በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም @matter_of_facts Channel on Telegram

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

@matter_of_facts


የ በውቀቱ ስዩምና አሌክስ አብርሃም አንድሁም ሌሎች አዝናኝና አስተማሪ ጽሁፎች ለማገኘት ከፈለጉ join አደርጉን

🙏እባካችሁ ለሌሎችም አጋሩልን🙏

@matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም ፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም (Amharic)

በውቀቱ ስዩም ፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም የተለያዩ አዝናኝና አስተማሪ ጽሁፎችን እና አጋሩልንን መዝገበታችሁን ይመልከቱ። እባካችሁ ለሌሎችም አጋሩልን! በስልክና በጉዞ ላይ ያሉ ሁሉን አስተማሪ ጽሁፎችን እንዴት ተመልከቱ፣ አጋሩልንን ለመላክ፣ እባካችሁ ከባለዘር አቀፍ ውስጥ በላይ እየተመለከተ ለመጫወት ይዘግቡ። ከዚህም በላይ በየቀኑ መረጃዎችን ይጠቀሙ። ይህንን ይጫኑ @matter_of_facts ተይዞ፣ ለእኛ ቅናትን ተላይተዩ።

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

18 Jan, 17:54


ለጥምቀት ያልሆነ ወግ...
(በእውቀቱ ስዩም)

ዓመት በአል በመጣ ቁጥር እልል ያልሁ አማኝ ነኝ፤ ጥምቀትንማ ከልደቴ በላይ ነው የማከብረው፤ ጎረምሳ ሳለሁ እኔና ይሁኔ በላይ አብረን ጥምቀት እንሄድና የጊዮርጊስን ታቦት እናጅባለን፤ ከዚያ የሎሚ ውርወራ ክፍለጊዜ ይቀጥላል ፤

ሎሚ ውርወራን የፈለሰፈው ኢትዮጵያዊ ደብተራ ግን ምንኛ ደንቅ ሰው ነው! ለምሳሌ የስፔን ሕዝብ በአል የሚያከብረው ቲማቲም በመወራወር ነው፤ አንድ ክፍለከተማ የሚመግብ ቲማቲም ሲወራወር ይውልና ፥ ሲመሽ ቀይ ወጥ ውስጥ የዋኘ ይመስል፥ ተጨመላልቆ ወደ ቤቱ ይገባል፤ እኔ ራሴ ባለፈው ዓመት ተሳትፍያለሁ፤ ቱሪስት ነው ብለው ሳይራሩልኝ፥ ያልታጠበ የድግስ ድስት አስመሰለው ለቀቁኝ ! በአልንስ አበሻ ያክብራት!

በጉብዝናየ ወራት፥ የጥምቀት ቀን ፥ ከይሁኔ በላይ ጋራ ሰንተራ ሜዳ ላይ እንሰማራለን፤ እኔ ከትርንጎ ጋራ የተዳቀለ ጠንካራ ሎሚ ታጥቄ ቆነጃጅቱን አማትራለሁ፤ ይሁኔ በላይ እንደኔ የሀብታም ልጅ ስላልበረ፥ ሎሚ afford ስለማያረግ እምቧይ ይወረውራል፤
ከዝያ “ ወርወሬ መታሁት ፥ ጥላሽን በእንቧይ”ብሎ ያንጎራጉራል፤

“ጥላዋን ከመታኸው እንደ ጥላ ስትከተልህ ትኖራለች “ የሚል ፈሊጥ ነበረው’

ሎሚ የምወረውርላቸው ሴቶች ባብዛኛው ይሽኮረመማሉ፤ ትዳር እንኳ ባይሆን ፈገግታ ይለግሱኛል፤ አንደኛዋ ግን ሎሚ ስወረውርላት “ አላማ አለኝ “ አለችና በእግሯ መልሳ ብትለጋው ግንባሬ ላይ ግልገል አናናስ የሚያህል እጢ በቀለ፤

ቅድም፥ ይህንን እያስታወስኩ፥ ሀያሁለት ማዞርያ ላይ፥ ቆሜ አላፊ አግዳሚውን እመለከታለሁ፤የለበስኩት ቲሸርት ከፊትለፊቱ የፋሲል ግንብ ተስሎበታል፤ ከሁዋላ ደግሞ የመጥምቁ ዮሀንስን ምሰል ይዟል፤

ዘናጭ ሴቶች በፊቴ እያለፉ ነው፤

ከሴቶች ጋራ ማውራት ያምረኛል ፤ ግን እንዴት እንደምጀምር ግራ ይገባኛል፤
አንዲቱ አጠገቤ ስትደርስ፥
“ ይቅርታ” ብየ ጀመርሁ፥

“ ምንም አይደል “ ብላኝ መንገድዋን ቀጠለች፤

ቀጣይዋ ከፊቴ ብቅ ስትል፥

“ እናት !” ስላት፥

“ አገር “ አለችኝ፥

ምን አይነቱን ከይሲ ትውልድ ነው ፈትቶ የለቀቀብን ብየ፥ ተስፋ ቆርጨ በማየት ብቻ ተወሰንኩ ፤ ሶስተኛይቱ ባጠገቤ ስታልፍ ዞር ብላ ፈገግ ያለችልኝ መሰለኝ ፤

“ እንኩዋን አደረሰሽ “ አልኳት፤

“ የጆቭሀ ምስክር ነኝ “

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

10 Jan, 04:11


ሎስአንጀለስን ሞቅናት!

(በእውቀቱ ስዩም)

ትናንትና ሎስአንጀለስ በእሳት ስትነድ፥ እኔ በአጋጣሚ ጓደኞቼን ለመሰናበት እዚያው ከተማ ውስጥ ነበርሁ፤ ሆሊውድ አካባቢ በእግሬ እየተንሸራሸርሁ ድንገት ቀና ብየ ሳይ፥ ከተማው እንደ ደመራ ይንቦገቦጋል፤ መጀመርያ ላይ ፥የዮዲት ጉዲትን ፊልም እየሰሩ ነበር የመሰለኝ፤ ብዙ ሳይቆይ የሳት አደጋ መኪና እየተብለጨለጨ ባጠገቤ አለፈ፤

ነገሩ “ሲርየስ” መሆኑን ያወቅሁት፥ የሆሊውድ አክተሮች ልጆቻቸውን እንኮኮ አዝለው፥ የቤት እቃቸውን ባንሶላ ጠቅልለው፥ ሲራወጡ ስመለከት ነው ፤ ደንብ አስከባሪ የሚያባርራቸውን የመገናኛ ቦንዳ ሻጮችን አስታወሱኝ፤ ቻክኖሪስ ባንድ የእሳት አደጋ ሰራተኛ ታዝሎ፥ ሳል እያጣደፈው ከቤቱ ሲወጣ አይቼ “እድሜ አተላ “ብየ ተከዝኩ::

እያወካ እየተጋፋ ከሚሸሸው ሰው መሀል ተቀላቅየ መሮጥ ጀመርሁ፤

ቀጣዩ ፌርማታ ላይ ትንፋሽ ለመሰብሰብ ቁጭ ባልሁበት፥ የሆነ ፖሊስ መጣና፤

“Are you ok?” አለኝ፤

“ እድሜ ልኬን ለፍቼ፥ እቁብ ጥየ ፥ ያፈራሁት ቤቴና ንብረቴ በእሳት ጋየ” ብየ መለስኩለት፤

“ስራህ ምንድነው ?”

መቸም በዚህ ሰአት ላይ ሊያጣራ አይችልም ብየ በማሰብ፥

“ ቀን የጣለኝ የሆሊውድ አክተር ነኝ “ አልሁት፤

“ምን ፊልም ላይ ሰርተሀል?”

”በማርቲን ሉተር ኪንግ የህይወት ታሪክ ዙርያ፥ በሚያጠነጥን ፊልም ውስጥ ከበድ ያለ ሚና ነበረኝ ” አልሁት፤

ፖሊሱ አልተፋታኝም፤

“ምን ሆነህ ነው የተወንከው?”

“ ማርቲን ሉተርኪንግ ፥ ሁለት መቶ ሺህ ህዝብ ሰብስቦ ንግግር የሚያደርግበት ትእይንት ትዝ ይለሀል?” አልኩት፤

“አዎ”

“ ከህዝቡ መሀል አንዱን ሆኜ ተውኛለሁ፤ ፊልሙ ጀምሮ አንድ ሰአት ከሶሰት ደቂቃ ከአምሳ ሁለት ሰከንድ ላይ ራሱን እሚነቀንቀው ሰውየ እኔ ነኝ “

ፖሊሱ ጥሩ ሰው ነው፤ ወስዶ ከተፈናቃዮች ጋራ ቀላቀለኝ፤ የከተማው ከንቲባ ዘለግ ያለ ንግግር አደረጉ ፤” የተወደዳችሁ ተፈናቃዮች ሆይ ! የከተማው አስተዳደር ቤታችሁን መልሶ እስኪገነባ ድረስ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ውስጥ ልናቆያችሁ እንገደዳለን ”ብለው ንግግራቸውን አሳረጉ

በመጨረሻ” የአደጋና ስጋት መስርያ ቤት” ሊቀመንበር ወደኔ ቀርቦ፥

“ የደረሰብህን ኪሳራ እስክናጣራ ፥ይቺን ነገር ላንዳንድ ነገር ትሁንህ “ አለና አምሳ ሺህ ዶላር የያዘች ትንሽ ብጫ ፌስታል አስጨበጠኝ፤

ብዙም ሳልቆይ፥ፌስቡኬ ላይ የሚከተለውን ማሳሰቢያ ጣል አረግሁ፤

Bewketu Seyoum marked himself safe from poverty .

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

07 Jan, 08:47


አገር -በቀል
(በእውቀቱ ስዩም)

ከአራት ቀናት በፊት የመሬት መንቀጥቀጥ አገሬን ሲጎበኛት እኔ ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ ሻንጣየን እየሸካከፍኩ ነበር፤ ድንገት የጨሰ የቢዘነስ ሀሳብ ብልጭ አለልኝ - የድንኩዋን ሪልስቴት መገንባት!

የምድር መፈራገጥ በዚህ ከቀጠለ አዲሳባና ተጎራባች ከተሞች ውስጥ ያሉ ነዋሪዎች ባለ ትልልቅ ፎቅ ህንጻዎች ላይ የመኖር ፍላጎታቸው ይቀንሳል፤ ሟርቴን አፌ ላይ እንደ ሰም ያቅልጠው እንጂ፥ በዚህ አያያዝ ፥ፎቆች መኖርያ መሆናቸው ቀርቶ መቀበርያ እንዳይሆኑ ያሰጋል፤ ስለዚህ ሰዎች፥ ቢደረመስ እንኳን ለክፉ በማይሰጥ የገለባ ጎጆ ውስጥ፥አለዝያም በድንኳን ውስጥ መኖርን መምረጣቸው አይቀርም፤

አባታችን አብርሀም ኣያሌ አመታት በድንኳን የኖረ ልዝብም ሆነ የከረረ ድሀ ስለነበረ አይደለም፤ በዘመኑ ኢለን መስክን የሚቦንስ ቱጃር ነበር፤ አብርሽ በዳስ ውስጥ የተጠለለው፥ ትልልቅ ህንጻ የመገንባት ጥበብ ስላልተገለጠለት አልነበረም፤ ለባቤል የተገለጠ ጥበብ ለአብርሀም እንዴት ይጋረድበታል? አብርሀም በድንኩዋን የኖረው ከምድሪቱ ባህርይ ስለገባው ነው፤

"አብርሀም ሪል ስቴት" የተባለ የድንኳን ሪልስቴት እገነባለሁ፤ ሕዝቤ ከከዋክብት ርቆ፥ ወደ ምድር ቀርቦ የሰላም እንቅልፍ ይተኛል! አለቀ!

ከጥቂት ቀናት በሁዋላ የእንቅጥቅጡ ጉልበት እየጨመረ ሄደ፤ የቢዝነስ ሀሳቤን ትቼ በሕይወት ስለመቆየት ማሰብ ጀመርኩ፤

ትናንት ከበየነ ጋር ዲሲ ውስጥ እየተራመድን ስጋቴን አዋየሁት፤

“ ወደ አገሬ ለመመለስ ዘጠኝ ቀን ቀርቶኛል ፤ መሬት እያሸበሸበች እንዳትቀበለኝ እፈራለሁ “

“ነገሩ እስኪለይለት እዚህ ለምን ትንሽ አትቆይም፤ ትኬቱን ለወር አራዝመው” አለኝ፤

“ ይሻላል?” አልሁት ፥በምክሩ ውስጥ ውስጡን እየተደሰትኩ፤

“አስብበት “

እያሰብኩበት ብዙ አልተራመድኩም፤ ከጫማየ ስር ያለው የበረዶ ጥፍጥፍ ሲያዳልጠኝ ትዝ ይለኛል፤ የሆኑ ሰዎች ባቅራቢየው ካለ ፎቅ የወረወሩኝ እንጂ አዳልጦኝ የወደቅሁ አልመሰለኝም፤ አየር ላይ ትንሽ ውየ መሬት ላይ ሳርፍ ባካባቢው የቆመው፥ የማርቲን ሉተር ሀውልት ተነቃነቀ፤

በየነ እንደ ቆሰለ አርበኛ አፋፍሶ ካነሳኝ በሁዋላ፥

“ተረፍክ?”

