Injibara University @injiuniversity Channel on Telegram

Injibara University

@injiuniversity


Injibara University (English)

Are you interested in staying updated with the latest news and events from Injibara University? Look no further than our Telegram channel '@injiuniversity'! Injibara University is a leading educational institution in Ethiopia, known for its commitment to academic excellence and innovation. Our channel provides followers with valuable information about upcoming seminars, workshops, and campus activities. It also serves as a platform for students, alumni, and faculty members to connect and engage in meaningful discussions. Whether you're a current student looking for important announcements or a prospective student interested in learning more about our programs, our channel has something for everyone. Join us today and be a part of the vibrant Injibara University community!

Injibara University

07 Feb, 11:25


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለፕሮፌሰር ጌትነት ታደለ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ የትምህርት ቤት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡
-----
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አየሁ ጓጉሳ ወረዳ ለሚገኘው ለፕ/ር ጌትነት ታደለ ትምህርት ቤት ከ500ሺህ ብር በላይ የሚያወጣ የቤ ሙከራ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡

ድጋፉን ያስረከቡት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ከተሰጠው ተልዕኮ አንዱ በሆነው ማህበረሰብ አገልግሎት አማካኝነት በአካባቢው በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ለሚገኙ መምህራን የተለያዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን ከመስጠት ባሻገር ተማሪዎች በተግባር የተደገፈ ትምህርት እንዲያገኙ ለማድረግ  የተለያዩ ቁሳቁሶችን በማሟላት ድጋፍ ሲያደርግ  መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር፣ ተመራማሪ እና በጎ ፈቃድ ሥራዎች ላይ በሚታወቁት በፕ/ር ጌትነት ታደለ አማካኝነት አዊ ብሄ/አስተዳደር አየሁ ጓጉሳ ወረዳ ለተሰራው ለአዘና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚሆን የፊዚክስ፣ የኬሚስትሪ እና ባዮሎጂ ትምህርቶች የተግባር ትምህርት ለመስጠት የሚያገለግሉ ከ500 ሺብር በላይ የሚገመቱ  የኬሚካል እና የቤተ ሙከራ  ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ዶ/ር ክንዴ አስረድተዋል፡፡

ድጋፉን የተረከቡት የአዘና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር  የሆኑት መ/ር አምሳሉ አስራ እና የትምህርት አጋርነት በኢትዮጵያ  የትምህርት ቤቱ አስተባባሪ መ/ር መዓዛው ደሳለኝ ናቸው፡፡

ጥር 30/2017 ዓ.ም፤ እንጀባራ ዩኒቨርሲቲ

Injibara University

06 Feb, 19:32


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ባህልን ከመጠበቅና ከማልማት አንጻር በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተገለጸ፡፡
--------------
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከለያቸውና በትምህርት ሚኒስቴር ከጸደቁት አራት የትኩረት መስኮች መካከል አንዱ የአገው ባህል ቋንቋ እና ታሪክ ሲሆን ባህልን ለማልማትና ለመጠበቅ በዩኒቨርሲቲው በኩል በርካታ ሥራዎች እየተከናኑ እንደሚገኙ የዩኒቨርሰቲው የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

ከእነዚህም መካከል በየዓመቱ የሚከበረውን የአገው ፈረሰኞች ማህበር በዓለም አቀፍ ደረጃ የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ ማስተዋወቅ ሲሆን አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ “የአገው ፈረስ ባህል” በሚል ብሄራዊ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ ማድረግ ተችሏል፡፡
በዚህ ዓመት በተከበረው 85ኛው የአገው ፈረሰኞች በዓል ዋዜማ በተዘጋጀው ሲምፖዚየም ላይ የአገው ፈረሰኞች በዓል በዓለም አቀፍ ቅርስነት በማስመዝገብ ሂደት ያለበትን ሁኔታ የሚያሳይ ዳሰሳ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) የቀረበ ሲሆን “አሱሪቴ” በተሰኘው ባህላዊ ትውን ጥበብ ላይ በመ/ር ብርሃኑ አሳየ እና በመ/ር ብርሃኑ ማተቤ እንዲሁም የባኩሳ ብሔራዊ ፓርክ ያለበትን ሁኔታ የሚያሳይ ጥናት ደግሞ በመ/ር እውነቱ ታዘበው (ዶ/ር) ቀርቧዋል።
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0GTaQNkyDVVFDFd2EUe1bNveGtatMy9G961fFQVnurthTohYEfCkN7AsGC9Uwqfxxl/?app=fbl

Injibara University

04 Feb, 20:16


የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል በታላቅ ድምቀት ተጠናቀቀ።

ጥር 27/2017 ዓ፣ም፤አዲስ አበባ

"ስፖርት ለአንድነት እና ለጋራ ዕድገት"በሚል መሪ ቃል አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከጥር 17-27 /2017 ዓ፣ም ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል ዛሬ ሲጠናቀቅ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ  በአጠቃላይ ውጤት 9ኛ ሆኖ አጠናቋል።

