Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ @ethionegarii Channel on Telegram

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

@ethionegarii


#NewsaboutEthiopia & the #Horn
ይህ የቴሌግራም ቻናል ትኩስ ዜናዎች፣ አዝናኝ መረጃዎች፣ ትንታኔዎች እና የስራ ቅጥር ማስታወቂያ የሚቀርብበት ነው።

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ አድርገው ቤተሰብ ይሁኑ።

http://youtube.com/@ethionegari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ (Amharic)

ኢትዮ ነጋሪ ማንኛውም ትኩስዎ የዩቲዩብ ቻናል ነው። እናንተ እንዴት ነው፡፡ በሚባለው የቴሌግራም ቻናል ላይ ይህች ዜናዎች፣ አዝናኝ መረጃዎች፣ ትንታኔዎች እና የስራ ቅጥር መረጃዎች እንዴት ተማሪውበት ነው፡፡ በየቀኑም በዩቲዩብ ቻናላችን ከተስበከው ቤተሰብን ወደ እኛ ሰብስክራይብ ያስቀምጡ፡፡ እባኮትዎን መዝገብ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ የልብ ትኩስዎችን ከአንድ ላይ በማናቸውም እርስዎ ይበልጥ ፡፡

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

11 Feb, 16:45


የዕለቱ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም

1. በትግራይ ክልል ሽረ እንዳስላሴ ከተማ በደረሰ የቦንብ ጥቃት 16 ሰዎች ጉዳት ደረሰባቸው። በትግራይ ክልል ሽረ እንዳስላሴ ከተማ በደረሰ የቦንብ ጥቃት 16 ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው ጊዜያዊ አስተዳደሩ ተናግረዋል። ጥቃቱ የደረሰው ትላንት ምሽት 3፡00 አከባቢ በከተማዋ በሚገኝ አንድ የመዝናኛ ክበብ ውስጥ እንደሆነ የተነገረ ሲሆን፤ 16 የሚገመቱ ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሶባቸው በከተማው በሚገኝ ሆስፒታል በህክምና ላይ ይገኛሉ፡፡ በአደጋው ህይወቱ ያለፈ ሠው የለም። ጥቃቱን አድርሰዋል ተብለው ከተጠረጠሩት መካከል አንድ ግለሰበብ መያዙን እና ሌሎችንም ለመያዝ ፖሊስ ጥረት እያደረገ መሆኑ ተነግሯል፡፡

2. በጉዳያ ቢላ ወረዳ ውስጥ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሟቾች ቁጥር 43 ደርሷል። ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ሻምቡ ከተማ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ መኪና በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉደያ ቢላ ወረዳ ውስጥ ጫሊ ጂማ በሚባል ቀበሌ ሲደርስ በመገልበጡ ነው አደጋው የደረሰው። መኪናው ወደ 87 የሚደርሱ ሰዎች ጭኖ ነበር፡፡ ተሸከርካሪው ከፍጥነት በላይም ሲያሽከርክር እንደነበር የተነገረ ሲሆን ከጠዋቱ 2 ሰዓት ገደማ በዚሁ አደጋ ከሞቱት በተጨማሪም በ42 ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን እና በ3 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት ደርሷል።

3. ኢትዮጵያ እርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ፖሊሲ በቀየሩ ቁጥር ችግር ውስጥ እንዳትገባ የራሷን ፖሊሲ ልታሻሽል ይገባል ሲል የኢትዮጵያ የሲቪል እና የሞያ ማህበራት ኮንግረስ መከረ፡፡ ሀገሪቱ ብዙ ሀብት እያላት በምግብ ዋስትና የምትቸገረውና የውጭ እርዳታ ጠባቂ የሆነችውም በፖሊሲ ችግር እንደሆነም ማህበሩ ይናገራል፡፡ በኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች፣ በድርቅና ስር በሰደደ ድህነት እርዳታ የሚጠብቁ ሰዎች እያሉ ከሰሞኑ የአሜሪካ እርዳታ መቆም ችግሩን ሊያወሳስበው ይችል የሚል ስጋት እንዳላቸው የሚናገሩም ብዙዎች ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ይህንን የምግብ ዋስትና ችግሯን ለመፍታት በሁሉም ዘርፍ ያሉ ምሁራንን ያሳተፈ ፖሊሲ አውጥታ ተገግባራዊ ማድረግ እንዳለባትም ማህበሩ ያስረዳል፡፡ በተለይ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ልትበረታ ይገባልም ብሏል፡፡

4. የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በአንድ ሰከንድ አንድ ኪሎሜትር መጓዝ የሚያስችላቸው ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ ተመረቀ። ኢትዮቴሌኮም ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር ያዘጋጀው ከመገናኛ ቦሌ መንገድ የሚገኝ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያን ክፍት አድርጓል። ተጠቃሚዎች 24/7 አገልግሎቱን ማግኘት የሚችሉ ሲሆን አገልግሎቱን ካገኙ በኋላ ክፍያውን በቴሌ ብር አማካኝነት የሚከፍሉ ይሆናል፣ የአንድ ኪሎ ዋት ክፍያ አስር ብር ነው ተብሏል። ሌሎች ተጨማሪ ሁለት ጣቢያዎች በግንባታ ላይ ሲሆኑ በቅርቡ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑ ተነግሯል።

5. የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፍልስጤማውያኑ የጦር እና የፖለቲካ ድርጅት /ሐማስ/ የያዛቸውን የእስራኤል ታጋቾች በሙሉ እንዲለቅ አስጠነቀቁ፡፡ እስከ ቅዳሜ እኩለ ቀን የጊዜ ገደብ እንደሰጡት ቢቢሲ ፅፏል፡፡ ትራምፕ ሐማስ ታጋቾቹን በሙሉ በተባለው ጊዜ ካልለቀቀ ጋዛን ገሐነብ አደርጋታለሁ ሲሉ መዛታቸው ተሰምቷል፡፡ ቀደም ሲል በእስራኤል እና በሐማስ መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም የታጋቾች እና የእስረኞች ልውውጡ ደረጃ በደረጃ በየምዕራፉ እንዲከናወን ይጠይቃል፡፡ ሐማስ ለመጨው ቅዳሜ ታቅዶ የነበረውን የታጋቾች መለቀቂያ በደፈናው ላልተወሰነ ጊዜ አራዝሜዋለሁ ብሏል፡፡ አዝማሚያው የጋዛውን የተኩስ አቁም ፉርሽ ሊያደርገው ይችላል ተብሎ ተሰግቷል፡፡


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

11 Feb, 13:38


በአዲስ አበባ ከተማ የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ ተከለከለ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄደውን የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ተከትሎ የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ መከልከሉን አስታውቋል።

ክልከላውም ጉባዔው እስኪጠናቀቅ ማለትም ከዛሬ ጀምሮ እስከ የካቲት 9 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ተነግሯል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

11 Feb, 11:49


በትራፊክ አደጋ የ26 ሰዎች ሕይወት አለፈ።

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ጉዳያ ቢላ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ26 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።

አደጋው ከሻምቡ ከተማ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው።

በደረሰው አደጋም የ26 ሰዎች ሕይወት ወዲያው ሲያልፍ 42 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን የዞኑ የትራፊክ ደህንነት ሃላፊ ኢንስፔክተር አስናቀ መስፍን ተናግረዋል፡፡

በአደጋው ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችልም ሃላፊው ገልጸዋል፡፡


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

11 Feb, 09:07


አሜሪካ እና እንግሊዝ ህወሀትን ለማሸማገል መቀሌ ገቡ።

በሕወሃት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በንግግር ለመፍታት የአሜሪካና የእንግሊዝ ባለስልጣናትን ጨምሮ የተለያዩ ዲፕሎማቶች መቀሌ መግባታቸው ተሰማ፡፡

በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ባወጣው መረጃ አምባሳደሮች፣ የአሜሪካ ኤምባሲ ከፍተኛ ዲፕሎማት ተወካዮች፣ ከአውሮፓ ህብረት፣ ከፈረንሳይ፣ ከጣሊያን እና ከእንግሊዝም የተውጣጡ ዲፕሎማቶች መቀሌ ገብተዋል፡፡

ዲፕሎማቶቹ ከጌታቸው ረዳ እና ከሕወሃት ሊቀመንበር ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል ጋር እንደሚነጋገሩ ተሰምቷል፡፡

ዲፕሎማቶቹ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ከተፈናቃዮች ተወካዮች ጋርም ተገናኝተው እንደሚወያዩ ከኤምባሲው ያገኘነው መረጃ ያሳያ፡፡

በህወሃት ባለስልጣናት መካከል የተፈጠረው መከፋፈልና አለመግባባት ለአንድ ከተማ ሁለት ከንቲባ እስከመሾም የደረሰ በመሆኑና በዚህም በተፈጠረው ሽኩቻ ህብረተሰቡ አገልግሎት ለማግኘት መቸገሩን በሰላማዊ ሰልፍ ጭምር መግለፁ ይታወሳል፡፡


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

11 Feb, 04:55


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ .ም


1.በኮሪደር ልማት በለሙ እና የእንግዶች መተላለፊያ በሆኑ መንገዶች ላይ አሽከርካሪዎች ለአጭር ደቂቃም ሆነ ለሰዓት በመንገድ ዳር መቆም እንደማይችሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ከዛሬ የካቲት 04 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እንግዶች ወደ አዲስ አበባ የሚገቡ መሆኑን የገለጸው ቢሮው ለአሽከርካሪዎች መልዕክቱን አስተላልፏል። በዚህም ከዛሬ የካቲት 04 ቀን 2017 ዓ.ም ከንጋቱ 12:00 ጀምሮ  እስከ የካቲት 09 ቀን 2017  ዓ.ም ማታ 12:00  ድረስ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ አካላት በኮሪደር ልማት በለሙና የእንግዶች መተላለፊያ በሆኑ መንገዶች ላይ ለአጭር ደቂቃም ሆነ ለሰዓት በመንገድ ዳር መቆም የማይፈቀድላቸው መሆኑን ቢሮው አስታውቋል።

2. በትግራይ ማንኛዉም አይነት የማዕድን ማውጣት ስራ ታገደ። የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር በክልሉ የሚከናወን ማንኛዉም አይነት የማዕድን ማውጣት ስራ እንዲቆም ወስኗል። ይህ ሕገወጥ የማዕድናት ምዝበራን ለመከላከል ያለመ ነው ተብሎለታል። በፌደራል መንግስት እና የክልል አስተዳደር ፍቃድ ተሰጥቷቸው ወርቅ እና ኮፐር ጨምሮ ሌሎች ማዕድናት የሚያመርቱ አካላትን ሁሉ ስራ እንዲያቆሙ የሚያደርግ ነው።

3. ከሰሞኑ በማህበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወር የነበረው የአንዲት ግለሰብ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ አመራር አውቅና ውጪ የተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። አንዲት ግለሰብ በአውሮፕላኑ መወጣጫ ደረጃ  ላይ የተለያዩ ዲኮሮችን በማድረግ የተነሳችው ፎቶ በማህበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወር መታየቱን የገለጸው አየር መንገዱ፤ ግለሰቧ የተነሳችው ለጥገና በቆመ አውሮፕላን ላይ ቢሆንም ድርጊቱ ከተቋሙ አመራሮች አውቅና ውጪ የተደረገ ነው ብሏል። ጉዳዩን በተመለከተ ምርመራ እያደረገ መሆኑን የገለጸው አየር መንገዱ፤ ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጭ ቀረጻ እንዲካሄድ በፈቀዱ አካላት ላይ አስተዳደራዊ ርምጃ እንደምወስድ እወቁልኝ ብሏል።

4. ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው ከዩናይትድ ስቴትስ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመለሱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ክልከላ አደረገብኝ አሉ። ፖለቲከኛው ትላንት ምሽት ባሰራጩት በፎቶ ግራፍ የተደገፈ የፅሁፍ መልዕክት የካቲት 3 ቀን 2017 ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ አትላንታ አዉሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው እንደነበር ገልጸዋል። ነገር ግን «የአገልግሎት ጊዜው ያላለፈ የኢትዮጵያ ፓስፖርት እና የተረጋገጠ የጉዞ ቲኬት ይዤ የተገኘሁ ቢሆንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግን በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲን አነጋግሬ የተለየ ፈቃድ ካልተሰጠኝ በስተቀር ወደ ኢትዮጵያ መጓዝ እንደማልችል በአትላንታ የኢትዮዽያ አየር መንገድ ሀላፊ በሆኑት በአቶ ተሾመ ገ/ስላሴ ተነግሮኝ ተመልሻለሁ።» ብለዋል። «መንግስት እኔን በወንጀለኛነት ከጠረጠረኝ ሊከሰኝና ሊያስረኝ ይችላል እንጅ ወደ አገሬ እንዳልገባ ሊከለክለኝ አይችልም።» ያሉት ልደቱ «የሀገሩን የጉዞ ሰነድ የያዘ ዜጋን ወደ ሀገሩ እንዳይገባ ለመከልከል የህግ ማዕቀፍ የለም» ብለዋል። ክልከላውን ተከትሎ በሌላ አየር መንገድ ተጓጉዘው ወደ ሀገር ቤት እንደሚመለሱም አቶ ልደቱ አረጋግጠዋል። አቶ ልደቱ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ጉዞ ስለመከልከላቸው አየር መንገዱ ለጊዜው ያለው ነገር የለም ።

5. ሀማስ ቀሪ የእስራኤል ታጋቾችን የመልቀቅ ሂደት ማራዘሙን አስታወቀ። እስራኤል የጋዛን የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣሷ ምክንያት የፊታችን ቅዳሜ ይደረጋል ተብሎ የነበረው ታጋቾችን የመልቀቅ ሂደት ለማራዘም መወሰኑን የሃማስ ቃል አቀባይ ገልጸዋል። ባለፉት ሦስት ሳምንታት ውስጥ እስራኤል የስምምነቱን ውሎች አልጠበቀችም የተባለ ሲሆን የተፈናቀሉ ሰዎች ወደ ሰሜናዊ ጋዛ የመመለስ ሂደት ማዘግየት፣ በተለያዩ  አካባቢዎች የቦምብ ድብደባ እና የተኩስ ኢላማ ማድረግ፣ እንዲሁም በስምምነቱ መሰረት የሰብአዊ እርዳታ በሁሉም መልኩ እንዳይገባ እስራኤል አድርጋለች ሲል ወቅሷል። የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር የሃማስ መግለጫ ተከትሎ በሰጡት ምላሽ  የተኩስ አቁም ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ የጣሰ ውሳኔ  ሲሉ ጠርተውታል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari


#Ethiopia #dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Feb, 15:41


የዕለቱ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም


1. በአፋር ክልል ባለ ብሔራዊ ፓርክ ባለፈው ቅዳሜ የተቀሰቀሰ ሰደድ እሳት እስካሁን በቁጥጥር ስር አልዋለም። በአፋር እና በኦሮሚያ ክልሎች መካከል በሚገኘው ሃላይዳጌ አሰቦት ብሔራዊ ፓርክ ከትላንት በስቲያ የተቀሰቀሰው ሰደድ እሳት እስከ ዛሬ ሰኞ ድረስ በቁጥጥር ስር አለመዋሉ ተነግሯል። በሰደድ እሳቱ 200 ሄክታር የሚገመት የፓርኩ ክፍል መቃጠሉ ተገልጿል። ከ1965 ዓ.ም ጀምሮ የዱር እንስሳት ጥብቅ ቦታ ሆኖ የቆየው ሃላይዳጌ አሰቦት ብሔራዊ ፓርክ፤ 1099 ገደማ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት አለው። ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ብሔራዊ ፓርክ ደረጃ ያደገው ቦታው፤ የ325 የእጽዋት ዝርያ፣ የ244 የአእዋፍ ዝርያ እና ከ42 በላይ አጥቢ እንስሳት መኖሪያ ነው።

2. በኢትዮጵያ በከፍተኛ ሁኔታ የሚጥል በሽታ መድሃኒት እጥረት ተፈጥሯል ተባለ። በኢትዮጵያ የሚጥል በሽታ መድሐኒት እጥረት መኖሩን ኬር ኢፕሊብሲ ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት አስታውቋል። የበሽታው ታማሚዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ቢሆንም ከፍተኛ የመድሃኒት አቅርቦት እጥረት እንዳለ እንዳለ ነው የተነገረው። አብዛኞቹ ለሚጥል በሽታ የሚያገለግሉ መድሃኒቶች ከውጭ የሚገቡ መሆኑን የተነገረ ሲሆን፣ በአንጻሩ አብዛኛው ታማሚዎች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ በመሆኑ ውድ ዋጋ ያላቸውን መድሃኒቶች ገዝተው መጠቀም እንደማይችሉ ተነግሯል።

3. ኢትዮጵያ ከ100 በላይ የደቡብ ሱዳን ተማሪዎች የትምህርት እድል ሰጠች። በጁባ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የገንዘብ ድጋፍ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና መርሃ ግብር ለመከታተል ከ100 በላይ የደቡብ ሱዳን ተማሪዎች የትምህርት እድል አግኝተዋል። የትምህርት እድሉ የተለያዩ ዘርፎችን ይሸፍናል የተባለ ሲሆን ሲቪል ምህንድስና፡ ኤሌክትሪካዊ ምህንድስና፡ ኮምፒውተር ሳይንስ እና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT)ን ያካተተ ነው ተብሏል። በዚህ አመት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና 110 ተማሪዎችን ስፖንሰር ያደረገ ሲሆን እስካሁን 79 ቱ ቪዛቸውን ጨርሰዋል በሳምንቱ ውስጥ ይነሳሉም ተብሏል።

4. ሜቄዶኒያ የአረጋዊያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የሚያግዛቸውን ሰዎች ቁጥር ወደ 20,000 ሺህ የማድረስ እቅድ አለኝ አለ፡፡ ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን በያዘው የገቢ ማሰባሰቢያ ፕርግራም ከ151 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን የማዕከሉ  መስራች እና ስራ አስኪያጁ ቢኒያም በለጠ ተናግሯል። ማዕከሉ ከ8 ሺህ በላይ አረጋዊያንን እና የአዕምሮ ህሙማንን እየደገፈ ይገኛል። ይህንን ቁጥር 20 ሺህ ለማድረስ አስቧል። በኢትዮጵያ ያሉትን 44 ቅርንጫፎችም ወደ 200 ከፍ የማድረግ እቅድ ይዟል። የማዕከሉን ሆስፒታል፣ የመኖሪያ ቤትና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ህንፃ ለማጠናቀቅ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል፡፡

5. የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሱዳኑን የፈጥኖ ደራሽ RSF የረሃብ ስጋት ባጠላበት ዳርፉር ርዳታ እንዳይደርስ እንቅፋት ሆኗል ሲል ከሰሰ። ድርጅቱ እንዳለው የፈጥኖ ደራሹ ቡድን በሰሜናዊቷ የዳርፉር ከተማ ኤል ፋሽር ካለፈው ዓመት የግንቦት ወር አንስቶ የተፈናይ መጠለያዎችን እያጠቃ ይገኛል። በሱዳን የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ እርዳታ አስተባባሪ “አር ኤስ ኤፍ በሰብአዊ የርዳታ ድርጅቶች ላይ የተጣሉ  የማያቋርጡ እገዳዎች እና የቢሮክራሲያዊ መሰናክሎች የህይወት አድን ርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች እንዳይደርስ እየከለከሉ ነው´´ብለዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#Ethiopia #Dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Feb, 12:51


