✍ ልብ ወለድ በፅዮን ✍ fiction ❤️😘 @itsmetsiyearsemalj Channel on Telegram

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

@itsmetsiyearsemalj


የጥበብ አፍቃሪ ኖት እንግዲያውስ ትክክለኛውን ቻናል አግኝተዋል። በቻናላችን 👉 በኔና በሌሎች የተፃፉ
👉ግጥሞች🌸
🌹ወጎች 🌸
🌹ልቦለዶች 🌸
አዝናኝ አስተማሪ ታሪኮችና ሌሎች ፅሁፎችን ያገኛሉ...

━━━━━━━━ ✦
ለማንኛውም አስተያየት
@itsmetsita
Paid Promotion
@Tsiyon_awit
ይጠቀሙ።

Join us
@itsmetsiyearsemalj

✍ ልብ ወለድ በፅዮን ✍ fiction ❤️😘 (Amharic)

በዚህ በላይ ወሮ ልብ ወለድ በፅዮን ለፅንፈኞች እና ፅኖች ሕይወት በሆነ ነው። ይህ በፅዮን ላይ ይገኛል፣ እና ይከናወንልናል። ይህንን በምረቃ በኔና በሌሎች የተፃፉ ግጥሞች ላይ በነሐስ ውስጥ ይገኛል። ለማንኛውም እናት አስተያየት በ@itsmetsita እና በ@Tsiyon_awit ላይ ይጠቀሙ። የተለያዩ ጉዳዮችን በአንድ ቀን እናት በማገኘት ለማቅረብ እንዲሆን አድርገናል ፣ በአገር አኳያ ምንም አልነበረውም። የእኔው እናት በ@itsmetsiyearsemalj ላይ ኃላፊዎችን እንወዳለን።

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

17 Feb, 16:10


አለቃውን ለመጥራት ወደ በሩ ብሄድ በሩ ተዘግቷል፡፡ በተከታታይ አንኳኳሁ፡፡ ሃምሳ አለቃው በበር አመታቴ ደንግጦ እየተቻኮለ መጣና፤ “ምነው! ማንበብ አልፈለክም?" አለኝ፡፡ መግቢያውን እንዲያነበው ሰጠሁት፡፡ አንብቦ እንደጨረሰ ምንም ነገር ያልገባው በመምሰል፤

"እና ምንድነው? ምን ተፈጠረ?" አለኝ፡፡ "አልማዝ መሞቷን እስካልነገርከኝ ድረስ ወደ ሚቀጥለው ገፅ ማለፍ አልችልም፤ ግዝት አለበት'' አልኩት፡፡ እሱም እንደመሳቅ እያለ፤ "አቶ አማረ፤ እኔ ለጥያቄዎ በሙሉ መልስ የሚሆንዎትን ዲያሪ ሰጥቼዎታለሁ፡፡ ማንበብና አለማንበብ የእርሰዎ የራስዎ ምርጫና ውሳኔ ነው" ብሎ ጥሎኝ ወጣ፡፡

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

17 Feb, 16:10


🍁🍁ዲያሪው 📝

ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_5


ሃምሳ አለቃው መልስ በመስጠት ፋንታ ትኩር ብሎ አየኝና፣ "አቶ አማረ ከዚህ, ባራት በወንጀል ተከሰው ወይም ታስረው ያውቃሉ?" ብሎ ያልጠበኩትን ጥያቄ አቀረበልኝ:: ያን መሰል ጥያቄ ይቀርባል ብዬ ስላልጠበቅሁ ክው አልኩ። ይኸን ታሪክ ምን ከወንጀል ጋርር ኣያያዘው? ነው ወይስ ከተሾመ ጋር መደባደሽን ስለነገርኩት ወንጀለኛ አድርጎ አይቶኝ ይሆን? ግን ይኸ ሊሆን አይችልም ?? ምናልባት የአልማዝ ጉዳይ ከወንጀል ጋር የተያያዘ ቢሆንስ? ግን ምን ሆና ይሆን? ተደብድባ ወይስ ተገድላ ይሆን? ሞት! ሞት እንኳን በፍፁም አይሆንም፡፡ እንኳን ሞቷን ከባድ እንቅልፏን እንኳ ማየትም ሆነ መስማት አልሻም፡፡ የሆነው ሆኖ ጥያቄውን መመለስ ግዴታ ነውና ምን መመለስ እንዳለብኝ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ እርግጥ ተከስሼና ታስሬ አውቃለሁ፡፡ የታሰርኩት ግን በደረቅ የሌብነት ወይም በሌላ ተመሳሳይ ወንጀል ሳይሆን በፖለቲካ ነው:: ነገር ግን ይህንን ሰፊ ታሪካዊ ተጋድሎና ታሪክ እየተነተነ ለደርግ ሃምሳ አለቃ መናገር ማለት በዶሮ ፊት ስለፈንግል እንደማውራት የሚቆጠርና ሌላ የከፋ ጣጣ የሚያመጣ ስለነበር፤ “አዎ ታስሬአለሁ፣ ነገር ግን በወንጀል ሳይሆን በፖለቲካ ነው" አልኩት ቀለል ባለ ሁኔታ፡፡ ወዲያው ፖለቲካው ምን እንደነበር እንኳን ሳይጠይቀኝ የተማርኩ በመሆኔና ፀጉሬም ጎፈሬ ስለነበር ሌላ ላይሆን ይችላል በማለት ይመስላል፣ አንዴ አንቱ አንዴ አንተ እያለ እየቀያየረ የሚጠራብኝን ቃል ወዲያው ወደ አንቺ ለውጦ፣ "አሃ ኢሕአፓ ነሻ! " አለኝ፡፡ ሣይታወቀኝ በውስጤ ተናደድኩ፡፡ ላመል ታህል ኮስተር ብዬ፤ "አዎ! ግን ይኼ ከመጣሁበት ጉዳይ ጋር ምንም የሚያገኛኘው ነገር የለም፡፡ ደግሞም መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ምሕረት አድርጎልኝ ከእስር ተፈትቼያለሁ:: ይልቁንስ ስለመጣሁበት ስለ አልማዝ ሁኔታ ለምን አትነግረኝም?'' አልኩት፡፡

ሃምሳ አለቃ አደፍርስ እኔን ትቶ አጠገቡ ካለው አስር አለቃ ጋር ማንሾካሾክ ጀመረ። ወሬያቸርስ እኔን ትረሱ ኣደ እኔ ዞር ብሎ ፤ "አቶ አማረ አንተን ያለምክንያት የምናነጋግርህ ይልቅ ለከ ሰማህ ተሳስተሃል፡፡ ከአንተ ልንሰማ የምንፈልገው ታሪክ ከአንተ ይልቅ ለእኛ ያለው ጠቀሜታ የጎላ ነው የታሪኩ መድበስበስ ወይችን ኣስደብ ብ ማወቅ የምንፈልገውን መረጃ ሊያድበሰብስ ይችላልና እውነቱን ሳትደብቅ ብትነግረን ላንተም ሆነ ለእኛ የተሻለ ነው፡፡ ስለዚህ ስለእሷም ሆነ ስለሁለታችሁ ግንኙነት ማወቅ የሚገባንን በሙሉ ብትገልፅልን እኛ ደግሞ በተራችን ስለእሷ ታሪክ ማወቅ የምትፈልገውን ልንነግርህ እንችላለን" አለኝ ፡፡ የሕይወት ታሪኳን ማወቅ ፈልጎ ይሆናል በማለት እና ሌላም አማራጭ ስላልነበረኝ ቀጠልኩ፡፡ “አልማዝ የተወለደችውና ያደገችው በሀረር ክፍለ ሀገር ጭናክሰን በተባለ ቦታ ነው:: ገጠር ውስጥ ትደግ እንጂ ቤተሰቦችዋ ሀብታም ገበሬዎች ስለነበሩ አስተምረው ለዩንቨርስቲ አብቅተዋታል፡፡ ይሁን እንጂ ምስቅለቅል ከሆነው የቤተሰብ ታሪኳ ጋር ተያይዞ ሕይወቷ በአብዛኛው ደስታ የራቀው ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ዘወትር ትሳቅ እንጂ ደስተኛ አልነበረችም፡፡ በአጭሩ የአልማዝ ታሪክ ይኼ ነው፡፡'' አልኩት፡፡ በመሃል ሃምሳ አለቃው አንድ የረሳውን ነገር እንዳስታወሰ ሰው አስር አለቃውን በጥድፊያ ተጣርቶ፣ "ሂድና ከመረጃ ቢሮ ዲያሪውን ይዘህ ና! " ብሎ ላከው፡፡ ይኼ እንቆቅልሽ የሆነ ሀምሳ አለቃ በቀላሉ እንደማይለቀኝ እየገባኝና ትእግስቴም እያለቀ በመምጣቱ፤ "ሃምሳ አለቃ፣ እኔ ከእርሶ ዲያሪ ጋር ምንም ጉዳይ ስለሌለኝ ይልቅ የአልማዝን ሁኔታ ቢያሳውቁኝና ብሄድ፡፡ ደግሞም ሥራ አለኝ " አልኩት፡፡ "ስለ ሥራችንና አሠራራችን ልትነግረኝ የምትችል አይመስለኝም፣ ወይም አይገባህም" አለኝ ኮስተር ብሎ፡፡ ዲያሪው እስኪመጣ መጠበቅ ነበረብን፡፡ እኔ ግን ውስጥ ውስጡን መብከንከን ጀመርኩ፡፡ አይገርምም? ለእኔ የፖሊስ ዲያሪ ምን ያደርግልኛል? የፖሊስ ዲያሪ ያው እዚህ ቦታ ላይ አንድ ወንጀለኛን ለማደን ሄደን እጅ አልሰጥ ብሎ ለማምለጥ ሲሞክር ተኩሰን እግሩ ላይ መትተን ያዝነው፡፡ አሊያም የኢሕአፓ ወንበዴዎች በሌሊት ወረቀት እየበተኑና መፈክር ግድግዳ ላይ እየለቀለቁ ሲያበላሹ ደርሰን እጅ ከፍንጅ ያዝናቸው ወዘተ የሚል ነው፡፡ ይኸ ደግሞ እኔ ከመጣሁበት ጉዳይ ጋር

የማይገናኝ ለእኔም ፋይዳ የሌለው ነገር ነው:: ከዚህ በላይ ደግሞ እንደእኔ ሐሳብ ከሆነ የፖሊስን የሥራ ዝርዝር ታሪክና አልማዝን የሚያ እንዳእኔ ምንም ነገር እንዲህ በማሰብ ላይ ላሁ:: አስር አለቃው አንድ መለስተኛ መጽሐፍ የሚያክል ዲያሪ ይዞ ከች አለ፡፡ ሃምሳ አለቃ አደፍርስም ዲያሪውን ተቀብፍ አቀበለኝና፤ "አቶ አማረ፤ ይህ የአልማዝ ዲያሪ ነው፡፡ የእርሶን ጥያቄ በሙሉ ስለሚመልስ ያንብቡት :: ስለአልማዝ መረዳት የሚፈልጉትን በሙሉ እዚህ ውስጥ ማግኘት ይችላሉ" ብሎ ሻይ ወይስ ቡና እንደምፈልግ ጠይቀኝ:: ዲያሪውን ቶሎ የማንበብ ፍላጎት ስላደረብኝ ወጣ፡፡ ቡና እንደምፈልግ ነግሬው ዲያሪው የአልማዝ ዲያሪ መሆኑን እንዳወቅሁ ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ውስጥ ገባሁ፡፡ "ያለጥርጥር ሞታለች ማለት ነው" አልኩ፡፡ አለበለዚያ እንዴት ዲያሪዋ ሊገኝ ይችላል? አልማዝ ምንም ትበድለኝ እንጂ ክፉዋን የምመኝና የምፈልግ ሰው አይደለሁም፡፡ ለእሷ ያለኝ ፍቅር ከዕለት ዕለት እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ የሚሄድ አይደለም፡፡ የመሞቷንም ነገር ሳስብ ልቋቋመው የማልችል የሀዘንና የተስፋ መቁረጥ ስሜት አንዣበበብኝ: የተስፋ መቁረጥ ስሜቴም ገንፍሎ ድምፅ ሳላሰማ ተንስቀሰቅሁ፡፡ ግን እንዴት ሊሆን ቻለ? ሞታም ከሆነ ሰው ገድሏት መሆን አለበት፡፡ አለበለዚያ እኔም እዚህ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ተጠርቼ ባልመጣሁ ነበር። ግን ማን ገድሏት ይሆን? ገዳይዋ በእርግጠኝነት ባይታወቅ ነው እንጂ ቢታወቅ ኖሮ እኔን እንዲህ ባላስጨነቁኝ ነበር፣ እያልኩ ማውጣትና ማውረዱን ተያያዝኩት፡፡ ያም ሆነ ይህ ከፊት ለፊቴ የቀረበውን እውነታ ማወቅ ነበረብኝና እምባ የወረደበትን ፊቴን ጠራርጌ ዲያሪውን አነሳሁ፡፡ ዲያሪው ቢያንስ ከመቶ በላይ ገፆችን የያዘ ወፍራም መጽሐፍ ሊወጣው ይችላል፡፡ ግን ማወቅ የምፈልገውን ነገር እስከሰጠኝ ድረስ ማንበብ ስለነበረብኝ ማንበቡን ተያያዝኩት፡፡

አጭር መማጸኛ

"በአገራችን ኢትዮጵያ ምንም እንኳን እያንዳንዱ ሰው የራሱን ታሪክ እየፃፈ ማስቀመጥ እምብዛም ያልተለመደና አዲስ ባህል ቢሆንም ጠቃሚነቱን መረዳት በቻልኩበት ወቅት ላይ ስደርስ ቢያንስ ከዩንቨርስቲ ጀምሮ ያለውን ታሪኬን ዕፎ ማስቀመጥና ለትውልድ ማስተላለፍ ጉዳት የሌለውና ጥቅሙ ግን የበዛ መሆኑን በማመኔ እነሆ ከዛሬ መስከረም 20/1975 ዓም ጀምሮ፣ ማለትም ለመጀመሪያ ጊዜ የዩንቨርስቲውን ደጃፍ ከረገጥኩበት ጊዜ አንስቶ ያሳለፍኳቸ ን ውሎዎች፣ ያጋጠሙኝን ችግሮችና ያገኘኋቸውን ደስታዎች በዚህ ዲያሪ ውስጥ አስፍሬአለሁ፡፡ ይህንን ዲያሪ እኔ ካለፍኩ በኋላ ለባለቤቴ ወይም ለልጆቼ፤ እነዚህ ከሌሉ ደግሞ ዕድሜ ሰጥቶቸው መቆየት ከቻሉ ለብቸኛ ዘመዶቼ ማለትም ለእናቴ ወይም ለአባቴ በውርስ እንዲተላለፍልኝ ይሁን:: ነገር ግን ከሁሉም በላይ አደራ የምለው በማንኛውም መንገድ እኔ በሕይወት እያለሁ ዲያሪዬን ከጥንቃቄ ጉድለትም ሆነ ወይም በሌላ መንገድ ከእጁ ወጥቶ ማግኘት የቻለ ሁሉ ከዚህ ገፅ አልፎ ወደ ውስጥ በመዝለቅ የሕይወት ታሪኬን እንዳያነብ በፈጣሪ ስም እማፀናለሁ፡፡" አልማዝ አስፋው መስከረም 20 ቀን 1975 ፊርማ አለበት ወዲያውኑ ወደሚቀጥለው ገፅ ከመሄዴ በፊት ንባቤን አቁሜ ሃምሳ

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

13 Feb, 16:31


በመምጣቱ ውበቷን ይበልጥ አጎላው፡፡ አልጋው እስኪጠበን ድረስ በየተራ እየተገለባበጥን መሳሳሙን ተያያዝነው፡፡ ከንፈሬ ከከንፈርዋና ከአንገትዋ ጋር እየተጫወተ፣ ቀስ በቀስ ሸሚዟን ፈትቼና ጡት መያዣዋን አውልቄ እንደጦር የቆሙትን ጡቶችዋን መዳሰስ ጀመርኩ፡፡ የጡቶችዋ ጫፎች ቀስ በቀስ መወጠር ጀመሩ፡፡ ወደ ታች

ሸርተት ብዬ በተራቸው እነሱንም መሳምና መላ አካልዋን መዳሰሱን ተያያዝኩት፡፡ አልማዝ ራሷን የሳተች እስኪመስል ድረስ ያለምንም ተቃውሞ ሁለመናዋን ሰጥታኝ ስለነበር በዚሁ ተደፋፍሬ የሱሪዋን ቁልፎች መፍታት ስጀምር ግን ከእንቅልፏ ባንና የተነሳች በሚመስል ሁኔታ ከነበረችበት ስመመን ወጥታ በንዴት ፊቷን አኮሳትራ እጄን መቆንጠጥ ጀመረች፡፡ እኔ ግን ተስፋ ሳልቆርጥ ደግሜና ደጋግሜ መሞከሬ አልቀረም ፡፡ በመጨረሻ ግን ቁንጥጫው ሲበዛብኝና ቁልፉ ቢፈታም ጂንሱ በቀላሉ የማያስገባኝ መሆኑን በመረዳቴ ሁሉንም ነገር የተወ መስዬ ልብሴን አወላልቄ አንሶላ ውስጥ ገባሁ፡፡ እሷ ግን ውስጥ ገብታ ለመተኛት አመነታች፡፡ በኋላ ግን እንድታምነኝ ስለወተወትኳትና ልትተኛበት የሚያስችል ሌላ አማራጭ ስላልነበራት ልብሷን አወላልቃ ውስጥ ገባች፡፡ ውስጥ እንደገባች ቀስ በቀስ አግባብቼ የተቋረጠውን የፍቅር ጨዋታ ቀጠልን፡፡ በላዬ ላይ አስተኝቻት ጡቷ ደረቴን እየገፋው፣ ከሰውነታችን በሚወጣው ሙቀት የተነሳ ገላችን በሙጫ የተያያዘ ያህል በላብ ተጣብቆ፣ ከንፈር ለከንፈር መሳሳምና ትንፋሽ ለትንፈሽ መለዋወጥ ቀጠልን፡፡ ትግሉም ከጂንስ ጋር መሆኑ ቀርቶ ከፓንት ጋር ሆነ፡፡ እንደተለመደው እጄ ወደ ፓንቷ ጎራ ካለ ግን ቁንጥጫው የማይቀር ነበር፡፡ በመጨረሻው ቁንጥጫው ቢበዛብኝ፤ "ለምን ትቆነጥጭኛለሽ " አልኳት፡፡ "ምን ነካህ! እኛኮ ገና ተማሪዎች ነን፡፡ ማርገዝ ቢመጣ እኮ ከሁሉም ነገር ልደናቀፍ ነው ::በዚህ ላይ ደግሞ እኔ ልጃገረድ ነኝ" አለችኝ፡፡ ልጃገረድ መሆኗን ባልጠራጠርም ከእሷው አፍ ስሰማ ግን እሷን የማግኘትና የመጀመሪያዋ የመሆን ስሜቴም ይበልጥ ጨመረ፡፡ "አልሚና እኔ በጣም እወድሻለሁ፡፡ ልጃገረድ መሆንሽንም አውቃለሁ፣ እኔ ደግሞ የምፈልገው አንቺን ለዘላለሙ የእኔ የብቻዬ ለማድረግ ነው፡፡ አንቺም እንደእኔ የምታስቢ ከሆነ ለእኔ ልትሰጪኝ የሚገባ ክቡር የቃል ኪዳን ማሰሪያ ቢኖር ክብረንፅኅናሽ መሆን አለበትና ለምን ትከለክይኛለሽ "አልኳት፡፡ "እኔም እወድሃለሁ፣ ካንተ መለየትም አልፈልግም፣ ግን ሁሉም ነገር መደረግ ያለበት በጊዜው ነው፡፡ አሁኑኑ ለማድረግ የሚያስቸኩለን ነገር የለም ። ለስጦታውም ቢሆን እኔ ዛሬ ተዘጋጅቼ አልመጣሁም፡፡ ደግሞም ክቡር የሆነውን ስጦታዬን በሠርጌ ዕለት እንጂ እዚህ አልቤርጎ ውስጥ ልሰጥህ አልሻም፡፡ አንተም ደግሞ እርግዝና ቢመጣ የሚያስከትለውን ችግር አስበህ የገባህልኝንም ቃል መጠበቅ አለብህ" አለችኝ

ይሁን እንጂ እየተሳሳምን በሄድን ቁጥር ልንቆጣጠረው ወደማንችለው የስሜት ማዕበል ውስጥ ገባን፡፡ በተለይ እኔ ሰውነቷ ሲነካኝ፣ በከፊል ወደ አውሬነት ተለውጬና፣ ቃል የገባሁትን ሁሉ ወደ ጎን ትቼ፣ በተደበላለቀ የፍቅርና የስካር ስሜት ተገፋፍቼ ኃይል በተቀላቀለበት ከፍተኛ ስሜት የጭኖቿን በሮች በርግጄ ገባሁ፡፡ ሁሉም ነገር ከተጠናቀቀና የእሷን ጩኸት ከስማሁ በኋላ ነበር ምን እንዳደረግሁ የተረዳሁት፡፡ የሚገርመው ግን በስሜትና በስካር ውስጥ ሆኜ የእሷን ልመና ለመስማት ጆሮዬ ፍፁም ፍቃደኛ አለመሆኑ ነበር፡፡ ከአልማዝ ዓይኖች እምባ ሲፈስ ሳይ ደነገጥኩ፡፡ “አልሚና ይቅርታ አድርጊልኝ፣ ወድጄ አይደለም፣ ልቋቋመው ያልቻልኩት ስሜት ገፋፍቶኝ ነው ቃሌን ያፈረስኩት፡፡ ይህንን ሁሉ ለማድረግ ያስገደደኝ ላንቺ ያለኝ ፍቅር ነው፡፡ ምንጊዜም ቢሆን የማልከዳሽ የሁልጊዜ ፍቅረኛሽ ነኝ፡፡ አትቀየሚኝ የኔ ፍቅር፣ ዛሬ የሰጠሽኝ ስጦታ ጊዜው ሳይታሰብ ቀድሞ ከመምጣቱ በስተቀር መቼም ቢሆን የኔው ነው፡፡ ይቅር በይኝ የእኔ ፍቅር'' እያልኩና እየሳምኩ ለመንኳት፡፡ "ሳመኝ" ብላ ዝምታዋን አስወገደች፡፡ ሀዘን ተወግዶ በቦታው ደስታ ተተካ፡፡ ሁሉም ነገር እንደገና ፍቅር በፍቅር ሆነ። ውሎ ሲያድርም በእኔ ላይ ያልተጠበቀ ነገር መጣ፡፡ ይኸውም ፍቅር መደበኛ፣ ትምህርት ግን የትርፍ ጊዜ ሥራ መሆኑ ቀጠለ፡፡ ማትሪክ አልፌ የገባሁት በፍቅር ልመረቅ እንጂ ለትምህርት የመጣሁ አልመስልህ እስኪለኝ ድረስ የዘወትር ሥራዬ አልማዝ ሥር መወሸቅ ሆነ፡፡ ድንገት ከአንድ አስፈሪ ቅዥታማ ሕልም ክፉኛ ደንግጦ እንደባነነ ሰው እኔም ከዚያ የቱ መነገርና የቱ መቅረት እንደነበረበት እንኳ ካልለየሁትና ገደቡን ከሳተ ትረካዬ ባንኜ ቀና አልኩና ከባድ ሽክም እንደወረደለት ሰው በረጅሙ ተነፈስኩ።ሃምሳ አለቃውን ፊት ለፊት አየሁት፡፡ የደከመው ቢመስልም ይህን ሁሉ ቅጥልጥል ታሪክ በጽሞና መከታተሉ ገረመኝ፡፡ አንዳች የተጠነሰስ ውስብስብ ነገር ቢኖር ነው እንጂ እንዴት ይህን ያህል ጊዜ ሰጥቶ በዝምታ ሊያደምጠኝ ቻለ? በማለት ጥርጣሬዬ ይበልጥ ጨመረ፡፡ ሃምሳ አለቃው በተራው በረጂሙ ተነፈስ፡፡ ከተጠየቅሁት በላይ እና ውጪ ማውራት ያልነበረብኝን ታሪክ ተገቢ ላልሆነ ሰው ማውራቴ ታወቀኝ፡፡ ታሪኩ ውስጥ ሰጥሜ ስለነበር ያለፈ ታሪክን የማወራ ሳይሆን አሁን በተደረገ አንዳች ድርጊት ውስጥ የተሳተፍኩ ያህል ነበር የተሰማኝ፡፡ እሱም በታሪኩ እጅግ ተመስጦ ስለነበር ማውራቴን ካቆምኩ በኋላ በእጅጉ ዘግይቶ፤ " ከዛስ? " አለኝ፡፡ እኔም ንዴት በተቀላቀለበት ድምፅ፤

"ሀምሳ አለቃ ከዚህ በላይ ምን እንድነግርህ ነው የምትፈልገው? ላንተ መንገር የማይገባኝን ታሪክ ሁሉ ሳልደብቅ አወራሁልህ። ከዚህ በላይ ምን እንዳወራልህ ነው 'አዛስ' የምትለኝ:: ይልቁንስ አንተ ስለ እግዚአብሔር ብለህ አልማዝ አሁን ስላለችበት ሁኔታ ንገረኝ አልኩት፡፡

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

13 Feb, 16:31


🍁🍁ዲያሪው 📝

ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_4

በኋላ ግን ያለ የሌለ ኃይሌን ተጠቅሜ ከላዬ ላይ ገፍትሬ ጥዬው ተነሳሁ፡፡ እሱ ግን ከወደቀበት ተነስቶ "እወድሻለሁ አልሚ" እያለ እንደገና ሊታገለኝ ሲል ተፈትልኬ ከዶርም ወጣሁ፡፡ ከዛ በኋላ ከኤልሳ ጋር ቅልጥ ያለ ጠብ ተጣላን፡፡ እንዴት የእኔን ፍላጎት እንኳን ሳትጠይቀኝ ከእሱ ጋር ተማክራ እንዲህ ታደርጋለች ብዬ ሳኮርፍ፣ ምክንያቷ ባይገባኝም እሷ ደግሞ ከእኔው ብሳ ተናዳ ሳንነጋገር ለዕረፍት ወደየቤታችን ሄድን፡፡ አስራ አምስት ቀን ሙሉ ስልክ ሳንደዋወል ዕረፍት አልቆ ተመለስን፡፡ በኋላ የዶርም ልጆች መጣላታችንን ስላወቁ እናስታርቃችሁ ይሉናል፡፡ እኔም ሆንኩ እሷ ሌላ ጓደኛ ስለሌለን ሳንግደረደር ለመታረቅ ተስማማን፡፡ በኋላም እርቅ ላይ ስንነጋገር ለካስ አጅሬ ለእሷ፤ "ዛሬ እዚህ ከአልማዝ ጋር ስለተቀጣጠርንና ለአንቺ መንገር ፈርታ ንገራት ስላለችኝ፣ ስትመጣ ብትወጪልኝ ብሎ ስለጠየቃት እንደወጣችና የእሷን ምክንያት ሳልጠይቅ ስላኮረፍኳት መቀየሟን ነገረችኝ። ባለመነጋገራችን ምክንያትና ያውም በማይሆን ነገር አላግባብ አስራ አምስት ቀን ሙሉ ባለመገናኘታችን ተቃቅፈን ተለቃቅስን ወደ ድሮው ጓደኝነታችን ተመለስን፡፡ ከዚያ በኋላ የተሾመን ዓይን ማየት ባልፈልግም ኤልሳ፤ "አሁን ተቀያይመን የግቢው ሰው ሲያይ ያልሆነ ነገር ሊያወራብን ይችላል፡፡ እኔ ወደፊት እንዳያስቸግርሽ እነግረዋለሁ" ስላለችኝ እንደድሮው ሳልዘናጋ ይኸው በጓደኝነታችን ቀጥለናል"፡፡ ብላ ብዙ ተጨማሪ ነገር ስጠብቅ ታሪኩን መሀል ላይ አቆመችው፡፡ ድንገት የሃምሳ አለቃውን አየሁት፡፡ የሚነገረው ታሪክ እንዳልገባው ሰው ወይም የሚተረክለትን ተረት እንደጠላ ህፃን ፊቱን አጨማዶ ይመለከተኛል፡፡ ቀጥልም አትቀጥልም የሚል _ ሁኔታ ስላላየሁበት ለአፍታ ያህል ዝም ካልኩ በኋላ አወራሬ ፈሩን ይሳት ወይም አይሳት ሳላመዛዝን ትረካዬን ቀጠልኩ፡፡ ይህንን እንደነገረችኝ ሌላ ማወቅ የምፈልገው ጥያቄ ስለነበር፤ “ከዛስ በኋላ አላስቸገረሽም?" አልኳት፡፡ "ከዛም በኋላ ባገኘኝ ቁጥር እንደሚወደኝ፣ የፈለገውን መስዋእትነት ከፍሎ የሱ እንደሚደርገኝ ይዝታል፡፡ እኔን ትቶ ይልቅ የምትወደውን አብሮ

አደጉን ኤልሳን ቢጠይቃት እሺ እንደምትለው እየደጋገምኩ ብነግረውም፣ እሱ ዓይኑን ከእኔ ላይ ማንሳት አልፈለገም፡፡ እኔ ደግሞ ለእሱ ቅንጣት ታህል ፍቅር የለኝም፡፡ በተለይ አንተን ካገኘሁ በኋላማ ለዓይኔም አስጠልቶኛል፡፡ ግን ኤልሳን ላለማስቀየም ስል ሳልወድ በግድ አልፎ አልፎ ሲመጣ አዋራዋለሁ፡፡ እንዲያውም ተስፋ ቆርጦ እንዲተው በማሰብ የውሸቴን ከአንተ ጋር ፍቅር እንደጀመርኩ ብነግረውም እሱ ግን መሟዘዙን አልተወም፡፡ ያም ሆነ ይህ እኔ ድርሻዬን አግኝቻለሁ፣ እሱም ጊዜው ሳያልፍበት አጠገቡ ያለውን ድርሻውን ቢያፍስ ይሻለዋል" ብላ ወገቤን አቅፋ ደረቴ ላይ ጋደም አለች፡፡ ይሆናል ብዬ ያልገመትኩትን ነገር በመስማቴ ቅናት ቢጀማምረኝም፣ እንደምትወደኝ በማወቄ ግን ሰውነቴ በደስታ ተፍነከነከ፡፡ ሳብ አድርጌ እቅፌ ከንፈሯን ሳምኳት፡፡ እሷም ስትጠብቀው የነበረውን ነገር ያገኘች ይመስል ያለ አንዳች መግደርደር ትስመኝ ጀመር፡፡ ቀስ በቀስ እየተሳሳምን ሳሩ ላይ ጋደም አልን፡፡ በከፊል እላይዋ ጋደም ብዬ ጣቶቼን ፀጉርዋ ውስጥ ወሽቄ እያፍተለተልኩ ከንፈሯን፤ ጉንጮችዋንና አንገትዋን ሳምኳቸው፡፡ ሰውነቴ እሳት አጠገብ የተቀመጠ ያህል ጋለ፡፡ ሳላስበው ለዓመታት ከተዘፈቅሁበት የሐፍረት አረንቋ ውስጥ በደቂቃዎች ውስጥ ተስፈንጥሬ ወጣሁ፡፡ በአንድ በኩል ሁሌ ስመኛትና ሳልማት የነበረችውን የፍቅር እመቤቴ የእኔ እንደሆነች በማረጋገጤ የአሸናፊነት ስሜት ተሰማኝ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የተሾመን ዛቻና ከሀብታም ቤተሰብ መምጣቱን ሳስብ የፈለገውን ማድረግ የሚያስችል ገንዘብ እንዳለውም ስለማውቅ ፍቅሬን እንዳይነጥቀኝ መፍራቴ አልቀረም፡፡ አዎ! አልማዝ ከዛ ቀን በኋላ እውነተኛ ጓደኛዬ ሆነች፣ ማለትም የፍቅር እመቤቴ፡፡ ነገር ግን ተሾመ በቀላሉ እጅ መስጠት ስላልፈለገ በየጊዜው ብቻዋን ባገኛት ቁጥር በጣም ያስፈራራት ጀመር፡፡ አንድ ቀን ከጥናት መልስ ከቤተመጻሕፍት ስንወጣ የአልማዝ ፊት ዓይኗ አካባቢ በልዟል፡፡ እንዳየኋት ደነገጥኩ፡፡ ምን እንደሆነች ብጠይቃትም ደህና ነኝ ከማለት ውጪ መልስ ልትሰጠኝ አልፈለገችም፡፡ ፈትሬ ስይዛት አማራጭ አልነበራትምና ተሾመ ማታ ብቻዋን ስትሄድ አግኝቷት "አንዴ አናግሪኝ" እያለ ሲለምናት፣ እሷ ግን ላለማናገር ብላ የያዘበትን እጁን መንጭቃ ለመሄድ ስትሞክር በጥፊ እንደመታትና በሕይወት እስካለ ድረስ ከእሱ ሌላ ባል አግብታ መኖር እንደማትችል ክፉኛ ዝቶባት እንደሄደ ነገረችኝ፡፡ በድርጊቱ ከመናደዴ የተነሳ ፊቴ ተለዋወጠ፡፡ "ይኸ አንተን የሚመለከት አይደለም፣ አትናደድ፣ ካላረፈ እኔ ራሴ እከሰዋለሁ፣ ዛሬ ልከሰው ነበር፡፡ አሁን እንዲህ ሆኜ ዲኑ ቢያይ ከትምህርት ቤት ስለሚያባርረው በእኔ የተነሳ ሕይወቱ እንዳይበላሽ ኤልሳ ስለለመነችኝና

ከእዚህ በኋላም አንዲት ነገር ቢያደርግ ለቤተሰቦቹ ስልክ ደውላ እንደምትነግራቸው ስላስፈራራችው ነው ዝም ብዬ ያለፍኩት" አለችኝ፡፡ እኔ የውስጤን በውስጤ ይዤ ያልተናደድኩ ለመምሰል ሞከርኩ፡፡ ይሁን እንጂ ማታ እንቅልፍ የሚባል ነገር በዓይኔ አልዞረም፡፡ ለበቀል ከመቸኮሌ የተነሳ ሌሊቱ አልነጋ አለኝ፡፡ ጠዋት መማሪያ ክፍልም ውስጥ ሆኜ ሳስብ የነበረው ምን ማድረግ እንዳለብኝ ነበር፡፡ ምሳ ከበላሁ በኋላ እየተጣደፍኩ ከግቢው ፊት ለፊት ወደአለችው ባቲ ተብላ ወደምትጠራው ጫት ወደሚሸጥባት መንደር ሄድኩ፡፡ ልክ ጫት እንደሚገዛ ሰው ሆኜ ስጠባበቅ፣ አጅሬ እንደተለመደው ብቻውን እየተጎማለለ ከሩቅ ሲመጣ አየሁት፡፡ ፌስታል ገዝቶ እኔ ወደ ነበርኩበት አካባቢ ጫት ለመግዛት ሲመጣ ድንገት ሳያስበው በቡጢ ፊቱ ላይ መትቼ ዘረርኩት፡፡ ድንጋጤው ሳይለቀውና ከወደቀበት ሳይነሳ ቁልቁል እያየሁትና የሌባ ጣቴን ቀስሬ በዛቻ እያወዛወዝኩ፤ "ሁለተኛ ትነካትና እገድልሀለሁ፣ በእሷ መጣህ ማለት በዓይኔ መጣህ ማለት ነው" አልኩት፡፡ አጅሬ እኔ መሆኔን ሲያይ ከወደቀበት ተስፈንጥሮ ተነሳ፡፡ ከአፍንጫው የሚወጣው ደም በአገጩ ላይ እየወረደ ደም የላሰች ውሻ መስሎ ከፊት ለፊቴ ቆሞ ሲያፈጥብኝ ፍርሀት ወረረኝ፡፡ ከመቅጽበት ለመከላከል እንኳን ፋታ ሳይሰጠኝ በቡጢ ነርቶ ብድሩን መለሰ፡፡ ምቱ ጠንካራ ቢሆንም ተንገዳግጄ ቆምኩ እንጂ እንደእሱ መሬት ላይ አልተዘረርኩም፡፡ ከዚያ በኋላማ ገላጋይ ደርሶ ባያድነኝ ኖሮ ይህ ግድንግድ ባላንጣዬ አዋርዶኝ ነበር፡፡ ደግነቱ ገላጋይ መሃላችን እንደገባ እኔ እንደእሱ ብዙም ያዙኝ ልቀቁኝ ሳልል ወደ ግቢ በጥድፊያ አመራሁ፡፡ ከኋላ ኋላዬ ለገላጋይ እያስቸገረ፤ "ቆይ አንተ የሴት ልጅ! እኔ ተሾመ አይደለሁም እሷን ካልደፋሁልህ፣ ያኔ ምን እንደምትሆን አያለሁ" እያለ ይፎክራል፡፡ ከአሁን አሁን ደረሰብኝ እያልኩ እፈራ ስለነበር ከድምፁ እየራቅሁ ሄጄ ዘበኞች ካሉበት ከግቢው በር ላይ ስደርስ "እፎይ" አልኩ፡፡ አገጬ አካባቢ ትንሽ አበጥ ከማለት ውጪ ባለመድማቴ የአሸናፊነት ስሜት ተሰማኝ፡፡ እርግጥ ዕድሜ ለገላጋይ! ብድሩን የሚመልስበት ተጨማሪ ጊዜ አላገኘም እንጂ ትንሽ ዕድል አግኝቶ ቢሆን ኖሮ "የተጨማደደ ጣሳ" ሳያስመስል አይለቀኝም ነበር፡፡" ድንገት ሳላስበው ሃምሳ አለቃው የሚቀደድ የወፍራም ካርቶን ድምፅ የመሰለ ሳቅ ሳቀና፤ “አሃ! የተባለው ሁሉ ልክ ነዋ! ተደባድባችኋላ!'' አለኝ፡፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

13 Feb, 16:31


*ምንድነው የተባለው? የእኛን ጠብ በተመለከተ የተባለ ነገር አለ እንዴ?" አልኩት፤ ስጋት ቢጤ ዳበስ እያደረገኝ፡፡ "ምን እንደተባለ ማወቁ ለአንተ ምን ያደርግልሀል? ይልቅ አሁን የምትለውን ቀጥል" አለኝ፡፡ ማለት የፈለገው ምን እንደሆን ባይገባኝም ከቆምኩበት በመጀመር፤ "አልማዝ የመጣላታችንን ወሬ ሰምታ ኖሮ፣ እንደማልጣላ ቃል ገብቼላት ሄጄ በመጣላቴ ተቆጣችኝ፡፡ እኔ ቢያንስ ንዴቴን ስለተወጣሁና "የብረት መዝጊያ የሆንኩ ባል" እንደምሆናት ለማሳየት በመቻሌ ቁጣዋ ምንም አልመሰለኝም፡፡ ይሁን እንጂ ሰውዬው ከዛ በኋላ መተናኮሉን ያቆማል ብዬ ባላስብም፣ እሷ ግን እንዳልጣላ በመፍራት ሳይሆን አይቀርም _ እሱን በተመለከተ ምንም ወሬ አውርታልኝ አታውቅም፡፡ እሱ ግን እኔን ባገኘኝ ቁጥር እየተፋብኝ ማለፉን ባያቆምም፣ ግቢ ውስጥ ግን ምንም ሊያደርገኝ ስለማይችልና በቻልኩት መጠን የልቤን ስላደረስኩ እየሳቅሁ አናድጄው አልፋለሁ፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ የፈለገውን ያህል ይንጨርጨር እንጂ አልማዝ እንደሆነ የእኔ ብቻ ሆናለች፡፡ ፍቅራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠነከረ ከመሄዱ የተነሳ እሷም ሆነች እኔ አንዲት ቀን እንኳን ሳንተያይ ለማሳለፍ አንፈልግም ነበር፡፡ በጠዋት የምንተያይባት ሰዓት የቁርስ ግዜ ስለነበረች ደርሳ እስከማያት እጓጓለሁ፡፡ ራቅ ብዬ እጠብቅና እሷ ከገባች በኋላ ወደ ካፍቴሪያ እገባለሁ:: ከዛም ፊት ለፊቷ ተቀምጬ በርቀት እያየኋት አንዴ ከጎረስኩ በኋላ ምግቤን የማወራርደው በውሀ ሣይሆን በእሷ ነው፡፡ ሌላው የመገናኛ ቦታችን ቤተመጻሕፍት ነው፡፡ ጥናት በተናጥል መሆኑ ቀርቶ በጋራ ማጥናት ጀምረናል:: ፊዚክሱን፣ ካልኩለሱን፣ ሜካኒክሱን የምንጋተረው በጋራ ሆኗል፡፡ እሷ በትምህርት ከእኔ የተሻለች ነበረች፡፡ በተለይ የእሷ ዕውቀት የተመሠረተው በክፍል ውስጥ በሚሠጥ ትምህርት እንጂ ብዙ ጊዜ ደጋግሞ በማንበብ አልነበረም፡፡ ትልቅ የማስታወስ ችሎታ ነበራት፡፡ እኔ ጎበዝ ተማሪ ብሆንም ጥሩ ነጥብ ለማምጣት ብዙ ስዓት ማጥናት ነበረብኝ፡፡ ቀስ በቀስ የፍቅር ጨዋታችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየደራ መጣ ። ከጥናት ጊዜው ቀነስ እየተደረገ ለፍቅር ጊዜ ጨመር ማድረግ ተዘወተረ። ፍቅራችን ከግቢው አጥር ወጥቶ በአለማያ ሐይቅ ዳርቻዎች፣ በሀረር ግንብ፣ በጀጎልና በደንገጎ የድሬደዋ ፀሐይ እየሞቀው ከሄደ ሰነባብቷል፡፡ አልማዝ የእኔ፣ እኔ የአልማዝ መሆናችንን የግቢው ተማሪ ሁላ ያውቀዋል፡፡ ጓደኞቼ፣ "አልማዝ ፈልጋህ ነበር" ሳይሆን "ሚስትህ መጥታ ነበር" ነው የሚሉኝ፡፡ እርሷንም እንዲሁ ጓደኞቿ "ባልሽ ፈልጎሽ አጣሽ የት ሄደሽ ነው?' ነበር

የሚሏት፡፡ እኔ ከትምህርት ውጪ ጥሩ ስፖርተኛም ነበርኩ፡፡ በጠረጴዛ ቴኒስና በቅርጫት ኳስ ለዩንቨርስቲው ሣይቀር ተሰልፌ ተጫውቻለሁ፡፡ አልሚና በተለይ የጠረጴዛ ቴኒስ ትወድ ስለነበር እሷን ማለማመድም ሥራዬ ነበር፡፡ አብረን ስንጫወት እኔ ስማች ስመታ አልሚና ምቱን በመመለስ ፋንታ እንዳይመታት ለመከላከል ፊቷን በራኬት ከልላ ስትሸማቀቅ ማየትና እንደድንገት ከመለሰች ደግሞ ስትቦርቅ መመልከትን የመስለ የሚያረካኝ ነገር አልነበረም፡፡ በዚሁ ሁኔታ ፍቅራችን እየደራ ሄደ:: አልሚናም ለኔ ፍቅረኛዬ ብቻ ሳትሆን ሕይወቴም ጭምር እየሆነች መጣች፡፡ አዎ! አንዴ ትዝ ይለኛል በገና እረፍት ጊዜ ሲኒማ ለማየት ድሬደዋ እንሄዳለን ብለን ተቃጥረን ነበር፡፡ አልሚና ጥናት ጥናት እያለች አስቸግራኝ በመጨረሻ ብዙ አግባብቼ የያዝኩት ቀጠሮ ነበር፡፡ ለዚህም ስል ገንዘብ ሳጠራቅምና ከጓደኞቼ ስለምን ነበር የከረምኩት፡፡ ታዲያ ተሳክቶልኝ ከዓለማያ በአውቶቡስ ተሳፍረን ድሬደዋ 773:: አልቤርጓችን ውስጥ ስናወጋና ስንሳሳም ውለን አየሩ ቀዝቀዝና ደንገዝገዝ ሲል የሲኒማው ሰዓት እስከሚደርስ ድረስ ተቃቅፈን መንሸራሸሩን ተያያዝነው፡፡ እዚህ ማንም የሚያውቀን ሰው ስለሌለ የሚያስፈራ ነገር አልነበረም፡፡ አልፎ አልፎ ጭር ያለ አካባቢ ስናገኝም እየተሳሳምንና እየተሳሳቅን እስኪደክመን ድረስ ተንሸራሸርን:: የፊልሙ ሰዓት ሲደርስም ተያይዘን ለማየት ገባን:: እንዳጋጣሚ ሆኖ ይታይ የነበረው Ghost የሚባል የፍቅር ፊልም ነበር። ታሪኩ የሚያጠነጥነው በሁለት ፍቅረኛሞች ጉዳይ ላይ ነበር። ባሏን የገደለ ውድ ጓደኛው ከእሷ ጋር ፍቅር ይጀምራል:: ግን የባሏ የሙት መንፈስ ከዚህ ሰው ጋር ፍቅር እንዳትጀምር በተለያየ ነገር ላይ እያረፈ ሰላም ይነሳታል:: በኋላ ላይ የባሏ የሙት መንፈስ አንዲት ምትሀተኛ ሴት ጋ በመሄድ በእሷ ውስጥ አድሮ ከሚስቱ ጋር እንድታገናኘው ይለምናታል፡፡ እሷም ይህንኑ ፈቅዳ ሚሰቱ ጋ ሄዳ የሱ ሙት መንፈስ እሷ ውስጥ ሆኖ ከሚስቱ ጋር እንዲገናኙና እንዲደንሱ ታደርጋለች፡፡ በኋላም የባሏ የሙት መንፈስ ያንን የገደለውንና ሚስቱን ሊያማግጥ የሞከረውን ጓደኛውን በመግደል ይበቀላል፡፡ ጓደኛው ከሞተ በኋላ ሰይጣኖች ነፍሱን ወደ ገሀነም እየጎተቱ ይዘዋት ሲሄዱ ይታያል፡፡ ይህንን ስታይ አልማዝ ታሪኩ በእሷ ላይ የተፈፀመ እስኪመስል ድረስ በጓደኛው ድርጊት እየተናደደች አስር “አያናድድም ይሄ ባለጌ! ባሏን ገድሎት ሲያበቃ ደግሞ ሚስቱን ሊነጥቀው! ምን ዓይነት ጨካኝ ሰው ነው!'' እያለች በመደነቅ መልክ በየመሀሉ ታወራኛለች:: እኔ ግን ለወጉ ያህል ፊልም ለማየት ሲኒማ ቤት ገባሁ እንጂ

ማየቱን ትቼ እቅፍ አድርጌ አንገቴ ስር ከትቼያት ግንባሯንና አንገቷን አልፎ አልፎ ልብ የሚሰቅለው ታሪክ ሲያልፍ ከንፈሯን ስስም አመሸሁ፡፡ አልማዝ ግን በፊልሙ እጅግ በጣም ተመስጣ ስለነበር መሳሟ ብዙም ደንታ አልሰጣትም፡፡ አንዳንዴ ለመሳም በምሞክርበት ጊዜ ፊልሙን ስለምከልልባት ፊቴን በእጇ ገለል እያደረገች ተንጠራርታ ፊልሙን ማየት ትጀምራለች:: እኔም በእሷ ሁኔታ እጅግ በጣም ተገረምኩ:: ፊልም እንግባ ስል የምንዳራበትን ቦታ ከመፈለግ አንጻር እንጂ ለፊልም ይኸን ያህል ፍቅር ይኖራታል ብዬ ገምቼ ስላልነበር አማራጭ አልነበረኝምና ፊልሙን እንድትጨርስ ፋታ ስጠኋት:: በመጨረሻ ግን ገዳዩ መሞቱን ስታይና ሚስቱም ከዚህ ሰው ጋር ሳትማግጥ ለማምለጥ በመቻሏ እጅግ በጣም ተደሰተች:: ከዚያ በኋላ ተራው የእሷ ሆነና ትስመኝ ጀመር። ራት ከበላን በኋላ አልማዝን ወደ አንድ ናይት ክለብ እንድንገባ በመከራ አሳምኜና ገፋፍቼ ገባን፡፡ መጠጣት የፈለገችው ለስላሳ መጠጥ ቢሆንም እንደምንም ገፋፍቼና ደላልዬ ቢራ ጠጣን፡፡ ደገምንም፡፡ መጀመሪያ ላይ ለመደነስ ፍቃደኛ ባትሆንም፤ ወትውቼ ያጠጣኋት ቢራ ሥራውን መሥራት ሲጀምር ግን ተነስታ መደነስ ጀመረች። በኋላም ቯልስ መደነስ ስንጀምር አልማዝ አንገቴን እየሳመች ደግማ ደጋግማ "እወድሃለሁ" አለችኝ፡፡ ያን ለስንት ጊዜያት ስናፍቀው የነበረውን መወደድ ዛሬ እስከምጠግበው ድረስ በቃላትም በተግባርም ከስከስኩት፡፡ እኔም ከንፈሯን በመሳም መውደዴን በአጸፋው ገለጽኩላት፡፡ በዳንሱ ስንጠግብ መሽቶ ስለነበር እየተጣደፍን ወደ መኝታ ክፍላችን አመራን፡፡ አልማዝ ጠጥታ ስለማታውቅ በመጠኑ ራሷን መቆጣጠር አቅቷት ወዲህና ወዲያ ስትወዛወዝ እደግፋት ስለነበር አቅፌያት ሳይሆን ተሸክሜያት የገባሁ እስኪመስለኝ ድረስ ደክሞኝ ነበር፡፡ ለመተኛት ከመቻኮሌ የተነሳ በጥንቃቄ አቅፌ አልጋ ላይ አሳረፍኳት፡፡ አልማዝ አልጋው ላይ ጋደም ብላና ዞማ ፀጉርዋ ትራሱ ላይ ተበትኖ ሳያት ከመቼውም ጊዜ በላቀ ሁኔታ ውብ ሆና ታየችኝ፡፡ በቀስታ እላይዋ ላይ ሆኜ ሁለመናዋን መሳም ጀመርኩ፡፡ ከንፈርዋን፣ ዓይኗን፤ጉንጯን፣ ግንባርዋን ባጠቃላይ ያልሳምኩት የፊቷ ክፍል አልነበረም፡፡ ይበልጥ እየተሳሳምን በሄድን ቁጥር መላ ፊቷ ፍም እየመሳለ

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

11 Feb, 17:50


እያገላበጥኩ

የሳምኩሽ አላት ብሎ የነገረኝ ትዝ ይለኛል አልኳት:: አልሚና ታሪኩ አላሳቃትም፡ እንደውም በሚገርም አስተያየት እያየቺኝ: "ስለሄደችበት ማለቱ ቀርቶ ስለሄደችለት አለ፣ በጣም ይገርማል ለመሆኑ አንተስ ትዳርን እንዴት ነው የምታየው?" ጥያቄው ያልጠበኩት ስለነበርና እንዲህ በቀላሉ የሚመለስ እንዳልሆነ ስለገባኝ ለጥቂት ሰኮንዶች በዝምታ ሳወጣና ሳወርድ ቆየሁና:: እንዳልኩሽ ይህንን የሚወስነው የትዳር አጋሬ ጠባይ ነው፡፡ በሆነውና ባልሆነ የምትነዛነዝ ከሆነ፣ አሊያም በእኔ ላይ ሌላ የምታፈቅር ከሆነ ትዳር ከእስር ቤትም አልፎ ሲዖል ሊሆንብኝ ይችላል፡፡ በተቃራኒው የምትወደኝ ታማኝና ጥሩ ጠባይ ያላት ሚስት ካጋጠመችኝ ደግሞ ገነት ሊሆንልኝ ይችላል:: ስለዚህ የትዳር ጓደኛን ጠባይ አስቀድሞ ጠንቅቆ አውቆ ማግባት ወሳኝ ነው" አልኳት:: መገረሟን አቁማ እንደመሳቅ እያለች! "እኔ የምልህ፤ ታዲያ የአንተ ፍቅረኛ ጠባይ ከየቱ ነው የሚመደበው?" አለችኝ:: አስተማሪ ይመስል አንዱን ጥያቄዋን ስመልስ ሌላ ጥያቄ እያመጣች ወደ ምፈልገው ቦታ ይዛኝ ሄደች:: ጥያቄዋ ግልጽ ነበር። ሌላ ሳይሆን ፍቅረኛ አለህ ወይስ የለህም? ማለቷ ነበር። ከዚህ የተሻለ አጋጣሚ አልነበረምና የሞት ሞቴን፣ የእኔ ፍቅረኛማ እዚሁ አጠገቤ ስለሆነች መመለስ ያለባት እኔ ላልሆን እሷው ራሷ ነች' አልኳት:: ያልጠበቀችውን ነገር በመስማቷ ይሁን ወይም በሌላ ምክንያት ፊቷ በአንድ ጊዜ ፍም መሰለ:: መልስ መስጠቱንም ትታ መሬት መሬቱን ማየት ጀመረች። እኔም ማፈሯን ሳይ ደነገጥኩ፣ ቸኩዬ እንዳላስቀይማትና ይብስ ብሎ ጓደኝነቷንም እንዳላጣ በመፍራቴ ይቅርታ ለመጠየቅም ቃጣኝ:: "የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም' ነውና ሁለቱን ጉንጮችዋን ይዤ አንገቷን ቀና አድርጌ ፊት ፊቷን እያየሁ፤ "አልሚና የተናገርኩት ያልጠበቅሺው ነገር ከሆነ እንዳትቀየሚኝ:: ያልገባሽ ከሆነ ደግሞ እንድታውቂው የምፈልገው እኔ ከአንቺ ጋር ከተዋወቅሁ ጀምሮ ሕይወቴ በደስታ መሞላቱን ነው:: ከአንቺ ጋር የማላልፈው እያንዳንዱ ደቂቃ ሕይወቴን በሀሴት ይሞላዋል:: ድሮ ለእኔ ዩንቨርስቲ ደረቅ የትምህርት ቦታ ማለትም ከከርቸሌ ትንሽ የሚተናነስ ነበር። ዛሬ ግን ከአንቺ ጋር በመተዋወቂ ሕይወቴ ታድሏል፡፡ ዩንቨርስቲ ለእኔ የደስታና የፍቅር ገነት እየሆነልኝ ነው! እጅግ በጣም እወድሻለሁ፤ አስቀይሜሽ ከሆነም ወይም ሌላ ፍቅረኛም ካለሽ ይቅርታ' አልኳት፡፡ እሷም ፊቷ ላይ የመደንገጥ ስሜት እየታየባት፡

"ፍቅረኛ! ስለምን ፍቅረኛ ነው የምታወራው፣ እኔ ፍቅረኛ የሚባል ነገር የለኝም" በማለት ኮስተር አለችብኝ፡፡ እኔም ይህንን ያነሳሁት ባላምንበትም ውስጥ ውስጤን ሲከነክነኝ ለነበረው ጥያቄ መልስ ለማግኘት ሆን ብዬ ያደረኩት ቢሆንም፣ አሁን ግን ድንጋጤዋንና ቁጣዋን ሳይ በመሃከላቸው አንድ የሆነ ነገር ሊኖር ይችላል ብዬ ስለገመትኩ እውነቱን ማወቅ ነበረብኝና በድፍረት፤ "ታዲያ ተሾመ ምንሽ ነው? እኔ አላምንበትም እንጂ የግቢው ሰው ሁሉ ተሾመ ፍቅረኛዋ ነው እያለ ነው የሚያወራው፡፡ ሁሌ አቅፎሽ ስለሚሄድ እኔም ቢሆን አንዳንዴ በመሃከላችሁ ያለው ግንኙነት ግራ ያጋባኛል አልኳት፡፡ አልማዝ እንደመሳቅ ብላ፤ "እ... ተሾመን ጠርጥረኸው ነው? ይኸውልህ ተሾመ እና ኤልሳ የአንድ አካባቢ ልጆች ናቸው፡፡ ከእሷ ጋር አብሮ አደግ ሲሆን ቤተሰቦቻቸውም በጣም ስለሚቀራረቡ በመሃከላቸው ከዝምድና የላቀ ግንኙነት አለ፡፡ እኔንና እሱን ያስተዋወቀችን እሷ ነች፡፡ ሁለቱ በጣም ስለሚቀራረቡ ከእሷ ጋር በጓደኝነት የሚፈላለጉ ስለመሰለኝ ከእኔ ጋር የሚያደርገው ነገር ሁሉ በሌላ ጎኑ ሊሆን ይችላል ብዬ ገምቼ ስለማላውቅ የምቀርበው ነፃ ሆኜ ነበር:: እንዳልከውም ሁሌ አቅፎኝ ሲሄድ አንድም ቀን እኔን ፈልጎ ይሆናል ብዬ ጠርጥሬ አላውቅም፡፡ እንዲያውም ከኤልሳ ይበልጥ ቅርበቱ ለኔ ነው፡፡ እኔ ታዲያ ሁሌ የሚመስለኝ ከኤልሳ ጋር መውጣት ባይጀምሩም መፋቀር ግን የጀመሩ ይመስለኝ ነበር፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ምናልባት ቢወዳትም መጠየቅ ፈርቶ እኔ እንድነግርለት ፈልጎ ሊሆን ይችላል ብዬ ስለምገምት አንድ ቀን ጥያቄውን ያነሳል ብዬ አስብ ነበር፡፡ ኤልሳ ግን እኔ ከእሱ ጋር እንድቀራረብ ትፈልጋለች፡፡ ነገር ግን ስለሱ ስጠይቃት እቅጩን ከመመለስ ፋንታ ነገሩን አድበስብሳው ስለምታልፍ ከእርሱ ጋር ፍቅር የጀመረች ነገር ግን ለእኔ መንገር የፈራች አድርጌ ተመለከትኩት፡፡ ታዲያ አንዴ የገና በዓል ሰሞን ሰው ሁሉ ለእረፍት ወደቤቱ ሄዶ እኔና ኤልሳ ብቻ ለመሄድ ስንዘገጃጅ ተሾመ ወደ መኖሪያ ክፍላችን መጣ:: ትንሽ እንደተጨዋወትን ኤልሳ፤ "ብቻዋን ላናግራት የምፈልገው ነገር አለ እያለ ነው፣ እኔ ልውጣላችሁ፣ እናንተ ተጫወቱ ብላኝ'' ወጣች፡፡ እኔም ያን ስጠብቀው የነበረውን ጉዳይ፣ ኤልሳን እንድጠይቅለት ፈልጎ ነው ብዬ ስለገመትኩ ባዶ ክፍል ውስጥ ሁለታችንን ብቻ ትታን ስትወጣ ምንም አልተጨነኩም፡፡ ነገር ግን ምን ይነግረኛል ብዬ አጠገቡ አልጋ ላይ ቁጭ ብዬ አፍ አፉን ስጠብቅ፣ አልጋ ላይ ገፍተር አድርጎ "እወድሻለሁ አልሚ" እያለ በጉልበት ሊስመኝ መታገል ጀመረ፡፡ ያልጠበቅሁት ነገር ስለነበር እላዬ ላይ ሆኖ ሲስመኝ ቶሎ ብዬ መናገርም ሆነ ማምለጥ አልቻልኩም:: ሰውነቱ ግዙፍ በመሆኑ እላዬ ላይ ሰው ሳይሆን ግዙፍ ግንድ, የወደቀብኝ ያህል ከብዶኝ ስለነበር በቀላጹ ላነሳው አልቻልኩም::

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

11 Feb, 17:50


ፊቴን ከአስፈሪ ፊቱ ላይ አዙሬ ወደ መስኮቱ እያየሁ ትረካዬን ቀጠልኩ። "ኤልሳቤጥ" አልኩ ምን ለማውራት እንደፈለግሁ ሳይገባኝ፡፡ “አዎ! ኤልሳቤጥ የጥቁር ቆንጆ ነች፡፡ ለእኔ ካልሆነ በስተቀር አብዛኛው ሰው ከአልማዝ የበለጠች ቆንጆ አድርጎ የሚመለከታት እሷን ነው:: በተለይ የቆዳዋ ቀለም፤ ሰልካካ አፍንጫዋ፣ ዞማ ፀጉርዋና የአካሏ ቅርፅ በሙሉ ቁንጅናን በምሳሌነት ለማሳየት የተፈጠረች ሞዴል አስመስሏታል፡፡ ዓይን ሳቢ ጥቁር ቀለሟ ከምትለብሳቸው ነጣ ያሉ ልብሷችዋ ጋር ተዳምረው በግቢው ካሉ ሴቶች ሁሉ ደምቃ እንድትታይ አድርጓታል፡፡ የውብ ፊቷ ቅርጽ ተመጥኖ የተሠራ ሲሆን አንገትዋ መለሎ ነው፡፡ ቁመትዋ እንደ አልማዝ ረዘም ያለ ሲሆን የሰውነቷ ቅርዕ ግን ከአልማዝ በተለየ ሁኔታ ስምንት ቁጥር የሚባል ዓይነት ነው፡፡ በዚህ ላይ ምንጊዜም ሳቅ የማይለያት ፍልቅልቅ ነች:: ስትስቅ ድምፅዋን ከፍ አድርጋ ስለምትስቅ ማንም ሰው ሳይወድ በግድ ማነው የሚስቀው ብሎ ለማየት ዞር ማለቱ አይቀርም፡፡ ዞሮም ካየ አሳሳቅዋ ማራኪ በመሆኑ ዓይኑ እሷው ላይ ተተክሎ ይቀራል፡፡ ኤልሳቤጥ የአዲስ አበባ ነዋሪ ስትሆን የሃብታም ቤተሰብ ልጅ በመሆኗ የዘመናዊ ልብስ ቅድ አዘውትራ የምትከታተልና የምትጋጌጥ ነች፡፡ ባጠቃላይ ቀጭን መሆኗ ካልሆነ በስተቀር ምንም የማይወጣላት ቆንጆ ነበረች፡፡ ወደ በኋላ ላይ እየተዋወቅን ስንሄድ ከኤልሳቤጥ ጋር የነበረን መቀራረብ እየጠነከረ መጣ:: እኔም የአዲስ አበባ ልጅ በመሆኔ የአገር ልጅ ሆኜ ነው መሰለኝ ለእኔ ያላት አመለካከት ጥሩ ነበር። በዚህም የተነሳ ከአልማዝ ጋር እንድንቀራረብ የተቻላትን ሁሉ ጥረት ታደርግ ነበር፡፡ ብቻችንን እንድናወራ ዕድል ለመስጠት ከቤተመጻሕፍት ቀድማ ወጥታ ትሄዳለች፡፡ ብዙውን ጊዜ ከቤተመጻሕፍት የመጨረሻዎቹ ወጪዎች እኔና አልማዝ ብቻችንን ስንሆን ወደ መኖሪያ ክፍላችን ከመግባት ይልቅ ግቢውን በጨለማ መዞርም የተለመደ ሆኗል፡፡ ታዲያ አንድ ቀን ማታ ግቢ ውስጥ ከተዟዟርን በኋላ በፅድ በተከበበ ውብ ሳር ሜዳ ላይ ተቀምጠንና ተቃቅፈን ወሬያችንን ተያያዝነው፡፡ አካባቢው ጭር ያለ ሲሆን ተማሪው ሁሉ ወደ ቤት በመግባቱ የሚያየን ሰው አልነበረም፡፡ በውስጤ እንደምወዳት የምገልፅበት ሌላ የተሻለ ቀን ላገኝ ስለማልችል ይቺን ቀን መጠቀም አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡ ግን ይህንን ሳስብ ልቤ ደረቴን ከፍቶ ሊወጣ የሚታገል እስኪመስለኝ ድረስ መምታት ጀመረ፡፡ ራሴን ተቆጣጥሬ ማውጋት ጀመርኩ:: መጀመሪያ ምን እንደማዋራት ግራ ገባኝ፣ በኋላ ግን ሁሌ በተገናኘን ቁጥር በምታነሳው በዚያ በፈረደበት የፊዚክስ አስተማሪ ጉዳይ ላይ ወሬ ተጀመረ፡

ዛሬ ትምህርት እንዴት ነበር? ያ የፊዚክስ አስተማሪ የሚያስተምረው ገባሽ? መቼም ጠልተሸው ልትሞቺ ነው'' አልኳት፡፡ አልሚና ከንግግር በፊት ሳቅ እየቀደማት፤ “ዛሬማ የሚገርም ነው! እነዚህ የሂሳብ ሰዎች ለምን እንደሆን አላውቅም ሁሉም ብሩህ አእምሮ እያላቸው ግን ጠጪዎች ናቸው:: እሱም ያው እንደነገርኩህ ሁሌ ሳይቀምስ አያድርም:: ዛሬማ ብታየው ያስቅህ ነበር፡፡ ትናንት ስክሮ ሳያድር አይቀርም፡፡ የሚገርመው አነጋገሩ ሁሉ የጤነኛ ሰው አልነበረም፡፡ ሰክሮ ማደሩ ብቻ ሳይሆን ስካሩ ሳይበርድለት ነበር የመጣው፡፡ ዓይኑ በርበሬ ከመምሰሉም በላይ ቆሞ እንኳን ማስተማር ተስኖት ቁጭ ብሎ ነበር ሲያስተምረን የነበረው:: ለዛውም አንዱን ፔሬድ እንኳን መጨረስ አቅቶት ባልተለመደ አኳኃን የክፍል ሥራ ሥሩ ብሎ ትቶን ወጣ" እያለች ላቋን ተያያዘችው፡፡ እኔ የምትናገረውን ሳይሆን የአነጋገር ዘይቤዋንና የሙዚቃውን ስልት ጠብቀው እንደሚንቀሳቀሱ ዳንሰኞች አብረው ክፍት፣ ዝግት የሚሉትን ዓይኖችዋንና አሳሳቋን ብቻ ነበር የማስተውለው:: በመሀል ግን ድምፅዋ ሲጠፋ መልስ እንደምትጠብቅ ገባኝና፤ “አዎን! እንዳልሽው የሰው ባህሪ ወደ መጨረሻው አካባቢ ከሚማረው ትምህርት ጋ ሳይያያዝ አይቀርም:: ለምን እንደሆነ ባይታወቅም አብዛኛውን ጊዜ መሀንዲሶች፣ የሂሳብ ሰዎችና እና የእርሻ ባለሙያዎች ጠጪዎች ናቸው:: በተደጋጋሚ ለሥራ ወደ መስክ የመውጣት ዕድል ስላላቸው ወደ መስክ ሲወጡ ከታሰሩበት ትዳር ከሚሉት እሥር ቤት ነፃ የሚወጡበት ጊዜ አድርገው ስለሚገምቱ ይጠጣሉ፣ ይዝናናሉ፡፡ በሌላ በኩል አስተውለሽ ከሆነ ኢኮኖሚስቶች በተለይ ገንዘብን አስመልክቶ ጠንቃቆች ናቸው፣ አንዲት ሳንቲም እንኳን ያለ ምክንያት እንድትወጣ አይፈልጉም:: የህክምና ዶክተሮች ደግሞ ጥንቃቄ ያበዛሉ፡፡ ስለጀርም አደገኛነት ስለሚያውቁ ነው መስለኝ ነገራቸው ሁሉ በጥንቃቄ የተሞላ ነው" አልኳት:: አልማዝ ወሬዬ ሳይጥማት ቀርቶ ይሆን ወይም በሌላ ምክንያት ባላውቅም መልስ ከመስጠት ተቆጥባ ትኩር ብላ ታየኝ ጀመር፡፡ እኔም ደንግጬ ዓይን ዓይኗን አየኋት፤ “እኔ የምልህ አማረ፣ ትዳር ከእስር ቤት ጋር የሚመሳሰል ነው እንዴ?" ብላ ስትጠይቀኝ ቆሌዬ ተገፈፈ፡፡ የምመልሰው ጠፍቶኝ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ መልስ መስጠት የግድ ነበርና፤ “አንዳንድ ባለትዳር ሰዎች ከቤት ሲወጡ ወይም ባለቤታቸው ለሆነ ጉዳይ ወደ ክፍለ ሀገር ወይም ከሀገር ውጪ ከወጣች "ዛሬ ከእስር ተፈትቼአለሁ መዝናናት ይቻላል" ሲሉ ስለሰማሁ ነው እንጂ እኔማ የት

አውቀዋለሁ፡፡ እርግጥ ዝም ብዬ እንደምገምተው አንዳንዴ ፍቅር ካለቀ እና ባልና ሚስት መነታረክ ከጀመሩ ትዳር ከእስር ሳይብስ አይቀርም:: እንደምታውቂው ከፍተኛ ወንጀል ካልሰራሽ በስተቀር እስር ቤትን ስትፈቺ ትገላገይዋለሽ:: ነገር ግን ልጅ ከወለድሽ በኋላ በትዳር ውስጥ ስምምነት ከሌለ ስቃዩ በመፋታትም እንኳን የሚያበቃለት አይደለም:: ተቆራጭ አምጣ፤ ንብረት እንካፈል፣ ልጄን ስጠኝ፣ ሁለተኛ ልጄን ብለህ እኔ ጋ እንዳትመጣ ወዘተ የሚሉት ንትርኮች ማለቂያም የላቸው፡፡ እንዲያውም አንድ ጓደኛዬ የነገረኝን አንድ ታሪክ ላጫውትሽ፡ አንዱ ባል አሁን እንደነገርኩሽ ትዳሩ በጭቅጭቅ የተሞላ ነው፡፡ ታዲያ ሚስቱ ወደ ውጪ ሐገር ለትምህርት ሄዳ ለትንሽ ጊዜ ከእስር ነፃ ወጥቶ ነበር:: የመታሰሪያው ጊዜ ደርሶ ሚስቱ ከውጭ ልትመጣ ስለሆነ ሊቀበላት ቦሌ አየር መንገድ ይሄዳል:: ከአውሮፕላን ወርዳ እንደመጣች ጉንጯን እንደነገሩ ሳም አድርጎ ሻንጣዋን ሊቀበላት ሲሄድ እሷ ግን ሁለት ሌሎች ባልና ሚስቶችን ወይም ፍቅረኛሞችን አትኩራ እያየች ስለነበር አልንቀሳቀስ ትለዋለች፡፡ በዚህ ግዜ ባል፤ "ነይ እንሂድ እንጂ፤ ምነው ቆመሽ ቀረሽ?" እያለ ይጣራል፡፡ ሚስት ግን ሁለቱ ስዎች ላይ ዓይኗን ተክላ "አየሀቸው እነዛ ባልና ሚስቶችን?" ትለዋለች። እሱም ዞር ብሎ ሲመለከት ሁለቱም ተቃቅፈው ከንፈር ለከንፈር ይሳሳማሉ፡፡ እንደገና ተላቀው ትንሽ ይሄዱና ተመልሰው መጥተው ተቃቅፈው ይላቀሳሉ፤ ይሳሳማሉ፡፡ ባልየውም በነገሩ ግራ ተጋብቶ፤ “እና ምን አዲስ ነገር ተፈጠረ?'' አላት፡፡ ሚስትየውም በቅናት መልክ፤ “ምን አዲስ ነገር ተፈጠረ ትለኛለህ! የሚያስቀኑ ፍቅረኛሞች ናቸው፡፡ እኔ ነኝ እንጂ ያልታደልኩት፡፡ እንዴት እንደሳምከኝ ትዝ ይልሀል፡፡ አብረን አንድ ቤት አድረን ጠዋት ለመሰነባበት የምትስመኝ እንጂ፤ በፍፁም ሁለት ዓመት ተለይታህ የመጣች ሚስትህን የምትስም አትመስልም” ብላ ስቅስቅ ብላ ልቅሶዋን ተያያዘችው:: ባልየውም ከመደንገጥ ፋንታ ሳቅ እያለ፣ “አልገባሽም እኮ! እሱ እኮ እየደጋገመ ቢስማት አያስገርምም:: ሚስቱ ወደ ውጪ ስለሄደችለት በደስታ እያቀፈ ቢስማት ምን የሚደንቅ ነገር አለው? አንቺ ግን እየሄድሽ ሣይሆን እየመጣሽብኝ መሆኑን አትዘንጊ፡፡ ትዝ ይልሽ እንደሆን ያኔ አንቺም ስትሄጅልኝ እኔም እንደዚህ ነበር

