Ministry of Finance - Ethiopia @ministry_of_finance Channel on Telegram

Ministry of Finance - Ethiopia

@ministry_of_finance


Welcome to the Official Telegram Account of the Ministry of Finance #Ethiopia.

Ministry of Finance - Ethiopia (English)

Welcome to the Official Telegram Account of the Ministry of Finance #Ethiopia. This channel serves as the primary source for all information related to the Ministry of Finance in Ethiopia. Whether you are a citizen, a business owner, or just interested in the economic landscape of the country, this channel is the place to be. Stay updated on the latest fiscal policies, budget allocations, economic reports, and more. Get exclusive insights from government officials, financial experts, and industry professionals. Join a community of like-minded individuals who are passionate about the financial well-being of Ethiopia. The Ministry of Finance is committed to transparency, accountability, and economic growth. By following this channel, you will have access to reliable information that will help you make informed decisions and understand the financial landscape of Ethiopia. Don't miss out on this opportunity to stay informed and engaged with the Ministry of Finance. Join us today and be part of the conversation! #Ethiopia #Finance #Economy

Ministry of Finance - Ethiopia

30 Jan, 09:35


የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ማኔጂንግ ዳይሬክተር በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው
ጥር 22 / 2017 ዓ.ም - የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ ከየካቲት 1 አስከ 2 / 2017 ዓ.ም ለሁለት ቀናት በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ፡፡
ባለስልጣኗ ከከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት የሚያደርጉ ሲሆን ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ እ.ኤ.አ በ2019 የተቋሙ ኀላፊ ከሆኑ በኋላ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ሲያደርጉ ይህ የመጀመሪያቸው መሆኑ ታውቋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ከከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እድገት፣ ቅድሚያ በሚሳጣቸው ፖሊሲዎች እና በኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ዙሪያ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
ዳይሬክተሯ በጉብኝታቸው ወቅት ከግሉ ዘርፍ ተወካዮች ጋር በኢትዮጵያ ስላለው የንግድ ሁኔታ እና በኢኮኖሚ እድሎች ዙሪያ ውይይት የሚያካሂዱ ከመሆኑም በተጨማሪ በሀገሪቱ በማህበራዊ ልማት የተሰሩ ስራዎችን እነደሚጎበኙ ታውቋል፡፡

Ministry of Finance - Ethiopia

29 Jan, 18:28


The Minister expressed gratitude to the Bank for the comprehensive financial and technical support to Ethiopia. The current portfolio reflects over USD 17 billion in investments across various sectors.
His Excellency gave an update on the bold macroeconomic reforms the country has undertaken, He discussed ongoing reforms in the tax and financial sectors to create a favorable investment climate and reaffirmed the Ethiopian government’s commitment to sustain its efforts in this area.
The Minister also congratulated the Bank and its donors on the robust IDA21 Replenishment. Ms. Bjerde commended Ethiopia for its successful implementation of macroeconomic and financial sector reforms and related gains to date, while reaffirming the World Bank’s commitment to continue supporting these initiatives. The Managing Director also highlighted the need for deepening the reforms to respond to the needs of the private sector.

Ministry of Finance - Ethiopia

29 Jan, 18:27


H.E. Ato Ahmed Shide meets with Ms. Anna Bjerde, World Bank’s Managing Director for Operations and Mrs. Victoria Kwakwa, Regional Vice President for Eastern and Southern Africa.
Today, January 29, 2025, H.E. Ato Ahmed Shide, Ethiopia’s Minister of Finance, met with World Bank delegation led by Ms. Anna Bjerde, the Managing Director for Operations at the World Bank to discuss development cooperation in Ethiopia.
H.E. Ato Ahmed Shide congratulated the World Bank on the successful conclusion of the Mission 300 Energy Summit held in Tanzania earlier this week. The Bank, in collaboration with other development partners, is working on Mission300 to reduce by 50% the population of Africa without access to electricity by 2030, which aims to bring light to 300 million people on the continent. His Excellency emphasized that energy is central to Ethiopia's economy, highlighting the country's vast potential for renewable energy generation and a key sector for collaboration with World Bank.