"ፍልውሀ ድርጅት 300 ሺህ ብር ተቀጣ"

የመንገድ መሠረተ ልማት አበላሽቷል የተባለው ፍልውሀ ድርጅት 300 ሺህ ብር ተቀጥቷል ተባለ።

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ምሽትን ተገን በማድረግ የቆሸሸ ውሃ አዲስ ወደ ተሠራው አስፓልት የለቀቀው የፍልውሃ አገልግሎት ድርጅት 300 ሺህ ብር በመቅጣት ያቆሸሸውን አካባቢ እንዲያጸዳ መደረጉ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በከተማዋ ደንብ የሚተላለፉ የግልና የመንግስት ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የምወስደውን እርምጃ አጠናክሬ እቀጥላለሁ ብሏል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Feb, 12:02


የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ከሠራተኞች ደመወዝ የፓርቲ አባልነት መዋጮ እንዳይቆርጡ የሚከለክል ረቂቅ ሕግ ተዘጋጀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የፖለቲካ ፓርቲ አባልነት መዋጮን ከሠራተኞቻቸው ደመወዝ ላይ "በቀጥታ" እየቆረጡ አባል ወደ ሆኑበት የፖለቲካ ፓርቲ የባንክ ሂሳብ እንዳያስገቡ የሚከለክል ረቂቅ ሕግ መዘጋጀቱ ተገልጿል።

በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የገዢው ፓርቲ አባል የሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች የአባልነት መዋጮ የሚከፍሉት በተቀጠሩበት መሥሪያ ቤት አማካኝነት ከወርሃዊ ደመወዛቸው ላይ ተቀናሽ እየተደረገ ነው።

የገዢው ፓርቲ አባላት የሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች በፈቃዳቸው ይህንን መዋጮ የሚያደርጉ ቢሆንም በተለያዩ ጊዜያት የመንግሥት ሠራተኞች ያለፍቃዳቸው ከደመወዛቸው ላይ መዋጮ መቆረጡን በመጥቀስ ቅሬታ የሚያቀርቡባቸው አጋጣሚዎች ነበሩ።

ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀው የማሻሻያ ረቂቅ፤ መሥሪያ ቤቶች ከሠራተኞቻቸው ደመወዝ ላይ የአባልነት መዋጮ የሚቁርጡበትን አሠራር ይከለክላል።

በተጨማሪም የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎች "ከማናቸውም ሰው የሚሰጥን ስጦታ ወይም እርዳታን" በግላቸው እንዳይቀበሉ ይከለክላል።

በረቂቁ መሠረት ይህንን ዓይነቱን ስጦታ ወይም እርዳታ መቀበል የሚችሉት "በፓርቲው በኩል" ነው።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#Ethiopia #dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Feb, 06:27


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም

1. ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከወሊድ ጋር ተያያዘ ብቻ 620 እናቶች መሞታቸው ተገልጿል፡፡የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እንደገለጸው ከወሊድ ጋር በተያያዘ 620 እናቶች ሞተዋል የተባለ ሲሆን ለየሞታቸው ምክንያት በዝርዝር አልተብራራም፡፡ በሌላ በኩል ባለፉት ስድስት ወራት በአገር ደረጃ ከፍተኛ የምግብ እጥረት መከሰቱን ተከትሎ 352 ሕፃናት ሲሞቱ 232‚389 ሕፃናት ደግሞ ለሕመም መዳረጋቸውን ኢንስቲትዩቱ ገልጿል፡፡

2. ጨፌ ኦሮሚያ  በርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የቀረቡለትን የተለያዩ ሹመቶችን አጽድቋል። 1ኛ  አቶ ከፋያለው ተፈራ፣ በምክትል በርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ በጨፌ ኦሮሚያ የመንግስት ዋና ተጠሪ፣ 2ኛ  አቶ አዲሱ አረጋ፣ በምክትል በርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ፣ 3ኛ  አቶ ሳዳት ነሻ፣ በምክትል በርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ፣ 4ኛ ፕሮፌሰር ነጻነት ወርቅነህ  የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ሃላፊ፣ 5ኛ አቶ ተስፋዬ ቱሉ  የኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ፣ 6ኛ ዶክተር ነመራ ገበየሁ የኦሮሚያ ማዕድን ልማት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር፣ 7ኛ አቶ ፍሰሃ በላይነህ የኦቢኤን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል።

3. በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ7 ሺህ ሊትር በላይ ቤንዚን ተያዘ። በአዲስ አበባ ከተማ በህገ-ወጥ መንገድ በጭነት አይሱዚ ሲዘዋወር የነበረ 7 ሺህ 831 ሊትር ቤንዚን በቁጥጥር ስር ውሏል ተብሏል፡፡ ቤንዚኑ በቁጥጥር ስር የዋለው በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ከአንፎ አደባባይ ወደ ጦር ኃይሎች በሚወስደው መንገድ በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር መሆኑ ተገልጿል፡፡

4. በትምህርት ተቋማት ላይ ያሉ ሴት ተመራማሪዎችም በሚሰሩት ስራ እና ባላቸው አቅም መጠን ወደ ፊት ሲመጡ አይታም ተብሏል፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ እንደሀገር  የምናጣው ነገር ቀላል አለመሆኑ ተነግሯል። ሴቶች በኢትዮጵያ ጥናት እና ምርምር ውስጥ ያላቸው ድምፅ እና መገኘት እንዳሉበት ያህል አለመሆኑን ተመልክቻለሁ ሲል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጥናት የሚያካሂደው ሪፍት ቫሊ ኢንስቲትዩት የተሰኘ ተቋም ተናግሯል፡፡ በዚህም ምክንያት ሴት ተመራማሪዎች እይታ እንዲያገኙ ያግዛቸዋል የተባለ ጥምረት አቋቁሜአለሁ ብሏል፡፡ ኢንስቲትዩቱ አቋቋምኩት ያለው የኢትዮጵያ ሴቶች ጥናት እና ተመራማሪዎች ጥምረት (እውነት) የተሰኘው ጥምረቱ በዩኒቨርስቲም ሆኑ ከዩኒቨርስቲዎች ውጭም ያሉ በማህበራዊ ሳይንስ ላይ ጥናት እና ምርምር የሚያካሂዱ ሴቶችን በቀዳሚነት የሚያስተናግድ ነው ተብሎለታል።

5. የእስራእል ወታደሮች ሰሜን ጋዛን ከደቡብ ጋዛ ከሚከፍለዉ የኖትዛሪም የጦር ቀጠና መዉጣታቸዉ ተገልጿል፡፡ የእስራኤል ወታደሮቿን የማስወጣት ተግባር ሃገሪቱ በቅርቡ ከሃማስ ጋር ባደረገችው የተኩስ አቁም ስምምነት ማዕቀፍ መሰረት የተፈፀመ መሆኑ ይታወቃል።የወታደሮቹ የመውጣት ውሳኔ እስራኤል እና ሃማስ አምስተኛ የእስረኞች ልውውጣቸውን ካጠናቀቁ በኋላ የመጨረሻዎቹ ሶስት እስራኤላውያን ምርኮኞች እና 183 ፍልስጤማውያን እስረኞች ከተፈቱ በኋላ የተከናወነ ነው ተብሏል። ባጋዛ ጦርነት ሁለት ሶስተኛ የሚሆኑት የጋዛ ህንፃዎች መዉደማቸዉ የተገለፀ ሲሆን፤ 46 ሺህ በላይ የሚሆኑ ፍልስጤማዉያን መገደላቸዉ ተነግሯል። እንዲሁም 700 ሺህ የሚጠጉ የሰሜን ጋዛ ነዋሪዎች ጦርነቱ በተጀመረበት ወቅት አሁን የእስራእል ወታሮች ለቀዉ በወጡት ኮሪደር በኩል ወደ ደቡብ ጋዛ ለመሸሽ ተገደዉ እንደነበር ተጠቁሟል፡፡ ከስምምነቱ በኋላም ከ300 ሺህ በላይ የሰሜን ጋዛ ነዋሪዎች በጦርነቱ ተሰደውበት ከነበረው የደቡብ ጋዛ ወደ ሰሜን መሻገራቸው ተነግሯል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari


#Ethiopia #dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

08 Feb, 16:07


የዕለቱ አበይት ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም

1. በኢትዮጵያ እየተባባሰ ከመጣው የመሬት መንቀጥቀጥ ጋር ተያይዞ እሳተ ጎመራ ሊፈጠር ይችላል ተባለ። ከምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ጋር የተያያዙ ተከታታይ የመሬት መንቀጥቀጦች በኢትዮጵያ እሳተ ጎመራ ሊፈጠር ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል። የአፍሪካ እና የአረብ ሳህኖች ቀስ በቀስ መለያየታቸው በመካሄድ ላይ ያለው የቴክቶኒክ እንቅስቃሴ ሀገሪቱን ለመሬት መንቀጥቀጥ እና ለእሳተ ገሞራ አለመረጋጋት ያላትን ተጋላጭነት ከፍ አድርጎታል። የቅርብ ጊዜዎቹ የመሬት መንቀጥቀጥ የመሰረተ ልማት ውድመት አስከትለዋል በተጨማሪም በአስር ሺዎች የሚቆጠሩትን አፈናቅሏል ተብሏል። በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ የዶፌን ተራራ አቅራቢያ 5.8 በሬክተር ስኬል የተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ እስከ አዲስ አበባ ድረስ መሰማቱ የሚታወስ ነው። የመሬት መንቀጥቀጡ ወደ 80,338 የሚገመቱ ነዋሪዎችን ከቀያቸው ያፈናቀሉ ሲሆን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የስኳር አምራቾች መካከል አንዱ የሆነውን የከሰም ስኳር ፋብሪካን ጨምሮ ጉዳቱ በቤቶች፣ መንገዶች እና ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ ዘልቋል ተብሏል።

2. የኢትዮጵያ እና የኬንያ መንግስታት በጋራ ድንበራቸው ላይ በሚገኙ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት መሸሸጊያ ቦታዎች ላይ ያነጣጠረ ነው ያሉትን የተቀናጀ ወታደራዊ ጥቃት ጀመሩ። ዘመቻው ይፋ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሃላፊ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከቀናት በፊት በናይሮቢ ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ ነው። ዘመቻው ሽብርተኝነትን፣ የኮንትሮባንድ ንግድን፣ የሰዎችን እና የጦር መሳሪያ ዝውውርን ጨምሮ የቡድኑን ተግባራት ለመበተን ያለመ መሆኑ ታውቋል።

3. በትግራይ ክልል ህገወጥ የማዕድን ቁፋሮ ፈተና እየሆነ ነው ተባለ። ከጦርነት ቀጠና ያላገገመው ክልሉ ይህ ህገወጥ የማዕድን ቁፋሮ መጨመር ደግሞ ሌላኛው ስጋቱ መሆኑ ተነግሯል። የክልሉ የማዕድን ሀብት፣ በተለይም የወርቅ ክምችት ለኢኮኖሚው ትልቅ አስተዋጽፆ አበርካች ነው ቢባልለትም ግን አሁን ማዕድናቱ በህገወጦች እየተበዘበዙ እና እየተራቆቱ ነው ተብሏል። ይህ መሆኑ ደግሞ ቀድሞውንም ለብዙ ነገር ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ይበልጥ እየጎዳቸው ነው።
በተጨማሪም ለሀገርም ሆነ ለክልሉ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ መሆኑ ይናገራል። በዚህም ምክንያት እንደ ጤና፣ ትምህርት እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ያሉ አስፈላጊ አገልግሎቶችን የመስጠት አቅሙን በእጅጉ ይጎትተዋል ተብሏል።

4. በ2017 በጀት ዓመት ባለፋት ስድስት ወራት 169 የDNA ምርመራ ተከናውኗል። የDNA ምርመራ አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም በሀገር ውስጥ ባለመኖሩ ናሙና ወደ ውጭ ሀገር ይላክ የነበረው መሆኑ ይታወሳል። በተለይ የሰዎችን ማንነት ለመለየት፤ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ለማረጋገጥ፣ ከተወላጅነት ጋር ስለሚነሱ ክርክሮችና ቤተሰባዊ ጉዳዮችን ለመመርመር የሚያስችል ብቃት መገንባቱን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል። በዚህም በተያዘው በጀት አመት ስድስት ወቀት 169 የDNA ምርመራ መከናወኑ ተገልጿል። ውጤቱ የተመዘገበው ላብራቶሪ በማደራጀትና በዘርፉ ተገቢውን የሙያ ዕውቀት ያላቸው ባለሙያዎችን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር አሰልጥኖ ወደ ሥራ በማሰማራት ነው ተብሏል።

5. በሺዎች የሚቆጠሩ የዩኤስኤአይዲ ሠራተኞች በግዳጅ እረፍት እንዲወጡ የሚያዘው የዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ ታገደ። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የተራድዖ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) ሠራተኞችን ደሞዛቸው እየተከፈላቸው የግዳጅ እረፍት እንዲወጡ በማሰብ ያስተላለፉትን ውሳኔ ዳኞች በግዚያዊነት አግደውታል። ትዕዛዙ 2 ሺህ 200 ሠራተኞች ደሞዛቸው እየተከፈላቸው ከሥራ ገበታቸው እንዲርቁ የሚያድርግ ሲሆን በረጅም ጊዜ ዕቅድ 10 ሺህ የሚደርሱ ሠራተኞችን ከሥራ ለማራቅ መታቀዱን ያመላክታል። ሆኖም ግን ጉዳዩን የያዘው ፍርድ ቤት 500 የሚሆኑ ሠራተኞች ከሥራ ገበታቸው መራቃቸውን በማስታወስ ተጨማሪ ሠራተኞችን ማራቅ ተገቢ ያለመሆኑን አስታውቋል። በዚህም ጉዳዩን አጢኖ ለመመርመር ለየካቲት 7 ቀጠሮ ይዟል።

#Ethiopia #dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

08 Feb, 10:50


በበጀት አመቱ ስድስት ወራት ከ1 ሺህ በላይ ሴቶችና ሕፃናት ተደፈሩ።

በዘንድሮው የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ደግሞ 1 ሺህ 195 ሴቶችና ሕፃናት የወንጀሉ ሰለባ ሆነዋል ተብሏል።

በአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተሞች ጾታዊ ጥቃት በመጠንም ሆነ በድርጊት አፈጻጸሙ እየጨመረ ነው።

በከተሞቹ ጾታዊ ጥቃት በመጠንም ሆነ በድርጊት አፈጻጸሙ እየጨመረ መምጣቱን የፍትህ ሚኒስቴር አስታውቋል።

በከተሞቹ እየታየ ያለው የጾታዊ ጥቃት ከዓመት ዓመት በመጠንም ሆነ በአሰቃቂ የድርጊት አፈጻጸም እየጨመረ እንደሆነ ታይቷል ያለው ፍትህ ሚኒስቴር በ2017 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የአስገድዶ መድፈር ጥቃት የተፈፀመባቸው ከ18 ዓመት በታች ያሉ ሴቶችና ሕፃናት ቁጥር ባለፈው ሙሉ የበጀት ዓመት ከተመዘገበው የበለጠ መሆኑን ተናግሯል።

በ2015 የበጀት ዓመት 1 ሺህ 334 ሴቶችና ሕፃናት ‹‹የግብረ ሥጋ ጥቃት በደል›› ተብሎ በሕግ የተቀመጠው ወንጀል ተፈፅሞባቸዋል፣ በ2016 የበጀት ዓመት የወንጀሉ ተጠቂዎች ቁጥር ወደ 1 ሺህ 355 ከፍ ማለቱ ተነግሯል።

“እነዚህ ቁጥሮች ሪፖርት የተደረጉት ብቻ ናቸው፤ ሪፖርት ያልተደረጉት ሲታከልባቸው ምን ያህል ችግሩ እየገነነ እንደመጣ መረዳት ይቻላል” የተባለ ሲሆን የሚፈፀሙት ተግባራት አሰቃቂነታቸው እየጨመረ እንደመጣም ተነግሯል።

አብዛኞቹ ጥቃቱ ሰለባዎች ሕፃናት መሆናቸውን እና ድርጊቱ በብዛት የሚፈፀመው ደግሞ በትምህርት ቤቶች አካባቢ ነው።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

08 Feb, 05:13


የዕለቱ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም

1. በኢትዮጵያ ከግጭቶች ጋር በተያያዘ ብቻ  92 የሚዲያ ሰራተኞች በቁጥጥር ስራ ውለዋል። እ.ኤ.አ. በ 2019 እና 2024 መካከል ቢያንስ 92 የሚዲያ ሰራተኞችን በቁጥጥር ስር ውለዋል። በ2024 የጋዜጠኞች ተከላካይ ኮሚቴ (CPJ) ባወጣው ዘገባ መሰረት በሀገሪቱ በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን ግጭት የሚዘግቡ ጋዜጠኞችን መንግስት "ከአማፂ ሀይሎች ጋር ግንኙነት አላችሁ ብሎ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተነግሯል። ጋዜጠኞች ይፋ ባልሆኑ እስር ቤቶች እና ወታደራዊ ማቆያ ካምፖች ውስጥ ታስረዋል የሚለው ሪፖርቱ “የፍርድ ቁጥጥር ሳይደረግበት፣ ቤተሰብ ወይም የህግ አማካሪ ሳያገኙ” በአስከፊ ሁኔታ ውስጥ ናቸው ብሏል። እ.ኤ.አ በ2024 ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የጋዜጠኞች እስር ከኤርትራ ቀጥላ ሁለተኛዋ ኢትዮጵያ ናት። ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድንም በስራ ላይ እያሉ በርካታ ጋዜጠኞች የተገደሉበትን ሁኔታ መኖሩን መዝግቧል።

2. የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት ይቀጥላል። የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

3. በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን መኪና በማስቆም በተደረገ እገታ አንድ ሰው ሕይወቱ አለፈ። ከሞተው ሰው በተጨማሪ አራት ደግሞ መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች ተናግረዋል ሲል DW አውርቷል። በሌላ አካባቢ ደግሞ የታገቱ 18 መንደኞችን የመንግሥት ኃይሎች ተታኩሰው ማስለቀቃቸው ተሰምቷል።

4. የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት ለመከላከል የሚያግዝ ረቂቅ አዋጅ ፀደቀ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 18ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ተጋላጭነትን ለመከላከል የሚያግዝ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡ ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ የአካባቢና አየር ንብረት ለውጥ ስምምነቶችና ሕግጋት ጋር የሚጣጣም የሕግ ማዕቀፍ ያለው ረቂቅ አዋጅ መሆኑ ተነግሯል። የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ረቂቅ አዋጅን፤ አዋጅ ቁጥር 1371/2017 አድርጎ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ማጽደቁን የምክርቤቱ መረጃ ያመላክታል።

