ጦብያን በታሪክ @ethiopiainhistory Channel on Telegram

ጦብያን በታሪክ

@ethiopiainhistory


ኖር

— ስለ ኢትዮጵያ የማነባቸውን /አልፎ አልፎም ጉዞዎቼን/ እዚህ አስቀምጣለሁ ደስ ካላችሁ አንብቡ። ሌሎች ከኢትዮጵያ ያልሆኑ ነገሮችን ባጋራም አብዛኛው ከወዲህ ነው፡፡

Predominantly (but not strictly) about Ethiopia and Ethiopian history. @hewansemon

ጦብያን በታሪክ (Amharic)

ጦብያን በታሪክ ለማንኛውም እናቶችና እናቶች ልጆች በእናትና ልጆቹን አሳዝናለን። ይህን የታሪክ ድራማ በመጠቀም ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊ ታሪኮች የሚገኘውን የሚያስፈልገውን ክፍል እንነሳ። ኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያ ታሪኮች እንዴት አድርገው ማምረቱን ማከብከብ ካለበት እንደኛና ላለበት አገልግሎት በቀር ለማንኛውም ኢትዮጵያዊ ታሪክ የተመረጠው ኬሚችንም በነንጉ ትዕዛዝ ሳይሆን ለመካሄድ የሚጠይቅዋውን የእንቅስቃሴወቭ ድርጅት አስተማራቢ ለእኛ ለዘመድና ለአንጋ፣ ልጅና በፓት፣ ለባለቤቱ፣ ለባለአባልና ለአሸነፋል ጉባኤ እና ለሌሎቹ ሰዎች የታሪኩ ስለተሰጡ እስከ ጦብያን በታሪክ አቅም ስማ።

ጦብያን በታሪክ

20 Feb, 12:57


በድጋሚ የቀረበ፡

የአደባባይ ችሎት እና የተጠየቅ ሙግት

የጥንቱ ችሎት በተነሳ ቁጥር . . . የሚነገርለት አንድ ነገር አለ። ይኸውም ተውኔታዊ ባህርይ የነበረው የከሳሽና የተከሳሽ አለባበስ፥ አቋቋም፥ ዘንግ አያያዝ፥ የሰውነት እንቅስቃሴ፥ የነገር አቀራረብና ባጠቃላይም ሞቅና ደመቅ ያለው ጥምር የአሞጋገቱ ስልት ነው። ተሟግቶ ለመርታት፥ ረትቶም እርካታ፥ ዝናና ክብርን ለመቀዳጀት በቅድሚያ የተሟጋቹን ንቃት፥ ብልህነትና ብርታት ይጠይቃል። ከዚህም የተነሳ ከሰውነት እንቅስቃሴው ሌላ፥ በተለይ የመሟገቻው ቋንቋ በተዋቡ ቃላት፥ በምሳሌያዊ አነጋገር፥ በተረት፥ በአፈታሪክ፥ በእንቆቅልሽና በመሳሰሉት ዘዴዎች የበለፀገና ለዛማ መሆን ይገባው ነበር። የነዚህ ሁሉ ውሁድ የችሎት ነፃ ትርኢት ነው እንግዲህ፥ ወጪ ወራጁን፥ አላፊ አግዳሚውን ሁሉ ይማርክና ያማልል የነበረው።

ሁሉንም ተሟጋቾች አይመለከት ይሆናል። ይህም ቢሆን የክት ልብስን ለብዞ፥ ድግድጋትን አሳምሮ (አደግድጎ)፥ ጎራዴም ሆነ ሽጉጥ በወገብ ላይ ገንደር አድርጎ፥ ረዢም ዘንግ ይዞ ግርማ ሞገስ በተቀላቀለበት ሁኔታ እችሎት ላይ መቅረቡ፥ ቀርቦም ወቅቱ ሲደርስ እየተንቆራጠጡና ነገርን እያራቀቁ መሟገቱ፥ ከአንድ ጥሩ ተሟጋች የሚጠበቅ ልማድ ወይም ወግ ነበር።

አንድ ተጓዥ እንዲህ ሲል የዛፍ ስር ሙግት ተሟጋቾችን ገልጿል «በተመልካቾች መካከል ተቀምጦ የነበረው ዳኛም የከሳሽን ጉዳይ በጥሞና አዳምጦ ካበቃ በኋላ፥ ተከሳሽ መልስ እንዲሰጥ ይጋብዘዋል። ተከሳሽም ተስፈንጥሮ ወደላይ በመዝለልና ሁለት እጆቹን ወደ ሰማይ በመዘርጋት፥ ክሱ የማይመለከተውና ንፁህ መሆኑን ለመግለፅ ይጥራል። ከዚያም በአንድ ጉልበቱ በርከክ ቀጥሎም ብድግ በማለትና በእግር ጣቶቹ ብቻ በመቆም ወደ ባላጋራው ሌባ ጣቱን ቀሰር ያደርጋል። ወዲያውም ሁለት እጆቹን በደረቱ ላይ ለጥፎ በአሳዛኝ መልክ ወደ ዳኛው ጠጋ ይላል። ይህ ሰው እነዚህን ሁሉ ድርጊቶች ሲፈፅም ከንፈሮቹ የማያቋርጡ ቃላትን እያነበነቡ ነበር።

ለነጋድራስ ገ/ሕይወት ባይከዳኝ ግን ይኽ ከንቱ ነበር፡ «አንዳንድ የውጭ ሀገር ስደተኞችም በልተን እንደር ሲሉ ያገራችን ሹማምንት ዛሬ የያዙትን የስህተት መንገድ እንዳይለቁ ያጠናክሩታል። አይዟችሁ እያሉም ከየመፃህፍቱ የለቀሙትን፥ —-አንዳንድ የተሰብሩ ቃላት ያስጠኗቸዋል። ያገራችንም ሹማምንት ሩቅ እንዳያዩ. . . አይናቸውን ሸፍነው ይከለክሏቸዋል። እውቀት አለንም ብለው ራሳቸው ይዞራል። ውሏቸውም ስራን ትተው በክርክርና በሙግት ብቻ ነው» ይላል።