Ministry of Finance - Ethiopia

15 Jan, 09:33


መንግስት ለነዳጅ ድጎማ እያደረገ በመሆኑም ከዓለም እና ከጎረቤት ሀገራትም ባነሰ ዋጋ እየቀረበ ይገኛልም ነው ያሉት።
ይህን በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚገባ ነዳጅ በከፍተኛ ጥንቃቄ ማቅረብ እና በቁጠባ መጠቀም ይገባል ያሉት ሚኒስትሩ፤ በዚህ ረገድ ያለውን ህገወጥ ንግድ እና ኮንትሮባንድ ለመከላከል ግብረ-ኃይል ተቋቁሟል ብለዋል።
የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ከፍተኛ ቅድመ ዝግጅት ተደርጎበት ወደ ትግበራ መግባቱን የጠቀሱት ሚኒስትሩ በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ተጎጂ እንዳይሆኑ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
ለዚህም 400 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት በማሳወጅ ነዳጅን ጨምሮ ማዳበሪያ፣ መድሀኒት፣ ዘይት እና ስኳር ከውጪ ሀገር ተገዝተው ለህብረተሰቡ በድጎማ እየቀረቡ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
ከዚህ ውስጥ 82 ቢሊዮን ብር ለአፈር ማዳበሪያ ግዢ ድጎማ፤ 60 ቢሊዮን ብር ደግሞ ለከተማና ገጠር ሴፍቲኔት ድጋፍ ይውላል ብለዋል።
ዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ ለሆኑ ሰራተኞችም ማሻሻያ መደረጉንም አንስተዋል።
ሌሎች ሀገራት መሰል ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሲተገብሩ ይህን አይነት ድጋፍ ሲያደርጉ አይታይም ያሉት የገንዘብ ሚኒስትሩ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በህብረተሰቡ ላይ ጫና እንዳይደርስ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት ከፍተኛ ሀላፊነት የሚሰማው መንግስት መሆኑን የሚያመለክት ነው ብለዋል።
ለማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ስኬት ዘላቂነትም መንግስት በየጊዜው ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ በብሔራዊ ማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ በኩል የሚያከናውናቸውን የክትትልና ድጋፍ ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ በሰጡት መግለጫ አመልክተዋል።

Ministry of Finance - Ethiopia

15 Jan, 09:32


መንግስት በየዓመቱ 4.5 ቢሊዮን ዶላር በማውጣት ከውጭ ሀገር የሚያስገባውን ነዳጅ ለህብረተሰቡ በድጎማ እያቀረበ ነው
ባለፉት ዓመታት ለነዳጅ ድጎማ ብቻ ከ267 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል - የገንዘብ ሚኒስቴር
*********************
ኢትዮጵያ ወደ ተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ ከገባች በኋላ ትግበራውን ማሳካት የሚያስችሉ የተለያዩ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ተናግረዋል።
አሁን ላይ በሀገሪቱ ውስጥ ያለው የእድገት እንቅስቃሴ የተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ያነሱት ሚኒስትሩ፤ የተለያዩ የኢኮኖሚ አመላካቾችም ይህንን በሚገባ እንደሚያሳዩ ነው በሰጡት መግለጫ ያመለከቱት።
ከተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ትግበራ ወዲህ የገቢ አሰባሰብ ማደጉ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት በከፍተኛ ደረጃ መሻሻሉ፣ የወጪ ንግድ የተሻለ አፈፃፀም የታየበት መሆኑ፣ የባንኮች ቁጠባ እያደገና ለኢኮኖሚው የሚያቀርቡት ብድርም በጠንካራ ሁኔታ ላይ መገኘቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ ለአብነት ጠቅሰዋል።
ማሻሻያውን ከግብ ለማድረስም ከልማት አጋሮች ጋር ያለው ትብብር ተጠናክሮ ቀጥሏል ነው ያሉት።

