የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

@eotc2921


የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ የነፍስ ስንቅ የምናገኝበት፦
✍️"ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም" ፩ኛ ቆሮ. ፰፥፪
#ለተጨማሪ፦👇👇
https://www.youtube.com/EOTC2921 https://www.facebook.com/eotc2921 https://www.tiktok.com/@eotc2921 https://www.instagram.com/eotc2921

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

07 Sep, 11:42


🌻🕊 ሥርዓተ በዓል ወጾም ዘኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን 🕊🌻

❀✞ ዓመተ ምህረት፥ ፳፻፲፯(2017 ዓ.ም)
❀✞ ወንጌላዊ፥ ማቴዎስ
❀✞ የዘመን መለወጫ ቀን፥ ረቡዕ
❀✞ አበቅቴ፥ ፩(1)
❀✞ መጥቅዕ፥ ፳፱(29)
❀✞ ጾመ ነነዌ፥ የካቲት ፫(3)
❀✞ ዐቢይ ጾም፥ የካቲት ፲፯(17)
❀✞ ደብረ ዘይት፥ መጋቢት ፲፬(14)
❀✞ ሆሳዕና፥ ሚያዝያ ፭(5)
❀✞ ስቅለት፥ ሚያዝያ ፲(10)
❀✞ ትንሣኤ፥ ሚያዝያ ፲፪(12)
❀✞ ርክበ ካህናት፥ ግንቦት ፮(6)
❀✞ ዕርገት፥ ግንቦት ፳፩(21)
❀✞ ጰራቅሊጦስ፥ ሠኔ ፩(1)
❀✞ ጾመ ሐዋርያት፥ ሠኔ ፪(2)
❀✞ ምሕላ ድኅነት፥ ሠኔ፬(4)

🌻🌼✞ እንኳን አደረሳችሁ ✞🌼🌻
🌻🌼✞ እንኳን አደረሰን ✞🌼🌻

🌻🌻 በእግዚአብሔር ፈቃድ 🌻🌻
🌾መጪው ፳፻፲፯ ዓ.ም፦
🌻የተከፋ፣ የአዘነና የአለቀሰ፤ የሚደሰትበት።
🌻የተራበና የተጠማ፤ የሚጠግብበት።
🌻የተሰደደ፤ በሰላም ተመልሶ የሚኖርበት።
🌻ፍቅር፣ ዕምነትና ትዕግሥት፤ የምንጎናጸፍበት።
🌻ዕውቀቱን፣ ጥበብና ማስተዋሉን፤ የምናገኝበት።
🌻ከችግርና ከመከራ፤ ተላቀን በሐይማኖት በምግባር የምንጸናበት ዘመን ይሁንልን። ✞አሜን✞
🙏✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ልዑል ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ✞🙏

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

13 Aug, 10:04


#የስርዓተ_ቅዳሴ_ተሰጥኦ_መቀበያ

✞የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን አስተምሮና ስርዓት የጠበቁ የተለያዩ መርሃ ግብሮች በየቀኑ ወደ እርስዎ ይቀርባሉ፡፡ ለወዳጅዎ #Share በመድረግ የበረከት ተካፋይ ያድርጓቸው✞
╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮
@EOTC2921
╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

16 Jul, 17:30


•✞ አቤቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ✞•

•✞የምንኮራበት ክብራችን የምንደምቅበት አክሊላችን አንተ ነህ፤ ቀና ያልንብህ ትምክህታችን፥ ያረፍንብህ ክንዳችን አንተ ነህ፤ እግራችን እንዳይሰናከል የምትጠብቀን፥ እንዳንባዝን የምታረጋጋን አንተ ነህ፨

•✞ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ፍቅርህን የሚመስለው የለም፡፡ እንዳንወድቅ የምትጠብቀን ብንወድቅ የምታነሣን አንተ ነኽ፤ እንዳንደክም የምትራራልን ብንደክም የምታበረታን አንተ ነኽ፤ እንዳንታመም ባንተ እንታመናለን ብንታመምም ስላንተ ተስፋ አለን፤

•✞ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? እንዳንሰናከል መላእክቱን ስለእኛ አዘጋጀኽልን፥ ጠላቶች እንደበዙብን አይተኽ ወዳጆችን አበዛኽልን፤ ፈተናዎቻችንን አይተኽ መውጫውን ደግሞ አመላከትከን  የቀደመውን ፍቅራችንን ብንቀንስ ያንተን ፍቅር አበዛኽልን፨ •✞

•✞ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ራቅንኽ፥ አንተ ወደኛ ቀረብክ፤ በግብራችን ናቅንኽ አንተ ግን እኛን አከበርክ፤ ያለአንተ መኖር እንደማንችል ታውቃለኽና ክፋታችንን ሳታይ ራራኽልን ስንፍናችንን ሳታይ ቀረብከን፨•✞

•✞ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ተወዳጅ ሆይ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን?

•✞ማንም የለንምና ክብራችንን አውቀን እንኖር ዘንድ አንተን ሳናስብ የምንውልበት ጊዜ አይኑረን፤ ክብርና ምስጋና ላንተ ይኹን፡፡
✞ ቅዳሴ ያዕቆብ ዘስሩግ

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

28 Jun, 05:39


🌿🌾✞ #ድንግል_ማርያም_በሉ ✞🌾🌿

ድንግል ማርያም በሉ ምዕመናን ሁላችሁ
በአማላጅነቷ ጥላ ስር ያላችሁ
እንደኔ ከፍቅሯ ፍቅርን ያገኛችሁ/፪/ //፪//
#አዝ

የሐና የኢያቄም የበረከት ፍሬ
ድንግል ስጦታዬ ክብሬ ከለላዬ
ጥላሽን ጣይብኝ ያኔ እጽናናለሁ
አረጋጊኝ ድንግል ባንቺ ታምኛለሁ
#አዝ

ድንግል እመቤቴ ድካሜን እዪና
ፍርኃት ጭኝቀቴን አርቂልኝና
የሕይወትን ፍሬ ሁሌ እንዳፈራ
ነይልኝ እናቴ ከዮሐንስ ጋራ //፪//
#አዝ

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

13 Jun, 12:03


•✞• ተንሥኡ ለጸሎት •✞•

ፍጹም በሆነ ሙሉ እምነት፥
ፍጹም በተመሰጠ ልቦና ፥
በፍጹም መጸጸት ፥ በንፁህ ልቦና
እሰግድ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
እሰግድ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
እሰግድ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ (አሐተ ስግደተ)
እንዘ አሐዱ ሠለስቱ ወእንዘ ሠለስቱ አሐዱ
ይሤለሱ በአካላት ወይትወሐዱ በመለኮት
እሰግድ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
እሰግድ ለመስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተቀደሰ በደሙ ክቡር
መስቀል ኃይልነ፥
መስቀል ጽንዕነ፥
መስቀል ቤዛነ፥
መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ፥
አይሁድ ክህዱ ንኅነሰ አመነ ወእለ አመነ በኃይለ መስቀሉ ድኅነ።

•••
አምላኬ ሆይ
ስላደረግህልኝ ነገር
ስለምታደርግልኝ ነገር
ስላላደረክልኝ እና ስለማታደርግልኝም ነገር ሁሉ አመሰግንሃለሁ።
ምንም ብበድልህ በፍጹም ቸርነትህና ፍቅርህ ጠብቀህ፥ በሕይወቴ ላይ ይህችን ሰዓት ጨምረህ፥ በተቀደስው ስፍራህ ስላቆምከኝ አመሰግንሃለሁ።

