Ethiopian Defence University(EDU) @ethiopiandefenseuniversity Channel on Telegram

Ethiopian Defence University(EDU)

@ethiopiandefenseuniversity


Educational

Ethiopian Defence University(EDU) (English)

Welcome to the Ethiopian Defence University (EDU) Telegram channel! This channel is dedicated to providing information and updates on all things related to defense and security in Ethiopia. Whether you are a military enthusiast, a student aspiring to join the defense sector, or simply curious about the country's defense policies, this channel is the perfect place for you

Ethiopian Defence University (EDU) is a leading institution in the country that offers specialized education and training for individuals interested in pursuing a career in defense and security. Through this channel, you will have access to valuable resources, news, and insights from experts in the field. Stay updated on the latest developments in Ethiopia's defense sector and gain a deeper understanding of the challenges and opportunities facing the nation

Who is it? EDU is a renowned institution that aims to equip individuals with the knowledge and skills needed to contribute to the defense and security of Ethiopia. By joining this channel, you will be part of a community of like-minded individuals who share a passion for defense and national security

What is it? The Ethiopian Defence University (EDU) Telegram channel is a platform where you can engage with experts, ask questions, and learn about the latest trends and advancements in defense and security. Whether you are a student, a professional, or simply interested in staying informed about the country's defense sector, this channel offers valuable insights and resources

Join us today and be part of the conversation on defense and security in Ethiopia! Stay informed, stay connected, and become a part of the EDU community.

Ethiopian Defence University(EDU)

06 Jan, 18:21


ዩኒቨርሲቲው በፈጣን የለውጥ ግስጋሴ ላይ መሆኑ ተገለፀ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 28 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የተቋሙን የልህቀት ደረጃ በሚያሳድግና የሃገሪቱን ክብር በሚመጥን አግባብ እያሳየ የሚገኘው ፈጣን የለውጥ ግስጋሴ መላው ሠራዊታችንን የሚያኮራ እንደሆነ የመከላከያ ጀኔራል መኮንኖች የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲን በጎበኙበት እለት አረጋግጠዋል ።

የዩኒቨርሲቲውን ሁሉን አቀፍ የለውጥ ግስጋሴ ተዘዋውረው የተመለከቱት ጀኔራል መኮንኖቹ ከአካባቢያዊ የውበት ገፅታው ጀምሮ በትምህርት ፣ በምርምር ፣በልማት ስራዎች በጠንካራ ሪፎርም ታግዞ ያመጣው ተጨባጭ ለውጥ ለሌላውም በአራዓያ ሊወሰድ የሚገባ እንደሆነም የሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች ገልፀዋል ።

የተቋሙ ቀልጣፋ የለውጥ ሂደት የሚያመላክተው የአመራሩን በሳል የአመራር ሰጭነት ቁርጠኛ መሆኑን የሚያሳይ ነው ያሉት ጀኔራል መኮንኖቹ ዩኒቨርሲቲው ከባለድርሻዎች ጋር ያለው ስኬታማ ትስስርና ቅንጅት የለውጡ ማሳያ መሆኑንም በትኩረት ተገንዝበዋል ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የያዘውን ሁለንተናዊ ለውጥ አጠናክሮ በመቀጠል ወደ ፊት የሰራዊታችንን የልህቀት ደረጃ በተለያዩ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ያላቸውን ሙሉ እምነት ገልፀዋል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

03 Jan, 05:25


የኢትዮ ቴሌኮም አመራሮች የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲን ጎብኝተዋል ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም

በኢትዮ ቴሌኮም ችፍ ቴክኖሎጂ ኦፊሰር አቶ ታሪኩ ደምሴ የተመራ ቡድን በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ እየተሰሩ የሚገኙ የትምህርት ፕሮግራሞች ፣ የጥናትና የምርምር ውጤቶች ፣የአይሲቲ መሰረተ ልማቶች ፣ የመማሪያ ክፍሎች እና ሌሎች አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ዲፓርትመንቶችን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል ።

በሃገራችን ሁለንተናዊ የለውጥ አውድ ላይ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተ የሚገኘው የአንጋፋው ተቋም አመራሮች መጣችሁ ስለጎበኛችሁን ደስተኞች ነን ያሉት የዩኒቨርሲቲው ኮማንዳንት ብርጋዲየረ ጀኔራል ከበደ ረጋሣ ኢትዮ ቴሌኮም በዩኒቨርሲቲው የለውጥ ሂደት ላይ መሟላት ያለባቸውን የመሰረተ ልማት ጉድለቶች ተገንዝቦ የቀጣይ ትውልድን በሚጠቅም አግባብ የራሱን የልማት አሻራ በማሳረፍ አርአያ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል ።

የሃገራችን ዳር ድንበር ክብርና ነፃነት በአየር ፣በምድር ፣በባህር እና በሳይበር ሌትና ቀን አይኑን ለአፍታ ሳይነቅል በጀግንነት እየጠበቀ የሚገኘውን የመከላከያ ሠራዊት በቴክኖሎጂ እውቀት የበቃ አድርጎ ለማዘመን ዩኒቨርሲቲው በመንግስትና በተቋም ትልቅ ተልዕኮ ተቀብሏል ያሉት ኮማንዳንቱ የሳይበር ስነ ምህዳሩን በማስፋት እየተስተዋለ ባለው የቀጠናው አውድ ላይ ሙያተኞችን በእውቀትና በክህሎት ብቁ አድርጎ ማፍራት አንዲቻል የሁሉም ሃገር ወዳድ ተቋማት በጎ ፍላጎት ሊኖር ይገባል ብለዋል ።

ዩኒቨርሲቲው የመከላከያን ክብር በልህቀት ማረጋገጥ በሚያስችል አግባብ  በትምህርትና በምርምር የተሻለ ሆኖ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ተደራሽ በማድረግ ከሃገራችን አልፎ በአህጉራችን ላይ ተዕፅኖ ፈጣሪ እንዲሆን እንደ ሀገር ሁሉም የዩኒቨርሲቲውን
የለውጥ ሂደት በተግባር በመደገፍ የድርሻውን አሳርፎ  ሃገራዊ ፍቅሩን መግለፅ አለበት ሲሉም ጀኔራል መኮንኑ ጥሪ አቅርበዋል።

የዩኒቨርሲቲው አሁናዊ ዘርፈ ብዙ የለውጥ ሂደት የሃገራችንን ክብር የሚመጥንና የሠራዊታችንን የእውቀት ቴክኖሎጅ በማድረግ ብቃት በሚያረጋግጥ አግባብ ላይ መሆኑ በብዙ መሠረታዊ ነገሮች እንዲደገፍ የሚያስገድድ ነው ያሉት አቶ ታሪኩ ደምሴ ኢትዮ ቴሌኮም በዩኒቨርሲቲው አስፈላጊ መሰረታዊ ክፍተቶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ በማጥናት የአለኝታነት ሚናውን በፍጥነት አንደሚወጣም አረጋግጠዋል ።

የሃገራችን መከላከያ  ሠራዊት ብቸኛው ወታደራዊ ከፍተኛ የትምህርት ማዓከል እንደ ሌሎች ሃገሮች ሁሉ የተለያዩ ጠቃሚና ተመራጭ የቴክኖሎጅ ውጤቶች በጥናትና ምርምር ግኝት የሚደረግበት እንዲሆን የዘረፉ ተቋማት ሁሉ  ከዩኒቨርሲቲው ጋር ልምድና እውቀታቸውን በማጋራት ተሳስረውና ተቀናጅተው መስራት ይገባል ሲሉም ችፍ ቴክኖሎጅ ኦፊሰሩ አመላክተዋል ።

ሉዕካን ቡድኑ በዩኒቨርሲቲው ኢንጅነሪግ ኮሌጅ ስር ከሚገኙ የትምህርት ዲፓርትመንቶች መካከል አርማመንት ዲፓርትመንት ፣ፓወር ኢንጅነሪግ ፣ኤሌክትሪካል ኢንጅነሪግ ፣ራዳር ላብ እና ዳታ ቤዝ ሩሞችን ተዘዋውሮ በመመልከት የበለጠ ቢሰፋና በአሁናዊ የቴክኖሎጅ ውጤት ቢታገዙ አገልግሎታቸው የበለጠ ፈጣን ፣ውጤታማና ምቹ ይሆናል ሲሉ ሃሳባቸውን አሥቀምጠዋል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ በላይነህ ፈንቴ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

01 Jan, 17:57


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚንስትር ዶክተር በለጠ ሞላ እና የተጠሪ ተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲን ሲጎበኙ .............

