መዓዛ ሠናይ @meazasenay Channel on Telegram

መዓዛ ሠናይ

@meazasenay


☞ስለ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖታችን እንወቅ
☞እንረዳ
☞እንማማር

ለበለጠ መረጃ @Tadi16 ላይ ማንኛውንም ሀሳብ አስተያየት እንቀበላለን፡፡

መዓዛ ሠናይ (Amharic)

መዓዛ ሠናይ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖታችን እንወቅ፣ እንረዳ፣ እንማማ። ምንድንዝበር እንደሚከተለው መረጃ @Tadi16 ላይ ማንኛውኝ ሀሳብ አስተያየት እንቀበላለን፡፡ ይህ እናቱ ለመሆን በቃሊቲ ከተማ ላይ ተከታይ ለአብርሃም፣ ማርሰኞ፣ ረቡዕ፣ ዓርብ እና ቅዳሜ በአሰቃቂ ቦታዎች እንቀበላለን። የሚቀጥሉት አገልግሎቶች ለመሆኑ ለአንዳች በተመሳሳይ እናት ነፃነታቸውን እናቅርብላለን።

መዓዛ ሠናይ

03 Feb, 04:50


"እስኪ ከእኔ ጋር ሆናችሁ ቅዱስ ዳዊት ምን ያህል እግዚአብሔርን ከልቡ ይወደው እንደነበር እናስተውል። ቀን ቀን ያስባቸው ዘንድ ግድ የሚሉት የመሪዎች፣ የአዛዦች፣ የመንግሥታቱ፣ የሕዝቡ፣ የሠራዊቱና ስለ ጦርነት ውሎዎቹ፣ ስለ ሰላም፣ ስለ ፖለቲካውና በቤቱ ውስጥ ወይም ከቤቱ ውጪ ወይም በጎረቤቶቹ ዘንድ ስላለው ችግር ማውጣት ማውረዱ ልቡን ከፍለው ይወስዱበታል።

በዕረፍት ጊዜው እያንዳንዱ ሰው ለመኝታው የሚጠቀምበትን ሰዓት እርሱ ደግሞ ለንስሐ ለጸሎትና ዕንባውን ለማፍሰስ ይጠቀምበታል፡፡ እንዲህ ያለ ተግባሩን የሚፈጽመው ዛሬን አድርጎ ነገን ሳያደርግ አይደለም። ወይም ደግሞ ሁለት ወይም ሦስት ሌሊት በማለፍ አይደለም፤ በእያንዳንዷ ሌሊት እንጂ፡፡ «ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ፣ መኝታዬንም በዕንባዬ አርሳለሁ።» የሚለው ቃል የዕንባውን ብዛትና ዕንባው አለማቋረጡን ይገልጽልናል፡፡

እያንዳንዱ ፀጥ ባለ ዕረፍት ውስጥ በሚሆንበት ጊዜ እርሱ ግን እግዚአብሔርን ብቻውን አግኝቶ ለዕንቅልፍ ባልተከደኑ ዓይኖቹ ያለቀስና ያዘነ የግል ኃጢአቶቹን ይነግረዋል፡፡ አንተም ብትሆን እንዲህ ዓይነቱን አልጋ ለራስህ ታበጅ ዘንድ ይገባሃል። በወርቅና ብር ተከበህ መተኛት ከሰዎች ቅናትን ከአርያም ደግሞ ቁጣን ይቀሰቅስብሃል፡፡ እንደ ዳዊት ያለ ዕንባ ግን የሲዖልን እሳት ያጠፋል፡፡

ሌላ አልጋ ደግሞ ላሳይህን? ይህ አልጋ የያዕቆብ ነው። ለስውነቱ ባዶ መሬትን ለትራሱ ደግሞ ድንጋይን የተጠቀመበት አልጋ! ይህ በመሆኑም ያን መንፈሳዊ ድንጋይና ያቺን መላእክት ሲወጡባትና ሲወርዱባት የነበረችውን መሰላል ሊመለከት ችሏል፡፡ (ዘፍ 28፣ ከ1ኛ ቆሮ 10፥4 ጋር አዛምድ፡፡) በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ድንጋዮች ለክርስቶስ ምሳሌ ሆነው ተጠቅሰዋል፡፡ እኛም እንዲህ ያሉ ሕልሞች እናይ ዘንድ ሕሊናችንን እንደዚህ ባሉት አልጋዎች ላይ እናሳርፍ፡፡ ነገር ግን ከብር በተሠሩ አልጋዎች ላይ ብንተኛ ደስታን ብቻ ሳይሆን የምናጣው ችግርንም እንጋፈጣለን፡፡

እጅግ በጣም ቀዝቃዛ በሆነ እኩለ ሌሊት አንተ በአልጋህ ውስጥ ተኝተህ ሳለህ ድሀው ሰው ግን በጭድ ክምር ላይ በደጅህ ወድቆ በብርድ እየተንቀጠቀጠና በረሀብ እየተገረፈ ተዘርግቷል:: አንተ ከስዎች ሁሉ ልበ ደንዳና ብትሆን እንኳ ለዚህ ለድሀ የሚገባውን ሳታደርግለት ለራስህ አላስፈላጊ ምቾቶችን መፍቀድህ እርግጠኛ ነኝ ራስህን እንድትረግም ያደርግሃል። «የሚዘምተው ሁሉ ለጦር ያስከተተውን ደስ ያሰኝ ዘንድ ትዳር በሚገኝበት ንግድ ራሱን አያቆላልፍም።» (2ኛ ጢሞ. 2፥4) ተብሎ ተጽፏልና፡፡

አንተም መንፈሳዊ ወታደር ነህ፡፡ እንዲህ ያለ ወታደር ደግሞ በመሬት ላይ ይተኛል እንጂ ከዝሆን ጥርስ በተሠራ አልጋ ላይ አይተኛም፤ እጅግ ያማረ ሽቶም ኣይቀባም፡፡ እንዲህ ያለው ተግባር በመድረክ ላይ እየተወኑ በግድ የለሽነት ከሚኖሩና ከጋለሞታ ሴቶች ጋር ጊዜያቸውን በማባከን የሚኖሩ የምግባረ ብልሹ ሰዎች ተግባር ነው፡፡ የእኛ ጥሩ መዓዛ ግን ሽቱ ሳይሆን መልካም ሥራ ሊሆን ይገባል፡፡ በሽቱ መዓዛ ከሚመጣው ጠንቅ የበለጠ ነፍስን የሚያቆሽሽ ነገር አይኖርም፡፡ በአብዛኛው አፍአዊ (ውጪያዊ) መልካም መዓዛ የሰው ውስጣዊ ማንነት ማደፍና መቆሸሽ ምልክት ነው፡፡

ዲያብሎስ ነፍስን በራስ ወዳድነት ተዋግቶ ሲያሸንፋትና በታላቅ ከንቱነት ሲሞላት አስቀድሞ አቆሽሾት ወይም አጉድፎት ወይም አበልዞት የነበረውን ሰውነት በሽቶ ያጸዳዋል:: ልክ በጉንፋን እንደተያዙና ያለማቋረጥ በአፍንጫቸው የሚወጣውን ፈሳሽ ለማጽዳት ልብሳቸውን፣ እጆቻቸውንና ፊታቸውን እንደሚያጎድፉ ሁሉ እንዲህ ያለው የክፉ ስው ነፍስም ሰይጣን በሰውነቱ ላይ ያፈሰሰበትን ኃጢአት ለማጽዳት ይሞክራል፡፡ ሽቶ ሽቶ ከሚያውድ፣ ከጋለሞታ ጋር ወዳጅነት ከመሠረተ፣ የዳንኪረኛነት ሕይወትን ከሚመራ ሰው ማን ጨዋና መልካም ነገርን መጠበቅ ይችላል? እስቲ ነፍስህ መንፈሳዊ መዓዛን ትተንፍስና ለአንተም ሆነ ለወዳጆችህ ታላቅ በረከትን ታድላቸው፡፡"

(ሀብታምና ድሀ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሰበከው -ገጽ 21-23 አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው)

መዓዛ ሠናይ

29 Jan, 10:08


አበው ስለ #እመቤታችን_ዕረፍት እንዲህ አሉ፦

"ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች "ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ።"
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ

"ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው። በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው። በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ። አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት [የተለያየ] ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ።"
#ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ

"የቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች የነበሩት ሐዋርያት በሥጋ የወለደችውን የእናቱን ዕረፍትና እርስዋን የሚመለከቱ የመጨረሻዎቹን ምሥጢራትም ማየት ነበረባቸው፡፡ ይህም የሆነው የክርስቶስ የዕርገቱ የዓይን ምስክሮች እንደሆኑ ሁሉ የወለደችውም እናቱ ወደዚያኛው ዓለም ለሸጋገርዋ ምስክሮች መሆን ስላለባቸው ነው።"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘደማስቆ

(በ Deacon Henok Haile የተሰበሰበ)

መዓዛ ሠናይ

29 Jan, 10:07


ስጋዋንም ያሳዪት ዘንድ ወደ መቃብርዋ በአደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ስጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ ነገራቸው። ሀዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን እርገቷን ስለ አላዩ እጅግ አዘኑ ስጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኃላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ስጣቸው እነርሱም እስከ ነሀሴ አስራ ስድስት በረስፋ ኖሩ።

የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት አመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሶስት አመት ከሰባት ወር በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት አመት በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት አመት ከሶስት ወር ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት አመት ነው።

የህይወት የድኅነት አለኝታ የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በፀሎቷም ከክፉ ነገር ይጠብቀን፤ በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።

(ስንክሳር ዘተዋሕዶ - #ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)

መዓዛ ሠናይ

29 Jan, 10:07


#በዓለ_አስተርዕዮ_ማርያም - #ጥር_21
ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በአል መታሰቢያ ነው። ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃበሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም አለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኃላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።

በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦
"ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሩዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሀንስን በዚች ሰአት አምጣው።እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሀዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።

በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሀንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ አለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ህይወት ትሄጂአለሽና። ይህም ስሙ ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኃላ ነው።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላትእግዚአብሄርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።

በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሀዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።

ወዲያውኑ ሁሉም ሀዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት አምላከችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆን ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ አለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት።

በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሀዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኃችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም አለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ።

ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት።

እመቤታችንም ማርያምም ይህን ነገር ከሀዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ።የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።

ፀሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሀዋርያትን እንዲህ አለቻቸው እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረገ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለቸወበት ቤት በቀረብ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።

ከዚህም በኃላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም አላት።

ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሀወሰርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጃዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሀዋርያትን አዘዛቸው።

ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት።

እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።

ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም አለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።

እመቤታችንም ከአረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሄር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።

ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሀዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።

በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።

ሀዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሀዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።

መዓዛ ሠናይ

28 Jan, 14:48


“ማግባት ለሚሹ”
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር

ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡

ስለዚህ ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡

አባቶች ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡

እናቶች ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡

እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡

እናንተ ልጃገረዶች ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡

የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡

መዓዛ ሠናይ

28 Jan, 14:48


"...ክርስቲያኖች ግን ክርስቲያኖች ለመኾናቸው መታወቅ የሚገባቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተው ምሥጢራትን ሲቀበሉ ብቻ ሳይኾን የትም ቦታ በሚኖሩት የቅድስና ሕይወት ነው፡፡ በአፍአ የከበሩ ሰዎች በአፍአ ከሚያሳዩት ምልክት እንደሚታወቁ ኹሉ፥ እኛም ልንታወቅ የሚገባን በነፍሳችን ክብር ነው፡፡ በሌላ አገላለጥ አንድ ክርስቲያን መታወቅ ያለበት በተሰጠው ልጅነት ብቻ ሳይኾን ለልጅነቱ እንደሚገባ በሚያሳየው አዲስ ሕይወትም ጭምር ሊኾን ይገባል፡፡ ይህ ክርስቲያን ለዓለም ብርሃንና ጨው ሊኾን ይገባዋል፡፡ ለዓለም ብርሃን መኾንህስ ይቅርና ለራስህ እንኳን ብርሃን መኾን ካልተቻለህ፣ የሚሰፋ ቁስልህን በዘይት ማሰርም ካቃተህ፥ ክርስቲያን መኾንህን የምናውቀው እንዴት ነው? ወደ ተቀደሰው ውኃ ገብተህ በመጠመቅህ ነውን? በዚህስ አይደለም ! ይህስ እንዲያውም ዕዳ ፍዳ ይኾንብሃል [እንጂ ክርስቲያን መኾንህን እንድናውቅህ አያደርገንም]፡፡ ይህ ሀብት (ልጅነት) ታላቅ ነውና ለዚህ ሀብት እንደሚገባ ለማይኖሩት ሰዎች ዕዳ ፍዳ መጨመሪያ ነው፡፡ አዎን፥ ክርስቲያን ለዓለም ብርሃኑን ማብራት ያለበት ከእግዚአብሔር በተቀበለው ጸጋ ብቻ ሳይኾን እርሱ ራሱም ድርሻውን በመወጣት ነውና፡፡ ክርስቲያን ካልኾኑት ይልቅ በኹለንተናው በአረማመዱ፣ በአተያዩ፣ በአለባበሱ፣ በአነጋገሩ ብልጫ ሲኖረው ነውና፡፡ ይህንም የምለው ልጅነትን የተቀበሉ ክርስቲያኖች ልጅነትን ተቀበሉ በመባል ብቻ ሳይኾን የሌሎች ሰዎች ረብ ጥቅም ይኾን ዘንድ ለተቀበሉት ልጅነት የሚገባና ሥርዓት ያለው ሕይወት እንዲኖሩ ስለምሻ ነው፡፡

አሁን ግን ከሌሎች ከማያምኑት ብልጫ ኖሮህ እንዳየው በምፈልገው ሕይወት፥ በኹሉም ረገድ ተቃራኒ ኾነህ አይሃለሁ፡፡ ለምሳሌ ከቦታ አንጻር፥ ቀኑን ኹሉ የፈረስ እሽቅድምድምንና ተውኔትን፣ ነውርን የተሞሉ ትርኢቶችንና የክፉዎችን ማኅበር፣ ርኵሰትንም የተሞሉ ሰዎችን ስትመለከት እንደምትውል አይሃለሁ፡፡ ከፊትህ አንጻር፥ ዘወትር ያለ ልክና እንደ አመንዝራ ሴት ስትስቅ እመለከትሃለሁ፡፡ ከአለባበስህ አንጻር፥ ከተዋንያንና ጠቢባን ነን ከሚሉ ሰዎች ምንም እንደማትለይ አስተውልሃለሁ፡፡ ከሚከተሉህ ሰዎች አንጻር፥ ብዙ ውዳሴ ከንቱንና ሽንገላን እንደምትሻ አይሃለሁ፡፡ ከንግግርህ አንጻር፥ ምንም ደኅና ነገር፣ በቁዔት ያለው ቃል፣ ለሕይወታችን የሚረባ ንግግር እንደሌለብህ አደምጣለሁ፡፡ ከማዕድህ አንጻርም ከዚያ ጽኑዕ የኾነ ወቀሳ የሚያመጣብህ እንደ ኾነ አያለሁ፡፡

ታዲያ እስኪ ንገረኝ ! ክርስቲያንን ክርስቲያን ከሚያስብሉት ነገሮች እጅግ የራቅህ ኾነህ እያለ፥ ክርስቲያን መኾንህን መለየት የምችለው በምንድን ነው? ክርስቲያን መባልህስ ይቅርና፥ ሰው ብዬ ልጠራህ የምችለውስ እንዴት ነው? እንደ አህያ ትራገጣለህና፤ እንደ ኮርማ ትሴስናለህና፤ እንደ ፈረስ ከሴቶች ኋላ ኾነህ ታሽካካለህና፤ እንደ ድብ ሆዳም ነህና ፤ ሥጋህን እንደ በቅሎ ሥጋ ትሰገስጋለህና፤ እንደ ግመል ቂም ትይዛለህና፤ እንደ ተኵላ ትነጥቃለህና፤ እንደ እባብ ትቈጣለህና፤ እንደ ጊንጥ ትናደፋለህና፤ እንደ ቀበሮ ተንኰለኛ ነህና፤ እንደ እባብ ወይም እንደ እፉኝት በጕረሮህ መርዝ አለና፤ እንደ ክፉ ጋኔን ከወንድምህ ጋር ትጣላለህና፡፡ ታዲያ ክርስቲያን የሚለውስ ይቅርና፥ በምንህ ሰው ብዬ ልጥራህ? ሰው የሚያስብል ምልክት ሳይኖርህ እንዴት ብዬ ከሰው ዘንድ ልቊጠርህ? የንኡሰ ክርስቲያኖችና የክርስቲያኖች ልዩነት ባሰብሁ ጊዜ ልዩነቱ የሰውና የአርዌ ገዳም ያህል ይኾንብኛል፡፡ ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? አርዌ ገዳም ብዬ ልጥራህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጭካኔህ ከአራዊተ ገዳም በላይ ነውና፤ [በሌላ መልኩ ደግሞ እነርሱ እንደዚያ የኾኑት ከተፈጥሮአቸው የተነሣ እንጂ እንደ አንተ ወደውና ፈቅደው አይደለምና፡፡] ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? ጋኔን ልበልህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጋኔን የሆድ ባሪያ አይደለምና፤ ፍቅረ ንዋይም የለበትምና፡፡ ታዲያ ከአራዊተ ገዳምም ከአጋንንትም የሚብስ ክፉ ግብር ከያዝህ፥ ንገረኝ - ሰው ብዬ እጠራህ ዘንድ ይገባኛልን? ሰው ለመባል እንኳን የሚበቃ ምግባር ከሌለህስ፥ ክርስቲያን ብለን ልንጠራህ የምንችለው እንዴት ነው?"

(የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመው  ድርሳን 4፥14-15 ገጽ 80-82 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)

መዓዛ ሠናይ

26 Jan, 10:09


የከተራና የጥምቀት መዝሙሮችን ለማጥናት 👇👇
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡

🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞

🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧

🎶 ዘወይን ዘወይን ✞

🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡

🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞

🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ

🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡

🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡

🎶 እንዘስውር ✧

እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
    join join join
     Join join join

መዓዛ ሠናይ

19 Jan, 07:18


የከተራና የጥምቀት መዝሙሮችን ለማጥናት 👇👇
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡

🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞

🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧

🎶 ዘወይን ዘወይን ✞

🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡

🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞

🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ

🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡

🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡

🎶 እንዘስውር ✧

እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
    join join join
     Join join join

መዓዛ ሠናይ

15 Jan, 06:50


ጥር 7 አጋእዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ በኃጢአት የተገነባውን የሰናዖር ግንብ ያፈረሱበት አንድነታቸውንና ሦስትነታቸውን በግልጽ ያሳዩበት አመታዊ ክብረ በዓል ነው
ኦ.ዘፍ ም 11
ከእመቤታችን እረዴት በረከት ያካፍለን

መዓዛ ሠናይ

12 Jan, 15:02


የከተራና የጥምቀት መዝሙሮችን ለማጥናት 👇👇
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡

🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞

🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧

🎶 ዘወይን ዘወይን ✞

🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡

🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞

🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ

🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡

🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡

🎶 እንዘስውር ✧

እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
    join join join
     Join join join

መዓዛ ሠናይ

11 Jan, 05:19


ሰብአ ሰገል ይዘው የመጡት ወርቅ ዕጣንና
ከርቤ ከየት መጣ?

በቅድምያ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ልደት በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ! በዓሉ የሰላምና የፍቅር ይሁንልን።

ጌታችን በተወለደ ጊዜ ሰብአ ሰገል የገበሩተለት ወርቅ ፣ ዕጣንና ከርቤ መገኛቸው ከገነት እንደሆነ ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን? ነገሩ እንደምን ነው ቢሉ ጥንት አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን በገነት ውስጥ በሰላምና በተድላ ይኖሩ ነበር። ታዲያ ዲያቢሎስ አትብሉ የተባሉትን እንዲበሉ ሐሳብ  አቅርቦ ካሳታቸው በኋላ ያን አትብሉ የተባሉትን በመብላታቸው ትዕዛዝ በመተላለፋቸው ሰባት ዓመት ከ47 ቀን በተድላ ከኖሩበት ገነት ተባረሩ። ከገነት ከወጡ በሁላ አዳምና ሔዋን በዚህ ምድር ላይ ኑሮአቸውን ሀ ብለው ጀመሩ።

አንድ ቀን አዳም እናታችን ሔዋንን በባል ልማድ ሊጨዋወታት (ሊገናኛት) ወዶ በመንገድ ጠብቆ አስደነገጣት ታዲያ ይህን ጊዜ ሥላሴ ተገልጠው "ምነው ማጫውን ሳትሰጠን ልጃችን ትነካለህን?" ቢሉት አዳምም "ጌታዩ የአንተ ያልሆነ የኔ የሆነ ምን አለኝና እሰጥሀለው!" ቢሊ "አይ ለኋልኛው ዘመን ሥርዓት ነውና ይህን ለእርሷ ስጣት እንኳ" ብለው ቅዱስ ሚካኤል ወርቁን ፣ ቅዱስ ገብርኤል ዕጣኑን ፣ ቅዱስ ሩፋኤል ደግሞ ከርቤውን ለአዳም ሰጥተውታል። አዳምም ተቀብሎ ለሔዋን ሰጣት ፣ ሔዋን ለሴት ሰጠችው ፤ ከሴት ሲወርድ ሰዋረድ ከኖህ ደረሰ፡ ኖህ በጥፋት ውኅ ዘመን ወደ መርከብ ሲገባ የአዳምን አጥንትና ወርቅ ፣ ዕጣን ፣ ከርቤውን በአንድነት ይዞ ገባ።

ኋላ የጥፋት ውኀው ጎደለና ከመርከብ ይዞትጰወጣ በሁላ ለሴም ሰጠው ፤ ሴምም መልከጼዴቅን ተገናኘውና የአዳምን አጥንት በጎለጎታ ቀበሩት። ለዚህም ነው የጌታችን የሥነ ስቅለቱ ስዕል ሲሳል ከሥር የራስ ቅል አጥንት የሚደረገው ያም የአዳም አጥንት ምሳሌ ነው። ከዚያም ሴም ለመልከጼዴቅ ወርቅ ፣ ዕጣን ፣ ከርቤውን በአደራ አስጠበቀው፡ መልከጼዴቅ ለአብርሃም ሰጠው።

ከአብርሃም ሲወርድ ሲወረድ በዳዊት በሰለሞን አድርጎ ከአካዝ ደረሰ፡ በአካዝ ዘመን ቴልጌልፌልሶር ማርኮ ወስዶ ከቤተ መዛግብት አኑሮታል፡ አባታቸው ዥረደሸት ፈላስፋ ነበር፡ አንድ ቀን በቀትር ከውኃ ዳር ሆኖ ሲፈላሰፍ በሰሌዳ ኮከብ ድንግል ሕፃን ታቅፋ አየ ያየውን በሰሌዳ ቀርጾ አሰቀመጠው ከመሞቱ በፊትም እንዲህ ያለ ኮከብ ሲወጣ ባያችሁ ግዜ ሰማያዊ ንጉስ ይወለዳልና ወስዳቹ ይህን ወርቅ ፣ ዕጣን ፣ ከርቤ ስጡት ብሎ ለልጆቹ ተናዞ ሞተ። በዚህ መልኩ ከእነዚህ ነገሥታት እጅ ደርሷል። በእርግጥ ታሪኩን ለመተረክ አንድ መጽሐፍ የሚበቃውም አይደለም ከረጅም በአጭሩ ግን ይህን ይመስላል።

ታዲያ ኮከቡም በታየ ግዜ የታዘዙትን ለመፈፀም 12
ነገስታት ፍርሻኩር የተባለ ንጉሥ እየመራቸው ከሀገራቸው ተነሱ እያንዳንዱ ነገሰታት 10 ሺህ የሚሆን ሠራዊት ይዘው በጉዞ ላይ እያሉ ኤፍራጥስ ወንዝ ሲደርሱ ፍርሻኩር የተባለው መሪያቸው ዘጠኙን ነገስታት ከነሰራዊታቸው ይዟቸው ተመለሰ ከተመለሱበት ምክንያት ውስጥ ግማሹ ስንቅ አልቆባቸው ሌሎቹ ደግሞ በሀገራቸው ጠላት ተነስቶባችዋል የሚል ወሬ ሰምተው ሲሆን ሌሎቹ ደግሞ ኢየሩሳሌም ለሰላሳ ሺ ሠራዊት አትበቃም ጠባብ ናት ብለው የተመለሱም አሉ። ምስጢሩ ግን ከበረከተ ልደቱ እንዲሳተፋ የተመረጡት ሦስቱ ብቻ መሆናቸውን የጠይቃል የተጠሩ ብዙዎች የተመረጡ ጥቂቶች ናቸው እንደተባለ።

መዓዛ ሠናይ

07 Jan, 17:00


ጌታችን ስለተወለደባት ምሽት ቅዱስ ኤፍሬም አንዲህ አለ....
.
‹‹ይህች ምሽት ንጹሕ የሆነውና እኛን ሊያነጻን የመጣው (አምላክ) የተገለጠባት ንጽሕት ምሽት ናት፡፡ ጆሮአችን ንጹሕ ይሁን፤ ዓይኖቻችንም ወደ ንጹሕ ነገር ይመልከቱ፤ የልባችን ስሜት ቅዱስ ይሁን! ንግግራችንም አክብሮትን ይሞላ!

ይህች ምሽት የዕርቅ ምሽት ናት፤ ስለዚህ ማንም ሰው ወንድሙን ተቆጥቶ እንዳያስቀይም! ይህች ምሽት ለዓለም ሁሉ ሰላምን ያስገኘች ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው አይሸበርባት፡፡ ይህች ምሽት የደግነት ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው ክፉ አይሁን! ይህች ምሽት የትሕትና ምሽት ናትና ማንም ሰው እንዳይታበይባት! ይህች ምሽት የደስታችን ቀን ስለሆነች የበደሉንን አንበቀልባት! የበጎ ፈቃድ ቀን ናትና የጭካኔ ቀን አናድርጋት! የጸጥታ ቀን ናትና በቁጣ የምንነድባት ቀን አናድርጋት!

ዛሬ እግዚአብሔር ወደ ኃጢአተኞች የመጣበት ቀን ነው ፤ ስለዚህ ጻድቅ ሰው በኃጢአተኞች ላይ አይኩራባቸው! ዛሬ እጅግ ባለጠጋ የሆነው አምላክ ስለ እኛ ደሃ የሆነበት ቀን ነው፤ ስለዚህ ሀብታም ሰው ድሆችን ወደ ገበታው ይጥራቸው፡፡ ዛሬ ያልጠየቅነውን ሥጦታ የተቀበልንበት ዕለት ነው፡፡ ስለዚህ እጆቻቸውን ዘርግተው እየጮኹ ለሚለምኑን ሰዎች የእርዳታ እጃችንን እንዘርጋ!