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በዚህ ፌስቲቫል በ4 የስፖርት አይነቶች ማለትም በእግር ኳስ፣በአትሌቲክስ፣በወርልድ ቴኳንዶ እና በባህላዊ ስፖርት ተሳትፎ በባህላዊ ስፖርት ቡብ ጨዋታ ዋንጫ እና ማዳሊያ በማግኘት አንጋፋ እና ነባር ዩኒቨርሲዎችን በመፎካካር በውድድሩ  ከ49 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች 9ኛ ሆኖ በማጠናቀቅ ስኬታማ ውድድር አሳልፏል።
ይህ ውጤት ከ4ኛ ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች ቀዳሚ ሲያደርገው በአማራ ክልል ከሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ከወልዲያ እና ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲዎች በቁጥር 3ተኛ ደረጃ ላይ ሆኖ አጠናቋል  ።
የዚህ ስፖርት ፌስቲቫል አጠቃላይ አሸናፊ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን የፀባይ ዋንጫ አዲግራት ዩንቨርሲቲ ወስዷል ።
በፌስቲቫሉ በባህላዊ ስፖርት ቡብ ጨዋታ ሴት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፣በቡብ ወንድ ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ፣በገበጣ ሴት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፣በገበጣ ወንድ ወልዲያ ዩንቨርሲቲ ፣ ፣በወርልድ ቴኳንዶ  ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ፣በእግር ኳስ ወሎ ዩንቨርሲቲ፣በቼዝ ሴት አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣በቼዝ ወንድ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣አትሌቲክስ ወንድ ሀረሚያ ዩኒቨርሲቲ እና አትሌቲክስ ሴት የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ  የዋንጫ አሸናፊ ሆነዋል።


ያለህን ዕምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!

Injibara University

20 Jan, 06:44


የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) የተፈተናችሁ ተማሪዎች በዚህ ሊንክ ውጤታችሁን ማየት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። https://result.ethernet.edu.et

Injibara University

18 Jan, 14:40


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

መልካም የከተራ በዓል!
ጥር 10/2017 ዓ.ም

Injibara University

16 Jan, 16:24


ማስታወቂያ

Injibara University

15 Jan, 15:31


የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና(NGAT) ተሰጠ፡፡
-----
ጥር 7/2017 ዓ.ም፡እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት የተሰጠው ሀገር አቀፍ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና(NGAT) ተጠናቋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የድህረ-ምረቃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር እሱባለው ስንቴ(ዶ/ር) በዛሬው ዕለት በተሰጠው የድህረ
ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና( NGAT) በዩኒቨርሲቲው 219 ተፈታኞች ፈተና መውሰዳቸውን ጠቅሰው ከእነዚህ ውስጥ 28ቱ ሴቶች ሲሆኑ ፈተናው በተያዘለት ሰዓት እና ጊዜ ያለምንም ችግር በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ገልጸዋል።

Injibara University

10 Jan, 19:10


በድጋሜ የወጣ ማስታወቂያ
----
ለርቀት ትምህርት የምዝገባ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን ስለማሳወቅ

Injibara University

10 Jan, 06:47


https://youtu.be/Ap8qqp53_Tw?si=h0qN2f3ysIecoWTN

Injibara University

07 Jan, 10:59


የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን ከተማሪዎች ጋር አክብረዋል።

በድጋሜ መልካም የገና በዓል!

Injibara University

06 Jan, 14:59


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

በዓሉ የሰላምና የፍቅር የአንድነት ይሁንልን
መልካም የገና በዓል!

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 2017 ዓ.ም

Injibara University

06 Jan, 14:37


ለ National Graduate Admission Test (NGAT) አመልካቾች በሙሉ፦
---------
የመግቢያ ፈተና የሚሰጠዉ ጥር 7/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 - 6:30 መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
ስለሆነም ተፈታኞች ከፈተና ሰዓቱ ቀደም ብላችሁ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግቢ በመገኘት የፈተና Username and Password መዉሰድ እና የመፈተኛ ክፍላችሁን ማወቅ ይጠበቅባችኋል፡፡

ማሳሰቢያ፡ ለፈተና ስትመጡ ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝን አትርሱ፡፡

ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

Injibara University

06 Jan, 13:35


የእንጅባራ ዩኒቨርሰቲ ጆርናሉን ዲጅታላይዝድ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
-----
ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲን Injibara Journal of Social Science and Business (JJSSB) የምርምር መጽሔት ዲጂታላይዝ ለማድረግ Open Journal System (OJS) የተባለ ሶፍት ዌር በተቋሙ ባለሙያዎች እንደሚገኝም
ተገልጿል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ባሻግር አንዱ ዓላማ ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት መስጠት መሆኑን ጠቅሰው እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ የምርምር እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር ክንዴ አያይዘውም ከዚህ በፊት ዩኒቨርሲቲው የምርምር ስራዎችን Injibara Journal of Social Science and Business (JJSSB) በማቋቋም የመጀመሪያ ጥራዝ መታተሙንና ይህን ወደ ዲጅታል ለመቀየር እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸው ይህን ተግባራዊ ለማድረግም በኢዲቶሪያል ውይይት እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምር፣ ህትመት፣ሥነ-ምግባርና ስርጸት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተሰራ ቢተው (ዶ/ር) በበኩላቸው Injibara Journal of Social Science and Business (JJSSB) በዓመት ሁለት ጊዜ እንደሚታተም ገልጸው የመጀመሪያው ዕትም ሀምሌ /2016 ዓ.ም መታተሙን ተናግረዋል፡፡
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0336vtN9cLHQ6jTvTziKqfLWm3pXGEYF44g8HvsvmnhzZADRS86SfYDuhoxe3PsaFEl/?app=fbl