5. 10 የናይጄሪያ ወታደሮች መገደላቸው ተነገረ።በቡርኪናፋሶ ድንበር አቅራቢያ በደረሰ ጥቃት በትንሹ 10 የናይጄሪያ ወታደሮች መገደላቸውን የናይጄሪያ ጦር እወቁልኝ ብሏል። ወታደሮቹ ሰኞ እለት በምዕራብ ታክዛት መንደር አቅራቢያ ባደረጉት ዘመቻ በደፈጣ ውጊያ  መገደላቸው ተነግሯል። ወታደሮቹ በተገደሉ ማግስቱ 15 የሚሆኑ አሸባሪዎች በአካባቢው በተደረጉ ጥቃቶች መገደላቸው ተገልጿል። ባለፈው ታህሳስ ወር በቡርኪናፋሶ ድንበር አቅራቢያ በታጠቁ ሃይሎች በተፈጸመ ጥቃት ሌሎች 10 የኒጀር ወታደሮች ሲገደሉ ሰባቱ መቁሰላቸው ተዘግቧል። ከ 2017 ጀምሮ በቡርኪናፋሶ፣ በማሊ እና በኒጀር መካከል ባለው ቀጠና በሚንቀሳቀሱ አሸባሪዎች ምክንያት በቲላቤሪ ክልል ውስጥ የሚገኙ የናይጄሪያ ወታደሮች ጥቃት እየደረሰባቸው ይገኛል ሲል አናዶሉ ዘግቧል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #Dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

07 Feb, 15:05


የዕለቱ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም

1. በአማራ ክልል የኮሌራ ወረርሽኝ ዳግም በመከሰቱ የሶስት ሰዎች ህይወት አልፏል። ህርዳርን ጨምሮ በተለያዩ የአማር ክልል አከባቢዎች የኮሌራ ወረርሽኝ መከሰቱን የአውሮፓ ህብረት የአስቸኳይ ምላሾች ማስተባበሪያ ማዕከል ባወጣው መረጃ አስታውቋል። ወረርሽኙም የሶስት ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል። በአማራ ክልል እንደገና በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ 160 ሰዎች መያዛቸውን የጠቆመው መረጃው በተለይም ደግሞ ምዕራብ ጎንደር ዞን በከፍተኛ ሁኔታ ተስፋፍቷል ብሏል።

2. በጎንደር ከተማ ሰባት ትምህርት ቤቶች በጸጥታ ችግር ምክንያት ትምህርት አቋረጡ። በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ ሰባት ትምህርት ቤቶች በጸጥታ ችግር ምክንያት ትምህርት ማቋረጣቸውን የከተማዋ አሥተዳደር ትምህርት መምሪያ ተናግሯል። ትምህርት ቤቶቹ ወደ ሥራ እንዲገቡ እና ተማሪዎች እንዲማሩ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል። በክልሉ እየተካሄደ ባለው ግጭት ሳቢያ በተያዘው የትምህርት ዘመን ይመዘገባሉ ተብሎ ታቅዶ ከነበረው 7 ሚሊዮን ተማሪዎች ውስጥ በትምህርት ላይ ያሉት 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ተማሪዎች ብቻ መኾናቸው ይታወቃል። በአማራ ክልል የተማሪዎች ምዝገባ እስከ የካቲት 30 እንደሚቀጥል እና እስከ ሐምሌ ወር መጨረሻ ትምህርት እንደሚሰጥ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ተናግሯል።

3. ስለ ሰላም ያልሰበክንበት መድረክ ባይኖርም በተግባር ለሰላም ስላኖርን በሀገሪቱ የሰው ደም መፍሰሱ ቀጥሏል።
በሀይማት ተቋማት እና በአማኞች በተለያዩ መድረኮች ስለሰላም እየተሰበከ ቢቆይም በተግባር ሰላም ባለመሰበኩ የንጹሀን ደም በየቦታው እየፈሰሰ ነው ሲሉ የሀይማኖት አባቶች ተናገሩ። በተግባር ካላዋልነው በቃል ብቻ ሰላም ሰላም ማለታችን ዋጋ የለውምም ብለዋል፡፡
የሀገሪቱ 98 በመቶ ገደማ ህዝብ ሀይማኖተኛ ነው እንላለን፣ የሀቅ አማኞች ከሆንን ታዲያ የትኛው ሀይማኖት ነው የሰው ደም አፍስሱ የሚለው? ሲሉም ጠይቀዋል፡፡
አሁን ላይ በኢትዮጵያ ሰላም እደፈረሰ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሀይማት ክብርና ልዕልና እየተነካ እራሳችንን እየጎዳን ነው በማለት ተናግረዋል፡፡

4. ኤች አይቪ ኤድስን መከላከል ላይ የሚከወኑ ስራዎች እየተቀዛቀዙ ነው። ይበልጥ ተጋላጭ ናቸው የተባሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ እየተሰራበት እንደሆነ ይነገራል በተለይ በወጣቶች የኤች አይ ቪ መከላከል ላይ ግን የሚከወኑ ስራዎች ከዚህ ቀደም እንደነበሩት አለመሆናቸው ተነግሯል፡፡ በወጣቶች ላይ አተኩሮ በተለያዩ ክልሎች ላይ በኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከል ላይ የሚሰራው ጣምራ ለማህበራዊ ልማት የተባለው ድርጅት እንደሚናገረው ከጥቂት አመታት ወዲህ ኤች አይ ቪን መከላከል ላይ የሚከወኑ ስራዎች ከወጣቶች ይልቅ ለቫይረሱ ተጋላጭ ናቸው የተባሉ ሌሎች ዜጎች ላይ አተኩሯል ብሏል። በኢትዮጵያ በየዓመቱ 7 ሺህ ያህል አዳዲስ ሰዎች በኤች አይቪ የሚያዙ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 70 በመቶ ያህሉ በአፍላ ዕድሜ ላይ የሚገኙ ወጣቶች ናቸው። በሀገሪቱ እድሜያቸው ከ15 በላይ በሆኑ ሰዎች መካከል የኤች አይ ቪ ስርጭት ምጣኔውም 0.87 በመቶ መሆኑ ተነግሯል።

5. የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል መዳኛ ፍርድ ቤት (ICC) ላይ ማዕቀብ እንዲጣልበት የሚየደርግ ትዕዛዝ ፈረሙ። ችሎቱንም ሕገወጥ ሱሉ መጥራታቸውን ቢቢሲ ፅፏል። በአሜሪካ እና የቅርብ አጋሯ የሆነችው በእስራኤል ላይ ያነጣጠረ  ያልተገባ ተግባር እያከናወነ ነው ሱሉ ትራምፕ ችሎቱን ወርፈውታል። ICC ከጥቂት ወራት በፊት  በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒ ጋንቴዝ ላይ አለም አቀፍ የመያዣ ትዕዛዝ እንዳይወጣባቸው ተነግሯል። ከዚያ ጊዜ አንስቶ የአሜሪካ መንግስት ICCን ክፉኛ ሲያብጠለጥለው ቆይቷል።

#ethiopia #Dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

07 Feb, 14:36


ከአንዲት እናት 20 ነጥብ 6 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕጢ በቀዶ ሕክምና ወጣላት።

በማይጨው ለምለም ካርል ሆስፒታል ከአንዲት እናት 20 ነጥብ 6 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕጢ በቀዶ ሕክምና መወገዱ ተገልጿል፡፡

የቦራ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ታካሚዋ እናት እድሜአቸው 63 ሲሆን፤ ዕጢው ለዓመታት አብሯቸው እንደነበር ተነግሯል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

07 Feb, 08:22


በኢትዮጵያ ሆን ተብሎ በሰው አማካይነት 10 የእሳት አደጋዎች ደርሰዋል ተባለ፡፡

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ባለፉት 6 ወራት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የደረሱ 103 የእሳት ቃጠሎ መንስኤዎችን በፎረንሲክ ምርመራ አጣርቻለሁ ብሏል፡፡

በምርመራው በአዲስ አበባ ከተማ የተከሰቱ 96 እንዲሁም በክልሎች ሰባት የእሳት ቃጠሎ አደጋዎች መንስኤዎች ይፋ መደረጋቸው ተጠቁሟል፡፡

በዚህ መሰረትም በኤሌክትሪክ ቴክኒክ ችግር ምክንያት የደረሰ 50 ቃጠሎ፣ በመካኒካል ችግር ምክንያት የደረሰ 11 ቃጠሎ፣ ሆን ተብሎ በዘው አማካኝነት የደረሰ 10 ቃጠሎ፣ በቸልተኝነት የደረሰ 17 እና በሌሎች ምክንያቶች የደረሰ 15 ቃጠሎ መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡

በገግማሽ ዓመቱ በ582 መኖሪያ ቤት፣ በ12 ተሸከርካሪዎች፣ በ1 ሺህ 965 ንግድ ቤቶች በስድስት ፋብሪካዎችና የተለያዩ ድርጅቶች በቃጠሎ ምክንያት ጉዳት ስለመድረሱ ሪፖርቱ አመላክቷል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሸማ ተራ ነባር የገበያ ማዕከልና በአካባቢው የደረሰው የእሳት አደጋ መንስኤም በኤሌክትሪክ ቴክኒክ ችግር የተከሰተ አደጋ መሆኑን በፎረንሲክ ምርመራ ማጣራት ችያለሁ ብሏል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ።

ይሁንና ፖሊስ በአደጋው ስለ ተሳተፉ ሰዎች ጉዳይ እና ተያያዥ ጉዳዮች በሪፖርቱ ላይ አልጠቀሰም።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

07 Feb, 05:25


የዕለቱ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም

1. ከጎረቤት ሀገራት የተዛመተ የፖሊዮ በሽታ የኢትዮጵያ ሕፃናት ላይ መታየቱን ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በኢትዮጵያ በ23 ሕፃናት ላይ በክትባት እጥረት የሚመጣ ከጎረቤት ሀገራት የተዛመተ የፖሊዮ በሽታ መታየቱን ተገልጿል። በሽታው እንዳይስፋፋም ባለፉት ስድስት ወራት በአማራ፣ አፋር፣ ጋምቤላ ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ ለአምስት ነጥብ አራት ሚሊዮን ህጻናት ክትባት መሰጠቱ ተነግሯል። በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታትም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአምስት ዓመት በታች ለሆኑ ለ14 ሚሊዮን ህጻናት የፖሊዮ ክትባት  ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው። ከሌሎች ሀገራት የሚመጣ የፖሊዮ በሽታ ለመከላከልም በድንበር አካባቢ የቅኝት ስራዎች መቀጠላቸውን እና ከሀገራቶቹ ጋርም በጋራ ለመስራት እየተሞከረ ነው ተብሏል።

2. በአዲስ አበባ አንዳንድ የመንግስት አገልግሎቶችን  በ3ተኛ ወገን ለማሰራት የሚያስችል ደንብ ፀደቀ። በሶሶተኛ ወገን ለማሰራት የታሰቡት የመንግስት ስራዎች የትኞቹ እንደሆኑ ግን አልተገለፀም። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 4ተኛ ዓመት 7ተኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። ወሳኔ ከተላለፈባቸው መካከል አንዳንድ የመንግስት አገልግሎቶችን በውል ለ3ተኛ ወገን ለማስራት የወጣውን ረቂቅ ደንብ ካቢኔዉ ያፅደቀበት ይገኝበታል። በከተማዉ  አስተዳደር በጀት ተመድቦላቸዉ የተገነቡ እና በመጠናቀቅ ያሉትን  አዳዲስ ሆስፒታሎችን ዘመኑን በዋጀ ህክምና መሳሪያ ለማሟላት እና አለም አቀፍ ደረጃን የሚያሟላ  አገልግሎት መስጠት ያስችላቸው ዘንድ  በዘርፉ ትልቅ ልምድ ካከበቱ የግል ሴክተር ጋር በአጋርነት ለመስራት ዉሳኔ አሳልፏል። የተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ላላቸው እና ተኪ ምርቶችን ለሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች ባቀረቡት የማስፋፊያ ቦታ ጥያቄዎች በሙሉ ድምፅ ፅድቋል። ካቢኔው የኮሪደር ልማት ውጤት ከሆኑት ሥራዎች አንዱ የብዙሀን ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ችግሮች የሚያቃልል እና የትራፊክ ፍስቱን የሚያሻሽለው የብስክሌት መጋራት አገልግሎት እና የብስክሌት መስመር አጠቃቀም ደንብንም አፅድቋል።



3. በአራዳ ክፍለ ከተማ ቤታችሁ አርጅቷል፤ እንድናስላቸሁ በሚል ቤታቸው ከፈረሰ በኋላ ክፍለ ከተማው ቃሉን ጠብቆ ቤት ገንብቶ ሳይሰጣቸው 6 ወር እንደሆናቸው ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ ክፍለ ከተማው በበኩሉ ቤቱን እንዲገነባ ሀላፊነት የተሰጠው አካል ቤቱን ለመገንባት በመዘግየቱ የተፈጠረ ችግር ነው ይላል፡፡ እስካሁን የቤቶቹ ግንባታ አልተጀመረም። ቤታችን ፈርሶ እቃችንን አውጥተን በአንድ ትምህርት ቤት ውስጥ እንድናስቀምጥ ከተደረገ በኋላ ለቤት ኪራይ ሳይሰጠን ጎዳና ላይ ከወደቅን 6 ወር ሊሞላን ነው ብለዋል፡፡እኛ ከዛሬ ነገ ቤቱ ተገንብቶ ይሰጠናል እንላለን ነገር ግን እቃችሁን ካስቀመጣችሁበት ትምህርት ቤት አውጡ ተባልን ይላሉ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ የአራዳ ክፍለ ከተማ በበኩሉ የቤት ግንባታው የዘገየው እንዲገነቡ ኃላፊነት በተሰጣቸው አካላት ምክንያት ነው፣ ቅሬታ አቅራቢዎች ቤታቸው ከፈረሰባቸው 6 ወር ቢሞላውን ዘግይቶም ቢሆን 15ሺ ብር ለሶስት ወር ቤት ኪራይ ተሰጥቷቸዋል ብሏል።


4. የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት እርዳታ ማቋረጡ ኢትዮጵያ በኤች አይ ቪ ላይ የምታደርገውን ትግል አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን የመንግስታቱ ድርጅት አስታወቀ።
ከሩብ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የቫይረሱ መድሃኒት ተጠቃሚዎችን ለአደጋ ያጋልጣል ሲልም አስጠንቅቋል።
ከኤች አይ ቪ/ኤድስ ጋር በተያያዘ #የአሜሪካ መንግስት ለኢትዮጵያ የሚሰጠው ድጋፍና እርዳታ መቋረጥ በኦሮሚያ እና ጋምቤላ ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ ከ270 ሺ በላይ ለሚሆኑ የቫይረሱ መከላከያ መድሃኒት ተጠቃሚዎችን ህይወት ይበልጥ ከባድ ያደርገዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኤች አይ ቪ/ኤድስ ፕሮግራም አስጠንቅቋል።

5. የዩጋንዳ ፖሊስ ከባንክ ማጭበርበር በተዘረፈ ገንዘብ ምክንያት ዘጠኝ የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ ሹሞችን አሰረ፡፡ ጉዳዩ የኮምፒዩተር መረጃ በማመሳቀል (ሐኪንግ) ከማዕከላዊ ባንክ ከተዘረፈ 62 ቢሊዮን የዩጋንዳ ሽልንግ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ተነግሯል። በኮምፒዩተር መረጃ ማመሳቀል ከባንኩ የተዘረፈው ገንዘብ የ17 ሚሊዮን ዶላር ያህል የምንዛሪ ግምት ያለው ነው ተብሏል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴ መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ ሹሞች በፖሊስ ተይዘው የታሰሩት በዘረፋው እጃቸው አለበት ተብሎ ነው።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #Dailynews #morningnews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

06 Feb, 14:59


የዕለቱ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም

1. የመንግትን ጥሪ ተቀብለን የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ዕድሉን እናገኛለን ብለን ወደ አዲስ አበባ ብንመጣ ጎዳና እስከ መውጣት ደርሰናል ሲሉ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች የመጡ ወጣቶች ተናገሩ፡፡ ወጣቶቹ መንግስት ያወጣውን አዋጅ ተከትሎ በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በኩል የሚሰጠውን ስልጠና መውሰዳቸውንና አስፈላጊውን ሰርተፍኬት እንደተሰጣቸውም ተናግረዋል። በነፃ ነው ተብሎ የሚነገርለት ይህ ስልጠና እስከ ስድስት ሺህ ብር መክፈላቸውን  አስረድተዋል፡፡ ይሁንና እዚህ መጥተው ስልጠናውን አጠናቀው ፈተናውንም ቢያልፉ ትሄዳላችሁ የተባሉት የውጭ ሃገር ስራ ስምሪት የውሃ ሽታ እንደሆነባቸውም ተናግረዋል፡፡ ያለንን ገንዘብ ለስልጠናና ለተለያዩ ወጪዎች በማውጣታችን ባዶ እጃችንን ቀርተናል ወደ የቤተሰቦቻችን ለመመለስ ተቸግረናል ብለዋል:: የስራና ክህሎት ቢሮ በመሄድ ምንድነው መፍትሄው ብንላቸውም ወደ ኤጀንሲው ሂዱ ይሉና ወደ ኤጀንሲው ስንሄድ ደግሞ የናንተ ጉዳይ አልተጀመረን በማለት በመሃል ቤት እኛ ለስቃይ ተዳርገናል ሲሉ ወጣቶቹ ተናግረዋል፡፡

2. በአማራ ክልል የ2017 የትምህርት ዘመን ከጀመረ መንፈቅ ቢሆንም ወደ ትምህርት ቤት የመጡ ተማሪዎች ቁጥር በተጠበቀው ልክ አይደለም፡፡ በተያዘው የትምህርት ዘመን 7 ሚሊዬን ገደማ ተማሪዎችን ለመመዝገብ ታቅዶ እንደነበር የሚናገረው የክልሉ ትምህርት ቢሮ እስካሁን ግን 2.7 ሚሊየን ብቻ ነው የተመዘገበው ብሏል፡፡ ከተመዘገቡት መካከል ደግሞ ወደ ትምህርት ቤት የመጡት 2.3 ሚሊየኑ ብቻ ናቸው፡፡ ወደ ትምህርት ገበታቸው ይመጣሉ ከተባሉ ተማሪዎች ከ40 በመቶ የማይበልጡ በመሆናቸው እና ተማሪዎች ሊመጡ ይችላሉ በሚል የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለሶስተኛ ጊዜ የተማሪዎች ምዝገባ ሊያካሂድ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ለሶስተኛ ዙር የሚመዘገቡ ተማሪዎችን በብሔራዊ በዓላት እና በክረምምት ወቅት ለማስተማር አቅደናል ብሏል፡፡

3. በኢትዮጵያ በከተሞች ያለውን የቤት አቅርቦት ችግር ለመፍታት በአማካኝ 471 ሺህ ቤቶችን መገንባት ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ በኢትዮጵያ በከተሞች ያለውን የቤት አቅርቦት ችግር ለመፍታት በዓመት በአማካኝ 471 ሺህ ቤቶችን መገንባት ይጠይቃል ሲል የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩቱ አስታወቀ። 68 በመቶ የሚሆኑ ዜጎች ቤት ለመስራት የብድር አቅርቦት ይፈልጋሉ። መንግስት በ10 ዓመት እቅዱ 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቤቶችን ለመገንባት እየሰራ ተብሏል፡፡

4. ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ፈቃድ ከወሰዱ 19 ሺህ የተጠጉ የውጭ ባለሀብቶች መካከል ወደ ስራ የገቡት 24 በመቶዎቹ ብቻ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በሌላ በኩል ወደ ስራ ለመግባት ገንዘባቸውን ፈሰስ ያደረጉት ደግሞ የመሬት እና የኤሌክትሪክ ሀይል አገልግሎት በጊዜ እንደማይቀርብላቸው በኦዲት ምርመራ ተረጋግጧል ተብሏል፡፡ ለተጠቀሱትና ለሌሎችም የኦዲት ግኝቶች ምን የማስተካከያ እርምጃ እንደወሰዱ የኮሚሽኑ የስራ ሀላፊዎች በፓርላማው ቀርበው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ምላሹም ለኢንቨስተሮቹ ፍቃድ ከመሰጠቱ በፊት በደንብ ሊጠኑ ይገባ ነበር ብሏል፡፡ በተጨማሪም ከክልሎች ጋር ተናቦ የመስራት ሰፊ ክፍተት አለ የተባለ ሲሆን የውጭ ኢንቨስተሮች ፍቃድ በተሰጣቸው በሁለት አመት ውስጥ ወደ ስራ ካልገቡ ፍቃዳቸው እንዲሰረዝ አስገዳጅ ህግ ቢኖርም እስከ 15 አመት በቅድመ ዝግጅት እና በዝግጅት ላይ ነን በሚል ወደ ስራ ያልገቡ ኢንቨስተሮች በርካታ ናችው ተብሏል፡፡ 

5. በናይጀሪያ 17 አዳጊ ወጣቶች ህይወታቸው አለፈ፡፡ በናይጀርያ ዛምፋራ ግዛት በአንድ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ማደሪያ ላይ በደረሰ ቃጠሎ የ17 አዳጊ ወጣቶች ሕይወት ተቀጠፈ፡፡ ቃጠሎው የደረሰው ከትናንት በስቲያ ሌሊት ቢሆንም ወሬው የተሰማው ግን ትናንት ማምሻውን ነው፡፡ በቃጠሎው ሕይወታቸው ካለፈው ሌላ 17 ተማሪዎች ደግሞ አካላዊ ጉዳት ደረሶባቸዋል ተብሏል፡፡ ቃጠሎው የተቀሰቀሰው ተማሪዎቹ በእንቅልፍ ላይ በነበሩበት ወቅት እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ የቃጠሎው መንስኤ ምን እንደሆነ ለጊዜውም አልታወቀም፡፡ በአደጋው ወቅት በተማሪ ማዳሪያ ክፍሎች ውስጥ ከ100 በላይ ተማሪዎች እንደነበሩ መረጃው አስታውሷል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #Dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

06 Feb, 13:44


የኬንያ ፖሊስ 58 ኢትዮጵየዊያን አሰረ።

ሕጋዊ የጉዞ ሰነድ ሳይዙ ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲጓዙ የነበሩ 58 ኢትዮጵያውያን በኬንያዋ ኪተንገላ ከተማ በፖሊስ ተይዘዋል።

በሞያሌ በኩል አድርገው ኬንያ የገቡት ኢትዮጵያዊያኑ ወደ ደቡብ አፍሪካ በመሸጋገር ላይ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል መዋላቸውን የሀገሪቱ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

ኢትዮጵያዊያኑ በቁጥጥር ስር የዋሉት ህብረተሰቡ ለፖሊስ በመጠቆሙ እንደሆነም ተገልጿል።

ፖሊስ ኢትዮጵያዊያኑን ሲያገኛቸው፣ በምግብ እጥረት ተጎድተውና ደክመው ነበር ብሏል።

በርካታ ኢትዮጵያዊን ወደ ደቡብ አፍሪካ በህገ ወጥ መንገድ ለመጓዝ በሞያሌ በኩል አድርገው ኬንያን እንደመሸጋገሪያ ይጠቀማሉ፡፡

ከሁለት ሳምንት በፊት በኬንያ እስር ቤት የነበሩ ከ50 በላይ ኢትዮጵያዊን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ መደረጉ ይታወሳል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #Kenya

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

06 Feb, 12:52


የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት የመገናኛ ብዙሃንና የጋዜጠኞች አጀንዳ ለይቶ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረከበ።

ምክር ቤቱ ምክክር እንዲደረግባቸው የኢትዮጵያ ሚዲያን የሚመለከቱ 72 ጉዳዮች ለይቻለሁ ብሏል፡፡
ምክር ቤቱ በጉዳዮቹ ላይ በመወያየት 6 ዋና ዋና የሚዲያ ዘርፍ አጀንዳዎችን ለይቶ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በዛሬው እለት አስገብቷል፡፡

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ምክክር እንዲደረግባቸው ከለያቸው ጉዳዮች መካከል የህዝብ ሚዲያ አስተዳደር፣ የመረጃ ነፃነት፣ መረጃ የማግኘት መብት ፣ ስርጭት እና ተደራሽነት የሚሉት ይገኙበታል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የፋይናንስ ዘላቂነት እና የማስታወቂያ ፍትሃዊነት ፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ሚዲያ መሰረተ ልማት ፣ የጋዜጠኞች ጥበቃ ደህንነትና ዋስትና እና የሃላፊነት ውክልና ሚዛኑ ያልተስተካከለ የስርዓተ ፆታ ጉዳይ እና የጋዜጠኞች ሁኔታ የሚሉ አሉበት፡፡

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ አማረ አረጋዊ ከላይ የተዘረዘሩት አጀንዳዎች የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃንና የጋዜጠኞች ጥያቄዎች ናቸው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ መገናኛ ብዙሃን ባለፉት 3 ዓመታት እንደ ሀገር እየተደረገ ያለው ሀገራዊ ምክክር ውጤታማ እንዲሆን አብሮን እየሰራ ነው ብለዋል።

ኮሚሽኑ በ1100 ወረዳዎች አጀንዳ የማሰባሰብ ስራ ተሰርቷል አብዛኛዎቹ ጥያቄዎች የሰላም ማስፈን፣ መልካም አስተዳደር እና ፍትህን የማስፈን ጥያቄዎች ናቸው ሲሉ ዋና ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል አጀንዳ የማሰባሰቡን ስራ በሚቀጥሉት 3 ሳምንታት ለመጨረስ አቅዶ እየሰራ ይገኛል ተብሏል።

ከአማራ ክልል በመቀጠል በትግራይ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰቡ ስራ ለመጀመር መታሰቡን ሲነገር ሰምተናል።

#ethiopia #Dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

06 Feb, 08:39


በአገር አቀፍ ደረጃ ከ176 ሺህ በላይ ተማሪዎች  የመውጫ ፈተና እየወሰዱ ነው።

በአገር አቀፍ ደረጃ በ87 የፈተና ማዕከላት 176,045 ተፈታኞች በዛሬው እለት የመውጫ ፈተና በመውሰድ ላይ እንደሚገኙ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

የመውጫ ፈተናው በዛሬ እለት  የወሰዱ ያሉ ተፈታኞች ከ18 ሺ በላይ መሆናቸውን የተነገረ ሲሆን በዚህም ዩኒቨርሲቲው በየአንዳንዱ የፈተና ክፍል ውሰጥ ካሉት ሁለት የመጠባበቂያ ኮሚፒዊተሮች ውጪ በዩኒቨርሲቲው ሰባት ኮሌጆች ላይ 21,706 ኮምፒዊተሮች እና 69 የመፈተኛ ክፈሎች ዝግጁ መሆናቸውን ተገልጿል።

በተጨመሪም በፈተናው ሂደትም ተንቀሳቃሽ ሰልከ ይዘው ወደ ፈተና ጣቢያው ለመገባት የሞከሩ ተማሪዎች መኖራቸው እና ከሲስተምም ሆነ ከኮምፒዊተር ጋር ተያይዞ የተከሰተ ችግር አለመኖሩን ተነግሯል፡፡

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

06 Feb, 07:04


ባህርዳር ዩንቨርሲቲ የዶክተር አንዷለም ዳኘ ግድያ በገለልተኛ አካል እንዲመረመር ጠየቀ

ከአራት ቀናት በፊት ከስራ ቦታ ወጥተው ቤታቸው አቅራቢያ ሲደርሱ በተተኮሰባቸው ጥይት የተገደሉት የባህርዳር ዩኒቨርሲቲው ዶክተር  አንዱአለም ጉዳይ በተለይ በህክምና ማህበረሰቡ ዘንድ ድንጋጤና ቁጣን ፈጥሯል።

የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ አባላት "ፍትህ ለዶክተር ለአንዱአለም ዳኜ" የሚል መፈክር በማሰማት ሰልፍ ማድረጋቸውን ዩኒቨርሲቲው በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል።

ዩንቨርሲቲው ከዚህ በተጨማሪም የቀዶ ጥገና ሀኪሙ ዶክተር አንዱአለም ዳኜን ቤተሰብ ለመደገፍ የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻ መጀመሩንም አስታውቋል።

ገቢውን ቤተሰቡን ለመደገፍ እና እሳቸውን ለመዘከርም ለመታሰቢያ ፕሮጀክቶች እንደሚውል ተጠቁሟል።

በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የሟቹ አንዱአለም ዳኜ ባልደረቦች በነበሩት በዶ/ር ኃይለማርያም አወቀ፣ በዶ/ር አምሳሉ ወርቁ እና በዶ/ር መኳንንት ይመር በሶስት የህክምና ዶክተሮች ስም የባንክ አካውንትም ተከፍቷል።

ዶ/ር አንዱአለም ዳኜ ባለትዳር እና የሁለት ልጆች አባት ናቸው። 

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

06 Feb, 04:43


የማለዳ ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 2 9 ቀን 2017 ዓ.ም

1. ምክር ቤቱ በዛሬ ውሎው የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ሥርዓትን ለመደንገግ የተዘጋጀውን ረቂቅ አዋጅ ጨምሮ የተለያዩ ሕጎችን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባው የፌዴራል የፍትህና የሕግ ኢንስቲትዩትን እንደገና ለማቋቋም የሚቀርብ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ በመርመር አዋጁን እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል። በተመሳሳይ ምክር ቤቱ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ እንዲሁም የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ሥርዓትን ለመደንገግ የተዘጋጁ ረቂቅ አዋጆችን አስመልክቶ የሚቀረብለትን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጆቹን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

2. በሜታ ወረዳ በትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ። በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አልፏል። አደጋው ከጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የጭነት ተሽከርካሪ ከቆቦ ከተማ ወደ ድሬዳዋ ሲያመራ ከነበረ ዶልፊን ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው፡፡ በተፈጠረው አደጋም የ8 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የተናገረ ሲሆን በሶስት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን ገልጿል፡፡

3. በግ እየጠበቀች የነበረችን የ9 ዓመት ህጻን አስገድዶ የደፈረ የ60 ዓመት አዛውንት በጽኑ እስራት ተቀጣ። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ አቶ እሳቱ ዳንጎረ የተባለው የ60 ዓመት አዛውንት ጽኑ እስራት የተወሰነበት ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ገደማ የግል ተበዳይ የ9 ዓመት ህጻን በጎች እየጠበቀች ባለችበት አስገድዶ የመድፈር ወንጀል በመፈፀሙ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ አቃቤ ህግም ከፖሊስ የደረሰውን የምርመራ መዝገብ መነሻ በማድረግ ለወረዳው ፍርድ ቤት ክስ አቅርቧል። ክሱን ሲመለከት የቆየው የወረዳዉ ፍርድ ቤት አከራክሮ ጥር 27 ቀን2017 ዓ.ም በዋለው 1ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሽ እሳቱ ዳንጎሮ በ16 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን የወረዳው ፖሊስ ጽፈት ቤት አስታውቋል፡፡

4. ለህብረተሰቡ የደህንነት ስጋት የሆኑ ችግሮችን ለማስወገድ የሚከናወነው ተግባር አጠናክሬ እቀጥላለሁ ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። በመዲናዋ በተለያዩ አካባቢዎች ሕጋዊ የንግድ ሽፋንን ለሕገ-ወጥ ተግባር በማዋል ሺሻ የማስጨስ እና ጫት የማስቃም አዋኪ ድርጊት ሲፈፀምባቸው የተገኙ የተለያዩ ሆቴሎች፣ ቪላ ቤቶች፣ የሌሊት ጭፈራ ቤቶች እና ሌሎች የንግድ ተቋማት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው እያደረኩ ነው ብሏል። ሕገ-ወጥ ተግባሩን ሲፈፅሙ እና ሲያስፈፅሙ የተገኙ ግለሰቦችም በሕግ አግባብ ተጠያቂ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው።

5. የአሜሪካው የስለላ ተቋም (ሲአይኤ) ሠራተኞቹ ሥራ እንዲለቁ እየጠየቀ ነው። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፌዴራል ሠራተኞችን ቁጥር ለመቀነስ የያዙትን ዕቅድ ለማስፈፀም ሲአይኤን ቀዳሚ አድርገዋል። ሠራተኞቹ በገዛ ፈቃዳቸው ሥራቸውን የሚለቁ ከሆነ የ8 ወር ደመወዝ እና ጥቅማጥቅማቸውን እንደሚያገኙ ተነግሯቸዋል። የተቋሙን ሠራተኞች ይመለከታል የተባለው የፌደራል ሠራተኞች ቅነሳ ዕቅድ የተቋሙን አንዳንድ የሥራ ክፍሎች እና ሞያዎች ግን አይመለከትም ተብሏል። ይህ ቅነሳ የትራምፕ የፌደራል መንግሥት ሰራተኞችን የመቀነስ አጀነዳ ጥረት መሆኑም ተነግሯል። ብዙ ተቋማት ጉዳዩን በአዎንታ ባያዩትም አዲሱ የሲአይኤ ዋና ዳይሬክተር ግን የትራምፕን ዕቅድ ለማስፈፀም የመጀመሪያው ሆነዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #morningnews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

05 Feb, 15:00


የዕለቱ አበይት ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም

1. በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ማንኛውንም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር አይቻልም። በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ማንኛውንም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር  እንደማይቻል የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል። አገልግሎቱ በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ የሚደረግ የድሮን እና ሌሎች በራሪ አካላት አጠቃቀምን በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል። በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋሉ የመጡ ድሮኖች እና መሰል ቴክኖሎጂ ወለድ መሣሪያዎች የሚፈጥሯቸውን ስጋቶች ለመከላከል የሚያስችል በቂ የቴክኖሎጂ እና የሰው ኃይል ዝግጅት ማድረጉን ተናግሯል። በተለይ ከመጪው የአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ጋር ተያይዞ ቅንጅቱን ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ማንኛውም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መሥሪያ ቤት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር እንደማይቻል አመላክቷል። በሥራ ምክንያት ድሮኖች መጠቀም አስፈላጊ ከሆነ ጠያቂው አካል የበረራውን ዓላማ፣ የሚበርበትን ቦታ፣ የድሮኑን አይነት እና የሞዴል ቁጥር በመጥቀስ አስቀድሞ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱን መጠየቅ እና ፈቃድ ማግኘት እንደሚገባ መግለጫው አስታውቋል፡፡

2. በኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በተከሰተው የመሬት መንቀጥጥ በአፋር፣ አማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች 90,000 ሰዎች ላይ ተጽዕኖ ማድረሱን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ። በድርጅቱ ሪፖርት መሠረት ምንም አይነት የሞት አደጋ ባይመዘገብም ሁለት ሰዎች ላይ ግን ጉዳት ደርሷል። ከ75,000 በላይ ሰዎችን ለከፍተኛ አደጋ ተጋላጭ ከሆኑ አካባቢዎች የወጡ ሲሆን 55,000 ሰዎች በአፋር እና 20,000 ሰዎች ደግሞ በኦሮሚያ እንዲሰፍሩ መደረጋቸውን ሪፖርቱ ገልጿል። በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ ዘጠኝ የጤና ተቋማት ላይ ውድመት ያደረሰ  ሲሆን የሰብአዊ እርዳታ ጥረቶችም በመከናወን ላይ ናቸው።

3. በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ለትግራይ ክልል ከ74 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ ነው ተብሏል። በተያዘው በጀት ዓመት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ለትግራይ ክልል ከ74 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑ ተነግሯል። የሰቆጣ ቃልኪዳን ስምምነት እ.አ.አ በ2030 በኢትዮጵያ የህፃናት መቀንጨርን ሙሉ ለሙሉ ለማስቀረት አልሞ በ2007 ዓ.ም ወደ ትግበራ የገባ መሆኑ ይታወቃል። ፕሮግራሙ በተከዜ ተፋሰስ አካባቢ የህፃናት መቀንጨርን በዘላቂነት መፍታት የሚያስችል ሲሆን እናቶችና ህፃናት የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ፤ ሴቶች በጓሮ አትክልትና በእንስሳት ተዋፅዖ ልማት ራሳቸውን በምግብ እንዲደግፉ የሚያግዝም ነው።

4. ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ዘርፉ በተለይ ወጣቶቿ ላይ ብትሰራ በብዙ ታተርፍበታለች ተባለ፡፡ በሀገሪቱ በሚገኙ የአቪዬሽን ማሰልጠኛ ማዕከላት የሌሎች አገር ዜጎች ስልጠና በመውሰድ እየተጠቀሙበት እንደሆነ ተነግሯል፡፡ኢትዮጵያ በዘርፉ በተለያዩ ማሰልጠኛዎች ያሉ ወጣቶችን በአግባቡ ብትጠቀምበት በሰው ኃይል ብዛት ባለሙያዎችን ለተለያዩ ሀገራት በማቅረብ የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኝላት እንደሆነ የዘርፉ ባለሙያ ይናገራሉ፡፡ በዚህ ረገድ ግን ዘርፉን በአግባቡ እየተጠቀሙበት ካሉ ሀገራት አንጻር ኢትዮጵያ አልሰራችበትም ተብሏል። ኢንዱስትሪው በኢትዮጵያ ያልተሰራበት በመሆኑም ሀገሪቱ ላይ የተለያዩ አለማቀፍ ተቋማት ገብተው እንዲሰሩ ለማድረግ በግልና የመንግስት አጋርነት ወይም ፐብሊክ (private partnership) ላይ  በደንብ ቢሰራ ለስራ እድል ፈጠራውም ይሁን ኢንዱስትሪ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያደርግ ነው ተብሏል።

5. በግሪክ ተከታታይ ርዕደ መሬት በመከሰቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከሳንዶሪኒ ደሴት ለቀው ወጡ፡በደሴቱ ለአራት ተከታታይ ቀናት የመሬት መንቀጥቀጥ በመመዝገቡ ነው ዜጎች ለቀው እንዲወጡ የታዘዙት፡፡
ሳንዶሪኒን አስራ አንድ ሺሕ ሰዎች ለቀው የወጡ ሲሆን ሰባት ሺሕ የሚሆኑት በመርከብ አራት ሺህ የሚሆኑት ደግሞ በአውሮፕላን ተጓጉዘዋል፡፡ ደሴቷን በመቶዎች የሚቆጠር ርዕደ መሬት የመታት ሲሆን ከባዱ ተብሎ የተመዘገበው ማክሰኞ የተከሰተው ሆኗል የደሴቷ ባለስልጣናት ቅድመ ጥንቃቄ ማድረጋቸውም ተነግሯል ፡፡
እስከሁን በመሬት መንቀጥቀጡ አደጋ የደረሰ ጉዳት እንደሌለም ዘገባዎች ይጠቁማሉ፡፡ ያም ሆኖ ግን ትምህርት ቤቶችን ተዘግተዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #Dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

05 Feb, 12:35


በቦሌ ኤርፖርት የታየው ጭስ ምክንያቱ ምንድን ነው?