መላእክትን በጽርሃ አርያም፥
ሰማእታትን በደም፥
ሐዋርያትን በአጽናፈ ዓለም፥
ጻድቃንን በገዳም ያጸናህ አምላክ፥ እኔንም በሃይማኖት፣ በጾም፣ በጸሎትና በምግባር እንድታጸናኝ እለምንሃለሁ።

አምላኬ ሆይ ምንም ዓይነት ፈተና እና መከራ ቢመጣብኝ እስከ መጨረሻዋ የህይወቴ ህቅታ ድረስ አንተን በማመን እንድታጸናኝ፣ በሕይወቴ ሁሉ አንተን በመፍራት እንድኖር፥ ሰው ሆኖ የማይበድል የለምና ዕድሜ ለንስሐ ለቅዱስ ቁርባንም እንድታበቃኝ እለምንሃለሁ፡፡

•••
እናቴ እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ፥ የእናት ልመና ፊት አያስመልስ፥ አንገትም አያስቀልስምና ከልጅሽ ከወዳጅሽ ተማልደሽ አማልጅኝ።

ለአባ ህርያቆስ
ለአባ ኤፍሬም
ለቅዱስ ያሬድ
ለቅዱስ ደቅስዮስ
ለበላኤሰብ የተለመንሽ እመአምላክ ለእኔም ለደካማው ለጎስቋላው ባርያሽ ተለመኝኝ።

እናቴ ሆይ ምስጋናሽ በዝቶልኝ እንደ ልብስ ለብሼው፤ እንደ ምግብ ተመግቤው፤ እንደ ውኃ ጠጥቼው እኖር ዘንድ እርጅኝ።

የኔ ኃጢአት ያንቺን ንጽህና አያረክሰውምና በብርሃን እጆችሽ ዳሰሽ ለነፍሴ የድኅነት ምክንያት ሁኚያት።

•••
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እስራኤላውያንን ከግብፅ ባርነት መርተህ ያወጣህ እኔንም ከዚህ ዓለም ባርነት ነፃ እንድታወጣኝ እለምንህሃለሁ።

የባህራን ወዳጅ፣ የአፎምያ ረዳት ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እኔ ደካማው አገልጋይህን እርዳኝ። የሚፈታተነኝን ሰይጣን ዲያቢሎስንም በበትረ መስቀልህ ቀጥቅጠህ ከእግሬ ስር እንድትጥልልኝ፣ በሄድኩበትም ሁሉ እንድትጠብቀኝ እማፀንሃለሁ፡፡

•••
አምላከ ነቢያት፥
አምላከ ሐዋርያት፥
አምላከ ደናግል፥
አምላከ መነኮሳት
ለቅዱሳንህ ለአብርሃም፥ ለይስሐቅ ፥ ለያዕቆብ የገባኸውን ቃልኪዳን አስበህ እንደ ክፋቴ፣ እንደ ጥፋቴ፣ እንደ በደሌ ሳይሆን እንደ ቸርነትህ ትምረኝ ዘንድ ቤተሰቦቼን፣ ሃገራችንን ህዝባችንን፣ ቤተክርስቲያናችንንና ሃይማኖታችንን ትጠብቅልን ዘንድ
ዝማሬ ዳዊትን፣
ተልእኮ አርድዕትን፤
ቅዳሴ መላእክትን፤
መስዋዕተ አቤልን፤
ዕጣነ ዘካርያስን የተቀበልክ አምላክ የእኔንም ጸሎት ትቀበል ዘንድ እለምንሃለሁ።

•✞• አቡነ ዘበሰማያት...•✞•

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

29 Apr, 10:17


#ስርዓተ_ጸሎት_ወስግደት_ዘሰሙነ_ሕማማት
•••✞✞✞•••✞✞✞•••✞✞✞•••

ከሁሉም በፊት የሰዓቱ ተረኛ አገልጋይ ቃጭል እየመታ ሦስት ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑን ይዞራል። የሰባት ቀን ውዳሴ ማርያም ፣ አንቀጸ ብርሃንና መዝሙረ ዳዊት በሙሉ ይጸለያል። የእለቱ ተረኛ መምህር (መሪጌታ) የእለቱን ድጓ ይቃኛል: ድጓው ከአራቱ ወንጌላት ምንባብ ጋር እንዲስማማ ሆኖ የተሰራ ነው። የተቀኘው ድጓ እየተቀባበለ እየተዜመ ይሰገዳል: ሶስት ጊዜ እየተመላለሰ ይባላል።

#የወንጌላቱ_ድጓ_እንደሚከተለው_ነው:-

📖 #በማቴዎስ ወንጌል:-
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ስምዕዎኬ ለእግዚእነ ኲልክሙ አብያተ ከርስቲያናት ከመ ዘአክበሮሙ ከመ ዘአክበሮሙ ለኦሪት ወለነቢያት በወንጌለ መንግሥት እንዘ ይብል ክርስቶስ ወልደ ዳዊት አማን አማን እብለክሙ: እስከ አመ የኃልፍ ሰማይ ወምድር የውጣ እንተ አሐቲ ኅርመታ ወአሐቲ ቅርጸታ ኢተኃልፍ እምኦሪት ወእምነቢያት: እስከ ሶበ ኲሉ ይትገበር ወይከውን ይቤ እግዚእ ዘበዕብራይስጢ ልሳን በወንጌለ ማቴዎስ ብርሃን ዘእምብርሃን።

📖 #በማርቆስ ወንጌል:-
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ስምዕዎኬ ለእግዚእነ ኲልክሙ አብያተ ከርስቲያናት ከመ ዘአክበሮሙ ለኦሪት ወለነቢያት በወንጌለ መንግሥት እንዘ ይብል ክርስቶስ ወልደ ዳዊት ኢይምሰልክሙ ዘመጻዕኩ እስዐሮሙ ለኦሪት ወለነቢያት ወኢከመ እንስቶሙ አላ ዳዕሙ ዘእንበለ ከመ ከመ እፈጽሞሙ ይቤ እግዚእ በወንጌለ ሰላሙ አማኑኤል ስሙ ማርያም እሙ።

📖 #በሉቃስ ወንጌል:-
ሃሌ ሉያ ይቤ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዘ ይሜሕረነ በወንጌለ ሉቃስ ወባሕቱ ይቀልል ሰማይ ወምድር ይኅልፍ እምትደቅ አሐቲ ቃል እምኦሪት።

📖 #በዮሐንስ ወንጌል:-
ሃሌ ሉያ ስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ በወንጌል ለዘመሐረነ በኦሪት ወበነቢያት ለዘናዘዘነ በከመ መሐረነ እግዚእነ ስብሐት ለእግዚአብሔር ከመ ናምልኮ ለዘፈጠረነ።

ይህ ሦስት ጊዜ ተመላልሶ ከተዘለቀ በኋላ "ለከ ኃይል" የሚለውን በመቀባበል ፲፪ ጊዜ ይበሉ : በመጨረሻም በ፲፫ኛው ከ "ለከ ኃይል" እስከ "እብል በአኮቴት" ድረስ አንድ ጊዜ በኅብረት ይበሉ:-

ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም፤
አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም፤
ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም፤
ኃይልየ ወፀወንየ ውእቱ እግዚእየ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኮቴት፤
አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስመከ ትምጻእ መንግሥትከ ወይኩን ፈቃድከ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር ሲሳየነ ዘለለዕለትነ ሀበነ ዮም ኅድግ ለነ አበሳነ ወጌጋየነ ከመ ንሕነኒ ንኅድግ ለዘአበሰ ለነ ኢታብአነ እግዚኦ ውስተ መንሱት አላ አድኅነነ ወባልሐነ እምኲሉ እኩይ እስመ ዚአከ ይእቲ መንግሥት ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም።

ከዚህ በመቀጠል "ለአምላክ ይደሉ" የሚለውን መጀመሪያ በመሪ እየቀደሙ በአንሺ እየተከተሉ አንድ ጊዜ ይዝለቁ: በሁለተኛው ክፍል ደግሞ እያስተዛዘሉ አንድ ጊዜ ይበሉ:-

ለአምላክ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለሥሉስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለማሕየዊ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለዕበዩ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለእዘዙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለመንግሥቱ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለሥልጣኑ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለምኲናኑ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለኢየሱስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለክርስቶስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለሕማሙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም:
ለመስቀሉ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም (በአርብ):
ለከ ይደሉ ኃይል:
ወለከ ይደሉ ስብሐት:
ወለከ ይደሉ አኮቴት:
ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም።

ከዚህ በመቀጠል የኦሪትና የነቢያት መፃህፍት ይነበባሉ: ቀጥሎም ከተአምረ ማርያም መቅድም እና ተአምር ጀምሮ ሎሎች ተአምራት ዘወትር በየጠዋቱ እንደተለመደው ይነበባሉ: መርገፋቸውን (የምንባባቱ የመግቢያ ጸሎታቸውና የመጨረሻ ጸሎታቸውን) ከሆሣዕና ሠርክ እስከ ዐርብ ሌሊት በአራራይ ዜማ ያድርሱ: ዐርብ ከጠዋት ጀምሮ ግን በዘወትር እንደተለመደው በዕዝል ዜማ ያድርሱ: ተአምረ ኢየሱስ ከተነበበ በኋላ ከወንጌል በፊት ዲያቆኑ ለሰዓቱ የተሰራውን ምስባክ መጀመሪያ በንባብ ቀጥሎም በዜማ ይበል: ሕዝቡም በአንድነት በዜማ ይቀበሉ።

ከዚያም ሁለተኛው ሥርዓተ ስግደት ይጀመራል: ዜማው የሚጀምረው አሁንም በቀኝና በግራ በመቀባበል ነው: አንዱ ይመራል ሌላው ይቀበላል:-

#በመሪ:- ክርስቶስ አምላክነ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ በሕማማቲሁ ቤዘወነ:
#በተመሪ:- ንሴብሖ ወናልዕል ስሞ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በዕበየ ሣህሉ:

ኪርያላሶን ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን:
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን እብኖዲ ናይን ኪርያላይሶን:
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን ታኦስ ናይን ኪርያላይሶን:
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን ማስያስ ናይን ኪርያላይሶን:
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን ኢየሱስ ናይን ኪርያላይሶን:
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን ክርስቶስ ናይን ኪርያላይሶን:
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን አማኑኤል ናይን ኪርያላይሶን፡
ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን ትስቡጣ ናይን ኪርያላይሶን።
ኪርያላይሶን የሚለውን ብቻ በመሪ ወገን ፳፩ ገዜ በተመሪ ወገን ፳ ጊዜ ይበሉ: ድምሩ ፵፩ ጊዜ ይሆናል።

✞ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን አስተምሮና ስርዓት የጠበቁ የተለያዩ መርሃ ግብሮች በየቀኑ ወደ እርስዎ ይቀርባሉ፡፡ ለወዳጅዎ #Share በመድረግ የበረከት ተካፋይ ያድርጓቸው ✞
╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮
https://t.me/EOTC2921
╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

08 Apr, 09:52


🌾•✞ ላንዴ እስከወዲያኛው ✞•🌾

ላንዴ እስከወዲያኛው
ያንን ሰው ባረገኝ ያችንም ሴት በሆንኩ
ላልወጣ ገብቼ ላልመለስ በሄድኩ

ምነው እሱን በሆንኩ ያን የቀኝ ወንበዴ
ብመስለው ለአንድ ቀን ባየው በመንገዴ
ለመስረቅ አይደለም ንብረት ለመቀማት አልያም ለመዝረፍ ህይወትን ለማጥፋት

በዚያ መንገድማ
ከሱስ ብበልጥ እንጂ መች ከእርሱ አንስና
እኔን ታውቀኝ የለ
የወንበዴ አለቃ የኀጢኣተኞች ዋና

ያ ጸጸት ያዘለ
በዚያች የጭንቅ ሠዓት "አስበኝ" እያለ
ከመስቀልህ ጥላ ከሥር ስለዋለ
ከአዳም ቀድሞ ገባ ምሕረት ተቀበለ /፪/

እኔም እንደ ጥጦስ ማታዬ እንዲያምር
ብትለኝ ምን አለ
"ከገነት ተጠለል ዛሬን ከኔ እደር" /፪/
#አዝ•••✞•••

ደግሞ ይህን ተመኘሁ ለንጊኖስን በሆንኩ
ያቺን ዕለተ አርብ ቀራንዮ በዋልኩ
ለአመጽ አይደለም ከአይሁድ ለማበር
አልያም ለመውጋት ያንተን ጎን በጦር

በዚያ መንገድማ
አንተን ለማሳመም ማን እኔን መሰለ
ስንቴ እንዳቆሰልኩህ
እኔን ታውቀኝ የለ ስንቴ እንዳቆሰልኩህ

ያ  ጲላጦስ ጭፍራ
በመስቀል ላይ ሳለህ በሞት በመከራ
በጦሩ ቢወጋህ ሴያዝን ሳይራራ
ከቀኝ ጎን አፍስሰህ ውኃን ከደም ጋራ
በፍቅርህ ስታስረው ዐይኑን ስታበራ
ትዕግስትህን ጎትቶት ባንተ እንደ ተጠራ
ምናለ እንደው እኔንም
ላንተ ብቻ እንዳድር ልቤ ብታበራ
ምናለ እንደው እኔንም ላንተ ብቻ እንዳድር
ልቤ ብታበራ ላንተ ብቻ እንዲያድር

•••✞•••✞•••✞•••
ላንዴ እስከወዲያኛው
ያንን ሰው ባረገኝ ያችንም ሴት በሆንኩ
ላልወጣ ገብቼ ላልመለስ በሄድኩ
ምነው በመስልኳት ያቺን ከመንዝራ
እንደርሷ ለአንድ ቀን ከፊትህ ብጠራ
ለዝሙት አይደለም ነፍሴን ለማሳደፍ
አልያም ለመርከስ መቅደስክን ለማጉደፍ