Ministry of Finance - Ethiopia

10 Jan, 11:35


የፌዴራልና የክልሎች የፋይናንስ፣ የገቢዎች፣ የፕላንና ልማት 29ኛው የምክክር መድረክ ተጀመረ
ጥር 2/ 2017 ዓ.ም - የምክክር መድረኩ በዋናነት ተግባራዊ እየተደገ ባልው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም፣ በመንግስት ፋይናንስ አሰተዳደር ስርዓት፣ በሀገራዊ የልማት እቅድ እና በገቢ ዘርፍ በተስሩ ስራዎች ላይ በማተኮር በጅማ ከተማ ተጀምሯል
በምክክር መድረኩ ላይ የመከፍቻ ንግግር ያደረጉት የገንዘብ ሚንስትር ክቡር አቶ አሕመድ ሽዴ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ በማድረግ ላይ መሆኗን አስታውሰው የሀገር ውስጥ ገቢን ማሳደግ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ላይ በመመስረት ዘላቂና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ሀገሪቱ ቅድሚያ የሰጠቻቸውን የልማት ፕሮግራሞች ፋይናንስ ለማድረግ ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ሲሉ ተናግረዋል፡
መንግስት የወጪ በጀትን በዋናነኛነት በሀገር ውስጥ ገቢ በመሸፈንና የበጀት ጉድለት ዝቅተኛ እንዲሆን በማድረግ ለኢኮኖሚ ዕድገት ምቹ የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታን ለማስፈን እየሰራ ይገኛል ሲሉ ክቡር ሚኒስትሩ ገልጸው የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ውጤታማነት በማረጋገጥ ረገድ ከፌዴራል እስከ ታችኛው የመንግስት መዋቅር ድርስ ርብርብ ማደረግ ይጠበቅብናል ሲሉ አሳስበዋል፡፡
በምክክር መድርኩ የመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ማሻሻያ ስራዎች ያመጡት ለውጦች ተገምግመው የተገኙት ውጤቶች አበረታች ቢሆኑም ለውጡን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ተመላክቷል፡፡

Ministry of Finance - Ethiopia

09 Jan, 16:25


በገንዘብ ሚኒስትሩ ክቡር አቶ አሕመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልሎች የፋይናንስ፣ የገቢዎችና የፕላን ልዑካን ቡድን የጋራ ምክክር መድረክ ለማካሄድ ጅማ ከተማ ገባ

Ministry of Finance - Ethiopia

30 Dec, 09:18


Quotation From the Interview of H.E Dr. Eyob Tekalign, State Minister of Finance, with Billene Seyoum, Press Secretary for Office of Prime Minister of Ethiopia, at Ethiopia in Focus

Ministry of Finance - Ethiopia

27 Dec, 14:24


The Reform of SOEs (State-Owned Enterprises) is committed to enhance efficiency and financial stability.
Restructuring and reform of critical SOEs like Ethio Telecom, is restoring operational efficiency and profitability.
Emphasis was given to institutional reforms to establish financially sustainable and globally competitive SOEs are promising.
Strengthening institutions to ensure continuity and sustainability beyond party or government transitions are Building Resilient
Regarding Long-Term Vision, Economic and Social Integration
Ethiopian economic development and growth endeavor is Anchored in the 10-year development plan, homegrown economic reform agenda and recently issued macroeconomic reform program.
Economic reforms are aimed at ensuring equitable opportunities and substantive freedoms for all citizens.
Ethiopia aims to become an African success story, akin to the Asian Tigers, by leveraging cultural and economic strengths.
Concerning Debt Management and Fiscal Discipline
External debt-to-GDP ratio cut from 30% in 2018 to 13%, showcasing significant progress in debt reduction.
The government is Committed to avoid transferring debt burdens to future generations.
The Public Finance Reforms focus on addressing historical inefficiencies and wastage in public spending.
The Sovereign Wealth Fund focuses on establishment of a fund to manage assets effectively, pay off debts, and create resources for future generations.

Ministry of Finance - Ethiopia

27 Dec, 14:24


The Highlights of H.E Dr. Eyob Tekalign, State Minister of Finance, Interview with Billene Seyoum, Press Secretary for Office of Prime Minister of Ethiopia, at Ethiopia in Focus.

The Key Takeaway of the interview.
Ethiopia's macroeconomic and economic reforms reflect a transformative agenda focused on debt reduction, institutional strengthening, and economic diversification. These reforms are underpinned by a long-term vision of inclusive growth, global competitiveness, and sustainable prosperity.
On Economic Growth and Diversification
The GDP of Ethiopia and per capita income doubled over the past five years.
The national Revenue Growth is tripling driven by reforms and improved economic governance.
Dynamic expansion in agriculture and manufacturing sectors is diversifying the economy.