«እመንደር ከዋለ ንብ አደባባይ የዋለ ዝንብ» እየተባለ ይተረታል - አደባባይ የፍርድ ችሎትን ይወክላል። ችሎት ለማየት በሚውል እና በማይውል ሰው ላይ ያለውን ማኅበራዊ ግምት ከተረዳን የገ/ሕይወት ባይከዳኝ ትችት የምር ሊያሳስበን ይችላል። ስራ ተፈቶ ክርክር ሲታይ ይዋል ነበር ማለት ነው? ፡)

ደግሞ ችሎት የአሞጋገትና የአነጋገር ስልትን የመቅሰሚያ፥ ህግና ዳኝነትን የመማሪያ፥ ከሹማምንትና ከመሳሰሉት ከፍተኛ ሰዎች ጋር የመተዋወቂያና ለዳኝነትም ሆነ ለሌላ ስልጣን የመመረጫ ቦታም ጭምር በመሆኑ አዳማቂዎቹ ወይም ደንበኞቹ ሙግት ያላቸውም፥ የሌላቸውም ነበሩ።

ባንድ ወቅት ከሳሽና ተከሳሽ እዳኛ ፊት ግራና ቀኝ ተቋቁመው ሲሟገቱ፤ አንደኛው የሌላውን ደካማ ጎን (እንከን) አውቆ ኖሯል። እንከኑም አደባባይን አላማዘውተሩና ከድህነቱም የተነሳ ሚስቱን ነጠላ እንጂ ኩታ አልብሷት እንደማያውቅ መሆኑ ነበር። ይህንን የተረዳው ጮሌ ተሟጋችም በዘመኑ የነበረውን የችሎት ላይ ያነጋግር ነፃነትና የአሞጋገት ስልትን በመጠቀም እንዲህ ብሎ ይሰድበዋል።

በላ ልበልሃ!
ያጤ ስርአቱን የመሰረቱ፡
አልናገርም ሀሰቱን፡
ሁሌ እውነት እውነቱን!
ላምህ ብትወልድ ዛጎላ፡
ሚስትህ ብትለብስ ነጠላ፡
አንተ ብትውል እጥላ!

ተሰዳቢው ተሟጋችም ምንም እንኳን አደባባይን የማያዘወትርና የኑሮ ደረጃውም ዝቅ ያለ ቢሆንም ቅሉ፥ ነገር አዋቂና አራቃቂ ነበርና፤ እሱም በበኩሉ በ’በላ ልበልሃ’ የአሞጋገት ስልት እንዲህ ብሎ መለሰለት ይባላል።

በላ ልበልሃ!
ያጤ ስርአቱን የመሰረቱን፡
አልናገርም ሀሰቱን፡
ሁሌ እውነት እውነቱን!
ላሜ ብትወልድ ዛጎላ
አውራውን አስመስል ብላ።
ሚስቴ ብትለብስ ነጠላ
ቀን እስቲያልፍ ብላ።
እኔ ብውል እጥላ፥
ያንተን ብጤ ነገረኛ ብጠላ!

😂 ዛሬ ይሄ ባህል ቢኖር እኔም ስራ ፈትቼ አደባባይ ፍርድ ሳይ ነበር የምውለው እምዬን።
***
‘የሞራል ውድቀት ዝንባሌ በትምህርት እድገት በኢትዮጵያ ላይ’ በሚለው መጽሐፋቸው ሀይሌ ወ/ሚካኤል እንዲህ ይላሉ፡ «በመካሰስና ነገር ካለበት ስፍራ በመዋል የኢትዮጵያ ህዝብ የታወቀ ሆኗል። ትልቅ ገበሬ ከመሆን አነስተኛ ጠበቃ መሆን ክብር ነው። ከአደባባይና ከትችት ቦታ መዋል የጨዋ ልጅ ምልክት ነው። የሰው ልጅነትህን በአንደበትህ ርቱዕነት ማረጋገጥ አለብህና»

ተሟጋችነት ከመከበሩ የተነሳ አንድ ተሟጋች ብቃት የሌለውን እንዲህ ብሎ ሰድቦታል፡ እዛው ችሎት አደባባይ

በላ ልበልሃ!
ያጤ ስርአቱን የመሰረቱ፡
አልናገርም ሀሰቱን፡
ሁሌ እውነት እውነቱን!
በሳማ ሲበላ ጣቱን የሚልሰው፥
አደባባይ ቆሞ አንድ እማይመልሰው፥
ሚስቱ ስትቆጣው እጓሮ እሚያለቅሰው፥
አንተም ከኔ ጋራ እኩል ሰው እኩል ሰው። 😄

ከሺበሺ ለማ ፡ ተጠየቅ
ገጽ 15 - 46

ጦብያን በታሪክ

20 Feb, 09:25


ነገ ጃንሜዳ በሚገኘው የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል ከቀኑ 9፡30 ላይ The Lost Wax: Light Up Lalibela's Church የተባለ ዶክዩመንተሪ ፊልም ይታያል ከዚያም ውይይት ይከተላል። እንደምታውቁት የፈረንሳይ መንግሥት የላሊበላን ውቅር አብያተ ክርስቲያን ለማሳደስ ብዙ ገንዘብ አውጥቷል። ብዙ ኢትዮጵያዊ እና የውጭ ምሁራንም ሲያግዙ ነበሩ/አሉ። ከሱ ጋር የተገናኘ ፊልም ነው።

ለበለጠ መረጃ እዚህ ተመልከቱ፡ https://cfee.hypotheses.org/11455

ጦብያን በታሪክ

19 Feb, 09:33


ክብር ለሰማዕታት። የካቲት 12

https://www.youtube.com/watch?v=RYGIZMJsuAo&t=2354s

ጦብያን በታሪክ

17 Feb, 18:14


For friends in Addis Abeba:

“In honor of Black History Month, we will be screening the groundbreaking romance/drama film Losing Ground (1982) directed by Kathleen Collins who is often cited as being the first African American woman to write and direct a feature length film, even preceding the likes of Julie Dash’s Daughters of the Dust.

Losing Ground revolves around a summer in the life of a married scholar and artist couple who are at a crossroads. It stars Seret Scott as the lead and her husband is played by the legendary cult filmmaker Bill Gunn (Ganja & Hess, Personal Problems).

Losing Ground never got distribution and was lost in obscurity for more than 30 years; it finally got a theatrical release in 2015 and is now considered one of the most important films of the 80s. Come join us on February 20, 2025 for a night of celebrating cinema!”