አየር መንገዱ የሀገር ውስጥ ተርሚናል አገልግሎቱ ለጊዜው መቋረጡን ገለፀ!!
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሀገር ውስጥ ተርሚናል አገልግሎቱ ለጊዜው መቋረጡን አስታውቋል፡፡

በዚህም የሀገር ውስጥ መንገደኞች በዓለም አቀፍ መንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል በኩል እንዲስተናገዱ አየር መንገዱ አሳስቧል፡፡

አየር መንገዱ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ፤ ዛሬ ከቀኑ 6:30 በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሀገር ውስጥ መንገደኞች ማስተናገጃ ሕንፃ ውስጥ ወደ በረራ ይዞ መግባት ከሚከለከሉ ቁሳቁሶች መካከል ከመንገደኞች የሚሰበሰብ የሲጋራ መለኮሻ (ላይተር) ጊዜያዊ የማስቀመጫ ስፍራ ውስጥ ጭስ በመከሰቱ ለመንገደኞች ደህንነት ሲባል ሕንፃው ለጊዜው አገልግሎት አቋርጧል ብሏል፡፡

#ethiopia #Ethiopianairlines #Flights

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

05 Feb, 09:30


የአራት ኪሎ ፕላዛ የምድር ውስጥ መተላለፊያ እና የመዝናኛ ስፍራ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

በአዲስ አበባ በኮሪደር ልማት የተገነቡ መሰረተ ልማቶችና የመዝናኛ ስፍራዎች መካከል አንዱ የሆነው የአራት ኪሎ ፕላዛ የምድር ውስጥ መተላለፊያ እና መዝናኛ ስፍራ ግንባታው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቅቆ ዛሬ ወደ አገልግሎት ገብቷል።

አካባቢው ከዚህ ቀደም ለተሽከርካሪ፣ ለእግረኞችና ለአካል ጉዳተኞች መተላለፊያነት አስቸጋሪ እንደነበር የተነገረ ሲሆን አሁን አካል ጉዳተኞችም በቀላሉ መተላለፍ የሚችሉበት የአሳንስር መጓጓዣ መኖሩ ተነግሯል።

በውስጡ የሀገር ውስጥ አልባሳት፣ መዋቢያዎች፣ ወርቅና ብር መሸጫ ቤቶች፣ የስልክ መሸጫዎች፣ የፈጣን ምግብ አገልግሎት እና መሰል የንግድ አገልግሎቶች አሉ ተብሏል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

05 Feb, 08:18


ኢትዮጵያ አራት አዲስ የፍጥነት መንገዶችን ልትገነባ ነው ተባለ
አማራ ክልልን ከአዲስ አበባ ጋር የሚያገናኙ ሁለት የፍጥነት መንገዶች የግንባታ ጥናት እየተደረገ ነው ተብሏል።
ከአዲስ    አበባ   በተለያዩ   መስመሮች   የሚወጡ   4   አዳዲስ   የፍጥነት   መንገዶችን  ለመገንባት  የሚያስችል  ጥናት እየተደረገ  ይገኛል፡፡
ጥናቱ   እየተደረገ   የሚገኘው    ከአዲስ  አበባ ደሴ፣ ከአዲስ  አበባ  ደብረማርቆስ ፣ከአዲስ  አበባ  ጅማ እና  ከአዲስ አበባ  ነቀምት  በሚዘልቁት   መንገዶች  ላይ  ነው ሲል አሚኮ ዘግቧል፡፡
እነዚህ    የፍጥነት  መንገዶች   የሚገነቡበት   የጥራት  ደረጃ ፣ የሚኖራቸውም   አጠቃላይ የጎን  ስፋት  ከፍ  ያለ  እና  የሚገነቡበት  መልክአ  ምድር  አብዛኛውን   ተራራማ  ቦታዎችን  የሚሸፍን  በመሆኑ  ከፍተኛ  የሆነ   ወጪ እና   የቆረጣ   ሥራዎችን  የሚጠይቁ  ናቸው፡፡
በጥናቱ   መሰረት   ፕሮጀክቶቹ   የሚኖራቸው   ርዝመት   በአማካይ   300  ኪሜ   ሲሆን   ግንባታቸውም   በተለያዩ  ምዕራፎች  እና  በተወሰነ   ኪሎሜትር ተከፋፍሎ የሚጀመር ይሆናል፡፡
በአሁኑ  ወቅት  የፕሮጀክቶቹ  የአዋጭነት፥ እንዲሁም  መሰረታዊ  የዲዛይንና  የዝግጅት ሥራ እየተከናወነ ሲሆን ለዝግጅት  ሥራው  የሚያስፈልጉ   የጥናት  ሥራዎችንም  ለማጠናቀቅ  እየተሠራ ነው።
አራቱን  የፍጥነት  መንገዶች  ለመገንባት የሚያስፈልገው   ወጪ  የሚሸፈነው  በመንግስትና   የግል አጋርነት  ትብብር   ነው፡፡
ከፍጥነት  መንገዶቹ  መካከል  የአዲስ  ጅማ እና አዲስ ደብረ ማርቆስ ፕሮጀክቶች ለገንዘብ ሚኒስቴር የመንግሥት የግል  አጋርነት  ቦርድ  የቀረቡ  ሲሆን  ቀሪዎቹም  በቅርቡ  ይቀርባሉ  ተብለው ይጠበቃል ።
የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር መረጃ እንደሚያመለክተው ፕሮጀክቶቹም በገንዘብ  ሚኒስቴር  የመንግሥት  የግል  አጋርነት  ትብብር  ቦርድ   ከጸደቁ  በኋላ  ወደ ቀጣይ ሥራ ይገባሉ።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

05 Feb, 06:21


የማለዳ ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም


1. ከዩ.ኤስ.ኤይድ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሃብትና ገንዘብን ለሶስተኛ ወገን እንዳያስተላልፉ ታገዱ። በአሁኑ ወቅት ከዩ.ኤስ.ኤይድ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ ድርጅቶች በማናቸውም መልኩ ሃብትና ገንዘብን ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ የተከለከለ መሆኑንና ይህን በሚተላለፉ ተቋማት ላይ እርምጃ እወዳለሁ ይወሰዳል ተብሏል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለሁሉም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንደተገለፀዉ ያለ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ግልፅ ፍቃድ ንብረት የማስተላለፍ፣ የማስወገድ፣ የመሸጥ ወይም ከመደበኛ/ፕሮጀክት ስራዎች ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ብቻ እንዲንቀሳቀሱ ጠይቋል። ይሁን እንጂ በማናቸውም መልኩ ሃብትና ገንዘብን ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ የተከለከለ መሆኑን የገለፀው ባለስልጣኑ ይህንን ማሳሰቢያ በመተላለፍ በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ ጠቁሟል። ከሰሞኑ በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (ዩ.ኤስ.ኤይድ) በኩል የእርዳታ ማቆም ውሳኔ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ መሆኑንና ዝርዝር ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ በቀጣይ አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል የሚከውን መሆኑን ተቆጣጣሪ አካሉ አስታውቋል።

2. ባለፉት ስድስት ወራት ከደረሱት የተሸከርካሪ ግጭቶች 40 አደጋዎች በቀለበት መንገድ ላይ የተከሰቱ ናቸው ተባለ። በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት በአጠቃላይ 150 የተሽከርካሪ ግጭት አደጋዎች የደረሱ ሲሆን፤ ከእነዚህም ውስጥ 40 አደጋዎች በቀለበት መንገድ ላይ የተከሰተ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ተናግሯል፡፡ ቀሪዎቹ 110 የግጭት አደጋዎች ደግሞ ከቀለበት መንገድ ውጪ የደረሱ ናቸው።
በመንፈቅ ጊዜ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በተሽከርካሪዎች ግጭት ሳቢያ ከ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ባለው የመንገድ መሰረተ-ልማት ላይ ጉዳት መድረሱን ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡

3. በኢትዮጵያ 28 ሺህ ሰዎች ለውሻ ዕብደት በሽታ መጋለጣቸው ተገልጿል። ከነዚህ ውስጥም93 በመቶዎቹ ከሞት ድነዋል ተብሏል። በተያዘው በጀት ዓመት በስድስት ወራት ውስጥ 28 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች በውሻ ዕብደት በሽታ (ራቢስ) መያዛቸውን የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል። በበሽታው ከተያዙት 93 በመቶ የሚሆኑት በተደረገላቸው ሕክምና ከሞት ተርፈዋል ብሏል ኢንስቲትዩቱ። የውሻ ዕብደት በሽታ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ በርካታ ሰዎች ለበሽታው ተጋላጭ ሆነዋል፣ በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ ወደ 28 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች በውሻ ተነክሰው የሕክምና ርዳታ ለማግኘት ወደ ጤና ተቋማት መጥተዋል ተብሏል። ከነዚህ ውስጥ 93 በመቶ የሚሆኑት የሕክምና ርዳታ በማግኘታቸው ከሞት መትረፋቸውን ተጠቅሷል፡፡

4. 1 ነጥብ 1 ሚሊየን ኩንታል ዳፕና ዩሪያ የጫኑ መርከቦች ወደብ ደረሱ። ለ2017/18 የምርት ዘመን 1 ሚሊየን 100 ሺህ ኩንታል ዳፕ እና ዩሪያ የጫኑ መርከቦች ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸውን የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ተናግሯል፡፡ ይህንን ተከትሎ እስከ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ከውጭ የተጓጓዘው የአፈር ማዳበሪያ መጠን ወደ 5 ሚሊየን 392 ሺህ 600 ኩንታል ከፍ ማለቱ ተጠቁሟል፡፡ ከዚህ ውስጥ 3 ሚሊየን 717 ሺህ 212 ኩንታል ወደ ሀገር ውስጥ ተጓጉዞ በኅብረት ሥራ ማኅበራት አማካይነት ለአርሶ አደሮች በመከፋፈል ላይ ይገኛል።

5. በምስራቃዊ ኮንጎ ጎማ ከተማ የሟቾች ቁጥር 900 መድረሱን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ። በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምሥራቃዊ ጎማ ከተማ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ከ900 በላይ ሰዎች መሞታቸውን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። የተባበሩት መንግስታት የጤና ኤጀንሲ በሰጠው መግለጫ በጎማ ከተማ ከጥር 18 ጀምሮ 2 ሺህ 880 የተጎዱ ሰዎች ወደ ተለያዩ የጤና ተቋማት መግባታቸውን ገልጿል። በአካባቢው ባለው ጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉ ሰዎች የህክምና አገልግሎት ለማግኘት በተቸገሩበት በዚህ ወቅት የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወረርሽኝ ፣የኮሌራ እና የኩፍኝ በሽታዎች ሊስፋፉ እንደሚችሉ እና በወረርሽኝ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ሊጨመር ይችላል ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስጠንቅቋል።

#ethiopia #morningnews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

04 Feb, 16:31


የዕለቱ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም

1. የቤትና ቦታ ግብር ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ግብር ከፋዮች ከወዲሁ ክፈሉ ሲል አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አሳሰበ፡፡ በአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ሚያዚያ 3 ቀን 2015 በጻፈው ድብደቤ የጣራና ግድግዳ እየተባለ የሚጠራውን የቤትና ቦታ ግብር ሁሉም ክፍለ ከተሞች እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ማስተላለፉ ይታወሳል፡፡ እናት ፓርቲ ይህንን የፋይናንስ ቢሮን ውሳኔ ሕግን ያልተከተለ፣ የከተማ አስተዳደሩም ባልተሰጠው ስልጣን ነው ስራ ላይ ያዋለው በሚል ውሳኔው እንዲሻር በፍርድ ክርክር ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ_ቤት ልደታ ምድብ የፌዴራል አስተዳደር ሥነ ሥረዓት ፍትሐብሔር ችሎት የከተማ አስተዳደሩ ያወጣው የጣሪያ እና ግድግዳ ግብር መመሪያን ባልተሰጠ ስልጣን የወጣ ነው፤ ህጋዊም አይደልም በሚል መመሪያውን እንደሻረው ፓርቲው በትናንትናው እለት በሰጠው መግለጫ መናገሩ ይታወቃል፡፡ ምንም እንኳ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ቢሽረውም በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የጣራና ግድግዳ እየተባለ የሚጠራ የቤትና ቦታ ግብር የሚከፍሉ ግብር ከፋዮች ግብሩ ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ መሆኑን ተገንዝባችሁ ከወዲሁ ግብራችሁን ክፈሉ ሲል ጠይቋል፡፡

2. በድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠና በሎጂስቲክ እና ንግድ ዘርፍ ለመሰማራት ፍቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች ምርቶቻቸውን ከጅቡቲ ወደ ነጻ የንግድ ቀጠናው ማስገባት ጀምረዋል ተባለ። በዘርፉ ለመሰማራት ፍቃድ ከወሰዱ የአገር ዉስጥና የዉጭ ባለሀብቶች መካከል ሞሃን ትሬዲንግ የተሰኘ ኩባንያ ከጅቡቲ ወደብ ወደ ድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጠና ምርቶችን ማስገባት ጀምሯል ተብሏል፡፡ በነጻ የንግድ ቀጠናው በሎጅስቲክስ ዘርፉ ላይ ለመሰማራት የመሬት ርክክብ ካደረጉ 7 ድርጅቶች መካከል አንዱ ሞሀን ትሬዲንግ ነው።

3. ኢትዮጵያ በግብርና፣ በጤናው፣ በትምህርት ያለባትን ችግር ለመቅረፍ የተለያዩ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች በማሳተፍ እየሰራሁ ነው ሲል የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ትረስት ፈንድ ተናገረ፡፡ ዲያስፖራው በኢትዮጵያ የሚገኙ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች የገንዘብ ችግር ሳይገጥማቸው የማህበረሰቡን ችግር መቅረፍ የሚችሉ ስራዎችን እንዲሰሩ አግዛለሁኝ ብሏል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ትረስት ፈንድ በትምህርት በጤናና በግብርና የሀገሪቱን ችግር ያቃልላሉ ተብለው የተከወኑ ስራዎችን አወዳድሮ የሽልማት መረሃግብርም አከናውኗል፡፡

4. የዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ። እንደ እ.ኤ.አ ከ2025 እስከ 2032 የሚተገበር የዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታ ይፋ ተደርጓል። ፍኖተ ካርታው የዲጂታል አገልግሎት ግንዛቤ ያለው አርሶ አደር እና አርብቶ አደር እንዲኖር ያስችላል የተባለ ሲሆን ግብርናውን በቴክኖሎጂ ማዘመን የሚቻልበትን ማዕቀፍ የያዘ ነውም ተብሎለታል። በሁለት ምዕራፍ ለሚተገበረው ፍኖተ ካርታ የግሉ ዘርፍ፣ የአርሶ አደሩ እና የአርብቶ አደሩ ትብብር ያስፈልጋል ተብሏል።

5. የኬንያ መንግስት በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ 'ልዩ የፀጥታ ዘመቻ' መጀመሩን አስታወቀ። የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት በማርሳቢት እና ኢሲዮሎ ግዛቶች በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ 'ልዩ የፀጥታ ዘመቻ' መጀመሩን ተናግሯል። አገልግሎቱ ትናንት ባወጣው መግለጫ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የሚጠቀምባቸውን መሸሸጊያዎች ለቆ እንዲወጣ ለማድረግ “ኦንዶአ ጃንጊሊ ኦፖሬሽን” የተባለ ዘመቻ ከትናንት ጥር 26 ቀን ጀምሮ እንደሚያካሄድ ገልጿል። በከፍተኛ ደረጃ የሚካሄደው ዘመቻ ለኬንያ ብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ስጋት የሚጥሉ እንደ የጦር መሳሪያ፣ የአደንዛዥ ዕፅ እና የሰዎች ዝውውር፣ ህገወጥ የማዕድን ማውጣት ያሉ ህገወጥ ስራዎችን የሚያከናውኑ ወንጀለኞችን ዒላማ ያደረገ ነው ተብሏል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

04 Feb, 09:13


በአፈር መደርመስ አደጋ የ8 ሰዋች ሕይወት አለፈ።

በጉጂ ዞን ሳባ ቦሩ ወረዳ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ 8 ሰዎች በአፈር መደርመስ አደጋ ሕይወታቸው አከፈ ተነገረ፡፡

አደጋው ትናንት 9 ሰዓት በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት ሥራ በተሰማሩ ዜጎች ላይ መድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ተናግሯል።

በአደጋው ለሕልፈት የተዳረጉ ሰዎችን አስከሬን ከተደረመሰው አፈር ውስጥ የማውጣት ሥራ ተከናውኗል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

28 Jan, 14:39


የዕለቱ አበይት ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 20 ቀን 2017 ዓ. ም

1. በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ተቀማጭ ገንዘብ 2.74 ትሪሊዮን ብር መድረሱን የብሔራዊ ባንክ ተናገረ። የሀገሪቱ ባንኮች ከዓመት ዓመት በተቀማጭ ገንዘብ፣ አጠቃላይ ባላቸው የፋይናንስ እሴት ለውጥ እያመጡ መሆኑም ተገልጿል። በተጨማሪም በቅርቡ የውጭ ባንኮች ሀገር ቤት ገብተው እንዲሠሩ የጸደቀው አዋጅ በዋናነት የውጭ ባለሀብቶች በባንክ መስክ ተሰማርተው ለኢኮኖሚው አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ በማሰብ ነው ተብሏል። የባንክ ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት መሆኑ የሀገር ውስጥ ባንኮች አዳዲስ አሠራርና አገልግሎት አግኝተው ለኢኮኖሚ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ከፍ እንዲል ነው ተብሏል።

2. በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ 6 ወራት 1 ሚሊየን 719 ሺህ 973 ሜትሪክ ቶን የገቢ ምርቶች ላይ የጥራት ቁጥጥር ሥራ መከወኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተናገረ። በ1 ሚሊየን 888 ሺህ 926 ሜትሪክ ቶን የገቢ ምርቶች ላይ የኢንስፔክሸን ሥራ ለማከናወን መታቀዱን የገለጸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፤ የዕቅዱን 91.05 በመቶ ማሳካቱን አስታውቋል፡፡ በምርቶቹ በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት እንዲፈተሹ በማድረግ የኢትዮጵያን ደረጃ ያሟሉ ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ፍቃድ መሰጠቱም ታውቋል። በዚህም የጥራት ቁጥጥር ከተደረገባቸው አስገዳጅ ደረጃ የወጣላቸው ገቢ ምርቶች መካከል 932.89 ሜትሪክ ቶን ምርቶች ከደረጃ በታች መሆናቸው በመረጋገጡ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ታግደዋል ተብሏል።