Ministry of Finance - Ethiopia

26 Dec, 10:51


የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ቁልፍ ዓላማዎች

Ministry of Finance - Ethiopia

06 Dec, 10:58


የገንዘብ ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት ሰራተኞችና አመራሮች 19ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አከበሩ

ህዳር 27 2017 ዓ.ም - የገንዘብ ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት ሰራተኞችና አመራሮች 19ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል "አገራዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አድነት!” በሚል መሪ ቃል አክብረዋል፡፡

በበዓሉ አከባበር ላይ ተገኘተው የመክፍቻ ንግግር ያደረጉት የገንዘብ ሚኒስቴር ሚንስትር ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ ፌዴራሊዝም ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በሕዝቦች ፍላጎትና ምርጫ የጋራ የሆነ የፖለቲካ ሥርዐት ለመገንባት የሚያስችል አስተሳሰብ ወይም አማራጭ ሀሳብ ነው ሲሉ ተናገረዋል፡፡

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ብዝኃነት መገለጫቸው በሆኑ አገራት ኅብረ ብሔራዊ ፌዴራል ሥርዐት ለሁሉም ማንነቶች ዕውቅና በመስጠት፤ አካባቢያቸውን በአቅምና ፍላጎታቸው መሠረት እንዲለሙ እድል በመሰጠት ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታል ሲሉ አቶ አህመድ ገልጸዋል፡፡

በዓሉን አሰመልክቶ የመወያያ ሰነድ ቀረቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን በበአሉ ማጠቃለያ ላይ ክቡር ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ኢትዮጵያውያን ብዝሀነታችንን መሰረት አድረገን የምናከብረው ታላቅ በአል መሆኑን አመለክተው ኢትዮጵያውያን የጋራ ሀገራችንን በጋራ መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

Ministry of Finance - Ethiopia

28 Nov, 12:01


ክቡር ሚኒስትሩ አያይዘውም የእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ፋይናንስ የሚያደርግ ግዙፍ ተቋም በመሆኑ አዲሱን የኢትዮጵያን ኤርፖርት ግንባታና የታዳሽ ሀይል ፕሮጀክቶችን ፋይናንስ እንዲያደርግ መጠየቃቸውንና በነዚህ ዘርፎች አብሮ ለማስታት ስምምነት ላይ መደረሱንም ገልጸዋል፡፡
የእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ፕሬዚዳንት ሚስተር ጂን ሊኩን በበኩላቸው ኢትዮጵያን ለመጀመሪያ ጊዜ መጎብኘታቸውና ከገንዘብ ሚኒስትሩ ከክቡር አቶ አህመድ ሺዴ ጋር ፍሪያማ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸው የእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ከኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ባንኩ በኢትዮጵያ ልማት ላይ ከአለም ባንክ፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክና ከሌሎች ባለድርሻ አካለት ጋር በአገርነት ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ አመልክተው በኢትዮጵያ የወደፊት ብሩህ ተስፋ እምነት እንዳላቸውና ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት መልከሙን ሁሉ እንደሚመኙ ገልጸዋል፡፡

Ministry of Finance - Ethiopia

28 Nov, 12:01


የገንዘብ ሚኒስትሩ ከእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ
ህዳር 19 / 2017 ዓ.ም - የገንዘብ ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሺዴ ከእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ፕሬዚዳንት ሚስተር ጂን ሊኩን ጋር በኢትዮጵያ መንግስትና በባንኩ መካካል ያለውን ትብብር በማጠናከር ላይ ያተከረ ውይይት አደረጉ፡፡
ሚኒስትሩ በእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክና በገንዘብ ሚኒስቴር መካካል ስለሚኖረው ትብብር ከባንኩ ፕሬዚዳንት ጋር በስፋት መወያየታቸውን ገልጸው ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገቷን ለማፋጠን በተለይ አንደ ሀገር እየተሰራ ባለው የረጅም ጊዜ የእድገት ፕሮግራም፣ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም፣ የግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚ እድገት ላይ ስላለው ሚና፣ ምቹ የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታ ለመፍጠር ስለሚደረገው ጥረት በስፋት መመካከራቸውን አስረድተዋል፡፡

Ministry of Finance - Ethiopia

27 Nov, 13:42


የገንዘብ ሚኒስትር ድኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከ ሸገር 102.1 ራዲዮ ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ

Ministry of Finance - Ethiopia

18 Nov, 11:22


This meeting marked a significant step towards fostering collaboration and knowledge exchange between the two nations, with the hope of replicating Ethiopia's success in South Sudan.

Ministry of Finance - Ethiopia

18 Nov, 11:22


She emphasized the significant role that social protection programs have played in reducing poverty in Ethiopia. Over the past two decades, these programs have been instrumental in supporting citizens, thanks to the commitment of both the Ethiopian Government and its development partners.
During the discussions, presentations were made regarding the budget, financial flows, and the organizational arrangements of the social protection programs. These insights covered the distribution of resources from the federal to the woreda level, ensuring that beneficiaries receive the support they need. The World Bank team also praised the Ethiopian government's leadership and dedication to implementing these programs effectively.