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

11 Feb, 17:50


🍁🍁ዲያሪው 📝

ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_3

ተወልጄ ያደግሁት ድሮ ቃጫ ፋብሪካ አሁን አዲሱ ኮካኮላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡ ከተማው ባልለማበትና ባልተሻሻለበት ዘመን ጫካ ውስጥ የነበረችው ጎጆ ቤታችን ትዝ ትለኛለች፡፡ ከቤታችን በስተጀርባ ያለው የቃጫ ፋብሪካ ግቢ ሰፊና በደን የተሸፈነ ነበር፡፡ ታዲያ እዚያ ውስጥ እንገባና እንደታርዛን ዛፍ ለዛፍ እየተንጠላጠልን፣ እንደ ቀይ ህንዶች (ሬድ ኢንዲያንስ) ቀስትና ጦር ሠርተን እየተዋጋን፣ እንደ ቬትናም ዘማች የአሜሪካ ወታደር ቅጠል ለብሰን፣ ፊታችንን ጥላሸት ተቀብተን ከእንጨት በተሠራ የማስመሰያ ጠመንጃ የምንታኮሰው፣ በፊልም እንዳየነው እንደ ኩንግ ፉ ካራቲስት ሆነን ያ!... ያ!... እያልንና እጆቻችንን እያወናጨፍን እንደ'ሱ ለመስራት ስንሞክር የነበረው ድርጊት ሁሉ ትዝ ይለኛል፡፡ ያኔ እንዲህ እንደዛሬው እምብዛም ለልጆቹ የሚጨነቅ ወላጅ አልነበረም፡፡ መርሁ "ልጅ በዕድሉ ያድጋል" የሚል ስለነበር ስለልጅ አስተዳደግ ማንም ደንታው አልነበረም፡፡ ልጅን በአግባቡ ቀርጾ ማሳደጊያ እድሜ የህፃንነት ዕድሜ ስለሆነ ለዚሁ ትኩረት መሰጠት አለበት የሚለው የሳይኮሎጂሰቶች የእነ ሲግመን ፍልስፍና ያኔ ቦታ አልነበረውም፡፡ ልጄ ያለው ተሰጥኦ ምንድነው ብሎ የሚከታተል፣ የሚጫወትበት አሻንጉሊት ወይም ኳስ የሚገዛለት፤ ልጄ ይዝናና ብሎ ቲያትር ቤት የሚወስድ ወላጅ ማየት የተለመደ አልነበረም፡፡ ለልጅ ገንዘብ መስጠት ያባልጋል፣ ሲኒማ የሰይጣን ሥራ ነው፣ ኳስ የሚጫወትና የሚዘፍን ልጅ ትምህርት አይገባውም፤ ወይ ቅሪላ አልፊ አሊያም አዝማሪ ሆኖ ይቀራል ወዘተ የሚሉ ማለቂያ የሌላቸው ምክንያቶች ይደረደራሉ፡፡ ይሁን እንጂ ለእኔ ሁሉም ነገር ከዛሬው የተሻለ ነበር። በሌላ አንጻር ደግሞ ማህበረ-ሰቡ ድንቅና የጋራ የሆነ ባሕላዊ እሴቶች ነበሩት፡፡ ያን ጊዜ ልጅ ሲባል ልጅነቱ የወላጆቹ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ጎረቤቶች ነበር፡፡ ቢርበው ሁሉ ጋ ገብቶ ይበላል፤ ቢታመም ወላጅ ባይኖር እንኳን ጎረቤት ያሳክመዋል፣ ያስታምመዋል፡፡ ሁሉም ጎረቤት እንዳሻው ወደ ፈለገበት ቦታ "ወላጆቹ ቢያዩኝ ምን ይሉኛል?" ብሎ ሳይሳቀቅ ይልከዋል፡፡ ሲያጠፋም እንዲሁ ሁሉም ይገስጸዋል፣ ይቀጣዋል፡፡ ለልጁ ግድ የሌለው ካልሆነ በስተቀር ለምን ልጄን ተቆጣችሁብኝ ወይም መታችሁብኝ ብሎ የሚጣላ ወላጅ የለም፡፡ ምክንያቱም ሁሉም የጎረቤቱን ልጅ የሚቆጣውና

ሲያጠፋ የሚመታው ባለጌ ሆኖ ማየት ስለማይፈልግና እንደራሱም ልጅ ስለሚያየው ነውና፡፡ ስለዚህ "ልጅህን እንዲህ ሲያደርግ አይቼ መታሁት" ብሎ ጎረቤት ቢናገር፤ አባት ወይም እናት "እግዜር ይስጥልኝ፣ ደግ አደረክ˚ ብሎ ያመሰግናል እንጂ ለምን ብሎ አይጣላም፡፡ ለመጫወቻውም ቢሆን ሁሉ ነገር ነበረን፡፡ የጨርቅ ኳስ፣ የጨርቅ አሻንጉሊት፣ የመዋኛ ወንዝ፣ ሌላም ሌላም ነበረን:: በየጠጅ ቤቱ የነበረው ቴሌቭዥንም ቢሆንም ከሲኒማ ቤት የሚተናነስ አልነበረም፡፡ ጠጅ ቤት በራፍ ላይ ተኮልኩሎ ቆሞ በሰካራም ጫጫታ መሀል ፊልም አይቶና ዘፈን ሰምቶ መምጣት ትዝታው አይረሳም:: ያውም ይኸ የሚሆነው ባለቤቱ ሳያይ በር ስር ተደብቀን ነበር፡፡ በተለይ የአባባ ተስፋዬ ሣህሉ የልጆች ጊዜ ፕሮግራምና ህብረ-ትርዒት ከሆነ ውሀ እየተደፋብንም ቢሆን አያመልጠንም፡፡ እንደድንገት ባለቤቶቹ ካዩን ግን አንድ ጣሳ ውሀ እላያችን ላይ መደፋቱ የማይቀር ነበር: ብዙ ሌሎች ጨዋታዎችም ነበሩን፡፡ ድምቡሼ ገላ፣ ያዕቆብ፣ ኩኩሉ፣ ሌባና ፖሊስ ወዘተ፡፡ የጊዜው ባህል ፈትሮ ይያዘው እንጂ አባቴ ከሌሎች አባቶች ጋር ሲነፃፀር ዘመናዊ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ልጅን ያቀርባል፣ በመደብደብ ሣይሆን በመምከር ያምናል፣ ለትምህርት ትልቅ ግምት ስለሚሰጥ የጠየቁትን ለማድረግ ወደ ኋላ አይልም፡፡ የማስታውሰው ጎርመስ ባልኩበት ግዜና የሴት ጓደኛ መያዝ በጀመርኩበት ወቅት ገንዘብ ሳገኝ የነበረው፤ ወይ በደብተር መግዢያ አሊያም በትምህርት ቤት መዋጮ ሰበብ ነበር፡፡ አባቴ የመጠጥ ሱሰኛ ስለነበር ምንጊዜም መጠጥ ሳይጠጣ ወደ ቤት አይገባም፡፡ ታዲያ ሁሌ የማስታውሰው ነገር ቢኖር ለቤተሰቡ የሚያስፈልገውን ከማድረግ ውጪ ለሌላ ጉዳይ ገንዘብ ለመስጠት ንፉግ ነበር፡፡ ለውጪው ሰው ግን በጣም ለጋስ ነበር፡፡ እናቴ በዚህ የተነሳ ስትናደድ "አንተ የቤት ቀጋ የውጭ አልጋ ነህ" ትለው ነበር፡፡ አባቴ በተለይ ሞቅ ካለው መጠጥ ቤት ውስጥ ያገኘውን የሚያውቀውንም ሆነ የማያውቀውን ሰው ሲጋብዝ ነበር የሚያመሸው፡፡ እንዲያውም አንዴ ትዝ ይለኛል፣ ማታ አምሽቶ ሲመጣ እዘርፋለሁ ብሎ ሊገድለው፤ ወይም አባቴ ሁል ግዜ ሽጉጥ ይዞ ስለሚሄድ፣ እንዳይገለው የምንፈራው አንድ ማጅራት መቺ ነው ተብሎ የሚጠረጠር ጎረቤታችን ነበር፡፡ ታዲያ አንድ ቀን እስከ ምሽቱ ስምንት ሰዓት ወደ ቤት ባለመግባቱ እደጅ ወጥተን ስንጠብቀው አገኘነውና፤ "ምን እየጠበቃችሁ ነው?'' አለን፡፡ "አይ አባቴ ስላልገባ እየጠበቅነው ነው" ብዬ በፍርሀት መለስኩለት፡፡

"አርፋችሁ ቤት ግቡ! እሳቸው ዱርዬውንም ሆነ ደህናውን ሰው ሲጋብዙ እያመሹ ማንም አይነካቸውም" አለን፡፡ እናቴ ተናዳ፤ "አዎ፤ እኔ ቸገረኝ ስለው ገንዘብ ለመስጠት ይንሰፈሰፋል! እዛ ግን አዳሜን ይጋብዛል፣ ና እንግባ!'' አለችኝ፤ "ማምሸቱን _ ነግረነው ከገባንማ እሱ ራሱ ጠብቆ አንድ ነገር ያደርገዋል" ብዬ እናቴን በማሳመን ወደ ቤት ሳንገባ የጠበቅንበት ሌሊት ትዝ ይለኛል፡፡ ታዲያ እኔ እየጎረመስኩ ስመጣና የሴት ጓደኛ ስይዝ ለመዝናናት ገንዘብ ስለሚያስፈልገኝ ያለኝ አማራጭ አንድ ብቻ ነበር፡፡ ይኸውም እንደምንም ብዬ ምክንያት እፈልግና በትምህርት ቤት መዋጮ ወይም በደብተር መግዢያ ሰበብ ከአስራ አምስት እስከ ሃያ ብር የሚደርስ ገንዘብ እንደምንም ብሎ ማግኘት ነበር፡፡ ይሄ ደግሞ በዚያ ጊዜ ለመዝናናት ከበቂ በላይ ነበር፡፡ ከዚህ ውጪ አስተዳደጌ ነፃ በመሆኑ ከምንም መጥፎ ነገር የነፃ ስሜት ነበረኝ፡፡ ጓደኞቼም ብዙ ነበሩ፡፡ ለሴት ልጅም አክብሮት ነበረኝ፣ ተወዳጅም ነበርኩ፡፡ አዕምሮዬ ለፍቅር እንጂ ለተንኮል፣ ለሸርና ለቂም በቀል ቦታ አልነበረውም፡፡ ለሰው ያለኝ ፍቅር ሴትንም ይበልጥ እንድጠጋ አጋልጦኛል፡፡ ብዙ የሴት ጓደኞች የነበሩኝ ቢሆንም እንደአልማዝ ግን የማፈቅራት አልነበረችም፡፡ የመጨረሻ ፍቅረኛዬም እሷ ትሆናለች የሚል ግምትም ነበረኝ፡፡ ያልተጠናቀቀው ፍቅራችን በጋብቻ ይጠናቀቃል ብዬ ወስኜ ነበር፡፡ግን ምን ያደርጋል 'ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ' ሆነ እንጂ! "የት ሄድክ ወንድም?"አለኝ ሃምሳ አለቃው፡፡ በሀሳብ ባህር ውስጥ ሰምጬ ስለነበር መግባቱን እንኳን አላየሁም ነበር፡፡ "እሺ አቶ አማረ ወደ አቋረጥነው ጉዳይ እንመለስና፤ ከአልማዝ ጋር ስላለህ ትውውቅ የጀመርከውን ብትጨርስልኝ'' ብሎ እንደመኮሳተር አለ፤ ሰውዬው እንኳንስ ተኮሳትሮ እንዲያውም የሚያስፈራ ነው፡፡ ሲያዩት የሰው ጭንቀት የሚያረካው፣ ሰው ሲፈራ የሚደሰትና በአስፈሪ መልኩ ተጠቅሞ እውነትን ከጭንቀትና ፍርሃት ውስጥ ፈልቅቆ ለማውጣት የሚታገል ይመስላል፡፡ በንግግር መሃል እስክሪፕቶውን ገልብጦ ጠረጴዛውን መታ መታ እያደረገ ሲያንኳኳ የሰው ሐሳብ እንዲሰባሰብ ከማድረግ ይልቅ እንዲበታተን ለማድረግ የሚጥር ይመስላል፡፡ ሥራውም እንደስሙ አደፍርስ ነው፡፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

09 Feb, 16:33


ድረስ ነበር? ለመጨረሻ ግዜ አልማዝን ያየሃት

መቼ ነው? በማለት ኮስተር ብሎ ጠየቀኝ፡፡ እኔም ንዴት በተቀላቀለው ሁኔታ "ሃምሳ አለቃ አደፍርስ፣ እኔም ብሆን እዚህ የመጣሁት የእኔንና የአልማዝን የሕይወት ታሪክ በማውራት ውድ ጊዜዬን ለማቃጠል ሳይሆን አልማዝ ምን እንደሆነች ወይም ምን እንዳጋጠማት ለማወቅ ነው፡፡ በሕይወት አለች ወይስ ሞታለች? ይልቅ ስለሱ ብትነግረኝ ይሻላል" አልኩት:: ፊቱን ቅጭም አድርጎ በአግራሞት እየተመለከተኝ "አቶ አማረ፣ እርስዎ የመጡት ስለአልማዝ ለማወቅ ሊሆን ይችላል፣ ወይም ነው እንበል፡፡ ነገር ግን ወደ እዚህ የመጡት እርስዎ ራስዎ ፈልገውና ጠይቀው ሳይሆን እኛ ጠርተንዎት ነው፡፡ እኛ ወደ እርስዎ ፍላጎትና ጥያቄ ከመግባታችን በፊት ከእርስዎ ማግኘት የምንፈልጋቸው ብዙ ጠቃሚ መረጃዎች ስላሉ የእርስዎን ጥያቄ አዘግይተው እኛ ለምንጠይቃቸው ጥያቄዎች ብቻ መልስ በመስጠት ቢተባበሩን መልካም ነው" አለኝ፡፡ ለየትኛው ጥያቄ መልስ እንደምሰጠው ግራ ገባኝ፡፡ የጠየቀኝ ጥያቄ እንዲህ በትንሽ ሰዓት ውስጥ የሚመለስ አይደለም፡፡ ይህ ታሪክ ከዓመታት በፊት ምንም ሳያምርበት የተጠናቀቀ ማሰሪያ የሌለው ታሪክ ነው፡፡ ይህ ታሪክ የእኔና የአልማዝ የሕይወት ታሪክ ነው፡፡ የሕይወት ታሪክ ደግሞ ከመወለድ ይጀምርና በሞት ይጠናቀቃል፣ ለታደለው፡፡ የእኔ ቢጤው ግን እንደዚህ ሳያምርበት ባጭሩ ይቀጫል፡፡ የፈለገው ጉዳይ አቅጣጫ የያዘለት የመስለው ሃምሳ አለቃ ያንን የቁጣ መፍለቂያ የመስለ ፊቱን በግድ በተገኘ ፈገግታ ፈታ አደረገው፡፡ ትኩረት ሰጥቶ መስማት የሚፈልገው ይህንን ተጀምሮ ያልተጠናቀቀ የሕይወት ታሪክ ነው፡፡ ይህንን ታሪክ እንኳን ላወራው ቀርቶ ልሰማው እንኳ ባልፈልግም አማራጭ አልነበረኝምና ታሪኩን ለመጀመር ስል በሩ ተንኳኳና አንድ የአስር አለቃ ሰላምታ ሰጥቶ፤ "ጌታዬ የፖሊስ አዛዡ ይፈልጉዎታል " ብሎ ወጣ፡፡ ለግዜው ቢገላግለኝም፣ መጨነቄ ግን አልቀረም፤ "ምን ይሆን? ይህን የተጠራሁበትን ጉዳይ የሚመለከት ይሆን?" አልማዝ ምን ሆና ይሆን? ግራ ገባኝ፡፡ በዚያች ጠባብ ክፍል ውስጥ ሀሳብ ባህር ውስጥ ገብቼ የሕይወቴን ውጣ ውረድና የመከራዬን መብዛት ማጠንጠን ጀመርኩ፡፡ የሸሸሁት የአልማዝ ታሪክ አሁንም ደስታን ሳይሆን ይኸው ጭንቀትና መከራን ይዞልኝ መጥቷል፡፡ እንደ ሃምሳ አለቃው አያያዝ ከሆነ ከዚህች ክፍል በሰላም እንደማልወጣ ታውቆኛል፡፡ "ግን ለምን የእኔ ሕይወት
የመከራ ሕይወት ብቻ ሆነ? ለምን ሕይወቴ በሙሉ ደስታ የተነፈገው ሆነ? ለሰው ላወራው የምችል ጥሩ ታሪክ ስርቼ እንዳልፍ ምነው ጌታ አልፈቅድ አለ?" አዎ! ትዝ የሚለኝና በሰላም ተጀምሮ ተጠናቀቀ የምለውና መኩራሪያ የሚሆን ታሪክ አለኝ ካልኩ ያው የልጅነቴ ታሪክ ብቻ ነው፡፡ "ተኖረና ተሞተ" እንደሚባለው "ታሪክ ተሆነና ተነገረ" ካልተባለ፡፡

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

09 Feb, 16:33


🍁🍁ዲያሪው 📝

ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_2

"አዎ! በስልክ እዚህ እንድመጣ ቀጥረውኝ ነበር፡፡ አልማዝ አስፋውን በተመለከተ ተፈልጌ ነው" አልኩኝ። የረሳውን ነገር ያስታወሰ በሚመስል ሁኔታ፤ በፊት፤ "እ! አቶ አማረ አንተ ነህ ? ተቀመጥ" አለኝ፡፡ እኔ ግን ከመቀመጤ "ምነው ለምን ፈለጋችሁኝ? በደህና ነው? አልማዝ ደህና አይደለችም እንዴ?" በማለት አከታትዬ ጠየቅሁት፡፡ ሃምሳ አለቃው በተረጋጋ መንገድ! "ይቀመጡ አቶ አማረ፤ ስለአልማዝ ሁኔታማ ከእኛ በላይ እርስዎ የሚያውቁ መስሎኝ በማለት አንዴ አንተ አንዴ አንቱ እያለ ጥያቄ አቀረበልኝ፡ እንደተቀመጥኩ፤ “አቶ አማረ፣ ሃምሳ አለቃ አደፍርስ አባላለሁ፡፡ አሁን የፈለግንዎት አልማዝን በተመለከተ ከእርሶ የምንፈልገው መረጃ ስላለ ነው::" “አልገባኝም የምን መረጃ ነው ከእኔ የምትፈልገው?" "መጨረሻ ላይ ስለነበረው ሁኔታ ነዋ"፡፡ "አልገባኝም ሃምሳ አለቃ፤ ግልፅ ብታደርግልኝ'። "እንዴት አልገባዎትም? የሚያውቁትን ነገር እኮ ነው የጠየቅሁዎት ማለትም ስለአልማዝ የሚያውቁትን ነገር ሁሉ አንድባንድ፣ በዝርዝርና በግልጽ እንዲነግሩን እንፈልጋለን፡፡ ይኸውም የት እንደተዋወቃችሁ፣ ግንኙነታችሁ ምን ዓይነት እንደነበርና በኋላም እንዴት እንደተለያያችሁ እያለ ያልጠበቅሁትን ጥያቄ ይጠይቀኝ ጀመር፡፡ እኔም መልስ በመስጠት ፋንታ አልማዝ የት እንዳለችና ምን አዲስ ነገር እንደተፈጠረ መጀመሪያ እንዲነግረኝ ወተወትኩት፡፡ ነገር ግን ይህንን የሚነግረኝ የሚጠይቀኝን ጥያቄ ሁሉ ከመለስኩ በኋላ መሆኑን ነገረኝ፡፡ አማራጭ አልነበረኝምና መልስ ለመስጠት ዓመታት ያስቆጠሩ ትዝታዎቼን ማሰባሰብ ጀመርኩ፡፡ ቤተመጻሕፍት ውስጥ የነበረውን የመጀመሪያ ትውውቃችንን ቆጠብ ባለ ሁኔታ ነገሬው መልስ እንዲሰጠኝ ብጠብቅም፣ ከእኔ ገና በጣም ብዙ መስማት የሚፈልግ መሆኑን ዳግመኛ ስለነገረኝ ሌላ አማራጭ አልነበረኝምና ትረካዬን ልቀጥል ስል፤

“አንድ ነገር ግልጽ ላድርግልዎት ታሪኩ መቀነጫጨብና የምንፈልገውን ቁምነገር የሚያሳጣን መሆን ስለሌለበት፤ ይህ አያስፈልግም ከምልዎት ውጪ ሁሉንም ይግለጹልን፡፡" አለኝ በአጽንኦት፤ "አዎ! ቤተመጻሕፍት ውስጥ በፈገግታ የተጀመረው ትውውቃችን በደጅም ቀጠለ፡፡ ቤተመጻሕፍት እንደተዘጋ እነሱ ፊት ለፊት እኔ ከኋላ ተከታትለን ወጣን፡፡ ተማሪው ሁሉ ወደ ማደሪያው አምርቶ ስለነበር የቀረነው እኛ ብቻ ነበርን፡፡ ከቤተመጻሕፍት ፊት ለፊት በአጫጭሩ ተከምከመው በግራና ቀኝ በተተከሉ ዕዶች የተከበበችውን "ላቭ ስትሪት" ወይም "የፍቅር ጎዳና" ተብላ የምትጠራውን ጠባብ መንገድ ለሁለት ዘግተው እየተሳሳቁ በዝግታ ይሄዱ ስለነበር ከኋላቸው ስደርስ ዝግ ለማለት ተገደድሁ፡፡ ለማለፍ ይቅርታ መጠየቅና መንገድ ማስከፈት ስለነበረብኝ እየፈራሁ በጥግ በኩል "ይቅርታ" ብዬ ለማለፍ ስሞክር ይብስ ተብሎ እሱም ተዘጋብኝ:: በሌላው ዳርቻ ለማለፍ ስሞክርም ለካስ ሆን ብለው የሚያደርጉት ድርጊት ኖሮ ያችንም መልሰው ዘጓት፡፡ ግር ብሎኝ ቆም እንደማለት ስል" "የት ለመሄድ ነው ችኮላው? ለጥናት ከሆነ ያጠናኸው ይበቃሃል። ጥናት ሲበዛ ጥሩ አይደለም፣ ያሳብዳል ይባላል፡፡ ስለዚህ አንዳንዴ እረፍትም ጠቃሚ መሆኑን አትዘንጋ" አለችኝ የኔ መካሪ፡፡ የምመልሰው ጠፍቶኝ ፈዝዤ ቆምኩ፡፡ ሁል ጊዜ እንዴት እንደማናግራት ሳወጣና ሳወርድ እውላለሁ፡፡አንዳንዴም በሕልሜ አገኛትና ከማውራት አልፌ አቅፌ ስስማት ይታየኛል፡፡ ግን አንድም ቀን ደፍሬ በውኔ አንዲት ቃል ትንፍሽ ብዬ አላውቅም፡፡ ከየት የመጣ ትንፍሽ ማለት! ቀና ብዬ እንኳን የማያት ብዙ ርቃ ከሄደች በኋላ ነበር፡፡ አንዳንድ ጊዜ "ዛሬስ የመጣው ይመጣል እንጂ ሳላናግራትማ አልመጣም" ብዬ ቆርጬ እወጣና በምታልፍበት መንገድ ላይ ስጠብቃት እውልና አጠገቤ ስትደርስ፣ "ኤጭ! ከጓደኞችዋ ጋር ነች፣ ያ ሴታ ሴት ተሾመ አጠገቧ አለ፣ ወይም ወደ ሆነ ቦታ ለመሄድ ስለቸኮለች አሁን ቀልቧን ሰብስባ አታናግረኝም እያልኩ ሰበብ ፈጥሬ እመለሳለሁ:: አንዳንዴ ደግሞ ብቻዋን ከወጣች እንደነገሩ ከተል እልና ባጋጣሚ ዞር ካለች አቅጣጫዬን ለውጬ እሄዳለሁ፡፡ ዛሬ ግን እሷው ቀድማ ስታናግረኝና መንገዱ ወለል ብሎ ሲከፈትልኝ የምናገረውና የማደርገው ጠፍቶኝ ፈዝዤ መቆሜ ምን ይባላል? አሁን ወደድኩም ጠላሁም ልወጣው ከማልችለው እውነታ ጋር ተፋጥጫለሁና መልስ መስጠት ስለነበረብኝ፣ "እ... እ.... አልቸኮልኩም " ብዬ በነበርኩበት ፈዝዤ ቆሜ ቀረሁ።

መፍራቴን እንዳወቁና እንዳዩ በሳቅ መንከትከት ጀመሩ፡፡ ሳቃቸውን ስሰማማ መላ ሰውነቱን ድንጋጤ ወረረው ::ይባስ ብሎም ጉልበቴ መብረክረክ፣ ላቤም በፊቴ ላይ ችፍፍ ማለት ጀመረ፡፡ አይገርምም! ላብ በጭለማ ያውም በብርድ ወቅት፡፡ እፍረቴን ለማስወገድ በሚመስል መልኩ እጇን ዘርግታ፣ "እንተዋወቅ፤ አልማዝ እባላለሁ፣ እሷ ደግሞ ኤልሳቤጥ ትባላለች" አለችኝ፡፡ አልማዝ ስልክክ ያለች ቆንጆ ነች ማለት ባይቻልም የደስ ደስ ያላትና ያያት ሁሉ የሚወዳት፣ ፊቷ የሚማርክ የቀይ ዳማ ነች፡፡ ኤልሳቤጥ ጠቆር ስለምትል የእሷን ቅላት ታጎላዋለች እንጂ ቀይ የምትባል አልነበረችም:: ከሁለመናዋ እኔን የሚስቡኝ ግን ጎላ ጎላ ያሉት ዓይኖችዋ እና ከፍልቅልቅ ሳቅዋ ጀርባ የተደበቁት ሳቅ አድማቂዎቹ ነጭ ሰልፈኛ የሚመስሉት ጥርሶቿ እንዲሁም ውብና ተመጥኖ የተሰራው ከንፈሯ ነበር፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ ቀጠንና ረዘም ያለች ሆና ከወደ ዳሌዋ ሰፋ ያለች ናት፡፡ አልማዝ ምንም እንኳን ለውበትዋ ብዙም የማትጨነቅ፤ መኳኳልና መሽቀርቀር የማታበዛ ብትሆንም፣ እንደነገሩ እንኳን ለባብሳ ስትወጣ መላ ሰውነቷ ውበትን ይላበሳል፡፡ እኔ በተለይ እሁድ እሁድ ልብስ ለማጠብ እንደነገሩ ሆና ስትወጣ ማለትም ለአለባበስዋም ሆነ ለመልኳ ብዙም ሳትጨነቅ ሳያት በጣም ታምረኛለች፡፡ ፀጉርዋ ዞማ ሆኖ ጀርባዋ ላይ አይተኛ እንጂ ሉጫ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ሌላው እኔን የሳበኝ የድምፅዋ ቃና ነው፡፡ ቤተመጻሕፍት ውስጥ ስትንሾካሾክም ሆነ መንገድ ላይ ስታወራ ስሰማት የሙዚቃ ቃና ያለው ድምፅዋንና አወራሯን ተከትለው ወደ ላይና ወደ ታች የሚንከባለሉት ዓይኖችዋ ማንንም የማማለል ችሎታ አላቸው፡፡ ምንም እንኳን ባጠቃላይ ከግቢው ተወዳጅ ሴቶች ውስጥ ብቸኛዋ ባትሆንም ከዋናዎቹ ቆንጆዎች ጎራ የምትመደብ ነበረች፡፡ለእኔ ግን ከሁሉም በላይ የቆንጆ ቆንጆ ነበረች::" ሃምሳ አለቃው ለዛ ቢስ ፈገግታውን እያሳየኝ፤ "የሚገርም ነው! ለምን ሰዓሊ ወይም ደራሲ አልሆንክም? በጣም ጥሩ ገለፃ ነው፡፡ እስኪ አሁን ደግሞ እንዴት እንደተዋወቃችሁ በዝርዝር ንገረን" አለኝ በትዕዛዛዊ ስሜት፡፡ አነጋገሩ የለበጣ ቢመስልም አማራጭ አልነበረኝምና ትረካውን ቀጠልኩ፡፡ "እዚያ የፍቅር ጎዳና ላይ ቆሜ ፈራ ተባ እያልኩ ስሜን ተናገርኩ፡፡ ጊዜው ቢርቅም ትክክለኛ ስሜን የተናገርኩ ይመስለኛል፡፡ ድንጋጤውም ቀስ በቀስ እየለቀቀኝ በመሄዱ በእነሱ ጨዋታ አምጪነት የቆጥ የባጡን መቀባጠር ጀመርን፡፡ እኔም ብዙም ቁም ነገር ያለው ጨዋታ ባላመጣም የተቻለኝን ያህል አወጋሁ፡፡ በመጨረሻም ወደ ፊት አብረን ለማጥናት ተነጋግረን ተለያየን፡፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

09 Feb, 16:33


ለመጀመሪያ ጊዜ ላናግራት በመቻሌና ህልሜ እውን በመሆኑ ዝጅግ ተደሰትኩ። ወደ መኖሪያ ክፍሌ ስሄድም የምራመድ ሳይሆን የምንሳፈፍ ነበር የመሰለኝ። ክፍሌ እንደገባሁም እየሙህኩ አልጋው ላይ ዘልዬ ወደቅሁ። ጓደኞቼ ደብተራቸውን ይዘው እያጠኑ ስለነበር ሁሉም ደንግጠው ምን እንደሆንኩ ይጠይቁኝ ጀመር:: አሁንም ሰው መረበሼ እንኳን ሳይታወቀኝ፣ “አናገርኳት! ተዋወቅን!" እያልኩ መጮህ ጀመርኩ። ጓደኞቼ ድንጋጤው ለቀቃቸውና በሳቅ ተንከተከቱ:: ማንን እንዳናገርኩ ግን መጠየቅ አላስፈለጋቸውም:: ሁሌ ፉከራዬ “ዛሬስ አናግሬያት ካልመጣሁ ወንድ አይደለሁም!" የሚል ስለነበር ማንን አናገርክ ለሚለው ላይጨነቁ፤ “እንዴት አናገርካት? ምን አለችህ?'' እያሉ ሁሉም ይጠይቁኝ ጀመር፡፡ እኔም አንበሳ እንደመጣ አዳኝ ገድሎ ወዲህና ወዲያ እየተንጎራደድኩ፣ ሳልጠይቅ መጠየቄን እያጎላሁ ትረካዬን ተያያዝኩት፡፡ መቼም በዚያች ጊዜ አለመኖራቸው እንጂ በዚያች ጨለማና ብርድ እንዴት በፊቴ ላይ ላብ ችፍፍ እንዳለ ቢያዩ ኖሮ ምን ይውጠኝ ነበር? ይሁን እንጂ የዘወትር ፉከራዬ በመጨረሻ በመሳካቱ ያልተደሰተ አልነበረም፡፡ ሲያጠና ሰው እንዳይረብሽው የአልጋውን ዙሪያ በነጠላ ጋርዶ የሚያጠናው አስጨናቂ እንኳን ሳይቀር የፉከራዬ በመጨረሻ እውን መሆን አስደንቆት ነጠላውን ከፈት አድርጎ፤ “ከዚያስ፣ ከዚያስ" እያለ በመጠየቁ ጓደኞቼ በሙሉ ከእኔ በላይ ይጨነቁ እንደነበር ገባኝ::" ሃምሳ አለቃው በትረካዬን መሀል ገብቶ፤ "ጥሩ አሟሟቂ ጓደኞች ነበሩህ ማለት ነው! እሺ በል መጨረሻችሁን በደንብ አሰማኝ" ብሎ በረጅሙ የፌዝ ሳቅ ሳቀብኝ፡፡ ምን እንደነካኝ ባላውቅም ተርክ ተርክ፤ ቀጥል ቀጥል የሚል ስሜት ስለተሳማኝ ካቆረጥኩበት በመቀጠል፤ “የመኖሪያ ክፍላችን ጠበብ ያለች ብትሆንም በተደራረበ አልጋ ላይ እየተኛን ለስድስት እንኖርባታለን:: ከእኔ በላይ ተሰማ፣ ከፊት ለፊቴ እታች ካለው አልጋ ላይ ሁሌ ጋቢውን ጋርዶ የሚያጠናው አስጨናቂ፣ ከሱ በላይ ስለሞን ይተኛሉ:: ሁለተኛዋ የማጥኛ ክፍላችን ውስጥ አፈወርቅ የተባለ የሲዳሞ ልጅ እና ወንድይፍራው በተደራራቢ አልጋ ላይ ይተኛሉ፡፡ አብዛኞቻችን የአዲስ አበባ ልጆች ስንሆን ከሌላ አካባቢ የመጡት ደግሞ ከሲዳሞ አፈወርቅ፣ ከጎጃም አስጨናቂ ብቻ ናቸው:: ወደ ዩንቨርስቲ

የመጣነው በአንድ አውቶቡስ ስለነበርና ስለተግባባንም የአካባቢያቸውን ልጆች ትተው ከእኛ ጋር አንድ የመኖሪያ ክፍል ውስጥ ገብተዋል። አፈወርቅ ከሁሉም በላይ ለእኔ የተለየ ፍቅር ነበረው፡፡ ቀደም ሲል መናገሬን እየረሳሁት የምደጋግማቸውን ታሪኮችን ሳወራ ምንጊዜም ሳይስለች እያዳመጠ ሁሌም ይስቃል:: እኔም ብሆን በሴት ፊት ወኔ ባይኖረኝም ወንድ ብቻ በተሰበሰበበት ቦታ ከሆነ ጥሩ ተጫዋች ስለሆንኩ የሚያስቅ ነገር አላጣም:: ለእኔ ካለው ፍቅር የተነሳ ገንዘብም ካገኘ ለእኔ ሲጋራ ለመግዛት አይሰስትም፡፡ በሌላ በኩል ተሰማ ራሱን የሚጠብቅ፣ መዘነጥና መተረብ የሚያዘወትር ነበር:: እኔ አንዳንዴ እየረሳሁ የነገርኳቸውን ታሪክ ደጋግሜ ከተናገርኩ የሰማበትን ድግግሞሽ ሳይረሳ "ሁለተኛ" ፣ "ሶስተኛ" እያለ ሲቆጥር ስሰማ ስለሚያሳፍረኝ ሁሌ እናደድበታለሁ፡፡ ይሁን እንጂ እሱም እንደ አፈወርቅ ለእኔ የተለየ ፍቅር አለው:: ሆኖም ያስቀመጠው ዕቃ ያለ እሱ ፈቃድ ከቦታው ከተነሳ ከእኔም ሆነ ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር ይጣላል። በዚህ የተነሳ “ሚ/ር ጥንቃቄ' እያልን እንጠራዋለን፡፡ እኔ ከሁሉም በላይ መጫወትና ማብሸቅ የምወደው ሰለሞንን ነበር:: የቤቱ ሰው ሁሉ የሚዝናናው በእኔና በእሱ ብሽሽቅ ነው፡፡ ታዲያ እሱም ቢሆን ለጊዜው ብቻ ይበሽቅ ይሆናል እንጂ በነጋታው ግን የተናገርኩትን ነገር እራሱ እያነሳ ይስቃል እንጂ አይቀየምም፡፡ እኔም ብሆን ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ የማካፍለው ሚስጥር ካለኝ የማወራው ለእሱ ነው:: የልብ ጓደኛዬ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ለትምህርት በጣም የሚጨነቅ ቢሆንም የጥናት ፕሮግራም ግን አልነበረውም፡፡ አንዳንዴ ሌሊቱን በሙሉ ሲያጠና ያድርና በነጋታው ቀኑን በሙሉ በየዶርሙ ስለሚዞር፤ አንዱ ላጥናበት እያለ ሲያባርረው ሌላው ጋ እየሄደ ሲያወራ ይውላል:: አንዳንዴ ልተኛ ብሎ ጋደም ይልና፤ ተመልሶ እኛ እያጠናን መሆኑን ሲያይ ደንግጦ ተነስቶ ማጥናት ይጀምራል:: ታዲያ አንዴ ትዝ ይለኛል፣ ከምሽቱ 3፡30 አካባቢ ልተኛ አለና 4፡00 ላይ እንድቀሰቅሰው _ ነግሮኝ ጋደም አለ፡፡ እኔም እንዳይተኛ የተለያዩ ነገሮችን እያነሳሁና እየተበሻሸቅን እያለ አራት ሰዓት ስለሆነ ከአልጋዬ ላይ ወርጄ ወደ እሱ በመሄድ መቀስቀስ በሚመስል መልኩ እየነቀነኩት፤ “ሰለሞን፡ ሰለሞን ተነስ አራት ሰዓት ሆኗል" እያልኩ ቀሰቅሰቅው፤ ምን ሊለኝ ነው ብሎ አይኑን አፍጥጦ እየጠበቀኝ ነበርና በመገረም መልክ ሰዓቱን ተመልክቶ፤ “ከይሲ! የጥናት ሰዓቴን ያቃጠልከው ሳያንስ ዓይኔ እያየ ትቀሰቅሰኛለህ" ብሎ ሊመታኝ ዘሎ የወረደው ትዝ ይለኛል::

ወንድይፍራው ለትምህርት ብዙም የማይጨነቅ ሆኖ ሳለ በጥናት እኛን ብቻ ሳይሆን የእርሻ ምህንድስና ተማሪዎች በሙሉ ያቃተንን የሂሳብ፣ የፊዚክስና ሌሎች ሂሳብ ነክ የሆኑ ትምህርቶችን የሚያስጠና ጎበዝ ተማሪ ነው፡፡ ብዙ ሰው የሚያውቀው በትምህርት ጉብዝናውንና በዝምተኛነቱ ቢሆንም በመኖሪያ ክፍል ውስጥ ግን ቀስ እያለ ተንኮል አዘል ቀልዶችን በመጣልና በማብሸቅ የሚታወቅ ነበር። በተለይ እኔና ሰለሞን ስንበሻሸቅ መስማትና መሳቅ ስለሚወድ በተቻለ መጠን ነገር እየለኮስ ያጣላናል፡፡ በዚህ ጠባዩ የተነሳ "ልዝቡ ሰይጣን" እንለው ነበር፡፡ ከመካከላችንም ብዙ ጊዜ ገንዘብ የሚላክለት እሱ ስለነበር ከደግነቱ የተነሳ እንደፈለግን ገንዘብ ከኪሱ ብንወስድም ቅር አይለውም ነበር።ከሁላችን የተለየ ጠባይ ያለውና ለማንኛችንም ጨዋታ ብዙም ደንታ የሌለው አስጨናቂ ነው:: እሱ በጥናት ጉዳይ ቀልድ አያውቅም :: ቀኑን በሙሉ ሲያጠና ቢውል ደስታው ነው፡፡ በጥናት መሀል ለማረፍ በማለት መጫወት ከጀመርንም፤ “እረ እናንተ ሰዎች አትረብሹኝ ላጥናበት፡፡ ጥናት ጨርሳችሁ ከሆነ ለምን ወደ ክበብ ሄዳችሁ አትጫወቱም?" እያለ ይነጫነጫል:: በዚህ ላይ ምንጊዜም የማልረሳት አንድ የብረት ሳጥን ነበረችው፡፡ ብዙውን ጊዜ ከሳጥኑ ውስጥ የሚፈልገው ነገር ካለ ሳጥኑን ከአልጋ ሥር ስቦ ሲያወጣ ጩኸቱ ሁላችንንም ከየእንቅልፋችን ይቀሰቅስናል፡፡ ታዲያ ዛሬ በዚህ ድርጊቱ ብንጣላውም ነገ ተመልሶ ማድረጉ ግን አይቀርም፡፡ ሆን ብሎ እኛን ለመቀስቀስ ወይም ለማናደድ የሚያደርገው ነገር ሳይሆን በዝንጋታ የሚያደርገው ስለነበር እሱን ከማኩረፍ ይልቅ፤ "ባቡሩ ባልሆነ ሰዓት መጥቶ ቀሰቀሰኝ፣ ወይም እንዴት ነው ዛሬስ ባቡሩ በዚህ አላለፈም?' እያልን በረባሹ የብረት ሳጥን ድምዕ እንቀልዳለን፡፡ ታዲያ ዛሬ እንዲህ ጓጉቶ ምን እንደተፈጠረ ሲጠይቀኝ መገንዘብ የቻልኩት የማይሰማ መስሎ ሲያዳምጥ እንደነበርና እሱም እንደ ሌሎቹ የእኔን መጨረሻ ለማወቅ መጓጓቱን ነው፡፡ ሃምሳ አለቃው መስማት የሚፈልገውን ታሪክ ትቼ ወደ ሌላ ጉዳይ በመግባት ስቀባጥርና ማእበል እንደሚያንገላታው መርከብ ከወዲያና ወዲህ ስወዛወዝ በማየቱ ሣይናደድ አልቀረም፡፡ በመሆኑም በንግግሬ መሀል ጣልቃ ገብቶ አቋረጠኝና ጥያቄና ቁጣ በተቀላቀለበት ሁኔታ፤ "አቶ አማረ እኔ የጠየቅሁህ ስለአልማዝ እንጂ ስለ ጓደኞችህ አይደለም:: ይልቅ የማይሆን ወሬ እያወራህ ውድ ጊዜዬን ከምታባክንብኝ ከአልማዝ ጋር ስለነበራችሁ ጓደኝነት እና ስለተፈጠረው ሁኔታ ብትነግረኝ ጥሩ ነው፡፡ ማለቴ ከአልማዝ ጋር በጓደኝነታችሁ ቀጠላችሁበት? ጓደኝነታችሁስ እስከ ምን

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

08 Feb, 16:28


ከአፍንጫ እንኳን የተሰጠው ለመተንፈስ እንኳን የምትበቃ ያህል አልነበረም፡፡ አብዝቶ የሰጠው ነገር ቢኖር ጭንቅላት ብቻ ነበር፡፡ የጭንቅላቱ ትልቅነት ከዓይኑ፣ ከከንፈሩና ከአፍንጫው ጋር የሚመጣጠን አልነበረም፡፡ በአጠቃላይ ሲታይ ለማስፈራራት የተፈጠረ ነገር ነበር የሚመስለው፡፡ አጠገቡ ቆሜ እያየኝ እንዳላየኝ ለመምሰል ያቺኑ ፊቱን አጨማዶ ተመልሶ አጎንብሶ ሲጽፍ ጭንቅላቱ ቅቤ የተቀባ ማሰሮ እንጂ የሰው ጭንቅላት አይመስልም፡፡ ትንሸ ቆየት ብሎ ይቀመጡ እንኳን ሳይለኝ፣ “እኔጋ ነው ?'' ብሎ አፈጠጠብኝ::

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

08 Feb, 16:28


ከመታየቱ ውጪ ከሌላ ተማሪ ጋር ሲሄዱ ማየት የተለመደ አይደለም፡፡ ተሾመ የአዲስ አበባ ልጅ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ወይ ብቻውን አሊያም ከእነሱ ጋር ብቻ ነው የሚታየው፡፡ እንደሚመስለኝ ከኤልሳቤጥ ጋር ቀደም ብለው የሚተዋወቁና ከአንድ አካባቢ የመጡ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ተሾመ ሽቅርቅር ሲሆን ቀለል ያሉ ልብሶችን በተለይም ቲ-ሸርትና ጂንስ አዘውትሮ ይለብሳል፡፡ ፀጉሩ በአጭሩ እንደተከመከመ ፅድ ያማረ ጎፈሬ ሲሆን ከረዥም ቁመናውና ከሰልካካ አፍንጫው ጋር ተደምሮ ግቢው ውስጥ ካሉ ወንዶች ይልቅ እሱ በሁለንተናው ጎላ ብሎ ይታያል፡፡ ጓደኝነቱ ለሁለቱም ሲሆን ኤልሳቤጥ ከሌለች አብዛኛውን ጊዜ ከአልማዝ ጋር ስለሚታይና ከሁለቱም ጋር ሲሄድም ቢሆን እጁን ሁል ጊዜ አልማዝ ትከሻ ላይ ጣል ስለሚያደርግ አብዛኛው የግቢው ተማሪ "የአልማዝ የፍቅር ጓደኛ ነው" እያለ ያማዋል፡፡ እንዲህ ሆኖ ማየት ስለማልፈልግ ሳይሆን አይቀርም፤ ግቢው ውስጥ የእሱንና የእሷን ፍቅረኛነት የማይቀበል ሰው ቢኖር ምናልባት እኔ ብቻ ሳልሆን አልቀርም፡፡ ቤተመጻሕፍት _ ውስጥ ግን ብዙውን ጊዜ አብረው የሚታዩት አልማዝና ኤልሳቤጥ ብቻ ናቸው፡፡ ተሾመ አብዛኛውን ጊዜ ዶርም ውስጥ ስለሚያጠና ወደ ቤተመጻሕፍት የሚሄደው አልፎ አልፎ ነው፡፡ አልማዝና ኤልሳቤጥ ቤተመጻሕፍት ውስጥ አብዛኛውን ጊዜ የሚቀመጡት እኔ ብዙውን ጊዜ ከምቀመጥበት መቀመጪያ ፊት ለፊት ነው፡፡ እኔ አዘውትሬ ቤተመጻሕፍት እየሄድኩ "የማጠናው" በእርግጥ ቦታው ለጥናት ከመኖሪያ ክፍላችን የተሻለ ቦታ ሆኖ ሳይሆን፣ አልሚናን አይቼ ለመመለስ ነበር፡፡ ሁል ጊዜ የምቀመጠው ከእርሷ ፊት ለፊት ሲሆን በየመሃሉ ጥናቴ እየተተወ መተያየት የተለመደ ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ አቀርቅሬ የማጠና ልምሰል እንጂ ቀልቤም ሆነ ጆሮዬ ያለው እነሱ ሹክሹክታና ሳቅ ላይ ነበር፡፡ መቼም ሰው ትኩረት ከሰጠ የሚያፈቅረውን ሰው መለየት አይሳነውም ብዬ ስለማስብ፣ እኔ

እሷን እንደማፈቅራት ሁሉ እሷም ለእኔ ፍቅር አላት ብዬ በመገመቱ ሳልታክት ፊት ለፊቷ ተቀምጬ ዓይን ዓይኗን ማየት ተያይዤዋለሁ፡፡ እሷም ብትሆን እንደእኔ አታብዛው እንጂ አልፎ አልፎ ሰረት እያደረገች ማየታ አልቀረም፡፡ነገር ግን እኔ ከእዚያ አልፌ እሷን ለማናገር ወኒ ሳላገኝ፤ እነሆ ቀናት በወራት፤ ወራት ደ5ሞ በዓመት ተተኩ፡፡ አንድ ቀን ታዲያ እንደለመድኩት እሷኑ ለማየት አንገቴን ቀና ሳደርግ አልሚና በፈገግታና በጥቅሻ ተቀበለችኝ፡፡ ጥቅሻው ለኔ ነው ብዬ ስላልገመትኩ ከበስተኋላዬ ሌላ ሰው ይኖራል ብዬ በማሰቤ ወደ ኋላ ዞሬ አየሁ፡፡ የነበረው ግን ግድግዳው ብቻ ነበር፡፡ ለካስ በመደንገጤ ጥግ መቀመጤን ጭምር ረስቼው ነበር፡፡ አስተያየቷ ትዝ ይለኛል፤ ፈገግ ብላ ቅዝዝ ባለ ዓይን የምትመለከተው እኔነ ነበር ፡፡ እፍረቴ ስለመጣ መልስ በመስጠት ፋንታ ቶሎ አንገቴን ሰብሬ የውሸት ጥናቴን ተያያዝኩት፡፡ ግን አላስችል ስላለኝ ትንሽ ቆየት ብዬ ቀና ስል አሁንም ዓይኗ እኔው ላይ እንደተተከለ ነበር፡፡ መልስ ስላልሰጠኋት ደንግጣ ነው መሰለኝ በፊቷ ላይ የሐፍረት ስሜት ይነበብ ነበር፡፡ እኔም ይህንኑ ለማሸነፍ የሞት ሞቴን ፈገግ አልኩ፡፡ የእኔና የአልማዝ የፍቅር ህይወት እዚሁ ላይ በፈገግታ ተጀመረ። ዛሬ የእኔ ፈገግታ በቦታው ባይኖርም ይኸው እሷ ግን አሁንም እንደሳቀች ነው፡፡ ፎቶዋን ወደ ግድግዳው አዙሬ ማታ ለብሼው ያደርኩትን የተጨማደደ ልብስ መቀየር ጀመርኩ፡፡ ከመቸኮሌ የተነሳ ሸሚዜን አዛንፌ፣ ጫማዬን አዟዙሬ እግሬን ለማስገባት ትግል ገጠምኩ፡፡ ጫማዬን እንደምንም ተጫምቼ፣ ልብሴን ለበስኩና ኮቴን ከመስቀያው ላይ አንስቼ እየተጣደፍኩ ወጣሁ፡፡ በሩን ሳልዘጋ ጉዞ ከጀመርኩ በኋላ ልዘጋው ተመለስኩ፡፡ ሠራተኛዬ ቤት ውስጥ እንደሌለች አሁንም ረስቼው ነበር፡፡ ከዚያም ታክሲ ተሳፍሬ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ጽ/ቤት ከነፍኩ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ጽ/ቤት ወደ ጎጃም በር በሚያስኬደው መንገድ ከሰሜን ሆቴል ዝቅ ብሎ ይገኛል፡፡ የእኔ ሰፈር ደግሞ የድሮው ቃጫ ፋብሪካ አሁን አዲሱ ኮካኮላ የሚባለው አካባቢ ስለነበር እዚያ ለመድረስ ቢያንስ ከአንድ ሰዓት በላይ ይወስዳል፡፡ በዚሀ ላይ እንደኔ በጭንቀት ለሚጓዝ ሰው አንድ ሰዓት ራሱ እንደ አንድ ቀን ሊረዝምበት ይችላል፡፡ እንደዛሬው ሳይሆን ከልጅነቴ ጀምሮ አለማያ እስከገባሁበት ጊዜ ድረስ ይህንን መንገድ ቢያንስ በሳምንት አንዴ እጓዝበት ነበር፡፡ በተለይ ፊልም ማየት ስለምወድና ጃንሆይ ቢያንስ በሳምንት አንዴ ልዕልት ፀሐይ ሆስፒታል የተኙ ህመምተኞችን ለመጎብኘት ሲመጡ ብር ስለሚሰጡን ከሲኒማ ኢትዮጵያ፣ ከሲኒማ አድዋ፣ ከሲኒማ ኢምፓየር ወይም ከሀገርፍቅርና ከማዘጋጃ ቤት አንዱ ጋ ላልገባ

አልቀርም ነበር፡፡ ለዚህም ካልሄድኩ ማዘጋጃ ቤት ቤተመጻሕፍት ለጥናት ሳልሄድ አልቀርም፡፡ በተለይም አሁን የምሄድበትን ፖሊስ ጣቢያ ድሮ ቋንቋ እማርበት ከነበረው ከጣሊያን ካልቸራል ኢንስቲትዩት አጠገብ እና ደርግ የኢሕአፓና የሌሎች ፖለቲካ ድርጅት አባል የሆኑ የፖለቲካ እስረኞችን እያስቃየ የሚገድልበት ወንጀል ምርመራ እየተባለ የሚጠራው እስር ቤት አካባቢ ስለነበር በደንብ አውቀዋለሁ፡፡ እንዲያውም ከጣሊያን ካልቸራል ኢንስቲትዩት ቋንቋ ተምረን ስንወጣ እዚያ ስንደርስ መንገድ ተሻግረን ነበር የምንሄደው፡፡ አንዳንዴ የደርግ መርማሪዎች የሚገርፉና የሚያሰቃዩት ሰው ሲያጡና ሲደብራቸው ከአላፊና አግዳሚ ሰው ውስጥ ኢሕአፓ ይመስላል የሚሉትን ያጎፈረ ወጣት ከመንገድ ላይ እየያዙ አስረው ስለሚያሰቃዩ ምንጊዜም በዚያ የምናልፈው በፍርሀት እየተርበደበድን ነበር፡፡ አራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አካባቢ ስደርስ ልቤ ምቱ ጨመረ። የምን ነገር ነው? የምን ጣጣ ነው? እንዴት ከዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላ እንዲህ ሊሆን ይችላል? ገና መልስ ያልተገኘለት ጥያቄ ነበር፡፡ አሁን መርበትበቱ ምንም ዋጋ የለውምና እውነታውን ለማወቅ ወደ ፖሊስ ጽ/ቤቱ ጉዞ ቀጠልኩ፡፡ በር ላይ ለቆመው ዘብ ተጠርቼ እንደመጣሁ አስረድቼና ተፈትሼ ወደ ቀጠረኝ ሃምሳ አለቃ ቢሮ አመራሁ፡፡ ቢሮዋ ጠባብ ናት፡፡ እዚያቹ ውስጥ ሁለት ፖሊሶች ተቀምጠው ስለነበር የፈለገኝ ሃምሳ አለቃ የቱ እንደሆን ጠይቄ ወደ እሱ ተራመድኩ፡። ሃምሳ አለቃው አንድ ተላልጣ ልታልቅ የደረሰች ጠረጴዛ ላይ አጎንብሶ እየጻፈ ስለነበር አጠገቡ መቆሜን ቶሎ አላየም ነበር። ቀና ብሎ ሲያየኝ ደነገጥሁ፡፡ ጠቆር ያለ ነው፡፡ በፊቱ ላይ በአግባቡ የተቀነባበረ መልክ የለውም፡፡ እግዚአብሄር ካላጣው የውበት ጥበብ በእሱ ላይ አድልዎ ሳይፈፅም አልቀረም፡፡ ፀጉሩ አለ እንዲባል ያህል ብቻ አለፍ አለፍ ብሎ ጣል ጣል የተደረገ ሲሆን፣ ይህም በዛ ተብሎ መመለጥ ጀምሯል፡፡ ዓይኖቹ ከትንንሽነታቸው የተነሳ ትንሽ ጠባብ ጉድጎድ ውስጥ የወደቁ ትንንሽ ብዮች እንጂ ዓይን አይመስሉም፡፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

08 Feb, 16:28


🍁🍁ዲያሪው 📝

          ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
           #ክፍል_1

ዱብዕዳ

ከተኛሁ በኋላ የተደወለውን ስልክ ማንሳት ሞት መስሎ ተሰማኝ: ዓይኔን እንደጨፈንኩ መብራት ለማብራት ግድግዳውን ዳበስኩት፡፡ ነገር ግን ማብሪያና ማጥፊያውን ላገኘው አልቻልኩም፡፡ ልማድ ሆኖብኝ ዓይኔን አንድ ጊዜ ከከፈትኩ በኋላ እንደገና እንቅልፍ ስለማይወስደኝ ብዙ ጊዜ እንቅልፌን ካልጨረስኩ ስልክ የማናግረው ዓይኔን እንደጨፈንኩ ነው፡፡ ኮመዲኖ ላይ የነበረውን ባትሪ አብርቼ ማብሪያና ማጥፊያውን ለመፈለግ ስል ዓይኔን ስከፍት ግን ያልጠበኩት ነገር ገጠመኝ፡፡ ምንም የተኛሁ ሳይመስለኝ ነግቶ ቤቱ በብርሀን ተሞልቶ ነበር፡፡ ለካስ ማታ ራሴን እስክስት ጠጥቼ ስለነበር ጫማዬንና ልብሴን ሳላወልቅ ወደ ግርጌ ዞሬ በመተኛቴ ነበር ማብሪያና ማጥፊያውን ማግኘት የተሳነኝ:: ወደ ራስጌ ዞሬ ስልኩን ኮመዲኖው ላይ ብፈልግም ላገኘው አልቻልኩም:: ሁሌ አምሽቼ ከመጣሁና የእረፍት ቀኔ ከሆነ ስልኩ እንዳይረብሽኝ ሳሎን ውስጥ ማስቀመጤ የተለመደ ስለሆነ ማታም እዚያው ወስጄው ኖሯል :: አማራጭ አልነበረኝምና ስልኩን እንድታቀብለኝ "ዓለሚቱ" እያልኩ ተጣራሁ፣ ግን መልስ የለም:: ረስቼው ነው እንጂ ለካስ ዘመድ ጥየቃ ብላ ሄዳለች፡፡ ዘመድ ያላት ሠራተኛ መቅጠር ጣጣ ነው፡፡ "ሴቶች ዘመዱን የጨረሰ ባል ስጠኝ" እንደሚሉት እኔ ደግሞ ዘመዶቿን የጨረሰች ሰራተኛ ስጠኝ እንዳልል ፈራሁ፡፡ ነጠላ ጫማ ፍለጋ አጎነበስኩ፡፡ ከሁሉ በላይ ጫማ መፈለግን የመሰለ ቦርጭን እንደሚያስተጣጥፍ ሥራ እጅግ የሚያስጠላኝ ነገር የለም፡፡ ላገኘው ስላልቻልኩ በባዶ እግሬ ሮጥ ሮጥ እያልኩ እንደምንም ብዬ ስልኩን ለማንሳት ወደ ሳሎን ለመሄድ ስደናበር ተበታትኖ የነበረው ወንበር አደናቅፎ ሊጥለኝ ሲል የመኝታ ቤቱን በር ተደግፌ ቆምኩ፡፡ እንደምንም ሄጄ የስልኩን እጄታ ወደ ጆሮዬ አስጠጋሁና፤ "ሀሎ" አልኩ፡፡ ምንም ድምፅ አልነበረም፡፡ ስደነባበር ደቂቃዎች ፈጅቼ ኖሮ ደዋዩ ሰው ተስፋ ቆርጦ ስልኩን ዘግቶት ነበር፡፡ ሶፋው ላይ ቁጭ ብዬ እንደመሳቅ ቃጣኝ፡፡ መሳቅ የቃጣኝ በሌላ ነገር ሳይሆን "እንዲህ አርበትብቶና አደናብሮ ያውም ለሚዘጋ ስልክ ምን አስሮጠኝ?" የሚለውን ሳስብ ነበር፡፡ እርግጥ በጠዋት የተደወለና ከእንቅልፌ ቀስቅሶ ያስነሳኝ ስልክ ስለነበር ነገሮችን አሰባስቤ ለማስብ ፋታ ባለማግኘቴ፣ አሊያም ዓለሚቱ እደጅ በማደሯ "አንድ ነገር ሆና ይሆን ያለወትሮዋ ደጅ ያደረችው?'' እያልኩ ስጨነቅ

ስለነበር ይኸው ሳይሆን አይቀርም እንዲህ ያሯሯጠኝ፡፡ የራሴ ነገር እየገረመኝ ወደ አልጋዬ ለመሄድ ስነሳ ስልኩ ዳግም አቃጨለ፡፡ ስልኩን አነሳሁና፣ "ሀሎ" አልኩ፡፡ "አቶ አማረ?" አለ በስልክ የሚያናግረኝ ሰው፡፡ "አዎ ነኝ " አልኩ ተጣድፌ፡፡ "ከዚህ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጽ/ቤት ነው':: "ምነው በደህና?" "አይ በደህና ነው፡፡ወ/ሮ አልማዝ አስፋውን ያውቋታል?" ራሴ በአንዳች ነገር የተመታ ያህል አዞረኝና ሶፋው ላይ ተመልሼ ቁጭ አልኩ፡፡ አልማዝንና ፖሊስን ምን አገናኛቸው? አንድ ነገር እንደተፈጠረ ስለተስማኝ ተቻኩዬ እንደማውቃትና ምን እንደተፈጠረ እንዲነግረኝ ጠየቅሁ። እሱ ግን ለጥያቄዬ መልስ ሳይሰጠኝ "ለጥያቄ ስለምንፈልግዎ እባክዎን አዲስ አበባ ፖሊስ ጽ/ቤት ድረስ ቢመጡልን" አለኝ፡፡ "ምንድነው ችግሩ ለምን አትነግረኝም? " አልኩት፡፡ "ሲመጡ ይደርሳል'' ብሎ ስልኩን ጆሮዬ ላይ ዘጋብኝ። መብረቅ እንደመታው ዛፍ እተቀመጥኩበት ደርቄ ቀረሁ፡፡ ምን ተፈጥሮ ይሆን? በሕይወት ትኖር ይሆን ወይስ ሞታለች? ግን እኔ ለምን ተፈለግሁ? እንዴትስ እዚህ ልትመጣ ቻለች? ከሳኝ ይሆን? ሌላ ሌላም ጥያቄ ጭንቅላቴ ውስጥ መመላለስ ጀመረ። ሁሉንም ነገር ማውጣትና ማውረዱ ጥቅም ስለሌለው፣ የሆነው ነገር ሆኗልና ፈጥኜ መድረስ ስላለብኝ እየተንገዳገድኩ ወደ መኝታ ቤቴ ገባሁ፡፡ ያጣሁትን ጫማ ለመፈለግ እጄን አልጋው ሥር ሰድጄ ስደባብሰ ሽታው መራኝና አፍንጫዬ ሥር አገኘሁት:: ልብሶቼን ለመልበስ ስፈላልግ ከራስጌዬ አጠገብ ኮሞዲኖው ላይ ከተቀመጠው ከአልማዝ ፎቶ ጋር ተፋጠጥኩ፡፡ ዓይኖቿ አሁንም ቦግ እንዳሉ ናቸው፡፡ ዘወትር የማይጠፋው ፈገግታዋ አሁንም አለ፡፡ እዚህ ግዑዝ አካል ላይም "ለዘላለም" ተጣብቆ ይኖራል፡፡ አሁን የሌለውና የማይሰማው ነገር ያ አሳዛኝ ድምዕዋ ብቻ ነበር፡፡

"ለምን ፈገግ አለች?" አልኩ፣ ትኩር ብዬ ፎቶዋን እያየሁ:: አስተያየቷንም ሳየው መሰለኝ፡፡ "አይ አንተ ምስኪን፣ አሁንም አለህ?" እያለች የምታፌዝብኝ አይ አልማዝ! አሁንም አይበቃትም? ለምን ሁሌ በእኔ ላይ እየሳቀች ታፌዛለች? በመውደዴ እንደጅል ቆጥራ ለምንስ ትጫወትብኛለች? ምን ይታወቃል፤ የበፊቱ አልበቃ ብሏት አሁን ደግሞ እንደገና እኔኑ ጥፋተኛ አድርጋ አሳኝ ሊሆን ይችላል አልኩ፡፡ ግን ለምን? ከእኔ ከምስኪኑ ምን ለማግኘት? ይኸ ሊሆን የሚችል አይደለም ፡፡ አንድ ነገር ሆና መሆን አለበት እያልኩ ወደ ጭንቀት ባሕር ሰጠምኩ፡፡ ፎቶዋን ደግሜ አየሁት፡፡ አይ አልማዝ! ሁሌ መሳቅ፣ ሲደሰቱም መሳቅ፣ ሲያሞኙም መሳቅ፣ ያኔም እንዲህ ነበረች፡፡ ጥንትም ገና ሳያት ያቀረበኝ ይኸው ሳቋ ነበር፡፡ ትዝ ይለኛል፤ አለማያ ዩንቨርሲቲ እያለን እሷ ለምሳ የምትሰለፈው ከሀረሮች ጋር ነበር፡፡ ያኔ ሁሉም ተማሪ በተለይ በምሳ ሰዓት ድካምና ረሀቡ ፀንቶበት ቢያወራም በሹክሹክታ፣ ቢራመድም በቀስታ ነበር፡፡ የሀረር ልጆች ብቻ ሲከፋቸው አይታይም:: ሁሌ መሳቅ፣ ሁሌ መደሰት ነው፣ ጫት ብቻ አይጥፋ እንጂ! ጫት ተገዝቶ ከተቀመጠ ችኮላው ለሱ ነው፡፡ ሁሌ ቀደም ብለው ሰልፍ የሚይዙት እነሱ ናቸው፡፡ ሁሌ ከሰዓት በኋላ እነሱን ያየ ሰው ደስተኛ መሆናቸውን ያለጥርጥር መናገር ይችላል፡፡ ግን ምን ያደርጋል? ማታ ማታ ብቻ ከምርቃና በኋላ ድብርት ይይዛቸዋል፣ አንደበታቸውንም ይቆልፈዋል፡፡ በዚህ ሰዓት አላርፍ ብሎ ከእነሱ ጋር መቃለድ ወይም አፉን መክፈት የፈለገ ሰው ካለ የሚከተለው ሊሸከመው የማይችል ከእናት ጋር የተያያዘ ስድብ ነው:: መጀመሪያ አካባቢ በተለይ ከወደስሜን የመጣ ሰው እንዲህ ዓይነት ስድብ ሲሰደብ አንቄ ካልገደልኩ ይል ነበር። አንዴ ትዝ ይለኛል አንድ ጎንደሬ ተማሪ በዚህ ስድብ ተናዶ፣ “እኔው እራሴ እምዬን? እሱው ራሱ እንኳን ቢሆን ይሻል ነበር፣ እንዴት ያለ ነውር ነው እናንተ ሆዬ!" በማለት ካልገደልኩ ብሎ ግቢውን እንደበጠበጠ ትዝ ይለኛል፡፡ የአልሚና ጠባይ ግን እንደጫት ቃሚዎቹ ፀሐይ ስትወጣና ልትጠልቅ ስትል አብሮ ሲለዋወጥ አይታይም:: ሁሌ ከፊቷ ላይ ፈገግታ አይጠፋም፡፡ ከሷ ጋር በመልክ ቀለሟ ተቃራኒ ከሆነች የሴት ጓደኛዋ ጋር ማለቂያ የሌለው ወሬ እያወሩ መንከትከት የተለመደ ጠባያቸው ነው፡፡

አልሚና ቀላ ስትል ጓደኛዋ ግን ጠቆር ያለ ግን ውብ ቀለም ያለው ፊት አላት፡፡ የግቢው ሰው በዚሁ ማለቂያ በሌለው ወሬያቸው የተነሳ ቢቢሲ ይላቸዋል፡፡ እነርሱ ቤተመጻሐፍት ውስጥ ካሉ ጥናት የለም፡፡ ሲንሾካሾኩ ድምፃቸው አጠገባቸው የተቀመጠውን ሰው ሁሉ ይረብሻል፡፡ እኔ ግን በድምፃቸው ተረብሼ ካጠገባቸው አልጠፋም፡፡ ብዙውን ጊዜ የታፈነ ሳቃቸው ቀልቤን ስለሚስበው ምን እንደሚያወሩ ለማዳመጥ ጆሮዬን ሳሾል ጥናቴ መና ሆኖ ይቀራል፡፡ ብዙውን ጊዜ የትም ቦታ ቢሆን አልማዝና ኤልሳቤጥ ስለማይለያዩና አፍ ለአፍ ገጥመው እያወሩና እየተሳሳቁ ሲሄዱ ቀልብን ስለሚሰርቁ ግቢው ውስጥ እነሱን የማያውቅ ተማሪ አለ ማለት አያስደፍርም፡፡ አልፎ አልፎ የእርሻ ኢኮኖሚክስ ተማሪ የሆነው ተሾመ የሚባለው ልጅ አብሮ ከእነሱ ጋር

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

28 Dec, 16:22


የመጨረሻ ክፍል
ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያስምንት

ድክምክም ብሎታል፡፡ግን ደግሞ አልጋው ላይ ተኝቷ በሀሳብ እየተንገላታ ነው፡፡ ሰለሞን በሁለት በኩል ስለት ባለው ሰይፍ የሚጫወት ህፃን አይነት ሰው እንደሆነ እየተሰማው ነው፡፡ሞያውን በተመለከተ ለሶስት አመት በከፍተኛ የፕሮፌሽናል ደረጃ በምድረ-አሜሪካ ሲሰራ አንድም ጊዜ እንደዚህ አይነት ክፍተት ተከስቶበት አያውቅም..በዛም በራሱ ሲመካና ሲኮራ ኖሮ ነበር፡፡አሁን ግን ወደሀገሩ ተመልሶ ባጋጠሙት የመጀመሪያ ደንበኞቹ ከፍተኛ የሚባል ሽንቁር ተከስቶበታል፡፡አንድ ባለሞያ የሞያውን ስነምግባር አክብሮ ስራውን መስራት የሚገደደው ለደንበኞች ደህንነትንና ጥቅም ሲባል ብቻ አይደለም…ለራሱ ለሞያው ክብርና ተቀባይነትም እያንዳንዱ ባለሞያ የስራ-አፈፃፀም ሁኔታ ትልቅ ድርሻ አለው፡፡በሙስናና በጥቅማጥቅም የሚታለሉ ዳኞችና አቃቢ-ህጎች በሞሉበት ሀገር ፍርድቤት ሊከበርና ሊታመን አይችልም፡፡ሌላውም ሞያ እንደዛው ነው፡፡ ይህን ስራ ከጀመረ ያጋጠመችው ትልቋ ደንበኛው በፀሎት ነች፡፡እርግጥ ቀጥታ ደንበኛው እሷ ሳትሆን ወላጆቾ ናቸው፡፡ከእነሱ ጋር እየሰራ ያለውን ስራ የሞያው ስነምግባር በሚፈቅደው መንገድ ጥርትና ጥልል አድርጎ እየሰራ ነው፡፡ቢሆንም ቀጥታ ቀጣሪው ልጃቸው በፀሎት ነች፡፡እሷ ፍላጎቱን ተረድታ አፈቅርሀለው ብትለው እንኳን ፍቅሯ እሱ ለወላጆቾ በሚያደርገው የሞያ ድጋፍ ተፅዕኖ ስር የወደቀ ወይንም በይሉኝታ ስሜት የተቀነበበ ሊሆን ይችላል…ይሄንን ማንም በእርግጠኝነት ማወቅ አይችልም…በዚህም ምክንያት ከእሷ ጋር ደግሞ ያለው ግንኙነት እየሄደ ያለበት መንገድ ትክክል እንዳልሆነ ያውቃል፡፡ከሞያ ስነምግባር ውጭም እንደሆነ ያምናል፡፡ይሄ ጉዳይ ነው በጣም እያስጨነቀው ያለው፡፡ ከበፀሎት ጋር የፍቅር ስሜት በተሰማበት ቅፅበት ሁለት ምርጫ ነበረው፡፡አንድም በእሷ ቀጣሪነት ወላጆቾን ለማከም የተዋዋለውን የስራ ውል አፍርሶ ነፃ መውጣትና.. ከልሆነም ልቡን ገስፆ እና ፍቅሩን በውስጡ አክስሞ ስራው ላይ ብቻ አትኩሮ መቀጠል፡፡ቢያንስ ስራውን በተዋዋለው መሰረት ሙሉ በሙሉ አጠናቆ እስኪጨርስ ድረስ እንደዛ ነበር ማድረግ ያለበት፡፡ግን ይሄው ሁለቱንም ማድረግ አልቻለም፡፡ ‹‹ግን እኮ ይሄ በስራ አለም ቆይታዬ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈፀምኩት የሞያ ስነምግባር ጥሰት ነው››ሲል እራሱን ለማፅናናት ሞከረ…..፡፡ንግግሩ ግን እራሱንም ሊያሳምነው አልቻለም፡፡ ‹‹ስህተት የመጀመሪያም ሆነ የመጨረሻ ያው ስህተት ነው››የገዛ አእምሮ መልሶ የነገረው ነበር፡፡ ‹‹አሁን ወደኃላ መመለስ አልችልም…ይሄንን ጉዳይ ከዳር ላድርስና ..ከእሷ ጋር ያለኝ የፍቅር ግንኙነት የሚደርስበትን ከፍታ አይቼ ውጤታማ የሚሆን ከሆነ ምን አልባት ሞያውን በክብር ብለቅና ወደሌላ ዘርፍ ብሸጋገር እንኳን ያዋጣኛል››ሲል ለጊዜው የታየውን መፍትሄ አስቀመጠ…የገዛ አእምሮው ግን ወዲያው ነበር አፍራሽ የሆነ ሀሳብ የሰጠው‹‹ሰውዬ ምን ነካህ..?ይሄንን ሞያ ለቀህ…ነጋዴም ብትሆን …ወይም ደራሲ… ሁሉም ሞያ አይነቱ እና ተጋላጭነቱ በመጠኑ ይለያይ እንደሆን እንጂ የራሱ ህጋዊም ሆኑ ሞራላዊ የስነምግባር ገደቦች አሉበት…በተለይ ፍቅርን በተመለከተ ሁሉም ሞያ ይፈተናል…አስተማሪ ብትሆን ተማሪህ ላይ አይንህን መጣል የለብህም…ማናጀር ሆነህ ፀሀፊህን መጎነታተል ስህተት ነው፡፡ሞያህን ሳይሆን አመለካከትህን ነው መቀየር ያለብህ… ራስህን አታሞኝ፡፡››አለው…. ለጊዜው በዚህ ጉዳይ ላይ ከዚህ በላይ ማሰብ አልፈለገም….ጉዳዩን ለጊዜ አሳልፎ ሰጠና ብድርብሱን ተከናንቦ እራሱን ለእንቅልፉን አሳልፎ ሰጠ ....ወዲያው ነበር ያሸለበው…የሚገርመው ደግሞ አይኖቹ በተከደኑ ከሁለት ደቂቃ በኃላ ነበር በፀሎት ነጭ ቬሎ ለብሳ ጭንቅላቷ ላይ የሚያብረቀርቅ የወርቅ አክሊል አጥልቃ ግራና ቀኝ ጎኗ ላይ የበቀሉ ውብ ክንፏቾን እያማታች ከሰማዩ ላይ ሰንጥቃ መጥታ እቅፉ ውስጥ ስትገባ በህልሙ ያየው፡፡
///
በፀሎትና ለሊሴ ከወንጪ ከተመለሱ ሁለት ቀን ሆኗቸዋል፡፡መሽተዋል…አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ ነው…በፀሎት እና ፊራኦል ግቢው ውስጥ ካለ ግዙፍ የመንጎ ዛፍ ስር ጎን ለጎን ቁጭ ብለው እያወሩ ነው፡፡
‹‹እንዴት ነበር ወንጪ?››
‹‹ውይ ሲዊዘርላድ በለው፡፡››
‹‹እኔ ወንጪን እንጂ ሲዊዘርላንድን አላውቃትም፡፡››
‹‹አኔ ደግሞ አውቃታለዋ ለዛ ነው ያነፃፀርኩልህ..ደግሞ ዘመዶቻችን እንዴት ደግና ቀሽት መሰሉህ?፡፡››
‹‹የእኔም ዘመዶች እኮ ናቸው አውቃቸዋለው››
‹‹አይ ቢሆንም ..አንተ ምንአልባት ከልጅነትህ ጀምሮ ስለምታውቃቸው …ብዙም ጣእም ላይሰጥህ ይችላል..ማለት ሁለም ሰው እንደእነሱ አይነት ዘመድ ያለው ስለሚመስልህ ተራ ነገር አድርገህ ልትቆጥረው ትችላለህ….እንደእኔ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደዛ አይነት ዘመድ ሲኖርህ ግን በቃ ..ከአሁኑ እንዴት እንደናፈቁኝ ብታውቅ››
‹‹ገና በሁለት ቀን››
‹‹አዎ በሁለት ቀን››
‹‹አሁን ከእኛ ስትለይና ወደቤትሽ ስትሄጂ እንናፍቅሻለን ..?ማለት እኔ ናፍቅሻለሁ?››ለቀናት በውስጡ ሲያብሰለስለው የነበረውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
‹‹ምን ማለት ነው….?ወደየትኛው ቤቴ ነው የምሄደው?››
‹‹ወደቦሌው ቤትሽ››

