ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት @finottebiirhan Channel on Telegram

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

@finottebiirhan


የአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ለማንኛውም ጥያቄ
@Finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት (Amharic)

የአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ለማንኛውም ጥያቄ በልዩ በዓላት፣ የህይወት ቤተክርስቲያን እና ሰንበት ትምህርት ላለው ቤተክርስቲያን በፊኖትህ ይሁን። ምክንያቱም ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት፣ ህይወት ቤተክርስቲያን፣ ትምህርት እና አገልግሎቶች ከመሆን በቀላሉ ማድረግ የሚሻል ነው። እናትህን ለሕይወት መንገደቅደም እና መናገሩን ለግንባታ ሃይሌ እንዲሰጡ ሊሰጥ ነው። ስለዚህም ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት @Finotebrhan ለአስተማሪ ተጠቃሚነትን እና መሹን በትክክል ታማኝ ፎቶዎች እንድናገኝ መረጃዎችን እንዲሁም ለአሁን ሊቀርብ እና ሊከብሩ ያሉ ፎቶዎችን በይዞና ይመልከቱ።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

07 Feb, 14:39


ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ መዝ 121-1
            #ፍኖተ_ሕይወት
መንፈሳዊ የሕይወት ጉዞ ወደ ፈታሔ ማኅጸን ካራ ደጋ ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተ-ክርስቲያን
#ባሉበት_ሆነው_ጉዞውን በኦንላይን_ይመዝገቡ_ጉዞውን_ይጓዙ
@finotebirhanbot

የአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡https://www.youtube.com/@finotebirhan328
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@finotebrhan

🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡

https://t.me/finottebiirhan
@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

07 Feb, 13:07


የጾመ ነነዌ የሦስት ቀን ምህላ እና የጸሎት መርሐ ግብር ።

በየዓመቱ ከዐብይ ጾም አሥራ አምስት ቀን ቀድማ በናፍቆት  በበረከት የምትፈጸመው ጾመ ነነዌ የፊታችን ሰኞ የፊታችን የካቲት 3 ይጀመራል ።

ይኽችን የበረከት ጾም በቅዳሴው በሥራ እና በትምህርት እንዲሁም በልዩ ልዩ ምክንያት መገኘት ላላቻሉት ጭምር በቤተክርስቲያን በሰርክ ሰዓት እንዲያሳልፉ በማለም የደብሩ ስብከተ ወንጌል ክፍል ሦስቱንም ተከታታይ ቀናት የምህላና የጸሎት መርሐ ግብር ያከናወናልና ከቀኑ 10 ሰዓት ተኩል ጀምሮ በመገኘት እንድትሳተፉ መንፈሳዊ ጥሪ ያስተላልፋል ።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

06 Feb, 10:48


ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ መዝ 121-1
            #ፍኖተ_ሕይወት
መንፈሳዊ የሕይወት ጉዞ ወደ ፈታሔ ማኅጸን ካራ ደጋ ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተ-ክርስቲያን
#ባሉበት_ሆነው_ጉዞውን በኦንላይን_ይመዝገቡ_ጉዞውን_ይጓዙ
@finotebirhanbot

የአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡https://www.youtube.com/@finotebirhan328
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@finotebrhan

🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡

https://t.me/finottebiirhan
@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

06 Feb, 06:19


ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ መዝ 121-1
            #ፍኖተ_ሕይወት
መንፈሳዊ የሕይወት ጉዞ ወደ ፈታሔ ማኅጸን ካራ ደጋ ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተ-ክርስቲያን
#ባሉበት_ሆነው_ጉዞውን በኦንላይን_ይመዝገቡ_ጉዞውን_ይጓዙ
@finotebirhanbot

የአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡https://www.youtube.com/@finotebirhan328
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@finotebrhan

🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡

https://t.me/finottebiirhan
@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

04 Feb, 19:48


የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ

የሰንበት ት/ቤታችን 45ኛ ዓመት 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ  የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም በ10:00 የሚካሔድ በመሆኑ የነባርና የመደበኛ አባላት በሙሉና ከካልዓይ በላይ የሆናችሁ የተከታታይ ትምህርት ተማሪዎች በዕለቱ በሰዓቱ በሰንበት ትምህርቱ ቤቱ አዳራሽ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

03 Feb, 17:20


ተለቀቀ!!!

💧💧#" ጉህና ቃሉ "💧💧

        
አዲስ የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር በሰንበት ት/ቤታችን የሕጻናት እና ማዕከላውያን መዘምራን  በቅርብ ቀን በሰንበት ትምህት ቤቱ የዩቲዩብ ቻናል ተለቀቀ።
https://youtu.be/A3Bxco1TE7M?si=BMPRRnRD-yKHwx8L

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

02 Feb, 12:40


ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡" ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት

ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤ/ክ  በሥርዐተ ቤተክርስቲያን ጋብቻችሁን  የፈጸማችሁ  የሰ/ት/ቤታች አባል  ወ/ሮ ወይንሸት አበራ እና አቶ አብርሃም ለገሠ የፈጸማቹት  ጋብቻ የአብርሃምንና የሣራን ፤ የይሰሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ ፤ ቅዱስ ዮሐንስ ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡

" ጋብቻ ንጹሕ ነው የወንድና የሴት አንድ መሆንንም እግዚአብሔር አክብሮታል "
                          መጽሐፈ ዲድስቅልያ


ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

30 Jan, 08:28


💧💧💧💧💧💧
በቅርብ ቀን ይጠብቁን
         

💧💧#" ጉህና ቃሉ "💧💧
አዲስ የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር በሰንበት ት/ቤታችን የሕጻናት እና ማዕከላውያን መዘምራን  በቅርብ ቀን በሰንበት ትምህርት ቤቱ የዩቲዩብ ቻናል ይጠብቁን።

💧💧💧💧💧
#Share
#Share
#Share
#Share

💧💧💧💧💧💧
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
💧💧💧💧💧💧

   ▭▭▭ ◎◎◎ ⃟ ◎◎◎ ▭▭▭

🔎ፌስቡክ ገፅ፡ https://www.facebook.com/finotebrhans

🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/@finotebirhan328

🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@finotebrhan

🔎ቴሌግራም ገፅ ለትምህርትና መረጃዎች፡ https://t.me/finottebiirhan

💧💧@finotebrhan💧💧

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

30 Jan, 07:37


የአስተርዮ ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል የሰርክ ጉባኤ በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን  ።

ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ


▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭
🔎ፌስቡክ ገፅ https://www.facebook.com/finotebrhans
@finote brhan
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

29 Jan, 14:30


የአስተርዮ ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን  ።

ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ


▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭
🔎ፌስቡክ ገፅ https://www.facebook.com/finotebrhans
@finote brhan
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

29 Jan, 14:09


እንኳን አደረሳችሁ የሚባልለት ሞት

ማንም ሰው እናትኽ ለሞተችበት ቀን እንኳን አደረሰኽ ቢሉት ሐዘን እንጂ ደስታ አይሰማውም።
የቅዱሳን ሞት ግን ነቢዩ ዳዊት እንደነገረን"በእግዚአብሔር ዘንድ የከበረ ነው" የቅዱሳኑ ሞት እንዲኽ ክቡር ከኾነ
አምላክ ሰው የኾነባት የድንግል ማርያም ሞት ከሌሎች እንዴት የከበረ ይኾን?
ክቡር ስለኾነ ክብር እናገኝበታለን:: https://www.youtube.com/watch?v=slVbrNbDHzs&t=251s

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

26 Jan, 01:55


የንግስ በዓል ጥሪ

አስተርእዮ ማርያም

በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን
 
   አይቀርም
 
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ

▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭
🔎ፌስቡክ ገፅ https://www.facebook.com/finotebrhans
@finote brhan
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡https://t.me/finottebiirhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

25 Jan, 19:04


ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ መዝ 121-1

መንፈሳዊ የሕይወት ጉዞ ወደ ፈታሔ ማኅጸን ካራ ደጋ ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተ-ክርስቲያን
@finotebrhan

የአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት በአብይ ፆም ወቅት የሚያዘጋጀው የፍኖተ ሕይወት (የሕይወት መንገድ) መንፈሳዊ ጉዞ የመጀመሪያውን መርሃ ግብር ወደ ፍቼ ደብረ ፅጌ ቅድስት ማርያም ሁለተኛውን ወደ አዳዲ ቅድስት ማርያም ገዳም እና  ሦስተኛውን ወደ ታሪካዊውና ጥንታዊው ገነተ አምባ ቅዱስ ሚካኤል መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና ቅድስት አርሴማ ቤ/ን  ገዳም በማድረግ ድንቅ የበረከት ጊዜ ማከናወኑ ይታወሳል፡፡
@finotebrhan

እነሆ አሁን ደግሞ አራተኛውን ዙር መርሐ ግብር የካቲት 30 ወደ ፈታሔ ማኅጸን ካራ ደጋ ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተ-ክርስቲያን ያደርጋል።
@finotebrhan

በቦታው የተደረጉ እና እየተደረጉ ያሉ ተዓምራት
፨ በቦታው እየተጸለየበት የሚታጠነው እጣን ለበርካቶች ከብዙ ህመሞች አድኗቸዋል።
፨ ፈታሄ ማህጸን እየተባለ የሚጠራው የቅድስት ሥላሴ ጸበል ስንጠመቅ በተለየ መልኩ ሰውነታችን ላይ ሲያርፍ የደስታ እና
የመንፈሳዊ ምናብ ዓለም እንዲያሰማን በማድረግ በ ለሆሳስ ከበሽታችን የምንድንበት ዝምተኛ ፈዋሽ ጸበል ነው። የቅድስት
አርሴማንም ፈዋሽ ጸበል በውስጡ ይዟል።
፨ በ ቅ/ት ሥላሴ የሚደንቅ ተዓምር በ ስሩ በሚገኘው አስፋልት እየተጓዙ በነበሩ የውጭ ሃገራት ዜጎችን (ፈረንጆች) የጫነ
መኪና ጸበሉ ጋ ሲደርሱ አልንቀሳቀስም በማለቱ ወርደው አካባቢውን ሲያጠኑ ጠይቀው ከተረዱ በኋላ በድርጅታቸው
አማካኝነት ከ ኢትይጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ጋር ተነጋግረው ያለምንም የደብሩ ተጨማሪ ወጪ ዘመናዊ በሆነ መልኩ
ሁለቱንም ጸበል ቤቶች ሰርተው ኣስረክበዋል።  እና ሌሎችም

በመሆኑም የዚህ ታላቅ መንፈሳዊ እና የበረከት ጉዞ ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ ሰንበት ትምህርት ቤት ጥሪዋን ታቀርባለች።
@finotebrhan

የአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡https://www.youtube.com/@finotebirhan328
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@finotebrhan

🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡

https://t.me/finottebiirhan
@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

24 Jan, 07:57


#ትኬቱን_እገዛለሁ
#፬ኛውን_ዙር_ፍኖተ_ሕይወት_ጉዞ_እጓዛለሁ
#profile picture
#add to story
#timeline
#state update

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

24 Jan, 07:48


#ትኬቱን_እገዛለሁ
#፬ኛውን_ዙር_ፍኖተ_ሕይወት_ጉዞ_እጓዛለሁ
#profile picture
#add to story
#timeline
#state update

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

23 Jan, 15:14


"ፕሮፋይል ፒክቸር" የመቀየር ቻሌንጅ!!!
ሁላችንም ይህንን ፎቶ በሁሉም የማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን "ፕሮፋይል ፒክቸር" በማድረግ ፍኖተ ሕይወት ቁጥር ፬ መንፈሳዊ ጉዞን እናስተዋውቅ!