3. በአማራ ክልል ካሉ ትምህርት ቤቶች ከ86.6 በመቶ በላዩ ደረጃቸውን ያላሟሉ ናቸው ተባለ። በግብዓት፣ሞሙ በሂደትና በዉጤት ረገድ ሲመዘኑ፤ ደረጃቸውን ያሟሉት ደግሞ 13 ነጥብ 4 እንደማይበልጡ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ተናግሯል። በዚህ ዓመት ይመዘገባሉ ተብሎ በዕቅድ ከተያዘው 7 ሚሊዮን ተማሪዎች ውስጥ በትምህርት ላይ ያሉት 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውም ተነግሯል። ተማሪዎች ውስጥ 400 ሺህ ያህሉ ወደ ትምህርት ተቋማት አለመሄዳቸው ተገልጿል።

4. ባለፉት አምስት ዓመታት ከሀገር ወጥተው የነበሩ ከ70 በላይ ቅርሶች ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ተናገረ። በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ተንቀሳቃሽ ታሪካዊ ቅርሶቿ በተለያዩ ዘመናት ከሀገር እየተዘረፉ ወጥተው በተለያዩ አገራት፣ ተቋማትና ግለሰቦች ዕጅ ይገኛሉ ተብሏል። ቅርሶች ከማንነትና ታሪካዊ መገለጫነታቸው ባሻገር ለቱሪዝም ኢኮኖሚው ሁለንተናዊ ፋይድ ያላቸው ናቸው።

5. ደቡብ ሱዳን በፌስቡክ እና በቲክ ቶክ ላይ ጥላ የነበረችውን እገዳ አነሳች። በደቡብ ሱዳን የሚኖሩ የሱዳን ዜጎች ላይ ተፈጽመዋል የተባሉትን ግድያዎች የሚያሳዩ ቪዲዮዎች መሰራጨታቸውን ተከትሎ ባለፈው ሳምንት በፌስቡክ እና በቲክ ቶክ ላይ ተጥሎ የነበረውን ጊዜያዊ እገዳ ማንሳቷን አስታውቃለች። የሱዳን ጦር በቪዲዮ የተቀረጸውን እና በማህበራዊ ድረ-ገጾች በሰፊው የተሰራጨውን ተንቀሳቃሽ ምስሎች "ግለሰቦች የሰሩት ጥሰት" ነው ሲል አውግዟል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#Ethiopia #dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

28 Jan, 07:14


በአባሎቻችን ላይ የሚደርሰው እስር ወከባና ግፍ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ተናገረ።

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣው በአባሎቻችን ላይ የሚደርሰው እስር ወከባና ግፍ የሰላማዊ ፖለቲካ ትግል ላይ አደጋ መደቀን እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኛ አለመሆን ነው የሚለው ፓርቲው አባሎቻችን እየደረሰባቸው ካለው ግፍ ወከባና እስር ነፃ እንዲሆኑ በአፅንኦት እንጠይቃለን ብሏል ባወጣው መግለጫ።

በዚህም ወደ 75 የሚጠጉ አባላቶቹ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች እንደታሰሩበት የተናገረው ኢዜማ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የታሰሩ አባላቶቹ በአፋጣኝ እንዲፈቱለት ጠይቋል።

በአባላቶቼ ላይ የሚፈፀመው ውክቢያ ሊቆም ይገባል ሲል ተናግሯል፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣው በአባሎቻችን ላይ የሚደርሰው እስር ወከባና ግፍ የሰላማዊ ፖለቲካ ትግል ላይ አደጋ መደቀን እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ቁርጠኛ አለመሆን ነው የሚለው ፓርቲው አባሎቻችን እየደረሰባቸው ካለው ግፍ ወከባና እስር ነፃ እንዲሆኑ በአፅንኦት እንጠይቃለን ብሏል ባወጣው መግለጫ።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

28 Jan, 06:39


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

1. ባለፉት ስድስት ወራት በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ በተፈፀመ በስርቆት ከ126 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሶበታል ተባለ። በኃይል ማስተላለፊያ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎች የተቋሙ ብቻ ሳይሆን የብሔራዊ ደህንነት ስጋት ሆነዋል ተብሏል። በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች 16 የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶዎች በስርቆት ምክንያት መውደቃቸውን እና በስርቆቱ ከ92 ነጥብ 32 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው 43 ሺ 671 ብረቶች መሰረቃቸውንም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ተገልጿል።

2. ኢትዮጵያ ከጣሊያን መንግሥት የ585 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማግኘቷ ተነገረ። የድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ እና የጣልያን የከፍተኛ ትምህርት እና ምርምር ሚኒስትር አና ማሪያ ፈርመውታል። ድጋፉ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ግቦችን ከማሳካት ባለፈ የሁለቱን ሀገራት ትብብር የሚያሳድግ መሆኑ ተነግሮለታል።

3. ኢትዮጵያ 10 ቢሊየን ዶላር በመክፈሏ ዕዳዋ ከ14 በመቶ በታች ሆኗል ተባለ። ከሀገራዊ ጥቅል ምርት ያለው ድርሻ ወደ 13 ነጥብ 7 በመቶ ዝቅ ብሏል ማለቱም ተነግሯል። የውጭ የዕዳ ጫና ከሀገራዊ ጥቅል ምርት ከ5 አመት በፊት የነበረው የ30 በመቶ እንደነበር ተጠቅሷል።

4. የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በኢትዮጵያ የመጀመያ የሰብዓዊነት ትምህርት ቤት ከፈተ። የሰብዓዊነት ትምህርት ቤቱ በሰብዓዊ እርዳታ ዘርፍ የሠለጠነ የሰው ሀብት ለማፍራት የሚያግዝ እንደሆነ ተነግሮለታል። የሰብዓዊነት ትምህርት ቤቱ ሰብዓዊነትን የተላበሰ ትውልድ ለማፍራት እና በተለያዩ ምክንያቶች ለሚከሰቱ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠትም ይረዳል ተብሏል።በዚህም የትምህርት ካሪኩለሙ ተዘጋጅቶ ማለቁን እና ከዛሬ ጀምሮ ምዝገባ የሚካሔድ መኾኑን እወቁልኝ ብሏል። ዘጠኝ አይነት ኮርሶች እንዳሉት ጠቅሰው ትምህርቱን በአካል እና በበይነ መረብ መከታተል ይቻላል ተብሏል።

5. የምሥራቅ አፍሪካ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርት በ2024 በ5 ነጥብ 1 በመቶ፤ በ2025 ደግሞ በ5 ነጥብ 7 በመቶ እንደሚያድግ የአፍሪካ ልማት ባንክ ትንበያ አሳዬ። እንደ እ.ኤ.አ በ2025 ኢትዮጵያ፣ ታንዛኒያ፣ ኡጋንዳ እና ሩዋንዳ ከ6 በመቶ በላይ ዕድገት በማስመዝገብ የቀጣናውን ሀገራት እንደሚመሩ ነው የተጠቀሰው። ይህ ዕድገት በዋናነት የቀጣናው መንግሥታት በመሠረተ ልማት ዝርጋታ ላይ በሚያፈሱት መዋዕለ ንዋይ፣ በሚተገብሯቸው ማሻሻያዎች እና በአገልግሎት ዘርፉ የተሻለ ምርታማነት የሚታገዝ እንደሆነ ተገልጿል።

#Ethiopia #morningnews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

27 Jan, 14:49


የዕለቱ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ሰኞ ጥር 19 ቀን 2017 ዓ. ም

1. በአማራ ክልል በጦርነት ምክንያት የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ ለመገንባት 100 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ተብሏል።የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አንዳስታወቀው ከሰሜኑ ጦርነት ጀምሮ አሁን በክልሉ ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት በርካታ ትምህርት ቤቶች ተጎድተዋል።ለአብነትም በምሥራቅ ጎጃም ዞን ከ400 በላይ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ቢሮው ጠቅሷል።በአጠቃላይ በክልሉ ጉዳት የደረሰባቸውን ትምህርት ቤቶች ወደ አገልግሎት ለመመለስ 112 ቢሊየን ብር ያስፈልጋልም ተብሏል።ቢሮው ባስጠናው ጥናት መሠረት ይህ ገንዘብ ትምህርት ቤቶችን ከመገንባትና መጠገን በተጨማሪ ተጓዳኝ የትምህርት ሥራዎችን ለማከናወን የሚውል ነው፡፡

2. ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ ጋር የተዋዋለችው የ700 ሚሊዮን ዶላር ብድር ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል። ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው ልዩ ስብሰባ የፋይናንስ ዘርፉን ለማጠናከርና የመንግስት አገልግሎትን ለማሻሻል የሚውሉ የብድር ስምምነቶችን አፅድቋል። የብድር ስምምነቶቹን አስመልክቶ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የልማት ማህበር ጋር ያደረገችው የ700 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት የፋይናንስ ዘርፉን ጤናማነትና ተወዳዳሪነት የበለጠ ለማሻሻል ያስችላል የተባለ ሲሆን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የካፒታል አቅምን እንደሚያሳድግ ተነግሯል፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት አራት ዓመታት የዕዳ ጫናዋ እየቀነሰ መጥቷል ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያና ዓለም አቀፉ የልማት ማህበር ለዘመናዊ የመንግስት አገልግሎት ማሻሻያ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል የ700 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነትም ለምክር ቤተ ቀርቧል። ምክር ቤቱ በብድር ስምምነቶቹ ላይ ከተወያየ በኃላ ስምምነቶቹን በ3 ድምፀ ተአቅቦ አና በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል።

3. ትላልቆቹ የግብርና ምርምር እና የእንስሳት ብዜት ማዕከላት የመሬት ይዞታቸውን በከተማ አስተዳደሮች እና በክልሎች እየተወሰደባቸው ነው ተባለ፡፡ የመሬት ይዞታቸው ተወስዶባቸዋል ከተባሉት ትላልቅ ማዕከላት መካከል የሆለታ፣ የጅማ፣ የቁልምሳ እና የቢሾፍቱ የግብርና እና የእንስሳት እርባታ ማዕከላት እንደሚገኙበት ተነግሯል፡፡ ይህ የተነገረው የግብርና ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የ6 ወር ዕቅድ አፈጻፀም ሪፖርት ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡ ማዕከላቱ የመሬት ይዞታቸው ባለመረጋገጡም ለግበርናው ዘርፍ ማበርከት የሚገባቸውን ከፍተኛ ሚና ያደናቅፋል ተብሏል።

4. ረጅም አመት ያገለገሉ የኤልክትሪክ መሰረተ ልማቶችን የመልሶ ግንባታ መከወን፣ የሀይል አቅርቦትን ለማሳደግ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን መገንባት እና ሌሎች ስራዎችን የያዘው ፕሮጀክት መጠናቀቂያው ላይ እየደረሰ ነው ተባለ፡፡ በአዲስ አበባ እና በዙሪያ ባሉ ከተሞች የሚሰሩት የማሻሻያ ስራዎችም ሲጠናቀቁ ከዚህ ቀደም የነበረው የሀይል መቆራረጥ ይቀንሳል ተብሎ ተስፋ እንደተጣለበት የኢትዩጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናግሯል፡፡ ለሀይል መቆራረጥ እንደምክንያት የሚነሱ ችግሮችን በመለየት ማሻሻያዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የተናገረው ተቋሙ ከሁለት እና ከሶስት አመት በፊት የተጀመሩት አራት አይነት ፕሮጀክቶችም የዚሁ አካል ናቸው ተብሏል፡፡ በተቋሙ እየተከወኑ ያሉት እነዚህ ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ወደ ትግበራ ሲገቡ ከዚህ ቀደም የነበረውን የሀይል መቆራረጥ ከግማሽ በላይ ይቀንሰዋል ተብሎ ተስፋ እንደተጣለበትም ተነግሯል።

5. እስራኤል እና ሃማስ የደረሱትን ስምምነት ተከትሎ በሺህዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን ወደ ሰሜን ጋዛ ማቅናት ጀምረዋል ተባለ፡፡ እስራኤል እና ሃማስ የደረሱት ታጋቾችን የመለዋወጥ ስምምነት ተከትሎ ነው ፍልስጤማውያኑ ተፈናቃዮች እስራኤል ተቆጣጥራው በነበረው ኔትዛሪም ኮሪደር በኩል ወደ ሰሜን ጋዛ እየሄዱ ያሉት፡፡ ፍልስጤማውያኑ በእግር እና በተሽከርካሪ ወደ ሰሜን ጋዛ እንዲገቡ መፍቀዷን የገለጸችው እስራኤል እስከ አሁን ድረስ ግማሽ ሚሊየን የሚጠጉ ዜጎች ወደ ከተማቸው እየገቡ ነው።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

27 Jan, 12:45


የፊጋ አካባቢ መንገድ ከነገ ጀምሮ ላልተወሰነ ቀናት ይዘጋል ተባለ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2ኛው ዙር ከሚለሙት የኮሪደር መስመሮች መካከል  የሲሚት- ጎሮ መንገድ አንደኛው መሆኑ ይታወቃል፡፡

ከዚሁ  ልማት ጋር በተያያዘ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የሲ ኤም ሲ- ፔፕሲ - ጎሮ - መንገድ  ልዩ ቦታው ሳፋሪ መብራት አካባቢ  ብሪቲሽ ትምህርት ቤት አጠገብ የመንገድ ቆረጣ ይከናወናል፡፡

በመሆኑም ከጥር 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከፊጋ  ወደ ሳፋሪ እንዲሁም ከሳፋሪ ወደ ፊጋ የሁለቱም አቅጠጣጫ መንገዶቹ ላልተወሰኑ ቀናት ዝግ  ስለሚሆኑ አሽከርከሪዎች ይህንኑ አውቃችሁ አማራጭ መንገዶችን  እንድትጠቀሙ ሲል የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

27 Jan, 08:08


ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት 600 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳቧ ተገለጸ

ባለፉት 6 ወራት 597 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር  በላይ ኢንቨስትመንት ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጠና መግባታቸውን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተናገረ።

ከ 80 በላይ የተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ኮርፖሬሽኑ ወደ ሚያስተዳድራቸው ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች መሳባቸው የተነገረ ሲሆን 14 የማምረቻ ሼድና ከ 70 ሄክታር በላይ የለማ መሬት ለባለሃብቶቹ መተላለፋቸው ተነግሯል።

በዚህም ኢንቨስትመንቶቹ በመቀሌ፣ በቦሌ ለሚ፣ በቂሊንጦ፣ በኮምቦልቻ፣ በድሬዳዋ ልዩ ነፃ ንግድ ቀጠና ፣በጅማ እና ሰመራ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ዉስጥ የሚሰማሩ መሆናቸው ተገልጿል።

ከተሳበዉ አጠቃላይ ኢንቨስትመንት ዉስጥ  በፋርማሲዩቲካል ፤ በአግሮ ፕሮሰሲንግ በተለይም ቡናና ሻይ፣ በኤሌክትሪክ መኪና መገጣጠም እና ሌሎችም የቴክኖሎጂና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ላይ የሚሰማሩት  የቻይና፣ የሩሲያ፣ የቬትናም እና የአገር ዉስጥ ባለሀብቶች መሆናቸው ተነግሯል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari


#ethiopia #FDIethiopia

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

27 Jan, 06:10


የማለዳ አንኳር ዜናዎች
ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ጥር 19 ቀን 2017 ዓ.ም

1. በኢትዮጵያ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የትምህርት አሰጣጥ ጥራትን ለመፈተሽም የሚያግዝ መመሪያ ሊወጣ ነው። ሀገሪቱ ከዚህ ቀደም የተቋማቱን የትምህርት ጥራትን የምትፈትሽበት ስርዓትና መመሪያ ባለመኖሩ የትምህርት ጥራታቸው እስከምን ድረስ ነው የሚለውን ለማወቅ አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል ተብሏል። መመሪያውም የመንግስት፣ የግል እና የቴክኒክና ሞያ ተቋማትን እንደሚመለከት ተነግሯል። አሁን ባለው አሰራር የከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ጥራት በተመለከተ የሚያስገድድ መመሪያ ባለመኖሩ በተገቢው መንገድ አይፈተሹም። ነገር ግን የጥራት ኦዲት መመሪያ ከወጣ በኋላ የተቋማቱን የትምህርት ጥራት ተፈትሾ ደረጃ ለመስጠት እንደሚያግዝ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ተናግሯል።

2. በአዲስ አበባ ከተማ ከመስከረም 2013 ዓም እስከ 2016 ዓ.ም ከፍጥነት ጋር በተገናኘ የመንገድ አደጋ የሞት መጠን  መቀነሱን ጥናት አሳየ። በ2013 ዓም የአሽከርካሪዎች አማካኝ የፍጥነት መጠን በሰዓት 52 ኪሎ ሜትር ሲሆን አሁን ላይ አማካኝ የፍጥነት መጠን በሰዓት ወደ 45 ኪሎ ሜትር ዝቅ ማለቱንም ተነግሯል። በዚህም የአሸከርካሪ ፍጥነትን በሰዓት አንድ ኪሎ ሜትር መቀነስ ሲቻል የሞት ምጣኔ በአምስት በመቶ ይቀነሳል። በከተማዋ ከፍጥነት ጋር በተገናኘ የሚያጋጥም ሞት መቀነሱ የተነገረው በብሉምበርግ ኢኒሼቲቭ የጆን ሆፕኪንስ ዓለም አቀፍ የጉዳት ምርምር ተቋም ከአዲስ አባባ ዩኒቨርስቲ የህብረተሰብ ጤና ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር ባደረገው የዳሰሳ ጥናት ነው።

3. በበጀት አመቱ ስድስት ወራት በአዲስ አበባ ከተማ ከ18 ሺህ በላይ ውሎና አዳራቸውን ጎዳና ላይ ያደረጉ ሰዎች ተነስተዋል ተባለ፡፡ ከጎዳና ላይከተነሱት ውስጥ ከ1300 በላዩም ሴቶች ሆናቸው የአዲስ አበባ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ተናገሯል፡፡ ከጎዳና ላይ የሚነሱ ህፃናትን ወደ ቀያቸው በመመለስ ትምህርት እንዲያገኙ እየተደረገ ነው የተባለ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ በሙያቸው ወደ ስራ እንዲሰማሩ አደርጋለሁ ብሏል ቢሮው። በሌላ በኩል ደግሞ በተለያዩ ገፊ ምክንያቶች በከተማዋ ውሎና አዳራቸውን ጎዳና ላይ ያደረጉ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል።
ከሁለት አመታት በፊት በተጠና ጥናት መሰረት በአዲስ አበበ ከተማ ከ60 ሺህ በላይ የጎዳና ነዋሪዎች መኖራቸውን ያመላክታል።

4. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው የ4ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ አጀንዳዎች  ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ማሳለፉን በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አስፍሯል። በዚህም መሰረት ካቢኔው የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ ታሳቢ ያደረገ የኤምባሲዎች የመሬት ጥያቄን እና የከተማዋን የኢኮኖሚ እንቅቃሴ ለሚያጎለብቱ፣ ሰፊ የስራ እድል እየፈጠሩ ላሉ፣ የዉጪ ምንዛሬ እያስገኙ ላሉ  የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረቻ ማስፋፊያ ቦታ ጥያቄዎችን መርምሮ ውሳኔ አሳልፏል።