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

01 Jan, 05:08


ሀገሪቱ በአስፈላጊ ቴክኖሎጂዎች ላይ ትልቅ አቅም እንድትፈጥር ዩኒቨርሲቲው እየሰራ ነው ፦
       ዶክተር በለጠ ሞላ

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 23 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ሃገሪቱ በቀጣይ በአስፈላጊ ቴክኖሎጂዎች ላይ ትልቅ አቅም እንድትፈጥር በትምህርትና በምርምር ስራዎች ላይ እየተወጣ ያለው ሚና አይተኬ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶክተር በለጠ ሞላ እና የተጠሪ ተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች የዩኒቨርሲቲውን ሁሉን አቀፍ የተልዕኮ አፈፃፀም ተዘዋውረው በጎበኙበት ዕለት አረጋግጠዋል።

ዩኒቨርሲቲው ሃገሪቱ ልትጠይቀው የሚችለውን የወትሮ ዝግጁነት አቅም ከአሁናዊ ቀጠናዊ ሁኔታው ጋር አናቦ በቁጭት ፣ በጥራት እና በትጋት እየሰራ ያለው ዘረፈ ብዙ ወታደራዊ የምርምር ስራ የመከላከያን የልህቀት ደረጃ በፍጥነትና በስኬት ሊያረጋግጥ የሚችል እንደሆነ መገንዘባቸውን ሚኒስትሩ ዶክተር በለጠ ሞላ ገልፀዋል።

በአዲስ ምልከታ ተቋሙን እንደገና አድሶ ተመራጭ ለማድረግ እየተሰራ ያለው ስራ እንደ ተቋምና እንደ ሃገር የሚያኮራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የመከላከያ ሠራዊታችንን በወታደራዊ የምርምር ዘርፎችና በቴክኖሎጂ ሽግግር ውጤቶች ላይ በቀጥታ ተጠቃሚ እንዲሆን ዘርፉ የሚመለከታቸው የሃገሪቱ ተቋማት ሁሉ ከዩኒቨርሲቲው ጋረ በቅንጅትና በትስስር በመስራት  የታሪክ ተመራጭነታቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋልም ብለዋል።

ሃገሪቱ የሚያስፈልጋትን ተመራጭ የቴክኖሎጂ አቅም ለመፍጠር ሁላችንም በተሰማራንበት ዘርፍ ላይ እንደ ወታደር በመሆን በታሪክ የሚዘልቅና ለትውልድ የሚጠቅም ስራ ሰርቶ ማለፍ ይጠበቃል ያሉት ዶክተር በለጠ ሞላ የዩኒቨርሲቲውን አቅም በቀጣይ ለማጠናከር ሚኒስትሩ በስሩ ከሚገኙ ተጠሪ ተቋማት ጋር በስፔስ ቴክኖሎጂ፣ በባዮና ኢመርጅንግ ዘርፍ ፣በአይሲቲ መሰረተ ልማት ፣ በሪቨርስ ኢንጅነሪግ ፣በሰው ሃብት ልማት እና በሌሎች ተቋሙን በሚያግዙ ዘርፎች ላይ የጋራ እቅድ አውጥቶ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኮማንዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሣ ዩኒቨርሲቲው እየሰራቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ጠቃሚ ስራዎች በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ቢደገፉ የሃገሪቱንና የተቋሙን የለውጥ ፍላጎት ማሳካት እንደሚቻል ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።

በሀገር ደረጃ ትልቅ አቅም ያለውን ከፍተኛ ወታደራዊ የትምህርት ማዕከል በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲጠናከር በማድረግ በኩል ከሚኒስትሩና ከተጠሪ ተቋማቱ ብዙ ይጠበቃል ያሉት ኮማንዳንቱ የተሻለ ትስስርና ቅንጅት በመፍጠር ለተቋምና ለሃገር ጥቅም ላይ የሚውሉ ስራዎችን በስኬት ከውኖ ታሪክ ማስቀመጥ  ያስፈልጋል ሲሉም አስገንዝበዋል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ በላይነህ ፈንቴ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

30 Dec, 12:20


ዩኒቨርሲቲው በበጋ ወቅት በመስኖ ለሚያለማው የጓሮ አትክልት ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ነው።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 21 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከተልዕኮው ባሻገር የጓሮ አትክልት የሚሰጠውን ጥቅምና ፋይዳ ተገንዝቦ የምግብ ዋስትናን በተሻለ አግባብ ለማረጋገጥ እና የተመጣጠነ የአመጋገብ ሰርዓቱን እውን ለማድረግ በበጋ ወቅት በመስኖ ለሚያለማው የጓሮ አትክልት የቅድመ ዝግጅት ስራ እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቋል።

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ዘርፎች ላይ የገቢ ማመንጨት እቅዱን አሳድጎ በመስራት የአምራችነት ሚናውን ተደራሽ በሆነ ውጤት በመቀየር የሰራተኛውን የኑሮ ውድነት ጫና በተወሰነ መልኩ ማቃለል የሚያስችል ተስፋ ሰጪ የልማት ስራዎች ላይ በትኩረት አጠናክሮ እየሰራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኮማንዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሳ ተናግረዋል ።

ተቋሙ የጓሮ አትክልት ልማት የሚሰጠውን ጥቅም በውል ተገንዝቦ የበጋን መስኖ በመጠቀም ንፁህና ለጤና ተስማሚ የሆኑ የተለያዩ ተወዳጅ የአትክልትና የፍራፍሬ ተዋፅኦዎችን በማልማት የግቢውን ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ ተጠቃሚ ለማድረግ ነገን አልሞ በተስፋ እየሰራ የሚገኝ የትምህርት ተቋም እንደሆነ ኮማንዳቱ ገልፀዋል።

ዩኒቨርሲቲው ከባለፈው አመት ጀምሮ መደበኛ የግብርና ልማት ስራዎችን በግቢው ውስጥና ከግቢው ውጪ የልማት ፍላጎቱን በብዙ ዘርፍ እያሰፋ መምጣቱ እንደ ተቋምና እንደ ሃገር ከምግብ ሰብል ተረጅነት ለመላቀቅ በሁሉም አውድ እየተደረገ ያለውን የልማት ንቅናቄ ውጤታማ የሚያደርግ መሆኑንም ጀኔራል መኮንኑ አረጋግጠዋል።

