ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) @referal_gibi Channel on Telegram

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

@referal_gibi


🖋️✍️ ይህ ቻናል በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ጉባኤ የተከፈተና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ትውፊትና አስተምህሮ የጠበቁ ትምህርቶች፣ ወቅታዊ መረጃዎች፣ ኪነጥበባዊ ፅሁፎች፣ ዝማሬዎች የሚለቀቁበት ነው።

ጽሑፎቹን ለጓደኞችዎ share በማድረግ የበኩልዎን ድርሻ ይወጡ! ያሎትን ጥያቄ ሀሳብ አስተያየት በ @referal_gibi_gubae ያድርሱን። 🙏

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) (Amharic)

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) በአማርኛ የእንግሊዝኛ ቋንቋዎችን እና እርምጃዎችን ከዚህ ቢሆኑ፣ የበኩልዎን ድርሻ ሀሳብ አስተዳዳሪዎች እና በሀሳቦች ለማድረግ አስተናግደን በመሄድ የተከፈተ ስለ እናምካቸው፡ Who is it? ጽሁፎችንና ታሪክገንባለችኋል፡ What is it? የዚህ ቻናል ይህንን አርዕስትን ቻናሉ የበኩልዎን ድርሻ ሀሳብ አስተያየት የሚያስችል በአቤትታሽ ምንጭ ይያዙ። በቃልኪነጥበቤስ ናይው ገበየርግ። ወደማስተካከል @referal_gibi ተከላከሉ።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

23 Jan, 17:06


እንዴት ቆያችሁ የተወደዳችሁ?
አሜን የእግዚአብሔር ስሙ ሁሌም የተመሠገነ ይሁን

የግራፊክስ እና ቪድዬ ኤዲቲንግ ማስታወቂያውን አይተው የተመዘገቡ ልጆች ቁጥር ስለሞላ ምዝገባውን በጊዜ ልንዘጋ ተገደናል። ስለነበረው ተሳትፎዋችሁ ከልብ እናመሠግናለን ።

መልካም ምሽት ይሁንላችሁ🙏
https://t.me/referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

20 Jan, 07:36


ጌታችን መጻጉዕን የፈወሰበትን፣ አልዓዛርን  ከሞት ያስነሣበትን፣ ዓይን ያበራበትን፣ በአጋንንት እስራት የተያዙትን ነጻ ያወጣበትን፣ ዕለት በክብረ በዓል ደረጃ ሳታከብር የቃናው ተአምር ከጌታችን ንዑሳን በዓላት ውስጥ ተደምሮ እንዲከበር ያደረገችበት ጥልቅ ምሥጢርን ስለያዘና ስላዘለ ነው፡፡ ይህ ሰርግ የሚደረገው  ጌታችን  ከአእላፋት  መላእክቱ  ጋር በሚመጣበት  በዕለተ  ምጽአት  ነው፡፡ ዕለተ  ምጽአት  ሙሽራዪቱ  ቅድስት  ቤተ ክርስቲያን በቅዱሳን ምግባር አጊጣ  የምትታይበት፣ የጽድቅ ዘይት ይዘው መገኘት የቻሉ ልባሞች  ከቤተ  ክርስቲያን ጋር ሰርጉን የሚታደሙበት፣ እንደ ቃናው ደስታ በሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት  መላእከት በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ  በኵራት ማኅበር፥  የሁሉም  ዳኛ ወደሚሆን ወደ  እግዚአብሔር፥  ፍጹማንም ወደ ሆኑት  ወደ ጻድቃን  መንፈሳት የምንደርስበት ዕለት ነው፡፡ (ዕብ.፲፱፥፳፪)

ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ የቃናን ሰርግ ከሰማያዊው ሰርግ ጋር አሰናስሎ ሲያመስግን እንዲህ ይላል፡፡ “ወደ ሰርግ በዓልዋ ዕለት ደስታን ይዘህላት ስለመጣህ ቃና ታመስግንህ! አክብረኸዋልና ሙሽራው የደፋው ዘውድ አንተን ያከብርሃል።  የሙሽራዋ አክሊልም የአንተን ድንቅ ሥራ ያደንቃል፡፡  ቤተ ክርስቲያንህን በሙሽራዋ መስለሃታልና  በቃና  መስታወትነት  ምሳሌዎች ሁሉ ትርጒማቸውን  አገኙ፡፡ የቃናዎቹ እንግዶች ደግሞ አንተ የመረጥሃቸው (ወደ  ሰማያዊው ራት) የጠራሃቸው  ናቸው::  ምጽአትህንም በሰርግ  ቤቱ ደስታ መሰልከው::”

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደ ሙሽራ አጊጣ፣ ለበጉ ሰርግ ያለ እድፍና ያለ ነውር ውብ ሆና ተዘጋጅታ በምትቀርብበት በዚያ ሰማያዊ ሰርግ ለመገኘትና ወደ በጉ ሰርግ ራት ገብተን፣ ካጌጡ ቅዱሳን ጋር ለመቀመጥና ለመብላት የበቃን ያድርገን!

መልካም በዓል!

ምንጭ፡- ትርጓሜ ወንጌል እና “ቃና ዘገሊላ”
በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

20 Jan, 07:36


ቃና ዘገሊላ
እንኳን አደረሳችሁ!

በቤተ ክርስቲያናችን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካደረጋቸው  እጅግ ብዙ ተአምራት መካከል በዓል አድርጋ የምታከብረው የቃና ዘገሊላውን ተአምር ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ተመዝግቦ እናገኘዋለን፡፡  “በሦስተኛውም  ቀን  በገሊላ  ቃና ሰርግ  ነበረ፥  የኢየሱስም  እናት በዚያ  ነበረች፤ ኢየሱስም  ደግሞ  ደቀ  መዛሙርቱም ወደ  ሰርጉ ታደሙ። የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፦ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም” አለችው። ኢየሱስም፦ “አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?  ጊዜዬ  ገና  አልደረሰም”  አላት። እናቱም  “ለአገልጋዮቹ፦   የሚላችሁን  ሁሉ አድርጉ” አለቻቸው። አይሁድም  እንደሚያደርጉት የማንጻት  ልማድ   ስድስት  የድንጋይ  ጋኖች   በዚያ  ተቀምጠው  ነበር፥   እያንዳንዳቸውም  ሁለት ወይም  ሦስት   እንስራ   ይይዙ ነበር። ኢየሱስም፦ “ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው” አላቸው። “እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው” አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።  “አሁን ቀድታችሁ  ለአሳዳሪው  ስጡት”  አላቸው፤  ሰጡትም። አሳዳሪውም  የወይን ጠጅ  የሆነውን  ውኃ  በቀመሰ ጊዜ  ከወዴት  እንደ  መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ ፦ሰው  ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን  የወይን ጠጅ  ያቀርባል፥  ከሰከሩም  በኋላ  መናኛውን፤ አንተስ  መልካሙን  የወይን  ጠጅ  እስከ  አሁን  አቆይተሃል”  አለው። ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።” (ዮሐ.፪፥፩-፲፩)

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

19 Jan, 05:45


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) pinned «በዓለ ጥምቀት እንኳን አደረሳችሁ! ጥምቀት ሥርዓቱ ከብሉይ ኪዳን ይጀምራል፡፡ አንድ አይሁድነትን ያልተቀበለ አዲስ ሰው ወደ ይሁዲነት ሲመጣ ከማኅበረ አይሁድ ከመቀላቀሉ አስቀድሞ ግዝረትን እና በውኃ  መታጠብን (መጠመቅ) እንዲፈጽም ይደረጋል፡፡ ይህም ለመንጻት ሥርዓት በዘሌዋውያን ካህናት  አማካኝነት  ይፈፀም ነበር፡፡ ውኃ መንጽኢ ነውና ማንም ሰው በተለያየ ምክንያት ቢረክስ  የሚነጻበት  (የኅፅበት)…»

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

19 Jan, 03:55


በዓለ ጥምቀት

እንኳን አደረሳችሁ!

ጥምቀት ሥርዓቱ ከብሉይ ኪዳን ይጀምራል፡፡ አንድ አይሁድነትን ያልተቀበለ አዲስ ሰው ወደ ይሁዲነት ሲመጣ ከማኅበረ አይሁድ ከመቀላቀሉ አስቀድሞ ግዝረትን እና በውኃ  መታጠብን (መጠመቅ) እንዲፈጽም ይደረጋል፡፡ ይህም ለመንጻት ሥርዓት በዘሌዋውያን ካህናት  አማካኝነት  ይፈፀም ነበር፡፡ ውኃ መንጽኢ ነውና ማንም ሰው በተለያየ ምክንያት ቢረክስ  የሚነጻበት  (የኅፅበት) ሥርዓት ለእያንዳንዱ  ምክንያት ነበረው፡፡  (ዘሌ. ፲፬፥፲፭-፳፪) ይህንንም ተዘርዝሮ እናገኘዋለን፡፡ ይህም በእውነት በውኃ ላይ የእግዚአብሔር  መንፈስ እንዳደረበት  ያስረዳል፡፡ (ዘፍ.፫፥፪) ተያይዞ እስከ ዘካርያስ ልጅ ቅዱስ ዮሐንስ ደርሷል፡፡

በመልአኩ  ቅዱስ ገብርኤል  ብሥራት የተወለደው  ጻድቅ፣ ቅዱስ ሐዋርያ ሰማዕት፣ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የዮሐንስ በረሃ በሚባለው እና ከሕፃናቱ ጀምሮ ባደገበትምድረ በዳ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ በብሕትውና ተወስኖ ሲኖር ቆይቶ ለክርስቶስ  መንፈቅ ሲቀረው  በ፴  ዘመኑ የዮርዳኖስ  አውራጃ  በምትሆን በይሁዳ  ‹‹ነስሑ  እስመቀርበት መንግሥተ ሰማያት፤ መንግሥተ ሰማያት በልጅነት፣  ልጅነት  በሃይማኖት ልትሰጥ ቀርባለችና በወንጌል አምናችሁ ንስሐ እያለ ሰበከ፤ በነቢይ ‹‹የጌታን መንገድ አዘጋጁ፤  ጥርጊያውንም አቅኑ  እያለ  በምድረ በዳ  የሚጮህ  ሰው ድምፅ›› እንደ  ተባለለት፡፡ (ኢሳ.፵፥፫፣ማቴ.፫፥፫)

ቃሉን የተቀበሉም ስለ ኃጢአት ስርየት ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ በፈለገ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ይጠመቁ ነበር፡፡ ይህም አማኞችን  ለክርስቶስ  ጥምቀት የሚያዘጋጅና በእግዚአብሔር  መንግሥት ውስጥ ለመሆን የሚያበቃ ነበር፡፡ ‹‹እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸክም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይበረታል፤  እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል›› (ማቴ.፫፥፲፩) ክርስቶስም ናዝራዊ ከተባለበት (ማቴ. ፥፳፫) ከናዝሬት  ወደ ዮርዳኖስ  ጥር ፲፩   ቀን  ወረደ፤  ቅዱስ  ዮሐንስም  ስለ  እርሱ  መሰከረ  ‹‹ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር  ዘያአትት ወያሴስል ኃጢአተ ዓለም፤ እነሆ  የዓለምን ኃጢአት  የሚያስወግድ የእግዚአብሔር  በግ፡፡›› (ዮሐ.፩፥፳፱)

ዮሐንስም ክርስቶስ በእርሱ እንዲጠመቅ መምጣቱን ባየ ጊዜ ወትሮ ባሪያ ወደ ጌታው ይሄዳል  እንጂ እንዴት ይህ ይሆናል?  አለው፤ ትሕትናን ከእናቱ ተምሯልና፤  ‹‹የጌታዬ  እናት ወደ  እኔ ትመጣ ዘንድ  እንዴት  ይሆንልኛል?››  እንዳለች ቅድስት ኤልሳቤጥ፡፡ (ሉቃ.፩፥፵፫)  ደግሞስ ሌላውን ሁሉ በስምህ አጠምቃለሁ፤  አንተን  በማን ስም አጠምቃለሁ?  ቢለው  ‹‹ወልዱ  ለቡሩክ ከሣቴ ብርሃን ተሣሃለነ››፤ ‹‹አንተ  ካህኑ ለዓለም በከመ  ሢመቱ  ለመልከ  ጼዴቅ››  ብለህ  አጥምቀኝ ብሎታል፤  ብርሃንን  የምትገልጥ የቡሩክ  አብ የባሕርይው  ልጅ ይቅር  በለን፤  እንደ  መልከ  ጼዴቅ  የዓለም ሁሉ ካህን  አንተ  ነህ››  እያልክ  አጥምቀኝ ብሎታል፤  ከዚያም ዮሐንስ ሊያጠምቀው ወደ ዮርዳኖስ ገብቷል፡፡

ዮርዳኖስ  የጥምቀቱ ቦታ  እንዲሆን  ጌታ የፈቀደው  አስቀድሞ  ትንቢት  አናግሮ  ምሳሌ መስሎ ‹‹ባሕርኒ ርእየት ወጎየት ወዮርዳኖስኒ ገብአ ድኅሬሁ ርእዩከ ማያት እግዚኦ  ርእዩከ ማያት ወፈርሁ፤ አቤቱ ውኆች አዩህ፤ ውኆችም አይተውህ ፈሩህ፤ ጥልቆችም ተነዋወጡ፤ ውኆችም ጮሁ፡፡›› (መዝ. ፸፮፥፲፮) ‹‹ባሕር  አየች፤  ሸሸችም፤  ዮርዳኖስም  ወደ ኋላ  ተመለሰ፤››  (መዝ.፻፲፫፥፫) ዮርዳኖስ መነሻው ከላይ ነቁ፤ አንድ ነው፤ ዝቅ ብሎ በደሴት ይከፈላል፤  ከታች ወርዶ ይገናኛል፡፡ የሰውም ልጅ አባቱ አንዱ አዳም ሲሆን እስራኤልና  አሕዛብ በግዝረት በቁልፈት  ተለያይተዋልና፡፡ ከታች ወርዶ እንደገና በወደብ እንዲገናኝ ሕዝብ እና አሕዛብ  በክርስቶስ  ጥምቀት አንድ  ሆነዋል፤  ከዚህም  የተነሣ  ጌታ የሁለቱ  ወንዝ  መጋጠሚያ  ላይ  በመጠመቅ አንድነታችንን  መልሶልናል፡፡  ይህንን  ውለታ በማሰብ (ይህን  የነጻነት  በዓል)  እናከብራለን፡፡

ከዚህም በላይ  የሥላሴ  ምሥጢር እኛ በምንረዳው መልኩ ያየንበትን በዓል የዕዳ ደብዳቤያችን የተፋቀበትን ቀን፣ ነጻነታችንን ያወጅንበትን፣ የእግዚአብሔር  ልጆች የሆንበትን  ዕለት  ከበዓልም  የሚበልጥ  ዐቢይ  በዓል  አድርገን  አናከብረዋለን፡፡  ይህንንም  ቀን  ቀድሶ  የሰጠን  ቅዱስ አምላክ ምስጋና ይድረሰው፤ አሜን፡፡
ከበዓሉ በረከት ረድኤት ያሳትፈን!

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

16 Jan, 19:31


ብታነቡት አንድ ሥርዓት ትፈጽማላችሁ ታቃላችሁ 👍

ጾመ ገሃድ

ገሃድ ምንድን ነው?

ገሃድ የቃሉ ትርጉም መገለጥ፣ መታየት ነው፡፡ በጥምቀት መገለጥ መባሉ ሰው የሆነው አምላክ በዓለም ሲኖር እስከ 30 ዓመት እድሜው ድረስ ሰዎችን ለማዳን የመጣ መሲህ ሰው የሆነበት፣ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ መሆኑን ሳያውቁ ከኖሩ በኃላ በ 30 ዓመት እድሜው በባሕረ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ እጅ ሲጠመቅ አብ በደመና ሆኖ ‹‹የምወደው ልጄ ይህ ነው›› በማለቱ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በራሱ ላይ ሲያርፍ በመታየቱ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ይሰቀላል ይሞታል ይነሳል ብለው የተናገሩለት መሲሕ እርሱ መሆኑ ተገልጦአልና እንዲሁም ሦስቱ አካላት በአንድ ጊዜ ታይተዋልና ምስጢረ ሥላሴ የተገለጠለት በመሆኑ ገሃድ ይባላል፡፡(ማቴ 3፡13-17)

ይህን በማሰብ የምንጾመው ጾም “የገሃድ ጾም” ይባላል፡፡

በዚህ መሠረት የአሁን የገሃድ ጾም የራሱ አዋጅ አለው

ስንክሳር ዘጥር ፲ እንዲህ ብሎ ያዛል

ወለእመ ፡ ኮነ ፡ ዕለተ ፡ በይረሙን ፡ ዘውእቱ ፡ አስተርእዮ ፡ በዕለተ እሁድ አው፡በዕለተ፡ ሰንበተ አይሁድ፡ይጹሙ፡በእለተ ፡ ዓርብ ፡እምቅድሜሁ፡እስከ፡ምሴት፡በከመ ተናገርነ፡ ቅድመ ዳዕሙ ይትዓቀቡ፡እምነ፡በሊዕ፡ጥሉላተ።

ጥምቀት እሁድ ስለዋለ አስቀድመን አርብ እስከ 12 ሰአት ይጾማል። በዋዜማው ደሞ ቅዳሜ ከቅዳሴ በኃላ ምግብ መመገብ ይቻላል። ግን ጥሉላት አይበሉም።
ለምሳሌ  ሥጋ ፣ ወተትና የወተት ተዋጽኦ......

በረከት የምናገኝበት ጾም ያድርግልን!!!

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

16 Jan, 06:10


📽🎞

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

16 Jan, 06:10


የ2016 የጥምቀት በዓልን በአሮማ ስናከብር ትዝታዎች
📷📷📷📸📸📸

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

29 Dec, 08:46


🌷 ፍሬ ግቢ ጉባኤ 🌷

አአትብ ገጽየ የአብነት ትምህርት የመጀመሪያ ቃል ነው በግቢ ጉባኤያችን አብነት ትምህርት አማካኝነት ይህን ቃል ልሳናቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ተናገረ ዕደ ሕሊናቸው የስብሐተ እግዚአብሔርን መጀመሪያ ጨበጠ ፣ የልቦናቸው ወገብ የእግዚአብሔርን ቃል ለመማር ዝቅ አለ ፣ እዝነ ልቦናቸው የጥሪውን ቃል አደመጠ ፣ እግረ ሕሊናቸው ለምስጋና በትጋት ተራመደና ተሰመዩ ዲያቆናት !

🔘ዲ/ን የቻለ ሙሉ..አብነት ነዑስ ክፍል ተጠሪ(3rd HI)
🔘ዲ/ን ሙሀባው ማረው(4th psycha)

🔘ዲ/ን ዮሴፍ ፈንታሁነኝ (5th Pharma)
🔘ዲ/ን አቤሴሎም ሰሎሞን (old 3rd Opta)
🔘ዲ/ን ዮሐንስ መንገሻ (Med PCI)
🔘ዲ/ን ወልደ ሚካኤል መኩሪያ (2nd psycha)

ዘወጠነ ወዘተግሀ፣ ወዘደክመ፣ ወዘጸንዐ ይፌጽም።
የጀመረ፣ የተጋ፣ የደከመና የጸና ይፈጽማል።

አንትሙ ዲያቆናት ሥዩማነ እግዚአብሔር ጌታችን እራሱ ከመረጣቸው ሐዋርያት የወጣ ነበረ እንዲሁ መስቀል ሥር ያልተለየውም ነበረ የእናንተም ማዕረግ መስቀል ሥር የሚያደርስ ይሆንላችሁ ዘንድ እንመኛለን።

ታህሣሥ 20|2017
ሐዋሳ ሪፈራል ግቢ ጉባኤ

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

28 Dec, 18:31


ይህ ቁርባን ክቡር ነው ፍጹም ሰማያዊ
በሊቀመዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ

https://t.me/referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

28 Dec, 04:07


በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን ስሙ በብዛት ተጠቅሷል:: ስለ ረዳትነቱና አማላጅነቱም ቤተ ክርስቲያን በስሙ ታቦት ቀርጻ: መቅደስ አንጻ በሥርዓት ክብሩን ትገልጻለች::

ከእነዚህም አንዱ ሠለስቱ ደቂቅን እንዳዳነ የሚታሰብበት አንዱ በዓሉ ዛሬ ነው::
"ለዝንቱ ዜናዊ መልአከ ኃይል::
በዛቲ ዕለት ከመ ይትገበር በዓል::
መምሕራን አዘዙ ወሠርዑ በቃል::" እንዲል:: (አርኬ)

ንጉሡ ከምርኮ ወጣቶች ለቤተ መንግስት ሲመርጥ ሦስቱ ቅዱሳንና ዳንኤል ተመርጠው የምቾት ሕይወት ተዘጋጅቶላቸው ነበር:: ነገር ግን በምግብና በአምልኮ ከአሕዛብ ጋር መተባበርን አልፈለጉምና ምርጫቸው ጾምና ጸሎት ከቆሎ ጋር ሆነ::

ምንም እንኳ በቤተ መንግስት ውስጥ ቢኖሩ: ምንም የነገሥታት ልጆች ቢሆኑ ለእነርሱ ከእግዚአብሔር ፍቅር የተሻለ አልነበረምና በጥሬ ቆሎ ተወስነው ኖሩ::

አምላካቸው ከሃሊ ነውና በውበትም ሆነ በጥበብ በባቢሎን ምድር ከነርሱ የሚደርስ አልተገኘም:: ንጉሡም በባቢሎንና በአውራጃዋ ላይ ሾማቸው:: ስማቸውንም በአማልክቱ ስም ሲድራቅ: ሚሳቅና አብደናጐ አላቸው::

ከነገር ሁሉ በኋላ አሕዛብ ቀንተውባቸዋልና የክፋት አዋጅን አሳወጁ:: ናቡከደነጾር 60 ክንድ ቁመት ያለውን የወርቅ ምስል አቁሞ ስገዱ ቢላቸው አይሆንም በማለታቸው ተቃጥለው እንዲሞቱ እሳት ተፈረደባቸው:: ነበልባሉ ከጉድጓዱ ወደ ላይ 49 ክንድ ቢነድም ቅንጣት ያህል ፍርሃት አልጎበኛቸውም::

ወደ እሳቱም ሲጥሏቸው መልዐከ አድኅኖ ቅዱስ ገብርኤል ደርሶ አዳናቸው:: ከሆነው ነገር የተነሳ አሕዛብ አፈሩ:: ናቡከደነጾር ግን ከዙፋኑ ተነስቶ የቅዱሳኑን አምላክ እግዚአብሔርን ባረከ::

ቅዱሳኑን ያዳነ ቅዱስ መልአክ እኛንም ያድነን ዘንድ እንደ አባቶቻችን
"አድኅነኒ ዘአድኃንኮሙ በአክናፊከ ምንትው::
አመ ውስተ እሳት ተወድዩ ሠለስቱ እደው::" እያልን እንለምነው::


የመልዐኩ ረድኤት በረከት እና ጠብቆት አይለየን

https://t.me/referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

28 Dec, 04:06


እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል: ቅዱስ ዮሐንስ ዘቡርልስ እና አቡነ ስነ ኢየሱስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

† ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት


በቤተ ክርስቲያን ክቡር ከሆኑ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ገብርኤል ብዙ የክብር ስሞች አሉት:: በተለይ ግን:-
ሊቀ አርባብ:
💫መጋቤ ሐዲስ
💫መልአከ ሰላም
💫ብሥራታዊ
💫ዖፍ አርያማዊ
💫ፍሡሐ ገጽ
💫ቤዛዊ መልአክ
💫ዘአልቦ ሙስና . . . እየተባለ ይጠራል::

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

27 Dec, 08:40


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) pinned «»

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

24 Dec, 05:27


ቁርባን ማለት ምን ማለት ነው?

ቁርባን ለሚለው ቃል ሁለት ፍች አለው፤
📍 አንደኛው ፍቺ ቁርባን ማለት ለእግዚአብሔር የሚያቀርቡት ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርብ ማለት ነው።

📍ሁለተኛው የቁርባን ፍች ቁርባን ማለት የሚቀበሉት የሚያቀብሉት ማለት ነው።

ስለዚህ ቁርባን ፤ ማለት ፣ ለእግዚአብሔር የሚቀርብ አምኃ ፣ መስዋዕት ፣ መንፈሳዊ ነገር ሁሉ ማለት ነው።


የምስጢር ቀን

5 የዝግጅት ቀናት  ቀሩ
  📌ታህሳስ 20

https://t.me/referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

22 Dec, 10:48


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) pinned «»

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

19 Dec, 06:22


ኅየንተ አበዊነ ጠቢባን ልጆችን የሰጠን የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ይመስገን !

እሱ እና እሷ ... እንዴት ያለ ድንቅ ጭውውት ነው ?! ወራዙት ሁሉ ሊያዩት የሚገባ በዕንባ ጀምረው በዕንባ የሚጨርሱት በምስጢራዊ ጥበብ የእግዚአብሔርን ቃል የሚያስተምር መንፈሳዊ ጭውውት !