RSVP here: https://posh.vip/e/losing-ground-film-screening

Losing Ground film screening
Century Cinema
Thu, Feb 20 at 6:00 PM - 8:00 PM (EAT)
Organised by Video-Bet

ጦብያን በታሪክ

17 Feb, 16:43


ይሄን አዲስ መጽሐፍ ያላያችሁ፡ ኢትዮጵያ ብቻ ወደ ሦስት ምዕራፎች አሏት።

ጦብያን በታሪክ

15 Feb, 11:10


በጀርመንኛ ከተጻፈ “Das Licht seiner Geburt“ (የልደቱ ብርኃን) ከሚል መጽሐፍ ያገኘኋቸውን ሥእሎች እዩማ። ሥእላቱ ከተለያዩ አብያተ ክርስትያን እና የብራና ማስቀመጫዎች የተወጣጡ ናቸው (እነ ማኅደረ ማርያም — ደብረ ታቦር፣ ደብረ ብርኃን ሥላሴ — ጎንደር፣ የSTUB Frankfurt/Main ብራናዎች ወዘተ)።
እመብርኃን ጥጥ ስትፈትል ያለው ነው በጣም ያማረኝ። ዳዊት በበገናንም ሹፉ:

(እዚህ ላይ
ዕዝራ በመሰንቆ ዳዊት በበገና፣
እግዜርም እንደሰው ይወዳል ምስጋና። የሚለውን የቀኛ/ች ምስጋናው አዱኛ ግጥም ትዝ አለኝ)

ጦብያን በታሪክ

14 Feb, 18:52


Donald Davies Microfilm Collection የተባለ በ20ኛው ክ/ዘ ፎቶ ተነስተው በማይክሮፊልም የነበሩ የኢትዮጵያና ኤርትራ ብራናዎች ስብስብ በቅርብ ዲጂታይዝ ተደርጎ በHMML ድረገጽ መጠቀም ለሚፈልግ ተለቋል።

እዚህ ማየት ትችላላችሁ ያሉትን ነገሮች: https://www.vhmml.org/readingRoom/view/833050
አላሳይም ካላችሁ የስብስቡን ሊንክ ንኩት

ለዜናው: https://hmml.org/collections/repositories/united%20states/donald-davies-microfilm-collection/?emci=57cdb2ed-91e5-ef11-90cb-0022482a94f4&emdi=76a9baea-ffea-ef11-90cb-0022482a94f4&ceid=23998276

ጦብያን በታሪክ

13 Feb, 12:35


Ethiopian Academy of Sciences ይኼን የመጽሐፍ ምረቃ ዝግጅት መጥሪያ ልከዋል። ለሁሉም ክፍት የሚሆን መሰለኝ።

ራስ መኮንን አዳራሽ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
የካቲት 13፣ 2017 ዓ.ም. ከቀኑ 8 ሰዓት

ጦብያን በታሪክ

11 Feb, 16:36


ባልደረቦቻችን በቪኦኤ*: https://amharic.voanews.com/a/amharic-as-a-foreign-language/7966555.html

ጦብያን በታሪክ

10 Feb, 17:06


ቪዲዮቤቶች ሁለተኛ ኤፒሶዳቸውን ለቀዋል፡፡ አብረሃም ገዛኸኝ እንግዳቸው ነው — ከሱ በእድሜ የሚያንሱት አዘጋጆች ስለሚወራው ነገር ይበልጥ የሚያውቁ ይመስላሉ ግን ስሙት። ቀለል ያለ መዝናኛ ማግኘት እራሱ አንድ ነገር ነውና በርቱልን። https://www.youtube.com/watch?v=Jci0fu2VFto

ጦብያን በታሪክ

03 Feb, 16:11


ሰላም ጤና ይስጥልኝ፡

ሸዋ ሮቢት አካባቢ ያላችሁ ወዳጆች፡ ሸዋ ሮቢት ውስጥ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም የምትባል ቤተ ክርስቲያን አለች? የምታውቁ ብትጽፉልኝ ወሮታ እመልሳለሁ።

እግዚአብሔር ይስጥልኝ

------------------------
Update:

አመሰግናለሁ። ከንግዲህ አትጨነቁ -- የጻፉልኝ ሰዎች አግዘውኛል

ጦብያን በታሪክ

02 Feb, 15:04


ዮሐናን አመስግኑልኝማ https://youtu.be/L3I7G9CyJrs?si=I3TVACwdHKGdJqKM

ጦብያን በታሪክ

31 Jan, 16:16


ሸጋ ዐርብ፡

https://www.youtube.com/watch?v=Fbs1HeSx2ak

ጦብያን በታሪክ

31 Jan, 08:35


ይኸውላችሁ፡ ዛሬ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር 9 ሰዓት ላይ (CFEE) የፈረንሳይ ኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል (ጃንሜዳ ያለው) ይሄን ውይይት በZOOM ያካሂዳል።

ርዕሱ፡ The Stelae Culture Complex in the Horn of Africa
By Dr. Ayele Tarekegn
 
On presential at the CFEE Library (Jan Meda)
 
Topic: FMSEH - CFEE 2025 Seminar Series (1)
Time: Jan 31, 2025 03:00 PM Nairobi
Join Zoom Meeting
https://univ-grenoble-alpes-fr.zoom.us/j/93176792250?pwd=FKbwRHGsjPAodxfRT1VfVPNDKhBt5y.1

Meeting ID: 931 7679 2250
Passcode: 875984


ለተጨማሪ መረጃ፡ https://cfee.hypotheses.org/10997

ጦብያን በታሪክ

27 Jan, 10:34


ሰላም ብለናል፡

ፊልም ለምትወዱ ወዳጆቻችን እነ ባንዱ ይኼን 'ቪዲዮቤት ፊልም' የተባለ ፖድካስት ጀምረዋል። 🎉 You can check it out here:

https://www.youtube.com/watch?v=HuGynsdFTPs

ጦብያን በታሪክ

18 Jan, 09:43


ቆንጅዬ ጥምቀት የሀገር ሰው። ❤️

ትዝታችንን፣ ናፍቆታችንን፣ ሰላም እና ፍቅራችንን ይመልስልን።

ጦብያን በታሪክ

16 Jan, 15:25


አባዬ የግጥም መድብል አዘጋጅቶ ዛሬ ታትሞ ተለቋል። በቅርብ ለገበያ ይለቀቃል፡፡ ድንገት መንገድ ላይ ካያችሁት ከቻላችሁ ግዙለት፣ ካልሆነም ገለጥ ገለጥ አርጉለት።