Injibara University

05 Jan, 18:07


የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቱሪዝም ሳምንት በታላቅ ድምቀት ተጠናቀቀ፡፡
--------//------
ታህሳስ 27/2017 ዓ.ም ፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

"ቱሪዝም ለሰላም እና ብዝሃነት” በሚል መሪ ቃል ለተከታታይ አምስት ቀናት ሲከበር የነበረው የቱሪዝም ሳምንት ዛሬ በደማቅ ሁኔታ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የባህል አምባሳደር በመምረጥ ተጠናቋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ማጠናቀቂያ ላይ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት አዕምሮ ታደሰ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው መርሃግብሩ ከታህሳስ 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ በል ልዩ ሁነቶች ሲከበር መቆየቱን አስታውሰው የቱሪዝም ሳምንት በስርዓተ ትምህርቱ የተካተተ በመሆኑ በቀጣይ ከዚህ በተሻለ ሁኔታ እንደሚከበር ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር አዕምሮ አያይዘውም ይህ መርሃግብር ስለ ቱሪዝም ግንዛቤ የተፈጠረበት፣ ተማሪዎች ልዩልዩ ችሎታቸውን እና ተሰጥኦቸውን ያሳዩበት እና መርሃ ግብሩ ግቡን ያሳከበት መሆኑንም ገልጸው መርሃግብሩ ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ለነበራቸው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid02jppNKEXFixWSxpz2xj7LXpdjkcMKfJzH24S6Ag3JyiLe8UdbE9BNLb6LYsrGKeszl/?app=fbl

Injibara University

04 Jan, 12:35


የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳተፉ፡፡

ታህሳስ 26/2017ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው የእንስሳት መኖ ሳር አጨዳ በጎ ፈቃድ ተሳትፈዋል፡፡
በበጎ ፈቃድ ሥራው የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ተማሪዎች የነገ ሀገር ተረካቢዎች በመሆናችሁ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን መስጠታችሁ ለዩኒቨርሲቲው ያላችሁን ቤተሰባዊነት ያሳችሁበት ተሳትፎ በመሆኑ ልትመሰገኑ ይገባል ብለዋል፡፡ ከዚህ በፊት የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ መምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም የአውት ሶርስ ሠራተኞች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መስጠታቸውን አስታውሰው ተማሪዎችም የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት በመሆናቸው በራሳቸው ተነሣሽነት በዚህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመሳተፋቸው አመስግነዋል፡፡
የአስተዳደር እና ልማት ም/ፕሬዝዳንት ወሀቤ ብርሃን(ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ለመማር ማስተማር እና ምርምር የሚያገለግሉ ዘመናዊ የከብት እርባታ እንዳለ አስታውሰው የታጨደው ሳር ለወተት ላሞች መኖ የሚያገለግል በመሆኑ ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰጭ ተማሪዎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡፡
በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱን የተማሪዎች ህብረት አስተባባሪነት የተሰጠ ነው።

Injibara University

04 Jan, 12:30


የቱሪዝም ሳምንትን በማስመልከት ጥናታዊ ጽሑፍ እና የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡

ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቱሪዝም ሳምንት 3ኛ ቀን "Analyzing the Cultural and Socio-Economic Implications of Awigni Music Lyrics in Awi Zone," Ethiopia የሚል ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) ቱሪዝም ለሀገራችን የሚሠጠው ጥቅም ከፍተኛ በመሆኑ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ያለበት አካባቢ የቱሪዝም ጸጋ ያለበት እና የቱሪዝም ኮሪደር በመሆኑ ጸጋውን ለመጠቀም የሚያስችል ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የቱሪዝም ኢንዲስትሪውን ለማሳዳግ ዩኒቨርሲቲው ለአካባቢው ማህበረሰብ የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት እና በምርምር በማገዝ ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰው ይህ የቱሪዝም ሳምንት መከበሩ ተማሪዎች እና ማህበረሰቡ ስለ ቱሪዝም ግንዛቤ እንዲኖራቸው የሚያግዝ ነው ብለዋል፡፡ ኮንፈረንሱ መዘጋጀቱ ወቅቱን የጠበቀ እና ፋይዳው ከፍ ያለ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid03421CfhrQ7WkXqM7eqyAC3v7Cq3TYETdsW8Y15yfGkyxt6uQSihr6XZK7baGf56Qzl/?app=fbl

Injibara University

02 Jan, 13:56


ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች የካይዘን አመራር ስልጠና ተሰጠ፡፡
----------
ታህሳስ 24/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክና አስተዳደር ሰራተኞች በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ እና በተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈፃሚ ትብብር የካይዘን አመራር ፍልስፍና ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈፃሚና የስልጠናው አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ የሽመቤት ጌታሁን ስልጠናው የተዘጋጀው ከለውጥ መሳሪያዎች ውስጥ አንዱ በሆነው ካይዘን ጽንስ ሃሳብ ላይ ሰራተኛውንና መካከለኛ አመራሩን ስልጠና በመስጠት ተግባራትን አቀናጅተን በመፈፀም የለውጥን ቀጣይነትና ውጤታማነት ማረጋገጥ የአሰራር ስርዓታችንና አመለካከታችን ለመቀየር ይረዳናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ለውጥ ማለት ከተለመደ አሰራር ወደ አዲስ አሰራር ከመሸጋገር በፊት ከአሮጌው በመላቀቅ አዲሱን በመላመድ መካከል ያለ ሁኔታ መሆኑንና የለውጥ መሳሪያዎች ባላቸው ፋይዳ ወጥ የሆነ ተቋማዊ አፈፃፀም እንዲኖር ለማስቻል ስልጠና መሰጠቱን አስረድተዋል፡፡
ስልጠናው የተሰጠው የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ዲን በሆኑት በይልቃል አንዷለም (ዶ/ር) እና በመምህር ታደሰ አማረ ሲሆን ለሁለት ተከታታይ ቀናት ተሰጥቶ በዛሬው እለት ተጠናቋል፡፡

