ራዕየ ማርያም ✝ @raiye_mariyam Channel on Telegram

ራዕየ ማርያም

@raiye_mariyam


በኖኅ ዘመን የነበሩ ሰዎች የተሰጣቸውን ትምህርት ችላ በማለት ሲጨፍሩና ሲደንሱ የጥፋት ውሃ ድንገት ጠራርጎ እንደወሰዳቸው የዓለም ኅልፈት የክርስቶስ መምጣት እንዲሁ ባልታሰበበት ሰዓት ነውና ተዘጋጅታችሁ ጠብቁ።

ሠማይ እና ምድር ያልፋሉ፤ ቃሌ ግን ፈፅሞ አያልፍም። ማቴ 24:35

ራዕየ ማርያም ✝ (Amharic)

ራዕየ ማርያም ✝ በኖኅ ዘመን የነበሩ ሰዎች ለማለት የተሰጣቸውን ትምህርት ችላ በማለት ሲጨፍሩና ሲደንሱ የጥፋት ውሃ ድንገት ጠራርጎ እንደወሰዳቸው የዓለም ኅልፈት የክርስቶስ መምጣት እንዲሁ ባልታሰበበት ሰዓት ነውና ተዘጋጅታችሁ ጠብቁ። ሠማይ እና ምድር ያልፋሉ፤ ቃሌ ግን ፈፅሞ አያልፍም። ማቴ 24:35nnራዕየ ማርያም ✝ የእናቱ ማርያም በዓለም አብዋት ምስጋናን እንዳይጠቀሱ ትምህርታቸውን በራሱ ድምፅ በጎ ሰላም በሦስት ባንድ ወይም በዓለም አንተን/እኛ ውስጥ ማድረግ እና ምድር ያልፋሉ። ይህ በዓለም ቅስምት የሚሆን ነው። ለአምልኮ ስትሆን ክርስቶስ ፍጥነትን አትማል፤ የክርስቶስ እየሖዶዶም።

ራዕየ ማርያም

29 Jan, 11:15


.....ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።

በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሐዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።

ወዲያውኑ ሁሉም ሐዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነሥተው ወደ እመቤታችን ደርሰው  ሰገዱላት አምላካችን  ከአንቺ የተወለደ ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ ዓለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት።

በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በዐልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሐዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያችሁ  ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኋችሁ እንደማየው አሁን አወቅሁ ከዚህ ከሥጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ሕይወት እሔዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም ዓለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ።

ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት።

እመቤታችን ማርያምም ይህን ነገር ከሐዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈጽሜ አመሰግናለሁ። የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።

ጸሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሐዋርያትን እንዲህ አለቻቸው ዕጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ። በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፋት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረጉ  ዕውሮች አይተዋልና፣ሐንካሶች ቀንተው ሔደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምጻሞች ነጹ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሔዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለችበት ቤት በቀረቡ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።

ከዚህም በኋላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሣ ከእሳት ባሕርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእርሳቸው ለማንም በአንቺ  ላይ ሥልጣን የለውም አላት።

ከሥጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሐዋርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጅዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንጽሕት ነፍሷን ከሥጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሃን ልብስ አጐናጽፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ሥጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሐዋርያትን አዘዛቸው።

ነፍሷ ከሥጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሃንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ሥጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ሥጋሽን ከነፍስሽ ጋር  አዋህጄ አስነሥቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሁነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት።

እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሠራህ አመሰግንሃለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሃለሁ በስሜ ወዳንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሁኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በሥራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ  ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉባትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መሥዋዕታቸውን ተቀበል።

ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሺኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ  ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ጸጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም ዓለም በሚመጣውም ዓለም አይጠፋም።

እመቤታችንም ከአረፈች በኋላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሐዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ሥጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእርሳቸው  አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን ዐልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በዐልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።

ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ  በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሐዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ ።

በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሦስት ቀን ኖሩ ዕረፍቷም የሆነው እሑድ ቀን በጥር ወር በሃያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሃናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ሥጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በዕፀ ሕይወት ሥር አኖሩዋት።

ሐዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሣ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኋላ ወደ ሐዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበሩዋትም ነገሩት ቶማስም ሥጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።
ሥጋዋንም ያሳዩት ዘንድ ወደ መቃብርዋ በአደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ሥጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ  ነገራቸው። ሐዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን ዕርገቷን ስለ አላዩ እጅግ አዘኑ ሥጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኋላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ስጣቸው እነርሱም እስከ ነሐሴ ዐሥራ ስድስት በተስፋ ኖሩ።