“መንጋጋየ ከመነቃነቁ በስተቀር ደህና ነኝ”

“ ከዚህ እድሜህ በሁዋላ መንጋጋ ምን ይሰራልሀል? እንዲህ አይነት አደጋ ገጥሟቸው በሕይወት የሚኖሩ ብዙ ሰዎች አይገኙም"

“ጎን አጥንቴ ላይ የስብራት ስሜት አለኝ” አልኩት እያቃሰትኩ፤

“ነጮች ሆስፒታል ብወስድህ፥ ሀኪሞች እግረመንገዳቸውን ሌላ በሽታ ሊያገኙብህ ይችላሉ፤ የማውቀው የቡርኪናፋሶ ወጌሻ አለ፤ እዚያ ልውሰድህ”

ወደ መኪናው አቅጣጫ እንደ ጀብ እያነከስኩ ትንሽ እንደተራመድሁ እንደገና ተንሸራተትሁ፤ በየነ እንደ በረኛ ቀለበኝና እንዲህ አለ፤

“ግዴለህም ወደ አገርህ በጊዜ ግባ! መሞትህ ካልቀረ አገር በቀል -ሞት ይሻልሀል”

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

03 Jan, 03:36


ከኛም ወዲያ ተኳሽ!
(አሌክስ አብርሃም)

አንድ ወዳጅ አለኝ... በየዓመቱ ጠመንጃ የሚገዛ! እውነቴንኮ ነው። ይሄ ወዳጀ ለፍቶ ግሮ ጥሮ ዶላሩ ጠርቀም ሲልለት ጠመንጃ ይገዛና እቤቱ ያውም ሳሎኑ ግድግዳ ላይ ባሰራው መደርደሪያ ላይ ይሰቅለዋል። ሰርቶ ለጠመንጃ! እንዲህ ያለ ሱስ ሰምቸ አላውቅም! የሰው አመሉ ብዛቱ እናንተ! ወደሰባት ጠመንጃ አራት የሚሆኑ ሽጉጦች ብዙ አይነት ጥይቶች የተደረደሩበት ባለመስተዋት መደርደሪያው ልክ የአገር ቤቱን የቁም ቡፌ ይመስላል። የግል ምሽግ!

ሚስት አላገባ ፣አልወለደ ፣ቤት አልሰራ፣ አይጠጣ ብሩን ለአልባሌ ነገር አያጠፋ በቃ Ak ck Jk እያለ ጠመንጃወቹን እንደልጅ በስስት ሲያያቸው ሲወለውላቸው ግራ ይገባኛል። ሆቢው ነው። በፈረንጆቹ የተለመደ ነገር ነው አሉ። እንግዲህ በየአመቱ ከከፈላችሁት የስራ ግብር መንግስት እንደቸርነቱ መጠን ቆንጥሮ ይመልስላችኋል። ለነገሩ አሰራር አለው። ሁልጊዜ በሚቀጥለው "ታክስ ሪተርን" ሊገዛ ስላሰበው ጠመንጃ በጉጉት እንዳወራልኝ ነው።

ታዲያ ባለፈው አዲስ ጠመንጃ ገዝቶ የፍንጥር ሊጋብዘን ቤቱ የወሰደን ጊዜ " ለመሆኑ መሳሪያወቹን ትተኩስባቸዋለህ?" አልኩት። ነገሩ ገርሞኝ! አልመለሰልኝም ይልቅ "በቀጣዮ ቅዳሜ ቀጠሮ እንዳትይዝ የሆነ ቦታ እንሄዳለን" አለኝ። ከከተማ ወጣ ብሎ በሰፊው የታጠረ ኮረብታ ነገር ነበር! ምድረ ፈረንጅ ክተት የተባለ ይመስል ጠመንጃውን ባጭር ታጥቆ ቡናውን በፍንጃል በርገሩን በፕላስቲክ አገልግል ቋጥሮ ተሰልፏል። አንድ ሻለቃ ፈረንጅ! ዶላር ሊተኩስ! በአንድ የተኩስ ልምምድ ያውም በሰዓት የሚከፍሉት ለደሀ ክረምት ያወጣል።

ጓደኛየም ጠመንጃውን እና አንድ እሽግ ካርቶን ጥይት ይዞ ወደሰልፉ ተቀላቀልን። መውዚር አማረኝ ያለ አሜሪካዊ እንግዲህ እዚህ መግቢያውን ከፍሎ አልያም የአባልነት ክፍያ ካለው ስሙን ነግሮ እስኪወጣለት ሲያኖጋው ይውላል። ከካርቶን የተሰሩ የሰው ምስሎች በተለያየ ርቀት ለኢላማ ተቀምጠዋል፣ አንዱ ተበሳስቶ ሲወድቅ ሌላ ከመሬት ተመዞ ይቆማል። (የካርቶን ትውልድ እላለሁ በውስጤ) የጆሮ መከለያ በገፍ አለ። ጓደኛየ ተራው ሲደርስ እንደሄድፎን የሚጠለቅ ነገር ለእኔ ሰጠኝና እያነጣጠረ ይለው ጀመር! እውነቱን ለመናገር ጎበዝ ተኳሽ ነበር። በጣም ሩቅ ያለ የካርቶን ኢላማ ልብ ልቡን እያለ ሲገነጣጥለው ነጮቹ በአድናቆት ያጨበጭቡለት ነበር።

"በል ያዝ" አለና ጠመንጃውን ደረቴ ላይ ቢለጥፈው እንደልጅ አቀፍኩት። አቤት አከባበዱ.... ይሄን ጉድ ነው እንደዛ አንጠልጥለው በሜዳ ተራራው የሚሮጡት? ራንቦ ይሄን ነው ባንዴ ሁለት ዮዞ ሆሊውድ ተኮስኩ ያለን? ደነቀኝ። የሰው ልጅ ፅናት! ያለዛን ቀን ጠመንጃ ነክቸም አላውቅ። ከአያያዝ እስካተኳኮስ ዘለግ ያለ ማብራሪያ ተሰጠኝና በል እንግዲህ ሜዳውም ፈረሱም ያው አለ ጓደኛየ ... እንደፎንቴን ውሃ ደሜ ወደአናቴ ሲረጭ ተሰማኝ። "ከእያንዳንዱ መከረኛ አፍሪካዊ ኋላ አንድ ጠመንጃ አለ" የሚል ጥቅስ እዛው ፈጠርኩ። ወደኢላማው ደረት ዓለምኩ...አነጣጠርኩ ...ትንፋሸን ዋጥኩ .....ቃታውን ባለ በሌለ ሀይሌ ሳብኩት 🚨🚀💣💱 የብዙ ነገር ድምፅና ምስል ነው የተሰማኝና የታየኝ።

መጀመሪያ የመሰለኝ ግን ሌላ ሰው ታንክ ተኩሶ ትከሻየን ያወላለቀው ነበር። አህያ ራሱ እንደዛ አይራገጥም! ሰደፉ የቀኝ ትከሻየን የረገጠኝ አረጋገጥ ሳልወድ እስክስታ ነው ያስወረደኝ። የሆነ አለምየ ሶራ! በረድ ሲልልኝ ጠመንጃው እጀ ላይ የለም ጓደኛየ ወስዶታል ....የጆሮ መከላካያውይ ዝቅ ሳደርግ "አንተ ወታደር ነበርክ እንዴ ? " አለኝ ወደኢላማው በአድናቆት እየጠቆመኝ! በግርምት ዞር ብየ ኢላማውን አየሁ፣ መሬው ተኳሹ መራዡ! ያንን የካርቶን ሰውየ አፍንጫው ላይ ቦድሸዋለሁ ... ህ! ድሮም እጀ ላይ ጠላት አይበረክትልኝም😎

ጠመንጃ መንፈስ ነው ነው ወገኖቸ! አሁን ይሄው አንዲት ቀለል ያለች ምንሽር ብሸምትና ሲደብረኝ ሄደት እያልኩ ያንን ካርቶን አሳሩን ባበላው... እያልኩ ማሰብ ከጀመርኩ ሰነበትኩ😀


https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

26 Dec, 14:59


ቁማችሁ የምትቀሩት ቁጭ ስለማትሉ ነው¡¡
(አሌክስ አብርሃም)

ሴቶች በተደጋጋሚ ግልፅ ወንድ እንወዳለን ትላላችሁ፤ አይመስለኝም እህቶቸ። ምንድነው ግን ችግራችሁ? እንደው አሁን ማን ይሙት ከጓደኛየ ብሩክ የበለጠ ጥሩ፣ ግልፅ ልጅ እዚህ ፌስቡክ ላይ ይቅርና በድፍን ኢትዮጵያ ይገኛል? መልሱልኛ ምን ትቅለሰለሳላችሁ?!

ግን ባለፈው ሳምንት የለጠፈውን ትሁትና ግልፅነት የተሞላው መልዕክቱን ብዙወቻችሁ እንዳላየ አልፋችሁታል። አትረጋጉማ! ቁጭ ብላችሁ አታነቡማ! ስልካችሁ ላይ ጭምር በጣታችሁ እየሮጣችሁ በየት በኩል ቁም ነገር ይድረሳችሁ? ጣታችሁን ላየውኮ በቆሎ የምትፈለፍሉ ነው የምትመስሉት...ስክሮላም ትውልድ¡ (በዚህ አያያዛችሁ እስከምፅዓት ቁማችሁ ብትቀሩ ይገርማል? ሩጣችሁ ሩጣችሁ ትንፋሽ ሲያጥራችሁ አንዱ ክንድ ላይ ተዝለፍልፋችሁ ትወድቃላችሁ፣ የመጀመሪያ እርዳታ ምናምን ብሎ ለራሱም የሌለውን አየር ልስጣችሁ ይልና ከንፈሩን ያሞጠሙጣል ... የፍቅር ኪስ ምናምን ትላላችሁ! ለበለጠ የህክምና እርዳታ "ተኝቶ መታከም" ይባላል...ኧረ ወዲያ እናንተን በመምከር ሸበትኩ) እና ጓደኛየ ብሩክ ምን ነበር መልዕክቱ ?

"ስሜ ብሩክ ፍስሀ እባላለሁ፣ ዕድሜየ 35 ሲሆን በሙያየ ሀኪም ነኝ። ትዳር መመስረት እፈልጋለሁ። ፎቶየ ከታች የምትመለከቱት ሲሆን ምንም አይነት ሱስ የለብኝም። የእውነት ለትዳር ዓላማ ያላት ፣ዕድሜዋ ከ25 -30 የሆነች፣ቢያንስ እስከ12ኛ ከፍልና ከዚያ በላይ የተማረች ሴት በውስጥ ብትፅፍልኝ ለመነጋገር ዝግጁ መሆኔን በትህትና አሳውቃለሁ" ይላል።

በሳምንቱ የኮሜንት ቦክሱ ተጨናንቆ እንደሚያገኘው በመገመት በማንበብና በመምረጥ እንድረዳው ቤቴ መጣ። እጁ እየተንቀጠቀጠ ከፈተው። ያሳዝናል ወገኖቸ። ሁለት ሰወች ብቻ ነበሩ የፃፉለት። 28.63 ሚሊየን ያላገቡ ሴቶች ባሉባት አገር ሁለት! የመጀመሪያዋ ሴት የፕሮፋይል ፒክቸሯ ላይ እንደምትታየው ጠይም እና ውብ ልጅ ነች "ሰላም ብሩክ። ሳራ እባላለሁ የ29 ዓመት ወጣት ስሆን ባለፈው ዓመት በሲቪል ምህንድስና በጥሩ ውጤት ተመርቂያለሁ። መልእክትህን ሳይ በግልፅነትህ ልቤ ተነክቷል። በአሁኑ ሰዓት ሳሪ ላቭ የተባለ የወላጆቻቸውን ፍቅር በቲክቶክ ሱስ የተነጠቁ ህፃናትን አሰባስቦ ፍቅር የሚሰጥ የበጎ አድራጎት ድርጅት መስርቸ በመንቀሳቀስ ላይ ነኝ። ይህንን መልዕክት የፃፍኩልህ የፈለካትን ሴት ካገኘህ በኋላ በሰርግ የምታገባ ከሆነ ከሰርግ ወጭህ ላይ በመቀነስ የተወሰነውን ለድርጅታችን በጎ አላማ እንድትለግስ ለመጠየቅ ነው " ይላል።

ሁለተኛውን መልእክት ከፈተው ... "ወንድሜ ብሩክ የጌታ ሰላም ይብዛልህ ....ትዳር መፈለግህ የተቀደሰ ሐሳብ ነው ግን ከማግባትህ በፊት እነዚህን አስር ነጥቦች ታስተውላቸው ዘንድ በጌታ ፍቅር ልኬልሀለሁ ....

1. ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም ባይሆንም መልካም ሚስት ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ናት ....
2. ልባምን ሴት ማን ያገኛታል ...
3... .....
10. በሚመችህ ሰዓት ቢሮየ ብቅ ብለህ ስለዚህ መልካምና የተወደደ ህብረት ብንነጋገር ...

ወንድምህ ፓስተር ቸሬ!

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

14 Dec, 13:44


ወገኖቸ ቅዳሜም ትሰራላችሁ እንዴ?
(አሌክስ አብርሃም)

ይሁን ግዴለም! ብቻ ይችን ነገር ስሙ! አሜሪካዊው ሰውየና ሚስቱ እሳት ለብሰው እሳት ጎርሰው ፍርድ ቤት ሄዱና ከአፍሪካ መጥቶ ከጎናቸው የሚኖር ጎረቤታቸውን ከሰሱ! በቃ ችሎት ገተሩት! ምን አገናኛቸው? በዶሮ ነው? በልጅ ነው? በሚስት ወይንስ በድንበር? በሁሉም አይደለም ! ነገሩ በጣም ወዲህ ነው። እንደውም እኛን ጭቁኖችን ሳይመለከተን አይቀርም!