የዛሬዋ ዕለት ለጸሎቶቻችን የሰማያትን በር ከፍታልናለች ፤ እኛም ይቅርታን ለሚጠይቁን ሰዎች በራችንን እንክፈት! ዛሬ አምላክ የሰውነትን ማኅተም በራሱ ላይ አተመ ፤ ሰውም የአምላክነትን ማኅተም ተጎናጸፈ!››

እንኳን ለአምላካችን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!

መዓዛ ሠናይ

04 Jan, 12:33


የከተራና የጥምቀት መዝሙሮችን ለማጥናት 👇👇
🎶 እግዚኡ መርሐ ♡

🎶 ከድንግል ተወልዶ ✞

🎶 በዮርዳኖስ የተጠመቀው ✧

🎶 ዘወይን ዘወይን ✞

🎶 ጥምቀተ ባሕር ♡

🎶 እርሱ ፍጹም ሊልቅ ✞

🎶 ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠመቀ

🎶 ዮሐንስ አጥመቆ ♡

🎶 ዮሐንስኒ_ያጠመቀ ♡

🎶 እንዘስውር ✧

እነዚህን ለማጥናት ከስር Join አድርጉ
    join join join
     Join join join

መዓዛ ሠናይ

02 Jan, 06:21


ታህሳስ24 የኢትዮጵያ ብርሃን የካህኑ የፀጋ ዘአብና የቅ.እግዚአርያ ልጅ ፃድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተወለዱበት አመታዊ ክብረ በዓል ነው
ከእመቤታችን እና ከአቡነ ተክለሃይማኖት እረዴት በረከት ያካፍለን

መዓዛ ሠናይ

02 Jan, 06:16


"ልጆቼ! የሚያሳፍር ነገር፣ የስንፍና ንግግር ወይም ዋዛ ፈዛዛ የማይገቡ ናቸውና በእኛ በክርስቲያኖች ዘንድ ከቶ አይሰሙ፡፡ እስኪ ንገሩኝ! የዋዛ ፈዛዛ ንግግር ጥቅሙ ምንድን ነው? እስኪ ንገሩኝ፤ አንድ ጫማ ሰፊ፣ ጫማ እየሰፋ በአንድ ጊዜ ሌላ ሥራ መሥራት ይችላልን? አይችልም፡፡ ከዋዛ ፈዛዛ የሚያሳፍር ንግግር ይወለዳል፡፡ የአሁኑ ጊዜ ደግሞ ለእኛ ለክርስቲያኖች ዋዛ ፈዛዛ የምንናገርበት ሳይኾን የንስሐችን ጊዜ ነው፡፡ እስኪ አሁንም ልጠይቃችሁና እናንተም መልሱልኝ! አንድ ቦክስ የሚጫወት ሰው ውድድሩን ችላ ብሎ ዋዛ ፈዛዛን ይናገራልን? እንዲህ የሚያደርግ ከኾነስ በተጋጣሚው በቀላሉ የሚሸነፍ አይደለምን? ታዲያ ባለጋራችን ዲያብሎስ‘ኮ የሚውጠውን ፈልጐ እንደሚያገሣ አንበሳ በዙርያችን ቁሟል፡፡ ጥርሱን እያንቀጫቀጨብን ነው፡፡ እኛን የሚጥልበት ወጥመድ በማዘጋጀት ላይ ነው፡፡ የደኅንነታችን መንገድ ላይ እሳት እየተነፈሰ ነው፡፡ ታዲያ ዲያብሎስ እንዲህ እኛን ለመጣል ሲተጋ እኛ ዋዛ ፈዛዛን፣ የሚያሳፍር ነገርን፣ የስንፍናንም ንግግር ስንናገር ቁጭ ልንል ይገባናልን?

የምወዳችሁ ልጆቼ! ጊዜው የምንተኛበት ጊዜ አይደለም፡፡ የተጋድሎ ጊዜ ነው እንጂ፡፡ ቅዱሳን ጊዜያቸውን እንደ ምን እንደሚያሳልፉት ማወቅ ትፈልጋላችሁን? እስኪ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስን አብረን እንስማው፤ እንዲህ ያለውን፡- “ሦስት ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሠጽ እዳላቋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ”፤ … “በብዙ መከራና ከልብ ጭንቀት በብዙም እንባ ጽፌላችኋለሁ…”፡፡ … “የሚደክም ማን ነው፤ እኔ አልደክምምን? የሚሰናከል ማን ነው፤ እኔም አልናደድምን?”፤ “… በድንኳኑ ያለን እኛ ከብዶን እንቃትታለን”፡፡ ታዲያ እነ ቅዱስ ጳውሎስ ጊዜያቸውን እንዲህ ካሳለፉ፣ ኃጥአን የምንኾን እኛ ጊዜያችንን በሳቅና ስላቅ ልናጠፋ ይገባናልን? በክርስቶስ ፍቅር የማፈቅራችሁ ልጆቼ! በንግግሬ አትማረሩ፡፡

ጊዜው የተጋድሎ ጊዜ ነው፤ ታዲያ ስለ ምንድን ነው የዘፋኞችን መሣርያ አንሥተን ከዓለም ጋር የምንዘፍነው? በጦር ግንባር ያለ ወታደር ከጠላት ሊመጣ የሚችለውን ጥቃት ለመከላከል ከመዘጋጀት ይልቅ ጊዜውን በዋዛ ፈዛዛ ያጠፋልን? አያጠፋም፡፡ ታዲያ እኛም‘ኮ የክርስቶስ በጎ ወታደሮች ነን፡፡ ..."

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)

መዓዛ ሠናይ

31 Dec, 06:16


ታህሳስ22 ሊቀ መልአክ ቅ.ገብርኤል እመቤታችን ያበሰረበት ቀን መጋቢት29 አብይ ጾም ላይ ስለሚውል ሊቀ ጳጳስ ደቅስዮስ ከልደት በዓል በፊት ከታህሳስ22 ጀምሮ ለ8 ቀናት አክብሮላታል በዚህም ደስ ተሰኝታ በሰው እጅ ያልተሰራና ሌላ ሰው የማይለብሰውና የማይቀመጥበት ልብስና ወንበር ሰታዋለች
ከእመቤታችንና ከቅዱስ ገብርኤል በረከት ረድኤት ያካፍለን

መዓዛ ሠናይ

28 Dec, 08:10


#ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ገብርኤል (#ታኅሣሥ_19)

ታኅሣሥ ዐስራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅ ያዳነበት ነው፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር ከአባታቸው ከይሁዳው ንጉሥ ከኢዮአቄም ጋር የማረካቸው አናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ እግዚአብሔር በዚህች ዕለት መልአኩን ልኮ ታላቅ ተአምር አድርጎላቸዋል፡፡

ንጉሥ ናቡከደነፆር እነዚህን ወጣቶች በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ጥበብን እያስተማረ ካሳደጋቸው በኋላ በባቢሎን ሀገሮች ሁሉ ውስጥ ሾማቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ ለዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ ለጣዖቱ ባለመስገድ እግዚአብሔርን ብቻ በማምለክ የጸኑት እነዚህ ሦስት ወጣቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ስለ እነርሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡-
‹‹ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው፡፡ ንጉሡም ናቡከደነፆር መኳንንትንና ሹማምቶችን፥ አዛዦችንና አዛውንቶችን፥ በጅሮንዶችንና አማካሪዎችን፣ መጋቢዎችንም፣ አውራጃ ገዦችንም ሁሉ ይሰበስቡ ዘንድ፣ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ይመጡ ዘንድ ላከ፡፡ በዚያን ጊዜም መኳንንቱና ሹማምቶቹ፣ አዛዦቹና አዛውንቶቹ፣ በጅሮንዶቹና አማካሪዎቹ፣ መጋቢዎቹና አውራጃ ገዦቹ ሁሉ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ተሰበሰቡ፤ ናቡከደነፆርም ባቆመው ምስል ፊት ቆሙ፡፡ አዋጅ ነጋሪውም እየጮኸ እንዲህ አለ፡- ‹ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የምትናገሩ ሆይ! የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ፣ ተደፍታችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቁ ምስል እንድትሰግዱ ታዝዛችኋል፡፡ ተደፍቶም የማይሰግድ በዚያን ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል፡፡› ስለዚህ በዚያን ጊዜ አሕዛብ ሁሉ የመለከቱንና የእንቢልታውን፣ የመሰንቆውንና የክራሩን፣ የበገናውንና የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ፣ ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የተናገሩ ሁሉ ተደፉ፤ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቅ ምስል ሰገዱ፡፡

በዚያን ጊዜም ከለዳውያን ቀርበው አይሁድን ከሰሱ፡፡ ለንጉሡም ለናቡከደነፆር ተናገሩ እንዲህም አሉ ‹ንጉሥ ሆይ! ሺህ ዓመት ንገሥ፡፡ አንተ ንጉሥ ሆይ የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ የሚሰማ ሰው ሁሉ ተደፍቶ ለወርቁ ምስል ይስገድ፤ ተደፍቶም የማይሰግድ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል ብለህ አዘዝህ፡፡ በባቢሎን አውራጃ ሥራ ላይ የሾምሃቸው ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም የሚባሉ አይሁድ አሉ፤ ንጉሥ ሆይ! እነዚህ ሰዎች ትእዛዝህን እንቢ ብለዋል፤ አማልክትህን አያመልኩም፥ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል አይሰግዱም፡፡› ናቡከደነፆርም በብስጭትና በቍጣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም ያመጡ ዘንድ አዘዘ፤ እነዚህንም ሰዎች ወደ ንጉሡ ፊት አመጡአቸው፡፡ ናቡከደነፆርም ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ሆይ! አምላኬን አለማምለካችሁ ላቆምሁትም ለወርቁ ምስል አለመስገዳችሁ እውነት ነውን? አሁንም የመለከቱንና የእንቢልታውን የመሰንቆውንና የክራሩን የበገናውንና የዋሽንቱን የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ ተደፍታችሁ ላሠራሁት ምስል ብትሰግዱ መልካም ነው፤ ባትሰግዱ ግን በዚያ ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ከእጄስ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው?›› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም መለሱ ንጉሡን ‹ናቡከደነፆር ሆይ! በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም፡፡ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፡፡ ነገር ግን ንጉሥ ሆይ! እርሱ ባያድነን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ› አሉት፡፡

የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም ላይ ቍጣ ሞላበት፡፡ የፊቱም መልክ ተለወጠባቸው፡፡ እርሱም ተናገረ የእቶንም እሳት ይነድድ ከነበረው ይልቅ ሰባት እጥፍ አድርገው እንዲያነድዱት አዘዘ፡፡ ሲድራቅንና ሚሳቅንም አብደናጎንም ያስሩ ዘንድ ወደሚነድድም ወደ እቶን እሳት ይጥሉአቸው ዘንድ በሠራዊቱ ውስጥ ከነበሩት ኃያላን አዘዘ፡፡ የዚያን ጊዜም እነዚህ ሰዎች ከሰናፊላቸውና ከቀሚሳቸው ከመጐናጸፊያቸውም ከቀረውም ልብሳቸው ጋር ታስረው በሚነድድ በእቶን እሳት ውስጥ ተጣሉ፡፡ የንጉሡም ትእዛዝ አስቸኳይ ስለሆነ የእቶኑም እሳት እጅግ ስለሚነድድ፣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም የጣሉአቸውን ሰዎች የእሳቱ ወላፈን ገደላቸው፡፡ እነዚህም ሦስቱ ሰዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ታስረው በሚነድደው በእቶኑ እሳት ውስጥ ወደቁ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም ‹ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን?› ብሎ ተናገራቸው፡፡ እነርሱም ‹ንጉሥ ሆይ! እውነት ነው› ብለው ለንጉሡ መለሱለት፡፡ እርሱም ‹እነሆ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል› ብሎ መለሰ፡፡ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ ‹እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም! ኑ ውጡ› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ፡፡

መሳፍንቱና ሹማምቶቹም አዛዦቹና የንጉሡ አማካሪዎች ተሰብስበው እሳቱ በእነዚያ ሰዎች አካል ላይ ኃይል እንዳልነበረው፣ የራሳቸውም ጠጕር እንዳልተቃጠለች ሰናፊላቸውም እንዳልተለወጠ፣ የእሳቱም ሽታ እንዳልደረሰባቸው አዩ፡፡ ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፣ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ፡፡ እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም አምላክ ላይ የስድብን ነገር የሚናገር ወገንና ሕዝብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ይቈረጣሉ፣ ቤቶቻቸውም የጕድፍ መጣያ ይደረጋሉ ብዬ አዝዣለሁ› አለ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም በባቢሎን አውራጃ ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋቸው፡፡›› ትንቢተ ዳንኤል 3፡1-30፡፡

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በመልአኩ አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

( ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ)

መዓዛ ሠናይ

25 Dec, 05:47


“ልጄ ሆይ፥ እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ ከሥቃይሽም ተፈወሽ አላት።” /ማር 5÷34/

"እምነት" በኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አስተምህሮ እግዚአብሔር ከፅንሰቱ እስከ እርገቱ ድረስ በምድር ላይ ሰው ሆኖ በፈቃዱቨ ያደረገውን ሁሉ ማመን መቀበል ሳያጎድሉ በምልዐት መቀበል ነው (ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ መድልተ ጽድቅ ቅጽ 1) የሰው ልጅ ውድቀቱ መነሳቱ በእምነት ማጣት እና ማግኘት ነው።

አስቀድሞ እግዚአብሔር የሰው ልጅ ሲፈጥረው እንደራሱ አድሮጎ በተፈጠረለት ማንነቱ በንፅሕናው ተፈጥሮ መልካምና ክፍውን ይለይ ዘንድ ነፃ ፍቃድ ሰጥቶ ፈጠው ከእርሱ በፈት የተፈጠሩት ፍጥረታት ሁሉ አዳም የእግዚአብሔር ስራ አይቶ በመድነቅ ከእግዚአብሔር ጋር በእምነት በታማኝነት አንድላይ ይኖሩ ዘንድ ፍጥረታት ተፈጠሩለት እግዚአብሔር ከዚህ ከተፈጠረለት ማንነት እንዳይወጣ አሰቀድሞ " ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ ነገር ግን መልካም እና ክፍውን ከሚያሳውቀው ዛፍ አትብላ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህ በማለት አዞት " ግን ከእግዚአብሔር ይልቅ የሴጣንን ምክር ሰምቶ አምኖ ሞትን በራሱ ላይ አመጣ የቀደመችው ሔዋን ሴጣንን አምና ሞትን  በእራሷና ከአብራኩ ካስገኛት አዳም ሞትን አመጣች።

ዳግማዊቷ ሔዋን ድንግል ማርያም ግን መጀመርያ ሞት በመጣበት መንገድ የእምነት ማጣት ትሞላ ዘንድ ቀድማ የሴጣንን ምክር በተቀበለችው ሔዋን  ፍንታ የመላኩን ቃል በእምነት በመቀበል ለፈጣሪ ያለንን እምነት መለሰችልን። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በእምነት በመኖራቸው የእምነታቸውን ፍሬ ያፈሩ እና በሕይወታቸው ሁሉን የእግዚአብሔር  ቻይነት የመሰከሩ እሩስም ታማኝነታቸውን በበረከት የመሰከረላቸው አሉ ከእንዚህም ውስጥ የመጥምቁ እናት ቅድስት ኤልሳቤጥ ናት እስከ  እርጅናዋ ዘመን ድረስ እግዚአብሔር ስታገለግል የኖረች የካህኑ ዘካርያስ ሚስት ኤልሳቤት ታሪኳ በሉቃ 1÷5 ተፅፎ እናገኛለች ኤልሳቤጥ በዘመኗ ሁሉ እግዚአብሔር ባይሰጣትም ልጅ እንደሚሰጣት አንድ ቀን አምና የእግዚአብሔር ሁሉ ቻይነት እመሰከረች ኖረች።

እግዚአብሔር የኤልሳቤጥን እሱን አምና ለዘመናት ሳታማርር መኖሯን አይቶ ጌታን የሚያጠምቀውን መጥምቁ ዮሐንስን ሰጥቷት እምነቷን መሰከረላት ይህ ሁሉ የሆነው በኤልሳቤጥ በእምነት መኖር ነው። ሰማዕታት የእግዚአብሔርን ክብር እየመሰከሩ በርሃብ እርሱን ምግብ አርገው ሁሉን  እንደማያሳጣቸው እየመሰከሩ ኖሩ እግዚአብሔር በገባላቸው ቃልኪዳን ዘወትር ፍጥረታትን በስማቸው እየመገበ እምነታቸውን መሰከረላቸው።

(ማቴ 20÷22) ተፅፎ የምናገኘው አንድ ታሪክ አለ ከአስራ ሁለት ዓመት ጀምሮ ደም ይፈሳት የነበረች ሴት ብዙ ባለመዳኒቶች ጋር ገንዘቧን የጨረሰች ግን የገንዘቧ ማለቅ ደሟ መፍሰሱን ያላስለቀቀላት" ያልቆመላት ሴት። ይች ሴት ክርስቶስን ልብሱን የነካው እንደሆነ እፈወሳለሁ ብላ በእምነት አምና ቀረበች ዳሰሰችውም ዳነች። ክርስቶስ ልጄ ሆይ አይዞሽ እምነትሽ አድኖሻል ብሎ መሰከረላት። ይህች ሴት የክርስቶስን በስጋ ውስጥ ሳይታይ ያለውን ሁሉን ቻይነት አምና ሊፈውሳት እንደሚችል አምላክነቱን በእምነት መሰከረች። ክርስቶስ በማይታየው እምነቷ የሚታየውን በሽታዋን በመፈወስ እምነቷን መሰከረላት።

ወዳጆቼ ብዙ የሚታይ በሽታ ይዞን ይሆናል እንደ ዘመኑ ሰው የመግደል በሽታ አልቅሶ እስካለየነው ደስታ የማይሰማን የመሆን በሽታ ፍቅርን በመግፍት አንጂ በተጠላን ልክ የማይገኝ ሲመሰለን በትውልድ ውስጥ ጥላቻ እየጫሩ የመኖር ይህ ሁሉ የሚታይ የግፍ ውጤት ሊቆም ያልቻለው የማይታየው እምነት ስለሌለን ፈጣሪ ሳይሆን ሴጣን እየመሰከረልን እየኖርን እንገኛል። ስለዚህ ፈጣሪ እንዲመሰክርልን ወደ እርሱ እንመለስ።

መዓዛ ሠናይ

24 Dec, 15:31


😥ገዳም እንሂድ...ይለኛል ወንድሜ።ዘማነቴን አያውቀውም። ሴሰኝነቴ አይገባውም።እኔ በምናብ ከፈጠርኳት ሴት ጋ ቀን ከሌት በራሴ አለም ስዳራ የኖርኩ መሆኔን ቢያቅብኝ እንኳን ገዳም አብሮኝም ቆሞ ለመታየት ያፍርብኝ ነበር አንተ ያሬድ ተነስ ሰአቱ እረፈደ ነው። ውጣ እንጂ...አለ።(ዛሬ የቁርጥ ቀን ነው።ገዳም ከመሄዱ በላይ የሚፈታተነኝን ግለ ወሲብ የት ጥዬው እንደምሔድ ጨንቆኝ ስገላበጥ ነው ያደርኩት እ....እሺ ይኸው ወጣሁ(ቦርሳዬን ሸክፌ ተከተልኩት።ለአመታት ልወጣበት ካልቻልኩት ድብቁ ሱስ የሚገላግለኝ ሀይል እንደሌለ አምኛለሁ። ተውኩት ስል እየመጣ፤ የሀጥያት ሀፍረት ሲያከናንበኝ ለአመታት ቆይቶብኛል።አንዳንዴ ግልግል ማለትም ያምረኛል.... ሰውዬ ውረድ እንጂ ምነው ዛሬ ፈዘካል....ከረጅም የፒስታ መንገድ በኋላ በጫካ የተከበበች መሀሪት ማርያም ቤተክርስትያን ደረስን።ጫማ ማድረግ የለም።ምግብ የለም። ስልክ አይገባም።ንሰሐ ሳይገቡ መውጣት...(ገና ከበሩ የግቢው ዘብ ህጉን ሲዘረዝረው ልቤ እንደ ሰም ቀለጠች።ስልኬ ላይ በድፍረት የተሸከምኳቸው የነውር ምስሎሽ በአይኔ እየዞሩ ስልኬን አስረክቤ ወንድሜን ተከትዬ ገባሁ...... "አረ አለም በምን ጣዕሟ" እያልኩ እያማረርኩ ነበር የመሸልኝ።ከተማ ጥዬው የመጣሁት ዝሙት ገዳም ስገባ ጭራሽ ያቅበዘብዘኝ ይዟል።ከፀሎቱ ይልቅ ዝሙት አእምሮዬን ወጥሮት የአንድ ሰአቱን ፀሎት እንደጨረስን ስሮጥ ወደ ጫካው ወረድኩ።ሱሴን ላስታግስ...በዝሙት ልወድቅ....እንደገና ደጁ ልበድል...... ሱሪህን ፍታው....!! አረ ተው ፈጣሪን ፍራ!! እዚህ ጨለማ ማን እንዳያይህ ነው!? ከውስጤ ጋ ትግል እየገጠምኩ ከተራራው ቅጠል እያንኮሻኮሸ የሚወርድ የአውሬ ድምፅ ስሰማ ሱሪዬን እየጎተትኩ ወደ ማደሪያው አመለጥኩ...... ጎረምሳው ና እስቲ እቺን ውሀ አድርስልኝ...(ከኪዳን ስንመለስ ጎልመስ ያሉ መለኩሴ ከሰው መሀል ጠሩኝ እሺ አባቴ ችግር የለም..... ባዶ እግሬን ሸንከል እያልኩ ለመለኩሴው ውሀውን በሩ ላይ አድርሼላቸው እንደዞርኩ ሳትገባማ አትሄድም።ና ግድ የለም ጦም ቢሆንም ትንሽ እረፍት አድርግ..... ኦና የሆነ።ጨለማ የወረሰው ቤት ተከትያቸው ገባሁ።እጣን እጣን ይሸታል።በቆርቆሮው ቀዳዳ የሚገባው ጨረር ቀይ ረጅም መጋረጃቸው ላይ ስላረፈ የሚታየው እሱ ብቻ ነው።የተደገፍኩበት ግድግዳ በምርጊት የቀረ የጭቃ ቤት መሆኑ ያስታውቃል።መሬቱም አባጣ ጎርባጣ አቧራማ መሆኑ እግሬ በዳበሳ ሰልሎታል.... ልጅ ያሬድ ተጫወት (አሉ ከጨለማ ውስጥ ለስለስ ያለ ድምፅ አውጥተው በስመአብ ወወልድ።አማተብኩ።ፈራሁ።ስሜን ማን ነገራቸው...??? አይዞህ እንግዲህ የመለኩሴ ቤት።እስቲ እቺን ገመድ ያዛት ልጄ አሉ ጨረሩ እጃቸው ላይ ሲያርፍ አረንጓዴ ገመድ አይቼ ተቀበልኳቸው ምን ላድርገው አባ??? አንገትህ ውስጥ አጥልቀው አልገባኝም።ለምን??ልላቸው ብዬ ገዳም መሆኑ ትዝ ብሎኝ እጄ እየተንቀጠቀጠ አንገቴ ውስጥ ከተትኩት።የሆነ ነገር ነብሴን እየጨነቃት ገመዱ እየተሳበ እየጠበቀ ሲመጣ ይታወቀኛል..... አ....አባ ም...ምንድነው??አልኳቸው የሞት ሞቴን ትንፋሽ እያጠረኝ ።እሳቸው ጋ ግን ከማጥበቅ ውጪ መልስ የለም አባ እያነቁኝ ነው።ገመዱን አስለቅቁኝ አባቴ.....(መልስ የለም አባ ልሞት ነው...(ትንፋሼ እየተቆራረጠ በግድ አወራሁ።ገመዱ እየገዘገዘኝ ደምስሬ እየተወጠረ የጣሬን ገመዱን ይዤ በመጨረሻ አቅሜ... አ....አባ (ስል ገመዱ ድንገት ሲረግብ እኩል ሆነና ትንፋሼን እየለቀቅኩ ተነስቼ ለማምለጥ ቃጣኝ ቁጭበል!! እንዴ ምንድነው ከኔ ሚፈልጉት?? ምን አድርግ ነው ሚሉኝ ቆይ.... ምንም አላልኩህም።ሞት እንዴት እንደሆን በትንሹ ላሳይህ ብዬ ነው።ልጅ ያሬድ ከመጣህ ቀን ጀምሮ አውቅሀለሁ ወንድምህ አንተን እዚህ ሲያመጣህ ተማክረን ነው።አየህ በመጀመርያ ቀን ንሰሐ ግባ ሲልህ አሻፈረኝ ብለካል ነገሩ በግድ ስለማይሆን ተውንክ።አንተ ግን ሌላ በደል.... ሌላ በደል!??? አዎ እንግዲህ እዚ ድረስ መጥተህ ከምትጠፋ ብነግርህ ይቀላል።ያንተን ችግር እኔም ወንድምክም እናቀዋለን።ባለፈው በለሊት ጫካ ውስጥ ከራስህ ስትታገል እንደ አውሬ ጩኼ ያባረርኩህ እኔ ነኝ።አስተውል ያሬድ ቅድም ገመዱን ስሰጥህ ቀለል አርጌ ነበር ሸምቀቆው እየጠበበ ሲመጣ ግን መተንፈስ አቃተህ።ግለ ወሲብም እንዲህ ነው።በተዘዋዋሪ በቀላሉ ትገባበትና እየጠበቀ ሲመጣ ግለ ሞት እራስን በፈቃደኝነት በነብስም በስጋም ማጥፋት ይሆናል።እራስህን ብቸኛው ሀጥያተኛ አድርገህ አታስብ ከመድሀኒቱ ቀድመህ ስለበሽታው ካላወቅክ አትድንም።መተፋፈሩ ይበቃል ከዚህ በላይ ሰይጣን እንዲያዋርድህ አትፍቀድ።ለመንፃት ሳትሰለች ተጠመቅ ንሰሐ ግባ ሰይጣን የደበቅክለትን ነውሩን በእግዜር ፊት ስትገልጥበት እግዚአብሔር ደሞ ከሰይጣን የዘማዊነት አሰራር ይከልልካል።አሁንስ ልጅ ያሬድ ምን ትለኛለህ አባ ለንሰሐ መች ልምጣ...እንዲ መሞት አልፈልግም።(ሲሰንፍ የነበረው ልቤ ያዋረደኝን ሰይጣን ለመጣል ሲነሳሳ ለእግዜር ደሞ ሲብረከረክ ተሰማኝ የመዳን ቀን ዛሬ ነው ልጄ ከመጣህ አሁኑኑ ሀጥያትህን ተናዘህ ሂድ...