@finotebirhanbot

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

20 Jan, 17:36


የ2017 ዓ.ም የበዓለ ከተራ ጥምቀትና ቃና ዘገሊላ አከባበር አስመልክቶ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ጽ/ቤት መልዕክት::

እንደወትሮው ሁሉ የ2017 ዓ.ም የከተራ የጥምቀትና ቃና ዘገሊላ በዓላት በረድኤተ እግዚአብሔር በሃይማኖታዊ ሥርዓቱና በትውፊቱ መሠረት አክብረናል።
ከሁሉ በፊት ጠብቆ ያደረሰን በበዓላቱም በሁሉ በኩል የረዳንን እግዚአብሔርን እናመሰግናለን።
በመቀጠልም:-
* የአቃቂ ቃሊቲ ወረዳ ቤተክህነት ጽ/ቤት
* የደብራችን የሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት
* መላው የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት
* የንዑሳን ክፍላት አባላት በተለይም የመዝሙርና ዜማ :የህጻናትና ማዕከላውያን : የምክርና ሥርዓት : የመገናኛ ብዙኃን : የአካባቢ ልማት
* በሁለቱም ቀናት ከ1 ሺህ በላይ የሚሆኑ አባለቶቻችንንና እንግዶቻችንን በታላቅ መስተንግዶ ያገለገሉንን የማኅበረ ፍቁራነ አኃው በእንተ ፍቅር አመራሮችና አባላት
* የማኅበረ ፍኖተ ኤማሁስና የማኅበረ ናታኔም አመራሮችና አባላት
* የአሃት ሰንበት ት/ቤት አመራሮችና አባላት
* የአቃቂ ቃሊቲ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
*የቅድመ ግቢ ጉባኤ አመራሮችና አባላት
* በገንዘብ በጉልበት በንብረትና በሙያ የተራዳችሁን የቤተክርስቲያናችን ልጆች
* ለመላው የሰበካው ምእመናን
በአጠቃላይ ከበዓሉ አስቀድሞ በበዓላቱ ወቅት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ አስተዋጽኦ የነበራችሁን ሁሉ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ጽ/ቤት በእጅጉ ያመሰግናል ድካማችሁንና አስተዋጽኦችሁን ለበረከት ያድርግላችሁ እያልን አሁንም አንድነታችንን አጽንተን ከፊት ይልቅ በትጋት የቤተክርስቲያንን አገልግሎት በጋራ እንድናፋጥን በዚህ አጋጣሚ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።
የሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት
ጥር 12 ቀን 2017 ዓ.ም

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

20 Jan, 12:21


ቃና ዘገሊላ

“በሦስተኛውም ቀን የገሊላ ክፍል በምትሆን በቃና ሰርግ ሆነ፤ የጌታችን የኢየሱስ እናትም በዚያ ነበረች። ጌታችን ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ። ...” ዮሐ.፪፥፩-፲፩

እንኳን አደረሳችሁ!


ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ


▭▭▭ ◎◎◎ ⃟ ◎◎◎ ▭▭▭

🔎ፌስቡክ ገፅ፡ https://www.facebook.com/finotebrhans

🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/@finotebirhan328

🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@finotebrhan

🔎ቴሌግራም ገፅ ለትምህርትና መረጃዎች፡ https://t.me/finottebiirhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

09 Jan, 10:21


የ2017 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ዝግጅት

አሥር ቀናት የቀሩት የብርሃነ ጥምቀቱ በዓል ቅድመ ዝግጅት እየተከናወነ ይገኛል ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዓመቱ በአደባባይ ከምታከብራቸው ታላላቅ በዓላት መካከል ቀዳሚ የሆነው ይኽ ጥር 11 የሚከበረው የጌታችንን መድኅኒታችን ኡየሱስ ክርስቶስ በየጥምቀት በዓል ነው ።

ይህ በዓል በሀገራችን በተለይም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በልዩ ሁኔታ በርካታ አድባራት እና ገዳማት በአንድነት ከሚከበርባቸው የባህረ ጥምቀት ሥፍራዎች መካከል የአቃቂ ባህረ ጥምቀት  ማክበሪያ ሥፍራ ነው ።

ባሳለፍነው ዓመት 44 ታቦታት በአንድነት ያከበሩበት ሲሆን ዘንድሮም እንዲሁ የሚከበር ይሆናል ። የበዓሉ ቅድመ ዝገጅት ቀድሞ የተጀመረ ሲሆን በየአድባራቱ ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ።

ከእነዚህ ተግባራት መካከል ይህ ከበዓሉ አስቀድሞ የሚተገበረው የጽዳት ሥራ ነው ። ከእያንዳንዱ አድባራት እስከ ባህረ ጥምቀት የሚከወን ሲሆን በደብራችን በየዓመቱ ይህንን ትልቅ ተግባር የሚፈጽሞ በሰንበት ትምህርት ቤታችን ሥር ታቅፈው የሚገኙት የፍኖተ ኤማሁስ ወጣቶች መንፈሳዊ ማኅበር አባላት በዛሬው ዕለት ታቦታታ የሚወርዱበት ጎዳናዎች የማጽዳት የማስተካከል ሥራ ሲከወኑ አርፈደዋል ። በቀጣይ በቀሩት ቀናትም ይሄው ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ።

እግዚአብሔር አምላክ ለወንድሞቻች የደጁን በረከት ያድልልን !!

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

07 Jan, 03:24


#አእላፋትዝማሬ #TheMelodyofMyriads

በአዲስ አበባ አእላፋት የተሳተፉበት " የአእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads " መርሐግብር በቦሌ በድብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ተከናውኗል።

ይህ ዘንድሮ ለ2ኛ ጊዜ የተከናወነው መርሐግብር ከአምናውን የላቀ የምእመን ቁጥር የተገኘበት እንደሆነ በስፍራው በመገኘት ለመገንዘብ ችለናል።

መርሐግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት እንዲሁም ብፁአን አባቶች ተገኝተው ነበር።

የዝማሬና የምስጋና መርሐግብሩ የልደት በዓልን በማይገባ ቦታ የሚያሳልፉ በእግዚአብሔር ቤት ሆነው እንዲያሳልፉ ለማድረግ ዓላማ ያነገበ ነው።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

07 Jan, 03:14


ወደ ልባችን እንመለስና በፍቅር፣ በዕርቅና በእኩልነት፣ በስምምነትና በወንድምነት ወደሚገኝ አንድነት እንምጣ፤ የልደቱ መዝሙር ያስተማረን ይህና ይህ ብቻ ነው፡፡

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ፤
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፤

በምሉእ ፍቅሩ ሰውን ከባርነት ወደ ነጻነት ለመመለስ በሥጋ ሰብእ የተወለደው ጌታችን  ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ፡፡

“ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዘሠምሮ ለሰብእ፤ ክብር በሰማያት ለእግዚአብሔር ይሁን›› በምድርም እጅግ ለወደደው የሰው ልጅ ሰላም ይሁን” (ሉቃ ፪÷፲፬)
ይህ ቃለ ሰላም በጌታችን ዕለተ ልደት የተነገረ ነው፣ ቃሉ የተነገረው እንዲሁ እንደ ተራ ነገር ሳይሆን በቃለ መዝሙር እየተደጋገመ ነው፡፡ የተዘመረውም በምድራውያን ደራሲዎች ሳይሆን በሰማያውያን መላእክተ እግዚአብሔር ነው፣ የያዘው መልእክትም ሰማያውያንና ምድራውያንን ሁሉ ያካለለ ነው፡፡ የመልእክቱ ገዢ ሓሳብም አምላክ ከሰውነታችን ጋር ባለመለያየት፣ ባለመጠፋፋት፣ ባለመቀላቀል፣ ባለመዋዋጥ፣ ባለመለዋወጥና ያለባዕድና አንድ አካል፣ አንድ ክዋኔ፣ አንድ ጠባይ ሆኖ በተዋሕዶ ተገልጾኣልና እግዚአብሔር ይክብር ይመስገን፡፡ የተዋሕዶውም ምስጢር ሰላምን ያሰፍናልና እግዚአብሔር ሰውን በእጅጉ መውደዱ ከዚህ ተዋሕዶ ዓውቀናል የሚል ነው፡፡

በእርግጥም እግዚአብሔር ሰውን ለመውደዱ ከዚህ የበለጠ ማሳያ ወይም ማስረጃ የለም፤ እንከን የለሽ ንጹህ አምላክ የእኛን ኃጢአተኛ ሰውነት አካሉ አድርጎ ተወለደ ሲባል ላስተዋለው ሰው ምንኛ ቢወደን ነው የሚለው ጥልቅ አድናቆትን ያጭራልና ነው፡፡ይህ ብቻም አይደለም በዚህ ነገረ ተዋሕዶ ምክንያት ሰውነታችን አምላክ ሆኖ በመንበረ ጸባኦት እንዲቀመጥ መብቃቱ የድኅነታችንና የክብራችን ከፍታ ምን ያህል አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንደደረሰ መንፈሳችን በአንክሮ ይረዳዋል፡፡ድምር ውጤቱም በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ፍጹምና አስተማማኝ ሰላም መፈጠሩን ያስረዳናል፤ ሰማያውያኑ መላእክተ እግዚአብሔር በመዝሙራቸው ያበሰሩን ይህንን የምስራች ነው፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

እኛ ክርስቲያኖች እግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ እግዚአብሔር በእጅጉ ይወደናል ስንል እንዲሁ ከሜዳ ተነሥተን ኣይደለም፡፡ በበደላችንና በኃጢአታችን ሳይጸየፈን ሰውነታችንን በረድኤት ወይም በኅድረት ያይደለ በኩነት ተዋሕዶ ወደ አምላክነት ደረጃ ከፍ ስላደረገው  ነው እንጂ፡፡ እግዚአብሔር በዚህ ፍጹምና ምሉእ ፍቅሩ ሰውነታችንን በመበረ ጸባኦት ኣስቀምጦ መላእክት ሳይቀሩ ፍጥረታትን በሙሉ እንድንገዛ አድርጎናል፤ ምክንያቱም መላእክት በዕለተ ልደት የዘመሩለት በተዋሕዶ አምላክም ሰውም ለሆነ ለቤተ ልሔሙ ሕፃን እንጂ ለመለኮት ብቻ ኣይደለምና ነው፡፡ የዕለተ ልደት መዝሙር ዛሬም በሰማያትም ሆነ በምድር በተዋሕዶ ሰውም ኣምላክም የሆነ አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመለክበታል፣ ይመሰገንበታል፡፡የሰማዩና የምድሩ ዕርቅ ወደ ኋላ ላይመለስ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በዚህ ተከናውኖኣል፣ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሰውም አዋጭ ምርጫ ይህ ዕርቅ ተጠብቆ እንዲኖር ነው፣ ያለ ዕርቅ ሰላም ሕይወት የለውምና፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