በዚያ መንገድማ
ነውርን በመሸከም መች ከእርሷ አንሳለሁ
ሕግህን በማፍረስ
እኔን ታውቀኝ የለ ምን እነግርሃለሁ

ያቺን... ድኩም ዘማ
በኃጢአቷ ቆስላ በበደሏ ታማ
ዓለም ተሰብስቦ ሕይወቷን ሊቀማ
እንዲወግሯት ሳትፈርድ ቸርነትህ ቀድማ
መሬቱን ስትጭር ድምጽህ ሳይሰማ
ነውሯን እንደቀበርክ በከሳሽ ፊት ቆማ
ዳግም አትበድዪ በፍቅር ሂጅ እንዳልካት
እንደው የእኔንም ነፍስ
ምናለ መልሰህ እንዲያ በማረካት /፪/
#አዝ•••✞•••

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

11 Sep, 03:44


🌻🕊 #ስርዓተ_በዓል_ወጾም_ዘኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ_ቤተ_ክርስቲያን 🕊🌻

🌻🌼✞ https://t.me/EOTC2921 ✞🌼🌻
❀✞ #ዓመተ_ምህረት፥ ፳፻፲፮(2016 ዓ.ም)
❀✞ #ወንጌላዊ፥ ዮሐንስ
❀✞ #የዘመን_መለወጫ_ቀን፥ ማክሰኞ
❀✞ #አበቅቴ፥ ፳(20)
❀✞ #መጥቅዕ፥ ፲(10)
❀✞ #ጾመ_ነነዌ፥ የካቲት ፲፰(18)
❀✞ #ዐቢይ_ጾም፥ መጋቢት ፪(2)
❀✞ #ደብረ_ዘይት፥ መጋቢት ፳፱(29)
❀✞ #ሆሳዕና፥ ሚያዝያ ፳(20)
❀✞ #ስቅለት፥ ሚያዝያ ፳፭(25)
❀✞ #ትንሣኤ፥ ሚያዝያ ፳፯(27)
❀✞ #ርክበ_ካህናት፥ ግንቦት ፳፩(21)
❀✞ #ዕርገት፥ ሰኔ ፮(6)
❀✞ #ጰራቅሊጦስ፥ ሰኔ ፲፮(16)
❀✞ #ጾመ_ሐዋርያት፥ ሰኔ ፲፯(17)
❀✞ #ጾመ_ድኅነት፥ ሰኔ ፲፱(19)

🌻🌼✞ #እንኳን_አደረሳችሁ ✞🌼🌻
🌻🌼✞ #እንኳን_አደረሰን🌼🌻

🌻🌻 #በእግዚአብሔር_ፈቃድ 🌻🌻
🌾✞ #መጪው_2016 ዓ.ም፦ ✞
🌻የተከፋ፣ የአዘነና የአለቀሰ፤ የሚደሰትበት።
🌻የተራበና የተጠማ፤ የሚጠግብበት።
🌻የተሰደደ፤ በሰላም ተመልሶ የሚኖርበት።
🌻ፍቅር፣ ዕምነትና ትዕግሥት፤ የምንጎናጸፍበት።
🌻ዕውቀቱን፣ ጥበብና ማስተዋሉን፤ የምናገኝበት።
🌻ከችግርና ከመከራ፤ ተላቀን በሐይማኖት በምግባር የምንጸናበት ዘመን ይሁንልን። ✞አሜን✞
🙏✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ልዑል ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ✞🙏

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

26 Jul, 03:44


#የሊቀ_መላእክት_የቅዱስ_ገብርኤልና_የቅዱስ_ቂርቆስ_በዓል ✞🍇🌾

❖ሐምሌ ፲፱ ዕለት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል አምላካቸው ክርስቶስን
አንክድም በማለታቸው የፈላ ጋን ውስጥ የተወረወሩት ቅዱስ ቂርቆስና እናቱን
ቅድስት ኢየሉጣ ተራድቶ ያዳነበት በዓል ነው።
❖ ይኸውም የቅድስት ኢየሉጣን ልጅ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ከሐዲው መኰንኑ
ይዞ “ስምኽ ማነው” ብሎ በጠየቀው ጊዜ “ነቅዕ ዘእምዐዘቅት ንጹሕ ወእማይ
ዘኢይማስን ክርስቲያን ስምየ” (ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውሃ
የተገኘ ስሜ ክርስቲያን ነው ሞክሼ ስም ከፈለግኽ ደግሞ እናቴ የሠየመችኝ
ቂርቆስ ነው) በማለት ክርስትናው መመኪያው የኾነው ይኽ ቅዱስ ሕፃን
መለሰለት፡፡
❖ መኰንኑም ለአማልክት ከሠዋኽ ስታድግ እሾምኻለኊ ክርስቶስን ካድ ቢለው ቅዱስ ቂርቆስ ግን “የሰይጣን መልእክተኛ ለእውነትም ጠላቷ የኾንኽ ከእኔ ራቅ” አለው፡፡ መኰንኑም ይኽነን ሰምቶ በመቈጣት የቅዱስ ቂርቆስ ደሙ እንደ ውሃ እስኪፈስስ ድረስ እንዲጨምቁት እና ጨውና ሰናፍጭ በኹለቱ የአፍንጮቹ ቀዳዳዎች እንዲጨመሩ ቢያደርግበት፤ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የጠነከረው ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን “ትእዛዝኽ ለጒረሮዬ ጣፋጭ ኾነ ከማርና ከሥኳርም ለአፌ ጣመኝ” እያለ አምላኩ ክርስቶስን አመሰገነ፡፡
❖ መኰንኑ በዚኽ ሳያበቃ እናትና ልጇ በክፉ አሟሟት እንዲሞቱ በማሰብ
የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች
እንዲመጡ አስደርጎ ሰባቱ በእናቱ አካላት፤ ሰባቱ በሕፃኑ ሰውነት ላይ እንዲሰካ ቢያስደርግም በጌታችን ትእዛዝ ግለቱ ጠፍቶ እንደ በረዶ በመቀዝቀዝ ምንም ምን ጒዳት ሳያደርስባቸው ቀረ፡፡
❖ ከዚያም ወደ ወኅኒ ቤት እንዲገቡና እንዲዘጋባቸው አደረገ፤ ከዚያም ሕፃኑና
እናቱ የሚሠቃዩበት ታላቅ መንኰራኲር ለ፵ ቀናት ተሠርቶ ካለቀ በኋላ ኹለቱንም
በደራቁ ራሳቸውን ላጭተው የእሳት ፍሕምን በላያቸው ላይ ቢያደርጉም
የእግዚአብሔር መልአክ ሥቃዮቹን ኹሉ ከእነርሱ አራቀላቸው፡፡
❖ የሕፃኑ ምላስ እንዲቈረጥ አዝዞ ቢያስቈርጠውም ጌታችን ምላሱን
መልሶለታል፡፡ “ወአዘዘ ካዕበ ያፍልሑ ማየ ውስተ ጽሕርት ዐቢይ ወይደይዎሙ
ለሕፃን ቂርቆስ ወለእሙ ኢየሉጣ” ይላል በታላቅ ጋን ውሃ አፍልተው ሕፃኑንና
እናቱን እንዲጨምሯቸው ሲያዝዝ ከሚፍለቀለቀው ውሃ ድምፅ የተነሣ ለጊዜው እናቱ ፍርሀት ሥጋዊ ቢያገኛትም ልጇም ወደ ጌታችን በጸለየላት ጊዜ ፍርሃቱ ርቆላት ከልጇ ጋር ስትገባ መልአከ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ውሃውን
አቀዝቅዞ ሐምሌ ፲፱ አውጥቷቸዋል፡፡
❖ በመጨረሻም የሰማዕትነትን አክሊል የሚያገኝባት ጊዜ ሲደርስ ጌታችን
ተገልጾለት ስሙን ለሚጠራ ኹሉ ቃል ኪዳንን ከሰጠው በኋላ ሥጋኽን በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርልኻለኊ አለው፤ ይኽነን በሰማ ጊዜ በእጅጉ ተደሰተ፤ ከዚኽም በኋላ ጥር ፲፭ በሌሊቱ እኲሌታ ከእናቱ ጋር አንገቱ ተቈረጠ የሰማዕትነትን ክብር ተቀዳጅተዋል።
❖ ጥር ፲፮ ደግሞ የቅዱስ ቂርቆስ ማኅበር የኾኑ ዐሥራ አንድ ሺሕ አራት
በሰማዕትነት ዐልፈዋል፡፡ ሊቁ አርከ ሥሉስም የቅዱስ ቂርቆስን ተጋድሎ በማዘከር፡-
“እግዚአብሔር ሤመ ረድኤቶ ለንእስናከ ዐቃቤ
ወስምዖ መጥበቤ
ፍትወ ምግባር ቂርቆስ ወምዑዘ ኂሩት እምከርቤ
ለዘተጽዕረ በምንዳቤ ወለዘቈስለ በጥብጣቤ
ለአባልከ ሰላም እቤ”
(እግዚአብሔር ረድኤቱን ለታናሽነትኽ ጠባቂን አስቀመጠ፤ ብልኅ የሚያደርግ
ምስክርነቱንም፤ ምግባርኽ ያማረ በጎነትኽ ከከርቤ ይልቅ የሚሸት ቂርቆስ፤
በመከራ የተቸገረ በግርፊያ የቈሰለ ለኾነ ሰውነትኽ ሰላም እላለኊ) እያለ ሕፃኑን ሰማዕት ያወድሳል፡፡
❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በመጽሐፉ፦
“ሰላም ለቂርቆስ ወሬዛ በመንፈስ
በልደት ንዑስ፤
ንጹሕ ከመ ዕጣን
ወፍሡሕ ከመ ወይን”፡፡
(በልደተ ሥጋ ታናሽ በመንፈስ ጐልማሳ፤ እንደ ዕጣን ንጹሕ እንደ ወይንም
አስደሳች ለኾነ ለቂርቆስ ሰላምታ ይገባል)
❖“ሰላም ለሰማዕታት እለ ምስሌሁ ፭፼ ወ፬፻፤ ፬፼ ወ፪፻፲ወ፬”፡፡
(ከርሱ ጋር ያሉ ፭፼ ከ፬፻፤ ፬፼ከ፪፻፲፬ ሰማዕታት ሰላምታ ይገባቸዋል) በማለት
አመስግኗል፨
ከመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
🙏✞[የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት የቅዱስ ቂርቆስ የእናቱ የኢየሉጣ፤ ስለአምላካቸው ስለ ክርስቶስ ፍቅር አንገታቸው በሰይፍ የተቆረጡት
የሰማዕታት በረከት ይደርብን።]✞🙏