ለብዙ ሰው ይጠቅማል #ሼር
https://t.me/meazasenay

መዓዛ ሠናይ

24 Dec, 15:30


አንብቡት እና ሼር አድርጉት።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

መዓዛ ሠናይ

18 Dec, 06:12


ታህሳስ9 የስማቸው ትርጓሜ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ አንድም የክርስቶስ እስትንፋስ የሆነ ጻድቁ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ የተወለዱበት አመታዊ ክብረ በዓል ነው
ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ያካፍለን

መዓዛ ሠናይ

12 Dec, 07:52


ታህሳስ 3
እመቤታችንን 3 አመት ካሳደጓት በኋላ ቅድስት ሐና ለባሏ ለቅ.ኢያቄም ልጃችንን ለቤተ እግዚአብሔር እንስጥ ቤተ እግዚአብሔርን ልታገለግል እንጂ በዚህ አለም እኛን ልታገለግል እንዳልተሳልን አስብ አለች
ቅ.ኢያቄምም ደስ ብሎት ወደ ቤተ እግዚአብሔር ወሰዷት ካህናትም ወጥተው ተቀበሏቸው በአንብሮተ እድም ባረኳቸው
ዳግመኛ መልአኩ ቅ.ፋኑኤል እመቤታችንን የመገበበትና
አቡነ ዜና ማርቆስ ያረፉበት አመታዊ ክብረ በዓል ነው
ከእመቤታችንና ከሁሉ ቅዱሳን በረከት ረድኤት ያካፍለን ።

መዓዛ ሠናይ

08 Dec, 02:49


🏆አስደሳች ዜና ለቻናል 🏵wner🏆.
🎗🎗🎗🎗🎗

የቻናሎ ሜምበር አላድግ ፣ አልጨምር ብሎቦታል። እንግዲያውስ የምሥራጅ አለን

በአጭር ጊዜ ውስጥ የቻናሎን ሜምበር የሚያሳድግ ምርጥ ዌቨር " ማኅቶት ፕሮሞሽን " ይዘንሎ መጣን።


ከ5ሺ ሜምበር በታች ያለው ቻናል ለጊዜው እደግመዋለሁ ለጊዜው አንቀበልም።

በተጨማሪ መንፈሳዊ ቻናል ብቻ‼️‼️‼️

ለመመዝገብ ከስር ያለውን ይጫኑ🤲
◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
█ ✞ 𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ✞ █
◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢

መዓዛ ሠናይ

03 Dec, 12:46


"ከሁለቱ የጽድቅ እንቅፋቶች እናስተውል"!

       ፩.ጸድቄአለሁና
       ፪. አልጸድቅም

ጸላኤ ሠናያት ሰውን የሚጎዳበት ሁለት ወጥመዶች  አሉት። አንዱ ጸድቂያለሁ ማሰኘት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አልጸድቅም ማሰኘት ነው። በሁለቱም ምክንያቶች ጽድቅ መሥራት አይቻልም። ጸድቄያለሁ የሚያሰኛቸው መናፍቃንን ነው። ለምን ሲባሉ ጌታን እወደዋለሁና ይላሉ። አምናለሁና ይላሉ።

ጌታን ስለምወደው ጸድቄያለሁና ጽድቅ አልሠራም የምትል ከሆነ የምትድን አይምሰልህ። ለምን ትለኝ እንደሆነ ጌታ ራሱ በመውደድ ብቻ አላዳነንምና። እወዳችሁአለሁና ዳኑ ብሎ በዙፋኑ ተቀምጦ ትእዛዝ ሰጥቶ አልቀረም።
ወዶ ምን አደረገ ትለኝ እንደሆነ፦

ምሉዕ ስፉሕ  ጌታ በጠባብ ደረት በአጭር ተወሰነ። ሰማይን በደመና የሚሸፍነው በጨርቅ ተጠቀለለ።
ከነደ እሳትነቱ የተነሳ ኪሩቤል የሚንቀጠቀጡለት በብላቴናዋ በድንግል ማኅፀን ተወሰነ። ምድርና ሰማይን የሚያቀልጣቸው የክብር መብረቅ በክንደቿ ታቀፈችው። በፊቱ የእሳት ጎርፍ የሚንቆረቆርለትን በከንፈሮቿ ሳመችው። አገልጋዮቹን የእሳት ነበልባል የሚያደርገውን  እንዳይበርደው እንስሶች አሟሟቁት። አዳራሹን በመብረቅ የሠራው በበረት ተኛ። ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን የተሠወረው ቅጠል ለበሰ። የስደተኞች ተስፋ ተሰደደ። የሰማይና የምድር አባት በየጥቂቱ አደገ። ምድርን በደሙ የሚያነጻት ማይን ያነጻት ዘንድ ተጠመቀ። የዓለማት ዓለም ማደሪያ አጥቶ ቀን በምኩራብ ሌሊት በተራራ ተንከራተተ። የመምህራን አምላክ ለማይሰማ ሕዝብ በሰው ቃል ዝቅ ብሎ አስተማረ። ለመምህራን  በሞገስ መከበርን የሰጠ እየተሰደበ አስተማረ። መላእክት እያመሠገኑ ለማመስገን የሚሳሡለት የአይሁድን ጽርፈት ሰማ። ለተበደሉት የሚፈርድላቸው በፍርድ አደባባይ ቆመ። ከፍርድ የሚያድነው ተፈረደበት። እስረኞችን የሚፈታ ታሰረ። ሰውን ወደ ሰማይ በልዕልና ስቦ የሚያሳርገውን ጎተቱት። መንሥኤ
ሙታኑን ጣሉት። ቁስለኞችን የሚፈውሰውን ቸንክረው አቆሰሉት። ራሱን ሊያለብስ የመጣውን አራቆቱት። ርኩሳኑን በደሙ ያጠበውን ርኩስ ምራቅ ተፉበት።የኃጢአትን እሾህ የሚነቅለውን የእሾህ አክሊል ደፉበት። የሕይወትን ውኃ መራራ አጡጡት። ዲያብሎስን በመስቀሉ የቸነከረውንበጦር ወጉት። ሕይዎት እርሱን ሰቅለው ገደሉት። የምድር መሠረት የሰማይን ጽንዓት በምድር ውስጥ ተቀበረ። ትንሣኤና ሕይወት ነውና ሞትን በሞቱ ደምስሶ ተነሣ!

ወደጄ ሆይ ጌታን ስለምወደው ስለማምነው ጸድቄያለሁ የምትል ከሆነ እንዲህ ብሎ ሲጠይቅህ ምን ትመልስለታለህ? ልጄ ሆይ እኔ አንተን ወድጄ ተሰቀልኩልህ።አንተ እኔን ወደህ ምን ሆንህልኝ?በዚህ ጊዜ ስለምወድህ ትጋት ትቼ ሰነፍሁልህ ልትለው ነው? ሁሉን የሚችል አምላክ በቃሉ ብቻ ማዳን እየቻለ ነገር ግን ፍቅሩን በመከራ ገልጦ ካዳነ ሰው ለአምላኩ ቃል ብቻ እንዴት ይበቃዋል?

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወረቅ እንዲህ ሲለን እንስማ!         
"ኢትበል እፈቅድ ባሕቲቱ=ወዳጄ እወዳለሁ ብቻ አትበል"ዋናተኛ ዋና እወዳለሁ በማለት ወንዝ ይሻገራልን?ሐናጺ መሆን የሚሻ ቤት መስራት በመፈለግ ብቻ ሙያውን ሳይለምድ ቤት መስራት ይችላልን? መርከበኛ መሆን የሚሻ መርከብ መቅዘፍን ሳይለምድ ሊቀ ሐመር መሆን ይችላልን?ጸሐፊስ መጻፍ በመፈለግ ብቻ ፊደል ሳያውቅ መጻፍ ይችላልን? መንጻት የሚፈልግስ ሳይታጠብ በመፈለግ ብቻ ይነጻልን? የተራበስ ስለ ምግብ በማሰብ ብቻ ይጠግባልን? ጽድቅንስ በመሥራት እንጅ በመውደድ ብቻ መዳን ይቻላልን?

ሁለተኛው ደግሞ  አልጸድቅም ማለት ነው።
እንደዚህ የሚያሰኛቸው ደግሞ ምእመናንን ነው። መጀመሪያ ጥቂት ጥቂት እያለ ከጽድቅ ስራ ያወጣቸዋል። ከዚያ እግዚአብሔር መሐሪ ነው እያሰኘ ኃጢአት እንዲጨምሩ ያደርጋቸዋል። ከዚያ ወዲያ ፍጹም ኃጢአተኛ ሲሆኑ በኋላ እንዳይመለሱ መቼም አልጸድቅ ያስብላቸዋል።

የእመቤ ታችን ልጆች ንቁበት። ላልጸድቅ ሲያሰኛችሁ ክርስቶስ የውበት ባሕር ነው ብላችሁ መልሱለት። በአንዲት ውኃ ብዙ ሰዎች ቢታጠቡ ትደፈርሳለች። ክርስቶስ ግን የጎሰቆሉ ሁሉ ወደ እርሱ ገብትው ሲነጹ የእነርሱ ጉስቁልና እርሱን የማይለውጠው የምሕረት ባሕር ነውና እየገባን እንንጻ! በጭቃ የተለወሰውን ወርቅ ወልውለው አጥርተው ለአክሊልነት ያበቁታል። በእግር ከሚረገጥ ጭቃ በታች የነበረውን አጥርተው ከራስ በላይ ያውሉታል። ከምእመንነት በታች ወርዶ ጌታውን የካደውን ቅዱስ ጴጥሮስን በንስሐ ጠርቶ ርእሰ ሐዋርያት እንዳደረገው  አትዘንጋ! እግዚአብሔር ቸር ነው ብሎ ኃጢአት መስራት ነው እንጅ ክፉ
እግዚአብሔር ቸር ነው እያሉ መመለስ ያድናል።

አሁንም ተስፋ ቆርጠን አንዘግይ! ለመመለስ ያብቃን!ደግሞ ማንንም የማትጸየፍ እናት አለችን።                                    ምን ብንገዳገድ እርሷን እየተመረኮዝን እንነሳ!( በትረ ሃይማኖት ድንግል ማርያም)
ርዕሰ_ሊቃውንት_አባ_ገብረ_ኪዳን

መዓዛ ሠናይ

02 Dec, 05:26


ኅዳር ፳፩
ጽዮን ማርያም

ኅዳር ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓሏ መታሰቢያ ነው።

“ታቦተ ጽዮን” የሚለውንም ስያሜ ያገኘችው ጽዮን ተብላ በምትጠራው የእስራኤል ከተማ ስም ነው፡፡ ጽዮን ማለት ተፀወነ፡ ተጠጋ፣ ተማጠነ ማለት ነው፡፡ ክቡረ ዳዊትም ጽዮንን አምባ፣ መጠጊያ አድርጎ ብዙ ጠላቶቹን ተዋግቶ አሸንፎ ድልን ተጎናጽፏል።

ጽዮን የተባለችው የታላቁ የዳዊት ከተማ የተገፉና የተበደሉ ሕዝቦች ሁሉ እውነተኛ ፍርድ ለማግኘት፣ ተሰብስበው የሚሰነብቱባት ከተማ ስለነበረች፣ ጽላተ ሙሴም በዚያ ስለነበረች በርሷ ተማጽነውም ችግራቸው ሰለሚቃለል ታቦቷ “ታቦተ ጽዮን” ተብላለች፡፡

ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን፣ ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች። "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው። "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው።

"ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው። ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል። ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው። በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን። (2ቆሮ.6፥16 ፣ ራዕይ.11፥19)

የአምላክ ማደሪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በቃል ኪዳን ታቦት ትመሰላለች ይኽቺም ፦
✿ የእግዚአብሔር የጌትነቱ መግለጫ የኾነችው፤
✿ በፍልስጥኤም ይመለክ የነበረ ጣዖትን ቀጥቅጣ ያጠፋች፤
✿ በድፍረት ሊነካት የሞከረ ኦዛን የቀሰፈች፤
✿ በታላቅ ክብር ወደ ሀገሯ ስትመለስ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በታላቅ መንፈሳዊ ደስታ በፊቷ የዘመረላት ፤
✿ ልጁ ሰሎሞንም ታላቅ ቤተ መቅደስ ሠርቶ በክብር ያኖራት ናት፡፡

ጌታ የታቦቷን አሠራር ሲነግረው "ሽምሽር ስጢን ከሚባል ከማይነቅዝ እንጨት ቀርጸኽ አብጅ ከታች እንደ ዙፋን አራት እግር አውጣለት ሞላልነቱን ኹለት ክንድ ከስንዝር ቁመቱ ክንድ ከስንዝር ወርዱን ክንድ ከስንዝር ኹለት ክንድ ከስንዝር ምስሃል ለዚኽ ቁመት የለውም አራት ቀለበት ኹለት ሙሎጊያ አበጅለት አፍአውን ውስጡን በንጹሕ ወርቅ ለብጠው በምስማኩና በምስማኩ ኹለቱን ኪሩቤል እንደሚናተፉ አውራ ዶሮዎች አንገታቸውን ደፋ አድርገኽ በላይ ሣልበት ዙሪያውን ፈለግ አውጣለት ብጽብጽ ወርቅ አፍስበት ጽላቶቹን በውስጡ አኑር" ብሎታል፡፡
ይኸውም ምሳሌ
ታቦት ፡- የእመቤታችን
ወርቅ፡- የንጽሕናዋ የቅድስናዋ
ታቹ መቀመጫው ፡- የንጽሓት እንስት
ላዩ መግጠሚያው ፡- የንጹሓን አበው
ግራ ቀኙ ፡- የሐና የኢያቄም
ወደ ውስጥ የገባችው:-የድንግል ማርያም ያቺ በመኻከላቸወም እንደኾነች እመቤታችንም ከሐና ከኤያቂም ለመገኘቷ ምሳሌ ነው።
ኹለት ክንድ ከስንዝር:- ከአዳም እስከ ኖኅ ባለው ዘመን 2260 ዘመን ይመስላል ይኸውም በኖኅ ዘመን አርአያ ድንግል ታቦተ ኖኅ ለመገኘቷ ምሳሌ፡፡
አንድ ክንድ ከስንዝር ቁመቱ :- ከኖኅ እስከ  ሙሴ ባለው ዘመን ይመስላል ይኸውም 1600 ዘመን ነው። በዚህ ዘመን አርአያ  ድንግል ጽላተ ሙሴ  ለመገኘቷ ምሳሌ ነው፡፡
አንድ ክንድ ከስንዝር ወርዱ:- ከሙሴ እስከ  እመቤታችን ባለው ዘመን ይመስላል ይኽውም 1640 ዘመን ይኾናል ይኽ በኾነ አርአያ ድንግል ታቦተ ኖኅ አርአያ ድንግል ጽላተ ሙሴ ምሳሌዎቿ የሚሆኑ አማናዊት ድንግል ማርያም ለመገኘቷ ምሳሌ ነው፡፡
አራቱ ቀለበት:- የአራት ወገን ንጽሕናዋ  ምሳሌ ይኸውም ክርእይ /ኃጢአትን ከማየት/፤ ከሰሚዕ/ኃጢአትን ከመስማት/ ፤ ከገሲስ/በእጅ ዳሰሶ ኃጢአትን ከመሥራት እና ከአጼንዎ /የኃጢአት መዐዛን ከማሽተት/ እመቤታችን ከነዚኽ ኹሉ ተጠብቃለችና
ኹለቱ ቀለበት:- የፍቅረ እግዚአብሔርና  የፍቅረ ቢጽ ምሳሌ
ኹለቱ ሥዕለ ኪሩቤል:- የጠባቂ መልአክ  የቅዱስ ሚካኤልና የአብሳሪ መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ምሳሌ ናቸው ይኽውም የብሉይ ሊቀ ካህናት በዓመት አንድ ቀን ገብቶ ከኹለቱ ኪሩቤል መካከል ቃል ሰምቶ ይወጣ ነበር ቅድስት ድንግል ማርያም በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ተጠብቃ ከቅዱስ ገብርኤል ቃል ሰምታ አካላዊ ቃልን በግብረ መንፈስ ቅዱስ ያለ ዘር ያለ ሩካቤ ፀንሳ ተገኝታለችና።

ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ ይኽንን መንፈሳዊ ምስጢር በጥልቅት በመመርመር ድንግል ማርያምን ፡-
👉በምስጢር የተመላች ታቦት
👉 እሳትን የተመላች ታቦት
👉የቅዱስ ቃል ታቦት
👉የቃል ኪዳን ታቦት በማለት ገልጿታል፡፡

ኅዳር 21 ቀን የሚከበረውም የእመቤታችን ምሳሌዎች የተገለጡበት እና የተለያዩ ሥራዎች የተሰሩበት ዕለት ስለሆነ ነው፡፡ እነዚህም፡-

1. ነቢዩ ዘካርያስ ሁለንተናው ወርቅ የሆነ፣ የዘይት ማሰሮ በራሱ ላይ የነበረበትንና ሰባት መብራቶች ያሉትን መቅረዝ ሲያበራ ያየበት ዕለት ነው፡፡ ዘካ. 4፤1-2። ዘካርያስ ያየው ብርሃን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ ዮሐ. 8፤12፡፡ ይህ ብርሃን የታየባትና የተገለጠባት መቅረዝ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፡፡ ብርሃን መቅረዝ እንዲያዝና እንዲገለጥ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ተገልጦልናል፡፡ ጨለማ ዓለምን አብርቷል፡፡ ብርሃን ክርስቶስን ወልዳለችና እርሷም እመ ብርሃን / የብርሃን እናት/ ትባላለች፡፡

2. ታቦተ ጽዮን ዳጎንን ገልብጣ በመጣል ኃይሏን የገለጠችበት ዕለት ነው፡፡ በፍልስጥኤማውያን ተማርካ ቤተ ጣዖት ወስደው ከጣዖታቸው ከዳጎን በታች አስቀምጠዋት ነበር፡፡ ታቦተ ጽዮን ግን በላይዋ ያለውን ዳጎንን ገልብጣ ጥላ እርሷ ከላይ ተቀመጠች፡፡ በታቦት የሚገለጠው የእግዚአብሔር ኃይል ነው፡፡ ምክንያቱም በታቦቱ ላይ ያለው ሕገ እግዚአብሔርና ስመ እግዚአብሔር ነው፡፡ የእግዚአብሔር ስም የጸና ክንድ ነውና ሁሉን ያሸንፋል። ስለዚህ ምንም እንኳ ለጊዜው ስትማረክ ደካማ ብትመስልም መማረኳ ግን ኃይሏን ለመግለጥ፣ ለአሕዛብ የጣዖትን ከንቱነት የታቦትን ክቡርነት ለመግለጥ ነበር፡፡

3. ቀዳማዊ ምኒልክ ታቦቱን ይዞ አክሱም የገባበት፣ ንግሥት ሳባ ታላቅ በዓል አድርጋ የተቀበለችበት፣

4. አብረሃ ወአጽብሐ በአክሱም ከተማ 12 ቤተ መቅደስ ያለው ቤተ ክርስቲያን በአስደናቂ ሁኔታ ሠርተው ከጨረሱ በኋላ ቅዳሴ ቤቱን ያከበሩበት፣ እንዲሁም

5. በ9ኛው መ/ክ/ዘመን ዮዲት ክርስትና ለማጥፋት በተነሳች ጊዜ በእርሷ ምክንያት ታቦተ ጽዮን ወደ ዝዋይ ሐይቅ የተሰደደችበት፡፡ በኋላም የሰላሙ ዘመን ሲመጣ ተመልሳ አክሱም የገባችበት በዚሁ በኅዳር 21 ስለሆነ በእነዚህ በተደራራቢ ታሪኮች ምክንያት በየዓመቱ በደመቀ ሁኔታ ይከበራል “ኅዳር ጽዮን በአክሱም ጽዮን” የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡

የእመቤታችን ልመናዋ ክብሯ አማላጅነቷም ከእኛ ከህዝበ ክርስቲያን ጋር ለዘለዓለም ጸንቶ ይኑር! አሜን!

መዓዛ ሠናይ

30 Nov, 09:10


⛪️የኢኦተቤክ አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ⁉️

👏 የቸብቸቦ መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
🎻 የበገና መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
👑 የቅዱሳን መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
⛪️ የንግስ መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
🤲 የምስጋና መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
🙏 የንስሐ መዝሙራት
📖▓⇨→Audio ⇨ግጥም
💍 የሠርግ መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
🌦 ወቅታዊ መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
🇪🇹 ለአገር የተዘመሩ
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም


👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
https://t.me/+lVXHSARuil5kZDU0
https://t.me/+lVXHSARuil5kZDU0
https://t.me/+lVXHSARuil5kZDU0
👆🏽🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔺‌‌👆🏽

መዓዛ ሠናይ

26 Nov, 07:10


"ምጽዋት የፊት መብራት ናት፡፡ አንድ ሰው በጨለማ ሲጓዝ ከኋላው መብራት ቢያበሩለትም እንኳ ከፊቱ የሚቀድመው የገዛ የአካሉ ጥላ እንቅፋት እየሆነበት ይጥለዋል፡፡ ወደ ፊት ያለውን መንገድ አጥርቶ እያየ ያለ ስጋት ለመሄድ እንዲችል የግድ የፊት መብራት ያስፈልገዋል፡፡ ጾም፣ ጸሎት እና ሌሎች መንፈሳዊ ትሩፋት እንደ ኋላ መብራት ናቸው፡፡ የፊት መብራት የተሰኘች ምጽዋት ካልታከለችባቸው እነዚህ ብቻቸውን ዋጋን አያሰጡንም፡፡ ከምጽዋት በላይ ታላቅ ነገር እንደሌለ ልንረዳ ይገባል፡፡"

ኢትዮጵያዊው አፈወርቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

መዓዛ ሠናይ

25 Nov, 07:57


"አንድ ሰውስ እንኳ ድኻ ነኝ ወይም ድኻ አደግ ነኝ ብሎ ተስፋ አይቁረጥ፤ ከድኻ ማኅበረሰብ የተገኘሁ ነኝ ብሎ ማንም አይዘን፤ ከአንካሳ ልብና ከሰነፍ ሕሊና በቀር የሚያሳዝን ምንም ምን የለምና። በጎ ምግባርን እንዳንይዝ የሚከለክለን አንዱና ብቸኛው ዕንቅፋት መንፋሳዊ ድካም እና የሕሊና ዓቅመ ቢስነት እንጂ ሌላ ምንም አይደለምና።

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ውዳሴ ጳውሎስ መጽሐፍ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)

መዓዛ ሠናይ

24 Nov, 15:54


#ጾመ_ነቢያት

እግዚአብሔር አምላካችን ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ መልበሱን፣ ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ወደ ግብጽ ግብር መሰደዱን፣ በባሕረ ዮርዳኖስ መጠመቁን፣ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ማብራቱን፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ሲል ልዩ ልዩ ዓይነት መከራ መቀበሉን፣ መሰቀሉን፣ መሞቱን፣ ከሙታን ተለይቶ መነሣቱን፣ ማረጉንና ዳግም ለፍርድ የሚመጣ መኾኑን በአጠቃላይ የማዳን ሥራውን በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው አስቀደመው በትንቢት ተናግረዋል፡፡ ትንቢቱ ተፈጽሞ ለመመልከትም ‹‹አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሣ፤ እጅህን ላክ›› እያሉ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው ኾኖ ዓለምን የሚያድንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት እያሰሉ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ የእግዚአብሔርን ሰው መኾን ሲጠባበቁ የኖሩት የነቢያት ትንቢትና ጸሎትም በእግዚአብሔር ሰው መኾን ፍጻሜ አግኝቷል፡፡

ይህን ምሥጢር በማሰብ በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ቀን ጀምሮ እስከ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ዋይዜማ ድረስ እንድንጾም አባቶቻችን መምህራነ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ሠርተውልናል፡፡ ይህ ጾም፣ ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ሲኾን፣ በስያሜም #ጾመ_ነቢያት (የነቢያት ጾም) እየተባለ ይጠራል፡፡ ወቅቱ ለአዳም የተነገረው የድኅት ተስፋ የተፈጸመበት ስለ ኾነም #ጾመ_አዳም (የአዳም ጾም) ይባላል፡፡ ስለ እግዚአብሔር ሰው መኾን በስፋት ትምህርተ ወንጌል የሚሰጥበት ወቅት በመኾኑም #ጾመ_ስብከት (የስብከት ጾም) የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት በመኾኑ ደግሞ #ጾመ_ልደት (የልደት ጾም) በመባል ይታወቃል፡፡ በተጨማሪም #ጾመ_ሐዋርያት እየተባለ ይጠራል፤ ምክንያቱም ቅዱሳን ሐዋርያት "በዓለ ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብረዋለን፤ በዓለ ልደትንስ ምን አድርገን እናከብረዋለን?" በማለት ነቢያት በጾሙበት ማለት ከልደተ ክርስቶስ በፊት ባለው ወቅት ጾመዋልና፡፡

በሌላ አጠራር ይኸው ጾመ ነቢያት #ጾመ_ፊልጶስ (የፊልጶስ ጾም) በመባል ይታወቃል፤ ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በአፍራቅያ እና አውራጃዋ ዅሉ እየተዘዋወረ በጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ወንጌልን በማስተማር፣ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ብዙዎችን ወደ አሚነ እግዚአብሔር ሲመልስ ቆይቶ ትምህርቱን በማይቀበሉ የአፍራቅያ ሰዎች አማካይነት በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን ሊቀብሩ ሲሉም ተሰወረባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ በዓት ዘግተው፣ ሱባዔ ገብተው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው የሐዋርያውን ሥጋ ይመልስላቸው ዘንድ እግዚአብሔርን ቢለምኑት ልመናቸውን ተቀብሎ ሱባዔ በያዙ በ፫ኛው ቀን የቅዱስ ፊልጶስን ሥጋ (በድን) መልሶላቸው በክብር አሳርፈውታል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ የሐዋርያውን ሥጋ ካገኙ በኋላ እስከ ጌታችን ልደት ድረስ ጾመዋል፡፡ ስለዚህም ጾመ ነቢያት 'ጾመ ፊልጶስ' እየተባለ ይጠራል፡፡

ከዚሁ ዅሉ ጋርም ወልደ አምላክ ክርስቶስን በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንደምትፀንሰው፣ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ካበሠራት በኋላ "ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ ፀንሼ ምን ሠርቼ እወልደዋለሁ?" በማለት ጌታችንን ከመውለዷ አስቀድማ እመቤታችን ጾማዋለችና ይህ ጾም #ጾመ_ማርያም በመባልም ይታወቃል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ በጾመ ነቢያት፣ ነቢያትም ሐዋርያትም፣ ቀደምት አባቶቻችንም ጾመው በረከት አግኝተውበታል፡፡ እኛ ምእመናንም የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት አምላክ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በረከት እንዲያሳትፈን በዚህ በጾመ ነቢያት ወቅት በጾም በጸሎት ተወስነን እግዚአብሔርን ልንማጸነው ይገባናል፡፡

      ጾሙን ጾመ ሥርየት፤ ጾመ መድኃኒት ያድርግል!