ዩኒቨርሲቲው የእርሻ ስራን ከማዘመን አንፃር ራሱን ችሎ ግሪን ሃውስ በመስራት በተለያዩ ዘዴዎች የምርት መጠንን የሚጨምሩ ምርጥ ዘሮችን እያበለፀገ እንደሚገኝ እና ከተለያዩ ተረፈ ምርቶች የተፈጥሮ ማዳበሪያን ከነሪያክተሩ በመስራት ለአካባቢውና ለሃገር የልማት እድገት ጥቅም ላይ የሚውሉ የምርምር ስራዎችንም ግብርናውን በሚያግዝ መልኩ በፍጥነትና በጥራት አየተሰሩ እንደሆነም ኮማንዳንቱ አመላክተዋል።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ በላይነህ ፈንቴ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

29 Dec, 09:50


የምርምርና ልማት ኢንስቲትዩቱ የመከላከያን አቅም ሊያሳድጉ የሚችሉ የምርምር ፕሮጀክቶችን እየሰራ ነው።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 20 ቀን 2017 ዓ.ም

ለመከላከያ ሠራዊት በቀጥታ ጥቅም ላይ መዋል የሚችሉ የተለያዩ ወታደራዊ የጦር መሳሪያዎችን በሪበርስ ኢንጅነሪግ ላይ ውጤታማ አድርጎ በፍጥነትና በጥራት እየሰራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ልማት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ሌተናል ኮሎኔል ዶክተር በሱፍቃድ ነጋሽ ተናግረዋል።

ክፍሉ በእቅድና በፕሮግራም የጥናትና የምርምር ስራዎችን ትኩረት ሰጥቶ በጥንቃቄ በመምራት ብቁ የሠው ሃይል በእውቀትና በክህሎት የተሻለ አድርጎ ከማፍራት እስከ ዘመናዊ ወታደራዊ ትጥቅ ድረስ ክፍተቶችን ተመራምሮ በግኝት ለመሙላት በስኬት እየተረባረበ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ሂደቱ በተጓዳኝ በምርምርና ጥናት ስራዎች ላይ ከፍተኛ ትኩረት በማድረግ ሠራዊታችንን መጥቀም የሚችሉ በርካታ ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶች ተግባራዊ እንዲሆኑ ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ መንገዶችን በማመቻቼት ለውጤት እየሰራ እንደሆነ ዶክተር በሱፍቃድ ገልፀዋል ።

የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም የተሻለ ማድረግ የሚችል ክትትልና ቁጥጥር እንደ አመራር አጠናክሮ በመስራት ለስራው ጥራትና ቅልጥፍና ተጨማሪ አጋዥ መሆን የሚችሉ አጫጭር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችም ለሙያተኛው በእቅድ እየተሰጡ እንደሆነም ሌተናል ኮሎኔል በሱፍቃድ አመላክተዋል ።

ክፍሉ የዩኒቨርሲቲውን ተልእኮ መሠረት አድርጎ በመስራት የሃገሪቱን እና የመከላከያን ፍላጎት ማሟላት በሚያስችል አግባብ የተጀመሩ ችግር ፈቺ ፕሮጀክቶችን በፍጥነትና በጥራት ተሰርተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ በሚያደርግ ሂደት ላይ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ልማት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ሌተናል ኮሎኔል ዶክተር በሱፍቃድ ነጋሽ አረጋግጠዋል ።

የዩኒቨርሲቲው ምርመርና ልማት ኢንስቲትዩት እየሰራቸው የሚገኙ በርካታ ችግር ፈቺ የምርምር ፕሮጀክቶችን በቅርበት በመከታተልና አመራር በመስጠት ከዩኒቨርሲቲው ኮማንዳንት ጀምሮ የተቋሙና የሃገሪቱ ከፍተኛ አመራሮች በቅርበት በመከታተል ያላቸው ሚና ከፍተኛ ነው ሲሉም ዳይሬክተሩ አመስግነዋል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ በላይነህ ፈንቴ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

28 Dec, 16:58


የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የግማሽ ዓመቱን የሴሚስተር ውጤት በስኬት ማረጋገጥ በሚያስችል ጠንካራ የመማር ማስተማር ሂደት ላይ መሆናቸው ተገለፀ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የበጀት ዓመቱን የግማሽ ሴሚስተር ውጤት በስኬታማነት ማረጋገጥ በሚያስችል ጠንካራ የመማር ማስተማረ አግባብ ላይ መሆናቸውን የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ተስፋዬ ቶሉ ገልፀዋል ።

በሁሉም የዩኒቨርሲቲው ኮሌጆች የሚገኙ ተማሪዎች በሚማሩባቸው የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ጊዚያቸውን በአግባቡ ጥቅም ላይ አድርገው ዘውትር በመማር ፣በማጥናት እና በመስራት ላይ መሆናቸው የግማሽ ዓመቱን የሴሚስተር ውጤት እንደ ዩኒቨርሲቲ በተሻለ አግባብ ማረጋገጥ እንደሚቻል ምክትል ፕሬዝዳንቱ ያላቸውን እምነት አረጋግጠዋል ።

ተማሪዎች የመረዳት ፣ የማገናዘብ ፣የማሰብ ፣የማሰላሰል እና ጠንቅቆ የመመልከት ሚናቸውን በተሻለ ትምህርትና በጠንካራ ጥናት አጎልብተው የግማሽ አመቱን የሴሚስተር ውጤት ስኬታማ አድርገው ተመራጭ ለመሆን ቀን በትምህርት ላይ ማታ ደግሞ በላይብረሪዎች ላይ አተኩረው እንደሚገኙ ዶክተር ተስፋዬ ቶሉ አመላክተዋል ።

ጊዜውን በፕሮግራም ከፋፍሎ የሚጠቀም ተማሪ ለማንኛውም ስኬት ቅርብ ነው ያሉት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ተማሪዎች የጥረትን ቁርጠኝነት የትጋትን አሸናፊነት በጥናትና በማሰላሰል ሂደት አጎልብተው እያንዳንዱን የትምህርት ፕሮግራም በተመራጭ ውጤት ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል ሲሉም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የበጀት አመቱን የመማር ማስተማር እቅድ በጠንካራ ውጤት የተሻለ ሆኖ ለመፈፀም የተለያዩ የትምህርት አሰራር ስርዓቶችን ነድፎ በትኩረት እየሰራ እነደሚገኝም ዶክተር ተስፋዬ ቶሉ አስታውሰዋል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ በላይነህ ፈንቴ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

28 Dec, 08:18


ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የጤና ትምህርት ተሠጠ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ/ም

ለኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በኤች አይቪ ኤድስ ፣ በአባላዘር በሽታዎች እና በሌሎች ተላላፊ በሽታዎች ዙሪያ ላይ ያተኮረ የጤና ትምህረት ተሰጥቷል ።

በኤች አይቪ ኤድስ በሽታ ዙሪያ እንደ ሃገር እየተሰጠ የሚገኘው ትኩረት ዝቅተኛ በመሆኑ የተጋላጭነቱ ውጤት ከቀን ወደ ቀን በአሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በተሰጠው የጤና ትምህርት ላይ በጥልቀት ማረጋገጥ ተችሏል ።

የበሽታውን ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍ እያደረጉት ከሚገኙ የመተላለፊያ መንገዶች መካከል ጥንቃቄ የጎደለው የግብረ ስጋ ግንኙነት ፣የአቻ ግፊት ተፅዕኖ እና አሁናዊ በሽታው እንደጠፋ የተሳሳተ ግምታዊ አስተሳሰብ መያዝ መሆናቸው በዝርዝር ተመላክቶ ግንዛቤ ተሰጥቷል ።