Injibara University

27 Dec, 07:15


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የአፈፃፀም ስምምነት ውል (performance contracting agreement) ተፈራረመ።

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት፣ የምርምር እና የማህበረሰብ አግልግሎትን ተደራሽነት፣ ጥራት እና አግባብነትን መሠረት ባደረጉ ቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች (KPIs) ላይ ያተኮረ የአፈጻጸም ስምምነት ውል በዩኒቨርሲተው ፕሬዝደንት በጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) አማካኝነት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ተፈራርሟል።

ዶ/ር ጋርዳቸው እንደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ብቃትና ጥራት ያለው ዜጋ ማፍራት፣ችግር ፈቺ ምርምር እና ማህበረሰብ አግልግሎት መስጠት የዩኒቨርሲቲው ተልዕኮ መሆኑንን ጠቅሰው የስምምነት ውሉ መሰረት ያደረገባቸው ቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች ቀደም ሲል በዩኒቨርሲቲው ተግባራዊ ሲደረጉ እንደቆዩ ገልጸዋል። በቀጣይነት በገቡት ስምምነት መሠረት ስራዎችን በየደረጃው ላሉ ስራ ክፍሎች እና ሠራተኞች በማውረድና ጠንክሮ በመስራት ከፍተኛ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚሠራ ጨምረው ተናግረዋል።
የቁልፍ ስራዎች አፈጻጸም ውሉ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ መለኪያዎች ላይ ያተኮረ እድገት እንዲኖራቸው እንደሚያስችል የተገለጸ ሲሆን ስምምነቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የክትትልና ግምገማ ስርዓት እንዲኖርና ዩኒቨርስቲዎች በተልዕኳቸው ላይ አትኩረው እንዲሰሩ እንደሚደረግ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ተገልጿል።
ስምምነቱ የተፈረመው ትምህርት ሚኒስቴር ከሁሉም የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የአፈጻጸም ስምምነት ውል በተፈራረመት ወቅት ሲሆን የትምህርት ሚኒስትሩን በመወከል የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲን በመወከል ደግሞ ዶ/ር ጋርዳቸው ወርቁ ፈርመዋል።

Injibara University

26 Dec, 17:02


የድኅረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ
-----
ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች (NGAT) የ2017 ዓ.ም ትምህርት ዘመን አጋማሽ የመግቢያ ፈተና ከጥር 7-9/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ቀደም ሲል መግለጻችን ይታወቃል።

ፈተናው ለአዲስ ድኅረ ምረቃ (የሁለተኛ እና የሦስተኛ ዲግሪ) አመልካቾች በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል። ፈተናውን ለመውሰድ ከታች በተቀመጠው ሊንክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

ለምዝገባ ይህን ሊንክ ተጠቀሙ።
https://ngat.ethernet.edu.et/login

Injibara University

26 Dec, 06:44


Dear All injibara University community

Please use the following registration link to sign up for the 5 Million Ethiopian Coders program: https://ethiocoders.et/. You can register using your institutional email, after which you'll be able to access and take courses on the platform.

Injibara University

25 Dec, 13:38


የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚያግዝ የምህንድስና ቤተ-ሙከራ መደራጀቱ ተገለጸ፡፡
------
ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

ዩኒቨርሲቲው የምህድስና ቤተ-ሙከራ ለማደራጀት Sediment Transport Apparatus, Closed- Pipe apparatus, Reynolds Apparatus, Overflow apparatus, Open Channel Flume and Quadrant የተሰኙ የቤተ ሙከራ ማሸኖችን ከ5 ሚሊዮን ብር ላይ ወጭ በማድረግ አደራጅቷል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት አዕምሮ ታደሰ (ዶ/ር) ዪኒቨርሲቲው የተምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የምህንድስና ትምህርትን ቤተሙከራ በማደራጀት በተግባር የታገዘ ትምህርት ለመስጠት ከፍተኛ በጀት በመመደብ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በዛሬው ዕለት ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገዙ 7 የሀይድሮሊክ ምህንድስና ቤተ-ሙከራ ዕቃዎች መደራጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው የ4ኛ ትውልድ ዩኒቨርሲቲ ቢሆንም የተለያዩ የቤተ ሙከራ ማሽኖችን በማሟላት ተማሪዎች ሌላ ቦታ ሳይሄዱ የተግባር ትምህርታቸውን እዚሁ እንዲማሩ በማድረግ ውጤታማ እና ተወዳደሪ የተማረ ሀይል ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡

https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid02CGT2yzZzf2VyMwWamL6jK5vvYL88L67PzDmzhWuP6RAHccF4P5rPQnc28zVb6kwVl/?app=fbl