ምንጭ፡–
#ዲያቆን_ኤፍሬም_የኔሰው -ማኅበረ ቅዱሳን ብሎግ
ፍትሐ ነገሥት ንባቡና ትርጓሜው፣ አንቀጽ ፲፭

መዓዛ ሠናይ

24 Nov, 04:29


⛪️የኢኦተቤክ አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ⁉️

👏 የቸብቸቦ መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
🎻 የበገና መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
👑 የቅዱሳን መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
⛪️ የንግስ መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
🤲 የምስጋና መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
🙏 የንስሐ መዝሙራት
📖▓⇨→Audio ⇨ግጥም
💍 የሠርግ መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
🌦 ወቅታዊ መዝሙራት
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም
🇪🇹 ለአገር የተዘመሩ
📖▓⇨→audio ⇨ግጥም


👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
https://t.me/+lVXHSARuil5kZDU0
https://t.me/+lVXHSARuil5kZDU0
https://t.me/+lVXHSARuil5kZDU0
👆🏽🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔺‌‌👆🏽

መዓዛ ሠናይ

22 Nov, 09:23



.....የቀጠለ

ድርሳን በእንተ ማርያም ኃጥእት
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን አምስት)

እርሷም በጸና ሃይማኖት ሆና አንተ ሰይጣን እስካሁን በኃጢአትና በበደል እንድኖር አድርገኸኛል፤ በእኔም ላይ ኀፍረትና ጕስቊልናን አምጥተህብኛልና፤ ዛሬ ግን እነሆ የማያልቅ ሀብትንና ክብርን ወደሚሰጠኝ በመንግሥተ ሰማያትም ርስትን ወደሚያድልኝ እሄድ ዘንድ መጥቻለሁና አሁን ግን ከእኔ ራቅ ብላ መለሰችለት፡፡

ጠላት ሰይጣንም በሃይማኖት እንደጸናች ባየ ጊዜ ከእርሷ ሸሽቶ ኢየሱስ ክርስቶስን ለምሳ ወደ ጠራው ወደ ፈሪሳዊው ስምዖን ሄደ፡፡ ስምዖንንም ሐሳቡን ያውከው ጀምር፡፡ ነቢይ ቢሆንማ ኑሮ ይህቺ የምትዳስሰው ሴት ኃጥእት እንደ ሆነች ያውቅ አልነበረምን? እንዲል አደረገው፡፡

ጠላት ሰይጣንም ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከፍጹም ጸጋው ሊለያት ወዶ ይህንን አደረገ፡፡ እርሷ ግን በሃይማት ጸናች፤ ወደ እሱርም ሄደች፤ በሩም ተከፍቶ አገኘችው፤ ያለ ኀፍረትም ገብታ ከጌታ ዘንድ ደረሰች፡፡ የተመለከቷት ሁሉ አደነቁ፡፡ እርሷም እያለቀሰች ከእግሩ በታች ሰገደች፡፡ እግሩንም በዕንባዋ እያጠበች በራሷ ጠጉር ታብሰው እየሳመችም ሽቱ ትቀባው ነበር።

እሷም እንዲህ ትለው ነበር፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ፈጣሪ፣ የነፍስና የሥጋ አዳኝ፣ የሕይወት ውኃ ምንጭ መገኛ ሆይ ወደ ሴት ባርያህ ተመልከት:: አንተ በጎ ነገርን አደረግህልኝ እኔ ግን በደልሁህ፡፡ ዳግመኛም ሀብትን ክብርን ሰጠኸኝ እኔ ግን ትእዛዝህን አፈረስሁ፡፡ አቤቱ ጌታ ሆይ እንደ እንስሳ የሆንሁ ከእነርሱም እንደ አንዱ የተቈጠርሁ ድኃና ኃጢአተኛ እኔን ይቅር በለኝ፡፡ ከኃጢአት ቀንበር በታች ተይዣለሁና፡፡

አቤቱ ከጠላት እጅ አድነኝ፡፡ ቀላል የሆነ ቀንበርህንም እንድሸከም አድርገኝ፡፡ አቤቱ የምሕረትህን በርም ክፈትልኝ፡፡ ከአንተ ዘንድ ይቅርታህንና የኃጢአት ሥርየትን ተስፋ አድርጌ የመጣሁ እኔን አቤቱ ተቀበለኝ፡፡ ከዚህም በኋላ እንዲህ ብላ አሰበች፡፡ ነፍሴ ሆይ እንዴት መድኃኒትሽን አትፈልጊም? እነሆ መድኅን በዚህ አለና፡፡ ባለ መድኃኒቱ ሳለ ስለምን ፈውስን አትፈልጊም? የሕይወት ውኃ ምንጭ በፊትሽ እያለ ስለምን ከእድፈትሽ አትነጭም?

ዳግመኛም ከንቱ ነገር ስትመለከቱ የኖራችሁ ዐይኖቼ ሆይ እነሆ አሁን ጌታን ታዩት ዘንድ አደላችሁ:: የረከሰውን ስትዳስሱ የነበራችሁ መዳፎቼ እነሆ አሁን የሰማያዊውን ጌታ እግሮችን ትዳስሱ ዘንድ ተሰጣችሁ፡፡ ከመለኮቱ እሳት የተነሣ አትፈሪምን? እነሆ አሁን ከደዌሽ ሁሉ ይፈውስሻል፡፡ ከእድፈትሽ ኹሉም ያነጻሻል፡፡ ኃጢአተኛ ነፍሴ ሆይ አሁን ፈጽሞ ታላቅ ሞገስን አገኘሽ፡፡ ከነቢዩ ከዳዊት ጋራ ስላደረገልኝ ሁሉ ለእግዚአብሔር ምን እመልሳለሁ? እያልሽ ትዘምሪ ዘንድ ይገባሻል፡፡

ኃጢአተኛዋ ሴት ታላቅ ልቅሶን እያለቀሰች እንደዚህ እያለች ተናገረች፡፡ ከዚህም በኋላ የሴቶችን ድካም አስወገደች፡፡ ደፍራም የጌታን እግር ያዘች፡፡ በዕንባዋ ታርሰው በራሷ ጠጕርም ታብሰው ነበር፡፡ በጌታ ዘንድ በፊቱ ባለሟልነትን ያገኘሁ እንደሆነ ወደ እርሱ እንድቀርብ ያደርገኛል ስለ ክፉ ሥራዬ ከእርሱ ከአባረረኝ ግን ዳግመኛ በሕይወት አልኖርም ብላ አስቀድማ በልቧ አስባ ነበርና፡፡ የጌታችን የበዛው ይቅርታውና ምሕረቱም በእዚያ ከተቀመጡት ይልቅ እርሷን ወደ እርሱ አቀረባት፡፡

በእርሱ ዘንድም ታላቅ ባለሟልነትን ባገኘች ጊዜ ደፍራ ሽቱውን በራሱ ላይ አፈሰሰች፡፡ ከዚህም ሁሉ ጋራ ወደ እሱ መለመንን እና ማልቀስን አልተወችም፡፡ ጠላትም የጌታችን ፍጹም ሀብቱ በእሷ ላይ እንደ በዛ ባየ ጊዜ ታላቅ ቅናትን በእሷ ላይ ቀና፡፡ ተቆጥቶም በስምዖን ላይ አደረ፡፡ ሕሊናውንም አወከው፡፡ ነቢይስ ቢሆን ኑሮ ይህቺ የምትዳስሰው ሴት ኃጥእት እንደ ሆነች ባወቀ ነበር እንዲል አደረገው፡፡

ከዚህም በኋላ ጌታችን ስምዖን ስለ እሷ ያሰበው ሐሳቡ ከእርሱ እንዳልተሠወረ፣ ከእሱ ዘንድ መንቀፍን፣ ራስን ማጽደቅንና በኃጥአን ላይም መመካትን ያስወግድ ዘንድ ሊያስረዳው ወደደ፡፡ ዳግመኛም እግዚአብሔር አምላክ በደለኞችን ማዳን እንደሚችል ወደ እሱ ከተመለሱም ከኃጢአታቸው እንደሚያነጻቸው ያስረዳው ዘንድ ወደደ፡፡......

ይቀጥላል......
(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 105-151)

መዓዛ ሠናይ

22 Nov, 09:23



.....የቀጠለ

ድርሳን በእንተ ማርያም ኃጥእት
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን አምስት)

ይልቁንም ኃጢአታችንን እያመን የበደሉን ሰዎችንም ይቅር እያልን ከምሕረት፣ ከምጽዋት፣ በብሩህ ገጽ እና በንጹህ ሕሊና ከመፋቀር ጋር ነው እንጂ፡፡ ዕንባችንን እናፍስ፣ የኃጢአታችንንም እድፍ እንጠብ፡፡ ለደዌያችን ፈውስን ለኃጢአታችንም ሥርየትን እናገኝ ዘንድም ያችን ሴት እንምሰላት፡፡

ዳግመኛም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌል እንዲህ ብሏልና፡፡ እውነት እውነት እላችኋላሁ ከእናንተ ሁለቱ በዚህ ዓለም ስለሚሹት ነገር ቢተባበሩ ከሰማያዊ አባቴ ዘንድ የለመኑት ይደረግላቸዋል። ሁለት ወይም ሦስት ሆነው በስሜ ቢሰባሰቡ እኔ በዚያ በመካከላቸው እኖራለሁ፡፡

ስለዚህም ወደ እርሱ በሃይማኖት የሚመለሱትን ሰዎች ልመናቸውን እንደሚቀበል አስረዳን፡፡ ከኃጢአቷ በተጸጸተች በዚች ኃጢአተኛ ሴት ላይ እና በእሱ ዘንድ ታላቅ ባለሟልነትን ባገኙ በሌሎች ሰዎች ላይ እንዳደረገው፡፡

እናንተም ጌታችንንስ ዐይተነው ቢሆን ኖሮ ትእዛዙን አብዝተን በሠራን ነበር በማለት አታመካኙ። ይህ ሐሳብ ከሃይማኖታችሁ መጉደል የሚሆን ነውና፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ባለጠግነቱ እግዚአብሔርን በሚፈሩት ላይ በሁሉም ጊዜ ያድራልና፡፡ ራሳቸውንም ከርኵሰት ያነጻሉ፡፡

ስለዚህም እግዚአብሔር በግልጥ እንደ ታያቸው እንደ ተመረጠ እስጢፋኖስ እንደጥበኛው ቆርኔሌዎስም፤ የእግዚአብሔርን መንግሥት ትመለከቷት ዘንድ የተዘጋጃችሁ ሁኑ። እነርሱ ልባቸውን አንጽተዋልና ሕሊናቸው በጥበብ በራ፡፡ ከክፉ ሥራ ሁሉ እንሸሽ ዘንድ አግባብ ነው፡፡ ሰውነታችንና ሕሊናችንንም መንፈስ ቅዱስ ያድርብን ዘንድ ልናነጻ ይገባል፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዳደረባችሁ አታውቁምን? ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፡፡ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና ያውም እናንተ ናችሁ ብሎ እንዳስተማረን ሰውነታችንን ከርኵሰት እናነጻ ዘንድ ወደደ፡፡ ስለዚህም መንፈስ ቅዱስም በእኛ ላይ ያድር ዘንድ በመልካም ምግባር እንኑር።

ወደ ክፉ ሥራ ከተመለስን ግን እነሆ መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ይለያል፡፡ የአጋንንትም ማደሪያ እንሆናለን፡፡ ቅዱስ በቅዱሳን ላይ ካልሆነ በቀር በሌላ አያድርምና፡፡ ዳግመኛም እኔ ቅዱስ ነኝና በእናንተ ላይ አድር ዘንድ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ አለ፡፡

ዳግመኛም እግዚአብሔር ቅዱስ ነው በቅዱሳኑ ላይም ያድራል አለ፡፡ በክፉ ሥራ ለሚኖሩትና በኃጢአትና በአመፃ ላሉት ግን ቅዱስ ወንጌል ስለ እነርሱ እንዲህ አለ፡፡ ርኵስ መንፈስ ከሰው በወጣ ጊዜ ዕረፍት እየፈለገ ውኃ በሌለበት ቦታ ያልፋል፤ አያገኝም፡፡ በዚያ ጊዜም ወደ መጣሁበት ቤት እመለሳለሁ ይላል፡፡ ቢመጣም ባዶ ሁኖ ተጠርጎ ያገኘዋል፡፡ ከዚያም ይሄድና ከእርሱ የከፉትን ሰባት ሌሎችን አጋንት ከእርሱ ጋር ይወስዳል፡፡ ገብተውም በዚያ ሰው ይኖራሉ፡፡ ለዚያ ሰውም ከፊተኛው ይልቅ ኋለኛው ይብስበታል፡፡.....

ይቀጥላል......

(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 105-151)

መዓዛ ሠናይ

22 Nov, 09:23



......የቀጠለ
ድርሳን በእንተ ማርያም ኃጥእት
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን አምስት)

ስለዚህም ስምዖን ሆይ የምነግርህ አለኝ አለው፡፡ እርሱም መምህር ሆይ ተናገር አለው፡፡ ጌታም ለአንድ አበዳሪ ሁለት ተበዳሪዎች ነበሩት በአንዱ ዐምስት መቶ ዲናር በሁለተኛውም ኀምሳ ነበረባቸው፡፡ የሚከፍሉትም ቢያጡ ለሁለቱም ተወላቸው፡፡ እንግዲህ ከእነሱ አብልጦ የሚወደው የትኛው ነው? አለው፡፡ ስምዖንም ብዙ የተወለት ይመስለኛል አለ፡፡ እርሱም በእውነት ፈረድክ አለው፡፡

ከዚያም ወደ ሴቲቱም ዘወር ብሎ ስምዖንን እንዲህ አለው ይህችን ሴት ታያታለህን? እኔ ወደቤትህ ከገባሁ ውኃስ እንኳ ለእግሬ አላቀረብህልኝም እርሷ ግን በዕንባዋ እግሬን አራስችኝ በጠጉሯም አበሰችኝ፡፡ አንተ አልሳምኸኝም፤ እርሷ ግን ከገባሁ ጀምራ እግሬን መሳም አላቋረጠችም፡፡

አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም፤ እርሷ ግን እግሬን ሽቱ ቀባችኝ፡፡ ስለዚህ እልሃለሁ እጅግ ወዳኛለችና ብዙ ኃጢአቷ ተሠርዮላታል፡፡ ጥቂት የሚወድ ግን ጥቂት ይሠረይለታል፡፡ እርሷንም ኃጢአትሽ ተሠርዮልሻል አላት፡፡

ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው ኃጢአትን እንኳን ይቅር የሚል ይህ ማነው? ተባባሉ፡፡ ሴቲቱንም እምነትሽ አድኖሻል በሰላም ሂጂ፣ እነዚህ ላደርገው የወደድሁትን አይከለክሉኝም፡፡

ስለ ኃጥአን ወደ ዓለም መጥቻለሁና ወደ እኔ ለሚመለሱት የማደርገውን ይቅርታዬን በጠላት ነገር የማስቀር አይደለሁም። እነዚህ ፊትን ያያሉ እኔ ግን ልብንና ኵላሊትን እመረምራለሁና፡፡ ኃጢአትሽን ይቅር ብየሻለሁና ፈጽሞ ደስ ይበልሽ፡፡ መታሰቢያሽንም ለዘለዓለም ሲያነሡ ይኖራሉ አላት፡፡

ያንጊዜም ስለ እርሷም ስለምን ይህን ያህል ሽቱ ታባክናለች በብዙ ተሽጦ ለነድያን አይሰጥም ነበር? ተባብለዋልና ስለዚህም ጌታችን ይህቺ ሴት ያደረገችው እነርሱ ካሉት በእጅጉ እንደሚሻል አስረዳቸው፡፡ ምጽዋትም የቀና ሃይማኖት ከሌላቸው ሰዎችም ትደረጋለችና ልባቸውም በጥበብ በራ፡፡

ከዚም በኋላ በዚች ሴት ላይ የቀናችሁ እናንተስ ጠላት በሕሊናችሁ ክፉ ሐሳቡን ዘራ፡፡ ነዳያንን ትራሩላቸው ዘንድ ካሰባችሁስ እንዴት ወደ እኔ በሚመጡት ላይ የምሕረትን ደጅ ትዘጉባቸዋላችሁ? ምጽዋት ሰውን ወደ እግዚአብሔር ታቀርበዋለችና፡፡ ይህችም ሴት አሁን ያላትን ሁሉ ገንዘብ አመጣች፡፡ ምንም ምን ያተረፈችው አልነበረም፡፡ ይህም የበጎ ነገር ሁሉ ፍጻሜ እንደሆነም ዐወቀች አላቸው፡፡

ስለዚህም ለእርሷ ታላቅ ጸጋ ተሰጣት፡፡ ልዑል እግዚአብሔር ስለ ኃጢአታችን ከመጸጸት በንጹሕ ልብም ወደ እርሱ ከመመለስ በቀር ከእኛ የሚፈልገው ነገር የለምና፡፡ ከእንቅልፉ የነቃ ከእሱም ክፋትን ያራቀና በጎ መሥራትም ያሰበ፤ በሩን ከመዝጋታቸው በፊት መግባትን የፈለገ፤ የሽያጩ ገብያ ሳይፈታ ለራሱ ዘይትንም የገዛ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ እግዚአብሔር የንስሓን መንገድ ሰጥቶናልና፡፡

ይልቁንም ሰነፉን ሁሉ ስለ ነፍሱ ድኅነት ታነቃው ዘንድ ስለተጸጸተች ስለዚች ኃጥእት ሴት ሥራ እነሆ የስንፍና ጊዜ አለፈ፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሓ ግቡ ያለው የንስሓ ጊዜም ደረሰ፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከኃጢአት ባርነት ነፃ ያወጣን ዘንድና አዳኝ በሆነ በመስቀሉም ኃይል ያድነን ዘንድ የቀናች ኃይማኖትን ይሰጠን፣ ልዩ በሆነች ትንሣኤውም ከውድቀታችን ያነሣን ዘንድ የዘለዓለም መንግሥቱንም ይከፍለን ዘንድ ወደ ዓለም መጥቷልና፡፡

ፍጹም ሀብቱን እንደሚገባ ተቀብለን እንከፍል ዘንድ ይገባናል፡፡ የንስሓ ጾምንም እንጹም፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቆመ ሳይቀመጥ ከዘረጋ ሳያጥፍ አርባ መዓልትና ዓርባ ሌሊት ጾሟልና፡፡ ከክፋት ሁሉ ርቀን በጎ ነገርን እንሠራ ያለ ነውርም ንጹሕ የሆነ ጾምን ልንጾም ይገባል፡፡ ከመብልና ከመጠጥ መጾም ብቻውን አይጠቅምምና፡፡.....

ይቀጥላል......

(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 105-151)

መዓዛ ሠናይ

22 Nov, 05:35



....የቀጠለ
ድርሳን በእንተ ማርያም ኃጥእት
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን አምስት)

ከዚህም በኋላ ተነሥታ ሄደች፡፡ ሽቱ ወደ ሚሸጠው ሰውም ደረሰች፡፡ ይህንን ሰው ቀድሞ ታውቀው ከእርሱም ሽቱ ትገዛ ነበር፡፡ በአያትም ጊዜ ደነገጠ ተከዘም፡፡ ጠርቶም እንዲህ አላት፡፡ አንቺ ሴት ሆይ ምን ሆንሽ? በአንቺ ላይስ የመጣው ምንድን ነው? ከሚወዱሽ የሞተ አለን? የምታዝኚውና የምትተክዢውም ስለ እርሱ ነውን? አላት፡፡

ዳግመኛም መልሶ ለሙታን የሚቀቡትን ሽቱ ትገዢው ዘንድ ትወጃለሽን፡፡ ወይስ ያየሽውና በፍቁሩ የተቃጠልሽለት መልከ መልካም ጎልማሳ አለን? ወይስ ሀብቱ ብዙ የሆነ ወደ ከተማ የመጣ ነጋዴ አለን? በዚህም ምክንያት ልታጠምጂው ገንዘቡንም ልትወስጂበት ትወጃለሽን? አላት፡፡

ሽቱ ሻጩም እንደዚህ ያለ ብዙ ነገርን ተናገረ፡፡ ሐሳቧን ከመልካም ነገር ይመልሰው ዘንድ የበጎ ነገር ጠላት በልቡ ይህን ነገር ዘርቷልና፡፡ እርሷም መልሳ እንዲህ የምትለኝ አንተ ሰው ሆይ እነሆ ስማ፡፡ ከወዳጆችሽ መካከል አንዱ ሞተን ላልኸኝ እውነት ብለሃል፡፡ ብዙ ኃጢአቴ በንስሓ ሙቷልና፡፡ እነሆ እኔም እቀብረው ዘንድ እሻለሁ፡፡

መልከ መልካም ወጣት አየሽን? ስላልኸኝም እውነት ብለሃል እነሆ አሁን የሰው ሁሉ ሰውነት ተስፋ የሚያደርጉት ስለ እርሱ ነቢዩ ዳዊት ውበቱ ከሰው ልጅ ሁሉ ይልቅ ያምራል ብሎ የተናገረለት መጥቷልና፡፡ እነሆ አሁን ወዳጅ፣ ጌታና መድኃኒት ይሆነኝ ዘንድ እሻለሁ አለችው፡፡

ዳግመኛም ነጋዴ ወደ ሀገር መጣን? ስለምትለኝም እውነት ብለሀል፡፡ እርሱ የሚሸጥ ከእርሱም የሚገዛ ብዙ ትርፍንና መድኃኒትን የሚያገኝበት ነጋዴ ነውና፡፡ እርሱ ከእኛ የሚያረጀውንና የሚጠፋውን ወስዶ የማይጠፋውንና የማያረጀውን ይሰጠናልና፡፡ ስለ ምድራዊውም ፈንታ ሰማያዊውን ይሰጠናል፡፡ ከዛሬም ጀምሮ ወደ እርሱ እሄድ በኋላውም እከተለው ዘንድ እሻለሁ፡፡ ወደ ሌላ የምሄድ አይደለም፡፡ እነሆ አሁንም በአመፃ የሰበሰብሁትን ገንዘቤን ሁሉ ውሰድና ለእርሱ እጅ መንሻ አድርጌ እወስድለት ዘንድ የሚገባኝን ስጠኝ፡፡

ሽቱ ሻጩም ነገሯን በሰማ ጊዜ ደነገጠ፡፡ ብዙ ገንዘብን እንዳመጣችለት አይቷልና፡፡ በልቡም እንዲህ ብሎ አሰበ፡፡ የምትሻውን ባልሰጣት እኔን ትታ እነሆ ወደ ሌላ ሂዳ ከእርሱ ትገዛለች፡፡ እኔም ይህን ያህል ገንዘብ አጣለሁ፡፡ በእርሱ ዘንድም ዋጋው ብዙ የሆነ የሽታው መዓዛም የበዛ ሽቱ አለ፡፡

ከዚህም በኋላ ፈጥነው ተነሡ፡፡ ያንን ሽቱም ዐያሳያት፡፡ በዐየችውም ጊዜ ትወስደው ዘንድ ወደደች፡፡ ያላትን ገንዘብ ኹሉም ሰጠችው፡፡ ያንን ሽቱም ይዛ በፍጹም ደስ እያላት ሄደች፡፡ በምትሄድ ጊዜም እነሆ ሰይጣን በአጌጠች ሴት ተመስሎ ወደ እርሷ መጣ፡፡ የዚህን ዓለም ፍቅር ጣዕሙን ይነግራት ጀመር፡፡ የጣመ የላመ መብላትን፣ ያማረ መልበስን ዕጣንና ሽቱን ሁሉ ያስታውሳት ጀመር። የልብን የሚያውቅ ጌታችን ግን የጠላትን ክፉ ሥራውን ገለጠላት፡፡......

ይቀጥላል ......

(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 105-151)

መዓዛ ሠናይ

21 Nov, 10:10


ወዳጆች ሆይ! ማፈር የሚገባን ኃጢአት ስንሠራ እንጂ ንስሐ ስንገባ አይደለም፡፡ ኃጢአት ሕመም ነው፤ ንስሐ ደግሞ መድኃኒቱ ነው፡፡ ከኃጢአት ቀጥሎ ሐፍረት አለ፤ ከንስሐ ቀጥሎ ግን በጌታ የኾነ ደስታ አለ፡፡ ነገር ግን ሰይጣን ይህን ቅደም ተከተል አዛብቶብን በኃጢአት ስንደሰት በንስሐም እናፍራለን፡፡

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

መዓዛ ሠናይ

20 Nov, 08:44



....የቀጠለ
ድርሳን በእንተ ማርያም ኃጥእት
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን አምስት)

ኃጢአተኛዋ ሴት እያለቀሰችና ደረቷን እየደቃች እንዲህ ብላ አሰበች፡፡ እንዴት እንደምትድንም አታውቅም ነበር፡፡ የጴጥሮስን መራራ ልቅሶን የተመለከተና ንስሓውን የተቀበለ ወደ ክብሩም የመለሰው፣ የቀራጩ ጩኸትም ከእርሱ ያልተሠወረ የልብን የሚያውቅ እግዚአብሔር ዳግመኛም የዚችንም ሴት ዕንባዋን ቸል አላለም፡፡ ያን ጊዜም ያቺ ሴት በንጹሕ ልብና በብሩህ ሕሊና እንደተመለሰች ዐወቀ፡፡

እርሷ ግን በእውኑ ቸሩ መምህር ሌሎችን ሰዎች እንደተቀበላቸው ይቀበለኝ ይሆንን? አናግረው ዘንድ አንድ ሰዓት ያክል ይታገሠኝ ይሆንን? በውኑ ስንፍናዬን ሁሉ እነግረው ዘንድ ወደ እርሱ ያቀርበኝ ይሆንን? የመዋረዴንና የኀፍረቴን ነገር ይሰማ ዘንድ ይቀበለኝ ይሆንን? በውኑ አንዲት ቃልን ይመልስልኝ ይሆንን? ብላ አሰበች፡፡

ዳግመኛም ነፍሴ ሆይ ምሕረት ቀርባለች፡፡ ባለመድኃኒቱም በዚህ አለ፡፡ መድኃኒቱም ሩቅ አይደለም፡፡ በእውኑ የምትደፍሪ መድኃኒትሽንም ተስፋ የምታደርጊ ከሆነ ወደ እርሱ ሂጂ አለች፡፡ ከዚህ በኋላ በሃይማኖት ጸናች፡፡ እንደዚህ ስትልም አሰበች:: ስለ ኃጥአን ሲል ወደ ዓለም የመጣው ይህ አይደለምን? ስለ እነርሱ እንደ እነርሱ ሰው የሆነ በመካከላቸውም የተመላለሰ ይህ አይደለምን? የኃጢአተኛውን መመለሱን እና ሕይወቱን እንጂ ሞትን አልፈቅድም ያለ እርሱ አይደለምን? አለች፡፡

ዳግመኛም መልሳ መቶ በግ ያለው ሰው ቢኖር ከእነሱም አንዱ ቢጠፋ ያልጠፉትን ዘጠና ዘጠኙን በበረሃ ትቶ የጠፋውን ይፈልግ ዘንድ የሄደ አይደለምን? ባገኘውም ጊዜ በትክሻው የተሸከመው ከአልጠፉትም ከዘጠና ዘጠኙ ይልቅ በእሱ ፈጽሞ ደስ ይሰኛል ብሎ የተናገረ እርሱ አይደለምን?