ከሳሽ ባል የ65 ዓመት ሰው ሲሆን ሚስቱም እዛው ዕድሜ ክልል አካባቢ ናት። በቂ ገንዘብ ስላልቆጠቡ ጡረታቸውን አራዝመው ትንሽ ለመስራት ያሰቡ፣ ግረው ጥረው የሚያድሩ ፈረንጆች ናቸው። እድሜ ልካቸውን ሰርተው ይሄን የሚኖሩበትን ቆንጆ ቤት ገዝተዋል፤ እዳውን በሰላሳ ዓመት ገና ሰሞኑን ከፍለው መጨረሳቸው ነው። ሁለት ልጆቻቸውን እንዲሁ በስንት ዓመት ብድር አስተምረው ራሳቸውን ችለው ሄደውላቸዋል። አርባ አመት ሙሉ ረዢም ረፍት ምን እንደሆነ አያውቁም፤ ወፍ ሲንጫጫ ወጥተው ጅብ ሲንጫጫ የሚመለሱ ላብ አደር ታታሪወች። ስራ ስራ ስራ ነው! አሁን ደግሞ መጦሪያ ለማጠራቀም ይሰራሉ። በአሜሪካ የተለመደ ስለሆነ ምንም ቅር ብሏቸው አያውቁም።

እንግዲህ ከአንድ አመት በፊት አንድ ናይጀሪያዊ ሰባት ልጆቹና ሚስቱ ጋር ሆኖ ከጎናቸው ያለውን ባለመዋኛ ገንዳ ቅንጡ የተንጣለለ ቪላ ገዝቶ ገባ። መልካም ጎረቤት ናቸውና አዲስ ገቢወቹን እንኳን ደስ ያላችሁ ሊሏቸው ሲሄዱ በጨዋታ መሀል ቤቱን በካሽ ከፍለው መግዛታቸውን ሰሙ። ብዙወች ቢያደርጉትም አሜሪካ በጣም ሀብታም ካልሆኑ እንዲህ ያለው ግዢ የተለመደ አይደለም። "What do you do for a living?" ቢሉ ናይጀሪያ ውስጥ ትንሽ የመንግስት ስልጣን የነበረው ሰው መሆኑንና መንግስት ጋር ባለመስማማቱ ከነቤተሰቡ አገሩን ትቶ መምጣቱን በትካዜ ነገራቸው። አዘኑ።

እያደር ግን የዚህ ናይጀሪያዊ ቤተሰብ አኗኗር ባልና ሚስትን ለከባድ ድብርት ዳረጋቸው። በእርግጥ ምንም የደረሰባቸው ነገር የለም፣ ስርዓት ያለው ጨዋ ቤተሰብ ነው። ግ...ን መዋኘት ነው...ጥግብ እስኪሉ መተኛት ነው...ደግሰው ወዳጅ ዘመዶቻቸው ጋር ዘና ማለት ነው...ውድ መኪና ፣ ልብስ መቀያየር ነው፣ ደስታ ነው። በቃ ድፍን ቤተሰቡ እንዲች ብሎ ስራ አይሰራ አይማር... እነዛ ሚስኪን ባልና ሚስቶች ምናምን የተቀባች ዳቦና ቡናቸውን ይዘው ጧት ሱክ ሱክ እያሉ ወደስራ ሲሄዱ የአጅሬው ቤተሰብ በጧት እነደፀሐይ ወጥቶ በረንዳው ላይ ቡናና ጠረጴዛ ሙሉ ምግብ አቅርቦ ቁርስ ደግሶ ቀኑን በከባዱ ሲጀምር ያያሉ...ማታ በስራ ጨርቅ ሁነው ሲገቡ... ጎረቤት ዋይኑ ተደርድሮ ግሪል ጥብሱ እየጠረነ ሙዚቃው በስሱ ተከፍቶ ሳቁ ጨዋታው ደርቶ ያገኙታል ... ቅዳሜና እሁድማ ሰርግ ነው። ባልና ሚስት የመስኮት መጋረጃቸውን ገለጥ ያደርጉና ተቃቅፈው መጎምጀት ሆነ ስራቸው።እና መረራቸው! ከባድ የስነልቦና ጥቃትና ዋጋ ቢስነት እንዲሰማን ከመሆናችንም በላይ የስራ ሞራላችን ሙቷል ...በየቀኑ በምናየው ቅንጡ ኑሮና ያላሰለሰ ረፍት፣ ቀኑ ሁሉ እሁድ እየመሰለን ነው...በቃ እሁድ ስራ የገባን እየመሰለን ነው አሉ። ከሰኞ እስከአርባችንን እሁድ አድርገውብናል!

የአሜሪካ መንግስት ህግ ላይ ቀልድ አያውቅም፣ ነገሩን በከፍተኛ ጥሞና ሰምቶ ሲያበቃ ምናላቸው ?
አይዟችሁ ቻሉት! 😀ኤዲያ አሜሪካ ምን ህግ አለ! እና ቅዳሜ በቁርጥ ቤት በር ስታልፉ ምናምን በምታዮት ሁሉ አይዞን! ከሰኞ እስከአርባችሁን እሁድ ጋር ያምታቱባችሁ ጎረቤቶች የፌስቡክ ሰለብሪቲወች ወዘተወች ቢኖሩ ....በቃ አይዞን!

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

13 Dec, 07:24


መኖር መኖር አሁንም መኖር!
(አሌክስ አብርሃም)

ወደካናዳ ወይም አሜሪካ ለመሰደድ ሚሊየኖች ይመኛሉ፤ ደፈር ያሉት ደግሞ በተለያየ መንገድ ይሞክራሉ። በህጋዊ መንገድ አልያም በህገወጥ። ባህር ጫካ በረሃ በማቋረጥ ለመኖር ኑሯቸውን በትነው፣ የተሻለ ህይወት ለማግኘት ህይወታቸውን አስይዘው በየሰዓቱ ሰወች ከመላው አለም ይፈልሳሉ።

ይሄውላችሁ እንግዲህ ካናዳ በተለያዮ የማይድኑ ህመሞች የተያዙና በፈቃዳቸው ህይወት በቃኝ ላሉ ሰወች በሰው ሰራሽ መንገድ እንዲሸኙ ከፈቀደች ሰነባበተች። (MAID) ይሉታል ስሙን ሲያሳምሩት። በዘመናዊ ህክምና እርዳታ መሞት ማለት ነው። ታዲያ ባለፈው ዓመት ብቻ ስንት ሰው በፈቃዱ እንደተገደለ ስሰማ ገረመኝም አዘንኩም፣ ከአስራ አምስት ሽ እስከ አስራ ሰባት ሸ ሰው!! ለዛውም ከቀረቡት ከሰላሳ ሽ በላይ የእንሙት ጥያቄወች "ለመሞት መስፈርቱን ያሟሉት" ናቸው። ከአስር በላይ አገራት ይህን ህግ ፈርመዋል፤ በየአገራቱም በርካታ ሽ ሰው በየቀኑ ይገደላል። አስገራሚው ነገር ይሄ አይደለም ...ለምን በማይድን በሽታ ለተያዙ ብቻ ይፈቀዳል? እኛስ ግብር ከፋይ ዜጎች አይደለንም ወይ "መሄድ ይሻለናል" ካልን ለምን በዘመናዊ መንገድ እንድንሄድ አይፈቀድልንም የሚሉ ዜጎች መበራከታቸው ነው። ወጣቶች ጭምር!

ወገኖቸ ኑሮ ወጣ ውረዱ ብዙ ነው...ተስፋ እንደእንቁላል ከእጅ ካመለጠ መመለሻው ችግር ነው። ተስፋችሁን ብቻ አጥብቃችሁ ያዙ! ችግር ተስፋ እንዳላስቆረጠን ሁሉ ሀብትም ተስፋ ቀጣይ አልሆን ብሏቸው እንዲህ ጣጥለው በፈቃዳቸው የሚሄዱ "የሐብታም" አገር ዜጎች ነገር ዓለምን እያስጨነቀ ነው። ለመሆኑ ሞታችሁን ሌሎች እንዴት ያዮታል? እንደቻይና! ቻይና ይሄን የሟች ቁጥር ስትመለከተው መሞታቸው ካልቀረ ለምን አልሸቅልበትም ያለች ትመስላለች ...ጃፖን በአንድ ደይቃ ካለስቃይ የሚገድል ማሽን ሰርታ ማስተዋወቋን ተከትሎ ...አንድ ደይቃ ሙሉ ስቃይማ ሰብዓዊነት አይደለም በ20 ሰከንድ ፀጥ የሚያደርግ ማሽን በሙከራ ላይ ነው ብላለች ተብሏል።

እኛ ግን በሰበብ አስባቡ ያልተመዘገበ ሞታችን ቁጥሩ የትየለሌ ቢሆንም ጀሊሉ በቃ እስኪለን መኖር መኖር አሁንም መኖር እንዳይሰለቸን!! አለመኖራችን ራሱ ኑሯችን ውስጥ እንጨው ተዋህዶ ጣዕም ሆኖ የለ?! እየኖርንም እያልኖርንም ነው ቢሆንም....

ከመኖር ብዙዙዙዙዙዙዙ አለ
ካለመኖር ምንም!! ብሏል ባለቅኔው።

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

01 Dec, 18:16


ሹፌሬ ፥ ሺህ አይፈሬ
(በእውቀቱ ስዩም)

ኢትዮጵያ ውስጥ በቅጡ ያልተጨበጨበላቸው ጀግኖች ሹፌሮች ናቸው፤ በሆነ ባልሆነው እየተዋከበ፥ በውሀ ቀጠነ እየተቀጣ አገልግሎት የሚሰጠውን የከተማ ሹፌር እናቆየው ፤ በዚህ ዘመን የክፍለሀገር አቆራራጭ ሹፌርን የሚያክል ጀግና ያለ አይመስለኝም፤ ልጅ ሆነን በሬድዮ፥

“ጠመዝማዛ መንገድ ኮረብታ
ሽቅብ ቁልቁለት
በረሀ አቁዋራጭ ጋላቢ ዳገት “

የሚል ዘፈን እናዳምጥ ነበር፤ ይህ ዘፈን በተዘፈንበት ዘመን፤ የሹፌሮች ዋናው ችግር ያገራችን መልክአምድር ነበር፤ አልፎ አልፎ መንገድ ላይ አድብቶ የሚዘርፍ ሽፍታ ይኖራል፤ ግን የዚህን ዘመን አይነት መፈጠርን የሚያስጠላ የጎዳና ውንብድና ታይቶ የሚታወቅ አይመስለኝም፤ በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ፥ የቤተሰባቸውን ሞሰብ እንጀራ ለማልበስ ከመኪና መሪ ጀርባ ለመቀመጥ የማያመነቱ ሹፌሮች ታሪክ ውለታቸውን ይክፈላቸው!

ምስጋናየ በደረቅ እንዳይሆን ፥ የቺን የቆየች፥ ሹፌር -ቀመስ ገጠመኝ ላካፍል፤

ከእለታት አንድ ቀን ሾፌሩና አውታንቲው(ረዳቱ) ሲገሰግሱ ሽፍታ አስቆማቸው ፤ “ ያላችሁን አካፍሉኝና ቀጥሉ” የሚል ወፍራም ትእዛዝ አስተላለፈላቸው፤ ሹፌሩ “ ባሻ! ደመወዛችንን ለመቀበል ሳምንት ይቀረናል ፤ ለዛሬ አስተምረህ ልቀቀን “ አለው፤ የዚያን ዘመን ሽፍታ የደም ጥማት አልነበረበትም፤ " እሺ ቀልድ ንገሩኝና እለፉ” አላቸው፤

አውታንቲው ወደ ሽፌሩ እየጠቆመ” እሱ ቀልድ የማይችል ለዛው ሙጥጥ ፍጡር ነው፤ እኔ በደናው ቀን ስቀልድ፥ እንኳን ሰው የቆመ ሀውልት በሳቅ እጥላለሁ፤ አሁን ግን እንኳን ቀልድ የገዛ ስሜ ጠፍቶብኛል! ለዛሬ ማረንና በሚቀጥለው ክበበው ገዳን ጭነነው እንመጣለን “ ብሎ ተለማመጠው፤

ሽፍታው ይሄንን ሰምቶ፥ ጋቢናው ከፈት አርጎ ሲያይ የሆነ ቋጠሮ ተመለከተ፤

“ፌስታሉ ውስጥ ያለው ምንድነው ?”

“ ቃርያ ነው”

ሽፍታው ቃርያውን ሲቆጥረው አርባ ፍሬ ሆነ፤

“በሉ እኩል ተካፈሉና ብሉት”

ሽፍታው ሁለቱ ምርኮኞቹ ሀያ ሀያ ቃርያ ተካፍሉው ሲበሉ እያየ፥ ራሱ በፈጠረው ሆረር ፊልም ከተዝናና በሁዋላ አሰናበታቸው፤ ሹፌረና ረዳቱ ከንፈራቸው ተቃጥሎ፥ ፊታቸው ያልተሟሸ ምጣድ መስሎ፥ እንባ የተቀላቀለ ንፍጥ እያዘነቡ ሲገሰግሱ መንገድ ዳር ያለ አንድ ምግብ ቤት ደረሱ፤

እንደገገቡ “እማማ፤ ሁለት እርጎና አንድ ሽሮ ፍትፍት “ብለው ጮሁ፤

የምግቤ ቤቱ ባለቤት አስተናጋጂነትንም ደርበው ይሰራሉ፤ የታዘዘውን በፍጥነት አመጡላቸው፤ ሁለቱ ነድቶ -አደሮች የሽሮ ፍትፍቱን አፈስ አፈስ አርገው የነደደ ምላሳቸውን ትንሽ እንዳበረዱ ሴትዮይቱ፥

“ ብሉ እንጂ! ማባያ ቃርያ ላምጣላችሁ እንዴ ?” ከማለታቸው፥

ሁለቱ ሹፌሮች ሞሰቡን ገብልብጠው፥ የበሩ ጠርዝ እሲገጫቸው ድረስ እየተደናበሩ ከወጡ በሁዋላ ቀነኒሳ በሚቀናበት ፍጥነት መንገዱን ፈጩት፤

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

20 Nov, 13:55


https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

17 Nov, 09:12


የተወጋ ትዳር!
(አሌክስ አብርሃም)

በነገራችን ላይ ቆንጆ ሴት ስላገቡ ቆንጆ ልጆች መውለድ እንደሚችሉ የሚያስቡ ወንዶች አሉ። ስለዚህ ለትዳር ቆንጆ ሴት ያሳድዳሉ። በሰው ምርጫ መግባት አልፈልግም። ግን የአንድ ጓደኛየን ተሞክሮ ማካፈል እፈልጋለሁ። ለነገሩ የሱም ተሞክሮ ለህይወታችን ምንም አይጨምርም እንተወው። ዋናው ነገር ግን ልጆች ሲወለዱ ሜካፕ፣ሂውማን ሄር ፣የተወጋ ከንፈር፣ በሰርጀሪም ይሁን በኤክሰርሳይስ የተስተካከለ የሰውነት ቅርፅና የተጠና አማላይነት ከእናታቸው አይወርሱም። በኋላ የኔ አይደሉም እንዳትሉ!