✞የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን አስተምሮና ስርዓት የጠበቁ የተለያዩ መርሃ ግብሮች በየቀኑ ወደናንተ ይቀርባሉ፡፡ ለወዳጅዎ #Share በመድረግ የበረከት ተካፋይ እናድርጋቸው✞
╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮
@EOTC2921
@Orthodox2921
╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

11 Jul, 16:52


#ቅዱስ_ጳውሎስና_ቅዱስ_ጴጥሮስ
📖ሐምሌ ፭

ሐምሌ አምስት በዚች ቀን የክቡራንና የዐበይት አባቶቻችን ሐዋርያት #የቅዱስ_ጴጥሮስ እና #የቅዱስ_ጳውሎስ የሰማዕትነታቸው መታሰቢያ ነው።

በዚህች ዕለት ስለክርስቶስ የተገፋ፣ ስለክርስቶስ የተወገረ፣ ስለክርስቶስ የተሰደደ፣ ስለክርስቶስ የታሰረ፣ ስለክርስቶስ ከአለም ሃሳብና መሻቷ የተለየ፣ ስለክርስቶስ ራሱን የለየ፣ ስለክርስቶስ ምእመናን ያነፀ፣ ስለክርስቶስ መልካምን መልእክት የፃፈ #ቅዱስ_ጳውሎስ ሰማዕት ሆነ። ነገር ግን በስጋ ሞተ በመንፈስ ግን ህያው ነው፤ የፅድቅን አክሊል ተቀበለ ከክርስቶስ ጋር መኖርን እንደናፈቀ አገኛት፤ ከእልፍ አእላፋት ቅዱሳን ማህበር ተቀላቀለ ከመላእክት ምስጋና ተጋራ በስጋ ህይወቱ ከእውቀት ከፍሎ እንዳወቀ በሰማያዊው ኑሮ በእጅጉ የበለጠ እውቀትን ተቸረ። በማይጠወልግ፣ በማይደርቅ፣ በማይዝል፣ ፍሬያማም በሆነ ክርስቶስ ግንድነት ላይ ቅርንጫፍ ሆኖ ተሰርቷልና በስጋ ኑሮው በድካም ዝለት ጠውልጎ እንደነበረ የሚጠወልግ አይደለም፤ በማስተማር ብዛት ጉሮሮው እንደደረቀ አሁን የሚደርቅ አይደለም፤ በብርቱ ክንድ ላይ በምቾት አለና የሚዝልም አይደለም፤ ክፉወች ሮማውያን ግን ቅዱስ ጳውሎስን ገደልን አሉ። አይሁድም እፎይ ጳውሎስ ሞተ አሉ። ቅዱስ ጳውሎስ ግን የናፈቀው ክርስቶስ ጋር ሊኖር ወደ ዘለዓለማዊው ህይወት ሄደ፤ ራሱን ህያው መስዋእት አድርጎ በክርስቶስ ፊት እንደ ንፁህ መገበሪያ ስንዴ ተፈጨ፤ አይሁድ በጳውሎስ መሞት ድል ያደረጉ ይመስላቸዋል ነገር ግን የፅድቅን አክሊል በራሱ ላይ አድርጎ ከፀሃይ ይልቅ እያበራ በሰማይ ሆኖ ቅዱስ ጳውሎስ አለ በማይደርቅ ግንድ ላይ የተተከለ ቅዱስ ጳውሎስ ፍሬ በሙላት የያዘ የለመለመ ቅርንጫፍ ሆኖ አለ በቅድስና በተዋበ የክርስቶስ አካል መካከል መልካም ብልት ሆኖ አለ

አይሁድ ግን ቅዱስ ጳውሎስን ገደልን አሉ በሰይፍ አንገቱን ቆርጠው በስጋ ገድለውታልና አላዋቂ አይሁድ ከሮማውያን ጋር አብረው ጳውሎስን ገደልን አሉ፤ እርሱ ግን ከአፈር በተበጀ ስጋ ሞት ቢሞት በእግዚአብሔር እስትንፋስ ስለተሰጠች ነፍስ ህያው ነው