የእግዚአብሔር ክብርና ሰላም በእጅጉ የተሳሰሩና የተቆራኙ ናቸው፤ እኛ እግዚአብሔርን ካከበርነው፣ ካዳመጥነው፣ ከታዘዝነውና ከተከተልነው ሰላም አለ ማለት ነው፡፡ ለሱ ካልታዘዝንና እሱን ካላከበርን ግን ዘላቂ ሰላምን ማግኘት ፈጽሞ የማይታሰብ ነው፤ ምክንያቱም ሰላምን ጨምሮ መልካም ነገር ሁሉ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ነውና፡፡ ዛሬ በሁሉም የዓለማችን ማዕዘን የሚታየው የሰላም መደፍረስ እግዚአብሔርን ካለማክበራችንና ለሱ ካለመታዘዛችን የተነሣ እንደሆነ መዘንጋት የለብንም፡፡ ዓለም ከእግዚአብሔር ቃል ርቃ ለመሄድ በእጅጉ እየኳተነች ነው፤ በዚህ እኩይ ተግባርዋ ደግሞ እግዚአብሔር ለስጋትና ለጉስቁልና አሳልፎ እየሰጣት ነው፡፡ እግዚአብሔር በምስጢረ ሥጋዌው ቢታረቃትም ዕርቁን ማክበር አቅቶአታል፤ ይህንን የእግዚአብሔር ጸጋ ቸል ብላ የምታደርገው ሩጫ የትም ሊያደርሳት እንደማይችል ብታውቅና በንስሓ ብትመለስ እግጅ ተጠቃሚ ትሆናለች፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

የእግዚአብሔር ቃል “እናንተስ ከማይጠፋ ዘር ተወለዳችሁ” ብሎ ተስፋውን እንደነገረን ምድባችን ከማይጠፋ ዘር እንዲሆን ክርስቲያኖች የሆን ሁላችን በአእምሮ ጐልብተን፣ በሥነ-ምግባር ኣምረን፣ ጤናማ ሕይወትን ልንመራ ይገባናል፡፡

የአምላካችንን በዓለ ልደት ስናከብር ነገረ እግዚአብሔርን፣ ነገረ ፍቅርን፣ ነገረ ዕርቅንና ነገረ ሰላምን በማኅበረሰባችን የማሥረጽ አጀንዳ ይዘን ልናከብር ይገባል፡፡
ጠቡ ፣ ጥላቻው፣ መለያየቱ፣ መጠፋፋቱ፣ ለወንድሜ  ከማለት ይልቅ ለኔ ለኔ ማለቱ ሲጎዳን እንጂ ሲጠቅመን ኣላየንም፡፡ አሁንም ወደ ልባችን እንመለስና በፍቅር፣ በዕርቅና በእኩልነት፣ በስምምነትና በወንድምነት ወደሚገኝ አንድነት እንምጣ፤ የልደቱ መዝሙር ያስተማረን ይህና ይህ ብቻ ነውና፡፡ በሌሎቹ ክፍለ ዓለማት እንደሆነው ሁሉ በሀገራችን የተከሠተው አላስፈላጊ ግጭት ብዙዎችን አሳጥቶናል፤ ብዙዎችንም ከቤት ንብረታቸው አፈናቅሎ ሜዳ ላይ ፈሰው የሰቆቃ ኑሮ እንዲገፉ አድርጎብናል፡፡ የሀገር ሀብት እንዲወድም ሆኖአል፤ ልጆቻችን ምናለ ከእንግዲህ ወዲህ ቢበቃንና ምድሪቱን የሰላም አየር እንድትተነፍስ ብንፈቅድላት፤ ይህ የወቅቱ የቤተክርስቲያናችን ዋነኛ መልእክትና ጥሪ ነው፡፡    

በመጨረሻም፡-

በዓለ ልደት የእግዚአብሔር በዓል ነውና፣ እግዚአብሔር በምድራችን ሰላምን ያወርድ ዘንድ ካለን ከፍለን ለተፈናቃዮች፣ ለነዳያን እና ለአካል ጉዳተኞች በመለገስ በዓሉን በመንፈሳዊ ደስታና በሰላም እንድናከብር አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤

መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር  አሜን!

      አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ
ተክለሃይማኖት
ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

07 Jan, 02:55



 
 ‹‹በጐለ እንስሳ ተወድየ አሞኀ ንግሡ ተወፈየ ወከመ ሕፃናት በከየ እንዘ ይስእል እምአጥባተ እሙ ሲሳየ፤ በእንስሳት በረት ተጨመረ፤ የንጉሡንም እጅ መንሻ ተቀበለ፤ ከእናቱ ጡቶች ምግብን እየለመነ እንደ ሕፃናት አለቀሰ፤›› (ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ ቍ. ፲፯)፡፡
(ኢሳ. ፱፥፪)፡፡ 
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደቱ በሰላምና በጤና አደረሳቹ!
 
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ

▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭
🔎ፌስቡክ ገፅ https://www.facebook.com/finotebrhans
@finote brhan
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡https://t.me/finottebiirhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

06 Jan, 20:25


ታኅሳስ 27 - መድኅኔዓለም

የወርኃ ታህሳስ መድኅኔዓለም የሰርክ ጉባዔው ።

ጉባዔው በልደት ዋዜማ አባቶች በተገኙበት በጸሎት በትምህርተ ወንጌል እና በዝማሬ ተከናውኗል ።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

06 Jan, 08:29


"እናንተም አባቶች ሆይ ÷ ልጆቻችሁን በጌታ ምክርና በተግሣጽ አሳድጉአቸው እንጂ አታስቆጧቸው"  ገላ ፮÷፬

የህጻናት እና ማዕከላውያን ክፍል የተማሪዎች የቅዱስ ቁርባን የመቀበል መርሐ ግብር   ታህሳስ 27 /2017 ዓ.ም እበረድኤተ እግዚአብሔር ተከናውኗል ።

ይህም የህጻናቱ የቅዱስ ቁርባን  ዓላማው በተለያየ ምክንያት ወላጆች ልጆቻቸውን ማቁረብ ያላቻሉትን ለመራዳት ፣ ወደፊትም ህፃናቱ  ወደ ውርዝና ዕድሜ ከፍ እያሉ በሄዱ ቁጥር ወደ አበ ንሰሃ  እየቀረቡ ዘወትር እንዲቀበሉ ላማድረግና በመካከላቸው ፍቅረ እግዚአብሔር እንዲያድርባቸው በማለት መርሐ በዓመት ሁለቴ ይክናወናል ።

የመጀመሪያው በጾመ ነቢያት በመጨረሻው ሳምንት የሚከናወነው እና ተግባራዊ የተደረገው ይኽ መርሐ ግብር ነው ። ከቅዱስ ቁርባን መርሐ ግብር በኋላም በተዘጋጀላቸው ሥፋራ በማሳረፍ በአንድነት የአጋፔ መርሐ ግብር አከናውነዋል ።

ቸሩ አባታችን መድኅኔዓለም ህጻናቱን በጥበብ እና በሞገስ አሳድጎ ለከበረው ለሰማያዊ መንግስቱ ይጫቸው ።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

06 Jan, 08:05


የነባር ዓባላት ጉባዔ ተከናወነ !!

የሰንበት ትምህርት ቤታችን ነባር አባላት ጉባዔ በትናንትናው የመድኅኔዓለም ሰንበት ተከናወነ ። እነዚህ ነባር አቫላት በቀደመው ዘመን የሰንበት ትምህርት ቤቱ መደበኛ አባል ሆነው በህይወት አጋጣሚ ራቅ ያለ የመንውሪያ ሥፍራ የቀየሩ እና በልዩ ልዩ ሁኔታ መደበኛ አገልግሎቱን መሳተፍ ያልቻሉ አባላት በወሩ የመጨረሻው ሰንበት ተሰባስበው የሚያከናውኑት መርሐ ግብር ነው ።

በመርሐ ግብሩ በጸሎት በዝማሬ እንዲሁም በትምህርተ ወንጌል የተከናወነ ሲሆን እረጅም ጊዜ ተገናኝተው ያልነበሩ ወንድሞች እና እህቶች ተገናኝተው  አሁን ስላለው የሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎት እና እንቅስቃሴ መረጃም ያገኙበትም ጭምር ሆኗል ።

የቀጣይ ወር ይኽው የነባር ዓባላት ጉባኤ ጥር 29/2017 ዓ.ም ከቅዳሴ ጸሎት በኋላ በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ ይከናወናል ።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

06 Jan, 07:18



“በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።”
  — ዮሐንስ 1፥1



ከእናቱ ጡቶች ምግብን እየለመነ እንደ ሕፃናት አለቀሰ፤›› (ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ ቍ. ፲፯)፡፡

▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

05 Jan, 02:56


ሉቃስ ፩÷፴-፴፩
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
መልአኩም እንዲህ አላት፦ ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ።
እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ።
ከእናቱ ጡቶች ምግብን እየለመነ እንደ ሕፃናት አለቀሰ፤›› (ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ ቍ. ፲፯)፡፡

▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

04 Jan, 07:45


ዕለተ ናታኔም

« ሌዋውያንንም እንዲያገለግሉ ዳዊትና አለቃዎቹ በሰጧቸው ናታኒም ውስጥ  ሁለት መቶ ሃያ ናታኒም አመጡ እነዚህም በሁሉ በስማቸው ተጠሩ  ። »

የሕጻናት እና ማዕከላውያን ክፍል የዕለተ ናታኒም መርሐ ግብር አከናወነ።
የሰንበት ት/ቤታችን  የሕጻናት እና ማዕከላውያን ክፍል  ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም የዕለተ ናታኒም መርሐግብር አከናውኗል ።  በመርሐግብሩም የክፍሉ አባል ተማሪዎች በቤተክርስቲያን ዙሪያ የጽዳት ሥራ አከናውነዋል።
የእዚህ መርሐ ግብር ዓላማውም ሕጻናት ቤተክርስቲያንን እንዲሁም ሰንበት ት/ቤትን በተለያዩ አገልግሎቶች እያገለገሉ  ማደግ  እንደሚገባቸው ማስተማር ፤  የቤተክርስቲያንን እና የሰንበት ት/ቤትን ጽዳት መጠበቅ እንደሚገባ ማስገንዘብ በእድሚያቸው ልግ ከአገልግሎት ጋር እየተዋሃዱ እንዲሄዱ በተግባር ማሳየት ነው ።


የህጻናት እና ማዕከላውያን ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

04 Jan, 04:28


የነባር ዓባላት ጉባዔ !