In conclusion, the South Sudanese delegation expressed their gratitude to the Ethiopian government for successfully implementing the social protection programs and for their commitment to continue funding these initiatives.

Ministry of Finance - Ethiopia

18 Nov, 11:21


South Sudan Delegation Visits Ethiopia's Social Protection Programs

On November 15, 2024, a delegation from South Sudan visited Ethiopia to learn about its current social protection programs. The delegation was led by Hon. Aya Benjamin Warille, Minister of Gender, Child and Social Service of South Sudan. The primary goal of their mission was to understand the implementation arrangements and financial mechanisms that support Ethiopia's social protection initiatives. The meeting was also attended by representatives from the World Bank, highlighting the global interest in these programs.

State Minister H.E Ms. Semereta Sewasew of Ministry of Finance has warmly welcomed the delegation and commended their efforts to learn from Ethiopia's experiences.

Ministry of Finance - Ethiopia

31 Oct, 14:25


H.E. Semereta Sewasew highlighted e-commerce as a catalyst for economic growth and youth employment, emphasizing the transformative potential of digital platforms in providing Ethiopian youth with new job opportunities and enhancing their role in the digital economy. She stated, “By harnessing platforms like AliExpress, we can expand job prospects for our young people, support innovation, and open new avenues for trade and investment. This partnership signals a strong commitment to establishing Ethiopia as a key player in the global e-commerce arena.”
In line with Ethiopia's ongoing initiatives to modernize logistics and position itself as a regional e-commerce hub, this partnership with AliExpress complements existing projects, including Ethiopian Airlines' newly established e-commerce hub. AliExpress’s entry is expected to enhance Ethiopia’s logistics capabilities by benchmarking best practices in supply chain management, customs processing, and delivery efficiency, providing valuable insights and learning opportunities for Ethiopia’s customs and logistics sectors.

Ministry of Finance - Ethiopia

31 Oct, 14:25


Ethiopia Expands E-Commerce Sector in Partnership with AliExpress, Fostering Youth Employment and Logistics Development
Addis Ababa, Ethiopia - October 30, 2024 – H.E. Semereta Sewasew, State Minister of Finance, held a strategic discussion with the Director of Key Accounts from Alibaba International Digital Commerce Group – AliExpress, alongside their respective teams, at the Ministry of Finance. This meeting marks a pivotal step in advancing Ethiopia’s e-commerce landscape as AliExpress officially launches its services in the country, focusing on job creation, local partnerships, and building Ethiopia’s technology, supply chain, and logistics infrastructure.

Ministry of Finance - Ethiopia

28 Oct, 10:57


The Minister expressed the government’s commitment to further deepen efforts to boost private sector investment, including in the energy, manufacturing, logistics, and telecom sectors with the aim to foster sustainable growth.
The two agencies commended Ethiopia’s efforts to create an enabling environment for investment while underscoring the importance of sustained efforts required to further improve the investment climate and unlock the full potential of private sector-led development.

Ministry of Finance - Ethiopia

28 Oct, 10:56


Ethiopia’s Finance Minister His Excellency Mr. Ahmed Shide meets with the International Finance Corporation & Multilateral Investment Guarantee Agency on the sidelines of the 2024 World Bank and IMF Annual Meetings
The high-level Ethiopian delegation, led by Minister Ahmed Shide, had fruitful exchanges with IFC’s Managing Director Mr. Makhtar Diop and MIGA’s Vice President Mr. Ethiopis Tafara on Ethiopia’s homegrown macroeconomic reform and ways to deepen strategic collaboration for private sector development.
The meetings discussed Ethiopia’s efforts and reforms to boost private sector investments, including recent opening of the retail, financial and other sectors to international investors.
H.E Ato Ahmed briefed the counterparts on the implementation of the homegrown macroeconomic reform and the positive early signs of progress, including positive business sentiment from private investors.

Ministry of Finance - Ethiopia

25 Oct, 13:24


The US counterparts on their side, commended the achievements of the reform to date, including the protection provided to vulnerable households during the reform transition period acknowledging the critical high level political leadership, and assured continued advocacy and support of the US for the timely resolution on the debt negotiations through the Global Sovereign Debt Roundtable and bilaterally.
The 2 sides agreed to deepen the US-Ethiopia partnership using bilateral as well as multilateral channels, including cooperation through the IMF and WB.