በዘር የሚተላለፉ የጤና ችግሮች፣ ደከም ያለ አዕምሮ፣ ባህሪ ወዘተ ግን ሊወርሱ ይችላሉ። እና ስትጋቡ ከፍቅር አልፋችሁ "ስለምርጥ ዘር" እስከማሰብ የደረሰ የከብት እርባታ መንፈስ ካደረባችሁ ቢያንስ ለትውልዱ ስትሉ ጤናና ባህሪ ላይ ላይ አተኩሩ።

ሴቶችም እንደዛው "ከሚያምር ረዢም ወንድ የሚያምር ልጅ " የሚል መፎክር ውስጣችሁ ካደረ ፣ የምትመርጡት ለምርጥ ዘር የሚሆን ኮርማ እንጅ ባል አይደለም። መለሎው ኮርማ የቅድም አያቱን ስንዝሮ ቁመትና መጋፊያ እግር ለልጃችሁ ሊያወርስ ይችላል። ሆስፒታል አቀያይረውብኝ መሆን አለበት እስክትሉ የጀነቲክስ አልጎሪዝም እብድ ነው። የሆነ ሁኖ መሠረቱ ከተወጋ ትዳር ቆንጆ የምትሉትም ይወለድ መልከ ጥፉ ዋጋው ውድ ነው። ከምታፈቅሯቸው ውለዱ ፣ ከፍቅር የተወለዱ መልአክ ናቸው። ልጆች ምንጊዜም ውብ ናቸው። አስቀያሚ የሚያደርጓቸው አስቀያሚ ሒሳብ የሚሰሩ ወላጆች ፣ የእነዚህ ወላጆች ስብስብ የፈጠረው ማህበረሰብ ነው። የተወጋ ትዳር የተወጋ ማህበረሰብ ይፈጥራል።

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

16 Nov, 18:15


ሰሞንኛ
(በእውቀቱ ስዩም)

በአብማይቱ እምላለሁ፥ ማይክ ታይሰን ቢያሸንፍ ኖሮ ትንሽ ቅር ይለኝ ነበር፤ የአምሳ ስምንት አመት ሰውየ የሀያ ስምንት አመት ጎረምሳ ፕሮፌሽናል ቦክሰኛ ባፍጢሙ ደፋው ፥ ቢባል የሰውየው የፍጽምና ማሳያ ይሆን ነበር፤ ፍጹምና እንከን አልባ የሆነን ሰው ደግሞ አርአያ ማድረግ ያደክማል፤

ከትልልቅ ሰዎች የምጠብቀው ልከተለው የምችለው አይነት አርአያነት ነው፤ ለካ በአምሳ ስምንት አመቴ ፥ጡንቻ መገንባት እችላለሁ፥ ስምንት ዙር ሪንግ ውስጥ የሚያስቆይ ትንፋሽ ማካበት እችላለሁ፤ ለካ በዚያ እድሜ የልጆቼን እጅ ሳልጠብቅ በጥረቴ እንጀራ መብላት እችላለሁ ፥ ብለህ እንድታስብ የሚያደርግ አንጋፋ ጀግና ሲገጥምህ ልብህ በተስፋ ይሞላል፤ ማይክ ታይሰን ምን ፈየደልህ ብትይኝ መልሴ ይሄ ነው፤ አምሳ አመትን ከዘራ በማማረጥ እንዳልጠብቀው አድርጎኛል፤ ከዚህ በላይ አነቃቂ የለም!

“ምንም ደሀ ቢሆን ባይኖረውም ሀብት
ከደጃፍ ሲቀመጥ ደስ ይላል አባት “

የሚል ጥቅስ እየተመሰጥን ነው ያደግን፤ አብዛኛው ሰው ወጣትነትን ሲሻገር የአካል እንቅስቃሴ እንዲያቆም ውጫዊና ውስጣዊ ግፊት ያድርበታል፤ ውጫዊው “ ካልጠገቡ አይዘሉ፤ ካልዘለሉ አይሰበሩ “ እያለ ይለጉምሀል፤ ውስጣዊው ደግሞ አሁን ከዚህ “በሁዋላ ቀንድ አላበቅል” እያልህ የሰውነትህን እምቅ አቅም ሳትረዳ እንድትሞት ያደርግሀል፤

ታይሰን ሀያ ሚሊዮን ዶላር ይሸለማል ተብሏል፤ ቀላል ጥሪት አይደለም፤ አያትየው የልጅ ልጆቹን መጦር ይችላል፤ ባንድ ሚሊዮን ብሩ የተጠረመሱ ፥ የመንገጭላው አጥንቶቹን ያስጠግንበታል፤ የተዳጠ አፍንጫውን ያስበይድበታል፤ በቀረው ደግሞ አለሙን እንደ ጥንቅሽ ይቀጭበታል፤ ምናልባት ሳይንቲስቶች በጥቂት አመታት ጊዜ ውስጥ የእድሜ ማደሻ ቅመም መፍጠር ከቻሉ ደግሞ የመሸመት አቅሙን አዳብሯል፤

ይህ በእንዲህ እንዳለ፥ ደጃፍ ላይ የሚያስቀምጠውን መንፈስ በካልቾ ብላችሁ በነገው ታላቁ ሩጫ ላይ ተሳተፉ፤

ልዝብ ደሀ ቢሆን ባይኖረውም ሀብት
ታላቅ ሩጫ ላይ፥
ወልመጥ ወልመጥ ሲል። ደስ ይላል አባት🙂

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

15 Nov, 07:27


Anyone from Ethiopia can order a mastercard from bybit

https://www.bybit.com/fiat/cards?source=referral&campaignId=1686258086857150464&ref=4RRGJLB

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

13 Nov, 16:21


በመኖር አጸድ ውስጥ
(በእውቀቱ ስዩም)

ጊዜ ከሰው መሀል- መርጦ ሲያቀማጥል
ማጣት አለ ደሞ፥
የወለዱትን ልጅ፥ ጉድፍ ላይ የሚያስጥል
በተፈሰከ ቀን፥ ጾምን የሚያስቀጥል::

እድልና ትግል በሚጫወቱበት
በደልዳላው ስፍራ
አለቃና ጭፍራ-
-ቃል ሲለዋወጡ፥ ውልና መሀላ
“አብረን እናድጋለን” ቢባል ለይስሙላ
ወንዙን ሳያጎድል ፥ሐይቁ መች ሊሞላ፤

ጸሐይ ብትወጣ
ፍጥረት በጠቅላላው ጸጋዋን ቢቀበል
የደመናም ጠበል፥
ለሁሉ ቢደርስም
አንደኛው አያድግም፥ አንዱን ሳያከስም::

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

13 Nov, 05:03


(ተስፋዬ ሃይለማርያም)

ባሻዬ! አንዱ ካድሬ ሹመት ተሰጠውና ወደ አንዱ መሥሪያ ቤት በኃላፊነት ተመድቦ ሄደ። ሰውዬው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጓደኛ ለመምሰል ብዙ ይሞክራል።

አንድ ቀን ቢሮው ውስጥ ቁጭ ብሎ ሳለ የቢሮው በር ተንኳኳ። ሰውዬው ወዲያውኑ አጠገቡ ያለውን የቢሮ ስልክ አንስቶ ማውራት ጀመረ። በሩን ከፍቶ የገባው ሠራተኛ ኃላፊው ስልክ ላይ መሆኑን አይቶ ሊመለስ ሲል ሃላፊው እንዲገባ በእጁ ምልክት አሳየውና እንዲህ እያለ በስልኩ ወሬውን ቀጠለ፣

"አመሠግናለሁ ዶክተር አብይ... አዎ ልክ ነዎት ጌታዬ.... አዎ አውቃለሁ... ይህንን ኃላፊነት ሲሰጡኝ በእኔ ላይ ትልቅ እምነት አሳድረው ነው....ኧረ በፍፁም አላሳፍሮትም... አዎ ኦቦ ሽመልስ ደውሎልኝ ነበር...አዎ ወይዘሮ አዳነችም ነግረውኛል...ምንም ችግር የለም... እሺ አመሠግናለሁ ጌታዬ... እሺ እላለሁ... ለእኔም ወይዘሮ ዝናሽን ሰላም ይበሉልኝ...አመሠግናለሁ ጌታዬ ...ቻው"

ኃላፊው ይህንን ተናግሮ ስልኩን ዘጋና ቢሮ ውስጥ ቆሞ ሲያዳምጠው ወደነበረው ሠራተኛ ዞሮ በፈግታ ጠየቀው፣

"እሺ ምን ፈልገህ ነው?

"የጠቅላላ አገልግሎት ሠራተኛ ነኝ። አሁን ያወሩበት የቢሮ ስልክዎ ስለተበላሸ ለመጠገን መጥቼ ነው"

ባሻዬ! የብልጽግና ፓርቲያችንን ስም የሚያስጠፉት እንደዚህ ዓይነት ሰዎች ናቸው።

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

10 Nov, 09:40


ቸርቿ ልትሸልመኝ ይገባል!
(አሌክስ አብርሃም)

አንዱ የቤተክርስቲያን ኪቦርድ ተጨዋች ትልቅ ስህተት ይሳሳታል። እሱ እንኳን ጥሩ ልጅ ነበር ፣ያ የተረገመ ሰይጣን የሆነ ቀን ኪቦርድ ከሚያስተምራት የፓስተሩ ሚስት ጋር አሳስቶት እንጅ። እሷም ጥሩ ልጅ ነበረች ዕድሜዋ ከባሏ በ22 ዓመት ከማነሱ ውጭ! እና ከማንኛውም አገልግሎት ይታገዱ በሚሉና ለዛሬ በምክር ይታለፉ በሚል ምእመኑ ለሁለት ተከፈለ። መከፈል ብቻ አይደለም በዓለም እንኳን ተሰምቶ በማይታወቅ ፣ማንም ከዚህ በፊት ባልተሳደበበት ፣ ገና በዛ ዓመት ከጥልቁ ተመርቶ ለገበያ በቀረበ ዜሮ ዜሮ ስድብ ጉባኤው ይሞላለጭ ጀመር። ከቃል አልፎ በጣት ምልክት ሁሉ እንካ እንች ምናምን እየተባባሉ። እና ልጁ በግርምት ስድድቡን ዛቻውን ሲኮመኩም ቆየ። የሱ ድርጊት ከሚያየው ጉድ አነሰበት። ሲወጣላቸው ሲረጋጉ "እሽ አስተያየትህ ምንድነው ይሉታል ንስሀ ትገባለህ ወይስ?"

ወገኖቸ ! የገረመኝ የእኔ መባለግ አይደለም። እኔኮ ስትቅለሰለሱ ስትፀልዩና ስትሰብኩ በትእግስት የጌታን መምጣት የምትጠባበቁ ነበር የመሰለኝ። ለካ እዚህ ተሰብስባችሁ ብልግናችሁን የምትተነፍሱበት አንድ ባለጌ ስትጠብቁ ነው የቆያችሁት። ሰበብ ሆንኳችሁ፣ ለዓመታት በፆሎት ያልተገለጠ አጋንንታችሁ በብልግናየ እየጮኸ ወጣ....ቸርቿ ልትሸልመኝ ይገባል😀

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

09 Nov, 18:59


ጉተታው
(አሌክስ አብርሃም)

ኤለመንታሪ ተማሪወች እንደነበርን አስማተኛ ነኝ የሚል ሰው በጆሮየ መኪና እጎትታለሁ ሃምሳ ሳንቲም ትኬት ቁረጡ እያለ ወደትምህርት ቤታችን መጣ..ማንም አልቆረጠለትም፤ እንደውም መፈንከት አምሮን ነበር። ከዛ በፊት ተታለን ነበራ! ጅል መሰልነው እንዴ?! ይህን የሰሙ ወላጆች ሁሉ ሳይቀር ተቆጡ። በኋላ እኛ ፈላወቹ የባነንበት ሰውየ ሀይስኩል ሄዶ መኪና በጆሮው እንደሚጎትት እና ትኬቱም አንድ ብር እንደሆነ ሲነግራቸው እንኳን ተማሪ አስተማሪና ወላጆች ሳይቀሩ ትኬት ለመቁረጥ ግድያ ሆነ። የተቆጡ ወላጆች ሁሉ ሐሳባቸውን ቀይረው ይጋፉ ጀመር። ግራ ገባን። እንደውም ቦታ ጠቦ ብዙ ትርኢቱን ሊመለከቱ የሄዱ ሴቶች እያዘኑ ተመለሱ። "በአጥርም ቢሆን ይሄን ጉድ እናያለን" ያሉም ነበሩ።

የገረመን ለመመልከት ከሚጋፉት ሴቶች ይበዙ ነበር። ሰውየው እውነትም አስማተኛ ነው ...ከኋላ ከፍሎ ባሰማራቸው ሰወቹ መኪናውን የሚጎትተው በጆሮው አይደለም ልጅ ፊት እንደዛ ስለማይባል ነው እንጅ በእንትኑ ...ነው የሚጎትተው" ብለው አውርተው ነበር። ህዝቡ ነቅሎ ገባ። ብለው ብለው መኪና ሊጎትቱበት? እየተባባለ። ልጆች እዛች ግድም እንዳንደርስ ተከለከልን። በኋላ ሰውየው አንዲት ታክሲ እንደምንም በጆሮው ትንሽ ጎተተ ። ህዝቡ አልተደነቀም፣ ልቡ የተሰቀለው ሌላው ጉዳይ ላይ ነበር። ቀጣዮን ለማየት አዳሜና ሂዋኔ እንደጓጓ "ትርኢቱ አለቀ" ብሎ ኩም አደረጋቸው አስማተኛው።

እንዴ እንትኑሳ?
ምኑ?
መኪናውን የምትጎትተው በእንትንህ...ነው አልተባለም እንዴ? አሉ ወደእንትኑ እየጠቆሙ።
ፈገግ ብሎ የሱሪውን ዚፕ እየነካ "በዚህማ ይሄን ሁሉ አንድ ከተማ ህዝብ ጎተትኩበት!!"😀

ይሄው እስከዛሬ እንትን ጋር የተያያዘ ወሬ እንደጉድ እየጎተተ ይሰበስበናል። እንዳለ ህዝቡ አስማት ሊያይ ኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅልሎ ገባኮ ጓዶች።😀 ያ የተረገመ ሰውየ በእንትኑ ጎትቶ ጊኒ አጎረን።

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

05 Nov, 14:43


እኛ የምንኖርባት ኢትዮጲያ ናት ወይስ ሌላ ?
ፖለቲከኞቹ የሚኖሩባት ኢትዮጲያ ግን ደስ ስትል።
ዜጋው መብላት ከብዶት 738 ሚሊዮን ዶላር ብድር መስጠት ትንሽ አይጋጭም?

