኮህን ማርክ።”
መሳፍንት 5፥12




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

09 Jan, 19:09


ነቢዩ ኤርምያስ




                        ክፍል-፲
                 (የመጨረሻ ክፍል)


በእግዚአብሔርና እግዚአብሔር ለእስራኤልና ለሕዝቡ ባለው የመጨረሻ ዐላማ ላይ ኤርምያስ እምነት ነበረው፡፡ በይሁዳ ላይ በቅርብ ጊዜ ጥፋት የሚመጣ ቢሆንም፣ እርሱ በእግዚአብሔር ለመታመን በቂ ምክንያት ነበረው፡፡ ውግዘት እያስተላለፈም እንኳ እግዚአብሔር በምድሪቱ ያሉትን ትሩፋን ወይም በባቢሎን የሚገኙትን ምርኮኞች (29፥1-4፤ 32፥ 1-15) ለመባረክ የነበረውን የመጨረሻ ዐላማ አየ፡፡ እስራኤል ዳግም እንደምትተከል የተነበያቸው ትንቢቶች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሸብረቀው ከሚገኙት መካከል ናቸው (3፥14-18፤ 30፥18-22 ፤ 31፥1-4፤ 33÷ 10-13)::

ኤርምያስ ያለ አንዳች ፍርሃት ፍጹም ግልጽነትን ለእግዚአብሔር አሳይቶአል፤ ከእርሱና ከሌሎች ጋር እግዚአብሔር ያደርገው በነበረው ተግባር ላይ ሳይቀር ጥያቄ አቅርቦአል (12፥1፤ 15፥10-18፤ 20፥7)፡፡ ይልቁንም ሁሉንም ሰው መውደድ የቻለ ሰው ነው (17፥7-8)፡፡ በባሮክ ታማኝነት (36፥32)፣ በሊቀ ካህናቱ በሶፎንያስ ወዳጅነት (29፥24-32)፣ በኢትዮጵያዊው በአቤሜሌክ እጅ ከሞት አደጋ በመትረፉ (38 ፥ 7-13) እና በንጉሥ ሴዴቅያስ ዘንድ ባገኘው አክብሮት (38፥14-28) ኤርምያስ ደስተኛ ነበር፡፡

ኤርምያስ በመራራ ቃላት በመንቀፍ ለኀጢአት ብርቱና የማይበርድ ጥላቻ ነበረው፡፡ የሕዝቡን ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ፣ ግብረ ገባዊና መንፈሳዊ ሕይወት በጥልቅ መረመረ፡፡ ነቢያት፣ ካህናት፣ ነገሥታት መሳፍንት፣ ዘመዶቹ እንኳ ሳይቀሩ ለእኛ ይወግናል ብለው ተስፋ አላደረጉም (ከ5፥1-5፤ ከ13፥1-14፤ 23 ፥ 1-4 ፤ ከ22 ፥ 13-19)፡፡

በእርሱ ዘመን ሕዝቡ ወደ ፍርድ እየተጓዙ ቢሆኑም እንኳ፣ የይሁዳ ሕዝብ እንደማይጠፉ ኤርምያስ እምነት የነበረው መሆኑን አሳየ፡፡ ከእግዚአብሔር ዐላማ የተነሣ ባቢሎን ሊቋቋሙት የሚችሉት ኀይል አልነበረም፤ ይህ ማለት ግን ከቶ ሕዝቡ ይጠፋል ማለት አይደለም (30፥11፡18-22 ፧ 31 ፥ 35-37 ፧ 33 ፥ 19-26)፡፡ በእርሱ ዘመን በነበሩት እንደ ከሓዲ ቢቈጠርም እንኳ፣ ሕዝቡ ወደፊት ህልውና እንደሚኖራቸው እርሱ የላቀ እምነት ነበረው (ምዕ 32 እና 37 እንዲሁም 25 ፥ 11 ፤ 29 ፥ 7-14)፡፡



ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 828




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

09 Jan, 18:48


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 2


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

09 Jan, 10:24


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ያዕቆብ ሆይ፥ እስራኤልም ሆይ፦ መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች ፍርዴም ከአምላኬ አልፋለች ለምን ትላለህ? ለምንስ እንዲህ ትናገራለህ?”
ኢሳይያስ 40፥27




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

08 Jan, 21:46


#መጻሕፍትን_በድምጽ

👉ርዕስ፦ እፎይታ
ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ያሬድ ጥላሁን
🔊ክፍል፦ 1


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

08 Jan, 18:58


👉ርዕስ፦ የዘላለም ኪዳን
ጸሐፊ፦ ዋችማን ኒ
🗣ተርጓሚ፦ ጳውሎስ ፈቃዱ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

08 Jan, 18:57


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

08 Jan, 14:31


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“የልብሱንም ጫፍ ብቻ ሊዳስሱ ይለምኑት ነበር፤ የዳሰሱትም ሁሉ ዳኑ።”
ማቴዎስ 14፥36



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

07 Jan, 14:06


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


ዛሬ ተወልዷል! ማን?

👉መድኃኒት፦ ከኃጢአት፣ ከሰይጣን፣ ከሞት ፍርሃት፣ ከፍርድ ነጻ ሊያወጣን የሚችል።
👉ክርስቶስ፦ በእግዚአብሔር የተቀባ
👉ጌታ፦ እራሱ እግዚአብሔር የሆነ

“ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።”
                ሉቃስ 2፥11

ይህን እናስተውል! አንርሳውም!!! መልካም በዓል!



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

07 Jan, 11:02


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እኛም አይተናል አባትም ልጁን የዓለም መድኃኒት ሊሆን እንደ ላከው እንመሰክራለን።”
1ኛ ዮሐንስ 4፥14



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

07 Jan, 10:51


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።”
                ሉቃስ 2፥11


"እስመ ናሁ ተወልደ ለክሙ ዮም መድኅን፡ ዘውእቱ ክርስቶስ እግዚእ፡ ቡሩክ በሀገረ ዳዊት።"
                 ሉቃስ 2፥11


"Harʼa magaalaa Daawit keessatti fayyisaan isiniif dhalateera; innis Kiristoos Goofticha."
                Luqaas 2:11


"እቲ መልኣኽ ድማ፡ እንሆ፡ ሎሚ መድሓኒ ኣብ ዓዲ ዳዊት ተወሊድልኩም ስለ ዘሎ፡ - ንሱ ኸኣ ክርስቶስ ጐይታ እዩ፡ - ንዅሉ ህዝቢ ዚኸውን ዓብዪ ሓጐስ ኤበስረኩም አሎኹ እሞ፡ ኣይትፍርሁ።"
                 ሉቃስ 2፥10-11



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

07 Jan, 05:54


ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

06 Jan, 19:41


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ



ወንጌላት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አገልግሎት ምን አሉ?


4. ጸሎት እና በእግዚአብሔር ላይ መደገፍ

ኢየሱስ በአብ ላይ ያለውን ጥገኝነት በማሳየት የእግዚአብሔርን መመሪያ በመሻት ደጋግሞ ይጸልይ ነበር።

በማለዳ መጸለይ፦ የጸሎትን አስፈላጊነት በማሳየት ጌታችን አርአያ ሆኖናል።

“ማለዳም ተነሥቶ ገና ሌሊት ሳለ ወጣ ወደ ምድረ በዳም ሄዶ በዚያ ጸለየ።”
            ማርቆስ 1፥35

የምልጃ ጸሎት፦ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እና ለአማኞች ሁሉ ጸለየ።

“ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ፥ ከቃላቸው የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑ ደግሞ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻ አልለምንም፤ አንተ እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፥ አንተ፥ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ።”
             ዮሐንስ 17፥20-21

5. ስልጣን እና ኃይል

ኢየሱስ መለኮታዊ ስልጣንን በትምህርቱ፣ በተአምራቱ እና በትእዛዙ አሳይቷል።

በተፈጥሮ ላይ ስልጣን፦ ማዕበሉን ጸጥ አሰኘው።

“ነቅቶም ነፋሱን ገሠጸው ባሕሩንም፦ ዝም በል፥ ፀጥ በል አለው። ነፋሱም ተወ ታላቅ ፀጥታም ሆነ።”
       ማርቆስ 4፥39

በአጋንንት ላይ ስልጣ፦ አጋንንትን አውጥቶ መንፈሳዊ ነጻነትን አውጇል።

“በልዩ ልዩ ደዌም የታመሙትን ብዙዎችን ፈወሰ፥ ብዙዎችንም አጋንንት አወጣ፥ አጋንንትም ክርስቶስ መሆኑን አውቀው ነበርና ሊናገሩ አልፈቀደላቸውም።”
          ማርቆስ 1፥34

ኃጢአትን የማስተሰረይ ስልጣን፦ አምላካዊ ስልጣኑን በመግለጥ ይቅርታን አወጀ።

“ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢአት ሊያስተሰርይ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ ብሎ፥ ሽባውን፦ አንተን እልሃለሁ፥ ተነሣ፥ አልጋህን ተሸክመህ ወደ ቤትህ ሂድ አለው።”
          ሉቃስ 5፥24

6. የመሥዋዕት ሞት እና ትንሣኤ

የኢየሱስ የመጨረሻ ተልእኮ ሞትንና ኃጢአትን በማሸነፍ በመነሳት ለሰው ልጆች ኃጢአት መሞት ነበር።

ስቅለት፡- በሞቱ የኃጢአትን ዋጋ ወይንም ቅጣት ከፈለ።

“ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።”
        ዮሐንስ 19፥30

ትንሳኤ፡- በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል በመንሳት ተነሳ በሞት ላይ ኃይሉን አረጋገጠ።

“እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ።”
             ማቴዎስ 28፥6




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

06 Jan, 13:31


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“የዳዊትንም ቤት መክፈቻ በጫንቃው ላይ አኖራለሁ፤ እርሱም ይከፍታል የሚዘጋም የለም፤ እርሱም ይዘጋል የሚከፍትም የለም።”
ኢሳይያስ 22፥22



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

06 Jan, 08:10


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ



“ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።”
                    ኢሳይያስ 9፥6


"እስመ ሕፃን ተወልደ ለነ፤ ወልድ ተውሀበ ለነ ወቅድመት ኮነ ዲበ መትከፍቱ፤ ወይሰመይ ስሙ ዓቢየ ምክር፡ አበ ዓለም፡ ወመልአከ ሰላም፤ እስመ አነ አመጽእ ሰላመ ለመላእክት በሕይወትሰ ዚአሁ።"
ኢሳይያስ 9፥6


"Mucaan nuuf dhalateera;
ilmi nuuf kennameera;
mootummaan gatiittii isaa irra jiraata.
Innis Gorsaa Dinqisiisaa, Waaqa Jabaa,
Abbaa Bara baraa, Mootii Nagaa
jedhamee ni waamama."
Isaayyaas 9:6


"ሕጻን ተወሊዱልና፡ ወዲ ተውሂብና እዩ እሞ፡ እቲ ግዝኣት ከኣ ኣብ መንኲቡ እዩ፡ ስሙውን ግሩም፡ መካር፡ ብርቱዕ ኣምላኽ፡ ኣቦ ዘለኣለም፡ መስፍን ሰላም ኪስመ እዩ።"
ኢሳይያስ 9፥6




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

05 Jan, 19:52


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ



ወንጌላት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አገልግሎት ምን አሉ?

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በኢየሱስ ክርስቶስ አገልግሎቶች ውስጥ ፍቅር፣ የርህራሄ፣ የማስተማር እና የመቤዠት ተልእኮ ይታያል። ከዚህ በታች የባህሪው እና የአገልግሎቱ ቁልፍ ገጽታዎች ከቅዱሳት መጻሕፍት እንመለከታለን

1. ፍቅር እና ርህራሄ

ኢየሱስ ለሰዎች በተለይም ለተገለሉት፣ ለኃጢአተኞች እና ለተቸገሩት ጥልቅ ፍቅርና ርኅራኄ አሳይቷል።

የታመሙትን መፈወሱ፦ ኢየሱስ ብዙ በሽተኞችን ፈውሷል።

“ኢየሱስም በምኩራቦቻቸው እያስተማረ፥ የመንግሥትንም ወንጌል እየሰበከ፥ በሕዝብም ያለውን ደዌና ሕማም ሁሉ እየፈወሰ፥ በከተማዎችና በመንደሮች ሁሉ ይዞር ነበር።”
ማቴዎስ 9፥35

ርኅራኄን ለሕዝቡ፦ ስለ ሕዝቡ ሥጋዊና መንፈሳዊ ፍላጎት ይገደው ነበር።

“ወጥቶም ብዙ ሕዝብ አየና አዘነላቸው ድውዮቻቸውንም ፈወሰ።”
ማቴዎስ 14፥14

ኃጢአተኞችን መውደድ፦ ከኃጢአተኞች ጋር አብሮ በልቷል እና ኃጢአታቸውን ይቅር በማለት ተልእኮው የጠፉትን ማዳን መሆኑን አሳይቷል።

“የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአለና አለው።”
ሉቃስ 19፥10


2. ማስተማር እና ስብከት

ኢየሱስ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት፣ ስለ ንስሐና ስለ ጽድቅ ሕይወት አስተምሯል።

የተራራው ስብከት፦ በፍቅር፣ ትህትና እና ብፁዓን ላይ ጥልቅ ትምህርት ሰጥቷል።

ማቴዎስ ምዕራፍ 5–7 - እነዚህ ምዕራፎች ብፁዓን፣ ስለ ይቅርታን እና በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ እንዴት መኖር እንደሚችሉ ያስተምራሉ።

ኢየሱስ መንፈሳዊ እውነቶችን ለማስረዳት በምሳሌ ተጠቅሟል።

“ኢየሱስም ለሕዝቡ ይህን ሁሉ በምሳሌ ተናገረ፤ በነቢዩም፦ በምሳሌ አፌን እከፍታለሁ፥ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የተሰወረውንም እናገራለሁ የተባለው ይፈጸም ዘንድ ያለ ምሳሌ አልተናገራቸውም።”
ማቴዎስ 13፥34-35

የንስሐ ጥሪ፦ ሰዎች ንስሐ እንዲገቡና ወንጌልን እንዲያምኑ አሳስቧል።

“ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እየሰበከና፦ ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ በወንጌልም እመኑ እያለ ወደ ገሊላ መጣ።”
ማርቆስ 1፥14-15

3. የአገልጋይ መሪነት

ኢየሱስ ከዓለማዊ የሃይል እሳቤዎች ጋር በማነፃፀር ትህትናን እና አገልጋይነትን አሳይቷል።

የደቀመዛሙርቱን እግር ማጠብ፦ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ አገልጋይነትን አሳይቷል።

"እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ። እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል።"
ዮሐንስ 13፥13-14

መስዋዕታዊ ፍቅር፡- ኢየሱስ በፈቃዱ ነፍሱን ለሰው ልጆች አሳልፎ ሰጥቷል።

“ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም።”
ዮሐንስ 15፥13


ይቀጥላል...



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

05 Jan, 13:39


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አሁን ግን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ ታይቶአል። እርሱ ሞትን ሽሮአልና እኔ ሰባኪና ሐዋርያ አሕዛብንም አስተማሪ እንድሆን በተሾምሁበት በወንጌል ሕይወትንና አለመጥፋትን ወደ ብርሃን አውጥቶአል።”
2ኛ ጢሞቴዎስ 1፥10-11




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

05 Jan, 11:04


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ።”
             ዕብራውያን 2፥14-15


እስመ ደቂቅ ተሳተፉ በሥጋ ወደም ውእቱኒ ተሳተፎሙ በዝንቱ ወከመ ቢጾሙ ኮነ ሎሙ ከመ በሞቱ ይስዐሮ ለመልአከ ሞት ዘውእቱ ሰይጣን። ወያዕርፎሙ ለኵሎሙ እለ በፍርሀተ ሞት ተኰነኑ በኵሉ መዋዕለ ሕይወቶሙ ወተቀንዩ ለግብርናት።
                 ዕብራውያን 2፥14-15


"Sababii ijoolleen sun foonii fi dhiiga qabaniif, Yesuusis duʼa ofii isaatiin diiyaabiloos isa duʼa irratti humna qabu sana balleessuuf jedhee namummaa isaanii qoodate; innis warra bara jireenya isaanii hunda garbummaa sodaa duʼaatiin hidhamanii turan bilisa baasuuf jedhee waan kana godhe."
             Ibroota 2:14-15


እምብኣርሲ ብሓቂ ንዘርኢ ኣብርሃም ኣልዓሎ እምበር፡ ንመላእኽትስ ኣየልዓሎምን እሞ፡ እቶም ውሉድ ብደምን ስጋን ካብ ዚሐብሩስ፡ ብሞቱ ነቲ ሓይሊ ሞት ኣብ ኢዱ ዝሐዘ ምእንቲ ኺስዕር፡ ንሱውን ድያብሎስ እዩ፡ ነቶም ብፍርሃት ሞት ብዘሎ ዘመኖም ብባርነት ተታሒዞም ዝነበሩ ዅላቶም ሓራ ምእንቲ ኼውጽኦም ኢሉ፡ ንሱውን ብእኡ ሐበሮም።
               ዕብራውያን 2፥14-16



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

04 Jan, 23:10


#እራሳችንን_እንመርምር



የምንወደው፣ የምናውቀው፣ የምናከብረው አልያም አንድ የማናውቀው ሰው ትልቅ የተባለ ይቅር ትንሽ የምትባል ስጦታ እንካችሁ ቢለን በምስጋና ተሽቆጥቁጠን ከመቀበል አልፈን ስለስጪው ደግነትና መልካም በተገኘው እድል እንናገር ነበር ግን በጣም ግርም የሚለው ነገር እግዚአብሔር ብቸኛውን አንድያ ልጁን እንካችሁ ብሎ ሰጥቶን፣ በደበዘዘና በደከመ ስሜት "አዎ፣ እግዚአብሔር ልጁን ላከ" እያልን ምንም እንዳልሆነ ነገር ዝም ብለን ወደየመንገዳችን ስንሄድና ስንሰማራ ያስተዛዝባል። መደነቅና በአግራሞት መሞላት እሺ ይቅርብን እንበል ቢያንስ አምላክ ልጁን ለምን ላከ አይባልም?🙊🙈 እሺ አምላክ ልጁን ላከ፣ ከላከስ እኔስ እንደግል ምን ላድርግ አይባልም ወይስ ነገሩ እንዴት ነው🤔


“በሬ የገዢውን አህያም የጌታውን ጋጣ አወቀ፤ እስራኤል ግን አላወቀም፥ ሕዝቤም አላስተዋለም።”
ኢሳይያስ 1፥3




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

04 Jan, 19:55


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


4. ዘካርያስ 9፥9-10

የመጀመሪያው መምጣት፡- “...ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል።”
        ዘካርያስ 9፥9

ኢየሱስ በድል ወደ ኢየሩሳሌም በገባበት ወቅት ተፈጸመ (ማቴዎስ 21፥4-5)።

ዳግም ምጽአት፡- “... ለአሕዛብም ሰላምን ይናገራል፤ ግዛቱም ከባሕር እስከ ባሕር፥ ከወንዙም እስከ ምድር ዳርቻ ድርስ ይሆናል።”
         ዘካርያስ 9፥10

ከዳግም ምጽአቱ በኋላ ያለውን ዓለም አቀፋዊ ግዛቱን ያመለክታል።

5. ዳንኤል 7፥13-14

የመጀመሪያው፡- “በሌሊት ራእይ አየሁ፤ እነሆም፥ የሰው ልጅ የሚመስል ከሰማይ ደመናት ጋር መጣ በዘመናት ወደ ሸመገለውም ደረሰ፤ ወደ ፊቱም አቀረቡት።”
        ዳንኤል 7፥13

ኢየሱስ ራሱን “የሰው ልጅ” ሲል ጠርቶታል (ማቴዎስ 26፥64)።

ሁለተኛው፡- “ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የሚናገሩ ሁሉ ይገዙለት ዘንድ ግዛትና ክብር መንግሥትም ተሰጠው፤ ግዛቱም የማያልፍ የዘላለም ግዛት ነው፥ መንግሥቱም የማይጠፋ ነው።”
        ዳንኤል 7፥14

ይህ ወደፊት በሙላት ስለሚመጣው ስለ ኢየሱስ አጽናፈ ዓለማዊ አገዛዝ ይናገራል።

6. መዝሙረ ዳዊት 22

የመጀመሪያው፡- “ልብሶቼን ለራሳቸው ተከፋፈሉ፥ በቀሚሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ።”
        መዝሙር 22፥18

የኢየሱስን ስቃይና ስቅለት ይገልጻል (ዮሐ. 19፥23-24)።

ሁለተኛው፡- "የምድር ዳርቻዎች ሁሉ ያስቡ፥ ወደ እግዚአብሔርም ይመለሱ፤ የአሕዛብ ነገዶች ሁሉ በፊቱ ይሰግዳሉ። መንግሥት ለእግዚአብሔር ነውና፥ እርሱም አሕዛብን ይገዛል።"
          መዝሙር 22፥27-28

ክርስቶስ ንጉሥ እንደ ሆነ ዓለም አቀፋዊ እውቅናን ይሰጣል።

7. ሚልክያስ 3፥1-2

የመጀመሪያው፡- “እነሆ፥ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል፤ ”
        ሚልክያስ 3፥1

ለኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ማዘጋጀት በመጥምቁ ዮሐንስ ተፈጽሟል (ማርቆስ 1፥2-3)።

ሁለተኛው፡- “...እናንተም የምትፈልጉት ጌታ በድንገት ወደ መቅደሱ ይመጣል፤ የምትወዱትም የቃል ኪዳን መልእክተኛ፥ እነሆ፥ ይመጣል፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።”
                ሚልክያስ 3፥1

ኢየሱስን ለማጥራት እና ለመፍረድ እንደሚመጣ ያመለክታል።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

04 Jan, 13:47


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔርም፦ ሰላም ለአንተ ይሁን አትፍራ አትሞትም አለው።”
መሳፍንት 6፥23




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

04 Jan, 11:40


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“ፈጥነውም መጡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ።”
           ሉቃስ 2፥16


"ወሖሩ ፍጡነ ወረከብዎሙ ለማርያም ወለዮሴፍ ወለሕፃንኒ ይሰክብ ውስተ ጎል።"
          ሉቃስ 2፥16


"Isaanis dafanii dhaqanii Maariyaamii fi Yoosefin, daaʼima bidiruu keessa ciisus argan."
              Luqaas 2:16


"ቀልጢፎም ከኣ ኸዱ፡ ንማርያምን ንዮሴፍን ነቲ ሕጻን ከኣ ኣብ መብልዕ ማል ደቂሱን ረኸቡ።"
              ሉቃስ 2፥16




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

03 Jan, 19:53


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ በርካታ ትንቢቶች የኢየሱስ ክርስቶስን የመጀመሪያም ሆነ የዳግም ምጽአት የሚያመለክቱ ሲሆኑ ብዙውን ጊዜ ሁለቱን ክንውኖች አጣምረው ይይዛሉ። ከዚህ በመቀጠል ከፊሉን እንመልከት፦

1. ኢሳ 9፥6-7

የመጀመሪያው፡- “ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤” ኢሳ. 9፥6
ይህ የሚያመለክተው የኢየሱስን መወለድ እና መገለጥ ነው።

ዳግመኛው፡- “...በዳዊት ዙፋንና በመንግሥቱ ላይ አለቅነቱ ይበዛል፥ ለሰላሙም ፍፃሜ የለውም። ” ኢሳ. 9፥7
ይህ የሚያመለክተው በዳግም ምጽአቱ የኢየሱስን ግዛት ነው።

2. ኢሳ 61፥1-2

የመጀመሪያው፦ “የጌታ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች የምሥራችን እሰብክ ዘንድ እግዚአብሔር ቀብቶኛልና” ኢሳ. 61፥1
ኢየሱስ ይህንን በሉቃስ 4፡18-19 በመጥቀስ በመጀመሪያ ምጽአቱ ተልዕኮውን አፅንዖት ሰጥቷል።

ዳግመኛው፡- “...አምላካችንም የሚበቀልበትን ቀን እናገር ዘንድ” ኢሳ. 61፥2
ይህ በዳግም ምጽአቱ ጊዜ ስላለው ፍርድ እና ተሃድሶ ይናገራል።

3. ሚክያስ 5፥2-4

የመጀመሪያው፡- “አንቺም ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ ...ከአንቺ ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል።” ሚክ. 5፥2
ይህ በቤተልሔም በኢየሱስ ልደት ተፈጸመ (ማቴ. 2፥1-6)።

ዳግመኛው፡- “እርሱም ይቆማል፥ በእግዚአብሔርም ኃይል በአምላኩ በእግዚአብሔር ስም ግርማ መንጋውን ይጠብቃል፤” ሚክ. 5፥4
ይህ የሚያመለክተው የወደፊት ግዛቱን እንደ የመጨረሻው እረኛ-ንጉሥ ነው።


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

03 Jan, 12:00


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል።”
ሉቃስ 1፥79



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

03 Jan, 11:22


ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች ጌታ ቢፈቅ በቅርቡ በጽሑፍ የምናቀርባቸውን ትምህርቶች በድምጽ፣ እንዲሁም መጻሕፍትንና ትርካዎችን በድምጽ ማቅረብ እንደምንጀምር እንገልጻለን።


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

03 Jan, 10:52


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“ከጥንት ጀምሮ በነበሩት በቅዱሳን ነቢያት አፍ እንደ ተናገረ፥ በብላቴናው በዳዊት ቤት የመዳን ቀንድን አስነስቶልናል፤”
              ሉቃስ 1፥69-70

"አንሥአ ለነ ቀርነ መድኀኒትነ እምቤተ ዳዊት ገብሩ። በከመ ነበበ በአፈ ነቢያቲሁ ቅዱሳን እለ እምዓለም።"
               ሉቃስ 1፥69-70

Inni mana garbicha isaa mana Daawit keessatti gaanfa fayyinaa nuuf kaaseera; akkuma afaan raajota isaa qulqulloota duriitiin dubbatetti
            Luqaas 1:69-70


"ከምቲ በቶም ካብ ጥንቲ ዝነበሩ ብኣፍ ቅዱሳት ነብያት እተዛረቦ፡ ኣብ ቤት ዳዊት ባርያኡ ቀርኒ ምድሓን ኣተንስኣልና፡"
                  ሉቃስ 1፥69-70




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

02 Jan, 18:38


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም በሥጋና በደም አልተካፈለምን?


                      ክፍል-፬
              (የመጨረሻ ክፍል)


በሌላ ጽንፍ፤ አንዳንድ ግለሰቦች “ከድንግል ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋና በደም ከተካፈለ አዳማዊ የውርስ ኃጢአት አለበት ማለት ነው?” ሲል ስጋታቸውን ይናገራሉ፡፡ ከሉቃስ ወንጌል የምንማረው ትምህርት ግን፥ ከዚህ ሥጋት የወጣ ሆኖ ነው የምናገኘው፥  

 “መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።” ሉቃ1፥35፡፡ 

ይህ ክፍል “ቃል ስጋ በሚሆንበት” ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ሥራ እንደነበረው የሚናገር ነው፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ምንድን ነው ብንል፥ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱሳችን የሚለውን “ይጸልልሻል” ቃል ይጠቁመናል፡፡ ይህ ቃል የግሪኩን “ኢፒሽኬዞ ἐπισκιάζω 1982 - episkiazó” የወከለ ሲሆን፤ የሁል ጊዜ ትርጓሜውም “መሸፈን፣ መከለል፣ መጠቅለል - overshadow, envelop” ማለት ነው (ይህ ቃል ጥቅም ላይ ከዋለባቸው ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ጋር ያነጻጽሩ ማቴ 17፥ 5፤ ሐዋ 5፥ 15)፡፡ ይህም ማለት መንፈስ ቅዱስ ከድንግል ማርያም ስጋና ደምን በመክፈል፣ በአባቶች በኩል ከሚመጣው አዳማዊ የውርስ ኃጢአት የመከለልና ያለ ወንድ ዘር ክርስቶስ ይወለድ ዘንድ ሥራን መስራቱን እንረዳለን፡፡ አንዳንድ ወገኖቻችን በዚህ “ይጸልልሻል” በሚለው ቃል ግር የሚሰኙ ካሉ፡- ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ላይ፤ “መጸለል” የሚለውን ቃል በአድራጊ ግስ ሲተረጎም “ማጥለል፣ ማጥራት፣ ጥሩ ማድረግ” ማለት እንደሆነ በገጽ 654 ላይ መመልከት ይችላሉ፡፡ ለዛም ነው መላዕኩ “ይጸልልሻል” ካላት በኃላ “ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።” በማለት ክርስቶስ ፍጹም ሰው ሆኖ ሲሆን፥ በውርስ ከሚተላለፈው አዳማዊ ኃጢአት ንጹህ ሆኖ ስለሚወለድ “ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ” ተብሎ ይጠራል ያላት፡፡

ተወዳጆች ሆይ፥ የሁላችን መድኃኒት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፥ በስጋና በደም መካፈሉንና በዚህች ምድር መገለጡን አለመቀበልና አለማመን፥ ከዲያብሎስ የሚመነጭ ትውልድ ገዳይ፥ መርዘኛ ኑፋቄ መሆኑን ቅዱስ ዮሐንስ በመልዕክቱ እንዲህ አስፍሮልናል፥

 “የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፥ ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥ አሁንም እንኳ በዓለም አለ።” 
1ዮሐ 4፥ 2-3፡፡

እንግዲህ ምን እንላለን? ቃል ሥጋ የሆነው ከድንግል በመወለድ እንጂ፥ አንዳንዶች እንደሚሉት ሰማያዊ ሥጋ ይዞ፥ ከድንግል ማህጸን በማደር አይደለም፡፡ ቃሉ የሚለን “ቃልም እግዚአብሔር ነበረ” እንጂ “ቃልም ሠማያዊ ሥጋ ይዞ ነበረ” አይለንም፡፡ እግዚአብሔር የነበረው ቃል ነው ከድንግል በመወለድ ሥጋ የሆነው ነው፡፡ ለዛም ነው ቅዱስ ዮሐንስ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ (ሰው ሆኖ) እንደመጣ አለማመን ከዲያብሎስ ነው በማለት አጽንኆት ሰጥቶ የጻፈልን፡፡ ይህ የክርስትናችን መሰረተ-እምነት ከመሆኑ ባሻገር ከዲያብሎስ የሆኑ አስተምህሮችን የምንለይበት የእምነታችን መመዘኛ ነው፡፡ ጌታችንም “እኔ የዳዊት ሥርና ዘር ነኝ” ሲል አንዳችስ እንኳ አልዋሸም፥ በርግጥም እርሱ የዳዊት ሥርና ዘር ነው፥ ስሙ ብሩክ ይሁን፥

“እኔ ኢየሱስ በአብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ይህን እንዲመሰክርላችሁ መልአኬን ላክሁ። እኔ የዳዊት ሥርና ዘር ነኝ፥ የሚያበራም የንጋት ኮከብ ነኝ።” ራዕይ 22፥ 16፡፡

የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።


ጥያቄ፣ አስተያየት፣ መከራከሪያ ነጥብ ያለው በግልጽ ያለፍርሃት መጽሐፍ ቅዱስን ማስረጃ በማድረግ ማቅረብ ይችላል።



ምንጭ፦ yebethknat.blogspot.com




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

02 Jan, 12:49


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በልቡ የታበየ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነው፥ እጅ በእጅም ሳይቀጣ አይቀርም።”
ምሳሌ 16፥5



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

02 Jan, 10:28


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ



“ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።”
             ዮሐንስ 1፥14


"ወውእቱ ቃል ሥጋ ኮነ ወኀደረ ላዕሌነ ወርኢነ ስብሐቲሁ ከመ ስብሐተ አሐዱ ዋሕድ ለአቡሁ ዘምሉእ ጸጋ ወጽድቀ ወሞገሰ።"
ዮሐንስ 1፥14


"Dubbiin foon taʼee nu gidduu jiraate. Nus ulfina isaa, ulfina Ilma Tokkicha ayyaanaa fi dhugaadhaan guutamee Abbaa biraa dhufe sanaa argineerra."
                Yohannis 1:14


"እቲ ቓል ስጋ ዀነ፡ ጸጋን ሓቅን መሊእዎ ኸኣ ኣባና ሐደረ። ክብረቱ ድማ ከም ክብሪ ናይቲ ሓደ ወዲ ነቦኡ ርኤና።"
ዮሐንስ 1፥14




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Jan, 21:49


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለማን እና ለምን ተወለደ?