አሁንም መልሳም እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበዳችሁ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ ያለ እርሱ እንዲህስ ከሆነ ለምን እሰንፋለሁ? ለምንስ ንስሓን አልፈልግም? እንደ እኔ ክፉን ሥራ የሠራ ሊሰንፍ አይገባውም፡፡ በእኔ መንገድም የሄደ ወደ ንስሓ ይመለስ ዘንድ ይገባዋል፡፡

እነሆ አሁን ወደ እሱ እሄዳለሁ የሚቀበለኝም ከሆነ ሰውነቴን በፊቱ እጥላታለሁ፡፡ በቸርነቱ ብዛትና በምሕረቱ ይቅር ባይ እንደሆነ እነሆ ዐወቅሁ፡፡ ካልተቀበለኝና ቸል ካለኝም እቈጣ ዘንድ ተገቢ አይደለም አለች፡፡

ይህንንም ተናግራ በሃይማኖት ጸናች፡፡ ፈጥና ተነሥታም ገንዘቧን ሁሉ ወርቋን፣ ብሯን፣ ልበሷንና የገዛችውንም ሁሉ ሰበሰበች። እርሱ የሁሉ ፈጣሪ ነውና ይህን ገንዘብ ወደ ጌታ ወስጄ ባይቀበለኝ እንግዲህ ምን አደርጋለሁ? አለች፡፡

እርሱም ያመኑበትንና የተከተሉትን ወርቅ ወይም ብር በመቀነታችሁ አትያዙ ብሎ አዝዟቸዋልና፡፡ ነገር ግን እኔ ወደ ገብያ እሄዳለሁ ለጌታ ላቀርበው የሚገባኝንም እገዛለሁ፡፡.....

ይቀጥላል.....

(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 105-151)

መዓዛ ሠናይ

20 Nov, 07:04


#ሺ_ጊዜ

ሺ ጊዜ ኃጢያት ስራ ነገር ግን ንስሃ ከመግባት አትቦዝን። የፈጠረህ እግዚአብሔር ጨርሶ አንተን መማር አይሰለችምና። እልፍ ጊዜ በድል ነገር ግን ከእግዚአብሔር አትኮብልል። ምክንያቱም እግዚአብሔር የደበሉ ወደ እርሱ የሚሸሸጉበት ዕሩሩህ እንጂ የሚሸሹት ጨካኝ አይደለምና።

በጣም ለቁጥር እንኳን በሚታክት ጥፋት ውስጥ ሁን ነገር ግን ከእግዚአብሔር ከእግሩ ስር አትጥፋ። እግሩ ስር ስትሆን ክብር አለህና በጥፋትህ ብዛት እኔ እንዴት ወደ እግዚአብሔር እቀርባለሁ ብለህ አትራቅ። እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንድትቀርብ ልጁን ለአንተ ሲል በመስቀል ሰውቶታልና።

ጉድ የሚያስብል ጉድ ውስጥም ሁን ነገር ግን ገበናህን ከሚሸሸግልህ ከእግዚአብሔር አትሸፍት። የሁሉ ሰው ተግባር በእግዚአብሔር ፊት ግልጥ ነው። እግዚአብሔር ሁሉንም ነገርህን እያወቀ ዝም የሚልህ ስለሚምርህ ነው እንጂ ለኃጢአትህ መዝገብ አዘጋጅቶ አይደለም።

ኃጢአቴ ብዙ ነው ብትልም የኃጢአትህ ክምር በጭራሽ እግዚአብሔርን እንዳይሸሽግህ። ከበደልህ ይልቅ የሞተልህን ተመልከት። እግዚአብሔር የኃጥዓን መፍትሔ ነው። ችግር ውስጥ እንዳለህ በተሰማ ቁጥር ወደ ባለመፍትሔው ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እጅግ ማትረፊያ ነው። ኃጢአት የሰው ልጅ ሁሉ ችግር ነውና።

የራስህን መንገድ ብትከተል ጨርሶ ልትወጣው ወደማትችለው መስመር ልትገባ ትችላለህ ከዚህ ይልቅ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።” (ማቴዎስ 11፥28) የሚለውን መለኮታዊ ቃል አምነህ ከነሸክምህ ወደ እግዚአብሔር ቅረብ። እርሱ እንዳለውም ያሳርፍሃልና።

የራስህን ኃጢአት እና የእግዚአብሔርን ጽድቅ እያመዛዘንክ አትኑር። በምንም መልኩ በእግዚአብሔር ልክ ጻድቅ ልትሆን እና የእርሱን የጽድቅ ጥማትም ልታረክ አትችልም። እንዲህ እስክሆን ወደ እርሱ አልቀርብም፣ ይሄንን ልማዴን እስከተው አልጠጋውም አትበል ያንን ልማድህን የሚያስክድ እና የሚያስተው አቅም እና ጸጋ በእግዚአብሔር ዘንድ እንጂ እራስህ ጋር አታገኘውምና።

እና ወዳጄ እሩጫ የሚሻለው ወደ እግዚአብሔር ሲሆን ነው። ጌታ እግዚአብሔር የማያሳፍርህ ተቀባይ፣ የማያሸማቀቅህ አዛኝ፣ ፊት የማይነሳህ አቃፊ ነው። እና ወደ እርሱ መምጣት የሁሉ ነገር መፍትሔ ነው።

መዓዛ ሠናይ

20 Nov, 06:34



....የቀጠለ
ድርሳን በእንተ ማርያም ኃጥእት
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን አምስት)

እንዲሁም ለዚያች ሴት የጸጋው ባለጠግነት በእርሷ ላይ ወጣ፡፡ ከሞት ወደ ሕይወት፤ ከክፋትም ወደ በጎነት ነፃ አወጣት፡፡ ስሟንም በዓለም ሁሉ እንዲዘክሩ አደረጋት፡፡ ከዚህም በኋላ ከዕለታት በአንዲት ቀን በቀደመው ግብሯ ሳለች የሐር ልብስን ለብሳ፣ አብዝታ አጊጣና ሽቱን ተቀብታ መልኳን በመስታውት ተመለከተች፡፡ የዐይኗ ውበት፣ የጉንጮቿ ቀይነትና የመልኳም ማማር አስደሰታት፡፡ ውበቷንም ስትመለከት ለአንድ ሰዓት ያክል ቆየች፡፡

ከዚህም በኋላ በጎ ሐሳብ ወደ እርሷ መጣ፡፡ ሞት ሆይ መጥተህ ይህን የምታስወግደው የመልኬን ደምግባትስ የምትለውጠው አይደለምን? አለች ይህስ በጎ መዓዛ ያለው ሽታ ወደ ክርፋቱ የሚለወጥ አይደለምን፡፡ የዚህስ ኃይልና ብርታት ፍጻሜው እርጅና እና ድካም አይደለምን? ዛሬ የሚወዱኝስ ነገ የሚነቁኝ አይደሉምን? ዛሬ ይቀርቡኝ ዘንድ የሚወዱስ ነገ ከእኔ የሚርቁ አይደለምን?

እንዲህስ ከሆነ ከልቅሶና ከፍጹም ኵነኔ በቀር ከዚህ ሁሉ እንግዲህ ምን አገኛለሁ? የዚህን ዓለም ገንዘብ ሁሉ ባተርፍ ከሥጋ ድካም ከእርጅና እና ከዐይን መጥፋት ሊያድነኝ ይችላልን? ከዚህስ ሁሉ ቢያድነኝ በውኑ ከሞት ሊያድነኝ ይችላልን? እነሆ ይህ ነገር አይቻልም፡፡

ነፍሴ ሆይ ቃልን ሁሉ እንዳገኘ የሚናገር ሰው በዚያ በፍርድ ቀን ይፈረድበታል ያለውን የዓለሙን ሁሉ ፈራጅ ምን ትመልሽለታለሽ? አለች፡፡ ነፍሴ ሆይ ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት፣ ወደ ጥልቁ ጨለማ፣ ትሉ ወደማያንቀላፋበት ቅዝቃዜው ወደማይሞቅበትና እሳቱ ወደማይጠፋበት ይወስዱሽ ዘንድ ከእውነተኛው ፈራጅ ትእዛዝ በወጣ ጊዜ እንዴት ትሆኚ ይሆን?

ነፍሴ ሆይ በዚች ሰዓት የሚረዳሽ ማነው? ነፍሴ ሆይ በውኑ በዚህ ዓለም ያገኘሽው መጽናናት ይልቁንም ወዳጆችሽ ኃጢአት ስለ መሥራትሽ በውኑ ይጠቅሙሻልን አለን? ኅብሩ ልዩ ልዩ በሆነ ከቀጭን የተልባ እግር በተሠራ ልብስ ስትደሰት የኖርህ ሰውነቴ ሆይ በምስጋና ጌታ እና ክፉ ሥራህን ሊሰሙ በሚቆሙ የብዙ ብዙ በሆኑ በመንፈሳውያን መላእክት ፊት ዕርቃንህን ስትቆም እንዴት ትሆን ይሆን?

ነፍሴ ሆይ በእውኑ በዚህ በሚያስፈራ የፍርድ ዐደባባይ የሚረዳሽ አለን? የዚህ ዓለም መብልስ በወዲያኛው ዓለም የትል ሲሳይ በምትሆኚ ጊዜ በእውኑ ይጠቅምሽ ይሆንን? ነፍሴ ሆይ በዚህ ዓለም የተደሰትሽው ምን ይረባሻል? ምንስ ይጠቅምሻል? ዐይኖቼ ሆይ በውኑ የሞት ጥላ በጋረዳችሁ ጊዜ የሚጠቅማችሁ የሚረባችሁ ኵል አለን?

አፌ ሆይ በውኑ መራራ የሞት ጽዋን በምትጠጣ ቀን የሚረባህ የሚጠቅምህ የዚህ ዓለም መብል አለን?

በአንተ ብዙዎችን የሸነገልሁብህ አንደበቴ ሆይ ሞት ዝም ባሰኘህ ጊዜ ምን ትሆን ይሆን? በውኑ ከዓለሙ ፈራጅ ጋር መመላለስ ይቻልህ ይሆንን? በቀለበትና በእንሶስላ ስታጌጡ የኖራችሁ እጆቼ ሆይ የሚያስፈራ ሞት በመጣ ጊዜ ምን ትሆኑ ይሆን? ሁል ጊዜ ወደ ዝሙት ስትሮጡ የነበራችሁ እግሮቼ ሆይ ሞት ባሠራችሁ ጊዜ ምን ትሆኑ ይሆን? ማምለጥንም ትፈልጋላችሁ፡፡ ግን አይቻላችሁም፡፡....

ይቀጥላል.......

(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 105-151)

መዓዛ ሠናይ

19 Nov, 18:25


ህዳር 11 የጌታችን አያት የእመቤታችን እናት የሆነችው ቅድስት ሐና ያረፈችበት አመታዊ ክብረ በዓል ነው

ከእመቤታችንና ከቅዱሳኑ ረድኤት በረከት ያካፍለን።

መዓዛ ሠናይ

19 Nov, 11:05



ድርሳን በእንተ ማርያም ኃጥእት
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን አምስት)

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ክቡር የሆነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሽቱ ስለ ቀባችው ኃጥእት ሴት የተናገረው ድርሳን ይህ ነው ጸሎቱና በረከቱ በሁላችን ላይ ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ አለ፡፡ ሥራን ሁሉ እንሰማ ዘንድ እንደሚገባም እንቀበለው ዘንድ ተገቢ ነው አለ፡፡ ለንጉሡ እንደ ሥልጣኑ ገናንነት መጠን፣ ለሹሙም እንደ አገዛዙ መጠን፣ ለመስፍኑም ለምስፍናው እንደሚገባው መጠን ጸጋው ለአንዱም ለአንዱ ለየራሱ እንደሚሰጠው ይህ ነገር የታወቀ ነውና፡፡

ይህም ለዚህ ለኃላፊው ዓለም ነው፡፡ ለሚያልፈው ሥጋዊ ዓለም እንደዚህ ከሆነ ይልቁንም የጌቶች ጌታ የነገሥታትም ንጉሥ ወደ ሆነው አምላክ፡የሚያቀርበንን በጎ ሥራ እንፈልግ ዘንድ የቅዱሳን አባቶቻችንና የሰማዕታትን መታሰቢያ በዓላቸውን እናደርግ ዘንድ የሚገባን አይደለምን? መጨረሻ የሌላትን መንግሥተ ሰማያትንም እንወርስ ዘንድ በፍጹም ደስታ እንቀበለው ዘንድም የሚገባ ነው፡፡

ተዘጋጅተው የጌታቸውን መምጣት እንደሚጠብቁ ባሮችም የተዘጋጀን ልንሆን ይገባል፡፡ ለዚህ ኃላፊ ለሆነው ዓለም ከንጉሥ ወይም ከመኰንኑ ትእዛዝ በወጣ ጊዜ እነሆ መልእክቱን ፈጽመው ከፍ ከፍ ሲያደርጉትና ሲያከብሩት እንመለከታለንና፡፡

ለዚህ ለኃላፊው ዓለም እንዲህ የሚያደጉ ከሆነ ክብር ይግባውና በነገሥታና በባለሥልጣናት ላይ ኃይልና ሥልጣን ያለውን የጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ትእዛዛትን ከዚህ እጥፍ ከፍ ከፍ ልናደርጋቸውና ልናከብራቸው አይገባምን? ቅዱስ ወንጌል ጌታው በመጣ ጊዜ በጎ ሥራ ሲሠራ ያገኘው አገልጋይ ብፁዕ ነው ይላልና፡፡

በበጎ ሥራ የተዘጋጀን እንሆን ዘንድ፣ ሕሊናችንንም ብሩህ እናደርግ ዘንድ በነገር ሁሉ ዐይነ ልቡናችንን ወደ እግዚአብሔር እናነሣ ዘንድ በዚህ በኃላፊው ዓለም ጭንቀትም የማንጨነቅ፡እንሆን ዘንድ ይገባናል፤ የማያልፈውንና የማይጠፋውን ትተን በሚያልፈውና በሚጠፋው የምንደክም ከሆን ግን እነሆ ልብ እንደሌላቸው እንደ ሰነፎች እንሆናለን፡፡....

ይቀጥላል......
(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 105-151)

መዓዛ ሠናይ

19 Nov, 11:05



ድርሳን በእንተ ማርያም ኃጥእት
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን አምስት)

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ክቡር የሆነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሽቱ ስለ ቀባችው ኃጥእት ሴት የተናገረው ድርሳን ይህ ነው ጸሎቱና በረከቱ በሁላችን ላይ ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ አለ፡፡ ሥራን ሁሉ እንሰማ ዘንድ እንደሚገባም እንቀበለው ዘንድ ተገቢ ነው አለ፡፡ ለንጉሡ እንደ ሥልጣኑ ገናንነት መጠን፣ ለሹሙም እንደ አገዛዙ መጠን፣ ለመስፍኑም ለምስፍናው እንደሚገባው መጠን ጸጋው ለአንዱም ለአንዱ ለየራሱ እንደሚሰጠው ይህ ነገር የታወቀ ነውና፡፡

ይህም ለዚህ ለኃላፊው ዓለም ነው፡፡ ለሚያልፈው ሥጋዊ ዓለም እንደዚህ ከሆነ ይልቁንም የጌቶች ጌታ የነገሥታትም ንጉሥ ወደ ሆነው አምላክ፡የሚያቀርበንን በጎ ሥራ እንፈልግ ዘንድ የቅዱሳን አባቶቻችንና የሰማዕታትን መታሰቢያ በዓላቸውን እናደርግ ዘንድ የሚገባን አይደለምን? መጨረሻ የሌላትን መንግሥተ ሰማያትንም እንወርስ ዘንድ በፍጹም ደስታ እንቀበለው ዘንድም የሚገባ ነው፡፡

ተዘጋጅተው የጌታቸውን መምጣት እንደሚጠብቁ ባሮችም የተዘጋጀን ልንሆን ይገባል፡፡ ለዚህ ኃላፊ ለሆነው ዓለም ከንጉሥ ወይም ከመኰንኑ ትእዛዝ በወጣ ጊዜ እነሆ መልእክቱን ፈጽመው ከፍ ከፍ ሲያደርጉትና ሲያከብሩት እንመለከታለንና፡፡

ለዚህ ለኃላፊው ዓለም እንዲህ የሚያደጉ ከሆነ ክብር ይግባውና በነገሥታና በባለሥልጣናት ላይ ኃይልና ሥልጣን ያለውን የጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ትእዛዛትን ከዚህ እጥፍ ከፍ ከፍ ልናደርጋቸውና ልናከብራቸው አይገባምን? ቅዱስ ወንጌል ጌታው በመጣ ጊዜ በጎ ሥራ ሲሠራ ያገኘው አገልጋይ ብፁዕ ነው ይላልና፡፡

በበጎ ሥራ የተዘጋጀን እንሆን ዘንድ፣ ሕሊናችንንም ብሩህ እናደርግ ዘንድ በነገር ሁሉ ዐይነ ልቡናችንን ወደ እግዚአብሔር እናነሣ ዘንድ በዚህ በኃላፊው ዓለም ጭንቀትም የማንጨነቅ፡እንሆን ዘንድ ይገባናል፤ የማያልፈውንና የማይጠፋውን ትተን በሚያልፈውና በሚጠፋው የምንደክም ከሆን ግን እነሆ ልብ እንደሌላቸው እንደ ሰነፎች እንሆናለን፡፡....

ይቀጥላል......
(ድርሳነ ሠለስቱ ሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመ ገጽ 105-151)

መዓዛ ሠናይ

19 Nov, 11:05


ትሕትና

ትሕትና የትንሽት ምልክት አይምሰልህ ፡፡ ታላቁ መስፍን ሙሴ ፣ ታላቁ ጌታ ክርስቶስ ትሑታን ነበሩ ፡፡ ባለጠግነት ትሕትናን ሊያሳጣህ ሲሞክር ጻድቁ አብርሃምና ጻድቁ ኢዮብ ትሑታን እንደ ነበሩ አስብ ፡፡ ሥልጣን ልብህን ከፍ ሲያደርግብህ “ለንጉሥ በቀን ላይ ቀን ትጨምራለህ” በማለት የተናገረውን ዳዊትን አስብ ፡፡ ምንም ብትነግሥ ለራስህ አንድ ቀን መስጠት አትችልምና ፡፡ ደግሞም “ሁሉም ከንቱ” ያለውን ሽቅርቅሩን ንጉሥ ሰሎሞንን ፣ ጠቢቡን ንጉሥ ይዲድያ የተባለውን በማሰብ አለባበስንና እውቀትን ናቀው ፡፡ ጉልበትህ ሊያስታብይህ ሲሻ ሶምሶምን አስብ ፡፡ ኃይልህ ከኃያላን ፣ ሥልጣንህ ከሠለጠኑት ፣ እውቀትን ካወቁት ጋር ቢነጻጸር በጣም ትንሽ ነው ፡፡ በምድራዊ ነገር ብቻ ሳይሆን በመንፈሳዊ ጸጋም ልትመካ አይገባህም ፡፡ ትምክሕት እጄ ሀብትን ፣ ጽድቄ ጸጋን አመጣልኝ ማለት በመሆኑ ቁጥሩ ከክህደት ነው ፡፡ በጸጋ ሳይሆን በባለጠጋው መመካት ግን ተፈቅዷል ፡፡ ኃጢአትህ እየበዛ ሲመጣ የሌሎች ስህተት እየታየህ ይመጣል ፡፡ ጽድቅ በውስጥህ እየተስፋፋ ሲመጣ የራስህ ደካማነት ይታይሃል ፡፡

ትሕትና በአደባባይ እንደ ለበስከው ነጭ ሸማ ነው ፡፡ ታጌጥበታለህ ፡፡ ትዕቢት ግን ያዋርድሃል ፣ የማያውቅህ ሳይቀር አይቶ ይጸየፍሃል ፡፡ ቁመተ ረጅሞች ሲኮሩ ሰማይን የምታይ ይመስልሃል ፡፡ አጭሮች ሲልመጠመጡ መቃብር የገቡ ይመስላል፡፡ የረጅምነት ውበቱ ዝቅ ማለት ነው ፡፡ ትዕቢተኛ ስትሆን ሰዎች እንከን እንዲፈልጉብህ መንገድ ትከፍታለህ ፡፡ ትሕትና ራስን የማወቅ ውጤት ነው ፡፡ ራሱን በትክክል የሚያውቅ ሊታበይና በሌሎች ሊፈርድ በፍጹም አይችሉም ፡፡ ትሕትና የሌሎችን ክብር ማወቅ ነው ፡፡ ማክበር መከበር ነውና ሌሎችን ስናከብር ትሕትና ታስከብረናለች ፡፡ ትሕትና ሁልጊዜ እንደሚማሩ ሁኖ መኖር ነው ፡፡ ትሕትና በጠፋበት ዘመን ሁሉም ሰው አስተማሪ ይሆናል ፡፡ ሁሉም ሰው ቅዱስ ነኝ በማለት ሌሎችን ያጣጥላል ፡፡ ጆሮ ጠፍቶ አፍ ብቻ የበዛበት ዘመን ዘመነ ትዕቢት ነው ፡፡ እገሌ ክፉ ነው ማለት በተዘዋዋሪ እኔ መልካም ነኝ ማለት ነውና ትዕቢት ነው ፡፡ ትሕትና የሰዎችን ትልቅ ድካም አሳንሶ ፣ ትንሽ ብርታታቸውን አጉልቶ ያሳያል ፡፡ ትሕትና እንዳልኖሩ ሁኖ ከሌሎች ልምድን መቅሰም ነው ፡፡

ከፍ ላሉት ዝቅ ማለት ትሕትና አይደለም ፡፡ ከፍ ያሉትማ ግርማቸው በግድ ያሰግዳል ፡፡ ትሕትና ዝቅ ላሉት የምናሳየው ፍቅርና ክብር ነው ፡፡ ለእግረኛ ቅድሚያ ስትሰጥ አንድ ነገር አስብ ፡- “መኪና ለሰው እንጂ ሰው ለመኪና አልተፈጠረም፡፡” እውነተኛ ትሕትና ለሚያንሱን መታዘዝ ነው ፡፡ ሰው እንደዚህ ሁኖ እንደማይቀር ብናስብ ስንት ሕጻናትን ስንት ድሆችን ባከበርን ነበር ፡፡ ትሕትና የልብ መሰበር ያመጣልና ለዝማሬና ለንስሐ ያበቃል ፡፡ አበባ ካልታሸ አይሸትም ፣ ፍራፍሬ ካልተጨመቀ አይጠጣም ፡፡ ሰውም ትሑት ካልሆነ መልኩ አይወጣም ፡፡ ትሕትና ያወቁትን ያለ ትችት ማስተማር እንጂ አላውቅም ማለት አይደለም ፡፡ እያወቁ አላውቅም ማለት ልግመት ፣ ሳያውቁ አውቃለሁ ማለት ራስን አለማወቅ ነው ፡፡ ያወቁትን በትጋት ማስተላለፍ ትሕትና ነው ፡፡ የተማርከው ሌሎችን ደንቆሮ ብሎ ለመሳደብ ሳይሆን በጨለማ ላሉት ብርሃን ለማወጅ ነው ፡፡ የጋን ውስጥ መብራት ከመሆን የሚያድነው ትሕትና ነውና ስታውቅ ትሑት ሁን ፡፡ ፍሬ ያለው ዛፍ ዘንበል ይላል ፡፡ ቀና የሚሉት ዛፎች ግን ፍሬ የሌላቸው ናቸው ፡፡ በእውነት ካወቅህ ያላወቅከው ስለሚበዛብህ ትሑት ትሆናለህ ፡፡ በአንድ ጥቅስ ጫካ የሚገቡ የአቡጊዳ ሽፍቶች ግን ትዕቢተኞች ናቸው ፡፡ “ድምፅና ቁንጫ ባዶ ቤት ይወዳል” ይባላል ፡፡ ቁንጫም እንደ ልቡ ይዘላል ፣ ባዶ አዳራሽም ድምፅን ያስተጋባል ፡፡ ጩኸት ማብዛት የባዶ ቤት ምልክት ነው ፡፡ ባዶ ሰው ከቀድሞ የከፉ የሰባት ኣጋንንት ማደሪያ ይሆናልና እባክህ ባዶ አትሁን ፡፡

ትሕትና የልብ ነው ፡፡ የልብ ያልሆነ ትሕትና የአንገት መሰበር ፣ የጉልበት መሸብረክ ብቻ ነው ፡፡ በልብ እየናቁ በአፍ ማክበር እርሱ ትሕትና ማጣት ነው ፡፡ ይልቁንም ትልቁን መንግሥት ፣ መንግሥተ ሥላሴን እየሰበክህ ትሑት ልትሆን ይገባሃል ፡፡ ትልቁን ትሕትና ነገረ ሥጋዌን እየተናገርህ ትሑት መሆን ያስፈልግሃል ፡፡ ተዋሕዶ ማለት ትሕትና ማለት ነው ፡፡ ባለጠጋው መለኮት ከድሃው ሥጋ ጋር የተዋሐደበት ማለት ነው ፡፡ የሥጋ ድህነት ለመለኮት ፣ የመለኮት ብልጥግና ለሥጋ እንዲነገር የፈቀደው ትልቁ የትሕትና ትምህርት ቤት ምሥጢረ ሥጋዌ ነው ፡፡ ምስኪኖችና ጦም አዳሪዎችን ፣ ኃጢአተኞችንና መንገድ የጠፋባቸውን ካላዘንክላቸው በተዋሕዶ አታምንም ማለት ነው ፡፡ የተዋሕዶ ምሥጢር ሲገባህ በቀራጮችና በኃጢአተኞች አታፍርም ፡፡ የወደቀውን ለማንሣት ዝቅ ትላለህ ፣ ወደ ሐኪም ቤት ለማድረስ አህያህን እንደ ደጉ ሳምራዊ ለቀህ እግረኛ ትሆናለህ ፡፡