በመደበኛው ጉባዔ መገኘት ለማይችሉ የሰንበት ትምህርት ቤታችን የቀድሞ አባላት የሚሳተፉበት በወሩ የመጨረሻው ሰንበት ጉባዔ እንደሚያከናውኑ ይታወቃል ።

የወኃ ታኅሳስ  ጉባዔም የፊታችን እሁድ  በዕለተ መድኃኔዓለም ታኅሳስ 27 በመሆኑ በተለያዩ ምክንያት እስክ አሁን መገኘት ያልቻላችሁ ወንድሞች እና እህቶች እንድትገኙ በቸሩ አባታችን መድኃኔዓለም ስም ጥሪ እናደርጋለን ።

ጉባዔው የሚከናወነው ከሥርዓተ ቅዳሴ ጸሎት በኋላ  በሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ ይሆናል ። መልእክቱ የደረሳችሁ  ለወንድሞች እና ለእህቶች በምትችሉ አማራጭ ሁሉ እንድታደርሱ ይሁን ።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

03 Jan, 18:47


ውሃ ስትቀጂ ክንፉን እያማታ
ሊያበስርሽ የመጣው በታላቅ ደስታ
ከሞገስሽ ብዛት (2) ሲታጠቅ ስፈታ
አቅርቦልሽ ነበር የክብር ሰላምታ
ከእናቱ ጡቶች ምግብን እየለመነ እንደ ሕፃናት አለቀሰ፤›› (ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ ቍ. ፲፯)፡፡

▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

03 Jan, 09:11


የግቢ ጉባዔ መርሐ ግብር

በሰንበት ትምህርት ቤታችን ሥር ከሚገኙ የትምህርት እና ሐዋርያዊ አገልግሎቶች መካከል የግቢ ጉባዔ የትምህርት መርሐ ግብር አንዱ ነው ።

ከእነዚህ የግቢ ጉባዔያት መካከል የአቃቂ አድቬንቲስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ናቸው ። በርካታ ጊዜ ያስቆጠረ ሲሆን ባሳለፍበው ጥቅምት ወር ነበር የእዚህን ዓመት መርሐ ግብር የጀመሩት ።

በሳለፍነው ሳምንትም ተማሪዎች በአንድነት ሆነ የጌታችን፡መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደትን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መርሐ ግብር ያከናወኑ ሲሆን መርሐ ግብር በጸሎት ፣ ትምህርት ወንጌል ፣ በበገና ዝማሬ እና ኪነ ጥበባዊ ትምህርቶች የተላለፈቡት ነበር ።

የጊቢ ጉባዔው መንፈሳዊ አገልግሎቱ አሁን ካለበት የበለጠ እና በርካታ ተማሪዎች ወደ ቤተ እግዚአብሔር መጥተው የሚታደሙበት እንዲሆን በሳምንት  አንድ ቀን ከሚከታተሉት ትምህርት ተጨማሪ  በየወሩ እንዲህ ያሉ ሰፊ መርሐ ግብራትም የሚከናወኑ ይሁናል ፡ ።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

31 Dec, 18:42


ለሰንበት ትምህርት ቤታችን ህጻናት እና ማዕከላውያን ክፍል አባላት  የጊዜ አጠቃቀምን በሚመለከት ስልጠና ተሰጠ ።

በሰንበት ትምህርት ቤታችን ከሚገኙ ዋና ንዑሳን ክፍላት መካከል አንደኛው የህጻናት እና ማዕከላውያን ክፍል ነው ። በእዚህ ክፍል ሥር እድሚያቸው ከሰባት ዓመት ጀምሮ እስከ አሥራ ሰባት ዓመት እድሜ ክልል የሚገኙ ታዳጊዎች የሚገኝበት ሲሆን በመንፈሳዊው በአስኳላውም ሙሉ ለሙሉ ጊዜያቸውን በትምህርት የሚያሳልፉ ናቸው ።

በሳምንቱ መጨረሻ መንፈሳዊ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከሰኞ እስከ ዓርብ ባሉት ጊዜያቶች መደበኛ የአስኳላ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ናቸው ። በእዚህም የትምህርት ህይወታቸው አጠቃላይ ውጤታማ ሁነው እንዲበቁ ያላቸውን ጊዜ ሳያበክኑ መጥነው እንዲጠቀሙበት የጊዜ አጠቃቀምን በሚመለከት በሰንበት ትምህርት ቤቱ ትምህርት እና ክፍል አማካኝነት የሰንበት  ትምህርት ቤቱ አባል እና ከፍተኛ የትምህርት ባለሙያ በሆኑት በመምህር አሳየኽን ሰብስቤ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል ።

ከእዚሁ ሥልጠና ጎን ለጎን በወሰዱ ሥልጠና ውጤታም እንዲሆን በክፍሉ አባላት እና በትምህርት ክፍል አማካኝነት ክትትል ድጋፍ ይደረግላቸዋል ።

ትምህርት እና ሥልጠና ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

31 Dec, 11:06


የህጻናት የእንኳን አደረሳችሁ መርሐ ግብር ።

በመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት  የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ እና መመሪያ ሀገር አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የጌታችን እና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደትን ምክንያት በማድረግ ታህሳስ 20 የህጻናት መርሐ ግብር ተከናወነ ።

በአቃቂ መንበረ ህይወት መድኅኔዓለም ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት በተዘጋጀው የአቃቂ ቃሊቲ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባዔ በክላስተር 4 ሥር የሚገኙ የደብራቱ ህጻናት እና  ታዳጊ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ተሳታፊውበታል ።

በእዚሁ መርሐ ግብር ትምህርተ ወንጌል ፣ ዝማሬ እና ኪነ ጥበባዊ ሥራዎች ከየደብራቱ በተውጣጡ  የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የቀረበ ሲሆን ታዳጊዎቹ እንዲተዋወቁ  እና በአንድነት የማስታወሻ የፎቶ መርሐ ግብርም አከናውነዋል ።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

26 Dec, 18:39


ትምህርታዊ ሥልጠና

በሰንበት ትምህርት ቤታችን ከሚገኙት ትምህርት ከሚሰጥባቸው ክፍላት መካከል ዋነኛው የህጻናት እና ማዕከላውያን ክፍል  ነው ።

በእዚህ ትምህርት ክፍል የሚገኙ ታዳጊ ህጻናት ከመንፈሳዊ ትምህርታቸው በተጓዳኝ በአስኳላው ትምህርታቸው ውጤታማ  ሆነው የሰንበት ትምህርት ቤት ኩራት ፣  ለቤተሰቦቻቸው ማዕረግ ፣ ለሀገር ደግሞ ተተኪ ትውልድ እንዲሆኑ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛል ።

ከእነዚህ መካከል ውጤታም የጊዜ አጠቃቀም እንዲኖራቸው ክትትል ይደረጋል ። ይሄንንም የጊዜ አጠቃቀማቸው ውጤታማ እንዲሆን ከትምህርት እና ሥልጠና ክፍል ጋር በመተባበር  የፊታችን ቅዳሜ  ታኅሳስ 19 ቀን ከቀኑ 9 ሰዓት በዕድሜያቸው የሚሆን ሥልጠና ስለሚሰጥ ወላጆች ልጆቻችሁ በሰዓቱ ወደ ሰንበት ትምህርት ቤት እንድትልኩ ።

ህጻናትና ማዕከላውያን ንዑስ ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

26 Dec, 12:30


ዐውደ ጥናት

የዐውደ ጥናቱ ርዕሰ ጉዳዮች

1ኛ. በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት መንፈሳዊ ትምህርት ተከታታይ ተማሪዎች ትንሿን ቤተ-ክርስቲያን ለመገንባት ያላቸው ትጋት፡፡

2ኛ. በኩሬው መንበረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አገልግሎትና የአጥቢያ መዕመናን ህይወት ፡፡

ዐውደ ጥናቱ የሚካሄድበት  ቦታ - በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤ/ክ አዳራሽ

ዐውደ ጥናቱ  የሚካሄድበት ቀን   - 20/04/2017 ዓ.ም.

ዐውደ ጥናቱ  የሚጀምርበትና የሚጠናቀቅበት ሰዓት  ፡-  ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡30 ሰዓት ድረስ ፡፡ 

አዘጋጅ - ጥናትና ምርምር  ንዑስ ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

26 Dec, 08:09


ዕለተ ውሂብ ታኅሣሥ 20/2017 ዓ.ም

“... ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው ወርቅና ዕጣን፥ ከርቤም፥ እጅ መንሻ አቀረቡለት።” ማቴ ፪፥፲፩

በኮከብ ተመርተው ወደ ቤተ ልሔም ምድረ ኤፍራታ የተጓዙትን የሰብአ ሰገልን ፍኖት በመከተል በፍቅር የሚከወን የወዳጅነት መገለጫ

ዕለተ ውሂብ (የስጦታ ቀን)
እንኳን አደረሳችሁ !!

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

25 Dec, 13:48


በምሥራቁ የሀገራችን ክፍል የሚገኘው ታላቁ ገዳም ቁሉቢ ደብረ ኃይል !!

በየዓመቱ ታህሳስ 19 የሚከበረው የታላቁ ገናና መላእክ ቅዱስ ገርኤል  ዓመታዊ ክብረ በዓል ይከበራል ። ይህ በዓል በመላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ገብርኤል አድባራት እና ገዳማታ በታላቅ መንፈሳዊ ክብር ይከበራል ።

ከእነዚህ ታላቅ ሥፍራዎች መካከል አንዱ እና ዋነኛው የብዙዎች ስዕለት ሰሚ የሆነው በምሥራቁ የሀገራችን ክፍል የሚገኘው የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዋነኛው ነው ።

በዘንድሮ ዓመታ ከእዚሁ ታላቅ በዓል ለመታደም የበረከቱ ተካፋይ ለመሆን በርካታ ምዕመናን ከተለያዩ የሀገራችን ክፍል በመነሳት እየተጓዙ ይገኛል ።

በሰንበት ትምህርት ቤታችን መንፈሳዊ ጉዞ ንዑስ ክፍለ በተሰናዳው የጉዞ መርሐ ግብር መሰረት በርካታ ምዕመናን በተካፈሉበት ወደ እዚሁ ታላቅ መካን ጉዞ እያከናወኑ ይገኛል ። በሰላማዊ መልካም ሁኔታ እየተጓዙ ሲሆን  ወደ እዚሁ ለምታቀኑ በሙሉ መልካም ጉዞ መልካም የበረከት በዓል ይሁንላችሁ !!

ገናናው መላእክ ቅዱስ ገብርኤል በአማላጅነቱ አይለያችሁ !!

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

25 Dec, 04:06


#ዕለተ_ውሂብ

“ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅና ዕጣን ከርቤም አቀረቡለት።” ማቴ ፪ ፥፲ ፩

ለወዳጅ ዘመድዎ ስጦታን ያበርክቱ እኛ መድረኩንም ስጦታ ማድረሱንም እንከውናለን ይዘዙን በቤተልሔም ዝማሬና የምስራች ዜና አጅበን ስጦታ እንሰጣለን።

በሞት ያጣናቸውን እንዘክራለን ፍጹም እረፍትን ያድላቸው ዘንድ እንጸልያለን በሀዘን ውስጥ ያሉትን በማጽናናት በምስራች ወንጌል እንበረታለን

ቀን ፡ ታህሳስ 20/2017 ዓ.ም
ቦታ ፡ በሰ/ት/ቤታችን አዳራሽ


👉 ስጦታ መስጠት ለሚፈልጉት አካል ይዘዙን እናደርሳለን በጉባኤም እናበረክታለን

👉 በዕለቱ ለስጦታ የሚሆኑ መጻሕፍትን በሰንበት ትምህርት ቤታችን ግቢ ውስጥ ያገኛሉ።

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

24 Dec, 05:48


ሰንበት ትምህርት ቤት !!