የእመቤታችንም የዕድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት ዓመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሦስት ዓመት ከሰባት ወር፣ በቤተ መቅደስም ዐሥራ ሁለት ዓመት፣ በዮሴፍም ቤት ሠላሳ አራት ዓመት ከሦስት ወር፣ ከጌታ ዕርገት በኋላ በወንጌላዊ ዮሐንስ ቤት ዐሥራ አራት ዓመት ነው።

የእመቤታችን የድንግል ማርያም በረከቷን ጣዕሟን ታሳድርብን ፤ እኛንም ቤተክርስቲያንንም ሀገራችንንም ከክፉ ትጠብቅልን🙏🏿
   
እንኳን አደረሳችሁ
        

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

29 Jan, 11:15


† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †

† ስንክሳር ዘወርኀ ጥር ፳፩ †

✞ በዓለ አስተርዕዮ ማርያም ✞

አንድ አምላክ  በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሃያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ ነው። ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃብሩ ቦታ ትጸልይ ነበረ ከዚህም ዓለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኋላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።

በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ጸለየች
ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሐንስን በዚች ሰዓት አምጣው። እንዲሁም ሕያዋን እንደሆኑ ሐዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሃቸውን አምጣቸው አንተ የሕያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።

በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሐንስን ደመና ተሽክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ጸጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ ዓለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ሕይወት ትሔጂአለሽና። ይህም ስሙ ክቡር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኋላ ነው።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላት።
እግዚአብሔርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም.....

ራዕየ ማርያም

18 Jan, 17:27


"ያመነ የተጠመቀ ይድናል  ያላመነ ግን  ይፈረድበታል:-  (ማር  16÷16  [[፩፮÷፩፮]]
ጥምቀት:- ማለት  መነከር : በውሃ ውስጥ ገብቶ መውጣት:መዘፈቅ:መጥለቅ ማለት ነው

  ማቴ 3:16-17(፫÷፩፮-፩፯)
" ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤" " እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።"

እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

18 Jan, 16:54


"ጌታ" ጥምቀቱን በውኃ ያደረገው ለምድርን ነው ቢሉ፦ ውኃ በኹሉ ቦታ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ይፈሳልና ፤ ጥምቀትም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደረጋልና ነው።

እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን
🥰

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

12 Jan, 08:57


ሽፍታው በመስቀል ላይ እያለ በአንድ ቃል ፀደቀ፡፡ከሐዋርያት አንዱ ሆኖ ተቆጥሮ የነበረው ይሁዳ ያን ሁሉ ድካሙን በአንዲት ምሽት አጥቶ ከመንግስተ ሰማያት ወደ ሲኦል ወረደ፡፡
ስለዚህ ማንም ሰው ስለ ራሱ መልካም ስራ አይመካ በራሳቸው የሚታመኑ ሁሉ ይወድቃሉና፡፡ 

አባ ዘንትያስ
https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

11 Jan, 07:08


https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

08 Jan, 16:47


ያዕቆብ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ ወንድሞቼ ሆይ፥ እምነት አለኝ የሚል፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?
¹⁵ ወንድም ወይም እኅት ራቁታቸውን ቢሆኑ የዕለት ምግብንም ቢያጡ፥
¹⁶ ከእናንተ አንዱም፦ በደኅና ሂዱ፥ እሳት ሙቁ፥ ጥገቡም ቢላቸው ለሰውነት ግን የሚያስፈልጉትን ባትሰጡአቸው ምን ይጠቅማቸዋል?
¹⁷ እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።
¹⁸ ነገር ግን አንድ ሰው፦ አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ፤ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ፥ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል።
¹⁹ እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ፤ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።
²⁰ አንተ ከንቱ ሰው፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን?
²¹ አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን በመሠዊያው ባቀረበ ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን?
²² እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደ ነበረ፥ በሥራም እምነት እንደ ተፈጸመ ትመለከታለህን?
²³ መጽሐፍም፦ አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት ያለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ።
²⁴ ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ።

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

07 Jan, 18:54


ማቴዎስ 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹-² እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።
³ በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፥ በዓይንህ ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም?
⁴ ወይም ወንድምህን፦ ከዓይንህ ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ እንዴትስ ትለዋለህ? እነሆም፥ በዓይንህ ምሰሶ አለ።
⁵ አንተ ግብዝ፥ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ፥ ከዚያም በኋላ ከወንድምህ ዓይን ጉድፉን ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ።

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

07 Jan, 17:09


https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

06 Jan, 17:49


🌺#ድንግል_ፈጣሪዋን_ወለደችው🌺


🌺ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ🌺


መልካም በአል


@raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

06 Jan, 17:49


https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

06 Jan, 16:00


++ ሰላም ለእናንተ ይሁን የክርስቶስ ቤተሰቦች የእመቤታችን የአስራት ልጆች እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለኢሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ በዓል ይሆንልን ዘንድ እመኛለሁ!! የእግዚአብሔር፣ ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት፣ የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃና ቃል-ኪዳናቸው ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን ይቆየን፡፡