የስድብ አምሮትህን ለመወጣት “ውሾች” ይላል ቃሉ ፣ የነቀፋ ጥማትህን “ተኩላ” ይላል ወንጌሉ እያልህ ከተወጣኸው ኃጢአትና በቅዱሱ ነገር መበደልህ ነው ፡፡ ውሻ ፣ ተኩላ ያለው ጠባያቸውን ለመግለጥ እንጂ ላንተ ስድብ ለማበደር አይደለም ፡፡ ትሕትና ተፈትኜ አልጨረስኩም ብሎ በራሱ በጣም አይመካም ፡፡ ገና በፈተና ዓለም ያሉ ሰዎችንም በጣም አያመሰግንም ፡፡ እባክህ ወዳጄ ትሑት ሁን ፡፡ የበላይ የበታች ሁሉም ልቡ ጎረምሳ ሁኗልና የሚያስተነፍስ መዓት ሳይመጣ ትሕትናን ገንዘብ እናድርግ ፡፡ ትሕትናን በማጣት ያሳዘንከውን እግዚአብሔር በብዙ ትሩፋት አታስደስተውም ፡፡ ትሕትና የእምነት መጀመሪያ ነውና ፡፡

መዓዛ ሠናይ

18 Nov, 05:56


ተወዳጆች ሆይ ኑ አባቶቼና ወንድሞቼ እግዚአብሔር ለርስቱ ለመንግሥቱ የለያችሁ ምእመናን ሆይ ኑ፡፡ የልጅነትን ማኅተም ያለባችሁ የክርስቶስ ወታደሮች ሆይ ኑ፡፡ ልጆቼ ይኽን ለነፍሳችን ድኅነት እግዚአብሔር ያዘጋጀውን ትምህርት ትማሩ ዘንድ ኑ፤ ጊዜ ሳለልን እንመካከር ዘንድ ኑ፡፡ ኑ ዘለዓለማዊ ሕይወትን ገንዘብ እናድርግ፡፡ ነፍሳችንን እንገዛት ዘንድ እንቻኮል፡፡

ዓይነ ልቡናችን ብሩህ ይኾን ዘንድ ኑ በዕንባ እንታጠብ (እናልቅስ)፡፡ ባለጸጋዉም ድኻዉም፣ ልዑላንም ሕዝቦችም፣ ወጣቶችም ጐረምሶችም፣ ሽማግሎችም ሕፃናትም፣ በአጣቃላይ ጣዕመ መንግሥተ ሰማያትን መውረስ ከምረረ ገሃነም መዳን የምትሹ ሁላችሁም ኑ፡፡

ከክቡር ዳዊት ጋር ሆነን ምሕረቱ የበዛ ባለጸጋውን እግዚአብሔርን “ነጽረኒ ወስምዓኒ እግዚኦ አምላኪየ" አቤቱ ፈጣሪዬ ልመናዬን ሰምተኽ በዓይነ ምሕረትህ እየኝ፤ ተመልከተኝ፡፡ "አብርሆን ለአዕይንትየ ከመ ኢኑማ ለመዊት" የሞት እንቅልፍ እንዳያንቀላፉ ዓይኖቼን አብራቸው” ብለን እንለምነው /መዝ.13፥3-4/፡፡ ከመንገድ ዳር ተቀምጦ ይለምን እንደነበረው እንደ ዓይነ ስዉሩ ሰውም፡- “ተሣሃለኒ ኢየሱስ ወልደ ዳዊት" የዳዊት ልጅ ኢየሱስ ሆይ ማረኝ” ብለን እንጩኽ/ማር.10፥48/፡፡ ዝም እንል ዘንድ የሚቈጡን ቢኖሩም እንደ በርጠሜዎስ ልጅ እንደ ጠሜዎስ ዓይነ ልቡናችንን እስኪያበራልን ድረስ አብዝተን ወደ ብርሃን ክርስቶስ እንጩኽ፡፡ ስለዚኽ ወደ ክርስቶስ እንቅረብ፤ ብሩህ ልቡናንም ገንዘብ እናድርግ፡፡ ገጻችንም ከቶ አያፍርም፡፡ ኑ! ሃይማኖትንና ምግባርን አንድም ልጅነትን መንግሥተ ሰማያትን ለመያዝ እንሩጥ። ይኽን ያደረግን እንደኾነም የዚህ ዓለም ነገር ከንቱ ሆኖ ይታየናል፡፡ ስለዚህ ራሳችንን ንቁ እናድርግ፤ በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ላይ ብንመጣም አይዘጋብንምና ኑ እንፍጠን፡፡ ምሽቱ ቀርቧል፤ ለኹሉም እንደየሥራው የሚከፍለው ልዑለ ባሕርይ ኢየሱስ ክርስቶስም ሊመጣ ነው፡፡
/#ንስሐ - #በቅዱስ_ኤፍሬም #መቅረዝ_ዘተዋህዶ_ብሎግ/

መዓዛ ሠናይ

17 Nov, 05:33


ህዳር8 ሥጋ የሌላቸው የአርባዕቱ እንስሳ(ኪሩቤል) በዓላቸው ሲሆን ዳግመኛ የአባ ኪሮስ ቅዳሴ ቤታቸው የተከበረበት አመታዊ ክብረ በዓል ነው
ከእመቤታችን,ከአባ ኪሮስ እና ከቅዱሳን ኪሩቤል ረድኤት በረከት ያካፍለን

መዓዛ ሠናይ

17 Nov, 04:00


🧲 የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቻናል

📚 ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት ብራና እና ወረቀት በpdf
መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥያቄ እና መልስ
📜 ኦርቶዶክሳዊ ግጥሞች
የግእዝ ቋንቋ ትምህርት
🎶 የኦርቶዶክስ የመዝሙር ግጥሞች
📙 ተከታታይ ትምህርቶች
📘 ስንክሳር የእየለቱ
📗 ብሂለ አበው
📓 መንፈሳዊ ተረኮዎች
📔 የአበው ምክር
📚 የተለያዩ መንፈሳዊ ትምህርቶች
🤵‍♂የመምህር ምህረተአብ አሰፋ ቻናል

የፈለጉትን መርጠው ይቀላቀሉ

🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
📖█▓▒░►𝑶𝑷𝑬𝑵◄░►𝑶𝑷𝑬𝑵▒▓█📖
📖█▓▒░►𝑶𝑷𝑬𝑵◄░►𝑶𝑷𝑬𝑵▒▓█📖
📖█▓▒░►𝑶𝑷𝑬𝑵◄░►𝑶𝑷𝑬𝑵▒▓█📖
📖█▓▒░►𝑶𝑷𝑬𝑵◄░►𝑶𝑷𝑬𝑵▒▓█📖

መዓዛ ሠናይ

16 Nov, 11:13


"ዲያብሎስ በእናንተ ላይ እጅግ ክፉ ነገርን በማምጣት አሳዝኖአችኋልን? እናንተም ኢዮብን አብነት አድርጋችሁ እግዚአብሔር ይመስገን በማለት አሳዝኑት፡፡ ዲያብሎስን ድል ማድረግ ስትሹ ይህን መሣርያ ዘወትር ያዙ፤ ምስጋና፡፡"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

መዓዛ ሠናይ

15 Nov, 05:44


ህዳር6 እመቤታችን ከልጇ ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ከስደት በተመለሱ ጊዜ ወደ ደብረ ቁስቋም የገቡበት ዓመታዊ በዓል

መዓዛ ሠናይ

12 Nov, 08:01


ልቡናውን ሰብስቦ መጸለይ አልችል ያለው ሰው አንድ ታላቅ አባትን እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፦ "አባቴ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ስጸልይ ልቡናዬ አይሰበሰብልኝም፡፡ አፌ ቢያነበንብም ልቡናዬ አይተረጕምም፡፡ እርስዎ እንደነገሩኝ ደግሞ ቅዱሳን በፍጹም አሳባቸው እያሰቡና እያራቀቁ እንባንና ጸጸትን እየጨመሩ የደረሱትን እኛ በልባችን ሌላ እያሰብን በአፋችን ብቻ እንደእነርሱ ብንናገር እንደ ገደል እንደ ዋሻ ሆነን በእግዚአብሔር እንደመቀለድ ነው፤ ጸሎትም አይሆንልንም፡፡ እንግዲህ የአፍ ጸሎቴ ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ባልተወው ይሻላል?"

እርሳቸውም፦ "ዕውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከመንገድ ላይ ያለ እባብ ለጊዜው ድምጹን ሰምቶ ይመታኛል ብሎ እንደሚሸሽለት ሁሉ አንተም አስተውለህ ባትጸልይም በአፍህ ውስጥ የቃለ እግዚአብሔርን መንኳኳት እየሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና ምንም ቅድመ እግዚአብሔር ባይደርስም ጸሎትህን አትተው። አጋንንትን ለማባረርም ጥቅም ነውና። ብዙ ከምትጸልየውም አንዳንድ ጊዜ ልብህ የሚወድቅባት ቃል ተጠራቅማ ወደ እግዚአብሔር ትደርሰልሃለች፤ ምንም ዝርወ ልብ ብትሆንም አፍህም ፍጥረቱ ነውና አንተው በዳይ አንተው አኵራፊ እንዳትሆን ባፍህም ብቻ ቢሆን መነጋገሩን አትተወው፡፡" ሲሉ መለሱለት።

(ምንጭ፦ ፍኖተ አእምሮ)

መዓዛ ሠናይ

08 Nov, 09:00


ከቅምሻ የቀጠለ
(ከኤፌሶን ወንዝ ከዲያቆን ሄኖክ መጽሐፍ)
በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ

ወዳጄ ሆይ ሰውነትህ በአምላክ ደም የተገዛ ክቡር ሰውነት ነው። አካልህ "አንተ" እንጂ "ያንተ" አይደለም። "በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ" ይላል። ስለዚህ በከበረ የእግዚአብሔር ልጅ ደም የተገዛ ሰውነትህን ለሰይጣን በርካሽ አትሽጠው::  አትግደል የሚለው ሕግ ራስህንም ይጨምራል::

ቤተ መቅደስ የሆነ ሰውነትህን ለማፍረስ አታስብ። "ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ" ፩ኛ ቆሮ. ፫፥፲፯ ሰዎች አስቀይመውህ ይሆን? "አሳያቸዋለሁ፤ ስሞት የእኔን ነገር ይገባቸዋል" ብለህ በሰዎች ተቀይመህ ራስህን አትጉዳ። እመነኝ ብትሞት ሰዎች ከሳምንት በላይ አያስታውሱህም። ለሕይወትህ ዋጋ ያልሠጡ ሰዎች ለሞትህ ዋጋ አይሠጡም። ፈጥነውም ይረሱሃል። ለሚረሱህ ሰዎች ብለህ የማይረሳህን አምላክ አታሳዝን። ሰው ስለ አንተ ግድ የለውም እግዚአብሔር ግን የራስህን ጸጉር ሳይቀር በቁጥር ያውቀዋል። እንኳንስ ራስህን ልትጎዳ አንዲት ጸጉር እንኳን ከአንተ እንድትወድቅ አይፈልግም። እግዚአብሔርን በኃጢአት ብታሳዝነው እንኳን ኖረህ ንስሓ እንድትገባ እንጂ እንድትሞት አይፈልግም። አባትህ ነውና ከእርሱ ጋር ባትሆንም እንድትኖር ይፈልጋል።

በምሳሌ ልንገርህ፦ ሁለት ሴቶች አንድን ሕፃን "የኔ ልጄ ነው" ብለው እየተከራከሩ ጠቢቡ ሰሎሞን ፊት ቀረቡ። ጠቢቡ ሰሎሞን ሰይፍ አመጣና "ልጁን ቆርጬ ለሁለት ላካፍላችሁ" አላቸው። አንደኛዋ ሴት "እሺ እንካፈል" ስትል እውነተኛዋ እናት ግን "ልጄ ከሚሞት እርስዋ ትውሰደው" አለች። እናት መሆንዋም በዚህ ታወቀ። (፩ኛ ቆሮ. ፫፥፩፮-፳፰)

ወዳጄ ያንተም ኑሮህ ከእግዚአብሔር ጋር ላይሆን ይችላል። ዓለም የራስዋ አድርጋህም ይሆናል። በሱስ ውስጥ ትዘፍቀህ፣ እንደ ሶምሶን በደሊላ እቅፍጀ፣ እንደ ዴማስ በተሰሎንቄ ውበት ተማርከህ ይሆናል። እግዚአብሔር ግን አባትህ ነውና ሞትህን አይፈልግም። "ልጄ ከሚሞት እርስዋ ትውሰደው" እንዳለችው እናት ፈጣሪህ ከነኃጢአትህም ቢሆን እንድትሞት አይፈልግም። ከእርሱ ጋር ባትኖርም መኖርህን ይፈልጋል። "የሟቹን ሞት አልፈቅድምና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ስለዚህ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ" ሕዝ. ፲፰፥፴፪

የይሁዳ ኃጢአቱ ጌታውን መሸጡ አልነበረም። ራሱን መግደሉ ነው። እግዚአብሔር የሚያዝነው ከበደልህ በላይ በእርሱ ተስፋ ቆርጠህ ራስህን ስትጎዳ ነው።

ወዳጄ የአንተን መኖር የሚፈልጉ ብዙ ናቸው። ፈጣሪ ወደዚህች ዓለም ያለ ምክንያት አላመጣህም። በአንተ አለመኖርም የሚጎድል ነገር አለ። አንተን የሚመስል ሌላ ሰው አልፈጠረምና ለዚህ ዓለም አንተን የሚተካ የለም፣ በክብር ወደዚህ ዓለም ያመጣህ አምላክ በክብር ወደራሱ እስኪወስድህ ድረስ "በራስህ ላይ ክፉ ነገር አታድርግ"

"የወኅኒውም ጠባቂ ከእንቅልፉ ነቅቶ የወኅኒው ደጆች ተከፍተው ባየ ጊዜ፥ እስረኞቹ ያመለጡ መስሎት ራሱን ይገድል ዘንድ አስቦ ሰይፉን መዘዘ። ጳውሎስ ግን በታላቅ ድምፅ፦ ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ፡ ብሎ ጮኸ" ሐዋ. ፲፮፥፳፯-፳፰ ይህ ሰው እስረኛ ያመለጠ መስሎት ራሱን ሊያጠፋ ሲል ጳውሎስ "ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ" አለው።

ወዳጄ አንተስ ተስፋ የቆረጥኸው ምን ያመለጠ መስሎህ ነው? የትምህርት ዕድል ያመለጠህ መስሎህ ነው? ገና ሺህ የትምህርት ዕድሎች አሉህ። ዕድሜህ ያመለጠህ መስሎህ ነው? ነገ የሚጠብቁህ ብሩሕ ዘመናት እኮ ቁጭ ብለው አሉ? የሚረዳኝ ሰው የሚያስብልኝ ሰው አጥቼያለሁ? ብለህ ከሆነም ካልሰሙህ ጥቂቶች በላይ ልንሰማህ የምንሻ "ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ"

መከራ ጸናብኝ ኑሮ ጨለመብኝ የሀገሪቱ ሁኔታ ተስፋ አሳጣኝ ብለህ ይሆን? እኛስ አብረንህ አይደልንም? አብረን ከገባንበት ችግር አብረን ብንወጣ አይሻልም? ከአንተ በባሰ ሁኔታ የታሰርንና የተገረፍን ጳውሎሶችና ሲላሶች "ሁላችን በዚህ አለንና በራስህ ክፉ አታድርግ" ስንልህ ስማን። ይልቅ አንተም እንደ ወኅኒው ጠባቂ "እድን ዘንድ ምን ላድርግ ብለህ?" ነፍስህን የምታድንበትን መንገድ ወደ መቅደሱ ቀርበህ ጠይቅ።

ወዳጄ ይህንን ጽሑፍ ያነበብኸውም በሕይወት ስላለህ ነው። የአንተን ዓይን የሚጠብቁ ብዙ ጽሑፎች፣ የአንተን ጆሮ የሚፈልጉ ብዙ ድምፆች፣ የአንተን መሐረብ የሚፈልጉ ብዙ ዕንባዎች፣ የአንተን ሳቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀልዶች ... ገና ብዙ ብዙ አሉ። ስለዚህ ሰይጣንን አሳፍረው። እንዲህ በለው "ጠላቴ ሆይ፥ ብወድቅ እነሣለሁና፥ በጨለማም ብቀመጥ እግዚአብሔር ብርሃን ይሆንልኛልና በእኔ ላይ ደስ አይበልህ" ሚክ. ፯፥፰

(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ - የኤፌሶን ወንዝ ገጽ 9-14)

መዓዛ ሠናይ

07 Nov, 13:13


++++++ጠባቧ_መንገድ++++++

"በተጨባጭ እውነታ ሰፊውንና ልቅ የኾነውን መንገድ ይዘን ሳለ ጠባቡንና የቀጠነውን መንገድ እየተከተልን እንደ ኾነ በማሰብ እንዳንታለል በራሳችን ላይ ቅርብ ትኲረት እናድርግ። ቀጥሎ የሰፈረው ነገር ጠባብ መንገድ ማለት ምን እንደ ኾነ ያሳይሃል፦ ሆድን ማጎስቆል (ስስትን መግደል)፣ ትጋሃ ሌሊት (ሌሊቱን ሙሉ መቆም)፣ ጥቂት ውኃ መጠጣት፣ ቍራሽ ዳብ መብላት (ከፊለ ኅብስት)፣ በተዋርዶ ድርቅ መንጻት፣ መናቅ፣ ፌዝን መቀበል፣ መሰደብ፣ የገዛ ፈቃድን ቆርጦ መጣል፣ በሚያስቆጣ ነገር መታገሥ፣ ባለ ማጉረምረም ንቀትን መታገሥ፣ ስድቦችን ቸል ማለት፣ ያልተገባ ጠባይን ጸንቶ መታገሥ፤ ሲታሙ አለመቆጣት፣ ሲዋረዱ አለመቆጣት፣ ሲነቀፉ ትሑት መኾን ነው። የገለጽናቸውን ጎዳናዎች የሚከተሉ ብፁዓን ናቸው፣ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ማቴ 5፡3-13።" እንዲል ዮሐንስ ዘሰዋስው። (ሳሙኤል ፍቃዱ (ተርጓሚ)፣ ምዕራግና ድርሳን፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 102)።

በዚህ አባት ጽሑፍ ውስጥ አንደኛ ራሳችንን መመርመር እንዳለብን ተገልጿል። ልቅ በኾነው ሰፊ መንገድ በተባለው የዓለማዊነት መንገድ ላይ መኾን አለመኾናችንን በትኩረት እንድናስተውል ምክረ ሐሳብ ቀርቧል። ኹል ጊዜም ቢኾን ትክክለኛ ወደ ኾነው መንገድ ለመግባት አስቀድሞ የቆምንበትን መንገድ እና በዚያ መንገድ እንድንጓዝ ያደረገንን ውስጣዊ ፍላጎት መረዳት ያስፈልጋል። ምን ያህልስ ጊዜ ልቅ በኾነው የኃጢአት መንገድ ተጉዘን ይኾን? ምን ያህልስ የዚያ መንገድ ጣዕም በውስጣችን ቀርቶ ይኾን? እንዴትስ ከዚያ መንገድ መውጣት እንችላለን። እያልን በእርጋታ ለራሳችን ጥያቄ እያቀረብን ራሳችንን እንመርምር።

ኹለተኛው መሠረታዊ ነገር ጠባብ መንገድ ማለት ምን ማለት እንደ ኾነ የተገለጸበት ነው። ጥቂት መመገብን ከመለማመድ ጀምሮ ማንኛውንም ክፉ የተባሉ ነገሮችን የሚያደርጉብንን መታገሥ ተገቢ መኾኑን ያስረዳል። መንገዱን ጠባብ ያሰኘውም፥ የተገለጹትን ነገሮች ለመተግበር እጅግ የሚከብዱ ስለ ኾነ ነው። ጽድቁንና መንግሥቱን እያሰብን የምንኖር ከኾነ ግን ከባድ ሊኾኑ አይችሉም። ጠባቡ መንገድ ጣዕመ መንግሥተ እግዚአብሔርን እያሰቡ ኃጢአትን መጥላትን ማዕከል ያደረገ ነውና። የሚንቁንን፣ የሚሰድቡንን፣ የሚያሙንን መታገሥ ለብዙዎቻችን አስቸጋሪ ነው። በእውነትም የሚጠሉንን ላለመጥላት እየታገልንን ኹሌ ራሳችንን ትዕግሥትን ብናለማምድ እግዚአብሔር ይረዳናል። ትዕግሥት በእኛ ጥረት ብቻ ሳይኾን ከእግዚአብሔርም ጸጋ ኾኖ የሚሰጥም ነገር ነውና። እኛ ከልባችን ክፉን በትዕግሥት ስንቀበል እግዚአብሔር ጽናቱን ይሰጠናል። የጠባቡ መንገድ መድረሻው መንግሥተ እግዚአብሔር መኾኑን በሕሊናችን ውስጥ አስቀምጠን፥ መንግሥቱን እያሰብን እንኑር። አንድ ሯጭ ትኲረቱን በሙሉ የሚያደርገው ቀድመውት ያሉ ተወዳዳሪዎች ላይ እንደ ኾነ ኹሉ እኛም ትኲረታችንን ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር አቅጣጫ ካደረግን በእኛ ላይ የሚደረጉ ክፉ ነገሮችን ኹሉ ሳናያቸው ማለፍ እንችላለን።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
           

መዓዛ ሠናይ

06 Nov, 13:49


አልቆም ያለ ደም

"በኋላውም ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች፥ የደምዋም ፈሳሽ በዚያን ጊዜ ቆመ" ሉቃ. ፰፥፵፬

ከዐሥራ ሁለት ዓመትም ጀምሮ ደም የሚፈሳት ሴት ነበረች፥ ትዳርዋንም ሁሉ ለባለመድኃኒቶች ከስራ ማንም ሊፈውሳት አልተቻለውም። ደምዋ ፈስሶ አያልቅም ወይ? ዓሥራ ሁለት ዓመት ሙሉ? እንዴት ያለ ሕመም ነው?! ሰው በክፉ ሽታዋ እስኪርቃት ድረስ የማይቆም ደም። ባለ መድኃኒቶች ሊያቆሙት ያልቻሉትን የደም ጎርፍ የናዝሬቱ ባለ መድኃኒት በቀሚሱ ብቻ አቆመው። በልብሱ ጫፍ ብቻ። ሳያያት ሳይነካት እጁን ሳይጭንባት በልብሱ ጫፍ ብቻ የደምዋን ዝናብ እንዲያባራ አደረገው። የሕመምዋን ማዕበል ገሠጸው።

በልብሱ ጫፍ ብቻ የሚፈውስ ሐኪም እንዴት ያለ ነው? ቀጠሮ ሳይሠጥህ ሳያናግርህ ቀና ብሎ ሳያይህ ስትነካው ብቻ የምትድንበት ከሆነ እርሱ መድኃኒት የሚያዝ ሐኪም ሳይሆን ራሱ መድኃኒት ነው። የልብሱን ጫፍ የነካ ከዳነ ሥጋውን የበሉ ደሙን የጠጡማ ምንኛ ይድኑ ይሆን? ሊፈውሳት አስቦ አልነበረም የዓሥራ ሁለት ዓመት ሴት ልጅ ከሞት ሊያስነሣ መንገድ ሲሔድ ግን እግረ መንገዱን የዓሥራ ሁለት ዓመት የቁም ሙትዋን ፈወሳት። መድኃኔዓለም እንዲህ ነው። ወደ በሽተኛው ሳይሔድ በቃሉ ብቻ ተናግሮ ይፈውሳል፤ በሽተኛው ቤት ገብቶ በአልጋው ላይ ይፈውሳል። ሊፈውስ ሲሔድም ይፈውሳል። እናም የሴቲቱ አልቆም ያለ ደም በልብሱ ጫፍ ብቻ ቀጥ አለ።

ጌታዬ ሆይ የእኔንስ ደም የምታቆመው መቼ ነው? ምን ደም ፈስሶህ ያውቃል ካልከኝ ኃጢአት የሚባል ደም ሲፈሰኝ አይታይህም? አንተስ በቃልህ "ኃጢአታችሁ እንደ ደም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች" ብለህ የለ? እንደ ደም የቀላው የእኔ ኃጢአት ነው። ይኸው ሲፈስ ከሴቲቱ በላይ ቆየ። ላቆመው ብል አልቆም አለኝ። ያላሰርኩበት ጨርቅ፣ ያልሞከርኩት ቅባት፣ ያልሔድኩበት ባለ መድኃኒት የለም። ገንዘቤን ከሰርኩ እንጂ ኃጢአቴ ግን መቆም አልቻለም። እንዲያውም መጠኑ እየጨመረ ነው። ባሕር ሆኖ ሊያስጥመኝ የደረሰ የኃጢአት ደም ከብቦኛል።

ለእኔ የሚሆን የቀሚስ ጫፍ ታጣ ይሆን? እኔ እንደ ሴቲቱ ታላቅ እምነት የለኝም ቀሚስህ ግን አሁንም ኃይል አለው። ልትፈውሰኝ ና አልልህም ስታልፍ ግን ልዳስስህና ልዳን። ጉዞህን ሳላሰናክል ሰው ሳይሰማ በልብስህ ጫፍ ብቻ ደሜን አቁምልኝ። የእኔን ደሜን መግታት ላንተ ምንህ ነው? ደምህንስ አፍስሰህልኝ የለ? እባክህን ደሜ ሳይቆም ሌላ ዓመት አልሻገር። እኔ ኃጢአቴን "ያለፈው ዘመን ይበቃል" ማለት ቢያቅተኝም አንተ ግን ይበቃሃል በልልኝ። በእምነት ማጣት የታጠፈውን እጄን ወደ ልብስህ ጫፍ ዘርጋልኝ። እኔ ማቆም ያልቻልኩትን የበደል ደም ጸጥ አድርገህ "አንድ ሰው ዳስሶኛል ኃይል ከእኔ ወጥቶአል" በል። እነጴጥሮስም ይደነቁ እኔም በሰላም ልሒድ።

(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ - የኤፌሶን ወንዝ ገጽ 168-170)

መዓዛ ሠናይ

06 Nov, 13:49


የጌታ ስቅለት በአበው

"አደምን የፈጠሩ እጆቹ በመስቀል ቀኖች ተቸነከሩ ወዮ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ቀኖች ተቸነከሩ ወዮ የማይሞተው ሞተ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡"
ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ

“እጆቹን እግሮቹን በተቸነከረባቸው ችንካሮች መወጋቱንም እናምናለን፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ እርሱ ደዌያችንን ወሰደ ሕማማችንንም ተሸከመ፤ እኛን ለማዳን ኃጢአታችንንም ለማሥተሥረይ መከራ ተቀበለ እንዳለ፣ በባሕርዩ ሕማም የሌለበት ሲሆን በሥጋ የታመመ ነው፤ በእርሱ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ድነናል አለ፡፡ በተገረፈና በተቸነከረም ጊዜ በመከራው ሁሉ መለኮትን ሕማም ተሰማው የሚል ሰው ቢኖር የተለየ የተወገዘ ይሁን፡፡”
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ሊቀ ጳጳስ

‹‹የሚሠዋ በግ እርሱ ነው፤ የሚሠዋ ካህን እርሱ ነው፡፡ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም መሥዋዕት የሚቀበል እርሱ ነው፡፡ በፈቃዱ መከራን በሥጋው የተቀበለ መከራንም ሁሉ የታገሠ እርሱ ነው፡፡ እንደ በግ ሊሠዋ መጣ፤ በግ በሚሸልተው ሰው ፊት እንዳይናገር አልተናገረም፤ በአንደበቱ ሐሰት አልተገኘበትም፡፡››
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ

‹‹ታመመ ሞትን ከተቀበለበት ከሥጋ ጋር ተዋሕዶ በመስቀል ላይ በፈቃዱ ለሥጋውያን ሞተ፤ ባሕርየ መለኮት ሥጋን ተዋሕዶ በማኅፀን ካደረ ጀምሮ ሥጋ ገንዘቡ እንደመሆኑ በሥጋ ይኸንን ሥርዐት ፈጸመ፡፡ ለማይመረመር ለመለኮቱ ባሕርይ እንደሚገባ ደግሞ እርሱ ኅብስት አበርክቶ ሁሉን ያጠግባል፤ አይራብም፤ አይጠማም፤ አይደክምም፤ አያንቀላፋም፤ አይታመምም፤ አይሞትም፤ ሕይወትን ለሁሉ ይሰጣል፡፡ ዳግመኛ በዛ በሲኦል ተገዝተው ያሉ ነፍሳትን ያድን ዘንድ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወረደ በመለኮቱም ሲኦልን በዘበዘ››
ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ
    
‹‹ሙሴም ሞትን ያጠፋ ዘንድ አልቻለም፤ እርሱንም ይዞ ገዛው እንጂ፤ ከእርሱም በኋላ የተነሡ ነቢያትንም ሁሉ ሞት ገዛቸው እንጂ፡፡ ክርስቶስ ግን በቸርነቱ ለሁሉ ሕይወትን ሰጠ›› 
ቅዱስ አቡሊዲስ ዘሮም

‹‹ምትሐት ያይደለ በእውነት ተራበ፣ ተጠማ እንጂ፡፡ ዳግመኛም ከኃጥአን ከመጸብሐን ጋር በላ ጠጣ፤ ያቀረቡለትንም በላ፡፡ ራሱን አሳልፎ ለመስቀል ሰጠ፤ እጁን እግሩን ተቸነከረ፤ ጎኑን በጦር ተወጋ፤ ከእርሱም ቅዱስ ምሥጢር የተገለጠበት ደምና ውኃ ፈሰሰ /ወጣ/፡፡››
ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

መዓዛ ሠናይ

03 Nov, 07:44


🧲 የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቻናል

📚 ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት ብራና እና ወረቀት በpdf
መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥያቄ እና መልስ
📜 ኦርቶዶክሳዊ ግጥሞች
የግእዝ ቋንቋ ትምህርት
🎶 የኦርቶዶክስ የመዝሙር ግጥሞች
📙 ተከታታይ ትምህርቶች
📘 ስንክሳር የእየለቱ
📗 ብሂለ አበው
📓 መንፈሳዊ ተረኮዎች
📔 የአበው ምክር
📚 የተለያዩ መንፈሳዊ ትምህርቶች
🤵‍♂የመምህር ምህረተአብ አሰፋ ቻናል

የፈለጉትን መርጠው ይቀላቀሉ

🇹 🇪 🇼 🇦 🇭 🇪 🇩 🇴
📖█▓▒░►𝑶𝑷𝑬𝑵◄░►𝑶𝑷𝑬𝑵▒▓█📖
📖█▓▒░►𝑶𝑷𝑬𝑵◄░►𝑶𝑷𝑬𝑵▒▓█📖
📖█▓▒░►𝑶𝑷𝑬𝑵◄░►𝑶𝑷𝑬𝑵▒▓█📖
📖█▓▒░►𝑶𝑷𝑬𝑵◄░►𝑶𝑷𝑬𝑵▒▓█📖

መዓዛ ሠናይ

02 Nov, 10:27


📚ይህንን መንካት ያለባቸው ኦርቶዶክስ ብቻ ናቸው

የቱን መፅሀፍ ይፈልጋሉ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬📚 የቱን ኦርቶዶክሳዊ መፅሀፍ ማንበብይፈልጋሉ? የሚፈልጉትን መፅሀፍ በመንካትመፅሐፉን ያግኙ። መልካም ንባብ 📖▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬📘📚 መፅሐፍ ቅዱስ 📘📚 የዋልድባ ገዳም ታሪክ📘📚 መጽሐፈ አክሲማሮስ 📘📚 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት   📘📚 መጽሐፈ አሚን ወሥርዓት📘📚 ሰባቱ ምስጢራተ ቤተከርስቲያን 📘📚 ሐይማኖተ አበው📘📚 ራዕየ ማርያም 📘📚 መልክዓ እግዚአብሔር 📘📚 ታቦተ ፅዮንን ፍለጋ📘📚 ፍካሬ ኢየሱስ ወትንቢተ ሳቤላ📘📚 መርበብተ ሰሎሞን 📘📚 የቶ መስቀል ትርጉም📘📚 ትንሳኤ ዘኢትዮጵያ 📘📚 የ666 ሳይንሳዊ ምስጢር 📘📚 ህይወተ ቅዱሳን 📘📚 ውዳሴ ማርያም 📘📚 እመጓ📘📚 ዝጎራ 📘📚 መርበብት 📘📚 አንድሮሜዳ 1 & 2 📘📚የሳጥናኤል ጎል 1 - 4እና ሌሎችንም መፅሐፍት የሚያገኙበትመንፈሳዊ የቴሌግራም ቻናል ነው ።አሁኑኑ 𝐉𝐎𝐈𝐍 ብለው ይቀላቀሉን▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

መዓዛ ሠናይ

01 Nov, 17:57


ባስልዮስ ሆይ! ንገረኝ...

በዚህ ዓለም የሥራ መስክ ገበሬ መርከብ ለመንዳት የማይነሣው፣ ወይም ወታደሩ የግብርናን ሥራ የማይሠራው፣ ወይም ሙያው መርከብ ነጂ የኾነ ሰው ጦር እንዲመራ እልፍ ጊዜ ቢጎተትም እንኳ እሺ የማይለው ለምንድን ነው? እያንዳንዱ ያለችሎታው ቢሰማራ የሚከተለውን አደጋ አስቀድሞ ስለሚያይ አይደለምን? ታዲያ ጥፋቱ ቁሳቁስና ንብረት በሚኾንበት ኹኔታ አስቀድመን ብዙ የምናስብና ግፊትና ግዴታን የማንቀበል ኾነን ሳለ፥ ክህነትን እንዴት እንደሚይዙትና እንደሚያገለግሉበት ለማያውቁ ቅጣቱ ዘለዓለማዊ በኾነበት ኹኔታ ግን ያለብዙ ማሰብና ማሰላሰል እንዲሁ በዘፈቀደ ወደዚህ ዓይነት ታላቅ አደጋ ውስጥ ዘለን እንገባለንን? የሌሎች ሰዎች ግፊትስ ምክንያት ሊኾነን ይችላልን? አንድ ቀን ፈታሒ በጽድቅ ኰናኒ በርትዕ የኾነው እግዚአብሔር ይጠይቀናል፡፡ ይህ ሰበብም አያድነንም፡፡

ከምድራዊ ነገሮች ይልቅ በመንፈሳዊ ነገሮች ላይ ይበልጥ ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናልና፡፡ በትንንሽ ነገሮች ላይ ጠንቃቆች ስንኾን እንታያለንና፡፡ እስኪ ንገረኝ! አንድ ሰው የቤት ሥራ ሙያ ሳይኖረው ብትሠራልን ስንለው እሺ ብሎ ቢመጣና ከዚያ በኋላ ግን ዕንጨቱንና ድንጋዩን ቢያበላሽና የሠራው ነገር ወዲያውኑ ተበታትኖ ቢወድቅ በራሱ ፈልጎ አለመምጣቱና በሌሎች ግፊት ሥራውን መጀመሩ በቂ ምክንያት ሊኾነው ይችላልን? በጭራሽ! የሌሎችን ግፊትና ጥሪ አልቀበልም ማለት ነበረበትና በርግጥም ተጠያቂ ነው፡፡

ታዲያ እንዲህ እንጨትና ድንጋይ ለሚያበላሽ ሰው በጥፋቱ ከመጠየቅና ከመቀጣት ለመዳን ምንም ምክንያት ከሌለው፥ ነፍሳትን የሚያጠፋ፣ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በግድየለሽነት የሚያንጽ ሰው’ማ እንዴት? የሌሎች ግፊትና ማስገደድ በቂ ምክንያት ይኾነኛል ብሎ ሊያስብ ይችላልን? እንዲህ ብሎ ማሰብስ ሞኝነት አይደለምን?

ፈቃደኛ ያልኾነን ሰው ማንም ሊያስገድደው እንደማይችል ለማሳየት ብዬ ሐተታ መስጠት አያስፈልገኝም፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት እንደ ተናገርኩት ይህ ፈቃደኛ ያልኾነ ሰው እጅግ ተጭነዉትና ግድ ብለዉት ሌሎች ብዙ መንገዶችንም ተጠቅመው ወደዚህ ኃላፊነት አመጡት እንበል፡፡ ታዲያ ይህ ከቅጣት ሊታደገው ይችላልን? እማልድሃለሁ፤ በፍጹም ራሳችንን አናታልል! ሕፃናት ሳይቀሩ በቀላሉ በሚያውቁት ነገር ላይ እንደማናውቅ ኾነን አናስመስል፡፡ እንደማናውቅ ማስመሰላችን በዚያች ዕለት ላይ በእውነት ያለ ሐሰት ምንም አይጠቅመንምና፡፡

(በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - በእንተ ክህነት መጽሐፍ)

መዓዛ ሠናይ

01 Nov, 09:27


"ብርሃን ወደ አንድ ቤት ውስጥ ሲገባ ጨለማን እንደሚያስወግድ ሁሉ፤ እግዚአብሔርን መፍራት ወደ አንድ ሰው ልብ ሲገባም አለማወቅን (በኃጢአት የሚወድቅባትን) ያስወግዳል።"

አባ እንጦንስ

መዓዛ ሠናይ

01 Nov, 09:27


አንድ ምድራዊ ንጉሥ "ጠላቱን ያልወደደ ሰው በሞት ይቀጣል" ብሎ አዋጅ ቢያውጅ ሁሉም ሰው በአካለ ሥጋ ላለመሞት ሲል ሕጉን ለመጠበቅ የሚፋጠን አይደለምን? ወዮ! ምድራውያን ነገሥታት በሥጋዊ ሞት እንዳይቀጡን ብለን ፈርተን የሚያወጡትን ሕግ ለመፈፀም የምንፋጠን ሆነን ሳለ፥ ለነገሥታት ንጉሥ ለእግዚአብሔር ሕግ አለመታዘዛችን እንደ ምን ያለ ወቀሳ ያመጣብን ይሆን?

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)

መዓዛ ሠናይ

01 Nov, 09:27


ልጆቼ፦ እግዚአብሔርን በእምነት በፀሎት እንሻው ከእኛ የጠፋ ገንዘባችንን ነቅተን ተግተን በብዙ ድካም እንድንሻው እንዲሁ ሃሳባችንን ወደ እግዚአብሔር ልናቀርብ ይገባናል፤ ልጃችን ቢጠፋብን ፈልገን በቅርብ ያላገኘነው እንደሆነ ሃይላችንን በድካም ድካማችንን በሃይል የምንለውጥ አይደለንምን? የጠፋውን ልጃችንን ስለመፈለግስ እናገኘው ዘንድ የብሱን በእግር ባህሩን በመርከብ የምንዞር አይደለንምን? ፈልገንም ያገኘነው እንደሆነ ዳግመኛ እንዳይጠፋብን ለመጠበቅ እንተጋ የለምን?

እንዲህ ከሆነ መሐሪ እግዚአብሔርን በእምነትና በፀሎት እንሻው ዘንድ ምን ያህል ይገባን ይሆን? እግዚአብሔርን ፈልጉት ነጋዴ ወርቅ ቢጠፋበት ወርቁን ያገኘው እንደሆነ ሁሉን ቦታ እንደሚፈልግ እንዲሁ እግዚአብሔርን ፈልጉት እናት ልጇ ቢጠፋባት እስክታገኘው ድረስ አርፋ እንደማትቀመጥ እንዲሁ እግዚአብሔርን ፈልጉት እግዚአብሔርን እሹት ፈልጉት እስክታገኙት ድረስ በእምነት በፀሎት እሹት፡፡”

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

መዓዛ ሠናይ

01 Nov, 09:27


"ብዙ ጊዜ ሰዎች ብልህ ነን እያሉ ይሳሳታሉ። ነገር ግን ብልህ የሚባሉት ብዙ የተማሩና ብዙ ያነበቡ ብዙ የሚናገሩ ብቻ አይደሉም። ይልቁንም ጠቢባን የሚባሉት ጥብብት መጥበቢት ብልህ ነፍስ ያላቸው፤ የእግዚአብሔርንና የሰይጣንን ለይተው ለእግዚአብሔር ሆነው የሚኖሩ ናቸው። ፍጹም ምልዓተ ኃጢአትንና ከጦር ይልቅ የሚወጉ የኃጢአት እሾሀቸውን የነቀሉ ናቸው ጠቢባን።

ጠቢባንስ እግዚአብሔርን ያለጥርጥር በሙሉ ልብ የሚያምኑት፤ አምነውም እንደ ፈቃዱ የተከተሉት፤ በክንፈ ጸጋ ተመስጠው ከልብ በሚወጣ ውዳሴ ከእርሱ ጋር ተዋሕደው የሚኖሩ ናቸው። የነፍሳቸውን ረብሕ ጥቅም አውቀው ዕለት ዕለት ያንን የሚለማመዱ በእውነት ጠቢባን እነዚህ ናቸው።"

(ቅዱስ አባ እንጦንስ)

መዓዛ ሠናይ

21 Oct, 11:16


ሰላም ቤተሰቦች
-ብሮሸር
_ማህተም-stamp design
- ባነር - Banner
-Business card
- አልበም ከቨር ዲዛይን - Album Cover
- መጽሐፍ ከቨር ዲዛይን - Book cover
- ሎጎ - Logo
-የሰርግ መጥርያ-invitation card
-ቲሸርት-T shirt

ላይ ካለው ከተጠቀሱት ውስጥ ማሰራት የምትፈልጉ በተመጣጣኝ ዋጋ እንሰራለን   +251928606993

መዓዛ ሠናይ

18 Oct, 05:45


ተግሣፅ ዘቅዱስ ኤፍሬም

ሕይወትህን በአግባቡ መምራት ትፈልጋለህን? እንግዲያውስ ትሕትናን ተለማመድ፤ ያለ ትሕትና ተገቢውን ሕይወት መምራት አይቻልም፡፡ ሥራህን ሁሉ በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ጀምር፡፡ ያን ጊዜ ፍሬዎችህ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይደርሳሉ።

ሰው ከትሕትና ከራቀ ከትክክለኛው መንገድ ርቋል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔርን የተወ ሰውን ርኵስ መንፈስ እንደ ሳውል ያስጨንቀዋል። የጠላት ወጥመድ በማር የተቀባ ነው፡፡ በማር ጣዕም የሚማረክ ሰው ሐዘንን ሁሉ በያዘ ወጥመድ ይያዛል። ትሕትናን ውደዱ፤ ያን ጊዜ ከሰይጣን ወጥመድ ውስጥ አትወድቁም፡፡ በትሕትና ክንፍ በበረራችሁ ቁጥር ሁል ጊዜ ከጠላት ወጥመድ በላይ ትሆናላችሁ።

ግልፍተኝነት እንደ በሰበሰ ረጅም ዛፍ ነው፤ ቅርጫፎቹ ሁሉ በቀላሉ የሚሰበሩ ናቸው᎓᎓ አንድ ሰው በወጣባቸው ጊዜ ከወጣበት ከፍታ ወዲያውኑ ይወድቃል፡፡ በመልካም ሐሳብ ልቡናው የበራ ሰው ግን ምስጉን ነው፤ ክብሩም ታላቅና ዘላለማዊ ነው።

እንግዲህ ራሳችንን ለመቆጣጠር እንጣር ያን ጊዜ ኃጢአታችንን እንረዳለን፡፡ ያን ጊዜም ሁል ጊዜ ራሳችንን ዝቅ እናደርጋለን፤ እንደ እባብ በእብሪት መወጠርን እና ራሳችንን ከፍ ከፍ ከማድረግ እንቆጠባለን፡፡ እንግዲህ ራሳችንን ዝቅ ዝቅ ማድረግን እንውደድ፤ በንጹሕ ልቡና ሆነን ምናልባት የተሰጠንን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በኃጢአት ከማቆሸሽ እንታደግ ይሆናል።

መልካም ጸሎት በሳግ እና በዕንባ የታጀበ ነው፤ በተለይ ደግሞ በምሥጢር የሚፈስ ዕንባ፣ በልቡናው ከፍታ ሆኖ የሚጸልይ ጌታውን በፊቱ ያያል። እኛ የምንኖረውና የምንሔደው በእርሱ ፈቃድ ነውና። ልቡናችሁ ከጠነከረ በጌታችን ፊት አልቅሱ እርሱ የዕውቀትን ብርሃን ይገልጥላችኋል፤ ወደ እርሱ የሚወስዳችሁ አዲስ ልብንም ይሰጣችኋል።

ንስሓ የገቡና ምሕረት የለመኑ ሰዎች ዕዳቸው ተሰረዘላቸው፤ ነገር ግን ለሠራኸው በደል ምሕረት ስትለምን ወንጀልን እና በደልን፤ በወንድምህም ላይ ቂም መያዝን መተው ይገባሃል። ፍቅር ሳይኖርህ ወደ እግዚአብሔር የምታደርገው ልመና ከተዘጋው በር ውጭ ይቀራል፡፡ የጸሎትን በር የሚከፍት ፍቅር ብቻ ነው፡፡

ወንድምህን ብታስቀይም እግዚአብሐርን ታሳዝናለህ፤ ካንተ ጋር ካለው ከወንድምህ ጋር ሰላምን ከፈጠርህ ግን በሰማይ ካለው ከእግዚአብሔር ጋር ትታረቃለህ፡፡ ወንድምህን በፍቅር ብትቀበለው፣ በደሉንም ይቅር ካልከው እግዚአብሔርን ተቀበልክ፡፡

ስለዚህ በተናደዱ ሰዎች በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ታረቅ፤ እንግዲህ የተበሳጩትን በማስደሰት እግዚአብሔርን አስደስተው፣ በታሰሩት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን ጎብኘው፣ በተራቡት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አብላው፤ በታረዙ ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አልብሰው፣ መንገደኛን በመቀበል እግዚአብሔርን በአልጋህ ላይ አስተኛው፤ እግሮቹንም እጠበው፣ በማዕድህም አስቀምጠው፣ እንጀራህንም ከእርሱ ጋር ተካፈል፤ ጽዋህንም ስጠው᎓᎓ እርሱ ታላቅ ፍቅሩን አሳይቶሃልና፤ እርሱ ስለ አንተ ብሎ ትበላው ዘንድ ሥጋውን ቆርሶልሃል፣ ትጠጣው ዘንድም ደሙን አፍስሷል።

(ድርሳነ ቅዱስ ኤፍሬም ገጽ 334 - 336  በዲ/ን መዝገቡ ከፍያለው የተተረጎመ)

መዓዛ ሠናይ

16 Oct, 14:54


ቅምሻ ፪ - ከአሐቲ ድንግል

ድንግል ማርያም እግዚአብሔር ስለመረጣት ነው ንጽሕት የሆነችው ወይስ ንጽሕት ስለሆነች ነው እግዚአብሔር የመረጣት?

አንዳንዶች ስለ ድንግል መመረጥ ሲነገር ሲሰሙ ሲመርጣት ላትመረጥ ነውን? እርሱ ጠበቃት እንጂ እርስዋ ምን አደረገች ሲሉ ይሰማሉ። እግዚአብሔር ሰለመረጣት ነው ንጽሕት የሆነችው የሚለው አደገኛ ክህደት ነው። ለምን ቢሉ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሰጠውን ነፃ ፈቃድ የሚንድ ነውና። ዳግመኛ እርሷ እግዚአብሔር ስለመረጣት ብቻ ከሆነ ንጽሕት የሆነችው እያንዳንዱ ሰው ንጹሕ የማይሆነው እግዚአብሔር ስላልመረጠው ነው ወደሚል የቅድመ ውሳኔ ክህደት የሚያመራ ጠማማ መንገድ ነው።

እንዲህ ከሆነ ደግሞ በዓለም ላይ ለሚሠሩ የርኩሰትና የአመፅ የበደል ውድቀቶች ሁሉ ተጠያቂው እግዚአብሔር እንጂ ሰው አይደለም ብሎ እግዚአብሔርን መሳደብ ነው። ምክንያቱም እግዚአብሔር የመረጠው ብቻ ንጹሕ ከሆነ ሁሉም የመንጻት ሥልጣን ካልተሰጠው በበደለኛነት ዘመናቸውን የፈፀሙ ሰዎች ተጠያቂ መሆን የለባቸውም፤ ከኃጢአት ለመንጻት ቢፈልጉ እንኳን አልተመረጡምና አይችሉም ማለት ነዋ! እንዲህ ከሆነ ሰዎች ሁሉ ሊድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ የሚወድ እግዚአብሔር (ጢሞ. ፪፥፫) ፈቃዱ ወዴት አለ? እርሱ የመረጣቸው ብቻ የሚነጹ ከሆነ ባልመረጣቸው ላይ ለምን ይፈርድባቸዋል? ፈታሒ በጽድቅነቱስ ወዴት አለ?

ነገር ግን ርቱዕ የሆነው የሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን የቀና የጸና አስተምህሮዋ እንዲህ አይደለም። እግዚአብሔር ሰዎችን ፍጻሜያቸውን አስቀድሞ አይቶ ይመርጣል እንጂ ወስኖ መርጦ የፈጠረው ሰው የለም። በወንጌል የእግዚአብሔር መንግስት በመካከላችሁ ናት ማለቱም ሰው ለመዳን የሚያስችለው ለመምረጥ የሚያበቃው ኃይል በእጁ እንዳለ ሲያጠይቅ ነው። በስሙ ለሚያምኑ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው የተባለውም ለዚህ ነው። በስሙ ለሚያምኑ የተሰጣቸው ስልጣን  የተባለው ለመዳንም ላለመዳንም የሰው ነፃ ፈቃድና ልጅነት እንደተሰጠ ሲያስረዳ ነው። እግዚአብሔር ወደ አቤልና ወደ መስዕዋቱ ተመለከተ የተባለውም አቤል የልቡን ቅንነት የመስዕዋቱን መበጀት ስሙርነት አይቶ ተመልክቶ አቤልን ተቀበለው እንጂ አቤል እንዲያ እንዲሆን አድርጎ ወሰኖ መርጦ አልፈጠረውም። በአንፃሩ ወደ ቃየልና መስዕዋቱ አልተመለከተም ማለት የቃየልን የልቡን ጥመት አየና የመስዕዋቱን አለመበጀት አይቶ አልተቀበለውም  ነገር ግን እግዚአብሔር ለክፋት ወስኖ አልፈጠረውም። እግዚአብሔር ሲኦል የሚገቡ ሰዎች እንዳሉ አውቆ ሲኦልን አዘጋጀ እንጂ ሲኦል በሚገቡ ሰዎች ላይ አስቀድሞ እንዲገቡ አድርጎ ወስኖ አልፈጠረም።

እናቱ ድንግል ማርያምን ከእናቷ ማሕፀን መርገም እንዳይኖርባት የጠበቃት እርሱ ነው ቅድመ ዓለም የአምላክ እናት እንድትሆን የመረጣትም እርሱ ነው። ነገር ግን ፍፃሜዋን በነፍስ በስጋ በአፍኣ ንጽሕት እንድትሆን አውቆ መረጣት እንጂ እርሱ ሰለወሰነ የጠበቃት የመረጣት አይደለችም። በዘመኗ ሁሉ በቅድስናዋ ተሸልማ እንደምትኖር አውቆ ከመርገም አነጻት፥ ኖሮባት አይደለም እንዳይኖርባት ጠበቃት እንጂ!

መንፈስ ቅዱስ ጠበቃት አነፃት መባሉም ፍፃሜዋን አይቶ መርገም እንዳይኖርባት ጠበቃት ማለት ነው እንጂ በዓለም ኃጢአት እንዳትሰራ ከለከላት ማለት አይደለም። ንጹህ ሆኖ መፈጠርማ አዳምም ተፈጥሮ ነበር በተፈጥሮ የተሰጠውን ንጹህ ጠባይ በቅድስና መጠቀም አልተቻለውም እንጂ እርሷ ግን ንጽሕናን ቅድስናን ደራርባ ይዛ ተገኝታለችና በዛው ድንግልናዋ ለአምላክ እናትነት በቃች። የሕይወት ፍሬን አፈራችበት እንዲመርጣት እግዚአብሔርን የሳበ በአምላክ ዘንድ ሞገስን የያዘ ንጽሕና ይዛ ተገኝታለችና እንድትመረጥ ሆና ተገኝታለች። ንጹሃንን ለክብር መምረጥማ ለፈጣሪ ድንቅ አይደለም ከእርስዋ ይልቅ ጠላቶቹን እኛን በደሙ ፈሳሽነት ይቅር ማለቱ አይደንቅምን?.......(ቀጣዩን መጽሐፉን ገዝተው ያንብቡ)

(ከርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ አሐቲ ድንግል ገፅ 272-277 ላይ የተቀነጨበ)

መዓዛ ሠናይ

15 Oct, 17:25


"ልጆቻችሁን ይዛችሁ ወደ ቤተክርስቲያን ኑ! ብቻችሁን አትምጡ፡፡ ብቻችሁን ከመጣችሁ ወደ ሌላ ይሔዳሉ እናንተ እዚህ መጥታችሁ የምትሰሩትን አያውቅም፡፡ ወዴት እንደሔዳችሁ አያውቅም፡፡ ወራሾቻችሁ አይሆንም፡፡

ስለዚህም ወደ ቤተክርስቲያን ስትመጡ ልጆቻችሁን ይዛችሁ ኑ፡፡ አሳዩአቸው ሥዕሉን ይሳሙ ቅዳሴ ጠበል ይጠጡ በእምነት አሻሹአቸው መስቀል እንድስሙ አስተማሯቸው ዕጣኑን ያሽትቱ ሥጋ ወደሙን ይቀበሉ ቃጭሉን ይስሙ ደውል ሲደውል ይስሙ ቄሳቸው ማን እንደሆነ ቤተክርስቲያናቸው ምን እንደሆነች በውስጧ ምን ምን እንደሚሰራ ያጥኑ ይማሩ።

ወደ ሰንበቴው እጃችሁን ይዘው ይከተሉ ወደ ማህበር ስትሔዱም ይዛችኋቸው ሂዱ ቆሎውን ዳቦውን ተሸክመው ወደ ሰንበቴው ይምጡ ይማሩ እነርሱም ነገ ይሄን እንዲወርሱ የነገ ባለአደራዎች መሆናቸውን እንዲያውቁ።"

ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ

መዓዛ ሠናይ

14 Oct, 14:49


#ከበሮ_ለምን_ይጮሀል?