ተማሪዎች ቅድሚያ ለጤናቸው መጠበቅ ከፍተኛ ጥንቃቄ በማድረግ የበሽታውን ስርጭት መግታት የሚችሉ የተለያዩ ክለባትን በማቋቋም እንደ አካባቢ ፣ እንደ ተቋም እና እንደ ሃገር የተሻሉ ቀስቃሽ ግንዛቤዎችን ሊፈጥሩ የሚችሉ ስራዎችን መሰራትና ተመራጭ ውጤት ማምጣት እንዳለባቸውም ተጠቁሟል ።

በሌሎች ተላላፊ በሆኑ የአባላዘር በሽታዎች ላይም ሠፊ ማብራሪያ በማዓከል ተማሪዎች የትምህርት ፣ የጥናት እና የምርምር ጊዚያቸውን ማስተጓጎል የሚችሉ የተለያዩ የጤና መታወክ ችግር እንዳይገጥማቸው ከግል ንፅህና ጀምረው ከፍተኛ ትኩረትና ጥንቃቄ በማድረግ እራሳቸውን መጠበቅ እንዳለባቸው ተጠቅሷል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፍንቴ
ፎቶ ግራፍ በላይነህ ፈንቴ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

23 Dec, 12:20


ክለቡ አምስተኛ ጨዋታውን በሰፊ ውጤት አሸንፎ  ወደ ሚቀጥለው ማለፉን አረጋገጠ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ታህሣሥ 14 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኡዴ ደንካካን 11 ለ 1 በሆነ ከፍተኛ ሠፊ ውጤት በማሸነፍ አንድ ቀሪ ጨዋታ አያለው ከምድ ቡ 15 ነጥብ እና ንጹህ 20 ጎል ይዞ ወደ ስምንቱ ማለፉን አረጋግጧል ።

ተጫዋቾች የዩኒቨርሲቲውን ክብር ፣ ስም እና ዝና ማስጠራት በሚያስችል ጠንካራ ሞራል የሚያደርጉት የልምምድ ውጤት በእያንዳንዱ ግጥሚያ ላይ ስኬታማ ድል እያስመዘገብን እንድናልፍ አድርጎናል ያሉት የክለቡ ዋና አሰልጣኝ ኮች ሻምበል አንዷለም ከበበው ሁሉንም የክለቡ ተጫዋቾችና የስፖርት ቤተሰቡን ከልብ አመስግነዋል ።

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

23 Dec, 05:34


"ስፖርት ለሁሉም በሁሉም ቦታ" መርሃ ግብር በመካሄድ ላይ ነው።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 14 ቀን 2017 ዓ/ም

የዘንድሮ የ2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ፌስቲቫል በድምቀት በመካሄድ ላይ ነው ።

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

21 Dec, 03:55


Ethiopia and Nigeria's top defense leaders are consulting in Nigeria on matters that will enable them to work together.

Federal Defense Forces on December 11, 2017

A delegation led by Brigadier General Kebede Regasa, Commandant of the Ethiopian Defense University, is at the headquarters of the Federal Republic of Nigeria to discuss bilateral military issues.

The discussion focused on common issues that can be used to increase the military professionalism of the Ethiopian and Nigerian defense forces in the field of education and training.

The military delegation led by Brigadier General Kebede Regasa will visit the country's defense institutions to work together on education, training, experience and similar issues that will benefit the defense forces of the two countries.

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

WE STRIVE FOR EXCELLENCE OF NATIONAL DEFENCE

Ethiopian Defence University(EDU)

08 Dec, 15:48


የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ እግር ኳስ ክለብ ምድቡን በዘጠኝ ነጠብ እየመራ እንደሆነ አስታወቀ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ የኒቨርሲቲ ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ እግር ኳስ ክለብ በዛሬው እለት ቢሾፍቱ ከተማ እያካሄደ በሚገኘው የክለቦች ውድድር ላይ ቶኩማን የእግር ኳስ ክለብን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፎ ምድቡን በዘጠኝ ነጥብ መምራት መቻሉን አረጋግጧል ።

ውድድሩ ከተጀመረ እስካሁን ሶስተኛ ጨዋታውን ያደረገው የዩኒቨርሲቲው እግር ኳስ ክለብ በተከታታይ ባደረጋቸው ጨዋታዎች ላይ የአሸናፊነት ድሉን በማስመዝገብ ምድቡን በዘጠኝ ነጥብ በመምራት አንደኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ክለቡ አስታውቋል ።

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

06 Dec, 18:00


የዩኒቨርሲቲው አመታዊ የስፖርት ፌስቲቫል ተጀምሯል ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሳቲ ህዳር 27 ቀን 2017ዓ/ም

"ስፖርት ለሁሉም በሁሉም ቦታ" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ዓ/ም የስፖርት ፌስቲቫል መርሃ ግብር በተለያዩ ስፖርታዊ ዝግጅቶች ላይ ማስጀመሩን አስታውቋል ።

በእለቱ ተገኝተው የመክፈቻ ስነ ስርዓቱን ያስጀመሩት የዩኒቨርሲቲው የሪሶርስ ማኔጅመንት ኮሌጅ አዛዥ ተወካይ ኮሎኔል መላኩ ደመላሽ ተመራጭ በሆነ ስፖርታዊ ጨዋነታችን መርሃ ግብሩን በማከናወን ዩኒቨርሲቲውን የሚያስጠሩ ብቁ ስፖርተኞችን ማፍራት የሁሉም ሃላፊነት ሊሆን ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል ።

በእግር ኳስ ውድድር መክፈቻውን ያደረገው የዩኒቨርሲቲው አመታዊ የስፖርት ፌስቲቫል መርሃ ግብር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት የሪሶርስ ማኔጅመንት ኮሌጅ አቻውን በማሸነፍ የመጀመሪያ ድሉን በስኬት ማረጋገጥ ችሏል ።

ተወዳጁና ተናፋቂው የዩኒቨርሲቲው አመታዊ የስፖርት ፌስቲቫል ብቁ ስፖርተኞችን በቴክኒክና በስነ ምግባር የተሻሉ አድርጎ ከማፍራት ባለፈ በስፖርት ቤተሰቡ ስነ አዕምሮ ላይ የሚፈጥረው በጎ ፉክክርና ተነሳሽነት የማይረሳ ነው ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

06 Dec, 17:27


የፀረ ፆታ ጥቃት በዩኒቨርሲቲው ተከብሮ ውሏል ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሳቲ ህዳር 27 ቀን 2017ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ"የሴቷ ጥቃት የእኔም ነው ፤ ዝም አልልም" በሚል መሪ ሃሳብ በአለም አቀፍ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ በአገራችን ደግሞ ለ19ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ የነጭ ሪቫን ቀን በዛሬው እለት በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል ።

በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች በጤና ላይ አካላዊ ችግር ከመፍጠር ባለፈ በስነ አዕምሮ ፣በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ዙሪያም የሚፈጥሩት አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ እንደሆነ በእለቱ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው የሰው ሃብት ልማትና ጠቅላላ አገልግሎት ምክትል ኮማንዳንት ተወካይ ኮሎኔል ደረጄ ቀልቤሳ ተናግረዋል ።

በየጊዜው ግንዛቤ በመፍጠር መሰራት እንዳለበት የጠቆሙት ከፍተኛ መኮንኑ ሴቶች በይቻላል መንፈስ ታግዘው በሁሉም መስክ ከወንዶች ጋር እኩል ውጤታማ ስራ እያከናወኑ መምጣታቸውንም አክለው አስረድተዋል ።