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

02 Nov, 13:52


ከአልፎጂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ

(በእውቀቱ ስዩም)

ከብዙ መጠፋፋት በሁዋላ ፥ በቀደምለት ከምኡዝ ጋራ ተገናኘን፤ ኑሮ እና እድሜ ለውጦታል፤ ተጫዋች የነበረው ሰውየ ተነጫናጭ እና ተናዳፊ ሆኖ ቆየኝ::

አሳዘነኝ!

ገና እንደተገናኘን “ እንዴት ነው አልዘነጥሁም?” አልሁት በወፍራሙ ፈገግ ብየ ::
“ላለፉት አስራ አምስት አመታት አንድ የቆዳ ጃኬት ለብሰህ ነው የማውቅህ ፥ከቻልክ ቀይረው ካልቻልክ አስቀልመው “ ብሎ ለከፈኝ፤

የእግር ጉዞ ጋበዝኩትና ፒያሳ ስንደርስ አስፋልቱ ዳር ድንክየ የመንገድ መብራት ተተክላ ተመለከትን :
:
“ ይቺ ደግሞ ምንድናት?” ስለው ፥

“ የአብሪ ትል መታሰቢያ ሀውልት መሆን አለባት “ ሲል መለሰልኝ፤

ትንሽ እንደ ሄድን እኔ በአዲሱ የእግረኛ መንገድ ዳር የለመለመውን ሳር እያየሁ ማድነቅ ጀመርሁ ፤” አሁን ደሞ በሳሩ ላይ የወተት ላም ቢያስማሩበት ጥሩ ነው፤ “ አለ ምኡዝ ::

“ ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም፤ ድሀ የአካባቢ ውበት አይወደለትም ያለህ ማንነው “ ብየ ሞገትኩት፤

እጁን በንቀት አወናጨፈና “ ለነገሩ አንተ የዘወትር ጎመን ተመጋቢ ስለሆነህ ሳር ግጣችሁ እደሩ ቢባል ሽግግሩ ብዙ የሚከብድህ አይመስለኝም”

አራት ኪሎ በስላሴ ትዩዩ ባለው መንገድ ስንደርስ ምኡዝ አንዲት አልፎሂያጅ ሴት አስቆሞ ጀነጀነ፤ “አላማ “አለኝ ብላ ፊትም ደረትም ነሳችው፤ “ከአራት የመሬት መንቀጥቀጥ እና ከሁለት የእርስበርስ ጦርነት ለጥቂት ተርፈሽ ስለ ምን አላማ ነው የምታውሪው? “ሲላት ጥላው ሄደች፤

በመልስ ጉዞአችን ላይ ከቀበና ድልድይ ስር በሚገኘው ፓርክ ውስጥ ወጣት ፍቅረኛሞች ትከሻ ለትከሻ ተደጋግፈው ሲያጠኑ ተመለከትን፤ ምኡዝ የድልድዩን አግዳሚ ተደግፎ ቁልቁል እያያቸው ” ይሄንን መናፈሻ “መፈሳፈሻ “አደረጋችሁት አይደል?” ብሎ ቆሊያቸውን ገፈፈው፤

ሰፈር ስንደርስ ፥ምግብ ቤት ገብተን ምሳ አዘዝን፡ ፡
ከፊትለፊታችን አንድ የማውቀው የሰፈራችን ልጅ ቁጭ ብሎ ሻይ ይጠጣል፤
ሲያፈጥብን “እንብላ “ ብየ ጋበዝኩት::
ልጁ ብዙ ሳይግደረደር ወንበር ስቦ ማእዱ ላይ ተጣደ፤

እኔና ምኡዝ እየበላን በአፍሪካ ቀንድ ዙርያ ይከሰታል ስለተባለው የመሬት መንሰንጠቅ መወያየት ጀመርን ::
ተጋባዡ የጥያን ደንጋይ የሚያክል ጉርሻ የዳጠውን ጉሮሮውን እህህ ብሎ ካጸዳ በሁዋላ፤

“ የመሬት መሰንጠቁ የሚከሰት ከሆነ፥ ኢትዮጵያ የባህር በር ብቻ ሳይሆን የባህር መስኮት ይኖራታል” አለ፤

ይኸኔ ምኡዝ በንዴት ፤-

“እጅህን የሰነዘርከው አንሶህ ሀሳብ ትሰነዝር ጀመር ! ተነስ!”

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

28 Oct, 08:56


ያከሸፈቻቸው ያከሸፏት አገር!
(አሌክስ አብርሃም)

የ8ኛ ክፍል ተማሪወች እንደነበርን ነው። አንድ ቀን የሆነ አስተማሪ ቀረ። በዛ ክፍት ክፍለጊዜ ሁላችንም ደስ ያለንን ስንሰራ (አብዛሀኞቻችን ወሬና መንጫጫት) አንድ ምስጋናው? የሚባል ስዕል መሳል የሚችል የክፍላችን ልጅ ብላክቦርድ ላይ በወዳደቀ ቾክ ሁለት ሰወችን ሳለ። ስዕል ስላችሁ ይሄ ዝም ብሎ የልጅ ስዕል አይደለም፣ ባስታወስኩት ቁጥር የሚገርመኝ የፊታቸው መስመር፣ ፊታቸው ላይ ያረፈው ጥላ፣ ልብሳቸው ላይ ያለው ፓተርን እና ጌጣጌጥ ሳይቀር ፎቶ የሚመሳስሉ ፖርትሬቶች። ደግሞ የሳለው ምንም እያየ አልነበረም። እማሆይ ቴሬሳ ሁለት እጆቻቸውን እንደህንዶች ሰላምታ አገናኝተው ግንባራቸውን እንዳስነኩ እጃቸው መሀል መቁጠሪያ ተንጠልጥሎ፣ እንዲሁም ቀዳማዊ ሀይለስላሴ ከነንጉሳዊ ልብሳቸው ወደጎን ዞር ብለው። ሁላችንም ተገረምን ተደነቅን። የስእሎቹ መጠን የእውነት ሰው ያካክሉ ነበር።

ቀጣዮ ክላስ ጅኦግራፊ ። ኮስታራው አስተማሪያችን ገባና ስዕሎቹን አየት አድርጎ "ማነው የሳለው?" አለ ። በአንድ አፍ "ምስጋናው" አልን በአድናቆት ጭምር። ራሱ ወደምስጋናው ወንበር ተራምዶ ለአንድ ክፍል ልጅ የያዘው ልምጭ ተሰባብሮ እስከሚያልቅ ቀጠቀጠው። ምስጋናው በህመም ተንሰፈሰፈ። እና በቁጣ "ይሄ የተከበረ የትምህርት ገበታ ነው ! ማንም እየተነሳ የሚሸናበት አይደለም፤ ደደብ!" ብሎ ደነፋ። ዳስተሩን አንስቶ አንዴ እጁን ሲያስወነጭፈው ሀይለስላሴን ለሁለት እማሆይ ቴሬሳን አናታቸውን ገመሳቸው። አጠፋፍቶ ማስተማሩን ቀጠለ። ምስጋናው ከዛ በኋላ እንኳን ሰሌዳ ላይ ወረቀት ላይ ሲስል አላስታውስም።

ብዙ ዓመታት አለፉ። አንድ ቀን አዲስ አበባ ፒያሳ መርከብ የምትባል ምግብ ቤት ምሳ በልተን ስንወጣ በር ላይ አንድ የጎዳና ተዳዳሪ በፌስታል ፍርፋሪ ሲበላ አየሁ ምስጋናው ነበር። ቢጎሳቆልም አልጠፋኝም። ዛሬ በምን አስታወስኩት? አንድ አሜሪካዊ ህፃን ሰሌዳ ላይ በቾክ የሳለው ስእል በአስተማሪዎቹና በትምህርት ቤቷ ርዕሰ መምህር ስለተደነቀ በቀስታ ሰሌዳውን አንስተው አንድ ቢሮ ግድግዳ ላይ እንደሰቀሉት አነበብኩ። ስዕሉ ለዓመታት እንዲቆይ የሆነ ነገር እናስደርጋለን ብላለች ርዕሰ መምህርቷ። አገር ባከበረቻቸው ትከብራለች ባከሸፈቻቸው ትከሽፋለች። ይህ ሒሳብ የገባቸው ብፁአን ናቸው። ለትውልድ ፍቅር ያወርሳሉና።

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

27 Oct, 05:58


ከ150 አመት በኋላ ዛሬ በህይወት ካለነው ሰዎች አንዳችንም በህይወት አንገኝም።

ዛሬ ላይ ከምንታገልላቸው ነገሮች 70 በመቶ የሚሆኑት ከ150 አመት በኋላ አንዳቸውም ለምልክት እንኳ አይገኙም፡፡ ፈጽመው ይጠፋሉ ይረሳሉ፡፡

እስኪ ወደ ኋላ 150 አመት እንሂድ፡፡ ወቅቱ 1872 ገደማ ነው የሚሆነው፡፡ ያኔ የሰው ልጅ እንደ እቃ በአደባባይ ተደርድሮ የሚሸጥበት ወቅት ነበር፡፡

በወቅቱ ብርቅ የነበረውን የፊት መስታወት ለማግኘት ሲሉ የገዛ ዘመዶቻቸውን የሸጡ ሰዎች ዛሬ የታሉ?

መስታወትንስ ዛሬ ላይ እንደ ሀብት የሚያስበው ማን ነው?

ማንም ጨው ወይም ጌጥ ወይም ሌላ ነገር ለማግኘት ሲሉ የተሻሻጡ ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡

ዛሬ ላይ እነዚያ ሰዎች የሞቱላቸው የገደሉላቸው የተካካዱባቸው የተሻሻጡላቸው አብዛኞቹ ነገሮች ይህ ነው የሚባል የረባ ዋጋ ያላቸው አይደሉም፡፡

በጊዜው ግን ለሰው ልጅ የሞትና የህይወት ልዩነት ነበሩ፡፡

የሰው ልጅ በየጊዜው የሚታገልላቸው አብዛኞቹ ነገሮች ዛሬ ላይ ዞር ተብለው ሲታዩ በጣም የሚያስቁ ናቸው፡፡

አሁን አሁን ላይ ዘመኑ የኢንተርኔት በመሆኑ ኢንተርኔት ትዝታችንን ያስቀምጥልናል ብለን እናስብ ይሆናል፡፡ግን ይህም አስተማማኝ አይደለም።

#ማጠቃለያው
ህይወትን ቀለል አርገህ ኑር፡፡ ምንም ሆነ ምንም ዘላለም የሚኖር የለም፥ ከዚህች ምድር በህይወት የሚወጣ ሰውም የለም፡፡

ዛሬ ልትሞትለት እና ልትገድልለት የተዘጋጀኸው መሬት ከዚህ ቀደምም ብዙዎች ተጋድለውለት ሞተው ጭራሽ እንዳልነበሩ ሁሉ ተረስተዋል፡፡

ከ150 አመታት በኋላ ዛሬ አንተ እንደ ትልቅ ሀብት የምታያቸው አብዛኞቹ ነገሮች ምንም ፋይዳ የሌላቸው ተራ ቁሶች ይሆናሉ፡፡

እና ምን ለማለት ነው ፥ ፍቅር ይግዛን ፥ መጠላለፍ ከጀርባ መወጋጋት መቀናናት መፎካከር ይቅርብን፡፡ ህይወት ከማንም ጋር የምታደርገው ፉክክር አይደለችም፡፡

ቀደምንም ዘገየንም መጨረሻችን መቃብር ነው፡፡

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

26 Oct, 17:13


ልስን ድሃ
(አሌክስ አብርሃም)

የዛሬን አያድርገውና "ያጣ የነጣ" የሚለው አባባል ድሃና ድህነትን የሚገልፅ አባባል ነበር። አሁን ላይ በተለይ የከተማ ድሃ ያጣል ግን አይነጣም። ከምግብ ሳይሆን ከሜካፕ እና ከፊልተር በሚፍለቀለቅ ወዝና ውበት በአካልም በሚዲያም እያማረ ይራባል። ድሃ ነው ግን አይነጣም ፣አይገረጣም። ሜካፑና ገፅታው እንዳይበላሽ የሚያለቅሰው ወደውስጡ ነው። ይህ ውበት የነጣና ያገጠጠ ድህነትን ከላይ በሚያብረቀርቅ ነገር በመለሰን የሚሸፋፍን ሲበዛ አሳሳች ውበት ነው። አንዳንዴ ባለቤቱን ራሱን ጭምር ይሸውዳል።

ልክ እንደመቃብር ሃውልት የውጩ ውበት የውስጡን አፅም ይሸፍንብናል። በዛ ላይ ሀውልቱ ላይ የሚፃፈው የተጋነነ ታሪክና የሚለጠፈው ፎቶ ለሟች ከማዘን ይልቅ በሀውልቱ እንድንደመም ያደርገናል። የሟች ቤተሰቦች ከሟቹም በላይ አንጀታቸውን አስረው ለሀውልት ባወጡት ወጭ ያለቅሳሉ። መፅሐፉ "እናተ በኖራ የተለሰናችሁ መቃብሮች ናችሁ" ያለውኮ እንዲህ ያለው የውስጥና የውጭ ባህሪ አልገጥም ቢለው ነው። ነገሩ ግለሰባዊ ብቻ አይደለም ከተሞችም ተመሳሳይ ባህሪ አላቸው። ለምሳሌ አዲስ አበባን ተመልከቱ። በመብራት፣ በቀለም፣ በህንፃ ተለስና ስትታይ ከምድራችን የድሃ ድሃ አገራት የአስከፊዋ ድሃ አገር ዋና ከተማ ትመስላለች? የድሀ ድሀ ፣ ልዝብ ደሃ፣ መራር ደሃ ከሚሉት ማዕረጎቻችን በተጨማሪ " ልስን ድሃ" የሚል የድህነት ደረጃ ጨምረናል።

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

21 Oct, 14:48


😂🤣🤣🤣😭😭A handsome man went into a hotel and asked to see the boss. When the boss came, the story began.

-The client: is room 39 empty?
-The boss: yes, sir.
-The client: can I book it?
-The boss: of course you can.
-The client: thank you.

Before going to the room, the client asked the boss to provide him with a black knife, a white thread 39 cm and an orange 73g.

The boss agreed though he was surprized at the weird things the client asked to have.

The client went into his room, he didn't ask for food or anything else.

Unfortunately for the boss, his room was next to room 39.