1. ለሰው ልጆች ሁሉ

ኢየሱስ የተወለደው ሰዎችን ሁሉ ከኃጢአታቸው ለማዳን ነው። የእርሱ ልደት ​​የእግዚአብሔርን የሰው ልጆችን ለመቤዠት እና በእግዚአብሔር እና በሰው ልጆች መካከል ያለውን የተበላሸ ግንኙነት ለመመለስ እቅድ ዋነኛ አካል ነው።
👉ማቴዎስ 1፥21
👉ዮሐንስ 3፥16

2. ትንቢትን ለመፈጸም

የኢየሱስ መወለድ ስለ መሲሑ መምጣት የተነገሩትን የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች እንዲፈጸሙ ምክንያት ሆኗል።
👉ኢሳይያስ 7፥14
👉ማቴዎስ 1፥22-23

3. የእግዚአብሔርን ፍቅር ለማሳየት

የኢየሱስ ልደት እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን ታላቅ ፍቅር፣ ጸጋንና እርቅን ያሳያል።
👉ሮሜ 5፥8
👉ሉቃስ 2፥10-11

4. ሰላምና እርቅን ለማምጣት

ኢየሱስ የተወለደው በእግዚአብሔርና በሰው ልጆች መካከል እንዲሁም በሰዎች መካከል ሰላምን ለማምጣት ነው።
👉ሉቃስ 2፥14
👉ኤፌሶን 2፥14-16

5. የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመመስረት

ኢየሱስ የመጣው የእግዚአብሔርን መንግሥት በምድር ላይ ለማስተዋወቅ ነው።
👉ኢሳይያስ 9፥6-7




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Jan, 18:14


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም በሥጋና በደም አልተካፈለምን?


                      ክፍል-፫



ተዋዳጆች ሆይ፥ የዕብራውያኑ ጸሐፊ እንደጻፈልን ጌታችን ኢየሱስ ከድንግል ማርያም ሲወለድ፥ በሥጋና በደም በመካፈል የአብርሃምን ዘር መያዙን ያስተምረናል፡፡ በዚህ ክፍል ልብ የምንለው የአንድን አካል፣ የአንድን እንስሳ፣ የአንድን ፍጡር፣ እንዲሁም መላዕክትን ዘር መያዝ የሚቻለው “በየወገኑ ካለው አካል በመካፈል” ብቻና ብቻ መሆኑን ነው፡፡ ለዛም ነው ቃሉ “የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላዕክትን አይደለም” የሚለን፡፡ ይህም ማለት ክርስቶስ ከድንግል ማርያም በስጋና በደም ሳይካፈል የሰውን ዘር በመያዝ ሰው ሊባል አይችልም፡፡ ጌታችን ግን በርግጥም ከቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋና ደምን በመካፈል (በመንሳት) ፍጹም ሰው በመሆኑ በእግዚአብሔር ፊት እኛን ሊወክለን ችሏል፥

· “ሊቀ ካህናት ሁሉ ስለ ኃጢአት መባንና መስዋዕትን ሊያቀርብ ከሰው ተመርጦ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ ስለ ሰው ይሾማልና” ዕብ 5፥ 1፡፡

“በዚያም ኢየሱስ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ሊቀ ካህናት የሆነው፥ ስለ እኛ ቀዳሚ ሆኖ ገባ።” ዕብ 6፥ 20፡፡

በእነዚህ ሁለት ክፍሎች ሊቀ ካህናት ሰዎችን በእግዚአብሔር ፊት ወክለው፥ የመካከለኛነት አገልግሎትን የሚፈጽሙት “ከሰው መካከል በመመረጥና በመሾም” መሆኑን ያስረዱናል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋና በደም ያልተካፈለና የሰውንም ዘር ያልያዘ ቢሆን ኖሮ፥ እኛን በእግዚአብሔር ፊት ወክሎ “ሊቀ ካህናችን” ሆኖ ማገልገል ባልቻለ ነበር፡፡ ነገር ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ወደ ሰማያዊቷ ድንኳን ስለ እኛ ቀዳሚ” ሆኖ መግባቱን ቃሉ ይመሰክርልናል፡፡ ከያዘውም የሰው ዘርና ከለበሰውም ሥጋ የተነሳ፥ እንደእኛው የሚደክም፣ የሚራብ፣ የሚጠማ፣ የሚተኛ፣ የሚነሳ፣ የሚያለቅስ፣ የሚያዝን፣ የሚደሰት... በመሆኑ ድካማችንን ሁሉ ስለሚያውቅ ሊራራልን ችሏል፥   

“ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም።” ዕብ 4፥ 15፡፡

ተወዳጆች ሆይ፥ ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ከድንግል ማርያም በሥጋና በደም ሳይከፈል ቢቀርና የሰውን ዘር ባይዝ ኖሮ፥ ድካማችን ሊያውቅና ሊራራልን እንደማይችል ተረዳችሁን? ደግሞስ ሰው ያልሆነና ሥጋችን ያልተካፈለ በእግዚአብሔር ፊት ሊወክለን ከቶ እንደማይችል አወቃችሁን? አንዳንድ ግለሰቦች ከድንግል ማርያም በሥጋና በደም መካፈሉን ማመን “ድንግል ማርያምን እንደማምለክ” ስለሚቆጥሩት ያለምንም መደላድል፥ ይህን መሰረተ እምነት ሲክዱ እንመለከታለን፡፡ እንደ እውነቱ ግን ድንግል ማርያም “እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤” ስትል የተናገረችው፥ የሰማይና የምድር ሁሉ ፈጣሪ፥ ፍጥረታትን ደጋፊና አሳላፊ የሆነው እግዚአብሔር ወልድ፥ ሰው ሆኖ ይወለድ ዘንድ እርሷን በመምረጡ ምክንያት፥ መሆኑን መስክራለች፥ “ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጎአልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው።” (ሉቃ 1፥ 48-49)፡፡ ከዚህ በመነሳት ልዑል አምላካችን እግዚአብሔር ወልድ፥ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ከኃጢአት ባርነት እኛን ለማዳን፤ ከሞትና ከሲኦል ፍርሃት ሊያወጣን፤ የእግዚአብሔር ልጆች እንሆን ዘንድ፤ ሰው ሆኖ እኛን ለመወከል ከድንግል ማርያም በስጋና በደም ተካፈለ፡፡



ይቀጥላል. . .



ምንጭ፦ yebethknat.blogspot.com



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Jan, 13:27


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እንዳይውጠኝ ከረግረግ አውጣኝ፤ ከሚጠሉኝና ከጥልቅ ውኃ አስጥለኝ።”
መዝሙር 69፥14



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Jan, 09:38


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“ከእሴይ ግንድ በትር ይወጣል፥ ከሥሩም ቍጥቋጥ ያፈራል።”
          ኢሳይያስ 11፥1


"ወትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ፤ ወየዓርግ ፍሬ እምኔሃ።"
ኢሳይያስ 11፥1

"Lataan tokko jirma Isseey irraa ni lata;
hidda isaa irraas dameen tokko ija naqata."
Isaayyaas 11:1

"ካብቲ ኽሩት ጒንዲ እሰይ ከኣ ሓደ ጠጥዒ ኺጭብጭብ እዩ፡ ሓደ ጨንፈርውን ካብ ሱሩ ፍረ ኺፈሪ እዩ።"
ኢሳይያስ 11፥1



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

31 Dec, 20:25


የጎርጎሮሳውያንን የዘመን ቀመር የምትከተሉ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! መልካም አዲስ ዓመት!


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

29 Dec, 19:04


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


በግሪጎሪያን እና በጁሊያን የቀን መቁጠሪያ መካከል ያለው ዋና ልዩነት ከፀሃይ አመት ጋር ለመስማማት የዝል አመት (leap year) እንዴት እንደሚቆጥሩ (ምድርን በፀሐይ ለመዞር የሚፈጅበት ጊዜ) ላይ ነው። ማብራሪያው እነሆ፦
የልዩነቱ ምክንያቶች፡-

1. የዝል ዓመት ስሌት፡-

የጁሊያን የቀን መቁጠሪያ፡- በጁሊየስ ቄሳር በ45 ዓ.ዓ ያስተዋወቀው በየ 4 አመቱ የዝል አመትን ያለምንም ልዩነት ያካትታል። ይህ ማለት በዓመት በአማካይ 365.25 ቀናት አሉ።

የግሪጎሪያን የቀን አቆጣጠር፦ በ1582 በጳጳስ ግሪጎሪ 12ኛ የተዋወቀ የቀን መቁጠሪያ ስልት ነው። ይህ አቀጣጠር የዝል ዓመትን ህግ በተወሰነ ያስተካክላል። አንድ አመት በ 4 የሚካፈል የዝል አመት ነው፣ በ100 ከሚካፈሉ አመታት በስተቀር በ400 ካልተከፋፈሉ በስተቀር ይህ ማስተካከያ አመቱን በአማካይ 365.2425 ቀናት ያደርገዋል።

2. ከፀሐይ ዓመት ጋር መጣጣም፦

የፀሐይ ዓመት በግምት 365.2422 ቀናት ነው። የጁሊያን ካላንደር የ365.25 ቀናት ግምት ከፀሐይ ዓመት ጋር ሲነፃፀር በዓመት 11 ደቂቃ ያህል እንዲበልጥ አድርጎታል። ለብዙ መቶ ዘመናት፣ ይህ እንደ ፋሲካ ያሉ አስፈላጊ ክስተቶች ላይ ተጽዕኖ በማድረግ ከእኩይኖክስ ጋር አለመግባባት አስከትሏል።

የጎርጎርዮስ አቆጣጠር በተወሰኑ ክፍለ ዘመናት (ለምሳሌ 1700፣ 1800 እና 1900 በጎርጎርያን አቆጣጠር የዝል ዓመታት አልነበሩም) ይህንን አለመጣጣም አስተካክሏል።

3. መቀበል

የግሪጎሪያን ካላንደር በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ሀገራት ተቀባይነት አግኝቷል። የካቶሊክ አገሮች ወዲያውኑ ተቀብለውታል፣ የፕሮቴስታንት እና የኦርቶዶክስ አገሮች ግን በኋላ ተቀብለውታል (ለምሳሌ፣ ሩሲያ በ1918)።

የትኛው የቀን መቁጠሪያ ትክክል ነው?

የጎርጎርዮስ አቆጣጠር ከጁሊያን የቀን መቁጠሪያ የበለጠ ትክክለኛ ነው ምክንያቱም የዝል አመት ማስተካከያዎቹ ከፀሃይ አመት ጋር በተሻለ ሁኔታ እንዲጣጣሙ ስለሚያደርግ ነው። ዛሬ ጥቅም ላይ የዋለው ዓለም አቀፍ እውቅና ያለው የቀን መቁጠሪያም ነው።



ምንጭ፦ E. G. Richards, Mapping Time: The Calendar and Its History (Oxford University Press, 1999).
Encyclopaedia Britannica. "Gregorian Calendar." britannica.com
NASA Solar System Exploration: "The Length of a Year." nasa.gov




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

29 Dec, 13:21


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤”
1ኛ ተሰሎንቄ 5፥8



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

29 Dec, 10:35


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ



“እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤”
              ሉቃስ 1፥32


"ውእቱ ዐቢይ ወይሰመይ ወልደ እግዚአብሔር ልዑል ወይሁቦ እግዚአብሔር አምላክ መንበረ ዳዊት አቡሁ።"
               ሉቃስ 1፥32

Innis guddaa ni taʼa; Ilma Waaqa Waan Hundaa Olii jedhamees ni waamama. Waaqni Gooftaanis teessoo Abbaa isaa Daawit ni kennaaf;
                Luqaas 1:32


"ንሱ ዓብዪ ኪኸውን፡ ወዲ ልዑልውን ኪብሃል እዩ፡ እግዚኣብሄር ኣምላኽ ድማ ዝፋን ኣቦኡ ዳዊት ኪህቦ እዩ።"
               ሉቃስ 1፥32




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

29 Dec, 06:00


#እራሳችንን_እንመርምር



እንደ ክርስቲያን በመንፈሣዊ ሕይወት ከፍታዎች ላይ እየተረማመድን እና እየበረርን እንዳለን እንደሚሰማን ያክል በድካም የምንዳክርበት ጊዜም እንዳለ ልንክደው የማንችለው ሃቅ ነው። ታዲያ ለዚህ ድካማችን በማስመሰል እና በ"ሃሌሉያ" ከምንሸፋፍነው ይልቅ "ጌታ ሆይ አድነኝ!" ብለን ብንጮህ ምን ይመስላችኋል?


“ነገር ግን የነፋሱን ኃይል አይቶ ፈራ፥ ሊሰጥምም በጀመረ ጊዜ፦ ጌታ ሆይ፥ አድነኝ ብሎ ጮኸ።”
ማቴዎስ 14፥30



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

28 Dec, 19:00


👉ርዕስ፦ ትንቢተ ዳንኤል የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎስ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ.አይ.ኤም


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

28 Dec, 18:57


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

28 Dec, 13:27


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።”
1ኛ ጴጥሮስ 2፥5




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

28 Dec, 10:12


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ

“ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም ድረስ በፍርድና በጽድቅ ያጸናውና ይደግፈው ዘንድ በዳዊት ዙፋንና በመንግሥቱ ላይ አለቅነቱ ይበዛል፥ ለሰላሙም ፍፃሜ የለውም። የእግዚአብሔር ቅንዓት ይህን ያደርጋል።”
                  ኢሳይያስ 9፥7


"ወዕበይ ቅድሜሁ ወአልቦ ማኅለቅተ ለሰላሙ ዲበ መንበረ ዳዊት ትጸንዕ መንግሥቱ፤ ወይትዌከፍ በጽድቅ ወበርትዕ እምይእዜ ወእስከ ለዓለም፤ ቅንአተ እግዚአብሔር ፀባኦት ይገብር ከመዝ።"
ኢሳይያስ 9፥7

Babalʼinni mootummaa isaatii fi
nagaan isaa dhuma hin qabu.
Innis murtii qajeelaa fi qajeelummaadhaan
hundeessee jabeessee dhaabuudhaan
yeroo sanaa jalqabee bara baraan
teessoo Daawit irra taaʼee mootummaa isaa bulcha.
Hinaaffaan Waaqayyoo Waan Hunda Dandaʼuus
waan kana ni raawwata.
Isaayyaas 9:7


"ብፍርድን ብጽድቅን ካብ ሕጂ ኽሳዕ ዘለኣለም ምእንቲ ኼጽንዓን ኬቚማንሲ፡ ኣብ ዝፋን ዳዊትን ኣብ መንግስቱን ዕቤት ግዝኣቱን ሰላሙን መወዳእታ የብሉን። ቅንኣት እግዚኣብሄር ጐይታ ሰራዊት ነዚ ኺገብር እዩ።"
ኢሳይያስ 9፥7




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

28 Dec, 00:05


#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?



ኢሳይያስ 59
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እነሆ፥ የእግዚአብሔር እጅ ከማዳን አላጠረችም፥ ጆሮውም ከመስማት አልደነቈረችም፤
² ነገር ግን በደላችሁ በእናንተና በአምላካችሁ መካከል ለይታለች፥ እንዳይሰማም ኃጢአታችሁ ፊቱን ከእናንተ ሰውሮታል።
³ እጃችሁ በደም ጣታችሁም በበደል ረክሳለች፥ ከንፈራችሁም ሐሰትን ተናግሮአል፥ ምላሳችሁም ኃጢአትን አሰምቶአል።
⁴ በጽድቅ የሚጠራ በእውነትም የሚፈርድ የለም፤ በምናምንቴ ነገር ታምነዋል ሐሰትንም ተናግረዋል፤ ጕዳትን ፀንሰዋል በደልንም ወልደዋል።
⁵ የእባብን እንቍላል ቀፈቀፉ፥ የሸረሪትንም ድር አደሩ፤ እንቍላላቸውንም የሚበላ ሰው ይሞታል፥ እንቍላሉም ሲሰበር እፉኝት ይወጣል።
⁶ ድሮቻቸውም ልብስ አይሆኑላቸውም፥ በሥራቸውም አይሸፈኑም፤ ሥራቸውም የበደል ሥራ ነው፥ የግፍም ሥራ በእጃቸው ነው።
⁷ እግሮቻቸው ወደ ክፋት ይሮጣሉ፥ ንጹሑን ደም ለማፍሰስ ይፈጥናሉ፤ አሳባቸው የኃጢአት አሳብ ነው፥ ጕስቍልናና ቅጥቃጤ በመንገዳቸው አለ።
⁸ የሰላምን መንገድ አያውቁም፥ በአካሄዳቸውም ፍርድ የለም፤ መንገዳቸውን አጣምመዋል፥ የሚሄድባትም ሁሉ ሰላምን አያውቅም።
⁹ ስለዚህ ፍርድ ከእኛ ዘንድ ርቆአል፥ ጽድቅም አላገኘንም፤ ብርሃንን በተስፋ እንጠባበቅ ነበር፥ እነሆም፥ ጨለማ ሆነ፤ ጸዳልን በተስፋ እንጠባበቅ ነበር፥ ነገር ግን በጨለማ ሄድን።
¹⁰ እንደ ዕውሮች ወደ ቅጥሩ ተርመሰመስን፥ ዓይን እንደሌላቸው ተርመሰመስን፤ በቀትር ጊዜ በድግዝግዝታ እንዳለ ሰው ተሰናከልን፥ እንደ ሙታን በጨለማ ስፍራ ነን።
¹¹ ሁላችን እንደ ድቦች እንጮኻለን፥ እንደ ርግብ እንለቃቀሳለን፤ ፍርድን በተስፋ እንጠባበቅ ነበር እርሱም የለም፤ መዳንም ከእኛ ዘንድ ርቆአል።
¹² ዓመፃችን በአንተ ፊት በዝቶአልና፥ ኃጢአታችን መስክሮብናልና፥ ዓመፃችን ከእኛ ጋር ነውና፥ በደላችንን እናውቃለንና።
¹³ ዐምፀናል፥ ሐሰትን ተናግረናል፥ አምላካችንንም ከመከተል ተመልሰናል ግፍንና ዓመፅንም ተናግረናል፥ የኃጢአት ቃልንም ፀንሰን ከልብ አውጥተናል።
¹⁴ ፍርድም ወደ ኋላ ተመልሶአል፥ ጽድቅም በሩቅ ቆሞአል፤ እውነትም በአደባባይ ላይ ወድቆአልና፥ ቅንነትም ሊገባ አልቻለምና።
¹⁵ እውነትም ታጥቶአል፥ ከክፋትም የራቀ ሰው ለብዝበዛ ሆኖአል። እግዚአብሔርም አየ ፍርድም ስለሌለ ተከፋ።
¹⁶ ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው።
¹⁷ ጽድቅንም እንደ ጥሩር ለበሰ፥ በራሱም ላይ የማዳንን ራስ ቍር አደረገ፤ የበቀልንም ልብስ ለበሰ፥ በቅንዓትም መጐናጸፊያ ተጐናጸፈ።
¹⁸ እንደ ሥራቸው መጠን እንዲሁ ቍጣን ለባላጋራዎቹ፥ ፍዳንም ለጠላቶቹ ይከፍላል፤ ለደሴቶችም ፍዳቸውን ይከፍላል።
¹⁹ እርሱ የእግዚአብሔር ነፋስ እንደሚነዳው እንደ ጐርፍ ፈሳሽ ይመጣልና በምዕራብ ያሉት የእግዚአብሔርን ስም፥ በፀሐይ መውጫም ያሉት ክብሩን ይፈራሉ።
²⁰ ለጽዮን ታዳጊ ይመጣል፥ በያዕቆብም ዘንድ ከኃጢአት ለሚርቁ፥ ይላል እግዚአብሔር።
²¹ ከእነርሱ ጋር ያለው ቃል ኪዳኔ ይህ ነው ይላል እግዚአብሔር፤ በአንተ ላይ ያለው መንፈሴ በአፍህም ውስጥ ያደረግሁት ቃሌ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም ድረስ ከአፍህ ከዘርህም አፍ ከዘር ዘርህም አፍ አያልፍም፥ ይላል እግዚአብሔር።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

27 Dec, 14:26


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“የተዋረዱትን ወደ ላይ ያወጣል፥ ኀዘንተኞችንም ለደኅንነት ከፍ ከፍ ያደርጋቸዋል።”
ኢዮብ 5፥11



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

27 Dec, 10:50


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና።”
            ዮሐንስ 3፥17


"እስመ ኢፈነዎ እግዚአብሔር ለወልዱ ውስተ ዓለም ከመ ይኰንኖ ለዓለም ዘእንበለ ከመ ያሕይዎ ለዓለም በእንቲኣሁ።"
ዮሐንስ 3፥17


"Waaqni karaa isaatiin addunyaa fayyisuudhaaf malee addunyaatti muruuf Ilma isaa gara addunyaatti hin ergineetii."
Yohannis 3:17


"ኣምላኽ ንወዱ፡ ዓለም ብእኡ ኽትድሕን እምበር፡ ንዓለም ኪፈርዳስ ኣይለኣኾን።"
ዮሐንስ 3፥17





ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

26 Dec, 18:06


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


የሕግ መጻሕፍት ስለኢየሱስ ምን ይላሉ?



4. የፋሲካው በግ (ዘጸአት 12፥1-30)

እስራኤላውያን በግብፅ ላይ ከደረሰው የመጨረሻ መቅሰፍት ለመዳን የበግ ጠቦትን እንዲሠዉና ደሙንም በበራቸው መቃን ላይ እንዲቀቡ መመሪያ ተሰጥቷቸዋል።

የፋሲካው በግ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፤ “የእግዚአብሔር በግ” (ዮሐ. 1፥29)፣ ደሙ አማኞችን ከመንፈሳዊ ሞት ያድናል።

5. ከሰማይ የወረደው መና (ዘጸአት 16፥4-35)

እግዚአብሔር አምላክ እስራኤላውያንን በምድረ በዳ በሕይወት የሚያቆያቸውን መና ሰጣቸው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን እንደ “ከሰማይ የወረደው እውነተኛ እንጀራ” (ዮሐንስ 6፥32–35)፣ መንፈሳዊ ስንቅ እና የዘላለም ሕይወት እንደሆነ ገልጿል።

6. የናሱ እባብ (ዘኍልቍ 21፥4–9)

እግዚአብሔር ሙሴን የናስ እባብ ሠርቶ በእንጨት ላይ እንዲሰቅለው አዘዘው። የናሱን እባብ የተመለከቱትም ከገዳዩ እባብ ንክሻ ተፈወሱ።

ኢየሱስ በዮሐንስ 3፥14-15 ራሱን ​​ከናሱ እባብ ጋር አነጻጽሮታል፣ ይህም በእምነት ወደ እርሱ የሚያይቱን ይድናል።

7. እንደ ሙሴ ያለ ነቢይ (ዘዳ 18፥15-19)

“አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ከገዛ ወንድሞችህ መካከል እንደ እኔ ያለ ነቢይ ያስነሣልሃል፤ እርሱን አድምጥ።”
          ዘዳግም 18፥15 (አዲሱ መ.ት)

ይህ ትንቢት በአዲስ ኪዳን እንደተረጋገጠው በኢየሱስ ላይ ተፈጽሟል (ሐዋ. 3፥22-23)። ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የገለጠ የመጨረሻው ነቢይ ነው።

8. የኃጢአት ስርየት ሥርዓት (ዘሌዋውያን 16)

የስርየት ቀን መስዋዕቶችን እና የሰዎችን ኃጢአት ለማስተስረይ የእንስሳት ደም ስርዓትን ያካትታል።

እነዚህ የአምልኮ ሥርዓቶች በዕብራውያን 9፥11-14 እንደተገለጸው የኢየሱስን የኃጢአት ስርየት መሥዋዕት ያመለክታሉ።

9. ማደሪያው ድንኳን እና መስዋዕት

የማደሪያው ድንኳን፣ ዕቃዎቹ፣ እና የመሥዋዕቱ ሥርዓት በዘፀአት እና በዘሌዋውያን ውስጥ የእግዚአብሔርን መገኘት እና የስርየት አስፈላጊነት ያመለክታሉ።

ኢየሱስ እነዚህን ምልክቶች እንደ ዋና ሊቀ ካህናት (ዕብራውያን 4፥14-16) እና ለኃጢአት ፍጹም መስዋዕት ሆኖ ፈጽሟል (ዕብ 10፥10)።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

26 Dec, 13:22


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እኔ ግን በምስጋና ቃል እሠዋልሃለሁ፤ የተሳልሁትንም እከፍላለሁ። ደኅንነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።”
ዮናስ 2፥10



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

26 Dec, 10:24


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።”
              ሉቃስ 1፥35


ወአውሥአ መልአክ ወይቤላ፦ “መንፈሰ እግዚአብሔር ቅዱስ ይመጽእ ላዕሌኪ ወኀይለ ልዑል ይጼልለኪ ወዘኒ ይትወለድ እምኔኪ ቅዱስ ውእቱ ወይሰመይ ወልደ እግዚአብሔር ልዑል።
ሉቃስ 1፥35

Ergamaan sunis akkana jedhee deebiseef; “Hafuurri Qulqulluun sirra buʼa; humni Waaqa Waan Hundaa Oliis si golbooba. Kanaaf inni qulqulluun dhalatu sun Ilma Waaqaa ni jedhama.”
Luqaas 1:35


እቲ መልኣኽ ከኣ መሊሱ፡ መንፈስ ቅዱስ ኪወርደኪ ሓይሊ ልዑልውን ኬጽልለኪ እዩ። ስለዚኸኣ እቲ ዚውለድ ቅዱስ፡ ወዲ ኣምላኽ ኪብሃል እዩ።
ሉቃስ 1፥35




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

25 Dec, 19:25


ለምን የጌታችን ልደት በተለያየ ቀን ይከበራል?


በክርስቲያናዊ ቤተ እምነቶች መካከል ባለው የቀን መቁጠሪያ ስርዓት እና ወግ ልዩነት ምክንያት የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በተለያዩ ቀናቶች ማለትም እ.ኤ.አ ዲሴምበር 25 እና ጃንዋሪ 7 (ታህሳስ 28/29) ይከበራል።

ዲሴምበር 25

የሮማ ካቶሊክ እና የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮችን ጨምሮ አብዛኞቹ የምዕራባውያን አብያተ ክርስቲያናት እንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር ዲሴምበር 25 የገናን በዓል ያከብራሉ። ይህ ቀን ለበዓልነት የተወሰነው በክርስትና የመጀመሪያዎቹ ክፍለ ዘመናት ውስጥ ነው፤ ምናልባትም በየክረምቱ አካባቢ ከሚከበሩ አረማዊ በዓላት ጋር ሰው ወደ ክርስትና ሲመጣ እንዳይቸገር ለማስማማት ወይም ለመተካት ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። የዲሴምበር 25 የቀን ምርጫ በመጀመሪያ የተጠቀሰው በአራተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ በሮም አልማናክ ውስጥ ነው።

ጃንዋሪ 7

እንደ ሩሲያ፣ ጆርጂያ እና ሰርቢያ ያሉ ብዙ የምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት እና የኢትዮጵያና የኤርትራ አብያተ ክርስቲያናት ገናን ጃንዋሪ 7 ያከብራሉ። በአሁኑ ጊዜ፣ በጁሊያን እና በጎርጎርዮስ አቆጣጠር መካከል የ13 ቀናት ልዩነት አለ፣ ይህም ገናን በጁሊያን ዲሴምበር 25 በጎርጎሪያን ጃንዋሪ 7 ጋር እንዲሆን አድርጎታል።

የዘመን አቆጣጠር ልዩነት

እ.ኤ.አ 1582 ጳጳስ ጎርጎርዮስ 12ኛ ያስተዋወቀው የጎርጎርዮስ አቆጣጠር፣ በጁሊያን አቆጣጠር ከፀሐይ ዓመት ጋር በተሻለ ሁኔታ እንዲጣጣም በጁሊያን አቆጣጠር ውስጥ የተስተዋሉ ስህተቶችን አስተካክሏል። ብዙ አገሮች እና አብያተ ክርስቲያናት የጎርጎሪያንን የቀን አቆጣጠር ሲከተሉ፣ በርካታ የምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት የጁሊያን የቀን መቁጠሪያን ለሃይማኖታዊ በዓላት ይጠቀማሉ። ይህም አሁን የምንመለከተውን የሚመስል የቀናት ልዩነትን አስከትሏል።

በቀጣይ የጎርጎርዮሳዊን እና የጁሊያን የዘመን አቆጣጠር ዋና ዋና ልዩነቶችን እንመለከታለን


ይቀጥላል...



