Hulu Addis Radio Show, Bisrat FM 101.1

@huluaddi1


ሁሉ አዲስ በብስራት ኤፍ.ኤም 101.1 ማክሰኞ እና ሀሙስ ከ10-12፤ አርብ ከ8-10 ሰዓት የሚቀርብ የመረጃ፣ የመዝናኛ እና የቁምነገር ፕሮግራም ነው

Hulu Addis Radio Show, Bisrat FM 101.1

21 Jan, 00:26


በመርካቶ ሸማ ተራ እሳት ቃጠሎውን ተንተርሶ 33 ግለሰቦች ዝርፊያ ሲፈፅሙ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ ።

በ9 ሰዎች ላይ የጤና ጉዳት ደርሷል ብሏል ።

በመርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ የደረሰውን የእሳት አደጋ መንስኤ እየመረመርኩ ነው - የአዲስ አበባ ፖሊስ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሸማ ተራ ነባር የገበያ ማዕከል እና በአካባቢው በደረሰ የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ገልጿል፡፡

የአደጋውን መንስኤ ለማጣራት የአዲስ አበባ ፖሊስ ከፌዴራል ፖሊስ የፎረንሲክ ምርመራ ቡድን ጋር በመቀናጀት ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።

አደጋውን ለመከላከል እና በአደጋው ምክንያት ሌላ ወንጀል እንዳይፈፀም እንዲሁም የአደጋ ተከላካይ ሰራተኞች ተግባራቸውን በአግባቡ መወጣት እንዲችሉ እና ተጨማሪ ጉዳት እንዳያጋጥም የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የመከላከያ ሠራዊት፣ ሪፐብሊካን ጋርድ፣ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የሠላምና ፀጥታ መዋቅር፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ሌሎች ተቋማት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ አደጋው እንዳይባባስ ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸውን ጠቁሟል፡፡

አደጋውን እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 33 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን እና ከአደጋው ጋር በተያያዘ በ7 ሰዎች ላይ ቀላል በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱንም አመላክቷል፡፡

አደጋውን ለመከለከል የፀጥታና ሌሎች ተቋማት እንዲሁም የአካባቢው ህብረተሰብ ላደረገው ድጋፍ እና ተባባሪነትም ፖሊስ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ በደረሰው የእሳት አደጋ የተሰማውን ሃዘን ገልፆ ወደ ፊት በምርመራ የደረሰበትን ውጤት ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግም ገልጿል፡፡

Hulu Addis Radio Show, Bisrat FM 101.1

21 Jan, 00:26


3 ሚልየን ብር ወጪ የተደረገበት "ዳናሽ" የተሰኘ ፊልም ለዕይታ ሊበቃ ነው

በኢነርጂ ፊልም ፕሮዳክሽን እና በቆንጆ ፒክቸርስ ተዘጋጅቶ በየሚ ፊልም ፕሮዳክሽን አማካኝነት ለሕዝብ ለመቅረብ የተሰናዳው በዓይነቱ ለየት ያለና ጠንካራ ሃሳብ ይዞ የመጣው ከፍተኛ ወጭ የወጣበት "ዳናሽ" የተሰኘው ፊውቸር ፊልም ጥቅምት 19 በአለም ሲኒማ ይመረቃል ሲሉ በዛሬው ዕለት አዘጋጆቹ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል።

"ዳናሽ" የተሰኘው ፊውቸር ፊልም የተለያዮ አንጋፋ እና ጀማሪ ተዋንያን የተሳተፉበት የፍቅር ፊልም ሲሆን ከቅድመ ዝግጅት አንስቶ 2አመት የፈጀ ሲሆን ቀረጻውን ለማድረግ 24 ቀናት ወስዷል :ፊልሙንም ለመስራት በአጠቃላይ 3ሚልየን ብር ወጪ የተደረገ ሲሆን 120 ተዋንያን ተሳትፈውበታል የፊልሙም ርዝማኔ 1ሰአት ከ46 ደቂቃ መሆኑ ተጠቁሟል ።

በ ፊልሙ በተዋናይነት ኤደን አይሸሹም፣ሄኖክ በሪሁን፣ጌታቸው ስለሺ፣አልማዝ አበበ እና ሌሎችም ሲሳተፉ በኤዲተርነት ዳንኤል ቴዎድሮስ እንዲሁም በሲኒማቶግራፊ ዳንኤል ግርማ እና ቃለአብ መንግስቱ ተሳትፈዋል።

ኢነርጂ ፊልም ፕሮዳክሽን ከዚህ ቀደም የፕሮዳክሽን ደረጃቸው ከፍ ያሉ በርካታ የጥበብ ሥራዎችን ለሕዝብ በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን በተለይ በቅርቡ ከሠራቸዉ ሥራዎች መካከል ለመጥቀስ ያህል እንደ አበባዬ የመሳሰሉ የሚውዚክ ቪዲዮ የፕሮዳክሽን ሥራዎችን ለሕዝብ እይታ በማቅረብ ይታወቃል፡፡

የሚ ፒክቸርስ በበኩሉ የተለያዩ ፊቸር ፊልሞችን እና በዲ ኤስ ቲቪ የተላለፉ ተከታታይ ፊልሞችን ለህዝብ አድርሷል፡፡ በቅርቡ ከሰራቸዉ ስራዎች መካከል "ቀይ መስመር" ፊልም ከተከታታይ "ደሞ ያለለት" አሰናድቶ ለእይታ አቅርቧል፡

Hulu Addis Radio Show, Bisrat FM 101.1

21 Jan, 00:26


የቡርኪናፋሶ ''በረከተ ገበሬዋ''