ወንድማችን ዘመን እና እኅታችን ሕይወት ነፍስ ዘርተው ያቀረቡትን ይኽን ጭውውት ዛሬ ሳይሆን አሁኑኑ ይመልከቱ !


https://youtu.be/BC25h0-5UeM

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

19 Dec, 06:21


ሀሳብ ተሰቃይቷል !


ሀሳብ ተሰቃይቷል ! በድንቅ አገላለጽ ረቂቅ መልዕክቶችን የያዘ በጌጠኛ ቀለማት ያሸበረቀ በጥበብ ሠረገላ አሳፍሮ የሚነጉድ የግጥም ማዕድ ! በእኅታችን ገጣሚት ትዕግሥት የቀረበ ደገኛ ግጥም አሁኑኑ ይመልከቱ !

በሕይወተ ወራዙት መንፈሳዊ የኪነጥበብ መርሐግብር ላይ የቀረበ ድንቅ ግጥም በሪፈራል ግቢ ጉባኤ የዩቲዩብ ገጽ ይመልከቱ ።


https://youtu.be/nYNAAh1EiT0

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

18 Dec, 10:13


📨2
#10_የዝግጅት_ቀናት
#ምን_ያህል_እንደሚወደን_በቃላት_መግለጽ
#አይቻልም_ከባድ_ነው!
🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️
ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ኃጢአት ይቅር ብዬህ አልነበረም?!" ብሎ ያለፈውን የኃጢአት ዶሴ አይመዝም! ምሕረቱ ለዘላለም የሆነው አባት ንስሐ የተገባበትን ኃጢአት ለሪከርድ የሚያስቀምጥበት መዝገብ ቤት የለውም
🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️
ከቋንቋ በላይ  የሚያወራውን በቀራንዮ ለእኛ የተሰቀለውን ክርስቶስን አይቶ መመለስ አለመቻል እንዴት ያለ የልብ መደንደን ነው?! በዚያ መከራ ውስጥ እያለፈ እንኳ፥ ከስቃዩ ጋር እየታገለ ከዓይኖቹ የሚረጨውን ነፍስን የሚያብረከርክ ፍቅር ፣ ስስት፣ ርኀራኄ ከማየትና ከማወቅ በላይ ሌላ መግለጫ ማሳያ አይኖርምና!
🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️🧎‍➡️
#10_የዝግጅት_ቀናት_አሉን
#ታህሳስ_20_የቅዱስ_ቁርባን_ቀን

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

17 Dec, 06:34


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

“ #አደራ_አለብኝ “
የጉባኤ ጥሪ ለግቢ ጉባኤ ምሩቃን በሙሉ!

“ #አደራ አለብኝ
“ በተለያዬ ጊዜ ከግቢ ጉባኤ የተመረቁ ወንድሞችና እኅቶች የሚሳተፉበት ታኅሣሥ 13/2017 ዓ/ም ዓለም አቀፍ የግቢ ጉባኤ ምሩቃን መርሐ ግብር በማኅበረ ቅዱሳን ሀዋሳ ማእከል ተዘጋጅቷል።

ከ1984 ዓ/ም ጀምሮ በግቢ ጉባኤ ሕይወት ያለፋችሁ እና የተመረቃችሁ በሀዋሳ እና ዙርያ የምትገኙ አባቶች ፣ እናቶች ፣ ወንድሞች እና እኅቶች በሙሉ በመርሐ ግብሩ እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል ።

ቀን: ታኅሣሥ 13/2017 ዓ/ም
ሰዓት: ከቀኑ 7:30

ቦታ: በሀዋሳ ደብረ ምሕረት
ቅ/ገብርኤል ገዳም
ደጄ ሠላም አዳራሽ
#አደራ አለብኝ!

©:በማኅበረ ቅዱሳን ሀዋሳ ማእከል ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ዋና ክፍል

#አደራ አለብኝ!
አዎ የቤተክርስቲያን አደራ አለብኝ!

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

16 Dec, 05:36


ንስሐ

...አንድ ወታደር ጦር ሜዳ ሔዶ ቢቆስል ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው አይወቅሰውም፡፡ አንተም ጠላትህ ዲያብሎስ ቢያቆስልህ ማንም አይወቅስህም፡፡ መንፈሳዊ ተጋድሎ ውስጥ ነውና ያለኸው፡፡ የምትወቀሰው ለቁስልህ መድኃኒት ማድረግህን ችላ ያልህ እንደ ኾነ ብቻ ነው፡፡

ይህ ከላይ የነገርኩህ ወታደር ከታከመ፥ ተመልሶ ወደ ጦር ሜዳ ይሔዳል፡፡ ጠላቱን ድል ሲያደርግም ሹመት ሽልማት ይሰጡታል፡፡

አንተም ከወደቅህበት ተነሥና ንስሐ የተባለ ሕክምናን ውሰድ፡፡ ከዚያም ጠላትህ ዲያብሎስን ድል አድርገህ ከክርስቶስ ዘንድ ሹመት ሽልማትን ተቀበል፡፡ ስለዚህ በርታ፡፡ በርታና ተነሥ ዘግይቻለሁ ብለህ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ፤ አሁንም መጀመር ትችላለህና፡፡
[ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ]

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

05 Dec, 05:42


ዛሬ ኅዳር 26 የጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተማርያም የእረፍታቸው መታሰቢያ በዓል ነው እንኳን አደረሰን  ህዳር 26 ይከበራል ሁላችሁም  የፃድቁ በረከት ረድኤት አይለየን ።

የጻድቁ በረከት ይደረብን ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ይጠብቁን አሜ

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

05 Dec, 05:42


ተአምሪሁ ለአቡነ ሀብተማርያም ጸሎቱ ወበረከቱ የሀሉ ምስለ ኵልነ ሕዝበ ክርስቲያን ለዓለመ ዓለም ።

ጸሎቱ እና በረከቱ በሁላችን ሕዝበ ክርስቲያን ጋር ይሁንና አባታችን ሀብተማርያም ያደረገው ተአምር ይህ ነው ።

ከእለታት በአንዱ ቀን አባታችን ሀብተማርያም በጎቹን እየጠበቀ ሳለ ብዙ የበግ እረኞችም አብረውት ነበሩ ። አንድ የበግ ጠባቂም መጥቶ የአባታችንን በትር ነጠቀውና ሔደ ፤ አባታችንም በትሬን ለምን ትቀማኛለህ አለው ፤ እረኛውም በትዕቢት ቃል " በጉልበቴ ነጥቄሃለሁ " አለው አባታችንም " እኔ ኃይል የለኝም ነገር ግን በጎቼን የምጠብቅበትን በትሬን እንዳትወስድብኝ በሕያው እግዚአብሔር ስም አምልሃለሁ " አለው ያም የበግ ጠባቂ  "እምቢ አልኩህ " አለው ።
አባታችንም " አንድ ጊዜ በፈጣሪዬ ስም አማልኩህ ከእንግዲህ ወዲያ ደግሞ አላምልህም ከአንተ ላይ የሚደረገውን ራስህ ታውቀዋለህ " ይህንንም ተናግሮ ዝም አለ ። በዚያን ጊዜ ያ የበግ ጠባቂ በአየር ላይ ተዘቅዝቆ ተሰቀለ ፤ " የእግዚአብሔር አገልጋይ ሀብተማርያም ማረኝ እያለ ይጮህ ጀመረ ፤ የልዑል እግዚአብሔርን ስም አቃሏልና ተሰቅሎ ዋለ እረኞችም ሁሉም አይተው አደነቁ ፈሩትም  " ይህን ሰነፍ ማርልን እግዚአብሔር ያደረገልህን ኃይል አይተናልና አሁንም ስለ እመቤታችን ብለህ ይቅር በለው " አሉት ። አባታችንም " በውኑ እኔ የሰቀልኩት ነውን በእግዚአብሔር ስም አማልኩት እንጂ የኃይሉን ጽናት በላዩ ሊገልጥ እርሱ እግዚአብሔር ሰቀለው እንጂ አሁንም እርሱ ከፈቀደ ያውርደው እርሱ መሐሪና ይቅር ባይ ነውና " ይህንንም በተናገረ ጊዜ ወርዶ በእግሩ ቆመ ወደ አባታችንም መጥቶ ሰገደለት ።

ጸሎቱ እና በረከቱ በሁላችንም ይኑር አሜን ።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

04 Dec, 07:26


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) pinned «»

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

04 Dec, 07:06


ኅዳር 25 | ቅዱስ_መርቆሬዎስ ሰማዕትነት ተቀበለ።
ቅዱስ_መርቆሬዎስ ስሙ ፒሉፓዴር (ፒሉፓተር) ይባላል። ትርጉሙም "የአብ ወዳጅ" ማለት ነው። በኋላ ሊቃውንት መርቆሬዎስ  አሉት። መርቆሬዎስ ማለት ገብረ ኢየሱስ ክርስቶስ (የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ) ነው።

የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ደግሞ ለሰማዕቱ ያላቸውን ፍቅራቸውን ጨምረው አቡ ሰይፊን (Abu Seifin- ባለ ሰይፉ አባት) ይሉታል።

ቅዱስ ገብርኤል በርበሮችን እንዲያጠፋ ከንጉሥ ዳኬዎስ ጋር ሲዘምት ሰይፍ ያቀዳጀው፣ ገጸ ከልብ (ፊቱ የውሻ፣ መኻሉ የሰው፣ እግሩ የአንበሳ፣ ታቹ የጋለ ነሐስ የሆነ ፍጡር) ጓደኛው የሆነ፣ እርሱ ሰማዕት ከሆነ በኋላ ጥቁሩ ፈረሱ ወንጌልን የሰበከ ቅዱስ ነው።

ከበርበሮች ጋር ጦርነቱ በእግዚአብሔር ኃይል ከተፈጸመ በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን ሊያደርግ ወደደ። ቅዱስ መርቆሬዎስ ግን አብሮት አልወጣም ወደ ቤቱ ሔደ እንጂ። በዚያንም ጊዜ ንጉሥ መልእክተኞችን ልኮ ቅዱስ መርቆሬዎስን ወደርሱ አስመጥቶ ለአማልክት ዕጣን አሳርግ እና ስገድ አለው።

በዚያንም ጊዜ ትጥቁንና ልብሱን ወረወረለትና ንጉሡን እንዲህ አለው፦ "እኔ ክብር ይግባውና ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም! ለረከሱ ጣዖታትም አልሰግድም።"

ንጉሥ ዳኬዎስም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ። እርጥብ በሆኑ የሽመል በትሮች እንዲደበድቡት አዘዘ። ሁለተኛም ከላም ቆዳ በተሠራ ጅራፍ ይገርፉት ዘንድ አዘዘ።

በዚያንም ጊዜ የአገር ሰዎች ስለ ቅዱስ መርቆሬዎስ እንዳይነሡበት
ፈርቶ ወደ ሆነች ወደ ቂሣርያ በብረት ማሠሪያ አሥሮ ላከው። በዚያም እንዲአሠቃዩት አዘዘ።

ከአሠቃዩትም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ እንዳዘዘ ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና ተጋድሎውን ፈጽሞ በመንግሥተ ሰማያት የሕይወት አክሊልን ተቀበለ።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

02 Dec, 15:21


💠 ጊዜው ገና ነው 💠
💠💠💠💠💠💠💠
💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

አንድ ምንጩ የማይታወቅ አስተማሪ የሆነ አፈ-ታሪክ አለ። በዚህ አፈ-ታሪክ መሠረት፥

ከዕለታት በአንዱ ቀን አጋንንት ስብሰባ አደረጉ ይባላል። ይህንን ስብሰባ የጠራው የአጋንንቱ አለቃም “ዓለምን ሁሉ ከእኔ ጋር ለማሰለፍ እፈልጋለሁ። ምን ይደረግ? ማንንስ ልላክ?” ብሎ ጠየቀ። ከሥሩ ያሉትም አንድ በአንድ እየተነሱ አሳቦችን ማቅረብ ጀመሩ። 

አንዱ ተነሳና፥ “እኔን ብትልከኝ፥ ፈጣሪ የለም ብዬ ሰዎችን ማሳመን እችላለሁ!” ብሎ ተናገረ። የአጋንንቱ አለቃ ግን፥ “እርሱ አይሠራም። ብዙዎቹ አያምኑህም። ፈጣሪ እንዳለ ያውቃሉ።” ብሎ መለሰ። 

ሌላኛው ተነሳና፥ “እኔን ከላክኸኝ፥ ገነትም ሆነ ሲኦል የሚባል ቦታ እንደሌለ አሳምናቸዋለሁ!” አለ። የአጋንንቱ አለቃ ግን፥ “እርሱም አይሠራም። ብዙዎቹ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ ያውቃሉ።” ብሎ መለሰ። 

ሌላው ደግሞ ተነሳና፥ “እኔን ላከኝ። ፈጣሪም አለ፥ ገነትም አለ፥ ሲኦልም አለ፤ ነገር ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ ለማሰብ ጊዜው አሁን አይደለም ብዬ አሳምናቸዋለሁ።” አለ። የአጋንንቱ አለቃም ደስ እያለው “ይህ ጥሩ መንገድ ነው!” በማለት አሳቡን ተቀበለና ላከው ይባላል።

ሰይጣን ማዘግየት ጥሩ ስልት መሆኑን ስለሚያውቅ፥ ለማዘግየት ይፋጠናል። በሐዲስ ኪዳን ላይ ቅዱስ ጳውሎስ "ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና፥ እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ፥ ሰይጣን ግን አዘገየን።” (1 ተሰ 2:18) ሲል እናገኘዋለን። ሰይጣን ላያስቀረን ይችላል፥ ግን ቢያንስ ሊያዘገየን ብዙ ይሞክራል።

እርሱ ዓለማዊ ጓዞቻችንን ለአፍታ ስንኳ አውርደን ከእግዚአብሔር ጋር ስላለን ግንኙነት እንድናስብ አይፈልግም። ስለ ጸሎት ብታስብ፥ "አሁን ደክሞሃል። ጊዜው አይደለም ሌላ ጊዜ ትጸልያለህ" ይልሃል። ለመጾም ብትዘጋጅ "አሁን ጉልበት ስለሚያስፈልግህ ብላ። የምትጾምበት ጊዜ አይደለም፤ ሌላ ጊዜ ትጾማለህ።" ይልሃል። ለመስገድ ብትዘጋጅ "ኧረ ተረጋጋ፤ ጊዜው አይደለም፥ ጾም ሲገባ ትሰግዳለህ" ይልሃል። ንስሃ ልትገባ ብትዘጋጅ "ቆይ እንጂ፥ ዘለህ ጨርሰህ አንዴ ብትታጠበው አይሻልም?" ለማለት የሚቀድመው የለም። ቅዱስ ቁርባን ልቀበል ነው ካልክ "አንተኮ ገና ነህ፥ ለወደፊት ጣጣህን ስትጨርስ ቀስ ብለህ አመቻችተህ ትቆርባለህ" ብሎ ያዘናጋሃል።

በዚህ ሁሉ መዘግየት ውስጥ መልአከ ሞት መቼ እንደሚመጣ ማን ያውቃል? ለመንፈሳዊ ነገር ስንነሳ፥ ሰይጣን "ጊዜው ገና ነው" ማለቱ አይቀርም። እኛ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል“ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (2ኛ ቆሮ 6፥2) እንደሚል እናስታውስ። ለመዳናችን ቀጠሮ አንስጥ።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

02 Dec, 00:15


#ተጋድሎ

"ወዳጄ ሆይ! የሚታገል ሰው ቢወድቅ አዲስ ነገር አይደለም፤ ወድቆ መቅረቱ ነው እንጂ፡፡ አንድ ቦክስ የሚጋጠም ሰውም ቢቆስል የሚያሳዝን ነገር አይደለም፤ የሚያሳዝነው ቁስሉን ችላ ያለው እንደ ኾነ ነው እንጂ፡፡ አንተም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ብትወድቅ አይደንቅም፤ ለቅጽበትም የማይተኛልህ ጠላት አለህና፡፡ ነገር ግን ወድቀህ አትቅር፡፡

አንድ ወታደር ጦር ሜዳ ሔዶ ቢቆስል ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው አይወቅሰውም፡፡ አንተም ጠላትህ ዲያብሎስ ቢያቆስልህ ማንም አይወቅስህም፡፡ #መንፈሳዊ_ተጋድሎ ውስጥ ነውና ያለኸው፡፡ የምትወቀሰው ለቁስልህ መድኃኒት ማድረግህን ችላ ያልህ እንደ ኾነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ከላይ የነገርኩህ ወታደር ከታከመ፥ ተመልሶ ወደ ጦር ሜዳ ይሔዳል፡፡ ጠላቱን ድል ሲያደርግም ሹመት ሽልማት ይሰጡታል፡፡ አንተም ከወደቅህበት ተነሥና #ንስሐ የተባለ ሕክምናን ውሰድ፡፡ ከዚያም ጠላትህ ዲያብሎስን ድል አድርገህ ከክርስቶስ ዘንድ ሹመት ሽልማትን ተቀበል፡፡ ስለዚህ በርታ፡፡ በርታና ተነሥ ዘግይቻለሁ ብለህ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ፤ አሁንም መጀመር ትችላለህና፡፡"

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

01 Dec, 17:38


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) pinned «»

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

01 Dec, 05:38


ንስሐ  ምንድን  ነው?

ንስሐ ነስሓ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ነው፡፡ ፍቹም ሐዘን፣ጸጸት፣ ቁጭት፣ምላሽ፣ መቀጮ፣ ቅጣት ፣ቀኖና፣ የኃጢአት ካሣ ማለት ነው፡፡(ኪዳነ ወልድ  ክፍሌ መዝገበ ቃላት)፡፡ ንስሓ ማለት ተነሳሂው በሠራው ጥፋት፣ ባደረገው ስሕተትና በፈጸመው ኃጢአት ማዘን፣ መቆርቆር፣ መጸጸት፣ ?ሲሰራው የነበረውን ኃጠአት መልሶ ላለመሥራት መወሰን ማለት ነው፡፡ ንስሐ ገባ ማለት አዘነ፣ ተጸጸተ፣ተመለሰ ፣ክፉ አመሉን ተወ፣ጠባዩን ለወጠ ማለት ነው፡፡

❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️

ንስሓ  ሰው በሕይወት እንዲኖር የሚያደርግ የእግዚአብሔር ጥሪ ነው፡፡ ይህን ጥሪ ሰምቶ የተከተለ በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን ያገኛል፤ የእግዚአብሔርን መንግሥት ይወርሳል፡፡ ንስሓ ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲን አንዱ ነው፡፡ ንስሓ ከሚደገሙት ምሥጢራትም ይመደባል፡፡ ንስሓ ምሥጢር መባሉ ኃጢአታችንን ተናዘን ቀኖናችን ሰንጨርስ ኃጢአታችን ተደምስሶ ንጹሕ እንሆናለን፤ ይህ ሲሆን ለተነሳሂው በግዙፍ አለመታየቱ ምሥጢር ያስብለዋል
ንስሓ በሰው ሕይወት ውስጥ ሲተረጎም፡-

፩. ንስሓ ኀጢአትን ሲሠሩ ከመኖር ይልቅ ከእግዚአብሔር ጋር መኖርን መመረጥ ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄርን መምረጥ ማለት ደግሞ መንገዱን፣ ፈቃዱንና ሐሳቡንም የእግዚአብሔር ማድረግ ማለት ነው፡፡ በእምነትና በምግባር ኖሮ የእግዚአብሔርን መንግሥት መውረስ ማለት ነው፡፡ “ለእኔስ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል፡፡“ እንዲል (መዝ፸ ፫፡፳፰)፡፡

፪. ንስሓ ስላለፈው ኃጢአት ስሕተት አብዝቶ ማልቀስና የባለፈውን ኑሮ መኮነን ማለት ነው፡፡ ነቢዩ ኢዩኤል “በፍጹም ልባችሁ በለቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ፡፡“ የሚለው ሰው ከልቡ ሲመለስ ስለ ኀጢአቱ ያለቅሳልና ፡፡ “በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትመሰሉ፡፡“( ሮሜ ፲፪፡፪) የሚለውም ይህንኑ የሚያጠናክር ነው፡፡

፫. ንስሐ ከኃጠአት እንቅልፍ መንቃት ነው፡፡ ኃጢአት በመንፈሳዊ ሕይወት ማንቀላፋት ሲሆን ንስሓ ደገሞ ከኃጠአት እንቅልፍ መንቃት ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ “ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደሆነ ዘመኑን ዕወቁ“ በማለት  የሮሜ ሰዎች ከኃጢአት እንቅልፍ ነቅተው ንሰሓ እንዲገቡ የሚመራ ጥሪ ነው፡፡ በኃጢአት ጠፍቶና አንቀላፍቶ የነበረው የጠፋው ልጅም ከኃጢአት እንቅልፍ በነቃ ጊዜ ወደ አባቱ ቤት ተመልሶ ልጅ ልባል ባይገባኝም  ከባለሙያተኞች  ቁጠረኝ ያለው በኃጢአት እንቅልፍ እያለ የሚያደርገውን አላወቀም ነበር ወደ ልቡ ሲመለስ ግን አስተዋለ፤ “ወደ ልቡ ተመለሰ፡፡“ እንዲል (ሉቃ ፲፭፡፩)፡

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

30 Nov, 12:03


የጽዋ መርሀግብራችን የመጨረሻ ይዘት

(ከመርሀግብራት በኋላ ሁላችንም ከያለንበት በመነሳት)

ሙሴ፦ማነህ ባለሳምንት ያስጠመድህ በኣስራ ስምንት እኔ ነኝ የምትል የማርያም ወዳጅ
ባለ ሳምንት(ቀጣይ ወር ተረኛ department)፦ እኔ አለሁ እህታችሁ/ወንድማችሁ ቢያውለኝ ቢያውላችሁ ቀጤማ ጎዝጉዤ ማይ ሹሜ እጠብቃችኋለሁ እስከዚያ___(ስመ-ክርስትና) ብላቸሁ በፀሎታችሁ አስቡኝ- - - - -ማደግደግ(መስገድ)

ሙሴ ፥- ማነህ ባለሁት ያስጠመድህ በአስራ ሁለት እኔ ነኝ የምትል የማርያም ወዳጅ
የሁለተኛ ወር (ተረኛ department)፦እኔ አለሁ እህታችሁ/ወንድማችሁ ቢያውለኝ ቢያውላችሁ ቀጤማ ጎዝጉዤ ማይ ሹሜ እጠብቃችኋለሁ እስከዚያ____(ስመ-ክርስትና) ብላቸሁ በፀሎታችሁ አስቡኝ

ሙሴ፦ ማነህ ባለ ሦስት ያስጠመድህ በአስራ ሦስት እኔ ነኝ የምትል የእመቤታችን የድንግል ማርያም ወድጅ
የሦስተኛ ወር (ተረኛ department)፦እኔ አለሁ እህታችሁ/ወንድማችሁ ቢያውለኝ ቢያውላችሁ ቀጤማ ጎዝጉዤ ማይ ሹሜ እጠብቃችኋለሁ እስከዚያ እከሌ(ስመ-ክርስትና) ብላቸሁ በፀሎታችሁ አስቡኝ

ካህን/ዲያቆን፦ አለሁ እንዳላችሁ አለሁ ይበላችሁ፣ እንዲህ እንደወደቃችሁ ኃይለ አጋንንት ይጣልላችሁ፣ ለቀጠሮ ያብቃችሁ፣ አቡነ ዘበሰያት((በክብር ተነሱ ይላቸዋል))

ሙሴ፦ ባለአራት ቤትህን አትሳት፣ ተጠራጠር፣ ብቅል ስቀል።

ሙሴ:-- ለሙሴ ዓኑ በሳሳ፣ እጁ ባዳላ፣ ጠላው በቀጠነ፣ ቆሎው ባረረ፣ ዳቦው በቀነበረ ማሩን ይቅር በሉን።(ከዚያም እሱም ግልገልሙሴውም በማህበሩ ፊት ይሰግዳሉ(ያደገድጋሉ))
ሕዝብ(ተማሪው ሁሉ) በአንድነት :--ይቅር

ካህን/ዲ/ን:- ይቅር እንዳልን ይቅር ይበለን...አቡነ ዘበሰማያት

ዲ/ን:- ሦስት ጊዜ በማጨብጨብ>>ስብሐት ለአብ..
ካህን/ዲ/ን:- ጸሎት..አቡነ ዘበሰማያት(የመጨረሻ ጸሎት ማሳረግ)(አባታችን ሆይ)

Riferal Gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

30 Nov, 05:59


#ኅዳር_21

እንኳን ለዓመታዊ በዓለ ጽዮን ማርያም በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን

#ቅድስት_ጽዮን_ድንግል_ማርያም

ኅዳር ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓልዋ መታሰቢያ ነው።

"ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው። አንድም በምሥጢሩ "ማሕደረ አምላክ" ማለት ነው። ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል።