በሰባ ዓመቱ ገጥሞ፣ ታይፕ አርጎ (በቤተሰብ ርብርብም) ያዘጋጀው ነው። (በቀን ቤት ውስጥ ስንት ግጥም እንደሚነበብልን አትገምቱም። አብሶ ያቺ ትርንጎ የምትለው ግጥሙን ሁሌ ሲያነብ የተወለደበት አርማንያ/ሰሜን ሸዋ/ ትዝ እያለው እንባ እንባ ስለሚለው የቤታችን ዓባይ ግጥም ናት።) ታድያ ስብስቡን እኔ ላርምልህ ስለው 'አይሆንም አንቺ ታሪኬን ታርሚያለሽ' ብሎ ኸገጣሚው ኤፍሬም ሥዩም ጋር ነው የከረሙበት። ይመቻቸው። ጨርሰዉት ታትሟል።

እዚህም ቻናል ላይ ስላለ በዛው በሰበቡ ስለሱ ትንሽ ስጎርር እንዲያይ ብዬ ነው 😍 በቅርብ ደግሞ የሕይወት ታሪኩ ይለቀቃል።

ፎቶዎች ይከተላሉ።

መጽሐፍ፡ ጥዱ የአያቴ እኩያ ዛፍ
ደራሲ፡ ስምዖን ማርዬ
ሽፋን ዲዛይን፡ ዮፍታሄ ኃይሉ
ጥር 8 2017 ዓ.ም.

ጦብያን በታሪክ

16 Jan, 15:00


የዛሬ ወር ገደማ ስለተአምረ ማርያም ከHMML አንድ ሌክቸር ይተላለፋል (ጋሽ ጌታቸው ኃይሌ ይሠሩበት የነበረው ተቋም ማለት ነው)። እዚህ ብትመዘገቡ መሳተፍ ትችላላችሁ፡

https://secure.hmml.org/a/winter-lecture-series

ጦብያን በታሪክ

16 Jan, 09:15


እቺን አዲስ የማስንቆ ክላሲካል ይኸው፡ መቆዘምያ https://www.youtube.com/live/DbITXs-TnLw

ጦብያን በታሪክ

16 Jan, 08:11


የመርስዔ ኀዘን ትዝታዬ መጽሐፍ ሲያልቅ ገና ጣልያን እራሱ አልገባም። እስካሁን ሳነባቸው የነበሩት ሰውዬ ድንገት እዛ ላይ ታሪካቸው ቆሞ ኤዲተሩ ልጃቸው ስለቀረው ሕይወታቸው እና ስለአሟሟታቸው የጻፈውን ሳነብ በቅርብ የማውቃቸው ሰው ድንገት የሞቱብኝ ያህል ነው ያስለቀሱኝ። ያረፉት ደርግ በገባ ባምስት ዓመቱ ነው። አስቡት ኢትዮጵያን በስንት ሞያቸው እና በየትልልቅ ድርጅቱ ሲያገለግሉ የነበሩ ሰዎች ሀገሪቷ እርስበርሷ ስትታመስ እያዩ ሲሞቱ። አሳዘኑኝ።

ሆነም ቀረም ልጃቸው የጻፈው ማሳረጊያ ምዕራፍ ዉስጥ ይሄን አይቼ ትንሽ አዝናንቶኝ ነው፡

በ1918 ዓ.ም. 14ቱ መጽሐፈ ቅዳሴ ታትሞ ኖሮ በ1942 የወጣውን ብላታ መርስዔ ኀዘን ናቸው አሻሽለው ያዘጋጁት (እነ ሊጦን፣ መስተብቍዕ እና ዘይነግሥ ተጨምረው) እና ከመጽሐፉ ሽያጭ የተገኘው ጥቅም ለማን ሄደ መሰላችሁ? «የኢጣልያ ጦር በ1929 ዓ.ም. ሕፅዋን (ጃንደረባ) ላደረጋቸው ድኾች ልጆች ለሚያድጉበት መንፈሳዊ ትምህርት ቤት እንዲሰጥ ተደርጎ ነበር» ይለናል መጽሐፉ። (ገጽ 225)

ጃንደረባ በግዕዙ ስልብ አገልጋይ ማለት ነው ፡) -- በየሚዲያው ለሚታየው አዲሱ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ ትውልድ ሲባል ምን እያልን እንደሆንን ለማሳየትም ነው። (ያው አሁን ትርጉሙን ለውጠን ይሆናል ግን አመጣጡን ማወቃችን አይከፋም)

--
መርስዔ ኀዘን ያገለገሉባቸውን፣ የሠሩዋቸውን ሁሉ የሚጠቅሰውን ምዕራፍ ፎቶ አንስቼ ከሥር ልኬያለሁ።

አሰላም-አሌይኩም

ጦብያን በታሪክ

10 Jan, 15:48


ሰላም ጤና አእላፋት ፡)

ዝክረ፡ ነገር በPDF ያለው አለ? እዚህ አንዴ የላኩት መስሎኝ ነበር የለም።

ከወዲሁ አመሰግናለሁ

*UPDATES: አግኝቼዋለሁ። እግዚአብሔር ይስጥልኝ። የምትፈልጉት እንደተለመደው ጻፉልኝ እልካለሁ ወይንም እዚህ ያግኙት፡ https://archive.org/details/zikre-neger/mode/1up?q=%E1%8B%9D%E1%8A%AD%E1%88%A8+%E1%8A%90%E1%8C%88%E1%88%AD

ጦብያን በታሪክ

08 Jan, 10:49


ሰላም ጤና፡

እነዚህን ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያዎች ተመልከቱማ፡

two openings in the ERC project "REDMIX - Unpacking Mixedness for an Inclusive History of the Red Sea, 1800s-2000s" (deadline 27/1/25):
-- "People and communities of mixed-ancestry in the Red Sea: historical and social dynamics (1800-2000)" https://bandi.mur.gov.it/bandi.php/public/fellowship/id_fellow/289968 (Bologna) and
--"Building a database and a digital archive on the mixedness in the Red Sea" https://bandi.mur.gov.it/bandi.php/public/fellowship/id_fellow/289967 (Turin)

ጦብያን በታሪክ

07 Jan, 10:58


ዐርብ የፆም ቀን ስለሆነ ገና ሲያርፍበት ስጋ ይበላል አይበላም የሚለው በአጤ ምኒልክ ዘመን ጭቅጨቅ አስነሳ አሉ። ንጉሠነገሥቱ አሰቡና ስጋ ጭራሽ ወደማይበሉ ዝነኛ አባት መልእክተኛ ሰደዱ።

መልእክቱም “እንዴት እናድርግ? ይጦማል ወይንስ አይጦምም?” የሚል ነበር።

እኚህ አባት መልሱ ግልጽ እንዲሆን ብለው በበዐሉ ዕለት ትንሽዬ የተቀቀለ ስጋ ወደ አፋቸው ወስደው አኘኩ። መልእክተኛውንም መልሰው ላኩት — እንዲህ ብለው: “ጌታየ ተወልዶ የምን ጦም ነው? ፍስሓ ነውንጅ!”