የነጭ ሪቫን ቀን የሚከበረው በሴቶች ላይ የተለያዩ ፆታዊ ጥቃቶች እንዳይፈፀሙ ግንዛቤ ለመፍጠር እና የሴቶች መብት ተከብሮ ኢኮኖሚያዊ ፣ማህበራዊ እና ስነ ልቦናዊ አቅማቸውን በማሳደግ በሁሉም አውድ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል ነው ያሉት ደግሞ የዩኒቨርሲቲው ስርዓተ ፆታ ቡድን መሪ ሌተናል ኮሎኔል ኤልሳቤት አዳነ ናቸው ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ ሠፊ ነጊ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

06 Dec, 07:35


የሥነ ልቦና ዳይሬክቶሬቱ ተወዳጅ የሻሂ ቡና ፕሮግራም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 27ቀን 2017 ዓ /ም

የኢትዮጵየ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ  ዳይሬክቶሬት የአባላቱን አንድነትና አብሮነት በፍቅር በማስተሳሰር ጠንካራ የስራ ሞራልን ማነሳሳት በሚያስችል አግባብ ተወዳጅ የሻሂ ቡና ፕሮግራም በመስራት የአራዓያነት ሚናውን በተግባር እየተወጣ ነው ።

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

24 Nov, 08:31


ዩኒቨርሲቲው በልማት ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራት ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ ነው ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 15 ቀን 2017ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በምግብ እራስን የመቻል ንቅናቄን መሠረት አድርጎ በመስራት ከጓሮ አትክልት እስከ በርሃ ድረስ ወርድ ሰፋፊ እርሻዎችን በማረስ ከፍተኛ ውጤት በተግባር ማረጋገጥ ችሏል።

ዩኒቨርሲቲው አካባቢያዊ የውበት ገፅታውን ምቹና ማራኪ ከማድረግ ባለፈ በተለያዩ የጓሮ አትክልቶች ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራት ለግቢው ማህበረሰብ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እየሰጠ ነው።

ዩኒቨርሲቲው ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ቅንጅትና ትስር በመፍጠር የተለያዩ የልማት አማራጮች ላይ ትኩረት አድረጎ በመሰራት በብዙ ውጤት ተጠቃሚ የሚያደርገውን የአሰራር ልምድ እንዳገኘም በአመጣው ውጤት ማረጋገጥ ችሏል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ መከላከያ የያዘውን ከፍተኛ የልማት አቅጣጫ የበለጠ ውጤታማ የሚያደርግ እና የሰው ሃይል ጉልበትን በቀላሉ የሚቀንስ ዘመናዊ የግብርና አሰራር ሲስተሞችን በተለያዩ አመራጮች  ላይ እየተመራመረ እንደሚገኝም ተመላክቷል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ አማኑኤል ታደሰ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

24 Nov, 03:08


ዩኒቨርሲቲው ስፋትና ልህቀቱን ውጤታማ በማድረግ በአፍሪካዊ ሃገራት ላይ ተመራጭ እየሆነ መጥቷል ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 15 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የመከላከያን ወታደራዊ የውጊያ አቅም ሊያሳግ የሚችል የሠው ሃይል በእውቀትና በክህሎት የላቀ አድርጎ በማፍራት ዘመኑን የዋጁ የቴክኖሎጅ ውጤቶችን ተደራሽ ለማድረግ እየተጋ የሚገኝ ተመራጭ ተቋም ነው ።

ዩኒቨርሲቲው የሃገሪቱን ወታደራዊ እና ቀጠናዊ የድፕሎማሲያዊ ግንኙነት ዘርፍ ሊያሳድግ በሚችል አግባብ የተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት ዜጎችን በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ እስተምሮ በማብቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ ተደራሽነቱን ከፍ እያደረገ የሚገኝ የሠራዊታችን የልህቀት ማዓከል ነው ።

የተለያዩ የውጭ ሃገራት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር በፍቅር ተዋህደው በደስተኝነት ትምህርታቸውን በመማር ጠንካራ ውጤት እያስመዘገቡ ይገኛል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ አማኑኤል ታደሰ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

23 Nov, 17:51


ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የወንጀል መከላከል ትምህርት ተሰጠ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 14 ቀን 2017 ዓ/ም

ለኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተሟላ ስነ ምግባርን ማረጋገጥ በሚያስችል አግባብ የወንጀል መከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መሰጠቱ ተመላክቷል።

ተማሪዎች የግቢውን መተዳደሪያ ደንብ አክብረው ተልዕኳቸውን በስርዓት በመከወን ከእምነት ማጉደል ፣ስርቆት፣አሉባልታ እና ስርዓት አልበኝነት ላይ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በሚያደርግ መልኩ የወንጀል መከላከል ትምህርቱ በጥልቀት ተሰጥቷል ።

ዩኒቨርሲቲው ወታደራዊ ፕሮፌሽናሊዝምን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ማድረግ በሚያስችል ሂደት ላይ መሆኑ ለተማሪዎች የተሟላና የተስተካከለ የስነ ምግባር ባለቤት እንዲሆኑ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነም በተለያዩ ሃሳቦች ላይ ተጠቅሷል ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት፣ከምርምር ፣ከማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት እና ከልማት ስራዎች ባሻገር አንድነትና አብሮነትን ፣ወንድማማችነትና ህብረ ብሔራዊነትን በሚያጎለብት አግባብ በተማሪዎች ስነ ዓዕምሮ ላይ እየሰራ የሚገኘው ጥልቅ የሃገር ፍቅር ስሜት ከፍተኛ ጥቅም እንዳለውም በህግ ትምህርቱ ሂደት ላይ ተመላክቷል ።

ተማሪዎች የተሟላና ተመራጭ ስነ ምግባራቸውን አጠናክረው በመቀጠል ለሌሎች የትምህርት ተቋማት አራዓያ መሆን እንዲችሉ ከትምህርት እስከ ጓዳዊ ዝምድና ከጥናት እስከ ፈጠራ ድረስ ያለውን ጠንካራ ውጤት አስጠብቀው እንዲቀጥሉ ግንዛቤ በመስጠት የወንጀል መከላከል ትምህርቱ ተጠናቋል።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ አማኑኤል ታደሰ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

22 Nov, 11:06


የ3ኛ ዓመት ሲቭል ኢንጅነሪግ ተማሪዎች በተግባር ልምምድ ላይ……

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 13 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የ3ኛ ኣመት ሲቭል ኢንጅነሪግ ተማሪዎች የተግባር ልምምድ እያደረጉ ነዉ ፡፡

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

21 Nov, 13:26


ዩኒቨረሲቲዉ ከመከላከያ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለዉን ዉይይት አደረገ ፡፡

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨረሲቲ በዛሬዉ እለት ከመከላከያ ዋር ኮሌጅ ፣ ስታፍ ኮሌጅ እና ከሰላም ማስከበር ማዓከል ጋር አንድ አይነት አስተሳሰብና ቅንጀት በመፍጠር የመከላከያን አቅም ወደፊት ማሳደግ በሚችሉ የትምህርት፣ የስልጠና እና የምርምር ስራዎች ላይ የጋራ ዉይይት አድርጓል ፡፡

የመከላከያን የዉጊያ አቅም ለማሳደግ በምህንድስና ፣በህክምና፣ በማኔጅመንት፣ በወታደራዊ ሳይንስና ሌሎችን ጨምሮ በየዘርፉ ትምህርትና ስልጠና እየሰጠ የሚገኘዉ የኢትዮጵያ መከላያከያ ዩኒቨርሲቲ ከመንግስተ በቀጥታ በጀተሪ መሆኑ የትምህርትና የምርምር ሂደቱን ስኬታማ ለማድረግ ሚናዉ ከፍተኛ እንደሆነም በዉይይቱ ተመላክቷል ፡፡