After midnight, the boss heard strange voices and noise in that client's room. Voices of wild animals and of utensils and dishes being thrown on the floor.

The boss didn't sleep that night. He kept thinking and wondering what might be the source of the noise.

In the morning, when the client handed the keys to the boss, the latter asked to see the room first.

He went to the room and found everything alright. Nothing unusual. He even found the thread, the black knife and the orange on the table.

The client paid the bill and gave the bellboys a very good tip and left the hotel smiling.

The boss was in a shock but he didn't reveal what he heard to the bellboys. In fact, he started to doubt himself.

After one year, the client showed up again. He asked to see the boss again. The boss was in a puzzle.

The client asked the same things: room 39, black knife, white thread 39cm and an orange 79g.

This time, the boss wanted to know the truth by all means possible. He spent a sleepless night, waiting for something to happen. After midnight, the same voices and noises started, this time louder and more indecipherable than the year before.

Again, before leaving, the client paid his bill and left a large tip on the table for the bellboys. The smile didn't leave his face.

The boss started searching for the meaning of everything the client asked to have. Why did he ask room 39? why the white thread? why the black knife??? In fact, the boss didn't arrive to any convincing answer to all these questions.

The boss now was eagerly waiting for the month of March, the month in which the client showed up.

To his surprise, on the first day of March, the same client showed up. He asked the same questions. Wanted to book the same room, wanted to have the same things as before.

The boss again heard the same noises, this time more louder than before.

In the morning, when the client was leaving the hotel, the boss apologized politely to the client and asked to know the secret behind the noises in the room.

-''If I tell you the secret, do you promise to never reveal it to anyone else?''
-''I promise I will never let anyone know''.
-''Swear''
-''I swear I won't reveal your secret''
So finally, the client revealed his secret to the boss.

Unfortunately, the boss was a sincere person. Until now he hasn't revealed his secret to anyone.

When he does, I will let you know... thank you for reading.

Do you want to come and bëãt me?

Me too, I'm looking for the guy who sent me this! 😆😆😳😳🕺🕺

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

20 Oct, 06:57


በዜሮ ...
(አሌክስ አብርሃም)

አንድ ጓደኛየ መንጃ ፈቃድ አውጥቶ መኪና መንዳት በጀመረ በመጀመሪያው ቀን በሰላም በእግሬ ከምሄድበት ጠራኝና
"ና ግባ አደባባዮን ላሻግርህ" አለኝ
"ግዴለም በእግሬ እሻገራለሁ" አልኩ። ነዝንዞ አስገባኝና ጋቢና አስቀመጠኝ። መንግስትና ህዝብ ንዳ ብሎ ፈቃድ ከሰጠው እኔ ማነኝ ችሎታውን የምጠራጠር ብየ ተመቻቸሁ። ገና በሩን ከመዝጋቴ ስለመኪና ባህሪና ስለአነዳድ ቴክኒክ ልቤ እስኪደክም ያስረዳኝ ጀመር። ያለምንም ዓላማ ከተማችንን አንድ ጊዜ አዞረኝ። እስከዚህ ደህና ነበር። "ይሄ ፍሬን ይባላል፣ ድንገተኛ ነገር ሰው ፣ አህያ ወይም የተናኘ ባል የሚነዳው መኪና ቢገቡብህ ማቆሚያ ነው" አለና አጎንብሶ ፍሬኑንን ይፈልግ ጀመረ...(ተናኘ ሹፌር ያገባች የቀድሞ ፍቅረኛው ናት ከነቂሙ ነው መንጃ ፈቃድ የያዘው) "ፍሬኑን እስክትፈልግ ግን ....ከማለቴ ፍሬኑን አግኝቶ ባለ በሌለ ሀይሉ ረገጠው። ወደፊት ተወርውሬ የሆነ ነገር ጋር ተጋጭቸ ተመለስኩ። ዘና ብሎ "አሁን የገጨኸው ዳሽ ቦርድ ይባላል የትም አገር የሚያጋጥም ነገር ነው" አለና ቀጠለ። ደረቴን ደግፌ እያሳልኩ ዝም አልኩ።

ብቻ እንዲህ አሰቃይቶኝ በመጨረሻ "አንዲት ብዙ ሹፌሮች ያልባነኑባት ቴክኒክ ላሳይህ ወደፊት ይጠቅምህ ይሆናል" አለኝ። ወይ እዳየ። ከዚህ ሁሉ ለዓመታት የነዳ ሹፌር ተደብቆ ገና በአንድ ቀን ምን ተገልጦለት ይሆን እያልኩ ሳስብ በከተማችን አለ ወደሚባለው ቁልቁለት መንገድ ወሰደኝና "አሁን እዚህ ቁልቁለት ላይ ሞተሩን ታጠፋውና በዜሮ ትሄዳለህ ...መሪዋ ላይ ብቻ መጫወት ነው...ነዳጅ አተረፍክ ማለት ነው አባቴ" ብሎ ትልቅ ግኝት እንደነገረኝ አይነት በኩራት ሀሀሀሀሀ ብሎ ሳቀ። እኔ ግን ነፍሴ ተጨነቀች። መኪናው ወደታች ፍጥነት እየጨመረ መምዘግዘግ ጀመረ ። ወገኖቸ ባጭሩ ፍሬን ቢረግጥ ምን ቢረግጥ (እኔን ሁሉ እግሬን ቢረግጥ) መኪናው አልቆምም አለ። አታምኑኝም ዞር ስል የሹፌሩ በር ተከፍቶ አጅሬው ሲዘል ተገጣጠምን። ለደይቃወች ራሱን በሚነዳ መኪና ከተጓዝኩ በኋላ .... መኪናዋና እኔ ለግንባታ ፒራሚድ መስሎ የተከመረ አሸዋና ጠጠር ክምር ጫፍ ላይ ጉብ አልን። እዚህ ቴውድሮስ አደባባይ ያለውን የአፄ ቴውድሮስን የመድፍ ሀውልት ነበር የምንመስለው።

አሁን ያለንበትን የኑሮ ሁኔታ ሳየው፣ የሆነ ቴክኒክ ላሳያችሁ ብሎ ያሳፈረን ሹፌር ዘሎ የወረደ እስኪመስለኝ ቀላል እየተምዘገዘግን ነው?! ብቻ ማረፊያችንን ያሳምረው። ለእኔ በነጠላው የደረሰ አምላክ በጅምላ ይድረስልን።

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

19 Oct, 19:39


መዘበራረቅ
(አሌክስ አብርሃም)

ዝብረቃ 1.

ተኝታችሁ ከተስማማችሁ በኋላ ተንበርክካችሁ "ታገቢኛለሽ?" ማለታችሁ ትንሽ የቅደም ተከተል ችግር አለበት ልበል? ለፆለት የሚንበረከከው ወንድ ከዚህኛው መንበርከክ በቁጥር እያነሰ መምጣቱ እንዳያስቀስፈን ጓዶች።

ዝብረቃ 2.

ፊልሙን ለመስራት 1.5 ሚሊየን ብር አወጣን ካላችሁን በኋላ የዋናዋ ገፀ ባህሪ ሰራተኛ እህት ልጅ ሁና የተወነችው እንስት የሽልማት መድረኮች ላይ 2.666 ሚሊየን ብር የፈጀ ቀሚስ(አውትፊት ይሉታል) ለብሳ የምትታይበት ሳይንስ ትንሽ ግራ ያጋባል። አንዳንዴ በውበትም በዋጋም ከፊልሙ የሚበልጥ ቀሚስ ስናይ የልብስ ሰፊወች አዋርድ እየመሰለን ተቸግረናል። ለነገሩ የትም አለም የተለመደ ነው።

የውጭ ዝብረቃ 3.

ኤለን መስክ የሚባል በቴክኖሎጅ ፍቅር ልብሱን ጥሎ ያበደ ሰውየ፣ የሆነ መሪ የሌለው መኪና እያስተዋወቀ ነው። በዓለም የመጀመሪያው ካለመሪ የሚንቀሳቀስ መኪና ነው አለ። እንኳን መኪና እእእእእ 😀 እሽ ይሁን። የሆነ ሆኖ መኪናው እናንተ ቤታችሁ ተቀምጣችሁ ብቻውን ሄዶ ኡበር /ታክሲ/ ይሰራል ይሸቅላል ሲል ነበር። እና ሮቦቶች የሰወችን ስራ አይነጥቁም? ሲባል ምናለ? ይንጠቋ! ሮቦቶች ይሰራሉ ሰወች ዘና ብላችሁ የኪስ ገንዘብ እየተሰጣችሁ ትኖራላችሁ። ከመጠግረር ምን አላችሁ? የምርጫ ቅስቀሳ የመሰለ ነገር።

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

17 Oct, 10:19


እንደምን ሰነበታችሁ ወገኖቸ?
(አሌክስ አብርሃም)

ቆይ ቆይ በየተራ ተናገሩ ምንድነው ለመርዶ እንዲህ መጣደፍ?! ስለኑሮው ሰምቻለሁ። ሶስት ሽ ዘመን የተኛ ኑሮ ምን እንዲህ አስፈንጥሮ እንዳስነሳው አልገባህ ብሎኛል። መነሳቱን ይነሳ ትንሽ እንኳን ሳይረጋጋ አይኑን እንደገለጠ ልብሱን እንኳን ሳይለብስ ሩጫው።

ሰው ልሸኝ ብየ በነጠላ ጫማና በቱታ እዚች ጋ ወጣ ብየ ስመለስኮነው ሶስት የመሬት መንቀጥቀጥ፣ አንድ የመሬት መንሸራተት፣ ሁለት ከተማ የሚያካክሉ ታሪካዊ ሰፈሮች መፈራረስ፣ አንድ ታሪካዊ የፖለቲካ ፓርቲ መንፈሽፈሽ ፣ አራት " እንደጦር የሚዋጋ የዋጋ ማስተካከያ" ሁለት ፌክ እና ሶስት የእውነት ታዋቂ ሰዎች ሞት፣ቁጥር ስፍር የሌለው ጦርነት፣ ሁለት "እንኳን ደስ አላችሁ" ፣ ወደሁለት አገር አየር መንገዳችን እንዳትመጣብን ጭቅጭቅ፣ የግብፅ ጦር ተግተልትሎ እዚህ አፍንጫችን ስር መምጣት...ጨምሩበት! የዛሬን አያርገውና ይሄኮ በአራት ትውልድ እንኳ ሊከሰት የማይችል ነገር ነበር። የሆነ ሆኖ ምናባቴ ልሰራ ነው ወደ ሶሻል ሚዲያ የተመለስኩት እስከምል ደህና ተዘባርቃችሁ ጠብቃችሁኛል። እስኪ አብሬ ልዘባረቅ😀

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

16 Oct, 14:58


እንደ ሰርከስ
(በእውቀቱ ስዩም)

መኖር በሀገርህ
የሰርከስ ትርኢት እንደማሳየት ነው
ስልጠናው ሳይኖርህ ::

በሚያድጥ ዳገት ላይ ፥በብጤህ መጋለብ
በሁለት መዳፎች፥ ሳይፎርሹ መቅለብ
-ደርዘን ሙሉ አሎሎ፥
አሎሎ ቢጠፋ ፥እሾህ ተደብልብሎ
በሳት ቀለበት ውስጥ ፥ማለፍ ሹልክ ብሎ፤

እንደ ህልም እሪታ፥ በሰለለ ገመድ
ባንድ እግር መራመድ፤

ይሄን ሁሉ አድርገህ፤ ትርኢቱም አልቆ
ካጥንቶችህ መሀል፥ አንዱ ተሰንጥቆ
አንደኛው ደንድኖ
እንደ በላኤ ሰብ፥ እጅህ ወንፊት ሆኖ፤

ምንም ባትታደል፥ አንቱ የሚባል ስም
አሞጋሽ ለክብርህ፥ ነጋሪት ባይጎስም
ምናልባት ካተረፍክ-
ያልተራገፈ ጥርስ ፥ያልተሰበረ ቅስም
የድል ሳቅህን ሳቅ፥ በተረፈው ጥርስህ
በወንፊት መዳፍህ፥ አጨብጭብ ለራስህ::

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

15 Oct, 17:34


በአዲስ አበባ የህዝብ ትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ጭማሪ ተደረገ፡፡

ግን እኔ ብቻ ነኝ መንግስት ምንም እያመጡም የሚል እልክ ውስጥ የገባ የሚመስለኝ🤔

@matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

11 Oct, 17:55


ሰሞኑን የማነባቸው ዜናዎች .....

ኢትዮ ቴሌኮም ባንዳንድ አገልግሎቶቹ ላይ የታሪፍ ማስተካከያ አደረገ።

የነዳጅ ዋጋ ማስተካከያ ተደረገ።

መንግስት ዋጋ ሲጨምር ማስተካከል ነው የሚባለው ማለት ነው🤔

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

09 Oct, 13:35


እንውጣ
(በእውቀቱ ስዩም)

ወንድ ልጅ አይጣ! ምን አይጣ? ሚስት አይጣ! መልስ አይጣ! መውጫ አይጣ! ይልቁንም ገንዘብ አይጣ!

በቀደም እሁድ ለታ፥ ኤቲኤም ማሸኑ ላይ ሄጄ ተገተርኩ ፤ ዞር ብየ ታዛቢ መኖር አለመኖሩን ካረጋገጥኩ በሁዋላ” ሁለት መቶ ብር” የሚለውን አማራጭ ጨቆንኩት ፤ ማሽኑ ካርዴን መለሰልኝና “ ውድ ደንበኛችን፤ ለሁለት መቶ ብር ብለንማ በሰንበት መጋዘናችንን አንከፍትም! እባክዎ ባቅርቢያዎ ከሚገኝ የባንክ ዘበኛ ይበደሩ “ የሚል ጽህፈት ሰደደልኝ ፤

ከላይ ያለው ቀደዳ ሲሆን፥ ከታች ያለውን ግን የገሀዱ አለሜ ነጸብራቅ ነው!