ዳግመኛም በብርሃኑ ብርሃንን በጨውነቱ መጣፈጥን በመድሃኒቱ መፈወስን የሰጣቸው ተወዳጅ የሐዋርያት አለቃ #ቅዱስ_ጴጥሮስን አይሁድ ቁልቁል ሊሰቅሉት ወደ ሮም አደባባይ ከወዳጁ ከጳውሎስ ጋር አጣደፉት፤ ጴጥሮስ ግን በትምህርቱ ብርሃን ጨለማቸውን ገፍፎላቸው፣ በእምነት መድሃኒት ሙታናቸውን አንስቶላቸው፣ ጎባጣቸውን አንቅቶላቸው አንካሳወቻቸውን አፅንቶላቸው ክፉ ጠላት ዲያብሎስንም አባርሮላቸው ነበር አይሁድ ግን ከወዳጃቸው ጴጥሮስ ይልቅ ጠላቶቻቸውን ሮማውያን ጋር አብረው አንድም ከወዳጃቸው ከክርስቶስ ይልቅ ከጠላታቸው ዲያቢሎስ ጋር አብረው ቅዱስ ጴጥሮስን እንደጌታውና መምህሩ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሊሰቅሉት ወደሮም አደባባይ አፋጠኑት። የማይጠፋውን ፋና ሊያጠፉ የማይደበዝዘውን ብርሃን ሊያደበዝዙ የማይሞት የክርስቶስን ልጅ ሊገድሉ በገሃነም ደጆች የማትናወጥ ክርስትናን ሊያናውጡ አይሁዳውያን የክርስቲያኖች ዋና ያሉትን ቅዱስ ጴጥሮስን በብዙ ስቃይ አንገላቱት፤ ተወዳጅ ሐዋርያ ቅዱስ ጴጥሮስ ግን የስጋ ሞቱ ዕረፍቱ እንደሆነ እጅግ አስቀድሞ አውቆ ነበር የአይሁድ ማሰቃየት ወደ ክርስቶስ የፀጋ ግምጃ ቤት እንደሚያደርሰው አውቆ ነበር የአይሁድ መጨከን ወደ ክርስቶስ አማናዊ ፍቅር እንደሚመራው አውቆ ነበር፤ “ገደልንህ” አሉት። እርሱ ግን “ወደ ዘለዓለማዊ ህይወት ክርስቶስ ገፋችሁኝ” አላቸው። “ክርስቲያኖችን ጨረስን” አሉት እርሱ ግን “የእኛ ሞት የክርስቲያኖች ዘር ነው” አላቸው፤ “አንተ ርጉም” አሉት እርሱ ግን “የክርስቶስ ምህረት በእናንተ ላይ ይሁን” ሲል በፍቅር ፀለየላቸው

እነሆ አባቶቻችን እነሆ ዋኖቻችን በክፋት በአንዳች እንኳን የሚከሰሱበት ምክንያት አልተገኘም በቀማኝነትም ማንም እነሱን ሊከስ የሚችል የለም ነገር ግን የሚሰድቧቸውን መረቁ ለሚያሳድዷቸው ፀለዩ ለተራቡት ምግብን ለተጠሙት መጠጥን አቀበሉ ድሆችን ተንከባከቡ ድውዮችን ፈወሱ የጨለማን ክፋት በፍቅር ብርሃን አረከሱ የዲያብሎስን ጭካኔ በክርስቶስ ርህራሄ ሰበሩ፡፡ እነሆ አባቶቻችን አስቀድመው ክርስቶስን አይተው ነበርና ክርስቶስን በትምህርቱ በተአምራቱ በሞቱም መሰሉት

እንኳን ለቅዱስ ጴጥሮስና ለቅዱስ ጳውሎስ አመታዊ መታሰቢያ እለት አደረሰን፡፡ በረከታቸው ይደርብን። አሜን!!
ምንጭ፦ ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮
https://t.me/EOTC2921
╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯‌‌

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

07 Jul, 04:08


#መጥምቀ_መለኮት_ቅዱስ_ዮሐንስ

📖ሰኔ ፴
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
እንኳን ለነቢዩ ለሰማዕቱ ለካህኑ ለሐዋርያው ለመጥምቀ መለኮት ለተወለደበት (ለልደት) በዓልና በሕንደኬ ካሉ ደሴቶቸ በአንዲቱ ውስጥ ለሚኖር ለገድለኛ ለሆነ ለአባ ጌራን ለዕረፍት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱሳን ማርያና፣ ከማርታ፣ ከመነኰስ ገብረ ክርስቶስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን

✝️✝️✝️
የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ሰምዑ አዝማዲሃ ወሰብአ ቤታ። እስመ አዕበየ እግዚአብሔር ሣህሎ ላዕሌሃ። ወተፈሥሁ ፍሥሃ ፈድፋደ። ወፈቀዱ ይስምይዎ በስመ አቡሁ ዘካርያስ። ወትቤ እሙ ዮሐንስሃ ይሰመይ"። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።

✝️✝️✝️
ነቢይ፣ ሰማዕትና ሐዋርያ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ልደት፦ ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው። ይህም በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው።

በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች። ዘመዶቿና ጎረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለርስዋ ደስ አላቸው። በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት። እናቱ ግን "አይሆንም ዮሐንስ ይባል" አለች። "ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም" አሏት።

አባቱንም ጠቅሰው "ማን ሊባል ትወዳለህ" አሉት። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ "ዮሐንስ ይባል" ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ።

ሰብአ ሰገልም መጥተው ከሔዱ በኋላ ሄሮድስ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃኑ ዮሐንስ ለሄሮድስ ነገሩት እንዲገድሉትም ጭፍሮችን ላከ ጭፍሮችም ወደ አባቱ ዘካርያስ መጡ ሕፃኑንም ከእርሱ ፈለጉት አባቱም አንሥቶ በትከሻዎቹ ተሸክሞ ወደ ቤተ መቅደስ ከእርሱ ጋራ እንዲሔዱና ሕፃኑን ከዚያ እንዲወስዱት ወታደሮችን ለመናቸው።

ከዚህም በኋላ ሕፃኑን በመሠዊያው ጠርዝ ላይ አኖረውና "ከዚህ ራሳችሁ ተቀብላችሁ ውሰዱት" አላቸው ወዲያውኑ የእግዚአብሔር መልአክ ነጥቆ ወደ በረሀ ወሰደው። ጭፍሮችም ባላገኙት ጊዜ አባቱ ዘካርያስን ገደሉት። ሕፃኑ ግን አድጎ ለእስራኤል እስከተገለጠበት ጊዜ ድረስ በበረሀ ውስጥ ኖረ።

"የእግዚአብሔርን መንገድ ጥረጉ ጥርጊያውንም አስተካክሉ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ የዐዋጅ ነጋሪ ድምጽ እነሆ" ብሎ ኢያሳያስ የተናገረለት ይህ ነው። ሚልክያስም ስለርሱ እንዲህ አለ "በፊትህ ጎዳናዬን አስተካክሎ የሚጠርግ መልአክተኛዬን እኔ እሰዳለሁ"።