‹‹ምን….ለሊሴ ነገረችህ››
‹‹እሷ ታውቃለች እንዴ?››
‹‹እሷ ካልነገረችሽ ታዲያ ማን ነገረህ?››
‹‹እራሴ ነኝ የደሰረስኩበት ..ወደ ወንጪ ከመሄዳችሁ በፊት ነው ያወቅኩት››
‹‹እኮ እንዴት ልታውቅ ቻልክ?››
‹‹ያው እንዳልኩሽ የእህቴን ልብ ከተቀበልሽ በኃላ በሩቅ ሆኜ ለረጅም ጊዜ ስከታተልሽ ነበር..ስለዚህ በደንብ አውቅሻለው…እዚህ ቤት ከመጣሽ ከሳምንት በኃላ ጀምሮ ከፍተኛ ጥርጣሬ አድሮብኝ ነበር..ከዛ ምን አደረኩ አንድ ቀን ስትተኚ ሻርፕሽን ሙሉ በሙሉ ከፊትሽ ላይ ገፍፌ ተመለከትኩሽ…እና ኦርጅናለዋ በፀሎት መሆንሽን አረጋገጥኩ፡፡
‹‹ትገርማለህ..ከዛ ፀጥ አልክ?››
‹‹ምን ላድርግ…ምንም ማለትና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላወቅኩም ነበር፡፡››
‹‹አሁንስ አወቅክ?››
‹‹አይ….አንቺ ንገርኝ እስኪ …ምን ልታደርጊ ነው…?እስከመቼ ነው ከወላጆችሽ ምትደበቂው?››
‹‹ወላጆቼን በቀደም አግኝቼቸዋለው..እዚህ መሆኔን ያውቃሉ››ብላ ያልጠበቀውን ዜና ነገረችው፡፡
‹‹ጥሩ..እሺ እነአባዬን እንዴት ልታደርጊ ነው….?እንደዋሸሻቸው ሲያውቅ በጣም ነው የሚያዝኑብሽ…በአንቺ ብቻ ሳይሆን እኛም አውቀን ከነሱ ደብቀን ዝም በማለታችን ምን እንደሚወጥን አላውቅም? በጣም ጨንቆኛል›ብሎ እውነተኛ ስሜቱን ነገራት፡፡
‹‹ይቅርታ ፊራኦል..እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ስላስገባዋችሁ በጣም አዝናልው…ግን በዚህ ሁለት ሶስት ቀን ውስጥ እፈተዋለው…ማለት እናንተ ቀድማችሁ እንደምታውቁ ሳላሳውቅ እፈተዋለው››
‹‹እስኪ እናያለን…››

‹‹እኔ የእህትህን ልብ የተሸክምኩ በፀሎት መሆኔን እርግጠኛ ስትሆን ምን ተሰማህ?››
‹‹ግማሽ ሀዘን ግማሽ ደስታ››
‹‹አልገባኝም››
‹‹ለረጂም ጊዜ ላናግርሽና ቀርቤ ላወራሽ የምመኝሽ የእህቴን ከፊል አካል የተሸከምሽው በፀሎት የገዛ ቤቴ መጥተሸ ከእኔ ጋር አንድ መአድ እየቆረሽ መሆንሽን ሳውቅ ፍጽም ድስታ ነው የተሰማኝ…በሌላ ጎኑ ደግሞ ያችኛዋን በፀሎት አፍቅሬት ስለነበር….ሌላ በፀሎት እንዳልሆንሽ ሳውቅ ቅር ብሎኛል››

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

28 Dec, 16:22


‹‹ከመቀመጫዋ ተነሳችና እላዩ ላይ ተጠምጥማ ጉንጩን እየሳመችው‹‹….የእኔ ወንድም
…..በጣም ነው የምወድህ……››አለችው
‹‹እኔም እህቴ በጣም ወድሻለው…አሁን እራት እየቀረበ ነው መሰለኝ ወደቤት እንግባ…››
‹‹እሺ እንግባ››ተባባሉና ተያይዘው ወደቤት በመግባት ከቀረው ቤተሰቡ ጋር ተቀላቀሉ፡፡
//
አቶ ለሜቻና ቤተሰባቸው በአጠቃላይ ሙሉ ትኩረቱ የበሬዱ የሶስተኛ አመት የሙት አመት መታሰቢያ ላይ ነው፡፡ይሄ ባለፈው ሁለት አመት በተመሳሳይ የመታሰቢያ ድግስ የተደገሰ ቢሆንም የዘንድሮ ግን በተለየ ሁኔታ ትኩረት ተሰጥቶታል ፡፡የዚህም ምክንያት በቤተሰቡ ውስጥ ተአምራዊ በሆነ መንገድ በፀሎት የምትባል ልጅ ስለተጨመረችና ከዛም ተያይዞ ከሞላ ጎደል የቤተሰቡ የገንዘብ ችግር ስለተሻሻለ፤ ከዚህ በፊት ከነበረው ከፍ ባለ ሁኔታ ለመደገስና በሟቾ ስም በርከት ያሉ ችግረኞችን በማብላት ነፍስ ይማር በማሰኘት የተወሰነ የመንፈስ እረካታና የአእምሮ መረጋጋት ለማግኘት ጠንክረው በጥሩ ሞራል እየደገሱ ነው፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ አቶ ኃይለልኡል ቤት በአይነቱ ለየት ያለ ድብልልቅ ያለ ድግስ እየተደገሰ ነው፡፡የእነሱ ምክንያት ደግሞ ሚያዚያ 20 ቀን የልጃቸው በፀሎት የልብ ንቅለተከላ ያደረገችበትና ሁለተኛ የመኖር እድል ያገኘችበት ስለሆነ ያንን ቀን በፌሽታና በምስጋና የማሳለፍ አላማ ያለው ነው፡፡ይሄንን ድግስ ያለፉትን ሁለት አመታት አድርገውታል፡፡ የዘንድሮው ግን በአይነትም ሆነ በመጠን ከፍ ያለ ነው፡፡ይሄም ዘንድሮ ሁኔታዎች የተለዩ

ስለሆኑ ነው፡፡ከቤታቸውም ከፊታቸውም የተሰወረችው የልጃቸው በፀሎት ከወር በኃላ ወደቤቷ ምትመለስበት ቀን ይሆናል የሚል ጉጉት ስላላቸው ልጃቸውን እጥፍ ድርብ በሆነ ፌሽታ ለመቀበል ያደረጉት ነው፡፡ከዚህም በተጨማሪ ሌላ የተለየ ምክንያት አላቸው ፡፡ባልና ሚስቶቹ ለአመታት ከገቡበት አስጠሊታ ግንኙነት እና የእርስ በርስ ጥላቻ ተገላግለው. ቀሪ ህይወታቸውን በመከባበር እና በፍቅር ለማሳለፍ ወስነውና ተስማምተው ቀሪ እንደአዲስ ለመጀመር የወሰኑበት ወቅት ስለሆነ ለእነሱም እንደ ዳግማዊ ሰርግ ነው…ለዛ ነው የተለየና እንከን አልባ ድግስ እንዲሆን እየጣሩ ያሉት…ያው እንደተለመደው የድግሱን ቅንጅት በሀላፊነት የወሰዱት ፕሮፌሽናል ባለሞያዎች ናቸው፡፡
የጭንቁ ቀን ደርሶል ፡፡አቶ ለሜቻና ወይዘሮ እልፌ ከሌሎች ጎረቤቶች ጋር በለሊት ነው ወደ ቤተክርስቲያን ሄደው ቅዳሴ የገቡት…በጸሎትን ጨምሮ ሌሎቹ ልጆች ግን ወደ ቤተክርስቲያን የሚወሰደውን ምግብና መጠጥ ሲያዘጋጁ ከቆዩ በኃላ አንድ ሰዓት ተኩል ሲል ዳቦ፤ እንጃራና ጠላውን በፒካፕ መኪና እስጭነው ቤተክርስቲያን በመውሰድ ለቄሶቹ የተዘጋጀውን ወደሰንበቴ ቤት አስገብተው ሌላውን ውጭ አስቀምጠው ቅዳሴው እስኪገባደድ መጠበቅ ጀመሩ ፡፡ልክ ቅዳሴው ተጠናቆ ሁሉም እንደወጣ አቶ ለሜቻና ወይዘሮ እልፌ ከቄሶቹ ጋር ወደሰንበቴ ቤት ቄሶቹንና ሌሎች ምዕመናንን ለማሰተናገድ ሲገቡ፡፡ በፀሎትና እና ለሊሴ ደግሞ ከሌሎች የሰፈር ወጣቶች ጋር በመሆን ቤተክርስቲያኑ የውጭ አጥር ጋር ተኮልኩለው ለሚገኙ የእኔ ቢጤዎችና፤ ምፅዋት ጠያቂዎች አንድ እንጀራ በወጥ ፤አንድ ጉማጅ ዳቦና አንድ ሀይ ላንድ ጠላ ለእያንዳንዱ እያደሉና ነፍስ ይማር እያስባሉ ካጠናቀቁ በኃላ ዕቃቸውን ሰብስበው እነአቶ ለሜቻ ከሰንበቴ ቤት እስኪወጡ መጠበቅ ጀመሩ…ሁሉ ነገር ከተጠናቀቀ በኃላ ቤተሰቡ ወደቤታቸው ከመመለሳቸው በፊት ቀጥታ ተያይዘው ወደበሬዱ መቃብር ነው የሄዱት፡፡የእሷ ምስል ያለበት ጥቁር ቲሸርት የለበሱት አስራ ምናምን ሰዎች የሀውልቱን ዙሪያ ገባ ከበው በዝምታ ሲፀልዩና አንዳንዱም ሲያነባ ከቀዩ በኃላ ሁሉም ቀስ በቀስ ስፍራውን እየለቀቁ ሄዱ…በመጨረሻ የቀሩት በፀሎት አቶ ለሜቻና ወ.ሮ እልፍነሽ ነበሩ፡፡
በፀሎት ይሄንን የልጅቷን ሀውልት ስታይ በጣም ትልቅ የሆነ ሀዘን ነው የተሰማት…‹‹በእሷ ምትክ..እኔ ነበርኩ እዚህ ስፍራ ከዚህ ሀውልት ስር መተኛት የሚገባኝ››ብላ ስታስበው እራሱ ዝግንን አላት…ልክ እንደሁል ጊዜውም የሌላን ሰው ህይወት ሰርቃ እየኖረች እንዳለች አይነት ስሜት ነው እተሰማት ያለው….የሚቀፍ አይነት ስሜት…›

አቶ ለሜቻ በዝምታ ሲያስተውሏት ስለቆዩ ያመማት መሰላቸው…‹‹ለማታውቃት ልጅ ይሄን ያህል ሀዘን ከየት የመጣ ነው?››በውስጣቸው ያብሰሰሉት ሀሳብ ነበር፡፡ በዝምታ ወደእሷ መጥተው ትከሻዋን በመያዝ…‹‹ልጄ በቃ እንሂድ ይበቃል››ሲሏት ከገባችበት ጥልቅ የመደንዘዝ ስሜት ባነነችና ቀና ብላ አየቻቸው…ትከሻዋን አቅፈው በፍቅር እየተመለከቷት ነው፡፡በሶስት ሜትር ርቀት ፈንጠር ብለው ወ.ሮ እልፍነሽ እያነቡ ይታዬታል…የአቶ ለሜቻን እጅ ያዘችና ‹‹አባዬ ና..››ብላ ወስዳ ከባለቤታቸው ጎን አቆመቻቸውና…ሁለቱም እግር ስር ድፍት ብላ አንድ አንድ እግራቸውን በመያዝ…‹‹አባዬ እማዬ እኔን ይቅር በሉኝ….በበሬዱ ይዣችኃለው ይቅር በሉኝ….ይቅር ካላላችሁኝ መኖር አልችልም….የእውነቴን ነው የምላችሁ ይቅርታችሁን ካላገኘው ሞታለው፡፡››ስትል ሁለቱም በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ…ምንም እየገባቸው አይደለም….‹‹ምን አጥፍታ ነው…?ምንስ ብታጠፋ ይቅርታ መጠየቂያው ቦታና ጊዜው ትክክል ነው?፡፡››በውስጣቸው የተፈጠረ ጥያቄ ነበር…ሁለቱም ግራና ቀኝ ትከሻዋን ይዘዘው ቀና ሊያደርጎት ሞከሩ ..ግን እልቻሉም፡፡
‹‹ይቅርታ ካላደረጋችሁልኝ አልነሳም››
‹‹ምን አጥፍተሸ ነው? ምንም አልገባንም እኮ››አቶ ለሜቻ ጠየቋት፡፡
‹‹አጭበርብሬችኃለው ..ዋሽቼያችኃለው..እኔ እናንተ ጋር የመጣሁት ከእንጀራ አባቴ ጠፍቼ አይደለም….››
‹‹እና ምን ሆነሽ ነው?፡፡››ወ.ሮ እልፍነሽ ጠየቁ፡፡
‹‹እኔ ማለት …የልጃችሁን ልብ በውስጤ ተሸክሜ የምዞር..በእሷ ምክንያት እየተነፈስኩ ያለው ልጅ ነኝ…..፡፡››
ሁለቱም የሚሰሙትን ለማመን አልቻሉም ..አቶ ለሜቻ ቀስ ብለው ትከሻዋን ይዘው አስነሷት…ፊቷን የተሻፋፈነችበትን ሻርፕ ቀስ ብለው ከላዮ ገፈፉና ጣሉት.. ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ ፊቷን ተመለከቱት‹‹አዎ እራሷ ነች››ትከሻዋን ያዙና ደረታቸው ላይ ለጠፏት…ግንባሯን፤ ጉንጮን፤ ፀጉሯን እየደጋገሙ ሳሟት‹‹….ልጄ አዎ አውቄው ነበር..አንቺ ወደቤቴ ያለምክንያት እንዳልመጣሽ ታውቆኝ ነበር….ከዛሬ ነገ ጥላኝ ትሄዳለች በሚል ስጋት ስሳቀቅ ነበር..አሁን ግን የራሴው ልጅ ነሽ የትም አትሄጂም..አዎ የራሴው ልጅ ነሽ››ተንሰፈሰፉላት….ፍፁም ያልጠበቀችውን ምላሽ ነው ያገኘችው፡፡
‹‹አዎ አባዬ ያንተው ልጅ ነኝ…ዘላለም ካአንተ መለየት አልችልም…እማዬ እኔ ልጅሽ ነኝ››ሶስቱም አንድ ላይ አርስ በርስ ተቃቅፈው ለበርካታ ደቂቃ ተላቀሱ ..በመከራ ነበር አካባቢውን የለቀቁት…ሁሉም የቤተክርስቲያኑ በራፍ ላይ ተሰብስበው እየጠበቋቸው ነበር….ግን በፊት ከነበሩት በተጨማሪ የበፀሎት እናትና አባት ልዩ አይነት ባስ መኪና አጠገብ ቆመው በራፍ ላይ ሲጠብቋቸው ነበር..ይሄ ደግሞ እነአቶ ለሜቻን ብቻ ሳይሆን በፀሎትንም ጭምር ነበር ያስደነቃት…እርስ በርስ ተቀራርበው ሰላምታ ከተለዋወጡ በኃላ ሁሉም በመኪና ውስጥ እንዲገቡ ተደረገ…በመኪና ውስጥ ጠቅላላ 25 የሚሆኑ ሰዎች ገቡ…ሹፌሩ መኪናውን ወደእነ አቶ ለሜቻ ቤት አቅጣጫ መንዳት ጀመረ…ቤታቸው ለመድረስ ግማሽ ኪሎ ሜትር ያህል ሲቀረው ግን ወደግራ ተጠመዘዘና አንድ ግቢው ውስጥ ገባ..ሁሉም ግራ ተጋባ….አቶ ኃይለልኡል መኪናው እንደቆመ በራፈ ከመከፈቱ በፊት ከተቀመጡበት ተነሱና መናገር ጀመሩ‹‹ ..ይቅርታ የማታውቁኝ ካላችሁ ኃይለልኡል እባላለሁ…የበፀሎት አባት ነኝ…በዛሬው ቀን በደም የተጣመሩ ሁለት ቤተሰቦች

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

28 Dec, 16:22


እዚህ ይገኛሉ ..የእኛና የአቶ ለሜቻ ቤተሰብ፡፡ይሄ ሁለት ቤተሰብ የተሳሰረው ዛሬ አብራን በሌለችው በበሬዱና አጠገባችን ባለችው በፀሎት ነው፡፡የእኔ ልጅ ዛሬ በህይወት ያለችው ከበሬዱ በተሰጣት ልብ ነው፡፡እዚህ እነአቶ ለሜቻ ቤት ለሟች ልጃቸው የሙት አመት መታሰቢያ ሲከበር በእኛ ቤት ግን ለልጃችን ንቅለ-ተከላ ተደርጎላት ዳግም የመኖር እድል ስላገኘች ድል ያለ የምስጋና ድግስ እናዘጋጅ ነበር ..ዘንድሮ ግን በፀሎት ውሳኔ እንደዛ ማድረግ አልቻልንም…እዚህ ግቢ አንድ ላይ መታሰቢያውንም ምስጋናውንም አብረን እንድናከብር ወስነናል..አሁን ሁላችንም ወርደን የተዘጋጀውን ዝግጅት እንታደም፡፡››የሚል ንግግር ካሰሙ በኃላ በራፉ ተከፈተ …
ዛሬ እየሆነ ያለው ነገር በጠቅላላ ምንም ያልገባቸው አቶ ለሜቻና ወ.ሮ እልፍነሽ አቶ ኃይለልኡልንና ባለቤታቸውን ተከትለው ከባስ ወረዱ፡፡ይሄንን ሰፈራ የሚገኘው በገዛ ቀበሌያቸውና በሰፈራቸው ስለሆነ በደንብ ያውቁታል፡፡ግቢው ንብረትነቱ የቀበሌው ሲሆን  ባለ5 ሺ ካሬ ግዙፍ ጊቢ ነው…ከመኪና ወርደው ሲመለከቱ ግቢው በሰዎች ታጭቆል ፡፡ ሰዎቹ ደግሞ አብዛኛው ጎዳና ተዳዳሪዎች፤የኔ ቢጤዎች የደከሙና የተጎዱ አቅመ ደካሞች…..ለአይን እንኳን ተቆጥሮ የማያልቅ የእንጀራ ክምር ..በበርሜል የተደረደረ ልዩ ልዩ የወጥ አይነት…ራቅ ብሎ ደግሞ በተንጠልጣይ ብረት ላይ የተደረደረ ጥሬ ስጋ እንደተራራ የተቆለለ የታሸገ ውሀ……

በሌላ ጎን ከአዳራሹ ፊት ለፊት ግዙፍ ፖስተር ይታያል…በፖስተሩ ላይ በቀኝ የበሬዱ ፎቶ በስተግራ ደግሞ የበፀሎት ፎቶ መሀከል ላይ የበሬዱ በፀሎት የምገባ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ይላል፡፡ብዛት ያላቸው ጋዜጠኛች ከወዲህ ወዲያ እየተዘዋወሩ ፎቶ ያነሳሉ ኢንተርቪው ያደርጋሉ፡፡
ማታ በሁለት ሰዓት ዜና ላይ በኢትዮጴያ ቴሌቭዝን የቀረበው ዜና የሚከተለው ነበር….
‹‹የታዋቂ የቢዝነስ ማን አቶ ሃይለልኡል ብቸኛ ልጅ ከጠፋችበት መገኘቷ ታወቀ…በፀሎት ከሶስት አመት በፊት ልቧ መስራት አቁሞ የነበረ ሲሆን በዛን ወቅት የመኪና አደጋ ደርሶባት አብራት ለህክምና ወደ ታይላንድ የሄደችው በሬዱ ለሜቻ ህይወቷ በማለፉ አባትዬው በሰጡት ፍቃድ መሰረት ልቧን ለበፀሎት በመለገሷ የልብ ንቅለ-ተከላ ሊደረግላትና ድና ወደሀገር ልትመለስ ችላለች…ባለፈው ወር የጠፋችው በፀሎት ኃይለልኡል የተገኘችው በእነዚሁ በአቃቂ ክፍለከተማ በሚኖሩት ልብ በለገሰቻት ልጅ ቤተሰቦች ቤት መሆኑ በጣም አነጋጋሪና አስደማሚ ታሪክ ሆነዋል፡፡
በዛሬው እለት የበሬዱ የሶስተኛ አመት የሙት አመት መታሰቢያ የነበረ ሲሆን በተመሳሳይ ሁኔታ ባለፉት ሁለት አመት እንደተደረገው በአቶ ኃይለልኡል ቤት የምስጋና ድግስ ሲደገስ የቆየ ቢሆንም..ዛሬ ግን ይሄ ቀርቶ አቶ ኃይለልኡልና ቤተሰባቸው በቤታቸው የደገሱትን ድግስ ሙሉ በሙሉ ሰርዘው በሞች በሬዱ ለሜቻ የትውልድ አካባቢ ለስሟ መታሰቢነት እንዲሆን ከዛሬ ጀምሮ በአካባቢው አቅም የሌላቸውና ችግረኞችን በቀን ሁለት ጊዜ የሚመግብ በሬዱ በፀሎት ምገባ ተቋምን ከፍተው ያስመረቁና በቦታውም ከ500 በላይ ሰዎችን በመመገብ ማስጀመራቸውን ማወቅ ተችሏል፡፡
በዚህም የሞች አባት የሆኑት አቶ ለሜቻ ስለሁኔታው ሲናገሩ‹‹በእውነት ልጄ ዛሬ ሞትን ድል ነስታ እንደተነሳች ነው የምቆጥረው..ልጄ በህይወት እያለች ለተቸገረ ሁሉ የምታዝን የዋህ ነበረች..አሁንም ከሞተች በኃላ ይሄው በስሟ ብዙዎች ጠግበው እንዲያድሩ ምክንያት ስለሆነች ኮርቼለሁ….ይሄንን እውን ያደረጉትን አቶ ኃይለልኡል እና ባለቤታቸውን አመሰግናለሁ….የእነሱ ልጅ የሆነችው በፀሎት ለእኔም ልጄ ነች….ከአሁን በኃላ በሬዱ ሞተች ብዬ አላዝንም…. ስትናፍቀኝ በፀሎትን አቅፌ አፅናናለሁ…ደግሞ እዚህ ስፍራ መጥቼ በስሟ ሰዎች ምግብ ቀምሰው ሲያድሩ ተመልክቼ ረካለው››በመላት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል…የሚል ነበር፡፡

ከድግሱ በኃላ አቶ ኃይለልኡልና ወ.ሮ ስንዱ ወደቤታቸው ሲሄዱ በፀሎት ግን ለሊሴን ተከትላ ወደእነሱ ቤት ነበር የሄደችው…በማግስቱ ግን ቤተሰቡ በአጠቃላይ ተሰብስበው ወደቦሌ ሄዱ ፡፡ሲደርሱ ሰለሞንም ነበር….ይህ ዝግጅትና ግንኙነት ለሁለቱም ቤተሰብ ልክ እንደቅልቅል ነው፡፡በዚህ ደግሞ ቁጥር አንድ የፈነጠዘችው በፀሎት ነች፡፡የእሷን ደስታና ፈንጠዝያ ሲከታተል የነበረው ሰለሞን ‹‹እሺ ይህቺን ልጅ ለማግባት ልጃችሁን ስጡኝ ብዬ ሽማግሌ ምልከው ለየትኛው ቤተሰብ ነው፡፡ብሎ እራሱን ጠየቀና ፈገግ አለ፡፡‹‹ግድ የለም እሷ ትስማማ እንጂ እኔስ ሁለት የሽማግሌ ቡድን ማቋቋም አያቅተኝም፡፡›› ሲል ለራሱ መልስ ሰጠ፡፡በተመሳሳይ ሁኔታ ፊራኦልም ከሰለሞን ጎን ተቀምጦ ፊት ለፊቱ በፀሎትን እየተመለከተ በውስጡ ‹‹እሺ አሁን የእህቴን ልብ ተሸክማ እህቴ ስለሆነች ልደሰት ወይስ. ፍቅሬን ተቀብላ ፍቅረኛዬ መሆን ስለማትችል ልከፋ?››በውስጡ የሚያመነዥገው ጥያቄ ነበር፡፡‹‹ፍቅሯ በዚሁ ቀጥሎ ከባሰብኝ ምንድነው የማደርገው?››በጣም ተጨነቀ፡፡

ተፈፀመ።

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

27 Dec, 18:04


ተናጋ…አቶ ኃይለ ልኡል ከተቀመጡበት ተነስተው ልጃቸውን በማቀፍ ልክ እንደባሌት ዳንስ በአየር ላይ ነው ያሽከረከሯት…..ለሊሴ እና ሰሎሞን ትዕይንቱን በተመስጦ እየተከታተሉ ነው፡፡

ይሄንን ትዕይንት ለሚከታተል ሰው ልጃቸው ለአለፈው አንድ ወር ብቻ ተለይታቸው የቆየች ሳይሆን በአራስነቷ ተሰርቃባቸው ከሀያ አመት በኃላ በተአምር የተገኘች አይነት ነው የሚመስለው፡፡
በነጋታው አምስቱም በቻርተር አውሮፕላን ተጭነው ወደአዲስ አበባ ተመሱ፡፡በፀሎት ግን ቀጥታ ወደቤቷ ሳይሆን ወደ ለሊሴ ቤት ነው መሄድ የፈለገችው..ውሳኔዋን ስትነግራቸው ሁለቱም ወላጆቾ ክፉኛ ተቃውመው ነበር፡፡
‹‹አባዬ እማዬ.ስሙኝ…እኔን ወደቤት ለመመለስ ባደረጋችሁት ነገር በጣም ኮርቼባችኃላው በጣም እንደምትወዱኝም አውቄለው…ግን አሁን መጀመሪያ ያበላሸሁትን ነገር ማስተካከል አለብኝ…ከአሁን ወዲህ እንድታውቁት ምፍልገው እናንተ ብቻ ሳትሆኑ እነሱም ወላጆቼ ናቸው….ከአሁን ወዲያ ብቸኛ ሳልሆን ወንድምና እህት አለኝ…ቦሌ ያለው የተንጣለለ ቪላ ብቻ ሳይሆን አቃቂ ያለውም ደሳሳ ቤት ቤቴ ነው፡፡እና የግድ አሁን ከለሊሴ ጋር ወደቤት መሄድ አለብኝ…ከዛ እስከአሁን የዋሸዋቸውን ናግሬ ይቅርታ ካገኘሁ በኃላ እመጣለሁ››
‹‹እንዴት አድርገሽ ነው የምትነግሪያቸው…?.››
‹‹አላውቅም… ብቻ የሆነ መንገድ ፈልጋለው››
‹‹ካልሽ እሺ ልጄ….ግን ታውቂያላሽ ከአምስት ቀን በኃላ ቤት ድግስ አለ…ንቅለ ተከላ የተደረገልሽ ቀን ነው..ያው እንደተለመደው ዘንድሮም እየተደገሰ ነው፡፡
‹‹አዎ አውቃለው…..የሚገርመው እነዛኞቹም ቤተሰቦቼ ጋር ድግስ አለ….በዛው በተመሳሳይ ቀን የሙት አመት መታሰቢያ ድግስ አለባቸው…የማ ለእኔ ልቧዋን የሰጠችኝ የበሬዱ የሙት መታሰቢያ….››ስትናገር የሚረግፈውን እንባዋን መገደብ አልቻለችም….እናትና አባቷም በሰሙት ነገር ሽምቅቅ ነው ያሉት….፡፡
‹‹እና በእለቱ የትኛውን ድግስ እንዳምሳተፍ ግራ ገብቶኛል..ግን አታስቡ ጥዋት እዚህ ቆይና ከሰዓት እናንተ ጋር መጥቼ የእኔን የምስጋና በአል አከብራለው….አዎ እንደዛ አደርጋለው››
በቃ የእኔ ቆንጆ …እንደሚሆን እንደርጋለን..አንቺ ምንም አትጨነቂ…አሁን ሹፌሩ እናንተን ቤታቸው ያድርሳችሁ እኛ ከሰለሞን ጋር በራይድ እንሄዳለን፡፡››አሉ አቶ ኃይልኡል

‹‹አረ አባዬ ግድ የለም እኛ በራይድ ብንሄድ ይሻላል፡፡››ለሊሴና በሬዱ ፈጠን ብለው አካባቢው ወደአለ ራይዱ ሄዱና .ውስጥ ገብተው ወደአቃቂ ሲያመሩ ሰለሞን እና ባልና ሚስቶቹን ሊቀበላቸው በመጣ መኪና ቦሌ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ሄዱ፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

27 Dec, 18:04


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያሰባት

ጨጓራው ሲለበልበው ይታወቀዋል…በቃ ውስጡ እየነደደ ነው…አሁን ምንም የማያውቀውን አዲስ ነገር አልነገረችውም…ምን እንዳበሳጨው ለራሱም አልገባውም….ሌላ ቢራ ከፈተና አንደቀደቀው…ስልኩን ደግመኛ አነሳና ደወለ…
‹‹ሄሎ ሶል ምነው?››
‹‹እባክሽ ስለሆነ ነገር ላማክርሽ ነበር… እኔ ክፍል ድረስ መምጣት ትችያለሽ?››
‹‹መቼ አሁን?››በመገረም ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ አሁን››
‹‹እሺ በቃ መጣሁ››
‹‹ስልኩን ዘጋና ከተቀመጠበት ተነሳ…መልሶ ቁጭ አለ‹‹ሰለሞን ምን እያደረክ ነው…?በዚህ ሰአት ስለምን ጉዳይነው የምታወራት.?›እራሱን በብስጭት ጠየቀ፡‹‹፡መልሼ ደውዬ በቃ ተይው ነገ ይደርሳል ማለት አለብኝ..››ወሰነና ስልኩን አነሳ….ቁጥሩን ከመጫኑ በፊት የመኝታ ቤቱ በራፍ ተቆረቆረ…..
ስልኩን ወደ አልጋው ወረወረና ተንደርድሮ ሄዶ ከፈተላት…በፀሎት ሮዝ ቀለም ያለው ስስና ልስልስ ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች… ፀጉሯን ወደላይ ጠቅልላ በሻሽ አንድ ላይ ጠፍራ አስራዋለች…ውብና መራኪ ሆና ነው እየመጣችው …ወደውስጥ ዘልቃ ገባች‹‹….ምነው በሰላም ነው…?አስደነገጥከኝ እኮ››
ፊት ለፊቷ ተገትሮ ቆመ….ግራ ገባት
‹‹ሶል ምን ሆነሀል…?.ምንድነው የምትነግረኝ?››ጉጉትና ፍራቻ በተቀየጠበት ስሜት ጠየቀችው፡፡

ተንደረደረና በሁለት እጆቹ አገጯን ግራና ቀኝ ክንዶን ይዞ ወደእሱ አስጠጋት… ከንፈሯ ላይ ተጣበቀ….በቀላሉ አለቀቃትም…ምን ይህል ደቂቃ እንደተሳሳሙ ሁለቱም አያቁም …ምን አልባት አንድ ደቂቃ ሊሆን ይችላል …ምን አልባትም ዘላለምም ሊሆን ይችላል….ግን የሁለቱም ልብ በየውስጣቸው ሲንፈራፈር ታውቋቸዋል…ሁለቱም በአየር ላይ የሚንሳፈፉበት ክንፍ እንዳበቀሉ አይነት ስሜት ተሰምቷቸዋል….ለሁለቱም ያልተጠበቀና ልዩ ክስተት ነበር….ሁለቱም ደግሞ ከገዛ ራሳቸው ጋር እንኳን ተነጋግረው ሳይወስኑ በነገሩ መሆን ተስማምተው በደስታ ፈንጥዘዋል፡፡በፀሎት አራት ተኩል ላይ ሰለሞን ክፍል የሄደች ስድስት ሰዓት ሲሆን ነበር ወደክፍሏ የተመለሰችው፡፡እሱንም ለሊሴ ምን ትለኛለች የሚል ይሉኝታ ቀፍድዷት እንጂ እዛው እቅፉ ውስጥ ሟሙታ እየቀለጠች ቢነጋ ደስ ይላት ነበር፡፡እሱም እንደዛው፡፡
በማግስቱ እስከአራት ሰዓት ከአልጋቸው መውረድ አልቻሉም ነበር፡፡
‹‹ልጁ ምን ይለናል ብዬ ነው እንጂ ቀኑን ሙሉ ከዚህ አልጋ ባልወርድ ደስ ይለኝ ነበር››ወ.ሮ ስንዱ ተናገሩ
‹‹ከአልጋው መውረድ ነው ወይስ ከእኔ እቅፍ መውጣት ነው ያስጠላሽ?››
‹‹አንተ ደግሞ…ለምን ታሳፍራኛለህ?››
‹‹ይሄውልሽ ነገ ወደአዲስአበባ እንመለስ የለ ..የልጃችንን የንቅለተከላ የተደረገላትን አመታዊ የመታሰቢያ በአል ድል አድርገን ከደገስን እና አንዳንድ ነገሮችን ካስተካከልን በኃላ..ለአንድ ወር ሲዊዘርላንድ እንሄዳለን፡፡›
‹ማ እና ማ?››
‹‹እኔ እና አንቺ..፡፡ያው አሁን ዳግመኛ እንደተጋባን እና ጉዞውንም ልክ እንደጫጉላ ሽርሽር ቁጠሪው››
‹‹በጣም አጓጓኸኝ ..ግን እኮ ይሄ ያለንበትም ስፍራ ከሲዊዘርላንድ አይተናነስም››
‹‹ገባኝ… ግን ራቅ ብዬ ካንቺ ጋር መጥፋት ነው የምፈልገው…››

‹‹ውይ የፍቅር ግርሻ እኮ መጥፎ ነገር ነው…ግን እንደምታየው ከልጄ ጋር ላለፈው አንድ ወር አልተገናኘሁም…እኔ ለሌላ አንድ ወር ከእሷ ውጭ ማሳለፍ አልችልም››
‹‹አንቺ ደግ…በቃ ይዘናት እንሄዳለን…ሶስታችን እንደቤተሰብ ከእንደገና አብርን በፍቅር እንቆማለት….››
‹‹እሱ ያስማማኛል፡፡››አሉና ከአልጋቸው ላይ ወረዱ…ተጣጥበውና ተዘጋጅተው ከክፍላቸው ሲወጡ አምስት  ሠዓት ሆኖ ነበር፡፡የሰለሞንን ክፍል ሲያንኳኩ አልነበረም…ደወሉለት
..በደቂቃዎች መጣላቸው፡፡
‹‹እንዴት ነበር አዳር?››
‹‹ዕድሜ ላንተ ሁሉ ነገር ውብና ማራኪ ነበር››አቶ ኃይለልኡል መለሱ፡፡
‹‹ጥሩ …አሁን እርግጠኛ ነኝ እርቦችኃላ?››
‹‹አዎ …የራበን ይመስለኛል›››
‹‹በሉ ተከተሉኝ …ቆንጆ ቁርስና ምሳ አንድ ላይ እንዲዘጋጅላችሁ አድርጌለው…››ብሎ ይዛቸው ሄደ..፡፡
በቀይ መንጣፍ ያሸበረቀ ግዙፍ የሞጃ ሳሎን የመሰለ ክፍል ውስጥ ነው ይዞቸው የገባው….ልክ አዲስ ሙሽሮች እንደሚስተናገዱበት አዳራሽ ውብና ልዩ ተደርጎ ዲኮር ተደርጓል….ግዙፉ ጠረጴዛና ጠረጴዛውን የከበቡት ወንበሮች ከቆዳ የተለበጡ ውብና ልዩ ናቸው…ልዩ ልዩ ባህላዊ ቅርሶች ግድግዳው ሞልተውታል፡፡እየመራ ወሰደና ወንበሩን እየሳበ ሁለቱንም አስቀመጣቸውና ..ከፊት ለፊታቸው ዞሮ ቆመ….
‹‹አቶ ኃይለልኡልና ወ.ሮ ስንዱ…ዛሬ የመጨረሻ ቀናችን ነው፡፡ማለቴ ከአሁን በኃላ ያለውን ቤታችሁ ተመልሳችሁ መደበኛ ስራችሁን እየሰራችሁ የምናከናውነው ይሆናል፡፡እስከአሁን ላለው ግን በእውነት እናንተ ለእኔ ትልቅ ውለታ ስለዋላችሁልኝ ላመሰግናችሁ እወዳለው..ይሄንን ስራ ከልጃችሁ ከበፀሎት ስቀበል በከፍተኛ ፍራቻና በወረደ የራስ መተማመን ነበር…እናንተ ግን ለልጃችሁ ስትሉ ጠንክራችሁ አጠነከራችሁኝ….በሶስት ወርና በአራት ወር እፈተዋላው ያላልኩትን በመሀከላችሁ ያለውን ውስብስብ ችግር በአንድ ወር አዚህ ደረጃ እንዲደርስ አድርጋችሁ አስደመማችሁኝ..ይህ አንድ ወር ለእኔ ታላቅ ትምህርት

ያገኘሁበት ነው..በሀገራችን የማህበራዊ ስሪትና ባህል የጋብቻ አማካሪ ብሎ ዘመናዊ አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ውጤታማ አይሆንም ተጠቃሚም አይኖርም ብዬ ተስፋ ቆርጬ ድርጅቴን ልዘጋ እያሰብኩ ባለሁበት ወቅት ነው የእናንተን ስራ ያገኘሁት…አሁን ግን ዘመናዊውን ሳይንስ በሀገራችን ተጫባች ሁኔታ አንፃር ቃኝተን በጥበብ ከተጠቀምነው የብዙ ውስብስብ ጋብቻዎችን ችግር ለመቅረፍ እንደሚቻልና ስራዬም ለማህበረሰቡ ጠቃሚ እንደሆነ እንድረዳ አድርጋችሁኛልና አመሰግናለው….በአጭር ቀናት ውስጥ ባሳያችሁት ውጤት ልጃችሁ ብቻ ሳትሆን እኔም ደስተኛ ነኝ፡፡
‹‹ልጄ ..አንተም እንደምትረዳው ወደእዚህ ጉዳይ ስንገባ ..አንተ ስለምትለው በእኔና ስንዱ መሀከል ስላለው ግንኙነት ማሻሻል ምንም አይነት ፍላጎትም ሆነ እምነት የለኝም ነበር…ልጄን ለማግኘት ስል ነበር ሳልወድ በግዴ የተስማማሁት…እያደረ ግን ሀሳቤን ሙሉ በሙሉ እንድቀይር አድርገሐኛል…ጋብቻዬ ጥሩ ባለመሆኑ ሕይወቴም ምን ያህል የተዛባ እና በጭንቀትና በሀዘን የተሞላ እንደሆነ እንዳስተውል አድርገሐኛል…እኔ ምን የህል አጥቼ ቤተሰቦቼንም ምን ያህል እንዳሳጣኋቸው እንዳስብና ወደቀልቤ እንድመለስ አድርገኀኛል..እኔ ነኝ አንተንም ሆነ ስንዱን ማመስገን አያለብኝ…በእውነት የእድሜ ልክ ባለውለታዬ ነህ…አንተ ከአሁን ወዲያ ልክ እንደልጄ ነህ….በማንኛውም ህይወት ጉዞህ እኔም ሆንኩ ቤተሰቦቼ ከጎንህ እንደሆን ልታውቅ ይገባል፡፡እርግጠኛ ነኝ ነገ ተነጋ ወዲያ አዲስአበባ እንደተመለስን ልጃችንም ወደቤቷ ትመለሰላች ብዬ ተስፋ አደርጋለው…እሷ ስትመለስ የተቀረውን ነገር እናወራለን፡፡››
ሰለሞን‹‹እሺ ጥሩ አሁን ስለራባችሁ …ከዚህ በላይ በወሬ አልያዛችው ››እጁን ሲያጨበጭብ ነጭ ዩኒፎርም የለበሰ አስተናጋጅ መጣ…..‹‹ምግብ ይቅረብ…መጀመሪያ የእጅ ውሀ አምጡ በላቸው››ሲል አዘዘው…ልጁ በቆመበት በራፍ ላይ ላሉት ልጆች ምልክት ሰጠው፡፡ውብ የሆነ ባህላዊ ነጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ወጣት ሴቶች ውብ የሆነ ወርቅ ቅብ ማስታጠቢያ በእጃቸው ይዘው መጡና….አንደኛዋ አቶ ኃይለልኡልን ሌለኛዋ ወ.ሮ ስንደን ለማስታጠብ ጎንበስ አሉ…ሁለቱም ታጥበው..ቀና ሲሉ በተመሳሳይ ቅፅበት ነው የአንደኛዋ ፊት ላይ አይናቸው ያረፈው….ከዛ በኃላ ያለው ነገር ለመግለፅ ሚያስቸግር ነበር..ምግብ አዳራሹ በወ.ሮ ስንዱ እልልታና ጩኸት

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

26 Dec, 18:52


‹‹ጥሩ ..እኔም ቢጃማ ነገር ብለብስ ደስ ይለኛል…››አሉና ሁለቱም ወደ የሻንጣቸው ሄዱ…ከ10 ደቂቃ በኃላ ሁለቱም በለሊት ልብሳቸው ለበሱና እጃቸውን ታጥበው የምግብ ጠረጴዛው ፊት ለፊት ተቀመጡ…ከአመታት በኃለ አንደኛው በሌለኛው እጅ በፍቅርና በሳቅ ታጅበው ራታቸውን በሉና ሻምፓኛቸውን ከፈቱ..ሁሉ ነገር ውብ ነበር…ልክ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተያዩ ነው የሆነው…የሁለቱም ልብ ምት እንደወጣት ልብ ነው ከቁጥጥር ውጭ የሆነው…ከአመታት በኃላ ነው የአንዳቸው ገላ ለሌለኛቸው ምላሽ በመስጠት እንደ እሳት ጎመራ መንቀልቀል የጀመረው….ከአስራ ምናምን አመት በኃላ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የአንደኛቸው ከንፈር ሌላኛቸው ላይ ያረፈው….የአንዳቸው እጅ የሌለኛቸውን ፓንት ወደታች አንሸራቶ ያወለቀው፡፡
///
በፀሎት እና ለሊሴ ዛሬ የመጨረሻ ቀን የወንጪ ቆይታቸው ነው፡፡በዚህም የተነሳ ቀኑን ሙሉ ላለፉት 15 ቀን ሲያስተናግዶቸው የነበሩትን ዘመዶቻቸውን በጠቅላላ እየዞሩ ተሰናብተው ጨለምለም ሲል ቀጥታ ሻንጣቸውን አንጠልጥለው የመጨረሻ አዳራቸውን በፓርክ ውስጥ ለማድረግ  እነአቶ ኃይለልኡል እንዳያዮቸው እየተጠነቀቁ ቀጥታ ሰለሞን ወደ ያዘላቸው ሎጅ ነው ያመሩት፡፡ክፍላቸው ከሰለሞን ክፍል ቀጥሎ የሚገኝ ሲሆን በለሁለት አልጋ ክፍልነው፡፡
ሰለሞን አቶ ኃይለልኡልና ባለቤታውን ራት ካበላና ወደ መኝታ ቤታቸው ካስገባቸው በኃላ ሌሊሴንና በፀሎትን እራት ለመጋበዝና ውቡን የመጨረሻውን ምሽት አብሮቸው ለማሳለፍ ይዞቸው ወጣ፡፡
ከሎጃቸው ፊትላፊት ባለው ጉብታ ላይ ቁጭ ብለው ሀይቁን ቁልቁል እያዩ እያወሩ ነው፡፡
‹‹በእውነት በሕይወቴ እንደዘንድሮ አስደማሚና አስደናቂ ነገር ገጥሞኝ አያውቅም›› በማለት የጫወታውን ርዕስ የመረጠው ሰለሞን ነበር፡፡
‹‹እንዴት ማለት?››አለችው ለሊሴ፡፡
‹‹እንዴ ..ይታይሽ አንድ ሴት ዝም ብላ በስልኬ በመደውል ስራ ልቀጥርህ እፈልጋለው
…አሁን  መቶ ሺብር  ልላክልህ  ፣  ስራውን  ስትጨርስ  5  ሚሊዬን  ብር  እንድታገኝ

አደርጋለው››ስትለኝ መጀመሪያ ቀልድ ነበር የመሰለኝ…ይገርምሻል የባንክ ቁጥሬን አንኳን ስልክላት ቆይ እስኪ ጉዷን አያለው ብዬ ነበር…እሷ ግን ብሩን ልካ አስደመመችኝ፡፡ወዲያው ከወላጆቾ ስር ጠፍታ በሀገር አቀፍ ደረጃ የምትፈለግ ልጅ ሆና አገኘኋት..በእውነት ያንን ሳውቅ በጣም ፈርቼ ነበር፣በዛ ተገርሜ ሳልጨርስ እንቺ ለማሪያም ድግስ በጠራሽኝ ጊዜ እናንተ ቤት ቁጭ ብላ አገኘኋት….ከዛ የሁሉ ነገር መነሻ አንቺ እንደሆንሽ ተረዳሁ…ምክንያቱም ስለእኔ ከአንቺ ባትሰማና ስልኬንም ካንቺ ዘንድ ባታገኝ ይሄን ሁሉ ታሪክ አምልጦኝ ነበር…ከዚህ ሁሉ የሚገርመው ደግሞ አሁን የምሰማው ነገር ነው…የአንቺ እህት ለእሷ ልቧን መለገሷ……ይገርምችኋላ ለቀናት እንዴት ያንን ቤት መረጠች …?ብዬ ስብሰለሰል ነበር..ለካ ከዛ ቤተሰብ ጋር ያላታ ትስስር ጥልቅና በደም የተገመደ ነበር›››
‹‹ታድዬ ደግሜ ደጋግሜ ነው ያስደመምኩህ ማለት ነው››አለችው በፀሎት
‹‹በጣም..እንጂ››
‹‹ምን እሱን ብቻ እኔንም ነው ስታስደምሚኝ የከረምሽው…በተለይ በቀደም ማንነትሽን ስትነግሪኝ….አብጄ እየቃዠው ነበር የመሰለኝ››አለች ለሊሴ፡፡
ለተወሰነ ጊዜ ዝም ተባባሉና በለሊሴ ጥያቄ ሌላ ርዕስ ተከፈተ
‹‹ሶል አሁን ቤተሰቦቾን የምታገኘው ከዚህ እንደተመለስን ነው እንዴ?››ስትል ያሳሰባትን ጥያቄ የጠየቀችው፡፡
‹‹ምነው ጠየቅሽኝ?››
‹‹እኔ እንጃ የእኛ ቤተሰብ በፀሎትን እንዲህ በቀላሉ ለማጣት ዝግጁ የሚሆኑ አይመስለኝም…በተለይ ስለማንናቷ እነ አባዬ ሲያውቁ በጣም ነው የሚከብዳቸው..››
‹‹በፀሎት ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደለሊሴ ተጠጋችና አቅፋ እየወዘወዘቻት‹‹‹እህቴ ስለምን ማጣት ነው የምታወሪው…?ከአሁን ወዲህ እኔ ሁለት ቤተሰብ ነው ያለኝ…አንድ ቀን እዚህ ቤት ካደርኩ በሚቀጥለው ቀን እዛ አድርለሁ….ከተቻለ እና ሁሉም ከተሳማማ ደግሞ ሁላችንም ተሰብስበን አንድ ቤት ውስጥ እንድንኖር ነው የምፈልገው…እርግጥ ይሄ በአንዴ አይሆንም አውቃለው…ግን ሁለቱም ቤተሰቦቼ ቀስ በቀስ በደንብ እንዲተዋወቁና እንዲግባቡ ካደረግኩ በኃላ አንድ ላይ ሰበስባቸዋለው…የቦሌው ቤታችን እኮ አርባ ምናምን

ክፍል ነው ያለው…ከዛ ውስጥ አስሩን አንኳን አንጠቀምበትም…..እና እህቴ ስለመለያየትና ስለማጣት ምንም አታስቢ››
ለሊሴም‹‹እህቴ  በጣም  ነው  የምወድሽ….ከእህቴ  ሀዘን  እንድፅናና  ስላደረግሺኝ አመሰግናለው፡፡››ብላ እሷም በተራዋ አቅፋ ጉንጮን ሳመቻት፡፡
‹‹በቃ በቃ…መላቀሱ ይብቃችሁ…ለማንኛውም በፀሎት ቤተሰቦችሽን የምታገኝው እንዴት እና መቼ እንደሆነ ነገ ጥዋት ቁርስ እየበላን እናወራለን፡፡››
‹‹ለምን አሁን አናወራም… ?››መለሰችለት
‹‹አይ አሁን መሽቷል…ተነሱ እናንተም ወደክፍላችሁ ግቡ››ብሎ ቀድሞ ተነሳ..ለሊሴና በፀሎትም ተከትለውት ተነሱ
ሰለሞን እነሱን ወደክፍላቸው አስገብቶ ወደገዛ ክፍሉ ገባና ቢጃማውን ቀይሮ ቀድሞ ያዘጋጀውን ቢራ ከፈፍቶ መጠጣት ጀመረ…ሁለት ጠርሙስ ካገባደደ በኃላ አስቴር ትዝ አለችው፡፡ ሞባይሉን አነሳና ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ ከምሽቱ አራት ሰዓት አልፏል…ደወለ….ከበርካታ ጥሪዎች በኃላ ተነሳ፡፡
‹‹ሄሎ ኪያ ተኝታሻል እንዴ ?ቀሰቀስኩሽ?››
አስቴር መለሰችለት‹‹አይ ወንድሜ ገና ለመተኛት እየተዘገጃጀው ነበር፡፡››
‹‹ደህና ነሽ?››
‹‹ደህና ነኝ…ምነው ቆየህ እኮ !አልጨረስክም አትመጣም እንዴ?››
‹‹ነገ ከሰዓት የምመጣ ይመስለኛል፡፡››
‹‹ጥሩ ነው…ልደውልልህ ነበር…››
‹‹ምነው በሰለም…፡፡››
‹‹አይ የፊታችን እሁድ የመስፍኔ ልደት ስለሆነ ሰርፕራይዝ ላደርገው አስቤላው…አንተም እንድትገኝ እፈልጋለሁ››
‹‹እንዴ እስከአሁን ወደመጣበት አልሄደም እንዴ?››

‹‹አይ ቀረ እኮ ….በፊትም ጥዬሽ የሄድኩት እየቆጨኝ ነው….ትዳሬን አክብሬ እዚሁ እየሰራሁ ከአንቺ ጋር ልጄን አሳድጋለው አለኝ››
‹‹እና መፋታቱን ሙሉ በሙሉ ተዋችሁት ማለት ነው?››
‹‹አንተ ደግሞ ስለምን መፋታት ነው የምታወራው….?በቃ ደህና እደር በሰላም ተመለስልኝ…መስፍኔ ከመኝታ ቤት እየጠራኝ ነው…››ብላ ስልኩን ዘጋችው፡፡
ጨጓራው ሲለበልበው ይታወቀዋል…በቃ ውስጡ እየነደደ ነው…አሁን ምንም የማያውቀውን አዲስ ነገር አልነገረችውም…ምን እንዳበሳጨው ለራሱም አልገባውም….ሌላ ቢራ ከፈተና አንደቀደቀው…ስልኩን ደግመኛ አነሳና ደወለ…

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

26 Dec, 18:52


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያስድስት

//
የባልና ሚስቶቹ የምክር አገልግሎት እንደቀጠለ ነው…ዛሬ ወንጪ ከከተሙ አስራአራተኛው ቀን ላይ ሲሆኑ በዚህ የ14 ቀን ጉዞቸው ከፍተኛ ለውጥ ላይ ደርሰዋል…
አሁን በዚህ ሰአት ከሁለቱም ፊት ለፊት ተቀምጦ ተራ በተራ እያያቸው እያተናገረ ነው..
‹‹ሰው ምን ጊዜም ከስህተት ጋር ሚኖር ፍጡር ነው፡፡ከሰው ጋር ስንኖር ስህተት ፈላጊ ከሆን በማንኛውም ሰው ላይ ከመጠን ያለፈ ስህተቶችን በቀላሉ ማግኘት እንችላለን…..ያ ደግሞ ከሰው ጋር አያኖረንም…አንዳችን የሌላችንን ክፍተት ለመድፈን መፈጠራችንን እስካላሰብን

ድረስ ምንም ነገር ሰላም ሊሆን አይችልም፡፡ደግሞ አስቡት የጋብቻ ዋናው አስፈላጊነትም ይህ ነው ፡፡ወንድ ልጅ በራሱ ፍፅም ወንድ ብቻ አይደለም..75 ፐርሰንት የወንድነት ሆርሞን ሲኖረው 25 ፐርሰንት ግን የሴት ሆርሞን በውስጡ ይዞል..ሴቷም በተመሳሳይ 75 ፐርሰንት የሴት ሆርሞን ሲኖራት 25 ፐርሰንት የወንድ ሆርሞን ይዛለች…አያችሁ የተፈጥሮን ረቅቂነት ..ሁለቱ ሲጣመሩ ...አንድ ሙሉ ወንድና አንድ ሙሉ ሴት ይገኛል ማለት ነው፡፡ለመዋሀድ ደግሞ ፍቅር ዋናው አገኛኝ መሰላል ነው፡፡››
‹‹ግልፅ ነኝ አይደል?››
‹‹አዎ .. ቀጥል››ሲሉ የተናገሩት አቶ ኃይለ ልኡል ናቸው
ሰለሞን ንግሩን ቀጠለ‹‹በአንድ መንደር ውስጥ ትኖር የነበረች ሴት ሶስት ሽማግሌዎች ከቤቷ አካባቢ ከውጭ በፀጥታ ተቀምጠው ተመለከተች። ሴትዬዎም ከቤቷ ወጣችና ወደሽማግሌዎቹ ቀርባ" እናንተን ከዚህ በፊት አይቼያችሁ አላውቅም።ግን እዚህ በደጃፌ ለረጅም ጊዜ ተቀምጣችኋል። እርግጠኛ ነኝ እርቦችኋል። እባካችሁ ወደቤቴ ዘልቃችሁ ግብና ቤት ያፈራውን ቅመሱ››አለቻቸው።
ከመካከላቸው አንደኛው ሽማግሌ‹‹የቤቱ አባወራ በቤት አለ?››ሲሉ ጠየቋት። እሷም መለሰች‹‹አይ የለም››ስትል መለሰች።
ሽማግሌውም"ስለዚህ ወደቤት መግባት አንችልም።"ሲሉ መለሱላት።
ሴትዬዋም ወደውስጥ ተመልሳ ገባች ።መሸቶ ባሏ እንደመጣ ስለሰዎቹ ነገረችው። ባሏም
‹‹በይ አሁን ሂጂና ወደውስጥ እንዲገብ ጋብዢያቸው››አላት።
እሷም ወጣችና ወደውስጥ እንዲገብ በድጋሚ ጠየቀቻቸው‹‹ባለቤቴ ቤት ነው ያለው..ወደውስጥ እንድትገብም ጋብዛችኋል...እባካችሁ ወደ ውስጥ ዝለቁና የሆነ ነገር ቅመሱ››
‹‹እኛ በአንድ ላይ ወደውስጥ መግባት አንችልም››አሏት
‹‹ለምን ?››ግራ ገብቷት ጠየቀች።

ከሽማግሌዎቹ አንድ መመለስ ጀመረ "ይሄውልሽ ..."ወደአንደኛው ጓደኛው በጣቱ እየጠቆመ "..እሱ አቶ ሀብት ነው ወደቤትሽ ከገባ ቤትሽ በሀብት ለዘላለም እንደተሞላ ይዘልቃል።...ይሄኛው ደግሞ አቶ ስኬት ነው ከአንቺ ጋር ተከትሎ ወደውስጥ የሚገባው እሱ ከሆነ ቤትሽ በስኬት ይሞላል።እኔ ደግሞ አያ ፍቅር እባላለሁ። እኔ ከገባሁ ደግሞ በዘመንሽ ሁሉ በቤትሽ ፍቅር ሞልቶ ይፈሳል።ክፍቱ ግን አስቀድመን እንደነገርንሽ ሶስታችንም በአንድ ላይ ወደውስጥ መግባት አንችልም። ስለዚህ ወደቤትሽ ተመለሺና ከባልሽ ጋር በመማከር ከሶስታችን ማንኛችንን ወደውስጥ እንደምታስገብ ወስኑ "በማለት አብራሩላት።
እሷም እንደተባለችው ወደውስጥ ተመልሳ የሰማችውን ሁሉ ለባሏ አስረዳችው። ባሏ በሰማው ነገር ፈነጠዘ‹‹አቶ ሀብትን እንጋብዘው ፤ይግባና ቤታችን በሀብት ይሙላው፤ከእሱ የሚበልጥ ምን አለ?።››አላት።
ሚስትዬው ግን ውሳኔውን ተቃወመች"ለምን ስኬትን አንጋብዘውም፤ከሀብት ይልቅ ስኬት ነው የሚጠቅመን"አለች። እቤት ውስጥ የነበረች የልጃቸው ሚስት ወሬቸውን ስታዳምጥ ስለነበረ ወደእነሱ ቀረበችና‹‹ለምን ፍቅርን አንጋብዘውም..ከሁሉም በላይ በቤታችን ፍቅር ቢሞላ ይሻላል››የሚል ሀሳብ አቀረበች።
ጥቂት ካሠላሠሉ እና ከተከራከሩ በኃላ ባልና ሚስቶቹም በሀሳቧ ተስማሙ ፤ሚስትም ተመልሳ ወጣችና ወደእንግዶቹ ሄደች። ‹‹ከመካከላችው ፍቅርን ለመጋበዝ ወስነናል፤አያ ፍቅር እባክህ ተነስና ወደቤታችን ዘልቀህ ግባ...የተዘጋጀውን መአድም አብረኸን ተቋደስ..ሌሎቻችሁ ስላልመረጥናችሁ ይቅርታ "ስትል ተናገረች።
ፍቅር ተነሳና ወደቤት ለመግባት መንቀሳቀስ ሲጀምር ስኬትና ሀብትም ከተቀመጡበት ተነስተው ከኃላው ተከተሉት። ሴትዬዋ ግራ ገባት ‹‹አብረን መግባት አንችልም.. ከመሀላችን አንዳችንን ምረጪ አላላችሁኝም ነበር እንዴ?"ስትል ጠየቀች።
ከመሀከላቸው አንደኛው ማስረዳት ጀመረ‹‹ልጄ ስትመርጪ ስኬትን ወይም ሀብትን መርጠሽ ቢሆን ኖሮ አንዳችን ብቻ ነበር ወደቤትሽ የምንገባው።አሁን ግን የመረጥሽው ፍቅርን ነው። እኛ ደግሞ ፍቅር በገባበት ሁሉ ተከትለን መግባት ግዴታችን ነው።እኛም እራሳችን የፍቅር ምርኮኞች ነን።በዚህ ምክንያት ሶስታችንም የግድ ወደቤትሽ እንገባለን። ካዘጋጀሽውም መአድ እንቋደሳለን።ቤትሽንም ዘላለም በሚትረፈረፍ ሀብት ፤ስኬትና ፍቅር እንሞላዋለን።"አሏት። እሷም በደስታ እየፈነጠዘች ወደቤቷ ይዛቸው ገባች።

አያችሁ እናነት ሀብታም ናችሁ ስኬታማም ናችሁ…አሁን እየጣርን ያለነው ከመሀከሏችሁ ሾልኮ ተሰዶ ነበረውን ዋናውን ፍቅር ለመመለስ ነው..ፍቅር ከተመለሰ ሁሉ ነገር ሙሉ ይሆናል››
ዛሬ በዚህ በሰጠኋችሁ ምሳሌ በመሀከላችሁ፤በቤታችሁና በአካባቢያችሁ ፍቅር ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ እያሰላሰላችሁ እንድታድሩ እፈልጋለው…ነገ እዚህ የምናሳልፍበት የመጨረሻ ቀናችን ነው…ተነገ ወዲያ ወደአዲስ አበባ እንመለሳለን….አሁን ዋናውን ነገር አጠናቀናል…በቀጣይ ቤታችሁ ሆናችሁ ልጃችሁም ተመልሳ ስራችሁን እየሰራች የምናደርገው ይሆናል…››በማለት የእለቱን ፕሮግራም አገባደደ
ባልና ሚስቶቹ ክፍላቸው ተያይዘው ሲገቡ የጠበቃቸው የተለየ ነገር ነበር፡፡የመኝታ ክፍላቸውን ግራና ቀኝ ግድግዳ ታኮ የነበረው ሁለት አልጋ ሁለቱም ወደመሀል ተስቦና አንድ ላይ እንዲገጥም ተደርጎ አንድ አልጋ ሆኗል….ግዙፉ የተዋሀደው አልጋ በነጭ ውብ አልጋ ልብስ ተሸፍኗል.. አልጋ ልብሱ መሀል ላይ በልዩ ዲዛይን የተሰራ ባለቀይ ቀለም የልብ ቅርፅ ይታያል..ሙሉ ወለሉ በቀይ ፅጌረዳ አበባ ከመሞላቱም በተጫማሪ ባለቆርቆሮ ልዩ ሻማ በመሀከል መሀከል ጣልቃ በማስገባት የተለያ ቀለም ያው ብርሀን እየረጩ ነው፡፡አደኛውን ግድግዳ ተጠግቶ በሚታይ ጠረጴዛ ላይ ሻማፓኝ መጠጥ ከውብ ብርጭቆዎች ጋር ይታያል…በሚገፋ ተሸከርካሪ ጠረጴዛ ላይ አስጎምዢ ምግቦች ተደርድረዋል…
ሁለቱም ባልና ሚስት በመጀመሪያ የተሳሳተ ክፍል የገቡ ነበር የመሰላቸው….የገዛ ሻንጣቸውንና ሌሎች የግል እቃዎችን ሲያዩ ተረጋጉና ወደውስጥ ዘልቀው በራፉን ዘጉት፡፡
‹‹ስንድ ይሄ ጉደኛ ልጅ የ20 አመት ጎረምሳ አደረገን እኮ..››
ወ.ሮ ስንዱ እንባቸው እየረገፈ ተናገሩ‹‹ያበቃልኝ መስሎኝ ነበር….እድሜ ለልጄ ይሄው ዳግመኛ ልጃገረድ ሆንኩ››
‹‹እንዴ ስንድ ዛሬ ሳቅና ፈንጠዝያ ነው እንጂ የምን ለቅሶ?››አሉን እጃቸውን ወደባለቤታቸው ጉንጮች በመላክ እንባቸውን ጠረጉላቸውና አቅፈው ሳሞቸው….‹‹በይ ዛሬ ምሽቱ የእኛ መሰለኝ..እንቀመጥ››
‹‹መጀመሪያ ልብሴን ልቀይርና ቀለል ያለ ልብስ ልልበስ…እስከዛ እንተ ቁጭ በል››

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

25 Dec, 16:21


‹‹አሁን ክፍላቸው አረፍ ብለዋል….ለሚቀጥሉት ሁለት ሶስት ሰዓት እረፍት ነኝ….›› በፀሎት‹‹እና ታዲያ ወደፍል ውሀ ለምን አንሄድም?››የሚል ሀሳብ አቀረበች፡፡ ‹‹በጣም የተቀደሰ ሀስብ ነው››ቀድሞ የተነሳ ሰለሞን ነው..ሴቶቹም ተከተሉት፡፡እያተሳሳቁና እየተጫወቱ በእግሩ ጉዞ እስካይ ብሪጁ ጋር ደረሱ…..
ለሊሴና ሰለሞን ቀድመው የብረት ተንጠልጣ ድልድዩ ላይ ቢወጡም በፀሎት ግን ልትደፍር አልቻለችም..‹‹ምነው ፈረራሽ እንዴ?››
‹‹ለምን አልፈራም…እየው እስኪ ቁልቁል በሆነ ተአምር ቢበጠስስ?››
‹‹አንቺ ደግሞ በለሊት ሞተር የምታበሪ ጀግና እዚህ ድልድይ ላይ መውጣት ትፈሪያለሽ?››ለሊሴ በትዝብት ጠየቀቻት፡፡
ወደተሸፈነ ፊቷ እያመለከተች‹‹በለሊት ሞተር መንዳቴ ያመጣብኝን ጣጣ አትመለከቺም?››አለቻት፡፡
ወደኃላ ተመለሰና እጇን ይዞ እየጎተተ አስወጣት ….ተጠመጠመችበትና እጆቾን በወገቡ ዙሪያ አዙራ ተለጠፈችበት፡፡ልክ የመጀመሪያ ልጁን ዳዴ እንደሚያስተምር አባት ቀስ ብሎ እየጎተተ ይዞት ይጓዝ ጀመረ…እንደምንም ድልድዩን ተሻግራ እግሮቹ መሬት ሲረግጡ እፎይ አለችና በረጅሙ ተነፈሰች….ሁለቱም ተሳሳቁባት፡፡
‹‹ተፈጥሮ እኮ ምትገርም ነች ..ከጎንና ጎን ሁለት መለስተኛ ኩሬዎች አሉ…ሁለቱም በተለያየ አይነት ቀለም ባላቸው ውሀዎች ተሞልተዋል ..አንደኛው ፈዛዛ አረንጓዴ አይነት ቀለም አለው…ውሀው በጭቃ የተሞላ እና ሙቅ ነው…በህመም የሚሰቃዩና ፈውስ ሚፈልጉ ሰዎች ውስጡ ይገቡና ሰውነታቸውን በጭቃ በመለቅለቅ ይዘፈዘፋሉ…ከዛ ቀላ ያለ ድፍርስ መሳይ ኩሬ ውስጥ ገብተው ይዘፈዘፋሉ..ደግሞ ከተራራው ላይ እየተንፏፏ የሚፈልቅና ውብና ንፅህ ሙቅ ፏፏቴ አለ…በአካባቢው ባለው ወንዝ አጎንብሰው ከወንዙ ሚጠጡ ፈረሶችና ከብቶች ዙሪያውን ያለው ጫካ ከዛፍ ዛፍ ሚዘሉ ዝንጀሮዎች ጦጣዎችና ጉሬዛዎች አካባቢውን በውብ ዜማ የሚያደምቁ የወፍ ዝርያዎች ሁሉም ድንቅ ነው፡፡
ጉብኝታቸውን አገባደው ሰለሞንም ወደሎጁ በፀሎትና ለሊሴም ወደአረፉበት የዘመድ ቤት ጉዞ ጀመሩ…ግን ማረፊያቸው ከመደረሳቸው በፊት ከተለያዩ 20 ደቂቃ በኃላ ነበር ሰለሞን

ለበፀሎት የደወለላት..ስልኩን አነሳችና ከለሊሴ ወደኃላ ቀረት ብላ አዋራችው…ጨርሳ እንደተመለሰች ወዲያው ነበር ለሊሴ በነገር የተቀበለቻት፡፡
‹‹እኔ ይሄ ሰውዬ ምኑም አላማረኝም?››
‹‹የትኛው ሰውዬ?››በፀሎት ያልገባ መስላ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ሀለቃዬ ነዋ››
‹‹ደግሞ ምን አደረገ?››
‹‹አንዴ …እዚህ ያለንበተ ድረስ መጣ …አብረን ረጅም ሰዓት አሳለፍን ..አሁን ከተለያየን ገና አንድ ሰዓት እንኳን አልሞላም …ግን ይሄው ደወለልሽ››
‹‹እና?››
‹‹እናማ …አፍቅሮሻል እያልኩሽ ነው…››
‹‹ጥሩ ነዋ››
ለሊሴ ያልጠበቀችውን መልስ ስላገኘች ይበልጥ ተገረመችባት‹‹ጥሩማ ጥሩ ነው…ግን አንቺስ ታፈቅሪዋለሽ ወይ…?››
‹‹አፈቅረዋለው እንዴ ?››እራሷን ጠየቀች..ቁርጥ ያለ መልስ ለማግኘት አልቻለችም››
ለሊሴ መልስ ስታጣ ንግግሯን ቀጠለች..‹‹ቅድም እንደነገርኩሽ ሁለታችሁም አብራችሁ ብትሆኑ እንደእኔ ደስተኛ የሚሆን ሰው የለም…ሀለቃዬ በጣም የማከብረው ሰው ነው፡፡ አንቺም የምወድሽ እህቴ ነሽ፡፡ የሁለታችሁ አንድ ላይ መሆን ልዩ ነው..ግን አንቺ ፍላጎት ማይኖርሽ ከሆነ ከአሁኑ ነው ግንኙነታችሁን ማቆም ያለብሽ…ምከንያም ከዚህ በላይ ስር እየሰደደ ሄዶ እሱ ሙሉ በሙሉ ፍቅር ውስጥ ከተዘፈቀ በኃላ አይሆንም ዞር በል ብትይው…በእኔ ስራ ላይም ከፍተኛ ተፅእኖ ይፈጥርብኛል..ታውቂያለሽ ስራውን በስንት መከራ ነው ያገኘሁት..በእናንተ ጉዳይ እንዲበላሽብኝ አልፈልግም፡፡››
በፀሎት በፀጥታ አሰበች..ሆነም ቀረ በቅርብ ቀን ሁሉ ነገር ፍርጥርጥ ማለቱ አይቀርም
..ታዲያ ለምን ልጅቷን አጨናንቃታለሁ? ስትለ አሰበችና ወሰነች..ወደማረፊያችው ሊደርሱ