እግዚአብሔር ከዘመነ አበው በሁዋላ በጊዜው ለእሥራኤላውያን ክብር፣ ሞገስ፣ አምባ የምትሆናቸውን ታቦተ ጽዮንን በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት ሰጥቷቸዋል። (ዘጸ. 31፥18) ከዚያም ለ500 ዓመታት ከእነሱ ጋር በመሆኗ በፈጣሪና በእነሱ መካከል ድልድይ ሆና ኖራለች።

ከዚያም ባለቤቱ ሲፈቅድ በዘመነ ሳባ በቀዳማዊ ምኒልክ (እብነ መለክ-እብነ ሐኪም) አማካኝነት ወደ ኢትዮዽያ መጥታለች። እነሆ በሃገራችን የ3ሺ ዓመት ቆይታዋን ልትደፍን የቀራት ጥቂት ዓመታት ብቻ ናቸው። ጌታ እንደ ፈቀደ ቅዱስ መስቀሉንና ታቦተ ጽዮንን ይዘን ይሔው በቸርነቱ እንኖራለን።

ያም ሆኖ ታቦተ ጽዮንን መስረቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀሳጢዎች እንዳሉ እናውቃለን። ግን አንጨነቅም። ምክንያቱም የመጣችውም የምትጠበቀውም በፈቃደ እግዚአብሔር ነውና እንጸልያለን እንጂ አንጨነቅም። በተለያየ ወሬም ራሳችንን አናማጥንም። ባለቤቱ እንድትሔድ ከፈቀደ ደግሞ ማንም ጉልበተኛ አያስቀራትም።

ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን፣ ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች። "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው። "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው።

"ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው። ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል። ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው። በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን። (2ቆሮ.6፥16 ፣ ራዕይ.11፥19)

በመጨረሻም ኅዳር ሃያ አንድ ቀን ጽዮን ማርያምን የምናከብርባቸውን ምክንያቶች እንመለከታለን።

#በዚህች_ቀን:-
✞ ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን) ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን።

✞ ታቦተ ጽዮን በምርኮ በሄደችበት በሀገረ ፍልስጤም ዳጎን የተባለ የአህዛብን ጣኦት አድቅቃ በድል የተመለሰችበትን ዕለት በማሰብ።

✞ በዘመነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በአሚናዳብ ሠረገላ ሁና ከአቢዳራ ቤት ስትመጣ ቅዱሱ ንጉሥ በታላቅ ሐሴት በፊቷ ዘመረ። አገለገለ። ምድራዊ ክብሩን እስኪረሳ ድረስ ለታቦተ አምላክ የተቀኘላት በማሰብ።

✞ ታቦተ ጽዮን ንጉሥ ሰሎሞን ወደ ሠራላት ቤተመቅደስ በክብር የገባችበትን ዕለት በማሰብ፤

✞ የቀደሙ ነብያት ስለእመቤታችን በተለያየ አምሳል ያዩበት ለምሳሌ፦ ነብዩ ዕዝራ በሃገር መንፈሳዊት፣ ሕዝቅኤል በተዘጋች ቤተመቅደስ፣ ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ ወዘተ ያዩበትን ዕለት በማሰብ፤

✞ ቀዳማዊ ምኒሊክ ከዐሥራ ሁለቱ ነገድ እስራኤል የበኩር ልጅ ጋር ሊቀ ካህናቱን አዛሪያስንና ታቦተ ጽዮንን ይዞ አክሱም የደረሰበትን ዕለት በማሰብ፤

✞ በዘመነ አፄ ባዜን (በ4 ዓ/ም አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ጽዮን በስደት መጥታ ገብታለች። በዚህ ጊዜም 2ቱ ጽዮኖች ሲገናኙ ታላቅ ብርሃን አክሱምን ውጧታልና ይህንንም በማሰብ፤

✞ በአብርሃ ወአፅብሃ ዘመነ መንግስት ክርስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ሆኖ አዋጅ የታወጀበትን በማሠብ፤

✞ አብርሃ ወአጽብሃ በወርቅና በዕንቁ ያሠሩት ባለ አሥራ ሁለት ክፍል ቤተ መቅደስ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ዕለት በመሆኑ፤

✞ በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዮዲት ጉዲት አብያተ ክርስቲያንን ስታቃጥል ታቦተ ጽዮንን ይዘው ወደ ዝዋይ ሀይቅ ከተሰደዱ በኋላ ዘመነ ሰላም ሲጀመር አክሱም በነበሩ ካህናት አስታዋሽነት ከዝዋይ ወደ አክሱም የገባችበት ዕለት በመሆኑ፤

በእነዚህ ምክንያቶች በመላው ኢትዮጵያ በተለይም በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ከፍ ባለ መንፈሳዊ በዓል እናከብራለን።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን 🙏
እኛንም በእመቤታችን በጸሎቷ የሚገኝ በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋር ይኑር።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

29 Nov, 07:37


ለእመቤታችን ጽዋ መርሀግብር ላይ የሚዘመሩ መዝሙሮች። ሁላችንም በአንድነት እናታችን ጽዮን እያልን እናመሰግናለን🤲

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

28 Nov, 15:10


🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲
💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

የጸሎት ጥበብ

ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገርን የተረዳ ያወቀ ሰው እግዚአብሔርን እንደሚገባ'ው አድርጎ ሲያነጋግረው ከዚያን ጊዜ አንሥቶ መልአክ ይኾናል፡፡ ነፍስ ከፈቃዳተ ሥጋ ሰንሰለት ነጻ የምትወጣው በዚህ መንገድ ነውና፤ ሕሊና ከፍ ከፍ የሚለው በዚህ መንገድ ነውና! ማደሪያችን ወደ ሰማይ የሚሻገረው በዚህ መንገድ ነውና፤ አንድ ሰው ግብረ ዓለምን የሚንቀው በዚህ መንገድ ነውና፤ አንድ ሰው የቱንም ያህል ነዳይ ወይም ባሪያ ወይም ተራ ወይም ዝቅ ያለ ቢኾንም እንኳን በንጉሥ ዙፋን ፊት የሚቆመው በዚህ መንገድ ነውና፡፡ እግዚአብሔር የሚመለከተው የንግግርን ውበት ወይም የቃልን ርቱዕነት ሳይኾን የመንፈስን ንጹህነት ነውና፡፡ በዚህ መንገድ መጥተን ወደ አእምሮአችን የመጣውን ብንናገርም እንኳን፥ ጸሎታችን ግዳጅ የሚፈጽም ኾኖናልን እንመለሳለን፡፡

እንግዲህ ይህን ማድረግ ምን ያህል ቀላል እንደ ኾነ ታስተውላለህን? በዚህ ዓለም ሰዎች ዘንድ አንድ ሰው ሌላውን ሰው ለመለመን የንግግር ክህሎት (ብልሐት) ያሻዋል፡፡ የሚለመነው ሰው በቀላሉ የማይገኝ ከኾነ ደግሞ አጃቢዎቹን ማሳመን ይኖርበታል፡፡ ጥሮ ለፍቶ ካገኘው በኋላም ጉዳዩን በዝርዝር ማስረዳት ይጠበቅበታል፡፡ እግዚአብሔርን ለማናገር ግን የዚሁ ተቃራኒ ነው፡፡ ከተሰበረ ልብ በቀር ሌላ ምንም ምን አያስፈልግም፤ ወደ እርሱ ለመቅረብም የሚከለክል ማንም አይኖርም፡፡ “እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ ሩቅ አምላክ አይደለሁም” ይላልና (ኤር.23፥23)፤ የምንርቀው እኛ ነን እንጂ እርሱ ዘወትር ቅርብ ነው፡፡

እግዚአብሔርን ለማነጋገር የንግግር ክህሎት (ብልሐት) አያስፈልገንም የምለውስ ለምንድን ነው? እንዲያውም ብዙ ጊዜ ድምፅም ቢኾን አያስፈልገንም፡፡ አንተ በልብህ ብትናገርና እግዚአብሔርን ማናገር እንዲገባ'ህ ብታናግረው እርሱ ጸሎትህን ለመስማት ዘንበል ይላል፡፡ ሙሴ ጸሎቱ የተሰማው በዚህ መንገድ ነውና፤ ሐና ጸሎትዋ የተሰማው በዚህ መንገድ ነውና፡፡ ወደ እግዚአብሔር እንዳይቀርቡ ብሎ ሕዝቡን ለማራቅ የሚቆም ወታደር የለም፤ አሁን ሰዓቱ አይደለም ብሎ የሚከለክል ዘበኛም የለም፡፡ እግዚአብሔርም፦ “አሁን ላነጋግርህ አልችልም፤ ሌላ ጊዜ ተመለስ” አይልም፡፡ ይልቅ ልታነጋግረው በመጣህበት ቅጽበት አንተን ለመስማት ይቆማል የምሳ ሰዓትም ቢኾን፣ የአራት ሰዓትም ቢኾን፤ እጅግ አስቸጋሪ ጊዜም ቢኾን፣ በገበያ ቦታም ቢኾን፣ በመንገድ ላይም ቢኾን፤ በባሕር ውስጥም ቢኾን፣፤ በዳኛ ፊት በምትቆምበት በችሎት ፊትም ቢኾን፥ እግዚአብሔርን ብትጠራው መጥራት እንደሚገባህ አድርገህ እስከ ጠራኸው ድረስ ጸሎትህን እንዳይሰማ የሚከለክለው ግድግዳ የለም፡፡

"የክርስቲያን መከራና ሌሎችም በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ"

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

27 Nov, 02:00


“እኔም ወንጌልን ማድረስ እችላለሁ” የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ሰብስክሪብሽን ዘመቻ ተቀላቀሉ።

Subscribe and share

https://youtube.com/@eotcmk?si=_we8ZKBkbmex6PJ3

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

26 Nov, 07:54


ንስሐ


ወንድሞቼ ሆይ! ጊዜ ሳለልን #ንስሐ እንግባና ለንስሐ የሚገባ ፍሬ እናፍራ፡፡ ጌታችን ምን እንዳለ እስኪ አድምጡ፡- “ንስሐ
ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይኾናል” /ሉቃ.15፡7/፡፡

ወንድሞቼ ሆይ! ስለምን ታድያ በኃጢአት፣ በስንፍና፣ በንዝህላል እንደተያዘዝን እንቆያለን? ስለምንድነው ተስፋ ቆርጠን የምንቆዝመው? በእኛ ንስሐ መግባት ምክንያት በሰማያት ታላቅ ደስታ የሚሆን ከሆነ ምንድነው የሚያስፈራን? ቅዱሳን መላዕክት ስለ እኛ ንስሐ እጅግ ደስ የሚላቸው ከሆነ ስለምንድነው እኛ ልል ዘሊል፣ ደንታ ቢስና ፈዛዛ የምንሆነው? የመላዕክት ጌታ ንስሐ ግቡ እያለ አስተምሮን ሳለ ምንድነው የምንፈራው? የማይከፈሉ ሦስት፣ የማይጠቀለሉ አንድ የሚሆኑ ሥላሴ ንስሐ እንገባ ዘንድ እየጠሩን ሳለ እኛ ያለምንም የንስሐ ፍሬ እንቆይ ዘንድ አግባብ ነውን?

ተወዳጆች ሆይ! በዚህ ጊዜአዊ ዓለም ርኵሰት ጣዕም አንታለል፡፡ እንዲህ ካልሆነ ግን እሳቱ የማይጠፋ ትሉ የማያንቀላፋ ምረረ ገሃነም ይጠብቀናል፡፡ ስለዚህ ከዘለዓለማዊው እሳት እንድን ዘንድ አሁን ጥቂት ብናለቅስ ይሻለናል፡፡

ተወዳጆች ሆይ! እስኪ እናስተውል፡፡ ስለምንናገረው ነገርም ችላ የሚለው ሰው ከቶ አይገኝ፡፡ ክርስቶስ ድንገት እንደ ብርሃን ብልጭታ ይመጣልና፡፡ ክርስቶስ ድንገት በመጣ ጊዜ በዙፋኑ ላይ ተቀምጦም ለሁሉም እንደየሥራው ሲከፍለው ማየት አያስፈራምን? የዚያን ጊዜ ሁሉም የየራሱን ሸክም ይሸከማል፡፡እያንዳንዱ ሰው በዚህ ምድር የዘራውን ያጭዳል፡፡ ሁሉም ዕራቆቱ ይቆማል፡፡ ሁሉም ወደ ክርስቶስ የፍርድ ዙፋን ይቀርባል፡፡ የዚያን ጊዜ ማንም ማንንም መርዳት አይችልም፡፡ ወንድም ወንድሙን ወይም ጓደኛ ጓደኛውን መርዳት አይችልም፡፡ ወላጆች ልጆቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ልጆች ወላጆቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ባሎች ሚስቶቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ሁሉም በፍርሐትና በረዐድ በመንቀጥቀጥም የእግዚአብሔርን ፍርድ ይጠብቃል እንጂ ማንም ማንንም መርዳት አይችልም፡፡

ወንድሞቼ ሆይ!ታድያ ለምንድነው ጊዜ ሳለልን የምንሰንፈው? ለምንድነው ልል ዘሊል የምንሆነው? ለምንድነው በምግባር በሃይማኖት የማንዘጋጀው? ለምንድነው ጊዜ ሳለልን የማናስተውለው? ለምንድነው ቃለ ሕይወትን ለመስማት የማንቻኰለው? ስለምንድነው ቃለ እግዚአብሔርን የማንሰማው? ስለምንድነው ቃለ ክርስቶስን ችላ የምንለው? ቃሉ በዚያ ሰዓት እንደሚፈርድብን አትገነዘቡምን? ቃለ ነቢያት ቃለ ሐዋርያት በዚያ ሰዓት እንደሚፈርድብን አታውቁምን? ካላወቃችኁ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ ያላቸውን አድምጡ፡- “የሚሰማችሁ እኔን ይሰማል፤ እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል” /ሉቃ.10፡16/፡፡ ዳግመኛም በሌላ አንቀጽ እንዲህ ብሏል፡- “የሚጥለኝ ቃሌንም የማይቀበለው ርሱ የሚፈርድበት አለው፤ እኔ የተናገርኩት ቃል ርሱ በመጨረሻው ቀን ይፈርድበታል” /ዮሐ.12፡48/፡፡ በመጨረሻው ቀን የሚፈርድብን ቃሉስ የትኛው ነው? በወንጌሉ እንዲሁም በሐዋርያትና በነቢያት አድሮ የተናገረው ቃሉ፡፡ እንኪያስ ወንድሞቼ ሆይ! ቃሉን ችላ የምንለው አንኹን፡፡ “ሰማይና ምድር ያልፋሉ፤ ቃሌ ግን አያልፍም” ያለውን አንርሳው /ማቴ.24፡35/፡፡

እንኪያስ እጅግ የምወዳችሁ ሆይ! ኑ! አስፈሪው ቀን ሳይመጣ ቃሉን ሰምተን ንስሐ እንግባ፡፡ የእግዚአብሔርን ምሕረት እንቀበል፡፡ እግዚአብሔር ዛሬ ምሕረቱን እንድንቀበል እንዲህ እያለ ያበረታታናልና፡- “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ” ማቴ.11፡28፡፡ በዚህ ቃሉ ትዕግሥተኛው፣ አፍቃሪውና ሰው ወዳጁ ጌታ ሁላችንም እንድን ዘንድ ይጠራናል፡፡ የጠራው የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ አይደለም፤.“ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ” ብሎ ሁላችንም እንጂ፡፡ “ባለጸጋም ቢሆን ድኻም ቢሆን ሁሉም ወደ እኔ ይምጣ፡፡ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም፡፡ ወደ እኔ የሚመጣውስ ማን ነው ትዕዛዛቴን የሚጠብቀው፤ ቃሌን የሚሰማው፤ በላከኝም የሚያምነው፡፡” የክርስቶስን ቃል ሰምቶ ንስሐ የሚገባው ንስሐም ገብቶ የንስሐን ፍሬ የሚያፈራ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ የማይሰማው ግን እጅግ ጐስቋላ ሰው ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፡- “በሕያው እግዚአብሔር እጅ መውደቅ የሚያስፈራ ነው” /ዕብ.10፡31/፡፡

#ቅዱስ_ኤፍሬም

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

25 Nov, 11:46


የቅዳሴ ተሰጥዖ እና የግዕዝ ትምህርትን ለመማር የምትፈልጉ


ማኀበረ ቅዱሳን ሀዋሳ ማእከል ዜማ እና ሥነ-ጥበባት ዋና ክፍል የቅዳሴ ተሰጥዖ እና የግዕዝ ትምህርትን ለመማር ለምትፈልጉ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አማኞች ለሆኑት በሙሉ ለማስተማር ምዝገባ ጀምሯል።

🏷ትምህርቱ የሚሰጥባቸው ቀኖች ሰኞ እና እሁድ ከ11:30 - 1:00

🏷ምዝገባ የሚያልቀው እስከ ኅዳር 19/2017

🏷ስልክ ቁጥር፡
0961957492
0927146731

https://t.me/referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

21 Nov, 11:12


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

🛎ድንቅ የምሥራች ለግቢ ጉባኤ ተማሪዎች በሙሉ!

ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ታላቁ ምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በተመራቂ(GC) ተማሪዎች እነሆ!

ይህ ልዩ የጉዞ መርሐግብር በብዙዎች በተለይ በተመራቂ(GC) ተማሪዎች በጉጉት የሚጠበቅ ቢሆንም ብዙውን የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ለማሳተፍ ስለታሰበ አስቀድመን ለማሳወቅ ወደድን፡፡

በቅርብ ቀናት ቦታው ደርሰው የመጡ ወንድም እኅቶቻችን ድንቅ ድንቅ ነገርን ነገረውናል፡፡ እንደውም ቢችሉ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ሁሉም ቦታውን ረግጠው በረከትንና ከአእምሮ ሊጠፋ የማችል ድንቅ ታምራትን አይተውና ሰምተው ቢመጡ መልካም ነው ብለውን ከገዳሙም ሌላ ብዙ ሚጎበኙ የበረከት ቦታዎች እንዳሉም ነግረውና፡፡ ታዲያ ማን ይቀራል? በተለይ GC አይታሰብም! የጉዞ ትልቁ አላማውም GC ተማሪዎች በመጨረሻ ሰዓት በዚህ ታላቅ ስፍራ ተሰብስቦ የማይረሳ ትውስታ መፍጠር ነው፡፡ብዙ መርሐግብራትም ተካተውበታል !

ጉዞው ታህሣሥ 5 እና 6(ቅዳሜና እሁድ) ሲሆን የጉዞ ዋጋ ለተመራቂ #1000ብር እና ተመራቂ ላልሆኑ #900ብር ብቻ ነው፡፡ ይህ ጉዞ ታላቅና ብዙውን ተሳታፊ የሚያደርግ ስለሆነ ቅድመ ሆኔታ፦ ጉዞ የሚሄድ ተማሪ በዚህ 8 ቀናት ውስጥ ለኮሚቴው ማሳወቅ ጊዴታ ነው፡፡ (መኪና &ምግብ) በተማሪ ቁጥር ማዘጋጀት ስላለብን!

👉ከዛሬ ጀምራችሁ በዚህ Account ብር አስገቡ፡፡ Screenshot መላክና ማሳወቅ እንዳትረሱ፡፡
1000348784696 adelhue T/tsadik wolede(0902292431)
1000405654982 Hana koru (0991200370)
ለበለጠ መረጃ፦@Getcch21
@Yemariyamlijh
ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ GC ተማሪዎች ኮሚቴ!!

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

21 Nov, 05:18


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን

ኅዳር 12-ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚበር ንሥረ አርያም የሚባል ውዳሴው እንደ ማር የጣፈጠ ንዑድ ክቡር የሆነ ለፍጥረቱ ሁሉ የሚማልድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የተሾመበት ዕለት ነው፡፡

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል፡- ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚ-መኑ' ካ-ከመ' ኤል-አምላክ ማለት ሲሆን በአንድነት ሲነበብ ‹‹መኑ ከመ አምላክ-እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው›› ማለት ነው፡፡ አንድም ለእግዚአብሔር አሸናፊ ድል አድራጊ የቸርነትና የርህራሄ መገኛ መዝገብ ማለት ነው፡፡
ገናናው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ዲያብሎስን ወደ ጥልቁ ጥሎት በእርሱ ምትክ ከሁሉ የበላይ ሆኖ በተሾመበት በዚህ ዕለት በበዓሉ መታሰቢያ በኅዳር 12 ቀን የክብር ባለቤት በሆነ በእግዚአብሔር ፈቃድ ክንፎቹን ወደ ሲኦል ያወርዳል፣ ኃጥአንንም ወደ አዲሲቱ ምድር ያወጣቸዋል ይኸውም የመላእክት አለቃ የሚካኤል ሠራዊት ይሆናሉ፡፡ ይቅርታ የተደረገላቸውና ምሕረት አግኝተው በአንድ ጊዜ በክንፉ ያወጣቸው ስፍር ቁጥር የላቸውም፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በየዓመቱ በኅዳር 12 ቀን እንዲህ እያደረገ እልፍ ነፍሳትን ያወጣል፡፡ የቤተ ክርስቲያን ወገኖች የሆኑትን ሁሉ እንደሥራቸው ወደ ምሕረት ቤት ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ይወስዳቸዋል፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ አብ መጋረጃ ውስጥ ይገባል፣ በዚህች ዕለት ምድራዊትና ሰማያዊት ስለሆነች ምሕረቱም ከመንበሩ በታች ይሰግዳል፡፡ ስለውኃ ምንጮች፣ ስለ ወይን ቦታዎች፣ ስለ ምድር ፍሬዎች በምድርም ላይ ስለሚኖሩ ስለ ሰው ልጆች ነፍስ ሁሉ፣ ስለ እንስሳትም፣ ስለ ሰማይ ወፎችም፣ ስለ ባሕር ዓሣዎችም፣ በምድር ላይና በባሕር ውስጥ ስለሚንቀሳቀሱ ሁሉ የምሕረት ባለቤት ከሆነ ከአብ ዙፋን በታች ሁልጊዜ በማመስገን ይሰግዳል፤ ልመናውንም እስኪሰማውና የምሕረትንም ቃል እስኪያስተላልፍለት ድረስ ከእግረ መንበሩ ሥር አይነሣም፡፡
ለዚህ ዓለም ምሕረትን የሚለምኑ ቅዱሳን መላእክትም በየዓመቱ ኅዳር 12 ቀንበእግዚአብሔር የዙፋኑ ዓውደ ምሕረት ዙሪያ ተሰብስበው ስለ ሰውና ስለ እንስሳትም ሁሉ ምሕረትን የሚለምን ቅዱስ ሚካኤል ከአብ መጋረጃ ውስጥ በወጣ ጊዜ ቸርና መሐሪ አብ ለቅዱስ ሚካኤል የሰጠው ልብሱን እነዚያ መላእክት ይመለከታሉ፣ ይቅርታን የማግኘት ምልክታቸው ነውና፡፡ ስለዚህ እነዚህ ቅዱሳን መላእክት በምድር ላይ ምሕረት እንደተደረገ ሰውንም እንስሳትንም ይቅር እንዳለ በዚህ ዓለምም የሚሆነውን ሁሉ አይተው ቅዱስ ሚካኤል በለበሰው ልብስ አምሳል ያውቁታል፡፡
ስንክሳሩ እንደሚለው ይህ እጅግ የከበረ ገናና መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ‹‹ከቅዱሳን ሰማዕታት ጋራ በመሆን ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ የሚያጽናናቸውና የዘወትር ጠባቂአቸው ሆኖ የሚራዳቸው እርሱ ነው፡፡›› የብዙዎቹንም ቅዱሳን ገድል ስንመለከት የዘወትር ጠባቂያቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡
ቅዱሳን በሕይወት ሳሉ ይህ ገናና መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ረዳትና የዘወትር ጠባቂ፣ እንደጓደኛም አማካሪ ሆኖ የተበቃቸውን ስንቱን ቅዱሳን ዘርዝረን እንቸላለን፡፡ እርሱ ያልረዳው ቅዱስ የለም፡፡ መከራውን ያላስታገሰው ሰማዕት የለም፡፡ ለቅዱሳኑ እንዲህ እንደጓደኛቸው ሆኖ ሲጠብቃቸው ይኖራል፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ሚካኤል ለኃጥአንና አምላካቸውን ለካዱ ሰዎች ደግሞ በቁጣ ለመቅሰፍት ይመጣባቸዋል፡፡ ሰናክሬም በእግዚብሔር ላይ ክፉ በመናገሩ በአንዲት ሌሊት ብቻ 185,000 (መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ) ሠራዊቱን ቅዱስ ሚካኤል በብርሃን ሰይፉ ፍጅቷቸው አድሯል፡፡ 2ኛ ነገ 19፡35፣ ኢሳ 37፡36፡፡
እግዚአብሔርን ለሚወዱና እርሱንም ለሚያከብሩት መታሰቢያውንም ለሚያደርጉለት ግን ከሚፈልጉት ነገር ከቶ አያሳጣቸውም፣ ዘወትርም ይጠብቃቸዋል፣ በኋላም በአማላጅነቱም ከሲኦል እሳት ያድናለቸዋል፡፡ እነሆ ይህ ገናና ክቡር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡- ‹‹የእግዚአብሔር ወዳጅ የሆነ ስሙ ዱራታዎስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ የሚስቱም ስም ቴዎብስታ ነው፡፡ እነርሱም ሁልጊዜ ያለማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ ያደርጉ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ በሀገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ፡፡ ለቅዱስ ሚካኤልም ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉትን እስኪያጡ ድረስ ቸገራቸው፡፡ ዱራታዎስም ሸጦ ለመልአኩ በዓል መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ የእርሱንና የሚስቱን ልብስ ይዞ ወጥቶ ሄደ፡፡
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም በታላቅ መኮንን አምሳል ለዱራታዎስ ተገለጠለትና ወደ ባለጸጎች ሄዶ በእርሱ ዋስትና በአንድ ዲናር አንድ በግ እንዲወስድ፣ ሁለተኛም ወደ ባለ ስንዴ ዘንድ ሄዶ በእርሱ ዋስትና ስንዴን እንዲወስድ ዳግመኛም ወደ ዓሣ አጥማጅ ዘንድ ሄዶ አንድ ዓሣ እንዲወስድ ነገር ግን ወደቤቱ ሳይርስ የዓሣውን ሆድ እንዳይቀድ አዘዘው፡፡ ዱራታዎስም እንደታዘዘው አደረገ፡፡ ወደቤቱም በተመለሰ ጊዜ ቤቱ ሁሉ በበረከት ተመልቶ አገኘው፡፡ እርሱም እጅግ ተደስቶ የዚህን የክበር መልአክ የመታሰቢያውን በዓል አደረገ፡፡ ጦም አዳሪዎችንና ድኆችን ጠርቶ አጠገባቸው፡፡
ከዚህም በኋላ ለዱራታዎስና ለሚስቱ ቅዱስ ሚካኤል ሁለተኛ ተገለጠላቸው፡፡ ዱራታዎስንም የዓሣውን ሆድ እንድሰነጥቅ አዘው፡፡ በሰነጠቀውም ጊዜ 300 የወርቅ ዲናር በዓሣው ሆድ ውስጥ ተገኘ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ዱራታዎስንና ሚስቱን ቴዎብስታን እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ከዚህ ዲናር ወስዳችሁ ለባለ በጉ፣ ለባለ ዓሣውና ለባለ ስንዴው ዕዳችሁን ክፈሉ፡፡ የቀረውም ለፍላጎታችሁ ይሁናችሁ እግዚአብሔር አስቧችኋልና በጎ ሥራችሁን፣ መሥዋዕታችሁንና ምጽዋታችሁን አስቦ በዚህ ዓለም አሳመረላችሁ፣ በኋለኛውም መንግሥተ ሰማያትን አጀጋጀላችሁ›› አላቸው፡፡
እነርሱም ይህን ነገር ሲሰሙ ደነገጡ፡፡ የከበረ ገናናው መልአክም ‹‹ከመከራችሁ ሁሉ ያዳንኳችሁ የመላእክት አለቃ እኔ ሚካኤል ነኝ፣ መሥዋዕታችሁንና ምጽዋታችሁን ወደ እግዚአብሔር ፊት ያሳረግሁ እኔ ነኝ፡፡ አሁንም በዚህ ዓለም ከበጎ ነገር እንድታጡ አላደርጋችሁም›› አላቸው፡፡ ይህንንም ከነገራቸው በኋላ ወደ ሰማያት ወጣ፡፡ እነርሱም በፍርሃትና በክብር ሰገዱለት፡፡››
የመላእክት አለቃ ቅዱስ የሚካኤል ጥበቃው አይለየን! ከበዓሉ በረከት ይክፈለን!