እንደ ተቋም ተባብሮና ተደጋግፎ በመስራት የመከላከያን የለዉጥ እምርታ ማረጋገጥ በሚያስችል አግባብ የአለምንና የአካባቢዉን የትምህርትና ስልጠና አካሄድ ተገንዝቦ የተሻለ ስራ ሰርቶ ማለፍ የሃገርንና የተቋምን ክብር ከማረጋገጥ በላይ ትዉልድን መጥቀም በሚያችል ሂደት ላይ ዉይይቱ ተካሂዷል ፡፡

ትምህርትና ስልጠና እየሰጡ የሚገኙ የመከላከያ የትምህርት ተቋማት የሌሎችን ሃገራት ልምድና ተሞክሮ በማምጣት የጋራ ትስስርና ቅንጅት በመፍጠር ተልዕኳቸዉን በስራ እና በዉጤት ለማረጋገጥ በጋራ እየተረባረቡ መቀጠል እንደላባቸዉም በተለያዩ ሃሳቦች ዳብሯል ፡፡

የትምህርት ተቋማቱ የተሳካ ዉይይት ካካሄዱ በኋላ በቀጣይ አብሮ መስራት የሚያስችላቸዉን የዉል ስምምነት በማድረግ ዉይይታቸዉን አጠናቀዋል ፡፡

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ አማኑኤል ታደሰ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

21 Nov, 08:15


ዩኒቨርሲቲው "ህፃናት የሚሉት አላቸው እናዳምጣቸው በሚል የህፃናትን ቀን  በተለያዩ ዝግጅቶች  አስቦ ውሏል።

የኢትዩጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ/ም

"ህፃናት የሚሉት አላቸው እናዳምጣቸው" በሚል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ35ኛ ጊዜ በሃገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ19ኛ ጊዜ የተከበረውን የህፃናት ቀን በትናንትናው እለት በዩኒቨርሲቲው ተከብሮ ውሏል ።

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

19 Nov, 12:33


የዩኒቨርሲቲዉን የለዉጥ ግስጋሴ በሁሉም አዉድ ማስቀጠል የሚችል ብቁ የአመራር ዝግጁነት አለ ሲሉ የዩኒቨረሲቲዉ ኮማንዳንት ተናገሩ ፡፡

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ እያሳየ የለዉን ሁሉን አቀፍ የለዉጥ ግስጋሴ በተደማሪ ዉጤት ማስቀጠል የሚችል ብቁ የአመራር ዝግጁነት አለ ሲሉ የዩኒቨረሲቲዉ ኮማንዳት ብርጋዴር ጀኔራል ከበደ ረጋሳ በአመራሩ የግንባታ ፕሮግራም ላይ ተገኝተዉ ተናግረዋል ፡፡

በልምድ ፣በክህሎትና በአስተሳሰብ ብቁ የአመራር ቁርጠኝነትን በመላበስ ተቋሙ የጀመረዉን የለዉጥ ማሳያ በትምህርት ጥራት፣ በምርምር ዉጤታማነት ፣ በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ተደራሽነት ፣ እና በልማት ተመራጭነት የላቀ አድርጎ በመስራት ተደማሪ ዉጤት ማረጋገጥ የሚችል ጠንካራ አመራር መገንባቱን ኮማንዳንቱ በገለፃቸዉ አረጋግጠዋል ፡፡

የመከላከያን ዘመናዊ የቴክኖሎጅ አጠቃቀም ማረጋገጥ የሚችል ብቁ የሰዉ ሃይል በእዉቀት ፣ በአስተሳሰብ እና በስነ-ምግባር ምቹ አድርጎ ማፍራት የዩኒቨርሲቲዉ ዋና ተልዕኮ መሆኑን ያስታወሱን ጀኔራል መኮንኑ የሠራዊታችንን የለዉጥ አዉድ ማረጋገጥ የሚችል ተመራጭ ስራ ሰርቶ ማሳየት ከአመራሩ ይጠበቃል ሲሉ አስገንዝበዋል ፡፡

በላይነህ ፈንቴ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

19 Nov, 12:14


የኢንጅነሪግ ኮሌጅ የ2ኛ ድግሪ ተማሪዎች የመመረቂያ ፅሁፍ እያስተቹ ነው ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኢንጅነሪንግ ኮሌጅ የ2ኛ ድግሪ ተማሪዎች የመመረቂያ ፅሁፋቸውን እያቀረቡ በማስተቸት ላይ ናቸው፡፡

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

17 Nov, 08:18


ኮሌጆቹ የዩኒቨርሲቲውን የለውጥ ግስጋሴ  ማስቀጠል በሚችል አግባብ ላይ መሆናቸውን አስታወቁ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨረሲቲ ህዳር 08 ቀን 2017 ዓ/ም

በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ስር የሚገኙት ሶስቱም ኮሌጆች የዩኒቨርሲቲውን እይታ በሁሉም አካባቢዎች በማስፋት የልህቀት ተደራሽነቱን በትምህርት ፣በምርምር ፣በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት እና በግብርና ልማት ስራዎች ላይ ተሳስረውና ተናበው በመስራት እያሳዬ ያለውን የለውጥ ግስጋሴ የበለጠ በውጤት ማስቀጠል እንደሚችሉ አረጋግጠዋል ።

ኮሌጆቹ የመማር ማስተማር ተልዕኳቸውን በእቅድና በጊዜ ፣በጥራትና በውጤት ተፈፃሚ አድርገው በመስራት የዩኒቨርሲቲውን ገናናነት ፣ተመራጭነት እና ተደራሽነት ማረጋገጥ በሚችል ተግባቦት ተዋህደው በመስራት የዩኒቨርሲቲውን እቅድ በየፈርጁ በውጤት እያሳለጡ እንደሚገኙም ገልፀዋል ።

አስደማሚ የለውጥ ገፅታን በሁሉም ዘርፍ እየገለጠ የሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የአሰራር ዘመናዊነትን አጎልብቶ የተቋማት የትብብር አድማሱን አስፍቶ ሃገርና ተቋም መጠቅም የሚያስችል ጠንካራ ስራ ለመስራት እያደረገ በሚገኘው የጎላ ርብርብ ላይ የኮሌጆቹ ሚና ከፍተኛ ድርሻ እንዳለውም አስረድተዋል ።

ኮሌጆቹ አንድ አይነት ጠንካራ የስራ ተነሳሽነትን በመፍጠር በዩኒቨርሲቲው የለውጥ ግስጋሴ ምህዋር ውስጥ ቀዳሚና ተመራጭ የሚያደርጋቸውን ልምድና ተሞክሮ አንዳቸው ከአንዳቸው እየተወራረሱ የፈጠራና የጥናት ክህሎታቸውን በማሳደግ የበጀት ዓመቱን እቅድ በውጤት ለማሳካት እየተረባረቡ እንደሆነም አመላክተዋል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ ሠፊ ነጊ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

05 Nov, 12:08


የዩኒቨርሲቲው እግር ኳስ ክለብ የመልስ ጨዋታውን አሸነፈ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የእግር ኳስ ክለብ በአዳማ ዩኒቨርሲቲ ስታድዮም ከአማያ ጋር ያደረገውን የደርሶ መልስ ጨዋታ 6 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የድል ግስጋሴውን አጠናክሮ ቀጥሏል ።