Injibara University

05 Dec, 06:25


የሀዘን መግለጫ
------
ተማሪ ሌሊሳ ጌታቸው በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
የ3ኛ አመት በ lifelong learning and community development ትምህርት ክፍል በመማር የነበረ ሲሆን ባጋጠመው ህመም ምክንያት ወደ ቤተሰቦቹ ሄዶ ህክምና ቢያደርግም በትናንትናው እለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በተማሪ ሌሊሳ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ይመኛል።

ኅዳር 26/2017 ዓ.ም

Injibara University

29 Nov, 12:16


የጫራታ ማስታወቂያ

Injibara University

25 Nov, 16:04


የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ

Injibara University

22 Nov, 18:51


‹‹ህጻናት የሚሉት አላቸው እናዳምጣቸው›› በሚል መሪ ቃል ዓለምአቀፍ የህጻናት ቀን ተከበረ፡፡
---------
ኅዳር 13/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

በዓሉ በዓለምአቀፍ ደረጃ ለ35ኛ ጊዜ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ ጊዜ እንዲሁም በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለ3ኛ ጊዜ በልዩልዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል።

በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) ህጻናት የወላጅ ፍቅርና የተሻለ እንክብካቤ በቅርበት እንዲያገኙ በማድረግ ጠንካራና ጤነኛ ሆነው እንዲያድጉ ትኩረት መደረግ አለበት በማለት የማዕከሉ መገንባትም የብዙ እናቶችን ችግር የሚቀርፍ መሆኑን ተናግረዋል። አያይዘውም የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህጻናት ማቆያ ማዕከል በኢትዮጵያ ከሚገኙ ዩኒቨርሲተዎች ውስጥ ካሉ የህጻናት ማቆያ ማዕከላት መካከል በጥራቱ የተሻለ እንደሆነ ጠቅሰው በቀጣይ የተሻለ መዋዕለ ህጻናትና ት/ቤት ለመገንባት ዩኒቨርሲቲው ዕቅድ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ባንቻለም ካሴ በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲው ህጻናት ማቆያ ማዕከል ሥራ ከጀመረ አንስቶ በዓሉ ለ3ኛ ጊዜ መከበሩን አውስተው ማዕከሉ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2015 ዓ.ም 42 ህጻናትን በመቀበል አገልግሎት መስጠት መጀመሩን እና በዘተያዘው በ2017 ዘመን ደግሞ 83 ህጻናት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0ij8ANfJyDs9sJdPSGeHPrQ8yA4qq3DBQkZMy2BfuiDr55amH1jg2K5qR63XspjtXl/?app=fbl

Injibara University

22 Nov, 18:50


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የድንች እና የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት በማከናወን ላይ መሆኑን አስታወቀ።
ህዳር 11/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የምርምር ካውንስል አባላት የተሳተፉበት የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት ማሳ እና የድንች ምርጥ ዘር ማጎንቆያ ክፍል ጉብኝት ተከናውኗል። ዩኒቨርሲቲው ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ በክረምት እያከናወነ ከሚገባቸው ተግባራት መካከል ‹‹ደንደአ›› የተሰኘ ስንዴ ከምርምር ድርጅት መስራች(C1) በመረከብ በ6 ሄክታር ላይ እያባዛ እንዳለና ሰብሉም በጥሩ ይዞታ ላይ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው የእርሻ ፕሮጀክቶች አስተባሪና የዘር ብዜት መሪ አማረ አለምነው(ዶ/ር) በማሳ ጉብኝቱ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ለአካባቢው ተስማሚና የተሻለ ምርት የሚሰጥ ‹‹በለጠ ›› የተሰኘ ድንች ዘር በ1.5 ሄክታር ላይ ለምቶ በማጎንቆያ ክፍል በርብራብ ለዘር ብዜት የተቀመጠን ድንችም አመራሩ እንዲገበኘው ተደርጓል፡፡
በጉብኝት ፕሮግራም ላይ የተገኙት የእንጅባራ ዩንቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጋርዳቸው ወርቁ በተመራማሪዎች እየተሰሩ ያሉት የምርምር ስራዎች እጅግ ተስፋ ሰጪ እና አበረታች መሆናቸውን ገልጸው ለተመራማሪዎች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ፕሬዚዳንቱ የገበሬው የምርጥ ዘር ፍላጎት በዩኒቨርሲቲው ብቻ እንደማይሟላ ገለጸው በሰፊው የምርጥ ዘር ብዜት ለማከናወን ከግብርና ምርምር፣ከሞዴል እርሶ አደሮች እና ከግብርና ጽ/ቤቶች ጋር በቅንጀት መስራት እንደሚያስፈልግ በጉብኝት ማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ አሳስበዋል።