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

20 Nov, 06:18


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) pinned «»

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

19 Nov, 17:10


#መልካም_ፈተና

<< ሥራህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፤ ዐሳብህም ትጸናለች። >> (ምሳ. 16፥3)

ነገ(ህዳር 11) የQualification ፈተና ለምትጀምሩ CII ተማሪዎች ግቢ ጉባኤያችን የቀና  ያማረ እና የሠመረ ይሆንላችሁ ዘንድ መልካም ምኞቱን ይገልጻል ።


📖 የአባቶቻችን የአብርሃም ፥ የይስሐቅ ፥ የያዕቆብ አምላክ ማስተዋሉን ፥ ጥበቡን ፥ አእምሮውን ያድላችሁ! 📖


🙏🙏እስራኤል ዘስጋን ከግብፅ ባርነት ያወጣ።  ሰለስቱ ደቂቅን ከእሳቱ ነበልባል ያዳነ። በማይነገር ፍቅሩ ከዙፋኑ ወርዶ የዘላለም ልጅነትን የሰጠን አምላከ አበው በሁሉ ይከተላችሁ !!!

መልካም ፈተና
!

ሀዋሳ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ
ህዳር 2017 ዓም


@referal_gibi    @referal_gibi
@referal_gibi    @referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

18 Nov, 13:31


የሪፈራል ግቢ ጉባኤ ምሩቃን ኅብረት

ሰላም ውድ ከግቢ ጉባኤያችን የተመረቃችሁ ቤተሰቦቻችን::

ከግቢ ከተመረቃችሁ ስንት ዓመት ሆኖዎታል:: ግቢ እያላችሁ የማይረሱ ጊዜያትን አብረዋችሁ ያሳለፋችሁ ወንድምና እኅቶቻችሁ ጋር ምን ያህል ትገናኛላችሁ?

ይህቺን የብዙዎቻችን ትልቁን የሕይወታችንን ታሪክ የምትይዘውን  ግቢ ጉባኤያችንንስ እንጠይቃለን??

ከላይ ላሉት ጥያቄዎች መልስ መመለስ ካቃተን ወይም በመልሶቻችን እርካታ ካልተሰማን ችግሩን የሚያቀልልልን በእርግጠኝነት የግቢ ጉባኤ ምሩቃን ኅብረት ያስፈልገናል ማለት ነው::

ይህ ህብረት ከተመሰረተ:-
    ለያንዳንዱ ባች ተወካይ ይኖረዋል

   ከግቢ ጉባዔ ስራ አስፈጻሚ ጋር በመሆን በአማካይ ለብዙዎቻችን የሚመቸውን የመገናኛ (ምስረታ) ቀን እንወስናለን::

የምስረታ መርሐግብራት ይዘት ይበልጥ ተሳታፊን ያማከለና እንግዶችን ከእንግዶችና ከተማሪዎች የሚያገናኝ እንዲሆን ከምስረታ committee ጋር ይሰራበታል::

በተወካዮቻችን በኩል የግቢ ጉባኤያችንን project'ዎች እናግዛለን

እናም ለነዚህ እና ሌሎች ሲባል የግቢ ጉባኤ ምሩቃን ኅብረት ለመመስረት ታቅዷል::

      @Sehinemaryam
      @BayeB21
@Dnobse

ሀሳቦቻችሁን አጋሩንና ወደ ትግበራ እንገባለን::

@referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

18 Nov, 03:40


💠💠ቶማስ ዘመርዓስ💠💠


የዚህንም አባት ትሩፋቱንና ገድሉን ሰው ተናግሮ ሊፈጽመው አይችልም እርሱ አስቀድሞ በጾም በጸሎት በስጊድ ቀንና ሌሊትም በመራራት ተጠምዶ የሚኖር ነው ። ከዚህም በኃላ መርዓስ ለሚባል አገር ኤጲስቆጶስ ይሆን ዘንድ የክብር ባለቤት ጌታችን መረጠው መንጋውንም እንደ ሐዋርያት ጠበቀ ። ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስም በነገሠ ጊዜ ክርስቲያኖችን ያሠቃያቸው ዘንድ ከመኳንቶቹ አንዱ ወደዚያች አገር ደረሰ እርሱም ቅዱስ ቶማስን ወደርሱ ያቀርቡት ዘንድ ጭፍሪቹን ላከ እነርሱም እየደበደቡ በምድር ላይ እየጎተቱ ወሰዱት ደሙም እንደውኃ ፈሰሰ ።

ከዚህም በኃላ መኮንኑ ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት ስገድ አለው ቅዱሱም እንዲህ ብሎ መለሰለት እኔ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለረከሱ ጣዖታት የሚሰግድ ሁሉ የተረገመ ነውና ።

መኰንኑም ተቆጥቶ እጅግ የበዛና ዕፁብ ድንቅ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው የነዳጅ ድፍድፍና አፍልተው በላዩ በአፉና በአፍንጫው ውስጥ ጨመሩ እንዲህም እያደረጉበት እስከ ብዙ ዘመናት ኖረ።

የእሊህ ከሀዲያን ልባቸው እንደ ድንጊያ የጸና ስለሆነ ቅዱስ ቶማስ ቶሎ እንዲሞት አልፈለጉም። ሌሎች ብዙዎች ሰዎችን ያሰፈሩአቸው ዘንድ የክብር ባለቤት ክርስቶስንም ይክዱት ዘንድ የሥቃዩን ዘመን አስረዘሙ እንጂ።

እርሱ የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል የጸና ነውና ማሠቃየቱን ከሀድያን በተቸነፉ ጊዜ ስለ ስሕተታቸውም ይዘልፋቸው ስለነበር ስለዚህ በጨለማ ቦታ ጣሉት በዚያም ሃያ ሁለት ዓመት ኖረ።

ከሀድያንም በየዓመቱ ወደርሱ ገብተው ከሕዋሳቱ አንዱን ይቆርጣሉ። በዚያም ቦታ አፍንጫውን ከንፈሮቹን ጆሮዎቹን እጆቹንና እግሮቹን ቆረጡ መንጋዎቹም ያረፈ መስሏቸው በየዓመቱ መታሰቢያውን ሲያደርጉ ኖሩ። ነገር ግን አንዲት ክርስቲያናዊት ሴት በጣሉት ጊዜ ስለአየችው ቦታውን ታውቅ ነበር እርሷ በሌሊት ወደርሱ ተሠውራ በመሔድ ትመግበዋለች ። ጻድቅ ቁስጠንጢኖስም እስከ ነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከ ገለጠ ድረስ እንዲህ ሲሠቃይ ኖረ።

ይህም ንጉሥ ክርስቶስን በመታመን የታሠሩ እሥረኞችን ሁሉ በሀገሮች ሁሉ በወህኒ ቤት ያሉትን ይፈቷቸው ዘንድ አዘዘ።

ይችም ሴት ሒዳ ስለ ቅዱስ ቶማስ ከእርሱ የሆነውን ሃያ ሁለት ዓመት ተጥሎ እንደኖረ ለካህናቱ ነገረቻቸው በውስጡ ወደሚኖርበትም ቦታ መራቻቸው። እነርሱም አንሥተው ተሸከሙት እየዘመሩና እያመሰገኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት በቤተ መቅደሱም ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡት ምእመናንም ሁሉ ወደርሱ እየመጡ ከእርሱ ይባረኩና የተቆረጡ ሕዋሳቱን ይሳለሙ ነበር።

ንጉሥ ቂስጠንጢኖስም የከበሩ የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት ኤጲስቆጶሳትን የአንድነት ጉባኤን በኒቅያ አገር በሰበሰበ ጊዜ ይህ የከበረ ቶማስ ከእሳቸው አንዱ ነው።

ንጉሡም ወደ እንርሱ ገብቶ ሰላምታ ሰጣቸውና ከእርሳቸውም ቡራኬ ተቀበለ። የዚህ የቅዱስ ቶማስን ተጋድሎውን በነገሩት ጊዜ ወደርሱ ቀርቦ ሰገደለት ሕዋሰቱም ከተቆረጡበት ላይ ተሳለመው አዝኖና እጅግም አድንቆ ሕዋሳቱን ዳሠሠው ፊቱንና ዐይኖቹን አሻሸው።

ከሀዲ አርዮስንም ተከራክረው ከረቱ በኃላ አውግዘው ለይተው ከወገኖቹ ጋር ከቤተ ክርስቲያን አሳደዱት። ከዚህም በኃላ መንፈስ ቅዱስ እንደ አስተማራቸውና እንደመራቸው የሃይማኖትን ትምህርት በአንደበታቸው ተናገሩ ሕግና ሥርዓትን ሥጋዊና መንፈሳዊ ፍርድንም ሠሩ።

ከዚህም በኋላ ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ ሔደ ካህናቱንና መንጋዎቹን ሁሉ ሰብስቦ አነበበላቸው እርሱንም እንዲአስተውሉት እንዲጠብቁትም በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው። ጥቂት ዘመናትም ከኖረ በኃላ በሰላም በፍቅር አረፈ የሹመቱም ዘመን አርባ ዓመት ነው በዚህም እግዚአብሔርን አገለገለው።

በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

17 Nov, 07:19


❤️ በቀንዱ የማይበራታ ላሕም ተብሎ የተመሰገነው የወልደ እግዚአብሔር ቅዱስ ሥጋው የሚፈትትባት፤ ክቡር ደሙ የሚቀዳባት በአራቱ ኪሩቤል አምሳል አራት መአዝን ያላት ቤተ ክርስቲያንን በገጸ ላሕም አምሳል ገልጦ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ ስማቸውን በመጥቀስ ሲያወድሳቸው፦

[“ሰላም ለ፬ እንስሳሁ ለአብ እለ ይጸውሩ መንበሮ እለ ስሞሙ አግርሜስ ገጸ አንበሳ፡፡ አግርሜጥር ገጸ ሰብእ፡፡ ባርቲና ገጸ ላሕም፡፡ አርጣን ገጸ ንስር፡፡ ለቀዳማዊ ገጹ ከመ አንበሳ፤ በአምሳለ ፈጣሪሁ ዘውእቱ አብ፡፡ ለካልዕ ገጹ ከመ ሰብእ በአምሳለ ወልድ፤ ዘውእቱ ነሥአ ፍጹመ ስባኤ፡፡ ለሣልስ ገጹ ከመ ንስር በአምሳለ መንፈስ ቅዱስ ዘውእቱ አስተርአየ በርእየተ ርግብ በሥጋ፡፡ ወለራብእ ገጹ ከመ ላሕም በአምሳለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፤ እስመ ፬ቱ መኣዝኒሃ”፡፡]

(የአብ ዙፋኑን ለሚሸከሙና ስማቸውም የአንበሳ መልክ ያለው አግርሜስ፤ የሰው መልክ ያለው አግርሜጥር፤ የላም መልክ ያለው ባርቲና፤ የንስር መልክ ያለው አርጣን ለተባሉ ለአራቱ እንስሳ ሰላምታ ይገባል፤ የመዠመሪያው ፊቱ እንደ አንበሳ ነው፤ ያውም በፈጣሪው በአብ ምሳሌ ነው፤ የኹለተኛውም ፊቱ ያውም ፍጹም ሰውነትን ገንዘብ ባደረገ በወልድ አምሳል እንደ ሰው ነው የሦስኛውም ፊቱ ያውም አካል ባለው ርግብ አምሳል በተገለጠ በመንፈስ ቅዱስ አምሳል እንደ ንስር ነው፤ ያራተኛውም ፊቱ እንደ ላም ነው፤ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ፤ መኣዝኗ አራት ናቸውና) በማለት ሰላምታን አቅርቦላቸዋል፨

በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

17 Nov, 07:19


ኅዳር 8 የእግዚአብሔርን ዙፋን የሚሸከሙ የኪሩቤልና የሱራፌል ዓመታዊ በዓል፤ ክብራቸውና ስማቸው


ክብራቸው ታላቅ የኾኑት የኪሩቤልን ነገር ሊቁ ኤጲፋንዮስ “ስሞሙ ኪሩቤል ካህናተ ቅዳሴ ወውዳሴ እምታሕተ ሐቌሆሙ አሐዱ ወእምላዕለ ሐቌሆሙ አርባዕቱ እለ ግሉፋን በአዕይንት” ብሎ እንደገለጸው ኹለተኞቹ አመስጋኞች የኾኑት ዐሥሩን ነገድ ስማቸው ኪሩቤል ሲባሉ ከወገባቸው በታች አንድ ከወገባቸው በላይ አራት አድርጎ ሲፈጥራቸው ዐይናቸው ብዙ ነው፤ አለቃቸውም ኪሩብ ሲኾን የሰው መልክና የአንበሳ መልክ ያለው ነው፡፡

ሦስተኛውን ዐሥሩን ነገድ ስማቸው ሱራፌል ሲባል የእነዚኽ አለቃቸው የንስር መልክና የእንስሳ መልክ ያለው ነው፤ አለቃቸውም ሱራፊ ሲባል ሲፈጥራቸውም ስድስት ስድስት ክንፍ አድርጎ ፈጥሯቸዋል፨

ልዑል እግዚአብሔር ከነገደ ኪሩቤል ኹለት ገጸ ሰብእ እና ገጸ አንበሳን፤ ከሱራፌል ኹለት ገጸ ንስርና ገጸ እንስሳን አንሥቶ ከኢየሩሳሌም ሰማያዊት በላይ ከሰማይ ውዱድ በታች አቁሞ በነርሱ ላይ ሰማይ ውዱድን እንደ መረሻት ጫነባቸው፤ በላይም ሕብሩ በረድ የመሰለውን ዙፋን እንደ ሠረገላ ጭኖባቸዋል፤ እነዚኽንም በምሥራቅ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን፣ በደቡብ በአራቱ መኣዝን ዠርባቸውን ወደ ውስጥ ፊታቸውን ወደ ውጪ እያደረገ አቁሟቸዋል።

ነቢዩ ሕዝቅኤል ስለዚኽ ነገር በምዕ ፩፥፲፪ ላይ “እያንዳንዱም ወደ ፊት ቀጥ ብሎ ይኼድ ነበር መንፈስም ወደሚኼድበት ኹሉ ይኼዱ ነበር ሲኼዱም አይገላመጡም ነበር” በማለት እንደተናገረ ገጽ ለገጽ ሳይተያዩ ሥላሴ በፈቀዱት ፍኖት አንዱ በኼደበት ሦስቱ እየተከታተሉ ይኼዳሉ፡፡

እነዚኽንም እንደ ነቢዩ ሕዝቅኤል ገለጻ ፲፮ ሲኾኑ የቀሩት ከውስጥ ስለኾኑ ስለማይታዩ አራቱ ግን ብቅ ብቅ ብለው ስለሚታዩ ዮሐንስ አራት ብሏቸዋል እንጂ እንደ ሕዝቅኤል ገጻቸው ፲፮ ነው ይላሉ መተርጉማን፡፡

ሊቁ “እምርእሶሙ እስከ ሐቌሆሙ አርባዕቱ ወእምሐቌሆሙ እስከ እግሮሙ አሐዱ ከመ ርእየተ እለ ቄጥሩ ዘውእቱ ዖፍ ዘይነብር በሀገረ ፋርስ” እንዲላቸው፤ ሊቁ ቅዱስ ያሬድም “ከመ ርእየተ እለቄጥሩ ገጸ በገጽ ኢይትናጸሩ” ብሎ እንደገለጻቸው በፋርስ ሀገር የሚኖረው እለቄጥሩ የተባለውን ዎፍ ከወገቡ በታች አንድ ከወገቡ በላይ አራት እንደኾነ እነዚኽንም ከወገባቸው በታች አንድ ከወገባቸው በላይ አራት አድርጎ ፈጥሯቸዋል ፡፡

ዮሐንስ በራእዩ በምዕ 4:7-9 ላይ "ፊተኛውም እንስሳ አንበሳን ይመስላል፥ ሁለተኛውም እንስሳ ጥጃን ይመስላል፥ ሦስተኛውም እንስሳ እንደ ሰው ፊት ነበረው፥ አራተኛውም እንስሳ የሚበረውን ንስር ይመስላል። አራቱም እንስሶች እያንዳንዳቸው ስድስት ክንፎች አሉአቸው፥ በዙሪያቸውና በውስጣቸውም ዓይኖች ሞልተውባቸዋል፤ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የነበረውና ያለ የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እያሉ ቀንና ሌሊት አያርፉም" ይላቸዋል።

ኪሩቤልን “እለ ብዙኃት አዕይንቲሆሙ” አላቸው፤ ከላይ እስከ ታች ድረስ ዐይንን የተመሉ ናቸውና፤ ይኽስ አይደለም እንደ ብርሌ እንደ ብርጭቆ እያብለጨለጨ ለዐይን ባልተመቸም ነበር ብሎ ዐልፎ ዐይን ዐልፎ ዐይን ነው፤ እንደ አልጋ መለበሚያ እንደ ሱቲ መጠብር እንደ ቀሽመሪ መታጠቂያ፣ እንደ ነብር ለምድ፣ እንደ ዐይነ በጎ፣ እንደ ማር ሰፈፍ ይላሉ፤ ይኽስ አይደለም ብሎ ዐይናቸው ከአንገታቸው በላይ ሰድ ነው፤ ይኽም እንደ መስታዮት እያወለወለ እንደ ብርጭቆ እያንጸበረቀ አይደለም ብሎ ኀላፍያትን መጻእያትን የሚያውቁ ስለኾነ እንዲኽ አለ እንጂ ዐይናቸውስ ኹለት ነው ይላሉ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቀደምት መተርጉማን ፡፡

በኢሳ ፮፥፩-፫ ላይ፡- “ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔርን በረዥምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየኹት የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን መልቶት ነበር፤ ሱራፌልም ከርሱ በላይ ቆመው ነበር ለእያንዳንዱም ስድስት ክንፍ ነበረው በኹለት ክንፍ ፊቱን ይሸፍን ነበር በኹለቱም ክንፍ እግሮቹን ይሸፍን ነበር በኹለቱም ክንፍ ይበር ነበር፤ አንዱም ለአንዱ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ኹሉ ከክብሩ ተመልታለች እያለ ይጮኽ ነበር” ይላል ይኽ መሸፈናቸው ያድናቸዋል ቢሉ? ትእምርተ ፍርሀት ነው፤ ዛሬ በዚኽ ዓለም ሴቶችን ሕፃናትን እንመታችኋለን ባሏቸው ጊዜ እጃቸውን መጋረዳቸው የሚያድናቸው ኾኖ ሳይኾን ትእምርተ ፍርሀት እንደኾነ ኹሉ፡፡

አንድም በኹለት ክንፋቸው ፊታቸውን መሸፈናቸው ፊትኽን ማየት አይቻለንም ሲሉ በኹለት ክንፋቸው እግራቸውን መሸፈናቸው ከፊትኽ መቆም አይቻለንም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ ያደርጋሉ አለ ትእምርተ ተልእኮ ነው፡፡

አንድም በኹለት ክንፋቸው ፊታቸውን መሸፈናቸው ባሕርይኽን መመርመር አይቻለንም ሲሉ፤ በኹለት ክንፋቸው እግራቸውን መሸፈናቸው ባሕርይኽን መረማመድ መተላለፍ አይቻለንም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወዲያ ወዲኽ ያደርጋሉ ከእእምሮ ወደ አእምሮ ለመፋለሳቸው፡፡

አንድም ኹለት ክንፋቸውን ወደ ላይ አድርገው ይታያሉ አለ ወደላይ ቢወጡ ቢወጡ አትገኝም ሲሉ፤ ኹለት ክንፋቸውን ወደታች አድርገው ይታያሉ ወደታች ቢወርዱ ቢወርዱ አትገኝም ሲሉ፤ ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ ያደርጋሉ ወዲያና ወዲኽ ቢሉ አትገኝም ሲሉ፤

አንድም ወደላይ መዘርጋት በሰማይ ምሉእ ነኽ ሲሉ ወደታች መዘርጋቸው በምድርም ምሉእ ነኽ ሲሉ፤ ወዲያና ወዲኽ መዘርጋታቸው በኹሉ ምሉእ ነኽ ማለታቸው ነው፤

አንድም ወደላይ መዘርጋት ትእምርተ ተመስጦ ወደታች መዘርጋት ትእምርተ ትሕትና፤ ወዲያና ወዲኽ ረብቦ መታየት ትእምርተ ተልእኮ ነው

በአጠቃላይ ኹለት ክንፋቸውን ወደላይ ኹለት ክንፋቸውን ወደታች ኹለት ክንፋቸውን ወዲያና ወዲኽ አድርገው ትእምርተ መስቀል መሥራታቸው በብሉይ ኪዳን ከኾነ እንዲኽ ባለ መስቀል ተሰቅለኽ ዓለምን ታድነዋለኽ ሲሉ በዘመነ ሐዲስ የኾነ እንደኾነ እንዲኽ ባለ ትእምርተ መስቀል ተሰቅለኽ ዓለምን አድነኸዋል ሲሉ ነው፡፡

የእነዚኽ አርባዕቱ እንስሳ መላእክት ፊታቸው በርካታ ምስጢራትን ሲያመለክቱ ገጸ ሰብእ በማቴዎስ፤ ገጸ አንበሳ በማርቆስ፤ ገጸ ላሕም በሉቃስ፤ ገጸ ንስር በዮሐንስ ተመስሏል።

ዳግመኛም የሰው ፊት ያለው መልአክ ለሰው ልጆች ይማልዳል። የአንበሳ ፊት ያለው መልአክ ለዱር አራዊት ይለምናል። የላም ፊት ያለው መልአክ ለእንስሳት ይጸልያል። የንስር ፊት ያለው መልአክ ለሰማይ አዕዋፋት ኹሉ ይለምናል በማለት ሊቃውንት ያመሰጥራሉ።

በሌላ ምስጢር የሰው ገጽ ያለው የጌታን ሰው የመኾንን ነገር፤ የላም መልክ ያለው በቀራንዮ ላይ ደሙን ማፍሰሱ፤ የአንበሳው መልክ ያለው የጌታችንን ትንሣኤ፤ የንስር መልክ ያለው የጌታን ዕርገት እንደሚያመለክቱ ቀደምት መተርጒማን ይተነትኑታል።

ዐምደ ሃይማኖት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም እጅግ ምጡቅ በኾነው ዕውቀቱ ዕጓለ አንበሳ የተባለው የወልድ የባሕርይ አባቱን አብን በአንበሳ ይመስለዋል።

ሥጋን ተውሕዶ ፍጹም ሰው የኾነው ወልድን የሰው መልክ ባለው መስሎ ገልጾታል፡፡

በአምሳለ ርግብ ወርዶ በወልድ ራስ ላይ ተቀምጦ የታየው መንፈስ ቅዱስን የንስር መልክ ባለው መስሎ አብራርቶ ጽፎታል።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

17 Nov, 06:57


አርባዕቱ እንስሳ

አንቅዕተ ማኅሌት አንቅዕተ ውዳሴ
ምግባቸው ምስጋና ልብሳቸው ቅዳሴ
ዘወትር ይቀኛሉ ለቅድስት ሥላሴ /፪/

ዐይኖቻቸው ብዙ ክንፎቻቸው ስድስት የሥላሴን መንበር የሚሸከሙት
ሱራፌል ኪሩቤል መገብተ ስብሐት /፪/
አዝ.....
ሰአሉ ለነ አርባዕቱ እንስሳ ገጸ ሰብእ ወገጸ አንበሳ
ገጸ ላሕም ወገጸ ንስር /፪/
አዝ.....
ዘወትር አይለዩም ከመንበሩ ዙሪያ ያመሰግናሉ ብለው ሃሌ ሉያ
ይሏታል ድንግልን እኅትነ ነያ /፪/
አዝ.....
ኪሩቤል ሱራፌል ምሉዓነ ግርማ ምስጋናቸው ሲፈስ ድምፃቸው ሲሰማ
ልብን ይመስጣል የምስጋናው ዜማ /፪/
አዝ.....
ሰአሉ ለነ አርባዕቱ እንስሳ ገጸ ሰብእ ወገጸ አንበሳ
ገጸ ላሕም ወገጸ ንስር /፪/

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

16 Nov, 14:36


✥✥✥ ነፍሱን የሚፈልጉት ሞተዋል ✥✥✥

‹‹ የሕፃኑን ነፍስ የሚፈልጉት ሞተዋልና እናቱንና ሕፃኑን ይዘህ ወደ እሥራኤል ተመለስ ›› (ማቴ ፪÷፲፫)

➙ሕጻኑን ሊገሉት የሚፈልጉት ማለት ሲችል የሕፃኑን ነፍስ የሚፈልጉት ያለበት ምክንያት ምን ይመስላችኋል?