በእለቱም ጥቅምት 24/2013 ዓ/ም የሰሜን ዕዝ አራተኛ ዓመት ሰማዓታትን በማስታወስ የሁለቱም ክለብ ተጫዋቾች በጨዋታው መሃል ላይ የህሊና ፆለት በማድረግ አስበዋል ።

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

03 Nov, 08:11


የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የአራተኛ ዓመት ዝክረ ሰሜን ዕዝ መታሰቢያ አደረጉ ።

የኢፊድሪ መከላከያ ሠራዊት ጥቅምት 24 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች "ጥቅምት 24 እንዳይደገም ሁሌም እንዘክረዋለን"በሚል የአራተኛ አመት ዝክረ ሰሜን ዕዝ መታሰቢያውን አድርገዋል ።

የዩኒቨርሲቲው የሠራዊት ስነ ልቦና እና ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተወካይ ሌተናል ኮሎኔል ዘመኑ ታምር እብሪት የወለደው የፖለቲካ ተልዕኮ ያሳበዳቸው የጎጥና የድርጅት አስተሳሰብ ተቀላቢ የነበሩ የእናት ጡት ነካሹች በሠራዊታችን ላይ ጥቅምት 24 ቀን 2013  ዓ/ም የፈፀሙት ያልተገባ  ክህደት እንደ ሀገር በጥልቀት ልንማርበት የሚገባ የታሪክ አጋጣሚ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል ።

የሰሜን ዕዝ ሰማዕታት በጀግናው ሠራዊታችን ስነ ዓዕምሮ ላይ ህብርት ፣አንድነት እና ቁጭትን በመፍጠር የማይቀዘቅዝ ሞራልና የማይዝል ጉልበትን በጋራ ሰድሮ በደማቅ የሀገር ፍቅር ስሜት ወኔ አስተማማኝ የማድረግ ብቃቱን በተግባር ያስመሰከረበት ታሪክም እንደነበር ከፍተኛ መኮንኑ አስታውሰዋል ።

ሠራዊታችን ከፖለቲካ ወገንተኝነት የፀዳ ሆኖ ለህዝብ ሠላም ለሀገር ክብር ውድ ህይወቱን እየከፈለ እንደሚገኝ የገለፁት ስነ ልቦና ተወካዩ እኛም እንደ ኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከፋፋይ ከሆኑ የቡድን ፣የጎጥ እና የሃይማኖት አስተሳሰቦች ራሳችንን በመጠበቅ ለህዝብና ለሃገር ሲሉ የከፈሉትን ውድ መስዕዋትነት እያስታወስን የመማር ማስተማር ተልዕኳችንን በስኬታማነት በመወጣት የሠራዊታችንን የቴክኖሎጅ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ አለብን ብለዋል ።

ዕለቱም የህሊና ፆለት በማድረግ ፣የዝክረ ሰሜን ዕዝ የ4ኛ ዓመት መታሰቢያ ፅሁፍ በማንበብ እና የተለያዩ መልዕክቶችን በማስተላለፍ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ታስቦ ውሏል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ አማኑኤል ታደሰ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

31 Oct, 06:24


ኮሌጁ ያለማውን ሰብል እየሰበሰበ ነው ።

ኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኢንጅነሪግ ኮሌጅ በግቢው ውስጥ ያለማውን ሰብል መሰብሰብ መጀመሩን አስታውቋል ፡፡

ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በደረሱ ሰብሎች ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በሚያደርግ አግባብ ኮሌጁ እያደረገ በሚገኘው የመሰብሰብ እርብርብ ላይ የስታፍ አባላቱ እና የሲቭል ሠራተኛው ትብብር ከፍተኛ እንደሆነም ተመላክቷል ።

ዘጋቢ ሰይድ አሊ
ፎቶ ግራፍ ለታ አለማየሁ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

30 Oct, 18:20


የህፃናት ማቆያ ማዓከሉ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅቱን እያጠናቀቀ እንደሚገኝ ገለፀ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ/ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የህፃናት ማቆያ ማዓከል ሙሉ በሙሉ የተሟላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት እያጠናቀቀ እንደሚገኝ ገልጿል ።

ማዓከሉ ከአስራ አንድ ክፍል በላይ  የህፃናት ማቆያን ጨምሮ ኪችን ፣ መዝናኛ ፣ስቶር እና  የቢሮ  ክፍሎችን በውስጡ በመያዝ ህፃናቱን የሚያዝናኑ የተለያዩ መጫወቻወችንም በየ ዘርፋቸው እያሟላ ነው ።

የዩኒቨርሲቲው የህፃናት ማቆያ ማዓከል ከህፃናቱ መዝናኛ ባሻገር ለምግብ ማብሰያ የሚውሉ የተለያዩ የኪችን እቃወችንም በየ አገልግሎት ፈርጃቸው እያስገባ እንደሚገኝ በቦታው ተገኝተን ማረጋገጥ ችለናል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ አማኑኤል ታደሰ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

29 Oct, 18:03


የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲን ተመራጭ የትምህርት ተቋም አድርገው መምረጣቸው እንዳስደሰታቸው የአንደኛ አመት ሲቭል ተመሪዎች ተናገሩ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ/ም

ለ2017 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲን ተመራጭ የትምህርት ተቋም አድርገው መምረጣቸው እንዳስደሰታቸው ወደ ዩኒቨርሲቲው ለመማር የመጡ የአንደኛ ዓመት ሲቭል ተማሪዎች ተናግረዋል ።

የዩኒቨርሲቲው አካባቢያዊ የውበት ገፅታ ሳቢ እና ማራኪ ከመሆን ባሻገር የተቋሙ የውስጥ አሰራር መመሪያዎች ፣ የመከባበርና የመደማመጥ ባህል ፣የሰዓት አጠቃቀም እና ውጤታማነት ከሌሎች የተለዬ ተመራጭ እና ተወዳጅ የትምህርት ማዓከል እንደሚያደርገው ሲቭል ተማሪዎች ገልፀዋል ።

ህብረትና አንድነትን ፣ወንድማማችነት እና ብዝሃነትን በጋራ አዋህዶ የተሟላ ስነ ስርዓትን በሚያላብስ አግባብ የትምህርት አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የወታደሮች የመከባበር ባህልና ጨዋነት ፣የነባር ተማሪዎች የተሟላ ስነ ምግባር ፣የድጋፍ ሰጪ ክፍሉ ቀና አገልግሎት እና የትምህርት አመራሩ በጎ የትህትና ምላሽ  በተማሪዎች ስነ ዓዕምሮ ላይ የበለጠ ደስታ እንደፈጠረባቸውም አስረድተዋል ።

ዩኒቨርሲቲው በሁሉም የትምህርት ዘርፍ ላይ የተሟላ የመማር ማስተማር አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ የተገነዘቡት የአንደኛ አመት ሲቭል ተማሪዎች የጥናተና የምርምር ስርዓቱን የሚያፋጥኑ ዘመናዊ መርጃ መሳሪያዎችን ያካተቱ ላብራቶሪዎች እና ወርክ ሾፖች መኖራቸውም የትምህርት አሰጣጥ ስርዓቱን የበለጠ ውጤታማ እንደሚያደርገው ማስተዋላቸውን ጭምር አንስተዋል።

ተማሪዎች ከገፅታ ትምህርት በተጓዳኝ እውቀታቸውን እና ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት የዩኒቨርሲቲው የቤተ መፅሃፍት ማዓከል እየሰጠ የሚገኘው የ24 ሰዓት የተሟላ አገልግሎት የበለጠ እንዳስደሰታቸውም ሲቭል ተማሪዎች ተናግረዋል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ አማኑኤል ታደሰ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