የኔታ ለተማሪዎቻቸው አንድ ጥያቄ አቀረቡ "ልጆች ከበሮ ለምን ይጮሀል?" የኔታ በቆዳ ስለተወጠረ ነው" አለ አንድ ተማሪ የዳዊት ማህደሩን በእጁ አንጠልጥሎ ለመመለስ እየቸኮለ። የኔታም "አይደለም!" አሉ ሌላኛው ተማሪም "የኔታ ከእንጨት ስለተሠራ ነው" አለ የለበሰውን ለምድ ከፍ ከፍ እያደረገ የኔታም ትንሽ ዝም ካሉ በኋላ "አይደለም!" አሉ ተማሪው ሁሉ ማውጣት ማውረድ ጀመሩ በሀሳብ ተወጠሩ።

ሁሉም የመጣለትንና የገመተውን መናገር ቀጠለ ግን የሚመልስ ጠፋ። አንድ የሁሉንም ምላሽ በእርጋታ ይሰማ የነበረ ተማሪ እጁን አወጣ። "እሽ ልጄ" አሉ የኔታ። ልጁም ድምፁን ከፍ አደረገና "የኔታ እድሉን ስለ ሰጡኝ አመሰግናለሁ" ብሎ እጅ ከነሳ በኋላ "የኔታ ከበሮ የሚጮኸው #ባዶ_ስለሆነ ነው" አለ።

የኔታም የልጁን ምላሽ በማድነቅ ከወንበራቸው በመነሳት "ልጄ ተባረክ" አሉ። ተማሪዎቹም በጭብጨባ አጀቡት። የኔታም ቀጠል አደረጉና ልጆች "ባዶ የሆነ ነገር ሁሉ ይጮሀል በውስጡ የሆነ ነገር ያለው እቃ ግን አይጮህም። የተማረም ሰው እንዲሁ ነው።

እውቀት ያለው አይጮህም፣ ጥበብ ያለው አይጮህም፣ ምንጊዜም ባዶ የሆነ ሰው ሲጮህ፣ ጥበብ የሌለው ሲፎክር እውቀት የሌለው ሲያቅራራ ይታያል። እና ልጆቼ እናንተ "ባዶ" እንዳትሆኑ እውቀትን ጨምሩ፣ በእውቀት ላይ ጥበብን፣ በጥበብ ላይ እግዚአብሔርን መፍራት ጨምሩ።

ምድራችንን በማስተማር እና በመስበክ የሞሉ ግን 'ባዶ' የሆኑ። ምድሪቱን በዝማሬ የሞሉ በሃይማኖት እና በምግባር ግን 'ባዶ' የሆኑ። ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚሉ ግን ጌታ የማያውቃቸው እንደ ሰው ተፈጥረው እንደ እንሰሳ በደመ ነፍስ የሚኖሩ ሰዎች ፣ በዝተዋልና" ብለው ቁጭ አሉ። ተማሪዎቹም የኔታን አመስግነው ትምህርታቸውን ቀጠሉ።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
              

መዓዛ ሠናይ

08 Oct, 14:46


በመስቀል ምልክት ሳታማትብ ከቤትህ አትውጣ፡፡ በትር፣ መሳሪያ፣ የማይበገር ምሽግም ይሆንሀል፡፡ ሰውም ሆነ ጋኔን አንተን ለማጥቃት አይደፍሩም፤ እንደዚህ ያለ ኃይለኛ የጦር ትጥቅ ታጥቀሃልና፡፡ ይህም አንተ ልክ እንደ ወታደር እንደሆንክ፣ ከአጋንንት ጋር ለመዋጋት ዝግጁ እንደሆንክ፣ በድልም አክሊልን እንደምታገኝ ምልክት ነው፡።

መስቀሉ ያደረገውን አታውቁምን? ሞትን አሸንፏል፣ ኃጢአትን አጥፍቷል፣ ሲኦልን ባዶ አድርጓል፣ ሰይጣንን ከዙፋን አውርዷል፣ አጽናፈ ዓለሙንም ወደ እግዚአብሔር መልሷል፡፡

ታዲያ ኃይሉን ትጠራጠራለህ? መስቀሉ ይህን ኹሉ ድንቅ ነገር አድርጎልናል፤ መስቀል በአጋንንት ፊት የቆመ የሽንፈታቸው መታሰቢያ ነው፤ ክርስቶስ እባቡን የገደለበት ሰይፍም ነው:: መስቀል የአብ ፈቃድ፣ የአንድያ ልጁ ክብር፣ የመንፈስ ቅዱስ ደስታ፣ የመላእክት ውበት፣ የቤተክርስቲያን ጠባቂ ነው፡፡ ጳውሎስም እንዳለው መስቀል የቅዱሳን መከታ ነው፤ የዓለም ኹሉ ብርሃንም ነው፡፡

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ➛የነፍስ ምግብ ገጽ 78 በፍሉይ ዓለም የተተረጎመ)

መዓዛ ሠናይ

07 Oct, 14:39


"የመሬት መንቀጥቀጥ የእግዚአብሔርን ቍጣ የሚናገር ዐዋጅ ነጋሪ ነው፡፡ ቀድሞ ይከሰትና ፈሪሐ እግዚአብሔርን ገንዘብ አድርገን እንድንለወጥና መዓቱን ከእኛ እንድናርቅ ያደርገናል፡፡"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ➛ የክርስቲያን መከራ ገጽ 88 ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው

መዓዛ ሠናይ

06 Oct, 08:42


መሰከረም 26  እንኳን ለፆመ ፅጌ በሰላም አደረሳችሁ

እመቤታችንን የሚወዷት በደስታዋ ጊዜ አብረው የሚደሰቱ በሀዘኗና በጭንቀቷ ጊዜ በፆምና በማህሌት ከአባ ጽጌ ድንግልና ከአባ ገብረ ማርያም ጋር የሚያመሠግኗት አረጋዊው ዮሴፍንና ቅ.ሰሎሜን የሚመስሉ ሰዎች ምንኛ የታደሉና የተወደዱ ሰዎች ናቸው

ዳግመኛም በዚች ቀን  ቅዱሰ ዮሐንሰ መጥምቀ መለኮት ፅንሰቱ ነው ፆሙ በረከተ ሥጋ ወነፍሰ የምናገኝበት ይሁንልን

ከእመቤታችንና ከቅዱሳን  እረዴት በረከት ያካፍለ፡፡

መዓዛ ሠናይ

05 Oct, 06:39


❤️እንኳን ለጽጌ ፆም አደረሳቹ?

መልካም ጾም እያልኩኝ እንዚህን ከታች የምታዩዋቸውን ቻናሎች ጋበዝኳችሁ!

https://t.me/addlist/uXhiFffRAV5mYTk8

መዓዛ ሠናይ

05 Oct, 06:13


የመስቀል በዓል መዝሙሮችን ለማጥናት👇👇
መስቀል አበባ.mp3
🎶መስቀል ተመሬኩዘን.mp3
🎶ደስ ይበለን.mp3
🎶እሰይ እልል በሉ.mp3
🎶ዮም መስቀል.mp3
🎶ቤተከርስቲያን ርእየቶ.mp3
🎶በመስቀሉ ቤዘወነ.mp3
🎶መስቀሉሰ.mp3
🎶መስቀል ብርሃን.mp3
🎶አለው ሞገስ.mp3
🎶መስቀል አብርሃ.mp3
🎶ርዕዩ ዕበዩ.mp3
🎶በኃይለ መስቀሉ.mp3
🎶ተሰኢነነ.mp3
🎶ትቤሎ ዕሌኒ.mp3
🎶ወይቤሎ መስቀል.mp3
🎶ኧኸ በመስቀልከ.mp3
🎶ወበእንተዝ አዘዙነ.mp3
🎶ዝንቱ መስቀል ረድኤት.mp3
🎶ደስ ይበለን.mp3
🎶መስቀል አበራ.mp3........
እነዚህን ለማጥናት Join አድርጉ
    join join join
     Join joinjoin

መዓዛ ሠናይ

04 Oct, 16:04


ልጄ ሆይ ማናቸውንም ነገር በምትፈፅምበት ጊዜ ሥራህን በፀሎት ጀምር። የምትሰራቸውን ሥራዎች ሁሉ በትምህርተ መስቀል ባርካቸው።

በምትበላም፣ በምትጠጣም ጊዜ፣ በምትተኛም፣ በምትነቃም ጊዜ፣ በቤት ውስጥም ሳለህ ይሁን በጎዳና፣ ማማተብን አትዘንጋ። የጌታህን ስቅለት አስታውሶ ከክፋት የሚጠብቅህ ይህን የመሰለ ጠባቂ ከቶ አታገኝም።

እርሱ ለምታደርጋቸው ድርጊቶችህ ሁሉ እንደ ግንብ ነው (ማስተዋልን ይሰጥኻል)። ማማተብን በስርዓት ይፈፅሙት ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት ሁሌም በፊታቸው ይስሉ ዘንድ ለልጆችህ በጥንቃቄ አስተምራቸው።

#ሊቁ_ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ

መዓዛ ሠናይ

30 Sep, 13:00



ቤተ ክርስቲያን እና ሆስፒታል
(በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)

እግዚአብሔር የሚወዳችሁ አንድም እግዚአብሔርን የምትወዱት ልጆቼ! ተጠራርታችሁ ወደ አባታችሁ ቤት ለመምጣት ያደረጋችሁትን ቅንአት ተመልክቼ ደስ ተሰኝቼባችኋለሁ፡፡ እኔም ይህን ቅንአታችሁን አይቼ ስለ ነፍሳችሁ ጤና ይበልጥ እንዳስብ አድርጎኛል፡፡

ቤተ ክርስቲያን ቀዶ ጥገና የሚደረግባት ሐኪም ቤት ናት፡፡ የሥጋ ቀዶ ጥገና ግን አይደለም፤ የነፍስ ቀዶ ጥገና ነው እንጂ፡፡ የምናክመው የሥጋን ቁስል አይደለም፤ መንፈሳዊ ቁስልን እንጂ፡፡ መድኃኒቱም ቃለ እግዚአብሔር ነው፡፡ ይህ መድኃኒት በምድር ላይ ከሚበቅሉት ዕፅዋት የተቀመመ አይደለም፤ ከሰማያት ከሚመጣው ቃል እንጂ፡፡ ይህን መድኃኒት በቁስል ላይ ለመጨመር ሐኪሞች አያስፈልጉም፤ የሰባክያነ ወንጌል አንደበት እንጂ፡፡ ቀዶ ጥገናውን ለማከናወን ብዙ ሰዓታትን አይፈጅም፡፡ ቀዶ ጥገናው ላይሳካ ይችላል ተብሎ የሚጠረጠር አይደለም፡፡ ከጊዜ በኋላ ወይም በሌላ ሕመም ምክንያት የተደረገው ቀዶ ጥገና ሊከሽፍ ይችላል ተብሎም አይገመትም፡፡

ሐኪሞች የሚሰጡን መድኃኒት እንዲህ ዓይነት ችግር ሊያጋጥመው ይችላል፡፡ ሐኪሞች የሚሰጡን መድኃኒተ ሥጋ ለጊዜው ብርቱ ነው፤ ሰውነታችን እያረጀ እንደሚሔደው ኹሉ መድኃኒቱም በጊዜ ሒደት ብርታቱን እያጣ ይሔዳል፡፡ ሌላ ደዌ ዘሥጋ ሲገጥመንም መቋቋም የሚችል አይደለም፡፡ ምክንያቱም መድኃኒቱን የቀመሙት ሰዎች ስለኾኑ፡፡ ከእግዚአብሔር የሚሰጠን መድኃኒት ግን እንደዚህ አይደለም፡፡ ምንም ያህል ጊዜ ቢቆይም አይበላሽም፤ ጊዜው አያልፍበትም፤ ኃይሉም ብርታቱም ያው ነው አይቀንስም፡፡

ሙሴ የተቀበለው ቃለ እግዚአብሔር በጊዜው የነበሩትን ሰዎች ፈውሷቸዋል፤ አሁንም ያ ቃል ይፈውሳል፡፡ የመፈወስ ኃይሉ ብርታቱ እስከ አሁን ድረስ አላጣም፤ ሌላ ምንም ዓይነት በሽታም አላሸነፈውም፡፡ ይህን መድኃኒት ለመግዛት ብር አይበቃውም፤ ቅን ልቡና ብቻ ነው የሚያስፈልገው፡፡ በዚህ መድኃኒት ባለጸጋውም ድኻውም እኩል ይታከማሉ፡፡ ወደ ምድራዊው ሆስፒታል ሲኬድ ባለጸጋው ብር ስላለው ያሻውን ሕክምና አግኝቶ ወደ ቤቱ ይመለሳል፤ ድኻው ግን ብር ስለሌለው መድኃኒቱንም መግዛት ስለማይችል ሳይታከም ከነሕመሙ ወደ ቤቱ ይመለሳል፡፡ ይህ ከቤተ ክርስቲያን የሚሰጠው መድኃኒት ግን በብር የሚገዛ አይደለም፡፡ ይህን መድኃኒት ለማግኘት የሚያስፈልገውም ብር ሳይኾን እምነትና ምግባር ነው፡፡ እምነትና ምግባር የከፈለ ሰው ይህን መድኃኒት ማግኘት ይቻሏል፡፡ እነዚህን የከፈለ ጤናውን አግኝቶ ወደ ቤቱ ይመለሳል፡፡ በመኾኑም ድኻውም ባለጸጋውም እኩል ታክመውበት ይሔዳሉ፡፡ እንደዉም ከባለጸጋው ይልቅ ድኻው በመድኃኒቱ ይበልጥ ተጠቅሞ ይሔዳል፡፡ ለዚህስ ምክንያቱ ምንድነው? ምክንያቱም ባለጸጋው ብር ስላለው በብዙ ሐሳብ የተያዘ ነው፡፡ ሀብታም ነኝ ብሎ ስለሚያስብ ትዕቢተኛ ነው፡፡ ሕይወቱን የሚመራው በቸልተኝነት ነው፡፡ በስንፍና ስለሚያዝ መድኃኒት የኾነውን ቃሉን ለማድመጥ ስልቹ ነው፡፡ ድኻው ግን በቅንጦትና በስንፍና ኑሮ ስለማይኖር፣ ጊዜውን በእንተ ፈንቶ ነገሮች ስለማያሳልፍ መድኃኒተ ነፍሱን ለማግኘት ንቁ ነው፡፡ ቃሉን ለማድመጥ ፈጣን ነው፡፡ ቸልተኝነት አይጠጋውም፡፡ የተባለውን ለማድመጥ ልቡናው ዘወትር ዝግጁ ነው፡፡ የሚከፍለው ክፍያ ብዙ ነው ማለት ነው፤ የሚያገኘውም መድኃኒት እንደዚያ ብዙ ነው፡፡

ይህን ኹሉ ዘርዝሬ መናገሬ ግን ባለጸጋውን ኹሉ በደፈናው መኰነኔ አይደለም፡፡ ድኻውንም ኹሉ እንደሁ ማመስገኔ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ሀብት በራሱ መጥፎ አይደለም፤ መጥፎ የሚያደርገው የእኛ አጠቃቀም ነው፡፡ ድኽነቱም በራሱ በጎ አይደለም፤ በጎ የሚያደርገው የኛ አጠቃቀም ነው፡፡ ባለጸጋው ነዌ ወደ ሲዖል የተወረወረው ሀብታም ስለነበረ አይደለም፤ ጨካኝና ሰብአዊነት የማይሰማው ክፉ ስለነበረ ነው እንጂ፡፡ አልዓዛርም በአብርሃም ዕቅፍ የተቀመጠው እንዲሁ ድኻ ስለነበረ አይደለም፤ ድኻም ቢኾን አመስጋኝ ስለነበረ እንጂ፡፡

ይቀጥላል......

(ገብረ እግዚአብሔር ኪደ - ከመቅረዝ ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ)

መዓዛ ሠናይ

29 Sep, 07:10


የመስቀል በዓል መዝሙሮችን ለማጥናት👇👇
መስቀል አበባ.mp3
🎶መስቀል ተመሬኩዘን.mp3
🎶ደስ ይበለን.mp3
🎶እሰይ እልል በሉ.mp3
🎶ዮም መስቀል.mp3
🎶ቤተከርስቲያን ርእየቶ.mp3
🎶በመስቀሉ ቤዘወነ.mp3
🎶መስቀሉሰ.mp3
🎶መስቀል ብርሃን.mp3
🎶አለው ሞገስ.mp3
🎶መስቀል አብርሃ.mp3
🎶ርዕዩ ዕበዩ.mp3
🎶በኃይለ መስቀሉ.mp3
🎶ተሰኢነነ.mp3
🎶ትቤሎ ዕሌኒ.mp3
🎶ወይቤሎ መስቀል.mp3
🎶ኧኸ በመስቀልከ.mp3
🎶ወበእንተዝ አዘዙነ.mp3
🎶ዝንቱ መስቀል ረድኤት.mp3
🎶ደስ ይበለን.mp3
🎶መስቀል አበራ.mp3........
እነዚህን ለማጥናት Join አድርጉ
    join join join
     Join joinjoin

መዓዛ ሠናይ

22 Sep, 13:36


📚ይህንን መንካት ያለባቸው ኦርቶዶክስ ብቻ ናቸው

የቱን መፅሀፍ ይፈልጋሉ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬📚 የቱን ኦርቶዶክሳዊ መፅሀፍ ማንበብይፈልጋሉ? የሚፈልጉትን መፅሀፍ በመንካትመፅሐፉን ያግኙ። መልካም ንባብ 📖▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬📘📚 መፅሐፍ ቅዱስ 📘📚 የዋልድባ ገዳም ታሪክ📘📚 መጽሐፈ አክሲማሮስ 📘📚 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት   📘📚 መጽሐፈ አሚን ወሥርዓት📘📚 ሰባቱ ምስጢራተ ቤተከርስቲያን 📘📚 ሐይማኖተ አበው📘📚 ራዕየ ማርያም 📘📚 መልክዓ እግዚአብሔር 📘📚 ታቦተ ፅዮንን ፍለጋ📘📚 ፍካሬ ኢየሱስ ወትንቢተ ሳቤላ📘📚 መርበብተ ሰሎሞን 📘📚 የቶ መስቀል ትርጉም📘📚 ትንሳኤ ዘኢትዮጵያ 📘📚 የ666 ሳይንሳዊ ምስጢር 📘📚 ህይወተ ቅዱሳን 📘📚 ውዳሴ ማርያም 📘📚 እመጓ📘📚 ዝጎራ 📘📚 መርበብት 📘📚 አንድሮሜዳ 1 & 2 📘📚የሳጥናኤል ጎል 1 - 4እና ሌሎችንም መፅሐፍት የሚያገኙበትመንፈሳዊ የቴሌግራም ቻናል ነው ።አሁኑኑ 𝐉𝐎𝐈𝐍 ብለው ይቀላቀሉን▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

መዓዛ ሠናይ

21 Sep, 06:05


📚ይህንን መንካት ያለባቸው ኦርቶዶክስ ብቻ ናቸው

የቱን መፅሀፍ ይፈልጋሉ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬📚 የቱን ኦርቶዶክሳዊ መፅሀፍ ማንበብይፈልጋሉ? የሚፈልጉትን መፅሀፍ በመንካትመፅሐፉን ያግኙ። መልካም ንባብ 📖▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬📘📚 መፅሐፍ ቅዱስ 📘📚 የዋልድባ ገዳም ታሪክ📘📚 መጽሐፈ አክሲማሮስ 📘📚 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት   📘📚 መጽሐፈ አሚን ወሥርዓት📘📚 ሰባቱ ምስጢራተ ቤተከርስቲያን 📘📚 ሐይማኖተ አበው📘📚 ራዕየ ማርያም 📘📚 መልክዓ እግዚአብሔር 📘📚 ታቦተ ፅዮንን ፍለጋ📘📚 ፍካሬ ኢየሱስ ወትንቢተ ሳቤላ📘📚 መርበብተ ሰሎሞን 📘📚 የቶ መስቀል ትርጉም📘📚 ትንሳኤ ዘኢትዮጵያ 📘📚 የ666 ሳይንሳዊ ምስጢር 📘📚 ህይወተ ቅዱሳን 📘📚 ውዳሴ ማርያም 📘📚 እመጓ📘📚 ዝጎራ 📘📚 መርበብት 📘📚 አንድሮሜዳ 1 & 2 📘📚የሳጥናኤል ጎል 1 - 4እና ሌሎችንም መፅሐፍት የሚያገኙበትመንፈሳዊ የቴሌግራም ቻናል ነው ።አሁኑኑ 𝐉𝐎𝐈𝐍 ብለው ይቀላቀሉን▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

መዓዛ ሠናይ

20 Sep, 11:17


"ከፊትህ አንድ መመሪያ አስቀምጥ፤ ይህም በመንፈሳዊ ሕይወታህ ውስጥ የምትዋጋው ታላቁ ውጊያ፣ ከራስህ ጋር የምታደርገው ውጊያ ነው፤ ወደ ኅሊናህ የሚገባውን ማንኛውንም ዓይነት ክፉ ፍላጎት ተሸክመኸው አትዙር፤  ልትቆጠብ የማትችል ከኾነ ጉዳዩን ለጊዜው አራዝመው፤ ከዚህ በኋላ ጉዳዩን መላልሰህ ለማራዘም ራስህን አስገድደው፤ በማራዘም ውስጥ የእግዚአብሔር ጸጋ ስለሚጎበኝህ እርሱ ያጽናናሃል... በመንፈሳዊ ትጋትህ ውስጥ ቸልተኝነትህን፣ ግዴለሽነትህን እና ቁም ነገር ማጣትህን የሚገልጹ የተለያዩ ነገሮችን ወደ አንተ እንዲመጡ አትፍቀድ።"

(መንፈሳዊ መንገድ - ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ፤ ትርጒም በአያሌው ዘኢየሱስ)

መዓዛ ሠናይ

17 Sep, 05:37


መስከረም 7 የመጥምቁ ቅ.ዮሐንስ እናት ቅድስት ኤልሳቤጥ ያረፈችበት ቀን ነው
ከእመቤታችን በረከት ያካፍለን

መዓዛ ሠናይ

15 Sep, 15:43


#ወንድሞቼ_ሆይ ወደ ቤተ ክርስቲያን ውድ ስጦታዎችን ይዛችሁ ስትመጡ አያለሁ፡፡ መልካም አድርጋችኋል፡፡ ነገር ግን ስትመለሱ ደግሞ መበለቶችን፣ ደሀ አደጎችንና ሕጻናትን ስትበድሉ አያችኋለሁ፡፡ ታድያ ይህን ሁሉ እያደረጋችሁ በወርቅ የተንቆጠቆጠ ምሥዋዕና ጽዋዕ ብታቅረቡ ምን ይጠቅማችኋል? ለምንስ መሥዋዕቱን ማክበር ስትፈልጉ አስቀድማችሁ ልባችሁን መባ አድርጋችሁ አታቀርቡም? ልባችሁ በጭቃ ተጨማልቆ ምሥዋዑ እንኳን ወርቅ ፕላቲንየምስ ቢሆን ምን ይረባችኋል? ምንስ ይጠቅማችኋል?

#ተወዳጆች_ሆይ!
አመጣጣችን በወርቅ የተለበጠ መሠዊያ ለማቅረብ ሳይሆን ይኸን ከልብ በመነጨ ለማቅረብ ይሁን፡፡ ከልባችን የምናቀርበው ነገር ሁሉ ከወርቅ የበለጠ መባ ነው፡፡

#ልብ_በሉ!
ቤተ ክርስቲያን የወርቅ ወይም የነሐስ ማቅለጫ ቦታ አይደለችም፤ ለቅድስና የተጠሩ ሁሉ እና የመላእክት ኅብረት እንጂ፡፡ስለዚህ ከስጦታችሁ በፊት ልባችሁን ይዛችሁ ኑ፡፡ እግዚአብሔር እኮ ሥጦታችንን የሚቀበለው ደሀ ሆኖ ሳይሆን ስለ ነፍሳችን ብሎ ነው፡፡

#ክርስቶስን_ማክበር_ትወዳላችሁን?
እንግዲያስ ዕራቆቱን ስታዩት ችላ አትበሉት፡፡ እናንተ ወደ ቤተ መቅደስ ስትመጡ እጅግ ውድ በሆኑ ልብሶች አጊጣችሁ ስትመጡ እርሱ በብርድና በመራቆት ሊሞት ነውና ብያንስ ትንሽ እንኳን እዘኑለት፡፡ ቤተ መቅደስ ረግጣችሁ ቤተ መቅደስ አትምጡ፡፡ በቃሉ “ይህ ሥጋዬ ነው” ያለው ጌታ በተመሳሳይ ቃሉ “ተርቤ ስታዩኝ አላበላችሁኝም፤ ከሁሉ ከሚያንሱት ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም” ብሏልና።

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

መዓዛ ሠናይ

15 Sep, 05:58


📚ይህንን መንካት ያለባቸው ኦርቶዶክስ ብቻ ናቸው

የቱን መፅሀፍ ይፈልጋሉ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬📚 የቱን ኦርቶዶክሳዊ መፅሀፍ ማንበብይፈልጋሉ? የሚፈልጉትን መፅሀፍ በመንካትመፅሐፉን ያግኙ። መልካም ንባብ 📖▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬📘📚 መፅሐፍ ቅዱስ 📘📚 የዋልድባ ገዳም ታሪክ📘📚 መጽሐፈ አክሲማሮስ 📘📚 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት   📘📚 መጽሐፈ አሚን ወሥርዓት📘📚 ሰባቱ ምስጢራተ ቤተከርስቲያን 📘📚 ሐይማኖተ አበው📘📚 ራዕየ ማርያም 📘📚 መልክዓ እግዚአብሔር 📘📚 ታቦተ ፅዮንን ፍለጋ📘📚 ፍካሬ ኢየሱስ ወትንቢተ ሳቤላ📘📚 መርበብተ ሰሎሞን 📘📚 የቶ መስቀል ትርጉም📘📚 ትንሳኤ ዘኢትዮጵያ 📘📚 የ666 ሳይንሳዊ ምስጢር 📘📚 ህይወተ ቅዱሳን 📘📚 ውዳሴ ማርያም 📘📚 እመጓ📘📚 ዝጎራ 📘📚 መርበብት 📘📚 አንድሮሜዳ 1 & 2 📘📚የሳጥናኤል ጎል 1 - 4እና ሌሎችንም መፅሐፍት የሚያገኙበትመንፈሳዊ የቴሌግራም ቻናል ነው ።አሁኑኑ 𝐉𝐎𝐈𝐍 ብለው ይቀላቀሉን▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █       █    ✞   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒    ✞    █▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

መዓዛ ሠናይ

13 Sep, 13:49


"የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል"
1ጴጥ. 4÷3

3,885

subscribers

145

photos

6

videos