ማርያምን ወንድ ልጅ አይጣ! ወንድ ልጅ በጣምም አያግኝ ! ሲያገኝ እንደኔ ጽጋበኛ ያለ አይመስለኝም! ከበቀደም ሁለት ቀን አስቀድሞ ልዝብ ሀብታም የሚያሰኘኝ ገንዘብ ሸቅየ ነበር፤ ሼክ አላሙዲን መክሰስ በሚበላበት ባርና ሬስቶራንት ገብቼ የምግብ ናዳ አዘዝሁ፤

ለማሳረጊያ ያዘዝኩት፥ ብርቱካን አናናስ እና ፓፓየ ጠረጴዛየ ላይ ተከማችቶ ያየ ሰው የሆነ የፍራፍሬ እርሻ የሚያስመርቅ የዞን ባለስልጣን ነው ምመስለው፤

ፈንጠር ብሎ የቀድሞ እግር ኳስ ተጫዋች የነበረ ሰውየ ተቀምጦ ያየኛል( ስሙን በሌላ ቦታ የገለጽሁት ሲሆን እዚህ ላይ አጅሬ እያልሁ እቀጥላለሁ)

አጅሬ ፈገግ ብሎ ሲያየኝ ከቆየ በሁዋላ “ ይሄን ያህል በምግብ ተጎድተሀል እንዴ ?” ብሎ ለከፈኝ ፤

እኔ ሰላማዊ ሰው ነኝ፤ አዝመራው የተባለ ዘመዴ ትዝ ይለኛል፤ ድሮ ከትምርት ቤት ስንመለስ የሰፈር ጎረምሶች አስቁመው ነገር ሲፈልጉን እኔ ከድብድብ ለማምለጥ ያሉ የሌሉ ዘዴዎችን ሁሉ አሟጥጬ እጠቀማለሁ፤ ጎረምሶቹ በለስላሳ ምላሴ ተማርከው በሰላም ሊያሰናብቱን ከጨረሱ በሁዋላ አዝመራው እመር ይልና ክምር እንዳየ ዝንጀሮ አንዱ ላይ ይወጣበታል ፤ ከቴስታ አቅም እንኳ ሶሰት አይነት ቴስታ ያውቅ ነበር፤ ሸራፊ ቴስታ- ማይግሪን የሚያስይዝ ቴስታ እና ለኮማ እሚዳርግ መርዘኛ ቴስታ-

ጎረምሶችን አሸንፎ ሲያበቃ የሚሸልላት አትረሳኝም፤

“ዘራፍ አዝመራ ! ( ከስሙ መጨረሻ ያለችውን “ው” ለቤት ምታት እንቅፋት ስለምትሆን ያስወግዳታል)
ቁመቱ አጣራ
ልቡ ተራራ”

ለወትሮው ሰላማዊ የነበርኩት ሰውየ ድንገት የአዝመራው መንፈስ ተጋባብኝ ፤ ብልጭ አለብኝ! በዚያ ላይ ለሁለት ወር የkick boxing ስልጠና መውሰዴ ተራራም ባይሆን የሰፈር ዳገት የምታክል ልብ አጎናጽፎኛል፤

ከለካፊየ ጋር ትንሽ የስድብ ልውውጥ ካደረግን በሁዋላ “ልብ ካለህ እንውጣ ! “ አልሁት፤ እሱ ግን ቸል ብሎኝ ድራፍቱን መቀንደሉን ቀጠለ፤ እኔ በዛቻየ ቀጠልኩ፤ አጅሬው ሰማኝ ሰማኝና በመጨረሻ በረጅሙ ተንፍሶ እንዲህ አለ፥

“ እንዲያው አሁን፥ አስሬ እንውጣ የምትለኝ ፤ ልትመታኝ ነው ብርድ ልታስመታኝ?”


https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

06 Oct, 19:46


የዛሬው ነገር

የምወደው ጉዋደኛየና ጎረቤቴ ደወለልኝ ፤

“በውቄ የት ነህ?"

“የት ነህ?”

“ ቤት”

“እንዳለ የኮንደሚኒየሙ ነዋሪ ውጭ ወጥቶ ሲተራመስ አንተ ቤት ምን ታረጋለህ?”

“ ውጭ ምን አለ?”ስል ጠየቅሁት፤

“ የመሬት መንቀጥቀጡ አንተ ጋ አልደረሰም እንዴ?”

ከስልኩ አሰር ደቂቃዎች በፊት ሶፋ ላይ ቁጭ ብየ የቆየ መጽሀፍ እየገረብኩ ነበር፤ የተቀመጥኩበት ሶፋው ከስሬ ሲዋዥቅ ትዝ ይለኛል፤ ከሶፋው አጠገብ ጠርዝ ላይ ያስቀመጥኩት የውሀ የላስቲክ ጠርሙስ እንደ ሲወዛወዝ አይቻለሁ፤ ግን የመሬት መንቀጥቀጥ የሚለውን ሀሳብ እንዴት ላምጣው? ሰሞኑን አላግባብ ስለወፈርኩ ሶፋውን እየተፈታተንኩት የሚል ሀሳብ ውልብ አለብኝ ፤

የሰው ልጅ አእምሮ ሞትን የሚያስታወሱ ነገሮች በሙሉ መጨቆን ልማዱ ነው፤

ከሀያ ቀን በፊት ቻናሌ ላይ በጫንኩት “የሹፌሩ ማስታወሻ “ በተባለ ትረካ ላይ “ አሙዋረትህ አትበለኝና ሰሞኑን የምንሰማው የመሬት መንሸራተት ሊመጣ ላለው የመሬት መንቀጥቀጥ ቀብድ ነው “ የሚል ቃል አስፍሬ ነበር፤

በሰላም እንደርና ይሄንን የነብይነት ተሰጥኦየን እንዴት እንደምንጠቀምበት የምንወያይ ይሆናል፤

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

06 Oct, 18:40


#Update

" እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ የለም፤ ሞገዱ በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ ነው ፤ አዋሽ አካባቢ ነው የተከሰተው በሬክተር ስኬል 4.9 ነው " - ዶክተር ኤልያስ ሌዊ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

" እስካሁን ባለው መረጃ እዚህ የመሬት መንቀጥቀጡ እዚህ አዲስ አባባ የተከሰተ ሳይሆን አዋሽ አካባቢ የተከሰተ ነው።

ግን በመሬት ውስጥ አልፎ እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ ልዩ ልዩ ቦታዎች ተሰምቷል።

ይሄን ግልጽ ማድረግ እንፈልጋለን እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ አይደለም። ግን በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ እዚህ ያሉ ህንጻዎችን አንቀጥቅጧል።

በሪክተር ስኬል 4.9 ነው ያገኘነው። ይሄም ከፈንታሌ የሚባል ተራራ አለ ወደ መተሃራ አካባቢ ነው የተከሰተው። እስካሁን ያለው መረጃ ይሄ ነው።

ሰውም ይረጋጋ እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይሆን ከሩቅ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሞገዱ በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ በተለይ እዚህ ሰሜን እና ሰሜን ምስራቅ ያሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በጣም ተረብሸዋል። ልክ ነው ከዛም ሊሰማ ይችላል።

በሬክተር ስኬል 4.9 ነው ይሄ ነው ያለው መረጃ።

ተጨማሪ መረጃ እንዳገኘን በግልጽ እንነግራለን። " ብለዋል።

ዛሬ ምሽት በአዲስ አበባ በነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ምክንያት በተለይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚኖሩ ነዋሪዎች ህንጻቸው ሲንቀጠቀጥ እንደነበር ገልጸውልናል። በዚህ ምክንያት ከቤታቸው ወጥተው መሬት ላይ ወርደው ተሰባስበዋል።

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

06 Oct, 18:22


ከ4.5 እስከ 4.9 ይሆናል በተባለ መጠን የመሬት መንቀጥቀጥ በአዲስ አበባ ከተማ ተከስቷል

በበርካታ የከተማው አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች በስጋት ላይ እንደሚገኙ ተረድተናል።

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

02 Oct, 03:28


የህልሜ በር ቁልፍ
(በእውቀቱ ስዩም)

ከመንገዷ ሸሸሁ
በማትውልበት ዋልሁ
በማታመሽበት፤ ሰፈር ውስጥ አመሸሁ
ፎቶዋን አክስየ
ፊት የሌለው ምስል በላዩ ላይ ስየ፥

“ይደምሰስ ስራዋ
ይወድም አሻራዋ ፥
የሰደድ ነበልባል እንደበላው ሰፈር
የመታሰቢያዋ አመዱ ይሰፈር
ወግ ታሪኳ ያክትም
ከንግዲህ በሁዋላ
እንኳን ወደ ቤቴ፤ ወደ ትዝታየ፥ ድርሽ አትላትም”

ብየ ፎከርኩና አልጋየን አነጠፍኩ
የሰራ አከላቴን፥ እንደ ጃንጥላ አጠፍኩ
አበባ ይመስል ፥ጉልበቶቼን አቀፍኩ፤

ታድያ ብዙም ሳይቆይ፥ በእንቅልፌ ስረታ
ኮቴዋን አጥፍታ
እንደ መንፈስ ገባች
ከትራሴ ግድም ከተማ ገነባች፤

ነግቶ ብንን ስል ፥ ያ ሁሉ ሙከራ
ከንቱ እንደ ሆን ገባኝ ፤ ሳይገድሉ ፉከራ
ሳይጥሉ ቀረርቶ
የህልሜ በር ቁልፍ ፥ መዳፏ ላይ ቀርቶ::
https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

29 Sep, 12:39


ለነገ መኖርህ ዋስትናህ……ገንዘብህ ! ጉልበትህ ! ቤተሰብህ ! ዝናህ ! እውቀትህ ! ብልሀትህም አይደለም ! እነዚህ ሁሉ አያድኑንም !!!

አዳኙ እሱ ያለ ምሶሶ ፤ ያለ ድጋፍ ያቆመህ ፈጣሪህ ነው ! ሁሌም ምን ይገርመኛል... ዘላለም ኗሪዎች የሆንን ፍጡራን ይመስል የክፋታችን ጥግ ፣ የተንኮላችን ጥግ ፣ የምቀኝነታችን ጥግ 🙆‍♂🙆‍♀

አንዱ መቃብር ሀውልቱ ላይ ምን አፃፈ አሉ..

የምቆይ ..! የምቆይ ..ይመስለኝ ነበር

@matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

24 Sep, 12:07


https://www.youtube.com/watch?v=7l1ZtRqaf8k

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

22 Sep, 16:21


የሰንበት ወግ
(በእውቀቱ ስዩም)

አካል ጉዳተኛን እንደ ደካማ ፍጡር መመልከት፥ ከባህላች አሉታዊ ገጽታዎች አንዱ ነው ፤ ግን እስቲ አስቡት ! ሙሉ አካል ያለው ሰው፥ ሙሉ አካሉን ምን ያህል ይጠቀማል? “ተጠቅመህ መልስ “ ይላል እቃ የሚያውስ ሰው! ከተፈጥሮም በለው ከፈጣሪ፥ የተዋስነውን አካል ሳንጠቀም የምንመልስ ጥቂት አይደለንም፤ ከህዋሳት አንዱን በአደጋ ወይም በተፈጥሮ ያጣ ሰው ፥ አንጎሉን እና ቀሪ ህዋሳቱን ሙሉ አካል አለኝ ብሎ ከሚመካው ሰው በላይ እንደሚጠቀም እናውቃለን፤ ለዚያ ነው፤ ዓለማችን ሆመርን የሚያክል ባለቅኔ ፥ ቬትሆቨንን የሚያክል ሙዚቀኛ ማፍራት ያልቻለችው፤

ቁምነገሩን ለማለዘብ የሚከተለውን የሰንበት ወግ ልጨምርበት፤

አምሳ አለቃ ገብረሀና(ማእረጋቸው ለዚህ ጨዋታ ሲባል ተቀይሯል🙂) ካንድ ቦታ ተነስተው ለጉዳያቸው ሲገሰግሱ ፥ መሽቶባቸው ፤ “የእግዜር እንገዳ ነኝ “ ብለው አንድ ቤት ተጠጉ፤

ባለቤትዋ መሸታ ቤት ያላት ወይዘሮ ናት፤ ውብ ደርባባ ሆና አንድ እግር ብቻ ነው ያላት ፤ ሌላውን እግሯን በአድዋ ጦርነት ወቅት ያጣችው ይመስለኛል::

መሸተኛው ሁሉ ተሰናብቶ ገብረሀና እና ሴትዮዋ ብቻቸውን ቀሩ፤ ሴትዮዋ ላምሳለቃ እራት አብልታ እግራቸውን አጥባ አነጠፈችላቸውና አልጋዋ ላይ ወጥታ ጋደም አለች፤ ገብረሀና ለመተኛት ቢሞክሩም እንቅልፍ አልጠጋቸው አለ፤ ድንገት የሆነ ከይሲ ሀሳብ መጣላቸው ::

ብድግ ብለው ወደ ሴትዮዋ አልጋ ተሳቡ፤ አልጋው ላይ ወጡና እንደ ሽቦ ተጠመጠሙባት፤ ሴትዮዋ “ አንቱ ቅሌታም ” ብላ አክብሮት ያልተለየው ስድብ ከወረወረችላቸው በሁዋላ ፥ ገፍተር አድርጋ ፥ ለሪጎሪ እንደ ሚመታ ኳስ አልጋው ጠርዝ ላይ አመቻቸቻቸው፤ ሴትዮዋ በደህነኛ እግሯ በሙሉ አቅሟ እርግጫ ስትሰነዝር የተዘጋ ስቴድየም የመበርገድ አቅም አላት፤ ይሁን እንጂ ገብረሀና ሽማግሌ እና የእግዜር እንገዳ መሆናቸውን ከግንዛቤ በማስገባት በስሱ ብትሰንብቃቸው እንደ ላስቲክ ኩዋስ ነጥረው ፥እንደ ናዳ ድንጋይ ተንከባልለው ግድግዳው ላይ እንደ ጥቅስ ተለጠፉ፤

ገብረሀና ፥ትንፋሻቸውን ሰብስበው ፥ አለመሞታቸውን ካረጋገጡ በሁዋላ ወደ ረገጣቸው እግር እየተመለከቱ እንዲህ ብለው ተራገሙ፤

“ የወንድምህን ቀን ይስጥህ ፤”

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

21 Sep, 12:20


#moonbix

|| ይህ የባይናንስ ፕሮጀክት ነው።

|| እንደ ሌሎች ኤርድሮፖች ብዙ ኮይኖች በአንዴ ለመሰብሰብ በጣም አስቸጋሪ ነው።

|| የተሻለ ዋጋ እንደሚኖረው ምንም ጥርጥር የለውም።

|| ብዙ ነጥብ ለመሰብሰብ ታስኮችን ስሩ እንዲሁም ጌም ተጫወቱ በየሰዓቱ 6 እድል ይሰጣል።

|| ቀድሞ የጀመረ 100% ተጠቃሚ ይሆናል። አሁኑኑ ብትጀምሩት ተጠቃሚ ትሆናላችሁ።


ለመጀመር

https://t.me/Binance_Moonbix_bot/start?startapp=ref_340268780&startApp=ref_340268780
Join the Moonbix Journey! Get 1000 Coins as a new player and stay tuned for exciting airdrops and special rewards from Binance!