(ከግእዝ መምሕሬ አባ ኅሩይ የሰማሁት ጨዋታ ነው።)

— በድጋሚ የቀረበ። መልካም ገና!

ፎቶዋ: AI ነገር ናት አ? A bit strange

ጦብያን በታሪክ

03 Jan, 13:23


እቺ ደብዳቤ የተጻፈችው ከሐኪም ወርቅነህ ለመርስዔ ኀዘን ወልደ ቂሮቆስ ነው። በ1919 ዓ.ም. ሐኪም ወ. ያዘጋጁትን የዓለም ጂዖግራፊ መጽሐፍ (እነብላቴን ጌታ ኅሩይ እና ሌሎች ቀድመው ከሌላ ቋንቋ ተርጉመው የጻፉት ነው) መ.ኀ ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ጋር በመሆን ለማሳተም በእርማት እየሠሩ ነበረ። ሥራው በ1920 ዓ.ም. ታትሞ ለሕዝብ ቀርቧል። ታዲያ ደብዳቤዋ በ1935 ዓ.ም. ስለተጻፈች ወይ ፈቃድ መኖሩን ቆይቶም ቢሆን ማሳየታቸው ነው፤ ካልሆነም perhaps መ.ኀ በራሳቸው ሌላ የጂኦግራፊ ሥራ ለማሳተም ፈልገው ሥራውን ለመጠቀም ጠይቀው ይሆናል።

እንድታዩ የፈለግኩት ግን የሐኪም ወርቅነህን ፊርማ ነው። የላቲን ፊደል በ(ከርሲቭ) ቅጥልጥል ሲጻፍ እንደሚጻፈው ነው ያደረጉት ፡)

+ አዲስ አበባም አጻጻፏ ለየት ይላል አ?

ከ፡ ትዝታዬ፡ ስለራሴ የማስታውሰው
በ፡ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ
ገጽ 185

ጦብያን በታሪክ

29 Dec, 09:33


ትዝታ ዘ አራዳ 50 ዐመት ሰለሞላው የእድገት በኅብረት ዘመቻ ይሄን ፕሮግራም አዘጋጅቷል :

መልካም ሰንበት

https://youtube.com/playlist?list=PLep9COCl9DsYnpzs7HOazxizAYgQ-MsuO&si=vL-OnrOZh0KfIoYB

ጦብያን በታሪክ

21 Dec, 09:08


የታሪክ ትምህርት ያለፈውን ስለማጥናት ብቻ ሳይሆን የታሪክ ጸሐፍያንንም ማጥናት እና መመርመር እንደሆነ የሚያሳይ ቆንጅዬ ሪቪው ይኸውላችሁ:

https://www.lrb.co.uk/the-paper/v46/n23/christopher-clark/the-murmur-of-engines

ጦብያን በታሪክ

19 Dec, 15:48


ስለ ቴዲ አፍሮ የተጻፊ አንድ ጽሑፍ አርሚ ተብዬ ያስተሰርያል አልበምን በስንት ጊዜ ድጋሚ ሰማሁት። ያ ነበር አይደል የቴዲ ከፍታ?

ለማንኛውም አልበሙ ይኸው፡ https://www.youtube.com/watch?v=Kg0IKw5TtIQ&list=PLvk301IOwigv5KzvGQiCo5TLsSciq-BBf

ጦብያን በታሪክ

17 Dec, 12:32


https://ices22.hu.edu.et/


22ኛው ዓለማቀፍ የኢትዮጵያ ጥናት ጉባኤ ሃዋሳ ይካሄዳል። ጽሑፍ ማቅረብ ለምትፈልጉ ማስታወቂያው ይኸው ተለቋል።

ጦብያን በታሪክ

13 Dec, 13:04


ለታሪክ ተመራማሪዎቻችን ደግሞ በቅርብ የወጣ ሥራ ይኸውላችሁ፡ በመካከለኛው ዘመን ሮም ስለነበሩት ስለ ተስፋ ጽዮን

ጦብያን በታሪክ

13 Dec, 06:51


እንዴት አደራችሁ?

ዛሬ እና ነገ እኛ ተቋም የሚካሄድ ጉባኤ አለ ስለ አማርኛ ቋንቋ። መሳተፍ የምትፈልጉ በዙም መግባት ትችላላችሁ።

ፕሮግራሙም ይኸው:

ZOOM: https://uni-hamburg.zoom.us/j/61830559382?pwd=8FFRB9TG08nJrEMGTPfuWEJ9kyAFO1.1

ጦብያን በታሪክ

10 Dec, 08:27


ሰላም ጤና፣

የደምሴ ዳምጤ፣ ይምበርበሩ ምትኬ እና ግርማ ነጋሽ የሚያዘጋጁት የስፖርት ፕሮግራም መክፈቻ ዘፈን ድንገት አግኝቼው ለትዝታው ያህል:

ተስፋዬ ገብሬ: ስፖርት

https://www.youtube.com/watch?v=x1CQCC993xE

ጦብያን በታሪክ

07 Dec, 09:12


ስለ ዳኛቸው ወርቁ ከትዝታ ዘአራዳ።

መልካም ቅዳሜ!

https://youtu.be/g5j2lWasAPc?si=qARAb7jujM-dHJw9

ጦብያን በታሪክ

06 Dec, 09:35


https://univ-grenoble-alpes-fr.zoom.us/j/94787677605?pwd=5YOcQ4el8fCCbCycd0alIsHJfOnvIu.1