Ministry of Finance - Ethiopia

25 Oct, 13:24


Ethiopian delegation led by H.E Ahmed Shide held Bilateral discussions with the US State Department and Treasury
On the sidelines of the 2024 WB-IMF Annual Meetings, the Ethiopian delegation led by Finance Minister H.E. Ahmed Shide held bilateral discussions with US Assistant Secretary of State for African Affairs Ambassador Molly Phee and the Assistant Secretary for US Treasury for International Affairs Brent Neiman.
H.E. Ahmed Shide briefed the US officials on the current economic and political situation as well as on the progress of the Government’s macroeconomic economic reform, and the crucial support needed from development partners, to support Ethiopia’s efforts to finalize the debt treatment negotiations under the G20 Common Framework.

Ministry of Finance - Ethiopia

25 Oct, 12:33


Dr Eyob also presented an innovative approach to the debt restructuring process by establishing a clear timeline requiring conclusion of the debt restructuring within six months following the approval of an IMF program by the board. Participants of the Round Table agreed on the need to ensure the efficiency, timelines and predictability of the debt restructuring process.

Ministry of Finance - Ethiopia

25 Oct, 12:33


The Ethiopian delegation attending the IMF/WB annual meeting has participated on the Global Sovereign Debt Roundtable
The Ethiopian delegation attending the IMF/WB annual meeting has participated on the Global Sovereign Debt Roundtable (GSDR)co-chaired by IMF Managing Director Kristalina
Georgieva, World Bank President Ajay Banga, and Finance Minister of Brazil Fernando Haddad(G20 chair). The GSDR deliberated on how to make the debt restructuring process more effective.
Speaking at the Round Table, State Minister of Finance Dr. EYOB Tekalign shared Ethiopia’s debt restructuring experience. In this connection, he underscored the criticality of making interim debt suspension arrangements automatic when countries are making good faith efforts to resolve their debt issues.

Ministry of Finance - Ethiopia

10 Sep, 15:44


ለመላው ኢትዮጵውያን እንኳን ለ2017 አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ፡፡ አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤናና የብልፅግና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡
አህመድ ሽዴ
የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር

Ministry of Finance - Ethiopia

09 Sep, 07:24


ጳጉሜን 4፤ 2016 - የኅብር ቀን
“ኅብረት ለሰላማችን"

Ministry of Finance - Ethiopia

08 Sep, 06:53


ጳጉሜን 3 የሉዓላዊነት ቀን - “ኀብር ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት”

Ministry of Finance - Ethiopia

07 Sep, 07:35


ጳጉሜን 2 የሪፎርም ቀን ሪፎርም ለላቀ አገልግሎት!

Ministry of Finance - Ethiopia

05 Sep, 15:27


በቻይና-አፍሪካ ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የገንዘብ ሚኒስቴር አቶ አህመድ ሽዴ በኢትዮጵያ እና ቻይና መካከል በሚደረጉ የንግድ ልውውጦች ላይ የሁለቱ ሀገራት ገንዘቦች ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚያስችል ስምምነት መደረሱን ገልፀዋል።

Ministry of Finance - Ethiopia

05 Sep, 14:27


ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ የሚሆነውን የኤሌክትሪክ እና የውሀ ፍጆታ መጠን ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 1021/2016

Ministry of Finance - Ethiopia

29 Aug, 11:47


2. የትራንስፖርት አገልግሎት

በተመሳሳይ መልኩ እንደ ውሃና ኤሌክትሪክ አገልግሎት የትራንስፖርት አገልግሎትም ላለፉት 22 ዓመታት ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ እንዲሆን የተደረገው አነስተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል ለትራንስፖርት የሚያወጣው ወጪ እንዳይንር እንዲሁም በጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚከፈለው ታክስ የዕቃዎችን ዋጋ መናር እንዳያስከትል በማሰብ ነበር፡፡
ሆኖም ከህዝብ እና የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት ውጪ ለሌሎች የትራንስፖርት አገልግሎቶች የዚህ አይነቱን ድጋፍ ማድረግ ተገቢ ባለመሆኑ፣ መንግስት ማህበረሰቡ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎትን እንዲጠቀም የተለያዩ ድጋፎችን በመስጠት እያበረታታና መሰረተ ልማቶችንም እየገነባ በመሆኑ ለትራንስፖርት አገልግሎት የተሰጠው ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የመሆን መብት ባለሶስት እግር ተሽከርካሪን ሳይጨምር ከስምንት መቀመጫ በታች ያላቸውን ሌሎች ተሽከርካሪዎች እንዳይመለከት ተደርጓል፡፡