Injibara University

22 Nov, 18:49


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቱሪዝም ዘርፍ የስልጠና እና የምርምር የትኩረት መስኩ መሆነን አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው ከአማራ ክልል እውቅና የተሰጠውን የቱሪዝምና ሆቴል ማሰልጠኛና የምዘና ማዕከል ( Tourism and Hotel management Training and Competency Centre) መርቆ ስራ አስጀምሯል። በምረቃ ፕሮግራሙ የተገኙት የእንጅባራ ዩንቨርስቲ ፕሬዚዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት (Tourism and Entrepreneurship Development) የቱሪዝም እና ስራ ፈጠራ ዘርፎች ከዩኒቨርሲቲው ዋና የትኩረት መስኮች አንዱ መሆኑን ጠቅሰው እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የሆቴል እና ቱሪዝም ኢንዱስትሪን በማስተዋቀቅ፣ በማዘመን እና በማሳደግ አካባቢውን፣ ክልሉን እና አገሪቱን ከዘርፉ ተጠቃሚ ለማድረግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል ። በአገራችን ቱሪዝም ከአምስቱ ቁልፍ የኢኮኖሚ እድገት ምሰሶዎች አንዱ ሆኖ መለየቱን፣ በቀጠናው ሰፊ እና ውብ ሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ የቱሪስት መስህቦች ያሉት እንዲሁም እንጅባራም የህዳሴ ግድብ መግቢያ በር (Gateway) መሆኗን የገለጹት ፕሬዚዳንቱ የእንጅባራ ዩንቨርሲቲ ይህንን ከግምት በማስገባት ቱሪዝም አንዱ የትኩረት መስኩ አድርጎ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid036TxFx1BmyZLP2s5HL7gP1GBT3Za5LaVSg6C9Wk1LGGKFKTeCPTTmNJkgTc3R1Vczl/?app=fbl

Injibara University

11 Nov, 20:30


የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ኔትወርክ እና ሲስተም ኦፕቲማይዜሽን ፕሮጀከት የርክክብ ስነ ስርዓት ተደረገ፡፡

ዩኒቨርሲቲውን በአይሲቲ ዘርፍ ደረጃውን ከፍ ለማድረግ በ37 ሚሊዮን ብር ወጭ በዋሊያ ቴክኖሎጂስ ሲሰራ የነበረው ፕሮጀክት ተጠናቆ ርክክብ ተደርጓል፡፡

በርክክቡ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው መማር ማስተማሩን ከቴክኖሎጂ ጋር በማገናኘት በተለይም ኢ-ለርኒንግን ለመጀምር ከፍተኛ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፣ በዛሬው ዕለትም ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲሰራ የነበረውን ኔትወርክ እና ሲስተም ኦፕቲማይዜሽን ፕሮጀክት ተጠናቆ ከዋሊያ ቴክኖሎጂስ መረከቡን ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር ጋርዳቸው አያይዘውም ፕሮጀክቱ ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ መጨረሱን ጠቅሰው ፕሮጀክቱን በተፈለገው ጥራት ሰርተው በማስረከባቸው ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የዋሊያ ቴክኖሎጂስ ፕሮጀክት ዋና ማናጀር ትግስት አምሳሉ እንደተናገሩት ዋልያ ቴክኖሎጂስ ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ጋር ከተዋዋለው ኔትወርክ እና ሲስተም ኦፕቲማይዜሽን ፕሮጀክት ሰርቶ ከማስረከብ በተጨማሪ የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ስልጠናዎችን በማቻቸት ለተቋሙ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠቱን ገልጸው በቆይታቸው ዩኒቨርሲቲው ላደረገላቸው መልካም ትብብር አመስግነዋል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአይሲቲ ስራ አስፈጻሚ አቶ አዱኛ አለበል እንደገለጹት ፕሮጀክቱ ከዚህ በፊት የነበረውን አጠቃላይ የኔትወርክ እና ሲስተም የሚያዘምን፣ ተደራሽነቱን እና ደህንነቱ እንዲጠበቅ የሚያደርግ በመሆኑ ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣የአይሲቲ ባለሙያዎች እና ዋሊያ ቴክኖሎጂስን አመስነዋል፡፡

#ጥቅምት 2/2017ዓ.ም፣እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

Injibara University

08 Nov, 13:47


የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች በወቅታዊ የሰላም ጉዳይ ተወያዩ፡፡
በውይይቱ  የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር እና የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም   ዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ  እና አስተዳደር  ሰራተኞች  ተገኝተዋል፡፡

በውይይቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር)  አጃንዳው በሰላም እና ጸጥታ ዙሪያ ውይይት ለማድረግ መሆኑን ገልጸው  ሰላም እጅግ ውድ እና ለሁሉም ነገር መሰረት ነው ብለዋል።

ዶ/ር ጋርዳቸው አያይዘውም የዩኒቨርሲቲው ምሁራን በክልላችን እየተስተዋለ ባለው የሰላም እና ጸጥታ  ችግሮች  ዙሪያ የመፍትሄ እና አሻጋሪ ሀሳቦችን እንዲያመነጩ እና ሀሳባቸውን እንዲሰጡ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ገልጸው ሁሉም የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች እና ምሁራን የሰላም ዘብ እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡

የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳደሪ እና የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባል አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው በመክፈቻ ንግግራቸው እንተናገሩት የዩኒቨርሲቲ ምሁራን የተለያዩ  አካላት ስብጥር መሆኑን ጠቅሰው ውይይቱ በዋናነነት ከሰላምና ጸጥታ አኳያ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ሚና ፣ከሰላም ዕጦት መውጫ መንገድ መወያየት እና አማራጭ የመፍትሄ ሀሳቦችን ለማሰባሰብ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በውይይቱ የተገኙት ኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት የ302ኛ ኮር ም/አዛዥ ኮሎኔል ሰጤ አራጌ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰላምን ለማስጠበቅ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ሰላም እና መረጋጋት እንዲመጣ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር ከፍተኛ ሃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
በውይይቱ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብ እና አስተያየቶች ተነስተው በሚመለከታቸው አካት ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ጥቅምት 29/2017 ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