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

03 Jan, 07:31


https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

02 Jan, 06:20


በንስሐ ሕይወት ለመኖር የምንሻ ከሆነ ለወደቅንበት ኃጢአት ምክንያት መደርደርና ለራሳችን ይቅርታን ለመስጠት መሞከር የለብንም። ኃጢአትን ከፈጸሙና ከሠሩ በኋላ ለኃጢአት ያበቃ ሌላ ምክንያት ማቅረብና በዚያም አንፃር ለመጽናናት መሞከር በራሱ ኃጢአት ነው። በዚህ አይነት ለኃጢአቱ ምክንያት እየደረደረ የሚጽናና ሰው ኃጢአትን እየለመደ ወደ ባሰ አዘቅት ከመውረድ በቀር ንስሐ ለመግባት አይችልም። ምንም ምክንያት ቢደረድር ኃጢአት ምን ጊዜም ኃጢአት ነውና። ለሠራነወ ኃጢአት የተለያዩ ምክንያቶችን በማበጀት ራሳችንን እያጽናናን ነፃ ለመሆን መጣር የለብንም ።

ስለ ሰሩት ኃጢአት ምክንያትን የደረደሩ አዳምና ሔዋንም ባቀረቡት ምክንያት ከመቀጣት አልዳኑም ። እግዚአብሔርም አዳም ስለ አቀረበው ምክንያት "የሚስትህን ቃል ሰምተኻልና ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዘዝኩህ ዛፍም በልተኻልና " በማለት ለኃጢአቱ የሚገባውን ቅጣት ሰጠው እንጂ አልተወውም። [ዘፍ3፥17] ይባስ ብሎ በእነርሱ ምክንያት በመጣው መርገም ቅጣቱ በትውልዳችን ሁሉ ሆነ እንደ እነርሱ ሁሉ እኛም ዘወትር ምክንያት በመደርደር ከኃጢአታችን የተነሣ ከሚመጣው ቅጣት ለማምለጥ የምንሞክር ሆንን ስለዚህ ንስሐ ለመግባት በጣም ስንቸገር እንታያለን ።

አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

28 Dec, 10:42


#ታህሳስ_19
እንኳን ለኅያሉ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን፥ አደረሳችሁ!!!

ራዕየ ማርያም

28 Dec, 10:40


“ስለዚህ፥ ሰማይና በውስጡ የምታድሩ ሆይ፥ ደስ ይበላችሁ፤ ለምድርና ለባሕር ወዮላቸው፥ ዲያብሎስ ጥቂት ዘመን እንዳለው አውቆ በታላቅ ቍጣ ወደ እናንተ ወርዶአልና።”
— ራእይ 12፥12

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

27 Dec, 10:38


https://youtu.be/zXtwpp0OomM?si=XO_RLGrASeJAMzII

ራዕየ ማርያም

18 Dec, 19:30


“እነሆ፥ እንደ ሌባ ሆኜ እመጣለሁ፤ ራቁቱን እንዳይሄድ እፍረቱንም እንዳያዩ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ ብፁዕ ነው።”
  — ራእይ 16፥15

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

18 Dec, 05:16


“ቀኒቱንና ሰዓቲቱን አታውቁምና እንግዲህ ንቁ።”
— ማቴዎስ 25፥13

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

17 Dec, 17:39


https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

17 Dec, 14:39


https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

17 Dec, 09:21


❖ ወዳጆቼ: ሆይ! ማፈር: የሚገባን: #ኃጢአት: ስንሰራ: እንጂ: #ንስሐ: ስንገባ አይደለም #ኃጢአት: ሕመም: ነው፤ ንስሐ: ደግሞ: #መድኃኒቱ: ነው፤ ከኃጢአት: ቀጥሎ: ህፍረት: አለ፤ #ከንስሐ: ቀጥሎ: ግን: #በጌታ: የኾነ: ደስታ: አለ፤ ነገር: ግን: ሰይጣን: ይህን: ቅደም: ተከተል: አዛብቶብን: 👉 በኃጢአት: ስንደሰት: በንስሐም: እናፍራለን" 😔👈

•• ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

https://t.me/raiye_mariyam

ራዕየ ማርያም

16 Dec, 09:52


#_የትምህርተ_ወንጌል_እና_የጸበል_አገልግሎት!

#_እሑድ_ታህሳስ_13_ጠዋት_2_ሰዓት

በመልአከ መንክራት በመምህር ግርማ ወንድሙ እና በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም!

ሼር በማድረግ መልእክቱን ለሌሎች አዳርሱ!

1,544

subscribers

148

photos

120

videos