ስለዚህ መንግስት አሁንም የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት አቅርቦቶችን ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ያደረገ ሲሆን ባለሦስት እግር ተሽከርካሪን ሳይጨምር፣ አሽከርካሪውን ጨምሮ ከስምንት ሰው በታች የመጫን አቅም ያላቸውን ተሽከርካሪዎች በመጠቀም የሚሰጥ የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲከፈልበት አድርጓል።

Ministry of Finance - Ethiopia

29 Aug, 11:46


በአዲሱ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2016 በውሃ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል እና በትራንስፖርት አቅርቦት ላይ ስለሚከፈል የተጨማሪ እሴት ታክስ

1. የውሃ እና የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት

የኤሌክትሪክ እና የውሃ አቅርቦት ላለፉት 22 ዓመታት ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ተደርጎ የነበረው አነስተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል ያለበትን የወጪ ጫና ለማርገብና ለማቃለል ታስቦ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ከአንድ ቤተሰብ ወርሃዊ አማካይ ፍጆታ በላይ ኤሌክትሪክ እና ውሃን በብዛት የሚጠቀመው የመክፈል አቅም ያለው የህብረተሰብ ክፍል በመሆኑ በተሰጠው መብት ይበልጥ ተጠቃሚ የሆነው ይህ የህብረተስብ ክፍል ነው፡፡ ይህ የህብረተሰብ ክፍል ታክሱ የሚያስከትልበት የወጪ ጫና ስለሌለ ድጋፉ ትርጉም አልነበረም፡፡

ድጋፉ ታሳቢ ያደረገውን የህብረተሰብ ክፍል ብቻ በሚጠቅም መልኩ ማስተካከያ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የመሆኑ መብት ተፈጻሚ የሚሆነው የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ መሰረት የሚወሰን ከአንድ ቤተሰብ ወርሃዊ ፍጆታ ያልበለጠ የኤሌክትሪክ እና የውሃ ፍጆታ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ ይህንን መጠን የሚወስን መመሪያ በጥቂት ቀናት ውስጥ ወጥቶ ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል፡፡

ስለዚህ መንግስት አነስተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል በመኖሪያ ቤቱ የሚጠቀመውን አማካይ ወርሃዊ የውሃና ኤሌክትሪክ ፍጆታ ከታክሱ ነፃ የሚያደርግ ሲሆን ከታክሱ ነፃ ከተደረገው በላይ የውሃና ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተፈፃሚ እንዲሆን ያደርጋል፡፡

Ministry of Finance - Ethiopia

23 Aug, 09:40


የገንዘብ ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል መርሀ ግብር አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ፡፡
ነሐሴ 17 / 2016 ዓ.ም - የገንዘብ ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሀ ግብር ላይ በመሳተፍ በአዲስ አበባ ከተማ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሜቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማህበር አካባቢ አራንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ፡፡
የገንዘብ ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሺዴ አረንጓዴ አሻራቸውን ካኖሩ በኋላ እንደገለጹት ላለፉት ተከታታይ አመታት በተካሄደው ሀገር አቀፍ አረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሀግብር የላቀ ሀገራዊ ንቅናቄና ህዝባዊ ተሳትፎ የታየበት መሆኑን ጠቁመው በዛሬው ዕለት በመላው ኢትዮጵያ በሚካሄደው በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዮን ችግኞች የመትከል መርሀ ግብር ላይ የገንዘብ ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ የማኖር አካል በመሆናችን ደስታ ይሰማናል ብለዋል፡፡
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ በበኩላቸው አረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሀ ግብር በሀገር ደረጃ ሁሉም ዜጎች የሚሳተፉበት ሀገር አቀፍ ንቅናቄ መሆኑን ጠቅሰው ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋንን ማስፋት ምርትና ምረታማነትን በማሳደግ ለሀገር ልማትና ኢኮኖሚያዊ እድገት የላቀ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰውም በስፍራው ተገኝተው አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡

Ministry of Finance - Ethiopia

12 Aug, 10:22


የተወሰኑ ሺህ የማይሞሉ ነጋዴዎችን ለመጠበቅ ስንል፤ በሀገር በቀል ነጋዴ ስም ሚሊዮኖችን የጎዳ የንግድ ሰርዓት ይዘን መቀጠል የለብንም፡፡ የንግድ ስርዓቱ ለውድድር ክፍት መሆን አለበት፡፡ ጎረቤት ሀገራት ያለ አንድ ዕቃ ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለ ዕቃ ፤ የበለጠ የሚወደድበት ምንም ምክንያት የለም፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ

Ministry of Finance - Ethiopia

30 Jul, 20:04


The Agreements were signed between H.E. Mr. Ahmed Shide, Minister, Ministry of Finance, and Ms. Maryam Salim, World Bank Country Director for Ethiopia, Eritrea, Sudan, and South Sudan representing the Government of Ethiopia and the World Bank, respectively.

