LK-Betoch

@lkbetoch


LK-Betoch

LK-Betoch

04 Jul, 21:48


የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባ  እስከ ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ

የመኖሪያ ቤት ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ 1320/2016 መውጣቱን ተከትሎ እንደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዋጁ ማስፈፀሚያ መመሪያ ቁጥር 7/2016 በማውጣት ሰኔ 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ በ30 ቀናት ውስጥ  ምዝገባ ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዞ በሁሉም ክፍለከተማ እና ወረዳዎች የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ምዝገባ እየተካሄደ እንደሚገኝ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት ከሰኔ1- ሰኔ 26/2016 ዓ.ም ድረስ 248,469 የኪራይ ውል የተመዘገበ ሲሆን አሁንም ምዝገባው እንደቀጠለ  የሚገኝ መሆኑንም የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር  ቢሮ ያሳውቃል።

በመሆኑም  በርካታ ተመዝጋቢ በመኖሩ ምክንያት ቀኑ እንዲራዘም በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጥያቄው በስፋት በመነሳቱ  እና ቀሪ ያልተመዘገበው የተከራይ አከራይ ውል እስከ ሰኔ 30/2016  መዝግቦ ለማጠናቀቅ አዳጋች እንደሆነ ተቋሙ የተገነዘበ ስለሆነ  በጊዜ ገደቡ ሳይመዘገብ የሚቀር ውል እንዳይኖር  ለማስቻል የምዝገባ ጊዜውን ማራዘም በማስፈለጉ የምዝገባ ጊዜው እስከ ሐምሌ 24/2016ዓም መራዘሙን ቢሮው ይገልፃል።

የግል መኖሪያ ቤት አከራይም ሆነ ተከራይ የሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች  ሳይዘናጉ የተቀመጠው የጊዜ ገደብ ሳይጠናቀቅ ጊዜያቸውን ተጠቅመው እንዲመዘገቡ ቢሮው በድጋሚ ያሳስባል።

የውል ምዝገባው  ከመደበኛ የስራ ሰአት ውጪ በምሽት  ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ የሚካሄድ ስለሆነ ተመዝጋቢዎች ሳይጨናነቁ በተመቻቸው ሰአት መሄድ እና መመዝገብ ይችላሉም ተብሏል።

LK-Betoch

29 Jun, 14:02


በየማህበራዊ ሚዲያዎቻችሁ ሼር አድርጉ👆

LK-Betoch

29 Jun, 13:56


[6/29, 4:47 PM] +251 91 131 2907: https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid05oYJYbm1k58hTpQ9RgzCjmUu1NeTZAHKwFKRskZaGFXnfL5i8yt4zN24Yk3DKcBBl&id=100069343323875
[6/29, 4:47 PM] +251 91 131 2907: በየማህበራዊ ሚዲያዎቻችሁ ሼር አድርጉ👆

LK-Betoch

27 Jun, 18:50


Photo from [email protected]

LK-Betoch

26 Jun, 17:47


የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባ ሊጠናቀቅ 11 ቀናት ብቻ ነው የቀሩት።

ሰኔ 30/2016 ዓ.ም የመጨረሻዋ የምዝገባ ቀን ነች። ስለሆነም ይህንን ምዝገባ ማከናወን ያለባችሁ እና እስከ አሁን ወደ ወረዳችሁ ሄዳችሁ ያልተመዘገባችሁ ነዋሪዎች በመጨረሻው ቀናት ከሚፈጠሩ ወረፋዎች እና መጨናነቆች ራስዎን ይድኑ ዘንድ አሁኑኑ ወደ ወረዳዎት በመሄድ ይመዝገቡ።

ከአዋጅና ከመመሪያው ውጪ የሆነ አካሄድ ከገጠምዎት ደግሞ በተጠቀሰው የጥቆማ የስልክ መስመሮች ጥቆማ ይስጡ።

LK-Betoch

20 Oct, 02:51


ማስታወቂያ

በ14ኛው ዙር የ20/80 እና በ3ኛው ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ዕድለኞች ሆናችሁ በተለያየ ምክንያት ውል ሳትዋዋሉ ለቀራችሁ በሙሉ :-

ውል መወያያ ለመጨረሻ ጊዜ ከጥቅምት 01/02/2016 ዓ.ም እስከ 30/02/2016 ዓ.ም ድረስ  ውል የተራዘመ ስለሆነ በጠቀሰው ወቅት አስፈላጊውን መረጃ በማሟላት በኮርፖሬሽኑ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሚሰጥበት ቦሌ ክ/ከተማ በመቅረብ እንድትዋዋሉ ኮርፖሬሽኑ ያሳውቃል።

በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ  ሳይዋዋል የቀረ ባለዕድለኛ በራሱ ጊዜ ቤቱን እንደተወው በመቁጠር ቤቱ ለኮርፖሬሽኑ ገቢ የሚደረግ መሆኑን እናሳውቃለን።

በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን

LK-Betoch

15 Sep, 15:02


በ14ኛ ዙር 20/80 እና 3ኛ  ዙር 40/60 ኮንዶሚንየም እድለኛ ሆናችሁ ውል የፈፀማችሁ የጋራ መኖርያ ቤት ባለቤቶች  በሙሉ የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ሰኞ ከ7/1/2016 ዓም ጀምሮ ከዚህ በታች በዝርዝር በተቀመጠው ፕሮግራም መሠረት የቁልፍ መረከቢያ ቅፅ መስጠት የምንጀምር መሆኑን እንገልፃለን።

የለሚ ኩራ ቤቶች አስተዳደር  ጽ/ቤት