ይህች ልጅ ስዋሚድዋ ሀቢዳዲ ትባላለች ሀገሯ የቶማስ ሳንካራዋ ቡርኪናፋሶ 🇧🇫🇧🇫

ገበሬ ነች ። ወላጆቿ ከሞቱ በኋላ በ16 ዓመቷ ግብርና ጀመረች።

ከትምህርት ይልቅ እርሻን መረጠች ፤ ከቤተሰቧ በውርስ ያገኘችውን 6 ሄክታር መሬት ''አሸሼ ገዳሜ ብላ አላጠፋችውም ''። 6 ሄክታር መሬቷን ለተለያዩ አዝርዕት እና ፍራፍሬ ከፋፍላ አሳረሰች ። ሩዝ፣ በቆሎ፣ ባቄላ፣ አኩሪ አተር እና ፍራፍሬ እና ሌሎችንም ዘራች ።

ከወላጆቿ የተረከበችውን 6 ሄክታር መሬት ለእርሻ ብቻ አዋለችው ። መሬቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ ዋና የገቢ ምንጭዋ ሆነ ።

ስዋሚድዋ በዚህ አመት 10,000 ከረጢት በቆሎ፣ 8,000 ከረጢት ሩዝ እና 5,000 ከረጢት የተፈጨ ለውዝ ሰበሰበች።

ከ900 በላይ ከብቶች፣ 500 ፍየሎች አልዋት ። 20 ወንድ እና 20 ሴቶች ቀጥራ ታሰራለች ። በቀላሉ ለማልማት የሚያስችል ትራክተርም አላት።

ከጋዜጠኛው ጋር ቆም ብላ ስታወራ Vx hilux መኪናዋን ተደግፋ ነው ። ከዚህ ተሽከርካሪ ሌላ እንደ 4 BMW፣ 2 Mercedes Benz wagon እና 3 range Rover መኪኖች አሏት። ለእያንዳንዱ ሰራተኛ 40 ሞተር ሳይክል ገዝታለች ።

በአሁኑ ጊዜ በአካባቢዋ የበጎ አድራጎት በስፋት ትሳተፋለች ። መብራት ቧንቧ ውሃ ለአካባቢዋ አስገብታለች ። ለበርካቶች እንጀራ እንዲወጣላቸው ምክንያት ሆናለች ።

#BurkinaFaso
#swamidwa #Habidadi

Hulu Addis Radio Show, Bisrat FM 101.1

21 Jan, 00:25


የደመወዝ ጭማሪ ተፈቅዶና በጀቱም ጸድቆ ክፍያው ከጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም.  ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ዛሬ አሳውቋል።

ከገንዘብ ሚኒስቴር የተፈቀደው በጀት፣ የአፈጻጸም መመሪያውንና የክፍያ ትዕዛዙን ለ12ቱ ክልሎች፣ ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችና ለፌደራል ተቋማት ዛሬ መተላለፉም ተገልጿል።

(ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይፋዊ የደመወዝ ስኬል ከላይ ተያይዟል)

Hulu Addis Radio Show, Bisrat FM 101.1

21 Jan, 00:24


ጅቦች የተወኑበት ፊልም ይመረቃል ።

ዛሬ በአለም ሲኒማ አዲስ ፊልም ይመረቃል ።

የፊልም ባለሙያው ፍፁም ካሳሁን እንደተናገረው ጅቦችም ተውነውበታል ። አንዴት ከተባለ ዛሬ ወደ አለም ሲኒማ ጎራ ብሎ 'የተረገመ ልጅ '' ፊልምን መመልከት ነው ።

ንጉሱ ሙሉጌታ ፣ወለላ አሰፋ፣ ማስተዋል ወንደሰን፣ዳዊት አባተ ፣ ዘላለም ይታገሱ እና ሌሎቹም ተሳትፈውበታል ።
በንጉሱ ሙሉጌታ ተደርሶ ሮቤል ሙሉጌታ ከዳይሬክቲንግ ጀምሮ በብዙ መልኩ አቅሙን አሳይቶበታል ። ።
''መቼ ነው ግን ሰውን ሳይሆን ፊልምን የምንደግፈው '' ብሎ የሚጠይቀው ፍፁም ካሳሁን ፊልሙን እንድትመለከቱ ጠቁሟል ።

የተረገመው ልጅ!‌‌

Hulu Addis Radio Show, Bisrat FM 101.1

21 Jan, 00:22


የአፍሪካ ጉባኤ አዳራሽ እድሳት ተጠናቀቀ
----------
የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን ቀደምት መሪዎች የመሰረቱበት የአፍሪካ አዳራሽ ( Africa Hall ) የተሰኘው ህንፃ ሲደረግለት የነበረው ጥልቅ እድሳት ተጠናቆ ለምርቃት ተዘጋጅቷል።

በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ( UECA) ውስጥ የሚገኘው አዳራሽ የቀድሞ መለያውን እና ታሪካዊነቱን እንደጠበቀ እድሳት ተደርጎለታል።

ከመንግስታቱ ድርጅት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እድሳቱ ተደርጓል።

የመላው አፍሪካ ታላቅ የታሪክ ማዕከል የሆነው የአፍሪካ አዳራሽ የታዋቂው ኪነ ህንፃ  ጠቢብ አርቱሮ ማዜዲ ሃሳብ ውልድ እና ከቁንጮ ስራዎቹ አንዱም ነው።

እአአ በ1961 በንጉስ አፄ ሃይለስላሴ የተገነባ ሲሆን በውስጥ የሎሬት አፈወርቅ ተክሌ እና ሌሎች የአፍሪካ ምርጥ ሰዓሊያንን ስራዎች ይዟል።

አዳራሹ በቀጣይ ሳምንት የኢትዮጵያ መሪዎች እና የተመድ ከፍተኛ ሃላፊዎች በተገኙበት ይመረቃል።