ራሱ መድኃኒታችንም ስርሱ ሲናገር "ሴቶች ከወለዱአቸው መጥምቁ ዮሐንስን የሚበልጠው የለም" ብሏል። ይህ የእግዚአብሔር ልጅ በአጠመቀውና የማትዳሠሥ ራሱን በዳሠሠው ጊዜ "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" የሚል የአብን ቃል ሰምቷልና።

ዳግመኛም ክብር ይግባውና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሲቀመጥ አየ። እኛንም መድኃኒታችን እንዲምረንና ይቅር እንዲለን በአማላጅነቱ እያመን መታሰቢያውን እናድርግ የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ በረከቱም እኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

✝️✝️✝️
ገድለኛው የሆነ አባ ጌራን፦ ይህም ቅዱስ በሕንደኬ ካሉ ደሴቶች በአንዲቱ ውስጥ የሚኖር ነው። እርሱም እግዚአብሔርን የሚፈራና የሚወደው ጾምና ጸሎትንም የሚወድ ነበር። ወደ እግዚአብሔርም የሚለምነውን ሁሉ ይሰማው ነበር። በጸሎቱም ከዚያች አገር ንዳድ፣ አባር፣ ድርቅ፣ በጠላት መማረክ፣ የደም መፍሰስና የመርከቦች መሥጠም ተወገደ የፈለገውንም ሁሉ በጸሎቱ ያገኝ ነበር።

ሰይጣንም ስለዚህ ስለ ተሰጠው ጸጋ ቀናበት በዕንቊ ያጌጠ ነገሥታትን ልብስ በለበሰች መልከ መልካም ሴት አምሳልም ታየው እርሷም ብቻዋን ትንጎራደድ ነበር። በአያትም ጊዜ ወደርሷ ሒዶ ሥራዋን ጠየቃት እርሷም እንዲህ አለችው "የንጉሥ ሰርስባን ልጅ ነኝ እኅቴ ከአባቷ ባሮች ጋራ በአመነዘረች ጊዜ ሁላችንንም ሊገድለን ፈለገ። ስለዚህ ፈርቼ በሌሊት ወጣሁ ወደዚች በረሀም መጣሁ ቅዱሱን ሰው አንተን በማግኘቴም እድለኛ ነኝ" አለችው። እርሱም "ወደ እኔ የሚመጡ ሰዎች እንዳያዩሽ ወደዚያች የዐለት ዋሻ ሒጂ" አላት።

በሌሊትም ከአራዊት የተነሣ እንደፈራ ሰው እየጮኸች መጥታ "የዱር አራዊት እንዳይበሉኝ ክፈትልኝ" አለችው። እርሱም ከፈተላትና ገባች በጎኑም ተኝታ ደረቱን አቀፈችው ልቡን ወደ ፍቅርዋ እስከ አዘነበለችው ድረስ ነገሯን አለሰለሰችለት። ያን ጊዜ ያደረበት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ተለየው ከእርሷም ጋራ ተኝቶ ኃጢአት እደሚሠራ ሆነ። ከስህተት ስካርም በነቃ ጊዜ በጠላት ሰይጣን ተንኰል ተሸንፎ እንደ በደለ አወቀ።

ከዚህም በኋላ ከሰይጣን ተንኰል የተነሣ ያገኘውን ሁሉ በሥጋውም ኃጢአት እንደሠራ ጻፈ። ከዚህ በኋላም ከደሴቱ ተራራ ድንጊያ አንሥቶ እስከሚሞት ድረስ ራሱንና ደረቱን እየደበደበ ኖረ። ነፍሱም ድና ወደ ዘላለም ሕይወት በጌታ ቸርነት ገባች።

ከዚህም በኋላ እንደ ልማዳቸው ከእርሱ ቡራኬ ሊቀበሉ ሰዎች መጥተው አላገኙትም በፈለጉትም ጊዜ ተኝቶ አገኙትና ያንቀላፋ መስሏቸው ጀምሩ ግን ሞቶ አገኙት አለቀሱለት ተሳለሙት ገንዘውም ቀበሩት።

ከዚህም በኋላ ሞቱ በጠላት ሰይጣን ተንኮል ምክንያት ስለመሆኑ የጻፈውን አገኙ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ጻድቃንና ሰማዕታት ጸሎት መንፈሳውያን በሆኑ በቅዱሳን መላእክትም አማላጅነት ይልቁንም አምላክን በወለደች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጸሎቷና በአማላጅነቷ ከሰይጣን ወጥመድ ያድነን።

የተባረ የሰኔ ወር በእግዚአብሔር ቸርነት ተፈጸመ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 30ስንክሳር።

✝️✝️✝️
"ሰላም ለዮሐንስ ግፋዕ ወቅቱል ንጹሕ ወቅዱስ ወስቡሕ ላእክ ወነቢይ ወሰማዕት ድንግል ካህን ጸያሒ ወሰባኪ መጥምቀ እግዚኡ"። ትርጉም፦ ጌታውን ያጠመቀና ሰባኪ፤ መንገድ ጠራጊ፣ ካህን ድንግል ሰማዕት፣ ነቢይና አገልጋይ፤ ምስጉን ቅዱስና ንጹሕ፤ ተገፍቶ የተገደለ ለኾነ ለቅዱስ ዮሐንስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።

✝️✝️✝️
የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "አሜሃ ይቤሉ አሕዛብ። አዕበየ ገቢረ ሎሙ እግዚአብሔር። ወኮነ ፍሡሓነ። መዝ 125፥2፥3። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥76-ፍ.ም።

✝️✝️✝️
የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ወተወከልኩከ እንዘ ሀሎኩ ውስተ አጥባተ እምየ። ላዕሌከ ተገደፍኩ እማኅፀን። እምከርሠ እምየ አንተ አምላኪየ"። መዝ 21፥9-10። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 7፥14-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 3፥7-10 እና የሐዋ ሥራ 19፥1-21። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥57-80። የሚቀደሰው ቅዳሴ የወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቅዳሴ ነው። መልካም የመጥምቀ መለኮት የልደት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
╭══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╮
https://t.me/EOTC2921
╰══•|❀:๑✞♡✞๑:❀|•══╯‌‌