የ10ደ ደቂቃ መንገድ ነበር ሚቀራቸው…‹‹ነይ እስኪ እህቴ ወደቤት ከመግባታችን በፊት እዚህ ዛፍ ስር ትንሽ እንቀመጥ…››
‹‹ምነው ቤት ብንገባ አይሻልም ..?ደርሰናል እኮ››
‹‹ገብቶኛል…የምነግርሽ ነገር ስላለነው፡፡››
‹‹እሺ›› አለችና ከመንገድ ዳር ወዳለች ዛፍ ሄዱና ጎን ለጎን ሳር ላይ ተቀመጡ….
‹‹ለሊሴ እኔ ሰለሞንን የማውቀው በቀደም ለማሪያም ቀን ሲመጣ አይደለም.››
‹‹ምን ማለት ነው?››
‹‹ማለቴ እርግጥ በአካል ፊት ለፊት የተገናኘነው የዛን ቀን ነው…..ግን ከዛን በፊትም  እንደዋወል ነበር››
‹‹የምታወሪው ምንም እየገባኝ አይደለም፡፡››
‹‹ትዝ ይልሽ ከሆነ ስራ የጀመርሽ ሰሞን ስለ እሱ ጥሩነት ደጋግመሽ ታወሪኝ ነበር..ለሆነ ስራ ስለምፈልገው ስልኩን ከአንቺ ሞባይል ወሰድኩና ደወልኩለት …ተነጋግረን ትስማማንና ቀጠርኩት፡፡››
‹‹ቀጠርኩት››
‹‹አዎ ቢሾፍቱ ለ15 ቀን የቆየበት ስራና አሁንም እዚህ የመጣበት ስራ የእኔ ስራ ነው….እርግጥ እዚህ እንደሚመጣ እኔም ከአንቺ እኩል ነው ያወቅኩት ቢሆንም የእኔን ወላጆች ይዞ ነው የመጣው››
ለሊሴ ከመገረምና ከመደንጧ የተነሳ ከተቀመጠችበት ተነሳች፣ጭንቅላቷን ያዘች፡፡‹‹እህቴ ቁጭ በይ ዋናውን ነገር አልነገርኩሽም››
‹‹ከዚህም በላይም ዋና ነገር አለ?››
‹‹አዎ ቁጭ በይ›› ቁጭ አለች…

‹‹እኔ ማለት….››
‹‹አንቺ ማለት?››
እጇን ያዘችና ጎትታ ደረቷ ላይ አስቀመጠች….‹‹ይሰማሻል?››
‹‹ምኑ?››
‹‹የልብ ምቴ››
‹‹አዎ ይሰማኛል….አመመሽ እንዴ? በፍጥነት ነው የሚመታው››
‹‹አይ ደህና ነኝ…እንዴት እደምነግርሽ ስለጨነቀኝ ነው ..ምን መሰለሽ…ይሄ አሁን ውስጤ የሚመታው ልብ የእህትሽ ልብ ነው፡፡››
‹‹አዎ፣ እሱማ አውቃለው የእህቴ ልብ ነው››
‹‹ማለቴ የበሬዱ ልብ ነው….እኔ ይሄንን ልብ ከእህትሽ ነው የተለገሰኝ››
‹‹ወይኔ  በፈጣሪ..ምን  እያልሽኝ  ነው….?አንቺ  ማለት….ወይኔ  በፈጣሪ…ለምን  ዋሸሺን
…..አሁን አባዬ ሲሰማ ምን ይላል….?››
በፀሎት ለሊሴን ለማረጋጋትና ሙሉን ታሪኳንና እቅዷን ለማስረዳት ከአንድ ሰዓት በላይ ነው የፈጀባት…ሁሉ ነገር ተስተካክሎና በመሀከላቸው የነበረው የተካረረ ስሜት ረግቦና ሰላም ወርዶ ወደቤት ተቃቅፈው ሲመለሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት አልፎ ነበር…
ወደመጨረሻው እየተንደረደርን ነው

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

25 Dec, 16:21


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያአምስት

ሰለሞንና የበፀሎት ቤተሰቦችን አብዛኛውን ጊዜያቸውን አካባቢውን ያለውን እያንዳንዱን መስህብ በመጎብኘት ነው የሚያሳልፉት….እያንዳንዱ ውይይትና ምክረ-ሀሳብም በመዝናናት ውስጥ ሆነው የሆነ ቦታ አረፍ ሲሉ ወይም ብና ለመጠጣት የሆነ ካፌ ሲቀመጡ በውይይትና በጫወታ መልክ የሚሰጥ ስለሆነ እንደ ቢሾፍቱ አስጫቂና ጭንቅላት የሚይዝ አይነት አልነበረም፡፡
በወንጪ ኢኮ ቱሪዝማ ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት እና ለጉብኝት ዝግጁ ከሆኑት ዋና ዋና አይን ሳቢና ቀልብ አስደንጋጭ የቱሪስት መስህቦች ውስጥ ጥቂቶቹ
ጎሮ በሚባለው ስፍራ የተገነባው ጎሮ ካልቸራል ሴንተር የወንጪ ኢኮቱሪዘም ፓርክ አንዱ መገለጫና ውበት ነው፡፡ በህንፃው ላይ ባህላዊ ምግቦች የሚገኙበት ውብ የሆነ ሬስቶራንት..ባህላዊ የሆኑ የእጅ ስራ ውጤቶች የሚሸጥባቸው ሱቆች…የተለያዩ ዝግጅቶችን ለማዘጋጀት የሚያገለግል እስከ 3መቶ ሰዎች ማስተናገድ የሚችል ውብ የሆነ አምፊ ትያትር ከአካባቢው ከሚገኙ አገልግሎቶች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ እና አካባቢው ላይ ሆኖ ቁልቁል ወደታች ሀይቁንና ከማዶው ያለውን ተራራ ሲያዩት ልብን ስውር የሚያደርግ የተለየ አይነት አስደማሚ እይታ አለው፡፡
ከጎሮ 2.3 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ነዲ ካልቸራል ሴንተር ደግሞ ሌላው ልብ ሰዋሪ ቦታ ነው፡፡ነዲ ከስሙም መረዳት እንደሚቻለው በአካባቢው የሚመረት የወንጪ ማር እና የማር ውጤቶች እንደብርዝና ጠጅን ጨምሮ መሸጫ እንዲሆን ታስቦ የተገነባ ህንጻ ነው…የህንፃው ጠቅላላ ዲዛይን አገልግሎቱን ታሳቢ ተደርጎ የተሰራ ስለሆነ ውብ ነው፡፡በማር እንጀራ ቅርፅ የተሰራ ሁለት ሶስት ጓደኛሞች ተቀምጠው ቁልቁል ሚታየውን ውብ እይታ ዘና እያሉ ወሬያቸውን የሚጠረቁበት ውብ ስፍራ አለ፡፡

ሙለታ ወንጪ ሬስቶራንት ሌላው በስፍራው የሚገኝ ውብ ቦታ ነው …በዚህ ስፍራ ሬስቶራንቶችና ሱቆች የፈረስ ማስዋቢያና ባህላዊ እቃዎች የሚሸጡበት ሱቆች ሲኖሩ ኩኪስ ብስኩት የመሳሰሉትም ቀላል ምግቦችን ማግኘት ይቻላል ፡፡
ነዲ ሰስፔንድድ የመስታወት ቴራስ ሌላው በአካባቢው ያለ ውብ ህንፃ ነው፡፡ይህ የመስታወት ወለል ግማሽ ክብ አይነት ቅርፅ ሲኖረው በሶስት ድርብርብ ተደርጎ የተሰራና እላዩ ላይ ወጥታው በመስታወቱ አሻግረው ወደታች ሲመለከቱ ከስር የሚታየው አስፈሪ ገደል መሳይ ግን በአረንጓዴ ሳርና ተክሎች የተሸፈና ውብ ስፍራ በማዶ የሚገኘው የጠራ ሀይቅ …በቃ አስፈሪ ግን ደግሞ አስደሳች እይታ ነው፡፡ይህ የመስታወት ቴራስ በአንድ ካሬ ሜትር ላይ 400 ኪ.ግራማ የመሸከም አቅም እንዳለው ቢታወቅም በርከት ያለ ሰው ከወጣበት ግን ከአሁን አሁን መስታወቱ ተፈርክሶ ሾልከን ወደገደሉ ብንንከባለልስ? የሚል የፍራቻ ስሜት ሰቅዞ የሚያሲዝ አይነት ነው፡፡ከዚህ አስደማሚ የመስታወት ቴራስ ጎን አምፊትያትር ያለ ሲሆን በተያያዥነትም…ልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚሰጥ ካፍቴሪያ አለ፡፡ከዚህ ስፍራ ቀጥታ ወደሎጅ የሚወስድ የመኪና መንገድ ከላይ የመስታወት ቴራሱ ላይ ሆነው ከስር ማየት ይቻላል፡፡
ከዛ ደግሞ የተፈጥሮ ፍል ውሀ ያለበት በደን የተሸፈነ ሲሆን በአካባቢው ጉሬዛ ፤ጦጣ አእዋፍት ፤አምቦ ውሀ የተፈጥሮ ፏፏቴ ይገኛል …ጎን ለጎን ያሉ ሙቅና ቀዝቃዛ ኩሬ የኬብል ድልድይ ፤ወንዝ ..ብዙ ብዙ አስደማሚ ተፈጥሯዊ ነገር ይገኛል፡፡የነዲ መዝነኛ ስፍራን እና የተፈጥሮ ፍል ውሀን የሚያገናኝ በብረት የተሰራ እስካይ ብሪጅ አለ፡፡ብሪጁ 72 ሜትር ርዝመትና ኖሮት ሀምሳ ሜትር ከፍታ እንዲኖረው ተደርጎ የተሰራ አስፈሪ ግን ደግሞ የራሱ የሆነ ውበትና የተለየ ስሜት የሚያጭር ልዩ ድልድይ ነው፡፡
እነዚህን ሁሉ ባለፈው አንድ ሰምንት ውስጥ የጎበኞቸው ቦታዎች ናቸው፡፡ በስምንተኛው ቀን ከቀኑ 9ሰዓት አካባቢ ለበፀሎት ደወለላት
‹‹ሄሎ..እንዴት ነሽ?››
‹‹አለሁልህ…ገነት ገብቼለሁ››
‹‹ወደድሽው ማለት ነው››

‹‹እንዴ ትቀልዳለህ እንዴ …?አካባቢው እኮ እንኳን እንደእኔ አፍጥጠው የሚያዩ ሁለት አይኖች ላሉት ሰው ይቅርና አይነ-ስውር ቢመጣበት እንኳን ውበቱ በሽታ ሳይቀር ይታወቀዋል፡፡››
‹‹ዋው ድንቅ አገላለፅ ነው….በጣም ማርኮሻል ማለት ነው…እኔንም አንድ ቀን ወስደሽ እንደምታስጎበኚኝ ትስፋ አለኝ፡፡››
‹‹በደንብ እንጂ…ለዛውም በቅርብ ነዋ››
‹‹አሁን የት ነሽ…?ላለፉት አንድ ሰዓት ለሊሴ ጋር በሳይክል አካባቢውን ስናካልል ነበር.. አሁን ድክም ብለን ነዲ ካልቸራል ሴንተር የሚባለው ስፍራ ላይ ነን ፡፡
‹‹ምነው…ጠጅ እየጠጣችሁ ነው እንዴ?››ሲል ጠየቃት
‹‹አይ ትኩስ ወለላ ማር እየበላን››
‹‹በቃ ..ሰዓታችሁን አልውሰድባችሁ…..ዘና በሉ››
‹‹እሺ ቸው…ለሊሴ ሀይ እያለችህ ነው፡፡››
‹‹ሀይ በይልኝ‹‹ስልኩ ተዘጋ፡፡
‹‹አንቺ ሀለቃዬን ምን ልታደርጊው ነው?››ለሊሴ በመገረም ውስጥ ሆና ጠየቀቻት፡፡
‹‹ምን አደረኩብሽ…?››
‹‹እንዴ እያየሁ…ከተዋወቃችሁ ገና ሳምንት ነው..ግን ይሄውና በየቀኑ ይደውልልሻል፣ ገባሽለት እንዴ?››
‹‹አረ አንቺ ደግሞ…››በፀሎት እንደማፈር ብላ ተሸኮረመመች፡፡
‹‹ምነው..ቢሆን ደስ ይለኛል..ምርጥ ሸበላና የተማረ ሰው ነው..በዛ ላይ ትህትና አለው…እና አንቺን እህቴን ብድርለት በጣም ደስ ይለኛል››
‹‹በይ አንቺ ካዳመጡሽ …ብዙ ታወሪያለሽ››

ለደቂቃዎች ሁለቱም ዝም ተባባሉና በየግላቸው ሀሳብ መብሰልሰል ጀመሩ፣…በፀሎት ድንገት‹‹አካባቢው ግን አያስደንቅም?››ብላ አዲስ የመወያያ ርዕስ ከፈተች፡፡
‹‹ በጣም እንጂ…እያንዳንዱ ስፍራ የራሱ የሆነ እይታ አለው…አሁን ጎሮ ጋር ሆነሽ ቁልቁል ስታይ የተለየ አይነት እይታ..ከሊበን ሆነሽ ስታይው ደግሞ የተለየ አይነት እንደምታይው እዚህ ሆነሽ ስትመለከቾ ደግሞ ሌለ አይነት…በእውነት ይሄ በጣም አስገራሚ ነው፡፡ቦታ በቀየርሽ ቁጥር የምታይውም ነገር ይቀየራል…››
‹‹አዎ እንግዲህ …አምላክ ሲጠበብ ወሰን የለውም….››
‹‹እውነት ነው አምላክ ሲጠበብ ወሰን የለውም››የሚል ጣልቃ ገብ ዓ.ነገር  ሁለቱንም ከተቀመጡበት በርግገው እንዲነሱ አደረጋቸው፡፡ሌላ ሰው ነበር ከጀርባቸው የተናገረው፡፡
‹‹አንተ….እንዴት?››
‹‹ያው እንደዚህ››አለና ሁለቱንም በየተራ ሰላም አላቸው፡፡ተያይዘው ተቀመጡ፡፡
‹‹እዚህ ሆነህ ነበር እንዴ የምትደውልልኝ…?››በፀሎት በገረሜታና ባለማመን ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ…››
‹‹እኔ ደግሞ ምን አይነት ሞኝ ነኝ ..የት ነሽ ስትለኝ ያለሁበትን በየዋህነት መዘርዘሬ››
‹‹ምነው ስለመጣው ከፋሽ እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም››
የሰለሞንንና የበፀሎትን የማያቆርጥ ጥያቄና መልስ በዝምታ እየታዘበች በውስጦ እነዚህ ሰዎች ምንድነው እንዲህ ያቀራረባቸው..?ሰውዬውስ እሷን ፍለጋነው እንዴ እዚህ የመጣው
?እያለች በውስጦ ተብሰለሰለች ፡፡ልክ ልቧን እንዳነበበ ለጥያቄዎቾ መልስ ይሰጣት ጀመር…‹‹ያው ባለፀጋዎቹ ደንበኞቼ እዚህ ካልመጣን ሲሉ ተከትያቸው መጠሁ..ያው አስገድደው ሲያስደስቱኝ ምን ላድርግ..እየመጣሁ ሳለሁ ደግሞ እናንተ እዚህ እንዳላችሁ ትዝ ሲለኝ..የበለጠ ዘና አልኩ››
‹‹እና ታዲያ ሰዎችህ የታሉ?››በፀሎት ከወላጆቾ ጋር ድንገት ፊት ለፊት የመፋጠጥ ስጋት አስጨንቋት ጠየቀች

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

24 Dec, 18:19


‹‹እሱማ ምን ጥርጥር አለው….ግን እንደው ትረዳዋለች ወይ የሚለው ጥርጣሬ አድሮብኝ ነው..እሷን ለማታለል ለማስመሰል ያደረግነው መስሎ እንዳይሰማት››ወ.ሮ ስንዱ ጥርጣሬያቸውን አሰሙ፡፡
‹‹እሷ የምታውቀንን ያህል እኛ እኮ ልጃችንን አናውቃትም …..››ሃይለልኡል የሚስታቸው ሀዘንና ጥርጣሬ ውደውስጣቸው እንዳይገባ እየታገሉ መለሱ፡፡
‹‹እሱስ እውነትህን ነው….የልጃችን ትልቅ ውለታ አለብን››
‹‹አዎ .አሁን ልጃችን በጣም በስላለች…ምን አስቤለው መሰለሽ….ካምፓኒው ውስጥ የሆነ ቦታ ይዛ ስራ መጀመር አለባት…እኔ በቅርቡ ጡረታ ወጥቼ ከአንቺ ጋር አለምን እየዞርኩ ዘና

ማለት ነው የምፈልገው…ከአሁን በኃላ በተጨናነቀው የቢዝነስ አለም ውስጥ ቀሪ ህይወቴን ማባከን አልፍልግም››
‹‹እና ስራውን ሙሉ በሙሉ እንድትረከብህ ነው የምትፈልገው?፡፡››
‹‹አዎ ከእኔ ጋር ሆና አንድ ሁለት አመት ከሰራች በቃ ከእኔ በተሻለ ውጤታማ እንደምትሆን እርግጠኛ ነኝ..እይ እስኪ እኔና አንቺን ወደስምምነት ለማምጣት የተጠቀመችበት የረቀቀ ውጤታማ ዘዴ….እንዴት እንዳቀናጀችው…ያን የመሰለ ባለሞያ እንዴት እንደመለመለች
…በእውነት ይህቺ የእኛ ልጅ ነች ብዬ እስክደነቅ ድረስ ነው ያስደመመችኝ፡፡››በንግግራቸው ኩራታቸውን ሲግልፁ ፊታቸውም በደስታ እያበራ ነበር፡፡

…በሶስተኛው ቀን
ሰለሞንና በፀሎት ቢያንስ በቀን አንድና ሁለት ጊዜ እየተደዋወሉ ለረጅም ሰዓት ማውራትና የተለያዩ ርዕሶች እያነሱ መወያየት ልምድ አድርገውታል..ይሄ ደግሞ እርስ በርስ የበለጠ እንዲተዋወቁና በደንበኝነት መልክ ሳይሆን ልክ እንደአንድ የልብ ጓደኛ ወጣ ባለ ርዕሶች ላይም ረጅም ሰዓት ማውራት ጀምረዋል፡፡፡ይሄ ጉዳይ ለሁለቱም በጣም ተመችቷቸዋል፡፡አሁንም ተደዋውለው እያወሩ ነው፡፡
በፀሎት‹‹አንድ ሰው እንዳፈቀረን እንዴት ማወቅ እንችላለን…?ለምሳሌ እኔ አንድ አብሮኝ ያለ ወንድ የእውነት እንደሚያፈቅረኝና በምን ማረጋገጥ እችላለው፡፡››ስትል ያስደነቀውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹ሴት ልጅ ካለገመች በስተቀር አንድ ወንድ እንደሚያፈቅራትና እንደማያፈቅራት በቀላሉ መለየት ትችላለች…አንዳንድ ጊዜ ግን ምን ይሆናል ?እሷ በጣም ካፈቀረችው እሱ እንደማያፈቅራት ብታውቅ እንኳን ሽንፈትን ላለመቀበል ብላ እንደሚያፈቅራት እራሷን ለማሳመን ትጣጣራለች..የዛን ጊዜ የምታያቸውን ምልክቶች ሁሉ በተቃራኒው ተርጉማ ለመረዳት ትሞክራለች››
‹‹እና ምልክቶቹ ምን ምን ናቸው?››

‹‹ለምሳሌ ድምፅሽን ለመስማት ብቻ ይጠራሻል።ስትስቂ ስቆ ስታለቅሺም ያለቅሳል። ከመተኛቱ በፊት በመጨረሻዋ ደቂቃና ከእንቅልፍ በነቃ በመጀመሪያው ደቂቃ ስለአንቺ ነው የሚያስበው።ያለምክንያት ሊያቅፍሽ እና ከሰውነቱ ሊለጥፍሽ ይፈልጋል።አንቺን ከነማንነትሽ ለመቀበል ፍቃደኛ ሆኖ ይገኛል።አንቺን በሌላ ለመቀየር ፍፅም ፍቃደኛ አይደለም።ስህተት ሲሰራ አንቺ እንዲያስተካክል ከመጠየቅሽ በፊት ቀድሞ ለማስተካከል ጥረት ሲያደርግ ታገኚዋለሽ፤ሁል ጊዜ ሊረዳሽ ጥረት ያደርጋል።እንቅልፍ አሸልቦሽ ሊመለከትሽ ነቅቶ ይጠብቃል።ግንባርሽን በስስት ይስማል።መክሳትሽም ሆነ ክብደት መጨመርሽ ከውበትሽ አንፃር ብዙም አያስጨንቀውም፡፡በጓደኞቹ መካከል እጆችሽን ይይዛል።ወይም አቅፎ ጉያው ይሸጉጥሻል።ወዘተ…እንግዲህ እኚንና መሰል ምልክቶችን በማየትና በማመዛዘን አንድ ሰው አፍቅሮሽ ይሁን ወይስ አይሁን መለየት ትችያለሽ››
‹‹እሺ ወሲብስ ምንድነው..?በፍቅር ውስጥ ያለው ድርሻስ?››
‹‹ወሲብን የፍቅር ተጣማሪሽ ጋር ያለሽን ግንኙነት ለማጠንከር እና ለማዋሀድ እንደ ሲሚንቶ የሚያገለግል ተፈጥሯዊ ቅመም ነው፡፡ወሲብ በአግባቡ ከተጠቀምሽበት ፍቅርን በማሳደግና በማጎልበት ትልቅ የሆነ ድርሻ አለው፡፡አይደለም ወሲብ መተሻሸትና መሳሳም እራሱ የፍቅር ግለትን ጠብቆ ለማስቀጠል ትልቅ ጥቅም አለው፡፡››
‹‹እና ከፍቅረኛሽ ጋር ተሳሳሚ እያልከኝ ነው››
‹‹ፍቅረኛው ካለ አዎ በደንብ..ጥናቶች እንደሚያሳዩት ሚስቶች በጋብቻ ውስጥ ከከራረሙ በኃላ ለመሳሳም ያላቸው ፍላጎትና ትኩረት በጣም ይቀንሳል ወይም እስከወዲያኛው ይጠፋል።ላጤዎች ደግሞ ብዙውን ጊዜ በዚህ ረገድ ትኩስና ያልተገደበ ፍላጎት ይኖራቸዋል፡፡ይሄ ግን አግባብ አይደለም ።ባልዬው ድንገት ውጭ ሌላ ላጤ ሴት ቢያጋጥመው ከኤክስፐርት ጋር ነው የሚላተመው...ልዩነቱ ሰፊ ስለሚሆንበት ይከብደዋል።ቶሎ ስህተቱን ለማረም እንዳይችል ይፈተናል።››
‹‹እኔ ግን ሳገባ እንደዛ አላደርግም…ለባሌ በጣም የምመቸው ይመስለኛል›››
‹‹እያስጎመዠሺኝ ነው››
‹‹ምን ያስጎመዠሀል ..አንተን አላገባ?››

‹‹ምን ይታወቃል….ካፈቀርሺኝ ለምን አታገቢኝም?››
‹‹ሳላውቅህ እንዴት ላፈቅርህ እችላለው?››
‹‹ከዚህ በላይ እንዴት ታውቂኛለሽ..ለወራት ድምፄን በስልክ ስትሰሚ ነበር…በቀደም ደግሞ በአካል አይተሸኛል…ምነው አላምርም እንዴ?››
‹‹አረ ቆንጆ ነህ…ግን ቁንጅና ብቻ በቂ አይደለም››
‹‹እስኪ እናያለን››
‹‹ለማንኛውም ለባልሽ መዋብ የምትጀምሪው ከእርቃን ገላሽ ጀምሮ መሆን አለበት...ፓንትሽንና ጡት ማሲያዛሽን የሚያየው ባልሽ ነው።...ለእነሱ ትኩረት መስጠት መቻል በባልሽ እና በአንቺ የፍቅር ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ይፈጥራል።ከላይ ያሉ ልብሶችሽን፣ ፀጉርሽን ፣ጌጣ ጌጦችሽን ለሁሉም ሰው በጋራ የምታደርጊያቸው መዋቢያዎች ናቸው።የውስጥ ልብሶችሽ ጥራት ግን የባልሽ ስሜት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እንደሚኖራቸው ግንዛቤ ሊኖርሽ ይገባል፡፡››
‹‹ገባኝ››

‹‹አይ ስለአንቺ እኮ አይደለም ያወራውት አጠቃላይ ስለፍቅር እና ፍቅረኛሞች ለማውራት ፈልጌ ነው…ባልሽ በአጋጣሚ የሚያገኛቸው እንግዳ ሴቶች ድንገት ፊቱ ልብሳቸውን የማውለቅ እድል ካገኙ እመኚኝ የውስጥ ልብሶቻቸው ብቻ አይደሉም ውብና አማላይ የሚሆነው.. ለሊቱንም ውብና አማላይ እና ያልተለመደ አይነት ያደርጉለታል።አንቺ ሚስቱ ነሽና ብዙ ኃላፊነትና የህይወት ውጣ ውረዶች ስላለብሽ የአመቱን ቀናቶች ሁሉ ውብና አማላይ ልታደርጊለት አትቺይም ግን በሳምንት አንድ ቀን ካልሆነም በወር አንድ ቀን መቼም ሊረሳው የማይችል እንደዛ አይነት ውብ ለሊቶችን በገፀ-በረከትነት ልታቀርቢለት ይገባል።የዛኔ ከውጭ፣በአጋጣሚ የሚፈቱኑትን በልበ ሙሉነት ሊያልፋቸው አቅም ይኖረዋል።››
‹‹ይገርማል …ምንም ሳልከፍልህ በነፃ የቅድመ ጋብቻ ስልጠና እየሰጠኸኝ ነው፡፡››
‹‹ያው ማወቅሽ ዞሮ ዞሮ ጥቅሙ ለእኔው ነው ብዬ ነው››
‹‹እንዴት ማለት?››
‹‹ነገርኩሽ እኮ…ምን አልባት እድለኛው ባልተቤትሽ እኔው ልሆን እችላለሁ››

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

24 Dec, 18:19


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያአራት

ለሊሴና በፀሎት በእቅዳቸው መሰረት በአንቦ በኩል አድርገው ወንጪ በመድረስ የለሊሴ አጎት ቤት ከደረሱ ሁለት ቀን ሆኗቸዋል፡፡በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ በአካባቢው ያሉ የአቶ ለሜቻ ዘመደች ጋር እየዞሩ ሰላም ማለት እና መጋበዙ እራሱ ማደረስ አልቻሉም…እሷ ብዙ የሀብታም ድግሶችና ፓሪዎችን እንጂ እንዲህ አይነት በየሳር ጎጆውና በየደሳሳ የቆርቆሮ ቤቶች እየዞሩ በግዳጅ መጋበዝ በህይወቷ አይታው የማታውቅ ትዕይንት ስለሆነ በጣም አስገራሚና ትንግርታዊ ነው የሆነባት..በየሄደችበት የሚቀርብላት እርጎ፤ ለወተት…የማር ወለላ…አንጮቴ……ጨጨብሳና  ገንፎ..ሁሉም  ውብ  ነበር፡፡በዚህም  የተነሳ  ወደፓርኩ

ለመሄድና ለመጎብኘት ጊዜ አላገኘችም..ቢሆንም በአካባቢው ቢያንስ የሚመጡትን 15 ቀን ስላምታሳለፍ ሁሉንም ነገር ለማድረግ በቂ ጊዜ እንዳላት ስላወቀች ብዙም አልተጨናነቀችም፡፡
ሰለሞንም የበፀሎትን ወላጆች ይዞ ወደወንጪ እያመራ ነው፡፡በመጀመሪያ እቅዱ ወደላንጋኖ ወይም ሰደሬ ይዞቸው ሊሄድ እንጂ ወንጪ የሚባል ስፍራ ፈፅሞ በአእምሮው አልነበረም..ግን በፀሎት ወደወንጪ እንደሄደች ስትነግረው ግን ወደያው ሀሰቡን ቀየረና ለእነአቶ ኃይለልኡል ሀሳብን ነገራቸው፡፡እነሱ የትም ሆነ የትም ለቦታም ብዙም ግድ ሳልልነበራቸው ወዲያው ነበር ሀሳቡን የተቀበሉት፡፡ከዛ ወዲያው ቻርተር አውሮፕላን ተከራይተው ወንጬ ኢኮቱሪዝም ፓርክ እንግዳ ሆነው ተከሰቱ፡፡ጉዞ ተገባዶ ከቻርተር አውሮፕላኑ እንደወረዱ እነሱን ባሉበት ትቶ ቀጥታ ወደኢንትራንስ ጌት ነው የሄደው
…ስለጠቅላላ የጉብኝቱ ፓኬጅ ማብራሪያ ጠየቀና ሁለት መኝታ ክፍል ተከራየ፡፡ የኤሌክትሪክ መኪና ተከራይቶ እቃቸውን በመጫን ቀጥታ ወደተከራየበት ሎጅ ይዞቸው ሄደ…
ሰለሞን ወላጆቾን ወደወንጪ ይዞ መምጣቱን ለበፀሎት አልነገራትም፡፡እሷ የምታውቀው ወደላናጋኖ እንደሚሄዱና ሲደርስና ሲመቸው እንደሚደውልላት ነው፡፡
ወንጪ ከአዲስ አበባ በ135 ሜትር ርቀት ላይ በደቡብ ምዕራብ ኦሮሚያ ክልል በአንቦ እና በወሊሶ ከተሞች መካከል የሚገኝ ድንቅ ስፍራ ነው ፡፡ወንጪ ሀይቅ ከባህር ወለል በላይ 3000ሜትር ከፍታ ላይ ሲገኝ 75 ሜትር ገደማ ጥልቀት ያለው ንፁህ እና ጥርት ያለ ሀይቅ ነው፡፡ሀይቁ ከ3000 ዓመት በፊት በተከሰተ እሳተ ጎመራ የተፈጠረ እንደሆነ ይነገራል፡፡በአካባቢው የሚነገሩ አፈታሪኮች እንደሚያስረዱት በወቅቱ እንደሶደም አይነት ተንቀልቃይ እሳተ ጎመራ ተነስቶ የአካባቢውን ፍጥረት ለረጅም ጊዜ እየበላ ከቆየ በኃላ ድንገት በቦታው አርባ አራት ምንጮች ተፈጥረው የሚንቀለቀለውን ውሀ ካጠፋት በኃላ በእሳተ ጎመራው አማካይነት የተፈጠረውን ረባዳ አካባቢ መሙላት ይጀምራል….ውሀው ግን ሞልቶ በመሀከል ትንሽ ደሴት በውሀ ሳትዋጥ ደረቅ መሬት ሆና ትቀራለች…ከዛ ያንን የታዘብ የአካባቢው ኑዋሪዎች ያቺ መሬት በውሀው ሳትሸፈን የቀረችው የተቀደሰች ስፋራ ስለሆነች ከአሁን በኃላ ቦታዋና እንደማመስገኛና ከፈጣሪ ጋር መገናኛ የተለየች ስፍራ አድርገን እንገለገልባታለን ብለው ይስማማሉ…በአሁኑ ወቅት በቦታው ላይ ቤተክርስቲያን ታንፆበታል፡፡

የውንጪ ኢኮቱሪዝም መዝናኛ..መንገዶቹ ጠባብ ስለሆኑና የመኪና መተረማመስ የአካባቢውን ተፈጥሮ እንዲያበላሽው ስለማይፈለግ .ማንኛውም ጎብኚ በራሱ መኪና ወደውስጥ ዘልቆ መግባት አይችልም…ግን ወደሎጆችም ሆነ ወደመዝናኛ ፓርኮች ወይንም ደግሞ ወደገበሬዎች መኖሪያ ቤት ለመሄድ የፈለገ ሰው የተለያዩ አይነት ቀላል የትራንስፖርት አማራጭ ተዘጋጅቶ ይጠብቀዋል..ለምሳሌ…የፈረስ ትራንስፖርት ..ሳይክል
…ኤሌክትሪክ መኪና ካልሆነም ደግሞ በጠባበቹ የአስፓልት መንገድ ግራ ቀኝ ያለውን ውብ ተፈጥሮና የፓርክ ክፍሎችን በመጎብኘት በእግሩ ወክ እያረገ ስጋውን ማዝናናት ነፍሱንም ማስፈንጠዝ ይችላል፡፡
አጠቃላይ የወንጪ የመንገድ ልማት 70 ኪሎ ሜትር አካባቢ ሲሆን ተራራውን የሚዞር 10 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ … ወደ ዲንዲ ሚሄድ ሀይ ወይ …ማራቶን ራጮች እንዲለማመዱበት ታስቦ የተሰራ የሩጫ ትራክ ሁሉም ውብ ነው፡፡በተለይ ተራራውን በሚዞረው መንገድ ላይ ሁለት ሶስት ሆነው ሳይክል እየነዱ ወይም ፈረስ እየጋለቡ ዙሪያ ገባውን መጎብኘት ገነት ደርሶ እንደመመለስ አይነት አስካሪ ስሜት ውስጥ ይከታል፡፡
አንድ ጎብኚ ሎጆቹን የመከራየት አቅም ማይኖረው ከሆነ እዛው ከሪስፕሽን በፓርኩ ግንባታ ምክንያት ከቦታቸው የተነሱ ገበሬዎች በመንግስት በካሳ መልክ የተሰራላቸው ዘመናዊ ቤቶች ውስጥ ከክፍሎቹ የተወሰኑትን ለቱሪስት እያከራዩ ገቢ እንዲያገኙ ታስቦ የተሰራላቸው ስለሆነ ቀጥታ እዛው ሬስፕሽን ቡክ ያደረገ ሰው የየትኛው የገበሬ ቤት እንደሚያድር ይነገረውና ቀጥታ እዛ ሄዶ በተመጣጣኝ ዋጋ ማደሪያ ያገኛል፡፡
ወንጪ ውበትን ለመግለፅ እግዜያብሄር እንደምሳሌነት ለማሳያ የፈጠራት ስፍራ ትምስላለች…ውበቷ ሀይቆ ብቻ አይደለም…ዙሪያዋን የከበቡት አረንጋዴ ልብስ የለበሱት ሰንሰለታማ ወጣ ገባ ተራሮች ፣አየሩ ሁሉ ነገር ጠቅላላ ውብ ነው፡፡አሁን ደግሞ ቦታውን የቱሪስት መነኸሪያ ለማድረግ የተገነቡት መሰረተ ልማቶች ይበልጥ ወደፍፁምነት ያስጠጋው ነው፡፡ደረጃቸውን የጠበቁ ሙሉ ተራራውን የሚሽከረከሩ የአስፓልት መንገዶች በእያንዳንዱ ኮርነር ላይ የታነፁ የተላያዩ ታሪክ እንዲሸከሙ ተደርገው በጥንቃቄና በጥበብ እንዲታነፁ የተደረጉ ህንፃዎች፤ ሎጆች፤ ካፌዎች ፤ፈንጠርጠር ብላው ከሩቅ የሚታዩ የገበሬ ቤቶች እርሻዎች …ሁሉ ነገር አይን ሞልቶ የሚፈስ የመንፈስ ትፍስህት ነው፡፡በወንጪ ኢኮቱሪዝም ፤የባንክ አገልግሎት፤ የአካባቢው ልጆች ተደራጅተው የሚሰጡት የሬስቶራንት አገልግሎት ፤የተለያዩ የባህል እቃዎች የሚሸጡበት ሱቆች..ካፍቴሪያ …አነስተኛና ትላልቅ

አዳራሾች…አንፊትያትሮች ሁሉም በአቅሙ ልክ አገልግሎት እንዲያገኝ ተደርጎ የተዘጋጀ ልዩ ልዩ አገልግሎቶች ይገኛሉ ፡፡
ወንጪ ኢኮቱሪዝም ባህልና ተፈጥሮን ማእከል አድርጎ የተገነባ ነው፡፡የወንጪ አካባቢ ስድስት ወር አካባቢ ዝናብ የሚዘንብባት ለምለምና እርጥብ ቦታ ነው፡፡እነሰለሞን የተከራዩት ክፍል የእሱ ባለአንድ አልጋ ሲሆን የባልና ሚስቶቹ ግን ሁለት አልጋ በአንድ ክፍል ያለበት ለቀቅ ያለ ዘመናዊና ባህላዊ እቃዎች በስምምነት ተሰባጥረው ያሳመሩት… ለሀይቁም ሆነ የአካባቢውን ተፈጥሮ ለማየትና ለማድነቅ ውብ እይታ ያለው በአንቦ ድንጋይ ተጠርቦ የተሰራ…በአሻራ ወይም በካርድ የሚከፈት ውብ ክፍል ነው፡፡ መኝታ ክፍሉ ዘመናዊ ማሞቂያ የተገጠመለት ስለሆነ ምቹ በሆነ የአየር ሁኔታ ውስጥ ተቀምጠው ወይም ተኝተው በተከፈተው መስኮት ቁልቁል ሀይቁን ሲመለከቱ ልብን ጥፍት ያደርጋል፡፡
ምሽት ነው…አራት ሰዓት አካባቢ..አቶ ኃይለ ልኡልና ባለቤታቸው ወ.ሮ ስንዱ አልጋ ክፍላቸው በረንዳ ላይ ቁጭ ብለው ቁልቁል የጨረቃዋ ብርሀን ወንጪ ሀይቅ ላይ ስታርፍ እና ከሀይቁ ጀርባው ያለውን ውብ ሰንሰለታማ ተራራ እያዩ ያወራሉ
‹‹ሃይሌ..ልጃችን ግን አሁን ወደአዲስአባ እንደተመለስን የምትመጣ ይመስልሀል?››
‹‹አታስቢ….ትመጣለች….››
‹‹እንደማስበው አሁን እሷ እንድንሆንላት የምትፈልገውን አይነት ወላጆች የሆን ይመስለኛል…፡፡››

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

23 Dec, 18:43


Online ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት ምን ልስራ ብላቹ ብትጠይቁ በጣም ብዙ ምርጫዎች አሉ።

ትርፋማ ሊያደርገኝ የሚችለው የትኛው Skill ነው?
የት ሄጄ ልማረው እችላለው?
በአጭር ጊዜስ ወደ ስራ ለመግባት እና ገንዘብ ለመስራት ምንድን ነው ማድረግ ያለብኝ?

እነዚህን ጥያቄዎቻቹን ለመመለስ የፊታችን ታህሳስ 16, 18 እና 20 ነጻ Online Webinar አዘጋጅቼላቹሃለው!

በዚህ Webinar የራሴን ልምድ እንዲሁም በዙሪያየ ያሉ ስኬታማ ሰዎችን ልምድ አምጥቼ እያንዳንዱን ነገር ብትንትን እያደረግን እንመለከታለን

ለመሳተፍ ከእናንተ የሚጠበቀው ኢንቴርኔት እና ስልክ ወይም ላፕቶብ በቂ ነው።
ታህሳስ 16, 18 እና 20, ከምሽቱ 2፡00ሰዓት

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

23 Dec, 17:39


ለሊሴ ግቢው ውስጥ ይዛው ገባችና መጀመሪያ ከአባቷ ጋር ከዛ ከወንድሞ ጋር አስተዋወቀችውና ይዛው ወደ ሌላ ክፍል ውስጥ ይዛው ገባች…ክፍሉ አዲስ የተሰራ መሆኑን ያስታውቃል….ጥግ ላይ በስርአት የተነጠፈ አንድ አልጋ ..ከዛ ሁለት ወንበር እና አነስተኛ ጠረጴዛ ይታያል..ጠረጴዛ ላይ ሁለት ነጭ ሻማ ተለኩሶ እየበራ ነው…የቤቱ ወለል ሙሉ በሙሉ ቄጤማ ተጎዝጉዞ አውዳአመት መስሏል…አልጋው ጠርዝ ላይ አንድ ወጣት ተቀምጣለች …ከዛ ውጭ ቤቱ ባዶ ነው፡፡
በፀሎት‹‹ግባ ዝለቅ…. ››የሚል ድምጽ ስትሰማ ካቀረቀረችበት ቀና አለችና ግባ እየተባለ ያለው ሰው ላይ አፈጠጠች…ጠይም ነው…ባለደማቅ ጥቁር ፀጉር…ቆንጆ ወንዳወንድ
ነው…ልክ እንደባንክ ቤት ስራአስኪያጅ ሽክ ብሎ ሰማያዊ ሱፍ ለብሶል..ሰማያዊ ሱፍ በነጭ ሸሚዝ…ከረባት አላሰረም….በቅፅበት ውስጥ ነው ሙሉ ቁመናው ውስጧ ስምጥ ብሎ የገባው፡፡ስሯ ደርሶ ሲቆም ከተቀመጠችበት ተነሳች…..‹‹ተዋወቂው ሀለቃዬ ነው….እሷ ደግሞ እህቴ ነች››
‹‹ሰለሞን እባላለሁ››ብሎ እጁን በትህትና ዘረጋላት፡፡
በደመነፍስ እጇን ዘረጋችለት..ጨበጣትና እየወዘወዛት ስሟን እስክትነግረው ይጠብቅ ጀመር…..ምን ብላ ትንገረው….ለእሷ በዛሬው ቀን ይሄ ሰው ያለችበት ቦታ ድረስ መጥቶ እጇን መጨበጥ የማታሰብ ነገር ነው….፡፡
‹‹ስምሽን ንገሪው እንጂ …?.›››
‹‹ስሜን የማን የእኔ..ማለቴ..››ተርበተበተች፡፡
‹‹ተዋትና ተቀመጥ ልጄ…..››እጇን ለቀቀና ወደመቀመጫው ሄዶ ተቀመጠ… ፡፡ ለሊሴ‹‹ተጫወቱ መጣው..››ብላ ወደ ዋናው ቤት ሄደች፡፡
‹‹ምነው ስምሽ ያስጠላል እንዴ?››ሲሌ ጠየቃት፡፡
‹‹እኔ እንጃ….ሰናይት እባላለሁ››
‹‹እና ሰናይት የሚለውን ስም ለመናገር ነው የተናነቀሽ?››
‹‹አይ …ሱፍ ለባሽ ክፍላችን ሰተት ብሎ ይገባል ብዬ ስላልጠበቅኩ ነው፡፡››
‹‹ቱታ ለብሼ መምጣት ነበረብኝ…?››
‹‹ለካ እንዲህ ነገረኛ ና አሽሟጣጭ ሰው ነው እንዴ? ››ስትል በውስጧ አሰበች…ዝም አለችው….. ወዲያው ለሊሴ እና እናቷ እንጀራና ወጡን ይዘው መጡ…እዛው የእጅ ውሀ አስታጠቡትና የሚበላ ቀረበለት…እንጀራውን ሲነሳ ደቦና ቆሎ ቀረበለት..ለእሱ ተብሎ የተገዛ ቢራ ተከፈተለት…..
‹‹እንዴ ቢራ እኔ ብቻ ነኝ እንዴ ምጠጣው…?››

‹‹ለጊዜው አዎ…አባዬ ትንሽ ቆይቶ መጥቶ ይቀላቀልሀል….እንግዶች ስለመጡ እማዬን ባግዛት ቅር ይልሀል..አልቆይም፡፡ ››
‹‹ሂጂ ችግር የለውም ..እህትሽ ታጫውተኛለች›› ለሊሴ‹‹ጥሩ ..በቃ መጣሁ››ብላ ወጣች
ሰለሞን ወደ በፀሎት ዞረና ‹‹አሁን ብቻችንን ቀርተናል….››አላት፡፡ ደንግጣ‹‹ ማለት?››
‹‹አትደንግጪ ሰኒ…ምን አስደነገጠሸ?››
‹‹አይ እሱማ ምን ያስደነግጠኛል…?አልደነገጥኩም…››እውነቱን ለመናገር ከመደንገጥም አልፋ ሰውነቷ በላብ እየተዘፈቀ ነው፡፡
‹‹አህቴ ስለአንተ ብዙ ነገር ነግራኛለች….››
‹‹እህትሽ ብቻ… እኔስ ብዙ ነገር ነግሬሽ የለ እንዴ?››
‹‹መቼ ..?የት ተገናኝተን….?››
መልስ ይመልስልኛል ብላ ስትጠብቅ ስልኩን አወጣና እያየችው ደወለ…ኪሷ ያለው ስልክ ተንጣረረ…አወጣችና አየችው…ምን እንደምትል እንዴት እደምታደርግ ግራ ገብቶት
አፍጥጣ እስክሪኑን እያየች ባለችበት ሰዓት ለሊሴ ከውጭ ገባች….ሰለሞን ስልኩን ዘጋው..የሚያንጣርረው የበፀሎት ስልክም ተቋረጠ…፡፡
‹‹በፀሎት ሀለቃዬን እንዳታስደብሪው››
‹‹አረ …የምን መደበር አመጣሽብኝ….እህትሽ ካንቺ በላይ ተጫዋች አይደለች እንዴ?››
‹‹እንግዲያው ጥሩ ..ቢራውን ጨምሪለት››ብለ ተመልሳ ወጥታ ሄደች፡፡
‹‹እሺ ጨምርለታለው››
መሄዷን ከረጋገጠች በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀና ብላ በትኩረት አየችው‹‹ምነው ቆንጆ ነኝ?››

‹‹በጣጣጣ…..ም››
‹‹አንቺም ልክ እንደጠበኩሽ ነሽ…ግን እንዳትታወቂ ነው የተሸፋፈንሽው….››
ቀስ ብላ ሻርፕን ከፊቷ አነሳችና አሳየችው…..ደነገጠ….ወዲያው በፍጥነት መልሳ አሰረችው፡፡
‹‹ምን ተፈጥሮ ነው?››
‹‹የጠፋው ቀን በሞተር ነበር ከቤት የወጣሁት..እና ይዚህን ጊቢ አጥር ጥሼ ከበሩ ጋር ተላትሜ ነው የቆምኩት….እግሬ ሁሉ ተሰብሮ ነበር…አሁን ግን ድኛለሁ››
‹‹ይሄንን እንዴት እስከዛሬ ሳትነግሪኝ?››
‹‹ለምን ነግርሀለው..?ምን እንድታደርግልኝ?››
‹‹ምን ባላደርግልሽስ….እኔ ላንቺ አንደዚህ ነኝ?››
‹‹እንዴት ነህ?››
‹‹ትናት ማታ እንደዛ ዳባሪ ስሜት ላይ ሆኜ ለማን ደወልኩ ?ላንቺ አይደል?››
‹‹በነገራችን ላይ በጣም ስታሳስበኝ ነበር…ለሊቱን ሙሉ ስላአንተ እየተጨነኩነው ያሳለፍኩት…..እንደማይህ ግን እንደማንኛውም ወንድ ወዲያው ማገገምና ወደተመደ እንቅስቃሴ መግባት ችልሀል፡፡››
‹‹ምን ጠብቀሽ ነበር…?ዛሬም አልጋዬ ላይ ተኮራምቼ እንዳለቅስ?››
‹‹አዎ.. እኛ ሴቶች ብንሆን እንደዛ ነው የምናደርገው››
‹‹ይሁን…አሁን እንደተመለስኩ እንዳልሺኝ አደርጋለው….በነገራችን ላይ ይሄንን የመቁሰልሽን ዜና ወላጆችሽ ቢሰሙ በቃ ቁም ስቅሌና ነበር የሚያሳዩኝ…››
‹‹ቆይ እንዴት እኔ መሆኔን አወቅክ…..ማለት እንዳየሁህ እኮ ስሜን ቀይሬ የነገርኩህ ማንነቴን የምትለይበት ምንም መንገድ እንደሌለ እርግጣኛ ሆኜ ነበር፡፡››
‹‹እንግዲህ ይሄን ያህል ነው የማውቅሽ….››
‹‹በጣም ነው ያስገረምከኝ››

‹‹ያው ሰውን ማስገረሙን ካንቺው ነው የኮረጅኩት››
‹‹እሺ..በመሀከላችን ስላለው ነገር ለሊሴ ምንም ማወቅ የለባትም››
‹‹እንዴ በመሀከላችን የሆነ ነገር አለ እንዴ?››
‹‹አትቀልድ››
‹‹እሺ እንዳልሽ››
‹‹በነገራችን ላይ ከለሊሴ ጋር ከነገ ወዲያ ወደወንጪ ልንሄድ ነው…የጋሼ ዘመዶች እዛ አሉ….እንዝናናለን፡፡››
‹‹ደስ ይላል..ያው እኔም ከተውሻቸው ወላጆችሽ ጋር የሆነ ቦታ ሄጄ ዘና እላለው…ሳስበው አንቺ እዚህ ስለተመቸሽ አነሱን ለእኔ ብትሰጪኝ ደስ ይለኛል፡፡;;
‹‹ውሰዳቸው››
‹‹ተይ በኃላ..እንደድሮ እንዳይመስሉሽ…ፍቅር ሲያገረሽ አደገኛ መሆኑን ያየሁት በእነሱ ነው…ጎረምሳ በያቸው››
ለሊሴ አባቷን አስከትላ መምጣቷን ጫወታቸውን እንዲያቆርጡ አደረጋቸው፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

23 Dec, 17:39


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያ ሶስት

በማግስቱ የናፈቀው ቢሮ የገባው አራት ሰዓት አካባቢ ነበር….የማታው ስካር አንጎበሩ ሙሉ በሙሉ አለቀቀውም…አሁንም ጭንቅላቱን እየወቀረው ነው፡፡ለፀሀፊው መምጣቱን
ስላልነገራት አልገባችም…ከፍቶ ገባና ቁጭ አለ ..የሚሰራው ስራ ስላልነበረ የሚያደርገው ነገር ግራ ገባው..ስልክ አውጥቶ ደወለ፡፡
‹‹እንዴት ነሽ…ለሊሴ?››
‹‹ደህና ነኝ ሰለሞን…እንዴት ነው ስራ?››
‹‹አሪፍ ነው..አሁን ተመልሼለሁ…ቢሮ ነው ያለሁት››
‹‹ውይ ለምን ሳትነግረኝ..ቀድሜ ገብቼ አፀዳድቼ ጠብቅህ ነበረ እኮ››
‹‹አይ ችግር የለውም..ቢሮው አሁንም ንፅና የተስተካከለ ነው››
‹‹አዎ እሱማ በሶስት ቀን አንዴ ከፍቼ አናፍሰዋለው….እና ስራህን ጨረስክ ማለት ነው?››
‹‹አይ አልጨረስኩም…በመሀል የሶስት ቀን እረፍት ስላለኝ ነው የመጣሁት…ለመሆኑ ያንቺ ነገር እንዴት ሆነ?››
‹‹የቱ?››
‹‹የሁለቱ ፍቅረኞችሽ ነገር?››
ለሊሴ ሰለሞን ባቀረበላት ሀሳብ መሰረት ከሁለት ፍቅረኞቾ መካከል አንዱን ለባልነት ለመምረጥ ምታደርገውን ጥረት ወዲያው ነበር የጀመረችው ….መጀመሪያ ነጋዴውን ለአንድ ወር ላታገኘው እንደማትችል ነግራ ከመንግስት ሰራተኛው ጋር ነበር የቀጠለችው..ሲደውልላት ትሄዳለች..ዝም ሲላት ትደውልለታልች….ከስራ መልስ ሳታገኘው ወደቤት አትገባም…እሁድ ቢያንስ ግማሹን ሰዓት ከእሱ ጋር ነች፡፡ይበልጥ ትኩረቷን ሰብስባ ከእሱ ጋር ባሳለፈች መጠን በፊት ከምታውቀው በላይ እያወቀችው …በፊት ከምታዳምጠው በላይ እያዳመጠችው መጣች፡፡አሁን ያለበትን የኑሮ ደረጃ ብቻ ሳይሆን ..

የወደፊት እቅዶቹንና እነዛን እቅዶች ለማሳካት እያደረገ ያለውን ተጋድሎም እየተረዳችና እየተገነዘበች መጣች…..እሱ ላይ ያላት ቅሬታ ባገባው እኔን አኑሮ ቤተሰቦቼንም እንድረዳ የሚያበቃኝ ህይወት ሊሰጠኝ አይችልም የሚል ነበር…አሁን ስታስበው ግን ያንን ከእሱ ብቻ መጠበቅ እንደሌለባት ነው የገባት…እሱ ባለው ቁርጠኝነት ላይ እሷ ተጨምራበት ካገዘችውና ከጎኑ ሆና አብራው ከታገለች ጎዶሎው ሊሞላ የሚችል አይነት እንደሆነ ተረድታለች…ግን ውሳኔ ላይ ከመድረሷ በፊት ለእሱ የመደበችለት ወር ተገባደደ እና ለዛኛው የሰጠችውን ተመሳሳይ ምክንያት ሰጥታ ..ለአንድ ወር ያህል ልትደውልለትም ሆነ ልታገኘው እንደማትችል ነገራ ወደነጋዴው ሄደች፡፡
በእውነት ነገዴው ጋር ልክ እንደወትሮ ሁሉ ነገር ተሰርቶ ያለቀ ሆኖ ነው የጠበቃት…ቤቱ የተዘጋጀ..እቃዎቹ የተደራጁ ናቸው…አዎ እያንዳንዱን ሀብቱንና አኗኗሩን ተራ በተራ አሳያት፣ቀጥታ እንዳገባችው ሕይወቷን ወደመስራት ሳይሆን የተሰራ ህይወት ውስጥ ገብቶ ለመኖር መሞከር ብቻ እንደሚጠበቅባት ተረዳች ፣ግን ለምን ልቧ ወደኃላ እንደሚጎትታት ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም‹‹…ታግዬ ያላሸነፉኩት በሌላ እጅ የተሰራ ህይወት ምን ትርጉም ይኖረዋል?››እራሷን ጠየቀች… መልሱ ቀላል አልነበረም….፡፡
ሁሉንም ሂደት አንድ በአንድ ዘርዝራ አስረዳችው፡፡ ሰለሞንም‹‹እና ምን ተሰማሽ?››ሲል ጠየቃት
‹‹አሁንም እንደተወዛገብኩ ነው…ግን በአእምሮዬ ውስጥ የሚመላለሱ ጥያቄዎች በፊት ከሚመላለሱት የተለዩ ናቸው…እንግዲህ እኔ በህይወቴ ጠንከር ያሉ ውሳኔዎችን የማስተላለፍ ከፍተኛ ድክመት እንደለብኝ ነው የተረዳሁት፡፡››
‹‹አይ እንደዛ አይመስለኝም …አንቺ ቀሪ ህይወትሽን አብሮሽ በደስታ የሚዘልቅና ከቤተሰቦችሽም ጋ ተሰስማምቶ የሚያኮራሽ ለፍፅምነት የተጠጋ ባል እየፈለግሽ ነው….በዚህ ምድር ላይ ደግሞ ለፍጽምና የተጠጋ ነገር መምረጥ ቀላል ነገር አይደለም፡፡አንድ ታሪክ ልንገርሽ..
‹‹ደስ ይለኛል››
ደቀ መዝሙሩ  መምህሩን ‹‹ፍፁምና በህይወታችን እንዴት አድርገን ነው ፍፅማዊ የሆነ ነገር መጎናፀፍ የምንችለው? ሲል ጠየቀው ፡፡ መምህሩም አሰብ አደረገና ‹‹የዚህን መልስ

እንድነግርህ ከፈለክ በፊት ለፊት በር ወደ ግቢው የአትክልት ስፍራ ቀጥ ብለህ ግባ ።በመንገድህ ከምታገኛቸው አበቦች መካከል በጣም የሚያምረውንና ደስ ያሰኘህን ቀንጥስና በጎሮ በር ውጣ …አንዴ ያለፍከውን አበባ ከእንደገና ወደኃላ ተመልሰህ መቅጠፍ አትችልም አሉት።›› አለው ።እሱም ትዕዛዙን አክብሮ እንዳተባለው ወደ አትክልቱ ስፍራ ገባና እስከመጨረሻው ጥግ ከተጓዘ በኃላ ባዶ እጅን በጓሮ በር ወጣ።
መምህሩ ‹‹ለምንድነው አንድ ቀንበጥ አበባ እንኳን ይዘህ መውጣት ያልቻልከው?››ሲሉ ጠየቁት፡፡
‹‹ምርጥ የተባለውን አበባ ወዲያው እንደገባሁ ነበረ ያገኘሁት... ግን የተሻለ አገኛለሁ ብዬ በማሰብ ሳልቀነጥስ ወደፊት ቀጠልኩ .. መጨረሻው ላይም ደረስኩ.. ወደኃላ የመመለስ እድል ስለሌለኝ ባዶዬን ለመውጣት ተገደድኩ›› ሲል መለሰ።
መምህሩ መልሱን ሲሰሙ ፈገግ አሉና ‹‹አዎ! ትክክል ነህ ፤ህይወት እንደዛ ነው ።ፍፁምናን ለማግኘት ይበልጥ በዳከርን ቁጥር ብኩን እየሆንክ ትሄዳለህ።እውነተኛ ፍፁምናን መቼም የትም አታገኝም።››ሲሉ መለሱለት። ‹‹ገባሽ አይደል?››
‹‹አዎ ገብቶኛል››
‹‹እንግዲያው ፍፅም በምናብ አለም ካስቀመጥሽው ወንድ ጋር የሚስማማ ባል እንደማታገኚ አውቀሽ ለሚማጡት 10 ቀናት ሁለቱንም ሳታገኚ አስቢበት..ከዛ ማንኛቸው ናቸው የበለጠ የሚናፍቁሽ..የትኛው ቢያቅፍሽ ትፈልጊያለሽ ….?ማንኛቸው የልጆችሽ አባት ቢሆኑ ይሻላል..?በህልምሽ እየደጋገመ የሚመጣው የትኛው ነው?፡፡ለ10 ቀን አስቢበት፡፡››
‹‹እሺ እንደዛ አደርገላው..ግን አሁን አሁን እየገባኝ ያለው እኔ ከባሌ ምን እጠብቃለው ብቻ ሳይሆን ለባሌስ ምን ይዤለት ሄዳለው…?የሚለውን በጥልቀት ማሰብና መዘጋጀት እንዳለብኝ ነው፡፡ ››
‹‹ጎበዝ ነሽ…ይሄ ትልቅ መረዳት ነው..በይ ደህና እደሪ››
‹‹ውይ …ከመዝጋትህ በፊት…ድፍረት አይሁንብኝና ዛሬ ቤት ለምን አትመጣም››
‹‹ለምን?››
‹‹እማዬ የማሪያም ድግስ አለባት….ማህበርተኞቹ እስከ10 ሰዓት ነው የሚቆዩት 11 ሰዓት ብትመጣ በጣም ደስ ይለኝ ነበር…››
‹‹አረ ተይ››
‹‹ምን አለበት…ቤተሰቦቼ በጣም ነው ደስ የሚላቸው››
‹‹11 ሰዓት ነው ያልሽኝ?፡፡››
‹‹አዎ 11 ሰዓት››
ብቻውን ሆኖ ስለአስቴር እያሰበ ከሚሰቃይ ከሰው ጋር ተቀላቅሎ የባጥ የቆጡን እያወራ ሊረሳት ቢሞክር እንደሚሻለው አሰበእና ‹‹በቃ እሺ መጣለሁ››አላት፡፡
‹‹በቃ አቃቂ ፖሊስ ጣቢያው ጋር ስትደርስ ደውልልኝ..ወጥቼ እቀበልሀለው››
‹‹እሺ ደውላለው››
ስልኩን ዘጋው፡፡ እሺ ማለቱን ፍጽም አላመነም….ጠበል ለመቅመስ ከሜክሲኮ
አቃቂ….ለመሆኑ በህይወቱ ጠበል የተጠራውና ጥሪውን አክብሮ የሄደው መቼ ነው..?ፍጽም አያስታውስም….
እንዳለችው …..እንደደወለላት ደቂቃ ሳታባክን ነው ወጥታ የተቀበለችው….መኪናውን
እዛው አስፓልት ዳር ፓርክ አደረገና ተከትሏት ይዛው ሄደችው.. ግን ወደሚያስደነግጥ ቦታ ነው ይዛው የሄደችው…ይሄንን ግቢ ትናንትና በዚህን ሰዓት መኪና ውስጥ ሆኖ ከአሰሪዎቹ ጋር በመሆን ሲሰልለው ነበር …‹‹ምን አይነት መገጣጠም ነው?››ለለሊሴ ምንም አይነት የመደነቅና የመገረም ስሜት ሳያሳያት ተከተላት፡፡አሁን ነገሮችን ገጣጥሞ ሲያስብ በፀሎት እሱን እንዴት እንዳገኘችውና ስልኩን ከማን እንደወሰደች ተገለፀለት፡፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

22 Dec, 16:50


ማለት አይደለም…አንዳንዱ ግንኙነቶች ምንም ቢለፋባቸውና ፍሬ አያፈሩም…ያንተም እንደዛ ሆኖ ይሆናል››
‹‹ይገርማል››
‹‹ምኑ ነው የሚገርመው?››
‹‹እኔ ሳልሆን አንቺ ነሽ የፍቅር አማካሪ መሆን የነበረብሽ››
‹‹እንግዲህ በችሎታዬ ከተማመንክ ስልጠና ሰጥተህ ወደፊት በረዳትነት ልትቀጥረኝ ትችላለህ››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር…ደሞዝሽ ይከብደኛል እንጂ››
‹‹አይዞህ..አትፍራኝ …አንደራደራለን››
‹‹አመሰግናለሁ…አንቺ ጋር መደወሌ ምክንያታዊ ባይሆንም ..ግን ሰርቷል አግዘሺኛል፣አሁን ትንሽ ቀለል አለኝ፡፡››
‹‹አሁን መጠጣቱ ይብቃህ…ሻወር ወሰድና ተኛ…ጥዋት ስትነሳ ሁሉ ነገር ቀለል ብሎህ ታድራለህ››
‹‹እሺ….እንዳልሺኝ አደርጋለው….ደህና እደሪ››

‹‹ደህና እደር››ብላ ስልኩን ዘጋችው ፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

22 Dec, 16:50


‹‹‹አይ ይሄ ለነገሮች ያለን ትርጉም ልዩነት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡እኔ ወላጅ አልባ ብቻ ሳልሆን ዘመድ አልባ በሆንኩበት በዛ ጨለማ ጊዜ እናትና አባትህ ያለምንም ማቅማማት ወደቤታቸው ወስደው ከዛሬ ጀመሮ አንቺም ሌለኛዋ ልጃችን ነሽ አሉኝ፡፡እውነትም እንዳሉት ለእህትህ ስህን የሚደረገው ሁሉ ለእኔም ይደረግልኝ ነበር..ለእሷ ቀሚስ ሲገዛ ለእኔም ዘለውኝ አያውቁም.. ከፓንት አቅም ለእሷ የተገዛው አይነት ለእኔም ይገዛልኝ ነበር… የእውነት ልጃቸው ነበርኩ..ዩኒቨርሲቲ ገብቼ አንድም ወር የኪስ ገንዘብ ለእኔ ከመላክ እረስተውና ዘለውኝ አያውቁም…እና ሁለቱም ሲሞቱ ከእናንተ እኩል ነው ያጣዋቸው…..አንተ የምትወዳቸውን ያህል እኔም ወዳቸዋለው…አሁን የሚናፍቁህን ያህል

እኔንም ይናፍቁኛል..እና እኔ የእውነትም አንተም ወንድሜ እነሱም ወላጆቼ እንደሆኑ ነው የማምነው..ይሄንን እምነቴን ማንም በየትኛውም ሎጂክ ተከራክሮ ሊያስቀይረኝ አይችልም…እምነት ያው ከቃሉም እንደምትረዳው ዝምብለህ ነገሩን በቀና ልብ መቀበል አይደል..እኔም እንደዛው ተቀብዬዋለው…፡፡አሁን እንተ የደም ትስስር የለንም ምናምን ብትለኝ.በአንዱ ጆሮዬ ገብቶ በአንድ ይፈሳል እንጂ በእኔ ስሜት ላይ ምንም የሚያመጣው ለውጥ የለም…አንተ እንደፈለከው ማመን ትችላለህ…እህቴ አይደለሽም ልትለኝም ትችላለህ…በግድ ላሳምንህ አልችልም..፡፡››
‹‹ይገርማል… ልጅ እያለንም ጭምር እንዲህ ነገሮችን ውስብስብ ማድረግ ትወጂ ነበር…እሺ አሁን ለምን ተመልሼ እንደመጣሁ ታውቂያለሽ?››
‹‹ያው የሰው ሀገር አይደል ..ደብሮህ ነዋ››
‹‹አይ አይደለም….ከመስፍን ጋር እንደተፋታችሁ ስሰማና ፣አገር ለቆ እንደሄደ ሳረጋግጥ…ዳግመኛ እድሌን ለመመከር ነው..ምን አልባት አሁን እነአባዬና እማዬ በህይወት ስለሌሉ እሺ ብለሽ ፍቅሬን ትቀበይዋለሽ..እኔንም ከቁም ሞት ቀስቅሰሽ ታድኚኛለሽ..ባል አድርገሽ ታገቢኛለሽ ብዬ ነው››
ዝም ብላ በፍዘት ታየው ጀመር…ቡዝዝ ባሉት አይኖቾ እንባ ሞላባቸው…
‹‹ወንድሜ እኔ በጣም ነው የምወድህ..ያንተ ከጎኔ መሆን የሚፈጥርልኝ ጥንካሬና የመንፈስ ከፍታ ልትገምተው አትችልም…አንተ የራስህን ሰው አግኝተህ አፍቅረህና አግብተህ እዚሁ
አጠገቤ አዲስአበባ እንድትኖር ነው የምፈልገው…እባክህ ወንድሜ መልሰህ ጥለሀኝ አትሂድ
..ዳግመኛ እሰደዳለሁ ካልከኝ..በጣም ነው የማዝነው..እራሴንም መቼም ይቅር አልለውም››
‹‹የምታወራው ምንም ሊገባው አልቻለም..እሱ የሚያወራው እሷን ስለማግባት እና አብሮ አንድ ቤት ስለመኖር…እሷ የምታወራው ስለእሱ ዳግመኛ መሰደድ…‹‹ድንገት ሳላውቅ ተመልሼ ሄዳለው ብያት ይሆን እንዴ ?››ሲል እራሱን ተጠራጠረ፡፡
‹‹ኪያ ምን ነካሽ…?ተመልሼ ሔዳለው ብዬሻለው…እንዴ..?››
‹‹አላልከኝም…ግን ወንድሜ በወላጆቻችን አጥንት ይዤሀለው፣ምንም ቢፈጠር ምንም ጥለኸኝ እንደማትሄድ ቃል ግባልኝ››

‹‹እሺ..እንዳልሽ ቃል ገባልሻለው…ምንም ቢፈጠር ምንም ተመልሼ በድጋሚ አልሰደድም፡፡››
‹‹ጥሩ….ማታ የምቀበለው እንግዳ መስፍን ነው››
የቤተሰቦቹን ሞት የሰማ ቀን እንኳን እንዲህ አልደነገጠም‹‹ምን ..?መስፍን….?ከየት…ወጭ አይደል እንዴ?››
‹‹አዎ..ለአለፉት ሁለት ሶስት ወራት ስንደዋወል ነበር..ችግሮቻችን ተነጋገርን ለመፍታት እና የተበላሸውን ግንኙነታንን ለማስተካከል ወስነን አሁን እየመጣ ነው…ዛሬ ሁለት ሰዓት ነው የሚገባው..ቀጥታ ከቦሌ እኔ ነኝ የምቀበለው..እየመጣ መሆኑን ቤተሰቦቹም አያውቁ..ማለቴ ከቦሌ ቀጥታ ወደቤት ነው ይዤው የምመጣው..ልጅንም በጣም ናፍቆል..እና ተነጋግረን ችግሮቻችንን መቅረፍ ከቻልን ነገሮች ወደድሮ ቦታቸው ይመለሳሉ ማለት ነው..ያው ታውቃለህ የፍቺው ጉዳይ ገና ፕሮሰስ ላይ ነው…ያ ማለት አሁንም በህግ ፊት ባልና ሚስቶች ነን››
ድንዝዝ ባለ ስሜት ንግግሯን እስክትጨርስ ዝም ብሎ አዳመጣት…በፍጽም ፀጥታ ነው የተቀመጠው…ሰውነቱ አይንቀሳቀስም…የአይኖቹ ቅንድቦች እንኳን መንቀሳቀስ አቁመው ነበር፣ትንፋሹ መተንፈስም እንዳቆመ አይነት የመታፈን ስሜት እየተሰማው ነው…ንግግሯን ካጠናቀቀች በኃላም እሱ በዝምታው እንደቀጠለ ነው፡፡
ግራ ገባት…የሆነ ነገር እንዲል እየጠበቀችው ነው…እንዲወቅሳት..እንዲረግማት….በእሷ እንዲያማርር እየጠበቀች ነው..እሱ ግን እንደዛ እያደረገ አይደለም…አስፈሪ ዝምታ ላይ ነው፡፡
‹‹ወንድ….ሜ››
‹‹ሂሳብ ክፈይና እንሂድ››ብሎ መኪናውን ቁልፍ ከጠረጴዛ ላይ አነሳና ቀመ ..ወደመኪናው መራመድ ጀመረ…ከቦርሳዋ ብር አውጥታ ጠረጴዛ ላይ ወረወረችና ፈጠን ብላ ከኃላው ተከተለችው፡፡በህይወቱ እደዛሬው ባዶነትና ተስፋ ቢስነት ተሰምቶት አያውቅም..ፍፅም ተስፋ መቁረጥ ማለት ምን ማለት እንደሆነ የገባውም ዛሬ ነው..በቃ መቼም ይህቺን ሴት ማግባት እንደማይችል አምኖ ተቀበለ…ባያገባትም ግን መቼም ደግሞ ማፍቀሩን እንደማያቆም ያውቃል፡፡

እቤት አድርሷት ብዙም ሳይቆይ ነው ወደቤቱ ያመራው፡፡የሚኖረው ወላጀቹ ቤት ነው ሁሉም ወንድሞቹ የራሳቸውን ህይወት መስርተውና የገዛ ቤታቸውን ሰርተው ቤቱን የለቀቁት ገና ወላጆቹ በህይወት እያሉ ነው፡፡እህቱም ሀገር ውስጥ አትኖርም አሁን በብቸኝነት እየኖረበት ያለው እሱ ነው፡፡ወደቤት ሲገባ ሙሉ ጠርሙስ ጎርደን ጅን ይዞ ነበር የገባው….ገና በቀኑ ነው መኝታ ቤቱን ዘግቶ መጠጣት የጀመረው…
ማታ አንድ ሰዓት ሲሆን ጥንብዝ ብሎ ሰክሮ ነበር‹‹ይሄን ያንን ጉረኛ ልትቀበለው ቦሌ አየር ማረፊያ ቆማ ብርድ እያንቀጠቀጣት ነው››አለ..አሳዘነችው…‹‹ለእሷ የምገባት እኔ ነበርኩ….››ማልቀስ አማረው..እዬዬ ብሎ ማልቀስ አማርው..ግን ማድረግ አልቻለም፡፡ስልኩን ከኪሱ አወጣና ‹‹ማውራት ከቻልሽ ደውይልኝ ››ብሎ ፃፈና ለከ..
ከ5 ደቂቃ በኃላ ተደወለለት‹‹ወይ እግዜር ይስጥሽ…አትደውይልኝም ብዬ ፈርቼ ነበር››
‹‹ምነው? ችግር አለ እንዴ…?ወላጆቼ ምን ሆኑ?››
‹‹‹እነሱ ሰላም ናቸው..በጣም ሰላም ናቸው…ዛሬ አዲስ አበባ ተመልሰናል..እነሱም እቤታቸው ናቸው….እኔ ግን…››ሲያወራ አፉ ይኮለታተፋል..
‹‹ምነው ?አንተ ምን ሆንክ?››
‹‹ተሰብሬለሁ…ሌላ ማወራው ሰው ስለሌለን ነው አንቺ ጋር የደወልኩት…አይገርምም ደህና ጓደኛ እንኳን የለኝም….ቢኖረኝም እንዲህ አይነት ነገር የምነግራቸው አይደሉም››
‹‹ወይኔ በፈጣሪ..እስኪ የሆንከውን ንገረኝ…?.››
‹‹በፀሎት…››
‹‹ወዬ››
‹‹አሁን ካለሽበት መጥተሸ አጠገቤ ብትሆኚና ብታጣጪኝ ደስ ይለኝ ነበር››
‹‹እኔም ደስ ይለኝ ነበር…እይዞህ አንተ ብዙ ነገር የምታውቅ ሰው አይደለህ..?››
‹‹ማወቅ ምን ይሰራል…በፍቅር ስትንኮታኮቺ እኮ ያንቺ ማወቅ እርባነ ቢስ ነው፡፡እኔ እንደውም ይሄንን የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ የሚባለውን ጫወታ መተው አለብኝ..አዎ ፍቃዴን መልሼ ቢሮዬን ዘጋለሁ…››