Injibara University

08 Nov, 05:27


#ማስታወቂያ
#ለትምህርት_ፈላጊዎች

Injibara University

07 Nov, 19:16


ለአካዳሚክ እና አስተዳደር ሴት ሠራተኞች የጡት ካንሰር የግንዛቤ ፈጠራ ሥልጠና ተሰጠ።

ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለአካዳሚክ እና አስተዳደር ሴት ሰራተኞች ስለ ጡት ካንሰር ምንነት፣አጋላጭ ሁኔታዎች እና ቅድመ መከላከያ መንገዶች ላይ ትኩረት ያደረገ የግንዛቤ ፈጠራ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

በመርሃ ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) የስልጠናው ዓላማ ብዙ ሴት እህቶቻችንና እናቶቻችንን እየነጠቀ ያለውን የጡት ካንሰር በተመለከተ የተሻለ ግንዛቤ መፍጠር መሆኑን ገልጸዋል፡፡፡

ፕሬዘዳንቱ አያይዘውም "በዩኒቨርሲቲው ሴት ሰራተኞች ላይ መስራት ለዩኒቨርሲቲው ዕድገት እና ስኬት የራሱ ጉልህ አስተዋጽኦ አለው" ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው መሰል ስልጠናዎች እና የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች ላይ በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ባንቻለም ካሴ "በሴቶች ዙሪያ የተለያዩ ስልጠኛዎችን እና ግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን መስራት ሴቶች በስራቸው ብቁ እንዲሆኑ ያስችላል" ብለዋል።

ሥልጠናውን የእንጅባራ ዩኒቨርሰቲ መምህር እና ጠቅላላ ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት ዶ/ር ዜናው አማረ እና የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የሚድዋይፈሪ መምህርት እና CPD አስተባበሪ የውብምርት ሻረው(ረዳት ፕሮፌሰር) ሰጥተዋል።

ጥቅምት 28/2017 ዓ፣ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

Injibara University

06 Nov, 18:44


#የሀዘን_መግለጫ
ወ/ሮ የሽሀረግ ይስማ ላለፉት ስድስት ዓመታት በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በጽዳት ሙያ ላይ ሲያገለግሉ ቆይተው ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ዩኒቨርሲቲው በወ/ሮ የሽሀረግ ይስማ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይመኛል።

Injibara University

02 Nov, 07:11


https://youtu.be/L2BAmZ2BwHY?si=sdIhEB_RRKbDhpyF

Injibara University

01 Nov, 11:50


https://youtu.be/KoDvQHvXGhg? Injibara University Main Website

https://www.inu.edu.et

Child websites of its colleges, institutes and schools.

1. College of Agriculture
https://cafcs.inu.edu.et
2. College of Natural and Computational Science
https://cncs.inu.edu.et
3. College of Business and Economics
https://cbe.inu.edu.et
4. College of Engineering and Technology
https://cet.inu.edu.et
5. College of Medicine and Health Science
https://cmhs.inu.edu.et
6. College of Social Science and Humanities
https://cssh.inu.edu.et
7. College of Education and Behavioral Sciebces
https://cebs.inu.edu.et
8. School of Law
https://sl.inu.edu.et
9. ICT Office
https://ict.inu.edu.et
10. Institute of Agaw Studies
https://ias.inu.edu.et

Injibara University

01 Nov, 06:28


የሀዘን መግለጫ
----
ወ/ሮ የንጉስነሽ ብርሃን ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በጽዳት ሙያ ላይ ሲያገለግሉ ቆይተው ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ዩኒቨርሲቲው በወ/ሮ የንጉስነሽ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይመኛል።

Injibara University

01 Nov, 05:13


Injibara University Main Website

https://www.inu.edu.et

Child websites of its colleges, institutes and schools.

1. College of Agriculture
https://cafcs.inu.edu.et
2. College of Natural and Computational Science
https://cncs.inu.edu.et
3. College of Business and Economics
https://cbe.inu.edu.et
4. College of Engineering and Technology
https://cet.inu.edu.et
5. College of Medicine and Health Science
https://cmhs.inu.edu.et
6. College of Social Science and Humanities
https://cssh.inu.edu.et
7. College of Education and Behavioral Sciebces
https://cebs.inu.edu.et
8. School of Law
https://sl.inu.edu.et
9. ICT Office
https://ict.inu.edu.et
10. Institute of Agaw Studies
https://ias.inu.edu.et

Injibara University

24 Oct, 13:00


የ2017 ዓ.ም አዲስ መደበኛ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲ ምደባን ለማየት ከታች የተቀመጡትን ሊንኮች ይጠቀሙ!
ድረ-ገጽ https://placement.ethernet.edu.et
ቴሌግራም
https://t.me/moestudentbot

ትምህርት ሚኒስቴር

Injibara University

18 Oct, 18:43


እንጅባራ ዩኒቨርስቲ ቀድም ሲል ለጥቅምት 14-15/2017 ዓ/ም የምዝገባ ጥሪ ማስተላለፍ ይታወቃል። በ2017 ዓ/ም አዲስ የተመደባችሁ እና በ2016 ዓ/ም የሬሜዲያል ተማሪዎች የነበራችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን እናስታውቃለን።
ማሳሰቢያ። የሌሎቻችሁ ጥሪ እንደተጠበቀ መሆነን እናስታውቃለ

Injibara University

16 Oct, 12:59


#ማስታወቂያ
------
የድኅረ-ምረቃ ትምህርት የምዝገባ ቀን የተራዘመ መሆኑን ስለማሳወቅ!