ሰንበት ትምህርት ቤት እድሚያቸው ከሰባት ዓመት ጀምሮ ያሉ ህጻናት ታዳጊ እና ወጣቶች በዕለተ ሰንበት ተሰብስበው የሚማሩበት መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ።

ህጻናት በመንፈሳዊ ትምህርታቸው ጎን ለጎን ላለው የአስኳላ ትምህርታቸው ጭምር ውጤታማ በመሆን ነገ ቤተሰቦቻቸውን ፣ ቅድስት ቤተክርስቲያንንና ሀገር ማገልግል  የሚችሉ እንዲሆኑ  ማድረግ የሚገባ ነው ።

ለእዚህ በሰንበት ትምህርት ቤታችን ህጻናት እና ማዕከላውያን ክፍል ፣ ትምህርት ክፍልና ቤተ መጽሐፍት ክፍል በመሆኑ ያላቸውን እውቀት  በንባብ  እንዲያሳድጉ ክትትል እና ድጋፍ ይደረግላቸዋል ።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

23 Dec, 09:17


+++በተከታታይ ትምህርት ንዑስ ክፍል አማካኝነት "ምሂረ ነዳያን" በሚል መሪ ቃል  በቤተክርስቲያኑ ደጃፎች ከምእመናን በሚያገኙት ምጽዋት የሚኖሩ ነዳያንን ማዕከል ያደረገ ልዩ ጉባኤ በረድኤተ እግዚአብሔር ዛሬ ተከናወነ። በዚህ በዓይነቱ ልዩ በሆነው ጉባኤ ከ120  በላይ ነዳያን የተሳተፉ ሲሆን ጉባኤውም በሰንበት ት/ቤቱ መዘምራን ዝማሬና በተጋባዥ ሰባኬ ወንጌል የስብከት አገልግሎት የተሰጠበት እንዲሁም ጉባኤው በሥጋም በነፍስም እንዲጠቀሙበት ታስቦ የተዘጋጀ በመሆኑ ያለውን ጠቀሜታ አውቀው በመሰባሰቡ እንዲበረቱ ግንዛቤ የተሰጠበት  በመጨረሻም የቁርስ አገልግሎት የተሰጠበት ድንቅ ጉባኤ በመሆን ተጠናቋል።ይህ ጉባኤ በእንዲህ መልኩ እንዲከናወን በገንዘብ : በጉልበት : በዕውቀት....የተራዳችሁትን ሁሉ በሰንበት ትምህርት ቤቱ ስም እያመሰገንን በቀጣይነት በየሩብ ዓመቱ የሚዘጋጅ በመሆኑ ሁላችንም በምንችለው ሁሉ እንድንደግፍ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።


የሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት
ታህሳስ 13/2017 ዓ.ም

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

23 Dec, 08:06


"የሰንበት ት/ቤታችን የትምህርት ክፍል ያዘጋጀው ምሂረ ነዳያን የተሰኘ መርሐግብር ተከናወነ።"

ታህሳስ 13/2017 ዓ.ም መ.ብ.ን

የአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የመጀመሪያውን የነዳያን ልዩ የትምህርተ ወንጌል መርሐ ግብር "ምሂረ ነዳያን" በሚል ርዕስ  ታህሳስ 13 ቀን 2017 ዓ.ም ቁጥራቸው 120 አካባቢ የሚሆኑ ነዳያን በተገኙበት በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ ተከናውኗል።

መርሐግብሩ በጸሎት ተጀምሮ በሕጻናት እና ማዕከላውያን ክፍል መዘምራን ዝማሬ እንዲሁም በመጋቤ ሐዲስ ቀሲስ ምናለ አዝናው ለእለቱ የተዘጋጀው ትምህርት ከተሰጠ በኋላ በሰንበት ት/ቤቱ ሊቀመንበር እንዲሁም በትምህርት እና ሥልጠና ክፍል ተጠሪ ጉባኤውን የሚመለከቱ መልእክቶች በማስተላለፍ እና የቁርስ መስተንግዶ በማከናወን መርሐግብሩ ተጠናቋል።

በቀጣይም ይህን የመሳሰሉ ጉባኤያትን ለማዘጋጀት መታቀዳቸውን የትምህርት እና ሥልጠና ክፍል አሳውቋል።

በመጨረሻም ለመርሐግብሩ መሳካት ልዩ ልዩ ድጋፍ ላደረጉ አካላት ክፍሉ ከፍ ያለ ምስጋናውን ያቀርባል።

የትምህርት እና ሥልጠና ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

03 Dec, 06:20


"የንስሐ ልጆች ቀን" መንፈሳዊ ጉባኤ
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን
ኅዳር 29 ቀን 2017ዓ.ም ከቅዳሴ በኋላ
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

01 Dec, 09:02


" የ ፳፻፲፯ ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት የአጋማሽ (Mid) ፈተና ተሰጠ። "

በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥርዓተ ትምህርት የዓመቱ እቅድ መሠረት የ ፳፻፲፯ ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት የአጋማሽ (Mid) ፈተና ኅዳር ፳፩ እና ፳፪ ለመስጠት ታቅዶ እንደነበር ይታወሳል፤
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤትም በእቅዱ መሠረት የመደበኛ ተከታታይ መንፈሳዊ ትምህርት የትምህርት ዘመኑ የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት አጋማሽ ፈተና ዛሬ ኅዳር ፳፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ከ ፩ኛ እስከ ፲፪ኛ ክፍል በእሑድ መርሐግብር ለሚማሩ መደበኛ ተማሪዎች ተሰጥቷል።
በቀጣይም የትምህርቱ መርሐግብር በመደበኛው መንገድ የሚቀጥል መሆኑን ለማስታወስ እንወዳለን።

ማስታወሻ!
በቅዳሜ መርሐግብር የሚማሩ ተማሪዎች አጋማሽ ፈተና በቀጣይ የሚከናወን መሆኑን እንገልጻለን።

የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የተከታታይ ትምህርት ንዑስ ክፍል።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

30 Nov, 18:31


በዓመቱ የትምህርት እቅድ መሠረት ነገ እሑድ የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት አጋማሽ (Mid) ፈተና መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም በመደበኛው #የእሑድ መርሐግብር የምትማሩ ከ 1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያላችሁ ተማሪዎች ከዚህ በላይ በተቀመጠው መርሐግብር መሠረት #ፈተናውን_የምትፈተኑ መሆኑን አውቃችሁ በሰዓቱ እንድትገኙ በማለት መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

ማሳሰቢያ:- ለፈተናው ስትመጡ አስፈላጊውን የፈተና ሥነምግባር ማሟላታችሁን እንዳትረሱ።

መልእክቱን ለሌሎች ያጋሩ!

የተከታታይ ትምሀርት ንዑስ ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

30 Nov, 15:07


የኅዳር ወር የሰሌዳ መጽሔት

የኅትመት ዝግጅት እና ስርጭት ንዑስ ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

29 Nov, 19:10


ኅዳር 21  በቅዳሴ ቅድመ ወንጌል የሚባል  ምስባክ

የአብነት እና አርድእት ንዑስ ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

27 Nov, 03:31


መንፈሳዊ ጉዞ

ዓመታዊው የታኅሳስ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊውን ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ በሰንበት ትምህርት ቤታችን ጉዞ ክፍል ወደ ታላቁ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ጉዞ ተዘጋጅቷል ።

ከወዲሁ እንድትመዘገቡ እንጋብዛለን !!

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

24 Nov, 17:03


የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላት ያላቸውን ሙያ ለሰንበት ትምህርት ቤቱ አገልግሎት ለመጠቀም ያለመ መደበኛ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላትን ማዕከል ያደረገ " የበጎ ፈቃድ ሙያዊ አገልግሎት ለሰንበት ትምህርት ቤት(ለቤተክርስቲያን)" በሚል የአቅም ማጎልበቻ ትምህርታዊ ሥልጠና በሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት አማካኝነት በረድኤተ እግዚአብሔር ዛሬ ተከናወነ።

የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ጽ/ቤት

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

24 Nov, 04:25


ጾመ ነቢያት        


[ የጾመ ነብያት ምስጢር ምንድነው ? ]   

ጾመ ነቢያት [ የገና ጾም ] ከልደት አስቀድሞ የሚጾም ጾም ነው ከህዳር ፲፭ [ 15 ] ጀምሮ ለ ፵፫ [43] ቀናት የሚጾም ሲሆን ፋሲካው [ ፍቺው ] በልደት በዓል ነው ይህም ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ቅዱሳንና ምዕመናን ጾመውታል፡፡

ጾመ ነብያት ስያሜውን ያገኘው ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ስለተፈጸመበት ነው በየዘመናቱ የተነሡ ነቢያት እግዚአብሔር ወደፊት ሊያደርግ ያሰበውን በእምነት ዓይን እያዩ ምስጢር ተገልጦላቸው የራቀው ቀርቦ  የረቀቀው ገዝፎ ጎልቶ እየተመለከቱ ትንቢት ተናገሩ ያዩትም መልካም ነገር እንዲደርስላቸው ጾሙ ጸለዩ፡፡

ነቢያት ከእመቤታችን ስለ መወለዱ ፥ ወደ ግብፅ ስለ መሰደዱ ፥ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ ፥ ብርሃን በሆነው ትምህርተ ወንጌል ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ ፥ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ ስለመቀበሉና ስለ መሰቀሉ ፥ ስለ ትንሣኤው ፥ ስለ ዕርገቱና ስለ ዳግም ምጽአቱ ትንቢት ተናግረው አላቆሙም፡፡

ለአዳም የተሠጠው ተስፋ ተገልጦላቸው ለተናገሩት ትንቢት ፍፃሜ እንዲያደርሳቸው ፈጣሪያቸውን ተማፀኑትም እንጂ በየዘመናቸው ፦ "አንሥእ ኃይልከ ፈኑ እዴከ" እያሉ ጮኹ በጾምና በጸሎት ተወስነውም እግዚአብሔር ሰው የሚሆንበትን ጊዜ በቀናት ፣ በሳምንታት ፣ በወራትና በዓመታት ቆጠሩ፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሥጋዌው ትንቢት በተናገረ በ፬፵፮ ዓመት ጌታችን ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኗል፡፡

ነቢያት ተስፋው በዘመናቸው ተፈጽሞ በዓይነ ሥጋ ለማየት ባይችሉም እግዚአብሔር ፦ "አያደርገውን አይናገር የተናገረውን አያስቀር" ብለው አምነው ከወዲሁ ተደሰቱ ለዘመነ ሥጋዌ ቅርብ የነበሩ እነ ነቢዩ ኢሳይያስ ጾሙ እንዴት መፈጸም እንዳለበት ተናግረዋልም [ኢሳ.፶፰፥፩] በመሆኑም በጌታ ልደት ትንቢተ ነቢያት ስለተፈጸመበት ይህ ጾም "የነቢያት ጾም" ይባላል የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት ስለሆነም "ጾመ ስብከት" ይባላል፡፡

ይህንን ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ብዙ ቅዱሳን ጾመውታል በዚህም ምክንያት የሚከተሉት ስያሜዎች አሉት፡ እነርሱም፦

† ፩. [    ጾመ አዳም   ]

አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገነት ከተባረረ በኋላ በፈጸመው በደል አዝኖ  ተክዞ  አለቀሰ [እንባ ቢያልቅበት እዥ እስከሚያፈስ  እዥ ቢያልቅበት ደም በዓይኑ እስከሚፈስና ዓይኑ ይቡስ ወይም ደረቅ እስከሚሆን ድረስ አለቀሰ] ጾመ ጸለየ ከልብ የሆነ ጸጸቱን፣ ዕንባውን፣ በራሱ መፍረዱንም እግዚአብሔር አይቶ ተስፋ ድኅነት ሰጠው፡፡ "ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ  በደጅህ ድኼ  በዕፀ መስቀል ተሰቅዬ ሞቼ አድንሃለሁ" የሚል ነው፡፡ [ገላ. ፬፥፬፣ መጽ.ቀሌምንጦስ] ስለዚህ ጾሙ የተሰጠው ተስፋ  የተቆጠረው ሱባኤ ስለተፈጸመበት "ጾመ አዳም" ይባላል፡፡

† ፪. [   ጾመ ነቢያት   ]

ነቢያትም የምሥጢረ ሥጋዌ ነገር ተገለጦ ስለታያቸው ክርስቶስ ለሰው ልጅ የሚከፍለውን የፍቅር ዋጋ በትንቢት ተመልክተው ጾመውታልና ጾመ ነቢያት ይባላል፡፡ ይህ ጾም ከአባታችን አዳም እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ድረስ የተነሱ አበውና እናቶች ድኅነትንና ረድኤትን ሲሹ የጾሙት ጾም ነው:: በተለይ አባታችን አዳም  ቅዱስ ሙሴ ቅዱስ ኤልያስ  ቅዱስ ዳንኤልና ቅዱስ ዳዊት በጾማቸው የተመሰከረላቸው ቅዱሳን ናቸው:: [ዘዳ.፱፥፲፱ ፣ ነገ.፲፱፥፰ ፣ ዳን.፱፥፫ መዝ.፷፰፥፲ ፻፰፥፳፬] ቅዱሳን ነቢያት በጭንቅ በመከራ ሆነው የጾሙት ጾም ወደ መንበረ ጸባኦት ደርሶ ወልድን ከዙፋኑ ስቦታል ለሞትም አብቅቶታል::

† ፫.  [   ጾመ ሐዋርያት  ]

ሐዋርያት "ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብራለን  ልደትን ምን ሥራ ሠርተን እናከብረዋለን?" ብለው ከልደተ ክርስቶስ በፊት ያሉትን ፵፫ ዕለታት ጾመዋልና፡፡

† ፬.  [   ጾመ ማርያም   ]

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ቅድስናዋን አይቶ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ወልደ አምላክን ያለ ሰስሎተ ድንግልና በግብረ መንፈስ ቅዱስ ጸንሳ እንደምትወልደው ቢነግራትም የትሕትና እናት ናትና "ምን ሠርቼ የሰማይና ምድርን ፈጣሪ እችለዋለሁ?" ብላ ጌታን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማለችና "ጾመ ማርያም" ይባላል፡፡

† ፭.  [   ጾመ ፊልጶስ   ]

ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ እያስተማረ ሳለ በሰማዕትነት ሲሞት  አስክሬኑ ከደቀመዛሙርቱ ስለተሰወረ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስክሬን እንዲገለጽላቸው ከኅዳር ፲፮ ጀምረው ጾመው በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስክሬን ተመልሶላቸዋል ነገር ግን አስከሬኑ ቢመለስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል፡፡

† ፮.  [   ጾመ ስብከት  ]

የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት የሰው ልጆች ተስፋ የተመሰከረበት  የምስራች የተነገረበት ስለሆነ ጾመ ስብከትም ይባላል፡፡

† ፯.  [   ጾመ ልደት   ]

የጾሙ መጨረሻ [ መፍቻ ] በዓለ ልደት ስለሆነ "ጾመ ልደት" ይባላል፡፡

በጾማችን በጸሎታችን - ስለ ቤተክርስቲያን ፥ ስለ ሀገር እና ስለ ሕዝብ በማሰብ በእንባ እራሳችንን ዝቅ በማድረግ እንጾም ዘንድ ይገባል፡፡


ወስብሐት ለእግዚአብሔር  ወለወላዲቱ ድንግል  ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!
                   🔹〰️🔹〰️🔹〰️
   መገናኛ ብዙሃን ንዑስ ክፍል
@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

23 Nov, 13:46


ኅዳር 15  በቅዳሴ ቅድመ ወንጌል የሚባል  ምስባክ

የአብነት እና አርድእት ንዑስ ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

23 Nov, 04:14


የኃያሉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከበረ።

ኅዳር 12 ቀን 2017 ዓ.ም

በመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች ዘንድ ኅዳር ፲፪ ቀን መልአኩ እስራኤላውያንን እየተራዳ ከግብፅ እንዲወጡ ያደረገበትን ተራድኢነትን በማሰብ  በመልአኩ መታሠቢያ አብያተ ክርስቲያናት ተከብሮ ይውላል።

በዚሁ መሠረት በዓሉ በዚሁ ዕለት በ2017 ዓ.ም አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ሊቃውተ ቤተ ክርስቲያን እና በርካታ ምእመናን በተገኙበት ተከብሯል።
በበዓሉ ላይ የደብሩ ሊቃውንተ እና የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች  ያሬዳዊ ዜማ አቅርበዋል።
                🔹〰️🔹〰️🔹〰️
   መገናኛ ብዙሃን ንዑስ ክፍል
@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

20 Nov, 21:52


እንኳን አደረሰን የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች!!!
#profile picture
#add to story
#timeline
#state update በማድረግ
ለምዕመናን ማድረስ ግዴታችን ነው።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

20 Nov, 15:33


ኅዳር ፲፪ በዓለ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት

እንኳን አደረሳችሁ!
የኅትመት ዝግጅት እና ስርጭት ንዑስ ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

14 Nov, 06:32


ኅዳር 6 በቅዳሴ ሰዓት ቅድመ ወንጌል የሚባል ምስባክ

የአብነት እና አርድእት ንዑስ ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

09 Nov, 16:22


ማኅሌተ ጽጌ ተፈጸመ
    ሕዳር 1

የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የአብነት እና አርድእት ንዑስ ክፍል
 
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ

▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭
🔎ፌስቡክ ገፅ https://www.facebook.com/finotebrhans
@finote brhan
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ https://t.me/finottebirhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

08 Nov, 19:03


ጥቅምት 27 ዓመታዊ ክብረ በዓል አብረውን ያሳለፉት ሰንበት ትምህርት ቤቶች !!

፩ኛ. ምሥካየ ኅዙናን መድኅኔዓለም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት

፪ኛ. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል ውሉደ ሰማዕት ሰንበት ት/ቤት

፫ኛ. ፋንታ ደብረ ጽጌ ቅዱስ ሩፋኤልና ቅድስት አርሴማ ፍኖተ ጽድቅ ሰንበት ት/ቤት

፬ኛ. ቱሉ ዲምቱ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ገብርኤል ሰንበት ት/ቤት

፭ኛ. መካና ደብረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ሰንበት ት/ቤት

፮ኛ. መጋላ ደብረ ጽጌ ቅዱስ አማኑኤል ሰንበት ት/ቤት

፯ኛ. ፋንታ ፈለገ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት

፰ኛ. ቱሉ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት

ቸሩ መድኅኔዓለም ሁላችሁንም በበረከት ይጎብኛችሁ !!

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

08 Nov, 18:21


https://t.me/+G5wqtif4RsRiZGU0

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

08 Nov, 14:30


ምስጋና፪
ዲያስጶራ የሆኑ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት በወርኃዊ የአባልነት አስተዋጽኦ እንዲሳተፉና የሰንበት ት/ቤቱን አገልግሎት እንዲደግፉ የሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት ባቀረበው ጥሪ መሠረት ከወንድማችን ሰሎሞን ዘመዴና ከእህታችን ሰብለ በቀለ ጋር  ወንድማችን ዲን ዘማሪ አማኑኤል ግርማ ከስዊድን አገልግሎቱን ተቀላቅሏል። ወንድማችን የላከልንን የአንድ ዓመት አስተዋጽኦ ከምስጋና ጋር ዛሬ ተቀብለናል።በዚሁ አጋጣሚ ሌሎች ወንድሞችና እህቶች አገልግሎቱን እንድትቀለቀሉ እየጋበዝን መልዕክቱ ለሌሎችም እንዲደርስ መረጃውን እንድታካፍሉ እንጠይቃለን።
የሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

08 Nov, 13:07


ምስጋና
የበዓለ ጥንተ ስቅለተ ክርስቶስና 45ኛ ዓመት የሰንበት ት/ቤታችን የምሥረታ በዓል በረድኤተ እግዚአብሔር በልዩ ልዩ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ተከናወነ።
በዓሉ የሁላችን በዓል መሆኑን በመረዳት ስንበት ት/ቤቱ በልዩ ልዩ መንገዶች ያቀረበውን መንፈሳዊ ጥሪ በመቀበል እግዚአብሔር በረዳችሁ መጠን አብራችሁን ለነበራችሁና ለደገፋችሁን አሃት ሰንበት ት/ቤቶች : መንፈሳዊ የጉዞና የጽዋ ማኅበራት : በጎ አድራጊዎች ምእመናን : የህጻናትና ማዕከላውያን : የመደበኛና ነባር የሰንበት ት/ቤታችን አባላት እንዲሁም የተከታታይ ትምህርት ተማሪዎች : በአካል ርቃችሁ ከባህር ማዶ በተለያዩ ዓለማት ያላችሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት ሁላችሁን በመድኃኔዓለም ሥም እጅግ አድርገን እናመሰግናለን። በዚሁ አጋጣሚ ያላለቁ ጥቂት ሥራዎችን እንድናጠናቅቅ አብሮነታችሁን እንጠይቃለን።
                        

   የሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት
   ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

04 Nov, 15:16


« ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ» ኤፌ 5 ፥ 9
ጥቅምት 27
በቅድሚያ ለቸሩ አባታችን መድኅኔዓለም ዓመታዊ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ እያልን ይህንን በሰንበት ትምህርት ቤታችን መዘምራን የተዘጋጀውን ዝማሬ እንጋብዛችኋለን ።
https://youtu.be/MdpThfrq5Fk?si=PjIePpmNo6HazvsH
Subscribe
#profile_picture
#add to_story
#timeline
#share
   #share
   #share

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

04 Nov, 11:57


ዛሬ ማታ 12:00 አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
ይጠብቁን

https://youtube.com/@finotebirhan328?si=9JkrwwwFrO8xrUts
Subscribe
#profile_picture
#add to_story
#timeline
#share
   #share
   #share

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

04 Nov, 10:03


“በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው።” ማቴ ፲፯ ፥ ፬
        ጥቅምት 27

ኑ በቤተልሔም  የእግዚአብሔር ክብር በሚገለጥበት ተራራ እንሰብሰብ የአምልኮ ሥርዓታችንንም እንፈጽም
#መድኃኔዓለም_አዳነን_በማይሻር_ቃሉ
#ጥቅምት_27_አልቀርም
#profile_picture
#add to_story
#timeline

አድራሻ :-አቃቂ መሃል ከተማ ጋራው ላይ
    #share
   #share
   #share
▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