‹‹ለምን ..ያ ደግሞ ምን ማለት ነው?››
‹‹አይታይሽም እንዴ…ከልጅነቴ ጀምሮ ሳፈቅራት የኖርኳትን ሴት የሆነ ዘዴ ተጠቅሜ እንድታፈቅረኝና እሺ ብላኝ እንድታገባኝ ማድረግ ካልቻልኩ እንዴት ነው ሌላ ሰውን ማገዝ የምችለው…ይሄው ለሁለተኛ ጊዜ አጣኋት …ያሁን ማጣት ደግሞ ይግባኝ የሌለው ነው…እራሴንም ሰዎችንም እያጭበረበርኩ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ፡፡›› ‹‹አይ..ያ እውነት አይደለም…ቤተሰቦቼን ምን ያህል እንዳገዝካቸው እኔ ነኝ ማውቀው..አረ የእነሱን ተወውና እኔን እራሱ በስልክ ብቻ በምታወራኝ ምን ያህል ጥንካሬና ብርታት እንደምትሰጠኝ አታውቅም..ፈፅሞ በምንም ምክንያት ተስፋ መቁረጥ የለብህም..ደግሞ አንድ ግንኙነት አልተሳካምና ጠቅላላ ያንተ ህይወት አበቃለት

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

22 Dec, 16:50


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያሁለት

ባልና ሚስቶቹን ቤታቸው ወስዶ እንደጣላቸው ቀጥታ የመኪናውን መሪ ወደአስቴር ቢሮ ነው የጠመዘዘው…ገብቶ ምሳ እንዲበላ ቢለምኑት እንኳን እሺ አላለቸውም፡፡እንደሚመጣ አልነገራትም ቀጥታ ከቢሮዋ ፊት ለፊት አቆመና ደወለ
‹‹ሄሎ ወንድሜ….እንዴት ነው ቢሾፍቱ በጣም ተመችታሀለች መሰለኝ?፡፡››
‹‹መጥቻለው….ምሳ አትጋብዢኝም?፡፡››
‹‹የእውነት መጣህ?››
‹‹አዎ ቢሮሽ ፊት ፊት መኪናዬን አቁሜያለው፡፡››
‹‹በቃ መጣሁ››ብላ ስልኩን ዘጋች….5 ደቂቃ ነው ያስጠበቀችው፡፡ገና የቢሮዋን የህንፃ ደረጃ ስትወርድ ጀምሮ ነው አይኑ ውስጥ የገባችው…ሙሉ ሮዝ ቀለም ያለው ጉረድ ቀሚስና ኮት ለብሳለች…ፀጉሯ ወደኃላዋ ትከሻዋ ላይ እንዲተኛ ተደርጎል…ውብ ሆናለች….መኪናዋን ስለምታውቃት ብዙም ሳትደነጋገር ቀጥታ ወደእሱ ነው ያመራችው…ይህቺ ሴት እህቱ እንድትሆን አይደለም የሚፈልገው…ጓደኛም እንድትሆነው አይደለም…የፍቅር አጋሩ ሚስቱ ሊያደርጋት ነው ምኞቱ..ይሄ ምኞቱ ደግሞ አሁን በቅርብ በውስጡ የበቀለ ስላልሆነ ህመሙ ቀላል አይደለም…ገና አፍ ፈቶ በኮልታፋ አንደበት መንተባተብ በጀመረበት በጮርቃነት እድሜው ጀመሮ እሷ ሚስቱ እንደሆነች ያስብ ነበር፣እርግጥ በዛን እድሜ ሚስት ማለት እራሱ ትርጉሙ ምን ማለት አንደሆነ አያውቅም ነበር፣ቢሆንም ጭላንጭል የሆነ ግንዛቤ ነበረው…ሚስት ማለት አንድ ክፍል ውስጥ አንድ አልጋ ላይ ሁሌ አብራ

የምትተኛ ሴት እንደሆነች ከአባትና ከእናቱ ግንኙነት መረዳት በቻለበት ጊዜ ነው፣ከእሱ ጋር ለዘላለም መተኛት ያለባት ሴት አስቴር እንደሆነች ወስኖ የነበረው፣በዛን የልጅነት ጊዜ እናቷ የቤታቸውን እንጀራ ልትጋግር ስትመጣ አስከትላት ስትመጣ ጀምሮ እዛው እሷን ማስቀረት ምኞቱ ነበር…እና ያ ምኞት ግለቱን ጠብቆ እየፋመ ነበር የቀጠለው…
ጊዜው ሲደርስ ግን ነገሮች ቀደም ብሎ እንዳሰባቸው ቀላል አልነበሩም…ገቢናውን ከፈተላት ገባች.. ጉንጩን አገላብጣ ሳመችው…ሁል ጊዜ የእሷ መሳም ከሌላው መሳም በጣም ይለይበታል…ወፈር ብሎ ወደፊት ግልብጥ ያለው ፍም ከንፈሯ ሰውነቱ ላይ ሲርፍ የተለየ ሙቀት ነው ሰውነቱ የሚያመነጨው…ልክ የጋለ ቢላዋ አካል ላይ ሲያርፍ የሚሰማው አይነት ትሽሽሽ..የሚል የማቃጠል የመለብለብና የመላጠ ስሜት……
‹‹አንተ ወፍረህ ነው የመጣሀው….ስራ ላይ ነበርክ ወይስ ጫጉላ ሽርሽር ላይ?››
‹‹በይው…አንቺም ተመችቶሻል…ምሳ የት አንብላ?››
‹‹ወደ እኔ ቤት ንዳው››
‹‹ምነው ከሰዓት ስራ የለሽም እንዴ?››
‹‹ዛሬ ቅዳሜ እኮ ነው…ግማሽ ቀን ነው የምንሰራው››
‹‹እና አራበሽም ..በልተን ብንሄድ አይሻልም?››
‹‹አይ ሰራተኛዬ አዘጋጅታ እየጠበቀችን ነው…ዘና ብለን ቤታችን ብንበላ ይሻላል….ወንድሜ ስለመጣህ ደስ ብሎኛል››
‹‹እኔም ከሰዓት ስራ ስለሌለሽ ደስ ብሎኛል››ብሎ መኪናዋን ወደ አስፓልት መሀል አስገባና ነዳት….የእውነትም ከሰዓት ስራ የለኝም ብላ ወደቤቷ ይዛው እየሄደች በመሆኑ ከፍተኛ ደስታ ተስምቶታል…ከአመታት በኃላ መልሶ ዛሬ እድሉን ይሞክራል፡፡አዎ በስደት ከሄደበት ባእድ ሀገር ተመልሶ የመጣውም ለዚሁ ነው፡፡ከባሎ እንደተለያየችና እሱም በዛ ንዴት ከሀገር ውጭ መሰደዱን ሲሰማ ነው ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ የመጣው…አንሆ ተመልሶ በመጣበት ባለፉት ስድስት ወሮች እሷን ከገባችበት ድባቴ እንድትወጣና ያልተሳካ ትዳሯ ከፈጠረባትን የስነልቦና መሰበር እንድታገግም እንደወንድም እንደ ጓደኛም ከዛም አልፎ እንደባለሞያም  ከጎኗ  ሆኖ  ሲያግዛትና  ሲደግፋት  ነበር…አሁን  ግን  ልቧ  ሌላ  ፍቅር

ለማስተናገድ ዝግጁ ነው ብሎ ያስባል..በዛ ላይ የእሱ እና የእሷ ፍቅር አዲስ ዛሬ የበቀላ ሳይሆን ድሮ በየሁለቱም ልብ ተዳፍኖ ያለ ነው…አሁን ያንን መቆስቆስና መልሶ እንዲቀጣጠል ትንሽ የፍቅር ቤንዚል ማርከፍከፍ ነው…ለዚህ ድርጊት ያበረታታው ሰሞኑን ያየው በአቶ ሃይለልኡል እና በወ.ሮ ስንዱ መካከል የተከሰተው የፍቅር ግርሻ ነው፡፡
‹‹አዎ…አስቴርን አገባታለሁ…ከበፊት ባሏ የወለደችውን አንድ ልጅም እንደልጄ አድርጌ አሳድገዋለው››በውስጡ አልጎመጎመ…‹‹እና በቅርብ ቀን እሷም ወንድሜ የምትለውን ጥሪ ትተውና ባሌ ብላ ትጠራኛለች…ልጇም አጎቴ ብሎ የሚጠራውን አቁሞ አባቴ እንዲለኝ
አደርጋለው››ይሄንን ስላሰበ ብቻ ውስጡ በደስታ ተፍነከነከ..ቤት ሲደርሱ እውነትም እንዳለችው ቆንጆ ምሳ ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው፡፡እየተጎራረሱ በሉ፡፡ከምግብ በኃላ ብና ተፈላላቸው..እሷ ሁለት ሲኒ እሱ አንድ ሲና ጠጡና ተጠናቀቀ፡፡
‹‹እዚሁ ልንገራት ወይስ ይዣት ወጣ ልበልና ዘና ያለ ቦታ ወስጄ ዘና ባለ ስሜት ላይ ከሆነች በኃላ ልንገራት ››እያለ ሲወዛገብ ቆየና‹‹እ…ፕሮግራማችን እንዴት ነው….?ወጣ እንበል ወይስ እዚሁ ነው የምንቆየው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ…ወጣ እንላለን..ሱፐርማርኬት ወጥቼ መሸማመት አለብኝ..መጠነኛ ድግስ ደግሳለው፣ማታ እንግዳ አለብኝ››
ንግግሯ ግራ አጋባውም.. ደነገጠም፡፡
‹‹የማታ እንግዳ ምን አይነት ነው?›› our
‹‹አንተም አለህበት…ዛሬ እዚህ ነው አይደል የምታድረው?››
እሷ ጋር እንዲያድር ስለጠየቀችው ደስ ብሏታል ..ግን እንግዳውስ…?ለመሆኑ ማን ነው
…?ሴት ነው ወንድ?፡፡‹‹እሺ ..እዚህ ነው የማድረው…ግን እንግዳውስ?››
‹‹እንግዲህ እሱን ከመጣ በኃላ ነው የምናውቀው…ልደር ካለ ግን እምቢ ማደር አትችልም የምለው አይነት ሰው አይደለም››በማለት ግራ አጋቢ መልስ ሰጠችው፡፡መልሷ ይብልጥ ቁርጠት ለቀቀበት…ይሄኔ ከመስሪያ ቤቷ ባለደረቦች አንዱ ነው….ሀለቃዋ ይሆን እንዴ…?ቢሆንስ ልደር ስላለ እንዴት እሺ ልትለው ትችላለች..?››ወይ ሴቶች ምን አይነት ቅኔ የሆኑ ፍጡሮች እንደሆኑ ሁሌ እንደደነቀው ነው፡፡ወንድም ሴትም በአንድ ላይ ሰው ተብሎ

መፈረጁ  አግባብ  አይደለም….አስተሳሰባችን  እምነትና  ፍላጎታችን  ምኑም  እኮ አይገናኝም››ሲል በውስጡ አብሰለሰለና..ነገሮች እስኪደርሱ ጠብቆ ለማየት ወሰነ…
‹‹ከዛ በፊ የተመቻቸ ጊዜ ካገኘው ነግራታለሁ…እንደውም ከማታው ፕሮግራሞ በፊት የእኔን ሀሳብ መስማት አለባት››የሚል ድምዳሜ ላይ ደረሰ‹‹በቃ እንሂዳ››አላት፡፡
‹‹እሺ፣ተነስ ብላ ቦርሳዋን አንጠለጠለችና ተነሳች..ተያይዘው ወጡ ..ያለችው ሱፐር ማርኬት ይዛው ከገባች በኃላ ምትፈልገውን ነገሮች ሁሉ ተገዝተው በመኪናው ከተጫኑ በኃላ.. ማኪያቶ እንጠጣ ብሎ አንድ ፀጥተኛ ካፌ ይዞት ገባና..ፊት ለፊት እንደተቀመጡ እንደምንም እራሱን አጠንክሮ ወደነጥብ መንደርደር ጀመረ
‹‹ለምን ወደውጭ እንደሄድኩ ታውቂያለሽ አይደል?››
‹‹ሁለተኛ ዲግሪህን ለመማር ነዋ››
‹‹አይ ያማ ሽፋን ነው….እውነተኛ ምክንያቴን አንቺም በደንብ ታውቂዋለሽ..ወደውጭ የሄድኩት ባንቺ ተበሳጭቼ ነው፡፡››
‹‹አንተን ለማበሳጨት ብዬ ግን ምንም ያደረኩት ነገር የለም››
‹‹እሱን ማግባት አልነበረብሽም››
‹‹ለምን …ታዲያ አንተን ወንድሜን ማግባት ነበረብኝ?››
‹‹ምን ችግር አለው?እርግጥ እንደወንድምና እህት አንድቤት አድገናል..ግን የስጋ ትስስር አልነበረንም›

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

21 Dec, 16:04


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያአንድ

ተካ አቶ ኃይለልኡል ባዘዙት መሰረት ሽጉጡን ሙሉ ጥይት ሞልቶ ወገቡ ላይ ከሸጎጠ በኃላ አጉሊ መሳሪያ ያዘና  ማንን ሳያስከትል ቀጥታ መኪና ውስጥ ገብቶ ወደ ቃሊቲ ነዳው….የሰውዬውን ጥርጣሬ ምንም አልተዋጠለትም…‹‹ልጅቷ ስንት አማራጭ እያላት እንዴት እዛ ጭንቁርቁስ ቤት ከጭርቁስቁስ ሰዎች ጋር ለመቆየት ታስባለች? ››ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡ ሊዋጥለት አልቻም…፡፡

በፀሎት ከጠፋችበት ቀን አንስቶ በመላ ሀገሪቱ ፍላጋ የተሰማሩትን በመቶ የሚቆጠሩ ግለሰቦችን የሚመራው ..መረጃ የሚቀበለው አዲስ ቦታ ስምሪት የሚሰጠው እሱ ነው፡፡እና የእሱ እቅድ የሆነ ቦታ መኖሯን በሆነ መንገድ ቀድሞ ቢደርስበት እንደምንም ብሎ የራሱ ሰው በሚስጥር እንዲያገኛት አድርጎ በእጅ አዙር 5 ሚሊዬኑን የሽልማት ገንዘብ ለመቀባበል አቅዶ ከልቡ እየሰራ ነበር...እርግጥ እንደዚህ እያደረገ መሆኑን ቀድመው ቢደርሱበት ያለምንም ማቅማማት ግንባሩን በጥይት እንደሚነድሉት እርግጠኛ ነው…ግን በህይወት የተሻለ ነገር ማግኘት ሪስክ መውሰድ የግድ እንደሆነ የሚያምን ስለሆነ ነገሩን ልክ እንደቁማር ነው ያየው..‹‹ወይ በላለሁ..ወይ ደግሞ እበላለው››ብሎ ነበር ውሳኔ ላይ ደርሶ በተግባር ሲንቀሳቀስ የከረመው፡፡…አሁን ሰውዬው እንደሚሉት ልጅቷ የገመቱት ቦታ የምትገኝ ከሆነ ያ ሁ እቅዱ ውሀ በላው ማለት ነው፡፡ቦታውን ራሳቸው ቀድመው አውቀው ስለነገሩት ሽልማት የሚሰጡበት ምንም ምክንያት የለም….መኪናውን ወደእዛ ሲያሽከረክር በውስጡ በፀሎት የተባለው ቤት በፍፅም እንዳትገኝ እየፀለየ ነበር፡፡እንደደረሰ ከመንገድ ማዶ አስፓልት ጠርዝ ላይ መኪናውን ፓርክ አደረገና የመኪናው መስኮት በከፊል ከፍቶ ማጊሊያ መነፅሩን ወደእነ አቶ ለሜቻ ግቢ አነጣጠረና ገቢ ወጪውን መመልከትና በመሀከልም የተለየ ነገር ያገኘ ሲመስለው በሞባይሉ ፎቶ ማንሳት ጀመረ…
ስራ የጀመረው ከጥዋቱ 5 ሰዓት አካባቢ ቢሆንም እሰከ 10 ሰዓት ሁለት ሶስት ጊዜ አሮጊት ሴት ስትወጣ ስትገባ ከማየት ውጭ በግቢው ውስጥ አይን የሚስብ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አልነበረም…ሰዓቱ እየረዘመ ሲሄድ ተስፋ እየቆረጠና እየተሰላቸ መጣ…ለዛሬ ይበቃኛል ብሎ 11 ሰዓት ላይ አካባቢውን ለቆ ወደቤቱ ሄደ ..
በማግስቱ በጥዋት ማለዳ አንድ ሰዓት ላይ ነበር የመጣው፣እና ሁለት ሰዓት ላይ የሚፈልገውን አገኘ ..ደጋግሞ ፎቶ አነሳው…በቤቱ አንድ ሴት ልጅ ብቻ እንዳላቸው አጣርቷል ..አሁን እየገቡ እየወጡ ያሉት ግን በተቀራራቢ እድሜ ላይ የሚገኙ ሁለት ወጣቶች ናቸው፡፡አንደኛዋ የቤቱ ልጅ እንደሆነች እርግጠኛ ነው…ሁለተኛዋ ግን የሚፈልጋት የባለፀጋው ቅምጥል ልጅ ትሁን አትሁን መለየት አልቻለም…የለበሰችው ልብስ የተለመደ አይነት ነው..በዛ ላይ ፊቷን ጭንቅላቷን ጭምር በሻርፕ ሸፍናለች…ዝም ብሎ ከመኪናው በመውረድና በእግሩ ወደ አጥሩ በመጠጋት ከቅርብ ርቀት በርከት ያለ ፎቶ አነሳና ለአቶ ኃይለ ልኡል ላከላቸው፡፡

አቶ ኃይለልኡል በዚህ ጊዜ ከባለቤታቸው ጋር በሰለሞን በሚሾፈር መኪና ከቢሾፍቱ ወደአዲስ አበባ እየተመለሱ ነበር፡፡ስልካቸው ድምፅ ሲያሰማ ከኪሳቸው አወጡና ተመለከቱት..መልዕክት መሆኑን ሲያዩ ከፈቱት…አይናቸው ተጉረጠረጠ….
‹‹እራሷ ነች ..ልጄ እራሷ ነች….ከጎናቸው ያለችው ሚሳታቸው ላይ ተጠመጠሙና ጉንጮቾን አገላብጠው ይስሙ ጀመር››
‹‹እንዴ ኃይሌ ምን ተፈጠረ..?ምን ተገኘ..አረ ንገረኝ?››
‹‹ይሄውልሽ..እንቺ እይው..ፊቷን ብትሸፋፈንም እራሷ ነች፡፡››ወይዘሮ ስንዱ ስልኩን ከባላቸው እጅ ተቀበሉና አፍጥጠው ተመለከቱ…..ከባላቸው በበለጠ በመደነቅ ኡኡ.አሉ…መኪናዋን በእልልታ አደባላለቁት…ሰለሞን የነገሩ ውል ስላልገባው መሪውን ጠመዘዘና የመንገዱን ዳር አስይዞ መኪናዋን አቆማት…በራፉን ከፍተው ወረዱ….እሱም ተከትሏቸው ወረደ‹‹አረ ለእኔም ንገሩኝ ምንድነው? እንዲህ የሚያስፈነጥዝ ደስታ፡፡››
‹‹ልጃችን የት እንዳለች አወቅን..እያት ተመልከት››ስልኩን ከሚስታቸው ተቀበሉና ለሰለሞን አቀበሉት..አንድ ፊቷ በቅጡ የማይታይ ወጣት ፎቶ ነው…ግን በፀሎት እንደሆነች ወዲያው ነው ያወቃት..ሙሉ ፊቷን ሳያይ እሷ እንደሆነች አንዴት እንዳወቀ አልገባውም…››
‹‹አየህ …ልጃችን እራሷ ነች…ሰው እንዳይለያት ነው ፊቷን የሸፋፈነችው……››
‹‹ለመሆኑ የት ነው ያለችው?››ጠየቀ ሰሎሞን፡፡
‹‹የት እዳለች ቆይ ነግራችኃላው››ብለው ስልኩን ተቀበሉና ደወሉ
‹‹ሄሎ….ፎቶው ደርሶኛል፡፡››
‹‹አዎ ሳስበው እሷ ትመስለኛለች››
‹‹አዎ እሷ እራሷነች…ከቦታው እንዳትንቀሳቀስ..እዛው ጠብቀን…ከቢሾፍቱ እየተመለስን ስለሆነ ከ15 ደቂቃ በኃላ ያለህበት እንደርሳለን››
‹‹ወጥታ ከሄደችስ…?ላስቁማት››
‹‹አይ..ልጄን ቀጥታ እኔው ነኝ የማገኛት..እንዳታስቆማት ትደነግጥብኛለች…ከቤት ከወጣች ዝም ብለህ በርቀት እየተከታተልክ ያለችበትን ታሳውቀኛለህ፡››

‹‹እሺ..ጌታዬ እንዳሉት አደርጋለው››
‹‹ጎበዝ ..እንዳስደሰትከኝ አስደስትሀለው…ቆንጆ ጉርሻ ይጠብቅሀል ››
‹‹እሺ ጌታዬ››ስልኩን ዘጉና‹‹በሉ ጊዜ አናባክን ..ግቡና እንሂድ››
‹‹እንዴ የት አንዳለች ንገረን እንጂ……?››ወ.ሮ ስንዱ ጠየቁ
‹‹ስንድ ልጃችን ሰዎቹ ጋር ነው ያለችው….››
‹‹የትኞቹ ሰዎች››
‹‹እነአቶ ለሜቻ ጋር..ማለቴ የልብ ለጋሾ ቤተሰብ ጋር ነው ያለችው››
‹‹ወይ ጉዴ….አሁን ምንድነው የምናደርገው?››እያሉ ወደመኪናው ገቡ፡፡ አቶ ኃይለልኡልም ተከትለዋቸው ገቡ….ሰለሞን በሰማው ያልተጠበቀ ነገር ግራ እንደተጋባና ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰላሰለ ገቢና ገባ፡፡ መኪናውን አንቀሳቀሳት…ባልና ሚስቶቹ በደስታ ሰክረው እሱን ከቁብ ሳይቆጥሩት እርስ በርስ በፈንጠዝያ ሲጎሻሸምና ሲሳሳሙ እሱ ምን ማድረግ እንዳለበትና ይሄንን ያለጊዜው ያጋጠመውን ነገር እንዴት እንደሚፈታ እያሰላሰለ ነበር የሚነዳው….
አቃቂ አቶ ለሜቻ ቤት ለመድረስ 500 ሜትር ያህል ሲቀራቸው የመኪናውን መሪ ወደግራ ጠመዘዘና ፊት ለፊት ከሚታየው ሆቴል ይዞቸው ገባ..ባልና ሚስቶቹ በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ
‹‹ሰለሞን…ምን እያደረክ ነው?››አቶ ኃይለልኡል ጠየቁ፡፡
‹መነጋገር አለብን››
‹‹ስለምን?››
‹‹አሁን ልጃቹህ ጋር ከመሄዳችሁ በፊት አረፍ ብለን መነጋገር አለብን››
‹‹ምን መነጋገር ያስፈልጋል…?በቃ እኔና እናቷ ሄደን ልጃችንን ወደቤት ይዘን እንሄዳለን….እንደምታየው  አሁን  ሁሉ  ነገር  ውብ  እና  የተስተካለከለ  ነው..አይዞህ

አታስብ…ከንተጋር  ያለንን  ነገር  እንቀጥላለን..ከሶስት  ቀን  በኃላም  ወደአልከው  ቦታ ትወስደናለህ››
መኪናውን  አቆመና  ሞተሩን  አጥፍቶ  ወደኃላ  ዞረ..ፊት  ለፊት  እያያቸው‹‹ይሄ  ነገር እንደምታስብት ቀላል ይመስላችኃላ?››
‹‹ማለት?››
‹‹አሁን ያለችበት ቤት ሄደችሁ በማንኳኳት..ነይ ልጄ በቃ አግኝተንሻል አሁን ወደቤትሽ ተመለሺ ብትሏት ..እሺ ብላ በደስታ ዘላ የምትጠመጠምባችሁ ይመስላችኃላ…እምቢ መሄድ አልፈልግም ብትል ምን ታደርጋላችሁ ?በግድ በጎረምሳ አሳዝላችሁ መኪና ውስጥ በመክተት ወደቤት ትወስዷታላችሁ….?ከዛስ..?አንድ ክፍል ውስጥ ቆልፋችሁባት በራፍ ላይ ሁለት ጠብደል ጠባቂ ታቆማላችሁ?እስኪ ንገሩኝ ምንድነው የምደርጉት?› በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ‹‹በእውነት እምቢ ብትለን ምንድነው የምናደርገው?›ወ.ሮ ስንዱ በተሰበረ ድምፅ ባላቸውን ጠየቁ፡፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

21 Dec, 16:04


አቶ ኃይለልኡልም እጅ በሰጠ ድምፅ‹‹አንተ ምን ብናደርግ ትመክረናለህ?››ሲሉ እሱኑ መልሰው ጠየቁት፡፡
‹‹ይሄውላችሁ እንደእኔ እንደእኔ በፀሎት ወደቤት መመለስ ያለባት በእናንተ ላይ የነበራት ቅሬታ ሙሉ በሙሉ ተቀርፎ…ሁሉን ነገር በራሷ መንገድ አረጋግጣና ፈቅዳ…ደስ ብሎት ነው
…ይሄውላችሁ አሁን አብዛኛውን አስቸጋሪ የነበረውን መንገድ ተጉዛችኃላ …እስኪ አስቡት ከአስራአምስተ ቀን በፊት ወደቢሾፍቱ ስንሄድ አንድ መኪና ውስጥ መቀመጥ እራሱ የሚቀፋችሁ ሰዎች ነበራችሁ፣ትዝ ይላችኃላ ጋሼ ገቢና ነበር የተቀመጥከው…አሁንስ ይሄው በደስታ ጎን ለጎን በራሳችሁ ፍቃድ ተቀምጣችሁ እርስ በርስ ተጣብቃችሁ የደስታ ወሬ እያወራችሁ ትሳሳቃላችሁ..ከባዱ ነገር እናንተን እዚህ ስሜት ላይ ማድረስ ነበር…ከአሁን ወዲህ ያለው ይሄንን ግንኙነት መሰረት እንዲይዝና ስር እንዲሰድ ማድረግ ብቻ ነው… ያ ደግሞ ቀላል ነው…ቢያንስ 15 ቀን መታገስ ያቅታችኃላ….?፡፡››
‹‹እና ባለችበት ትቀመጥ እያልክ ነው…?ያለችበት ሁኔታ… እቤቱ የሰዎቹ ኑሮ ምኑም አይመቻትም እኮ…››
ከቀናት በፊት ስላለችበት ቤት ሲጠይቃት ያለችው ነገር ትዝ አለውና ፈገግ አለ፡፡

‹‹እውነቴን ነው..እርግጥ ሽማግሌው በጣም ጥሩና ደግ ሰው ናቸው….ቢሆንም ኑሮቸው ከእጅ ወደአፍ ነው..ልጄ ከቤት ስትወጣም ደህና ብር እንኳን ይዛ አልወጣችም››
‹‹አይዞችሁ እስከዛሬ ድምጻን አጥፍታ ኖረች ማለት በጣም ቢመቻት ነው….ደግሞ እንዳላችሁ ባይመቻትም ለ15 ቀን ምንም አትሆንም፡፡አለመመቸትን ማጣጣም በቀጣይ ለሚመጣ መመቸት መደላደል መፍጠር ነው፡፡››
‹‹እሺ ቢያንስ እንሄድና ከሩቅም ቢሆንም እንያት››
‹‹እንደእሱ ይቻላል››አላና ያጠፋውን የመኪና ሞተር አስነሳው፡፡
ሰለሞን መኪናውን ነዳና  ከተካ መኪናው ፊት ለፊት አቆመ….ተካ መኪናውን ከፊቷ ወጣን ወደእነሱ መጣ ..ሰለሞን የገቢናው በራፍ ከፈተለት ……ገባና ቁጭ አለ››
ወደኃላ ዞረና…..‹‹አሁንም ውስጥ ነች…እንዴት ነው ምናደረገው? ››
‹‹ቆይ እስኪ ተረጋጋ ስትወጣ እንያት….››ሁሉም አይናቸውን የግቢው መውጫ መግቢያ ላይ ተከሉ….በርከት ያሉ ሴቶች ሲወጡ ሲገቡ ይታያል፣››
‹‹ምንድነው ብዙ ሰዎች ይታያሉ… ችግር አለ እንዴ?››አቶ ኃይለ ልኡል ጠየቁ፡፡
‹‹አይ ጌታዬ ችግር የለም… እኔም በመጀመሪያ ግራ ገብቶኝ ነበር…ስጠይቅ ግን ፣ሰዎቹ ነገ የማሪያም ፅዋ ማህበር አለባቸው ..የድግሱ ስራ ለማገዝ የመጡ ጎራቤቶች ናቸው››
‹‹እ …እንደዛ ነው….››በፀሎት ወጥታ ከሩቅ ለማየት ከአንድ ሰዓት በላይ በትዕግስት መጠበቅ ነበረባቸው….ግቢ ውስጥ ካለ የማንጎ ዛፍ ስር ቆማ ከአቶ ለሜቻ ጋር እየተሳሳቀች ስታወራ ነበር የተመለከቱት…ሁለቱም ወላጆች ሄደው ልጃቸው ላይ ለመጠምጠም የሚተናነቃቸውን ስሜት በመከራ ነበር የተቆጠጠሩት፡፡ሁለቱም ስሜታዊ ሆነው እንባ አውጥተው እስከማልቀስ ደርሰው ነበር፡፡
‹‹አሁን በቃ ይበቃናል…ከዚህ በላይ እዚህ ከቆየን  ራሳችንን ማጋለጥ ይሆናል…ድንገት እዚህ እንዳለች እንደደረስንባት ካወቀች….ቦታ ለመቀየር ታስብና ዳግመኛ አድራሻዋን ትሰውርብን ይሆናል፡፡››ሰለሞን ነው የተናገረው፡፡
‹‹አዎ ትክክለ ነህ….እንዴት ነው ምናደርገው ታዲያ? እሱ እዚሁ ይጠብቃት አይደል…?››.

‹‹አይ ምንም ጠባቂ አያስፈልግም…ባይሆን በየቀኑ እየመጣ ለተወሰነ ደቂቃ ሰላም መሆኗን ብቻ ካረጋገጠ ይበቃል፣አሁን ሁላችንም ነን አካባቢውን መልቀቅ ያለብን፡፡››ሰለሞን ቁርጥ ያለ ውሳኔውን አስተላለፈ…የተቃወመው ወይም የተከራከረው አልነበረም፡፡
‹‹እሺ ይሁን …..በቃ ተካ አንተም ወደቤትህ ሄደህ እረፍ …ነገ ደውልልሀለው››ብለው አሰናበቱት…‹‹እሺ ጌታዬ እንዳሉ››ብሎ ገቢናውን ለቆ ወረደና ወደአቆማት መኪና ተንቀሳቀሰ…..ሰለሞንም ባልና ሚስቱን ይዞ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተፈተለከ….

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

20 Dec, 16:35


ጥቅም አልባ ነው። ለፍቅረኛ ወይም ለትዳር አጋር የሚኖር አክብሮት ጥልቅና ሩቅ መሆን አለበት። ከልብ የመነጨ ብቻ ሳይሆን ከነፍስም የተጨለፈ መሆን አለበት።ሚስት ለባሏ ሚስት ብቻ አይደለችም..የሴት ጓደኛ…የእናት ምትክ ዘመድ ጭምር መሆን አለባት..ባልም ለሚስቱ ወንድ ጓደኛ..ከዛም አልፎ የአባት ምትክ ዘመድ መሆን አለበት፡፡የማወራው ግልፅ ነው አይደል?››
‹‹አዎ ..በጣም ግልፅ ነው..ቀጥል››

ትንፋሽ ወስዶ ከንፈሩን በምራቁ አረጠበና ንግግሩን ካቆመበት ቀጠለ‹‹…ከቤት ወጥታችሁ ስትለያዩ የሚኖር ሽኝት እና ከውጭ ውላችሁ ስትመለሱ እርስ በርስ የሚኖር የሞቀ አቀበል በጣም ወሳኝ ኩነት ነው።ተሳሳሞ ደህና ዋል..ደህና ዋይ ተባብሎ መለያየት እና ሲገናኙ እንዴት ዋልሽ…?እንዴት ዋልክ? ተባብሎ በናፍቆት መሳሳም በመሀከል ያለን ግንኙነት ያደረጃል ፍቅርም ግለቱን ጠብቆ እንዲጓዝ ያግዛል።በመጨረሻው ሚቻላችሁ ከሆነ እቤት ከገባችሁ  በኃላ  ለተወሰነ  ሰዓት  ስልክ  የሚጠፋበት  እና  ቲቨ  የሚዘጋበት  ልዩ የሆነ የቤተሠብ የጋራ የመጫወቻና የመወያያ ሰአት ቢኖር እንደቤተሠብ ለሚኖር መስተጋብር ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል።
‹እና ሌላው ልጃችሁ ላይ ያላችሁ አቋም ትልቅ ማስተካከያ ሊደረግበት ይገባል፡፡››
‹‹ማለት?››
‹‹በፀሎት ነገሮች ተስተካክለው ወደቤት ስትመለስ..ለምሳሌ ስትወጣ ስትገባ በጋርድ እንድትጠበቅና እንድታጀብ ማድረግ አይገባችሁም..እንደማንኛውም ሰው በነፃነት ከፈለገችው ሰው ጋር ወጥታ ከፈለገችው ጋር የመመለስ መብት ሊኖራት ይገባል፡፡››
‹‹ሰለሞን እዚህ ላይ አንድ ያልገባህ ነገር አለ…እኔ እኮ ልጄን በጋርድ ማስጠብቀው ወድጄ አይደለም…..ልጄ ልብ በሽተኛ ነኝ..የልብ ንቅለ ተከላ ተደርጎላታል …በጣም ጥንቃቄ የምትፈልግ ልጅ ነች..ድንገት መንገድ ላይ ወድቃ አጉል እንዳትሆንብኝ ስለምሰጋ ነው ዘወትር ሰዎች በዙሪያዋ እንዲሆኑ የማደርገው፡፡››ሲሉ ተቃውሞቸውን ያሰሙት አቶ ኃይለልኡል ናቸው

‹‹ቢሆንም ለዛ መፍትሄው ያ አይደለም….ይሄ የልጅቷን ነፃነት ከመንፈጉም በላይ በራስ የመተማመን ችሎታዋን በጣም ይጎዳዋል…በየሄደችበት በሰው መጠበቅ የመታፈን ስሜት እንዲሰማት ነው የሚያደርጋት፣እና የእዛ ውጤት ደግሞ እንዲህ አሁን እንዳደረገችው ራሷን ነፃ ለማውጣት አላስፈላጊ ጣጣ ውስጥ እንድትገባ ትገደዳለች››
‹‹ትክክል ልትሆን ትችላለህ …ግን ያው ነፃ ትሁን… ብቻዋን ትንቀሳቀስ ብዬ ከፈቀድኩላት አንዳንድ አላስፈላጊ ቦታዎች ትሄድና የማይሆን ነገር ትሰራለች፡፡››
‹‹ለምሳሌ የት?››
‹‹ይሄውልህ የልብ ንቅለ ተከላ ሲደረግላት ልብ የሰጠቻት ልጅ ቤተሰቦች እዚሁ አዲስ አበባ አቃቂ አካባቢ ነው የሚኖሩት ..ልጄ አሁን አሁን ተወች እንጂ በፊት ሰሞን ቀንና ሌት እዛ ካልወሰድከኝ እያለች ታስቸግረኝ ነበር፣..እኛ ደግሞ ከልጅቷ አባት ጋር ስንስማማ በምንም አይነት ከእኛ በአካል መገናኘት እንደማይፈልጉ ነው ያነገሩን..እሷ ቤታቸው ሄዳ ቢያገኟት ልጃቸውን ስልምታስታውሳቸው ሀዘናቸውን ክፉኛ ትቀሰቅሳባቸዋለች.. እንደዛ አይነት ውለታ የዋሉልኝን ሰውዬ ደግሞ የማይፈልጉትን ነገር ማድረግ ላሳዝናቸው አልፈልግም..አንድ ለዛ ነው የማስጠብቃት››ንግግራቸውን እየተናገሩ ሳለ የሆነ እስከዛሬ ያላሰብት ገራሚ ሀሳብ በአእምሯቸው ብልጭ አለ….እንዴት እሰከዛሬ ትዝ ሊላቸው እንዳልቻለ ግራ ገባቸው‹‹ልጄ እነሱ ጋር ሄዳ ቢሆንስ?››ሀሳቡን በውስጣቸው አፍነው ያዙት፡፡
‹‹የልጃችሁን ደስተኝነትና ሳቅ የምትፈልጉ ከሆነ ለችግሮች ሁሉ ሌላ መፍትሄ አበጁላቸው..ደግሞ ለበፀሎት በግልፅ ነገሮችን ቢያስረዶት ይገባታል…ብስልና አስተዋይ የ22 ዓመት ወጣት ነች….ይልቅ እናንተ  በመሀከላችሁ ያለውን ችግር ፈታችሁ ሰላም ከሆናችሁና ስትወጣ ስትገባ የሚከታተላት ሰው መመደብ ካቆማችሁ የልጃችሁን ደስታና ሳቅ መመለስ ብቻ ሳይሆን መቼም መልሳችሁ አታጦትም››
ወ.ሮ ስንዱ መለሱ ‹‹እሺ እንዳልክ እናደርጋለን….ኃይሌ እንዲህ ማድረግ ያቅተናል እንዴ?››
‹‹አረ አያቅተንም..ችግር የለውም ሁሉን ነገር እኔ አስተካክለዋልው..አሁን ከፈቀድክልኝ ወደካማፓኒው አንድ አጭር ስልክ መደወል አለብኝ..ከባድ የስራ ጉዳይ ነበረ ..ምን እንዳደረሱት ልጠይቃቸው፡፡››

‹‹ችግር  የለም..በቃ  ጨርሰናል..አሁን  ለጥዋት  ጉዙ  እቃችንን  መሸካከፍ  መጀመር እንችላለን፡፡››
‹‹ጥሩ…››ብለው ቀድመው ከመቀመጫቸው ተነሱና  ወደክፍላቸው በመሄድ ስልካቸውን ካስቀመጡበት አንስትው በጀርባ በኩል ባለው በር ከቤት ወጡ….  ስልክ ደወሉ…
‹‹ስማ አቃቂ ለልጄ ልብ የሰጠቻት ልጅ ቤተሰቦችን ታውቃቸወላህ አይደል..?››
‹‹አዎ አውቀዋለው››
‹‹አሁኑኑ እዛ ሂድና ቀስ ብለህ ማንም ሳያይህ ወደቤታቸው የሚገባውንና የሚወጣውን ሰው ተከታተል…ከተቻለህ ሁሉንም ፎቶ አንሳ››
‹‹እሺ….ግን በቀጥታ ምን ለማጣራት ነው የምንፈልገው…?ነገሩን ማወቄ ስራዬን ያቀልልኛል››
‹‹አዎ….ምን መሰለህ..ለማንም እንዳትናገር..ልጄ ምን አልባት እዛ ቤት ተደብቃ ይሆናል የሚል ጥርጣሬ አድሮብኛል…እና ከአሁኑ ጀምረህ በቃ እስክልህ ደረስ እንዳልኩህ ተከታተለልኝ…እሷን በተመለከተ የሆነ ትንሽም ቢሆን ፍንጭ ካገኘህ ወዲያው አሳውቀኝ፡፡››
‹‹ስልኩን ዘጉና ኪሳቸው ውስጥ ከተው ወደውስጥ ተመለሱ …ወ.ሮ ስንዱ አልጋቸው ላይ አረፍ ብለው አገኞቸው ፡፡በራፉን ዘጉን የራሳቸውን አልጋ ትተው ወደባለቤታቸው ሄዱና ከጎናቸው ተቀመጡ፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

20 Dec, 16:35


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያ

‹‹አግብተሀል እንዴ?››
ድንገት ከርዕሳቸው ውጭ የሆነ ጥያቄ ስለጠየቁት ድንግርግር አለው፡፡
‹‹ለምን መሰለህ የጠየቅኩህ..?እንዲሁ ሳስበው አንተን ያገባች ሴት በጣም እድለኛ ትመስለኛለች….፡፡››
‹‹ምን አልባት ልትሆን ትችላለች ..እስከአሁን ግን አለገባሁምም አረ እንደውም ፍቅረኛም የለኝም››
ፈገግ አሉ….‹‹ሸክላ ሰሪ በገል ይበላልል›› አሉ…ብዙ ማወቅም እኮ መጥፎ ነው››
‹‹እንዴት?››
‹‹የምትፈልገውን ሁሉ የምታሟላ ሴት ለማግኘት በጣም ይከብድሀላ…ሁሉን ነገር አሟልታ ጥንቅቅ ያለች ሴት አታገኝም..በዛ እርግጠኛ ሆኜ ልነግርህ እችላለው…ግን ምትወድህና ምትወዳት ልጅ ሆና እራሷን ለመለወጥና ለማሻሻል የምትጥር ከሆነ በቂ ነው…አንተ ጎበዝ አንደበተ ርትኡ ባለሞያ ስለሆንክ መስመር ታስይዛታለህ››
እንዴት ብሎ መምከሩን ትቶ ተመካሪ እንደሆነ አልገባውም፡፡‹‹እሺ…የእናንተን ጉዳይ ከዳር ካደረስኩ በኃላ አስብበታለው….ምን አልባት እናንተ ትሆናላችሁ የምትድሩኝ…››
‹‹ለዛውም ድል ባለ ድግስ ነዋ››

‹‹እሺ..አሁን ይበቃናል…የምሳ ሰዓት ስለደረሰ ወደሳሎን እንሂድ››
‹‹አዎ ..ይበቃናል..ይሄኔ ኃይሌ ብቻውን ደብሮታል››
ፈገግ እለ ….. ከመቀመጫው ተነሳና ወደውጭ መራመድ ጀመረ…ወ.ሮ ስንዱም ተከተሉት፡፡


ከሳምንት በኃላ……..
በቢሾፍቱ ቆይታቸው በባልና ሚስቶቹ መካከል አስገራሚ የሚባል ለውጥ ነው የታየው፡፡ቢያንስ እረስ በርስ በመሀከላቸው ያለ ንግግር የጥሩ ጓደኛሞች መምሰል ከጀመረ ሰነባብቷል…ይሄ ለውጥ ሰለሞንን ይበልጥ እንዲበረታታ እና ሙሉ ኃይሉን ስራው ላይ እንዲያውል አግዞታል፡፡
‹‹እንግዲህ ዛሬ የመጨረሻ ቀናችን ነው ነገ ወደአዲስአባ እንመለሳለን…ሶስት ቀን እረፍት እንወስድና ምን አልባትም ለመጨረሻ ጊዜ ለሌላ 15 ቀን ወደሌላ መዝናኛ ቦታ እንሄዳለን፡፡በቀጣይ የምንሄድበት ከዚህ የተለየ ነው…ሌሎች ሰዎች ማለቴ ጎብኚዎች የሚኖሩበት ቦታ ነው…እዛ ምንሄደው ነፃ ሆናችሁ እንድትዝናኑ ነው..እኔም አብሬያችሁ ኖራለው ግን ነፃ ናችሁ…እዚህ እንዳለው ብዙ ማዕቀብና እገዳ የለም…ስልካችሁን እንደፈለጋችሁ መጠቀም ትችላላችሁ.ሰሻል ሚዲያ ቴሌቪዝን ማየት ትችላላችሁ …ከሰው መተዋወቅና መገባበዝ ትችላላችሁ..አንድ ማትችሉት ነገር መለያየት ብቻ ነው….ለ15 ቀን የምታደርጉትን ሁሉ አብራችሁ ታደርጋላችሁ..››
‹‹ገባን ..ያልከው 15 ቀን የመጨረሻችን ይመስለኛል››
አዎ እኔም እንደዛ ነው የማስበው..በእውነት እዚህ ባሳለፍነው 15 ቀን ሁለታችሁም ካሰብኩት በላይ ከፍተኛ ጥረት አድርጋችኃል …እናም ትልቅ ለውጥ እንዳመጣችሁም ይሰማኛል…እናንሰትስ ምን ይሰማችኃል…?አቶ ኃይለልኡል እስኪ ከእርሶ ልጀምር፡፡

‹‹እኔ በጣም ደስተኛ ነኝ…እስከዛሬ ሚሲቴን ብቻ የምበድል መስሎ ነበር የሚሰማኝ ለካ ልጄንም ራሴንም ጭምር ነበር እያሰቃየው የነበረው….እውነት አንተና ልጄ የእድሜ ልክ ባለውለታዎቼ ናችሁ››
ፊቱን ወደወ.ሮ ስንዱ ዞረና ተመሳሳዩን ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡
‹‹አዎ…ኃይሌ እንዳለው ደስተኛ ነን…በፊት ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጌ ገዳም ገብቼ መመልኮስ ነበር ምኞቴ ..ምክንያቱም ህይወት አስጠልታኝ ነበር…ቤቴም ኑሮዬም ይቀፈኝ ነበር…ጨለማ የሆነ ሀዘን ውስጥ ገብቼ ነበር..አንድ ያለችኝ አስደሳች ነገር ልጄ ብቼ ነበረች
..እሷም ከጠፋች በኃላ ደግሞ ነገሮች ለእኔ ምን ያህል አስቸጋሪ እንደሚሆኑ መገመት ቀላል ነው…አሁን ግን እንደዛ አይደለም የሚሰማኝ….ደግመኛ እንደመወለድ አይነት የመታደስ ስሜት እየተሰማኝ ነው…የመከራና የሀዘን ቆዳዬን ከላዬ ገፍፌ ጥዬ በአዲስ ተስፋና ፍቅር ተወልጄለሁ..አሁን ቤቴም ባሌም ይናፍቁኛል….ሃይሌን ከዚህ በፊት ለሆነው ሁሉ ይቅር ባዬዋለሁ.. እሱም ይቅር እንደለኝ ገምታለው፡፡››
ኃይለልኡል ተፈናጥረው ከመቀመጫቸው ተነሱና ሚስታቸው ላይ ተጠመጠሙ…ሁለቱም ተቃቅፈው መላቀስ ሲጀምሩ….ሰለሞንንም ስሜታዊ አደረጉት፡፡ተላቀው ወደቦታቸው ለመመለስ..ከ10 ደቂቃ በላይ ፈጅቶባቸዋል፡፡
ሰለሞን ንግግሩን ቀጠለ‹‹ጥሩ እንግዲህ… እዚህ ደረጃ ላይ ከደረስን አንዳንድ አጠቃላይ ስለሆኑ ነገሮች እናውራ፡፡ያው እናንተ በጋብቻ ውስጥ ረጅም እድሜ ስለአሰለፋችሁ ከእኔ የበለጠ ልምድ እንዳላችሁ አውቃለሁ....አሁን የማወራው የምታውቁትን ነገር ነው…ላሳውቃችሁ ሳይሆን ላስታውሳችሁ ፈልጌ ነው››
‹‹ጥሩ እየሰማንህ ነው ….ቀጥል››
‹‹እንግዲህ እቤት የባል ብቻ አይደለም፣የሚስትም ብቻ አይደለም፣ እቤት የልጆችም ጭምር ነው።በዚህ ምክንያት ለሁሉም ኑዎሪዎች እኩል ምቹ መሆን አለበት።እናንተ ከአሁን ወዲያ በቤታችሁ የሚዘረጋው ስርአት ህግና የአኗኗር ዘየ..ሶስታችሁን በእኩል ከግምት ያስገባ መሆን አለበት፡፡ሌላው ንብረታችሁን በተመለከተ የእኔ የሚለውን ቃል ከመጠቀም የእኛ የሚለውን የጋራ ቃል መጠቀም የተሻለ ነው።የእኛ ቲቪ..የእኛ ቤት...የእኛ ጊቢ የእኛ ፋብሪካ፣ብሎ የመናገር ልምድ ሊኖራችሁ ይገባል።እያንዳንድ የቤተሰብ አባል የእዛ ቤተሠብ

የአክሰዬን ባለድርሻ ናቸው።ያንን ደግሞ በተግባርም በስነ-ልቦናም መረጋገጥ አለበት።በቤተሰብ ቢዝነስ ውስጥ ስለሚፈጠር ዋና ዋና ክስተት ስለትርፍም ሆነ ኪሳራ ሁሉም ሰው በተገቢው መጠን መረጃ ሊኖረው ይገባል….ሁሉንም ኃላፊነት አንዱ አካል ብቻ ጠቅልሎ መውሰድ የለበትም…እዚህ ላይ በተለይ አቶ ኃይለልኡል ብዙ ነገር ማስተካከል የሚጠበቅቦት ይመስለኛል››
‹‹ገብቶኛል..እሺ…አስተካክላለው፡፡››

‹‹ሌላውና ወሳኙ … የተለየ ችግር ከሌለ በስተቀር ባልና ሚስት መኝታ ክፍላቸውንም ሆነ አልጋቸውን መለየት የለበቸውም…በተጨማሪም ባልና ሚስት በምንም አይነት ሁኔታ ወደመኝታቸው ሲሄድ አኩርፈውና በውስጣቸው ተበሳጭተው ወይ ቂም ይዘው መሆን የለበትም።መኝታ ክፍል ለባለትዳሮች እንደቤተመቅደስ ነው መሆን ያለበት ። የሚሳሳሙበት... የሚተቃቀፉበት.... የሚዋደድበትና የሚፋቀሩበት ….ስለጋብቻቸው እና ስለልጆቻቸው ደህንነትና ሰላም የሚማከሩበትና የሚፀልዩበት የገመና መክተቻ ቦታቸው ነው መሆን ያለበት ። ስለዚህ ... ቅያሜያቸውን ሆነ ቅሬታቸውን ሳሎን ጨርሰው ለጭቅጭቃቸው መፍትሄ አበጅተውለት እና ይቅር ተባብለው ነው በሳቅና በፈገግታ ወደመኝታቸው መሄድ ያለባቸው። አዎ ወደመኝታ ክፍላቸው ሲያመሩ በፍፁም ሰላምና ፍቅርና መሆን አለበት...የበለጠ ለመፍቀር...የበለጠ ለማረፍና ..የበለጠ ለመታደስ ።ይሄ ሁለታችሁንም በእኩል ደረጃ የሚመለከት ጉዳይ ነው፡፡››
ሁቱም አንገታቸውን እላይ እታች በማነቃነቅ መስማማታቸውን ገለፁ ‹‹ሌላው በቤት ውስጥ አንደኛው ሌለኛውን ማገልገል አለበት...ማገልገል ማለት በፍፅም ፍቃደኝነትና ፍላጎት አንደኛው ሌላኛውን መርዳት ማለት ነው።ባል የቤቱ ንጉስ ከሆነ ሚስት ደግሞ ንግስት ነች ማለት ነው ልጆች ደግሞ ልኡላን ናቸው።ማንም ከማንም የበለጠ አስፈላጊ አይደለም...ማንም ከሌላኛው ያነሰ አይደለም።ለቤቱ ሙሉነትና ፍፁምነት ሁሉም የየራሱ ኃላፊነትና ድርሻ አለው።በፍቅርና በጋብቻ ህይወት ውስጥ እርስ በርስ ያለ መከባበር በጣም ወሳኝ ነው።አንድ ለሌላዎ ጥያቄዎችን አስተያየቶችን ሲኖሩት በትህትና እና ክብር በተሞላ ሁኔታ ጥያቄውን ማቅረብ አለብት።እርስ በርስ ያለ ግንኙነት የማስመስል መሆን የለበትም...እንግዳ ሲኖር የሚደረግ አርቴፊሻል የማስመሰል እንክብክቤ እና አክብሮት

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

19 Dec, 16:16


እያልን ብና እንጠጣ››
‹‹ጥሩ….እንሄድ››ብለው ሶስቱም ከተቀመጡበት ተነሱና እቤቱን ለቀው ወጡ


////




በማግስቱ…….
ሰሎሞን ባለትዳሮችን ቢሾፍቱ ይዞ ከከተመ አራተኛ ቀኑ ነው፡፡የዛሬው ፕሮግራም ሁለቱን በተናጠል ማነጋገር ስለሆነ አሁን ከወ.ሮ ስንዱ ጋር አንድ ክፍል ውስጥ ለብቻ ፊት ለፊት ቁጭ ብለው እያወሩ ናቸው፡፡
‹‹ወ.ሮ ስንዱ አሁን ነገሮች እንዴት እየሄዱ ነው?››
‹‹እድሜ ላንተ …ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነው…ከስንት ዓመት በኃላ ከኃይሌ አንደበት መልካም ነገር መውጣት ጀምሯል››
‹‹ጥሩ እንግዲህ ሰው ምን ጊዜም ከስህተት ጋር ሚኖር ፍጡር ነው፡፡ከሰው ጋር ስንኖር ስህተት ፈላጊ ከሆን በማንኛውም ሰው ላይ ከመጠን ያለፈ ስህተቶችን በቀላሉ ማግኘት እንችላለን…..ያ ደግሞ ከሰው ጋር አያኖኑረንም…አንዳችን የሌላችንን ክፍተት ለመድፈን መፈጠራችንን እስካላሰብን ድረስ ምንም ነገር ሰላም ሊሆን አይችልም፡፡››

‹‹ትክክል ነህ..በህይወት ዘመናችን አውቀንም ሆነ ሳናውቅ…እርስ በርስ በጣም ተጎዳድተናል…በእልህም በጥፋት ላይ ጥፋት እየደረብን የሁለታችንንም ጣር ስናበዛው ነበር››
‹‹ያለፈው አፏል..አሁን ማሰብ ለነገው ነው፡፡የትናንቱን ጥፋት እያነሳን የምንመረምረው ከልባችን ይቅር እንድትባባሉ እንዲያግዛችሁ እና ዳግመኛው ተመሳሳይ አይነት ስህተት በህይወታችሁ እንዳትሰሩ ነው፡፡››
‹‹ገብቶኛል ልጄ በጣም ገብተኛል..ግን ምን መሰለህ ሀይሌ አንዳንዴ እንዲህ እንደምታየው አይምሰልህ… ህፃን ሆኖ የህፃን ስራ ሲሰራ ታገኘዋለህ ››
‹‹ውቃለው ይሄ የእሷቸው ብቻ ሳይሆን የብዙ ሰዎች ባህሪ ነው….ሰባ አመት ቢሞላን እንኳን ሁላችንም ውስጥ ሳያድግ ህፃን እንደሆነ የሚቀር ማንነት አለ…ሁሌ ውስጣችን ሆኖ ስነልቦናችንን የሚያናውፀው…እናታችን ጉያ ውስጥ እንድንወሻቅ የሚያስመኘን …አባታችን ጭንቅላታችንን እንዲዳብሰንና አይዞህ እንዲለን የሚያስናፍቀን…..አያጂቦ የሚያስፈራን ጭራቅ በህልማችን የሚመጣብን… አዎ ሳያድግ በጮርቃነት የቀረ ማንነት አለን….ለዛ ነው ልጅነት ላይ በሆነ ጎኑ የተሰበረ ሰው አድጎም በቀላሉ ጤነኛ መሆን የማይችለው….ለዛ ነው ጉዳቱ የሚያሳድደው..ለዛነው አንዳንድ ጉድለተችና የህይወት ሽንቁሮች የእድሜ ልክ ህመም ሆነው የሚቀሩት..ልጅነታችን ላይ ተጠጣብቀን እንድንቀር የሚያስገድደን፡፡››
እንግዲህ እኔ አሁን ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጌ ትቼ ከእሱ ለመስማማት ነው የምፈልገው…ግን ሰላማችን ምን ያሕል ይቆያል ?የሚለውን በእርግጠኛ ሆኜ ለማንም ማስተማመኛ መስጠት አልችልም››
‹‹ይገባኛል…የእርሶ ግምት ወደፊት በግንኙነታችሁ እንቅፋት ሊሆነ ይችላል ብለው የሚያስብት ወይም የሚያሰጋዎት ነገር ምንድነው?››
‹‹ይሄማ ግልፅ ነው…እንደምታየኝ እኔ እድሜዬ አምሳ ሞልቷል….ልክ እንደሀያ አመት ወጣት ላስደስተውና ፍላጎቱን ሁሉ በሚፈልገው መልክ ላሟላለት አልችልም..እሱ ደግሞ ከእንቡጦች ጋር መቅበጥና መዳራት ለምዶል፡፡››
‹‹ይሄውሎት ወ.ሮ ስንዱ ..ወሲብ ብቻውን ለወንድ ልጅ በቂ አይደለም፣አንድ ሚስት ለባለቤቷ ሌላ ማንኛውም ሴት ልትሰጠው የምትችለውን ነገር ሊኖራት ያስፈልጋል።ወንድ

በወሲብ ስለተመቸችው ብቻ ከአንድ ሴት ጋር ለዘላለም አብሯት አይኖርም። ወንድ ልጅ ሚስቱ ክብር እንድትሰጠው ይፈልጋል።››
‹‹አዎ ..እሱስ ትክክል ነህ …በዚህ በዚህ ብዙ ጥፋት አለብኝ..ሁልጊዜ እሱን መከራከርና ንግግሩን ሁሉ በመቃረን ማሸማቀቅ ሆነ ብዬ የማደረገው የዘወትር ድርጊቴ ነው፡፡››
‹‹አዎ…ወንድ ልጅ አንድ ገበያ ህዝብ ቢንቀው መታገስ ይችል ይሆናል ..የምታፈቅረውን ሴት ወይም የባለቤቱ ንቀት እና ችላ ባይነት የሚቋቋምበት ምንም አይነት ፅናት የለውም።‹ሴት የላከው ሞት አይፈራም› የሚባለው ለምን ይመስሎታል…አንድ ሴት የምታፈቅረውን ወንድ አክብራ አበረታታ በትህትና ምንም ነገር እዲያደርግላት ብትጠይቀው አይኑን ሳያሽ
ያደርገዋል ለማለት ተፈልጎ ነው››
‹‹ገባኝ ልጄ ይሄ የእኔ ትልቁ ስህተት ነው..እንደማርመው ቃል ገባልሀለው››
‹‹ጥሩ…እንግዲህ ቅድም እንዳሉት ወሲብ ላይ ያሎትን ነገር ብዙም አይጨናነቁበት …በመሀከል ያለ ጥልና ጭቅጭቅ ሲወገድ..ፍቅርና መተሳሰብ በቦታው ሲተካ የወሲብ ችሎታውም ሆነ አምሮቱ አብሮ ይመጣል…ደግሞ ያው ሁላችንም እንደምናውቀው ወሲብ እርካሽና ገንዘብ ያለው ሁሉ ሊገዛው የሚችል ነገር ነው።አንድ ሚስት  ስብዕናዋን ከወሲብ በላይ በሆኑ ነገሮች መገንባትና ማነፅ አለባት። ወንድ ልጅ እራሷን በሜካፕ ዲኮር ከምታደርግ ሴት ይልቅ ለችግሮች መፍትሄ የማመንጨት ብልሀት ባላት ሴት ይሳባል።አንድ ሴት ወንዶች የሚፈልጉትን ነገር ሳይሆን ሁል ጊዜ ባሏ የሚፈልገውን ነገር ማድረግ አለባት፡፡" በፍቅር የተሠራ ኃጢአት ፍቅር ከሌለበት አምልኮ ይበልጣል›ይባላል፡፡››
‹‹አልገባኝም ይህ ደግሞ ምን ማለት ነው?››
‹‹ይህ ማለት ወንዶች ሁሉ ወንድ በመሆናቸው ብቻ አንድ አይነት አይደሉም ለማለት ነው…አንድ ሚስት የባለቤቷን ልዩ ባህሪዎች ጥንቅቅ አድርጋ ማወቅ አለባት…ምን ይወዳል..?ምን ይጠላል…?ምን አይነት ምግቦች ይመቹታል…?ምንአይነት መጠጥ ያስደስተዋል…?ሚስቱ ምን አይነት ልብስ ስትለብስ ፊቱ ይፈካል…?የመሳሰሉትን ዝርዝር ባህሪዎችኑ ማወቅና ያንን ታሳቢ አድርጎ መንቀሳቀስ ይጠበቅባታል…ይሄ ለወንዱም ይሰራል፡፡ አንድ ሚስት እሷ ሴት ስለሆንች ባለቤቷም ሌላ ሴት እንደሆነ ማሰብ የለባትም።በሁለቱ መሀከል የማይካድ የጻታ ልዩነት አለ፡፡የፃታ ልዩነት ማለት ደግሞ የባህሪ እና የፍላጎትም ልዩነትም ጭምር ማለት ነው።

‹‹አዎ ..እሱስ እውነትህን ነው››
‹‹አዎ..ለምሳሌ ባሎች ቢያንስ በሳምንት አንድ ቀን ሚስታቸው በቀጥታ በእጆቾ ያበሰለችውን ምግብ መመገብ በጣም ያስደስታቸዋል… ሌላው ሁል ጊዜ ችግር እያወራች
ከምታማርር እና ሁሉን የውጭ ስራዎች ባሏ እንዲሰራቸው ከምትጠብቅ ሴት ይልቅ ጀግና እና ችግርን ፊት ለፊት ለምትጋፈጥ ሴት ክብር አለው። ››
‹‹አሁን  ምን  እንደተረዳሁ  ታውቃለህ..አንዳንድ  ጥቃቅን  ናቸው  ብለን  ትኩረት የማንሳጣቸው ነገሮች በህይወታችን ትልቅ ዋጋ እንደሚያስከፍሉን ነው፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ብለዋል››
‹‹አግብተሀል እንዴ?››
ድንገት ከርዕሳቸው ውጭ የሆነ ጥያቄ ስለጠየቁት ድንግርግር አለው

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

19 Dec, 16:16


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራዘጠኝ

ሰሎሞን ሁለቱን ባለትዳሮች ፊት ለፊት አስቀምጦ እያወራ ነው፡፡‹‹የፈለገ ጥረት ብናደርግ ለእያንዳንዱ ብሎን የራሱን ትክክለኛ መፍቻ ካልተጠቀምን ልንፈታው አንችልም!! በህይወታችንም ውስጥ ችግሮች ሲያጋጥሙን ተረጋግተን ለችግሩ ትክክለኛ የመፍትሄ ሀሳብ ማስቀመጥና ለተግባራዊነቱ መንቀሳቀስ ካልቻልን እንዲሁ ስንባክን እና በችግሩ ውስጥ ስንዳክር ነው የምንኖረው፡፡ይሄንን በስራ አለም በትክክል እየተገበራችሁ ውጤታማ እንደሆናችሁ አውቃለው…በትዳር ህይወታችሁስ?ዋናው ጥያቄ እሱ ነው፡፡››
አቶ ኃይለልኡል ተቀበሉት‹‹ገብቶናል…እንደምንም ብለን በመሀከላችንን የተፈጠረውን ክፍተት በማስወገድ እና ፍቅራችንን መመለስ እንዳለብን በደንብ ተረድተናል…አዎ እንደምታየውም ጥሩ መሻሻል እያሳየን ይመስለኛል፡፡››
ሰለሞን ቀጠለ‹‹ጥሩ ግን ፍቅር ብቻውን በሰላም ለመኖር በቂ አይደለም፡፡በመሀከላችው ምንም አይነት ጥል የሌለ ጥንዶች በመሀከላቸው ፍቅር እንዳለ እርግጠኛ መሆን አይቻልም…እንደዛውም ዘወትር በነጋ በጣባ የሚጣሉና የሚጨቃጨቁ ጥንዶችም በመሀከላቸው ያለው ፍቅር አልቋል ወይም ቀዝቅዞል ማለት አይደለም….ከዛ ይልቅ እንዴት እርስ በርስ እንደሚግባቡ እና አንዱ የአንዱን ፍላጎት እንዴት እንደሚረዳ አልገባቸውም ማለት ነው፡፡ስለዚህ አሁን መልሳችሁ ማደስ የሚገባችሁ ፍቅራችሁን ብቻ ሳይሆን እርስ በርስ የመግባባት ችሎታችሁንም ጭምር ነው፡፡አንዳችሁ ሌላችሁን በጥልቀት ለመረዳት እስከምን ድረስ ለመጓዝ ትፈቅዳላችሁ?ይሄ ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡››

ወ.ሮ ስንዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናገሩ‹‹ትክክል ነህ ልጄ… ለፍቀራችን መበላሸት ዋናው ምክንያት እንደውም እርስ በርስ የመግባባት ችሎታችን ስለተበላሸ ነው….እሱም እኔን እኔም እሱን ለመረዳት ምንም የምናደርገው ጥረት አልነበረም…ሁለታችንም እርስ በርስ እንከን ነበር የምፈላለገው….ያንን በደንብ ተረድቼለው፡፡››
‹‹አዎ ይሄ ችግር የእናንተ ብቻ ሳይሆን የአብዛኛው ባለትዳር ችግር ነው…አንድ ሰው በፍቅር ሲወድቅ በመጀመሪያ ስለራሱ ምቾና ደስታ እንጂ ስላፈቀረው ሰው ደህንነት አይደለም የሚጨነቀው…ሁለቱም ተጣማሪዎች በጋብቻ ጥምረት ውስጥ ለእነሱ የሚመች ሰፋ ያለ ግዛት ቶሎ ብሎ ለመያዝ ይጣጣራሉ…ሁለቱም ተመሳሳይ ፍላጎት ስላላቸው ፍትጊያ ይፈጠራል…አንዱ የሌለኛውን ድምበር ማለፍ…ይሄኛው የዛኛውን ቀይ መስመር መደፍጠጥ ይጀምራል……ከሁለት አንዱ በፍጥነት ነቅቶ ወደኃላ በመመለስ መረጋጋት ውስጥ ካልገባ ችግሩ መስመር ይስታል፡፡
እኔ 25፡50፡25 የሚል ፕሪንስፕል አለኝ፡፡በትዳር ውስጥ እሷ(ሚስትዬው) እሱ(ባልዬው) እና እነሱ (ባልና ሚስቶቹ)አሉ፡፡እና ስሜታቸው፤ፍላጎታቸው፤የህይወት አላማቸው ወ.ዘ.ተ ተጠቅልሎ መቶ ፐርሰን ቢሰጠው፡፡እሷ የግሏ ፍላጎት በግሏ የሚያስደስታት ነገር፤ መዝናኛ ቦታ፤ጓደኞች፤ 25 ፐርሰንት ትይዛለች….እሱም ለብቻው 25 ፐርሰንት ይይዛል፡፡50 ፐርሰንቱ ግን የጋራቸው ነው፡፡በጋራ የሚያቅዱበት፤በጋራ የሚሰሩበትና የሚለፉበት ቤት መስራት፤ልጆች መውለድና ማሳደግ…ወዘተ፡፡ሁል ግዜ ተሰፍሮ 25፤50፤25 ላይሆን ይችላል፡፡በተለይ ሴቶች ከእነሱ 25ፐርሰንት 10ሩን ወይም 15 ቱን ቆርሰው ለጋራቸው ያውሉታል…ወንዶች ደግሞ ከሞላ ጎደል አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ከጋራቸው ላይ ቆረስ አደርገው የእነሱን 25 ፐርሰንት 30 እና 40 አንዳንዴም ከ50 በላይ ያደርሱታል..የዛን ጊዜ የጋብቻው ባላንስ ይናጋል፡፡ምሰሶው መነቃነቅ ይጀምራል..እርማት ካልተደረገለት ጋብቸውን እያከሳ ይሄድና መጨረሻ ያከትምለታል፡፡…የምናገረው ግልፅ ነው አይደል››
‹‹አዎ..በጣም ግልፅ ነው፡፡››
‹‹በምሳሌ ይበልጥ ለማስረዳት አንድ ገጠር የምትኖር አክስቴ ከአስር በላይ ባሎች አግብታለች፡፡ግማሹን እነሱ ናቸው የፈቷት ግማሾቹን እራሷ ነች ያደረገችው፡፡ከሁሉም ግን የሳበኝን አንደኛውን ልንገራችሁ፡፡አገባሁት አለች..በጣም ሰላማዊ ..ምንም አይነት ክፉ ነገር ማይናገር…የጠየቅኩትን ሁሉ የሚያሞላልኝ ሰላማዊ ሰው ነበር አለች፡፡በፊት ከለመደቻቸው ተደባባዳቢ እና ተጨቃጫቂ ባሎች ጋር የትኛውም ፀባዩ የሚገጥም

አልነበረም፡፡ግን ብዙም ሳይቆይ ሰለቻት….ሁሉ ነገር ዝም እና ጭጭ ያለ ሆነባት…በቃ ግንኙነታቸው ውስጥ ነፍስ አጣችበት ፡፡አንድ ቀን በለሊት ተነሳና በሬዎቹንና ሞፈር ቀንበሩን ይዞ ወደማሳ ወጣ …ሲሄድ ቁርስም አልሰጠችውም..ምሳም ይዛ መሄድ ቢገባትም አልወሰደችለትም..ጭራሽም አልሰራችም…በጣም የባሰው ነገር ደግሞ የቤቱን እቃ ብረትድስት ፤ሰሀን ፤ብርጭቆ አንድም ሳታስቀር ከቤት ጀምራ የቤቱን መግቢያ ደጃፍ…ወለሉን ጠቅላላ አዝረክርካ እና ሞልታ ኩርሲ ላይ ቀጭ ብላ ትጠብቀው ጀመር ፡፡.
ከዛ መጣ…ከውጭ ጀምሮ ያዝረከረከችውን እቃ አንድ በአንድ ጎንበስ ብሎ እየለቀመ…‹‹እታዋቡ …ሰላም ነሽ….?ምንም አልሆንሺብኝም አይደል….?››እያለ ሁሉንም እቃ ወደመደርደሪያ መልሶ ስሯ ቁጭ ብሎ በልምምጥ ጭንቅላቷን መዳበስ ጀመረ..
ከዛ ይህቺ አክስቴ ምን ብታደርግ ጥሩ ነው‹‹ ብድግ አለችና ሻንጣዋን ይዛ‹‹እንዴት ቁርስ አላበላሁህ ..ምሳ አለመጣሁልህ….ቤቱን እዲህ አዝረክርኬ ነው የጠበቅኩህ..ምን እስካደርግህ ነው የምትጠብቀው…?ምንም አይነት የወንድነት ወኔ የለህም እንዴ…?ሁለት ሴት አንድ ቤት አይኖርም… ነውር ነው››ብላ ጥላው ወጣች..በዛው ፈታችው ፡፡አያችሁ ትዳር በጣም ውስብስብ ግንኙነት ነው፡፡የበዛ ጭቅጭና ጥል ብቻ ሳይሆን የበዛ ሰላምና ፀጥታም ሊያፈርሰው ይችላል፡፡፡ዋናው በሁሉም ነገር ሚዛን ጠብቆ መጓዝን መልመድ ነው፡፡››
የተወሰነ ትንፋሽ ወሰደና ፊትለፊቱ ካለ የታሸገ ውሀ በማንሳት አንዴ ተጎንጭቶለት ከንፈሩን አረጣጠበና ንግግሩን ቀጠለ፣እነሱም ልክ በቅርብ ፈተና እንደደረሰበት ቸካይ ታማሪ በጥሞናና በትኩረት እየተከታተሉት ነው‹‹አሁን ልብ በሉ፣ ጥረታችን በመካለላችሁ ያላውን ግጭትና ጭቅጭቅ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ አይደለም..አይ እንደዛማ አይሆንም እናንተ ሰው ናቸው፣ሁለት ሰዎች ደግሞ በአንድ ጣሪያ ስር አብረው እስከኖሩ ድረስ በሆነ ነገር መነጋገራቸውና በነገሩ ላይ የተለያየ ተቃራኒ ሃሳብ ማንፀባረቃቸው አይቀርም…ስለዚህ መነጋገርና መጨቃጨቅ ኖርማል ነው…አሁን ምንድነው ምናደርገው.. በማንኛውም ጉዳይ ላይ አለመግባባት ተከስቶ ስትነጋገሩ በምን መልኩ ነው ኮምንኬት የምታደርጉት..?ነገሩን ማስረዳትና ማሳመን ላይ ነው ትኩረታችሁ ወይስ ያንን ምክንያት አድርጎ በስድብና በዘለፋ ማጥቃትና ልብ መስበር…አያችሁ ትልቁ ችግር መጋጨታችን ሳይሆን በያንዳንዱ ግጭታችን አንዳችን ለሌላቸውን የልብ ቁስለትና የነፍስ ህመም መስጠታችን ነው፡፡ማጥፋት ያለብን እርስ በርስ መወጋጋቱን ነው…አንዳችን ሌላችን ላይ በምንም አይነት ሰበብ የሚያቆስል ነገር ጦር አስበን አይደለም አምልጦን እንኳን መወርወር ለብንም፡፡እርስ በርስ ከፍ ባለ ቃላት በተነጋገራችሁ ቁጥር ደግሞ እየተጣላችሁ መሆኑን አታስቡት..መጣላት ቃሉ እራሱ አሉታዊ ነው፡፡እየተጣላችሁ ሳይሆን በጋለ ስሜት እየተነጋገራችሁ ነው፡፡በቃ እንዲህ ነው ማሰብ ያለባችሁ፡፡እንደዛ ካሰባችሁ ቀጥታ ችግሩ በጋለ ስሜት መነጋገራችን ብቻ ስለሆነ ስሜታችሁን በማረጋጋት ነገሩን ትፈታላችሁ፡፡እየተጣላን ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ግን ጋና ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ወይም ሽማግሌ ልትፈልጉ ነው፡፡ልብ በሉ ጮክ ብሎ መናጋገር ሁል ጊዜ መጣላት አይደለም አብዛኛውን ጊዜ በጋለ ስሜት መነጋገር ነው፡፡ለዘሬው ይበቃናል…አሁን ወደመናፈሻው እንሂድና ትንሽ ዘና