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

17 Sep, 06:02


የአነቃቂ ንግግር ዲስኩር አቅራቢ እንዲህ ሲል ለተሰበሰበው ህዝብ ንግግር አደረገ፣

"የህይወቴ ምርጥ ጊዜያት ከሌላ ሰው ሚስት ጋር ያሳለፍኳቸው ጊዜዎች ናቸው"

ይህንን ሲናገር ህዝቡ በድንጋጤ ክው አለ። ተናጋሪው የህዝቡን ስሜት ከተረዳ በኋላ እንዲህ ሲል ጨመረበት ፣

"ያቺ ሴት እናቴ ናት! " ብሎ ሲናገር ህዝቡ በፉጨትና በጭብጨባ አቀለጠው።

ይህንን ንግግር ያዳመጠው ሌላው ሰው ቤቱ ሄዶ ሊሞክረው ፈለገና ራት ላይ ለሚስቱ "የህይወቴ ምርጥ ጊዜያት ከሌላ ሰው ሚስት ጋር ያሳለፍኳቸው ጊዜዎች ናቸው...." ብሎ ቀጣዩን ሃሳብ ከመናገሩ በፊት ሚስቱ በያዘችው የጋለ መጥበሻ አናቱን ብላው አሁን ሆስፒታል ይገኛል።

ባሻዬ!

1.የአንዳንድ አነቃቂዎችን ንግግር እንደ አደገኛ ጨዋታ በቤት ውስጥ አትሞክረው፣

2. copy ያደረግኸውን ንግግር በአግባቡ paste ካላደረከው አደጋው የከፋ ነው።

በአጭሩ Don't copy if you cannot paste.

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

16 Sep, 05:44


10 days left for hamsters listing

start if you didn't
https://t.me/hamSter_kombat_bot/start?startapp=kentId340268780

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

14 Sep, 03:47


ገላጣ
(በእውቀቱ ስዩም)

ዛሬ የተከበረውን የዓለም አቀፍ ራሰ በራዎች ቀን ሳልዘክር ወደ ምኝታየ ብሄድ የሶቅራጥስ አጽም ይወጋኛል፤

ሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “በራሕ”የሚለውን ቃል ሲተረጉሙት-“ በራ፥ መላጣ፥ ራሰ ገላጣ፥ ከቦታው የታጣ፥ የራሱ ቁርበት፥ ሳንባና ጉበት የሚመስል “ ይላሉ (መጽሀፈ ስዋሰው ወግስ ፥ ገጽ 287፤ በትርጉሙ ውስጥ ያሉትን አሉታዊ ቃላት ብዛት ለተመለከተ አለቃ ባለ ሙሉ ጠጉር እንደሆኑ መገመት አያቅተውም፤

አለቃ “ራሰ ገላጣ “ ቢሆኑ ኖሮ “ራሰ በራ ” የሚለውን ሲተረጉሙ “ራሱ የበራለት፤ ታጥቦ የተወለወለ የንጉስ ብርሌ የመሰለ፥ መላጣ፥ ከፎረፎርና ከቅማል ስጋት ነጻ የወጣ “ብለው ሊተረጉሙት ይችሉ ነበር፤

በታሪካችን ትልልቅ ራሰ በራ ተጽእኖ ፈጣሪዎች ነበሩ፤ ከጌቶች መካከል ብንጠቅስ፥ ራስ ስኡል ሚካኤል፥ አጤ ምኒልክ፥ ራስ ዳርጌ፥ መለስ ዜናዊ፥ ከደራሲ ፥ሀዲስ አለማየሁ፥ ጃርሶ ኪሩቤል ሞትባይኖር፥ መንግስቱ ለማ፥ ሊጠቀሱ ይችላሉ፤ ( ሎሬት ጸጋየ ገብረመድህን ራሰ በራ ነው ወይስ የተሸጋሸገ ጎፈሬ ነው የሚለው በታሪክ ሲያከራክር ይኖራል )

“ለኔ እየሰጠችኝ ደረቁን እንጀራ
እስዋ በነካካው በራሰው ልትበላ"

የሚለውን ጥንታዊ ውስጠ ወይራ ዘፈን መናሻ አድርገን ብንናገር ፥ ሴቶች ከሚያበጥር ይልቅ የሚወለውል ወንድ የበለጠ እንደሚማርካቸው መረዳት አያቅትም፤

ስለ ጸጉር ጨዋታ በተነሳ ቁጥር ፈገግ የምታሰኝኝ ድምጻዊ አብነት አጎናፍር የተናገራት ናት፤ አብነት እንዲህ አለ፤

“ ከጥቂት ጊዜ በፊት ጸጉር ላስተክል ቱርክ ሄጄ ፤ ጸጉር የሚተከለው ሰውየ መላጣ መሆኑን ሳይ ትቸው ተመለስኩ"🙂

በዚህ አጀንዳ ላይ ሌሎች የከተማው ነዋሪዎች ያላቸውን አስተያየት ለመስማት ከፈለጉ ከታች የጫንኩትን ትረካ ያድምጡ ::

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

12 Sep, 06:57


ማን ያውቃል
(በእውቀቱ ስዩም)

የመስቀል ወፍና የአደይ አበባ
ቀጠሮ እንዳላቸው መስከረም ሲጠባ
ማን ያውቃል?

(ገጣሚ መንግስቱ ለማ)

ከሁሉ አስቀድሜ፥ እጅግ የሚያምር የበአል ስርአትን ለፈጠሩልን ካህናት አባቶች እና እናቶች ምስጋና አደርሳለሁ፤ ላይን ውብ የሆነውን አበባ፥ ለጆሮ የሚጥመውን ማህሌት፤ ለአፍንጫ ጣፋጭ የሆነውን እጣን እና የሚያውድ ሳር ሁሉ አግኝተን የምናጣጥመው በበአል ነው፤

ይገርማል!

“የማይታረድበት አመትባል እና ጋቢ የማይለብስ ባል ግርማ ሞገስ የላቸውም “ ይል ነበር ጋሽ አሽኔ፥ የሰፈራችን ሸማኔ -፥የጋቢው ምርት የጠበቀውን ያክል አልሄድለት ሲል፤

ለዚያ ነው ትናንት እንዃን አደረሳችሁ ከማለት የተቆጠብኩት፤ በውነት ትናንትና ' እንኳን ተቃረባችሁ እንጂ እንኳን አደረሳችሁ” ለማለት የማይቻልበት ሁኔታ ላይ ነበርን፤

በዚህ አገር ታሪክ ውስጥ፥ ከተመዘገቡት ማሰቃያ ስልቶች አስከፊው “ወፌ ይላ” መገረፍ ይመስለኝ ነበር፤ ከፊትለፊትህ ባለው ቴሌቪዥን የአውዳመት የሙዚቃ ቪድዮ ውስጥ ፥ አጋም የመሰለ ያዶሮ ወጥ በትልቅ ሰታቴ ውስጥ ሰንተከተክ እያየህ በጦም ፍርፍር ማሳለፍን የመሰለ ስቃይ የለም፤ ለማንኛውም፥ በቀጣይም እንዲህ ያለ ሁኔታ ሊደገም ስለሚችል እነ ደመረ ለገሰ፥ የአመት በአል የሙዚቃ ቪድዮ ስትሰሩ ፥ የሱፍ ፍትፍተና ስንግ ቃርያን ማካተትን አትርሱ፤

ዘልዛይመር ያልያዛችሁ የኔ ዘመነኞች እንደምታስታውሱት፥ ልጆች እያለን በእንቁጣጣሽ መባቻ፥ የአበባ ስእል ቤት ከቤት እያዞርን ፍራንካ እንሰበስብ ነበር፤ እኔ ከፍተኛ የስእል ፍላጎት ቢኖረኝም፥ አበባ መሳል ብዙ አይሳካልኝም፤ የሰፈራችን አባዎራዎች የዘረጋሁላቸውን ወረቀት ይቀበሉና ፥የመርዶ ደብዳቤ የሚያነቡ ይመስል ፊታቸውን ዝፍዝፍ አድርገው ይገረምሙኛል፤ ሽልንግ ይሰጠኛል ብየ ስጠብቅ “ አሁን ይሄ አበባ ነው አሜባ ?” የሚል ዘግናኝ ሂስ የሚሰጠኝም አይጠፋም ፤ አጋነንከው በሉኝና፥የኛ ሰፈር ወላጆች ልጆቻቸውን "አበባ" ብለው መሰየም ያቆሙት የኔን ስእል ካዩ በሁዋላ ይመስለኛል፤

በተቃራኒው ደስታ የሚባል ጉዋደኛ ነበረኝ፤ ደስታ የንቁጣጣሽ ስእል ሰሎ ቤት ለቤት ሲያዞር እናቶች ተቀብለው ፥ስእሉን አይተው ያንን የጥይት ማስቀመጫ ሳንዱቅ የሚያክል ግንባሩን ስመው ፤ ብር ይሰጡትና ስአሉን በፍሬም አድርገው ከዋናው በር ፊትለፊት ባለው ግድግዳ ላይ ይሰቅሉታል፤ “ስታድግ አፈወርቅ ተክሌን የምትተካ ሰአሊ ይወጣኻል” የማይለው ሰው አልነበረም፤
በቅርብ የሆነ ጊዜ ሳገኘው የዲሽ ጥገና ባለሙያ ሆኖ አገኘሁት፤

የልጅነታችንን አስንተን ሰናወጋ በትካዜ እንዲህ አለ፤

“ የስእል ችሎታየ የሆነ ጊዜ ላይ ጥሎኝ ቢጠፋም፥ ከቤት ወደ ቤት የሚያዞረኝ አባዜ ግን አብሮኝ ቀጥሏል"

“የመስቀል ወፍና ትልቅ ዲፎ ዳቦ
የበአል ቀንና ማንአልሞሽ ዲቦ
ቀጠሮ እንዳላቸው ማን ያውቃል?

( ገጣሚ፥ መንግስቱ ሀይለማርያም)

መልካም አውዳመት ፤ በጎ ዘመን ይሁንላችሁ!

https://t.me/matter_of_facts

በውቀቱ ስዩም፣ አሌክስ አብርሃምና ሌሎችም

30 Aug, 11:38


አዝመራው
(በእውቀቱ ስዩም)

አንድ ዲያስፖራ ጓደኛ ነበረኝ፤ ስለኢትዮጵያ ባወጋ ቁጥር “ያገሬ ሴቶች እሸት እኮ ናቸው ‘ ይላል፤ “ ፈጣሪየ! ከአገሬ እሸቶች አንዷን መርቀህ ስጠኝ” እያለ እንደሚጸልይ ሁሉ አጫውቶኛል፤ አንድ ቀን ከአሜሪካ ወደ አገሩ ገብቶ ፥ከአየር ማረፍያ ወደ እናቱ ቤት በታክሲ እየሄደ ነው፤ ባጋጣሚ በወቅቱ፥የሴቶች ታላቅ ሩጫ ቀን ነበር፤ የመዲናይቱ ቆነጃጅት በሙሉ አረንጓዴ ማልያና ቁምጣ ለብሰው አስፓልቱን ሞልተው ይሮጣሉ፤ አጅሬ ታክሲው ውስጥ ሆኖ እያየ አሁንም አሁንም ምራቁን ሲውጥ ከቆየ በሁዋላ እንዲህ አለ፤

“ ጌታየ ሆየ ቸርነት አያልቅብህ! አንዲት እሸት ስለምንህ አዝመራው መሀል ጣልኸኝ”

ትናንትና ወደ ወደ ፒያሳ ወክ ሳደርግ አራትኪሎ አስፓልት ላይ ከመቶ እማያንሱ ቆነጃጅት ባለ አበባ ቀሚስ ለብሰው አሸንዳ ይጨፍራሉ፤ ልቀላቀላቸው ፈለግሁ፤ ግን “እኔጋ ና እኔ ጋ ና” እያሉ እንዳይጣሉብኝና ፤ መንግስት ባህል አሸበርህ ብሎ እንዳይከሰኝ ሰጋሁ፤ ያም ሆኖ በስሜት ተነድቼ በመካከላቸው ራሴን አገኘሁት፤

ሴቶቹ ድንገት ተጠቃቀሱና ጭፈራቸውን አቆሙ፤

ዋናዋ አቀንቃኝ “ይቅርታ! ወንድ መጨፈር አይችልም” አለቺኝ፤

“ ከበሮ በመምታት እህቶቼን እንዳገለግል ይፈቀድልኝ “ አልኳት፤

“ ከበሮ የሚመቱ በቂ እህቶች አሉን” አለች ክርር ባለ ድምጽ፤

“እሺ ለለውጥ ያክል ክራር እየመታሁ ወይም እምቢልታ እየነፋሁ ላጅባችሁ”

ሴቶቹ በህብረት ገላመጡኝና እየጨፈሩኝ ትተውኝ አለፉ፤

የእርመን ቤተክሲያን አካባቢ ሲደርሱ በእግረኛ መንገድ ሳይክሌን እየጋለብኩ ደረስኩባቸው ፤

“ችግርህ ምንድነው?’ አለችኝ አቀንቃኚዋ፤

”ምን አጠፋሁ?”

ልጇን እንደምትመክር እናት ጎንበስ ብላ፤ እንሶስላ የሞቀ መዳፏን ተከሻየ ላይ ጭና ፥
“ አሸንዳ የሴቶች በአል ነው፤ ወንድ አይደባለቅበትም ፤ አይገባህም?” ብላ ጮኸችብኝ፤

“ ሽልማት መስጠትስ አልችልም? ”አልኳት፤

“ ወደ ቤትህ ሂድና ሽልማቱን በእህትህ ላከው “

https://t.me/matter_of_facts