29 Oct, 12:44


በተሰማሩበት የትምህርት ተልዕኮ ላይ ዉጤታማ እንደሚሆኑ ከሠራዊቱ ክፍሎች ተወጣጠዉ ለተምህርት የመጡ ተማሪዎች ተናገሩ ፡፡

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ/ም

በተሰማሩበት የትምህርት ተልዕኮ ላይ ጠንካራ ዉጤት በማምጣት ሠራዊታችን የሰጣቸዉን አደራ በጀግንነት እንደሚወጡ ከሁሉም ከመከላከያ ክፍሎች ወደ ኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ለትምህርት የመጡ ተማሪዎች ተናግረዋል ፡፡

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ሁለንተናዊ ገፅታ የትምህርት ተነሳሽነትን የሚያጎለብት ነዉ ያሉት ከሠራዊቱ ክፍሎች የመጡ አዲስ ተማሪዎች በተመደቡበት የትምህርት ፕሮግራም ላይ ጠንክረዉ በመማር የተሰጣቸዉን ሃላፊነት በስኬታማነት እንደሚወጡም አረጋግጠዋል ፡፡

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ አማኑኤል ታደሰ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

29 Oct, 08:40


ዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ስርዓቱን ማጎልበት የሚችል ውይይት ከመምህራኖች ጋር ማድረጉን ገለፀ ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የበጀት ዓመቱን የመማር ማስተማር ስርዓት ጠንካራ እና ተመራጭ አድርጎ በመስራት የተሻለ ውጤት ማምጣት የሚያስችለውን ውይይት ከመምህራኖች ጋር ማድረጉን ገልጿል ። 

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኮማንዳንት ብርጋዲየር ጀኔራል ከበደ ረጋሳ የትምህርት ጥራቱን በውጤት ለማረጋገጥ የመማር ማስተማር ሂደቱን ማጎልበት የሚችል ጠቃሚ የሆነ የተሻለ ሃሳብ በማምጣት ለተቋምና ለሃገር ጠቃሚ የሆነ ትውልድ በእውቀትና በክህሎት የበቃ አድርጎ መፍጠር የመምህራኖች ትልቅ ሃላፊነት ነው ብለዋል ።

ዩኒቨርሲቲው ብዙ መልካም ስራዎችን በስኬታማነት እየሰራ ነው በዚህ ውስጥ ደግሞ የመምህራኖች ሚና ከፍተኛ ነው ያሉት ኮማንዳንቱ ጊዜውን በአግባቡ የሚጠቀም የሃገርና የተቋም ተቆሮቋሪ የሆነ ተማሪን በማፍራት ሂደት የዩኒቨርሲቲውን ገናናነት በውጤት ማስጠራት እንዲችሉም አስረድተዋል ።

ዩኒቨርሲቲው የመምህራኖችን አስተዳደራዊ ችግሮች በተጓዳኝ ለመፍታት በሂደት እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ጀኔራል መኮንኑ ከሌሎች የትምህርት ተቋማት ጋር ቅንጅትና ትስስር በመፍጠር በኩልም በትምህርት ፣በጥናትና ምርምር ዘርፍ ላይ ለተቋምና ለሃገር የሚውል ጠንካራና ጠቃሚ ሃሳብ ማቅረብ ከመምህራን የሚጠበቅ ቀዳሚ ተግባር ነው ሲሉ አስገንዝበዋል ።

የመማር ማስተማር አገልግሎቱ ውጤት በሚያመጣ አግባብ ጥራት ያለው አድርጎ ለመስራት በአካዳሚክ ዘርፋ ውሰጥ የሚስተዋሉ አስተዳዳራዊ ችግሮች ካሉ በውይይት ለይቶ በማውጣት መፍታትና ማጠናከር እንደሚገባም  ጀኔራሉ አመላክተዋል።

ዩኒቨርሲቲው የሠራዊታችንን ዘመናዊ የቴክኖሎጅ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ በሚገኘው ጠንካራ የምርምር ስራዎች ላይ መምህራኖች ግንባር ቀደም ተዋናይ በመሆን  ታሪካዊ ስራ ሰርተው የዩኒቨርሲቲውን ውጤታማነት ማረጋገጥ እንዲችሉም ኮማንዳንቱ ጥሪ አቅርበዋል ።

ዘጋቢ በላይነህ ፈንቴ
ፎቶ ግራፍ አማኑኤል ታደሰ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !

Ethiopian Defence University(EDU)

28 Oct, 08:52


በትውልዱ ስነ ዓዕምሮ ላይ ጠንካራ የሆነ የሀገር ፍቅር ስሜት እንዲጎለብት አድርጎ መስራት ያስፈልጋል ።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጥቅምት 18  ቀን 2017 ዓ/ም

የዛሬን ችግር ሳይሆን የነገን ተስፋ በሚያመላክት አግባብ በልጆች ስነ ዓዕምሮ ላይ  በህብረ ብሔራዊነት የደመቀች  ፣የምትወደድ እና  የተከበረች ፣በተስፋ የለመለመችና ያማረች ኢትዮጵያን መፍጠር የሚያስችል ግንዛቤ መስጠት ተገቢ ነው ።

የነገ የሀገር ተረካቢው ትውልድ የሀገር ፍቅር ስሜቱ ጠንካራ ፣ጥልቅ እና በተስፋ የተሞላ እንዲሆን በሚያስችል አግባብ ሀገሩን የሚወድ ፣ስለ ሃገሩ የሚቆረቆር ፣ሃገራዊ ወንድማማችነትን አጥብቆ የሚፈልግ እና ነገን በተስፋ የሚያልም ስነ ዓዕምሮ እንዲኖረው አድርጎት መስራት
ከመቸውም ጊዜ በላይ ያስፈለጋል ።

ሀገሩን የሚወድ ዜጋ ሁሉ የሀገሩን መከላከያ ሠራዊት ያከብራል ፣ይወዳል  ፣ይደግፋል ይህ ደግሞ ሊሆን የሚችለው በሀገር ፍቅር ስሜት የተገነባ ትውልድ በጥልቀት ሲፈጠር ብቻ ነው  ።

የሀገር ዳር ድንበር ፣ክብርና ነፃነት ሚስጥር በውል የሚገባው ትውልድ ሁሉ ለሠላሙና ለልማቱ ዋስትና እና መከታ በሆነው የሀገሩ መከላከያ ሠራዊት በጀግንነቱ ኮርቶ፣በማድረግ ብቃቱ ተማምኖ ይደግፋል፣ ያበረታታል፣ያከብራል ።

ለሀገር ሉዓላዊነት ክብርና ነፃነት መሠረቱ ጠንካራ የሆነ ሠራዊት መገንባት እንደሆነ ጠንቅቀው የሚገነዘቡ ዜጎች ትልቅ ትንሽ ሳይሉ የሠራዊታቸውን የመስዋትነት  ውለታ በክብሩ ቀን በጋራ ቁመው ስምና ዝናውን ከፍ አድርገው በድምቀት ይዘክራሉ ።

በላይነህ ፈንቴ

📌telegram channel
👇👇👇👇
https://t.me/EthiopianDefenseUniversity
📌website 🌍
👇👇👇👇
http://www.etdu.edu.et
📌Facebook
👇👇👇👇
https://www.Facebook.com/ethdefuni

ለመከላከያ ሰራዊታችን ልህቀት እንተጋለን !