ምንጭ፦ www.biblicalarchaeology.org


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

25 Dec, 16:43


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አምላክህ እግዚአብሔር መሐሪ አምላክ ነውና አይተውህም፥ አያጠፋህምም፥ ለአባቶችህም የማለላቸውን ቃል ኪዳኑን አይረሳም።”
ዘዳግም 4፥31



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

25 Dec, 14:12


የጊዜ ቀመራችሁ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ለሆነ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለጌታችን እና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
🎄መልካም በዓል🎄

ከዚህ ጋር በተያያዘ የጌታችን ልደት ለምን ሁለት የተለያዩ ቀናት እንደሚከበር (December 25 እና January 7) ከአፍታ ቆይታ በኋላ እንመለስበታለን።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

25 Dec, 13:59


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።”
             ኢሳይያስ 7፥14

"ናሁኬ በእንተ ዝንቱ ይሁበክሙ እግዚአብሔር ትእምርተ፤ ናሁ ድንግል ትፀንስ፡ ወትወልድ ወልደ፡ ወትሰምዮ ስሞ፦ አማኑኤል።"
ኢሳይያስ 7፥14

"Kanaafuu Gooftaan mataan isaa mallattoo isiniif kenna: Kunoo durbi tokko ni ulfoofti; ilma ni deessi; Amaanuʼel jettees isa moggaafti."
Isaayyaas 7:14

"ስለዚ እግዚኣብሄር ባዕሉ ትእምርቲ ኺህበኩም እዩ፡ እንሆ፡ ድንግል ክትጠንስ፡ ወዲ ኸኣ ክትወልድ እያ፡ ስሙውን ኣማኑኤል ክትሰምዮ እያ።"
ኢሳይያስ 7፥14




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

24 Dec, 10:35


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ነገር ግን ለዚህ ዓለም ከሚመችና የአሮጊቶችን ሴቶች ጨዋታ ከሚመስለው ተረት ራቅ። እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ።”
1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥7



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

24 Dec, 07:57


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“እነሆ፥ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል፤ እናንተም የምትፈልጉት ጌታ በድንገት ወደ መቅደሱ ይመጣል፤ የምትወዱትም የቃል ኪዳን መልእክተኛ፥ እነሆ፥ ይመጣል፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።”
             ሚልክያስ 3፥1


"ናሁ አነ እፌኑ መልእክየ ዘይጸይሕ ወይርኢ ፍኖትየ ቅድመ ገጽከ፡ ወይመጽእ ውስተ ጽርሑ ግብተ እግዚአብሔር ዘአንትሙ ተኀሥሡ መልአከ ሥርዓትየ ዘአንትሙ ትፈቅዱ፤ ናሁ ይመጽእ፡ ይቤ እግዚአብሔር ዘኵሎ ይመልክ።"
                 ሚልክያስ 3፥1

“Kunoo ani ergamaa koo isa fuula koo duraan karaa naaf qopheessu nan erga. Ergasii Gooftaan isin eeggattan akkuma tasaa gara mana qulqullummaa isaa ni dhufa; ergamaan kakuu kan isin hawwitan sun ni dhufa” jedha Waaqayyo Waan Hunda Dandaʼu.
                 Miilkiyaas 3:1

"እንሆ፣ ኣነ ልኡኸይ እልእኽ ኣሎኹ፣ ንሱ ቐቅድመይ መገዲ ኺጸርግ እዩ። ብኡብኡ ኸኣ እቲ እትደልይዎ ጐይታ ናብ መቕደሱ ኺመጽእ እዩ፣ እቲ እትናፍቕዎ መልኣኽ ቃል ኪዳን እንሆ፣ ይመጽእ ኣሎ፣ ይብል እግዚኣብሄር ጐይታ ሰራዊት።"
              ሚልክያስ 3፥1



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

24 Dec, 06:05


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


የሕግ መጻሕፍት ስለኢየሱስ ምን ይላሉ?



ከቅዱሳት መጻሕፍት መካከል የመጀመሪያዎቹ አምስቱ  መጻሕፍት (ዘፍጥረት፣ ዘጸአት፣ ዘሌዋውያን፣ ዘኍልቍ እና ዘዳግም) ፔንታቱክ በመባል ይታወቃሉ። መጻሕፍቱ ጌታችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በስም አይጠቅሱም ሆኖም፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ለማመልከት በክርስቲያናዊ ሥነ-መለኮት ዘርፍ ውስጥ በቀላሉ ልንገነዘባቸው የምንችላቸው በርካታ ትንቢቶችን እና ምሳሌዎችን ይዘዋል። ከዚህ በታች መጻሕፍቱ ካነሷቸው አሳቦች መካከል ዋና ዋናዎቹን እነሆ፦

1. የሴቲቱ ዘር (ዘፍ 3፥15)

“በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።”
       ዘፍጥረት 3፥15

ይህ ክፍል የመጀመሪያው ወንጌል በመባል ይታወቃል፣ ይህ ቁጥር ኢየሱስ በሰይጣን ላይ ስላደረገው ድል ጥላ እንደሆነ ተመላክቷል። “የሴቲቱ ዘር” የሚያመለክተው ክርስቶስን ነው፣ እርሱም በመጨረሻ ክፋትን የሚያሸንፍ ነው።

2. ከአብርሃም ጋር የገባው ቃል ኪዳን (ዘፍ 12፥3፣ 22፥18

“... የምድር ነገዶችም ሁሉ በአንተ ይባረካሉ።” ዘፍጥረት 12፥3

“የምድር አሕዛብ ሁሉም በዘርህ ይባረካሉ፥”
   ዘፍጥረት 22፥18

የአብርሃም ዘር አሕዛብን ሁሉ እንደሚባርክ የተነገረው ተስፋ በኢየሱስ ተፈጽሟል፣ አዲስ ኪዳን (ገላትያ 3፡16) ኢየሱስን የተስፋው ዘር እንደሆነ ይገልጻል።

3. የይስሐቅ መስዋዕት (ዘፍ 22፥1-14)

አብርሃም ልጁን ይስሐቅን እንዲሠዋ ታዝዟል። እግዚአብሔር ግን ምትክ አውራ በግ አዘጋጀ።
ይህ ክስተት ኢየሱስን የኃጢአተኞችን ቦታ የሚወስድ የመሥዋዕቱ በግ እንደሆነ ያሳያል። ይስሐቅ ለመሥዋዕትነት የሚቀርበውን እንጨት ተሸክሞ መስቀሉን ከተሸከመው ኢየሱስ ጋር ሲመሳሰል ይታያል።


ይቀጥላል...



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

23 Dec, 21:15


👉ርዕስ፦ የገላትያና የያዕቆብ መልእክት፣
የጥናት መምሪያና ማብራሪያ
ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎስ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

23 Dec, 21:10


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

23 Dec, 13:58


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ካህኑ የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔር መልእክተኛ ነውና ከንፈሮቹ እውቀትን ይጠብቁ ዘንድ ይገባቸዋል፥ ሰዎችም ሕግን ከአፉ ይፈልጉ ዘንድ ይገባቸዋል።”
ሚልክያስ 2፥7




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

23 Dec, 10:05


#ቃልም_ሥጋ_ሆነ


“አየዋለሁ፥ አሁን ግን አይደለም፤ እመለከተዋለሁ፥ በቅርብ ግን አይደለም፤ ከያዕቆብ ኮከብ ይወጣል፥ ከእስራኤል በትር ይነሣል፥ የሞዓብንም ማዕዘኖች ይመታል፥ የሤትንም ልጆች ያጠፋል።”
                ዘኍልቁ 24፥17


"እሬእዮ ወአኮ ይእዜ፡
ወአስተበፅዖ ወአኮ ዘይቀርብ፡
ይሠርቅ ኮከብ እምያዕቆብ፡
ወይትነሣእ እምእስራኤል፡
ወያጠፍኦሙ ለመላእክተ ሞአብ፡
ወይጼውዎሙ ለኵሉ ደቂቀ ሴት።"
            ዘኍልቁ 24፥17


"Ani isa nan arga; garuu amma miti;
ani isa nan ilaala; garuu dhiʼootti miti.
Yaaqoob keessaa urjiin tokko ni baʼa;
Israaʼel keessaa bokkuun tokko ol kaʼa.
Inni adda warra Moʼaab,
buqqee mataa ilmaan Seet hundaas ni caccabsa."
                 Lakkoobsa 24:17


"እርእዮ ኣሎኹ፡ ሕጂ ደኣ ኣይኰነን፡
እጥምቶ ኣሎኹ፡ ግናኸ ቀረባ ኣይኰነን፡
ካብ ያእቆብ ኰዀብ ይወጽእ፡
ካብ እስራኤል ከኣ በትሪ መንግስቲ ትትንስእ፡
ንሳ ንመሳፍንቲ ሞኣብ ትወቕዖም፡
ንዅሎም ደቂ መዕገርገርቲ ትጭፍልቖም።"
               ዘኍልቁ 24፥17




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

22 Dec, 17:06


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ሌሎቹ ደግሞ እንዲፈሩ፥ ኃጢአት የሚሰሩትን በሁሉ ፊት ገሥጻቸው።”
1ኛ ጢሞቴዎስ 5፥20



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

30 Nov, 09:53


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ።”
ይሁዳ 1፥21



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

29 Nov, 20:50


የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት


6. ምሳሌዎች እና ታሪኮች

ሉቃስ በሌሎች ወንጌሎች ውስጥ የማይገኙ በርካታ ምሳሌዎችን ያካትታል፣ ብዙ ጊዜ በጸጋ እና በርኅራኄ ላይ ያተኩራል።

ምሳሌዎች፡-አባካኙ ልጅ (ሉቃስ 15፥11–32)። ባለጠጋው እና አልዓዛር (ሉቃስ 16፥19–31)።

7. የሕክምና ቃላት

እንደ ሃኪም (ቆላስይስ 4፥14) ሉቃስ አልፎ አልፎ የህክምና ቃላትን እና ስለ በሽታዎች እና ፈውሶች ትክክለኛ መግለጫዎችን ይጠቀማል።

ምሳሌ፡- ሆዱ የተነፋ ሰው መፈወስ ሲገልጽ (ሉቃስ 14፥2) ሉቃስ የተለየ የሕክምና ቃል ተጠቅሟል።

8. የዘመን ቅደም ተከተል እና ጭብጥ ማደራጀት

ሃኪሙ ሉቃስ ትረካውን በጊዜ ቅደም ተከተል እና በጭብጥ አዋቅሮታል። ብዙውን ጊዜ የጌታችን እና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሕይወት ክስተቶች ከሰፋፊ ሥነ-መለኮታዊ ጭብጦች ጋር ያገናኛል።

ምሳሌ፡- በሉቃስ-ሐዋርያት ውስጥ ያለው ሥርዓት ያለው ቅደም ተከተል የኢየሱስን ሕይወት ከጥንቷ ቤተ ክርስቲያን እድገት ጋር ያገናኛል (ሐዋ. 1፥1-2)።

9. የመዝሙር እና የግጥም ውህደት

ሉቃስ በብዛት ዝማሬዎችን እና የቅኔ ምንባባትን አካቷል። የማርያም ውዳሴ፣ ዘካርያስ አድናቆት፣ የመላእክት ክብር እና የስምዖን ቅኔያዊ ምንባቦችን ያካትታል።

ምሳሌዎች፡- (ሉቃስ 1፥46-55)። (ሉቃስ 2፥29–32)።


ይቀጥላል...



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

29 Nov, 18:36


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በአምላክህም በእግዚአብሔር ፊት እንዲህ ብለህ ተናገር፦ አባቴ የተቅበዘበዘ ሶርያዊ ነበረ፤ በቍጥር ጥቂት ሳለ ወደ ግብፅ ወረደ በዚያም ተቀመጠ፤ ታላቅ የሆነ የበረታም ቍጥሩም የበዛ ሕዝብ ሆነ።”
ዘዳግም 26፥5



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

28 Nov, 17:32


እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት
                
         


የጠለቀ መንፈሳዊ ጉዞ ለመጓዝና እየጨመረ የሚሄድ ርካታና እረፍት እንድናይ ካስፈለገ፣የክርስትና ሕይወት ትጋትን ይጠይቀናል(ዕብ 4:11)፡፡ በተለያየ ቦታ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃሉ እንደሚያስተምረን ትጋታችን እየጨመረ ሲሄድ፣ የእግዚአብሔር ጸጋም በሕይወታችን እየጨመረ ይሄዳል፡፡ እናም ለመንፈሳዊ ነገር ያለን መሻት እያደገ ይሄዳል፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ግሥገሣ ውስጥ ባለማሰለስ ስንገኝ፣ እሱን ለማወቅ ያለን ራብ እየተቀጣጠለ ስለሚመጣ፣እየጨመረ ለሚሄድ ፍለጋ እንጠናከራለን፡፡ ይህንን በእንግሊዝኛው አገላለጽ positive vicious cycle ይሉታል፡፡ ማለትም ትጋቱ የጨመረ መንፈሳዊ ራብን ይወልዳል፤ የጨመረው መንፈሳዊ ራብ ደግሞ ሌላ ከፍ ያለ ትጋትንና ግሥገሣን ይወልዳል፡፡ መቼም ይሄ ኡደት ማቆሚያ የለውም እኛ በሥጋዊ አካሄዶች እስካላጠፋነው ድረስ!

በነገራችን ላይ እየጨመረ የሚሄድ የክርስትና ሕይወት ብዙ ግብዓቶችን ይፈልጋል ፡፡ መልካም የእምነት ውጊያንና ዲያቢሎስን በኃይል ጸንቶ መቃወም ይጠይቃል ፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል ሳይታክቱ ማሰላሰልና በፊቱ ጥሩ የሆኑ ጊዜዎችን ማሳለፍ ግድ ይለናል ፡፡ ሁኔታዎችንና ሥጋችንን ሳናዳምጥ የሚከፈሉ ዋጋዎችን እንደ ጌታ ፈቃድ መክፈልን ይጠይቀናል፡፡

ሦስት በተሰናሰለ መንገድ የተቀመጡ ድርጊቶች በውጤት ሂደት እንዲህ ተቀምጠዋል፡-

ድርጊት(Action)-->ልማድ(Habit)-->ጠባይ(character)

ይህንን መርሕ ለመግለጽ ጸሎትን እንደ ምሳሌ ልውሰድ ፡፡ ጸሎትን ደጋግመን ስናደርገው ወደ ልማድነት ይቀየራል ፡፡ በሕይወታችን ልማድ እየሆነ የመጣውን ተግባር እየጨመርን ደጋግመን ስናደርገው፣ ጠባያችን ወይም መገለጫ ባሕርያችን ይሆናል ፡፡ ከዚያማ ውጤቱ እንዲህ ይሆናል፡-

“መጸለይ እንጂ አለመጸለይ አንችልም፡፡”
“በፊቱ መሆን እንጂ አለመሆን ያቅተናል፡፡”
እጅግ ሊጓጓለት የሚገባ ድንቅ ለውጥ!

የላይኛውን ሐሳብ የሚደግፉና የክርስትና ሕይወት እየተቀጣጠለ፣ እያደገና እየጨመረ የሚሄድ ሕይወት እንደ ሆነ የሚጠቁሙ ብዙ ክፍሎች አሉ ፡፡ ለምሳሌ ሦስቱን ልጥቀስ፡-

“እስከ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ” (ኤፌሶን 3፥19)

“በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ” (ሮሜ 12፥11)

“መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና” /ብዙ የሚያሰክሩ ነገሮች እንዳሉ ልብ ይሏል/(ኤፌሶን 5፥16-20)

ስሚዝ ዊግልስዎርዝ እንዲህ ብሎ ነበር፡-“If you are in the same place today as you were yesterday, you are a backslider.”(ትርጉሙ፡-በዛሬው ቀን ትላንትና የነበርክበት ቦታ ላይ ከተገኘህ የኋሊት እየሄድክ ነው)

በተሰጠ ማንነት፣ ልባችን መሉ በሙሉ በጌታ ላይ ሆኖ ከላይ በተጠቀሰው ዓይነት ፍለጋ(craving) እና ትጋት ስንቀጥል፣ የጌታ አብሮሆት ከመቸው በሚበልጥ ሁኔታ በሕይወታችን ዕውን ይሆናል ፡፡ ከዚህም የተነሣ የምናገኘው የመጀመሪያው በረከት በቃላት ልንገልጸው የማንችለው ሰላም፣ መረጋጋትና ደስታ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ መረዳታችንም እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ጌታን በሚገባ እያወቅነው እንመጣለን፡፡ስለዚህ ለውጣችን ወደ ኋላ የማይቀለበስና ዘላቂ ይሆናል ፡፡ መንፈሳዊ ዓይኖቻችን በጨመረ ሁኔታ እየተከፈቱ ስለሚመጡ፣ ብዙ ረብ የሌላቸውን ነገሮች የመጣል መነሣሣትና አቅም እያገኘን እንመጣለን ፡፡

እንደዚህ በጽናት ሳናሰልስ የጌታን ፊት በጨመረ ሁኔታ በፈለግን ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ኃይል በውስጣችን እየጨመረ ስለሚሄድ፣ ብዙ ቀንበሮች ከሕይወታችን ይሰበራሉ ፡፡ ስለዚህም “ሸክሙ ከጫንቃህ ቀንበሩም ከትከሻህ ላይ ይሰበራል” የሚለው ቃል በሕይወታችን ይፈጸማል (ኢሳ.10፡27)፡፡ እናም ከበፊቱ ይልቅ በሕልውናው ውስጥ መቆየት አያስቸግረንም፡፡ ቃሉ እንዲህ ይላልና፡-

“እርሱንም ሳታዩት ትወዱታላችሁ፤ አሁንም ምንም ባታዩት በእርሱ አምናችሁ የእምነታችሁን ፍጻሜ እርሱም የነፍሳችሁን መዳን እየተቀበላችሁ በማይነገርና ክብር በሞላበት ሐሤት ደስ ይላችኋል” (1 ጴጥሮስ 1፥8-9)

ለዚህ አሳብ ጥሩ እይታ የሚሰጠን ኢዮብ 28፥1-11 ነው ፡፡ ይህ የምንባብ ክፍል የማዕድን ሠራተኛ ከባዶ ተነሥቶ የሚያደርገውን ግሥገሣ ነው የሚያሳየው ፡፡ “ዓይኑ ዕንቁን እስክታይ ድረስ” ፣ “የተሸፈነው ነገር ወደ ብርሃን እስኪወጣ ድረስ” ይተጋል ፡፡ እጁን ወደ ቡላድ ድንጋይ ይዘረጋል ፡፡ መጨረሻ ላይ ከብዙ እልህ አስጨራሽ ትግልና ጉዞ በኋላ የከበሩ ማዕድናትን ያገኛል፤ክፍሉ የልፋቱን ውጤት እንዲህ ይገልጸዋልና ፡-

“ሰው ወደ ቡላድ ድንጋይ እጁን ይዘረጋል፤ ተራራውንም ከመሠረቱ ይገለብጣል። ከድንጋይ ውስጥ መንዶልዶያ ይወቅራል፤ ዓይኑምዕንቍን ሁሉ ታያለች።   ፈሳሹም እንዳይንጠባጠብ ይገድባል፤የተሰወረውንም ነገር ወደ ብርሃን ያወጣል።”(ቁ.9-11)

አዎ ይህ ክፍል ምሳሌያዊ በሆነ አገላለጽ፣ እንደ ማዕድን ሠራተኛው ያለ መታከት እንድንተጋና የጌታን ፊት እንድንፈልግ ያስተምረናል ፡፡

የእግዚአብሔር ቃል ተግተው “የሚሹኝ ምስጉኖች/የተባረኩ ናቸው” (ምሳሌ 8፡34) ይላልና፤ “እናንተም ትጠሩኛለችሁ፤ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፣እኔም እሰማችኋለሁ። እናንተ ትሹኛላችሁ፣በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ። ከእናንተም ዘንድ እገኛለሁ፡፡”(ኤር.29፥13-14) ይላልና ጨክኖ የጌታን ፊት የሚፈልግ ሰው ይዋል ይደር እንጂ፣ የእግዚአብሔር በረከት ታገኘዋለች፡፡

አዎ፣ ጌታ አጥብቀው ለሚሹት ሰዎች በእርግጥ ይገለጣል፡፡ የበለጠ እንድናየው፣ የበለጠ በእርሱ ላይ እንድንደገፍና እንድንጠጋው ያደርገናል፡፡ በተጨማሪም ጌታ ተገልጦ ሕይወታችንን ሲጎበኝ የሚመጣው ለውጥ ለሌሎች በረከት ያደርገናልና በትጋትና በጨመረ ሁኔታ ተግተን እንፈልገው!



ምንጭ:- ዶ/ር በቀለ በላቸው፤ ባለጸጋ ክርስትያን መጽሔት




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

28 Nov, 12:16


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በቸርነትህ የተቤዠሃቸውን ሕዝብህን መራህ፤ በኃይልህ ወደ ቅዱስ ማደሪያህ አገባሃቸው።”
ዘጸአት 15፥13



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

27 Nov, 20:52


#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት


#ጊብዓ

ጊብዓ፤ ጉብታ ወይም ኮረብታ ማለት ነው።
1. በይሁዳ የነበረ ከተማ።  ኢያሱ 15፥57።
2. ከኢየሩሳሌም ወደ ሰሜን አምስት ኪ.ሜ. ያህል ርቆ የሚገኝ የብንያም አገር ከተማ። የብንያም ጊብዓ በአሁን ጊዜ ከኢየሩሳሌም በስተሰሜን የምትገኝ ዘመናዊቷ ቴል ኤል ፉል ላይ እንደነበረች ይገመታል። የአርኪኦሎጂ ቁፋሮዎች የጥንት ምሽግ ቅሪቶችን በቁፋሮ አግኝተዋል፣ ይህም ግምቶችን እውነተኛ ሊሆኑ እንድሚችሉ አረጋግጧል።
የጊብዓ ሰዎች አስጸያፊ ብልግና ስላደረጉ እስራኤላውያን የብንያምን ወገን ለማጥፋት ተነሡ፤ ሆኖም 600 ሰዎች አምልጠዋል፤ መሳ. 19፥11-20፡48። ግን ንጉሥ ሳኦል የጊብዓ ሰው ነበረና መናገሻ ከተማውን በጊብዓ አደረገ፤ 1ሳሙ. 10፥26፤ 22፥6። በብሉይ ኪዳን ዘመን ጊብዓ ምሽግ ከተማ ነበረ፤ ከክርስቶስ ልደት ወዲህ ግን ባድማ ሆኗል።

ጊብዓ የምትታወቅባቸው ዋና ዋና የታሪክ ሁነቶች፦

👉የሌዋዊው ቁባት በጊብዓ ሰዎች በተፈጸመባት አሳቃቂ ግፍ የደረሰው ቁጣና ያስከተለው መዘዝ (መሳ. ምዕራፍ 19-21)

👉ጊብዓ የእስራኤል የመጀመሪያው ንጉሥ የንጉሥ ሳኦል የትውልድ ከተማ ነበረች። (1ኛ ሳሙኤል 10፥26፤ 1ሳሙ 15፥34-35)

👉የጊብዓ ትንቢታዊ ውግዘቶች፡- ነብያት ከጊዜ በኋላ ጊብዓን በመሳፍንት ውስጥ በተመዘገቡት ድርጊቶች ምክንያት የእስራኤል የሥነ ምግባር ውድቀት ምልክት እንደሆነች ጠቅሰዋል። (ሆሴዕ 9፥9፤ ሆሴዕ 10፥9።


ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 242




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

27 Nov, 12:50


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በእውነት ኤፍሬም ለእኔ የከበረ ልጅ ነውን? ወይስ የተወደደ ሕፃን ነውን? በእርሱ ላይ በተናገርሁ ቍጥር አስበዋለሁ፤ ስለዚህ አንጀቴ ታወከችለት ርኅራኄም እራራለታለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።”
ኤርምያስ 31፥20



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

27 Nov, 05:17


#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?


ኤርምያስ 23
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³³ ይህ ሕዝብ ወይም ነቢይ ወይም ካህን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ምንድር ነው? ብሎ ቢጠይቅህ፥ አንተ፦ ሸክሙ እናንተ ናችሁ፥ እጥላችሁማለህ፥ ይላል እግዚአብሔር ትላቸዋለህ።
³⁴ የእግዚአብሔር ሸክም የሚለውን ነቢይንና ካህንን ሕዝብንም ያን ሰውና ቤቱን እቀጣለሁ።
³⁵ አንዱም አንዱ ለባልንጀራው፥ አንዱም አንዱ ለወንድሙ እንዲህ ይበል፦ እግዚአብሔር የመለሰው ምንድር ነው? እግዚአብሔርስ ምን ነገር ተናገረ?
³⁶ ለሰው ሁሉ ቃሉ ሸክም ይሆንበታልና የእግዚአብሔር ሸክም ብላችሁ ከእንግዲህ ወዲህ አትጥሩ፤ የሠራዊትን ጌታ የአምላካችንን የእግዚአብሔርን የሕያውን አምላክ ቃል ለውጣችኋልና።
³⁷ ለነቢዩ፦ እግዚአብሔር ምን መለሰልህ? እግዚአብሔርስ የተናገረው ምንድር ነው? ትላለህ።
³⁸ ነገር ግን፦ የእግዚአብሔር ሸክም ብትሉ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ፦ የእግዚአብሔር ሸክም አትበሉ ብዬ ልኬባችኋለሁና፥ እናንተም ይህን ቃል፦
³⁹ የእግዚአብሔር ሸክም ብላችኋልና ስለዚህ፥ እነሆ፥ ፈጽሜ እረሳችኋለሁ እናንተንም ለእናንተና ለአባቶቻችሁም የሰጠኋትን ከተማ ከፊቴ እጥላለሁ።
⁴⁰ የዘላለምንም ስድብ ከቶም ተረስቶ የማይጠፋውን የዘላለምን እፍረት አመጣባችኋለሁ።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

26 Nov, 16:52


የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት


3. ዓለም አቀፋዊ ትኩረት

ሉቃስ የኢየሱስን ተልእኮ ዓለም አቀፋዊ እንደሆነ አጽንዖት ሰጥቷል፣ ይህም ለሁሉም ሰዎች ማለትም አሕዛብን፣ ሴቶችን፣ ድሆችን እና የተገለሉ ቡድኖችን ጨምሮ መቀላቀልን ያሳያል።

ምሳሌ፦ በሉቃስ ውስጥ ያለው የዘር ሐረግ የኢየሱስን የዘር ሐረግ ከአዳም ጀምሮ ያሳያል (ሉቃስ 3፥23-38)። ይህም ጌታችን እና መድኋኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው አይሁዳዊያንን ብቻ ሳይሆን የሰውን ዘር በሙሉ ለማዳን እንደመጣ ለማስገንዘብ ነው።

4. ለተገለሉ ቡድኖች ትኩረት መስጠት

ሉቃስ ስለሴቶች፣ ሳምራውያን፣ ቀራጮች እና ኃጢአተኞች ታሪኮችን በልዩ ሁኔታ አጉልቶ ያሳያል።
 
ምሳሌዎች፡- የደጉ ሳምራዊ ምሳሌ (ሉቃስ 10፥25–37)። ኃጢአተኛዋ ሴት ኢየሱስን ሽቶ ስለቀባችው ታሪክ (ሉቃስ 7፥36–50)።

5. በጸሎት እና በመንፈስ ቅዱስ ላይ ማተኮር 

ሉቃስ ጸሎትን እና የመንፈስ ቅዱስን ሥራ በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት እና በቀደመችው ቤተክርስቲያን ውስጥ በተደጋጋሚ ሁኔታ ትኩረት ሰጥቶ ያነሳዋል። 

ምሳሌ፡- የኢየሱስ ጸሎት (ሉቃስ 3፥21፣ 5፥16፣ 6፥12፣ 22፥39–46)። በጰንጠቆስጤ የመንፈስ ቅዱስ መውረድ (ሐዋ. 2፡1-4)።


ይቀጥላል...



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

26 Nov, 12:33


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ሰው ብፁዕ ነው።”
ሮሜ 4፥8




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

26 Nov, 03:47


👉ርዕስ፦ የሮሜ መልእክት የጥናት መምሪያ እና ማብራሪያ፣
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
ጸሐፊ፦ ስቲቭ ስትራውስ
🗣ትርጉም፦ ጌቱ ግዛው
✏️እርማት፦ ኃይሌ ጀናይና ግርማይ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ. አይ. ኤም


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

26 Nov, 03:47


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

25 Nov, 19:23


ነቢዩ ኤርምያስ




                        ክፍል-



መሲሓዊ ትንቢትን በተመለከተም ኤርምያስ መሲሓዊውን ጊዜ በዝርዝር አይገልጽም፡፡ የመሲሑ ማንነት በመጽሐፉ ላይ በጒልሕ አልተመለከተም፡፡ ይሁን እንጂ ኤርምያስ አንዳንድ ፋይዳ ያላቸውን መሲሓውያን ምንባቦች ይሰጣል ፡-

1. ከኪዳኑ ታቦት የላቀ የእግዚአብሔር መገለጥ እውን እንድሚሆን መታወጁ (3፥14-17)

2. የዐዲሱ ኪዳን መገለጥ (31፥31-34)

3. የዳዊት ኪዳን ፍጻሜ ላይ ከመድረሱ ጋር ተያይዞ (33 ፥ 14- 26) የሙሴ ውብ ሐሳብ እውን መሆን (ዘፀ 19፥6)፡፡

የትንቢተ ኤርምያስ ዘላቂ ፋይዳ የሚገኘው በዐዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉትን ይዘቶች (በአርባና በኀምሳ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፤ በዮሐንስ ራእይ ላይ ከግማሽ በላይ ይገኛሉ) ኢርቱዕ በሆነ መልክ በመግለጽ ብቻ ሳይሆን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ስላለው ግንኙነት ለማወቅ ድንቅ የሆነ መማሪያ መጽሐፍ በመሆኑ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከዚህ ላይ የግል እምነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ ይገኛል፤ እንዲሁም በዳዊት ሥርወ መንግሥት ውስጥ (23፥1-8፤ 33፥ 14-18) የካህንነትንና የንጉሥነትን ምንነት ለመረዳት እውነተኛ መንገድ በመሆኑ ነው፡፡ በምዕራፍ 30-33 ላይ ለሕዝቡ ብሩህ ተስፋዎች በብዛት መገኘታቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይህን ክፍል “የመጽናናት መጽሐፍ” እስከ ማለት አበቃቸው፡፡ በኤርምያስ ትንቢት ውስጥ በእጅጉ ዝነኛ የሆነው ምንባብ ስለ ዐዲሱ ኪዳን ይናገራል (31፥31-34):: ይህም የሚናገረው እስራኤል በቦታዋ ስለ መመለሷ እንጂ ስለ ግለ ሰባዊ ትንሣኤ አይደለም፡፡

ኤርምያስ እንደ ሌሎቹ የብሉይ ኪዳን ነቢያት ባለመሆኑ፣ ጽሑፉም ከሕይወቱና ከሐሳቡ ጋር የተሳሰረ በመሆኑ፣ የእርሱ ትንቢት ተማሪ የሆነ ሰው የዚህን የእግዚአብሐር ሰው ውስጣዊ ሕይወትና ባሕርያት በጥልቅ ማጤን ይኖርበታል፤ ከእነዚህም አንዳንዶቹ ቀደም ሲል በመጠኑ ተዳስሰዋል፡፡ ከተፈጥሮኣዊ ችሎታዎቹ፣ ከጥልቅ ስሜቶቹ (ውስጣዊ ስሜቶቹ)፣ ከተነሣሽነቱ፣ ከጌታ ጋር ስላለው የግል ግንኙነት ገጽታዎች በተጨማሪ፣ የኤርምያስ ንስሓዎች ተብለው የሚጠሩ፣ ከጌታ ጋር ያደረጋቸው ውይይቶች በጠላቶች ላይ ያወረዳቸው ርግማኖችና በተለይ የጸሎት ሕይወቱ ይገኛሉ፡፡ ልቡንና መንፈሳዊ መሻቶቹን እንደ እርሱ የገለጠ የብሉይ ኪዳን ነቢይ የለም፡፡ ጨዋና ፈሪ ቢሆንም እንኳ (አንዳንዶች በእርሱ ላይ እንደ ለጠፉት ግን ከቶ ሴታሴት አልነበረም፣ ከእግዚአብሔር ጥሪና እግዚአብሔር ከሰጠው ዐደራ የተነሣ ለተግባሩ በጽኑ የቆመ ሰው ነበር፡፡ ከዐላማው ሊነቃነቅ አልቻለም፡፡ በይሁዳ ውስጥ እንደ እርሱ ያለ አገሩን የሚወድ ሰው አልነበረም፤ ይሁን እንጂ የይሁዳን ኀጢአት አይቶ እንዳላየ ለማለፍ አወላውሎ ከቶ አያውቅም᎓᎓ ሕይወቱ የብቸኛና የገለልተኛ ሕይወት ነበር፤ የሰውን ኅብረትና ፍቅር ቢናፍቅም እንኳ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ቤተ ሰውና የቅርብ ወዳጆች አልነበሩትም:: ለወገኞቹ ጥልቅ ፍቅር ቢኖረውም እንኳ ሥቃያቸውንና ብሔራዊ ጥፋታቸውን ይፋ ያደርግ ዘንድ በመለኮት ዐደራ ተሰጥቶት ነበር፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር የነበረው ኅብረት የተለየ ጥልቀትና ቅርርብ ነበረው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ይህን ያህል ግልጽ በመሆኑ፣ በዘመናችን የሚገኙት አያሌ የእርሱ መጽሐፍ ተማሪዎች ይህማ እግዚአብሔርን እንደ መሳደብ ወይም ተገቢውን ክብር እንደ መንፈግ የሚቈጠር ነው ከማለት አድርሷቸዋል፡፡



ይቀጥላል...



ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 827-828



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

25 Nov, 15:03


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።”
ኤፌሶን 5፥20




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

24 Nov, 15:16


የሃኪሙ ሉቃስ ጹሑፎች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት


በአዲስ ኪዳን የሉቃስ ወንጌል እና የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊ ሃኪሙ ሉቃስ፣ በልዩ የአጻጻፍ ስልትና ዘዴዎች ይታወቃል። ሥራዎቹ በሥነ-ጽሑፋዊ ውስብስብነታቸው (አስደናቂ የግሪክ ቋንቋ እውቀቱ)፣ በታሪካዊ ዝርዝርነታቸው፣ በሥነ-መለኮት ጥልቀት እና በሁለንተናዊ እይታ ተለይተው ይታወቃሉ። ከዚህ በታች የእሱን ዘይቤ እና ስልቶች አጠቃላይ እይታ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንመለከታለን፦

1. ታሪካዊ እና የምርምር አቀራረብ ዘዴ

የሉቃስ አጻጻፍ ጥንቃቄ የተሞላበት ታሪካዊ ምርምርን ያንጸባርቃል። ብዙ ጊዜ ምንጮችን እና ምስክሮችን ይጠቅሳል፣ ይህም ለትክክለኛነቱ እና ለምርምር እና ጥናት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።

ምሳሌ፡- ሉቃስ በወንጌሉ መግቢያ ላይ ጥልቅ ምርምር እና ጥናት እንዳደረገ በግልጽ ተናግሯል።

“የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።”
ሉቃስ 1፥1-4


2. የግሪክ ሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ አጠቃቀም ዘዴ

ሐኪሙ ሉቃስ በአዳዲስ ቃላት እና መዋቅር የበለፀገ፣ ትምህርቱን እና አንባቢውን የማሳተፍ ችሎታውን የሚያንፀባርቅ ድንቅ የግሪክ ዘይቤን ይጠቀማል።

ምሳሌ፦ ወቅታዊ አረፍተ ነገሮችን መጠቀሙ፣ እንደ መቅድም (ሉቃስ 1፡1-4)፣ የተራቀቀ ድንቅ የግሪክ የአጻጻፍ ስልት ያሳያል።


ይቀጥላል...



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

24 Nov, 10:51


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ዓለም እናንተን ሊጠላ አይቻለውም፤ እኔ ግን ሥራው ክፉ መሆኑን እመሰክርበታለሁና እኔን ይጠላኛል።”
ዮሐንስ 7፥7



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

24 Nov, 09:57


#እራሳችንን_እንመርምር


የነፍስ ድካም እና ዝለት መድኃኒቱ ምን ይሆን? ነፍስን የሚያዝሉ ነገሮችስ የትኞቹ ናቸው?

“በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ።”
ዕብራውያን 12፥3




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

23 Nov, 12:21


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures


https://www.youtube.com/watch?v=OihTSJOA2Gg

ቅዱሳት መጻሕፍት

23 Nov, 10:35


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ደግሞ ታገሡ፥ ልባችሁንም አጽኑ፤ የጌታ መምጣት ቀርቦአልና።”
ያዕቆብ 5፥8



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

22 Nov, 18:48


የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክቶች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት


10. የብሉይ ኪዳን ቅዱሳት መጻሕፍትን በብዛት መጠቀም


ሐዋርያው ጳውሎስ የመከራከሪያ ነጥቦቹን ለመደገፍ ብዙ ጊዜ የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎችን ይጠቅስ ወይም ይጠቀም ነበር።
ምሳሌ፡- ሮሜ 4 በእምነት መጽደቅን ለማስረዳት የአብርሃምን ታሪክ ይጠቀማል።

11. መዘርዘር

ጳውሎስ ዝርዝሮችን ለማጉላት እንደ በጎ ምግባር፣ ስለሥጋ ወይም መንፈሳዊ ስጦታዎች ያሉ ነጥቦችን ለማጉላት ተጠቅሟል።
ምሳሌ፦ ገላትያ 5፥22-23 የመንፈስ ፍሬዎችን ይዘረዝራል።

12. ምስጋና እና ጸሎት

አብዛኞቹ ደብዳቤዎቹ የሚጀምሩት ለተቀባዮቹ በምስጋና እና በጸሎት ነው።
ምሳሌ፡- ፊልጵስዩስ 1፥3-11 የምስጋና እና የማበረታቻ ጸሎትን ይጨምራል።

13. ሁለትነት እና ንፅፅር

ጳውሎስ ሕግን ከጸጋን፣ ሥጋን ከመንፈስን፣ እና ሞትን ከሕይወት ጋር ያነጻጽራል።
ምሳሌ፡- ሮሜ 8 እንደ ሥጋ መኖርን እና እንደ መንፈስ ፈቃድ መኖርን ያነጻጽራል።

14. ኪያስመስ (አንድን በተለየ መንገድ መድገም)

ጳውሎስ አንዳንድ ጊዜ የኪያስመስ መዋቅርን ይጠቀም ነበር፣ እሱም ሃሳቦች በመስታወታዊ ቅደም ተከተል (A-B-B-A) ለአጽንዖት ይቀርባሉ።
ምሳሌ፡- በ2ኛ ቆሮንቶስ 4፥8-9፣ የመከራ እና የነጻነት ምሳሌ ኪያስመስ ይፈጥራል።

15. ኢሻቶሎጂካል(የነገረ ፍጻሜ) ትኩረት

የክርስቶስን መምጣት እና የአማኞች የመጨረሻ ተስፋ ላይ በማተኮር ጽፏል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ተሰሎንቄ 4፥13-18 ስለ ትንሣኤና ስለ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት ይናገራል።

የጳውሎስ ሁለገብ የአጻጻፍ ስልት የተለያዩ አንባቢዎችን በብቃት እንዲደርስ አስችሎታል። ይህም ምሁራዊ ጥልቀትን ከእረኝነት ሙቀት ጋር በማጣመር። ይህ ጥልቀት ጽሑፎቹን ዘላቂ ተጽዕኖ አላብሷቸዋል።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

22 Nov, 12:34


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም፦ የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው።”
ሚልክያስ 3፥8




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

21 Nov, 20:14


ትህትና



ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖርና አሸናፊ ለመሆን ትህትና እጅግ አስፈላጊ ባህሪ ነው፡፡ ካለ ትህትና ከእግዚአብሔር ጋር እንጣላለን፡፡ እንዲያውም እግዚአብሄር ትዕቢተኛውን ይቃወማል፡፡

"ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ።" ያዕቆብ 4፡6

ትህትና ይህን ያህል አስፈላጊ ከሆነ ትህትና ግን ምንድነው ብለን መጠየቅ ጥበብ ነው፡፡ ትህትናን በደንብ ልንማረውና ልናጠናው ተግተንም ልንለማመደው የሚገባ የተወደደ ባህሪ ነው፡፡

ትህትና ለሁሉም ሰው ያለ አክብሮት ነው፡፡ ትሁት ሰው ለወገኔ ይጠቅማል በማለት አንዱን ከሌላው ሰው በወገናዊነት አያበላልጥም፡፡ ትሁት ሰው ለሁሉም ከፍ ያለ አክብሮት ያለው ሰው ሲሆን ሁሉንም ለማገልገልና ለመጥቀም የተዘጋጀ ነው፡፡

"ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ::" ፊልጵስዩስ 2፡3

ትሁት ሰው ሌላው ሰው ከእርሱ እንደሚሻል በቅንነትና በእውነት የሚያምን ነው፡፡ ትሁት ሰው ራሱን ብቻ አስፈላጊ አድርጎ የማይመለከት ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው የሰውን ሁሉ አስፈላጊነት የሚረዳ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው በሌላው ሰው ስጦታ ጥሪና ጠቃሚነት የሚያምን ነው፡፡

"ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር::" ፊልጵስዩስ 2፡3

ትሁት ሰው የራሱን ብቻ የማይፈልግ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ሌላውንም የሚጠቅመውን ነገር ለማድረግ የሚፈልግ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ራስ ወዳድ አይደለም፡፡ ትሁት ሰው ለሌላው ጥቅም በትጋት የሚሰራ ሰው ነው፡፡

"እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ" ፊልጵስዩስ 2፡4

ትህትና እንደ ክርስቶስ ራስን አዋርዶ መኖር ነው፡፡ የሰው ትህትና የሚጀምረው ከአሳብ ነው፡፡ ሰው ገና በአሳብ ደረጃ ራሱን ካላዋረደ በትህትና ሊመላለስ አይችልም፡፡ ትሁት ሰው የትህትና መልክ ብቻ ሳይሆን የትህትና ሃሳብና ውሳኔ ያለው ነው፡፡

"በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።" ፊልጵስዩስ 2፡5

ከኢየሱስ የምንማረው ትሁት ሰው ለደረጃ ግድ እንደሌለው ነው፡፡ ትሁት ሰው ስለደረጃ አይጣላም አይጨቃጨቅም፡፡ ትሁት ሰው ትኩረቱ ማገልገል ሰውም መጥቀም በሰው ላይ ዋጋን መጨመር ሰውን ማንሳት ላይ እንጂ ስለስምና ስለስልጣን ወይም ጥቅም አይደለም፡፡ ትሁት ሰው የትም ማገልገል ስለሚችል መቼም ለመውረድ የተዘጋጀ ነው፡፡

"እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥" ፊልጵስዩስ 2፡6

ትሁት ሰው እግዚአብሔርም እንዲያዋርደው የማያደርግ ቀድሞ ራሱን የሚያዋርድ ነው፡፡ ትሁትን ሰው የምናውቀው ሁኔታ ስላልተመቸው በመዋረዱ ሳይሆን ከፍ የሚያደርግ ሁኔታ እያለ በራሱ ፈቃድ ራሱን የሚያዋርድ ሰው ነው፡፡

ትሁት ሰው ሰዎችን ለመጥቀም በምድር ላይ እንዳለ የሚያውቅ ሰው ሲሆን ሰዎች ሲጠቀሙበት እንደ እድል እንጂ እንደ ሽንፈት የማይቆጥር ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ሰዎች እንደተጠቀሙበት የሚሰማውን አፍራሽ ስሜት የማይቀበል ሰዎች እንዲጠቀሙበት የሚፈቅድ የባሪያ ልብ ያለው ለራሱ የማይሰስት ሰው ነው፡፡

"ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥" ፊልጵስዩስ 2፡7

ትሁት ሰው ነገሮችን ካደረገ በኋላ ክፍያውን የማይተምን በትህትናው የማይመካ ስላደረገው ስራ ዋጋውን ራሱ የማይተምን ሃላፊነቱን ብቻ እንደተወጠ የሚሰማው ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው ምንጩ እግዚአብሔር እንደሆነ የሚረዳ እንካ በእንካ አገልግሎት የሌለው ሰው ነው፡፡

"እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ፦ የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል በሉ።" ሉቃስ 17፡10

ትሁት ሰው ማንነቱን ጠንቅቆ የተረዳ ፣ ክብሩን የሚያውቅ ፣ የእርሱ ዝቅ ብሎ ማገልገል ምንም እንደማያዋርደው የሚያውቅ ሰው ነው፡፡ ትሁት ሰው በእግዚአብሔር ካለው ክብር እርሱን ሊያዋርደው የሚችል ምንም ነገር እንደሌለ የተረዳ ነው፡፡

"ኢየሱስ አብ ሁሉን በልጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥ ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ።" ዮሐንስ 13፡3-5



ምንጭ:- አብይ ዋቁማ



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

21 Nov, 13:38


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።”
ኤፌሶን 1፥3



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

20 Nov, 19:08


#የሮሜ_መልእክት_ጥናት




ሮሜ 10፥1-4


የዚህ ምዕራፍ ጭብጥ እስራኤል አሁን እግዚአብሔርን የመግፋቷ ጉዳይ ነው፡፡ ጳውሎስ ከመለኮታዊ ሉዓላዊነት (ምዕራፍ 9) ወደ ሰው ተጠያቂነት ያመራል፡፡ ባለፈው ምዕራፍ (ሮሜ 9:30-33) የጽድቅን ጭብጥ ካስተዋወቀ በኋላ የእስራኤልን የእምቢታ ሦስት ገጽታዎች ያብራራል፡፡

እስራኤል እንደ ሕዝብ የመሢሑን መምጣት በጉጉት እየጠበቁ ሊቀበሉት የተዘጋጁ እንደነበሩ አድርጋችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡ ለዘመናት የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችን ያውቃሉ፤ ሕጉንም ሲሠሩበት ኖረዋል፣ እርሱም ወደ ክርስቶስ እንዲመራቸው የተሰጠ እንደ «ሥራ መሪ» ነበር (ገላ. 3፡24)፡፡ እግዚአብሔር ሕዝቡን ሊያዘጋጅ ፈልጓል፣ ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ አልተቀበሉትም፡፡ ‹‹የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፣ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም» (ዮሐንስ 1፡11)፡፡ እርግጥ ነው፣ መምጣቱን ሲጠባበቁ የነበሩት ቅሬታዎች ነበሩ፣ ለምሳሌ ስምዖንና ሐና (ሉቃስ 2፡25-38)፤ ነገር ግን አብዛኛው ሕዝብ ክርስቶስ ሲመጣ ዝግጁ አልነበረም፡፡

ይህን አሳዛኝ ነገር እንዴት መግለጽ እንችላለን? እስራኤላውያን መሢሑን ያልተቀበሉበትን ብዙ ምክንያቶች ጳውሎስ አቅርቧል፡፡

ሀ) ደኅንነት እንደሚያስፈልጋቸው አልተሰማቸውም ( 10፥1)

ጳውሎስ ለእስራኤላውያን ወይም ለአይሁዳውያን ወደ እግዚአብሔር የሚጸልየው ለምንድን ነው?
በሮሜ 9÷18 እግዚአብሔር ምሕረት ለሚያደርግለት ምሕረቱን ያሳያል፥ ልቡን ሊያጠነክር የሚፈልገውንም ያጠነክረዋል ብሎ ከጻፈ፤ አሁን ታዲያ ለአይሁዳውያን ደኅንነት ሲጸልይ ምን ጥቅም ያገኝበታል? ጳውሎስ እግዚአብሔርን ለማግባባት ይሞክራልን? ወይስ በጸሎቱ የእግዚአብሔርን አስተሳሰብ ለመለወጥ ይጥራል?

መልሱ አዎን ነው። እጅግ በሚያስደንቅ መንገድ፤ እግዚአብሔር በፀሎታችን እንድናግባባው ይፈቅዳል። ይህን በማስረጃ ለማስደገፍ በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጣም ብዙ ምሳሌዎች አሉ። በተጨማሪም በጸሎታችን የሰይጣንን ሥራ ማሰናከል እንችላለን። ከእግዚአብሔር ቃል ቀጥሎ
ጸሎት በጣም ኀይለኛ የሆነ መንፈሳዊ የጦር መሣሪያ ነው (ኤፌ. 6፥17-18)። አንድ ነገር ለማግኘት በኢየሱስ ስም ብንጸልይ፥ እግዚአብሔር ይመልስልናል (ዮሐ. 15፥16)። ስለዚህም ጳውሎስ ለአይሁዳውያን ይጸልያል።

ጳውሎስ ከሕዝቡ ጋር ተስማምቶ ወንጌልን ተቃውሞ ኢየሱስን እንደ አታላይ የቆጠረበት ጊዜ ነበር፡፡ እስራኤላውያን ደኅንነት የሚያስፈልጋቸው አይሁድ ሳይሆኑ አሕዛብ ብቻ እንደሆኑ ቆጠሩ፡፡ በብዙ ምሳሌዎቹ እነዚህን የተሳሳቱ አሳቦች ኢየሱስ አንድ በአንድ አንሥቶአቸዋል፡- ታላቁ ወንድም (ሉቃስ 15፡11- 32) እና ፈሪሳዊው (ሉቃስ 18:9-14) ሁለት ምሳሌዎች ናቸው፡፡ እስራኤላውያን ከሮም ነፃ የሚወጡበት የፖለቲካ አርነት ቢፈልጉም፣ መንፈሳዊ ደኅንነት እንደሚያስፈልጋቸው ግን አልተረዱም ነበር፡፡


ይቀጥላል...



ምንጭ፦ ዋረን ደብልዩ ዌርዝ ቢ፤ ተስማማ፤ ገጽ 104-105፣ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 374




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

20 Nov, 12:55


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አንተ በምሕረትህ ብዛት በምድረ በዳ አልተውሃቸውም፤ በመንገድም ይመራቸው ዘንድ የደመና ዓምድ በቀን፥ የሚሄዱበትንም መንገድ ያበራላቸው ዘንድ የእሳት ዓምድ በሌሊት ከእነርሱ አልራቀም።”
ነህምያ 9፥19




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

19 Nov, 20:58


የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክቶች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት


5. የግጥም እና የመዝሙር ይዘቶች

ጳውሎስ ሥነ-መለኮታዊ እውነቶችን ለማጉላት መዝሙሮችን ወይም ቅኔያዊ ምንባቦችን አካቷል።
ምሳሌ፡- ፊልጵስዩስ 2፡6-11 ስለ ኢየሱስ ትህትና እና ከፍ ያለ የክርስቶስ መዝሙር ይዟል።

6. የወላጅ እና የዲሲፕሊን ድምጸት ያላቸው መልእክቶች

በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ያሉ ስህተቶችን ወይም ግጭቶችን ለመፍታት አንዳንድ ጊዜ የማስተካከያ ዘዴ ይጠቀማል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ቆሮንቶስ በቤተክርስቲያን ውስጥ መለያየትንና ብልሹ ባህሪይን ይገስጻል።

7. መምሰል እና ምሳሌ

ጳውሎስ የክርስቶስን ምሳሌ በመከተል የእሱን እምነትና ሕይወት እንዲኮርጁ አንባቢዎቹ አበረታቷቸዋል።
ምሳሌ፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥1፦ “እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ።”

8. የባህል ማጣቀሻዎች እና ምስለት

ሐዋሪያው ጳውሎስ ለአድማጮቹ የተለመዱ ዘይቤዎችን እና ምሳሌዎችን ተጠቅሟል። ለምሳሌ ከስፖርት ፣ ከግብርና እና ከወታደራዊ ሕይወት ጋር እያነጻጸረ ይጠቀማል።
ምሳሌ፡- 1ኛ ቆሮንቶስ 9፡24-27 የክርስትናን ሕይወት ከሩጫ ጋር ያነጻጽራል።

9. ልባዊ ምክር እና ማበረታቻ

ጳውሎስ አንባቢዎቹን በቅዱስና በጽድቅ ሕይወት እንዲመሩ ደጋግሞ ይመክራል።
ምሳሌ፡- ኤፌሶን 4-6 ግንኙነትን እና መንፈሳዊ ጦርነትን ጨምሮ ለክርስቲያናዊ ኑሮ መመሪያዎችን ይዟል።



ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

19 Nov, 11:24


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።”
ራእይ 1፥3



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

18 Nov, 20:26


👉ርዕስ፦ የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ
The Applied New Testament Commentary by Thomas Hale ከሚለው የተወሰደ
🗣ተርጓሚ፦ መስፍን ተስፋዬ፣ ተስፋዬ መስፍን፣ ምንሊክ አስፋውና ቴዎድሮስ በየነ ናቸው።
✏️ዋና ኦርታኢ፦ ደረጀ በቀለ ሲሆኑ ሰሎሞን ጥላሁንም አግዘዋል።
🖨አሳታሚ፦ ራዕይ አሳታሚ



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

18 Nov, 20:26


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

18 Nov, 14:08


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ በጌታ ጸንታችሁ ብትቆሙ፥ አሁን በሕይወት እንኖራለንና።”
1ኛ ተሰሎንቄ 3፥8



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

17 Nov, 16:34


የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክቶች የአጻጻፍ ስልት እና ይዘት


ሐዋርያው ​​ጳውሎስ የተለያዩ የአጻጻፍ ስልቶችን እና ቴክኒኮችን በመልእክቶቹ ውስጥ ተጠቅሟል፣ ይህም ትምህርቱን፣ የራሱን ባህላዊ ነባራዊ ሁኔታ እና የጻፈላቸውን የተለያዩ የመልእክቱ ተቀባዮቹን ሁኔታ የሚያንጸባርቅ ነበር። የተጠቀመባቸው ቁልፍ መንገዶች እና ዘዴዎች እነሆ፦

1. ዶክትሪን እና ሥነ-መለኮታዊ ጹሑፍ

ጳውሎስ ውስብስብ ሥነ-መለኮታዊ ሃሳቦችን በተለይም ስለ ድነት፣ ጸጋ፣ መጽደቅ እና እምነት ለማብራራት ብዙ ጊዜ ጽፏል።
ምሳሌ፡- ሮሜ ስለ ኃጢአት፣ ድነት እና የእግዚአብሔር ጽድቅ ስልታዊ ሥነ-መለኮታዊ ሙግቶችን ይዟል።

2. የግል እና መጋቢያዊ ቃና ያለው ድምጽ

ለአንባቢዎቹ እውነተኛ እንክብካቤ እና ፍቅር አሳይቷል፣ ብዙ ጊዜ “ወንድሞች እና እህቶች” ብሎ ይጠራቸዋል።
ምሳሌ፡- በ1ኛ ተሰሎንቄ ውስጥ፣ ጳውሎስ አማኞችን አመስግኗል እናም እነርሱን ለመጎብኘት ያለውን ጉጉት ገልጿል።

3. ሪቶሪካል ጥያቄዎች

ሪቶሪካል ጥያቄዎች "rhetorical question" ማለት መልሱ ምን እንደሆነ እየታወቀ መልስ እንዲመለስ ሳይሆን በአንባቢው ወይንም በሰሚዎቹ አእምሮ ውስጥ ጥያቄ ከስቶ ለማሰላሰል የሚገፋፋ ነው። ሀሳብን ለመቀስቀስ እና አንባቢዎችን ለማሳተፍ የአጻጻፍ ጥያቄዎችን ተጠቅሟል።
ምሳሌ፦ ሮሜ 6፡1፡ "እንግዲህ ምን እንላለን? ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት እንኑርን?"

4. አመክንዮአዊ ሙግት

ጳውሎስ አድማጮቹን ለማሳመን አመክንዮ በመጠቀም ሙግቶቹን በጥንቃቄ አዘጋጀ።
ምሳሌ፦ ገላትያ በዘዴ ይሟገታል በህግ ላይ ለድነት መታመንን እና በክርስቶስ ያለውን እምነት አጽንዖት ይሰጣል።


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

17 Nov, 10:47


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“የሥጋንም ሰውነት በመገፈፍ፥ በክርስቶስ መገረዝ፥ በእጅ ባልተደረገ መገረዝ በእርሱ ሆናችሁ ደግሞ ተገረዛችሁ፤”
ቆላስይስ 2፥11




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

17 Nov, 04:33


#እራሳችንን_እንመርምር



በሕይወት ዘመናችን መመካታችን እና እምነታችን ምን ላይ እንዲሆን እንሻለን? ምንደሰተው እና ልባችን በሐሴት የሚሞላው ምን አይነት ሰው ስናይ ነው?

“ነፍሴ በእግዚአብሔር ትከብራለች፥ ገሮችም ሰምተው ደስ ይላቸዋል።”
መዝሙር 34፥2

“በቃልህ ታምኛለሁና የሚፈሩህ እኔን አይተው ደስ ይላቸዋል።”
መዝሙር 119፥74




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

16 Nov, 12:01


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ጽድቅን የሚያደርገውን በመንገዶችህም የሚያስቡህን ትገናኛቸዋለህ። እነሆ፥ አንተ ተቈጣህ እኛም ኃጢአት ሠራን ስለዚህም ተሳሳትን።”
ኢሳይያስ 64፥5



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

15 Nov, 20:17


#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?


ሉቃስ 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁵ ወገባችሁ የታጠቀ መብራታችሁም የበራ ይሁን፤
³⁶ እናንተም ጌታቸው መጥቶ ደጁን ሲያንኳኳ ወዲያው እንዲከፍቱለት ከሰርግ እስኪመለስ ድረስ የሚጠብቁ ሰዎችን ምሰሉ፤
³⁷ ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።
³⁸ ከሌሊቱም በሁለተኛው ወይም በሦስተኛው ክፍል መጥቶ እንዲሁ ቢያገኛቸው፥ እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው።
³⁹ ይህን ግን እወቁ ባለቤት በምን ሰዓት ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ፥ በነቃ፥ ቤቱም እንዲቆፈር ባልፈቀደም ነበር።
⁴⁰ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

15 Nov, 10:22


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ታላቅነትህን የጸናችውንም እጅህን ለእኔ ለባሪያህ ማሳየት ጀምረሃል፤ በሰማይና በምድርም እንደ ሥራህ እንደ ኃይልህም ይሠራ ዘንድ የሚችል አምላክ ማን ነው?”
ዘዳግም 3፥24




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

14 Nov, 18:14


ነቢዩ ኤርምያስ




                        ክፍል-

በኤርምያስ ዘመን ግብረ ገባዊ ዝቅጠት በሰፊው የተሠራጨ ሲሆን፣ ኢፍትሓዊነትም በዚያው ልክ ተስፋፍቶ ነበር (5፥1-9፤ 7 ፥ 1-11 ፤ 23 ፥ 10-14)፡፡ ካህናትና ነቢያት እንደ ሌሎቹ አይሁድ ጥፋተኞች ነበሩ (6፥ 13-15)፡፡ ሆኖም ሕዝቡ ሃይማኖታዊ ሥርዐትን ፈጸሙ፡፡ እግዚአብሔር ግን በዚህ ውጫዊ ሥርዐት ከቊጣው የሚመለስ አልነበረም:: ኤርምያስ ከፍርድ ሊያመልጡ እንደማይችሉ ሰበከ፡፡ እግዚአብሔር ድርቅን፣ ረኃብንና የውጭ ወራሪዎችን ቀደም ሲል ተጠቅሞአል (14፥1-6፤ 4 ፥ 11-22) ፤ ከዚያም በናቡከደነፆር በኩል የመጨረሻ ጒብኝቱን ያካሂዳል (25፥9)፡፡ ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር ፍቅርና ለኪዳኑ ያለው ታማኝነት ፍርዱ አጥፊ ወይም የመጨረሻ እንዲሆን አያደርጉም:: የወደፊት ተስፋ ነበር፡፡ ከባቢሎን ምርኮ መመለስ እውን እንደሚሆንና (25፥11፤ 29፥10) ባቢሎን ራሷ እንደምትጠፋ (ምዕራፍ 50-51) ኤርምያስ አስቀድሞ ተናገረ፡፡ የእስራኤልን ተስፋ ተጨባጭ መገለጥ ለመስጠት አለወላወለም (32፥1-5)::

ኤርምያስ ለአሕዛብም አገልግሎት ነበረው፡፡ በዚያ ዘመን ለነበሩት ሁናቴዎች ናቡከደነፆር የእግዚአብሔር መሣሪያ መሆኑን አየ (27፥ 6)፡ ፤ ሌሎች ሕዝቦች ናቡከደነፆርን እንዳይቃወሙትም አስጠነቀቀ (27፥1-11)፡፡ ሕዝቡ ሁሉ በጽድቅ እንዲጓዝ በእግዚአብሔር ስም ጥሪ አቀረበ (ምዕራፍ 46-51)፡፡ እግዚአብሔር ለሰዎች ሁሉ ደኅንነት ግድ ያለው መሆኑን በመግለጽም ድምፁን አሰማ (29፥ 1-14 በተለይ ቊጥር 7)፡፡

በኤርምያስ አገልግሎት ውስጥ የነበረው ዐቢይ አጽንዖት፣ ከማንኛውም ነገር ይልቅ መንፈሳዊ ጒዳዩ የላቀ መሆኑ ነው፡፡ የይሁዳ እምነት ጊዜያዊ ገጽታ የቱን ያህል ዝቅተኛ መሆኑን አስተዋለ፡፡ የእምነት ብጤዎቹ ቀጥሎ የተመለከቱትን ይበጅ ብለው መያዛቸውንም አየ፤

(1) የጌታን ኪዳን በአፍኣዊ መልኩ መቀበል (11፥1-5)፣

(2) ግዝረት (9 ፥ 25-26)

(3) ቤተ መቅደሱ (7፥1-15)፣

(4) የመሥዋዕት ሥርዐት (6፥20፤ 7፥21-23)፣

(5) የሙሴን ሕግ በውጫዊ መልኩ መቀበል (8፥8)፣

(6) የሐሰት ትንቢት (2 ፥ 39-40)፣

(7) ጸሎት (11 ፥ 14 ፤ 15፥ 1)፣

(8) ዙፋኑ (22 ፥ 1-9)፣ እናም

(9) ታቦቱ (3፥16)፡፡

ከማንኛውም ነቢይ ይልቅ ኤርምያስ ስለ ንስሓ አብዝቶ ሰበከ፡፡ በማንኛውም ጊዜ ያሳስበው የነበረ ዋና ጒዳይ የእያንዳንዱ ሰው (የግለሰቡ) የልብ ሁናቴ ነበር፡፡ የዐዲሱ ኪዳን ገለጻው (ትንታኔው) በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በእጅጉ ድንቅ ነው (31 ፥ 31-34)፡፡ ይህ እውነት በጌታችን ሥራ ላይ የቱን ያህል ዘልቆ እንደ ገባ ዐዲስ ኪዳን ያሳያል፡፡

ኤርምያስ በሩቅ ስላለው ስለ ወደፊቱ ወቅት የተነበየው እስራኤል በንስሓ ወደ ጌታ እንደምትመለስ ነው (32 ፥ 37-40)፡፡ መሲሕ በፍትሕና በጽድቅ በእርሷ ላይ ይነግሣል (23፥5-8)፡፡ በዚያን ጊዜ የሕዝቡ ትሩፋን በረከትን ያገኛሉ (3፥17፤ 16፥19)፡፡


ይቀጥላል...



ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 827




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

14 Nov, 12:51


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አካሄድን እንደ ቃልህ አቅና፤ ኃጢአትም ሁሉ አይግዛኝ።”
መዝሙር 119፥133



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

13 Nov, 16:57


👉ርዕስ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፣
ከ "ZONDERVAN NIV
BIBLE COMMENTARY VOLUME 1: Old Testamen" የተተረጎመ
🗣ተርጓሚዎች፦ ምንሊክ አስፋው፣ ንጉሤ ቡልቻ፣ ተጋፋው ትርፌ፣ ሰሎሞን ጥላሁን፣ ናሁሠናይ አፈወርቅ፣ ፍትሐ አምላክ እንየው፣ ደርበው አዱኛ፣ መስፍን ታዬ፣ ቁምላቸው ፋንታሁን፣ ዮናስ አስፋው፣ ፍሥሓ ፈይሣ፣ ተስፋዬ መስፍን፣ ወርቁ ኤጀሬ እና ቴዎፍሎስ ቀነዓ ናቸው፡፡
አርታዕያን፦ ንጉሤ ቡልቻ፣ ናሁሠናይ አፈወርቅ፣ ሰሎሞን ጥላሁን፣ ደርበው አዱኛ፣ ምንሊክ አስፋው እና ፍሥሓ ፈይሣ
📝ዋና አርታዒ ፦ ፍትሐ አምላክ እንየው ናቸው፡፡
🖨አሳታሚ፦ ራዕይ አሳታሚ


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

13 Nov, 16:57


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

13 Nov, 13:37


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና፥ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ።”
ሮሜ 8፥5




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

12 Nov, 20:29


#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት


#ሰሊሆም

ሰሊሆም ማለት የተላከ ማለት ነው። ኢየሱስ የዕውሩን ዓይን በጭቃ ከቀባ በኋላ «ሂድና ታጠብ» ብሎ ወደ ሰሊሆም ላከው፤ ዮሐ 9፡6-7። ለመጠመቂያ የሚሆን ውሃ የተጠራቀመበት ኩሬ። ከኢየሩሳሌም በደቡብ በኩል ዖፊል በተባለው ጎጥ ሥር ይገኛል። ሕዝቅያስ ውሃውን ከግዮን ምንጭ በቦይ ወደዚህ አስገብቶታል። በፊት በኢየሩሳሌም ቅጥር ውስጥ ነበር። ዛሬ ግን በኋላ ከተሠራው ቅጥር ውጭ ነው፤ ኢሳ. 22፥9-11። በብሉይ ኪዳን በተለይም በኢሳይያስ 8፥6 መሠረት ሰሊሆም ጸጥ ብለው በሚፈሱ ምንጮች የተከማቹ ሲሆኑ፣ እነዚህ ምንጮች ኢየሩሳሌም በጠላት በምትከበብበት ጊዜ ሁሉ የሚያገለግሉ በመሬት ውስጥ የሚሄዱ ስውር ውሆች ናቸው፡፡ እነዚህም ወኪሎች በሆኑት ነገሥታት ማለትም ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸው ከዳዊት ዘር በሆኑት ነገሥታት በኩል እግዚአብሔር በቸርነቱና በበረከቱ እስራኤልን በሰላምና በጸጥታ የሚገዛበትን ሁኔታ በምሳሌነት የሚገልጹ ናቸው፡፡



ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 71፣ ምሉእ ሕይወት፤ ገጽ 1014




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

12 Nov, 10:42


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 9፥24




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

12 Nov, 05:24


#የሮሜ_መልእክት_ጥናት



ሮሜ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወንድሞች ሆይ፥ የልቤ በጎ ፈቃድና ስለ እስራኤል ወደ እግዚአብሔር ልመናዬ እንዲድኑ ነው።
² በእውቀት አይቅኑ እንጂ ለእግዚአብሔር እንዲቀኑ እመሰክርላቸዋለሁና።
³ የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
⁴ የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።


ሮሜ 10 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወንድሞች ሆይ፤ ስለ እስራኤላውያን የልቤ ምኞት፣ እግዚአብሔርንም የምለምነው እንዲድኑ ነው።
² ለእግዚአብሔር ቀናተኞች እንደሆኑ ስለ እነርሱ መመስከር እችላለሁና፤ ቅናታቸው ግን ከዕውቀት የተነሣ አይደለም።
³ ከእግዚአብሔር የሚመጣውን ጽድቅ ስላላወቁና የራሳቸውን ጽድቅ ለመመሥረት ስለ ፈለጉ፣ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
⁴ ለሚያምን ሁሉ ጽድቅ ይሆን ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።


ሮሜ 10 (ሕያው ቃል)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወንድሞቼ ሆይ፥እሥራኤላውያን እንዲድኑ ያለኝ ምኞትና ጉጉት ይህ ነው አይባልም። ጌታ እንዲያድናቸውም የዘወትር ጸሎቴ ነው።
² እነርሱም ስለ እግዚአብሔር ከፍ ያለ ቅንዓት እንዳላቸው አውቃለሁ። ነገር ግን ይህ ቅንዓታቸው በትክክለኛ እውቀት ላይ የተመሠረተ አይደለም።
³ ከእግዚአብሔር የሚሰጠውን ጽድቅ ንቀው፥ ሕግን በመጠበቅና በበጎ ሥራ ላይ የተመሠረተውን የራሳቸውን የጽድቅ መንገድ በመከተል እውነተኛውን ጽድቅ እምቢ አሉ።
⁴ በእርሱ የሚያምኑ ሁሉ እንዲጸድቁ ክርስቶስ ሕግን ፈጽሞላቸዋል። ስለዚህ ሕግን በመጠበቅ ለመጽደቅ አይቻልም።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

11 Nov, 20:18


የቀጠለ...

የጠጣር ልብ አደገኛ ውጤቶች



የጠጣር ልብ የሚያስከትሉት ውጤቶች ግለሰቡ ላይ ብቻ አይደለም። በአጠገቡ ያሉትን ሰዎች ይጎዳል። ግትር የሆነው ልበ ቅንነት በቤተሰብ ፣ በቤተክርስቲያን አመራር እና በአጠቃላይ ድርጅት ላይ ተጽዕኖ ይሳድራል ፡፡ልበ ጠጣርነት አንድ ሰዉን ብቻ አይጎዳም በዙሪያው ያሉትን ሁሉ ይነካል ፡፡

“እኔ እስከዚ ድረስ ብቻ ነው መግዋዝ የምችለው” የሚለው ይህ አስተሳሰብ ነው ፡፡ እነሱ ልክ እንደበፊቱ አያምኑም ፡፡ የእነሱ የዓለም አመለካከት ሊቆጣጠሩት ለሚችሉት ነገር ቀንሷል። በዚህ ምክንያት ፣ ጠጣር ልብ ከሚያስከትላቸው መዘዞች አንዱ በአካባቢዎ ያሉ ሰዎችን መጉዳቱ ነው፡፡ ሰዎች ይጎዳሉ ፣ ቤተሰቦች ይጎዳሉ ፡፡ ጋብቻ፣ በአካባቢዎ ያሉ ግንኙነቶች አሉታዊ  ተፅኖንው ያጠቃዋል፡፡

2. የሚጎዳቸውን ነገር አይተውም፡፡

ምንም እንኳን እነዚህ የማምለጫ መሳሪያዎች አሉታዊ ተፅእኖን ቢያስከትሉም ጠጣር ልቦች ብዙውን ጊዜ ሱስ የሚያስይዝ ልምምዶችን ይፈልጋሉ።

እናም እነሱን ትጠይቃቸዋለህ “ለምን ይህን መጥፎ ልማድ ትሰራላችሁ? ለምን ይህን ታደርጋለህ?” ብዙ ጊዜ መለወጥ እንደማይፈልጉ የሚገልጽ ቀዝቃዛ ምላሽ ያገኛሉ።

ምንም እንኳን ልምዳቸው ስሜታቸውን እና አካላዊ ጤንነታቸውን እንኳን የሚጎዳ ቢሆንም ምንም እንኳን በቤተሰቡ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ቢኖረውም ለእነሱ ግድ አይሰጥም ፡፡

ከባድ ሲሆንብዎ ጊዜ ከዚ በኋላ ከሚያስከትላቸው ውጤቶች ጋር ከእንግዲህ አይገናኙም ፡፡ ጠጣር ልብ ያላቸው ሰዎች በሚያስደንቅ ሁኔታ ግትር ይሆናሉ ፡፡ እነሱ እንደዚህ ይላሉ ፣ “እኔ እንደዚ ነኝ፡፡ ይቀበሉት ወይም ይተዉት፡፡”

3. የእግዚአብሔርን እንቅስቃሴ እና የአቅጣጫ ፍሰት ያግዳሉ፡፡

የእግዚአብሔር ሥራ ሁሉ የሚከናወነው በመንፈስ ቅዱሱ መሪነት ፣ ተነሳሽነት እና ኃይል ሰጪነት ነው ፡፡ነገር ግን ጠንካርነት በሚኖርበት ጊዜ ወደ እርስዎ የሚመጡ የገነት ምልክቶችን አይለዩም። በእውነቱ ፣ እግዚአብሔር ሩቅ ነው ብለው ያስባሉ እርሱ ሩቅ ስለሆነ አይደለም ፣ ነገር ግን ልብዎ በዚያ የትስስር ግንኙነት ስለጠነከረ ነው ፡፡

የትኛውም ቡድን ቢሆኑ ፣ ጠጣርነቶ በቡድኑ ውስጥ ያሉትን ይጎዳል ፡፡ የእግዚአብሔር አቅም ይታገዳል ፡፡ የእርስዎ ጠጣርነት በሌሎች ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው።

4. ሊያንቀሳቅሳቸው በሚችሉ ነገሮች ላይ ስሜት አልባ እና ቀዝቃዛ ይሆናሉ፡፡

ጠጣር ልብ ሲኖርዎት ፣ የበለጠ እንዳይነቁ እና ከህይወትዎ ተለይተዉ እንዲወጡ ያደርግዎታል። ይህ ከእግዚአብሔር የፍቅር እና ግንዛቤ ፀጋ መውጣት አይደለም ፣ ነገር ግን የአከባቢያዊ ግንኙነቶችዎ ላይ ተፅህኖ ማምጣትም ነው ፡፡

በተለምዶ ፣ የተወሰኑ ነገሮች ልብዎን ያንቀሳቅሱ እና ወደ መለወጥ ይመራዎታል ፡፡ አሁን ፣ እነዚያ ቀስቃሾች ከእንግዲህ እንኳን አይነክዋችሁም።

እግዚአብሔር ወደ ፍላጎቶችዎ ያስገባዎታል ፡፡ እግዚአብሔር ተዛማጅ ስለሆነ ፍላጎቱን በእናንተ ላይ አይጭንም። በችግር ቦታ ውስጥ ቢሆኑም እንኳን በትዕግስት ይወዳችኋል ፡፡ እርሱ ግን ጠንካራነትህ ወደ ሚወስድህ እንድትሄድ ያደርግሃል ፡፡ እራሳችንን ለማነቃቃት ልባችን እንዲቀልልልን አንዳንድ ግዜ አስቸጋሪ ጊዜዎችን ማለፍ አለብን ፡፡



ምንጭ፦ www.hiyawkal.org




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

11 Nov, 14:15


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በዚያም ኢየሱስ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ሊቀ ካህናት የሆነው፥ ስለ እኛ ቀዳሚ ሆኖ ገባ።”
ዕብራውያን 6፥20



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

10 Nov, 18:45


የጠጣር ልብ አደገኛ ውጤቶች



የምንኖርበት ጊዜ ልባችንን ልያጠጥር ስለሚችል ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ልባችንን በትኩረት መከታተል አለብን ፡፡

በአንድ ሌሊት አይከሰትም። አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር በንቁ ጉዞ ሊኖር ይችላል ከዚያም ቀስ በቀስ ወደ ደረቅነት ወደ ሚቀዘቅዘው ይሸጋገራል፡፡ ትክክል የሆነውን ያውቃሉ ፡፡ ግን ከእንግዲህ ግድ የላቸውም ፡፡ ግዴለሽነት ልባቸውን ይገዛል። የሌላውን ችግር እንደራስ በቀላሉ ማግኘት አይቻልም። በአንድ ወቅት እምነት ጠንካራ እና ንቁ ነበር ፣ መቀዝቀዝ ፣ ጥርጣሬ እና ነቀፋ ወረረዉ፡፡ ልጅ-መሰል እምነት ይቀልጣል እናም እንቅፋትን ይታገሱታል።

ልብን መለወጥ እንዴት ከባድ ነው ጠንካራ ልብን ማዳበር የምንችልባቸው የተለያዩ መንገዶች አሉ ፣ ግን ሁለት ዋናዎች መጥቀስ ተገቢ ነው-

1. እዉነትን መስማት ግን ተግባራዊ አለማድረግ፡፡

ጠንካራ ልብ በቀላሉ ሊያድግ ከሚችልበት አንድ ትልቁ መንገድ ምን ማድረግ እንዳለብን ስናውቅ እርምጃ ሳንወስድ ስንቀር ነው፡፡ የምንኖረው ከማንኛውም የበለጠ እውቀት እና ማስተዋል በሚገኝበት ትውልድ ውስጥ ነው። ሁልጊዜ እውነትን ለመስማት እድል አለን ፡፡ ችግሩ ፣ ብዙ እንሰማለን ፣ ግን በጣም ትንሽ ነገር ላይ እርምጃ እንወስዳለን፡፡

እኛ በታላላቅ አስተማሪዎች ተከብበናል ፣ ግን ብዙዎች ስለእሱ ምንም አያደርጉም ፣ ይህም ውሎ አድሮ ጠንካራ እና ቀዝቃዛ ወደ ሆነው ልብ እንዲያድጉ ያደርጋቸዋል ፡፡

ብዙዎች የሆነ ነገር በመስማታቸው ምክንያት “እናዉቃለን” ብለው በማሰብ ተታለዋል ። ግን ያ እውነት በዕለት ተዕለት ኑሯቸው ውስጥ ንቁ እውነታ አይደለም ፡፡እውነት በእዉነታዉ ላይ ተግባራዊ ካልተደረገ እና በውሳኔዎችም ውስጥ እንዲታይ እስካልተፈቀደ ድረስ እውነት ትርጉም የለውም። ሌሎች ትክክል የሆነውን ነገር በትክክል ያውቃሉ ፣ ግን እርምጃ ላለመውሰድ ይመርጣሉ። የክርስትና ሕይወት ግቡ የሰማችሁትን መውሰድ ነው ፣ ያዕቆብ 1፥22 እንደሚናገረው “ቃሉን የምታደርጉ እንጂ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ” ፡፡

በአንዳንድ መንገዶች ፣ አንድ ጠንካራ ልብ ለመጽሐፍ ቅዱስ እውነት የተጋለጠ ሰው ግን በነገሩ ምንም ባለማድረግ ሊገለፅ ይችላል፡፡

2. የልብዎ ችግር በጊዜ መፍትሄ አለማግኘቱ፡፡

ጠንካራ ልብ የሚያዳብርበት ዋነኛው ምክንያት የተሰበሩ ልምዶች እና የተሰበሩ ጉዳዮች ሁልጊዜ የሚያስፈልገውን ፈውስ የማይቀበሉ ከሆነ ነው። አሁን ሰዎች በብዛት ከባድ እየሆኑ ነው ምክንያቱም እግዚአብሔር የሕይወታቸውን ጥልቅ ሥቃይ እንዲፈውስ ስላልፈቀዱ ነው ፡፡

ቅሬታ፣ ለሌሎች አለማሰብ ጠንካራ ልብ ሊያዳብሩ ከሚችሉ ዋና ነገሮች ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ጠንካራ ልብን ካሸናፊዎቹ የሚለየው ቅሬታን እንዴት መወጣት አለመቻሉ ነው፡፡

በስህተት የተያዘ እና ጥልቅ ቅሬታ የልብ ገዳይ ሊሆን ይችላል ፡፡ጥልቅ የህመማችን ቅሬታ ለማከም ካልሞከርን ወደ ቂም መያዝ ፣ መለያየት እና ወደ የከፋ መቀዝቀዝ ያመራናል፡፡ የልብ ጡንቻዎቻችን ያላቅቅብናል፡፡

ሁሉም ሰው ለብስጭት እና ለችግሮች የራሱ ድርሻ አለው። ብዙዎች በሥቃይ ውስጥ እግዚአብሔርን መጋበዝ ይመርጣሉ ፡፡ ምንም እንኳን እጅግ በጣም ከባድ ቢሆንም ፣ ከዚህ በፊት የማያውቋቸውን የእግዚአብሔር ተፈጥሮ ገጽታዎችን ያያሉ ፡፡ በመከራ ፣ በማጣት በብስጭት ጊዜያት ታላቅ ጥንካሬ እና ብስለት ያገኛሉ። ሆኖም በተመሳሳይ ጊዜ ፣ ብዙዎች በመንፈስ እና በስሜት ይወሰዳሉ፡፡

በተጎዳን ወይም በተቃጠልንባቸው ወቅቶች ውስጥ ማለፍ እንችላለን እናም እግዚአብሔር ጠንካራ ቦታዎችን በማለስለስ ልባችንን መፈወስ ይፈልጋል ፡፡ ለጥንካሬ ተስፋ አለ ፡፡ነገር ግን ያ ጥንካሬ የማይጣስበት ጊዜ ይመጣል ፡፡ እግዚአብሔር ራሱ በፊትህ ሊወጣ ይችላል እናም ምንም ነገር አይለውጠዉም ፡፡


ይቀጥላል...


ምንጭ:-  www.hiyawkal.org



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

10 Nov, 12:08


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ቅጥር እንደሌላት እንደ ፈረሰች ከተማ፥ መንፈሱን የማይከለክል ሰው እንዲሁ ነው።”
ምሳሌ 25፥28



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

10 Nov, 10:52


#እራሳችንን_እንመርምር



ነገ ስናስብ ተራራ የሚያሳክልብንና በጭንቅ የሚወረን ለነገ ያለን መመካት ነው። ዛሬ ነገ ላይ ይኖራሉ ያልናቸው ነገሮች ላይኖሩ እንደሚችሉ ምን ያክሎቻችን በእርግጥ እናውቀዋለን? ዛሬ ላይ ሆነን፣ ነገ አልታየኝም ማለት ነገ ይጨልማል ያለው ማን ነው?

“ቀን የሚያመጣውን ምን እንደ ሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።”
ምሳሌ 27፥1


“ራሳችሁን ከፍቅረ ንዋይ ጠብቁ፤ ባላችሁ ነገር ረክታችሁ ኑሩ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር፣ “ከቶ አልተውህም፤ በፍጹም አልጥልህም” ብሎአል።”
ዕብራውያን 13፥5 (አዲሱ መ.ት)





ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

09 Nov, 12:48


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥”
ዕብራውያን 10፥12



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

08 Nov, 16:32


ነቢዩ ኤርምያስ




                        ክፍል-


ነገር ግን መጨረሻው ሩቅ አልነበረም:: በዘጠነኛው የአገዛዝ ዘመኑ (588)፣ ሴዴቅያስ ከፈርዖን ኡፍራ ጋር ግምባር በመግጠም በናቡከደነፆር ላይ ዐመፀ:: ባቢሎን ይሁዳን በመውረር ምላሽ ሰጥታ በ586 ከተማዋ በእጇ ስትወድቅ ወረራው ፍጻሜ ላይ ደረሰ (2ነገ 36፥17፤ ኤር 38 ፥ 28-39፥ 10)፡፡ በወረራው ዘመን ሁሉ ሴዴቅያስ እጁን ይሰጥ ዘንድ ኤርምያስ አደፋፈረው (21 ፥ 1-10 ፤ 34፥ 1-5፤ 17-22 37 ፥ 3-10፤ 16-17 ፤ 38፥ 14-23)፡፡ በአንድ ወቅት የግብፅ ሰራዊት እየገፋ መምጣት፣ የባቢሎንን ተዋጊ ሰራዊት ያፈገፍግ ዘንድ አስገደደው፤ ይሁን እንጂ ወረራው ተመልሶ ቀጠለ (37 ፥ 1-10)፡፡ በዚህም ጊዜ ሴዴቅያስ ፍርሀት ያደረበት ሰው ስለ ነበር፣ ኤርምያስ በይሁዳ በሚገኙት ጠላቶቹ ግፍ ደረሰበት (37 ፥ 11-21፤ ምዕ 38)፡፡ በዚህ ወቅት ኢየሩሳሌም የወደቀችበት ዕለት፣ በዓለም ዙሪያ በሚገኙ አይሁድ ዘንድ፣ በአቢብ ወር በዘጠነኛው ቀን በሐዘን የሚታሰብ ሲሆን፣ በብሉይ ኪዳን ውስጥ በእስራኤል ላይ ከፍተኛው የእግዚአብሔር ፍርድ ነበር፡፡ ሴዴቅያስ ለማምለጥ ሲሞክር ተያዘ፤ ወንዶች ልጆቹም ዐይኑ እያየ በፊቱ ታረዱ፤ ዐይኑም ወጣ፤ ከዚያም ከተከታዮቹ ጋር ወደ ባቢሎን ተጋዘ፡፡

ከከተማዪቱና ከቤተ መቅደሱ ውድመት በኋላ የባቢሎን ንጉሥ፣ ጎዶልያስን የይሁዳ ገዥ አድርጎ ሾመው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ (በቂ ማስረጃ በሌለበት ሦስት ወር ወይም ጥቂት ዓመታት ሊሆን ይችላል)፣ ጎዶልያስ ከዳዊት ቤት በሆነው ወገን ተገደለ፤ ይህም አፍቃሬ ግብፅ በሆኑት ሰዎች ቀስቃሽነት ሳይፈጸም አልቀረም፡፡ የብርቱው መከራ ሰለባዎች የሆኑት የባቢሎንን የዐመፅ ምላሽ በመፍራት ኤርምያስንና ባሮክን ዐብረዋቸው እንዲሸሹ በማስገደድ ወደ ግብፅ ወረዱ፡፡ ስለዚህ ከምእት ዓመታት በፊት በሙሴ አማካይነት ከፈርዖን ትድግና የተገኘበት ዑደት በዚህ ጊዜ ፍጻሜ ላይ ደረሰ፡፡ ሌላው የሚያስገርመው ጒዳይ ደግሞ በአገልግሎቱ ዘመን ሁሉ በግብፅ ላይ እንዳይታመኑ ሲመክር የነበረው ኤርምያስ ያለፈቃዱ የምድር ሕይወቱን በዚያ እንዲጨርስ መደረጉ ነው፡፡ ስለዚህ በእስራኤል ውስጥ ዐይነተኛ ዘመን የነበረው መለኮታዊ አገዛዝ አከተመ፡፡ በሴሎ የማደሪያው ድንኳን መውደሙም የመሳፍንትን ዘመን ደመደመው፡፡ የሰሎሞን ቤተ መቅደስ መውደም በእስራኤል ዘንድ የንጉሣዊ አገዛዝ ዘመን ማክተሙን አመለከተ፡፡ በቲቶ (ጥጦስ) ዘመን (70 ዓ.ም.) ሁለተኛው ቤተ መቅደስ መውደሙ እስከ ዐዲሱ ዘመን ድረስ እስራኤል በምድሯ ላይ የምትኖርበት ዘመን በአደገኛ ሁኔታ ማክተሙን አመላካች ነበር፡፡

ነገረ መለኮታዊ አጽንዖት

የኤርምያስ መልእክት ጒሉሓን ባሕርያት፣ ለእርሱ ዘመንና ለእኛ ዘመን ዐቢይ ፋይዳ አላቸው፡፡ ኤርምያስ በዕድሜ ዘመኑ ሁሉ የደረሰበትን ሐዘንና ተቃውሞ ለመዝለቅ የበቃው በእግዚአብሔርና እግዚአብሔር በሰጠው ተስፋ ጽኑ እምነት ስለ ነበረው ነው (18+7! 29:14: 32:1-5):: የሕይወቱም የአገልግሎቱም ሁለት ትኲረቶች እግዚአብሔር (ማለት ቸርነቱ፣ በሰው ዘር ላይ ያለው ባለቤትነቱ፣ ንስሓና እምነት እውን ይሆኑ ዘንድ ግድ መሰኘቱ) እና ተንከራታች ሕዝቡ ሲሆኑ፣ ይህም የሥጋዊና የመንፈሳዊ ሕይወታቸውን ደኅንነት ያካትታል፡፡

ኤርምያስ እግዚአብሔር የፍጥረት ሁሉ አምላክ መሆኑን በማመን (27፥5)፣ ስለ እግዚአብሔር ከፍ ያለ ሐሳብ አለው፡፡ የአሕዛብ አማልክት ህልውና የላቸውም (10፥11 (በአራማይስጥ ቋንቋ መጽሐፍ ውስጥ ብቸኛ ጥቅስ ነው)፤ 14 14፥ 22)፡፡ እግዚአብሔር የሰውን ልብ ክፋት ያውቃል (17፥9-10)፤ ይሁን እንጂ በእርሱ ላይ የሚታመኑትን ለመባረክ በመናፈቅ (17 ፥ 7) ሕዝቡን በጥልቅ ይወዳል (31፥1-3)፡፡ የጣዖት አምልኮና ልበ ደንዳናነት እንዲሁም ንስሓ አልባ አገልግሎት በእርሱ ፊት አስጸያፊዎች ናቸው (19:4-6 14፥12)፡፡ እግዚአብሔርን ሕይወት በሌላቸው ጣዖታት ከመወከል የበለጠ በእርሱ ላይ የሚሰነዘር ስድብ የለም፡፡ ኤርምያስ ያለመታከት በመቃወም ስብከት ያቀረበበት ልዩ ኀጢአት የጣዖት አምልኮ ነበር፡፡ ሦስት ዐይነት ሐሰት አስቈጣው፡-

(1) ንስሓ ይገባ ዘንድ የተደረገውን ጥሪ ሁሉ አልቀበልም እያለ ምንም አልሆንም የሚል ዐመፀኛ የሆነ ከንቱ ዋስትና፣

(2) ሕዝቡን በአደገኛ አስተማማኝነት እንዲሸፈኑ ያደረጉ የሐሰት ነቢያት፣

(3) ጣዖታትን በከንቱ ማምለክ፡፡  አምልኮ ለበኣል፣ ለሞሎክና ለሰማይ ንግሥት (ለኢሽታር) ይደረግ ነበር፡፡ የእነዚህ አማልክት ምስል በቤተ መቅደስ ውስጥ ሳይቀር ተቀምጦ ነበር (32፥34፤ ከ7፥31 ፤ ከ19፥5፤ ከ32 ፥ 35፤ ከ44፥18-19)፡፡


ይቀጥላል...