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የነሳው ሥጋ ብቻ ነው የሚሉ እንደ አቡሊናርዮስ ያሉ ወደፊት ይነሳሉና ለእነርሱ መልስ ለማሳጣት ፈልጎ ነው ፡፡ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የነሣው ሥጋን ብቻ ሳይሆን ነፍስንም እንደሆነ ለማጠየቅ ነው ፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መንግሥቱን የሚቀማው መስሎት ሊገለው ይፈልገው የነበረው አንድ ሄሮድስ ሆኖ ሳለ ለምን ነፍሱን የሚፈልጉት ሞተዋልና ብሎ በብዙ ቁጥር ጠራቸው ቢሉ ፡፡

>>>ሄሮድስ ዋናው ስለሆነ ለሌሎቹም የምክር ጋናቸው ስለሆነ ሄሮድስ ከሞተ ሌሎችም አይፈልጉትም ሲል ነው ፡፡ በተጨማሪ ግብጽ በቆየባቸው 3 ዓመታት ከሄሮድስ በተጨማሪ እርሱን የሚመስሉ ሁሉ ሞተዋልና ነፍሱን የሚሹት ሰዎች ሞተዋል ብሎ በብዙ ቍጥር ጠራቸው ፡፡

ነገር ግን በሄሮድስ ፋንታ ይሁዳን ለመግዛት አርኬላዎስ እንደነገሠ ሰምቶ የክፉ ልጅ ክፉ ነውና እንዳይተናኮለኝ ብሎ ይህ እንኳን ባይሆን ልጆቻቸው የሞቱባቸው የይሁዳ ሰዎች ልጆቻችን ያለቁት በእናንተ ምክንያት አይደለምን ብለው ቢጣሉንስ ብሎ ቅዱስ ዮሴፍ ወደ ይሁዳ መሔድ ፈራ “ ልጄ እንደ ናዝራዊ ሶምሶን ናዝራዊ ይባላል ተብሎ በነቢይ ቃል የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ናዝሬት ገብቶ ኖረ ፡፡ ”  (ማቴ ፪÷፳፫) ወደ ገሊላ ደርሶ ናዝሬት በምትባል ሀገር ኖረ ፡፡ ይቆየን

<በአምኃ ሥላሴ>

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

16 Nov, 10:59


እንደምን ቆያችሁ መዝሙር ስለጠና እናንተን በመጠበቅ ላይ ነን ቶሎ ብጥመጡልን 🙏🙏🙏

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

16 Nov, 05:28


መልዕክት፡
📍ዛሬ የሚካሄደው የመዝሙር ስልጠና ካለው የአየር ሁኔታ ጋር ከሰዓት ወደ ቤተክርስትያኝ መሄድ ሊከብድ ሰለሚችል ስልጠናው የሚካሄድበት ቦታ ቤተ እብርሃም እንዲሆን ታስቧል

ስለተፈጠረው የማስታወቅያ መቀያየር ታላቅ ይቅርታ እናቀርባለን
🙏

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

16 Nov, 04:38


🌹 እንኳን  ለአጋዝተ አለም ቅድስት ስላሴ ወራዊ እንዲሁም ለሰማዕቱ ለቅዱስ ጊዮርጊስ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን

ኅዳር 7 የሰማዕቱ ቅድስ ጊዮርጊስ ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት ዓመታዊ በዓሉ
ነው፡፡
ኀያሉ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋድሎውን ከፈጸመ በኃላ ሥጋውን ወደ ሀገሩ ልዳ አምጥተው በስሙ ቤተ ክርስቲያን አንፀው ሥጋውን በዚያ አኖሩ፡፡ ሕንፃ ቤተክርስቲያኑንም በወርኃ ኀዳር ሰባት ቀን ኤጲስ ቆጶሰ አባ ቴዎድሮስ ቀድሶ አከበራት፡፡፡ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶሰ በኃያሉ ሰማዕት ቅዱስ
ጊዮርጊስ ላይ አድሮ ሰለ አደረገው ኃይለ ተዐምር መሠከረ፡፡

በዚች በህዳር 7 ቀን በልዳ ከተማ ተሠራችው ቤተክርስቲያን የሆነው ተአምር
ይህ ነው ዲዮቅልያጥያኖስ አውኀዮስ የሚባል መኮንን ከብዙ ሰራዊት ጋር ይቺን ቤተክርስቲያን ሊፈርስ ላከው፡፡ እሱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥዕል ወዳለበት ደረሰ፡፡ በሥዕሉም ፊት የፋኑስ መብራት ነበር፡፡ እየዘበተ በበትር መትቶ ሰበረው፡፡ ሰባሪው ተፈንጥሮ ራሱን መታው፡፡ ፍርሃት እንቅጥቅጥ መጣበትና ተዘረረ፡፡
ተሸክመውም ሲወስዱት በክፋ አሟሟት ሞተና ከባሕር ጣሉት፡፡ ዲዮቅልጥያኖሰ
ይህ በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ፡፡ ከዚያም ራሱ ተነሥቶ ኼደ፡፡ ከዐውድ ምሕረት ወንበር አዘርርግቶ ተቀምጦ ሳለ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ከወንበሩ ገልብጦ መታው፡፡ ሰራዊቱም ትተው ኼዱ፡፡ እሱም 7ዓመት ሙሉ ዐይኖቹ ታውረው ቁራሽ
እንጀራ አየለመነ ኑኖሮ በኀሣር ሞተ፡፡ ይህ ታአምር የተፈፀመ ኀዳር 7ቀን ነው፡፡

🙏የሰማዕቱ ቅድስ ጊወርጊስ ተራዳይነቱ አይለየን፡፡

የጽሁፍ ምንጭ (ገድለ ቅድስ ጊወርጊስ)።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

15 Nov, 11:31


."... እመ አምላክ እኛንም እንዲመልሰን ለምኝልን"
እመቤታችን የሕይወታችን የማዕዘን ራስ የተቀመጠባት ጽዮን።መለኮትን የመሸከም ኃይለ ድንግልና ያላት ተማምነው የሚጠጉባት ሀገረ ምስካይ!ፊትን ወደ እርስዋ ባዞሩ ጊዜ የድኅነት ብርሃን የሚወጣባት እመ ብርሃን።የተዳደፉትየሚነጹበት የደስታ ፏፏቴ የሚፈልቅባት የታተመች የውኃ ጉድጓድ።ዓለምን የሚያጠግብ ፍሬን የተመላች የታጠረች ገነት።የደስታውን ዘለላ ያፈራችው የወይን ሐረግ።ከጉድጓድ ወጥተን እስከ ሰማይ የምናርግባት ረጅሚቱ የወርቅ መሰላል።ማዕዷ የማይታጠፍ ሲሳየ ዓለምን በውስጧ የያዘች መሶበ ወርቅ።ንጉሥ ክርስቶስ ተገልጦ የነገሠባት የፍትሕ አደባባይ።በእሳተ ገሃነም ለነደዱ የምሕረት ዝናም ይዛ የደረሰች ፈጣን ደመና።እርሱዋ እናቴ ልጅዋ አምላኬ ከሆነችልኝ የምሻው ይህንን ነው።
እርስዋ እናቴ መሆኗን የማስብበትን ያህል የሚያበረታኝ ምንም የለም።

እመቤቴ ሆይ ከስደት እንደተመለስሽ ከቤታቸው፣ ከሀገራቸው የተሰደዱትን እንዲመልስ ከልጅሽ አማልጅን።ከእውነት በሐሰት፣ ከእምነት በክሕደት የተሰደዱትን መልሻቸው።ከትሩፋት በሐኬት የወጣነውንም መልሽን።ከሥደት ስትመለሺ በቃል ኪዳን የተቀበልሻት ኢትዮጵያን መከራዋ አብቅቷል የሚሉ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልንና ሚካኤልን እንዲልክልን ልጅሽን ለምኝልን።

አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
ኅዳር ፮-፫-፳፻፲፯ ዓም.
ሜልበርን አውስትራሊያ

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

15 Nov, 08:30


ደብረ ቁስቋም

ኅዳር ፮ ቀን የአርያም ንግሥት፣ የፍጥረታት ሁሉ እመቤት፣ የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይዛ አረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍንና ቅድስት ሰሎሜን አስከትላ ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት የስደት እና የመከራ ዓመታት በኋላ በስተደቡብ የምትገኘው ደብረ ቁስቋም ላይ ያረፉችበት ዕለት ይከበራል፡፡

ደብረ ቁስቋም በደቡብ ግብጽ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ይህ ተራራ የተቀደሰ ተራራ ስለመሆኑ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ታኦፊሎጎስ በድርሳነ ማርያም ‹‹ይህም ከሀገሮቹ ሁሉ ተራሮች የሚበልጥ (የተለየ) ከፍ ያለ ተራራ ነው፡፡ በውስጡ ቅዱስ አግዚአብሔር ያድራል፡፡ ይህንን ተራራ የእግዚአብሔር ልጅ ወዶታል፤ አክብሮታልምና፤ ከዓለም ሀገሮች ሁሉ ከተቀደሰች እናቱ ጋር አድሮባታልና፡፡ ከመላእክት ቤት ያድር ዘንድ አልወደደም፤ ቢታንያንም አልመረጠም፡፡ ከተራራው ላይ ባለች ገዳም ቤት ውስጥ አደረ እንጂ፤ ነቢዩ ዳዊት የጽዮንን ተራራ ወደደ፤ በአርያምም መቅደሱን ሠራ እንዳለ፡፡››

በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ ሄሮድስ ክርስቶስን ለመግደል በፈለገ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለአረጋዊው ዮሴፍ በሕልሙ ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ›› ባለው መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ (ማቴ. ፪፥፲፫-፲፭)

በስደቱም ጣዖታተ ግብጽ እየተሰባበሩ ሲወድቁ፤ በእነርሱም አድረው ሰውን ሲያስቱ የነበሩ አጋንንትም ሲሸሹ ታይተዋል፤ ደግሞም ጌታችን ዳግማዊ አዳም ነውና በምክረ ከይሲ (ዲያብሎስ) ምክንያት ተሰዶ የነበረው ቀዳማዊ አዳምን ለመካስ ተሰደደ፤ በዚህም አጋንንትን ከሰው ልቡና አውጥቶ አሳደደ፡፡

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

15 Nov, 08:30


እመቤታችን ቅድስት ማርያም ከጌታችን ኢየሱስ ጋር ከመሰደዷ አስቀድሞ ነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹ወይወርድ እግዚእነ ውስተ ምድረ ግብጽ እንዘ ይጼዐን ዲበ ደመና ቀሊል፤ ጌታችን በፈጣን ደመና (በእመቤታችን ጀርባ) ተጭኖ ወደ ግብጽ ይወርዳል›› ተብሎም በተናገረው መሠረት ትንቢቱ ተፈጽሟል፡፡ (ኢሳ. ፲፱፥፩)

ጌታችን ኢየሱስ  በደብረ ቁስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቱን ሰበሰባቸው፤ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንንም አክብሮ የቁርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ሰጥቷቸዋል፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከጌታችን ኢየሱስ ጋር በቁስቋም ተራራ ስድስት ወራትን ያረፈች ሲሆን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅዳር ፮  የእነርሱን ስደትና ወደ ሀገራቸው እስራኤል መመለሳቸውን በማስታወስ ታከብራለች፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!!

ምንጭ፤ ድርሳነ ማርያም (ትርጉም ፳፻፫ ዓ.ም)
              ስንክሳር ዘወርኃ ኅዳር

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

14 Nov, 07:17


👉ይቅርታ የስልጠናው ቦታ ለውጥ ተደርጎበታል። ቤተ-አብርሃም ሳይሆን ቤተክርስትያን ባለው የግቢ ጉባኤው አዳራሽ ላይ የሚሰጥ ይሆናል።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

14 Nov, 06:29


📌የመዝሙር ስልጠና

ከማኅበረ ቅዱሳን ሀዋሳ ማዕከል በተጋበዙ መምህራን "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክን መዝሙር እና የመዝሙር መሣርያ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ስልጠና

🗞መዝሙር ለምን እንዘምራለን?
🗞ለምን መዝሙር ከጥራዝ ብቻ ይዘመራል?
🗞ከጥራዝ ውጭ ለምን አይዘመርም?
🗞ኦርቶዶክሳዊ የመዝሙር ዜማ መሳርያዎች የትኞቹ ናቸው?

እነዚህን ጥያቄዎች የሚመለሱበት ስልጠና እነሆ ብለን ቅዳሜ ከ7:00 ጀምሮ ቤተክርስትያን ባለው የግቢ ጉባኤ አዳራሽ እጠብቃችኅለን

🗓 ቀን : ቅዳሜ ሕዳር 7/2017
ሰዓት ፡ 7:00-11:00
📍 ቦታ: ደ/ኢየሱስ ወቅ/አርሴማ ቤተክርስቲያን ሪ/ግ/ጉ/ አዳራሽ


https://t.me/referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

13 Nov, 16:44


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) pinned «»

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

13 Nov, 10:41


ይህን መጽሐፍ ከቤተ መጽሐፍታችን ወስዳችሁ አንብቡት።ለሕይወታችሁ መሪ፣ጠቃሚ ምክሮችንና ታሪኮችን ታገኙበታላችሁ🙏

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

11 Nov, 11:24


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL):


ውድ ቤተሰብ እንዴት ቆያችሁ?
አሜን የእግዚአብሔር ስሙ የተመሠገነ ይሁን።

ትንሽ የሚያሳዝን ዜና ይዘን መጥተናል።
በኮሪደር ልማት የተነሳ ሐመር ሱቅ ለጊዜው ተዘግቷል። በመሆኑም አሁን ከሐመር ሱቅ መግዛት ሚፈልግ ሰው በቤተ - አብርሃም በጊዜያዊነት እየተሸጠ ይገኛል። በዛው ቤተ-አብርሃም ስትሄዱ በዛው መግዛት ትችላላችሁ ። አዲስ ነገር ሲኖር እናሳውቃችኅለን

ሐመር የሁላችን ናት በመሆኑም በዚህ ከባድ ጊዜ አብረን እንድንተባበር በትህትና እንጠይቃለን🙏


https://t.me/referal_gibi
https://t.me/referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

11 Nov, 11:14


አልቆም ያለ ደም

"በኋላውም ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች፥ የደምዋም ፈሳሽ በዚያን ጊዜ ቆመ" ሉቃ. ፰፥፵፬

ከዐሥራ ሁለት ዓመትም ጀምሮ ደም የሚፈሳት ሴት ነበረች፥ ትዳርዋንም ሁሉ ለባለመድኃኒቶች ከስራ ማንም ሊፈውሳት አልተቻለውም። ደምዋ ፈስሶ አያልቅም ወይ? ዓሥራ ሁለት ዓመት ሙሉ? እንዴት ያለ ሕመም ነው?! ሰው በክፉ ሽታዋ እስኪርቃት ድረስ የማይቆም ደም። ባለ መድኃኒቶች ሊያቆሙት ያልቻሉትን የደም ጎርፍ የናዝሬቱ ባለ መድኃኒት በቀሚሱ ብቻ አቆመው። በልብሱ ጫፍ ብቻ። ሳያያት ሳይነካት እጁን ሳይጭንባት በልብሱ ጫፍ ብቻ የደምዋን ዝናብ እንዲያባራ አደረገው። የሕመምዋን ማዕበል ገሠጸው።

በልብሱ ጫፍ ብቻ የሚፈውስ ሐኪም እንዴት ያለ ነው? ቀጠሮ ሳይሠጥህ ሳያናግርህ ቀና ብሎ ሳያይህ ስትነካው ብቻ የምትድንበት ከሆነ እርሱ መድኃኒት የሚያዝ ሐኪም ሳይሆን ራሱ መድኃኒት ነው። የልብሱን ጫፍ የነካ ከዳነ ሥጋውን የበሉ ደሙን የጠጡማ ምንኛ ይድኑ ይሆን? ሊፈውሳት አስቦ አልነበረም የዓሥራ ሁለት ዓመት ሴት ልጅ ከሞት ሊያስነሣ መንገድ ሲሔድ ግን እግረ መንገዱን የዓሥራ ሁለት ዓመት የቁም ሙትዋን ፈወሳት። መድኃኔዓለም እንዲህ ነው። ወደ በሽተኛው ሳይሔድ በቃሉ ብቻ ተናግሮ ይፈውሳል፤ በሽተኛው ቤት ገብቶ በአልጋው ላይ ይፈውሳል። ሊፈውስ ሲሔድም ይፈውሳል። እናም የሴቲቱ አልቆም ያለ ደም በልብሱ ጫፍ ብቻ ቀጥ አለ።

ጌታዬ ሆይ የእኔንስ ደም የምታቆመው መቼ ነው? ምን ደም ፈስሶህ ያውቃል ካልከኝ ኃጢአት የሚባል ደም ሲፈሰኝ አይታይህም? አንተስ በቃልህ "ኃጢአታችሁ እንደ ደም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች" ብለህ የለ? እንደ ደም የቀላው የእኔ ኃጢአት ነው። ይኸው ሲፈስ ከሴቲቱ በላይ ቆየ። ላቆመው ብል አልቆም አለኝ። ያላሰርኩበት ጨርቅ፣ ያልሞከርኩት ቅባት፣ ያልሔድኩበት ባለ መድኃኒት የለም። ገንዘቤን ከሰርኩ እንጂ ኃጢአቴ ግን መቆም አልቻለም። እንዲያውም መጠኑ እየጨመረ ነው። ባሕር ሆኖ ሊያስጥመኝ የደረሰ የኃጢአት ደም ከብቦኛል።

ለእኔ የሚሆን የቀሚስ ጫፍ ታጣ ይሆን? እኔ እንደ ሴቲቱ ታላቅ እምነት የለኝም ቀሚስህ ግን አሁንም ኃይል አለው። ልትፈውሰኝ ና አልልህም ስታልፍ ግን ልዳስስህና ልዳን። ጉዞህን ሳላሰናክል ሰው ሳይሰማ በልብስህ ጫፍ ብቻ ደሜን አቁምልኝ። የእኔን ደሜን መግታት ላንተ ምንህ ነው? ደምህንስ አፍስሰህልኝ የለ? እባክህን ደሜ ሳይቆም ሌላ ዓመት አልሻገር። እኔ ኃጢአቴን "ያለፈው ዘመን ይበቃል" ማለት ቢያቅተኝም አንተ ግን ይበቃሃል በልልኝ። በእምነት ማጣት የታጠፈውን እጄን ወደ ልብስህ ጫፍ ዘርጋልኝ። እኔ ማቆም ያልቻልኩትን የበደል ደም ጸጥ አድርገህ "አንድ ሰው ዳስሶኛል ኃይል ከእኔ ወጥቶአል" በል። እነጴጥሮስም ይደነቁ እኔም በሰላም ልሒድ።

(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ - የኤፌሶን ወንዝ ገጽ 168-170)

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

09 Nov, 06:05


ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ ሥሙር !