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

19 Dec, 01:44


የአባቶች ቀን ..እወድሀለው… ዘላለም ኑርልኝ› ብላ የለጠፈችውን ሰው አሳየኝ…አየሽ እኔ ጎስቆላ አባቷን አለም ፊት በአደባባይ ይዛ ለመውጣት አልተሳቀቀችም..እንደውም በኩራት ነበር ያደረገችው…..ከአራት አመት በፊት ምን ሆነ መሰለሽ..እኔ አባትሽ የተቀደደና ያደፈ ቱታ ለብሼ አንድቤት ጣሪያላይ ወጥቼ ቆርቆር እየጠገንኩ ነበር…ስራዬን ጨርሼ ከጣሪያው በመሰላል በመውረድ ላይ እያለሁ እታች ትላልቅ ሱፍ ለባሽ ሰዎች ቤቱን እየተመለከቱት ነው…ከመሀከላቸው ልጄ በሬዱ ነበረችበት…ለካ ያ ቤት የባንክ እዳ ኖሮበት ጫረታ ላይ ሊያወጡት ከባንክ የመጡ የስራ ኃላፊዎች ነበሩ ..የልጄ ሀለቃዎች…ልክ ልጄን እንዳየኋት ተመልሼ ወደላይ መውጣት ጀመርኩ..ለካ ልጄም በዛው ቅፅበት አይታኝ ኖሮ‹‹…አባዬ
..አባዬ ና አንዴ ውረድ››ስትል የት ልግባ….ምርጫ ስላልነበረኝ ወደታች ወረድኩ…ቆሻሻዬን ሳትጠየፍ ጉስቁልናዬን ከቁም ነገር ሳጥቆጥር አገላብጣ እየሳመች ወደሀለቆቾ ይዛኝ ሄደችና…‹‹አባቴ ነው ..ተዋወቁት ብላ አስተዋወቀችኝ…አክብራ አስከበረችኝ››እነሱን ከሸኘሁ በኃላ ለብቻዬ ገለል ብዬ እንደህፃን ልጅ አለቀስኩ…እና ምን ልልሽ ነው እኔ ነኝ እድለኛው፡፡››
‹‹አይ ጋሼ…እኔ አንተ አባቴ ብትሆን በጀርባዬ አዝዬ ድፍን አዲስአበባን እዞር ነበር….››
‹‹አይ አንቺ…አሁንም አባትሽ ነኝ ..አይደል እንዴ?››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው ..አንተ ያደረክልኝ…ግማሹን አባቴ አድርጎልኝ አያውቅም፡፡ማለቴ አሁን እየተነፈስኩ ያለሁት ባንተ ደግነት ነው››
‹‹አይ አንቺ ልጅ….››
‹‹ጋሼ››
‹‹አቤት ልጄ››
‹‹አንድ ነገር ልጠይቅህ ነበረ.. ግን ፈራሁ››
‹‹እንዴ ..እኔ እኮ አባትሽ ነኝ ምን ያስፈራሻል?››
‹‹እንተን.ማለቴ ያው በህመሜ ምክንያት ረጅም ጊዜ ስተኛና ከቤት ሳልወጣ ስለቆየሁ ተጨናንቄያለው…ለተወሰነ ቀን ከለሊሴ ጋር ላንጋኖ ወይም የሆነ ቦታ ሄደን ትንሽ ተዝናንተን ብንመጣ ብዬ ነበር››
‹‹ከለሊሴ ጋር ስራዋስ ልጄ?››

‹‹አልሰማህም እንዴ….ሀለቃዋ እኮ ለስራ ሌላ ሀገር ለአንድ ወር ስለሄደ ፍቃድ ሰጥቶታል፡፡››
‹‹እንደዛ ነው››፣አሉና መልስ ሳይሰጡ ወደትካዜ ውስጥ ገቡ…ምን ብለው ሁለት የደረሱ ሴቶችን እንደሚፈቅዱላቸው ምን ብለውስ እንደሚከለክሎቸው ግራ ገባቸው››
‹‹በፀሎትም መልሱን ለመስማት አፏን ከፍታ በጉጉት መጠበቋን ቀጠለች››
‹‹የእኔ ልጅ ያልሽው ትክክል ነሽ..አየር መቀየርና ትንሽም ዘና ማለት አለብሽ…ግን ሁለታችሁም ሴቶች ናችሁ …ለምን ወንጪ አትሄዱም››
‹‹እንዴ ጋሼ..ደስ ይለኛል….ቦታው አሪፍ ይመስለኛል››
‹‹አዎ ቦታውማ ገነት በይው..ግን ከቦታውም በላይ ትውልድ አካባቢዬ ነው..አሁንም ዘመዶቼ እዛ አሉ..ወንድሞቼ እህቶቼ ብዙ ናቸው..ለሊሴም ቦታውን በደንብ ታውቀዋለች..እዛ ከሄዳችሁ እኔ አባታችሁ ምንም አላስብም….የፈለጋችሁትን ያህል ቀን መቆየት ትችላላችሁ..ግን የእናትሽ የጽዋ ማህበር የዛሬ ሳምንት ነው..ከዛ በፊት እንድትሄዱ አትፈቅድላችሁም››
‹‹አመሰግናለው ጋሼ..››ከመቀመጫዋ ተነሳችና አቅፋቸው ግንባራቸውን ሳመቻቸው፡፡››
‹‹ልጄ አመሰግናለው››
‹‹እኔ ነኝ እንጂ ማመሰግነው››
‹‹አይ አመሰግናለው ያልኩሽ ሁል ጊዜ በድርጊቶችሽ ልጄ በሬዱን ስለምታስታዊሺን ነው..አፈሩን ገለባ ያድርግላትና እሷም እንደእዚህ አንደአንቺ የሆነ ነገር ጠይቃኝ እሺ ካልኳት አቅፋ ትስመኝ ነበር….››
‹‹ይቅርታ ጋሼ እሷን እንድታስታውስ ስላደረኩ››
‹‹አይ…እንዳስታውሳት ስለምታደርጊኝ ሚከፋኝ መሰለሽ….?ልጄን መቼም መርሳት አልፈልግም…ደግሞ የምትረሳም ልጅ አይደለችም…የእኔ በሬዱ ቶሎ ተወልዳ በፍጥነት አድጋ…በጮርቃነቷ በስላ..በችኮላ ጥሩጥሩ ነገሮችን ሰርታ እኔ አባቷን አስደስታ የሞተች ድንቅ ልጅ ነች.…በይ የሆነች ለቅሶ ቢጤ አለችብኝ፣ደረስ ብዬ ልምጣ..እስከዛ ከእናትሽ ጋር

ተጫወቺ…››አሉና የሚተናነቃቸውን እንባ እንደምንም ተቆጣጥረው ወደውስጣቸው በመመለስ ከመቀመጫቸው ተነሱ፡፡
‹‹እሺ ጋሼ…እንዳትቆይ››
‹‹አልቆይም ልጄ..››አሉና ኮፍያቸውን ከጠረጴዛ ላይ አንስተው ጭንቅላተቸው ላይ አስተካከለው እያደረጉ ቤቱን ለቀው ወጡ

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

19 Dec, 01:44


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራስምንት

ሰለሞንና በፀሎት በስልክ እያወሩ ነው፡፡
‹‹ለመሆኑ የት ነው ያለሽው?››ሲል ጠየቃት
‹‹ምነው ጠየቅከኝ?››
‹‹አይ ..እንዲሁ ደህንነትሽ አሳስቦኝ ነው….ምን አልባት የማይመች ቦታ ካለሽ ልረዳሽ እችላለው፡፡››
‹‹ምነው ወደቤትህ ወስደህ ደብቀህ ልታኖረኝ አሰብክ››

‹‹ምነው ..ችግር አለው.?.የእውነት የማይመች ቦታ ካለሽ ንገሪኝ››
‹‹አሁን ካለሁበት ቦታ የተሻለ ሊመቸኝ የሚችለው ምን አልባት ገነት ነው….እሱንም ደግሞ ስላላየሁት እርግጠኛ አይደለሁም››
‹‹እንዴ…ከእናትና  አባትሽም  ቤት  የተሻለ  ቦታ  ነኝ  ነው  የምትይኝ…ይሄንን  ማመን አልችልም፡ ››
‹‹ነገርኩህ እኮ…››
‹‹‹እ ..ገባኝ››
‹‹ምኑ ነው የገባህ?››
‹‹ከእናትና አባት ቤት በበለጠ የሚመች ቦታ የፍቅረኛ ቤት ነው››
‹‹በጣም ተሳስተሀል..አዲስ ቤተሰብ አግኝቼለሁ…አራት ናቸው..ሽማግሌ አባትና እናት፣አንድ ዋንድ ሴትና ወንድ ልጅ አላቸው..ሀለት ክፍል ሰርቢስ ውስጥ ነው የሚኖሩት፣ኑሮቸው ከእጅ ወደአፍ ነው… ፍቅራቸው ግን ሞልቶ የፈሰሰ ነው….ለዘላለም ልጃቸው አድርገው ተቀብለውኛል…ከአሁን ወዲህ ባለው ህይወቴ ሙሉ አነሱ ወላጆቼ እና ቤተሰቦቼ እንደሆኑ እንዲቀጥሉ ምንም ነገር አደርጋለው››
‹‹የሚገርም ነው….እናትና አባትሽ ይሄንን ንግግርሽን ቢሰሙ ልባቸው የሚሰበር ይመስለኛል፡፡››
‹‹እንግዲህ ምንም ማድረግ አልችልም…በእነሱ ስህተት ነው ከቤት የወጣሁትና እነሱን ያገኘሁት…አሁን አግኝቼ በደንብ አጣጥሜቸዋለው…እና ወደቤት ብመለስ እንኳን ወላጆቼን ከእነሱ ጋር ነው ማነፃፅራቸው…እና ለእነሱ ቀላል የሚሆንላቸው አይመስለኝም››
‹‹….ለመሆኑ ማንነትሽን ያውቃሉ?›
‹‹አይ አያውቁም.. እኔ ለእነሱ እናቷ የሞተችባት እና የእንጀራ አባቷ ሰክሮ በለሊት ሊደፍራት ሲል አምልጣ የወጣች ሚስኪን ሴት ነኝ››
‹‹ይሄንን ታሪክ አንቺ ነሽ የፈጠርሽው?››

‹‹አዎ…..››
‹‹የምትገርሚ ልጅ ነሽ ..እኔጋም መጥተሸ ተመሳሳይ ታሪክ ብትነግሪኝ አምኜ ልረዳሽ መሞከሬ አይቀርም ነበር››
‹‹የእነሱ እኮ መርዳት አይደለም….እናትና አባት መሆን ነው…..እንደልጃቸው መቀበል››
‹‹ የእውነት አዲሶቹን ቤተሰቦችሽን እኔ እራሱ ለመተዋወቅ ጓጓሁ› ›
‹‹መጓጓትህ ትክክል ነህ››
‹‹ነገሮች ከተስተካከሉ በኃላ ታስዋውቂኛለሽ ብዬ ገምታለው››
‹‹መጀመሪያ እስኪ እኛ ለመተዋወቅ ያብቃን››
‹‹እንዴ እኛኮ በደንብ ተዋወቅን፣ለአመታት የማውቅሽ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው..ያው አካል ለአካል አልተገናኘንም ብዬ ነው፡፡››
‹‹ባክሽ የስልኬ ጋላሪ ባንቺ  ፎቶዎ ተጨናንቆል  ››ብሎ ያልጠበቀችውን አስደንጋጭ ነገር ነገራት፡፡
‹‹እንዴ በምን ምክንያት?››
‹‹እንዴ ..ደንበኛዬ አይደለሽ?››
‹‹እና የሁሉንም ደንበኞችህን ፎቶ ትሰበስባለህ ማለት ነው?››
‹‹ቆንጆ እና የተለየ የሆኑትን ..አዎ››
‹‹በቻይንኛ ቆንጆ ነሽ እያልከኝ ነው፡፡››
‹‹እ..ምነው አይደለሽም እንዴ?››
‹‹እኔ እንጃ ….ለማንኛውም ደስ የሚል ስሜት እንዲሰማኝ አድርገሀል…እና እኔስ የአንተን ፎቶ የማግኘት መብት ያለኝ አይመስልህም?››

‹‹አይ..አዲሶቹን ቤተሰቦችሽን እንድምታስተዋውቂኝ ቃል ካልገባሽ የምታገኚ አይመስለኝም››
‹‹አዲሶቹን ቤተሰቦቼን….እኔ እንጃ ..ስለምሰስታቸው የማደርገው አይመስለኝም››
‹‹‹ትገርሚያለሽ…፣ዋናዎቹን ቤተሰቦችሽን እኮ ተቆጣጥሬቸዋለው…..ለማንኛውም ይህን የመሰለ ቤተሰብ ስላገኘሽ ደስ ብሎኛል….ይሄውልሽ በህይወት ውስጥ ሶስት አይነት ሰዎች አሉ፡፡ቅጠል የሆኑ ሰዎች… ቅርንጫፍ የሆኑ ሰዎችእና… ስር የሆኑ ሰዎች።ቅጠል የሆኑ ሰዎች ወቅትንና ሁኔታዎችን ጠብቀው ወደ ህይወትሽ የሚገብ ናቸው።ደካሞች ስለሆኑ በእነሱ ተፅዕኖ ስር ፈፅሞ እንዳትወድቂ። ከአንቺ የሚፈልጉትን የሆነ ነገር ስላለ ነው ወደህይወትሽ የሚመጡት... የመከራ ንፍስ በህይወት ዙሪያ ሲነፍስ መርገፍ ይጀምራሉ።እነዚህ ሰዎች አንቺን ማፍቀር የሚቀጥሉት በዙሪያሽ ያሉ ነገሮች ጥሩ እስከሆኑ ጊዜ ብቻ ነው።ንፋስ እንደመታው የወየበ ቅጠል ከላይሽ ላይ ተዘንጥለው ይረግፋሉ። ቅርንጫፍ ሰዎች ደግሞ በአንፃራዊነት ጠንካሮች ናቸው ግን ልትጠነቀቂያቸው ይገባል።ህይወት ጨከን ስትል መገንጠላቸው አይቀርም። ምክንያቱም ጠንከር ያለ የህይወት ጫና የመሸከም አቅም የላቸውም።ነገሮች ጨለምለም ሲሉ እና ተስፋም የሌላቸው ሲመስሉ ጥለውሽ ዞር ለማለት አያመነቱም። ሌሎቹ ልክ እንደአንቺ አዲሶቹ ቤተሰቦች ስር የሆኑ ሰዎች ናቸው። እነዚህ በህይወትሽ በጣም አስፈላጊ ሰዎች ናቸው።ለመታየት ብለው የሚሰሩት ስራ የለም።በመከራሽም በደስታሽም ጊዜ አብረውሽ ናቸው።አስከሞት የታመኑሽ ናቸው።ሲያፈቅሩሽ በነፃ ምንም መልስ ካንቺ ሳይጠብቁ ነው፣እንደዚህ አይነት አንድ ወይም ሁለት ሰው ከጎንሽ ማግኘት የህይወት ዘመን ሽልማት ነው፡፡
‹‹ጥሩ አድርገህ ገልጸኸዋል፡፡እነሱ ብቻ ሳይሆኑ፣አንተም ለእኔ ስር ነህ…በቃ ቸው…ነገ እንደዋወላለን፡፡››
‹‹ቸው …..ደህና ሆኚ››ብሎ ስልኩን ከዘጋ በኃላ …ባለበት ቆሞ ትካዜ ውስጥ ገባ..ይህቺን ልጅ በተመለከተ የተለየ አይነት ኬሚስትሪ በሰውነቱ እየተረጨ ነው….ነገሮች ወዴት እያመሩ ነው?››ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡

በማግስቱ……
በፀሎት ከሞላ ጎደል ጤንነቷ እየተመለሰ ነው…አረ እንደውም ድናለች ማለት ይቻላል..የእግሯ ስብራት ሙሉ በሙሉ ተጠግኖ በደንብ መራመድ ችላለች..የፊቷ ቁስለትም ሙሉ በሙሉ ጠጓል..አሁን ብቸኛ ችግሯ ፊቷ ላይ ተሸነታትሮ የሚገኘው ጠባሳ ብቻ ነው….እንግዲህ ግማሽ ፊቷን ባደረሰው በተበታተነው ጠባሳ ውስጥ ምን ያህሉ እንድሚጠፋና ከበፊት ቆዳዋ በቦታው እንደሚመለስ ምን ያህሉ ደግሞ እንዳዛው እንደሚቀር ምንም የምታውቀው ነገር የለም…ያንን ለማወቅ በርከት ያሉ ተጨማሪ የማገገሚያ ቀኖች ያስፈልጋታል…ከዛ በኃላ የቆዳ ስፔሻሊስቶች ጋር ሔዳ ሰርጀሪ መሰራትም የግድ ያስፈልጋት ይሆናል….ለጊዜው ያ እያሳሰባት አይደለም…‹‹እሱን ጊዜው ሲደርስና ሁሉ ነገር ተስተካክሎ ወደቤት ከተመለስኩ በኃላ አስብበታለው››ብላ ወስናለች….አሁን ከጎኗ አቶ ለሜቻ ቁጭ ብለው እያጫወቷት ነው፡፡
‹‹ለልጆቾህ ያለህ ፍቅር ያስገርመኛል››
‹‹አይ ልጄ ሁሉም ወላጆች እኮ ልጆቻቸውን አብዝተው ይወዳሉ…››በትህትና መለሱላት፡፡
‹‹እሱን ማለቴ አይደለም..የእናንተ የተለየ ነው…አይኖችህ ከልጆቾህ ላይ አይነቀሉም….ሙሉ ትኩረትህ ልጆቾህ ላይ ነው..ስለእለት ውሏቸው ታውቃለህ….ጥዋትና ማታ አብረሀቸው ባንድ መሶብ ቀርበህ ሁለቱንም እያጎረስክ ነው የምትበላው፣ብዙ ብዙ ነገር…››
‹‹ልጄ ወድጄ አይደለም እኮ…. እንደምትይው እኔ አባትሽ በብዛት ተትረፍርፎ ያለኝ ፍቅር ነው…ገንዘብ ኖሮኝ ይሄን ስሩ ብዬ መቋቋሚያ..ወይም መነገጃ ጥሪት አልሰጣቸው….ሁል ጊዜ ታዲያ ይሄንን ነገር በምንድነው የማካክሰው ብዬ ሳስብ አንድ የማገኘው መልስ…ጊዜዬንና ፍቅሬን ሳልሰስት መስጠት ነው..አዎ ቢያንስ በዛ ነው ልክሳቸው የምችለው፡››
‹‹ግን እንሱ ምን ያህል እድለኞች መሆናቸውን ያውቃሉ?›› ‹‹አይ እነሱ ሳይሆኑ እኔ ነኝ እድለኛ….ምንም ባላደርግላቸው እንኳን ማንም ፊት በኩራት አባዬ ብለው ይጠሩኛል፡፡በቀደም ለሊሴ ይሄ ፌስቡክ ነው ምን በምትሉት ነገር ላይ በተንዠረገገ ፂሜንና በጎፈረ ፀጉሬ የተነሳሁትን የተጎሳቆለ ፎቶ ለጥፋ አባዬ መልካም

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

17 Dec, 17:07


በቃ አሁን ቀጥታ ወደማዳመጡ እንግባ ››አለና ኮምፒተሩን ከፈተና ለ.ወሮ ስንዱ አቀበላት…አቶ ኃይለልኡል ያለምንም ንግግር ከተቀመጠበት የራሱ አልጋ ተነሳና ሄዶ ወ.ሮ ስንዱ አልጋ ላይ ከጎኗቸው ተቀመጠና በኮምፒተር የሚታየውን የራሳቸውን ንግግር ለማደመጥ ዝግጁ ሆነ…ሰለሞን በፀጥታ ከተቀመጠበት ተነሳና ክፍልን ለቆ በራፍን ዘጋላቸውና ወጥቶ ሄደ


ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

17 Dec, 17:07


‹‹የተለየ ስትል?› ‹‹እስከአሁን ወደእኔ መጥተው የሚያናግሩኝ ከሁለት አንዱ ማለቴ ባልዬው ወይም ሚስትዬው ናቸው….የእናንተ ግን ልጃችሁ ነች ያናገረችኝም የቀጠረችኝም፡፡››
‹‹አዎ እሱስ ትክክል ነህ››
‹‹ስለዚህ አሁን ስራችንን ስንጀምር እሷን እያሰብን መሆን አለበት ፡፡በፍቅር የታነፀ ትዳር ውስጥ ያላደጉ ልጆች በመጨረሻ በስነ-ልቦናም ሆነ አካላዊ በሽታ እንደማያጣቸው የተረጋገጠ ነው። ልጅ ስናሳድግ ጥሩ ልብስ ፣ጥሩምግብና ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት እንዲያገኙ መጣር ብቻ ሳይሆን የተሞላ ፍቅርም እየመገብን ማሳደግ እንዳለበት እንደወላጅ ግንዛቤው ሊኖረን ይገባል።የመፈቀር እና የመፈለግ ስሜት ማጣት በከፍተኛ ሁኔታ የልጆችን በራስ የመተማመን ችሎታን ከመሸርሸሩም በላይ ለአእምሮ ውጥረትና ድብርትም እንዲዳረጉ ያደርጋቸዋል።ለልጆች በፍቅርና በእንክብካቤ ማደረግ ደስተኛ ሆኖ ለመኖር ብቻ ሳይሆን ጤነኛም ሆኖ ለመኖር በጣም አስፈላጊ ነገር ነው።በወላጆቹ የሚወደድ እና ወላጆቹም የሚወድት ልጆች በጣም ደስተኛ ናቸው።በፍቅር ውስጥ መኖር ጤነኛ ሆኖ ለመኖር እና የበሽታ የመከላከል አቅማችንን ለመጨመር እንደሚያግዝ በሳይንስ የተረጋገጠ ነው።ስለዚህ ልጆቻችን በፍቅር ታንፀው የመፈለግና የመወደድ ስነልቦና ኖሮቸው ማደግ አለባቸው፡፡ለዚህም ወላጆች ሁሉ ትኩረት ሰጥተው መስራት አለባቸው፡፡፡ እንደውም እናንተ እድለኛ ናችሁ፡
‹‹እድለኛ ናችሁ ስትል?››
‹‹እንዴ በፀሎት እኮ በጣም የምትገርም ብስልና በቀላሉ የማትሰበር ልጅ ነች፣አብዛኞቹ በእሷ እድሜ ያሉ ልጆች በእንደዚህ አይነት ችግሮች ውስጥ ሲያልፉ ከፍተኛ ድብርት ውስጥ ይገቡና ለተለያዩ ሱሶች ይጋለጣሉ ..ከዛም አልፈው በህይወት ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ይገቡና እራሳቸውን ወደማጥፋት ይሄዳሉ….በፀሎት ግን ያደረገችው ከውጥረቱ ራሷን ዞር አድርጋ እናንተን ለመርዳትና ወደመስመር ለመመለስ መጣር ላይ ነው ያተኮረችው››
‹‹አዎ እውነትህን ነው …በልጄ ታላቅ ኩራት ተሰምቶኛል….ምንም ጭረት ሳይነካት ወደቤቷ እንድትመለስ ማድረግ ያለብኝን አደርጋለሁ..ማለት ሁለታችንም ማድረግ ያለብንን እናደርጋለን አይደል ስንዱ?››
‹‹አዎ ትክክል ነህ…ለዛም አይደል እዚህ የተገኘነው››

‹‹እንግዲያው ጀመርን …ከአሁን በኃላ የምናወራውና የምንናገረው ሁሉ እየተቀዳ ነው.››.ብሎ አይፓዱን አስተካክሎ ተጫነውና ቦታውን ይዞ ተቀመጠ…››
ለሶስት ሰዓት ቀጠለ…..በመጀመሪያ ወ.ሮ ስንዱ አቶ ኃይለመለኮት ላይ ያላቸውን ቅሬታ እስከአሁን በደሉኝ የሚሉትን ነገር እንዲያወሩና አቶ ኃይለመለኮት ደግሞ ለደቂቃ እንኳን ሳያቆርጡ እንዲሰሙ አደረገ…በቀጣዩ ሰዓት ደግሞ አቶ ኃይለልኡል በተራቸው ሚስታቸው ላይ ያላቸውን ቅሬታ በዝርዝር እንዲናገሩ አደረገ……..ቀጣዩን አንድ ሰዓት ደግሞ እራሱ ሰሎሞን ጥያቄ እየጠየቃቸው ሁለቱም ተራ በተራ እዲመልሱ ተደረገና የጥዋቱ ክፍለጊዜ አለቀና ሶስቱም ተያይዘው ወደሳሎን ሄዱ ..ምሳው በስርአት ተዘጋጅቶ ስለጠበቃችው ሶስቱንም ጠረጴዛውን ከበው ፀጥታ በተጫነው ና እርስ በርስ በተፈራራ በሚመስል ሁኔታ ምሳቸው ተበልጦቶ አለቀ..ብና ተፈልቶ ስለነበረ በረንዳ ላይ ቁጭ ብለው ንፋስ እየተቀበሉ ጠጡ
‹‹አሁን ለአንድ ሰዓት ያህል መኝታ ክፍላችሁ ገብታችሁ አረፍ በሉ….ሰዓት ሲደርስ እኔ መጥቼ ቀሰቅሳችኃላው››
እሺ ብለው ሁለቱም ከመቀመጫቸው ተነሱ..ሰለሞን ከኃላ ተከተላቸው….››መኝታ ቤታቸው እንደደረሱ ሊከፍቱ ሲታገሉ‹‹ይቅርታ ሳልነግራችሁ መኝታ ቤታችሁ ተቀይሮል..ተከተሉኝ››ብሎ ቀደማቸው፡፡
‹‹የማ…? የእኔም ነው የተቀየረው?››
‹‹አዎ ወ.ሮ ስንዱ….ሁለታችሁም ተከተሉኝ..››
ግራ በማገባት ሁለቱም በዝምታ ከኃላው ተከተሉት …የኮሪደሩ መጨረሻ ላይ ካለው በራፍ ሲደርስ ቆመና ከፈተው….‹‹ግቡ ››
‹‹ማ እኔ ነኝ እሷ?››
‹‹ሁለታችሁም››
እርስ በርስ ተያዩ…ቀጥሎ በጋራ እሱ ላይ አፈጠጡበት…አንድ ክፍል ውስጥ አብረው ከተኙ አስር አመት አልፏቸዋል..አሁን በአንዴ እንዴት….?ጉዳዩ ሁለቱንም እኩል ነው ያስበረጋጋቸው፡፡

ጫን ባለ የአዛዥነት ቃና‹‹እባካችሁ ግቡ››አላቸው
ምርጫ ስላልነበራቸው አቶ ኃይለልኡል ቀድመው ገቡ…ወ.ሮ ስንዱ ተከተሏቸው….ሁለቱም ጎን ለጎን ቆመው ክፍሉን ዙሪያ ጋባ ቃኙት …ሻንጣቸው ሆነ ጠቅላላ እቃቸው በየቦታው ተቀምጦል…ሁለት አልጋ ማዶ ለማዶ ግድግዳ ተጠግቶ ይታያል…፡፡
ያው ..ሁለት አልጋ አለ …ተነጋገሩና አንዳንደ አንድ ተካፈሉ …በቃ መልካም እረፍት..ሰዓቱ ሲደርስ መጥቼ ቀሰቅሳችኃላው››አለና ከክፍሉ ወጥቶ በራፉን መልሶ ዘግቶላቸው ወደገዛ ክፍሉ ሄደ፡፡
///
የሁለት ሰዓት የረፍት ጊዜ ከሰጣቸው በኃላ በጥዋቱ ጊዜ ባለው ፕሮግራም የቀረጸውን ወደኮምፒተሩ ገለበጠና ይዞ ወደእነሱ ክፍል አመራ…በስሱ ቆረቆረ…ወዲያውን ነበር የተከፈተለት፡፡
‹‹መጣህ ..?እየጠበቅንህ ነበር››
‹‹አዎ መጥቻለው››
‹‹ስንዱ ተነሽ..እንሂድ››አቶ ኃይለልኡል ተናገሩ፡፡
‹‹አይ ቆይ መሄድ አያስፈልግም ….እዚሁ እናድረግው››
‹‹ይሻላል ..እሺ ግባ..››ብለው በራፉን ለቀቁለትና ወደውስጥ በመመለስ አልጋቸው ጠርዝ ላይ ተቀመጡ ፡፡ወ.ሮ ስንዱም የራሳቸው አልጋ ላይ እንደተቀመጡ ነው፡፡
ወንበር ሳባና ከሁለቱ መካከል ተቀመጠና ኮምፒተሩን ጠረጳዛ ላይ አስቀመጠው፡፡
‹‹ይሄውላችሁ በትዳር ውስጥ ችግር መፈጠርና አለመስማማት የእናንተ ብቻ ሳይሆን የሚሊዬን ጥንዶች ችግር ነው..እመኑኝ ያልተስማማንበት ነገር ይህ ነው ያ ነው ብላችሁ ቀኑን ሙሉ ስትዘረዘሩ ብትውሉ የእናንተ ከሌላው ትዳር ውስጥ ከተፈጠረው ችግር የተለየ ሊሆን ይችላል እንጂ የባሰ ግን አይደለም፡፡ስሙኝ አብዛኛውን ጊዜ በትዳር ውስጥ ችግር ሲከሰት በትዳር ውስጥ ችግር የፈጠረውን ነገር ከማየት ይልቅ እራሱ ትዳርን እንደችግር የመውሰድ  አዝማሚያ  ይታያል።ያ  ደግሞ  ከትዳራቸው  ውስጥ  ሾልኮ  ስለመውጣት

ስለመፋታት እንዲያስብ ያደርጋቸዋል።እንደሀሳባቸው ትዳራቸውን ፈተው የተሻለ ወዳሉት ወደሌላ ትዳር መሸጋገር ቢችሉም ችግሩም አብሯቸው ነው ወደአዲሱ ትዳራቸው የሚሸጋገረው።
መፍትሄው ትዳሩን እንደችግር ወስዶ ያልሆነ ድምዳሜ ላይ ከመድረስ ይልቅ ትዳሩ ውስጥ የተከሰቱ ችግሮች ምን ምን ናቸው ብለው በመለየት እነሱን ለማስወገድ መጣር እና በዛ ሂደት የጋብቻውን ህልውና ማስቀጠል ይበጃል።ምክንያቱም የመኪናህ ጓማ ቢያልቅ ጎማውን ትቀይራለህ እንጂ መኪናዋን ሙሉ በሙሉ አታስወግድም።አይደለም ጎማ ሞተሩ ቢነክስ እንኳን ሞተር አስወርደህ ከእንደገና ተፈቶና ተበታትኖ ችግሩ ተለይቶ ከተወገደ በኃላ መልሶ ይገጣጠምና መኪናው እንደነበረ ይቀጥላል... ጋብቻም እንደዛ ነው የሚደረገው።እና አሁን እያደረግን ያለነው በመሀከላችሁ ያለውን ችግር የመቃቃራችሁን መንሴ መለየት ነው፡፡አሁን በጥዋቱ ክፍለ ጊዜ ሁለታችሁም የተናገራችሁትን እዚህ ኮምፒተር ላይ ከፍትላችኃላው በጋራ አብራችሁ ታዩታላችሁ…ይሄ መልሳችሁ የተናገራችሁትን እንድታዳምጡና የትኛው ትክክል ነው..የትኛው ንግግራችሁ ተጋኗል የሚለውን መልሳችሁ እንድታስበቡበት ይረዳችኃላ…

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

17 Dec, 17:07


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራ ሰባት

ይዘውት የሄዱት ቦታ ከቢሾፍቱ ከተማ በባቦጋያ ሀይቅ አካባቢ ከከተማው ወጣ ብሎ የሚገኝ ቪላ ነው፡፡ይህ ቪላ ቤተሰቡ ከውጥረት ረገብ ለማለት ሲፈልግ የሚገለገልበት ስፋራ ነው፡፡ለአለፉት አንድ አመት ከግማሽ ማንም ዝር ብሎበት አያውቅም ነበር፡፡ሰለሞን ስፍራውን ሲያይ ከውበትም ሆነ ከፀጥታ አንፃር ሲታይ ሙሉ በሙሉ እሱ እንደሚፈልገው አይነት ሆኖ ነው ያገኘው፡፡አንድ ሺ ካሬ ሜትር በላይ የሚሆን ቅፅር ግቢ ነው፡፡መሀከል ላይ ግዙፍና ባለግርማ ሞገስ ጥንታዊ ግን ደግሞ ጥሩ ይዞታ ላይ ያለ ግዙፍ ቪላ ቤት አለበት…ግቢው ውስጥ እድሜ ጠገብ ግዙፍ ባለግርማ ሞገስ የባህር ዛፍና የጥድ ዛፎች ስብስባ ላይ እንደተቀመጠ ታዳሚ እዚህም አዛም ዙሪያውን ተሰራጭተው ይታያሉ…ገና ግቢውስጥ ገብተው እንዳቆሙ የቤት ጠባቂዎች በልና ሚስቶች በፍጥነት መጥታው መኪናዋ አጠገቡ ቆሙ፡፡መኪናዋን ሲነዳ የነበረው እራሱ ሰሎሞን ስለነበረ….ሞተሩን

አጠፋና ቀድሞ ወረደ…አቶ ኃይለመለኮትን ወ.ሮ ስንዱም ወረዱና ከጠባቂዎቹ ጋር ሰላምታ መለዋወጥ ጀመሩ…ከዛ ቀጥታ ወደ ቤት ነው የገቡት….ቀድመው ደውለው ስለነበር..እቤቱ ምሉ በሙሉ ፀድቶና የእነሱም መኝታ ክፍል ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው….
ታፈሰ ‹‹ጋሼ ባዘዙኝ መሰረት ሶስት ክፍል ለመኝታ አዘጋጅቼያለው…ይሄው እርሶ እዚህ ግቡ….እትዬ ደግሞ ቀጥሎ ያለው …ወንድም አንተ ደግሞ የፊት ለፊተኛው ክፍል…..ድንገት ስለሆነብን ሁሉንም ነገር ማዘጋጀት አልቻልንም….የጎደለውን ንገሩኝና ከተማ ወጣ ብዬ ገዝቼ አሟላላሁ››
አቶ ሃይለመለኮት ወደሰለሞን እያመለከቱ‹‹ተፈሰ…ይሄውልህ እዚህ 15 ቀን ነው የምንቆየው….በዚህ 15 ቀናት ውስጥ የእኛም ሆነ የአንተ ሀለቃ እሱ ነው….ምንም ነገር ቢያዝህ እሱ ያለውን ነው የምታደርገው…እኛም እንደዛው››ሲሉ መመሪያ አስተላለፉ፡፡
ታፈሰ…የአቶ ኃይለልዕልን ንግግር ከበፊት ቆፍጣና ባህሪያቸው ጋር አልሄድ ስላለው ..ግራ በመጋባት አፍጥጦ ያያቸው ጀመር…እሱ እንደሚየውቀው እኚ ግዙፍ አዛውንት ለሰው ምንም ሊሰጡ ይችላሉ የአዛዥነት ቦታቸውን ግን ፈፅሞ ሸርፈው እንኳን ለሌላ ሰው ይሰጣሉ ብሎ ማመን ይከብደዋል፡፡
‹‹ታፈሰ ..ሰምተኸኛል…የሁሉ ነገር አዛዣችን እሱ ነው››ደገሙለት፡፡
‹‹አዎ ..ገባኝ ጌታዬ…እንዳሉት ይደረጋል››
‹‹አሁን ሁላችንም ወደክፍላችን እንግባና ትንሽ አረፍ እንበል ..አይደል?››ወ.ሮ ስንዱ የሰለሞንን አይኖች በልምምጥ እያዩ ጠየቁ፡፡
ቆይ አንዴ ክፍላችሁን ልይ ብሎ..ለአቶ ኃይለልኡል የተመደበውን ከፍቶ አየው፡፡ቀጥሎ የወ.ሮ ስዱን ከፈተና አየው፡፡‹‹ጥሩ በቃ ግቡና እረፉ››
ሁለቱም ገቡና የየራሳቸውን ክፍል ዘጉ
‹‹አንተም ወደክፍልህ ግባ ጌታዬ..እኔ ደግሞ እቃችሁን ከመኪና ላውርድ››
‹‹ቆይ አብሬህ ልምጣ››ብሎ ተከተለው፡፡የታፈሰ ባለቤት ለእንግዶቹ ምግብ እያበሰለች ስለነበር ታፈሰ እቃዎቹን ማለት ይዘው የመጡትን አስቤዛ እና ሻንጣዎች ሲያወርድና ወደቤት ሲያስገባ ሰሎሞን አገዘው፡፡እንደጨረሱ፡፡‹‹ተለቅ ያለ ክፍል የለም?››ሲል ጠየቀው፡፡

‹‹ምን አይነት ክፍል…ማለቴ ለምን የሚሆን?››
‹‹ለመኝታ ቤት የሚሆን ..ሁለት አልጋ የሚያዘረጋ››
‹‹ቆይ ..ኮሪደሩ መጨረሻ ላይ ያለው ክፍል ሰፋ ይላል››
‹‹ማየት እችላለሁ?››
‹‹አዎ ይቻላል….››ብሎ ይዞት ሄደና ከፈተለት…ሰለሞን ወደውስጥ ዘልቆ ሳይገባ በራፉ ላይ በመቆም አንገቱን ወደውስጥ አስግጎ ተመለከተው….አቦራ የጠጣና ለብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ ያልዋለ ቢሆንም የሚፈልገው አይነት ክፍል ነው፡፡››
‹‹ታፈሰ ይሄንን ክፍል በአስቸኳይ ልታስፀዳልኝ ትችላለህ….?››
‹‹እችላለሁ..አፀዳዋለው››
‹‹አይ ብቻህን ይከብድሀል..ሰው ቅጠርና በፍጥነት ወለሉም ግድግዳውም ይፅዳ….ውስጥ ያሉት እቃዎችም ወደሌላ ክፍል ይዘዋወሩ››
‹‹እሺ››
ተሰናብቶት ንፁህ አየር ሊቀበልና እግረመመንገዱን አካባቢውን ለመቃኘት ወጥቶ ሄደ፡፡
///
በማግስቱ ጥዋት 3 ሰዓት ላይ ሁለቱንም የማይጣጣሙ ባለትዳሮችን አንድ ክፍል ጎን ለጎን እንዲቀመጡ አደረገና እሱ ከፊት ለፊታቸው ተቀመጠ..ጉሮሮውን አፀዳዳና የመግቢያ ንግግሩን ጀመረ
‹‹በሰዎች መካከል ለተለያየ አለማ ተብለው የሚደረጉ የእርስ በርስ ጉድኝቶችና ቁርኝቶች አሉ፡፡ከነዛ መካከል ግን በጣም ውስብስቡ የጠበቀውና የጠለቀው ግንኙነት በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል የሚፈጠር የጋብቻ ጉድኝት ነው፡፡በጋብቻ ውስጥ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ሁሉ ጊዜ ቀላል የተባለ መንገድ አይገኝም….አንዱ ጋብቻ ውስጥ የሚፈጠረው ችግር ከሌላው ጋብቻ ችግር በአይነትም በይዘትም ፍፁም የተለየ በመሆን ችግሩን ለማስተካከል የሚወሰደውም እርምጃ የዛኑ ያህል የተለያ ነው፡፡በዛ ላይ ሁሉም ችግሮች እዲፈቱ  በጥንዶቹ  መካከል  ስክነት፣  ትዕግስትን፣ጥረትን  እና   እራስ  መግዛትን

ይጠይቃል፡፡አሁን ልብ በሉ ፣ጥረታችን በመካለላችሁ ያላውን ግጭትና ጭቅጭቅ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ አይደልም..አይ እንደዛማ አይሆንም እናንተ ሰው ናቸው፣ሁለት ሰዎች ደግሞ በአንድ ጣሪያ ስር አብረው እስከኖሩ ድረስ በሆነ ነገር መነጋገራቸውና በነገሩ ላይ የተለያየ ተቃራኒ ሃሳብ ማንፀባረቃቸው አይቀርም…ስለዚህ መነጋገርና መጨቃጨቃችሁ ኖርማል ነው…አሁን ምንድነው ምናደርገው በማንኛውም ጉዳይ ላይ አለመግባባት ተከስቶ ስትነጋገሩ በምን መልኩ ነው ኮምንኬት የምታደርጉት..?ነገሩን ማስረዳትና ማሳመን ላይ ነው ትኩረታችሁ ወይስ ያንን ምክንያት አድርጎ በስድብና በዘለፋ ማጥቃትና ልብ መስበር…አያችሁ ትልቁ ችግር መጋጨታችን ሳይሆን በያንዳንዱ ግጭታችን አንዳችን ለሌላቸውን የልብ ቁስለትና የነፍስ ህመም መስጠታችን ነው፡፡ማጥፋት ያለብን እርስ በርስ መወጋጋቱን ነው…አንዳችን ሌላችን ላይ በምንም አይነት ሰበብ የሚያቆስል ጦር አስበን አይደለም አምልጦን እንኳን መወርወር የለብንም፡፡
እርስ በርስ ከፍ ባለ ቃላት በተነጋገራችሁ ቁጥር ደግሞ እየተጣላችሁ መሆኑን አታስቡት..መጣላት ቃሉ እራሱ አሉታዊ ነው፡፡እየተጣላችሁ ሳይሆን በጋለ ስሜት እየተነጋገራችሁ ነው፡፡በቃ እንዲህ ነው ማሰብ ያለባችሁ፡፡እንደዛ ካሰባችሁ ቀጥታ ችግሩ በጋለ ስሜት መነጋገራች ብቻ ስለሆነ ስሜታችሁን በማረጋጋት ነገሩን ትፈታላችሁ፡፡እየተጣላን ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ግን ገና ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ወይም ሽማግሌ ልትፈልጉ ነው፡፡ልብ በሉ ጮክ ብሎ መናጋገር ሁል ጊዜ መጣላት አይደለም ..አዎ አብዛኛውን ጊዜ በጋለ ስሜት መነጋገር ነው፡፡ሌላው በምንም አይነት ሁኔታ ንግግራችሁ ሰው ፊት አይሁን፡፡የምንወደው ሰው ላይ ያለንን ቅሬታ ብቻውን በሆነበት ጊዜ ነው መናገር ያለብን…እንደዛ ሲሆን ነው ውጤታማና ጥፈቱን ለማረም ፍቃደኛ የሚሆነው…ወቀሳው..ሰው ፊት ሲሆን ግን ሰውዬው የበለጠ በእኛ ቅሬታ እንዲያድርበት መንገድ ያመቻቻል፡፡
‹‹እንግዲ ሁላተችሁም እንደምታውቁት አሁን ለእኛ እዚህ መገኘት ዋናዋ ምክንያት በፀሎት ነች፡፡እኔ በስራ በተለይ ከሀገር ውጭ በነበርኩበት ጊዜ በጣም ብዙ ባለትዳሮችን አማክሬያለሁ ትዳራችውም መካከል ያለውን ችግር በመተጋገዝ ለመፍታት ችያለሁ....በብዙዎችም ረክቼለው..ከብዙ ቤተሰቦች ጋርም እቤተሰብ ለመሆን ችያለው….ግን እመኑኝ እንዲህ እንደእናነተ የተለየ ጉዳይ ገጥሞኝ አያውቅም››

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

16 Dec, 18:29


.ከሶስት ቀን በኃላ
አቶ ለሜቻ ነገሮችን ተቀብለው….ቱታቸውን ለብሰውና ሌሎች ሁለት ሰዎችን ቀጥረው ቀጥታ ቤቱን ወደመገንባት ስራ ገቡ..ይሔ ሁኔታ የቤቱን ሰው ሁሉ በጣም ሲያስደስት በፀሎትን ደግሞ በይበልጥ አስፈነጠዛት፡፡ቢያንስ አንድ ነገር ልታደርግላቸው በመቻሏ የውስጥ እርካታ ተሰማት….ማንነቷን በሚያቁበት ቀን መልሰው ብስጭት እና ቁጭት ውስጥ እንደሚገቡ እርግጠኛ ነች..ቢሆንም ግን ምርጫ ያላትም…በዚህ ጉዳይ ላይ እሷቸው ትክክል ናቸው ብላ አታስብም…ሰው እርስ  በርሱ  መረዳዳትና  አንዱ  የሌላውን  ኑሮ  ማቃናት  ያለና  የነበረ  ተግባር

ነው….እሷቸው ይሄንን ጉዳይ ከክብር አንፃር ማየታቸው የእሷቸውን ኑሮ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላ የቤተሰቡ ኑሮ እየጎዳ ያለው፡፡
ስራውን ከጀመሩት በኃላ እንደፊቱ አልከበዳቸውም..እንደውም ይበልጥ ጉጉት አሳደረባቸውና ከወር በኃላ ለሚከበረው ከልጃቸው የ3ተኛ አመት የሙት አመት መታሰቢያ ቀን በፊት ጥንቅቅ አድርገው መጨረስ አቅደው ቀን ከሌት መስራት ጀምረዋል፡፡አዎ ልጃቸው በህይወት ብትኖር ኖሮ እሰከዛሬ ይሄንን ቤት ሰርታ እንደምትጨርስ ያምኑ ነበር…አሁንም የሙት አመት መታሰቢያዋን ሲደግሱ የሙት መንፈሷ ሊያያቸው እንደሚመጣ እርግጠኛ ናቸው… ታዲያ ያንን ጊዜ ለእነሱ ቤት መስራት ህልሞ ስለነበረ ተሰርቶ ስታየው በጣም ደስ ብሏት እንደምትመለስ እርግጠኛ ናቸው…፡፡
እንደ ወትሮ መሽቶ ቤተሰቡ ሁሉ ተሰብስበው በሳቅና በጫወታ እራታቸውን በልተው ቡና ተፈልቶ ተጠጥቶ ከተጠናቀቀ በኃላ አምስት ሰዓት አካባቢ ሁሉም ሰው ወደመኝታው ሄደ…ፊራኦልም የውስጡን በውስጡ ይዞ ልክ እንደወትሮ እንደተኛ ሰው ሆኖ አደፈጠ…..በጨለማ ውስጥ አፍጥጦ እስከሰባት ሰዓት ድረስ በሀሳብ ሲባትት ነበር…ልክ ሰባት ሰዓት ሲሆን ቀስ ብሎ ከተኛበት ሶፋ ላይ ተነሳና መብራቱን አበራ ..የቤቱን ዙሪያ ገባ ቃኘ….በፀሎትና ለሊሴ ተዘረጋግተው እንደተኙ ነው፡፡ከወላጆቹ ክፍልም ምንም የሚሰማ እንቅስቃሴ የለም…..ቀስ ብሎ ወደሴቶቹ መኝታ ተጠጋ… ሁለቱም አይናቸውን ጨፍነው ጥልቅ የሚባል እንቅልፍ ውስጥ ናቸው፡፡ይሄኔ ህልም እያለሙ እንደሚሆን ገመተ…ቀስ አለና በፀሎት በተኛችበት በኩል ዞሮ ከራስጌዋ ጎን ካለ መቀመጫ ላይ ተቀመጠ…ቁልቁል አዘቅቆ አያት…ቀስ ብሎ እጁን ዘረጋና ፊቷ ላይ የተጠቀለለውን ሻርፕ ጫፍ ይዞ ጎተተው…ቀስ በቀስ ከፊል ፊቷ እየታየው መጣ …ሻርፑን ሙሉ በሙሉ ከፊቷ አስወገደእና በትኩረት ይመለከታት ጀመር…..ድንገት ተገላበጠችን በጀርባዋ ተንጋለለች ..በዛን ጊዜ ሙሉ በሙሉ ለእይታው ተጋለጠች….አሁን እርግጠኛ ሆነ…ምንም እንኳን የተወሰነ መጓሳቆል ቢታይባትም …ምንም እንኳን ቀኝ የፊቷ ክፈል ላይ ብዛት ያላቸው ጭረቶችና ጠባሳዎች ቢኖሩም እራሷ ነች…ለአመታት በድብቅ ከሩቅ ሲያያት የነበረችው..የእህቱን ውድ ልብ በውስጧ የተሸከመችው ልጅ….
‹‹እሺ አሁን ምንድነው የማደርው?››እራሱን ጠየቀ…ቀስ ብሎ ሻርፑን መልሶ ፊቷን ሸፈነና ከተቀመጠበት ተነስቶ መብራቱን አጠፋና ወደ መኝታው ተመለሰ….ሙሉ ለሊቱን እንቅልፍ ሊወስደው አልቻለም…..
አሁን ያወቀውን ነገር ባያውቅ ምኞቱ ነበር….አንዳንድ ማወቆች ሸክማቸው ያጎብጣል..አውቆ የሆነ ነገር ማድረግም አለማድረግም እዲህ አስቸጋሪ ሲሆን ምነው ምንም ነገር ባላወቅኩ ኖሮ ያስብላል፡፡ይህቺን ልጅ አፍቅሯት ነበር…የሞች እህቱን ልብ የተሸከመችው ልጅ መሆኗን ሳያውቅ በፊት ከእሷ ፍቅር ይዞት ነበር..ለእሷም ሆነ ለማንም ይሄንን ስሜቱን ተናግሮ አያውቅም….ግን እሱ በፍቅር እንደተነደፈ እርግጠኛ ነበር‹‹እሺ አሁን ምንድነው የማደርገው….?››እራሱን ጠየቀ…ብዙ ጊዜ ስለፍቅር ና ውበት ሲያወራ እርዕስ የምትቀይረውና ወሬውን የምትገፋው ለምን እንደሆነ አሁን ገባው…‹‹ይህቺ ልጅ ተአምረኛ ነች››ሲል አሰበ‹‹እራሷን በበሬዱ ቦታ ለመተካት እየጣረች ነው…አዎ ወደቤታችን የመጣችው ድንገት በአጋጣሚ ሳይሆን ሆነ ብላ አስባና አቅዳበት ነው… አንተ ወንድሜ ነህ ስትለኝ እንዲሁ ለአባባል ብቻ የምትጠቀምበት ይመስለኝ ነበር..ለካ እሷ ከአንጀቷ ነው፡፡››ሲል አሰበና በድቅድቅ ጨለማው ፈገግ አለ….‹‹ይሄን ጉድ ወላጆቹ ሲሰሙ ምን አይነት ምላሽ እንደሚሰጡ አሰበ…..ለመገመት አንኳን አልቻለም፡፡በተለይ አባቱ በበሬድ ጉዳይ ስሜተ ስስ እንደሆነ ያውቃል….ፈራ …በጣም ፈራ…. ‹‹ግን እሷስ እስለመቼ እንዲህ ከወላጆቾም ተሰውራ እውነቱን ከእኛም ደብቃ ትዘልቃዋለች..?እቅዷ ምንድነው?››ሊገባው አልቻለም፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

07 Nov, 12:44


ሳንፎርድ፡ ዘመናዊ እና ቦታን የሚቆጥብ የቤት እቃዎችን ለ ቤትዎ

ጥራት እና ጥንካሬ መለያችን የሆንን ሳንፎርድ ፈርኒቸር ለቤትዎ ዘመናዊ እና ቦታን የሚቆጥብ የቤት እቃዎችን ይዘን ከች ብለናል።

ሶፋ ፣ አልጋ ፣ የቲቪ ማስቀመጫ ፣ የመመገብያ ጠረጰዛ እና ወንበር ዲዛይኖቻችንን ከምቹነት ከጥራት እንዲሁም ከውቤት ጋር የተጣመሩ ናቸው።

ከ15 አመት በላይ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች እርሶዎን በሚመጥን ዋጋ ቤቶትን እናሳምርልዎ!!!

አሁኑኑ ይደዉሉ ፦ +251978777775 / +251976777775

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

06 Nov, 13:27


ቤቶን እና ቢሮዎን እናሳምርልዎ

ሳንፎርድ ፈሪኒቸር

👉🏼 ለልጆዎ ምቾት ጥራት ያላቸው አልጋዎች፣
👉🏼 ለቤትዎ ዘመናዊ እና ውብ ቲቭ ስታንዶችን፣
👉🏼 ለቢሮዎ ውበትን ከጥራት ጋር ያዋሃዱ ጠረጴዛ እና ወንበሮች፣
👉🏼 እንዲሁም ለኪችኖ ፤ በፈለጉት ድዛይን የሚያምሩ ኪችን ካቢኔቶችን፣ በተመጣጣኝ ዋጋ ሰርተን እናስረክብልዎ!!!

ወርክ ሾፕአችንን ጦር ሀይሎች ወደ ቤተል በሚወስደው መንገድ ድሪም ታወር አጠገብ ያገኙታል።

ለበለጠ መረጃ፡ 0978777775/0976777775 አሁኑኑ ይደውሉ!

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

25 Oct, 12:58


ሳንፎርድ፡ ዘመናዊ እና ቦታን የሚቆጥብ የቤት እቃዎችን ለ ቤትዎ

ጥራት እና ጥንካሬ መለያችን የሆንን ሳንፎርድ ፈርኒቸር ለቤትዎ ዘመናዊ እና ቦታን የሚቆጥብ የቤት እቃዎችን ይዘን ከች ብለናል።

ሶፋ ፣ አልጋ ፣ የቲቪ ማስቀመጫ ፣ የመመገብያ ጠረጰዛ እና ወንበር ዲዛይኖቻችንን ከምቹነት ከጥራት እንዲሁም ከውቤት ጋር የተጣመሩ ናቸው።

ከ15 አመት በላይ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች እርሶዎን በሚመጥን ዋጋ ቤቶትን እናሳምርልዎ!!!

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

19 Oct, 06:58


ወጣት ነህ፣ ትማራለህ ፣ ምንም ገቢ የለህም
ወይም ሰራተኛ ነህ ገቢህ በቂ አይደለም, በside የonline ስራ ለመስራት ያልፈነቀለከው ድንጋይ የለሞ: ግን ጠብ የሚል ነገር የለም::


ከላይ የነገርኳቹህ ችግሮች የኔም ችግሮች ነበሩ: መስራት እየቻልኩ ትናንሽ ወጪዎችን እንኳን ከቤተሰብ መጠበቅ ከባድ ነበር

ብዙ ሞክሬ የዩኒቨርሲቲ ተመሪ እያለሁ የጀመርኩት የ Facebook Ad Agency በወር ከ 70ሺ - 100ሺ ገቢ እያመጣ ቢዝነሴን እንዳቋቁም ጉልበት ሰቶኛል።

ዮናስ እባላለሁ፣ አሁን ላይ የ 2 ድርጅት መስራች እና ስራ አሰኪያጅ ነኝ::

የኔን ህይወት የቀየረውን Facebook Advertising አሰራር ፤ እያንዳንዱን ነገር ላሳያችሁ የፊታችን ጥቅምት 9 እና 10 የ Online Webinar አዘጋጅቻለሁ

በዚህ Webinar
- እጅግ ታማኝ እና እኛ የምንጠቀምበትን የ Mastercard አወጣጥ Live አሳያችኋለሁ
- ጥሩ የሚከፍል ደንበኛ እንዴት እንደምታገኙ እናያለን
- ብዙዎቻችሁን ያስመረረው Facebook ad Restriction እንዴት መከላከል እንደምትችሉ።

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

18 Oct, 05:17


ወጣት ነህ፣ ትማራለህ ፣ ምንም ገቢ የለህም
ወይም ሰራተኛ ነህ ገቢህ በቂ አይደለም, በside የonline ስራ ለመስራት ያልፈነቀለከው ድንጋይ የለሞ: ግን ጠብ የሚል ነገር የለም::


ከላይ የነገርኳቹህ ችግሮች የኔም ችግሮች ነበሩ: መስራት እየቻልኩ ትናንሽ ወጪዎችን እንኳን ከቤተሰብ መጠበቅ ከባድ ነበር

ብዙ ሞክሬ የዩኒቨርሲቲ ተመሪ እያለሁ የጀመርኩት የ Facebook Ad Agency ተማሪ በወር ከ 70ሺ - 100ሺ ገቢ እያመጣ ቢዝነሴን እንዳቋቁም ጉልበት ሰቶኛል።

ዮናስ እባላለሁ፣ አሁን ላይ የ 2 ድርጅት መስራች እና ስራ አሰኪያጅ ነኝ::

የኔን ህይወት የቀየረውን Facebook Advertising አሰራር ፤ እያንዳንዱን ነገር ላሳያችሁ የፊታችን ጥቅምት 9 እና 10 የ Online Webinar አዘጋጅቻለሁ

በዚህ Webinar
- እጅግ ታማኝ እና እኛ የምንጠቀምበትን የ Mastercard አወጣጥ Live አሳያችኋለሁ
- ጥሩ የሚከፍል ደንበኛ እንዴት እንደምታገኙ እናያለን
- ብዙዎቻችሁን ያስመረረው Facebook ad Restriction እንዴት መከላከል እንደምትችሉ።

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

17 Oct, 15:38


‹‹እንዴት እንዲህ ይሆናል..?ይሄ እኳ የእኔ ሞት ነበር›…በምን እዳህ ሞቴን ትሞትልኛለህ..?››ተንበርክካ አቅፋው ትወዘውዘው ጀመር….፡፡ሁሉ ነገር አስጠላት….፡፡‹‹በቃ እኔም አብሬህ መሞት ነው የምፈልገው…››ይሄንን ስትወስን ስለመንትያ ወንድሟ እንኳን ማሰብ አልፈለገችም፡፡.ከካርሎስ  ጋር ተስተካክላ ተኛች፡፡መሳሪያውን በጉሮሮዋ ትክክል አስተካከለች..እጆን ዘርግታ ምላጩን ለመሳብ ሞከረች…ግን አልተመቻትም…..፡፡የመሳሪያውን አቅጣጫ  ቀየረች..በዛ ቅፅበት ግን ጭለማ የዋጠው አዳራሽ በብርሀን ተጥለቀለቀ…የብርሀኑ መጠን ከአይኗ ማየት  አቅም በላይ ስለሆነ ጨፈነች…ብዛት ያላቸው የእግር ኮቴ እና የመሳሪያ ቅጭልጭልታ ሰማች…ደስ አላትና መሳሪያውን ለቀቀች፡፡ የካርሎስን በድን አቅፋ ተኛች..የእሷ ሀሳብ እየመጡ ያሉት የዳግላስ ሰዎች ስለሆኑ እዛው በተኛችበት ተኩሰው በመግደል ከካርሎስ ጋር እንድትሞት ያደርጉኛል ብላ ነበር….ስሯ ደርሰው አንጠልጥለው ሲሸከሞትና በብስጭት አይኖቾን ገልጣ ሰታያቸው ግን ያሰበቻቸው እንዳልሆኑ ገባት፡፡የአካባቢው መንግስት ወታደሮች እንደሆኑ ተረዳች..ወዲያው አንከብክበው ወስደው ወደውጭ አወጧት…በአካባቢው ክንፏን ጥላ የተኮፈሰች ዳኮታ አውሮፕላን ውስጥ   ይዘዋት ሲገቡ ወንድሞ ናኦል የሆነ አረንጓዴ ፎጣ ተከናንቦ በድንጋጤ እየተንቀጠቀጠ አየችው፣ከጎኑ ስትቀመጥ…ከወለሉ ላይ የተዘረረውን የምስራቅን አስከሬን ተመለከተች፡፡ወንድሟ ላይ ተጠመጠመችበት…..አውሮፕላኗ  በአየሩን እየሰነጠቀች ጥቅጥቁን የአማዞን ደን አናት ላይ እየተምዘገዘገች ብራዚሊያ ስታርፍ ሁሉ ሁለቱ መንትዬች እንደተቀቀቀፉ  ነበር፡፡
….
እንግዲህ ዛሬ ያ ክስተት ከተከሰተ ከአራት ቀን በኃላ እዛ አማዞን ስምጥ ውስጥ የሆነውን እና ያዩትን በጠቅላላ ለሚመለከተው አካል መረጃ ሰጥተው…የካርሎስም እሬሳ ከሌሎች ተለይቶ ከቦታው ተነስቶ ወደቤተሰቦቹ እንዲላክ አድርገው…የምስረቅን ሬሳ  በሚያምር ውብ ሳጥን አሳሽገው ወደሀገራቸው ለመብርር  ዝግጁ ሆነው እየጠበቁ ነው፡፡
ግን መንትዬቹ ከዚህኛው እጦታቸው እና የልብ ስብራታቸው ያገግሙ ይሆን….?ደግመኛ ለማፍቀርስ መች ይሆን ዝግጁ የሚሆኑት…?ለዚህ ሁሉ ጥያቄ ለጊዜው መልስ ባይኖርም አንዳቸው ለአንዳቸው ሲሉ በህይወት መኖራቸውን  እንደሚቀጥሉ ግን በእርግጠኝነት ማወቅ ይቻላል፡፡

ተፈፀመ።

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

17 Oct, 15:37


‹‹እየተኮሰች ተሸለክልካ በመሀከላቸው ያለውን ርቀት ወደሳባት ሜትር አጠበበች…፡፡አሁን በግልፅ እየታያት ነው….አልማ ተኮሰች…ሆዱን ቦተረፈችው…አጎራና መሬት ተዘረረ…..፡፡ከግራና ከቀኝ ጠባቂዎች ወጡና ግማሹ ወደእሷ እየተኮሱ ለጓደኞቻቸው ሽፋን መስጠት ጀመሩ፡፡ ሁለቱ ደግሞ በደም የጨቀየውን ዳግላስን እየጎተቱ ወደተከፈተው ጉድጎድ አስገቡት…ወደታች ይዘውት ወረዱ.፡፡ከዛ እነሱ ተከተሉ…አንዱን ግንባሩን ብላ አስቀረችው፡፡ወደጉድጓዱ ተስፈነጠረች…ወንድሟን ይዘውት ሄደው ከሆነ መከተል አለባት…አንድ እርምጃ ሲቀራት እንዴት እንደሆነ በማታውቀው ዘዴ ወለሉ ተመልሶ ተዘጋ ፡፡ወደውስጥ የሚያሾልክ ምንም አይነት ቀዳዳ ሆነ ክፍተት በአካባቢው የለም፡፡መሳረያውን በወለሉ ላይ አርከፈከፈች…በንዴትና ተስፋ መቁረጥ በጉልበቷ ተናበረከከች…በዚህ ጊዜ ከኃላዋ አንድ በጣም ደስ የሚል ከገነት የመሰላ የጥሪ ድምፅ ሰማች‹‹…ኑሀም ኑሀሚ››
‹‹ዞር አለች››
‹‹ኑሀሚ ካርሎስ ነኝ››
ተንደርድራ ድምፅ ወደሰማችበት አካባቢ ተስፈነጠረች…..ኦ እራሱ ነው….በወገቡ ዙሪያ ቦንብ ደርድሮ እንደዘንዶ የተጠመዘዘ ዝናር በጀርባው አንጠልጥሎ ዘመናዊ አውቶማቲክ መሳሪውን ደቅኖ አገኘችው…ተጠመጠመችበትና ከንፈሩ ላይ ተጣበቀች….
‹‹የእኔ ፍቅር መጣህ..ይሄ ጉድጓድ እንዴት ነው የሚከፈተው? የምታውቀው ነገር አለ..?ወንድሜን ይዘውት ሳይሄዱ አይቀርም››ቃተተች፡፡
‹‹ተረጋጊ ውዴ..ወንድምሽን ወደውጭ ነው ይዘውት የሄዱት….ምስራቅ ልታስጥለው ተከትላዋለች ፡፡ሚረዷትን ሁለት የእኔን ሰዎች ሰጥቻታለው፡፡ስለአንቺ ስትነግረኝ አንቺን ለማስመለስ ነው ወደእዚህ የመጣሁት››
‹‹እንዴት ?ማለቴ ምስራቅን እንዴት አወቅካት?››ግራ ያጋባትን ነገር ጠየቀችው፡፡
‹‹የእሷንም የወንድምሽንም ፎቶ እኮ አሳይተሸኛል….እሷም ካርሎስ ነኝ ስላት አወቀችኝ…በይ አሁን ቶሎ ብለን ከዚህ ስፍራ እንውጣ…….››
ተያይዘው ወደግራውንድ ፍሎር መውጫውን ደረጃ ተያያዙት ፡፡መሳሪያ ከወዲህ ወዲያ ይተኮሳል፤ ራቅ ብሎ ቦንብ ይፈናዳል..የሰው ጩኸትና ለቅሶ ከየቦታው ይሰማል..አየሩ የተጠበሰ እና ያረረ የሰው ስጋ በክሎታል፡፡የግራውንድ ፍሎሩ ላይ በሰላም ደረሱ፡፡ ወደውጭ ወደሚያስወጣቸው በራፍ እየተቃረቡ ሳለ….የአውሮፕላን ድምፅ ሰሙ ካርሎስ እሷን ከስር አደረገና ከላዬ ላይ ተኛባት..ወዲያው የሚያደበላለቅ የፍንዳታ ድምፅ ተሰማ፡፡
…../////….
ምስራቅ ከህንፃው እንደምንም ተሹለክልካ መውጣት ከቻለች በኃላ በቋጥኞች መካከል እራሷን ሸሽጋ ናኦልን ፍለጋ አካባቢውን መቃኘት ጀመረች….ከውስጡ ይልቅ ውጩ በጨረቃ ብርሀን የፈካ ስለሆነ ለእይታ ምቹ ነው፡፡ ብዙም ሳትደክም ሶስት ጋንግስተሮች ናኦልን መሀከላቸው አድርገው በቅርብ እርቀት ወደሚገኝ የጥበቃ ማማ ይዘውት ሲሄዱ ተመለከተች፡፡ከዛ ወደእዛው ለመሄድ ወደግራዋ ዞር ስትል ከእሷ አንድሜትር ርቀት ከፊት ለፊቷ ካለው ቁጥቋጦ ውስጥ የተወሸቀ አንድ ሰው በግንባሯ ትክክል መሳሪያውን ደቅኖ ተመለከተች…ፊቷ ላይ ባትሪውን ለቀቀባት..
በእጇ ላይ ያለው የቦንብ ቀለበት ውስጥ እጣቶን ሰንቅራ…አሳየችው….፡›
‹‹ተረጋጊ ..ካርሎስ ነኝ››ሲላት እፎይታ ተሰማት‹‹ኑሀሚስ?››አስከትሎ ያቀረበላት ጥያቄ ነበር፡፡
ከዛ ከኃላው የነበሩ ሁለት ሰዎችን ጠርቶ እንዲረዷት ነገራቸውና እሱ ኑሀሚን ፍለጋ ወደውስጥ ገባ…..
…////..
ምስራቅ ካርሎስ የሰጣትን ሁለቱን ሰዎች ከኃላዋ አስከትላ ናኦል ወዳለበት ተጠጋች….ሰዎቹን ለማደናገር ናኦል ካለበት ሀያ ሜትር ርቀት አካባቢ ባለች ጎጆ ቤት ላይ ቦንቡን ወረወረች፡፡ አካባቢው በፍንዳታ ተናጋ ፡፡በናኦል ዙሪያ የነበሩ ጋንግስተሮች ሀሳብ ተበታተነ ፡፡በዚህ ጊዜ ምስራቅ አጠገቧ ያሉ አጋዞቾን ናኦልን እንዳይመቱ እየተጠነቀቁ ተኩስ እንዲከፍቱ አዘዘቻቸውና እሷ በጀርባ በኩል ዞራ በደረቷ መሳብ ጀመረች…፡፡አሁን በሶስት ሜትር ርቀት ናኦል እየታያት ነው፡፡በዙሪያው ያሉት ጋንግስተሮች ተበታትነው ሁለት ብቻ ናቸው የቀሩት …ከጀርባቸው ተስፈነጠረችና በአንደኛው ላይ እጆቾን በጉሮሮው ዙሪያ ሰቅስቃ አንገቱን ቀነጠሰችው፡፡በግራ ያለው ጓደኛው መሳረያውን ወደእሷ ሲያዞር ከጎኑ ያለው ናኦም ተጠመጠመበት….መሳሪያው ያለ ኢላማ መንጣጣት ጀመረ……፡፡ምስራቅ በፍጥነት ደረሰችለትና የሰውዬውን ፊኛ በእርግጫ ነረተችው…፡፡.አጓራና መሳሪያውን ለቀቀው..፡፡ናኦል ወዲው መሳሪያውን በማንሳት በልቡ አካባቢ ለቀቀበት..፡፡ሰውዬው ፀጥ አለ….፡፡ምስራቅ ናኦል ላይ ተጠመጠመችበት‹‹…ተርፈሀል..ኦዎ አገኘሁህ›› ብላ ግንባሩን ጉንጩን ትልሰው ጀመር…..፡፡‹‹እወድሀለው እሺ …በጣም ነው ምወድህ…ደግሞ አልፈታህም..እሺ…ደግሞ…..››ንግግሯን ሳትጨርስ መሳሪያ ሲንጣጣ ሰሙ ..ግን አርፍደው ነበር…የተተኮሱት ጥይቶች ሁሉ በምስራቅ ጀርባ ውስጥ ነበር የተቀረቀሩት…ላካ ከጀርባ ከለላ ይዞ የጎደኞቹን ሞት ሲመለከት የነበረ ሌላ ጋንግስተር ነበር….የካርሎስ ጓደኞች ተኩሱን ተከትለው ወደተኳሹ ደራርበው በመተኮስ ገደሉት..ግን ያመጣው ውጤት አልነበረም፡፡ ምስራቅ በናኦል እቅፍ ውስጥ እንዳለች ዝልፍልፍ ብላ ወደታች መንሸራተት ጀመረች፡፡
….///..
የአውሮፕላኑን ጆሮ ሰንጣቂ ድምፅ ተከትሎ ህንፃ ውስጥ የነበሩረው ካርሎስ ኑሀሚን ከስር አድርጎ እሱ ካላዬ ተኛ…ወዲያው ከአውሮፕላኑ በተለቀቀ ከባድ ቦንብ አካባቢው በፍንዳታና በእሷት ጉማጅ ተናጋ…የሰው ጆሮ ጭው ከሚያደርግ ቀፋፊ ድምፅ ውጭ ሌላ ነገር መስማት አቆመ…ማንም በህይወት ያለ ሰው አይኑን መከፈት አቃተው….ምፅአት የታወጀ መሰለ፡፡ከምን ያህል ደቂቃ በኃላ እንደሆነ አታውቅም….ኑሀሚ ወደቀልቦ ቀስ በቀስ ተመለሰች..ገሮሮዋን ክፉኛ እየከረከራት ነው..መተንፈስም ከባድ ሆኖባታል…እንደምንም አይኗን ስትከፍት ከላዮ ካርሎስ ተኝቶል..‹‹የእኔ ፍቅር…ታፈንኩ እኮ..‹››ምንም እየመለሰላት አይደለም…እንደምንም ከላዬ አንከባለለችውና ከስሩ ሾልካ ወጣች..የሆነ የተደፋ ውሀ አካባቢውን ያጥለቀለቀው መሰላት… ተነከረችበት…ካርሎስን ወዘወዘችው……በእጁ ይዞት የነበረውን ባትሪ ተቀበለችውና አባራችበት፡፡ውሀ የመሰላት ደም ነበር..ካርሎስ ጭንቅላቱ ከኃላ በኩል ፈርሶል ….ጀርባው በቦንብ ፍንጥርጣሪ ወንፊት ሆኖል፡፡.ህልም ውስጥ ያለች ነው የመሰላት፡፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

17 Oct, 15:37


የመጨረሻ ክፍል
ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-34
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

‹‹በል አስወጣቸው››ዳግላስ አንቦረቀ፡፡
‹‹ምን እየሆነ ነው ምን አጠፋን?››ኑሀሚ በተመሳሳይ የድምፅ ቃና  ጠየቀችው፡፡
‹‹ጠላቶቼ ይሄንን ቦታ እንዴት ሊያውቁት ቻሉ?››
‹‹እኛ ታዲያ ምን እናውቃለን? የራስህን ሰዎች አትመረምርም››
‹‹መሳሪያውን ወደ ግንባሯ ደቀነና‹‹እንደንዴቴ ሶስታችሁንም እዚህ ግንባር ግንባረችሁን ደፍቼያችሁ እሄድ ነበር፡፡ግን እንዳደረሳችሁብኝ ኪሳራ በሰላም እና በቀላሉ መሞት አይገባችሁም…ሶስታችሁም እባክህ ግደለን እያላችው በየቀኑ እንድትለምኑኝ ነው የማደርገው…በተለይ አንቺን…በሉ ያዟቸው..››

እሱን ከበው የነበሩ ጋንግስተሮች ወደቤት ውስጥ ገቡን ሶስቱንም እየገፈተሩ ወደውጭ አስወጣቸው…..በኮሪደሩ አልፈው ሳሎን ገቡ …ከዛ በደረጃው ወደግራውንድ ይዘዋቸው ሄዱ…ሰው ሁሉ ይተረማመሳል….መሳሪያዎች ከመጋዘን እየወጡ ይታደላሉ..ሀገር ወራሪ መጥቶ ለፊልሚያ እየተሰናዱ ነው የሚመስለው….ወደምድር ቤት ይዘዋቸው ወረዱ….ምድር ቤት ያለው  ትርምስ ከግራውንዱም ይብሳል….የተመረቱትን ኮኬይን አሰተካክለው ካርቶን ውስጥ በማስገባት ያሽጋሉ… ሌሎች ደግሞ የታሸገውን ወደጥግ እየወሰዱ ይደረድራሉ….ዳግላስ  እነኑሀሚን ለጠባቂዎቹ ተዋቸውና እያንቧረቀ ትእዛዝ በመስጠት ወደሰራተኞቹ ሄደ፡፡
‹‹እንዴ ይሄን ሁሉ ኮኬይን የሚደረድሩት እንዴት ሊየደርጉት ነው?››ምስራቅ ነች በሹክሹክታ የጠየቀችው፡፡
ኑሀሚን‹‹አልገባኝም ….ምን አልባት…..››ብላ ግምቷን መናገር ስትጀምር ያልጠበቁት ነገር ከፊት ለፊታቸው ተመለከቱ፡፡ የምድር ቤቱ ጥግ ላይ ያለ ወለል እንዴት አድርገውት እንደሆነ አይታወቅም ሲከፈት አዩ…
‹‹እንዴ!! ከዚህ በታች እቤት አለ እንዴ?››ናኦል ነው በገረሜታ የተናገረው፡፡
‹‹አይ እቤት አይመስለኝም….ከዚህ አካባቢ                                   ማምለጫ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ነው፡፡
‹‹አንቺ እውነትሽን ሳይሆን አይቀርም…››
ስትል ሰዎች በካርቶን የታሸገውን ካርቶን እየተሸከሙ በተከፈተው ወለል በመሄድ እንደመሰላል  ባለ ብረት እየተንጠለጠሉ ወደታች መውረድ ጀመሩ፡፡፡
‹‹ሰዎች ትክክል ነኝ…ይሄ ከዚህ ስፍራ ማምለጫ የምድር ውስጥ መንገድ ነው….እናም እኛንም በዛ ውስጥ ይዘውን ሊሄዱ ነው››ኑሀሚ ነች ተናጋሪዋ፡፡
ምስራቅ‹‹የሆነ ነገር ማድረግ አለብን ..እዛ ውስጥ ይዘውን ገብተው ከዚህ ካስመለጡን እንዳለው ለወራት አስቃይቶ ነው የሚገድለን..መሞታችን ካልቀረ ደግሞ እዚሁ ለማምለጥ እየሞከርን ብንሞት ይሻላል››
‹‹ትክክል ነሽ ለማምለጥ መሞከሪያ ጊዜው አሁን ነው››ናኦልም በምስራቅ ሀሳብ ተስማማች፡፡
ምስራቅ ‹‹ናኦል››ስትል ተጣራች፡፡
‹‹በጣም ነው የምወድህ እሺ፣ማለቴ አፈቅርሀለው››አለችው፡፡
‹‹አውቃለው እኔም አፈቅርሻለው…ግን እያስፈራሺኝ ነው››
‹‹አትፍራ….ኑሀሚ አንቺንም ወድሻለው››
አቦ አንቺ ደግሞ አትረብሺኝ …ኑዛዜ አስመሰልሺው….ትኩረቴን እየበታተንሺው ነው…..ተመልከቱ እነዛ ሁለት ሰዎች ለእያንዳንዱ ሰው የእጅ ቦንብ እያደሉ ነው….ሲቀርብን በፍጥነት የተወሰነ ቦንብ በእጃችን ማስገባት አለብን…ከዛ…..››ኑሀሚ ንግግሯን ሳታገባድድ ምስራቅ ወደጎን ተስፈንጥራ  ጠረጴዛ ስር ሾልካ በመግባት ስትሰወር እነሱን ሲጠብቁ የነበሩ ጠባቂዎች የሚወስዱት እርምጃ ግራ ገብቷቸው ወዲህ ወዲያ ሲራወጡ ኑሀሚ የናኦልን ክን ድ ይዛ በግራ በኩል ስትሮጥ ከጠባቂዎቹ አንዱ ተወርውሮ የናኦል እግር ላይ ተጠምጥሞ አስቀረው….ኑሀሚ ወንድሟን ለቃ ሩጫዋን ቀጠለችና ከኮኬይኑ ካርቶን ጀርባ ተሰወረች….አንዱ መሳሪየውን ደቅኖ ተከተላት…በአየር ላይ ተንሳፈፈችን ጉሮሮውን ዘጋችለት…እጥፍጥፍ ብሎ ስሯ ወደቀ..መሳሪያውን ተቀበለችና ምላጩን ተጭና ዝም ብላ አንደቀደቀችው…እቅዷ ትርምስ መፍጠር ነው…ያሰበችው ተሳካላት፡፡ ሰው በፊትም ስጋትና ድንጋጤ ላይ የነበሩ ሰራተኞች የመሳሪያ መንደቅደቅ ሲሰሙ ሚይዙት የሚጨብጡት ጠፍቷቸው ከወዲህ ወዲያ መተረማመስ ጀመሩ ፡፡ይህ ደግሞ ለነኑሀሚ ጥሩ ሁኔታ ፈጠረላቸው፡፡
///
ወደቀኝ ታጥፋ ጠረጴዛ ተከልላ የተሰወረችው ምስራቅ ተንሸራታ ቦንብ የምታድለው እንስት ላይ ነው የተከመረችባት …ልጅቷ በድንጋጤ ቦንብ ያለበትን ካርቶን ለቀቀችው፡፡ መሬት ወድቆ ተዘረገፈ….ምስራቅ ልጅቷን በአንድ እጇ ይዛ በሌላ እጆሶስት ሚሆኑ ቦንቦችን ያዘች….ከግራ በኩል ይተኮስባት ጀመር..ምርጫ ስላልነበራት ልጅቶን ከፊት ለፊቷ  አቆመቻት…የሚተኮሰው ጥይት ሁሉ ልጅቷ ሰውነት ውስጥ ተሰገሰገ….ምስራቅ ወደኃላ አፈገፈገችና ቦታዋን ለቀቀች….ተኳሹ መሬት ላይ ከተዘረገፍት ቦንቦች አንድን አገኘው….አካባቢው ባልተጠበቀ ፍንዳታ ተናጋ…ዋና ዋና መብራቶቹ ጠፉና ጭላንጭል ድንግዝግዝ ብርሀን ብቻ ቀረ… ምድር ቤቱ በጥቁር ጭስ ተዋጠ…ምስራቅም ኑሀሚም በየፊናቸው  ናኦልን ሲፈልጉ ድንገት ተገናኙ….