5. በሱዳን በአንድ ሆስፒታል በተፈፀመ የአየር ጥቃት የ70 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተነገረ። በሱዳን ዳርፉር ጥቃት የደረሰበት ሆስፒታል በጦርነት እየታመሰች በምትገኘው ሱዳን ኢል ፋሻር  ብቸኛ አገልግሎት ሰጪ ነበር ተብሏል። በአፍሪካ ውስጥ በርካታ አካባቢዎች የእርስ በእርስ ጦርነት እየጨመረ መምጣቱን የሚናገሩት የአለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ በጥቃቱ ወቅት በሆስፒታሉ "በህክምና ላይ ባሉ ታካሚዎች የተሞላ ነበር" ብለዋል። በዚህም በጥቃቱ በዋነኛነት የተጎዱት ሴቶች እና ህጻናት ናቸው። በሱዳን መንግስት እና በ RSF መካከል በተፈጠረው የእርስ በእርስ ጦርነት በዓለም ላይ ካሉት አስከፊ ሰብአዊ ቀውሶች አንዱ ሲሆን ከ20,000 በላይ ሰዎችን ገድሏል ከ11 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ደግሞ ተፈናቅሏል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

25 Jan, 18:17


የባቡር ትኬት በኦንላይን መቁረጥ ሊጀመር ነው።

የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር አ.ማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ታከለ ኡማ(ኢ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው በኦንላይን ትኬት በመቁረጥ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት መሰጠት ሊጀመር መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር አ.ማ ከየካቲት 2017ዓ.ም  ጀምሮ በኦንላይን ትኬት በመቁረጥ የህዝብ መንገደኞች ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት  እንደሚጀምር አስታወቀ፡፡

አክሲዮን ማህበሩ ከየካቲት 2017 ጀምሮ በኦንላይን ቦታ በማስያዝ  የህዝብ መንገደኞች ትራንስፖርት አገልግሎት  እንደሚጀምር ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልፀዋል።

ጥራት ያለዉ እና ቀልጣፋ የጉዞ አገልግሎት  ለመስጠት ፣ ትክክለኛ የመንገደኛ መረጃን ለማረጋገጥ እንዲሁም ከችግር የጸዳ ጉዞን ለማመቻቸት አስፈላጊ በመሆኑ ለሁሉም የሀገር ውስጥ ተሳፋሪዎች ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) በመጠቀም ኦንላይን ቦታ ለመያዝም  ሆነ ለመጓዝ  መስፈርት መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Jan, 17:21


ኢትዮጵያውያኑ ከእስር ተለቅቀው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

በታይላንድ በስራ ቅጥር ሽፋን ለእስር ተዳርገው የነበሩ 38 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

በሕገ ወጥ ዓለም አቀፍ የሰው አዘዋዋሪዎች በሥራ ቅጥር ሽፋን ወደ ማይናማር ተወስደው ችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ለመታደግ መንግሥት ጥረቱን መቀጠሉን ገልጿል፡፡

ከሰሞኑ በሕንድ ኒውዴልሂ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮንም ወደ ታይላንድ ልዑክ በመላክ በእስር ላይ ይገኙ የነበሩ 38 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንዲለቀቁ ማድረጉ ተገልጿል፡፡

ማይናማር ውስጥ ከነበሩት መካከልም ከከስቸጋሪ ሁኔታ አምልጠው ወደ ታይላንድ የሚገቡ ስደኞች ሕጋዊ ሠነድ ባለመያዛቸው ለእስር ተዳርገው ነበር መባሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

ይህን ተከትሎም ሚስዮኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ባደረገው ጥረት 38 ኢትዮጵያውን ከእስር ተለቅቀው ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ማድረጉ ተጠቅሷል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Jan, 15:38


የዕለቱ አበይት ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ጥር 16 ቀን 2017 ዓ .ም


1. በአማራ ክልል ከ120 በላይ ንጹሀን መገደላቸው ተገልጿል። በአማራ ክልል ከ6ሺ በላይ የሚሆኑ ሰዎች በጊዜያዊ ማቆያዎች እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች (ኢሰመኮ) አስታውቋል። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች  የዘፈቀደ እና የጅምላ እስራቶች ተፈጽመዋል ያለው ኮሚሽኑ ባለፉት 4 ወራት ብቻ ከ6ሺ በላይ ሰዎች በተመረጡ 4 ቦታዎች ማለትም በዳንግላ፣ ጭልጋ (ሰራባ ወታደራዊ ካምፕ)፣ በኮንቦልቻ እና ሸዋሮቢት ከተሞች በሚገኙ ጊዜያዊ ማቆያዎች ታስረው ይገኛሉ
ብሏል። ከተያዙት ሰዎች መካከል አብዛኞቹ ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡም በሩብ ዓመቱ ሪፖርቱ ይፋ አድርጓል።

2. ለድንጋይ ከሰል የሚወጣውን ምንዛሬ የሚያስቀሩ አራት የድንጋይ ከሰል ፋብሪካዎች በዚህ ዓመት ይመረቃሉ ተባለ።  ፋብሪካዎቹ በሙሉ አቅም መስራት ሲጀምሩ ኢትዮጵያ በዓመት ከሚያስፈልጋት 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ቶን የድንጋይ ከሰል በተጨማሪ እስከ 400 ሺህ ቶን ትርፍ ማምረት እንደሚችሉ የማዕድን ሚኒስትሩ ኢ/ር ሀብታሙ ተናግረዋል። በዳውሮ ዞን ተገንብቶ ዛሬ በጠ/ሚ ዐቢይ የተመረቀው ኢቲ የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካ ከአራቱ ፋብሪካዎች አንዱ ነው። ፋብሪካው በዓመት 450 ሺህ ቶን ያለቀለትና ጥራት ያለው የድንጋይ ከሰል ማምረት ይችላል ተብሏል፡፡ ይህም የሀገሪቱን 25 በመቶ የድንጋይ ከሰልን ፍላጎት እንደሚሸፍንም ነው የተነገረለት፡፡ ኢትዮጵያ እስከ ቅርብ ዓመታት ድረስ ለሲሚንቶ ፋብሪካዎች እስከ 300 ሚሊዮን ዶላር በማውጣት የታጠበ የድንጋይ ከሰል ከውጪ ስታስገባ እንደነበርም ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

3. የአማራ ክልል የሰላም እና ጸጥታ ይዞታውን ገምግሟል። በግምገማው ባለፉት 6 ወራት
ተከናወኑ ባላቸው የህግ ማስከበር ስራዎች በየጊዜው በሚፈጠር የጸጥታ መደፍረስ ሲቸገር የነበረው ሕዝባችን እፎይታን አግኝቷል ብሏል። ሆኖም በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በመንግስት እና የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተቀሰቀሱት ግጭቶች እንደቀጠሉ ናቸው። ጦርነቱ ሁለት ዓመት ሊሞላው ጥቂት ወራት ብቻ ቀርተውታል።

4. በሊባኖስ እና በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 359 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።በሊባኖስ በአስቸጋሪ ሁኔታ የነበሩ እና ለአደጋ የተጋለጡ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ መቀጠሉን ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ገልጿል። በያዝነው ሳምንት ውስጥ ብቻ156 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ተብሏል።በዚህ ሳምንት ውስጥ ከሊባኖስ ወደ ሀገር የተመለሱት 156 ዜጎች 143 ሴቶች 13 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ ከተመላሾች መካከል 18 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሚገኙበት ተገልጿል።በተመሳሳይ በሳምንቱ 185 ወንዶች፣ 15 ሴቶች 3 ጨቅላ ህፃናት በድምሩ 203 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ከሳውዲ አረቢያ 90 ሺህ ዜጎቿን መልሳለች።

5. ዶናልድ ትራምፕ በዜግነት የሚገኝ ዜግነትን ለማስቀረት ያስተላለፉት ውሳኔ በፍርድ ቤት ታግዷል። ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ የበርካታ ሀገራት ዜጎች የሚወልዷቸው ልጆች የአሜሪካ ዜግነት እንዲያገኙ በሚል ወደ ዋሽንግተን ሄደው ይወልዳሉ። ይህ ህግ በአሜሪካ የህገወጥ ስደተኞችን ቁጥር እንዲያሻቅብ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል እንዱ በመሆኑ ዶናልድ ትራምፕ ህጉ እንዲሻር አዘው ነበር። ይሁንና የሀገሪቱ ፍርድ ቤት የትራምፕን ውሳኔ ህገመንግስታዊ አይደለም በሚል እንዳይፈጸም አግዶታል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Jan, 12:44


በአማራ ክልል 120 ንጹሀን መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አሳውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ጋምቤላ ክልሎች ያደረጋቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርት ዛሬ  ይፋ አድርጓል፡፡

በአማራ ክልል በሶስት ወራት ውስጥ 120 ንጹሀን ዜጎች መገደላቸውን እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ቦታዎች ላይ ይኖሩ የነበሩ 84 ንጹሃን ዜጎች እንደተገደሉ ኢሰመኮ በሪፖርቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡

ኮሚሽኑ እንደለጸው ሪፖርቱ ከመስከረም ወር አጋማሽ 2017 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ 2017 ዓ.ም አጋማሽ ባለው ጊዜ ውስጥ ያለውን ጊዜ የሚመለከት ነው ብሏል፡፡

ሪፖርቱ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በግጭት ዐውድ ውስጥ ባሉ አካባቢዎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን በሙሉ የሚሸፍን አይደለም ያለው ኮሚሽኑ በእነዚህ አካባቢዎች በነጻነት ተንቀሳቅሶ የተሟላ ክትትልና ምርመራ ለማካሄድ ምቹ ሁኔታ ባለመኖሩ፣ ውጤታማ ክትትልና ምርመራ የተከናወነባቸውን ጉዳዮች ብቻ በማሳያነት እንዳቀረበም ገልጿል፡፡

ኢሰመኮ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው በግጭት በተጎዱ አካባቢዎች ከደረሱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢ ሆነው ከቀጠሉ ጉዳዮች መካከልም ከፍርድ ውጭ ግድያ መፈጸም፣ በግጭት ዐውድና አካባቢ የሚደርስ የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ ዋነኞቹ ናቸው ተብሏል፡፡

እንዲሁም የዘፈቀደ፣ የጅምላና የተራዘመ እስራትና የተፋጠነ ፍትሕ እጦት፣ አስገድዶ መሰወር፣ እገታ፣ በመዘዋወር መብትና በመጓጓዣ መንገዶች ላይ የሚፈጸም ሕገ-ወጥ ገደብ፣ የሀገር ውስጥ መፈናቀል እና የዳኝነት ነጻነት መሸርሸሮች እንዳሉም ኢሰመኮ በሪፖርቱ ላይ ጠቅሷል፡፡

በአማራ ክልል በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ከ120 በላይ ንጹሃን ዜጎች እንደተገደሉ የገለጸው ኢሰመኮ ግድያው በአብዛኛው በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች የተፈጸመ ሲሆን የፋኖ ታጣቂዎች ደግሞ የመንግስት አመራሮችን ጨምሮ ንጹሃን ዜጎች ላይ ግድያ እንደፈጸሙ በሪፖርቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡

የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ፋኖ ናችሁ እና ለፋኖ ትረዳላችሁ በማለት ንጹሃንን ሲገድሉ የፋኖ ታጣቂዎች ደግሞ የመንግስት አገልጋዮች ናችሁ በሚል ግድያውን ይፈጽማሉ ተብሏል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ቦታዎች ላይ ይኖሩ የነበሩ 84 ንጹሃን ዜጎች እንደተገደሉ በሪፖርቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡

ንጹሃኑ የተገደሉት በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና በተለምዶ ኦነግ ሸኔ ተብለ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን አባላት ሲሆን የመንግስት የጸጽታ ሀይሎች ለኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ትረዳላችሁ እያሉ ግድያውን ፈጽመዋል ተብሏል፡፡

የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ደግሞ መንግስትን ትረዳላችሁ በሚል ንጹሃን ዜጎችን እንደሚገድሉ ተገልጿል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች የዘፈቀደ እስር እየፈጸሙ እንደሆነ እና በአማራ ክልል ብቻ ከ6 ሺህ በላይ ዜጎች ዳንግላ፣ ጭልጋ፣ ኮንቦልቻ እና ሸዋ ሮቢት ከተሞች ከህግ ውጪ በእስር ላይ ናቸው ተብሏል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Jan, 12:37


በአየር ብክለት ምክንያት ትምህርት ቤቶች ተዘጉ

በታይላንዷ ዋና ከተማ ባንኮክ ባጋጠመ የአየር ብክለት ምክንያት በዛሬው ዕለት ከ350 የሚበልጡ ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ መደረጉን የከተማው ባለ ሥልጣናት ተናግረዋል።

በዚህም ምክንያት ለሳምንት ያህል ነጻ የህዝብ ማመላለሻ ትራንስፖር መፈቀዱን ያስታወቁት የከተማዋ ባለሥልጣናት፣ ይህም በከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ የምትታወቀውን ከተማ ከትፍፍጉ ለማሳረፍ እና ከመኪኖች የሚወጣውን ጭስ ለመቀነስ እንደሆነ ተናግረዋል።

በአካባቢው የሚታወቀው የአየር መበከል ችግር ባንኮክን በተደጋጋሚ የሚያጠቃት ሲሆን፣ የአሁኑ ግን እ.አ.አ ከ2020 በኋላ በርካታ ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ ምክንያት የሆነ ትልቅ ክስተት ነው ተብሏል።

ክስተቱ በአምስት ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ መሆኑንም ባለሥልጣናቱ ጨምረው ገልጸዋል::

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Jan, 09:04


ጉምሩክ ኮሚሽን አገልግሎትን ለማዘመን የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን ሊተገብር ነው

ጉምሩክ ኮሚሽን በድንበር የሚተላለፉ የጭነት እና የዕቃ እንቅስቃሴዎችን በዘመኑ ቴክኖሎጂ የሚቆጣጠር 'ኤሌክትሮኒክ ካርጎ ትራኪንግ' ሥርዓትን ተግባራዊ ሊያደርግ መሆኑ ተገለጸ።

በ'ኤሌክትሮኒክ ካርጎ ትራኪንግ' ሥርዓት፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረት አድርጎ የድንበር ቁጥጥር እንዲሁም ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች ልማትና ትግበራ ላይ ያተኮሩ ውይይት ተካሄዷል።

በውይይቱ ላይ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፕሮጀክቶቹ ስራ አስኪያጅ ሽብሩ ተመስገን (ዶ/ር) እና ሌሎች የኮሚሽኑ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡

የኮሚሽኑን አገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመንና የሕግ ተገዥነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ተናግረዋል።

ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት 'የኤሌክትሮኒክ ካርጎ ትራኪንግ' ሥርዓትን ጨምሮ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሙሉ ትግበራ ለማሸጋገር እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Jan, 08:27


በአዲስ አበባ አሰቃቂ ወንጀል የፈጸመው ሰው የሞት ፍርድ ተወሰነበት

ባለቤቱን ገድሎ ስጋዋን ከትፎ መጸዳጃ ቤት ዉስጥ የከተተዉ ተከሳሽ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበት

ፀሃዬ ቦጋለ በየነ የተባለ ተከሳሽ ከነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 5፡00 እስከ ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡30 ድረስ ባለው ጊዜ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አርሴማ ፀበል አከባቢ ባለቤቱ የነበረችውን ሟች ወንበር ላይ ተቀምጣ እያለ ሳታየው ከኋላዋ በመምጣት በሊጥ ማዳመጫ ዱላ ማጅራትዋን በመምታት ህይወቷ እንዲጠፋ አድርጓል መባሉን ከፍትሕ ሚኒስቴር ሰምተናል።

ግለሰቡ ባለቤቱን እራሷን እንድትስት ካደረገ በኋላ እዛው ትቷት ከቤት ወጥቶ በመሄድና ከተወሰነ ሰዓታት በኋላ ተመልሶ በመምጣት ሟች እራሷን ስታ ከወደቀችበት መሬት ለመሬት በመጎተት እቤት ውስጥ ወደሚገኘው መታጠቢያ ቤት በማስገባት አንድ እግሯን ከዳሌዋ ጀምሮ በመቁረጥና ሙሉ የእግሯን ስጋ አጥንቷ ባዶ እስኪሆን ድረስ መልምሎ በማውጣት ስጋዋን አድቅቆ በመክተፍና በመቆራረጥ መጸዳጃ ቤት ውስጥ ጨምሯል።

ወንጀለኛዉ የቆረጠውን እግሯን ለሁለት በመስበርና በፌስታል በመቋጠር ፀጉሯን በመቀስ በመቁረጥ ቀሪ አስከሬንዋ ላይ ጨርቅና የተለያየ መዘፍዘፊያ በመጫን እዛው መታጠቢያ ቤት ውስጥ በማስቀመጥ እስከ ነሃሴ 30/2014 ዓ.ም ድረስ ምንም እንዳልተፈጠረ እቤት ውስጥ እያደረ ከቆየ በኋላ ከጷግሜ 1/2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መስከረም 16/2015 ዓ.ም ድረስ ቤቱን ዘግቶ ተሰዉሮ ነበር ብሏል።

በዚህም ምክያንት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ተጣርቶ በፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ በሴቶችና ህጻናት ላይ ሚፈፀሙ ወንጀሎች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት በወ/ሕ/አ539/1/ሀ/ መሰረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የሰው ግድያና ከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት ክስ ቀርቦበት ክርክር ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በክርክሩ ሒደትም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ እንዲከላከል ብይን ቢሰጥም የመከላከያ ማስረጃ አቅርቦ የቀረበበትን ክስ ሊከላከል ባለመቻሉ ፍ/ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠት በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የወሰነ የነበረ ቢሆንም ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው ይግባኝ መሰረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የወሰነውን የእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ውሳኔ በመሻር ተከሳሹ በሞት እንዲቀጣ ወስኖበታል ሲል ፍትህ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

#ethiopia #Crime #Deathpenality

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Jan, 05:52


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ጥር 16 ቀን 2017 ዓ .ም

1. ኢትዮጵያ የጥናት እና ምርምር ውጤቶችን በመኮረጅ በዓለም ቀዳሚዋ ሀገር ተብላለች። መቀመጫውን ሕንድ ያደረገው ዓለም አቀፍ ሪሰርች ዋች እንዳለው ከሆነ ኢትዮጵያ በሌሎች ሀገራት የተሰሩ ጥናቶችን ቀጥታ ትቀዳለች። ሳውዲ አረቢያ፣ ፓኪስታን፣ ቻይና እና ግብጽ ከኢትዮጵያ በመቀጠል የጥናት ውጤቶችን የሚኮርጁ ሀገራት ናቸው። እነዚህ ሀገራት የሌሎች ሰዎችን ጥናት ሲኮርጁ የሚቀጣ ህግ የላቸውም ተብሏል።

2. የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር በወታደራዊ አመራሮች መግለጫን ከመፈንቅለ መንግሥት ለይቼ አላየውም ብሏል። የትግራይ ወታደራዊ አመራሮች በትናንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ ጊዜያዊ አስተዳድሩ እንዲፈርስ እና እንደ አዲስ እንዲደራጅ ወስነናል ብለዋል። ጊዜያዊ አስተዳድሩ ባወጣው መግለጫ የወታደራዊ አመራሮች መግለጫ የፕሪቶሪያ ስምምነቱን የሚጥስ እና በተደራጀው ጊዜያዊ አስተዳድር ላይ መፈንቅለ መንግሥት መሆኑን ገልጿል።