ማኅሌተ ጽጌ | ፩ | 🌷

ኢየኃፍር ቀዊመ ቅድመ ስእልኪ ወርኃ ጽጌረዳ አመ ኃልቀ፤ዘኢየኃልቅ ስብሐተኪ እንዘ እሴብሐኪ ጥቀ፤ተአምርኪ ማርያም ከመ አጠየቀ፤ጸውዖ ስምኪ ያነሥእ ዘወድቀ፤ኃጥአኒ ይሬሲ ጻድቀ፡፡

ትርጉም 🌷

እጅግ ብዙ የማያልቅ ምስጋናሽን እያመሰገንኩኝ : የጽጌረዳ ወራት ባለቀ ጊዜ በስዕልሽ ፊት መቆምን አላፍርም : ማርያም ተዓምርሽ እንዳስረዳ ስምሽን መጥራት የወደቀን ያነሳል : ኃጥኡንም ጻድቅ ያደርጋል ።

ምስጢር 🌷

የጽጌረዳ ወራት ባለቀ ጊዜ በሥዕልሽ ፊት መቆምን አላፍርም ማለቱ ከመስከረም 26 - ኅዳር 5 የቆየው የጽጌ ወቅት ቢያልፍም እኔ ግን ምስጋናሽን አላቋርጥም ይላል የዚህ ክፍል ጥንተ ነገሩ ዘካርያስ የሚባል ሰው የእመቤታችንን ሥዕል ያገኛል ፤ በጣም ተደሰተ ፤ የእመቤታችን ፍቅር አደረበትና ምን ላድርግላት ብሎ ተጨነቀ ።

ወቅቱ የጽጌ ነበርና እለት እለት 50 አበባ ለሥዕሏ አደርጋለሁ አለ ። እንዳለውም በየቀኑ ሀምሳ ጽጌሬዳ እየቆረጠ ለሥዕሏ ያደርግ ነበር ። በኋላ የአበባ ጊዜ ሲያልፍ አበቦችን ማግኘት ስለማይችል ምን ላድርግ ብሎ አሰበ ፤ በአበቦቹ ፈንታ ሀምሳ ጊዜ በሰላመ ቅዱስን አደርሳለሁ ብሎ ማድረስ ጀመረ ።

ከእለታት በአንዱ ቀን ወደ ሌላ ሀገር ሲሄድ መንገድ ላይ ሽፍታዎቹ አግኝተውት እርሱ በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል መልአክ እያለ ይጸልያል ፤ እመቤታችን ለሽፍቶች ተገልጣ አንድ በሰላመ ቅዱስ ሲል አንድ አበባ ስትቀበል ይመለከታሉ ፤ ሀምሳውን ሲጨርስ ሀምሳ አበባ ።

የዚህን ጊዜ ሽፍታዎቹ በግንባራቸው ተደፍተው ሰገዱለት ፤ በኋላም አምነው መነኮሳት ሆነዋል ። እናም ይህ የጽጌ ምሥጋና ቢያልቅም የእመቤታችን ምሥጋና እንደማይቋረጥ ሲገልጽ ነው ፤ በውዳሴ ማርያም ፣ አርጋኖን ፣ ማኅሌት ፣ ሰዓታቱ ትመሰገናለችና ።

ስምሽን መጥራት የወደቀን ያነሣል ማለቱ አንድ እመቤታችን የሚወድ ሰው ነበር ፤ ከተወደደ ልጇ ጋር ሥዕሏን ስሎ በመሰላል ወጥቶ ዲያቢሎስ በሲኦል ነፍሳትን መከራ ሲያጸናባቸው እየሣለ እያለ ዲያቢሎስ ተናድዶ መሰላሉን መትቶ ሊጥለው ወደ ታች ሊወድቅ ሲሄድ ከሳላት ሥዕል የእመቤታችን እጅ ወጥቶ ይዞ አድኖታል ።

ኃጥኡንም ጻድቅ ያደርጋል ሲል በቃልኪዳኗ ልጄ ወዳጄ ማርልኝ ብላ ስትለምን ስለ እናትነቷ ይምራልና ኃጥኡንም ጻድቅ ያደርጋል ብሏል ።

ማኅሌተ ጽጌ | ፪ | 🌷

ኅብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወፀዓድዒድ አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር ተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌ ሥሙር አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማይ ወምድር ከመ በሕፅንኪ ያስምክ ፍቁር ።

ትርጉም 🌷

የሚያብረቀርቅ ቀይነ ነጭ ቀለም ያለው አርአያው የብር ዝንጉርጉር የሆነ ንጹሕ ተዓምርሽ በወርቅ አምሳል የተሰራ ነው ፤ እነሆ የተወደደ መልካም ማኅሌተ ጽጌ ተፈጸመ ፤ የሰማይና የምድር ንግሥት ማርያም ሆይ የተወደደ ልጅሽ በእቅፍሽ እንዲጠጋ (እንዲንተራስ ) በእርሱ አማጽኝ ።

ምስጢር 🌷

ቀይና ነጭ ቀለም ያለው ማለቱ ቀይ በትስብእቱ ነጭ በመለኮቱ ማለትም ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ ዝንጉርጉርም ያለው ሰው እና አምላክነቱን ነው  ( እንዘ ተኃቅፊዮ ላይ በሰፊው አይተናል )
ተአምርሽ በወርቅ አምሳል የተሰራ ነው ሲል ወርቅ የንጽሕና ምሳሌ ነውና እመቤታችንም ንጽሕተ ንጹሐን ናትና ። |  ኵለንታሃ ወርቅ |

ወርኀ ጽጌ አልቋል ሲል ተፈጸመ ማኅሌተ ጽጌ ስሙር አለ የሰማይና የምድር ንግሥት ( መዝ 44 )

ማኅሌተ ጽጌ | ፫ | 🌷

ለንጉሠ ነገሥት ሰሎሞን ከመ ተፈሥሐ ልቡ፤በዕለተ ወፃእኪ መርዓት ለአንበሳ ትንቢት እምግቡ፤ማዕከለ ማኅበር ፍሡሓን ተአምረኪ ዘይነቡ፤እዜምር ለኪ ጽጌ ሐና ወፍኖተ ነፈርዓፅ እሌቡ፤ከመ ጣዕዋ ሐሊበ ዘይጠቡ።

ትርጉም

የሀና አበባ  ሆይ!ሐሴትን በተመሉ ( ማኅበረ ጻድቃን)ማኅበር መካከል ተአምርሽን የሚናገር የነገሥታት ንጉሥ ሰሎሞን ሙሽሪት  ከአንበሳዉ ትንቢት ዋሻ በወጣሽ ጊዜ ልቡ ሐሴት እንዳደረገ  እንደ ሚጠባ እንቦሳ የመፈርጠጫ ቦታየን አስተውላለሁ፤ እዘምርልሽም አለሁ።

ለዓመቱ ያድርሰን !
ስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር ... አሜን !

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

09 Nov, 02:56


ስንክሳር ዘጥቅምት ፴

ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ

ጥቅምት ሠላሳ በዚህች ቀን ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳት አለቃ የሆነ ወንጌልን የጻፈ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ የተወለደበት ነው።

የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አርስጦቡሎስ ነው እርሱም ከአምስቱ አገሮች የሆነ የእናቱም ስም ማርያም ነው እርሷም በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ተጽፋለች እርሱም አስቀድሞ ስሙ ዮሐንስ ነው። በግብረ ሐዋርያት ማርቆስ በተባለ በዮሐንስ እናት ቤት ሐዋርያት ይጸልዩ ነበር ተብሎ እንደ ተጻፈ። እርሷም ባለጸጋ ነበረችና የዮናናውያንን የሮማይስጥን የዕብራይስጥን ትምህርት ለልጅዋ ለማርቆስ አስተማረችው።

በአደገም ጊዜ በርናባስ ወንጌልን ለመስበክ ከጳውሎስ ጋራ ሲሔድ ይዞት ሔደ በእነርሱም ላይ የሚደርስባቸውን መከራ አይቶ በጵንፍልያ ከተማ ሳሉ ትቷቸው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።

ሐዋርያትም በተመለሱ ጊዜ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ማመን አሕዛብ እንደ ተመለሱ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ላይ ድንቅ ተአምራትን እንዳደረገ ተናገሩ። ይህ ብላቴና ማርቆስም ከእርሳቸው ስለ መለየቱ አዘነ ተጸጸተ።

ከዚያም አብሮአቸው ሊሔድ ፈለገ አስቀድሞ ትቷቸው ስለተመለሰ ጳውሎስ ሊአስከትለው አልወደደም በርናባስ ግን ወሰደው አጎቱ ነውና። በርናባስም ከአረፈ በኋላ ወደ ሮሜ አገር ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ ሒዶ ለእርሱ ደቀ መዝሙሩ ሆነ በዚያም ቅዱስ ጴጥሮስ የተረጐመለትን ወንጌልን ጻፈ በሮሜ አገርም አስተማረበት። ከዚያም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዝና በሐዋርያትም ትእዛዝ ወደ እስክንድርያ አገር ሔደ። በውስጥዋም የከበረ ወንጌልን አስተማረ ደግሞም በአፍራቅያና በአምስቱ አገሮች በርቃ በሚባልም አገር ወደ እስክንድርያ ከተማ በገባ ጊዜ ጫማው ተቆረጠ።

በዚያም በከተማው መግቢያ ጫማ ሰፊ ነበረ። ቅዱስ ማርቆስም እንዲሰፋለት ለርሱ ሰጠው ሲሰፋም ጣቱን ወግቶ ሰነጠቀው ከእርሱም ደም ፈሰሰ በዮናኒም ቋንቋ ኢታስታዖስ አለ ትርጓሜውም አንድ እግዚአብሔር ማለት ነው። ቅዱስ ማርቆስም ስሙን የምትጠራው አውቀኸው ነውን አለው እንጠራዋለን እንጂ አናውቀውም አለ።

እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ከፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ አባታችን አዳም ትእዛዙን እንደተላለፈ የጥፋት ውኃም እንደ መጣ ሙሴንም እንደላከውና እስራኤልን ከግብጽ እንዳወጣቸው ሕግንም እንደ ሠራላቸው ናቡከደነጾርም ወደ ባቢሎን ማርኮ እንደወሰዳቸውና ከሰባ ዓመት በኋላ ወደ አገራቸው ኢየሩሳሌም እንደ ተመለሱ ክርስቶስ ሥጋ በመልበስ ወደ ዓለም ስለ መምጣቱ ነቢያት ትንቢት እንደ ተናገሩ ያስተምረው ዘንድ ጀመረ።

ከዚያም በኋላ ወደ ምድር ምራቁን ትፍ ብሎ ጭቃ አድርጎ ጣቱን ቀባው ወዲያው ዳነ በጌታችንም አመነ። ያም ሰፊ ስሙ አንያኖስ ነው። ቅዱስ ማርቆስንም ወደ ቤቱ ወስዶ ልጆቹን ዘመዶቹንም ወደ ርሱ አቀረበ እርሱም አስተምሮ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው።

በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑ ሰዎች በበዙ ጊዜ የቅዱስ ማርቆስን ዜና ሰምተው የአገር ሰዎች ሊገድሉት ተሰበሰቡ እርሱም አንያኖስን ኤጲስቆጶስ አድርጎ ሹሞ ልጆቹን ቄሶችና ዲያቆኖች አድርጎ ከዚያም ወደ በርቃ ወደ አምስቱ አገሮችም ወጥቶ አስተማረ። በቀናች ሃይማኖትም አጸናቸው በእርሳቸውም ዘንድ ሁለት ዓመት ኖረ ኤጲስቆጶሳትን ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው።

ከዚህም በኋላ ወደ እስክንድርያ ተመለሰ ምእመናንም ተጨምረው በዝተው በታወቁ ቦታዎች ሁሉ በባሕሩም ዳር በላሞች መካበቢያ በሚባለውም አብያተ ክርስቲያን ሠርተው አገኛቸው።

ከሀድያንም የከበረ ሐዋርያን ይገድሉት ዘንድ በብዙ ድካም ፈለጉት እርሱም አምስቱን አገሮች ሲጐበኝ በሥውር ወደ እስክንድርያ ከተማ ይገባ ይወጣ ነበር። በአንዲትም ዓመትም ከአምስቱ አገሮች ተመልሶ ሚያዝያ ዐሥራ ሰባት ቀን በመድኃኒታችን የትንሣኤ በዓል ወደ ቤተክርስቲያን ገባ ሕዝቡም ሁሉ በዙሪያው አሉ። ከሀድያንም ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብተው በአንገቱ ውስጥ ገመዶችን አድርገው በከተማው ሁሉ ጎተቱት። እነርሱም ገና እንደፍየል ሙክት እንጎትተዋለን እያሉ ይጮኹ ነበር ። በላሞች መካበቢያና በሀገሪቱ አደባባይ በከተማውም ዙሪያ በየቀኑ ሲጎትቱት ኖሩ።

ሌሊትም በሆነ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሐዋርያት ጋራ በነበረበት አርአያ ሁኖ ተገለጠለት ሰላምታም ሰጥቶ አጽናናው ቃል ኪዳንም ሰጠው። እነሆ አንተ ከወንድሞችህ ሐዋርያት ጋር ተካከልህ አለው። እርሱም በልቡናው ፈጽሞ ደስ አለው። በማግሥቱም ሁለተኛ ገመዶችን በአንገቱ አድርገው በአገሮች ሁሉ ጎተቱት በቀኑም መጨረሻ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።

ከሀዲዎችም ታላቅ እሳትን አንድደው የቅዱስ ማርቆስን ሥጋ ከውስጡ ጨመሩ ። በክብር ባለቤት ጌታችን ፈቃድም ንውጽውጽታ ጨለማ ቀዝቃዛ ነፋስ መብረቅና ነጐድጓድ ሆነ። ፀሐይም ጨለመ ከሀዲዎችም ሸሹ ምእመናንም መጥተው የሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስን ሥጋ ወሰዱ ምንም ጥፋት ሳይደርስበት ደኀና ሆኖ አገኙት በመልካም ልብስም ገንዘው በጥሩ ቦታ አኖሩት መታሰቢያውንም አደረጉ።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን!!!

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

08 Nov, 03:43


ስንክሳር ዘጥቅምት ፳፱

ቅዱስ ድሜጥሮስ ሰማዕት

በዚህችም ቀን በከሀዲው ንጉሥ በመክስምያኖስ ዘመን ቅዱስ ድሜጥሮስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ ከተሰሎንቄ ሀገር ነው የከበረች የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት ተምሮ በቀናች ሃይማኖት ጸና ሕዝቡንም የሚያስተምር ሆነ ክብር ይግባውና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት በመስበክ ብዙዎችን ከስሕተት መለሳቸው።

ስለዚህም በከሀዲው ንጉሥ ዘንድ ወነጀሉት ንጉሡም ወደርሱ እንዲአመጡት አዘዘ በንጉሡም ዘንድ አንድ ሥጋው የደነደነ የጸና ዐጥንቱ የሰፋ ሰው ነበረ ለሰዎችም ሁሉ እሱ ሁሉን የሚያሸንፍ እሱን የሚያሸንፈው የሌለ ይመስላቸው ነበር ንጉሡም ይወደዋል ይመካበታል እንዲህም ይል ነበር ይህን አካሉ ግዙፍ የሆነ ሰው ለሚያሸንፍ እኔ ብዙ ገንዘብ እሰጠዋለሁ።
በዚያንም ጊዜ ስሙ በስጥዮስ የሚባል አንድ ክርስቲያናዊ ሰው ተነሥቶ ወደ ቅዱስ ድሜጥሮስ ሔደ እንዲጸልይለትና በሥጋውም ሁሉ አሸናፊ በሆነ በመስቀል ምልክት እንዲአማትብበት ለመነው። እርሱም በላዩ ጸለየለት በሥጋውም ሁሉ ላይ በመስቀል አማተበበት ከዚህም በኋላ ወደ ንጉሥ ገብቶ ከዚያ ሥጋው ግዙፍ ከሆነው ጋር ያታግለው ዘንድ ለመነው ንጉሡም ፈቀደለት በታገሉም ጊዜ ሥጋው የደነደነውን ያ ክርስቲያናዊ ሰው አሸንፎ ጣለው ንጉሡም አዘነ አደነቀም ሥጋው የደነደነውም በመሸነፉ አፈረ ተመክቶበት ነበርና።

ንጉሡም ስለዚህ ነገር ወታደሮቹን ጠየቀ እነርሱም ቅዱስ ድሜጥሮስ በላዩ እንደጸለየለትና በሥጋውም ላይ በመስቀል ምልክት እንዳማተበበት ነገሩት።

ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ በቅዱስ ድሜጥሮስ ላይ እጅግ ተቆጣ ለአማልክትም ዕጣን እስከሚአሳርግ ድረስ እንዲገርፉት አዘዘ ንጉሡም እንዳዘዘ እንዲሁ አደረጉበት የንጉሡንም ትእዛዝ ባልሰማ ጊዜ እስከሚሞት በጦሮች እንዲወጉት ሁለተኛ አዘዘ።

ለቅዱስ ድሜጥሮስም ይህን ፍርድ ነገሩት ሃይማኖቱን ትቶ ለአማልክት የሚሰግድ መስሏቸው ነበርና ቅዱስ ድሜጥሮስም እኔ ከዕውነተኛ አምላክ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለረከሱ አማልክት እሰግድ ዘንድ ዕጣን ማሳረግም አልፈቅድም የወደዳችሁትን አድርጉ አላቸው።

በዚያንም ጊዜ ንጽሕት ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ እስከ ሚሰጥ በጦር ወጉት ሥጋውንም በጣሉት ጊዜ ምእመናን ወደ ርሳቸው ወሰዱት የስደቱም ወራት እስከሚያልፍ በሣጥን አድርገው በቤታቸው ውስጥ ሠውረው አኖሩት።

የስደቱም ወራት ከአለፈ በኋላ እግዚአብሔር ገለጠውና ከዚያ አወጡት ያማረች ቤተ ክርስቲያንንም በተሰሎንቄ አገር ሠሩለት ሥጋውንም በውስጧ አኖሩ ድንቅ የሆነ ታላቅ ተአምርን እያደረገ እስከ ዛሬ አለ።

ሽታውም እጅግ ጣፋጭ የሆነ የሽቱ ቅባት ከእርሱ ይፈሳልና በእምነት የሚቀቡትን በሽተኞች ሁሉንም ያድናቸዋል። ይልቁንም በዕረፍቱ መታሰቢያ ቀን ከሌሎቹ ዕለታት ተለይቶ በብዛት ይፈሳል ከአውራጃው ሁሉ ብዙዎች ሰዎችም ይመጣሉ ከዚህም ቅባት ወስደው በማሰሮቻቸው ያደርጋሉ ይቺ ምልክትም እስከ ዓለም ፍጻሜ በመኖር እንደምትገኝ ደጋጎች ካህናት ምስክሮች ሆኑ።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን!!!

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

07 Nov, 16:39


MK TV || ዘጋቢ ፊልም || የ35 ፋብሪካ ባለቤት ገዳም በግብፅ
https://youtube.com/watch?v=5i9nrU_m7ng&si=w-lRU00-mfbfpgEZ

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

07 Nov, 02:00


#አቡነ_ይምዓታ_ጻድቅ

ጥቅምት ሃያ ስምንት በዚህች ቀን ከዘጠኙ ቅዱሳን አንዱ የሆኑት ጻድቁ አቡነ ይምዓታ አረፉ።

ጻድቁ ገድላቸውን የፈጸሙት በኢትዮዽያ ቢሆንም ሃገረ ሙላዳቸው የጥንቱ የሮም ግዛት የሆነችው ታናሽ እስያ ናት። አባ ይምዓታ ከዘጠኙ (ተስዓቱ) ቅዱሳን አንዱ ናቸው። ዘጠኙ ቅዱሳን ተወልደው ያደጉት ምንም በአንድ የሮም ግዛት ሥር ቢሆንም መነሻ ቦታቸው ግን የተለያየ ነው።

ሁሉንም አንድ ያደረጋቸው መንፈስ ቅዱስ በኪነ ጥበቡ ነው። በምክንያት ደረጃ እንግለጸው ከተባለ ደግሞ የአንድነታቸው ምሥጢር፦
1.የቀናች ሃይማኖታቸው ተዋሕዶ
2.ዓላማ (የእግዚአብሔር መንግስት) እና
3.ገዳማዊ ሕይወት ነው።

አባ ይምዓታን ጨምሮ ሁሉም ቅዱሳን ዘራቸው ከቤተ መንግስት ነው። እነርሱ ግን ምድራዊውን ክብር ንቀው ሰማያዊውን ክብር ገንዘብ ማድረግን መርጠዋል። አስቀድመው ቅዱሳት መጻሕፍትን ያጠኑት አበው በተለያየ ጊዜ እየመነኑ ከሮም ግዛት ወደ ግብጽ በርሃዎች ወርደዋል።

በምናኔ ቅድሚያውን አባ ዸንጠሌዎንና አቡነ አረጋዊ ይይዛሉ። ዘመኑ የተዋሕዶ አማኞች የሚሰደዱበት 5ኛው መቶ ክ/ዘመን ነበርና እምነትን ላለመለወጥ ዘጠኙ ቅዱሳን ስደትን መረጡ።

በወቅቱ ደግሞ ለስደት መጠለያ የምትሆንና ከኢትዮዽያ የተሻለች ሃገር አልነበረችም። ስለዚህም በ470ዎቹ ዓ/ም አልዓሜዳ በኢትዮዽያ ነግሦ ሳለ ቅዱሳኑ በአረጋዊ መሪነት መጡ።

ንጉሡም ሲጀመር የእግዚአብሔር እንግዳ ስለሆኑ ሲቀጥል ደግሞ ቅድስናቸውን ተመልክቶ መልካም አቀባበልን አደረገላቸው። ማረፊያ ትሆናቸውም ዘንድ አክሱም ውስጥ አንዲት ቦታን ወስኖ ሰጣቸው። ይህች ቦታ "ቤተ ቀጢን" ትባላለች።

አባ ይምዓታና 8ቱ ቅዱሳን ወደ ሃገራችን እንደ ገቡ የመጀመሪያ ሥራቸው ቋንቋን መማር ነበር። ልሳነ ግዕዝን በወጉ ተምረው እዛው አክሱም አካባቢ ሥራቸውን አንድ አሉ። በወቅቱ በአቡነ ሰላማ፣ በአብርሃ ወአጽብሐና በአቡነ ሙሴ ቀዳማዊ የተቀጣጠለው ክርስትና በተወሰነ መንገድ ተቀዛቅዞ ነበርና እነ አባ ይምዓታ እንደ ገና አቀጣጠሉት።

ሕዝቡን በራሱ ልሳን ለክርስትና ይነቃቃ ዘንድ ሰበኩት። የካደውን እየመለሱ የቀዘቀዘውን እያሟሟቁ ለዓመታት ወንጌልን ሰበኩ። ቀጣዩ ሥራቸው ደግሞ መጻሕፍትን መተርጐም ሆነ።

ከሃገራቸው ያመጧቸውን ቅዱሳት መጻሕፍት ተከፋፍለው ወደ ግዕዝ ልሳን ተረጐሟቸው። በዚህም ለሃገራችን ትልቁን ውለታ ዋሉ። ይህ ሁሉ ሲሆን እነ አባ ይምዓታ የሚመገቡትም ሆነ የሚጸልዩት በማሕበር ነበር። በመካከላቸውም ፍጹም ፍቅር ነበር። ጸጋ እግዚአብሔር አልተለያቸውም።

የነ አባ ይምዓታ ቀጣዩ ተግባራቸው ደግሞ ገዳማዊ ሕይወትን ማስፋፋት ሆነ:: ይህንን ለማድረግ ግን የግድ መለያየት አስፈለጋቸው:: እያንዳንዱም መንፈስ ቅዱስ ወደ መራው ቦታ ሔደ:: ዸንጠሌዎን በጾማዕት፣ ገሪማ በመደራ፣ ሊቃኖስ በቆናጽል፣ አረጋዊ በዳሞ፣ ጽሕማ በጸድያ፣ ሌሎችም በሌላ ቦታ ገዳማትን መሠረቱ።

አባ ይምዓታ ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ምርጫቸው ገርዓልታ (እዛው ትግራይ) ሆነ። ጻድቁ ወደ ቦታው ሲሔዱ ወንዝ (ባሕር) ተከፍሎላቸዋል። ወደ ቦታው ደርሰውም ገዳም አንጸዋል። በቦታውም ብዙ ተአምራትን ሠርተው በርካታ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው፣ ለዘመናት ተጋድለው በገርዓልታ በዚህች ቀን አርፈዋል።

የአቡነ ይምዓታ ፍልፍል ዋሻ ቤተ መቅደስ ትግራይ ገርዓልታ ልዩ ስሙ ‹‹ጎሕ›› ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ይገኛል፡፡ ቤተ መቅደሱ ሰማይን እንደ ምሰሶ ደግፈው የያዙ የሚመስሉ በጣም ረጃጅም ተራሮች መካከል በአንደኛው ጭፍ ላይ ይገኛል፡፡ ቤተ መቅደሱ ከባሕር ወለል በላይ በ2300 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ቤተ መቅደሱ ያለበት የተራራው ርዝመት ብቻውን 300 ሜትር ነው፡፡ ቤተ መቅደሱ በር ላይ ለመድረስ በጭንቅና በፍርሃት ሆኖ ተራራውን እንደዝንጀሮ በእጅ እየቧጠጡ መውጣት ይጠይቃል፡፡ እርሱም ቢሆን በገዳሙ አባቶች እገዛና ድጋፍ ካልሆነ መውጣት የማይቻል ነው፡፡

ቤተ መቅደሱ እጅግ የሚደንቀው በተፈጥሮአዊ አቀማመጡ ብቻ አይደለም ውስጡ ያሉት የግድግዳ ላይ ሥዕሎችም እጅግ ድንቅና ጥንታዊ ናቸው፡፡ ስለዚሁ የአቡነ ይምዓታ እጅግ አስደናቂ ቤተ መቅደስ ገድለ አቡነ አረጋዊ "በሞት በዐረፉ ጊዜ የሥጋቸው ሥርዓተ ግንዘት በመላእክት እጅ ነው የተከናወነው፡፡ ይልቁንም ቁመቱና ርዝመቱ ከታላላቅ ገደል እጅግ በጣም የሚበልጥ የድንጋይ ዓምድ ከወንዝ ማዶ ዘንበል ብሎ መጥቶ ሥጋቸውን በክብር ተቀብሎ በተራራው ጫፍ ላይ እስከዛሬም ድረስ ፈጽሞ ሳይነቃነቅና ሳይናወፅ ቀጥ ብሎ ቆሞ ይገኛል በማለት ይገልጻል።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

#ስንክሳር_ዘወርኅ_ጥቅምት

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

06 Nov, 02:11


መድኃኔዓለም (በዓለ ስቅለት)

ጥቅምት ሃያ ሰባት በዚህች ዕለት የአምላካችን የ #መድኃኔዓለም የስቅለቱ መታሰቢያ ነው።

#መድኃኒታችን ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና በቸርነቱ ስለኹላችን ድኅነት ሲል ራሱን ወድዶ ፈቅዶ ለሞት አሳልፎ በመስጠት ፍጹም ፍቅሩን አሳይቶናል። በቅዱስ ወንጌልም እርሱም #መድኃኒታችን " ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር የለም" ብሎ ነግሮናል። እውነት ነው፣ ራስን ነፍስን ስለጠላት ነፍስ አሳልፎ ከመስጠት በላይ ምን ድንቅ ነገርና ምን ድንቅ ፍቅር አለ?