Ministry of Finance - Ethiopia

30 Jul, 20:04


Since becoming a founding member of the World Bank, Ethiopia has benefited from the Bank's unwavering support, which has spanned various administrations and developmental phases. The past five years have seen a remarkable intensification of this support, making the World Bank the largest source of development finance. Currently, Ethiopia accesses over USD 2 billion annually in concessional financing from IDA, with half of this amount provided as grants.
The World Bank’s portfolio in Ethiopia is now around USD 15.5 billion, with USD 7 billion ready for disbursement. Additionally, the International Finance Corporation (IFC) maintains an investment portfolio in Ethiopia valued at USD 319 million. On another hand, the Multilateral Investment Guarantee Agency (MIGA) is actively engaged with USD 1.15 billion in guarantees mainly covering the telecommunications sector and is expected to grow over the coming years
“The Government of Ethiopia extends its profound gratitude to the World Bank for its continued support, which has been instrumental in supporting Ethiopia's ambitious homegrown reform program and development endeavors. This partnership is pivotal in our collective pursuit of sustainable development and poverty alleviation” said H.E. Ato Ahmed Shide, Minister, Ministry of Finance.

Ministry of Finance - Ethiopia

30 Jul, 20:03


Ethiopia Signs USD 1.5 Billion Support with the World Bank
July 30, 2024:- We are pleased to announce a significant reinforcement of its long-standing partnership with the World Bank.
A new financial package, through the First Sustainable and Inclusive Growth Development Policy Operation, has been agreed upon, consisting of a USD 1 billion grant and a USD 500 million loan, USD 1.5 billion in total aimed at bolstering the ongoing economic reform initiatives of the Ethiopian government. This substantial support from the World Bank, which is phase one, is a testament to the depth of our enduring alliance and shared commitment to Ethiopia's development aspirations.

Ministry of Finance - Ethiopia

30 Jul, 13:43


ማሳሰቢያ⚠️⚠️
ሐምሌ 23/ 2016 ዓ.ም - ከቅርብ ግዚያት ወዲህ አንዳንድ አጭበርባሪ ግለሰቦች የገንዘብ ሚኒሰቴርን አርማና የክቡር ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ ፎቶን በመጠቀም በተለያዩ ድረ-ገጾችና የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ ገንዘብ ሚኒስቴር ለስራ ፈጣሪዎችና ለግል ድርጅቶች የሚሰጥ የድጋፍ ገንዘብ ያዘጋጀ በማስመሰል ግለሰቦች እንዲያመለክቱና መመዝገቢያ ገንዘብ እንዲከፍሉ በመጠየቅ ላይ ናቸው፡፡
እነዚህ አጭበርባሪ አካላት በተለይም ገንዘብ ሚኒስቴር ከአለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋር የሚያደርገውን የልማት ድጋፍና የብድር ስምምትን እየተከተሉና የቅርብ ጊዜ የሚኒስትሩንና የአለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ሀላፊዎችን ፎቶ በማስደገፍ ግለሰቦች ለገንዘብ ድጋፉ እንዲመዘገቡና ፎርም እንዲሞሉ እየወተወቱ ስለሆነ ህብረተሰቡ ከነዚህ አጭበርባሪዎች ራሱን አንዲጠብቅ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያሳስባል፡፡
በተጨማሪም ህብረተሰቡ ገንዘብ ሚኒስቴር በህግ ከተሰጠው ተግባርና ሀላፊነት ውጪ ለግለሰቦች፣ ለስራ ፈጣሪዎችና ለግል ድርጅቶች ገንዘብ የሚያከፋፍልበት አሰራር እንደሌለው አውቆ እንዳይታለል እያሳሰብን ከሚመለከተው አካል ጋር በመተባበር በአጭበርባሪዎች ላይ ክትትል እያደግን መሆናችንን እናሳውቃለን፡፡

12,688

subscribers

821

photos

27

videos