‹‹ናኦልን አይተሸዋል…?››ኑሀሚ ነች ጠያቂዋ፡፡
‹‹አላየሁትም እየፈለኩት ነው፡፡ወደውጭ ይዘውት ወጥተው ሊሆን ይችላል›››ምስራቅ መለሰች፡
‹‹አይ በምድር ውስጥ ይዘውት ገብተው ከሆነስ..?እኔ ወደእዛ ልሂድ አንቺ ወደውጭ ውጪና ፈልጊው፡፡››
‹‹እርግጠኛ ነሽ….?››
‹‹አዎ ጊዜ አናጥፋ…››ተስማሙ……
ምስራቅ ወደውጭ መውጫው ከሚራኮቱት ሰዎች ጋር እየተጋፋች ስትሄድ ኑሀሚ ደግሞ ወደውስጠኛው የምድር ውስጥ መሹለኩያ ሮጠች…..፡፡
ኑሀሚ አስር ሜትር ርቀት ሲቀራት ወደእሷ ተተኮሰባት… ወደግራዋ ተስፈነጠረችና የሆነ የብረት ካዝና ስር ከለላ ይዛ እራሷን ለመከላከከል መተኮስ ጀመረች…

‹‹አንቺ ሸርሙጣ..ነይ ውጪ››የዳግላስ ድምፅ መሆኑን ለየች….እልክ ተናነቃት፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

17 Oct, 15:37


ከእሷ ፍቅር  ከካርሎስ የተላከ መልእክት እንደሆነ ገባት፡፡‹‹እኛን ለማስመለጥ ነገ ልክ በዚህን ሰዓት ጥቃት ይፈፅማሉ ማለት ነው›› ስትል አሰበችና ..ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደመታጠቢያ ቤት ስትሄድ ዳግላስ ደግሞ ታጥቦ ሲወጣ መንገድ ላይ ተላለፉ ፡፡
ታጥባ እንደመጣች ከመቀመጧ በፊት ከመንገድ ላይ ተቀብሎ‹‹ወደበረንዳ እንሂድ›› አላት፡፡   ፊለፊት ወደሚታየው የሳሎኑ በረንዳ ይዞኝ ይሄዳል ብላ  ጠብቃ ነበር ..እሱ ግን በተቃራኒው ወደውስጥ ነበር እየጎተተ የወሰዳት፡፡ ግራ ገባት…፡፡መኝታ ቤቱን ከፈተና ወደውስጥ አስገባት…፡፡ወለሉ መሀል ላይ ያለው አስር ሰው የማስተኛት ብቃት  ያለው  የነገስታት የሚመስለው ግዙፍ አልጋ ነጭ እና ውብ አልጋልብስ ለብሶ ይታያል፡፡ ሙሉ አልጋውና ወለሉ  በአጠቃላይ በአበባ ተበትኖበት ለሙሽራ የተዘጋጀ ክፍል ይመስላል..ይሄንን አይነት ክፍል ይዟት የገባው ካርሎስ ቢሆን ኖሮ በደስታ ብዛት እራሷን ሁሉ ልትስት ትችል ነበር..አሁን ግን ድንጋጤና ፍርሀት ነው የተሰማት፡፡ ቀጥታ መኝታ ቤቱን ሰንጥቆ አለፈና የኃላውን በራፍ በመክፈት ወደባልኮኒው ወጣ…በፍዘትና በተንቀረፈፈ እርምጃ ተከተለችው፡፡ባልኮኒው ላይ ሁለት ምቹ ወንበሮች እና አንድ በመጠጥ የተሞላ  ውብ አነስተኛ ጠረጴዛ  አለ…አንድን እንድትቀመጥበት ጎተተላትና ከተቀመጠች በኃላ ሌለኝ ላይ ተቀመጠ…በእውነት  ባልኮሊው ላይ ተቀምጦ  ጥቅጥቁን የአማዛን ደን በዛ ጭለማ ስትመለከት ልዩ አይነት የድንዛዜ አይነት ስሜት ነው የተሰማት….በአለም ላይ የሚገኝ አንድ ውስን ቦታ ሳይሆን በቤርሙዳ ቀለበት ውስጥ ሾልካ ሌላ ፕላኔት ላይ የተጣለች አይነት ስሜት እንዲሰማት ነው ያደረጋት..መጠጡን እየተጎነጩ ብዙም ያልደመቀ የፈራችውን ያህልም በውጥረት ያልተጨናነቀ ገዜ እያሳለፉ ቀጠሉ…የዚህ የእራት እና የመጠጥ ግብዣው መጨረሻ የቱ ላይ እንደሚያከትም እንዳስጨነቃት ነው..ግን ደግሞ እንዲህ አይነት ፈተና የሚገጥማት ለዚህች ቀን ብቻ ነው‹‹ ልክ ነገ  በዚህን ሰዓት የእኔ ጀግና ከሌሎች ዳግላስን ማጥፋት ከሚፈልጉ  ጠላቶቹ ጋር በመተባበሩ ያስመልጠኛል…ከዛ ምን አልባትም…ሁሉነገር እንደታሰበው በድል ተጠናቆ ከምወደው ካርሎስ ጋር በደስታ ተቃቅፌ ምሳሳምበት ሰዓት ይሆናል››በማለት በውስጦ አሰበችና ሳይታወቃት   ፈገግ አለች፡፡
ሁኔታዋን በትኩረት ሲከታተል የነበረው ዳግላስ ‹‹ፈገግታው ከምን የመነጨ ነው?››ሲል ጠየቃት
‹‹እየሰከርኩ መሰለኝ ይሄ መጠጥ ይብቃኝ….››አለችውና ከጥያቄው ጋር የማይገባኝ መልስ ሰጠችው፡፡
‹‹ገና መች ጀመርነውና….ዘና ብለሽ ጠጪ..እንደምታይው አልጋውም ዝግጁ ነው››አላት..፣፣ለእሱ እስኪታወቀው ድረስ ደነገጠች፡፡
‹‹አይዞሽ አትደንግጪ…መተኛት ብቻ ነው….ሳትፈልጊ የሚሆን ነገር የለም››አላት
‹‹ይሄ ያንተ ባህሪ አይደለም››አለችው
‹‹እና የማን ባህሪ ነው?››  በፈገግታ ጠየቃት፡፡
‹‹እዛ ሊማ አውሮፕላን  ውስጥ አግኝቼው የነበረው  የሚስኪኑ ዳግላስ  ባህሪ ነው››
‹‹ያው እሱን ነው የምወደው ስላልሽ፣ካንቺ ጋር ባለኝ ግንኙነት በተቻለኝ መጠን እሱን ለመሆን እየጣርኩ ነው››
‹‹ይሳካልህ ይመስልሀል?››
‹‹አዎ የአንቺን ልብ ለማሸነፍ …..የግድ ሊሳካልኝ ይገባል››አላትና የጎደለውን ብርጭቆዋን ሞላላትና የእሱን እየቀዳ እያለ ኪሱ ውስጥ ያለው ሞባይል ድምፅ አሰማ ..ጠርሙሱን አስቀመጠና ስልኩን ከኪሱ አውጥቶ ከፈተና አየው..ደነገጠ፡፡
‹‹ምንነው ?ምን ተፈጠረ?››
የኮሎምቢያው ምክትል ጠ/ሚንስቴር ነው የደወለልኝ..በጣም ወሳኝ ጉዳይ መሆን አለበት …አለና አነሳው፡፡ይሄ ሰው የአካባቢው መንግስታትን ጉምቱ ባለስልጣኖች በጉቦ አጨማልቆ እየተጠቀመባቸው እንደሆነ አሰበች በጣም ተገረመች፡፡ እያወሩ ያሉት በስፓኒሽኛ ስለሆነ ምን እየተነጋገሩ እንደሆነ መረዳት አልቻለችም..ግን ከዳግላስ ንዴትና የፊት መቀያየር ነገሩ ከበድ ያለ እንደሆነ ገብቷታል…ስልኩን ዘጋና ከተቀመጠበት ተነሳ….ወደመኝታ ቤቱ ሄደ..በተቀመጠችበት ሆና እየተከታተለችው ነው፡፡ጎንበስ አለና ቁም ሳጥኑ ስር ያለውን ካዝና ከፈተ ፡፡የሆኑ ሰነዶችን አወጣና በአነስተኛ ቦርሳ ከተተና ትከሻው ላይ አንጠለጠለው፡፡ሽጉጡን አወጣና አቀባበለ…ከዛ በግራ በኩል ወዳለው ግድግዳ ሄደና የሆነ የብሬከር ሳጥን የሚመስል የፕላስቲክ ክዳን ያለውን ነገር ከፈተና ተጫነው..ጆሮ ሰቅጣጭ ሳይረን ግቢውን አናጋው…..ግቢውን ለሚጠብቁ ጋንግስተሮችና ለመላው የግቢው ኑዋሪዎች አደጋ ላይ መሆናቸውን እንዲያውቁ ያደረገው ነገር እንደሆነ ገባት፡፡ ኑሀሚ ከመደንገጧ የተነሳ ከተቀመጠችበት መነቃነቅ አልቻለችም..ቀጥታ ወደእሷ ሄደና የያዘውን ሽጉጥ ግንባሯ ላይ ደቅኖ በአንድ እጁ ክንዷን በመያዝ እየጎተተ  ከመኝታ ቤት ይዞት ወጣ.፡፡ሳሎኑ ባዶ ነው፡፡ቀጥታ ወንድሟና ምስራቅ ወዳሉበት ክፍል ነው ይዞት የሄደው …በራፉ ጋር ሲደርሱ ሽጉጡን ከግንባሯ አነሳና የበራፍ ቁልፍ ላይ አነጣጥሮ ተኮሰው ፡፡ የበራፉ ቁልፍ ብረቶች ተበታትነው ወለሉ ላይ ወደቁ ..በእርግጫ ሲለው በራፉ ወለል ብሎ ተከፈተ…፡፡
ምስራቅና ናኦል እርቃን ሰውነታቸው ከአልጋ ላይ ተንከባለው ወርደው እራሳቸውን ከጥቃት ለመከላከል ከለላ ለመያዝ ሲሞክሩ  ነበር…ዳግላስ ኑሀሚን ወደውስጥ ወረወራትና በራፉን  መልሶ ዘጋው…..፡፡
ሁለቱም ከያሉበት ወደኑሀሚ ተንደረደሩና ከግራና ከቀኝ አቀፏት‹‹ምንድነው የሆነው…?.ሳይረኑ ምንድነው…?ለምንድነው የተበሳጨብሽ…?ልትገይው ሞክረሽ ነው?››በጥያቄ ብዛት አጣደፋት፡፡
‹‹አይደለም…ከኮለምቢያ ም/ጠቅላይ ሚንስቴር የሆነ ስልክ ከተደወለለት በኃላ ነው ነገሮች ሁሉ የተቀያየሩት..››
‹‹ወይኔ  የእኛ ሰዎች ሊያስመልጡን እየሞከሩ መሆናቸው ነግረውት ነው፡፡››
‹‹አዎ እንደዛ መሰለኝ….የእነካርሎስ እቅድም ይሰናከላል..በቃ አሁን እራሳችንን ለማዳን መንቀሳቀስ አለብን››
‹‹ምን እናድርግ››
ኑሀሚ የለበሰችውን የእራት ቀሚስ ከላዬ ላይ ሞሽልቃ አወጣችና  የራሷን ሱሪ ለበሰች..ሁሉም ልብሳቸውን እና ጫማቸውን አድርገው ዝግጁ ሆኑ፡፡
‹‹እናንተ እዚህ ጠብቁኝ እኔ  ይሄንን  የመስኮት ግሪል የምናፈርስበትን ነገር ይዤ እመጣለው፡፡››አለች ኑሀሚ፡፡
‹‹እንዴ ግሪሉ በምን ይፈርሳል…?››ግራ የገባው ናኦል ጥያቄ አቀረበ፡፡

‹‹እኔ እንጃ አላውቅም…፡፡ብቻ መሳሪያም ቢሆን ይዤ መጣለሁ፡፡ከዛ ከእዚህ ዘለን ገንዳ ውስጥ ለማረፍ እንሞክራለን… ››
‹‹ብንሰበርስ?››

‹‹እንሰበራ …ዋናው ማምለጣችን ነው››

ምስራቅ‹‹እንደዛ ከሆነ እኔ እሻላለሁ….እኔ ልሂድ›› ብላ ወደውጭ መራመድ ስትጀምር ኑሀሚ ፊቷ ተጋረጠች….፡፡
ኑሀሚ ለመስማማት አልፈቀደችም‹‹እኔ እሄዳለው አልኩሽ…››.ብላ እሷን ወደውስጥ ገፍትራ ልትወጣ በራፍን ስትከፍት ዳግላስ አስፈሪ ሆነው  አስፈሪ መሳሪያ በታጠቁ አራት ሰዎች ታጅቦ በራፍ ላይ ገጭ አለባት…..ከዛ በድንዛዜ ወደኃላዋ አፈገፈገች፡፡

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

17 Oct, 15:35


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-33
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ናኦልና ኑሀሚ ብራዚል ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ  ይገኛሉ.. ከኢትዬጵያ ደህንነት መስራቤት ተልእኮ ተሰጥቶችው የመጡ ሁለት የደህንነት ሰዎች አብረዋቸው አሉ…ሁለቱ መንትዬች በኮንክሪት ግግር እንደቆመ ሀውልት ጎን ለጎን ተጣብቀው  ቆመዋል…ከፊት ለፊታቸው በአንድ ሜትር ርቀት አንድ የታሸገ የሬሳ ሳጥን ወለል ላይ ተቀምጦ ይታያል…እሬሳውን ጭኖ ወደኢትዬጵያ የሚበረው አውሮፕላን በሰላሳ ሜትር ርቀት ላይ ይታያል…እዛ ሬሳ ሳጥን ውስጥ ለዘላለም አሸልባ  የተኛችው ምስራቅ ነች፡፡

ናኦል እና ኑሀሚ ከዳግላስ ወጥመድ አምልጠው የሲኦል ወጥመድ ከሆነው ከእዛ ጥቅጥቅ ደን ውስጥ ወጥተው እንሆ አስተማማኝን ቦታ ላይ ቆመዋል…ከአንድ ሰዓት በኃላ በአገራቸው አየር መንገድ ወደሀገራቸው ለመብረር ዝግጅታቸውን ሁሉ አጠናቀዋል…ግን እዚህ ለመድረስ የከፈሉት መሰዋዕትነት ሁለቱንም እስከወዲያኛው ያፈራረሳቸው ነው፡፡አሁን በድናቸው ነው የሚንገዋለለው፡፡እግዚያብሄር በእድሜያቸው መጀመሪያ በዛ በህፃንነታቸው ጊዜ  ሚወዱዋቸውን ወላጆቻቸውን በመንጠቅ አሸማቆቸው ነበር  በእድሜያቸው አጋማሽ ደግሞ በእድሜ ልካቸው አብራቸው የነበረችውን፤ ከጎዳና አንስታ ህይወት የሰጠቻቸውን፤የተዘረፈውን  የወላጆቻቸውን ንብረት ያስለመለሰልችላቸውን.. እናም ከዛም አልፍ እሷን ለማትረፍ አህጉር አቆርጣ እዚህ ሁሉ ጣጣ ውስጥ የገባችላቸውን የዚህችን  ሴት ህይወት ማጣት ለሁለቱም ቅስም ሰባሪ ነው፡፡ለናኦል ደግሞ ነገሩ የተለየ ነው….ይህቺን ሴት ገና የ12 ዓመት ልጅ እያለ እዛ በረንዳ ፤ላይ ካያት ቀን ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ይወዳት ነበር…እዚህ ነገር ውስጥ ያስገባት እራሱ ነው፡፡እህቴ ጠፋችብኝ አፋልጊኝ ብሎ ደወላላት..እሱን ለመርዳ ከጎሬዋ ወጣች..ለብቻው ልትተወው ስላልፈለገች አህጉር አቋርጣ ተከትላው መጣች ..አንድ ወር ሊደፍን ትንሽ ቀን ለቀረው ቀናት በመከራና በስጋት ውስጥ ቢሆኑም እንኳን እጅግ ጣፋጭ የሆነ የፍቅር ህይወት አሳልፈዋል….የህይወትን ጣእም እና የፍቅርን ትርጉም አሳይታዋለች ..አስተምራዋለች፡፡….ከእሷ ጋር የመሰረቱት የውሸት ትዳር ለእሱ በህይወቱ ካጋጠመው ተጨባጭ እውነቶች መካከል ምን እልባትም ዋነኛው  ነው…በሰላም ወደሀገራቸው ሲመለሱ ለምኖና እግሯ ላይ ወድቆ ጋብቻቸው ባለበት እንዲቀጥልና በእሷ እቅፍ ውስጥ ለዘላለም መቅለጥ ነበር የሚፈልገው፡፡እቅዱ እንደዛ ነበር….ብቸኛ ምኞቱም ያ ነበር..፡፡ግን አሁን ሁሉ ነገር እንዳልነበረ ሆኗል….፡፡በሰልም እየሰቀችና እተፍለቀለቀች አብራው የመጣችው ሴት ይሄው ህይወት አልባ በድን እሬሳ ሆነ  በሳጥን ውስጥ ታሽጋ  ወደሀገሯ እየተመለሰች ነው፡፡እና ደግሞ በጣም እያበሳጨው ያለው ነገር  ምንም እንዳልተፈጠረ በህይወት ቆሞ አየር እየሳበ መሆኑን ሲያስብ ነው….ደግሞ እኮ የእሱን ሞት ነው ሞተችው፡፡
ነገሩ እጌት ነው  የተከሰተው  ብለን ወደኃላ ዞረን ስናስታውስ……
..
ከአራት ቀን በፊት  ነው፡፡ከምሽቱ ሁለት ሰዓት አካባቢ  የታገቱበት ክፍል ተከፈተ….የመጣው  የተለመደው የዳግላስ ተላላኪ ነው፡፡
ወደኑሀሚ አትኩሮ እየተመለከተ ‹‹ጌታዬ እየጠበቀሽ ነው››አላት፡፡

ኑሀሚ ከ30 ደቂቃ በፊት አምጥቶ የሰጣትን ውብ የራት ቀሚስ ለብሳና ተዘጋጅታ  የጠበቀችው ነበር፡፡ምስራቅንና ወንድሟ ናኦልን ተራ በተራ ጉንጫቸውን ሳመችና በዝግታ እርምጃ ልጁን ተከትላ ወጣች፡፡ቀደም ብሎ የተላከላትን ቀሚስ ለብሳ ወደታባለችው የእራት ግብዣ መሄድ የምርጫ ጉዳይ አይደለም…ግዴታ ነው..፡፡በሰዓቱ እያስጨነቃት የነበረው  ከእራት ቡኃላስ ሚለው ነበር?….ወደአልጋ እንሂድ ቢለኝስ?እንደዛ ስታስብ ዝግንን የሚያደርግ ቀፋፊ ስሜት ነበር የተሰማት፡፡እሷ ግን እኮ እንደዛ አልነበረችም፡፡ለአላማዋ ጥቂትም ጥቅም ይኑረው እንጂ ከማንም ወንድ ጋር ተጋድሞ ወሲብ መፈፀም ልክ እንደካርታ ጫወታ  ዘና ብላ ምትፈፅመው ቀላልና ትርጉም የማይሰጣት ጉዳይ ነበር…ደግሞም በሰላይነት ሕይወቷ እንዲጠቅማት በእንደዚህ አይነት ጉዳይ ላይ በቂ ስልጠና ወስዳለች…አሁን ግን አንድ ነገር ገብቷታል..ለካ በዛን ጊዜ ነገሩ ቀላልና የማያስጨንቅ ሆኖ የሚታያት  ስለሰለጠነችበት ብቻ አልነበረም…ልቧ ኦናና ባዶ ስለነበረ ነበር እንጂ፡፤አሁን ግን አንድ ሰው ገብቶበታል…ያ ሰው ደግሞ እሷን ለማዳን በቅርብ ርቀት ባለ ጫካ ውስጥ ሆኖ እቅዱን ስለሚያሳካበት ዘዴ እየተጨነቀና እያሰበ ነው…እና  እሷ ካለፍላጎቷም ቢሆን ከሌላ ሰው ጋር ወደአልጋ የመሄድን ጉዳይ በቀላሉ ምታየው አይደለም….ይሄ ነው ያስጨነቃት…የተንጣለለው ሳሎን ውስጥ ስትገባ ግዙፉ ጠረጴዛ በምግብና በመጠጥ ተሞልቶ ተመለከተች፣አንድ ሴትና ሁለት ወንድ አስተናጋጆች ፈንጠር ብለው ግድግዳውን ተደግፈው ትእዛዝ በመጠባበቅ ላይ ናቸው…እንደገባች ዳግላስ ከተቀመጠበት ተነሳና ወደእሷ ተራመደ…ቀለል ያለ አለባበስ ነው የለበሰው…ከላይ ሰማያዊ ሸሚዝ ከዳለቻ ጅንስ ሱሪ ጋር አድርጎል…በፈገግታ ተጠጋትና እጁን ለሰላምታ ዘረጋላት…ፈራ ተባ እያለች እጇን ሰነዘረችና ጨበጠችው፡፡

እጇን ሳይለቅ እየጎተተ ወደ ጠረጴዛው ወሰዳትና  ወንበር ስቦ አስቀመጣት..ከዛ ራመድ አለና  ከፊት ለፊቷ ሄዶ ተቀመጠ፡፡ወዲያው ለአስተናጋጆች በእጁ ምልክት ሲያሳይ ተንደርድረው መጡና ብርጭቆቸውን በመጠጥ ሞልተውላቸው ወደቦታቸው ተመለሱ፡፡
ከተቀዳለት መጠጥ አንዴ ጠቀም አድርጎ ከተጎነጨለት በኃላ‹‹እንዴት ነው ቆይታ ?››ሲል ጠየቃት፡፡
ያለምንም ማስተባበል‹‹በጣም አሰልቺ ነው››ስትል ፍርጥም ብላ መለሰችለት፡፡
‹‹እንግዲህ የአጋጣሚ ጉዳይ ሆነና ለስራ ጉዳይ ወጣ ማለት ነበረብኝ…አሁን ግን ተመልሼለው…ከዚህች ደቂቃ ጀምሮ ፍፅም ደስተኛ እንድትሆኚ የተቻለኝን አደርጋለሁ…ከነገ ጀምሮ የአማዛንን ድንቅ ውበት ጎዲያ ጎድጓዳዋን እያዞርኩ አሳይሻለው..እንስሳቱን ፤ወፎችን ፤ፏፏቴዎችንና ወንዙን ሁሉንም አንድ በአንድ አሳይሻለው..እናም ከቦታው ጋር በፍቅር እድትተሳሰሪ የተቻለኝን እጥራለው..ከቦታው ብቻ ሳይሆን ከእኔም ጋር ፍቅር እንዲይዝሽ እፈልጋለው››ሲል ተናዘዘላት፡፡
‹‹እርግጠኛ ነህ ከአንተ ፍቅር እንዲይዘኝ ማድረግ ትችላለህ?››
‹‹እንግዲህ እቅዴ እንደዛ ነው››
‹‹ጥሩ ነው››ብላ በአጭሩ መለሰችለት
‹‹ምኑ ነው ጥሩ?››በጫወታው እንዲገፉበት ስለፈለገ ጥያቄውን ቀጠለበት፡፡
‹‹እስከማውቅህ ድረስ ሁሉንም ነገር    በጉልበትና በማስግደድ ነው የምታደርገው…..ቡኃላ እንዳፈቅርህ ማድረግ ሲያቅትህ እንዳትተኩስብኝ ነው የምፈራው…፡፡››ስትለው ከጣሪያ በላይ ተንከትክቶ ሳቀ..‹‹በይ በባዶ ሆዴ ከዚህ በላይ መሳቅ አልችልም ..እራት እንብላና ወደበረንዳ ወጣ ብለን መጠጣችንን እየተጎነጨን የጀመርነውን ጫወታ እንጨርሰዋለን…››አለና ሰሀን አነሳ …እሷም እንደእሱ አደረገኝ..እራት በልተው አስኪያጠናቅቁ ሀያ ደቂቃ አካባቢ የፈጀባቸው ሲሆን በዛን ጊዜ ውስጥ ብዙም የረባ  ነገር እልተነጋገሩም…፡፡.እራቱ እንደተጠናቀቀ ዳጋላስ እጁን ሊታጠብ ቀድሞ ወደመታጠቢያ ክፍል ገባ …ወዲያው ከአስተናጋጆቹ አንዱ እቃ የሚያነሳሳ መስሎ ተጠጋት እና ጎንበስ ብሎ‹‹ነገ በዚህን ሰዓት››አላት፡፡፡አልገባትም‹‹ዋት››አለችው፡፡ደገመላት‹‹ነገ በዚህን ሰዓት..ተዘጋጁ››ብሎ የተበላበትን  ሰሀን ሰበሰበና እንዳቀረቀረ ከሳሎን ወጥቶ ሄደ፡፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

15 Oct, 16:34


‹‹ሰውዬው ነካ ያደርገዋል እንዴ?››በማለት እያጉረመረሙ ሶስቱም በንዴት ወደክፍላቸው ገቡ ፡፡

‹‹ሰውዬው ግን እንዴት አንቺን ነጥሎ ጠረጠረ..ነው ወይስ ወዶሽ ይሆን….?››ምስራቅ ነች በቀልድ መልክ አስተያቷን የሰነዘረችው፡፡


   ‹‹ ባክሽ እርሺው ብሽወቅ ነገር ነው…የሚናገረውን ነገርም አያውቅም እኮ!! እስኪ እዚህ ኪሴ ውስጥ ምን ይኖራል?›› ብላ እጇን ወደኪሷ ስትከት የሆነ ነገር አገኘች፡፡ወዲያው መዛ አላወጣችውም…‹‹ወደሽንት ቤት ግቢ››የሚለው የሰውዬው ትዕዛዝ ትዝ አላት…ሁሉም ነገር ትርጉም ሰጣት፡፡‹‹ቆይ ሽንቴ መጣ ብላ ወደሽንት ቤት ሮጠችና ገብታ በራፉን ከውስጥ ቀረቀረች፡፡እጇን ወደኪሷ ከተተች፡፡ አወጣች፡፡ ወረቀት ነው፡፡እርግጠኛ ነች፡፡ይሄንን ወረቀት ያስቀመጠላት የፈተሸት ወታደር እንደሆነ እርግጠኛ ነች፡፡‹‹ግን ማን ነው የላከላት?መልዕክቱ ምንድነው ?….በመስገብገብ ገለጠችው፡፡ማንበብ ቀጠለች፡፡

የእኔ ፍቅር ከአንቺ አጠገብ ነው ያለሁት፡፡ትንፋሽሽ ሁሉ ይሰማኛል..የልብ ምትሽ ድውድውታም ልክ እንደ ጃዝ ሙዚቃ እያዳመጥኩት ነው….ከነገ በኃላ በማንኛውም ሰዓት የሆነ ነገር ሊፈጠር ስለሚችል ሶስታችሁም ዝግጁ ለመሆንና ላለመነጣጠል ሞክሩ….ፍንዳታ ስትሰሙና ግርግር ሲፈጠር እንደምንም ከህንጻው እንዴት መውጣት እንደምትችሉ ከአሁኑ አስቡበት፡፡በተቻለ መጠን ከውስጥ የሚረዳችሁ ሰው እናመቻቻለን፡፡ ከዛ በጀርባ ባለው በመዋኛ ገንዳው በኩል ወዳለው ጫካ ነው የምትመጡት….በዛ በኩል ያለውን ጥበቃ ቀድመን ስለምናፀዳው ሁሉ ነገር ቀላል ይሆናል….በይ ይሄንን ወረቀት እንዳነበብሽ አስወግጂው…ይሄ ቅዠት አብቅቶ አብሬሽ ወደኢትዬጵያ እስክጓዝ ቸኩያለሁ››ይላል…..

ውስጧን የሚያነዝር አይነት ደስታ ነው የተሰማት…ከዚህ በፊት ከወደደችው በላይ ወደደችው…እናም ደግሞ ናፈቃት…አሁን በዚህችው ደቂቃ አግኝታ ልትጠመጠምበትና ልትስመው ተመኘች..ወረቀቱን አፎ ውስጥ ከተተችና አኘከችው….ከራሰና ከተበጣጠቀ በኃላ ገንዳ ውስጥ ተፋችውና ውሀውን ለቀቀችበት ፤እየተበታተነ በቱቦ ውስጥ ገብቶ ተሰወረ….አፏን ተጉመጠመጠችና የተቀረቀረውን ክፍል ከፍታ ወጣች…ወንድሟና ምስራቅ አልጋው  ላይ ጎን ለጎን ተኝተው ሲጎነታተሉ ነበር የደረሰችው፡፡የእሷን መምጣት ሲመለከቱ አደብ ገዝተው በተኙበት እሷን መመልከት ጀመሩ፡፡ወደእነሱ ሄዳ መሀከላቸው ሰቅስቃ ገባችና እንደእነሱ ተጋደመች፡፡
‹‹እህቴ ደግሞ ››ናኦል ተነጫነጨ

‹‹እህቴ ምን?››

‹‹ይሄ ሁሉ ክፍት ቦታ እያለልሽ በመሀከላችን ምን አስገባሽ?››

‹‹እንደውም እነዚህ ሰዎች እራት እስኪያመጡልን ትንሽ እንተኛ…››የሚል ያልጠበቁትን ሀሳብ አቀረበች፡፡

‹‹እንተኛ…?.በዚህ ሰዓት ?ገና አንድ ሰእት እኮ ነው››ናኦል ተቃውሞውን አሰማ፡፡

‹‹አውቃለሁ ግን እንተኛ በቃ….ከውስጥ ግቡ ››አለችና ብርድልብሱን ሰቅስቃ ከውስጥ ገባችና እነሱም እንዲገቡ አደረገች….ምስራቅ ኑሀሚ ለምን ባልተለመደ መልኩ በዚህ ሰዓት መተኛት እንደፈለገች ለማወቅ ሰልጓጓች እናድርግ ያለቻትን ያለተቃውሞ አደረገች …ናኦል ግን ምንም የጠረጠረው ነገር ስለሌለ አሁንም በንጭንጩ እንደገፋበት ነው፡፡

መተኛታችን ካልቀረ እኔ ብቸኛ ወንድ ስለሆንኩ ከመሀከላችሁ ልተኛ?››አዲስ ጥያቄ አቀረበ፡፡

‹‹አይቻልም ይልቅ ብርድልብሱን ተከናነቡ››ኑሀሚ ፍርጥም ብላ ሀሳቧን ሰነዘረች፡፡

ሙሉ በሙሉ በብርድልብሱ ተሸፋፈኑ፡፡ ሁለቱንም እጇቾን  በሁለቱም አንገት  ሰቅስቃ አስገባችና ወደደረቷ አስጠግታ አቀፈቻቸው››ከዘ ሁለቱንም ጆሮ ወደአፎ እንዲጠጋ ካደረገች በኃላ በሰለለ ሹክሹክታ‹‹እንድንሸፋፈን የፈለኩት ከሰዎቹ ካሜራ ለመሰወር ነው፡፡የምነግራችሁ ነገር አለኝ…ካርሎስ የዳግላስን ጠላቶች አሳምኖ ይዞቸው መጥቷል…እዚሁ አጠገባችን ቅርብ ቦታ ነው ያሉት..እዚህ መሀከላችንም ሰው አላቸው…ቅድም ሲፈትሸኝ ነበረው ሰውዬ ከእነሱ ጋር ነው የሚሰራው…እንደዛ ያደረገው ለአኔ መልእክት ለማሳተላለፍ ብሎ ነው…ከነገ ጀምሮ በማንኛውም አመቺ በሆነ ሰዓት ጥቃት ይፈጽማሉ..ምንኛውንም አይነት ተኩስ ወይም ፍንዳታ ስንሰማ ከእዚህ ህንጻ በአፋጣኝ ለመውጣት መሞከር እንዳለብንና ከወጣን በኃላ በጓሮ በኩል ባለው የማዋኛ ገንዳ ባሻገር ወደአለ ጫካ እንድንጓዝ ነግሮናል፡፡››ስትል ወረቀቱ ላይ ያነበበችውን በአጠቃላይ ምንም ሳታስቀር ነገረቻቸው፡፡

‹‹ከዚህ ህንፃ ታዲያ እንዴት ነው የምናመልጠው፡፡››ናኦል በተመሳሳይ ሹክሹክታ ጠየቀ፡፡

‹‹እኔ እንጃ…ግን በደንብ በማሰብ  የሆነ ዘዴ ማግኘት አለብን……ከተቻለ እነሱ ከውጭ ማጥቃት ሲጀምሩ እኛም ከውስጥ የተቻለንን እንድናደርግ የሚረዳን መሳሪያ ብናገኝ ጥሩ ››ምስራቅ ነች ሀሳብ ያቀረበችው፡፡

‹‹መሳሪያው እንኳን ብዙም አይቸግረንም…እንደሚታወቀው እዚህ እኛ የምንኖርበት ፍሎር ላይ የሚኖሩ ጠባቂዎች ከአራት አይበልጡም… እነሱን በእጅ ለእጅ ፊልሚያ አሸንፍን መሳሪያቸውን መንጠቅ ከባድ አይደለም..ችግሩ እስቴሩን ተጠቅመን ወደታችኛው ወልል ስንሄድ ነው፣፣እዛ ያሉት  ከሀምሳ በላይ ነፍሰበላ አውሬዎች ናቸው ..በእነሱ መሀለ ሰንጥቀን ማምለጥ የማይታሰብ ነው፡፡››ስትል ስጋቷን ተናገረች

‹‹ታዲያ ምን ይሻለናል››ናኦል በጭንቀት ጥያቄ አቀረበ፡፡

‹‹በመስኮት በኃላ በኩል ቀጥታ ወደምድር የምንወርድበትን ዘዴ ማሰብ አለብን፡፡ገመድ ማግኘት አለብን ማለት ነው…..በዛ ላይ ደግሞ መስኮቶቹበብረት ፍርግርግ የተከለሉ ናቸው››

ምስራቅ ትክክል ነሽ…ብቸኛና አስተማማኙ የማምለጫ መንገዳችን በመስኮት በኩል ነው.. ፍርግርጎቹን በሆነ ዘዴ ማስወገድ አለብን ማለት ነው…እንደገመድ የምንተቀምበትን መንጠላጠያም ማግኘት ይጠበቅብናል….ለማንኛውም ዛሬ ለሊት ይሄንን ስናስብ እና ስናሰላስል ማደር አለብን..እስከ ነገ ጥዋት ድረስ ጥርት ያለ እቅድ ነድፈን ዝግጅት እናደርጋለን…ሌላው ደግሞ…››ብላ ልትቀጥል ስትል የበራፍ መከፈት ድምጽ ሰሙና ከተቃቀፉበት ተላቀው የለበሱትን ብርድ ልብስ ከፊታቸው ላይ ገለጡ፡፡የዘወትር አገልጋያቸው…አንድ ሰማያዊ ፔስታል በእጁ ይዞ  በራፉ ላይ ቆሟል

‹‹እ ምን ፈለክ?››አለችው ኑሀሚ

‹‹እንቺ …ይሄ ላንቺ ነው…..ይሄንን ልበሺና ተዘጋጂ..ከ30 ደቂቃ በኃላ መጥቼ ወስድሻለው፡፡››

ግራ ተጋብታ‹‹ወዴት ነው የምትወስደኝ?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹ሀለቃ ዳግላስ እራት አብረሽው እንድትበይ ይፈልጋል››በማለት ያልጠበቀችውን ድብ እዳ ነገራት

‹‹ዳግላስ !!አለ እንዴ?››

‹‹አዎ ከአንድ ሰዓት በፊት ነው የደረሰው››

‹‹እና ከ30 ደቂቃ በኃላ መጥተህ ለእራት ከእሱ ጋር እንድንበላ ትወስደናለህ ማለት ነው?››

አይ አነሱ እዚሁ ነው ሚበሉት….አንቺን ብቻ ነው የምወስድሽ››አለና ፔስታሉን በቅርቡ ባለ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጦ ወጣና በራፉን መልሶ ከውጭ ቆልፎ ሄደ….እነ ኑሀሚ እርስ በርስ ተፋጠው በገረሜታ ተያዩ፡፡
ከዚህ እስርና ወጥመድ የማምለጥ ተስፋቸው  ከፍ ባለበት ቅፅበት የዳግላስ ከሳምንት መጥፋት በኃላ ድንገት መከሰት መርዶ ይሁን  የምስራች መለየት አልቻሉም፡፡

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

15 Oct, 16:33


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-32
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ሶስት ኢትዬጵያዊ ታጋቾች በአማዛን ጥልቅ ማህፀን ውስጥ በጋንግስተሮች ዙሪያቸውን ተከበው
ውጥረት ያለበት ህይወት መግፋ ከጀመሩ አንድ ሳምንት  አለፋቸው፡፡በእያንደንዱ ቀን የሆነ ተአምር ይፈጠርና ነፃ እንሆናልን የሚል ጉጉት ውስጣቸውን ሲንጠው ነው የከረመው…በጣም አስጨናቂው ነገር ደግሞ  ኑሀሚ ቦታው ላይ ደርሳ ልደታቸውን ካከበሩበት ቀን በኃላ ዳግላስ አላዩትም…..የሚያስፈልጋቸውን ነገር የሚያደርጉላቸው  ወደውጭ አስወጥተው ግቢውስጥ እንዲናፈሱ የሚያደርጎቸው እሱ የመደባቸው ሰራተኞች ናቸው፡፡ይሄ ጉዳይ ደግሞ ይበልጥ አሳስቧቸዋል….

አሁን ግቢ ውስጥ ባለ ለመናፈሻ እንዲያገለግል በተሰራና ዙሪያውን በአበባ ባጌጠ አረንጓዴ መናፋሻ ቦታ ተጠጋግተው ተቀምጠዋል…ከእነሱ በአስር ሜትር ርቀት አምስት የሚሆኑ ጠባቂዎች ሙሉ ትጥቃቸውን እንደታጠቁ ፈንጠርጠር ብለው እየጠበቋቸው ነው፡፡እንደተለመደው ግቢውን የሚጠቡቁ ደግሞ ቁጥቸው በውል የማይታወቁ በየሰዓቱ ፈረቃቸው የሚቀያር መደበኛ ጠባቂዎች በየአስር ሜትሩ በተተከለ ማማ ላይ ከባባድ መሳሪያቸውን ወደውጭ ደቅነው …አካባቢውን በንቃት እየተጠባበቁ ነው፡፡በእውነት ይሄንን ሁኔታ የሚያይ ማንኛውም ግለሰብ ይሄ በእንዲህ አይነት ጥንቃቄ የሚጠበቀው ግቢ የግለሰብ መኖሪያ ሳይሆን የሀገር መሪ ቤተመንግስት ነው የሚመስለው፡፡

‹‹የእኔ ማር ሰውዬሽ መች ነው ተመልሶ የሚመጣው?››ምስራቅ ነች ኑሀሚን የጠየቀቻት፡፡
‹‹ምነው እኔ ሳይናፍቀኝ አንቺን ናፈቀሽ እንዴ?››ስትል አሽሙሯን በአሽሙር መለሰችላት፡፡
‹‹የእውነት  አሁን ያለንበት ሁኔታ ግራ የሚያጋባ ነገር ነው….ነገሮች ለቀናት ምንም ለውጥ ሳያሳዩ ባሉበት ዝም ሲሉ ያስፈራል፡፡በተለይ እንዲህ እኛ ባለንበት ሁኔታ ላይ ለሆነ ሰው ነገሮች እንቅስቃሴ አልባ ሲሆኑ ያሰለቻሉ…››አለች ምስራቅ፡፡

‹‹እኔ ግን ብዙም አልሰለቸኝም….በአለም ላይ በጣም ከምወዳቸው ሁለት ሰዎች አጠገብ ነው ያለሁት….››ሲል ተናገረ ናኦል፡፡የተናገረው የእውነት የሚሰማውን ነገር ነው፡፡እርግጥ አሁን ያለበት ሁኔታ ለህይወታቸው ዋስትና የሌለው በማንኛውም ሰዓት ምንም አይነት ነገር ሊደርስባቸው የሚችል እንደሆነ ያውቃል…፡፡ግን ደግሞ ከዚህ ሁኔታ በሆነ ተአምር ነፃ የሆነ ወደሀገር መመለሳቸውንም በፈንጠዝያ ሚጠብቀው የምስራች አይደለም፡፡ምክንያቱም ከነፃነት በኃላ  ምስራቅን የማጣት ስጋት አለበት፡፡ተልኮቸን በድል ተጠናቋል ከአሁን ወዲህ ፍቅር ፍቅር የምንጫወተው ነገር ትርጉመ ቢስ ስለሆነ እዚህ ላይ ያብቃና ወደበፊት  ሁኔታችን እንመለስ ትለኛለች የሚል ከፍተኛ ስጋት አለው…..ለዛ ነው ነጻነቱን ልክ እንደምስራቅ እና እህቱ ኑሀሚ አብዝቶ የማይናፍቀው፡፡

‹‹ግን ሰዎቻችን ምልክቱ አልደረሳቸውም ማለት ነው….እንዴት እስከአሁን አንድ ነገር ሳያደርጉ››ኑሀሚ ነች ምስራቅን የጠየቀችው፡፡

‹‹እርግጠኛ ነኝ ምልክቱ  ያለንበት ቦታ በትክክል ይነግራቸዋል…ግን ደግሞ እንደምታይው አካባቢው የአማዞን ብብት ስር ነው የሚገኘው…ጉዳዩን አስመልክቶ የአካባበውን መንግስታትን ማሳመንና የእነሱን እርዳታ ማግኘትም ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ድርድር የሚጠይቅ ውስብስብ ጉዳይ ነው፡፡ምን አልባት ሰውዬው አሜሪካን ጨምሮ በአካባቢው መንግስታት ጥቁር መዝገብ ላይ የሰፈረ…በአለም አቀፍ አሸባሪነት መዝገብ ላይ ተመዝግቦ በየስርቻው የሚፈለግ በመሆኑ የኢንተርፖልንም ሆነ የኤፍ.ቢ.አይን ቀልብ ሊስብ እና ከአነሱ ተገቢው እርዳታ ለማግኘት የሚያስችል ይመስለኛል፡፡ያ ከሆነ ደግሞ በቅርቡ የሆነ ነገር እንጠብቃለን ማለት ነው…በዛ ላይ ያንቺም አፍቃሪ በገባው ቃል መሰረት የሆነ ነገር ሊያደርግ  ይችል ይሆናል፡፡

‹‹እሱ እንኳን ቢችል ኖሮ እስከአሁን የሆነ ነገር ያደርግ ነበር…እኔን ለማዳን በዚህ አስፈሪ ጫካ ውስጥ ብቻውን ሲባክን የሆነ አውሬ እራት ሆኖ ቢሆንስ የሚል ፍራቻ ውስጤን እየበላው ነው፡፡››አለች ቅዝዝ ብላ፡፡

ምስራቅ ኑሀሚ የምትናገረውን ቃል ብቻ ሳይሆን የስሜቷን መቀያየር ጭምር በትኩረት እየተከታተለች ነበርና ‹‹ውይ ትንሿ እህቴ ጉድ ሆነሻል››አለቻት፡፡
‹‹ማለት?››

‹‹ከልጁ ፍቅር ይዞሻል አይደል?››አለቻት፡፡

‹‹አይ አልያዘኝም…››ብለ የመከላከያ ሀሳቧን ታቀርባለች ብላ ጠብቃ ነበር…ኑሀሚ ግን ይበልጥ በሀሳብ ውስጥ ገብታ ጭልጥ ብላ ጠፋች፡፡በመካከላቸው ረጅም ፀጥታ ሰፈነ..ግን ድንገት አንደበቷ ተከፍቶ ማውራት ጀመረች‹‹ብታይው በጣም ደስ የሚል ልጅ ነው….ይሄንን የአማዞን ደን ልክ እንደፍቅረኛው ነው የሚወደው…ስለእያንዳንዱ እንስሳትም ሆነ የዛፍ አይነቶች ጥልቅ የሆነ እውቀት አለው…ከጭንቅላቱ የሚፈልቀው እውቀት ልክ እንደአማዞን ወንዝ ጥልቅና ሩቅ ነው፡፡ሰውን ሲንከባከብ እንደእናት ነው፡፡ከአደጋ ሲጠብቅሽ አባትሽን ነው የሚመስለው…ቀልድ ይችላል…..በቃ ምን ልበልሽ ሁሌ ከጎንሽ እንዲሆን ምትመርጪው አይነት ልዩ ሰው ነው፡፡እናንተ ወደእዚህ መጥታችሁ ዳግላስ እጅ ባትገቡና በጀመርነው መንገድ አምልጠን ቢሆን ኖሮ አብሮኝ ወደኢትዬጵያ ለመብረር ወሰኖ ነበር…ልንጋባ ነበር…››ስሜቷ ገንፍሎ እንባዋ መንጠባጠብ ስለጀመረ ንግሯን መቀጠል አልቻለችም፡፡

ናኦል ልክ እንደእሱ ሁሉ እህቱ ጥልቅ በሆነ የፍቅር ፍላፃ መመታቶ ስላዛዘነው ከተቀመጠበት ተነሳና ስሮ ቁጭ ብሎ አቅፎ ደረቱ ላይ አስተኛት‹አይዞሽ እህቴ…በሆነ ተአምር ነገሮች ይስተካከላሉ….በፍቅር መያዝ ምን ማላት እንደሆነ በደንብ ይገባኛል…ያፈቀርነውን ሰው እስከወዲያኛው የማጣት ስጋት ምን ያህል ነፍስን እንደሚያስጨንቅም አውቀዋለው…..አይዞሽ ነገሮች ሰላም ይሆናሉ…ደግሞም…››ንግሩን ሳይጨርስ የአንድ ወታደር ቅፅበታዊ ጨኸት የታከለበት ትዕዛዝ አስቆመው…

‹‹ተነሱ በቃ …ለመናፈስ የተፈቀደላችሁ ጊዜ ተገባዶል፡፡ወደክፍላቹ ተመለሱ››የሚል ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ሶስቱም ከተቀመጡበት ተነሱና ፊታቸውን ወደህንፃው አዙረው መራመድ ጀመሩ…ከኃላቸው ሲከተላቸው የነበረው ጠባቂ …..‹‹አንቺኛዋ ማነሽ››ሲል ወደኑሀሚ እየተመለከተ ጠየቀ፡፡

ዞረችና ‹‹አቤት..ምን አጠፋው?››ስትል አፈጠጠችበት፡፡

‹‹ቁሚ እስኪ››

ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ሶስቱም ስላልገባቸው ሁሉም ባሉበት ቆሙ
ሰውዬው ሁለቱን ችላ አለና ቀጥታ ወደኑሀሚ ተጠግቶ የመሳሪያውን ማንገቻ በአንገቱ ከተተና በጀርባው አዙሮ አንጠለጠለው..ከዛ ሁለቱን እጆቹን ነፃ አድርጎ ተጠጋት…በተሰባረ እንግሊዘኛ ‹‹በኪስሽ ምንድነው የያዝሽው?››ሲል የተጨማደደ ፊቱን እንዳጨለመው ጠየቃት፡፡

ይበልጥ እየተጠጋችው‹‹ምን ያዝኩ ?ምንም….ከፈለክ ፈትሸኝ››አለችው፡፡

‹‹አይ ተይው በቃ›› ይለኛል ብላ ጠብቃ ነበር፡፡ እሱ ግን ከላይ ጀምሮ ነካ ነካ እያደረገ ፈተሸና ኪሷ ውስጥ እጆቹን ከቶ መፈተሸ ጀመር…ኑሀሚ ንዴቷ እንዳያሸንፋትና ይሄን እየተፈታተናት ያለውን ሰው መሳሪያውን ነጥቃ  በሰውነቱ ላይ በማርከፍከፍ ወንፊት አድርጋ ልትጨርሰው የሚፈታተናትን ስሜት እንደምንም አግታ አስቀረችው፡፡

ፈተታሸና‹‹…በቃ ቀጥሉ፣፣፣ደግሞ ፊኛሽ ተነፍቷል…ክፍል እንደገባሽ ወደ ሽንት ቤት ግቢና ሽንትሽን ሽኚ››የሚል ትእዛዝ አስተላለፈ….
ምንድነው የምታወራው…የምን ሽንት ቤት ነው››
እንግዲህ ነገርኩሽ…ወደሽንትቤት ግቢ››ብሎ ቀድሞ ወደህንፃው መራመድ ጀመረ..

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

13 Oct, 23:43


‹‹ትቀልዳለህ እንዴ…ከዛኛው ዳግላስ ፍቅር ሊይዘኝ እኮ ትንሽ ነበር የቀረኝ …ተጨማሪ አንድ ቀን አብረን ማሳለፍ ብንችል አልቆልኝ ነበር››
‹‹ይሄኛውንም ዳግላስ እኮ ገና እየተዋወቅሽው ነው…ከዛኛው የተሻለ ተወዳጅና ተመራጭ ሊሆን ይችላል››
‹‹አይ በፍፅም …ይሄኛውም ትገደል ብሎ የሞት ፍርድ የፈረደብኝ ነው…ይሄኛው ዳግላስ በአውሬ ሊያስበላኝ የነበረ ነው….ይሄኛው በመርዝ ተመርዤ እንድሞት አድርጎኝ የነበረ ነው፡፡››
‹‹አዝናለው…..ያኛውን ዳግላስ ባመጣልሽ ደስ ይለኝ ነበር..ግን እንደምታይው አሁን ፊትሽ ያለው ይሄኛው ደግላስ ነው፡፡ግን የጊዜ ጉዳይ ነው ይሄኛውንም ዳግላስ ላደረገብሽ ነገር ይቅር ትይዋለሽ…እንደዛኛውም ልትወጂው ትችያለሽ….››
‹‹እኔ እንጃ… አይመስለኝም›› አለችና ሌላ ነገር ልትመልስላት ስትል ምስራቅ ቅፅበታዊ ጆሮ ሰንጣቂ ጩኸት አሰማች… ሁለቱም ተሯርጠው ወደእሷ ሄዱ….አካባቢዋ ያለው የገንዳ ውሀ በደም ቀልሟል… ኑሀሚ አውሬ የነደፋት ነው የመሰላት፡፡
ጎትተው ከገንዳው አወጧት..ናኦል የሚሆነው ግራ ተጋብቶ ወዲህ ወዲያ በድንጋጤ እየተወራጨ ነው፡፡
‹‹አታስቡ ትንሽ ነገር ነው …ወደታች ወደወለሉ ሰምጬ ስዋኛ የገንዳው ወለል ላይ አረፍኩና የሆነ ስለት ነገር ነው እግሬን የቆረጠኝ…..››ስትል ሁኔታውን አብራራችላቸው፡፡
ውስጥ እግሯን አንስተው ሲያዮት መሀከሉ ላይ ሽርክት ብሎ ተቆርሷል … በውስጡ የተቀረቀረበትም ጠጠር ተፈንቅሎ የወጣ ነው የሚመስለው፡፡ዳግላስ አበደ ፡፡ ሰረተኞቹን ጠርቶ ጮኀባቸው….እንዴት ስለት ነገር ገንዳ ውስጥ እንዳስገቡ ጠየቃቸው…መልስ መስጠጥ የቻለ  አልነበረም….የሚደርባቸው ቅጣት እየሳቡ በመንቀጥቀጥ ሰሙት፡፡
ወዲያወ የግቢው ሀኪም መጣና ቁስሉን አፀድቶላት በተገቢው መንገድ አሸገለት…ከዛ ሁሉ ነገር ተረጋጋና ሁሉም ልብሳቸውን ለባብሰው ዝግጅቱን ለማተዳም ጠረጴዛ ከበው ተቀመጡ፡፡በግዙፍ ጠራጴዛ ምግቡ ተደረደረ፡፡ መጠጡ ተኮለኮለ፡፡ ጉብታ የሚያህል ባለደረጃ ኬክ እየተገፈ መጣ…አከባቢው ሁሉ በባለ ቀለም የሻማ ብርሀን ተንቦገቦገ…በህይወታቸው በጣም የሚገርም …የሚያምረውንና ውዱን የልደት በዓለቸውን ማክበር ጀመሩ….በሀከል ኑሀሚ ወደምስራቅ ጆሮ ጠጋ ብላ…‹‹እግርሽን ለምንድነው የቆረጥሽው››ስትል ጠየቃቻ..ሆነ ብላ እንደዛ እንዳደረች ያወቀችው እሷ ብቻ ነች፡፡
ዛሬም እንደድሮው የምትገርሚ ሴት ነሽ..አንቺን ደብቆ የሆነ ነገር ማድረግ መቼስ አይተሰብም…ከኢትዬጵያ ስነሳ እንዳይገኝ ተደርጎ እግሬ መሀል የተቀበረ ችብስ ነበር..አሁን ሶስታችንም አንድ ቦታ በመገኘታችን ለሰዎቻችን  መልዕክት ማስተላለፊያ ጊዜው ስለሆነ ነው ያደረኩት..አንቺን እስክናገኝ ነበር የምጠብቀው… አሁን ምልክቱን ሰጥቻቸዋለው….እንግዲ ከቻሉ ያድኑናል››አለቻት፡፡
ኑሀሚ ለይ የተስፋ ብርሀን በውስጧ ሲፈነጥቅ ታወቃት…የካርሎስ ሙከራ ባይሳካ እንኳን ሌላ ትስፋ አላቸው ማለት ነው…በህይወት ተደረራቢ ተስፋ አለ ማለት ደግሞ ለመኖርም ተደረራቢ የኃይል ክምችት አለ ማለት ነው፡፡ዛና ባላ ሁኔታ ልደቷን ማክበር ጀመረች…ዳግላስን እንደጠላቷ እና ለቀናቶች ሊገድላት ሲያሳድዳት እንደነበረ ሰው ሳይሆን ልክ እንደ ረጅም ጊዜ ጓደኛዋ እየተንጠለለችበትና እየተላፋቸው አብራው መደነስ ጀመረች፡፡

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

13 Oct, 23:43


እንደተባሉት ያው ልጅ ቤቱን ከፍቶ ይዞቸው ወጣ፡፡ቀጥታ ከህንፃው በጎሮ በኩል ካለ እስካአሁን ካላዩት በአበቦች ያሸበረቀ የቅርጫት ኳስ ሜዳ ስፋት ያለው የተንጣለለ የመዋኛ ገንዳ ያለበት ቦታ ነው የወሰዳቸው፡፡ ገንዳው ዳር ባለ በሰራሚክ ንጣፍ ባማረ ጎጆ የምግብ አይነትና፤ የመጠጥ አይነቶች ሞልተውበታል….ዙሪያውን መቀመጫዎች ሲኖሩ አስተናጋጅ መሰል ሁለት ሴትና አንድ ወንድ ዝግጅቱን ለማሳመር ከላይ ወደታች ይሯሯጣሉ፡፡ይዞቸው የመጣው ሰው ለገንዳው እይታ ምቹ የሆነ መቀመጫ ሰጣችውና ሶስቱም በተርታ ተቀመጡ፡፡
..በትካሻቸው ከባድ መሳሪያ የተሸከሙ ሰዎች በአከባቢ ራቅ ካለ ስፍራ በየተወሰነ ርቀት ፈንጠር ፈንጠር ብለው ሁኔታውን በጥንቃቄ ሲቃኙ ይታያል ፡፡ጥርት ካለው ከአማዞን ደን ሚነፍሰው ልስልና እርጥብ አየር ጋር አብሮ የሚነፍስ ጥኡም የላቲን ሙዚቃ እየተሰማ ነው፡፡በአካባቢው ሌላ ሰው የለም፡፡ድንገት ከገንዳው ብልቅ ብሎ ወደ ዳር የሚወጣ ሰው ተመለከቱ… ከእነሱ በ5 ሜትር ርቀት ላይ ስለሆነ ማንነቱ ጥርት ብሎ ይታያቸዋል፡፡
ወደ ኑሀሚ በፈገግታ እየተመለከተ‹‹በሰላም ተመልሰሽ ወደቤትሽ በመምጣትሽ ደስ ብሎኛ››አላት፡፡
‹‹እንዴት አልመጣ ….ብጨክን ብጨክን ባንተ ጨክኜ መቅረት እችላላሁ››ብላ ምፀቱን በምፀት መለሰችለት…መልሷ በጣም አሳቀው፡፡
‹‹በጣም ናፍቀሺኝ ነበር….በህይወቴ እንደአንቺ ለማግኘት ያስቸገረኝ ሰው የለም….ድሮም ውድ ነገር ለማግኘት በጣም ከባድ መስዋዕትነት ይጠይቃል…ለማንኛውም መልካም ልደት ለሁለታችሁም…..ሰዎቹ መሰናዶቸውን እስኪያጠናቅቁ ትንሽ ልዋኝ.. ከመሀከላችሁ መዋኘት …የሚፈለግ ሰው ካለ ግን መጥቶ መወኘት ይችለል፡፡››ብሎ ወደገንደው መሀል እየዋኘ ሄደ፡፡
ምስራቅ ብድግ ብላ ልብሷን ማወላለቅ ጀመረች….ሁለቱም መንትያዎች ‹‹ሴትዬዋ አበደች እንዴ›› የሚል እይታ አፍጥጠው ያዮት ጀመር…፡፡
‹‹ፍቅር..ምን እየሰራሽ ነው››ናኦል ነው የጠየቃት…በእነዚ ሰው በላ አውሬ በሆኑ ሽፍቶች ፊት እርቃን ሰውነቷን ማሳየቱን ጥሩ ሆኖ አላገኘውም፡፡፡
‹‹ምን ነካችሁ ዛሬ እኮ የአናንተ ልደት ብቻ አይደለም..ጥምቀትም ጭምር ነው..ታዲያ ባገኘነው አጋጣሚ ብንጠመቅ ምን ይላችኃል?፡፡›› ብላ ጎንበስ በማለት ጫማዋን አወለቀችና ወለሉን እየነካካች ወደ ገንደው ተንቀሳቀሰች….ኑሀሚ ተነሳችና እሷ አንዳደረገችው ልብሷን በፍጥነት አወላለቀች.‹‹ሴቶቹ ጤናም የላቸው እንዴ››በማለት አልጎምጉሞ ባለበት መንቋራጠጡን ቀጠለ…ኑሀሚ ልብሷን አውልቃ እንዳጠናቀቀች ሄደችና ምስራቅ ጎን ቆመች…ዳግላስ ገንዳው መሀከል ባለ ከመነደሪ ላይ ተኝቶ ጭንቅላቱን በክንዱ ደገፍ በማድረግ አይኖቹን ሁለቱ እንሰት ላይ ተክሎ በገረሜታ ከሩቅ ይመለከታቸው…እንዲሁ ለማለት ያህል ጋበዛቸው እንጂ ያደርጉታል ብሎ አልጠበቀም ነበር…የኑሀሚን ሙሉ ተክለ ቁመና ሲያይ በሰውነቱ ሁሉ ሙቀት ተረጨና ውጥርጥር አለ…ለሳምንታት ሲያልመውና ሲመኘው የነበረው ገላ ይሄው በእሱ ቁጥጥር ስር ሆኖ ከፊት ለፊቱ እየታየው ነው….እሱ የእዚህ አካባቢ ገዢና አስተዳዳሪ ብቻ ሳይሆን የዚህ አካባቢ አምላክ ..ሁሉን አድራጊ..ሁሉን ፈጣሪ እንደሆነ ነው ሚያስበው፡፡፡
ኑሀሚ ምስራቅ ላይ ተለጥፋ ቆመችና ከንፈሯን በእጇቾ ከልላ‹‹ምን አቅደሽ ነው››ስትል ጠየቀቻት፡፡
‹‹ምን አቀድኩ››

‹‹ጫማሽን ምታወልቂ አስመስለሽ… ስለት ነገር ከወለሉ ላይ አንስተሸ ፓንትሽ ጠርዝ ላይ ስትወትፊ አይቼሻለው››
‹‹አይዞኝ አታስቢ የሰውዬውን ጉሮሮ አልበጥስብሽም››

‹አትቀልጂ…ሙከራችን በደንብ የታሰበበትና እና የሚያዋጣ መሆን አለበት…አትቸኩይ..››

ምስራቅ‹‹አታስቢ …አልኩሽ እኮ›› ብላ ተንቀሳቀሰችና ዘላ ገንዳ ውስጥ ገባች….ኑሀሚም ተከተለቻትና ገባች…ምስራቅ ወደግራ በኩል መዋኘቷን ስትቀጥል… ኑሀሚ ቀጥታ ወደ ዳግላስ መዋኘት ጀመረች….የምስራቅ እቅድ ዳግላስን መግደል ከሆነ ልታስቆማት ይገባል..አሁን ባሉበት ሁኔታ እሱን መግደል….የሚያመጣው ምንም ጥሩ ነገረ የለም..፡አነዛ አወሬ ታጣቂዎች በደቂቃዎች ውስጥ ቦጫጭቀው ይጥሏቸዋል…ከፋም ለማም ከሱ ጋር መደራደርና እሱኑ እለስልሰው ይዞው ትክክለኛው ጊዜ እስኪመጣ መጠበቁ የታሻለ እንደሆነ ታስባለች፡፡እና ወደእሱ የሄደችው ልትከላከልለት ነው፡፡
ስሩ ስትደርስ ‹‹እሺ ደግላስ ማለት የትኛው ነህ፡፡ስትል ጠየቀችው ፡፡

‹‹ማለት››

‹‹ዳግላስ ማለት አሁን አጠገቤ እዚህ አማዞን ደን መሀከል በነፀው ህንፃ ልዩ በሆነ ገንዳ ውስጥ እየዋኘ ያለው ነው ወይስ ከዛ ፔሩ ሊማ አግኝቼው ኤኪዬቶስ አንድ አልጋ ክፍል ውስጥ አብሬው ያደርኩት ሰው ነው››
‹‹ላንቺ ..የትኛው ቢሆንልሽ ትምርጫሽ››

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

13 Oct, 23:42


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-31
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

የተወሰነ አርፈው ናፈቆታቸውን ካቀዘቀዙ በኃላ ናኦል‹‹እህቴ ዛሬ ቀኑን ታውቂያለሽ….››ሲል ግራ ያጋባትን ጥያቄ ጠያቃት፡፡
ወንድሜ ደግሞ መንጋትና መምሸቱን ካልሆነ በስተቀር እለቱና ቀኑኑ መለየት ካቀምኩ ቆየሁ…ለካ በህይወታችን ውስጥ ያሉ አብዛኛዎቹ ነገሮች በመከራ ቀኖቻችን ውስጥ ስንሆን ትርጉም አይኖራቸውም፡፡››
‹‹እንግዲያው ልንገርሽ ዛሬ ጥር 11 ነው …ልደታችን ነው፡፡››

ያልጠበቀችውን ዜና ነው የነገራት….መላ ሰውነቷን ነው የወረራት‹‹ኦ …ደሰስ ይላል…››መልሰው ተንጫጩ …..
ምስራቅ‹‹እናንተ ለምን እነዚህ አስተናጋጆቻችንን ጥቂት ውለታ አንጠይቃቸውም…››የሚል ድንገቴ ሀሰብ አቀረበች፡፡
‹‹ምን ››

ልደታችሁን  ለማክበር  የሚሆን  ጥቂት  ሻማ  …የተወሰነ  ከረሜላ  ካለ…ኬክም  ቢገኝ አንጠላም…ኮኬይንም  ቢያቀርቡልን ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው…››አላች…ተሳሳቁ፡፡
‹‹ሌላውን አላውቅም.. ኮከይኑ ግን አይጨክኑብንም…..›› ምስራቅ ወደ መጥሪያው ሄደችና ተጫነችው…
‹‹እንዴት ፍቅር ምን ፈልገሽ ነው››ናኦል ምስራቅን ጠየቃት..ኑሀሚ ሁለቱንም አፈራረቀች ና       በገረሜታ ታያቸው ጀመር..ምስራቅ የእሷን ምልከታ ሳታስተውል ‹‹ትቀልዳላችሁ እንዴ.. ከመጠየቅ ደጅ አዝማችነት ይቃራል፡፡ሲባል አልሰማችሁም፡፡››በማለት በራፉ በድጋሚ ለማንኳኳት እጇን ስትሰነዝር  ….በድንገት በራፉ ተከፈተ…፡፡
ኑሀሚን ያመጣት ወጣቱ ልጅ ነው በራፉን የከፈተው…. የሚፈልጉትን ጠየቀችው፡፡ ‹‹ሀለቃዬን ጠይቄ ከፈቀደ የሚሆነውን አደርጋለው››ብሎ መልሶ በራፉን ዘግቶ ሄደ….፡፡ኑሀሚ ግን  በነበረችበት እንደፈዘዘች ነው፡፡
‹‹ምንድነው ያፈዘዘሽ››