🚨ማሳሰቢያ የጊዜ አቆጣጠር ካልተጠቀሰ በቀር ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ነው።



ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 826




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

07 Nov, 16:14


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።”
1ኛ ጴጥሮስ 2፥5



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

06 Nov, 21:14


ለቃሉ መታዘዝ




መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው፡ ለታሪክ፡ለምርምር፡ ለጠቅላላ ዕውቀት፡ ለግንዛቤ፡ ወይም ለመረጃ አይደለም። የተጻፈበት ቀዳሚ ዓላማ ለሕይወት ነው።

"የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም  ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤" ዕብ ፬፡፲፪

መጽሐፍ ቅዱስን መታዘዝ አለብን ስንል መጽሐፉ ከዳር እስከ ዳር ይህን አድርግ ይህን አታድርግ በሚሉ ትእዛዛት የተሞላ መጽሐፍ ነው ማለታችን አይደለም። እግዚአብሔር እንድንታዘዘው የሚፈልገውን ሃሳብ በቃሉ ውስጥ በተለያየ መንገድ አስቀምጧል። ይህንንም ማስተዋል የኛ ድርሻ ይሆናል።

« እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም።» ኢዮ ፴፫፥፲፬፤

እግዚአብሔር ከሚያስተምርባቸው መንገዶች የሚከተሉት ዋናዎቹ ናቸው።

፩. በቀጥተኛ ትዕዛዝ

መጽሐፍ ቅዱስ አድርግ፣ አታድርግ የሚሉ ቀጥተኛ ትእዛዛት አሉት፤ ለምሳሌ እንደ አሥርቱ ቃላት እና ትእዛዛተ-ወንጌል፤ እነዚህንም በቀጥታ መፈጸም ይጠበቅብናል።

«አትግደል፤ አትስረቅ፤ አታመንዝር…. በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤ አትጨነቁ፤ ጽድቁን ፈልጉ።…» ዘጸ ፳፤ ማቴ ፮።

፪. በምክር መልክ

በቅኔ እና በጥበብ መጻሕፍት ውስጥ በምሳሌ፣ በምስጋና፣ በግጥም፣ በጸሎት መልክ በተጻፉት በምክር ያስተምራል። እነዚህም በመከራ ጊዜ ድጋፍ፣ መጽናኛ የሚሆኑ ኃይል ያላቸው ቃላት ናቸው።

            «እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው የሚያስደነግጠኝ ማን ነው?» መዝ ፳፯፥፩

፫. በሰዎች ታሪክ

ደካማም ይሁኑ ብርቱ፣ ከድካማቸው እንድንማር፣ ብርታታቸውን እንድንከተል በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ታሪካቸው የተጻፈላቸው ሰዎች ሁሉ ምንጊዜም ለኛ የሚያስተምሩት ነገር  አለ። ለምሳሌ አብርሃም የእግዚአብሔር ወዳጅ ለመባል የበቃው በእምነት ባሳየው መታዘዝ በመሆኑ እኛም እንደ አብርሃም በእምነት እግዚአብሔርን ብንታዘዝ የበረከቱ ተካፋዮች እንደምንሆን እግዚአብሔር ተናግሯል።

«መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ። በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ። እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ። » ገላ ፫፣፰

፬. በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዚች ምድር የመጣው አንደኛ ለቤዛነት (ዓለምን ሁሉ ለማዳን) ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ለአርአያነት ወይም በኑሮአችን እንድንመስለው በተግባር ለማስተማር ነው። ከልደቱ እስከ ሞቱ መላው የክርስቶስ ሕይወቱ ለእኛ አስተማሪ ነው።

« የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።» ፩ ጴጥ ፪፣፳፩።

ልጆች ለወላጆቻቸው እንዲታዘዙ መጀመሪያ በቃል በ፲ቱ ትዕዛዛት በኋላም ሰው ሆኖ በተግባር እየታዘዘ  አስተማረን - የሕይወት መምህር ኢየሱስ ክርሰቶስ። ይህን በማስታወስ ቅዱስ ጳውሎስ ልጆች ለወላጆች እንዲታዘዙ ይመክራል።

« ልጆች ሆይ፥ ለወላጆቻችሁ በጌታ ታዘዙ፥ ይህ የሚገባ ነውና። መልካም እንዲሆንልህ ዕድሜህም በምድር ላይ እንዲረዝም አባትህንና እናትህን አክብር፤ እርስዋም የተስፋ ቃል ያላት ፊተኛይቱ ትእዛዝ ናት።» ኤፌ ፮፣፩

የአዳም አለመታዘዝ ለሰዎች ሁሉ ሞትን እንዳመጣ የክርስቶስ መታዘዝ ደግሞ ሕይወትን አስገኝቷል። ሮሜ ፭፣ ፲፱ ይመልከቱ።

መታዘዝ የበረከት ብቻ ሳይሆን የሕይወትም ጉዳይ ነው። ክርስቶስ እንደታዘዘ የሕይወትንም መንገድ እንዳመጣ እኛም በእርሱ በማመን፣ እምነታችንንም በመልካም ሥራ በመግለጽ ስንታዘዝ የዘላላም ሕይወትን እናገኛለን።

ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስን መጀመሪያ በእግር ቀጥሎም በግብር ተከተሉት ሲባል ሕይወታቸው በሙሉ እርሱን የሚመስል ሆኖ ለእግዚአብሔር በመታዘዝ ኖሩ ማለት ነው። እኛም በክርስቶስ በስሙ ተጠርተን ክርስቲያኖች (የክርስቶስ) ስንባል ሕይወታችንም እርሱን የሚመስል ሊሆን ይገባዋል ማለት ነው።

ለእግዚአብሔር ከምናቀርብለት ከየትኛውም መሥዋዕታችን ይልቅ ለእግዚአብሔር እንደመታዘዝ ያለ ነገር የለም።  

"በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን? እነሆ፥ መታዘዝ ከመሥዋዕት፥ ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል።"  ፩ሳሙ ፲፭፣፳፪።

በብሉይ ኪዳን ለእግዚአብሔር ይቀርብ የነበረው መሥዋዕት የአውራ በግ፣ ዋኖስ፣…. ነበር። በሐዲስ ኪዳን እነዚህን አናቀርብም፤ የቀረበ አንድ መሥዋዕት አለ። እርሱም የእግዚአብሔር በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እንግዲህ እኛ የምናቀርበው መሥዋዕት ምስጋና ነው። ጸሎትም ወደ እግዚአብሔር እናደርሳለን። ምጽዋት በእግዚአብሔር ስም ለተቸገሩት እንሰጣለን። ወደ እግዚአብሔር ከሚደርሱት ምስጋና፣ ጸሎት፣ ጾም፣ ምጽዋት….ከእነዚህ ሁሉ በላይ/በፊት ለእግዚአብሔር መታዘዝ እንደሚቀድም ቃሉ ያስተምረናል።

እንግዲህ በመጽሐፍ ቅዱስ የሚገኘው የእግዚአብሔር ቃል እያንዳንዳችን አድራሻ ያደረገ የሰማያዊ አባታችን መልእክት ስለሆነ በእምነት ስንቀበለው፣ በተግባርም ስንታዘዘው ያን ጊዜ የበረከቱ ተካፋዮች እንሆናለን። የእግዚአብሔር ቃል ከወተት እስከ አጥንት በተለያየ ደረጃ የሚገኝ በመሆኑ እኛም በመጀመሪያ በመንፈስ ሕጻናት ሆነን የቃሉን ወተት እየተመገብን በእርሱ ስናድግ እየተገለጠልን፣ እየተረዳነው እንመጣለን።

« ከጊዜው የተነሳ አስተማሪዎች ልትሆኑ ሲገባችሁ፥ አንድ ሰው ስለ እግዚአብሔር ቃላት መጀመሪያ ያለውን የሕፃንነትን ትምህርት እንዲያስተምራችሁ እንደ ገና ያስፈልጋችኋልና፤ የሚያስፈልጋችሁም ወተት ነው እንጂ ጠንካራ ምግብ አይደለም። » ዕብ ፭፣፲፪

ቃሉ እንዲሠራብን ከኛ ግንዛቤን ሳይሆን ተግባራዊ ምላሽን  ይፈልጋል። ስለዚህ ለቃሉ እንታዘዝ።

«ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።» ያዕ ፩፣፳፪

ቃሉን ሰምተን እንድንታዘዝ ጸጋውን ያብዛልን!!!


ምንጭ:- abrhamha.blogspot.com




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

06 Nov, 10:55


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ያም እድል ፈንታው ነውና ሰው በሥራው ደስ ከሚለው በቀር ሌላ መልካም ነገር እንደሌለው አየሁ፤ ከእርሱ በኋላስ የሚሆነውን ያይ ዘንድ የሚያመጣው ማን ነው?”
መክብብ 3፥22



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

05 Nov, 19:39


#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት


#ቀርጤስ

ቀርጤስ ከግሪክ ደሴቶች ትልቁ እና ከዋናው ግሪክ በደቡብ ምስራቅ የምትገኝ ከተማ ናት። በጥንት ጊዜ፣ በአውሮፓ ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ የላቁ ባህሎች አንዱ ተደርጎ በሚቆጠር ኃይለኛ በሚኖአን ሥልጣኔ (2700-1420 ከክርስቶስ ልደት በፊት) ትታወቅ ነበር። በአዲስ ኪዳን ዘመን፣ ቀርጤስ የአይሁድ ማህበረሰቦችን ጨምሮ በባህሏ እና በተለያዩ ህዝቦቿ የምትታወቅ የሮማ ግዛት አካል ነበረች።

ከሊታውያን የቀርጤስ ሰዎች ነበሩ፤ 1ሳሙ. 30፥14። በጰንጠቆስጤ ቀን ከቀርጤስ የመጡ አንዳንድ ሰዎች በኢየሩሳሌም ነበሩ፤ ሐሥ. 2፥11። ጳውሎስና ቲቶ በቀርጤስ ቤተ ክርስቲያንን መሠረቱ ቲቶ 1፥5-14።

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ቀርጤስ ቁልፍ ነጥቦች፡-

ስትራቴጂካዊ ቦታ፦ የቀርጤስ መገኛ በሜዲትራኒያን ባህር ውስጥ ለንግድ እና ለጉዞ አስፈላጊ መስቀለኛ መንገድ አድርጎታል።

የባህል ጠቀሜታ፦ ደሴቲቱ ተረት እና ፍልስፍናን ጨምሮ የበለጸገ ባህላዊ ቅርስ ነበራት።

የሥነ ምግባር ዝና፡- የቀርጤስ ሰዎች የሚታወቁት በመዋሸትና በሥነ ምግባር ብልሹነት ነበር (ቲቶ 1፥12)

ክርስቲያናዊ ተልእኮ፡- የጳውሎስ የቀርጤስ ጉብኝት እና ቲቶ መሪ አድርጎ መሾሙ ክርስትና ወደ ደሴቲቱ መስፋፋቱን ያመለክታል።



ምንጭ፦ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፤ ገጽ 89፣ The Book of Titus: A Counter-Cultural Gospel for Cretans: https://bibleproject.com/articles/titus/
Crete Meaning - Bible Definition and References:

https://www.biblestudytools.com/dictionary/crete/




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

05 Nov, 17:16


👉ርዕስ፦ የመናኝ ጉዞ
ጸሐፊ፦ ዮሐንስ ቡንያን
🔈ክፍል ስድስት


ይቀጥላል...


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

05 Nov, 11:48


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን፥ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው።”
ቲቶ 3፥6-7




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

04 Nov, 20:04


ተሐድሶ መቼ ይጠበቃል?


፩. በክርስቲያን ነን ባዮች መሃል ወንድማዊ ፍቅርና ክርስቲያናዊ መተማመን ሊኖር ግድ ሲል።

፪. የአሳብ መለያየት፣ ቅናት እና ክፉ ንግግር በክርስቲያን ነን ባዮች ቦታ ሲይዝ።

፫. በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ዓለማዊ መንፈስ ሲኖር። ክርስቲያኖች በአለባበስ፣ ሀብት በመሰብሰብና በጭፈራ በዓለም መደነቅን በመፈለግ የዓለምን ነገር ሲመርጡ ሲታይ።

፬. ቤተ ክርስቲያን ምዕመኖቿ በኃጢአት ሲዘፈቁና ወደ ኃጢአት ሲገቡ።

፭. አገልጋይ በየትኛውም ደረጃ የሚያገለግለውን ሕዝብ አመኔታ ባጣ ጊዜ።

፮. ሰው በተሰበከው መጠን ልቡ ንስሃ ከመግባት ይልቅ የሚደነድን ከሆነ።

፯. አማኞች የጌታ መልክ የማይታይባቸው ከሆነ።

፰. ጸጋ የማያድግበት ከሆነ እና አማኙ ከሳምንት ሳምንት ለክርስትና ግዴታው የማይነሳሳ ከሆነ

፱. መጸለይ ከባድና አስቸጋሪ ሲሆን።

፲. ክርስቲያኖች ኃጢአታቸውን እርስ በእርሳቸው መናዘዝ ሲያቅታቸው

፲፩. ክርስቲያኖች መስዋዕትነት መክፈል በሚያስፈልግበት መስዋዕትነትን ለመክፈል ፈቃደኛ መሆን ሲያቅታቸው




ምንጭ፦ ቻርለስ ፊኒ፤ ተሐድሶ እንዲሆን፤ ከገጽ 6-10




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

04 Nov, 19:51


ፕሮቴስታንት ማለት ምን ማለት ነው?




ፕሮቴስታንት የሚለው ቃል በላቲን ፕሮቴስታሪ ከሚል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም "በአደባባይ ማወጅ" ወይም "ተቃውሞ ማድረግ" ማለት ነው። ቃሉ በመጀመሪያ እ.ኤ.አ በ1529 በስፔየር አመጋገብ ላይ በፖለቲካዊ አውድ ውስጥ ጥቅም ላይ ዋለ። ከዚህ በመቀጠል በስብሰባ ላይ የጀርመን መሳፍንት እና የንጉሠ ነገሥት ከተሞች ቡድን የለውጥ አራማጁን ማርቲን ሉተርን ያወገዘውን የዎርምስን አዋጅ ለመደገፍ የተላለፈውን ውሳኔ ተቃወሙ። እነዚህ ተቃዋሚዎች የሀይማኖት ነፃነት መብት እና የእምነታቸው ተግባር ላይ የሚጣሉ ገደቦችን በመቃወም የካቶሊክ አብላጫውን ድንጋጌ በመቃወም መደበኛ የሆነ “ተቃውሞ” አቅርበዋል።

እንቅስቃሴው በሃይማኖታዊ ገጽታው ብቻ ሳይሆን በተሃድሶ ላይ በማተኮር እና በተቋቋሙት የሃይማኖት ባለስልጣናት ላይ በማተኮር "ፕሮቴስታንቲዝም" በመባል ይታወቃል። በጊዜ ሂደት፣ “ፕሮቴስታንቶች” ከተሃድሶ የተነሱትን እና ከሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የተለየ ማንነት ያለው የትኛውንም የክርስቲያን ቤተ እምነት በሰፊው ለማመልከት የሚውል ቃል ሆነ።


ምንጭ፦
👉MacCulloch, Diarmaid. The Reformation: A History. Viking, 2003.
👉Bainton, Roland H. Here I Stand: A Life of Martin Luther. Abingdon-Cokesbury, 1950.
👉The Oxford Dictionary of the Christian Church, edited by F.L. Cross and E.A. Livingstone, 2005.



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

04 Nov, 13:24


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ነገር ግን ሩጫዬንና ከጌታ ከኢየሱስ የተቀበልሁትን አገልግሎት እርሱም የእግዚአብሔርን ጸጋ ወንጌልን መመስከር እፈጽም ዘንድ ነፍሴን በእኔ ዘንድ እንደማትከብር እንደ ከንቱ ነገር እቆጥራለሁ።”
ሐዋርያት 20፥24



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

03 Nov, 18:01


👉ርዕስ፦ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ተሐድሶ፣ ቅጽ 1፣ ሳታድግ ያረጀች የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን
ጸሐፊ፦ ወ/ዊ ጸጋአብ በቀለ
🗓 የታተመበት ዓመት፦ 2006 ዓ.ም


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

03 Nov, 18:01


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

03 Nov, 11:06


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 16፥13



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

02 Nov, 20:52


ሃይማኖትስ ይታደሳል?
      


ክርስትና በአስተርእዮተ እግዚአብሔር ላይ የተመሰረተ እምነት ነው (ለምሳሌ ዮሐ. 1፥18፤ ገላ. 2፥2)። ጌታ እግዚአብሔር በዘመናት ሁሉ የገለጠው እውነትና የሰጣቸው ተስፋዎች ሁሉ ፍጻሜም ነው። በክርስቶስ መገለጥ ያልተፈጸመ ምንም የለም፤ "በእግዚአብሔር የተሰጡ ተስፋዎች ሁሉ 'አዎን' የሚኾኑት በእርሱ ነውና" (2ቆሮ. 1፥20 ዐ.መ.ት)። በእግዚአብሔር ልጅ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት የመጣው አስተርእዮ የቀዳሚዎቹ ፍጻሜ ብቻ ሳይኾን፣ የመጨረሻውና ከሁሉ በላይ የላቀ መገለጥ ነው (ዕብ. 1)። እንግዲህ ይህ መገለጥና እምነት እውነተኛ ፍጹም ቢኾንም፣ እኛ ሰዎች በምንሰጠው ምላሽና ተግባር ላይ ግን ጉድለት ሊከሠት መቻሉ እውነት ነው፤ የሰው ልጅ መሳሳቱ አይቀርም። የመታረሙና መታደሱ አስፈላጊነትም የሚመነጨው ከዚሁ የሰው ድካም ውስጥ ነው።

የሰው ልጅ እውነተኛን እምነት በመበረዝ በኑፋቄ ጮረቃ ሲያልኮሰኩሰው እግዚአብሔር በተሐድሶ ውሃ ያጠራዋል። በዚያን ጊዜ ምርቱን ከግርዱ መለየት ይኖራል። ፍሬውን ከገለባው ማበጠር ይከተላል። ለዚህም ዐላማ ሲል እግዚአብሔር በምሕረቱ የተሐድሶ ነፋስ ያነፍስበታል። በዚህ ማጥራትና ማንፈስ ሂደት ደግሞ የሚሠራ ብቻ ሳይኾን የሚፈርስ የቁሻሻ ክምር ይኖራል። ይህን መሳይ ታላቅ ተግባር ለማከናወን ብሩህ አእምሮ የታደሉ ዐዳሾች ያስፈልጋሉ ማለት ነው። ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ እንዳሉት፣ "አሕይዎና ተሐድሶ (Revival and Renewal or Reformation) ተደላድሎና ተመቻችቶ በተቀመጠ ሥርዐት (Establishement) ውስጥ የዛገና የሚራገፍ ነገር የሚያይ የአእምሮ ችሎታና የተፈጥሮ ተሰጥዎ ካላቸው ታላላቅ ሰዎች ዘንድ የሚመጡ ሐሳቦች ናቸው።"

ስለዚህ ሃይማኖትም ቢኾን "በዛገና በሚራገፍ ነገር" ብልሽት ከገጠመው ይታደሳል። እግዚአብሔር ራሱ አሮጌውን በዐዲሱ ዐድሷል። አሮጌውን በዐዲሱ ሰው ተክቶታል (ኤፌ. 4፥24፤ ቆላ. 3፥10)። ነቀፋ የተገኘበትን ፊተኛውን ኪዳን  (ኤር. 31፥ 31-34) ለዐዲሱ ስፍራ አስለቅቆታል (ዕብ. 8፥6-7)። ስለዚህም፣ "ዐዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቶአል፤ አሮጌውና ውራጅ የሆነውስ ሊጠፋ ቀርቦአል" (ዕብ.8፥13) የተባለው ቃል ተጻፈ። አዎን! ሃይማኖትም ቢኾን ቅይጥነት ሲገዳደረው፣ አደፋ ሲጠናወተው መለኮተ መድኀኒት ያዝዝለታል።

"ማፍረስም መስራት ነው" ከሚለው ጽሁፍ የተቀነጨቡ ሃሳቦች

ከእግዚአብሔር የተቀበልናቸውን ጠቃሚ ሀብታት አንድም በማበላሸት ካቆሸሽናቸው፣ ደግሞም ለእርሱ ክብር ከማድረግ ይልቅ ለሥጋዊ ትምክሕትና ሌላውን ወገን ለማክፋፋት ካዋልናቸው ዐላማቸውን ስተዋልና የተሐድሶ ነፋስ ያሻቸዋል። 

መጽሐፍ ቅዱሳችን ራሱ የተሐድሶ መጽሐፍ ነው።  እግዚአብሔር በታሪከ ድነት ውስጥ ያቆመው ዋነኛ መርሕም የተሐድሶ ምልሰት ነው።      

ቅዱሱን መጽሐፍ የልብ ዐይኖቻችን ተከፍተውልን ካነበብነው ተሐድሶን እንናፍቀው እንደኾነ እንጂ እናክፋፋው ዘንድ ዐቅም አይኖረንም። ይህም[በክርስቶስ የሆነው ድነት] በእግዚአብሔር ምሕረትና ጸጋ አማካይነት ወደ ቀደመው ክብር፣ ጸጋና ቦታ የመመለስና የመታደስ ወንጌል ነው። ከውድቀት በኃላ ለአዳም የተሰጠው ያ ተስፋ ቤዝዎታዊ ተሐድሶ ነበር።     

ተሐድሶን ለማምጣትና ወደ እውነቱ ለመመለስ ሲባል የሐሰት ትምህርት ላይ መጨከን ግዴታ ነው እንጂ፣ አማራጭ አልነበረም፤ ዛሬም ሊሆን አይችልም።

"ልዩ ወንጌል" ወደ ቤተ እግዚአብሔር ሲያቀና እንቢ ማለትና አዋኪዎች ያስገቡትን ኑፋቄና የአጋንንት ትምህርት ማፍረስ ተሐድሶ ነው። ይህ ሊኮነን ሳይኾን ሊወደስ የሚገባው ዘመቻ ነው። ጥያቄው ለምን፣ መቼ፣ የት፣ ምንና እንዴት ይታደስ የሚለው እንጂ "ዝንቡ እሽ የሚባል የለም" ብሎ ማፍጠጥ መፍትሔ አይኾንም። በደፈናው "ሃይማኖት አይታደስም" እያልን ከማገንገን፣ ለምን እንደማይታደስ ብናስረዳ ጥሩ ነበር። ጌታ ኢየሱስ አዳሽ አልነበረምን? ሐዋርያቱስ? የአሮጌው መነካት ባይመቸንም እንኳ፣ ለተሻለው ስፍራ እንዲለቅ ውራጅ የኾነው ትምህርትና ልምምድ ይፈርሳል።

ማንኛውንም ነገር በደባልነት ደርበን ለማምለክ ብንሞክር፣ ይህ ብክለት ነውና ሃይማኖት ይታደሳል። ማንኛውም ነገር ከመለኮታዊው አስተምህሮ በተፃሮ ሲቆም፣ ወይም ቅይጥነት ሲዳበለው ተሐድሶ ያስፈልጋል። የእግዚአብሔር ሰው ነኝ የሚል ሁሉ አምልኮተ ባዕድን፣ ርኩሰትን፣ ጥንቆላን፣ ኑፋቄን። በወንጌል ስም መነገድን፣ ወዘተ. ማፍረስ ግድ ይለዋል። በእግዚአብሔር ከተሰጠው መመሪያ ውጭ በሰው የተገነቡ መሠዊያዎች እስከሚሰነጠቁና ዐመዳቸው እስከሚፈስ ድረስ ቢሰነጣጠቁ እንደነቃለንን(1ነገ. 13)?     



ምንጭ፦ ሰሎሞን  አበበ ገብረ መድሕን፤ የትሩፋን ናፍቆት፣ ማፍረስም መስራት ነው፣ ጌታቸው ኃይሌ ፤ ደቂቀ እስጢፋኖስ:- በሕግ አምላክ




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

02 Nov, 09:22


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ለቍጣም የዘገየ ይሁን፤”
ያዕቆብ 1፥19



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Nov, 20:35


ርዕስ፦ ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ
ብራና ሴሚናር 2016፣ ወደ ተነሳንበት መመለስ፣ የተሐድሷውያን አምስቱ "ብቻዎች"


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Nov, 20:34


ርዕስ፦ በጸጋ ብቻ
ብራና ሴሚናር 2016፣ ወደ ተነሳንበት መመለስ፣ የተሐድሷውያን አምስቱ "ብቻዎች"


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Nov, 20:33


ርዕስ፦ ክርስቶስ ብቻ
ብራና ሴሚናር 2016፣ ወደ ተነሳንበት መመለስ፣ የተሐድሷውያን አምስቱ "ብቻዎች"


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Nov, 20:32


ርዕስ፦ በእምነት ብቻ
ብራና ሴሚናር 2016፣ ወደ ተነሳንበት መመለስ፣ የተሐድሷውያን አምስቱ "ብቻዎች"


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Nov, 20:29


ርዕስ፦ ቅዱሳት መጻሕፍት ብቻ (ቃሉ ብቻ)
ብራና ሴሚናር 2016፣ ወደ ተነሳንበት መመለስ፣ የተሐድሷውያን አምስቱ "ብቻዎች"


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Nov, 16:38


የቀጠለ...



፫. ድነት በእምነት ብቻ “Sola Fide,”
“Salivation by Faith Alone”


ለጸጋ ያለን ምላሽ እምነት ነው። እምነት እጅግ ቀላል የሚመስል ከባድ ነገር ነው። እምነት ከባድ ያደረገው ለማመን አስቸጋሪ የሆነውን ነገር እንድናምን እኛን መጠየቁ ነው። በአዲስ ኪዳን ውስጥ 150 ጊዜ ኃጢአተኛ ድነት የሚያገኘው በእምነት ብቻ እንደሆነ ተገልጿል። የሰውን ነፍስ ማዳን የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ሲሆን ይህን እውን የሚያደርገው ሰዎች በልጁ የመስቀል ሥራ ሲያምኑ ብቻ ነው። እምነት ሥራ ሳይሆን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ሙሉ በሙሉ መደገፍ ማለት ነው።

በሮማን ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ድነት ሂደት ነው። ድነት በኢየሱስ ክርስቶስ ባለን እምነት፣ በሥራና ቅዱስ ሚስጢራትን በመፈጸም እንደሚገኝ ያምናሉ። እምነትና ሥራም ለድነት አስፈላጊነታቸው ላይ ያሰምራሉ። ማርቲን ሉተር ሲናገር፦ “እምነትና ሥራ እንደ እሳትና ሙቀት የማይለያዩ ቢሆኑም ለነፍስ ድነት በክርስቶስ እናምናለን እንጂ ለመዳን መልካም ሥራ አንሰራም። እምነትና ሥራ አንድ ባይሆኑም በፍጹም ማለያየት አይቻልም፤ መልካም ሥራ እምነታችንን የማይከተል ከሆነ የሚያድን እምነት እንደሌለን ያመለክታል። የዳነው በእምነት ብቻ ነው፤ ነገር ግን ብቻውን በሆነ እምነት ግን አይደለም። ያለ ሥራ እምነት ሙት ነውና (ያዕ. 2፡17-20)። እንደዚሁም ሥራ የእምነት ውጤት እንጂ እምነት የሥራ ውጤት አይደለም። መልካም ሥራ የመዳናችን መሠረት ሳይሆን ማስረጃ ነው (ኤፌ. 2፡10)። መልካም ሥራ የመዳናችን ምልክት እንጂ ምክንያት አይደለም። ስለዚህ ለመዳን እናምናለን እንጂ አንሠራም፤” ብሏል።

ድነት ነጻ ስጦታ ነው። ድነት በጾምና ጸሎት፣ ለደሃ በመወጽወት፣ በባሕታዊነት፣ ራስን በማጎሳቆል፣ በመገርጣትና በመራብ፣ በተዝካር ድግስ፣ አማላጆችና ቅዱሳን በተባሉ ልዩ ሰዎች መካከለኛነት፣ በቤተ ክርስቲያን አባልነት ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ሥራ በማመን ብቻ ነው።

#እምነት_ምንድነው? ለሚለው ቃሉ መልስ አለው፦ “እምነት ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጠን የማናየውንም ነገር የሚያስረዳን ነው” (ዕብ. 11፡1)። በዚህ ክፍል ስለ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እምነት የሚያስረዱን ሁለት ቁልፍ ቃሎች “ማስረገጥ” እና “ማስረዳት” የሚሉት ናቸው። ማስረገጥ ማለት፦ “ምርኩዝ መሆን” “መደገፍ” ማለት ነው። እምነት ለድነታችን እንደ ጠንካራ ምርኩዝ በክርስቶስ እንድንደገፍ ይረዳናል። ሁለተኛው ቃል “ማስረዳት” የሚል ሲሆን ይህም እምነት አንድ ግልጽ ያልሆነውን ነገር የመረዳት አቅም እንደሚሰጠን ያመለክታል።

“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።” (ዮሐ. 3፡16)

፬. ድነት በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ “Solus Christus,” “In Christ Alone”

“እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም።” (ሮሜ. 8፡1) ኃጢአት የሌለበት ፍጹም ጽድቅና ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ በሰው ልጆች ሁሉ ምትክ መሞቱና መነሳቱ ከአብ ጋር መታረቅ ሆኖልናል። ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ለብዙዎች ቤዛ እንደ ሆነ ተናግሯል። ስለዚህ ድነት በእርሱ ብቻ ነው።

“ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።” (ዮሐ. 14፡6)

“የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ።” (1ዮሐ. 5፡13)

“መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ ይነግሣሉ እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ።” (ራዕ. 5፡9-10)

፭. ለእግዚአብሔር ክብር ብቻ “Soli Deo Gloria,” “For the Glory of God Alone”

የዳንነው በእግዚአብሔር ኃይል ለእግዚአብሔር ክብር ብቻ እንደሆነ በማወቅ በእርሱ ፊት በእውነተኛ ቅድስናና አምልኮ መኖር ይገባናል። በእግዚአብሔር ፊት፣ በእግዚአብሔር ሥልጣን ሥር ለእግዚአብሔር ክብር ብቻ መኖር አለብን።

“የእግዚአብሔርንም መሠዊያ ደግሞ አደሰ፥ የደኅንነትና የምስጋናም መሥዋዕት ሠዋበት ይሁዳም የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን እንዲያመልኩ አዘዘ። ሕዝቡ ግን ገና በኮረብታው መስገጃዎች ይሠዋ ነበር ቢሆንም ለአምላኩ ለእግዚአብሔር ብቻ ነበር።” (2ዜና 33፡16-17)



ምንጭ፦ "ተሐድሶ" ቅጽ-1 በጸጋአብ በቀለ ከገጽ 243-248
       



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

01 Nov, 11:36


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“የእግዚአብሔርን ጸጋ አልጥልም፤ ጽድቅስ በሕግ በኩል ከሆነ እንኪያስ ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።”
ገላትያ 2፥21




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

31 Oct, 18:19


የፕሮቴስታንት ተሐድሶ አምስቱ ምሶሶያት



የፕሮቴስታንት ተሐድሶ መሪዎች ማርቲን ሉተር፣ ጆን ካልቪን፣ ኡልሪች ዝዊንግሊ፣ ጆን ኖክስ በዘመኑ ከነበረችው ከሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ልዩ የሚያደርጋቸውን አምስት ነገረ መለኮታዊ ቁልፍ የአስተምህሮ ምሶሶያት አስቀምጠዋል። እነዚህ የተሐድሶ ምሶሶያት “አምስቱ ሶላዎች” (Five solas) ተብለው ይታወቃሉ። ሶላ (sola) ማለት የላቲን ቃል ሲሆን ትርጉሙም “ብቻ” ማለት ነው። አምስቱ ብቻዎች የተባሉት፦

፩. ለድነት መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ “Sola Scriptura,” or “Scripture Alone”.

መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል ነው። “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል” የሚልና ተመሳሳይ ዓረፍተ ነገር በብሉይ ኪዳን 3,808 ጊዜ ተጠቅሷል። በፔንታቱክ 700 ጊዜ፣ በታሪክ መጽሐፍት 400 በኢሳይያስ ብቻ 150 ጊዜ፣ በሕዝቅኤል 350 የተጻፈ ሲሆን ይህም የቃሉ ምንጭና ባለቤት እግዚአብሔር እንደሆነ ያመለክታል።

በቤተ ክርስቲያን ያለው ልምምድ፣ አስተምህሮና ማንኛውም ሥርዓት በመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ይዳኛል፣ ይመራል፣ ይገመገማል፣ ይታረማል፣ የሚል ሲሆን ማርቲን ሉተር በአንድ ወቅት ፍርድ ቤት ቀርቦ አቋሙን እንዲለውጥ ሲጠየቅ፦ “መጽሐፍ ቅዱስና ሕሊናዬ መሳሳቴን ካልገለጡልኝ በስተቀር የሮም ጳጳስና አማካሪዎቹን ትምህርት አልቀበልም፤ እርስ በእርሳቸው ይጣረሳሉና። አእምሮዬና ልቤ ለእግዚአብሔር ቃል እሥረኞች ናቸው። የሕሊናዬ ተቃዋሚ ሆኜ መሰለፍ አይሆንልኝም። ከዚህች አቋሜ ፍንክች አልልም። እግዚአብሔር ይርዳኝ። አሜን" ብሏል::

፪. ድነት በጸጋ ብቻ “Sola Gratia,” or “Salivation by Grace Alone”.

“ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና ይህም የእግዚአብሔር ሥጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም” (ኤፌ. 2፡8)።

“ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና“ (ቲቶ 2፡11)።

“ጸጋ” የሚለው ቃል በፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ወሳኝ ጥቅልና ሰፊ ጽንሰ አሳብ ያዘለ ቃል ነው። ብዙ ሰዎችም በተሳሳተ መንገድ የሚረዱት ቃል ነው። ጸጋን ከአንደበት ይልቅ ተቀብለን ስንኖርበት እናውቀዋለን። ጸጋን ከኢየሱስ ክርስቶስ ነጥለን ማየት አንችልም። የሚያድን ጸጋ የተገለጠው በኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ሐዋሪያው ዮሐንስ በአራተኛው ወንጌል መግቢያ ላይ ጠቅሶታል “ሕግ በሙሴ ተሰጥቶን ነበርና ጸጋና እውነት ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ሆነ” (ዮሐ. 1፡17)። ሐዋሪያው ጳውሎስ ከዮሐንስ በላይ በጸጋ አስተምህሮ ላይ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ስንመለከት የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናትም በጸጋ ላይ የተለየ ትኩረት ቢሰጡ አያስደንቅም።

“በክርስቶስ ኢየሱስ ስላመናችሁ በተሰጣችሁ በእግዚአብሔር ጸጋ ምክንያት ሁልጊዜ ስለ እናንተ አምላክን አመሰግናለሁ፤” (1ቆሮ. 1፡4)

“ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።” (1ቆሮ.15፡10)

“የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።” (2ቆሮ. 13፡14)


ይቀጥላል...


ምንጭ፦ "ተሐድሶ" ቅጽ-1፤ በጸጋአብ በቀለ፤ ከገጽ 230-243





ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

31 Oct, 14:25


ርዕስ፦ "፺፭ቱ የማርቲን ሉተር መከራከሪያ ነጥቦች"




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

31 Oct, 13:30


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

31 Oct, 11:28


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እንግዲህ ኀጢአታችሁ እንዲደመሰስ ንስሓ ግቡ፤ ከመንገዳችሁም ተመለሱ፤ ከጌታም ዘንድ የመታደስ ዘመን ይመጣላችኋል፤”
ሐዋርያት 3፥19 (አዲሱ መ.ት)




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

31 Oct, 09:09


#ተሐድሶ




የተሐድሶ እና የመነቃቃት ልዩነት (Reformation vs Revival)


መነቃቃት ተሐድሶ አይደለም፤ ተሐድሶም መነቃቃት አይደለም። በተለምዶ ብዙውን ጊዜ እነዚህ ሁለት የተለያዩ ጽንሰ አሳቦች እንደ አንድ አሳብ ሲቀርቡ ይታያሉ። ሁለቱ አሳቦች ተደጋጋፊና ለቤተክርስቲያን እጅግ በጣም አስፈላጊ ሲሆኑ ልዩነታቸውን ማወቅ ግን ግድ ይላል።

👉የመነቃቃትና የተሐድሶ ልዩነት በንጽጽር ቦቢ ግልያም እንዲህ አስቀምጠዋል፦

ቤተክርስቲያን አካል እንደሆነች አስቡ፤ በዚህም መሠረት መነቃቃት ለልብና ለአእምሮ ሕይወትና መታደስን እንደሚያመጣ ነው። ተሐድሶ ደግሞ የአካል አጥንቶችን እንደሚገጣጥም ነው። መነቃቃት የእምነትን፣ እሴቶችንና ውሳኔዎችን ለውጥ ያስገኛል። ተሐድሶ ደግሞ የባህሪ፣ የአወቃቀርና የትጥቅ ለወጥ ያመጣል። መነቃቃት ንጹህ ውሃ ወደ ውሃ ጉድጓድ መጨመር ነው። ተሐድሶ ደግሞ በውሃ ጉድጓድ ላይ ያሉትን ቀዳዳዎች መድፈን ነው። በመነቃቃትና በተሐድሶ መካከል ያለው የመጀመሪያ ልዩነት መነቃቃት በግለሰብ ደረጃ ሊጀምር የሚችል ሲሆን ውጤታማ ተሐድሶ ግን ከላይኛው የሥልጣን መዋቅር፣ ከቤተ ክርስቲያን አመራር ወይም ከአንድ ቤተ እምነት ይጀምራል።


Revival is an ongoing experience in the life of every believer. Since our natures are fallen, the Holy Spirit leads us to spiritual renewal every day. God’s mercies are new every morning (Lam. 3:23). God daily pours out fresh supplies of His grace and power on those who kneel before His throne. Spending time in His presence we are changed. The psalmist cried out, “I am afflicted very much; revive me, O Lord, according to Your word” (Ps. 119:107, NKJV).

Reformation is the outgrowth of revival. New Testament writers used different words to describe reformation. The apostle Paul called it “sanctification by the Spirit” (2 Thess. 2:13). In Romans he described it as being “transformed by the renewing of your mind” (Rom. 12:2). In Hebrews the apostle urged us to be “partakers of His holiness”(Heb. 12:10). Peter encouraged believers to “grow” in grace (2 Peter 3:18). John defined it as practicing “righteousness” (1 John 2:29).

Reformation is simply choosing to allow the Holy Spirit to realign our lives with biblical values; to submit to God’s will in every area of our lives. It is the commitment to please God in everything we do; the willingness to make any change necessary to live in harmony with God’s commands. Ellen White defined revival and reformation this way: “Revival and reformation are two different things. Revival signifies a renewal of spiritual life, a quickening of the powers of mind and heart, a resurrection from spiritual death. Reformation signifies a reorganization, a change in ideas and theories, habits and practices. Reformation will not bring forth the good fruit of righteousness unless it is connected with the revival of the Spirit. Revival and reformation are to do their appointed work, and in doing this work they must blend” (Selected Messages, book 1, p. 128).



ምንጭ፦ ተሐድሶ ቅጽ-1 በጸጋአብ በቀለ ከገጽ 29-33፣ revivalandreformation.org፣ Selected Messages, book 1, p. 128



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

30 Oct, 20:21


#ተሐድሶ


መጽሐፍ ቅዱስ የተሐድሶ (Reformation) መጽሐፍ ነው። ብሉይ ኪዳን በእግዚአብሔር የተፈጠረው ፍጹም ሰው፣ ከመውደቁ የተነሳ፣ ፍጥረተ ዓለሙ በኃጢአትና በሰይጣን ግዞት ውስጥ ያሳለፉትን መራራ፣ ጨላማና ያረጀ የቀድሞ ሕይወት ይወክላል። አዲስ ኪዳን ደግሞ በሰይጣን መታለል ወድቆ  የኃጢአት ግዞተኛ የሆነውን የሰው ልጅና ፍጥረተ ዓለሙን ሊያድስ ትልቅ የሕይወት ዋጋ ስለከፈለው ስለ ኢየሱስ ይተርካል።

ተሐድሶ

👉የሕያውነት ምልክት ነው።
👉የልጅነት ኪዳን ነው።
👉በሰው ድካም የእግዚአብሔር ኃይል
     የሚገለጥበት መንገድ ነው።
👉የእግዚአብሔር ቃል መለወጥ
     ሳይሆን ሰዋዊና እንደ ቃሉ ያልሆኑ
     አደናቃፊ ሰዋዊ ሥርዓት መለወጥ
     ነው።
👉ሰው ያለመቻሉን ለፈጣሪው
     በማሳወቅ ትዕቢቱን የሚሽርበት
     መንገድ ነው።
👉አሮጌ ነገራችን በአዲስ የሚተካበት
     ድንቅ ሂደት ነው።
👉የመክበር እንጂ የመዋረድ ምልክት
     አይደለም።
👉የእግዚአብሔርን ትክክለኛነት የሰውን
     ስህተተኝነት የሚያመለክት ሚዛን
     ነው።

በዓለማችን ላይ ተሐድሶ የማያስፈልጋት የክርስቶስ ቤተክርስቲያን የለችም። ተሐድሶ የብሉይ ኪዳን ቁልፍ ትምህርት ነው። እንደገና ካልተሰራን እንደገና መስራት አንችልም።

ተሐድሶ የሚለው ቃል የግዕዝ ቃል ሲሆን፣ የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ተሐድሶን በገቢር ግስ (ሐደሰ) ሲፈታው፦ ማደስ፣ መለወጥ፣ ሐዲስ ማድረግ፣ ማጥናት ፣ ማበረታታት፣ መስራት፣ መጠገን፣ በተጨማሪም አዲስ ነገር ማውጣት፣ መፍጠር ነው።

ተሐድሶ የሚለውን የአማርኛ ቃል፣ ኢንግሊዘኛው በሶስት ቃል (Reformation, Renewal, Restoration) በማለት ያብራራል። አንድ በአንድ ስንመለከታቸው፦

፩. Re-formation፦ እንደገና መስራት፣ እንደገና መለወጥ፣ የሚል አንድምታ ሲኖረው፣ በግሪክ ደግሞ “ዳዮርቶሲስ” (Diorthosis) የሚል ቃል ነው። ትርጉሙም የተበላሸውንና የተመሰቃቀለውን ነገር በትክክለኛ ቦታ ሥርዓት አስይዞ ማስቀመጥን፣ ወደ ቀድሞ ይዞቱ መመለስን፣ የቀድሞውን ፈር የለቀቀውን አዲስ ሥርዓት ማስያዝን ያመለክታል።

፪. Re-newal፦ ማደስ፣ የቀድሞውን መልክና ውበት መመለስ፣ የዚህ ቃል መሠረት "አናካይኖ" (Anakaino) የሚል የግሪክ ቃል ሲሆን፣ ትርጉሙም አዲስ ማድረግ ማለት ነው።

፫. Re-storation፦ ወደ ቀድሞ ሥፍራ ወይም ባለቤት መመለስ። ይህ ቃል "አካታስታቶስ" (Akatastatos) ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን፣ ስፍራውን የለቀቀውን፣ የተሰረቀውን፣ የተወሰደውን ወደ ሥፍራው መመለስን ያመለክታል።



🗞ምንጭ፦ ተሐድሶ ቅጽ-1 በጸጋአብ
                    በቀለ ከገጽ 22-27




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

30 Oct, 12:19


🔜 Coming soon...

👉ተሐድሶ (Reformation) ምንድነው? መሠረቶቹስ
👉ተሐድሶ ያስፈልጋል ወይስ አያስፈልግም?
👉ተሐድሶ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው ወይስ በተለምዶ የመጣ?
👉የሉተር ተሐድሶ የክርስቶስን ቤተክርስቲያን ጎዳ ወይስ ጠቀመ?
👉"ፕሮቴስታንት" ማለት ምን ማለት ነው?



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

30 Oct, 10:42


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ኢየሱስ፦ ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው።”
ዮሐንስ 5፥8



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

29 Oct, 11:17


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በመኝታቸው ላይ ሆነው ያለቅሱ ነበር እንጂ በልባቸው ወደ እኔ አልጮኹም፤ ስለ እህልና ስለ ወይን ጠጅ ይሰበሰቡ ነበር፤ በእኔም ላይ ዐመፁ።”
ሆሴዕ 7፥14




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

28 Oct, 23:40


#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?


ሐዋርያት 13
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁶ እናንተ ወንድሞቻችን፥ የአብርሃም ዘር ልጆች ከእናንተ መካከልም እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፥ ለእናንተ የዚህ የመዳን ቃል ተላከ።
²⁷ በኢየሩሳሌም የሚኖሩ ሰዎችና አለቆቻቸው እርሱንና በየሰንበቱ የሚነበቡትን የነቢያትን ድምፆች ስላላወቁ በፍርዳቸው ፈጽመዋልና፤
²⁸ ለሞትም የሚያደርስ ምክንያት አንድ ስንኳ ባያገኙበት፥ ይገድለው ዘንድ ጲላጦስን ለመኑት፤
²⁹ ስለ እርሱም የተጻፈውን ሁሉ በፈጸሙ ጊዜ ከእንጨት አውርደው በመቃብር አኖሩት።
³⁰ እግዚአብሔር ግን ከሙታን አስነሣው፤
³¹ በሕዝብም ዘንድ ምስክሮቹ ለሆኑት ከእርሱ ጋር ከገሊላ ወደ ኢየሩሳሌም ለወጡት ብዙ ቀን ታያቸው።
³² እኛም ለአባቶች የተሰጠውን ተስፋ የምስራቹን ለእናንተ እንሰብካለን፤
³³ ይህን ተስፋ እግዚአብሔር በሁለተኛው መዝሙር ደግሞ፦ አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወለድሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ኢየሱስን አስነሥቶ ለእኛ ለልጆቻቸው ፈጽሞአልና።
³⁴ እንደገናም ወደ መበስበስ እንዳይመለስ ከሙታን እንደ አስነሣው፥ እንዲህ፦ የታመነውን የዳዊትን ቅዱስ ተስፋ እሰጣችኋለሁ ብሎአል።
³⁵ ደግሞ በሌላ ስፍራ፦ ቅዱስህን መበስበስን ያይ ዘንድ አትሰጠውም ይላልና።
³⁶ ዳዊትም በራሱ ዘመን የእግዚአብሔርን አሳብ ካገለገለ በኋላ አንቀላፋ፥ ከአባቶቹም ጋር ተጨምሮ መበስበስን አየ፤
³⁷ ይህ እግዚአብሔር ያስነሣው ግን መበስበስን አላየም።
³⁸-³⁹ እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፥ በእርሱ በኩል የኃጢአት ስርየት እንዲነገርላችሁ፥ በሙሴም ሕግ ትጸድቁበት ዘንድ ከማይቻላችሁ ሁሉ ያመነ ሁሉ በእርሱ እንዲጸድቅ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

28 Oct, 13:57


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው።”
ዮሐንስ 3፥19



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

27 Oct, 22:13


👉ርዕስ፦ የዮሐንስ ወንጌል የጥናት መምሪያ እና ማብራሪያ
በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ትመማ) መልክ የተዘጋጀ
ጸሐፊ፦ ሉዊስ ቢክስቢ እና ቲም ፌሎስ
🗣ትርጉም፦ መስፍን ተስፋዬ
እርማት፦ ፍቃዱ ገብሬ
🖨አሳታሚ፦ SIM Publishing



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

27 Oct, 22:13


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

27 Oct, 18:55


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አቤቱ፥ ቀኝህ በኃይል ከበረ፤ አቤቱ ቀኝህ ጠላቱን አደቀቀ።”
ዘጸአት 15፥6



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

27 Oct, 11:51


#እራሳችንን_እንመርምር


ስለመንፈሳዊ ነገር እና በእግዚአብሔር ቤት እንዴት መኖር እንደሚገባ ማወቅ አስፈላጊነት እንዴት ታዩታላችሁ? በእርግጥ ቅዱሳት መጻሕፍት ስለዚህ ነገር ምን ይሉናል?

“ስለ መንፈሳዊ ነገርም፥ ወንድሞች ሆይ፥ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 12፥1

“ብዘገይ ግን፥ በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤ ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።”
1ኛ ጢሞቴዎስ 3፥15



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

26 Oct, 18:44


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ሳሙኤልም አደገ፥ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ነበረ፤ ከቃሉም አንዳች በምድር ላይ አይወድቀም ነበር።”
1ኛ ሳሙኤል 3፥19



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

25 Oct, 21:51


https://www.youtube.com/watch?v=mb_MamlcHlw


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

25 Oct, 11:11


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እንግዲህ ሕግን በእምነት እንሽራለንን? አይደለም፤ ሕግን እናጸናለን እንጂ።”
ሮሜ 3፥31



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

24 Oct, 15:19


#እንወያይ


የፕሮቴስታን ተሐድሶ ከፈነዳ 500 ዓመታትን ከዘለቀ ሰነበተ። ኦክቶበር 31፣ 1517 እ. ኤ.አ ማርቲን ሉተር 95ቱን መከራከሪያ ነጥቡን ሲለጥፍ ጅማሮውን አገኘ። ይህ መሠረት በማድረግ የቻናላችን ቤተሰቦች የሆናችሁ ፕሮቴስታንት፣ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ ወይም የሌላ ወገን የሆናችሁ ይህ ተሐድሶ ምን አመጣ? ጠቀመን ወይስ ጎዳን? ጠንካራ እና ደካማ ጎኖቹን በቅንነት እና በጨዋነት ከመጽሐፍ ቅዱስ አንጻር እየገለጽን እንወያይ።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

24 Oct, 11:17


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በምንም ነገር አትናወጡ። ለጌታ ሥራ ዘወትር የምትተጉ ሁኑ፤ ምክንያቱም ለጌታ የምትደክሙት በከንቱ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ።”
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥58 (አዲሱ መ.ት)




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

24 Oct, 08:26


#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?



2ኛ ጢሞቴዎስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ አንተ ግን ትምህርቴንና አካሄዴን አሳቤንም እምነቴንም ትዕግሥቴንም ፍቅሬንም መጽናቴንም ስደቴንም መከራዬንም ተከተልህ፤
¹¹ በአንጾኪያና በኢቆንዮን በልስጥራንም የሆነብኝን የታገሥሁትንም ስደት ታውቃለህ፤ ጌታም ከሁሉ አዳነኝ።
¹² በእውነትም በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ።
¹³ ነገር ግን ክፉዎች ሰዎችና አታላዮች፥ እያሳቱና እየሳቱ፥ በክፋት እየባሱ ይሄዳሉ።
¹⁴ አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤
¹⁵ ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል።
¹⁶-¹⁷ የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

23 Oct, 11:42


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤”
2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥14



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

23 Oct, 10:05


ራስን መግዛት - ትልቁ ስልጣን


"የመንፈስ ፍሬ ግን . . .  ራስን መግዛት ነው፡፡" ገላ. 5:22፣ 23

የመንፈስ ቅዱስ ፍሬ የክርስትና ሕይወት እውነተኛ ባህሪ ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በገላ. 5:22-23 ዘጠኝ የተለያየ ገጽታ ያሏቸውን ፍሬዎች ጠቅሷል፡፡ አንድ ሰው የሚሰጡትን መንፈሳዊ ስጦታዎችና መክሊቶች ተጠቅሞ ለእግዚአብሔር ስለሚሠራው ሥራ የመንፈስ ፍሬ በቀጥታ የሚነግረን ነገር ባይኖረውም ነገር ግን ግለሰቡ እንዴት ለእግዚአብሔር ሊኖር እንደሚገባ በግልጽ ያሳየናል፡፡ ስለ ግለሰቡ ማንነት ፍንጭ ይሰጠናል፡፡ በገላ. 5፡22-23 የተጠቀሱት ሁሉም መልካም ምግባሮች በኢየሱስ ውስጥ ተገልጠው መታየት ችለዋል፡፡ በመሆኑም የመንፈስ ፍሬ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት እውን መሆን የቻለው በእኛ ውስጥ በሚኖረው የኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት ነው፡፡ የመንፈስ ፍሬ በእኛ ውስጥ በሚከናወነው የመንፈስ ቅዱስ ስራ አማካኝነት የሚታይ የጸባይና የሕይወት ለውጥ ጭምር ነው፡፡ በእራሳችን የእግዚአብሔር ልጆች መሆን እንዳልቻልን ሁሉ በእራሳችን የባህርይ ለውጥ ወይም መንፈሳዊ ፍሬዎችን ማምጣት አንችልም፡፡

የመንፈስ ፍሬ ሙሉ ለሙሉ ሰብዓዊ በሆነ ጥረት ብቻ ልናገኘው የምንችለው ነገር አይደለም፡፡ “ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም በእናንተ የሚሠራ እግዚአብሔር ነውና።” (ፊል. 2፡13)  እኛ የእግዚአብሔር ልጆች የምናደርጋቸው ማንኛውም አይነት መልካም ነገሮች ሁሉ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ የሚሠራው ስራ ውጤት ናቸው፡፡

በክርስትና ሕይወት እውነተኛ ፍሬ የምናፈራበት ቀዳሚ ምስጢር በክርስቶስ መኖር ነው፡፡ እርሱ በእኛ፤ እኛ በእርሱ፡፡ ከክርስቶስ ውጪ እውነተኛ የመንፈስ ፍሬ ማፍራት አንችልም፡፡ የመንፈስ ፍሬ ከውጪ የሚጫንብን ነገር ሳይሆን በውስጣችን የሚኖረው የክርስቶስ ሕይወት ውጤት ነው፡፡ የመንፈስ ፍሬ--የወይኑ ግንድ ከሆነው ክርስቶስ፤ ቅርንጫፍ ወደ ሆኑት አማኞች የሚፈስ የእርሱ ሕይወት ውጤት መሆኑን ኢየሱስ በዮሐ. 15፡1-11 ይነግረናል፡፡ ፍሬውን የሚያሳድገው በኢየሱስ የሚሠራው አምላካዊ ሥራ ነው፡፡ የአማኙ ኃላፊነት በክርስቶስ መኖር ነው፡፡ ክርስቶስ ሃሳባችንን ሲሞላው በድርጊቶቻችን የሚገለጥ ይሆናል፡፡ ኢየሱስ በእኛ ውስጥ ሕያው ሆኖ ይኖራል፡፡ ክርስቶስ በእኛ ውስጥ የኖረው ህይወት በውስጣችን  ፍሬ ስለሚያፈራ በምላሹ የእርሱን ባህርይ የምናንጸባርቅና የምናሳይ እንሆናለን፡፡

ራስን መግዛት በገላትያ 5:22 ከተጠቀሱ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች አንዱ መሆኑን ብዙዎቻችን እናውቃለን። ሁላችንም ባንሆን አንዳንድ ጊዜ ራሳችንን መግዛት  አቅቶን  መሆን  የማይገባንን  ሆነን  ራሳችንን አሳዛኝና አላስፈላጊ ሁኔታዎች ውስጥ እናገኘዋለን።  ብዙ ጥፋትም አድርሰን እናውቃለን። ራስን መግዛት እንደየሰው ዓላማ የተለያየ ቢሆንም በሁሉም የሥራ እና የኃይማኖት መስክ የተወደደ ነገር ነው። ራስን ስለ መግዛት መማርና ኑሮውን መለማማድ ከባድ ቢሆንም ወደ እምነት ብስለት ይመራናል። መድኃኒት ይመራል ነገር ግን ጤንነትን ይሰጣል።

በአሁኑ ወቅት፣ ራስን ስለ መግዛት መወያታቸን አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

በዛሬው ጊዜ በሰዎች ላይ የሚደርሱት አብዛኞቹ ችግሮች የሚመነጩት ራስን ካለመግዛት ነው። አንዳንዶች ራሳቸውን መግዛት ስለሚያቅታቸው ከትምህርት ወይም ከሥራ ጋር በተያያዘ ዛሬ ነገ የማለት ልማድ የሚታይባቸው ከመሆኑም ሌላ የሚጠበቅባቸውን ነገር በትጋት ለማከናወን ይቸገራሉ። በተጨማሪም ራሳቸውን የማይገዙ ሰዎች ተሳዳቢዎች፣ ሰካራሞችና ዓመፀኞች ሲሆኑ፣ አላስፈላጊ ዕዳ ውስጥም ሊዘፈቁ እንዲሁም ለፍቺ፣ ለሱስ፣ ለእስር፣ ለስሜት ቀውስና ለዝሙት ተጋላጮች ናቸው፡፡ እነዚህ ችግሮች ራስን አለመግዛት ከሚያስከትላቸው መዘዞች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው። በግልጽ ማየት እንደሚቻለው ራሳቸውን መግዛት የሚያቅታቸው ሰዎች በራሳቸውም ሆነ በሌሎች ላይ ጉዳት ያስከትላሉ። የሚያሳዝነው ራስን የመግዛት ችግር ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ መምጣቱ ነው። አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ድርጊታቸው በራሳቸውም ሆነ በሌሎች ላይ የሚያስከትለውን መዘዝ ሳያገናዝቡ ፍጹም ባልሆነው ሥጋቸው ምኞት እየተነዱ ሕይወታቸውን እንዳሻቸው የሚመሩ ብዙዎች አሉ። ሰዎች ክፉ ነገር እንዲያደርጉ ለሚቀርብላቸው ጥያቄ እምቢ ለማለት አቅሙም ፍላጎቱም እንደሌላቸው ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በዘመናችን ጎልቶ ይታያል።

በዘመናችን ያለውም ባሕል ራስን መግዛትን አያበረታታም። እንደፈለጉ መሆንን በሚያበረታታው ባሕላችን አዋቂዎችም ሆንን ልጆች የፈለግነውን እንድናደርግ የሚያነሳሳ መልእክት ሁልጊዜ ይዥጎደጎድብናል። በቅን ልቦና ተነሳስተው ምክር የሚለግሱንም ሆኑ ለገንዘብ ሲሉ የማይረባ ምክር የሚሰጡን ሰዎች ምንጊዜም ስሜታችንን ማስተናገድ እንዳለብን ሲናገሩም እንሰማለን። በመጨረሻዎቹ "ቀናት” ውስጥ እንደምንኖር ከሚያሳዩት ምልክቶች መካከል አንደኛው ሰዎች “ራሳቸውን የማይገዙ” መሆናቸው ነው (2ኛ ጢሞ 3፥3)፡፡ በዚህ በመጨረሻው ዘመን ውስጥ ክርስቲያኖች እራሳቸውን ከሌሎች የሚለዩበትን አንዱን የሆነውን ራስን የመግዛት ባህሪን እያሳዩና እያንፀባረቁ መኖር አለባቸው፡፡

ራስን መግዛት ስንል ምን ማለታችን ነው?

ራስን መግዛት ከውስጣችን ሊወጣ የሚታገለንን ማናቸውንም የስጋ ፍላጎትና ምኞትን መቆጣጠርና መግዛት ራስን መግዛት ይባላል፡፡ ራስን መግዛት  ማለት ስሜትን መቆጣጠር፤ መሻትን ማሸነፍ፤ ሁለንተናን ለእግዚአብሔር ፈቃድና ክብር ማስገዛት ማለት ነው፡፡ ራስን መግዛት ከውስጥ የሚመነጩ እና ከውጭ የሚመጡ ግፊቶችን መቋቋም መቻል ነው፡፡ ራስን መግዛት ለቁጣ፣ ለቂም በቀልና ለጥላቻ፣ ለሥጋዊ ጥቅም፣ ለስካር . . .  ወዘተ በአምሮአችንና በልባችን ግፊት ከሚመጣ ፈተና ራስን ማዳን እና ለሌሌችም ምስክር መሆን ነው። ራስን መግዛት ብዙ የሥጋ  እና  የዓለም  ክብር  ግብዣዎችን እምቢ ማለት ነው፡፡ ራስን  መግዛት  በሀሳብ፣በቃላትና  በተግባር የሚገለጥ ነገር ነው።


ምንጭ፦ habtamumeressa.blogspot.com




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

22 Oct, 12:22


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“እግዚአብሔርን እንወቀው፤ የበለጠ እናውቀውም ዘንድ እንትጋ፤ እንደ ንጋት ብርሃን፣ በእርግጥ ይገለጣል፤ ምድርን እንደሚያረሰርስ የበልግ ዝናብ፣ እንደ ክረምትም ዝናብ ወደ እኛ ይመጣል።”
ሆሴዕ 6፥3 (አዲሱ መ.ት)




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

21 Oct, 20:52


የቀጠለ ...