04 Nov, 09:47


በሥመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ʺእስመ ኩሎሙ እለ ይሴፈዉከ ኢይትኃፈሩʺ, አንተን ተስፋ የሚያደርጉ አያፍሩም መዝ24(25) ፦3
  በነገር መጀመሪያ ከሁሉም አሰቀድሞ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርጎ ያፈረ ባለመኖሩ ያለፉትን አርባ አምስት የአገልግሎት ዓመታት የረዳን ያገዘን ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ታናሽነታችንን ሳይንቅ በደላችን ሳይቆጥር የተወደደውን ታላቅ የምሕረቱ ዓይኖቹን ዘንበል በማድረግ የሚመለከተን ለድካማችን ብርታት ለጥፋታችን ፍጹም ምሕረትን፤ ይቅርታ እያደረገ እየሰጠንም ሳይሰለቸን ጆሮዎቹን ዘንበል አድርጎ በጊዜውም ያለጊዜውም የልመና ጩኸታችንን ሳይንቅ የሚሰማን ነገ ከነገም ወዲያ ሰው ይሆናል ትሆናለች ብሎ በአባታዊ ፍቅሩ ጥበቃው ሳይለየን ወደቁ ሲባል በበረከት እጆቹ አንስቶን አበቃላቸው ደከሙ ስንባል አበርትቶን ደግሞ ሌላ ዘመን ሌላ አዲስ ዓመትን ለንስሐ ሳይሰስት ያለዋጋ በመቸር የሚሰጠን የአገልግሎት የጥቅም ዘመን የሚጨምርልን ከእኛ ጋር በአገልግሎት የነበሩ ዛሬም ወደዕቅፉ ለተሻለ ዘላለማዊ ክብር የወሰዳቸውን የሚሰበስብ የሁላችንም ያላነውም የተጠሩትንም በረት የለወጡትንም ጭምር የቅድስተ ቅዱሳን የድንግል ማርያም ልጅ የቅዱሳኑ አምላክ የኛም አምላክ እንደዚሁም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰላም እና በጤና በሩቅ እና በቅርብ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ያላችሁ የሰንበት ትምሕርት ቤታችን አባላት እንኳን ለዚሕች ተጨማሪ የደስታ የምስጋና የአገልግሎት የሥራ ዘመን አደረስን አደረሳችሁ፡፡           
  ባሳላፍናቸው ጥቂት የስራ እና የአገልግሎት ዘመናት ከሰራነው ይልቅ ያስታጎልነው ከጠቀምነው ይልቅ የተጠቀምነው እንደሚሻል ለሁላችንም የሚገባንና የምንረዳው ቢሆንም የማንጠቅም የማንረባ ባርያዎቹ ብንሆንም እንደምንጠቅም እንደምንረባ ቆጥሮን በቤቱና በቅጥሩ ውስጥ የተሻለ ሥም እና በረከት ሁልጊዜም ሳያጓድል እየሰጠን ዛሬ ላይ ያስቀመጠን ያስገኘን በአንድ ቃል ለጥቅማችን ነው፡፡ ጌታችን በወንጌል የነገረን ʺየሚያገለግለኝ ቢኖር ይከተለኝ፤ እኔም ባለሁበት አገልጋዬም ደግሞ በዚያ ይሆናልʺ ዮሐ.12፦26 ያለንን ሁልጊዜ ዘወትር ስናስበው ስናሰታውሰው የአገልግሎታችን መድረሻ ማረፊያ ከእርሱ ጋር እንደሚሆን ሲገባን ስንረዳው እንኳንም ለዚህ በረከት ፈቀደልኝ እንድንል በአድናቆት ይገባናል፡፡ ቅዱሳኑም ይሕንን ተረድተው ገብቷቸው አውቀውትም ከእግዚአብሔር ጋር መኖር ከዓለምም መሰደድ ቢሆንም ማትረፊያቸው እንደሆነ ቀድመው ስላተሙት ʺታምነናል ይልቁንም ከሥጋ ተለይተን በስደት መኖር በጌታም ዘንድ ማደር ደስ ይለናልʺ በ2ኛው ቆሮ5፦8 ያለውን ሰምተው ኖረውበት የሚያገኙትን አውቀው የሚገቡበትን ሥፍራ ተረድተው ከእግዚአብሔር ጋር ኖረው ወደ እግዚአብሔር ወደ አባታቸው መኖሪያ አብረውት ለዘለዓለም በምሥጋና ያለድካም በሃሴት ለመኖር ሔደዋል ፡፡ አሁን ካለነው የሰንበት ትምሕርት ቤት ወጣቶች እንደዚሁም ሁላችንም አገልጋዮች የሚጠበቅብን በድካም አብዝተን በመከራም አትረፈን አባቶቻችን መስለን የማያልፈውን ዓለም በሚያልፈው ዓለም እና ግብር ተክተን ለውጠን ጥቂቱን ኖረን ብዙውን አትረፈን ወደሰሪያችን መመለሰ ይሻለናል፡፡ 2ኛው ቆሮ11፦23,27፣2ኛው ቆሮ12፦9-10
የቀጣዩ ዘመን አገልግሎት የሚታዩትን ነገሮች በጥሞና ተረጋግተን ስናስተውል ብዙም ዕውቀት በማይፈልግ ሁኔታ ለመረዳት እንደምንችለው የክርሥቲያናዊ ኑሮአችን አገልግሎታችን ተደራሽ እንዲሆን አቅደን መሥራት፤ አስተውልን መወሰን፤ የሚባክን ጊዜም ይሁን ንበረት ከቶውንም እናጠፋለን ብሎን የማይሆነውን እንደ የዋህ ሰው የማንል ነገርግን ለመቀነስ ተግተን የምንሰራ ልንሆን ጊዜው የሚጠይቀው የማይታለፍ ከታለፈም የበዛ ዋጋን የሚያስከፍል ዓቢይ ተግባር ነው እንላለን፡፡ በነገሮች ሁሉ እንዳለፈው ዘመን እኛ ተኝተን አንቀላፍተን ጠላት በመልካም እርሻችን ቤተክርሥቲያን ላይ ክርዳድ ሲዘራባት ሁልጊዜ መካች ብቻ ሳንሆን ስልታዊ  የሆነ ተግባራዊ የሚሆን፤ ሁሉም አማኝ ሊያምንበት ሊረዳውና ሊደግፈው የሚችል ኦርቶዶክሳዊ ንድፍ ዕቅድ በማዘጋጀት ከውስጥም ከውጭም ያለብንን የተደራጀ ጥቃት በአባቶቻችን በመተማመን መውጣት መግባት በመሰማሪያ ሜዳችን ቤተክርሥቲያንም በጥንቃቄ ሩጫችንን ለመፈጸም ከአባታችን ከእግዚአብሔር ጋራ ያለንን ንግግር ሳናቋርጥ በጥበብ እና በሞገስ እንደዚሁም በጸጋው እንደሚያድጉ ልጆቹ ዘወትር ካደረግ ነው ይልቅ የቀረብንን በማስታወስ ሁልጊዜም አንዱ ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን ለሌላው ብርታቱ፤ ለመውደቁ ሳይሆን ለመነሳቱ የሚጥር፤ ጥፋትም በሚከሰትበት ወቅት ሌላ ጊዜ እንዳይደገም መረጃ አደራጅቶ ተማምኖም በመሰነድ፤ ፊት ለፊት ሳያፈሩ ሳይፍሩም ከቂም ከበቀል እርቆ በመወቃቀስ ለቀጣዩ ሥራ፤ ለሚቀጥለው የነፍስ ማዳን ሥራ፤ ለወንጌለ መንግስቱ መስፋፋት ከበረት የሚወጡትን በመቀነስ የሚጨመሩትን በማብዣት ላይ እንድናተኩር ሁላችንንም ዕለት ዕለት የቤተክርስቲያን ጉዳይ እንዲያሳስበን ቅድሚያም ልንሰጠው የሚገባን ዋነኛ ጉዳያችን ልናረገው የሚገባው እግዚአብሔርን እንደ ፈቃዱ ለማገልገል መቻላችን ሊሆን ይገባል፡፡                               
  አ/ መ/ ሕ/መ/ቤ/ክ/ፍ/ብ/ሠ/ት/ቤት
                                                                      
ተጻፈ በጥቅምት  2017 ዓ.ም
 መ.ብ.ቀ.ኢ ሶሎሞን ወንድምአገኝ

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

03 Nov, 08:24


“በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው።” ማቴ ፲፯ ፥ ፬
        ጥቅምት 27

ኑ በቤተልሔም  የእግዚአብሔር ክብር በሚገለጥበት ተራራ እንሰብሰብ የአምልኮ ሥርዓታችንንም እንፈጽም
#መድኃኔዓለም_አዳነን_በማይሻር_ቃሉ
#ጥቅምት_27_አልቀርም
#profile_picture
#add to_story
#timeline

አድራሻ :-አቃቂ መሃል ከተማ ጋራው ላይ
    #share
   #share
   #share
▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

02 Nov, 09:24


፩ኛ ዓመት ፭ኛ ሳምንት
ማኅሌተ ጽጌ ዘኃምሳይ ሰንበት
    ጥቅምት ፳፬

የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የአብነት እና አርድእት ንዑስ ክፍል
 
ሊንኮቹን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ

▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭
🔎ፌስቡክ ገፅ https://www.facebook.com/finotebrhans
@finote brhan
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ https://t.me/finottebirhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

02 Nov, 06:33


“በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው።” ማቴ ፲፯ ፥ ፬
        ጥቅምት 27

ኑ በቤተልሔም  የእግዚአብሔር ክብር በሚገለጥበት ተራራ እንሰብሰብ የአምልኮ ሥርዓታችንንም እንፈጽም
#መድኃኔዓለም_አዳነን_በማይሻር_ቃሉ
#ጥቅምት_27_አልቀርም
#profile_picture
#add to_story
#timeline

አድራሻ :-አቃቂ መሃል ከተማ ጋራው ላይ
    #share
   #share
   #share
▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

01 Nov, 18:24


በቅርብ ቀን አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
ይጠብቁን
https://vm.tiktok.com/ZMhChDeTk/
#profile_picture
#add to_story
#timeline
#share
   #share
   #share

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

01 Nov, 17:51


በቅርብ ቀን አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
ይጠብቁን
https://vm.tiktok.com/ZMhChDeTk/
#profile_picture
#add to_story
#timeline
#share
   #share
   #share

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

01 Nov, 11:09


እንኳን አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
ለ፵፭ኛ ዓመት የምስረታ በዓል  አደረሳቹ

ለነገ የቤተክርስቲያን ገፅታ የምትጨነቁ ከሆነ ዛሬ የሰንበት ትምህርት ቤትን አገልግሎት በልባችሁ አኑሩ
#_ብፁዕ_አቡነ_ጎርጎርዮ_ካልዕ
#መድኃኔዓለም_አዳነን_በማይሻር_ቃሉ
#ጥቅምት_27_አልቀርም
#profile_picture
#add to_story
#timeline

አድራሻ :-አቃቂ መሃል ከተማ ጋራው ላይ
    #share
   #share
   #share
▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

01 Nov, 09:10


“በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው።” ማቴ ፲፯ ፥ ፬
        ጥቅምት 27

ኑ በቤተልሔም  የእግዚአብሔር ክብር በሚገለጥበት ተራራ እንሰብሰብ የአምልኮ ሥርዓታችንንም እንፈጽም
#መድኃኔዓለም_አዳነን_በማይሻር_ቃሉ
#ጥቅምት_27_አልቀርም
#profile_picture
#add to_story
#timeline

አድራሻ :-አቃቂ መሃል ከተማ ጋራው ላይ
    #share
   #share
   #share
▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

01 Nov, 07:52


ማስታወቂያ!