‹‹የእኔ ፍቅር አለሽ እኮ…አንቺም ወዬ አልሺው ››

‹‹እና ›

‹‹እኔ እዚህ በአማዞን ጫካ ከአውሬውም ከሰው አውሬውም ለማምለጥ በመጣር ፍዳዬን በማይበት ሰዓት እናንተ ፍቅሬ ማሬ መባባል ጀመረችሁ››
‹‹ታዲያ በመሀከላችን ያለውን ለዘመናት የታፈነ ፍቅር ጭረን ካላቀጣጠልነው አንቺን ለመፈለግና ለማግኘት የሚያስችለንን ብልሀትና ጥንካሬ ከየት እናመጣን…. በነገራችን ላይ ያው አንቺ ወደ እዚህ እንደመጣሽ ሰሞን ነው የተጋባነው…››
‹‹የተጋባነው››

አዎ …ወዳሻንጣዋ ሄደችና የጋብቻ ሰርተ ፍኬታቸውን አውጥታ አሳየቻት…..ማመን አልቻለችም…ምስራቅ የሚያደርጉትን ሆነ የሚያወሩትን ሁሉ ሰዎቻቸው እየተመለከቷቸው እንደሆነ ታውቃለች….የጀመሩትን ማስመሰል አስከወዲያኛው መቀጠል አለባቸው….አዎ ከዚህ እስኪወጡ ከናኦል ጋር ባልና ሚስቶች ናቸው….ከወጡስ በኃላ አንዴት ይሆናል የሚለውን እርግጠኛ አይደለችም…..ልጁን በፊት ከምትወደው በተለየ መንገድ ወዳወለች…..ጠረኑ ክፉኛ ለምዳዋለች…..ፍቅሩ ልቧ ውስጥ እየተንጠባንጠበ ነው…..ይሄንን የጋብቻ ሰርተፍኬት እንደቀልደ በቃ አሁን ጉዛችን አበቅቶለታል ብላ ቀዳዳ የወረቀት ቅርጫት ውስጥ ለመክተት ጥንካሬው መቼም ቢሆን የሚኖራት አይመስላትም፡፡
ከተረጋጉ በኃላ ኑሀሚ ሰውቷን ለመታጠብ ፈለገች እና ወደሻወር ቤት ገባች፡፡ታጥባና ነፅታ ስትወጣ ክፍላቸው ውስጥ የተለየ ነገር ነበር የጠበቃት….በርከት ያሉ የሴት ቀሚሶች እና ሙሉ የወንድ ሱፍ ሱሪ የያዘ ተሸከርካሪ የልብስ መደርደሪያ ወለሉ መሀከል ላይ ተቀምጦ ናአልና ምስራቅ ፊት ለፊቱ  ቆመው በአድናቆት እየተመለከቱት ደረሰች፡፡
ያገለደመችውን ፎጣ በደንብ አጥብቃ አሰረችና ‹‹ምንድነው ይሄ››ስትል ጠየቀች፡፡

‹‹ይህን ያመጣው ልጅ..በጠየቃችሁት ጥያቄ መሰረት ልዳታችሁን ለማክበር ተፈቅዷል…..ከዚህ የሚሆናችሁን ልብስ መርጣችሁ ልበሱና ልደቱ ወደሚከበርበት ቦታ ከ30 ደቂቃ በኃላ መጥቼ ወስዳችኃላው›› ብሎል፤ብለው አስረዷት፡፡
‹‹አንቺ ሰዎቻችን ደግ ናቸው…….መጀመሪያ በደንብ አስደስተውን የምንፈልገውን ነገር እንድናደርግ ከፈቀዱልን በኃላ ከዛ አመስግነናቸው እንድንሞት ነው የፈለጉት፡፡››አለች ምስራቅ፡፡
‹‹እሱስ ቢሆን ማን አየበት  ይመስገን ነው››….ብላ ካመጣጡላቸው ቀሚሶች መካከል ለእሷ
የሚሆናትን መምረጥ ጀመረች….በሀያ ደቂቃ ውስጥ ሶስቱም ልክ እቤተ-መንግስት ከንግሱ ጋር የእራት ግብዣ እንዳላባቸው መኮንንቶች ሽክ ብለው ዘንጠውና አምረው በቀጣይ
የሚሆነው መጠበቅ ጀመሩ፡፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

13 Oct, 23:42


ልጅ የእሷን ንግግር ከቁም ነገር ሳይቆጥር ቁልፉን ከፈተና በራፉን ወደውስጥ ገፋው….
ወለል ብሎ ሲከፈት ገፍትሮ ወደ ውስጥ ይከተኛል ብላ ስትጠብቅ ከውስጥ ያልጠበቀችው ፀጋ ነበር የጠበቃት..ወንድሟና ምስራቅ ቢጃማቸውን እንደለበሱ በሚያምር እና ምቾቱ በተጠበቀ መኝታ ክፍል ውስጥ ጎን ለጎን ቆመው በራፉ ላይ አፍጥጠው ስታይ ማመን አልቻለችም፡፡ ተንደርድራ ሄዳ ተጠመጠመችባቸው.. ሁለቱም ወደላይ ተሸክመው በአየር ላይ እያሸከረከሯት መጨፈር ጀመሩ…ልጁ ለደቂቀ ያህል ፈንጠዝያቸውን ከታዘበ በኃላ መልሶ በራፉን ዘግቶና ከውጭ ቆልፎ ወደስራው ሄደ….፡፡
ከናፍቆተቸው ለመውጣት አንድ ሰዓት በላይ በመተቃቀፍ እና መሳሳም አስፈልጎቸው ነበር…፡፡


ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

13 Oct, 23:41


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-30
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ኮሎምቢያ/አማዞ ደን ማህፀን ውስጥ
ካርሎስ በተሰበረ ልብ ምርጫ አልባ ሆኖ በህይወቱ የመጨረሻውን ፍቅር ያፈቀራትን ይቺን ጠይም ኢትዬጵያዊ ሴት ሳይወድ በግድ ከማናአስ ወደ ቲጎና በፕሌን… ከዛ ደግሞ በጀልበ ከብራዚል ድንበር ወደኮሎምቢያ አሻግሯትና ላቲሲያ ከተማ ጫፍ ድረስ ሸኛት፡ከዛ እሱ ከዳግላስ የንፍስ ጠላቶች ጋር ለመደራደር ደቡብ ምእራብ ኮሎምቢያ ድንበር ተጠግታ ወደምትገኘው የቪንዚዎላዋ ሳና-ካርሎስ ከተማ ጉዞ ጀመረ …፡፡
ይህቺን ያፈቀራትን አፍሪካዊ ሴት ማዳን ማለት እራሱን ማዳን ማለት ነው፡፡ሰው እራሱን ለማዳን ደግሞ ምንም ያደርጋል፡፡ዳግላስን ያገኙትን ማንኛውንም አጋጣሚ ተጠቅመው ሊያጠፉት የሚፈልጉ የቢዝነስ ተፎካካሪዎች እንዳሉት ያውቃል..እሱ ደግሞ ስለ ዳግላስ የቢዝነስ ሚስጥሮች ፤ መግቢያ መውጫውን ፤ድክመትና ጥንካሬውን በደንብ ያውቃል…አሁን የሚያገኛቸው ሰዎቹ ደግሞ ሃይልና ብር አላቸው….እነሱ እሱን አምነውት ከተቀበሉትና አብረውት ለመስራት ከወሰኑ ዳግላስን እስከወዲያኛው አስወግዶ ኑሀሚንና ወንድሟን ነፃ ለማውጣት የሰለለችው ቢሆን ተስፋ አለው፡፡ያ ተስፋ ካልተሳካ ነፍሱን እንደሚያስከፍለው ያውቃል…ቢሆንም ግድ የለውም…ያቺ የሰለለች ተስፋ ከመቶ አንድ ፐርሰንት ብትሆንም እንኳን  ከመሞከር ወደኃላ አይልም..ለዛ ነው እሷን ወደዳግላስ ልኮ እሱ የዳግላስን ጠላቶች አግኝቶ ለመደራደር ጊዜ ሳያባክን ጉዞ የጀመረው፡፡
ኑሀሚ ካርሎስ እንደነገራት ላቲሲያ ከተማ በተቀመጠችበት ሆቴል ነው አንድ ሰዓት እንኳን ሰትቆይ የዳግላስ ሰዎች በቁጥጥር ስር ያዋሏት፡፡በመጀመሪያ እዛ ላቴሲያ ከከተማው ወጣ ብሎ አማዞን ወንዝ ደር ካለ ወደ አንድ  ሰዋራ ቤት ነበር የወሰዷት፡፡ለአራት ቃናት ያህል እዛው አስቀመጧት፡፡በየቀኑ የሚያስፈልጋትን ያህል ምግብ ፤ልብስ እና መጠጥ ያቀርቡላታል፡፡ግን ማንም ሊናግራት የሚደፍር ፤ብታናገራቸውም የሚመልስላት አልነበረም፡፡በየቀኑ ምግብ እና መጠጥ እንዲሁም የሚያስፈልጋትን ነገር የሚያመጡ ሁለት ሰዎች አሉ….መጥተው እቤቱ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠውላት ይሄዳሉ….ብታናግራቸው አይመልስላትም፡፡ጠባቂዎቾ እርስ በርስም ቁጥብ ቃላትን ሲለዋወጡ ብትሰማ እንኳን በማይገባት ቋንቋ ስለሆነ ምንም መረዳት የምትችለው ነገር አልነበረም ፡፡ይበልጥ ልትቆጣጠረው የሚከብዳት ጥልቅ ድባቴ ውስጥ እየገባች መጣች፡፡እሷ ካለችበት ቤት አስር ሜትር እርቃ ባለች ጎጆ አንድ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ ጎረምሳ ሁሌ ንቁ ሆኖ ሲጠብቃት  ታየዋለች…ወደእሷ መጥቶ ለማውራት   አይሞክርም…እሷም ወደእሱ ለመቀረብ ምንም ጥረት ኣላደረገችም፡፡ይህን ጠበቂ ወይ ጥላው ወይ ገድላው በቀላሉ ማምለጥ እንደምትች ታውቃለች…..ግን ያ አይደለም እቅዷ፡፡ አሁን ሂጂ አምልጪ የሚላት አዛኝ ሰው ቢኖር እራሱ እሺ ምትልበት ሁኔታ ላይ አይደለም ያለችው፡፡አሁን የእሷ ጥረት ወደፊት ስምጥ ወደሆነው የአማዞን ደን ማህፀን ውስጥ ገብቶ ወንድሟን ማግኘት ነው…ምንም ያህል ዋጋ ቢያስከፍላት ግድ የላትም፡፡እንደው ወንድሟንና ምስራቅን የማትረፍ እድሉ ባይኖራት እንኳን የዩትን መከራ አብራ አይታ የሚጎነጩትን ሞት አብራ ለመሞት ነው ፅኑ ፍላጎቷ፡፡
እርግጥ ካርሎስ እንዳላት ከዳግላስ ጠላች ጋር በማበር ስለእሱም ሆነ ስለድርጅቱ… ስለሚኖርበት አከባቢና ..ስለግዛቱ የሚያውቀውን መረጃ ሁሉ በመስጠት እሱን እንዲያወድሙትና በዛ ግረግር መካከል እሷን ከወንድሟ እና ከምስራቅ ጋር ሊያስመልጣቸው የተቻለውን ሁሉ እንደሚጥር ቃል ገብቶላታል….ደግሞ የገባውን ቃል ለማክበር የተቻለውን ያህል እንደሚጥር እርግጠኛ ነች…ምን አልባትም በእነዚህ አራት ቀኖች የሚፈልጋቸው ሰዎች ጋር ተገናኝቶ እቅድ እየነደፈ ይሆናል፡፡
አሁን እሷን የጨነቃት እስከመቼ እዚህ አፍነው እንደሚስቀምጧት ነው..የመጨረሻ ተሰላቸች፡፡ እና የሆነ ነገር አድርጋ ትኩረታቸውን ማግኘት እንዳለባት እና ትኩረታቸውን ለማግኘት ደግሞ እንሱን ማበሰጨት አንድ ዘዴ እንደሆነ አመነች፡፡ውጭ እሷ እንድታመልጥ ሳይሆን ከውጭ ሌላ ሰው መጥቶ እሷ ላይ ጥቃት እንዳያደርስ ጥበቃ እያካሄደ የሚመስለውን ወጣት ልታጠቃው እቅድ ነደፈች፡፡ከልተፈታተናት ላትጎዳው ወስናለች…..አፀፋዊ ምላሹ ጠንካራ ከሆነ ግን ቢሞትም ግድ የላትም…፡፡
ዝም ብላ ካለወትሮዋ ወደእሱ ተንቀሳቀሰች፡፡መሳሪውን አዘቅዝቆ እንደያዘ ባልተለመደ እንቅስቃሴዎ ግራ ተጋብቶ አፍጦ እያያት ነው፡፡ቀረበችው፡፡ በመሀከላቸው ያለው ርቀት ሁለት ሜትር ብቻ ሆነ፡፡ወስና እግሯን ልታወናጭፍ ስትል ከወደ በራፉ ብዛት ያለው የእግር ኮቴና ድምፅ ሰማችና ባለችበት ተረጋግታ ቆመች፡፡ፊቷን አዙራ ስታይ እውነትም ሶስት የሚሆኑ የታጠቁ ግሰበች ናቸው ..ወደ እነሱ እየመጡ ነው፡፡ ፊት ለፊቷ በቆመው ልጅ እድለኝነት ተገረመችና ፈገግ አለች፡፡
ወዲያው ነበር አፋፍሰው ይዘዋት የወጡት፡፡የ 20 ደቂቃ የእግር መንገድ ካስኬዷት በኃላ ወንዝ ዳር አካባቢ ደረሱ፡፡ወዲያው ጀልባ ላይ ነው ይዘዋት የወጡት…ከዘ በኃላ ለአንድ ሰአት ተኩል ያህል ከጀልባ  አልወረዱም..አሰልቺ የሆነ ጉዞ ነበር የተጓዙት፣ከዛ ባልጠበቀችው ሁኔታ እዛ ጥቅጥቅ ደን ውስጥ ሚኪና ነው የጠበቃት፡፡አንከውክወው መኪናው ውስጥ አስገቧትና ጥቁር ጨርቅ በጭንቅላቷ አጥልቀው አንገቷ ድረስ በማልበስ ሙሉ በሙሉ እይታዋን ከለሉት፡፡ በጥቅጥቅ ደን ውስጥ የእግር መንገድ በምትመስል ቀጭን መንገድ ጫካውን እየሰነጠቁ፤አውሬዎችን እያስደነበሩ፤ለሁለት ሰዓት ያህል ይዘዋት ተጓዙና  ድንገት የመንገዳቸው መጨረሻ ደረሱ፡፡መኪናዋ እንደቆመች የተሸፈነችበት ፅልመታዊ ጥቅር ልብስ ከጭንቅላቷ ላይ ገፈው አነሱላት፡፡ወዲያው ከአካባቢው ብርሀን ጋር እራሷን ማሳማማት አልቻለችም…ብዥ አለባት፡፡ቀስ እያለች ዙሪያ ገባዋን ማየት ስትችል እዛ ደን ውስጥ ይገኛል ብላ ያልጠበቀችው  አንድ ግዙፍ ግቢ ከፊተ ፊቷ ገጨ ብሎ አየች፡፡እንድትወርድ በምልክት ነገሯት፡፡ ወረደች፡፡ውስጧን በደስታ ተጥለቀለቀ…አዎ ቦታው እራሱ ነው፡፡ወንድሟና ምስራቅ ጎን ለጎን ሆነው እዚህ ስፍራ የተነሱትን ፎቶ ነው የላከላት…ወንድሟን ልታገኝ በመሆኑ ተደስታ እግሮቾን በአየር ላይ አድርጋ ዘለለች ፡፡
ይዘዋት ከመጡት መካከል አንዱ በተሰባበረ እንግሊዘኛ እንድትከተለው ነግሯት ወደዋናው ቤት ይዞት ሄደ.፡፡አንደኛ ፎቅ ላይ እንደወጡ አንድ ልጅ እግር ወጣት ተቀበላትና ታጣቂውን አሰናብቶ እሷን ይዞት ወደውስጥ ገባ፡፡ግዙፉን ሳሎን እየሰነጠቁ አለፉ… የተወሰኑ ኮሪደሮችን ከለፉ በኃለ የሆነ ክፍል ጋር ሲደርሱ ቆመና ከኪሱ ቁልፍ አውጥቶ መክፈት ጀመረ፡፡
‹‹እናንተ ሰዎች ያማችኃል እንዴ..አሁንም ክፍል ውስጥ አስገብታችሁ ለተጨማሪ ቀን ለትቆልፉብኝ ነው…ወንድሜን እንድታገናኙኝ አፈልገለሁ…ለሀለቃህ ለዳግላስ ንገረው… ወንድሜን አገናኘኝ ብላለች በለው….አሁኑኑ ንገረው››

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

10 Oct, 17:04


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-29
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ሁለቱም እርቃናቸውን ተኝተው ፊት ለፊት እየተያዩ ማውራት ቀጠሉ?

"የሆነ ነገር ትጠይቀኛለህ ብዬ ስጠብቅ ነበር  ግን ማድረግ አልቻልክም"አለችው

እንደመደንገጥ ብሎ ፀጉሯን በእጆቹ እየላገ"ምንድነው የእኔ ፍቅር?ምን ልጠይቅሽ?"

"ከዚህ በፊት የዛሬ ሳምንት አካባቢ ከዚህ ደን በሰላም ከወጣን ደግመህ ጠይቀኝ ብዬህ ነበር...አሁን ሳስበው ግን ጥያቄውን ሙሉ በሙሉ ረስተኸዋል…በፊትም ከልብህ አልነበረም የጠየቅከኝ ማለት ነው "አለች እንደማኩረፍ ብላ።
"አንቺ በጣም ተሳስተሻል...ያንን ጥያቄ ለደቂቃም ረስቼው አላውቅም..አሁን ደግሜ ብጠይቃትና እምቢ ብትለኝ እንዴት ነው የምቋቋመው?"ብዬ ሰግቼ ነበር ...
"እና "

"እናማ...አንቺ ቆንጆ ጠይም ወጣት ወደሀገርሽ ይዘሽኝ ብትበሪ ምን ይመስልሻል?"

"ይዞ መሄድን ይዤህ ሄዳለው።ግን ልመለስ ብትል ማንም አይሰማህም"

"ይሁን ተስማምቼያለው...አልፎ..አልፎ ሀገሬ ሲናፍቀኝ ይዘሽኝ መጥተሽ እንደምታሳይኝ እተማመናለው።››
"እሱን ፀባይህ እየታየ የሚወሰን ነው።"ብላ ከመኝታዋ ተነሳችና እርቃን ገላዋን ለእሱ እይታ አጋልጣ ወረደች..ቀጥታ ወደሰካችው ስልኳ ሄደችና ነቀለችው።ተመልሳ መጣችና አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ ብላ ወደሀገር ቤት ወንድሟ ጋር ደወለች.፡፡ከሰከንዶች በኃላ የወንሟን ተወዳጅ ድምፅ በጆሮዋ ሲንቆረቆር ልትሰማ እንደሆነ ስታስብ ሰውነቷን ሌላ ዙር ሙቀት ወረራት...ግን እንዳሰበችው የወንድሟ ሞባይል ሊጠራ አልቻለም...ደግማ ሞከረች።በሁለተኛ ቁጥሩም ሞከረች ተመሳሳይ ነው።
"ብሽቅ...በዚህ ቀን ሞባይሉን ያጠፍል"ተበሳጨች።ሌላ ተለዋጭ ሀሳብ መጣላት።የምስራቅ ቁጥርን ከሞባይሏ ፈለገችና ደወለች።ልክ እንደወንድሟ ስልክ የእሷም አይሰራም።
‹‹የሰዎቹ ስልክ ሁሉ አይሰራም"በተኛበት አይኖቹን እያቁለጨለጨ እየተመለከታት ለነበረው ካርሎስ ነገረችው። ከተኛበት ተነሳና ከአልጋው ወርዶ አልጋ ልብሱን ከአልጋው ላይ ገፎ እርቃን ሰውነቷን በማልበስ"አይዞሽ ተረጋጊ...አህጉር አቋራጭ ጥሪ እኮ ነው እያደረግሽ ያለሽው፡፡ ኔትወርኩ ችግር ሊኖርበት ይችላል...አሁን ባይሆን ጥዋት ሲነጋ ሊሰራ ይችላል...ካልሆነም ሌላ ዘዴ እንፈልጋለን።››ሲል ሊያፅናናት ሞከረ፡፡
ሌላ ዘዴ ሲላት በአእምሮዋ ተለዋጭ ዘዴ ብልጭ አለባት፡፡ ለወንድሞ...ነፃ እንደወጣችና ከቀናት በኃላ ወደሀገሯ እንደምትመለስ ልትፅፍለት ወሰነችና ኢሜሏን ከፈተች። ከአለም እይታ በተሰወረችባቸው 20 በሚሆኑ ቀናቶች በርካታ ኢሜሎች ተልከውላታል።አብዛኛዎቹ ከወንድሟ.. ከዛም ከመስሪያ ቤቷ ሲሆን ለመጨረሻ ጊዜ ግን የተላከላት ከማትጠብቀው ሰው ነበር… በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነስታ ስትቆም ካርሎስ አልብሷት የነበረው አልጋ ልብስ ከላዩ ላይ ወደቀና እርቃኗን ቀረች...
‹‹ምንድነው ፍቅር...?››

‹‹ሰውዬው ተደጋጋሚ መልዕክት ልኮልኛል?››
ግራ ገባው"የትኛው ሰውዬ?"
"ሀለቃህ...ዳግላስ?"

ከመደንገጡ የተነሳ ተንደርድሮ ወደእሷ ቀረበና ሞባይሉን ከእጇ ተቀበላትና ኢሜሉን ተራ በተራ እየከፈተ አየ...ከዛ በድንጋጤ እግሮቹ ዝሎ ወለሉ ላይ ተዘረፈጠ..ኑሀሚም ድንጋጤው ክፍኛ አዝሏት ስሩ ተንበረከከች፡፡
ስልኩን ተቀብላው ኢሜሉን በማንበብ የሆነውን ለመረዳት የሚያስችል ጥንካሬ ከውስጧ ማግኘት አልቻለችም።ሽው እያለ መጥቶ እርቃን ሰውነቷን የሚገርፋት እርጥብ አየር ነፍሷን ጭምር እያቀዘቀዘው ነው።
"ምንድነው የሆነው?"ጥንካሬዋን አሰባስባ የሆነውን ሁሉ ከእሱ አንደበት ለመስማት ጠየቀችው።ስልኩን መልሶ ከፈተና በኢሜሏ የተላከለትን ፎቶዎች አወጣና"ወንድምሽ...እዚህ መጥቷል"አላት
"ወንድሜ ?እዚህ እንዴት?››ካርሎስ የሚያወራው ነገር ምንም እየገባት አይደለም፡፡

"አላውቅም ግን..እይ ተመልከቺ ዳግላስ እጅ ነው ያለው...ፎቶውን ወደእሷ አቅርቦ እያሳያት"ይሄውልሽ...ይሄንን ቦታ በደንብ አውቀዋለው፡፡ ማንም ሊደርሶበት የማይችለው የዳግላስ ምሽግ የሆነው ሳንቹዋሪ ነው።››
ፎቶውን ተቀበለችና በፍዘት ትመለከተው ጀመር...ዥውውውው አለባትና ቀድሞ ስልኩ ከእጇ ላይ ተንሸራቶ ወደቀባት...ፈጠን ብሎ ሊደግፍት ሲንቀሳቀስ ቀድማ ወደኃላዋ እራሷን ስታ ተዘረረች...በፋጥነት ተነሳና አፋፍሶ አቅፎ አልጋ ላይ አስተኛት።ልብስ ደራርቦ አለበሳትና ከድንጋጤ እስክትወጣ መጠበቅ ጀመረ።

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

10 Oct, 17:03


ማናአስ ሲገብ ፍርሀታቸው ከላያቸው ላይ ረግፎ ...የድል ብስራት ፈንጠዝያ ልባቸውን ሲያሞቀውና ...በሀሴት ነፍሳቸው ስትደንስ እየታያቸው ነበር፡፡ በእኩለ ለሊት ለስድስት ቀን ተኩል ከተጓዙበት ጀልባ ወርደው የከሳ አካላቸውንና የወፈረ ተስፍቸውን ይዘው የወረዱት፡፡ቀጥታ ወደከተማዋ መካከል ተጓዙ።ከተማዋም ልክ እንደእነሱ ደምቃና በቀለማት አሸብርቃ ነበር።ልክ እነሱን በፈንጠዝያ ለመቀበል እንዲህ ጠብ እርግፍ ብላ ተዘጋጅታ ያማረች ሙሽራ ነው የምትመስለው ።
እንደምንም የሚያረፍበት ቤርጎ ፈልገው ያዙና ተከራይተው ወደውስጥ ገቡ፡፡ እቃቸውን አራግፈው አስቀመጡ፡፡እሷ ፈጥና ስልኳን እና ቻርጀሯን አወጣችና ሰከችው፡፡ነፃ መውጣቷን ለወንድሞ ደውላ እስክትግረው እና ድምፁንም አስክትሰማ ቸኩላለች፡፡ስልኩን ከሰካች በኃላ ወደአልጋው ሄዳ ቁጭ አለች..ከርሎስም ከጎኗ ተቀመጠ፡፡
‹‹ምንድነው አንተ ከተማዋ እንዲህ ያሸበረቀችው?"ስትል በመንገዷ ያየችውን ነገር ካርሎስን ጠየቀችው።
"ገና በዓልን ለማክበር ነው እንዲህ ሽር ብትን የምትለው...በየአመቱ በዚህ ጊዜ የተለመደ ነው።››
"ውይ ገና ደረሰ ማለት ነው?"
"ታከብሪ ነበር እንዴ?"
"ገናን እንኳን በተለየ ሁኔታ አላከብርም..ግን በሀገሬ ኢትዬጰያ ከ10 ቀን በኃላ የሚከበረውን የጥምቀት በአል ነው በተለየ ሁኔታ የማከብረው።ታውቃለህ አሁን እግዚያብሄር ፈቅዶ እዚህ ከደረስኩ ተጨማሪ ቀናቶችን ማባከን አልፈልግም ....ቀጥታ ወደሀገሬ ሄጄ ከእንዳልኩህ መጪውን የጥምቀት በዓል በሀገሬ ምድር ላይ ከወንድሜ ጋር ማክበር አለብኝ።››
‹‹እና በሳምንት ውስጥ ትሄጂያለሽ ማለት ነው?"ሲል በቅሬታ ጠየቃት።

"አይ ነገ ወደብራዚሊያ ብበር...ከተሳካልኝና ትኬት ማገኝ ከሆነ ከነገወዲያ ወደሀገሬ እበራለሁ..."
"ቆይ ክብረ በዓሉ ሀይማኖታዊ ነው?ማለቴ እንዲህ በትኩረት ልታከብሪው የጓጓሽበት ምክንያት አልባኝም።"
""ሀይማኖተዊነቱ እንዳለ ሆኖ አንድም እኔና ወንድሜ የተወለድንበት የልደት ቀናችን ነው...ሁለተኛው ደግሞ እናትና አባታችንን በሞት የተነጠቅንበት ቀን ነው። በዚህም ምክንያት ግማሽ ደስታ ግማሽ ሀዘን...ከፊል ሳቅ ከፊል ለቅሶ የምናለቅስበት ቀን ነው።በእንደዛ አይነት ቀን ወንድሜን ብቻውን እንዲሆን ማድረግ አልችልም።ለቅሶውንም አብሬው ማልቀስ ሳቁንም ከእሱ ጋር መሳቅ ነው የምፈልገው።››
ካርሎስ ለረጅም ደቂቃ በትካዜ ዝም አለና"አሁን ደስታዬ ሁሉ ጥሎኝ በነነ"አላት፡፡

ደንግጣ በመሀከላቸው ያለውን ክፍተት አስወግዳ ወደእሱ ተጠጋችና "ምነው? ምን ተከሰተ?"ስትል ጠየቀችው።
"እኔ እንጃ አንዳንድ ነፃነት አዙሮ አዙሮ እጦትና ቦዶነት ላይ ነው ሚጥለን… አሁን ነው ያወቅኩት።እንደዚህ ጥልቅ ብቸኝነትና የሚሸረካክት የእጦት ስሜት እንደሚሰማኝ ባውቅ ኖሮ ምን አልባት እዛው የአማዞን ጥቅጥቅ ደን ውስጥ እየዟዟርን ዘላለማችንን እንድንኖር አደርግ ነበር"

አንተ ምን አይነት ክፉ ነህ..ትከሻውን በፍቅር ነቀነቀችውና ወደራሷ ጎትታ ጉንጩን ሳመችው፡፡ ወደኃላዋ ስትመለሰ መልሶ ጎተተና ከንፈሯ ላይ ተለጠፈባት፡፡ ...በቀላሉ ሊላቀቁ አልቻሉም፡፡ ተያይዘው አልጋው ላይ ወደኃላቸው ተዘረሩ   ፡፡ከዛ ለመጀመሪያ ጊዜ በምቾት በሚያነጥረው አልጋና በሚለሠልሰው ፍራሽ ላይ ለስላሳ ፍቅር ሰሩ...በሁለቱም ምናብ በተሻለ ምቹ ቦታ ፍቅር መስራት የተሻለ እርካታ ያስገኛል የሚል ስሌት ነበራቸው።ግን እንደዛ አይደለም ...እንደውም ከስቃይ የተለወሰ ተራክቦ ልዩ እና ቸኮሌት አይነት ጣዕም አለው።

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

10 Oct, 17:02


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-28
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ካርሎስና እና ኑሀሚ በአምስተኛ ቀናቸው ነበር ከአከባቢው የተንቀሳቀሱት፡፡በዛን ወቅት ኑሀሚ የተመረዘችው መርዝ ሙሉ በሙሉ ከሰውነቷ ተወግዶ… የሟሸሸ የነበረም ሰውነቷ ተነቃቅቶ….ጥንካሬዋም በተወሰነ ፐርሰንት ተመልሶ ነበረ፡፡ ባለውለታቸውን የሆነችውን ጎጆ በፍቅር ተሰናብተው አካባቢውን ለቀው የአማዞንን ወንዝ ደርቻ ተከትለው በምስራቅ አቅጣጫ ለአንድ ሰዓት ተኩል በእግር ከተጓዙ በኃላ አንድ እሮጌ ጀልባ የያዘ ግለሰብ አጋጠማቸው፡፡ከእሱ ጋር በገንዘብ ተደራደሩና ታብቲንጋ ከተማ ድረስ እንዲያደርሳቸው ተስማምተው ጉዞ ጀመሩ፡፡የዛኑ ቀን አመሻሽ ላይ ያሰቡበት ቦታ ደረሱ፡፡
‹‹ይህቺ ከተማ የአየር ትርንስፓርት አገልግሎት አላት ነው ያልከኝ..?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹አዎ አላት..ማኑሳ ድረስ መሄድ ይቻላል፡፡››
‹‹ታድለን…በቃ ነገሮች ወደመጨረሻው ምዕራፍ እየተቃረበ ነው ማለት ነው…ተዲያ ወደከተማው እንግባና የአየር ትኬት ካገኘን እንሞክራ››
‹‹አይ ወደከታማ መግባት አንችልም..፡፡እንደምታያት ይህቺ አንስተኛ የጠረፍ ከተማ ብራዚል ውስጥ ትገኝ እንጂ ለኮሎምቢያ ቅርብ መሆኗን እንዳትረሺ..ያ ማለት ደግሞ የዳግላስ ተፅእኖ በተወሰነ መልኩም ቢሆን ይኖራል ማለት ነው፡፡ በተለይ ወደ ብራዚል ከገባን ቀጥታ የአየር ትራንስፖርት የሚገኝባት ከተማ ይህቺ ስለሆነች ቀጥታ ወደእዚህ እንደምንመጣና ወደአየር መረፊያ ጎራ እንደምንል በቀላሉ ይገምታል..ስለሆነም ከተማው ውስጥ ዋና ዋና ቦታዎች እና በተለይ ደግሞ አየር ማረፊያ ላይ ሰዎቹን እንደሚያስቀምጥ እርግጠኛ ነኝ፡፡
‹‹እና ምን ይሻለናል?፡፡››በስጋት ጠየቀችው፡፡
‹‹ረጅሙን መንገድ ነው የምንመረጠው..ማለት አሁንም ወደ ምስራቅ ጉዞችንን እንቀጥልና ወደ ቤንጃሚን ኮንስተንት ከተማ ነው የምንሄደው፡፡››
‹‹ቤንጃሚን ኮንስተንት ደግሞ ማን ነች?››
ቤንጃሚን ኮንስተንት አማዞን ደን ውስጥ ከበቀሉ የብራዚል የጠረፍ ከተሞች ውስጥ አንዷ ስትሆን ከተማዋ ጃዋሪ በተባለ ወንዝና በአማዞን ወንዝ ተከባ የምትገኝ ትንሽ ከተማ ነች፡፡ከዚህ አሁን ካለንበት ከተማ በጀልባ የሁለት ሰዓት ቢፈጅብን ነው፡፡ማንም ወደ ዛች ከተማ ይሄዳሉ ብሎ እይገምተንም…እዛ ከደረስን በኃላ የተሻለ የተባለ ዘመናዊ ጀልባ እንከራይና ቀጥታ ወደ ማናአስ እንጓዛለን፡፡
‹እንዳልክ …ግን የሆነ ቻርጅ ያለበት ቦታ ፈልግን ስልኬን ቻርጅ ማድረግ አለብኝ፡››የምታስበውን ነገረችው፡፡
‹‹ምን ሊያደርግልሽ?››
‹‹ትቅዳለህ..ለወንድሜ ደውዬ ቢያንስ እስከሁን በጤና መሆኔን ላሳውቀው ነዋ፡፡››
‹‹አይ አይሆንም…ስልክሽን አብርተሸ ለወንድምሽ ደወልሽለት ማለት ያለሽበትን አካባቢ ቀጥታ ለሀገርሽ መንግስት እናም ጉደዩን ለሚከታተሉ ለአካባቢው መንግስታት አሰወቅሽ ማለት ነው..ያ ሆነ ማለት ደግሞ ዳግላስም በቀላሉ ዜናውን አገኘ ማለት ነው፡፡እና ሁሉም እኛን ለማግኘት በአካባቢው አሰሳ ይጀምራሉ…ከዚህ በፊት እንዳለኝ ልምድ ደግሞ ከየትኛውም መንግስት ቀድሞ ደጋላስ አፈፍ እንደሚያደርገን እርግጠኛ ነኝ››
‹‹እና ምን ይሻላል?››
‹‹የሚሻለውማ..ማናስ እስክንገባ መቻል….ነው…ወንድምሽም ዘላለም ከሚያጣሽ…ስድስት ሰባት ቀን በናፍቆት እና በትካዜ ቢሰቃይ ይሻላል፡፡አሁን አንቺ እዚሁ አካባቢ እራስሽን ከሰው እይታ ከልለሽ ትጠብቂኛለሽ… እኔ እራሴን ለውጬ ከታማ ገብቼ እመለሳለሁ››
‹‹እንዴ… እኔን እዚህ ብቻዬን ጥለኸኝ ምን ትሰረለህ?››
እጁን ወደኪሱ ሰደደና የሆነ መሀረብ አውጥቶ ቋጠሮውን ፈታና ሁለት የጨው አንኳር የሚመስል አብረቅራቀ መአድን አነሳና በእጇ መዳፍ ላይ አስቀመጠ፡
‹‹ምንድነው?››በመገረም እያየች ጠየቀችው፡፡
‹‹እንቁ ነው..በደኑ ውስጥ በአጋጣሚ በስራ ላይ እያለው በእጄ የገባ ነው..እንደዚህ አይነት ንብረት በምንም አይነት ሁኔታ ቢሆንም በእጅ ከገባ ለገዛ ጥቅም ደብቆ መስቀመጥ በሞት የሚያስቀጣ አደገኛ ወንጀል ነው..በወቅቱ ለዳግላስ ማሰረከብ ነበረብኝ…እኔ ግን ደመነፍሴ አንድ ቀን አጣብቂኝ ውስጥ ስገባ  ይጠቅምሀል ብሎ ሹክ ስላለኝ..የመጣው ይምጣ ብዬ ደብቄ አስቀምጬው ነበር፣.እና አሁን ወደከተማ ሄጄ ወደገንዘብ ልቀይረው...እረጅም የጀልባ ጉዘ ስለሚጠብቅ ብዙ ገንዘብ ያሰፈልገናል…››
መጀመሪያ እንቁውን መለሰችለት..መልሶ በመሀረቡ ቋጠረውና ወደኪሱ ከተተው..፡፡
ከሷ የእጅ ቦርሳዋን አነሰችና ዚፕን ከፈተች፣ከላይ ያሉትን እቃዎች አወጣች ፡፡ፊቱን አዙሮ ሊሄድ ሲል ከስር እንደታሸገ የተቀመጠውን ዶለር መዥርጣ አወጣችና እጁ ላይ አስቀመጠችለት፡፡
‹‹ይሄ አይበቃም?››
አይኖቹ በመገረም ደመቁ‹‹አንቺ ይሄን ሁሉ ብር ከየት አመጣሽ?››
የዛሬን አያድርገውና ሀለቃህ ዳግስ ነበር የሰጠኝ..እና አይበቃም›››….ብላ እንዴት እንዳገኘች ታሪኩን አስረዳችው
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..ይሄ እኮ በጣም ብዙ ብር ነው….በይ አሁን ጀልበ እንፈልግ››አለና ብሩን መልሶላት ቦርሳ ውስጥ ከከተተ በኃላ ተያይዘው ወደፊት ለፊት መራመድ ጀመሩ፡፡
እንደተነጋገሩት እዛው አድረው ንጊት ላይ ወደ ቤንጃሚን ኮንስተንት ከተማ በጅልባ ተጓዙ፡፡ እዛ አንድ ሰዓት ብቻ በማሳለፍ ሌላ ዘመናዊ የተባለ ጀልባ ተከራዩና ወደአማዞኒያ ግዛት ዋና ከተማ ማናአስ ጉዞ ጀመሩ፡.ያው ጉዞ ቀላል አልነበረም….6 ቀን ነው የፈጀባቸው ፡፡ግን ደግሞ በህይወት ረጅም ዘመን ለመኖር ስድስትና ሰባት ቀን መስዋት ማድረግ ያን ያህል ክፉ የሚባል ስላልሆነ አላማረረችም ፡፡
…ታብቲንጋ….ሳኦ ፍረንሲስኮ…ኮረንቲዛ….ዲ አማተራ…ሳኦ ዶሚንጎ….ሳንታ አንቶኒኦ….ሳኦ ፍሊክስ… ሳንታ ሉዚያ… የመሳሰሉን አያሌ ታዋቂ ቦታዎችንና የኣማዞን ወንዝ ዳር ከተሞችን አቋርጠው ማናአስ ከተማ ደረሱ ፡፡
ማናአስ(Manaus) በሀገረ ብራዚል የኣማዞኑያ ግዛት ዋና ከተማ ነች፡፡በብራዚል 2.2 ሚሊዬን ኑዋሪዎች የሚኖሩበት 7ተኛው ትልቋ ከተማ ስትሆን ከተማዋ በአማዞን ደን ውስጥ ከተቆረቆሩ ከ1 ሚሊዬን በላይ ኑዋሪዎች ካሏቸው ሁለት ትልልቅ ከተሞች መካከል አንዶ እና ዋነኛዋ ነች.››
በዛ ላይ የአማዞን ደንን እና የአማዞን ወንዝን ሚስጥር ለመበርበር እና ጥናት ለማጥናት ከመላው አለም የሚሰባበሰቡ ሳይንተስቶችና ተመራማሪዎች በዋናነት የሚከትሙባት ከተማ ነች፡፡በዚህ የተነሳ የአማዞን ልብ የሚል ቅፅል ስም ይሰጧታል፡፡በተጨማሪ አንዳንዶችም የትርፒካሎ ፓሪስም እያሉ ያሞካሻታል፡፡
ማናአስ  ከተማና አካባቢው በኬሚካል ፕሮጀክት..በለውዝ ምርት ….በሳሙና ምርት….በመርከብ ግንባታ እና በጎማ ተክል ምርት በጣም የታወቀች ነች፡፡፡በተለይ በጎማ ምርት ከ1800 አመት በፈት ጀምሮ የታወቀች በመሆኗ ከሀገሪቱ ሀብታም ከተሞች ግንባር ቀደሞ እንድትሆን አስችሏታል፡፡ማናአስ ከተማ በ2014 እ.ኤ.አ የአለምን ዋንጫ ካስተናገዱ 12 የብራዚል ከተሞች አንዷ እንደሆነች ይታወቃል፡፡በከተማዋ ምስራቅ አቅጣጫ ድፍርሱ የኒግሮ ወንዝ እና ሰማያዊው የሶሊመስ ወንዝ አንድ ላይ ተቀላለቅሎ ወደአማዞን በገባርነት የሚፈስባት ልዩና አስደማሚ ስፍራንም በመደመም ማየት ይቻላል፡፡

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

06 Oct, 16:48


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-27
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ
///
እቤት ውስጥ ከገብ በኃላ እንኳን ናኦል እና ምስራቅ ለረጅም ደቂቃ ደንዝዘውና ፈዘው ማህል ወለል ላይ በዝምታ ተገትረው ነበር።

ናኦል እንባ እየተናነቀው"ምስራቅ ምን ውስጥ ነው የገባነው..?ይሄ ሰውዬ ተጫወተብን"አላት ።
ምስራቅም ወደእሱ ተንደረደረችና አቀፈችው ።አንገቱ ስር ሽጉጥ ብላ በጆሮው "አትደንግጥ...እቅድ አለኝ"አለችው።

ዝም አለ...ከዚህ ለመውጣት ምን አይነት ተአምራዊ ዕቅድ ሊኖራት እንደሚችል ምንም ሊገለፅለት አልቻለም።ቢሆንም ከሞስራቅ ጋር ባሳለፋቸው በርካታ አመታት ብዙ ተአምር መሳይ ነገሮችን ስትከውንና ደጋግሞም ሲሳካላት ታዝቦልና የተናገረችው ነገር ንቆ ሊያልፈው አልደፈረም።...
ብራዚል/አማዞን ደን ውስጥ
አካባቢው ድቅድቅ ጨለማ ነው፡፡ጨረቃዋም በሰማይ ላይ ብርሀን አልፈነጠቀችም፡፡ከዋክብቱም የከሰሙ መስለዋል ፡፡ኑሀሚ ካርሎስ የሰራላት የአንጨት ርብራብ አልጋ ላይ ተኝታ የእጇ ጥዝጣዜ ታዳምጣለች፡፡እርግጥ ከትናንቱ የተሻ ጤንነት ላይ ብትገኝም ሰውነቷ ግን ሙሉ በሙሉ እደዛለ ነው፡፡በህይወቷ በእንዲህ አይነት ደካማንትና አቅመ ቢስነት ተሰምቷት አያውቅም፡፡ ካርሎስ በሶስት ቀን ውስጥ ሙሉ በሙሉ እደምታገግም ነግሯት ነበር ፡፡ አሁን አሁን ያለችበት ሁኔታ ስታስበው በሶስት ወር ተሽሏት ከዚህ አካባቢ የምትንቀሳቀስ እየመሰላት አይደለም፡፡ያም ሆኖ ግን ትናንትና ጉሮሮዋን ፈጥርቆ ነፍሷን ሊነጥቃት የነበረው ሲኦላዊ ህመም ዛሬ በሙሉ አቅሙ የለም፡፡ያ የሆነው ደግሞ ካርሎስ እጇ ላይ ባሰረለት የባህል መድሀኒት ምክንያት ነው፡፡
እንደምንም አንገቷን ወደ ዳር ሸርተት አድርጋ አየችው፡፡ እዛው ርብራብ አልጋ ጎን ባለ ጠፍጣፍ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ አንገቱን በካኔቴራው ሙሉ በሙሉ ሸፍኖ የእንጨት አልጋውን ቋሚ ተደግፎ ጨልጥ ያለ እንቅልፍ ተኝቷል፡፡ አሳዘናት፡፡ቢቻላት ኩርምት ብሎ በተቀመጠበት እንቅልፍ የወሰደውን ይሄን መልካም ሰው ጎትታ ወደራሷ ስባ እሷ የተኛችበት የእንጨት ርብራብ ላይ ከጎኗ ሽጉጥ አድርጋው ብትተኛ ደስ ይላት ነበር ፡፡
ወዲያው ሀሳቧን ሳትጨርስ ነጎድጓድ በሰማዩ አንፀባራቂ ብርሀን እየረጨ ያንቧርቅ ጀመር፡፡የሚያስፈራ ደራጎናዊ ድምፅ አካባቢውን ያናጋው ጀመር፡፡ ኑሀሚ እንኳን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እንደዚህ አይነት ቦታ ሆና ይቅርና በሀገሯ ሰማይ ስር በገዛ ቤቷ እያለች ሳይቀር እንዲህ አይነት ነጎድጎድ በጣም ነው የሚያስፈራት፡፡፡እንደምንም ደካማ እጃን አንቀሳቀሰችና ትከሻው ላይ አኑራ በመወዝወዝ..‹‹ካርሎስ ካርሎስ›› ስትል ጠራችው፡፡

በርግጎ ተነሳ‹‹..ምን …አመመሽ እንዴ?››
‹‹አይ ነጎድጎድ ፈራለሁ››
ከተቀመጠበት ተነሳና ወደእሷ ተንቀሳቀሰ….ርብራቡ ጠርዝ ላይ ከጎኗ ተቀመጠና እጆቿን በእጆቹ ውስጥ አስገብቶ ያሻሽላት ጀመር፡፡ከእሱ ሰውነት ወደእሷ እየተላለፈ ያለው ሙቀት ብቻ ሳይሆን ብርታትና ጥንካሬ ጭምር ነው፡፡
በድጋሚ‹‹በጣም እኮ ነው የፈረሁት››አለችው፡፡
‹‹አይዞሽ…ስጋታችን፤ፍረሀቶችንና እና ጥርጣሬዎቻችን ሰው በመሆናችን የተሰጡን ፀጋዎች ናቸው፡፡ካለበለዚያማ እህያና በቅሎ መሰል አይነት ስሜቶች ስለሌላቸው ከእኛ የተሻሉ እደለኞች ናቸው ልንል መሆኑ ነው?፡፡››
‹‹እሱስ እውትህን ነው››አለችና ይበልጥ ተለጠፈችበት

ወዲያው ሰማዩን አግቶ ይዞ የነበረውን ዝናብ ዘረገፈው፡፡የተሰራችው ጊዜያዊ ጎጆ ሙሉ በሙሉ በዛ ድቅድቅ ጨለማ የሚወርደውን የዝናብ ውሀ አግዳ ለማስቀረት ጥንካሬው አልነበራትም፡፡ሁለቱም በ5 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በዝናብ ራሱ፡፡እሷ ከህመሙና የሰውነት ጥንካሬዋ በመዳከሙ የተነሳ ዝናቡንና ቅዝቃዜውን መቋቋም ስላልቻለች ትዘፈዘፈች፣ካርሎስ የሚያደርገው ጠፋበት፡፡ ሙሉ በሙሉ ወደእንጨት አልጋው ወጣና ከእሷ ተስተካክሎ ተኛ…አቀፋትና ወደራሱ አስጠግቶ ከሰውነቱ ለጠፋት፡፡የናፈቀውን የእናቱን ጡት እንዳገኘ ህፃን ልጥፍ አለችበት፡፡የተሻለ ምቾት ተሰማት፡፡ከዝናብ ውርጅብኝ የምትሸሸግበት መጠለያ ዋሻ ያገኘች አይነት ስሜት ተሰማት፡፡ እጆቹን በረጠበ ልብሷ ስር ሰቅስቆ በማስገባት ሰውነቷን ላይ አሳረፈና ይዳብሳት ጀመር..፡፡ከዛ ቀስ እያለ ከንፈሩን ከንፋሯ ላይ አሳረፈና በቀስታ ይመጣት ጀመር፡፡አሁን ከውስጧ እየተቀጣጠለ ያለው ሙቀት ወደላይኛው የሰውነት ቆዳ በመድረስ ከላይ የሚያርፋባትን ዝናብ የሚያስከትልባትን ቅዝቃዜ እያተነ የሚያስወግድላት እየመሰላት ነው፡፡ጭልጥ ያለ ምናባዊ ህልም ውስጥ ነው የገባችው፡፡ከንፈራቸው ሳይላቀቅ ዝናቡም ከመቆሙ በፊት እሷ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰዳት፡፡

ስትነቃ ጎጆዋ በጥዋት የደመቀ የፀሀይ ፈንጣቂ አድምቋታል፡፡ሁሉ ነገር ብሩህ ፣ ሁሉ ነገር ዳማቅ ሆኖ ነው እየታየ ያለው፡፡እራሷን ለማንቀሳቀስ ሞከረች፡፡ አሁንም ሰውነቷ እንደተሳሰረ ነው፡፡ወደ ጎን አንገቷን መልሳ ተመለከተች፡፡ ለሊት ጎኗ ተኝቶ የነበረው ጉብል አሁን የለም፡፡አይኖቾን ብታንከራትትም ጎጆው ባዶ ነው፡፡ አንደምንም እራሷን አበረታታ ከተኛችበት ተነሳች፡፡ ዱላ መሰል እንጨት ተደግፋ እንደምንም እግሮቾን እየጎተተች ወደጎጆዋ በራፍ ሄደች፡፡ፊት ለፊቷ ያለው አማዞን ወንዝ እየተገማሸረ ጥሩ አቋም ላይ አንዳለ የማራቶን ራጭ ወደፊት እየገሰገሰ ነው፡፡አካባቢውን የሞሉት ውብና ማራኪ ወፎች ወዲህና ወዲያ አክሮባት እየሰሩ ይዝናናሉ.. አይኖቾን አሩቅ ስታማትር ካርሎስ በ500 ሜትር ርቀት በፓንት ብቻ አማዞን ወንዝ ውስጥ ጠልቆ ገብቶ ዓሳ ላመስገረ ሲዳክር ተመከተችው፡፡ፈገግ አለችና ወደ ውስጥ ተመለሰች፡፡ወደ ሻንጣቸው ተጠጋች ፡፡ውሀ የማያሳገባውን የሻንጣ ዚፕ ከፍታ ውስጥ ያለውን የካርሎስን ማስታወሻ ደብተር ከእነእስኪሪብቶው አወጣች፡፡እዛው መሬት ይዛ ተቀመጠችና ለመፅሀፍ ተዘጋጀች፡፡
ሀሳቧ ለወንድሞ ደብዳቤ ለመፅሀፍ ነው፡፡ለሊት እንዛ በአየሩ ነጎድጓድ ሲረጭ… ከሰማይ ዶፍ ዝናብ ሲወርድ… በውስጧ በተፈጠረባት ፍራቻ ድንገት ብሞትስ? ወንድሜ የሆነ ነገር ሳልለው እንዴት ይሆናል? ብላ አሰበችና በሰላም ለሊቱ ነግቶ ለጥዋት ፀሀይ ከበቃች ለወንድሟ ደብዳቤ ጻፋ እንደምታስቀምጥ ለራሷ ቃል ገባች፡፡ድንገት ብትሞት ካርሎስ ደብዳቤውን ለወንድሞ አንደሚያደርስላት እርግጠኛ ነች፡፡ ደብዳውን መፃፍ ጀመረች፡፡
ወንድሜ-
…የእኔ ትዝታ
ደህና ሁን
….. ቀንና ማታ
ትዝ ይልሀል ይሄን ዘፈን እየደጋገምኩ ስዘፍንልህ? በጣም እኮ ነው የምወድህ...ገና እናታችን ማህፀን ውስጥ ሆነን እንኳን ምርጥ ጎደኛዬ ነበርክ..እና እዛም ሆነን በጣም ነበር የምወድህ...ከተወለድን በኃላም የእናታችንን ግራና ቀኝ ጡት ተካፍለን አይን ለአይን እየተያየን በፍቅር ስንጠባ ሁሉ እወድህ ነበር...ወላጆቻችን ሞተው ቤታችን ሁሉ በለቀስተኞች ተሞልቶ ዋይ ዋይ በሚባልበት በዛን ወቅት እናትና አባቱን አጥቶ ወንድሜ እንዴት ይቋቋመዋል?ብዬ አጨነቅ ነበር...ግን እኮ የሞቱት የእኔም ወላጆች ነበሩ፤የተጎዳሁት እኔም ነኝ...ግን ደግሞ ከእኔ በላይ አንተ ታሳዝነኝ ነበር።ጎዳና ተጥለን ስንኖርም የእኔ ረሀብ ሳይሆን ያንተ ሆድ መንጓጓት ነበር የሚያሳምመኝ።ብቻ ገና ከፅንሰታችን ጀምሮ እስከዚህች ሰዓት ድረስ አንተ ብቸኛ ወንድሜ ነህ...አንተ ብቸኛ የልብ ጓደኛዬ ነህ...አንተ ብቸኛ ዘመዴና የልቤም የነፍሴም ሰው ነህ።

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

06 Oct, 16:48


ወንድምአለም ለስራ በመጣሁበት የሠው ሀገር አንድ ትዝታውን ተነጥቆ አእምሮው የተናጋበትን ሰው በሰባአዊነት ረዳለሁ ብዬ የማልወጣበት ቅርቃር ውስጥ ገብቻለሁ።ሠውን ለመርዳት ሲሉ ችግር ውስጥ መግባት እኮ የአንተ እንጂ የእኔ ባህሪ አልነበረም።ግን ያው ሰው ነኝና አንዳንዴ ስህተት እሰራለሁ… እናም … በቀላሉ የማይታረም ስህተት ሰራሁ።ልረዳው ያልኩት ሰው ኮኬይን አምራች አለምአቀፍ ሽብርተኛ ሆኖ ተገኘ።እኔንም አፍነው አማዞን ማህፀን ውስጥ ጣሉኝ፡፡ ላንተ ለወንድሜ ለመትረፍ ስል ብዙ ታገልኩ፤ሊቀብሩኝ ከቆፈሩት ጉድጓድ ሌላ ሰው ገድዬ በመቅበር ለማምለጥ ሞክሬ ነበር።ከዛ እንደውቅያኖስ ዝርግ እንደሸረሪት ድር የተጠማዘዘና የተወሳሰበ ከሆነው ደን በቀላሉ ወጥቶ የአንተ የወንድሜን አይን ለማየት መቻል ቀላል ሆኖ አላገኘሁትም።ካርሎስ በሚባል አንድ ቀና ሰው ድጋፍ ለማምለጥ ባደረኩት ጥረት ከአጋቾቼ እገታ የራቅኩ ቢሆንም በአጋጣሚ በአንድ መርፌ መሠል እሾህ እጣቴን ተወግቼ ተመርዤለሁ...እርግጥ ይሄ ካርሎስ የተባለው መልካምና ተወዳጅ ሰው ከጫካው ባህላዊ መድሀኒት ፈልጎ አክሞኛል … ፍፅሞ እስከወዲያኛው በመዳኔ እርግጠኛ ባልሆንም የተወሰነ ለውጥ ግን እያየሁ ነው፡፡
አንድ ሩሲያ የስለላ ስልጣና ስወስድ መምህሬ የነበረ ሰው ‹‹በጉዞህ ተስፋ አትቁረጥ...ይሄ የሚሆነው ግን ነገሮች በትንሹም ቢሆን እያደጉና እየተሻሻሉ ከሄድ ብቻ ነው።ነገሮች ባሉበት የቆሙ ከሆነ ወይም እድገታቸው የኃሊት ከሆነ በጊዜ ተስፋ መቁረጥ እና አቅጣጫን ማስተካከል የብልህ ውሳኔ ነው።››ይል ነበር፡፡
ምን አልባት መርዙ ቀድሞ ሰውነቴን የመረዘው መሠለኝ።እና ምን አልባት ወደነእማዬ የመሄጂያ ቀኔ የደረሠ ይመስለኛል።እና እንደዛ ከሆነ መጠንከር አለብህ።አታየኝም ብለህ ብትዝረከረክና እራስህን ብትጥል በጣም ነው ሚደብረኝ።
ይበልጥ ጠንካራና ትልቅ ሰው መሆን አለብህ።ቸኮሌት ፍብሪካው ሲያልቅ ሁሌ በየአመቱ በልደት ቀኔ አንድ ሶስት ካርቶን ለህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ላሉ ህፃናት በእኔ ስም ትሰጥልኛለህ።እነሱ ደስ ሲላቸው እያየሁ እኔም ደስ ይለኛል።
ምስራቅን ቸው በልልኝ።ወንድሜን አደራ ብሎሻል በልልኝ።በጣም ነው የምወድህ የእኔ ወንድም።፡፡
ፅፋ ስትጨርስ ወረቀቱን አጣጠፈችና ከጀርባው የወንድሟን ሙሉ አድራሻ ከነስልክ ቁጥሩ ፅፍበት አጣጥፍ አስቀመጠች።

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

06 Oct, 16:46


ልጅም ቶሎ ያንጠለጠለውን የእጅ ቦርሳ ጠረጴዛ ላይ አደረገና ከብር የተሠራ የሚመስል ሁለት የእጅ ብራስሌት መጀመሪያ ምስራቅ እጅ ላይ ቀጥሎ ናኦል እጅ ላይ አጠለቀና ከኪሱ ስልኩን አውጥቶ በማብራት ሲነካካ እጃቸው ላይ ያጠለቀላቸው ብራስሌት ቀለሙን ከብራማነት ወደ ደማቅ ሰማያዊነት ቀየረ።ዝም ብሎ ሁኔታውን ሲከታተል የነበረው ዳግላስ መናገር ጀመረ
"አሁን እንግደህ እህታችሁን እኔ ሳልሆን ለእናንተ ማመጣላችሁ ..እናንተ ናችሁ ለእኔ የምታመጡልኝ..." ብሎ ኑሀሚ የእሱን ሰው ገድላ ከሌላ ከእሱ ሰው ጋር እንደኮበለለች...እስከአሁንም በመላው አማዞን ደን ውስጥ ቢያስፈልጋት ሊያገኛት እንዳልቻለ...እሷን መሞቷን ካላረጋገጠ ወይም በህይወት እጅ ካላስገባት የሰላም እንቅልፍ እንደማይወስደው..ወንድሟን ያስመጣበት ምክንያት ተሳክቶላት እንኳን ማምለጥ ብትችል ለወንድሟ ደህንነት ስትል በፍቃዷ መልሳ እጅ እንድትሰጥ አቅዶ ያደረገው እንደሆነ አብራርቶ ከአሁን ሰዓት በኃላ እዛው እሱ የሚኖርበት ወለል ላይ የራሳቸው ክፍል እንደሚሰጣቸው እና እጃቸው ላይ በተጠለቀላቸው አንባር ሙሉ የ24 ሰዓት ክትትል እንደሚደረግላቸው ነገራቸው። እሷ መጥታ በፍቃዷ እጇን እስክትሰጥ ወይንም መሞቷ እስኪረጋገጥ ድረስ ከክፍላቸው መውጣት እንደማይችሉ...ፀባያቸውን እስካሳመሩና ችግር ለመፍጠር እስካልሞከሩ ድረስ የሚፈልጉት ነገር እንደሚያሟላላቸው አብራርቶላቸው.. ወደክፍላቸው እንዲወስዳቸው አዘዘ...።የታዘዘውም ታጣቂ እየጎተ ወሰዶ አንድ ለቀቅ ያለ ሻወርና ማንበቢያ ክፍል ያለው ባለአንድ ክፍል ቤት ውስጥ አስገብቶ ከውጭ ዘጋባቸው።እቤት ውስጥ ከገብ በኃላ እንኳን ሁለቱን ለረጅም ደቂቃ ደንዝዘውና ፈዘው ማህል ወለል ላይ በዝምታ ተገትረው ነበር።

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ልብ ወለድ በፅዮን fiction ❤️😘

06 Oct, 16:45


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-26
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ፔሩ/ኢኪዬቶስ
ጥዋት ምስራቅ እና ናኦል ከእንቅልፋቸው አርፍደው ቢነቁም እርስ በርስ ለመተያየት ግን ተፋፍረው ነበር፡፡
‹‹ምነው የእኔ ፍቅር አመመሽ እንዴ?››ሲል የመጀመሪያውን ዓ.ነገር ተናገረ፡፡
‹‹አይ ደህና ነኝ…ማታ የጠጣውት የሀገሬው መጠጥ መሰለኝ እራሴን አሞኛል፡፡››
‹‹አዎ አንቺ.. እሱ ነው እንዴ …እኔም እኮ ጭፍግግ ብሎኛል››
‹‹መሰለኝ…በል አሁን ልብሳችንን ለባብሰን እታች እንውረድና ቁርስና ብና ነገር እንጠጣበት››
‹‹..እርግጠኛ ነኝ  በቡና ይሻለናል?፡፡››ሁለቱም ተስማሙና ልብሳቸውን ለባብሰው ፊታቸውን ተጣጠቡና ተያይዘው ወደታች ወደሆቴሉ ወረዱ፡፡ ጎን ለጎን ተቀምጠው ቁርስ አዘዙ፡፡ሁለቱም ያስደበራቸው ነገር ምን አንደሆነ ያውቃሉ፡፡ማታ የፈፀሙት ወሲብ ነው፡፡እርግጥ በወቅቱ ሁለቱም ፍፅም ደስታኛ ነበሩ፡፡አሁን እራሷቸውን እስኪያማቸው ድረስ እንዲህ ሀሳብ ላይ የጣላቸው ነገስ እንዴት ነው የምንቀጥለው…?የሚለው ነው፡፡የቀረበላቸውን ቁርስ በልተው ቡናቸውን ጠጥተው ሂሳብ ሲጠይቁ አስተነጋጆ ‹ተከፍሏል› አለቻቸው፡፡ግራ ተጋብተውና ደንግጠው‹‹ማነው የከፈለው ?››ሲሉ በአንድነት ጠየቁ፡፡
‹‹እዛ ጋር ተቀምጦ የነበረው ሰውዬ ነው…ከ5 ደቂቃ በፊት ውጥቶ ሄዶል፡፡ ይሄንን ወረቀት ስጪያቸው ብሎኛል፡፡›› ብላ ብጣሽ ወረቀት አቀበለቻቸው፡፡ናኦል ፈጠን ብሎ ተቀበላትና አንድላይ አነበቡት፡፡
‹‹አሁን ወደ ክፍላችሁ ተመለሱና ሻንጣችሁን ሸክፋችሁ ለጉዞ ዝግጁ ሁኑ፡፡››ይላል፡፡
‹‹ደግሞ ሌላ ጉዞ?››እሱ ነበር ተናጋሪው፡፡
እንደተባሉት ወደ ሆቴላቸው ተመለሱና ሻንጣቸው በፍጥነት ሸከፉ..ወዲያው የሆቴሉ ስልክ ጠራ….ምስራቅ አነሳችው‹‹ወደታች ውረዱ.. ታክሲ ቀሞ ይጠብቃችኋል››የሚል ጎርናና ድምፅ መልዕክቱን ተናገረና ድምፁን አቋረጠው፡፡
ትእዛዙን ተከትለው ..ሻንጣቸውን እንደያዙ ቀጥታ ከሆቴል ሲወጡ ባለታክሲውን አይኑን በጥቁር መነፅር ሸፍኖ በራፍ ከፍቶ ሲጠብቃቸው አገኙ።ያለምንም ንግግር ሻንጣቸውን እየጎተቱ ስሩ ደረሱ።ሻንጣቸውን ተቀበለና ወደመኪናው ኃላ ወስዶ ካሶኒውን ከፈተና ሻንጣዎችን አስገብቶ መልሶ ከደነውና ወደሹፌሩ መቀመጫ ሲሄድ ምስራቅ እና ናኦል ወደውስጥ ገብተው ከኃላ ወንበር ጎን ለጎን ተቀምጠው ነበር።ቀጥታ 25 ደቂቃ በመንዳት ከከተማው ውጭ ነበር የወሰዳቸው።ምን ሊከሰት ነው በሚል ግራ መጋባትና ጉጉት ነገሮችን ሲጠብቁ ቀጥታ ታክሲዎ ቻርተር አውሮፕላን ያለበት ቦታ ደርሶ ነበር ያወረደቻቸው።ከዛ ቆመው እርስ በርስ እየተያዩ ሻንጣቸው ከታክሲዋ ወረደና አውሮፕላኑ ላይ ተጫነላቸው።
ናኦል እና ምስራቅ በተሳፈሩበት አነስተኛ ቻርተር ሄሌኮፍተር ውስጥ ከካፕቴኑ ውጭ ሌላ አንድ ሰው ነው ያለው።ገብተው እንደተቀመጡ መጀመሪያ ሻንጣቸውን እንዳለ ዘርግፎ በውስጡ ያለውን ዕቃ እያብጠረጠረ ተመለከተ። ከዛ በመሳሪያ በመጠቀም መቅረፀ ድምፅ ወይም አቅጣጫ መከታተያ መሳሪያ መያዝ አለመያዛቸውን ፈተሸ።ከዛ በኃላ የሁለቱንም ሞባይል ተቀበለና ያለምንም ማብራሪያ በታክሲ ይዞቸው መጥቶ አሁንም እስኪበሩ ድረስ አታች ቆሞ ይጠብቃቸው ለነበረ የታክሲ ሹፌር በግዴለሽነት ወረወረለት.፡፡አንድን ሲቀልበው ሌላው አምልጦት መሬት ላይ ተፈጠፈጠ.....።ጎንበስ ብሎ አነሳውና ሁለቱንም ኪሱ ከቶ ታክሲው ውስጥ በመገባት መኪናዋን አስነስቶ በመጣበት አቅጣጫ ተመልሶ ሲሄድ በተቀመጡበት ሆነው በገረሜታ ተመለከቱት።
ወዲያው ጎኗቸው ያለው ፈታሻቸው አውሮኘላኑን እንዲያንቀሳቅስ ለካፒቴኑ በእጅ እንቅስቃሴ ምልክት ሰጠው...። ከ3 ደቂቃ በኃላ አውሮኘላኗ አየር ላይ ተሠቀለች።አፍንጫዋን ወደኃላ አዞረችና አረንጎዴ ውቅያኖስ ወደሚመስለው ጥቅጥቅ የአማዞን ደን መክነፍ ጀመረች ።አይናቸውን ዝቅዝቅ ወደታች ሲመለከቱ አማዞን ወንዝ ሰሌሜ ሰሌሜ እየጨፈረ በአማዞን ደን እንብርት ዙሪያ ጥምዝ ሲሰራ የአማዞን ደንን ወገብ ሸብ አድርጎ ለማሰር በእግዜር ከዘንዶ ቆዳ የተሠራ ሰማያዊ ቀበቶ ነው የሚመስለው።
ከሁለት ሰዓት በስጋት የተሞላ ምቾት አልባ በረራ በኃላ አውሮኘላኗ ከፍታዋን መቀነስና አፍንጫዋን ወደታች ደፍታ ለማረፍ መምዘግዘግ ጀመረች። እታች አንድ የተንጣለለ ግቢ ውስጥ ባለአንድ ፎቅ ግዙፍ ህንፃ መኖሩን የታያቸው ለማረፍ መሬት ከተቃረብ ኃላ ነው።
አውሮፕላኖ አርፈ… ሁለቱም ከውስጧ እንዲወጡ ሲደረግ ሜዳው ጠቅላላ እጅግ ዘመናዊ መሳሪያ በታጠቁ አስፈሪ ታጣቂዎች ተሞልቶ ነበር።ናኦል ከመፍራቱ የተነሳ እራሱን ችሎ መቆም አቃተውና ወደምስራቅ ተጠግቶ እጇን ጨምድዷ ያዛት፡፡እሷም የእሱን ያህል አይሁን እንጂ ፈርታለች፡፡ሁኔታዎችም ካሰበቻቸው በላይ አስፈሪና የተወሳሰብ ሆኖባታል። ወዲያው አንድ ታጣቂ ወደእነሱ ቀረበና በተወለካከፈ የእንግሊዘኛ ቃል"ተከተሉኝ"አለና ቀድሞቸው ፊቱን አዙሮ መራመድ ጀመረ...።የተያያዘ እጃቸውን አላቀቁና ተከተሉት  ።
ፊት ለፊት ባለው የህንፃው ትልቅ ባለጣውላ በራፍ እየመራቸው ገባና ወደ ውስጥ ይዘልቃል ብለው ሲጠብቁ ወደጎን በመታጠፍ በደረጃው ወደአንደኛው ፎቅ ይወጣ ጀመር። እርስ በርስ ተያዩና በዝምታ ተግባብተው ተከተሉት። የተወሰነ ኮሪደር ካለፍ በኃላ ግዙፍ አዳራሽ መሳይ ሳሎን ውስጥ ነው ይዞቸው የገባው።
የገብበት ክፍል ሳሎን ነው ብለው ከማሰብ ይልቅ ሙዚዬም ነው ማለት ይቀላል።ግድግዳው ላይ በሰልፍ የተገጠገጡ ግዙፍ ስዕሎች ፣በየቦታው የተቀመጡ ቅርስ መሣይ ውድ እቃዎች፣ በሀውልት ቅርፅ የታነፁ የእንስሳትና የሰው ቅርፆች።ልክ ቱሪስት ሆነው በተጋበዙበት ሙዚዪም ዙሪያ ገባውን እየተዞዟሩ እየጎበኙ ያሉ ነው የሚመስለው።ሁኔታውን በመደመም ከሚመለከቱበት  "የተከበራችሁ ባልና ሚስቶቹ እንግዶቻችን በቀላሉ ወደማይገባበት...ከገብም ወደማይወጡበት የዘላለም ምድራዊ ቤታችሁ ወደሆነው ወደገንት እንኳን በሰላም መጣችሁ።"የሚል ጎርናና ድምፅ ከኃላቸው ሲሰሙ ነው ከተመስጦቸው ነቅተው ወደአሉበት ነባራዊ ሁኔታ እራሳቸውን የሠበሠብት።ሁለቱም በአንድነት ድምፅ ወደሰሙበት አቅጣጫ እኩል ፊታቸውን  አዙረው ተመለከቱ፡፡ ከፊታቸው ያለው ሰውዬ እስከአሁን አካባቢውን ከረገጡ ጀምሮ ካዬቸው ሰዎች የተሻለ የዋህ...ገራገርና ያለቦታው በስህተት የተገኘ የሚመስል ደግ ፊት ያለው ሰው ሆኖ አገኙት ይበልጥ አስገረማቸው።
"ዳግላስ እባላለሁ...ከሀገራችሁ ከኢትዬጰያ ወደእዚህ ያስመጣዎችሁ እኔ ነኝ..ይቅርታ ማለቴ አንተን ያስመጣሁህ እኔ ነኝ ..ባለቤትህ እንኳን በራሷ ፍቃድ የፍቅር ጉዳይ ሆኖባት ነው የመጣችው።"
"ገባን....እንዳልከው ቃልህን አምነን አህጉር አቋርጠን ውቅያኖስ ሰንጥቀን እዚህ ድረስ መጥተናል...አሁን ከእህታችን አገናኘን"ናኦል ነው ጠያቂው።
ዳግላስ ተንከትክቶ ሳቀ....እንደምንም ከሳቁ ወጣና ተጣራ....የተጠራው ልጅ እግር በእጅ አነስተኛ ቦርሳ አንጠልጥሎ እያለከለከ መጥቶ በፍራቻ አንገቱን በመድፍት ስሩ ቆመ "በል ምን ይገትርሀል...ብራስሌቱን አጥልቅላቸው። "ቆፍጣና ትዕዛዝ ሰጠው።

8,578

subscribers

15

photos

15

videos