የእግዚአብሔር ቃል እውቀት



የእግዚአብሔር ቃል እውቀት የሌላቸው ሰዎች ትክክለኛው መንገድ (ሃይማኖት) የቱ እንደሆነ መጠየቃቸው የተለመደ ነው፤ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥም የየትኛውም የሃይማኖት ድርጅት ስም ባለመጻፉ የትኛው ሃይማኖት ትክክል እንደሆነ ለማወቅ በመፈለግ ግራ ይጋባሉ፡፡ ነገር ግን ይህ ጥያቄም ሆነ ግራ መጋባት ሊመጣ የሚችለው የእግዚአብሔርን ቃል በጥልቀት ካለመረዳት ነው፤ ምክንያቱም እንደ እግዚአብሔር ቃል ስናስብ እግዚአብሔር ሰዎችን ሁሉ የሚጠራው ልጁን አምኖ ወደመከተል እንጂ ወደ የትኛውም የሃይማኖት ጎራ አይደለምና፡፡

ሰው ላለመሳሳት ከፈለገ ዛሬም ያለው አማራጭ የእግዚአብሔርን ቃል ማወቅና የተጻፈውን ሁሉ አንድም ሳይቀር አምኖ መቀበል ብቻ ነው፤ ይህ ካልሆነ ግን «መጽሐፍ ቅዱስ አለኝ፤ ከቤቴም አኑሬዋለሁ» ማለቱ ብቻውን ከስህተት አያድንም፤ ክብር ይግባውና ጌታ ኢየሱስም መጻሕፍቱ እያሏቸው በእምነት ነገር የሳቱ ፈሪሳውያንን «መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ» ብሎአቸው ነበር፤ (ማቴ.22፡29፣ ማር.12፡24)፡፡

በዕለታዊ ኑሮም ቢሆን ከስህተት የምንጠበቀው የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ሲኖረን ነው፤ መዝሙረኛው ዳዊት ስለዚህ ሲናገር «ጐልማሳ መንገዱን በምን ያነፃል? ቃልህን በመጠበቅ ነው» (መዝ.118፡9)፣ «አንተን እንዳልበድል ቃልህን በልቤ ሰወርኩ (ቊ.11)፣ «ሕግህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴ ብርሃን ነው» (ቊ.105) «ከቃልህ የተነሣ አስተዋልሁ፣ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ»(ቊ.104) ብሏል፡፡

2. ላለመጥፋት ይጠቅማል

በጥንት ዘመን እንደነበረ በመጽሐፍ የተመዘገበለት ነገር ግን በአሁን ጊዜ የሌለ የቀደመው ዓለም የጠፋው የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ስላልነበረው ነው፤ ከጥፋት ውኃ በፊት የነበረው ያ ዓለም ከሌሎች ሰባት ጋር ጽድቅን የሚሰብከውን ኖኅን ሊሰማው አልቻለም ነበር (2ጴጥ.2፡5)፤ «በዚህም ምክንያት ያን ጊዜ የነበረው ዓለም በውኃ ሰጥሞ ጠፋ» (2ጴጥ.3፡6)፤ ምክንያቱም አላዋቂነትን ወደው ነበርና (ምሳ.1፡22)፡፡ ግለሰብም ሆነ ሕዝብ እንዲሁም አገር የሚጠፉበት ዋነኛው ምክንያት የእግዚአብሔርን ቃል ካለማወቅ የተነሣ በሚፈጸሙ መንፈሳዊና ሥጋዊ በደሎች ነው፡፡ ሰው የጌታን ቃል ካላወቀ መጥፋቱ አይቀሬ ነው፡፡ በዚህ መልኩ ከበደሉ የተነሣ በእግዚአብሔር ፍርድ የሚጠፋ ሁሉ አስቀድሞውኑ የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ማጣቱ ከእግዚአብሔር ፊት ያጠፋው(ያራቀው) መሆኑ ግልጥ ነው፤ ከዚህም አንጻር ስለጠፉት ቤተ እስራኤል «ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአልና» ተብሎ ተነግሯል (ሆሴ.4፡6)፡፡ እዚህ ላይ ሕዝበ እስራኤልን የሚያስተምር ሰው አልነበረምን? ብሎ መጠየቁ መልካም ነው፤ እስራኤል የሚያስተምሯቸው መምህራን፣ መሥዋዕት የሚያቀርቡላቸው ካህናት፣ ትንቢት የሚናገሩላቸው ነቢያት እንደዚሁም የሚያነቧቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ነበሯቸው፡፡ ችግሩ ግን ነቢያት የሚናገሩትንና መጻሕፍት የሚመሰክሩትን የእግዚአብሔርን ቃል አውቀው አለመታዘዛቸው ነው፡፡ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስም ስለ አንድ ባለጠጋ ሰውና ስለደሃው አልዓዛር የተናገረው ታሪክ ሰው በእጁ ያሉትን መጻሕፍት በመጠቀም ከፍርድ የሚድንበትን የእግዚአብሔር ቃል እውቀት መያዝ እንደሚኖርበት ያስረዳል (ሉቃ.16፡27-31)፡፡ እንግዲህ ላለመጥፋት ከተፈለገ መፍትሔው የእግዚአብሔርን ቃል አውቆ መገኘት ብቻ ነው፡፡

3. ለሚጠይቁን ለመመለስ ይጠቅማል

ብዙውን ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል እውቀት በሚገባ ሳይኖር ሲቀር በእምነት ነገር አላዋቂ ከሆኑ ወይም ከማያምኑ ሰዎች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ መስጠት አይቻልም፡፡ ማንኛውም አማኝ ስለሚያምነው ነገር በተጠየቀ ጊዜ መልስ መስጠት ይችል ዘንድ የእግዚአብሔር ቃል ዕውቀት በሙላት ሊኖረው ይገባል፤ ስለዚህም መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር «የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ» ይላል (ቈላ.3፡16)፤ እንደዚሁም በሌላ ስፍራ «በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያት ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት የተዘጋጃችሁ ሁኑ» ይላል (1ጴጥ.3፡15)፤ ዳግመኛም «ለሚጠይቅህም እውነትን ቃል መመለስ ይቻልህ ዘንድ በምክርና በዕውቀት የከበረን ነገር አልፃፍሁልህምን?» የሚል እናነባለን (ምሳ.22፡21)፡፡

የቃሉ እውቀት አስተማሪ

ብዙዎች እንደሚያስቡትና እንደሚናገሩት መጽሐፍ ቅዱስ የተደበቀና የተሸሸገ ምሥጢር አይደለም፤ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ «የአፌ ቃላት ሁሉ ጽድቅ ናቸው፤ ጠማማ ዘወርዋራም አይደሉም፤ እነርሱ በሚያስተውሉ ዘንድ የቀኑ ናቸው፤ ዕውቀትንም ካገኙአት ሰዎች ጋር የተስማሙ ናቸው» ተብሎ ተነግሮአል (ምሳ.8፡8)፤ ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው እግዚአብሔርን በሚፈልግ እውነተኛ ልብ ሆኖ ቢያነበው የቃሉን እውቀት በመንፈስ ቅዱስ አስተማሪነት ይማራል (ዮሐ.14፡26)፤ ይህ አስተማሪም ሁሌ ከተማሪው አይለይም፤ በየትኛውም ሰዓትና ጊዜ እንዲሁም ቦታ ይህ አስተማሪ መጽሐፍ ቅዱስን የሚያነቡትን ሁሉ ሲረዳ ይኖራል፤ እርሱ የሚመጣና የሚሄድ አይደለም፤ ስለእርሱም «አስተማሪህ ከአንተ ከእንግዲህ አይሰወርም ... ጆሮችህ በኋላህ መንገድህ ይህች ናት በእርስዋም ሂድ የሚለውን ቃል ይሰማሉ» ተብሏል (ኢሳ.30፡21)፡፡ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ለጃንደረባው እንዳደረገው መንፈስ ቅዱስ ለአንባቢው መጻሕፍትን በማብራራት የሚመራውን ሰው ይልክለታል (ሐዋ.ሥራ8፡29-35)፡፡

ምንም እንኳ መታዘዝ ስለማንችል አእምሮአችን እንዳይወቅሰን መጽሐፍ ቅዱስን ባናነብ ይሻለናል የሚሉ ሰዎች ቢኖሩም ያለእግዚአብሔር እውቀት መኖራቸው ከተጠያቂነት ስለማያድናቸው መልካም አይሆንላቸውም፤ ምክንያቱም «ነፍስ ዕውቀት የሌላት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም» ተብሎአልና (ምሳ.19፡2)፡፡


ምንጭ:- ewnetone.com




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

21 Oct, 11:26


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“አሁን እኔ ጐሽ ለመባል የምሻው በሰዎች ዘንድ ነው ወይስ በእግዚአብሔር ዘንድ? ወይስ ሰዎችን ደስ ለማሰኘት እየተጣጣርሁ ነው? ሰዎችን ደስ ለማሰኘት የምጥር ብሆን ኖሮ፣ የክርስቶስ አገልጋይ ባልሆንሁ ነበር።”
ገላትያ 1፥10 (አዲሱ መ.ት)




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

20 Oct, 21:05


የእግዚአብሔር ቃል እውቀት




ዛሬ በዓለማችን በሃይማኖት ሽፋን ሕሊናን በመሸንገል ለሚመጣው መራራ ቅጣት ራስን የማዘጋጀት ዝንባሌ የሚታየው በእውቀትና በመረዳት ሳይሆን ከእግዚአብሔር ቃል ውጭ በሆነ ከንቱ ሐሳብ በመመራት እንደሆነ ይታያል፡፡ አንዳንድ ጊዜም የተሳሳተ የሃይማኖት ትምህርትን በእግዚአብሔር ቃል ለመደገፍ የሚደረገው ጥረትም ቃሉን ካለመረዳት የመነጨ መሆኑን እናስተውላለን፡፡

ብዙ ዓመታት ያስቆጠረ ውሸት እውነት ሊመስል ቢችል እንኳ ውሸትነቱ መገለጡ አይቀሬ ነው፤ ለዚህም ደግሞ እውነት የሚመስለውን ነገር ሁሉ መርምሮ ለማረጋገጥ ብቸኛው መሣሪያ ጊዜ የማይለውጠው ሕያው የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነው፤ እርሱ ለእኛ እንደ ወንፊት ነው፤ እንክርዳድ የሞላበትን የፈጠራ ትምህርት እንለይበታለን፤ እግዚአብሔር ይመስገን፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ቃል የያዘ ብቸኛና ታላቅ መጽሐፍ ነው፤ ይኸም መጽሐፍ የአባቶቻቸውን የቆየና የተሳሳተ መንገድ እንደ ጽድቅ ቆጥረው በመመካት ይጓዙ ለነበሩት የእስራኤል አዲስ ትውልድ ሲናገር «በአባቶቻችሁ ሥርዓት አትሂዱ፣ ወጋቸውንም አትጠብቁ፣ በጣዖቶቻቸውም አትርከሱ» በማለት ያስጠነቅቃል (ሕዝ.20፡18)፡፡

ጌታችን ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ቃል ዕውቀት ወደ ጐን በመተው የሰውን ሥርዓት በመጠበቅ ለእርሱ የሚቀኑ የሚመስላቸውን ሰዎች ደጋግሞ ገሥጿል፤ ባሕልና ወግን የሚሰብኩትን የሕግ መምህራንንም «የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል» (ማቴ.15፡9፣ ማር.7፡1-3) በማለት ተናግሯል፡፡ ይህም ንግግሩ እግዚአብሔርን እንደሚገባ ሳያውቁ የሚቀርብ አምልኮ ከንቱ መሆኑን ያስረዳል፡፡

እርግጥ ነው ለሰዎች ዓይን «መልካም የምትመስል መንገድ አለች፤ ፍጻሜዋ ግን ሞት ነው» እንደተባለው ከጥንት የኖረም ቢሆን እንደ እግዚአብሔር ቃል ያልሆነ መንገድ ሁሉ ፍጻሜው «ሞት» ብቻ ነው (ምሳ.16፡25)፡፡ ነገር ግን ሰው በጌታ በኢየሱስ ብቸኛ አዳኝነት ካመነ ከቀድሞ አባቶቹ ከወረሰው ከንቱ ኑሮ ይድናል፤ ጴጥሮስ ስለዚህ ነገር ሲጽፍ «ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን ነውርና እድፍ እንደሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክርስቶስ ደም እንደተዋጃችሁ ታውቃላችሁ» (1ጴጥ.1፡19) ብሏል፡፡

የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ጥቅሞች

የእግዚአብሔር ቃል በሰው አንደበት ተነግረው የማያልቁ ብዙ ጥቅሞች እንዳሉት ቃሉን የሚጠቀሙበት ሁሉ ያውቁታል፡፡
የእግዚአብሔር ቃል፦

👉አስተዋይ ለመሆን (መዝ.118፡98፣104)፣
👉ጌታን ላለመበደል (መዝ.118፡11)፣
👉በሥራችን መከናወንን ለማግኘት (ኢያ.1፡7-9)፣

👉የልብ ደስታን ለማግኘት (ኤር.15፡16)፣
👉ለበጎ ሥራ ለመዘጋጀት (2ጢሞ.3፡15)፣
👉ለትምህርታችን (ሮሜ.15፡3-4)፣
👉የክፋት መንፈሳዊ ሠራዊትን ለመዋጋት (ኤፌ.6፡10)፣ ይጠቅማል፡፡ እንደዚሁም የእግዚአብሔር ቃል እውቀት በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ቀጥሎ በዝርዝር የምንመለከታቸው ሌሎች ጥቅሞችም አሉት፡፡

1. ላለመሳሳት ይጠቅማል

ሁላችንም የሔዋን መሳሳት እንዴት እንደነበረ እናውቃለን፤ የሔዋንም የመጀመርያ ጥፋቷ ፍሬ ቆርጣ መብላቷ አልነበረም፤ ቀዳሚው ጥፋቷ ከፈጣሪ ቃል ይልቅ የፍጥረትን ድምፅ ማዳመጧ ነበር፡፡ ይህም ድምፅ ፍጹም ወዳጅና ተቆርቋሪ ከሚመስል ጠላት የመጣ ነበር፡፡ ማስጠንቀቂያ ከታከለበት የጌታ ቃል ይልቅ ማባበያ የተሞላው የፍጥረት ድምፅ አሳታት፡፡ ዛሬም ጠላት በምንም ዓይነት ጽድቅን ፊት ለፊት ተቃውሞ አይሰብክም፡፡ ግማሽ እውነት ግማሽ ውሸት በዘመኑ የሚሠራበት የሰይጣን ብልሃት መሆኑ ከታወቀ ውሎ አድሮአል፤ አንድ የቲያትር ተዋናይ(አርቲስት) ገጸ ባሕርይውን መስሎ ለመታየት ብዙ ነገሮችን ሊያደርግ ይችላል፤ ለምሣሌ ሰው ሰራሽ ፂም ሊያደርግ ረዥም ቀሚስ ሊለብስ ይችላል፤ አስመስሎም ይናገራል፤ ነገር ግን ያንን የወከለውን ነገር መሆን አይችልም፤ ከለበሳቸው አልባሳት ውስጥ ያለው ራሱ ነውና፡፡ በመሆኑም እንዲህ ካለው የሰይጣን ማታለል ለመዳን የሚቻልበት ብቸኛው መሣሪያ የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ነው፡፡ ሰዎችም ቢሆኑ በተመሣሣይ መንገድ የክርስትናን መልክ ተላብሰው ሊያታልሉ ሲሞክሩ አሁንም መፍትሔው ያው የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ነው፡፡


ይቀጥላል...



ምንጭ:- ewnetone.com




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

20 Oct, 14:35


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ክፉ ከሆነ ከአሁኑ ዓለም ያድነን ዘንድ እንደ አምላካችንና እንደ አባታችን ፈቃድ ስለ ኃጢአታችን ራሱን ሰጠ።”
ገላትያ 1፥4



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

20 Oct, 13:45


#እራሳችንን_እንመርምር

በሕይወታችን የሚያደናቅፍ ነገር በሞላበት አልፎም ተርፎ ስንፍገመገም የሚያቆም እና የሚያጸና በሚፈለግበት ጊዜ ረድኤት እና መድኃኒት ከየት ይገኛል?

"ሕግህን የሚወዱ ፍጹም ሰላም ያገኛሉ፤ ሊያደናቅፋቸውም የሚችል አንዳች ነገር የለም።"
መዝሙር 119፥165 (ሕያው ቃል)




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

19 Oct, 18:49


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ከአፉም ሕጉን ተቀበል፥ በልብህም ቃሉን አኑር፤”
ኢዮብ 22፥22




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

19 Oct, 13:36


👉ርዕስ፦ የትንቢተ ኢሳይያስ የጥናት መምሪያ እና ማብራሪያ በትምህርተ መለኮት ማስፋፊያ (ት.መ.ማ) መልክ የተዘጋጀ
ጸሐፊ፦ ቲም ፌሎውስ
🗣ትርጉም፦ ግርማዊ ቡሾ
🖨አሳታሚ፦ ኤስ አይ ኤም (SIM Publishing)



ይህ በጣም ሰፊ የሆነ በትንቢተ ኢሳይያስ ላይ የሚያተኩረው የጥናት መምሪያ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ በተሰማሩ ሰዎች ላይ ሲሆን የጥናት መምሪያውን በብዙ የተለያዩ መንገዶች መጠቀም ይቻላል።

👉በግል የእግዚአብሔርን ቃል ለማጥናት
👉በአዋቂዎች የሰንበት ትምህርት ቤት ወይም
👉በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት መጠቀም ይቻላል።



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

19 Oct, 13:36


ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

18 Oct, 10:58


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዘላለም ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ ለጥቂት ጊዜ መከራን ከተቀበላችሁ በኋላ ራሱ ፍጹማን ያደርጋችኋል ያጸናችሁማል ያበረታችሁማል።”
1ኛ ጴጥሮስ 5፥10



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

17 Oct, 20:37


ነቢዩ ኤርምያስ




                        ክፍል-


በኢዮአቄም የዐሥራ አንድ ዓመት ዘመነ መንግሥት ውስጥ የከርከሚሽ ጦርነት ተካሄደ (ከ46 ፥ 2 ጋር ያነጻ)፡፡ በመካከለኛው ምሥራቅ የኀይል ሚዛን ከግብፅ ወደ ባቢሎን መተላለፉን ያመላከተ ስለ ሆነ፣ ዘላቂ ፋይዳ ያለው ሁኔታ (ክሥተት) ነበር፡፡ ይህ ሽንፈት በግብፅ የመስፋፋት ምኞት ላይ የመጨረሻ በትር ሲሆን፤ ከለዳውያን በምዕራቡ ዓለም ላይ የበላይነት እንዲኖራቸው ዋስትናን ሰጠ፡፡ ይህ ሁኔታ ለዘመኑ ወደ ዐዲስ ምዕራፍ መሸጋገሪያ ነበር፤ ለእስራኤልም የወደፊት ዕጣ ፈንታ ዐቢይ ሚና ነበረው፡፡ ባቢሎናውያን ኢዮአቄምን በሥልጣናቸው ሥር ገዥ (መስፍን) አልባ አደረጉት፤ ጥቂት የማይባሉትን የአይሁድ መሳፍንት ያጋዙ ሲሆን (2ነገ 24 ፥ 1)፣ ከእነዚህ ከተጋዙት መካከል ዳንኤል አንዱ ነበር (ዳን 1፥1)፡፡

አንዳንድ ሊቃውንት በናቡደነፆር ይህ የኢየሩሳሌም ለመጀመሪያ ጊዜ መወሰድ የአይሁድ የሰባ ዓመት፣ የባቢሎን ግዞት መጀመሪያ ነው ይላሉ (25፥11)፤ ከዚህም ጋር የዳዊት ሥርወ መንግሥት መፍረስ ጀምሮ ነበር፡፡

ኢዮአቄም የጣዖት አምልኮን ደገፈ፤ በመንግሥቱ በሰፊው ይካሄድ ለነበረው ማኅበራዊ ኢፍትሓዊነትም ደንታ አልነበረውም (22 ፥ 13-19 2ነገ23፥37)፡፡ ኤርምያስ በዘመነ ንግሣቸው ትንቢቱን መናገር ከቀጠለባቸው ነገሥታት መካከል ኢዮአቄም የእግዚአብሔር መልእክትና የእግዚአብሔር መልእክተኛ ደመኛ ጠላት ነበር (ከ26 ፥ 20-23 ፤ ከ36 ፥ 20-26)፡፡ በ598-597 በባቢሎን ላይ ዐመፀ፤ ነገር ግን አልተሳካለትም፤ ከዚህም የተነሣ የይሁዳን መከራ አባባሰው (2ነገ 24 ፥ 1-5)፡፡ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት ኤርምያስ ሥቃይ ደረሰበት፤ አሤሩበት፤ በከንቱ ስሙ ጠፋበት፤ ታሰረም፡፡ ንጉሡ የተጻፈውን ትንቢት አወደመበት፤ ነቢዩ ግን ከመለኮታዊ ተልእኮው አልተነቃነቀም (ከ11፥ 18-23 ፤ ከ12 ፥ 6፤ ከ15፥15-18፤ ከ18፥18፤ ከ20 ፥ 2 ፤ ከ26፥ 10-11:24፤ ከ36፥ 23)፡፡ ኤርምያስ እንደ ተነበየው (22 ፥ 18-19) ኢዮአቄም በዐሥራ አንደኛው ዓመት የሥልጣን ዘመኑ 598-597 በኢየሩሳሌም በዐመፅ ሞተ፡፡ ኢዮአቄም በናቡከደነፆር ሥልጣን ዘመን ወደ ባቢሎን መጋዙን የዜና መዋዕል ጸሓፊ አስፍሮአል (2ዜና 36፥6-7፤ እንዲሁም ዳን 1፥1)፡፡

(መ) ኢዮአኪን፤

የኢዮአቄምን ዙፋን የወረሰው ልጅ ኢዮአኪን ነው እንዲሁም ኢኮንያንና ኮንያ ይባላል [አዲሱ መደበኛ ትርጉም በ22 ፥ 24፤ በ24፥1 ላይ ያለውን ይመልከቱ]፤ በዙፋን ላይ የቈየውም ሦስት ወር ብቻ ነው (ከ2ነገ 24፥8)፡፡ ነገር ግን ይህ በዐሥራዎቹ የዕድሜ ዘመኑ መግዛት የጀመረው ንጉሥ ጨካኝ ንጉሥነቱን ጒልሕ አስኪያደርግ ድረስ በሥልጣን ላይ ቈየ፤ ይህንኑ ጨካኝ ንጉሥም ኤርምያስ በብርቱ አወገዘው (22፥24-30)፡፡ በባቢሎን ላይ የኢዮአኪን አባት ያካሄደው ዐመፅም በ597 ናቡከደነፆር ኢየሩሳሌምን እንዲወርር አስገደደው፤ ይህም ኢዮአኪን መሸነፉን አምኖ በተቀበለ ጊዜ ነበር (2ነገ 24፥17)፡፡ እርሱም ከብዙ የይሁዳ ገዥ መደቦች ጋር (ከእነርሱ መካከል ነቢዩ ሕዝቅኤል ይገኝ ነበር [ሕዝ 1፥2] ወደ ባቢሎን ተጋዘ፤ ቤተ መቅደሱም ተመዘበረ (2ነገ 24 ፥ 10-16)፡፡ ኢዮአኪን ሠላሳ ሰባት ዓመት ሙሉ በባቢሎን እስረኛ ነበር፡፡ በክፉው በአልጋ ወራሹ፤ በናቡከደነፆር ልጅ በዮርማሮዴቅ ከእስራት ነጻ ሆነ (2ነገ 25 ፥ 27-30)፡፡ አይሁድ እርሱ በዳዊት ዙፋን ላይ ተመልሶ ይነግሣል ብለው ለረዥም ዘመናት ባልተለመደ ሁኔታ ተስፋ ያደርጉ ነበር፡፡ ሕዝቅያስም ንጉሥ ሆኖ በእግሬ ይተካል ያለው ሴዴቅያስን ሳይሆን ኢዮአኪንን ነበር፡፡

(ሠ) ሴዴቅያስ፤

ታላቁ ናቡከደነፆር ካከናወናቸው አያሌ ተግባሮች መካከል ንጉሥ አድርጎ መሾምና ስም መለወጥ ይገኛ ሉ፡፡ ናቡከደነፆር ኢዮአኪንን ካጋዘ በኋላ የኢዮስያስን ልጅ ፤ የኢዮአኪንም አጎት የሆነውን ማታንያንን በይሁዳ ዙፋን ላይ አስቀመጠው፤ ስሙንም ሴዴቅያስ ብሎ ለወጠው (2ነገ 23 ፥ 34 ፤ 24 17: 2ዜና 36 10 ኤር 13) ይህም ሐቅ በባቢሎናውያን ዜና መዋዕል የተረጋገጠ ነው፡፡ የሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት ገና እንደ ተጀመረ፣ ይሁዳ ተከታታይ ወረራና ግዞት የደረሰበት ሲሆን፣ ገዦች በተለዋወጡ ቊጥር ተሸራርፎ የቀረው መንግሥት የሊቃውንት መኻን ሆኖአል፡፡ ሲዴቅያስ ደካማ፣ ወላዋይ፣ መልካም ሰብእናም የጐደለው ሰው ነበርና ውጤታማ አስተዳደርን እውን ለማድረግ ከዐቅሙ በላይ ሆኖ አገኘው፡፡ የባቢሎን አሻንጉሊት ሆኖ ለንጉሡ ታጥቆ ለመኖር በእስራኤል አምላክ ስም የማለ ሲሆን፣ በማንኛውም ውሳኔው ላይ አፍቃሬ ግብፅ በሆኑት ሹሞቹ ተጽዕኖ ሥር የሚገኝ ሰው ነበር፡፡

የእግዚአብሔር ሰው የነበረውን ኢዮስያስን አቈይተን፣ ሴዴቅያስ ከኤርምያስ ጋር የነበረው ግንኙነት ቀደም ካሉት የይሁዳ ነገሥታት ይልቅ በጣም የጠበቀ ነበር፡፡ ሆኖም ኤርምያስን ከመሳፍንቱ ተንኰለኛ ዕቅድ ለመጠበቅና ለናቡከደነፆር ይገዙ ዘንድ ኤርምያስ በተደጋጋሚ ይፋ ያደረገውን ከእግዚአብሔር የተቀበለውን ምክር ለመከተል ዐቅም የነበረው ሰው አልነበረም፡፡ ሴዴቅያስ በነገሠ በአራተኛው ዓመት ከኤዶም፣ ከሞዓብ፣ ከአሞን፣ ከጢሮስና ከሲዶን ነገሥታት ጋር ግምባር በመግጠም (27-3-11): በባቢሎን ላይ ዐመፀ:: ተወካዮችን ወደ ኢየሩሳሌም ሲልኩም ዐላማቸው ይህ ነበር፡፡ ይህን ሤራ ኤርምያስ አወገዘው፤ በመጨረሻም ይኸው ሤራ ከንቱ ሆኖ ቀረ:: በዚያው ዓመት ሴዴቅያስ ባቢሎንን የጐበኘበት ምክንያት፣ ታማኝነቱን ለናቡከደነፆር ለመግለጽ ታልሞ ሳይሆን አይቀርም (51፥ 59)፡፡


ይቀጥላል...


🚨ማሳሰቢያ የጊዜ አቆጣጠር ካልተጠቀሰ በቀር ዓመተ ቅድመ ክርስቶስ ነው።



ምንጭ፦ የብሉይ ኪዳን ማብራሪያ፤ ገጽ 825-826




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

17 Oct, 11:32


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ለእናንተም የምነግራችሁ ለሁሉ እላለሁ፤ ትጉ።”
ማርቆስ 13፥37



ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

17 Oct, 04:53


#የእግዚአብሔር_ቃል_ምን_ይላል?



1ኛ ጢሞቴዎስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ማንም ኤጲስ ቆጶስነትን ቢፈልግ መልካምን ሥራ ይመኛል የሚለው ቃል የታመነ ነው።
² እንግዲህ ኤጲስ ቆጶስ እንዲህ ሊሆን ይገባዋል፤ የማይነቀፍ፥ የአንዲት ሚስት ባል፥ ልከኛ፥ ራሱን የሚገዛ፥ እንደሚገባው የሚሰራ፥ እንግዳ ተቀባይ፥ ለማስተማር የሚበቃ፥
³ የማይሰክር፥ የማይጨቃጨቅ ነገር ግን ገር የሆነ፥ የማይከራከር፥ ገንዘብን የማይወድ፥
⁴ ልጆቹን በጭምትነት ሁሉ እየገዛ የራሱን ቤት በመልካም የሚያስተዳድር፤
⁵ ሰው ግን የራሱን ቤት እንዲያስተዳድር ባያውቅ፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን እንዴት ይጠብቃታል?
⁶ በትዕቢት ተነፍቶ በዲያብሎስ ፍርድ እንዳይወድቅ፥ አዲስ ክርስቲያን አይሁን።
⁷ በዲያብሎስ ነቀፋና ወጥመድም እንዳይወድቅ፥ በውጭ ካሉት ሰዎች ደግሞ መልካም ምስክር ሊኖረው ይገባዋል።
⁸ እንዲሁም ዲያቆናት ጭምቶች፥ በሁለት ቃል የማይናገሩ፥ ለብዙ ወይን ጠጅ የማይጎመጁ፥
⁹ ነውረኛ ረብ የማይወዱ፥ በንጹሕ ሕሊና የሃይማኖትን ምሥጢር የሚይዙ ሊሆኑ ይገባቸዋል።
¹⁰ እነዚህም ደግሞ አስቀድሞ ይፈተኑ፥ ከዚያም በኋላ ያለ ነቀፋ ቢሆኑ በዲቁና ሥራ ያገልግሉ።
¹¹ እንዲሁም ሴቶች ጭምቶች፥ የማያሙ፥ ልከኞች፥ በነገር ሁሉ የታመኑ ሊሆኑ ይገባቸዋል።
¹² ዲያቆናት ልጆቻቸውንና የራሳቸውን ቤቶች በመልካም እየገዙ እያንዳንዳቸው የአንዲት ሴት ባሎች ይሁኑ።
¹³ በዲቁና ሥራ በመልካም ያገለገሉ ለራሳቸው ትልቅ ማዕርግና በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው እምነት ብዙ ድፍረት ያገኛሉ።
¹⁴ ፈጥኜ ወደ አንተ እንድመጣ ተስፋ አድርጌ ይህን እጽፍልሃለሁ።
¹⁵ ብዘገይ ግን፥ በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤ ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።
¹⁶ እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ።




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

16 Oct, 11:02


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን።”
ቆላስይስ 4፥6




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

15 Oct, 11:22


.    ==❀❀❀===❀❀❀==      
              የዕለቱ ጥቅስ 
     ==❀❀❀===❀❀❀==
“ልቤን ወደ ክፉ ነገር አትመልሰው፥ ዓመፅን ከሚያደርጉ ሰዎች ጋር ለኃጢአት ምክንያት እንዳልሰጥ፤ ከምርጦቻቸውም ጋር አልተባበር።”
መዝሙር 141፥4




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures

ቅዱሳት መጻሕፍት

14 Oct, 20:58


#ከተማ_ወይም_ቦታ_በቅዱሳት_መጻሕፍት



#ቤትአዌን

ቤት-አዌን(በዕብራይስጥ ቤይት አቨን፣ בֵּית אָוֶן፣ የከንቱነት ቤት፣ ማለትም የክፋት፣ ጣዖት አምልኮ ቤት። በብንያም ተራሮች በቤቴል በስተምስራቅ የሚገኝ ቦታ ነው። 1ሳሙ 13፡5፣ በኢያሱ 18፡12 ላይ የቤተ-አዌን “ምድረ በዳ” (ሚድባር = የግጦሽ መሬት) በሚል ተጠቅሷል። በሆሴዕ 4:15፣ ሆሴዕ 5:8፣ ሆሴዕ 10፡5፣ ስሙ በዚህ ነቢይ በተገለጸው ቃል መሠረት ወደ አጎራባች ቤቴል - አንድ ጊዜ “የእግዚአብሔር ቤት” ወደ ነበረው፣ ከዚያ በኋላ ግን “ከንቱ” ወደሚለው የጣዖት ቤት ተላልፏል። ታልሙዲስቶች በየቦታው ቤቴል-አቨንን ከቤቴል ጋር አንድ እንደሆኑ ያወራሉ (ኮምፕ ሽዋርዝ፣ ፓለስት ገጽ 89) ይህ ቅርበት ቃሉ በቅጽል ስምነት ተቆጥሮ ሊሆን ይችላል፤ ማለትም ቤቴል የወርቅ ጥጆች አምልኮ መቀመጫ ከሆነች በኋላ ማለት ነው። ይሁን እንጂ ቤተ-አዌን የሚለው ስም በትክክል ከቤቴል (ኢያሱ 7፡2፣ ወዘተ.) የተለየ አካባቢ ነበር፣ እና ከደቡብ-ምስራቅ ሀያ ደቂቃዎች በስተደቡብ-ምስራቅ በምትገኘው ቋጥኝ ቡርጅ ቤቲን ላይ በምትገኝ መንደር ላይ ያለ ይመስላል። ቤቲን (ቤቴል)፣ እና ከቴል ኤል-ሃጃር (አይ) በስተ ምዕራብ ሀያ ደቂቃ (Van de Velde፣ Memoir፣ p. 294) የሚገኝ ስፍራ ነው።


ምንጭ፦ www.biblicalcyclopedia.com




ወደ ቻናሉ ለመ🀄️🀄️ል፦ @Holy_scriptures