ጦብያን በታሪክ

04 Dec, 16:18


Via here’s the zoom link for this: https://www.eventbrite.com/e/forum-for-medieval-studies-in-ethiopia-and-the-horn-conference-tickets-1083342238799?aff=oddtdtcreator

ጦብያን በታሪክ

03 Dec, 09:29


የፊታችን አርብ ይሄ ኮንፍረንስ ይካሄዳል። በአካል ጃንሜዳ ያለው የፈረንሳይ ኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል መሳተፍ ትችላላችሁ። መሳተፍ ለማትችሉ የZOOM አድራሻ እንደደረሰኝ እልክላችኋለሁ።

Conference: Advances in Medieval Studies in the Horn of Africa
2nd Anniversary of the Forum for Medieval Studies in the Horn of Africa (FMSEH)
3rd International Hybrid Conference
Friday 6th December 2024
From 11am to 6pm (ከጠዋት 3 ሰዓት እስከ 10 ሰዓት ከሰዓት*), at CFEE Library (Jan Meda)

ፕሮግራሙ ይኸው፡

ጦብያን በታሪክ

26 Nov, 15:11


አቤ ጉበኛ አንድ ለናቱ መግቢያ ላይ የጻፈውን አይታችኋል? እዩትማ:

ጳውሎስ ኞኞ “ይህን ሥራ ስሠራ ከሚስቴ ውጪ ያገዘኝ ማንም የለም። ደኅና እንሁን ብቻ” ካለው ጋር ተመሳሰለብኝ 😄

ሁለቱም የቴዎድሮስ ታሪክ መጽሐፎቻቸው ላይ ነው ደግሞ እንዲህ ያሉት። የካሳ ወኔ ነሸጥ እያረጋቸው ነው?

ጦብያን በታሪክ

23 Nov, 07:09


መልካም ቅዳሜ።

https://youtu.be/ZkYy1aROoQk?si=eUlVXCMnhi1HteoS

ጦብያን በታሪክ

20 Nov, 19:14


የሚመጣው ሳምንት ረቡዕ ኅዳር 18 ቀን፣ በኢትዮጵያ ሰዐት አቆጣጠር 8 ሰዐት ላይ “Rethinking Political Legitimacy: Tewodros II and the Fekkare Iyesus” በሚል ርዕስ ፐሬዘንቴሽን/ሌክቸር አቀርባለሁ። መሳተፍ የምትፈልጉ በዚህ ዙም አድራሻ መቀላቀል ትችላላችሁ።

https://uni-hamburg.zoom.us/j/92260268033?pwd=YkpBUXNlV3kzdEZhT3p4TUJONlpFQT09

ጦብያን በታሪክ

19 Nov, 12:08


Prague የሚዘጋጀው የአፍሪካ ጥናት ኮንፍረንስ call for papers/abstracts ከተለቀቀ ሰንብቷል፡

https://www.ecasconference.org/2025/call-for-papers/

ጦብያን በታሪክ

19 Nov, 07:21


ዘንድሮ ቀኃሥ ሃምቡርግ /ጀርመን ሀገር/ የመጡበትን 70ኛ ዐመት በማስመልከት ነፍ ፕሮገራሞች ተዘጋጅተዋል። አንዱ ትናንት የተለቀቀው የNDR ዝግጅት ነው። የኛ ተቋም ሰዎችም አሉበት ማየት ለምትፈልጉ :-)

https://www.ndr.de/fernsehen/sendungen/hamburg_journal/Hamburg-damals-Kaiser-von-Aethiopien-kommt-1954-nach-Hamburg,hamj153340.html

ጦብያን በታሪክ

12 Nov, 08:00


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል የአሁኑ ሐሙስ እና አርብ አንድ ጉባኤ እና ዐውደረ‍እዕይ ያካሂዳል። ስለባርያ ንግድ ነው። ማስታወቂያው ይኼው:

ጦብያን በታሪክ

11 Nov, 11:52


ሰላም ጤና

ኢቲቪ/አሁን EBC/ የሚሠራ ሰው አለ እዚህ? ወይ እዛ የሚሠራ ሰው የሚያውቅ? ከarchives ክፍል መረጃ ፈልጌ ነው። አመሰግናለሁ

ጦብያን በታሪክ

07 Nov, 08:19


በጎንደር ዘመነመንግሥት ከሮ ስለነበረው የተዋሕዶዎች እና የቅባቶች የሃይማኖት ክርክር

የቅብዓቶች ባህል «የእግዚአብሔር ቃል በድንግል ማርያም ማኅፀን ሲፀነስ ከእርስዋ የተነሣው ሥጋ በመንፈስ ቅዱስ ቅብዓት የአብ የባሕርይ ልጅ ሆነ» ሲል
የተዋሕዶዎች ደግሞ «የእግዚአብሔር ቃል በድንግል ማርያም ማኅፀን ሲፀነስ ከእርስዋ የተነሣው ሥጋ በተዋሕዶ የአብ የባሕርይ ልጅ ሆነ» የሚል ነው።

ታድያ በጎንደር ዘመነ መንግሥት የነዚህ ሁለት ዕይታዎች ክርክር በየዘመኑ እየተነሣ እርስበርስ ሲሸናነፉና በአዋጅ ሲያስነግሩ ኖረዋል።

ለምሳሌ፡

«በአእላፍ ሰገድ ዮሐንስ ዘመን፣ 1672 ዓ.ም. ጥቅምት 10 ቀን የሃይማኖት ጉባኤ ቆሞ ነበርና የቅብዓቶች አፈ ጉባኤ አባ አካለክርስቶስና የተዋሕዶዎች አፈ ጉባኤ አባ ኒቆላዎስ በየበኩላቸው ከመጻሕፍት እየጠቀሱ በንጉሡ ፊት በብዙ ተከራከሩ። በክርክሩም ላይ አባ አካለክርስቶስ ተረትቶ ጳጳሱና እጨጌው አወገዙት። ንጉሡ አእላፍ ሰገድ ዮሐንስም የተዋሕዶዎችን መርታት የቅብዓቶችን መረታት አይተው «ከበረ ሥጋ በተዋሕዶ» ተብሎ አዋጅ እንዲነገር አደረጉ። እርሳቸው ራሳቸው ግን የግል እምነታቸውን ሲገልጡ «እኔ ራሴ በተረቺዎቹ በኩል ነኝ» ብለው ተናገሩ ይባላል።»