ለተከታታይ ትምህርት የ 11ኛ ክፍል በቅዳሜ ማታ መርሐግብር ለተመዘገባችሁ እና ከዚህ በፊት የ10ኛ ክፍል ትምህርትን በቅዳሜ መርሐግብር አጠናቅቃችሁ ወደ 11ኛ ክፍል ለተዘዋወራችሁ ተማሪዎች በሙሉ።

የቅዳሜ የ 11ኛ ክፍል ትምህርት ለመጀመር ዝግጅታችንን እያጠናቀቅን ስለሆነ ከዚህ በፊት በቅዳሜ የተመዘገባችሁም አሁን ቅዳሜ ማታ ለመማር የምትፈልጉ በጠቅላላ በአስቸኳይ ስማችሁን ለተከታታይ ት/ት ንዑስ ክፍል አባላት ወይም በ ቴሌግራም አድራሻ @Finotebrhan እንድታስመዘግቡ ይሁን።

ማሳሰቢያ!

በቂ ተመዝጋቢ የማይገኝ ከሆነ የቅዳሜው የ 11ኛ ክፍል መርሐግብር የሚሰረዝ መሆኑን እና በእሁድ መርሐግብር ብቻ ትምህርቱ የሚቀጥል መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።

ማስታወሻ!

10ኛ ክፍል የሚባለው በቀድሞው የክፍል አቆጣጠር #ራብዓይ ሲሆን 11ኛ ክፍል ደግሞ #ኃምሳይ ይባል የነበረው ክፍል መሆኑን እናሳውቃለን።

የተከታታይ ትምህርት ንዑስ ክፍል

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

31 Oct, 18:19


#፵፭
       
  #share
   #share
   #share
▭▭▭▭  ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝  ▭▭▭▭
🔎ዩቲዩብ ገፅ፡ https://youtube.com/channel/
@finote brhan
🔎 ቲክቶክ፦ http://tiktok.com/@
@finotebrhan
🔎ቴሌግራም ገፅ፦
ትምህርትና መረጃዎች፡ t.me/@finotebrhan

@finotebrhan

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

31 Oct, 14:20


“በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው።” ማቴ ፲፯ ፥ ፬
        ጥቅምት 27

ኑ በቤተልሔም  የእግዚአብሔር ክብር በሚገለጥበት ተራራ እንሰብሰብ የአምልኮ ሥርዓታችንንም እንፈጽም
✝️#መድኃኔዓለም_አዳነን_በማይሻር_ቃሉ
✝️#ጥቅምት_27_አልቀርም
https://vm.tiktok.com/ZMhQQ18h1/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

31 Oct, 13:41


“በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው።” ማቴ ፲፯ ፥ ፬
        ጥቅምት 27

ኑ በቤተልሔም  የእግዚአብሔር ክብር በሚገለጥበት ተራራ እንሰብሰብ የአምልኮ ሥርዓታችንንም እንፈጽም
✝️#መድኃኔዓለም_አዳነን_በማይሻር_ቃሉ
✝️#ጥቅምት_27_አልቀርም
https://youtu.be/su5SPWIAw9Q

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

22 Oct, 10:28


የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን ሰየመ።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የጥቅምት 2017 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን ሰይሟል።

ምልዓተ ጉባኤው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የመክፈቻ መልዕክት ዛሬ ጠዋት መጀመሩ የሚታወቅ ሲሆን ከቅዱስነታቸው የመክፈቻ መልእክት በኋላም የመወያያ አጀንዳ ቀርጸው የሚያቀርቡ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳትን ነው የሰየመው።

በዚህም መሰረት

1.ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ
2.ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ
3.ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
4.ብፁዕ አቡነ ማርቆስ (ዘስያትል)
5.ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ
6.ብፁዕ አቡነ  ኤጲፋንዮስ
7.ብፁዕ አቡነ ኤልሣዕ የተመረጡ ሲሆን አጀንዳ የማርቀቅ ተግባራቸውን በማከናወን ላይ ይገኛሉ።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ የሚያቀርቡትን ረቂቅ አጀንዳ ከመረመረና ማስተካከያ ካደረገበት በኋላ የጸደቀውን አጀንዳ መሰረት በማድረግ በቅደም ተከተል እየተወያየ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

22 Oct, 07:44


"እኛም በዚህ ዓለም የእግዚአብሔር ወኪሎች ስለሆንን ቢሰሙንም ባይሰሙንም ዓለማውያን ሹማምንትን  የማስተማርና የመምከር ኃላፊነት አለብን" ቅዱስ ፓትርያርኩ


የ2017 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመጀመሪያ መደበኛ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት በመንበረ ፓትርያርክ የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መልእክት ተከፍቷል።

ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው በዛሬው ዕለት መደበኛና አመታዊ ጉባኤው መጀመሩን ያበሠሩ ሲሆን አክለውም ይህ ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚገኙና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን መሪና ጠባቂ ነው፤ ከዚያም ባሻገር እንደ ቃሉ እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ቃሉን በመስበክ ፍጥረተ ሰብእን በሙሉ የመጥራት ተልእኮ ለእኛ የተሰጠ የቤት ስራ ነው ብለዋል።

ሁላችን እንደምንገነዘበው አሁን የምንገኝበት ዘመን የጸላኤ ሠናያት መንፈስ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ከምንም ጊዜ በበለጠ ጦሩን ሰብቆ የተነሣበት ጊዜ ነው፤ አሁን ያለው ዓለም በሀገራችንም ሆነ በሌላው ክፍለ ዓለም ላሉ ኦርቶዶክሳውያን ከባድ ፈተና ተደቅኖብናል ብለዋል።

ቅዱስነታቸው አክለው ምንም ቢሆን የተቀበልነው ኃላፊነት የእግዚአብሔር ነውና በሚሰራው ሁሉ በሿሚው አምላክ ከመጠየቅ አያመልጥ ፤ እኛም በዚህ ዓለም የእግዚአብሔር ወኪሎች ስለሆንን ቢሰሙንም ባይሰሙንም ዓለማውያን ሹማምንትን  የማስተማርና የመምከር ኃላፊነት አለብን፡፡ ይህ የሁለታችን ኃላፊነት እንደ እግዚብሔር ፈቃድ ስንፈጽም የሕዝብ ሰላምና በረከት፣ ፍቅና አንድነት፣ ዕድገትና ልማት በአስተማማኝ ሁኔታ ይረጋገጣል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን እየሆነ ያለው ይህ አይደለም፤ አለመግባባት በዝቶአል፣ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቶአል፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡ ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቶአል፤ ይህ ለአንድ ሀገር ወይም ሕዝብ የውድቀት ምክንያት ከሚሆን በቀር ከቶውኑም የዕድገት ምልክት ሊሆን አይችልም ብለዋል።

ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ክፉ ድርጊት እየተፈጸመ ያለው በእኛው ልጆች በኢትዮጵያውያን መሆኑ ነው፤ ስለሆነም በከተማም፣ በጫካም፣ በገጠርም በየትኛውም ስፍራ የምትገኙ ልጆቻችን ምንም ይሁን ምን ሀገርንና ሕዝብን ከመጉዳት ተቆጠቡ፡፡ በተለይም ከቤተ ክርስቲያንና ከሀገር እንደዚሁም ሕዝቡን ከሚያገለግሉ ካህናትና ሲቪል ሰራተኞች እባካችሁ እጃችሁን አንሡ፤ ቤተ ክርስቲያን እኮ የእናንተና የሕዝቡ ሁሉ እናት ናት፤ በእናታችሁ ላይ መጨከንን እንዴት ተለማመዳችሁት? አሁንም ንስሐ ግቡ ያለፈው ይበቃል በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም በእግዚአብሔር ስም ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንና ልጆቻችን የምናስተላፈው ወቅታዊ መልእክታችን ይህ ነው፡፡ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎትና የስራ አፈጻጸም ላይ ለመምከርና ለመወሰን ኃላፊነት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት መደበኛና ዓመታዊ ጉባኤውን የጀመረ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናበስራለን በማለት የጉባኤውን መጀመር አስታውቀዋል።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

21 Oct, 09:01


የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በነገው ዕለት ይጀመራል !

ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የጥቅምት 2017 ዓ.ም  ምልዓተ ጉባኤ በነገው ዕለት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ይጀመራል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ጥቅምት 12 እና በዓለ ትንሣኤ በዋለ በ25ተኛው ቀን ምልዓተ ጉባኤውን የሚያከናውን መሆኑ ይታወቃል።

ምልዓተ ጉባኤው በዛሬው ዕለት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በሚደረገው የጸሎት መርሐግብር የሚከፈት ሲሆን ከነገ ጀምሮ ቅዱስ ሲኖዶስ በልዩ ልዩ ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያንና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ  እንደሚወያይ ይጠበቃል።

ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት

21 Oct, 07:40


አጣሪ ኮሚቴው ሪፖርቱን ለቋሚ ሲኖዶስ አቀረበ።

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተከስተዋል የተባሉትን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተመለከተ በዝርዝር በማጣራት ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር እንደያቀርብ የተሰየመው አጣሪ ኮሚቴ ባለፉት አሥራ አምስት ቀናት ሲያከናውናቸው የሰነበተውን የማጣራት ሥራዎች በማስመልከት ያዘጋጀውን ሪፖርት ዛሬ ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም ለቋሚ ሲኖዶስ አቅርቧል።

አጣሪ ኮሚቴው አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአካል ተገኝቶ ማጣራት እንዳይችል።የተከለከለ መሆኑን በመጥቀስ መረጃውን ለሣሰባሰብ ይቻል ዘንድ ተበዳዮች በስልክ፣በቴሌጌራምና በዋትስ አፕ መልዕክቶች፣በአካል በመቅረብ፣በሰነድ ማስረጃ በማስደገፍ፣በድምጽና 3:30 ርዝማኔ ባለው በቪዲዮ በተቀረጸ ማስረጃ ጭምር መረጃዎችን ማሰባሰቡን፣መተንተኑን፣
ማደራጀቱንና ጥቅም ላይ ማዋሉን ገልጿል።

በሪፖርቱም ከመልካም አስተዳደርና ከብልሹ አሰራር ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች በማስረጃ ተደግፈው የቀረቡ ሲሆን በማጣራት ስራው የተረጋገጡ ጉድለቶችንና ጥፋቶችን መሰረት በማድረግም በጊዜያዊነትና በቋሚነት ችግሮቹን ለመፍታትና የካህናትና የአገልጋዮችን ቅሬታ ዘላቂነት ሊፈቱ ይችላሉ ተብለው የቀረቡ  በሰባት ነጥቦች የተተነተኑ  የመፍትሔ ሐሳቦችና በዘጠኝ ነጥቦች የተተነተኑ ችግሮቹን በዘላቂነት ሊፈቱ ይችላሉ ተብሎ የታመነባቸው የመፍትሔ ሐሳቦችን አቅርቧል።ይኸው የጥናት
ሰነድ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ቀርቦ ውሳኔ የሚሰጥበት ይሆናል።