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የ2ኛ(በመደበኛ እና ተከታታይ ት/ት) እና 3ኛ ዲግሪ ትምህርት ፕሮግራሞች አመልካቾችን ተቀብሎ ለማስተማር ቀደም ሲል ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል።

ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ምዝገባ ማካሄድ ላልቻላችሁ የምዝገባ ቀን ከጥቅምት 6 እስከ ጥቅምት 29/2017 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ በመሆኑ በተጠቀሱት ቀናት በማመልከት መማር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

በዚህሊንክ በመግባት በኦንላይን መመዝገብ ትችላላችሁ!
https://application.inu.edu.et/
ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

Injibara University

11 Oct, 13:52


የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
------
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ መሠረት ከታች ሥማችሁ የተዘረዘረ አመልካቾች በተጠቀሰው ቀን በዩኒቨርቲው ግቢ ውስጥ በመገኘት ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳውቃለን።
የፈተና ቀናትም:-
1. ለጤና ሳይንስ ኮሌጅ አመልካቾች ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም
2.ለተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም
3. ለምህንድስናና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ አመልካቾች ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም መሆኑን እንገልጻለን።

Injibara University

10 Oct, 12:47


ማስታወቂያ
-----
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በሪሜዲያል ፕሮግራም በኤክስቴንሽን መርሃ-ግብር ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለሪሜዲያል ትምህርት መግቢያ ውጤት ያላችሁ ተማሪዎች በሙሉ የምዝገባ ጊዜ ከጥቅምት 01 - 15 /2017 ዓ.ም ድረስ ስለሆነ ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ባሉት ቀናት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የትምህርቱ አጠቃላይ ክፍያ፡-
1. ለተፈጥሮ ሳይንስ የመመዝገቢያ ክፍያን ጨምሮ 2,350 ብር
2. ለማኅበራዊ ሳይንስ የመመዝገቢያ ክፍያን ጨምሮ 1,950 ብር
አመልካቾች በዩኒቨርሲቲው የንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000258464428 አጠቃላይ ክፍያ በመክፈል ዋናውን የባንክ ደረሰኝ ከ 2 ፎቶ ኮፒ ጋር በመያዝ ሬጅስትራር ጽ/ቤት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የተከታታይና ርቀት ትምህርት ዳይሬክቶሬት

Injibara University

04 Oct, 14:31


ማስታወቂያ፦
----
የመግቢያ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን ስለማሳወቅ
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 4ኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች የምዝገባ ፕሮግራም መስከረም 29 እና30/2017 ዓ.ም መሆኑ ቀደም ሲል ተገልጾ የነበረ ቢሆንም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ባለመጠናቀቃቸው የምዝገባ ጊዜ ጥቅምት 14 እና 15/2017 ዓ.ም መሆኑን እናሳውቃለን።

Injibara University

01 Oct, 13:03


በስርዓተ ትምህርት ዝግጅት እና ትምህርት ምዘና ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ፡፡
-----
ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን በስርዓተ-ትምህርት ዝግጅት እና በትምህርት ምዘና ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሠጥቷል፡፡

ስልጠናውን የከፈተቱት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራት ማረጋገጫ እና ማጎልበቻ ኦዲቲንግ ስራ አስፈጻሚ ዓለም አምሳሉ( ዶ/ር) የስልጠናው ዓላማ መምህራን በትምህርት ምዘና እና በመማሪያ ግብዓቶች ዝግጅት ዙሪያ የተሻለ ግንዛቤን እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

ስልጠናውን የሰጡት የዩኒቨርሲቲው የመምህራን ትምህርትና ስርዓተ ትምህርት ጥናት ትምህርት ክፍል መምህርና የከፍተኛ ዲፕሎማ ስልጠና አስተባበሪ የሆኑት ቱጂ ኢሬሶ(ረዳት ፕሮፌሰር) እና የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ሙሉዓለም አለማየሁ ናቸው፡፡

ስልጠናው በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከትምህርት ጥራት ማረጋገጫ እና ማጎልበቻ ኦዲንቲንግ ስራ አስፈጻሚ በጋራ የተዘጋጀ ሲሆን ለሁለት ቀናት ሲሰጥ ቆይቶ በዛሬው እለት ተጠናቋል፡፡

መስከረም 21/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

Injibara University

26 Sep, 12:14


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

መልካም በዓል
ድሩፃ!
መስከረም 16/2017 ዓ.ም

Injibara University

26 Sep, 10:52


የፈተና ውጤት ማሳወቂያ፦
-----
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው የረዳት ሌክቸረር ማስታወቂያ ተወዳድራችሁ ያለፋችሁ ስማችሁ ከዚህ በታች የተገለጸ መሆኑን እያሳወቅን ማስታወቂያው ከወጣበት ከዛሬ ጀምሮ የሥራ መልቀቂያ/የሥራ አጥ ማስረጃ በመያዝ እስከ መስከረም 21/2017 ዓ.ም ድረስ በዩኒቨርሲቲው የብቃትና ሰው ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ እንድታመለክቱ እናሳስባለን።

መስከረም 16/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