እንዲሁም፡ «ቅብዓቶች በአድራር ሰገድ ቴዎፍሎስና በአድባር ሰገድ ዳዊት ዘመን አሸናፊዎች ሆነው ነበርና «በቅብዓት የባሕርይ ልጅ» እንዲባል ዓዋጅ እየተነገረላቸው ደስ የተሰኙበት ጊዜም ነበር።»


ምንጭ፡ ትዝታዬ - ስለራሴ የማስታውሰው (1891–1923)
በመርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፣ ገጽ 112–113

ጦብያን በታሪክ

06 Nov, 10:30


የአዲስ መጽሐፍ ማስታወቂያ፡ Pierre Guidi's Educating the Nation in Ethiopia: State, Society and Identity in Wolaita (1941-1991)

ጦብያን በታሪክ

01 Nov, 12:30


1907 ዓ.ም. እና ቡና
~ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ከዘገቡልን ~

«እንዲሁ ደግሞ ዕጣን እየተጨሰ ቡና የመጠጣት ልማድ በባላገር የተጀመረው በዚያው ጊዜ ነው። ከዚያ በፊት ግን ይህ ዓይነት ልማድ የሚታየው በነጋዴዎችና በእስላሞች በተለይም በቃልቾች ዘንድ ነበር። በበረሃ ስፍራ የሚኖሩ ነፍጠኞችም የዚሁ የቡና ልማድ ነበረባቸው።

ስለዚህም እነዚያ ነፍጠኞች ወይም ነጋዴዎች ወደ አገር ቤት በተመለሱ ጊዜ ዕጣን እያጨሱ ቡና ይጠጡ ነበርና ሌላውም እነሱን አይቶ ተከተለ። ይልቁንም የየመንደሩ ሴቶች የቡና ማኅበር እያበጁና ተራ በተራ እየተጠራሩ ቡና ሲያፈሉና ሲጠጡ መዋል ጀመሩ። ይኸውም ልማድ በባላገርም ሆነ በከተማ እየተስፋፋ ስለሄደ ብዙ ሰው የቡና ሱሰኛ ሆነ።

በዚያ ጊዜው ጨዋው ህዝብና የቤተ ክህነት ሰዎች ዕጣን አጭሶ ቡና መጠጣትን እንደ ነውር ወይም እንደ አምልኮ ባዕድ አድርገው ይመነለከቱት ነበር። ስለዚህም እነዚያን የቡና ማኅበርተኞች በመንቀፍ

ነይ ቡና ጠጪ
መቼም አታዳምጪ
ነጭ ቡና* እንጠጣ
ድሩም ማጉም መጣ

እየተባለ በየሠርግ ቤቱ ይዘፈን ጀመር። ሆኖም ውሎ አድሮ ነቀፌታውና ነውርነቱ እየቀረ ሄዷል።»

-------
*ነጭ ቡና፡ «በዚያን ጊዜ ድርና ማግ ሲዘጋጅ ደቦ ጠርቶ፣ ቡና እየጠጡ የማስፈተል ባህል ተለምዶ ስለነበር «ነጭ ቡና» ማለታቸው ከድርና ከማጉ ጋር በማያያዝ ዘፋኞች ለፌዝና ለነቀፋ ይዘፍኑት የነበረ ነው። ምንጭ - አቶ ሥዩም ዘነበ (አቶ ሥዩም የታሪክ ጸሐፊው ዘመድ፣ በ90 ዓመት ዕድሜው አሁንም በሕይወት ያለ ነው።)»
----

ምንጭ፡ ትዝታዬ፣ ስለራሴ የማስታውሰው፣ ገጽ 102

መልካም ዐርብ ☕️ ለቡና ወዳጆች በሙሉ ፡)

ጦብያን በታሪክ

30 Oct, 08:31


አመሰግናለሁ። ደርሶኛል። የምትፈልጉት ጻፉልኝ እና እልክላችኋለሁ

ጦብያን በታሪክ

30 Oct, 08:24


ሰላም ኤቭሪባዲ፡

ከግዕዝ ሥነ ጽሑፍ ጋር ብዙ አፍታ ቆይታ በPDF ያለው አለ?

ከብዙ ምስጋና ጋር።

ጦብያን በታሪክ

17 Oct, 10:39


አጼ ምኒልክ እንደታመሙ ስለሕመማቸው ብዙ አይነት ወሬ ይነገር ነበረ። መርስዔ ኀዘን ግን ለራሳቸው የመሰላቸውን እንዲህ ሲሉ ይተርካሉ፡

« «በነሐሴ ወር በጾመ ፍልሰታ ውስጥ አንድ ቀን ጧት ጃንሆይ ለጸሎት ወደ ሥዕል ቤት ኪዳነ ምሕረት ሄደው ጸሎት ከአደረሱ በኋላ ወደ ቤተ መንግሥታቸው ተመለሱ። እንቍላል ግንብ አጠገብ ያለው የወለሉ ሜዳ የድንጋይ ደረጃ ተነጥፎበታል። ጃንሆይ መንገድ ሲሄዱ ፈጠን ፈጠን እያሉ ነውና ከእልፍኛቸው አጠገብ ለመድረስ ጥቂት ሲቀራቸው የዝናም ውሐ የሸፈነው የድንጋይ ደረጃ አዳለጣቸውና በድንገት ሸብረክ አሉ። የተከተሏቸውም ሰዎች በቶሎ አንሥተው ከእልፍኝ አስገቧቸው። ከዚህ ቀን ጀምሮ ታመው እልፍኝ ዋሉ» ሲባል ሰምቻለሁ። ስለ ሕመማቸው ለመጀመሪያ ጊዘ ለሕዝብ የተነገረው ግን እግራቸውን ታመዋል እየተባለ ነበር።»


ይህ የሆነው በ1900 ዓ.ም. መሆኑ ነወ።
ከዚሁ ገጽ በላይ ደግሞ የፈንጣጣ ክትባት እንዴት ይሰጥ እንደነበረም ይገልጻሉ። እሱን ፎቶ ላይ ታገኙታላችሁ።

ምንጭ፡ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፣ ትዝታዬ - ስለራሴ የማስታውሰው 1891-1923
ገጽ፡ 66

ጦብያን በታሪክ

17 Oct, 08:58


ሰላም ጤና ወዳጆች፡ በሃምበርግ ዩኒ በየሳምንቱ ረቡዕ ምሽት Music in Africa የተባለ ለሁሉም ክፍት የሆነ የምርምር ማቅረቢያ ፕሮግራም ጀምረናል። ለ14 ሳምንታት ይቆያል። በZOOM መሳተፍ ለምትፈልጉ ፕሮግራሙ ይኸው።

ረቡዕ ከምሽቱ 1 ሰዓት በኢትዮጵያ አቆጣጠር ጀምሮ ማለት ነው።
እዛ እንገናኝ።

ጦብያን በታሪክ

16 Oct, 15:16


አራዳ ጊዮርጊስ፡ ከዓድዋ በፊት እና ከዓድዋ ጦርነት በኋላ የተሠራው ሕንጻ ቤተክርስቲያን

ምንጭ፡ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፣ ትዝታዬ - ስለራሴ የማስታውሰው 1891-1923
ገጽ፡ 62

ጦብያን በታሪክ

14 Oct, 07:25


ይኼ መጽሐፍ ያለው አለ?