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

23 Jun, 05:37


#ድንቅ_ተአምር_በኪዳነ_ምሕረት

ዕለቱ ታህሳሥ 3 ቀን 2003 ዓ/ም ነበር፡፡ አንድ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረች እህት በእርኩስ መንፈስ ተጠምዳ ነበር፡፡ እናም የያዛት መንፈስ እጅግ ከባድ ነበር፤ መንፈሱ እርሷን ብቻ ሳይሆን በቤተሰቧም የተሰራጨ ነበር፤ ታዲያ ልጅቷ በዚህ ቀን ያ መንፈስ ተነሳባትና ከአለችበት ዩኒቨርሲቲ ዶርም አንስቶ በእግሯ ወደ አዲስ አበባ መስመር እስከ ባኮ ድረስ ይወስዳታል፡፡ ልጅቷ ታዲያ ስልክና መታወቂያዋን በእጇ አንቃ እንደያዘች ነበር ያ እርኩስ መንፈስ አብሮ የማይታመነውን ሩቅ መንገድ የወሰዳት፡፡
ጓደኞቿ በጣም ተጨንቀው የሚያረጉት ግራ ገባቸው ስልክ ይደውላሉ፤ አንስቶም ያስፈራራቸዋል፣ ይዝትባቸዋል ይባስ ብሎ አሁን አታገኟትም ገደል ልከታት ነው፡ አንዴ ባህር ልከታት ነው ይላቸዋል፡፡ ታዲያ የተረበሹት ልጆች ወደ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት አገልጋይ ወደነበሩት ቀሲስ ሙሴ ይደውላሉ፡፡ እርሳቸውም በመገረም ስልክ ተቀብለው ሲደውሉ አያነሳም ነበር፡፡
ከዚያም እዛው ባኮ አካባቢ ጠመዝማዛ ቦታ ላይ አንድ መኪና ከነቀምቴ ወደ አዲስ አበባ ይጓዛል፡፡ ልክ ከማዞሪያው ሲደርስ የመኪናው ባውዛ/የፊት መብራት/ ተሻግሮ የሆነ ቦታ ላይ ያርፋል፡፡ ከውስጥ ያሉት ሹፌርና ጓደኞቹ የሆነ የሚረብሽ ነገር ያያሉ•••
ከመሀል ነጭ ለባሽ በዙሪያዋ ጥቋቁር ነገር ከበዋት ያያሉ፤ ለማመን የሚከብድ ነገር እየተባባሉ፡ ወረዱ ከዚያም ቀስ ብለው መጠጋት ጀመሩ፡ የእጅ መብራት አብርተው በደንብ ሲያዩ በዙሪያዋ የከበቧት ጅቦች ነበሩ፡፡ እነሱም በመጨነቅ ስሜት ማነው የሆነ የተገደለ ሰው፡ ወይም የተመታ ሰው መሆን አለበት፡ ብለው ጅቦችን አባረው መጠጋት ጀመሩ፡፡
ጠጋ ብለው ሲያዩ አይኖቿን ሳታርገበግብ እንዳፈጠጠች፡ በእጆቿ የግቢ መታወቂያ እና ስልክ የጨበጠች ልጃገረድ ነበረች፡፡
ከዚያም ለሦስት አንስተው ጋቢና አስገቧት፡፡ ጠጋ ብሎ ልብ ትርታዋን አዳመጠ አልሞተችም ልጅቷ መተንፈስ ጀመረች፡፡
ከዚያም ስልኳ ጠራ፡ ቀሲስ ነበሩ የደወሉት፡ አነሱና ያዩትን ሁሉ ነገሯቸው ይዘዋት ሊመጡ ሲሉ፡ የጓደኛቸው መኪና ከአዲስ አበባ ወደ ነቀምቴ እየከነፈ መጣ እነሱም የሆነውን ነግረዋቸው እንዲወስዷት አዝዘው ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡ ከዚያም ቀሲስ ግቢው ድረስ ለመቀበል ሄዱ ልጆችም እንዲሁ አብረው ተቀበሏት፡፡ ጊዜውም ጨልሞ ነበር ከዚያም ልጅቷ ካህኑን ባየች ጊዜ ባሰባት ጭራሹን በድንጋይ ልጆችን ልትፈጃቸው ነበር፡፡ በስንት ትግል ይዘዋት ያ መንፈስ አልሄድ ብሎ ስለነበር በቅድስት ኪዳነ ምሕረት፤ በስላሴ ስም ገዝተው እጇን በነጠላ አስረው ወደ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ወሰዷት፡፡ ከቤተ ክርስቲያን አጥር ሲደርሱ አልሄድም አለች፡፡ ቢገፋ ሂድ ቢሉ እቢ አልሄድም ከፊት ሰው ይቅደምልኝ አለች ከዚያም አንድ ሰው ቀድሞ የእጅ መብራት ሲያበራ የአንድ ጅብ አይኖች ከርቀት መብራት ጀመሩ ያን ጅብ አባረው ወደ ውስት አስገብተው ቀሲስ ሙሴም የተለመደ ጸሎታቸውን እያረጉ ማስለፍለፍ ጀመሩ፡፡
ከዚያም ልጅቷ እንዴት እንደሄደች ሁሉን አንድ በአንድ ተናገረች፦ ከዚያ ድረስ የወሰዷትም በኪዳነ ምሕረት ጠበቃ ነበር፡፡ አንዴ ከባህር ሊከቷት ሲሉ ኪዳነ ምሕረት በጨረሯ እየወጋች ታስቀራታለች አንዴም በገደሉ፣ አንዴም በመኪና ጎማ ከተው ሊገድሏት ነበር፤ ብቻ በቅድስት ኪዳነ ምሕረት ጨጨር እየተወጉ ማድረግ ሳይችሉ ከዚያ ቦታ በጅብ ተከባም ተቀመጠች ጅቦችም እንዳይበሏት ተገዝተው ዙሪያዋን ከበው ጠበቋት እንጂ መብላት እንኳ አልተፈቀደላቸውም ነበር፡፡
ከዚያም አልወጣም ያለው እርኩስ መንፈስ ይባስ ብሎ ቤተሰቦቿ ካልተጠመቁ ንስሃ ካልገቡ አለቅም አለ፡፡ ለጊዜው ከልጅቷ አስለቀቁትና ወደ ማንነቷ ተመለሰች፡፡ ከዚያም ልጅቷ ዊዝድራው ሞልታ/ትምህርት ለጊዜው አቁማ ጸበል መከታተል ጀመረች፡፡ ያ እርኩስ መንፈስም በቁጥር 328 ነበር፡፡ ያ መንፈስ በሌላ ጊዜ ስልክ ለንስሐ አባቷ እንዳትደውል እንዳትገናኝ በአንድ ወንድ ልጅ አድሮ ያውም ሴቶች ዶርም ገብቶ ከፖርሳዋ ነበር ሰርቆ የወሰደው፡፡ ያ መንፈስም በኪዳነ ምሕረት ስም ስለተገዘተ ይዞት እንዲመጣ ታዘዘ እንደተባለውም ልጁ ስልኳን ይዞ መሰስ ብሎ ቤተ ክርስቲያን መጣና ሰጣት፡፡ ሁሉም ቤተሰቦቿ ተነግረው ስለነበር ሁሉም በያሉበት ተጠመቁ ንስሃ ገቡ፡፡ ከብዙ ውጣ ውረዶች በኃላ ልጅቷ ለመመረቅ የቀራትን አንድ አመት ከመንፈቅ ጨርሳ በሰላም ተመረቀች፡፡
የቅድስት ኪዳነ ምሕረት ጣዕምና ፍቅሯ፣ ምልጃና ጸሎቷ፣ ረድኤትና በረከቷ ከሁላችንም ጋር ለዘላለሙ ይኑር አሜን፡፡

ከቀሲስ ሙሴ የኪዳነ ምሕረት አገልጋይ ካህን የሰመሁት አስደናቂ ነገር በጥቂቱ ነበር
ተፃፈ፡ በገ/ስላሴ መንግስቴ ኅዳር 8/2012 ዓ/ም

🙏 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር🙏

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች

19 Jun, 07:28


ሚካኤል የዋህ እግዚአብሔር ዘሤሞ፤
እስመ ኢየአምር ወትረ በቀለ ወተቀይሞ፤
ወላሊበላ ጻድቅ ብእሴ ፍቅር ወተሳልሞ፤
አፎምያ ብጽዕት ወባሕራን አበሞ፤

እንኳን አደረሰን !