ምንዳርአለው ፍልስፍና📚

@mndarallewbooks


አዳዲስ ሀሳቦች፣ መጽሀፍት፣ ነባር እሴቶችና ንጻሬዎች የሚቀርቡበት ነው።

ምንዳርአለው ፍልስፍና📚

17 Oct, 19:23


ባለቤትና ፖሊሲ የሌለው ኢኮኖሚ ፣ ቀን የኑሮ ውድነትና የዋጋ ግሽበት ሲከረትፉት የሚውሉት አንሶ ፣ ማታ ሙስና ሲያሻምደው ያድራል

ምንዳርአለው ፍልስፍና📚

09 Sep, 07:39


ከገበያ ለረዥም ግዜ ጠፍታ የነበረችው "ራስን መሠለል" በድጋሜ ታትማ በሁሉም መፃህፍት መደብሮች አሁን  ትገኛለች፡፡

ምንዳርአለው ፍልስፍና📚

26 Aug, 20:21


ከገበያ ለረዥም ግዜ ጠፍታ የነበረችው "ራስን መሠለል" በድጋሜ ታትማ በሁሉም መፃህፍት መደብሮች አሁን ትገኛለች፡፡

ምንዳርአለው ፍልስፍና📚

23 Aug, 18:18


የራስን መሰለል ዋና አከፋፋይ አንዋር መፃህፍት መደብር ፣ ትራኮን ህንፃ 1ኛ ፎቅ ይገኛል፡፡ ስልክ ፦0930013422

ምንዳርአለው ፍልስፍና📚

21 Aug, 12:17


ከገበያ ለረዥም ግዜ ጠፍታ የነበረችው "ራስን መሠለል" በድጋሜ ታትማ በሁሉም መፃህፍት መደብሮች ከዛሬ ጀምሮ ትገኛለች፡፡

ምንዳርአለው ፍልስፍና📚

14 Aug, 12:02


‹‹፡ በዘመቻ ቻቻና፣ በወረት ከበርቻቻ ካልሆነ በስተቀር በራሱ ጊዜ እንቦጭን ለመንቀል የሚተጋ አንድ ሰው የለም፡፡ የካሮት አትክልትን ባየበት ቦታ ሁሉ ለመንቀል የሚቋምጥ ግን መአት ነው፡፡በሚንረል ምልዖቱ ፣ በንጥረ- ምግብ ይዘቱ ተወዳጅና ተመራጭ ነውና፡፡

ሙጃ በቅሎ፣ እዛው  አፍርቶ እዛው ደርቆ እዛው ባለበት እስኪበሰብስ የሚያጭደው ቀርቶ የሚነካው የለም፡፡ ስንዴን ወይም ጤፍን  ወይም ገብስን ግን ገና ከማሸቱ ማጭዱን ይዞ የመድረቂያውን ቀን የሚጠባበቀው ብዙ ነው፡፡የረሀብ ጌታ፣የምጣኔው አለኝታ፤ የጎታው ነጭ ወርቅ፣የዋድያቱ ነጭ አዝሙድ፣ የምጣዱ ላይ ነፍስ አድን ነውና፡፡

ቅንጭብ ላይ ድንጋይ የሚወረውር የለም፡፡ የብርትኳን ወይም የማንጎ ወይም የእንኮይ ዛፍ ላይ ግን ሁሉም ድንጋይ ይወረውራል፡፡ ጣፋጭ ፍሬ ስለሚያፈራ፡፡ ቅንጭብና ቁልቋል ላይ መጥረቢያ የሚያነሳ ሰው የለም፡፡ ዝግባ ጥድና ባህርዛፍ ላይ ግን መጥረቢያውም ዶዘሩም ያጓራል፤ ለቤቱ ካስማ ለድልድዩ ጋድማ፣ ለህንጻው ማማ ናቸውና፡፡››
ሰዉን ናሰው ምዕራፍ 2

ምንዳርአለው ፍልስፍና📚

12 Aug, 19:07


"የእምነት ውል ሲደበዝዝ የክህደት ፊርማ ይደምቃል፡፡ ከፅናት የተፋታ ኑባሬ ከክህደት ጋር ሲጋባ ቡፌው የራሱ ቃል ነው" የፍትህ ስርቅታ

ምንዳርአለው ፍልስፍና📚

06 Aug, 21:45


‹‹፡ በዘመቻ ቻቻና፣ በወረት ከበርቻቻ ካልሆነ በስተቀር በራሱ ጊዜ እንቦጭን ለመንቀል የሚተጋ አንድ ሰው የለም፡፡ የካሮት አትክልትን ባየበት ቦታ ሁሉ ለመንቀል የሚቋምጥ ግን መአት ነው፡፡በሚንረል ምልዖቱ ፣ በንጥረ- ምግብ ይዘቱ ተወዳጅና ተመራጭ ነውና፡፡

ሙጃ በቅሎ፣ እዛው አፍርቶ እዛው ደርቆ እዛው ባለበት እስኪበሰብስ የሚያጭደው ቀርቶ የሚነካው የለም፡፡ ስንዴን ወይም ጤፍን ወይም ገብስን ግን ገና ከማሸቱ ማጭዱን ይዞ የመድረቂያውን ቀን የሚጠባበቀው ብዙ ነው፡፡የረሀብ ጌታ፣የምጣኔው አለኝታ፤ የጎታው ነጭ ወርቅ፣የዋድያቱ ነጭ አዝሙድ፣ የምጣዱ ላይ ነፍስ አድን ነውና፡፡

ቅንጭብ ላይ ድንጋይ የሚወረውር የለም፡፡ የብርትኳን ወይም የማንጎ ወይም የእንኮይ ዛፍ ላይ ግን ሁሉም ድንጋይ ይወረውራል፡፡ ጣፋጭ ፍሬ ስለሚያፈራ፡፡ ቅንጭብና ቁልቋል ላይ መጥረቢያ የሚያነሳ ሰው የለም፡፡ ዝግባ ጥድና ባህርዛፍ ላይ ግን መጥረቢያውም ዶዘሩም ያጓራል፤ ለቤቱ ካስማ ለድልድዩ ጋድማ፣ ለህንጻው ማማ ናቸውና፡፡››
ሰዉን ናሰው ምዕራፍ 2

ምንዳርአለው ፍልስፍና📚

02 Aug, 10:45


ኤክነሚክስ የምዕራቡን ዓለም ምጣኔያዊ ችግሮች ለመፍታት በምዕራባዊ ጭንቅላት የተቀመረ ሳይንስ ነው፡፡ እሱ ላይ ተመስርቶ የኛን ሀገር አይነት ችግር እፈታለሁ ብሎ ማሰብ ፣ ለሀብታም የታዘዘን መድሀኒት ድሀ ቢውጥ ከደዌው ያመልጥ ፤ ብሎ ከማሰብ የከፋ ነው፡፡