ሐተታ መናፍስት ዘፊሎሶፊ ወቴዎሎጊ ባሕረ ሐሳብ ፍካሬ ከዋክብት ከእነትርጓ[ሜው]። ወዐውደ ነገሥት ከእነጠልሰሙ። አሁንም ፍካሬ ኢየሱስ ተጨምሮበት

በ፡ ዘመንፈስ፡ ቅዱስ፡ አብርሃ፡ ዘብሔረ፡ ዓድዋ

ጦብያን በታሪክ

14 Oct, 06:33


Silk-Road ተብሎ የሚጠራው ቻይናን ከሮም/አውሮፓ/ በጥንት ዘመን ያገናኝ ነበር ተብሎ የሚታሰበው መንገድ በብዛት ፈጠራ እንደነበረ እና ከቻይና በላይ ሕንድ ለዓለም ያበረከተችው ጎላ እንደሚል የሚያስረዳ The Golden Road: How Ancient India Transformed the World የሚል መጽሐፍ ታትሟል። ስለሱ ይሄን አሪፍ ዳሰሳ ተመልከቱማ፡

https://www.lrb.co.uk/the-paper/v46/n17/ferdinand-mount/one-way-traffic

ጦብያን በታሪክ

05 Oct, 14:39


ስለ አለቃ ገብረ ክርስቶስ፡ የብሉይና የሐዲስ ሊቅ እንዲሁም የቅኔ መምህር በአጼ ዮሐንስ፣ በንጉሥ ኃይለመለኮት እና በአጼ ምኒልክ ዘመን

አለቃ ገብረ ክርስቶስ በአንኮበር የተከበሩ ሊቅ ነበሩ። አጼ ዮሐንስ በ1873 ዓ.ም. አራት ጳጳሳትን ለማስመጣት ወደ ግብጽ አራት መልእክተኞችን ሲልኩ ከሸዋ በኩል የተላኩት ናቸው። ሹመት ቦታቸው አፈርባይኔ ተክለሃይማኖትና አንኮበር ሚካኤል ነው።

አለቃ ለማ ኃይሉ ስለሳቸው ሙያ ብዙ መስክረዋል። መጽሐፈ ትዝታ ላይ ከገጽ 114--116 ላይ ታገኙታላችሁ። ከሥርም አለ።

ላሁን ልጽፍ የፈለግኩት ግን አለቃ ገብረክርስቶስ የቅድሥት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያው አለቃ እንዲሆኑ ከሸዋ በአጼ ምኒልክ ተጠርተው ቤተክርስቲያኑ በመቃኞ እንዳለ እና ሥራው ገና ሳይጀመር አዲስ አበባ በገቡ በ14ኛው ቀን ድንገት ሞተው የሥላሴ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያ ተቀባሪ መሆናቸው ገርሞኝ ነው። «ለሹመት የተዘጋጁት ሊቅ ለመቃብር ማሟሻ በመሆናቸው በዚያ ሰዓት ዕፁብ ድንቅ ተብሎ ነበር»ይላሉ መርስዔ ኀዘን (ገጽ 40)።

ምንጮች፡ 1/ ትዝታዬ - ስለራሴ የማስታውሰው 1891-1923 በመርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ
ገጽ 39-40፤ 2/ መጽሐፈ ትዝታ ዘአለቃ ለማ በመንግሥቱ ለማ፤ እና 3/ የመካነ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አጭር ታሪክ በመርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ።

ጦብያን በታሪክ

04 Oct, 09:17


አንዳንድ ፎቶዎች ከ1896 ዓ.ም.፡

1/ አጼ ምኒልክ ሰርኪስ ባቡርን ሲመለከቱ። በእሳት እና በውሃ እንፋሎት የሚሠራ ነበር።
2/ በኖራ ግንብ የተሠራው እና ወደ አራዳ ጊዮርጊስ የሚወስደው መንገድ በሚያልፍበት ወንዝ ላይ የተሠራው የራስ መኮንን ድልድይ (በ1896 ዓ.ም. እየተሠራ ነበር)

ምንጭ፡ ትዝታዬ -- ስለራሴ የማስታውሰው 1891-1923፣ በመርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ
ገጽ 34 እና 35

ጦብያን በታሪክ

30 Sep, 15:38


ሰላም ጤና: ይኼን መጥሪያ ተመልከቱማ

“Dear colleagues, dear students,
 
On Tuesday 1st October, at Ethio-french Alliance (Piassa) is organized a closing event of the exhibition Ethiopia Land of Champions :
 
5pm – Documentary screening Town of runners
6.45pm – Conference “Altitude between Beliefs and Physiological Realities”
 
Four researchers, Benoit Gaudin (Versailles Saint Quentin University/CFEE), Zeru Bekele (AAU), Vincent O. Onywera (KCA University), and Elias Abichakra, will explore the controversial role of altitude in the exceptional long distance running skills of East Africans athletes.”

ጦብያን በታሪክ

26 Sep, 17:25


ቆንጅዬ የደመራ/መስቀል በዓል ለምታከብሩ ሁሉ።

ከ22 ማዞሪያ፤ ገብርኤል፡ ወአርሴማ።

ጦብያን በታሪክ

23 Sep, 11:29


ወዳጃችን በረከት እቺን መጽሐፍ አሳትሟል። የት እንደምትገኝ ማወቅ ለምትፈልጉ ብትጽፉልኝ ከደራሲው ጋር አስተዋውቃችኋለሁ።