ቸሩ አምላካችንን የአስቆሮቱ ይሁዳ ሊያስይዘው የሊቃነ ካህናቱን አገልጋዮች እየመራ አመጣቸው። እነርሱንም ማንን ትፈልጋላችሁ ሲላቸው የናዝሬቱ #ኢየሱስን አሉት፣ እኔ ነኝ ቢላቸው የቸሩን አምላክ ድምጽ ሰምቶ አይደለም መቆም በሕይወት መጽናት የሚቻለው የለምና ወደ ኋላቸው ተስፈንጥረው ወደቁ። ደጋግሞም እንዲህ ኾነ። በኋላ ግን እኔ ነኝ ብሎ በፈቃዱ ይሁዳ ስሞ አሳልፎ ሰጣቸው።

ከያዙት በኋላ እያዳፉና እየጎተቱ በሰንሰለት አስረው ወደ ቀያፋና ሐና ግቢ ወሰዱት፣ እስከ ሦስት ሰዓትም አላሳረፉትም ሲያሰቃዩት አድረዋል፣ በራሱም ላይ ሰባ ሦስት ስቊረት ያለው ወደ ሦስት መቶ እሾኾችን የያዘ የእሾህ አክሊል ጎንጉነው ቢያደርጉበት የራስ ቅሉን ቀዶ ገብቶ እስከ ልቡ ዘልቋል። እንደምን ጭንቅ ነው? እንዲህም አድርገው ደግሞ እያፌዙ ርኲስ ምራቃቸውን ይተፉበትና በዘንግም ደጋግመው ይመቱት ነበር። እየተፈራረቁ ያለ ምንም ርኅራኄ ቸሩን አምላክ ሥጋው እየተቆረጠ እስኪወድቅ ድረስ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት ጽኑዕ ግርፋትን ገርፈውታል። የገረፉበትም ጅራፍ በላዩ ላይ ሥጋን እየጎመደ የሚጥል፣ ሕመሙ አንጀት ሰርሥሮ የሚገባ በስለት የተያያዘበት ነበር።

በኋላም አላሳረፉትም እንዲህ አድርገውትም በሊቶስጥራ አደባባይ ያንን ዕርጥብ #መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት። እርሱ ግን ይህን ኹሉ ግፍ ሲያደርሱበት አንድም አልተናገረም ነበር። በቀራንዮም በአምስት ጽኑዕ ቅንዋት (ሳዶር፣ አላዶር፣ ዳናት፣ አዴራ እና ሮዳስ) ቸንክረው ዕርቃኑን ሰቀሉት።

በዚህች ቀን ድንግል #ማርያም ልቧ በሐዘን ተሰበረ መጽናናትንም አልፈለገች ነበር፤ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ እናቱንም እናት ትሆነው ዘንድ በእግረ #መስቀሉ አደራን ተቀበለ። ቅዱሳት አንስት በፍጹም ሀዘንና በዋይታ ዋሉ። በስልጣኑም ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ። ሰባት ድንቅ የኾኑ ተአምራትንም አድርጎ አምላክ መኾኑን ገለጠ። ይህም ጽኑዕ የኾነ ለሰማይ ለምድር የከበደ ነገር ሲከሰት ፀሐይ አምላኬን ዕርቃኑ እንዴት አያለሁ ብላ ጨለመች። ጨረቃ ደም ኾነች፣ ከዋክብቱም ረገፉ፣ ንዑዳን ክቡራን ንጹሐን መላእክትም ትዕግስቱን እያደነቁ በጽኑዕ ሐዘንና መደነቅ ከቅዱስ ዕፀ #መስቀሉ ፊት እንደሻሽ ተነጠፉ።

አስራ አንድ ሰዓት በሆነም ጊዜ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር ቅድስት ሥጋውን ከ #መስቀሉ አውርደው በክብር ገንዘው በአዲስ መቃብር ቀበሩት። በሦስተኛውም ቀን እንደተናገረ ተነሳ።

በዛሬዋ ቀን ቤተ ክርስቲያን የ #መድኃኔለምን የስቅለት በዓል በደማቁ ታከብራለች፤ ይህም የለውጥ በዓል ነው፡፡ #ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ደሙን ያፈሰሰው ስጋውን የቆረሰው መጋቢት 27 ቀን ነው፤ ይህ በዓል ግን በዐቢይ ጾም ስለሚውል በዐቢይ ጾም ሀዘን እንጂ ደስታ ስለሌለና በዓል ማክበር ስለማይፈቀድ፤ ወደ ጥቅምት 27 ተዛውሮ ደስ ብሎን እንድናከብረው ቤተ ክርስቲያን ስርዓት ሰርታልናለች፡፡

እርሱ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ ያለ ልዑለ ባሕርይ ከ #አብ ከ #መንፈስ_ቅዱስ ጋር በጌትነቱ ዙፋን ተቀምጦ ያለ ለእርሱም ምስጋና የክብር ክብር ገንዘቡ የሆነ ራሱን ሰውቶ ያዳነን የመንግሥቱን ደጆች በፈሳሽ ደሙ የከፈተልን ለእርሱ ስግደትአምልኮት ይገባዋል ለዘላለሙ የ #መስቀሉም በረከት በላያችን ይደር አሜን።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

06 Nov, 02:09


🌼🌼እንኳን ለጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የስቅለት በዓል መታሰቢያ አደረሳችሁ🌼🌼

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

05 Nov, 07:32


📸📸📸📸

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

05 Nov, 07:23


👉 ከነዚህ በተጨማሪ በግል እንዲሁም ሁለት ወይም ሶስት ሆናችሁ የተነሳችሁትን photoዎች ለማግኘት
ከስር በተጠቀሱት Account እየገባችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ!

@Hbtesh_Asefa
@Sehinemaryam
@ethio_c

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

05 Nov, 07:10


📸📸

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

05 Nov, 07:09


📸📸📸📸

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

05 Nov, 07:09


📸📸📸📸

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

05 Nov, 07:09


📸📸📸📸
#በጎ
#ኪን

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

04 Nov, 19:12


📸📸📸📸📸📸📸📸📸📸📸
የ 2016 የምሥረታ በዓል ቅኝት በፎቶ
ነገ(ማግሰኞ) ጠዋት የምንልክ ይሆናል!
በዋናው የቴሌግራም ገፃችን ላይ ይጠብቁን !!


#ሠናይ_ምሽት

@referal_gibi
@referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

04 Nov, 03:57


ከጥቅምት_25 ስንክሳር

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥቅምት ሃያ አምስት በዚህች ቀን #ቅዱስ_አቡነ_አቢብ (አባ ቡላ) አረፈ፣ የመላእክት አምሳል የሆነ #አባ_እብሎይ አረፈ፣ የከበረ #ቅዱስ_ዮልዮስ_ሰማዕት ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ነው፣ የደብረ ሊባኖሱ #አባ_ሕፃን_ሞዐ ቃልኪዳን የተቀበሉበት ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አቡነ_አቢብ (አባ ቡላ)

ጥቅምት ሃያ አምስት በዚህች ቀን ታላቅና ክብር የሆነ አቢብ የተባለ መስተጋድል አባ ቡላ አረፈ።

የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አብርሃም የእናቱም ስም ሐሪክ ነው እነርሱም ከሮሜ አገር ሉፊ ከሚባል አውራጃ ናቸው በዘመናቸውም ከሀዲው ንጉሥ መክስምያኖስ በክርስቲያን ወገኖች ላይ መከራ ስለ አመጣ ስደት ሁኖ ነበርና እነርሱም በስደት ብዙ ዘመን ኖሩ።

ልጅንም በአጡ ጊዜ የተባረከ ልጅን ይሰጣቸው ዘንድ በጾም በጸሎት ተወስነው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ የእግዚአብሔርም መልአክ በሕልም ተገለጠላቸውና ፍሬ የመላበትን ዘለላ ሰጣቸው።

ይህም ቅዱስ በተፀነሰ ጊዜ በቤታቸው አጠገብ ታላቅ ዛፍ በቀለ በቅጠሉም ላይ በሮማይስጥ ቋንቋ ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ በጽዮንም አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ያከበረው የሚል ጽሑፍ ነበረበት።

በተወለደም ጊዜ ክርስትና ሳያስነሡ ዓመት ሙሉ አኖሩት እመቤታችን ማርያምም ለሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ለሰለባስትርዮስ ተገልጣ ወደ አብርሃም ቤት ሒዶ ሕፃኑን እንዲአጠምቀው አዘዘችው እርሱም ሒዶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቀው ስሙንም ቡላ ብሎ ሰየመው እናትና አባቱም ሳይነግሩት ቡላ ስለ ሰየመው አደነቁ ዕፁብ ዕፁብ አሉ።

ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ በጸለየ ጊዜ የቊርባን ኅብስትና ወይን የተመላ ጽዋ ከሰማይ ወረደ እርሱም ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን ከሕፃኑ ጋር አቀበላቸው በዚያንም ጊዜ ሕፃኑ የአንድ ዓመት ልጅ ሲሆን በባሕርይ በህልውና በመለኮት ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነ አብ በግብር በአካል በሰም ልዩ ነው በባሕርይ በህልውና በመለኮት ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነ ወልድ በግብር በአካል በስም ልዩ ነው በባሕርይ በህልውና በመለኮት በአብ ከወልድ ጋር አንድ የሆነ መንፈስ ቅዱስ በግብር በአካል በስም ልዩ ነው ብሎ ተናገረ።

ከጥቂት ዘመንም በኋላ አባትና እናቱ ኅዳር ሰባት ቀን ሙተው ሕፃኑ ብቻውን ቀረ።

ሕፃኑም ዐሥር ዓመት በሆነው ጊዜ ለጣዖት መስገድን የሚያዝ ከሀዲ መኰንን መጣ ቅዱስ ቡላም በሰማ ጊዜ ወደ መኰንኑ ሒዶ የረከሱ አማልክቶቹን ረገመ መኰንኑም በአካል ታናሽነቱን አይቶ እጅግ አደነቀ በዚያንም ጊዜ በችንካር እንዲቸነክሩት ሥጋውንም እንዲሠነጣጥቁት ቆዳውንም ከዐጥንቱ እንዲገፉ እጆቹንና እግሮቹንም በመጋዝ እንዲቆርጡ ጀርባውንም እንዲገርፉ በሾተሎችና በጦሮች መካከል አድርገው ከመንኰርኵር ውስጥ እንዲጨምሩት ዳግመኛም በመንገድ ላይ እንዲጐትቱት አዘዘ የመላእክት አለቃ ሚካኤልም መጥቶ አዳነው ያለ ጉዳትም ጤነኛ አደረገው።

ከዚህም በኋላ ወደ ሌላ መኰንን ሒዶ እርሱንና የረከሱ ጣዖቶቹን ረገመ መኰንኑም ተቆጥቶ በሚያዝያ ወር ዐሥራ ስምንት ቀን ራሱን በሰይፍ ቆረጠው ቅዱስ ሚካኤልም ከሰማይ ወርዶ ከሙታን ለይቶ አስነሣው ወደ አንድ ገዳምም ወስዶ የምንኲስና ልብስንና አስኬማን በመስቀልም ምልክት አለበሰው። እንዲህም አለው ከቅዱሳን ጻድቃን አንድነት ትሆን ዘንድ እግዚአብሔር አዝዞሃል።

ያን ጊዜም ቅዱስ አባ ቡላ ከደረቅ ተራራ ላይ ወጣ ያለ ማቋረጥም በውስጧ እየተጋደለ ኖረ። የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራውንና ስቅለቱን በአሰበ ጊዜ ከረጅም ዕንጨት ላይ በመውጣት ራሱን ወደታች ሁል ጊዜ ይወረውር ነበር።

በአንዲትም ቀን ከዛፍ ላይ በተወረወረ ጊዜ ሰይጣን ሊገድለው ስለ በረታበት ሞተ ያን ጊዜም ክብር ይግባውና መድኃኑታችን ከሞት አነሣውና እንዲህ አለው ከእንግዲህ ስምህ ቡላ አይሁን አቢብ ይባል እንጂ የብዙዎች አባት ትሆናለህና።

እርሱም የክርስቶስን ፍቅር እጅግ ጨመረ ፊቱንም እየጸፋ ሥጋውን በየጥቂቱ እየቆረጠ ጀርባውንም ሰባት መቶ ጊዜ እየገረፈ ኖረ ጌታችንም ይፈውሰው ነበር በየእሑድም ቀን ከቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም እንደተወለደ በሌሎች ቀኖችም እንደተያዘና ከአይሁድ መከራ እንደ ተቀበለ ሁኖ ይገለጽለት ነበር።

ስለዚህም ሳይበላ ሳይጠጣ አርባ ሁለት ዓመት ኖረ ዳግመኛም ናላው ፈስሶ እስቲአልቅ ዐሥራ ሁለት ወር በራሱ ተተክሎ ኖረ። በአንዲትም ቀን የጌታችንን መከራ በአሰበ ጊዜ ሰይፉን በአንጻሩ ተከለ ከዕንጨት ላይም ወጥቶ በላዩ ወድቆ ሞተ ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምም ከአእላፍ መላእክት ጋር መጥታ የእኔና የልጄ ወዳጅ ሰላምታ ይድረስህ አለችው ። ከበድኑም ቃል ወጥቶ የሰማይና የምድር ንግሥት እመቤቴ ሰላምታ ይገባሻል አላት እርሷም በከበሩ እጆቿ ዳሥሣ ከሞት አስነሣቸው።

ዕድሜውንም ፈጽሞ ከዚህ ዓለም የሚወጣበት ጊዜ ሲደርስ ክብር ይግባውና ጌታችን ክርስቶስ በእጁ ልዩ የሆኑ አክሊሎችን የሚያበሩ ልብሶችንም ይዞ ተገለጠለት ወዳጄ አቢብ ሆይ በማያልቅ ተድላ ደስታ ደስ አሰኝህ ዘንድ ወደእኔ ና ስምህን ለሚጠራ መታሰቢያህን ለሚያደርግ እኔ ኃጢአቱን አስተሠርይለት ዘንደ በራሴ ማልኩልህ ወይም ለተራቆተ የሚያለብሰውን ለተራበም የሚያጠግበውን ለተጠማ የሚያጠጣውን የገድልህን መጽሐፍም የሚጽፈውን ወይም የሚያነበውንና የሚሰማውን በጸሎትህም የሚታመኑትን ሁሉ እስከ ዐሥር ትውልድ እምራቸዋለሁ ይህንም ብሎ አፉን ሳመው በደረቱም ላይ አድርጎ ወደአየር አወጣው የመላእክትንም ምስጋና በሰማች ጊዜ ነፍሱ ከሥጋው ተለየች ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ገባች።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

02 Nov, 09:04


🌷 ማሕሌተ ጽጌ ፭ ኛ ሣምንት 🌷

እንዲህም አለ ?!


አንድ የቀድሞ የግቢ ጉባኤ ተማሪ የነበረ አሁን በሥራ ላይ የሚገኝ ወንድማችን ለሰላምታ በስልክ ደወለልኝና ስናወራ ወቅቱ ዘመነ ጽጌ ነውና ማሕሌተ ጽጌ ትሄዳለህ ? ስል ጠየቅሁት ፦

" አወ እሄዳለሁ ጽጌን እማ ካልሄድኩ
እንዴት ይሆናል " አለኝ


ቤተክርስቲያን አለ ? ብየ ጠየቅኩት የጎረቤት ሃገራት አዋሳኝ ሥፍራ ነው ያለና ከዚህ በኋላ ነበር እንዲህም አለ የሚያስብል ምላሽ የሰጠኝ

" በቅርብ እንኳን የለም በመኪና የ 300 ብር መንገድ ተጉዤ ነው የምሄደው አለኝ "

ደርሶ መልስ ነው 300 ብር ? ብየ ጠየቅሁት

" አይ ደርሶ መልስ 600 ብር ነው " ብሎ መለሰልኝ ።

በእውነት በማይመች ሁኔታ ውስጥ አብዝቶ ለምስጋና መትጋት በምን ይገለጻል ? ግቢ ጉባኤ በንጽሐ ፍቅር በድንኳንሽ ጥላ አቅፈሽ ያሳደግሻቸውን ልጆች ሳስብ በእናትነትሽ እደነቃለሁ ። ልጆችሽ ያለ ጊዜውም የጸኑልሽ እናት ግቢ ጉባኤ ምንኛ የታደልሽ ነሽ ? እንዲህ ለመታመን ዛሬ በግቢ ያለን የእናታችንን ድምጽ እንስማና ማሕሌተ ጽጌ በአንድነት እንሂድ !

ማሕሌተ ጽጌ | ፩ | 🌷

ተአምረ ፍቅርኪ በማኅበረ ጻድቃን ተወደሰ፤ ወፈድፋደሰ በላዕለ ኃጥአን ነግሠ፤ እስመ አንሥአ (አሕየወ) ሙታነ ወሕሙማነ ፈወሰ፤ ቦ ዘይቤ አጽገየ ዘየብሰ፤ ወቦ ዘይቤ አድባረ አፍለሰ፡፡

ትርጉም 🌷

የታምርሽ ተወዳጅነት በጻድቃን ማሕበር ዘንድ ተመሰገነ ይልቁንም በኃጥአን ዘንድ ከፍ ከፍ አለ ሙታንን አስነስቷልና ሕሙማንንም ፈውሷልና የደረቀውንም እንዲያብብ  ተራራውም እንዲፈልስ አድርጓልና

ምስጢር 🌷

በኃጥአንም ዘንድ ከፍ ከፍ አለ ማለቱ ጻድቃን ስለ መልካም ሥራቸው ዋጋ ያገኛሉ ኃጥአን ግን ገድል ቱሩፋት የላቸውምና በአንች በተሰጠሽ ቃል ኪዳን ልጅሽ ይምራቸዋል ሲል ነው ፤ አባ ሕርያቆስ አዘክሪ ድንግል ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን እንዲል ።

ሙታንን አሥነስቷልና ሕሙማንን ፈውሷልና አለ እመቤታችን በእናቷ ማህጸን ሳለች የቅድስት ሐና ጥላ ሲያርፍባቸው ሕሙማን ይፈወሱ ሙታን ይነሱ ነበር ከተወለደችም በኋላ ድንቅ ተዓምራትን ፈጽማለች በበተአምረ ማርያም ተመዝግቦ እናገኛለን አንድም በኃጢአት የወደቁትን ተአምርሽ ያስነሳቸዋል ሲል ።

ተራራን አፍልሷል ማለቱ በሊቀ ጳጳሱ በአባ አብርሃም ዘመን በግብፅ ሃገር የነገሠ ስሙ ለማዝ የሚባል ንጉሥ “ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ፦ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም።” ማቴ17፥20 መጽሐፋችሁ ይላል ይኽን ፈጽማችሁ አሳየኝ ካልሆነ ዝቅ ብየ ባታችሁን ከፍ ብየ አንገታችሁን እቆርጣችኋለሁ አላቸው ።

ሊቀ ጳጳሱም ንጉሡን ፫ መዓልት እና ፫ ሌሊት እንዲሰጠው ጠይቆ መነኮሳት ካህናቱን ሰብስቦ እንዲጸልዩ ነገራቸው ። በ፫ ኛው ቀን የእመቤታችንን ሥዕል ተማጸነ ። እመቤታችንም ይህ ለአንተ አይቻልህም “ዓይንህም ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት " ማቴ 5:29 ያለውን ስለ ልጄ ፍቅር ዓይኑን በጫማ መስፊያው ያወጣ ፤ ድሃዎችን የሚረዳ ለስምዖን ነው እንጅ አለችው | ስምዖን ጫማ ሰፊው | ።

አባ አብርሃምም እመቤታችን እንደነገረችው ስምዖንን አግኝቶ 40 ጊዜ አቤቱ ጌታ ሆይ ይቅር በለን ብላችሁ ጸልዩ አለው እንዳለውም አድርጎ 3 ጊዜ ሰግደው በመስቀሉ ተራራውን ቢባርከው ተራራው ተነሥቶ ወደ ሰማይ ከፍ ከፍ አለ ሲሰግዱም 3 ጊዜ ተራራው ወደ ቦታው ተመለሰ ።

ማሕሌተ ጽጌ | ፪ | 🌷

ለምንት ሊተ ኢትበሊ እምአፈ ኃጥእ ውዳሴ፤ ይበቍዓኒ ዘብየ እምአፈ ጻድቃን ቅዳሴ፤ ጽጌ መድኃኒት ማርያም ዘሠረፅኪ እምሥርወ እሴ፤ እመ ተወከፍኪ ኪያየ አባሴ፤ ተአምረኪ የአኲት ብናሴ።

ትርጉም 🌷

ከእሴይ ስር የተገኘሽ የመድኀኒት አበባ  ማርያምሆይ ከኃጥአን ምስጋና ይልቅ በኔዘንድ ያለ የጻድቃን ምስጋና ይበቃኛል አትበይ እኔን ኃጢአትኛውን ብትቀበይኝ ታምርሽን ጨረቃ ያመሰግናል ያደንቃል

ምስጢር 🌷

ከእሴይ ሥር የተገኘሽ የመድኃኒት አበባ ማለቱ “ከእሴይ ግንድ በትር ይወጣል፥ ከሥሩም ቍጥቋጥ ያፈራል።” ኢሳ11፥1 ያለውን ይዞ ነው ጻድቃን ዘወትር ያመሰግኑሻልና በቃኝ አትበይ እኔን ኃጢያተኛውን ብትቀበይኝ ተአምርሽን ጨረቃ ( ቅዱሳን ) ያመሰግናሉ ።

ስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
አሜን !

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

01 Nov, 13:24


የመሐረነ አብ ፀሎት

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

31 Oct, 05:17


Sigawan Antsito / Kal Bekalu tenagerat/#መርጌታ_ፀሃይ_ብርሃኑ #ስጋዋን_አንፅቶ_በማርያም_አ...
https://youtube.com/watch?v=QnQTtET0vAY&si=xcqt0pGthSqX4ypn

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

31 Oct, 05:17


🌺🌷 ስጋዋን አንጽቶ 🌷🌺

ሥጋዋን አንጽቶ በማርያም አደረ
ቃሉን በነቢያት ቀድሞ ያናገረ (፪)
ቀድሞ ያናገረ

ቃል በቃሉ ተናገራት(፪)
ማርያምን አከበራት
እግዚአብሔር መረጣት
ቃል ተናገራት


ፍጥረታት በሙሉ ያመሰግኑሻል
የሕይወታችን በር ድንግል ናት ይሉሻል   (፪)
ድንግል ናት ይሉሻል
 አዝ-------
እግዚአብሔር አብ ላከ አንድያ ልጁን
ያንቺን ሥጋ ለብሶ እኛን እንዲያድን(፪)
እኛን እንዲያድን
 አዝ------
ድንግል ሰገዱልሽ መላእክት በራማ
በአንቺ ላይ ስላለ የመላእክት ግርማ(፪)
የመላእክት ግርማ
አዝ----
ዓለሙን ያዳነው ያንቺን ሥጋ ለብሶ
ዘለዓለም ነዋሪ ነው በሰማያት ነግሦ(፪)
በሰማያት ነግሦ
        
 (መሪጌታ ፀሐይ ብርሃኑ)

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

29 Oct, 17:37


#መልካም_ፈተና

<< ሥራህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፤ ዐሳብህም ትጸናለች። >> (ምሳ. 16፥3)

ነገ የQualification ፈተና ለምትጀምሩ old PCII  ተማሪዎች ግቢ ጉባኤያችን የቀና  ያማረ እና የሠመረ ይሆንላችሁ ዘንድ መልካም ምኞቱን ይገልጻል ።


📖 የአባቶቻችን የአብርሃም ፥ የይስሐቅ ፥ የያዕቆብ አምላክ ማስተዋሉን ፥ ጥበቡን ፥ አእምሮውን ያድላችሁ! 📖

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

29 Oct, 13:19


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) pinned «»

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

28 Oct, 18:28


ለመምጣት ባይመቻችሁም ካላችሁበት ሆናችሁ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ያስላለፋችሁል መልእክቶቻችሁን ለማስተላለፍ ሟክረናል::

በስልክ እንኳን አደረሳችሁ ያላችሁን

#Dn_Dr_Nigus
#Dr_Kassahun

እናመሰግናለን😍

ለ20ኛ የግቢ ጉባኤያችን ልደት እግዚአብሔር ያድርሰን ከአሁኑ ተዘጋጁ

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

28 Oct, 18:28


#Dr_Getasew
#Dn_Dr_Buzayehu
#Dr_Birhanu
#Dr_Getachew_worku
#Dn_Dr_Bereket
#Dr_Hiywot
#Dr_Hana
#Dr_Yeneneh Asefa
#Dr_Misge
#Dr_Biruk
#Dr_Mikiyas
#Dn_Abreham_Endle
#Dn_Abreham_Tadesse
#Elias
#Sister_Bethelhem
#Zelalem


መጥታችሁ በዓሉን ከኛ ጋር ስላከበራችሁ እጅግ አድርገን እናመሰግናለን።
በሰላም ወደየ ቤታችሁ እንደገባችሁ ተስፈ እናደርጋለን።

መምጣት አስባችሁ አቅዳችሁ ያልተሳካላችሁ እና ሌሎችም ለቀጣይ ዓመት ምሥረታ ያብቃን ያብቃችሁ።

የምሥረታ በዓል አከባበራችን በተሳካ ኹኔታ ተጠናቋል።

ስለኹሉም ነገር  እግዚአብሔር ይመስገን

        @referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

28 Oct, 16:08


Enkuan aderesen aderesachu

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

28 Oct, 16:06


Ekuan aderesachihu

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

28 Oct, 16:05


እንደ ቀልድ ያየናቸው ጊዜያት ትዝታው በልብ ሁሌም ይኖራል ። ትምህርት ክፍል ያሳለፍኩት ሁሌም አይረሳኝም በሰዓቱ ያልታወቀኝ መልካም ቦታ ነበረ። ዲ/ን አብርሃም ዲ/ን ባይሳ ዝምታ ማርቲ ለምለም አጋር ዮርዲ አልሚ
ብቻ መልካም ጊዜ ነበረኝ ብዙ ተምሬበታለው
ሁላቹም እንኳን አደረሳችሁ እግዚአብሔር ይጠብቃቹ መልካም ጊዜ

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

28 Oct, 16:05


Enkuan adersachu baye betam des belognal rejem gize lemetat akeje neber neger gn ke akeme belay selhonebgn nw yekerewut yikirta betam

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

26 Oct, 17:04


#እየጠበቅናችሁ_ነው!

በአካል መገኘት ለማትችሉ ግን ይህንን ደስታችንን በጋራ ለምትደሰቱ በሙሉ!

  ማስተላለፍ የምትፈልጉትን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እና ማንኛውም ሀሳብ ላኩልን እየጠበቅናችሁ ነው😊!

📩📩📩📩📩📩📩📩📩📩📩📩
 ሐሳብ ወይም መልዕክት መስጫ

[
@BayeB21 , @Sehinemaryam  ]
ላይ ላኩልን ይደርሰናል!

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

26 Oct, 15:35


🔔🔔ደረሰ! ደረሰ! ደረሰ!🔔🔔

በጉጉት የምንጠብቀው የምንናፍቀው
ከቀድሞ የግቢ ጉባኤ ልጆችን ጋር  የምናገኝበት  ታላቅ እና የማይገኝ ብርቅዬ ምሽት!

የህይወት ልምዳቸውን እና ተሞክሯቸውን ሊያካፍሉን በናፍቆት እየጠበቁን ነው!

#ይህን_ምሽት_ከእንግዶች_ጋር!

#ከ ምሽት 2:00 ጀምሮ
#ቤተ_አብርሃም
#ጥቅምት_16/2017ዓም

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

26 Oct, 04:31


መርሃ ግብራቱ የሚካሄዱበት ቦታዎች

📍የጠዋትና የሠርክ መርሃ ግብራት - ደ/ኢየሱስ ወቅ/አርሴማ ቤተክርስቲያን አውደ ምህረት

📍አውደ ርዕይ - ደ/ኢየሱስ ወቅ/አርሴማ ቤተክርስቲያን የወንዶች መጠለያ ውስጥ (በመጋረጃ የተሸፈነው ቦታ)

#ግቢ_ጉባኤ_ልደትሽ_ልደታችን_ነው

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

24 Oct, 07:09


🎉🎊🎉🎆🎆🎆🎆🎉🎊🎉🎊🎉

እንኳን ለ፲፱ኛ ዓመት የሪግግጉ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!!



      🎊    🎉   🎆   🎊      🎉

                   🌹🌹🌹🌹
                   🌹💐💐🌹
  🎉        🌹💐💐💐🌹      🎊
          🌹🌹🌹💐💐🌹
                   🌹💐💐🌹
                   🌹💐💐🌹     🎆
                   🌹💐💐🌹
     🎊         🌹💐💐🌹
                   🌹💐💐🌹
                   🌹💐💐🌹       🥳
                   🌹💐💐🌹
         🎉     🌹💐💐🌹
                   🌹💐💐🌹
                   🌹💐💐🌹     🎊
                   🌹💐💐🌹
                   🌹💐💐🌹     🎉
🎊              🌹💐💐🌹
     🌹🌹🌹🌹💐💐🌹🌹🌹🌹
     🌹💐💐💐💐💐💐💐💐🌹
     🌹💐💐💐💐💐💐💐💐🌹
     🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
    
                          
#ቀን_ብቻ_ቀረ

ቀን:-   ጥቅምት 15፣ አርብ 🎇ማታ 11፡30 ይጀምራል!

  ቦታ:-  
#ደብረ_ኢየሱስ አውደ ምሕረት ላይ ለተከታታይ 3 ቀናት
       
               @referal_gibi 💐

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

21 Oct, 09:38


"ወትትሐሠይ ነፍስየ በእግዚአብሔር እስመ አልበሰኒ ልብሰ ሕይወት ወከደነኒ ክዳነ ሐሤት ከመ ትርሲተ መርዓዊ ወከመ ሰርጐ መርዓት"

ትንቢተ ኢሳይያስ ፷፩÷፲

ከእርሷ ተጠግተን በክርስቶስ ፍቅር የኖርንባት ፤ በቃሉ ትምህርት ሐሴት ያደረግንባት ፤ በዝማሬ ነፍሳችን የረካችባት እመ ኲሉ አርድእት ግቢ ጉባኤ ክርስቶስ ኢየሱስ የማዳንን ልብስ እንዳለበሰን ትእምርት ይሆን ዘንድ የልደት በዓል ቲሸርቴን ልበሱ ተጎናፀፉ ትለናለች ።

“ሁልጊዜ ልብስህ ነጭ ይሁን...  ።” መክ 9፥8 ነጩን ልብስ ለብሰን አክሊል እንደ ለበሰ ሙሽራ እንዳጌጠችም ሙሽሪት ደምቀን የእናታችንን ልደት እናከብር ዘንድ ቲሸርቱን እንግዛ ።

💰 ዋጋ     : # 300 ብር
📍 አድራሻ ፡ ሐመር ሱቅ
💎 ከአስተማማኝ የብድር አማራጭ ጋር !

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

20 Oct, 07:00


" መሳለቂያ እንዳንሆን ኢየሩሳሌምን እንቅጠር "
ንህምያ 2:17

እስራኤላውያን በታሪካቼው ከባቢሎን ምርኮ ቀጥሎ ትልቁ በፋርስ የተማረኩበት ጊዜ ነበር ። የ እስራኤል ዘሥጋ ቁልፉ የሚባሉ ሰዎችን ማርከው ፤ ቤተ መቅደሱን ፤ አጥር ቅጥራቼውን አፈረሱ ።

ከምርኮኞቹ አንዱ የነበረው ንህምያ ከብዙ ጊዜ ምርኮ በኋላ በንጉሡ ፈቃድ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ " መሳለቂያ እንዳንሆን ኢየሩሳሌምን ቅጥር እንሥራ " አለ ። የፈረሰውን ቅጥርም በ 52 ቀናት ሠርተው አጠናቀቁ ።

ተወዳጆች እኛም መሳለቂያ እንዳንሆን ኢየሩሳሌምን እንቅጠር ። ኢየሩሳሌም ግቢ ጉባኤን እንቅጠር ። የክርስቶስ ፍቅር የተገለጠባት ፤ የቃሉን ወተት የጠጣንባት ፤ ከእርሷ ተማርከን መሄድ የማንፈልግባት ግቢ ጉባኤ ለእኛ ኢየሩሳሌም ናት ።

እናም እኛ እንደ እስራኤላውያን የእናታችንን ቅጥር የምንሰራው በዲንጋይ በአሸዋ አይደለም የግቢ ጉባኤ ቅጥሮች እኛ ነን እንጅ ። ሁላችንም ከያለንበት ለእናታችን ፲፱ ኛ ዓመት በመሰብሰብ ቅጥር እንሁናት ። ግቢ ጉባኤአችን ከበን በዙሪያዋ እንመላለስ ።

የቀደመውን ጊዜ እናስብ ፤ ከግቢ ጉባኤ ያላገኘነው ምን አለ ? በማይመች ሁኔታ ውስጥ ብንሆን እንኳ ስለ ፍቅሯ እንሰብሰብ ። መሳለቂያ እንዳንሆን ግቢ ጉባኤን እንቅጠር ። በስራ ላይ የምትገኙ ወንድም እኅቶቻችን ከ ጥቅምት 15-17 በእናታችሁ ቤት እንድትገኙ በእግዚአብሔር ስም ተጠርታችኋል ።


በእናታችን ቤት እንሰብሰብ !
እግዚአብሔር በሰላም ያገናኘን !

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

18 Oct, 16:44


ማኅሌተ ጽጌ ፫ ኛ ሳምንት

በቀደመው ሳምንት እንዘ ተሐቅፊዮ ሲባል ለምን ዲያቆናት ምስለ ፍቁር ወልዳ ሥዕል ይዘው ካህናት ማዕጠንት ያጥናሉ ?


የማኅሌተ ጽጌ ደራሲዎች አባ ጽጌ ድንግል እና አባ ገብረ ማርያም የጽጌዋ ምስጋና የተገለጠላቼው ከ ፱ ዓመታት ጸሎት በኋላ ነበር ። በየዓመቱ መስከረም 26 ሲደርስ በጋራ የአበባዋን ምስጋና በጋራ ያደርሱ ነበር ።

እንዘ ተሐቅፊዮ ሲሉ የእመቤታችንን ከተወደደ ልጇ ጋር ያለውን ሥዕለ አድኅኖ ይዘው ሲያመሰግኗት እመቤታችን ተገልጣ ትባርካቼው ነበር ። ስለዚህም ነው ምስለ ፍቁር ወልዳን መያዛቼው ። ዛሬም ልጅሽን ይዘሽ ነይ እያልን ስሟን ስንጠራት ትባርከናለችና ።

ማኅሌተ ጽጌ 🌷

ትመስል እምኪ ማርያም ዕለተ ሣልስተ ወራብዕተ፤ዘወለደት ጽጌ ወፀሐየ ዓለም ብርህተ፤ካዕበ (ወካዕበ) ትመስል ሳብዕተ ዕለተ፤እስመ ፈረየት ኪያኪ ተአምረ ግዕዛን ሰንበተ፤ ለእለ በሰማይ ወምድር ዘኮንኪ ዕረፍተ።

ትርጉም 🌷

አበባ እና ብርህት የዓለም ፀሐይ የወለደች
ማርያም እናትሽ ሐና ሶሥተኛዋን እና
አራተኛዋን ዕለት ትመስላለች ፤ ዳግመኛም ሰባተኛዋን ዕለት ትመስላለች በሰማይና በምድር ላሉ እረፍት የሆንሽ የነጻነት ምልክት
ሰንበት አንችን አፍርታለች ።

ምስጢር 🌷

እመቤታችን በሰባቱ ዕለታት ትመሰላለች ፤ የፍጥረት የመጀመሪያ ቀን እሑድ ነው ደራሲው እናትሽ ሐና ሦስተኛዋን ዕለት ማክሰኞን ትመስላለች ማለቱ እንደምን ነው ቢሉ በሦስተኛው ቀን አዝዕርት ፣ አበባዎች ፣ፅጽዋት ተገኝተዋል ከእናታችን ሐናም የፈካች አበባ ፍሬዋ ክርስቶስ የሆነ እመቤታችን ተገኝታለችና ሦስተኛዋን ዕለት ትመስላለች አለ ።

ወራብዕተ አለ የፍጥረት አራተኛ ቀን ረቡዕ ነው በዚህ ቀን ፀሐይ ፣ ጨረቃ ፣ ከዋክብት ተገኝተዋል ፀዓዳ የሆነች አማናዊት ፀሐይ ካንች ተገኝታለችና ሲል መስሏታል ። “ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”ራእይ 12፥1

ሰባቸኛዋን ቀንም ትመስላለች አለ ቀዳሚት ሰንበት ናት በዚች ዕለት አምላካችን ከሥራው ሁሉ ያረፈባት ዕለት ናት እመቤታችንም በሰማይና በምድር ላሉ ፍጥረታት ዕረፍት ናትና አንችን ያስገኘች ሐና ሰባተኛዋን ዕለት ትመስላለች ይላል ።

ጥያቄ ?

አዳም በገነት ለምን ያህል ጊዜ ኖረ ?
ከነ ቀኑ ድረስ መናገር አሸናፊ ያደርጋል ።
በሰው ልቦና ያልታሰበ ልዩ ሽልማት ያስገኛል ።


በማኅሌት ከእመቤታችን በረከት እንሳተፍ ! 🌷

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

15 Oct, 09:25


እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ገብረ ሕየወት) ዓመታዊ የእረፍት መታሰቢያ በዓል በሠላም አደረሳችሁ!

#ጥቅምት_5

ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ዕረፍቱ መጋቢት 5 ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15 ላይ በዐቢይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሐዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሐዘን እንጂ። የመጋቢት 27 ስቅለት ጥቅምት 27 ቀን እንደሚከበረው ሁሉ ወደ ጥቅምት 5 ቀን ተዛውሮ እንዲከበር ተደረገ፡፡

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።


https://t.me/referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

13 Oct, 12:08


" የሞትክለት እንዴት ይሙት ?! "
...
        

🔘 ውብ ምስጢር የቋጠሩ ሀረጋት ፣ በጋራ የመደርደራቼው አንዳች ፍቺ ፣ የመዋሀዳቼው ረብ ትርጉም ፤ የቅኔአቼው ሰም እና ወርቅ ሲተረጎም ፤ ያዘሉት ምስጢር ሲደላደል ፤ ዕደ ሕሊና ሰማያትን ይጨብጣል ። እግረ ልቦና በጥበብ ተመልቶ ይረማመዳል ።

🔘 " የሞትክለት እንዴት ይሙት " ደጋግመው ቢሰሙት ንቃተ መንፈስን የሚያድል ፤ ልብን ዘልቆ የሚፈስ የግጥም ውሃ ! ሁላችሁም ጠጥታችሁ ትረኩ ዘንድ የተጠማ ሁሉ ይጠጣ እንላለን !

🎤 "....መቆም ከብዶት ሲንገዳገድ
የዓለም ፍቅር እየገዛው
ቁልቁል ሲወርድ ከጸጋህ ላይ
የዘመኑ ደዌ ስቦት
ከአባቱ ቤት ጠፍቶ ሄዶ
የሞትክለት እንዴት ይሙት
የሞትክለት ለምን ይሙት "

👤 በገጣሚት ፡ ዕሌኒ መኮነን

| ከግጥሙ የተወሰደ |

ይኸን ድንቅ ግጥም በሪፈራል ግቢ ጉባኤ የዩቲዩብ ገጽ ይመልከቱ !


https://www.youtube.com/watch?v=p9vyeXU5pic

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

11 Oct, 19:01


#ስለ_ጽዮን_ዝም_አልልም ኢሳ 62 : 1

✝️ ቤተ አብርሃም ለ ፲፱ ዓመታት ✝️

አብርሃም በዘመኑ ድንኳኑን አቁሞ በአራቱም አቅጣጫ የሚመጡ እንግዶችን እየተቀበለ ከድካማቸው እንዲበረቱ እግራቸውን አጥቦ ፤ ለሰውነታቸው ኃይል ለመንገዳቸው ስንቅ ይሆን ዘንድ መልካሙን ፍሬዳ ጥሎ ያስተናግድ ነበር።
እነሆ የኛዋ ቤተ አብርሃምም ከምሥረታዋ ጀምሮ በዓራቱ አቅጣጫ የሚመጡ ልጆቿን ከድካማችሁ እረፉ እያለች እግሮቻችን አጥባ ተቀብላ ለመንፈሳችን ብርታት የሕይወታችን ስንቅ የሚሆነንን መልካሙን የእውቀትና መንፈሳዊ መዕድ እየመገበች እነሆ ፲፱ ዓመት ሆናት ።
እኛም "ወኢያረምም በእንተ ጽየን" የበላነውን የጠጣነውን ስለአገኘንባት ስለ እናታችን ስለ፦

  📍ድንግል ማርያም
  📍ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
  📍ግቢ ጉባያችን


ዝም አንልም ልደቷ ልደታችን ነው ብለን ለማክበር ጥቅምት 15 - 17 2017 ዓ.ም ቀጠሮ ይዘናል።
እናታችን የሐዋሳ ዩ/ሪ/ግ/ግ/ጉ እናንተ ልጆቿን የትናችሁ በላ እየተጣራች ዝግጅቷን እያጠናቀች ትገኛለት።
እናት ጠርታ መቅረት አይታሰብምና ከወዲሁ እንድትዘጋጁ በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን።

https://t.me/referal_gibi

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

11 Oct, 15:27


እንኳን ለእመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር
ለተሰደደችበት ለዘመነ ጽጌ በሰላም አደረሳችሁ ! የእመቤታችን ምስጋና ሁለተኛ ሳምንት ትርጓሜ ! 🌷


| ፩ |ማኅሌተ ጽጌ፦ 🌷

ከመ ታቦት ሥርጉት በወርቀ ዓረብ ወተርሴስ፤በድንግልና ማርያም ሥርጉተ ሥጋ ወነፍስ፤ ተአምረ ነቢር አርአይኪ በቤተ መቅደስ፤ኢያቄም ወሐና ቀንሞስ ቀናንሞስ፤ እምዘ ጸገዩኪ ለጳጦስ በዓመት ሠላስ

ትርጉም

ማርያም ሆይ! በዐረብና በተርሴስ ወርቅ እንደ ተሸለመ (ተለበጠ) ታቦት በድንግልና ጌጥ በነፍስ በሥጋሽ የተሸለምሽ ነሽ ሀና እና ኢያቄም ሽቶዎች ካበቡሽ ( አበባ ካረጉሽ) በኋላ በሦስት ዓመትሽ የመቀመጥ ተአምርን በቤተ መቅደስ ዓሳየሽ


አንድምታ

ይህ ክፍል በ ሦስት ዓመቷ የእመቤታችንን ወደ ቤተ መቅደስ መግባት ይናገራል ፤ በዚህ እድሜ ህጻናት ከቤተሰቦቻቸው ለቅጽበት መለየት የማይፈልጉበት ሲሆን አንች ግን እመቤታችን ቤተ መቅደስ ከ ኢያቄም አባትሽ ከሐና እናትሽ ተለይተሽ ተቀመጥሽ እያለ ይደነቃል ።


| ፪ |ማኅሌተ ጽጌ | የዘወትር ቀለም | 🌷

እንዘ  ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ ፣አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፣ንዒ  ርግብየ  ትናዝዝኒ  እምላህ፣ወንዒ  ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፣ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ

ትርጉም

ነጭና ቀይ መልክ ያለው አበባ የሚባል ልጅሽን ታቅፈሽ
ወደ ቤተመቅደስ እንደገባሽበት ተአምርና ንጹሕ ጊዜ ሁሉ ደስ ካለው ከገብርኤልና  እንደ አንቺ ርኅሩህ ከሆነው ከሚካኤል ጋር ከኀዘን ታረጋጊኝ ዘንድ ነዪ።


አንድምታ

ነጭ እና ቀይ መልክ ያለው አበባ ማለቱ ወልድ እኁየ ፀዓዳ ወቀይህ እንዲል ፀዓዳ በመለኮቱ ወቀይህ በትስብእቱ ሲል ነው ይኸም ፍጹም ሰው ፍጹም
አምላክ የሆነ ልጅሽን ይዘሽ ነይ ።

ተውህቦ ምሕረት ለሚካኤል ወብስራት ለገብርኤል እንዲል ቅዳሴአችን አብሳሪ ( ደስተኛ ) ከሆነው
ከቅዱስ ገብርኤል ሩኅሩኅ ከሆነው ከሚካኤል ጋር ከሀዘኔ ከጭንቀቴ ታረጋጊኝ ዘንድ ወደ እኔ ነይ ።


| ፫ |ማኅሌተ ጽጌ | የዘወትር ቀለም | 🌷

ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ  ዘየኃቱ፤ዘተጽሕፈ ብኪ  ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤አክሊለ ጽጌ ማርያም  ለጊዮርጊስ ቀጸላ  መንግሥቱ፤አንቲ  ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡

ትርጉም

ባሕርይ ከሚባል ከሚያበራ ዕንቁ ይልቅ የጠራ የወርቅ ጌጥ የኾንሽለት፣
(የጊዮርጊስ) የስሙ ምልክትና የሞቱ መታሰቢያ የተጻፈብሽ፣
ለጊዮርጊስ የመንግሥቱ ዘውድ የሆንሽ የአበባ አክሊል ማርያም ሆይ፣
አንቺ ለእርሱ ኹሉን ታሰግጂለታለሽ፣
እርሱ ግን ላንቺ ይሰግዳል።


አንድምታ

የስሙ መታሰቢያ ማለቱ ማርያም ከሚለው ስም 'ማር ' የሚለውን ወስዶ ማር ጊዮርጊስ ይላልና ትርጓሜውም ቅዱስ ጊዮርጊስ ነው ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሦስት ጊዜ ሞቶ በአራተኛው የሕይወት አክሊል እንደተቀበለ ማርያም የሚለው አራት ፊደል መሆኑ በዚህ ወክሎ የሞቱ መታሰቢያ ማለቱ ለዚህ ነው ።


የጊዮርጊስ የአበባ አክሊል ማርያም ማለቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋድሎውን እንደፈጸመ የሕይወት አክሊል ተቀብሏል እመቤታችንም ዕፀ ሕይወት ናትና የጊዮርጊስ አክሊሉ ነሽ ይላታል ።

በደብረ ቁስቋም እመቤታችን ለግብፅ ምእመናን ተገልጣ ጊዮርጊስ በነጭ ፈረስ በምስራቅ ተገልጦ ለእመቤታችን እሰግድ ለኪ እያለ ሲሰግድ አንች ደግሞ እነሱን ታሰግጅለታለሽ ሲል ነው ።


ጥያቄ | Comment ላይ ይመልሱ |
| ቀድሞ ለመለሰ ..............|

ለምን እንዘ ተሐቅፊዮ ሲባል ዲያቆናት ምስለ ፍቁር ወልዳ ሥዕል ይዘው ካህናት ማዕጠንት ያጥናሉ ? ትርጓሜው ምንድን ነው ?


“እናትህ እነኋት አለው ። ” ዮሐ 19፥27 ወደ እናታችን ምስጋና ማኅሌተ ጽጌ !

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

11 Oct, 06:31


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) pinned Deleted message

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

11 Oct, 05:08


እሴብሕ ጸጋኪ ኦ እግዝእትየ ማርያም ዕፅ ልምልምት ወፍሬ ጥዕምት፤ እምሐና ወኢያቄም ዘሠረፀት። 
🌷🌷ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ሐረገ (ዐፀደ) ወይን አንቲ ማርያም 

ትመስሊ ፊደለ፤ ወትወልዲ ወንጌለ፤ ወታገምሪ መስቀለ።
🌷ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ሐረገ (ዐፀደ) ወይን አንቲ ማርያም

ትመስሊ ሰማየ፤ ወትልዲ ፀሐየ፤ ወታገምሪ አዶናየ። 
🌷🌷ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ሐረገ (ዐፀደ) ወይን አንቲ ማርያም

ትመስሊ መሶበ፤ ወትወልዲ ኮከበ፤ ወታጸግቢ ርኁበ።
🌷🌷ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ሐረገ (ዐፀደ) ወይን አንቲ ማርያም

ትመስሊ መቅደሰ፤ ወትወልዲ ንጉሠ፤ ወታገምሪ መንፈስ ቅዱሰ።
🌷🌷ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ሐረገ (ዐፀደ) ወይን አንቲ ማርያም

ትመስሊ ጽላተ፤ ወትወልዲ ታቦተ፤ ወታገምሪ መለኮተ።
🌷🌷ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ሐረገ (ዐፀደ) ወይን አንቲ ማርያም

ትመስሊ ደመና፤ ወትወልዲ ኅብስተ መና፤ ወታገምሪ ጥዒና። 
🌷🌷ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ሐረገ (ዐፀደ) ወይን አንቲ ማርያም

ትመስሊ ገራህተ፤ ወታፈርዪ ሰዊተ፤ ወታጸግቢ ነፍሳተ።
🌷🌷ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ሐረገ (ዐፀደ) ወይን አንቲ ማርያም

ትመስሊ ስኂነ፤ ወትወልዲ መድኅነ፤ ወትፌውሲ ቁሱላነ።
🌷🌷 ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ሐረገ (ዐፀደ) ወይን አንቲ ማርያም

ትመስሊ ምሥራቀ፤ ወትወልዲ መብረቀ፤ ወታለብሲ ዕሩቀ።
🌷🌷ሐረገ ወይን ሐረገ ወይን ሐረገ (ዐፀደ) ወይን አንቲ ማርያም
ለአብ መርዓቱ ለወልድ ወላዲቱ ወለመንፈስ ቅዱስ ጽርሐ ቤቱ

ስብሐት ለኪ፤ እምዘበላዕነ ሥጋ ወልድኪ፤ ወእምዘሰተይነ ደመ መሢሕኪ፤ አግብርትኪ ወአእማትኪ ለዓለመ ዓለም። አሜን።

ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL)

10 Oct, 15:05


ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ግቢ ግቢ ጉባኤ (OFFICIAL) pinned «»