3. የኢትዮጵያ እስልምና ጠቅላይ ምክር ቤት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው እንግልት እንዲቆም ጠይቋል። ምክር ቤቱ ለትምህርት ሚንስቴር በጻፈው ደብዳቤ ሙስሊም ተማሪዎች ከአለባበስ ጋር በተያያዘ እየደረሰባቸው ያለውን እንግልት ትምህርት ሚንስቴር እንዲያስቆም ሲል ጠቅሷል። በዲላ ዩንቨርስቲ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ከሰሞኑ ወደ ግቢ አትገቡም እንደተባሉም ተገልጿል። ከዚህ በተጨማሪም በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች ከአለባበሳቸው ጋር ተያይዞ ወደ ትምህርት አትገቡም መባላቸው ይታወሳል።

4. የህዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕምባ ጠባቂ ሆነው የተሾሙት ወ/ሮ ስመኝ ውቤ የገለልተኝነት ጥያቄ ተነሳባቸው።የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በትናንትናው ዕለት  ወ/ሮ ስመኝ ውቤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕምባ ጠባቂ ሆነው እንዲያገለግሉ ማጽደቁ ይታወሳል፡፡ አዲሷ ተሿሚ ከዚህ በፊት በበርካታ ተቋማት የፓርቲ ሹመቶችን ተቀብለው በሀላፊነት ማገልገላቸው አሁን በተሾሙበት ተቋም ውስጥ ገለልተኛ አገልግሎት ላይሰጡ ይችላሉ በሚል በምክር ቤት አባላት ጥያቄ ተነስቶባቸዋል። ይሁንና ምክር ቤቱ በአብላጫ ድምፅ ሹመቱን አጽድቋል።

5. በአካሊፎርኒያ በድጋሚ የሰደድ እሳት አደጋ ማጋጠሙ ተገልጿል። ለሁለት ሳምንት የቆየው የካሊፎርኒያው እሳት አደጋ ከ250 ቢሊዮን ዶላር በላይ ንብረት አውድሞ መቆሙ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ድጋሚ አዲስ ሰደድ እሳት አደጋ ደርሷል። እሳቱን ለመቆጣጠር የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጥረት እያደረጉ ነው ተብሏል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#Dailynews #ethiopia

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Jan, 18:25


''በማህበራዊ ሚዲያ በታቦተ ሕጉ ላይ የተሳለቁ ግለሰቦችን በሕግ ይጠየቃሉ'' - የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ

በጥምቀት በዓል በታቦተ ሕጉ ላይ የተሳለቁ፣የትንኮሳ ስብከቶችና አለባበሶችን በማኅበራዊ ሚዲያ ያሠራጩ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦችና ቡድኖች በሕግ እንደሚጠየቁ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ገለጸ፡፡


የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰሞኑን ግለሰቦችና ቡድኖች ሃይማኖታዊ ቅራኔ እና ጥላቻ ሊፈጥሩ የሚችሉ በቪዲዮ የለቀቁትን አሉታዊ መልእክቶችን እና ተግባራትን በፍጥነት ለማረም በጽሕፈት ቤቱ ጋዜጣዊ መግለጫ እና ማብራሪያ ለሚዲያ አካላት ሰጥቷል፡፡

በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ  እንዳብራራው ከእምነቱ ሥርዐት ባፈነገጠ መንገድ አንዳንድ ኃላፊነት የማይሰማቸው ግለሰቦችና ቡድኖች የሌላውን እምነትና ሥርዐት በማንቋሸሽ፣ ክብረ ነክ ተግባራትን በመፈጸም፤ በተለይም በጥምቀት በዓል ታቦተ ሕጉ ላይ በመሳለቅ፤ የኢስላማዊ አለባበስ መገለጫ የሆነውን ጀለቢያ በመልበስ ሙስሊሞች በመምሰል የትንኮሳ ስብከቶችና ዝማሬዎች በማቅረብ፣ የትንኮሳ አለባበሶች ጭምር በመጠቀም በማኅበራዊ ድረገጽ የለቀቁት አጫጭር ቪዲዮችዎች የእምነቱ ተከታዮችን ማስቆጣቱን ያብራራል፡፡

ይህ ዓይነቱ ተግባር በሀገራችን ለዘመናት የዘለቀውን የመከባበር፣ በሰላም አብሮ የመኖር እሴትን የሚሸረሽር ድርጊት መሆኑን የገለጸው መግለጫው፤ በሁሉም ሃይማኖቶች የሚወገዝ የድፍረት ድርጊት በመሆኑ ይህን የፈጸሙ ግለሰቦችና ቡድኖች በሕግ ሊጠየቁ እንደሚገባ፣መጠየቅም መጀመሩን መግለጫው ያስረዳል፡፡

ማንኛውም ግለሰብም ይሁን ቡድን ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ የሌሎችን መብትና ጥቅም በሚጻረር አግባብነት የሌለውና ግጭት ቀስቃሽ ተግባራት የሚፈጽም ማንኛውም ሕገ ወጥ ተግባር በዝምታና ሊታለፍ እንደማይገባው ይገልጻል፡፡ 

በመጨረሻም ማኅበራዊ ድረገጾችን እና ሚዲያዎችን በመጠቀም የጥላቻ ንግግሮች፣ ትንኮሳዎችና ክብረ ነክ ድርጊቶች የሚፈጽሙ ግለሰቦችና ቡድኖች ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት፡- ከመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን፣ ከፍትሕ የጸጥታ አካላት ጋር በቅርበት እየሠሩ እንደሆነ የወጣው መግለጫ ያስረዳል፡፡ 

አያይዞም ይህ ዓይነቱን ተግባር ለመከላከል የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ሥርዐት ላይ በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መግለጫ ያስረዳል፡፡

#EOTC

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Jan, 17:22


በተሽከርካሪ አደጋ ሁለት ሰዎች ወዲያው ህይወታቸው አለፈ

ዛሬ ከቀኑ 7:00 ሠዐት በአማራ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን በሞጃና ወደራ ወረዳ  ዙብአንባ ቀበሌ  ልዩ ቦታው ሞፈር ውሀ ጅረት አካባቢ ከአበባ ወደ መሀልሜዳ ሲጓዝ የነበረ ተሽከርካሪ መንገድ ስቶ በመገልበጡ 2 ሠዎች ወዲያው ሲሞቱ አንድ ሠው ከባድና አንድ ሠው ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን የአማራ ፖሊስ አሳውቋል።

ተጎጅዎች በደብረብረሀን ሪፈራል ሆስፒታል እየታከሙ ናቸው።

ዛሬ በዚሁ  በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ፤ ዳውንት ወረዳ ኩርባ ከተማ መነሻውን ያደረገና ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ የ25 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ይታወቃል።

እንዲሁም በስልጤ ዞን ጠዋት በደረሰ አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት አልፏል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Jan, 15:56


የዕለቱ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም

1.  የትግራይ የጸጥታ ኃይል ለሁለት ተከፈለ፡፡የትግራይ የጸጥታ ኃይል ኃላፊነቱን በአግባቡ እየተወጣ አይደለም ሲል የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር ወቀሰ፡፡ አስተዳደሩ ከተሰጠው ኃላፊነት ውጭ ለውጭ ኃይሎች እየሰራ ነው ሲል በክህደት ከሷል፡፡ በመሆኑም የጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ተነስተው በወርሀ ነሀሴው የእነ ዶ/ር ደብረጽዮን ህወሓት ጉባኤ በተመረጡ ሰዎች እንዲተኩ ስለመወሰኑ አስታውቋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን አባላቱን ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ሊያስወጣ እንደሚችልም ነው፤ ለባለፉት 5 ቀናት ተሰብስቦ የነበረው የጸጥታ ኃይሉ በተወካዩ በሌ/ኮሎኔል ገብረ ገብረጻዲቅ በኩል በሰጠው መግለጫ ያስታወቀው፡፡

2.  ጦርነትና ግጭት ባለበት ሁኔታ መመካከር አይቻልም በሚል የብሔራዊ ምክክር ጉዳዮች ‹ሊታገቱ› እንደማይገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ተናገሩ፡፡ ትናንት በተወካዮች ምክር ቤት በተዘጋጀ የምክክር መድረክ ላይ ለውይይት መነሻ የሚሆን ጥናታዊ ጽሁፍን ያቀረቡት ሚኒስትሩ ጉዳዩ እንደ ቅድመ ሁኔታ መታየት የለበትም ብለዋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን የምክክሩን አስፈላጊነት ተጠየቅ ውስጥና እንደሚከተውና የመቶ ሚሊዮኖችን አጀንዳ በጥቂቶች ታጋች እንደሚያደርገው ተናግረዋል፡፡

3.  በሰሜን ወሎ ዞን ዳውንት ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ25 ሰዎች ሕይወት አለፈ።አደጋው መነሻውን ኩርባ ከተማ አድርጎ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ በመገልበጡ ምክንያት የደረሰ ሲሆን ተሳፍረው የነበሩ የ25 ስዎች ሕይወት ማለፉን የወረዳው ፖሊስ አስታውቋል። በአደጋው ከባድ ጉዳጥ የደረሰባቸው 14 ሰዎች ደግሞ ወደ ደላንታ እናደሴ ሆስፒታሎች መወሰዳቸውንም ነው የፅሕፈት ቤቱ ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ጌታቸው አራጌ የተናገሩት፡፡

4.  የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ ቦይንግ 777F እቃ ጫኝ አውሮፕላን ተረከበ፡፡ አውሮፕላኑ የካርጎ ጭነት አገልግሎት አድማስን ለማሳደግ የራሱ አስተዋፅዖ ከማበርከቱ በተጨማሪ እያደገ የመጣውን የካርጎ አገልግሎት ለማስተናገድ የራሱ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው አየር መንገዱ አስታውቋል፡፡የካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ያለውን የላቀ የአየር እቃ ጭነት አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠሉን የገለጸው አየር መንገዱ፤ አውሮፕላኑ አየር መንገዱ ማህበራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ረገድ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን የሚያግዙና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ ለተሰማሩ ተቋማት የሚለገሱ ቁሳቁሶችን ጭኖ ስለመምጣቱም ገልጿል።

5.  ትራምፕ የዩክሬን ጦርነት በ100 ቀናት ውስጥ እንዲቆም አዘዙ፡፡ጦርነቱን የማስቆሙ ኃላፊነት ለዩክሬንና ሩሲያ ልዩ መልዕክተኛቸው ለጡረተኛው ወታደራዊ ጄነራል ኬት ኬሎግ ስለመስጠታቸውም ተሰምቷል፡፡ ሆኖም ትዕዛዙ ሰምሮ ጦርነቱን በተጠቀሱት 100 ቀናት ውስጥ ለማስቆም ይቻላል ወይ የሚለው በብዙዎች ዘንድ ጥርጣሬን አጭሯል፡፡ ድርድሩን ራሳቸው ትራምፕ የመቆጣጠር ፍላጎት አላቸው መባሉም ይሳካ ይን የሚሉ ጥያቄዎችን እያስነሳ ይገኛል፡፡ ውጥኑ ሰምሮ ጦርነቱን ማስቆም ከሚቻልበት ምዕራፍ ላይ የሚደረስ ከሆነም በድርድሩ ራሳቸው እንደሚሳተፉ ትራምፕ አስታውቀዋል፡፡  

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #Dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Jan, 15:22


ፕሬዚዳንት ትራምፕ 10 ሺህ ወታደሮችን በሜክሲኮ ድንበር ለማሰማራት ያስባሉ ተባለ

ከጥቂት ቀናት በፊት የፕሬዚዳንትነቱን መንበር የተረከቡት ዶናልድ ትራምፕ ስደተኞች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ለመከላከል 10 ሺህ ወታደሮችን በሜክሲኮ ድንበር ለማሰማራት እንደሚያስቡ ከመንግሥት የውስጥ ማስታወሻ የተገኘ መረጃ አሳየ።

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት 1,500 ወታደሮች አገራቸው ከሜክሲኮ የምትዋሰንበት ድንበሩን የማጠር ስራ እንዲያከናውኑ ቀደም ብለው ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

እነዚህ ወታደሮች "በህግ የማስከበር ስራ" ውስጥ እንደማይሳተፉ አንድ ወታደራዊ ምንጭ ተናግረዋል።

በድንበር የሚሰማሩ ወታደሮች ቁጥር 10,000 እንደሚሆን የቢቢሲ የአሜሪካ አጋር ሲቢኤስ ኒውስ የተመለከተው የውስጥ የመንግሥት ማስታወሻ ጠቁሟል።

ዶናልድ ትራምፕ ስደተኞች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ለማድረግ የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም ሁለት ሲ-17 እና ሁለት ሲ 130 የተሰኙ አውሮፕላኖች እና ሄሊኮፕተሮች ወደዚሁ ድንበር እንደሚላኩ ተገልጿል።

የመከላከያ ተጠባባቂ ጸሐፊ ሮበርት ሳልስስ "ህገወጥ መጻተኞች" ሲሉ የጠሯቸውን ከ5,000 በላይ ስደተኞችን ወደ ሌሎች አገሮች ለማባረር መስሪያ ቤታቸው በወታደራዊ በረራዎች ያግዛል ብለዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ምክር ቤቱ "ህገወጥ ስደትን ለመቆጣጠር" በሚል የተሻሻለውን 'ሌክን ራይሊ አክት' የተሰኘውን ህግ አጽድቋል።

ስልጣን በተቆጣጠሩባት እለት በርካታ መመሪያዎችን ያስተላለፉት ትራምፕ ይህ የመጀመሪያ ድላቸው ነው ተብሏል። ምክር ቤቱ ይህንን ረቂቅ ህግ ማሳለፉን ተከትሎ ህግ ሆኖ ለመውጣት ትራምፕ መፈረም ይኖርባቸዋል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Jan, 15:18


የኢትዮጵያ አየር መንገድ የዕቃ ጫኝ አውሮፕላን በዛሬው ዕለት ተቀብሏል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎቱን ይበልጥ ለማላቅ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡

አየር መንገዱ በዛሬው ዕለት ቦይንግ 777F ዕቃ ጫኝ አውሮፕላንን ተቀብሏል፡፡

አውሮፕላኑ አየር መንገዱ እየሰጠ ያለውን አስተማማኝና ዓለም ዓቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የአየር ዕቃ ጭነት አገልግሎት ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚያግዝ ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ፤ “ይህ አዲስ የካርጎ አውሮፕላን አየር መንገዱ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን የሚያግዙና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ለተሰማሩ ተቋማት የሚለገሱ ቁሳቁሶችንም ወደ ሀገር ውስጥ ይዞ መጥቷል” ብሏል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Jan, 14:50


በካሳንቺስ ከ13 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ተጀመረ

የአበባ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመንግስትና የግል አጋርነት በካሳንቺስ አያት የመኖሪያ መንደር 13 ሺህ 752 የመኖሪያ ቤቶችን ግንባታን በይፋ አስጀምረዋል።

ቤቶቹ በመንግሥት እና በአያት ሪል ስቴት አጋርነት 13 ሺህ 752 ቤቶች ይገነባሉ የተባለ ሲሆን ቤቶቹን  በ18 ወራት ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዟል።

በካዛንቺስ አካባቢ የሚከናወኑ አጠቃላይ የመኖሪያ ቤት ግንባታዎች ሲጠናቀቁም ከ100 ሺህ በላይ ዜጎች የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ጠቁመዋል።

የአያት ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ አብይ ማሞ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ የሚገነቡት መንደሮች የመኖሪያ ቤትን ጨምሮ የንግድ ሱቆች፣ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ ትምህርት ቤት እና ጤና ጣቢያ እና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ያሟሉ ናቸው ተብሏል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #addisababa #housing

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Jan, 14:13


የታንኳ ቀዘፋ ውድድር እና የጀልባ ትርዒት በባህርዳር እየተካሄደ ነው፡፡

በአማራ ክልል በጥር ወር ከማከበሩት ደማቅ ሁነቶች አንዱ በባህር ዳር ከተማ እና በጣና ሀይቅ ላይ የሚካሄደው "ጥርን በባህር ዳር" ዝግጅት አንዱ አካል የሆነው የታንኳ ቀዘፋ ውድድር እና የጀልባ ትርዒት እየተካሄደ ነው ።

ላለፉት ሰባት ዓመታት ሲካሄድ የቆየው ይህ አስደናቂ በዚህ አመትም ጥር ወር ከገባ ጀምሮ በተለያዩ መርኃ-ግብሮች ሲካሄድ ሰንብቷል።

በጣና ሃይቅ ላይ እየተካሄደ ያለው የጥርን በባሕር ዳር የባህል፣ የገጽታ ግንባታ እና የቱሪስት መስህብ ሥራ ሆኖ ቀጥሏል።

የታንኳ ቀዘፋ ውድድር፣ የጀልባ ትርዒትና ሽርሽር ከሚካሄዱ ሁነቶች መካከል የሚጠቀሱ መሆናቸውን ከአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Jan, 11:56


በስልጤ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ


በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን በሁልባራግ ወረዳ ከአዲስ አበባ ወደ አርባ ምንጭ ይጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከባጃጅ ጋር ተጋጭቶ የ8 ሰዎች ሕይወት አልፏል።

ዛሬ ከጠዋቱ 3፡30 አካባቢ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በወረዳው ከቢለዋንጃ ወደ ኬራቴ ሲጓዝ ከነበረ ባጃጅ ጋር ተጋጭቶ አደጋው እንደተከሰተ የስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ ኮማንዳር ኑረዲን ሀምዳላ ገልጸዋል።

በተጨማሪም በአደጋው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎችም ስለሚገኙ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችልም ኮማንዳር ኑረዲን ሀምዳላ ተናግረዋል።

የትራፊክ አደጋው መንስኤ ከገደብ በላይ በፍጥነት ማሽከርከር እንደሆነ የዞኑ ኮሚዩኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Jan, 09:47


ወ/ሮ ስመኝ ውቤ የህዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕምባ ጠባቂ ሆነው ተሾሙ

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 16ኛ መደበኛ ስብሰባው ወ/ሮ ስመኝ ውቤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕምባ ጠባቂ ሆነው እንዲያገለግሉ አጽድቋል፡፡

በተጨማሪም ዶ/ር የኔነህ ስመኝ የኢትዮጵያ ህዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም ምክትል ዋና ዕምባ ጠባቂ እንዲሁም አቶ አባይነህ አዴቶ የኢትዮጵያ ህዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም የዘርፍ ዕምባ ጠባቂ ሆነው መሾማቸው ተገልጿል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Jan, 07:15


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም

1. በአዲስ አበባ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከ41 ሺህ በላይ ህጻናት ተወልደዋል ተባለ።
የከተማዋ ወሳኝ ኩነት እንደገለጸው በስድስት ወራት ውስጥ 41 ሺህ 183 ህጻናት ልደት ማስረጃ ሰጥቻለሁ ብሏል።ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት  ጋር ሲመሳከር ብልጫ አሳይቷል ተብሏል። ተቋሙ ከልደት በተጨማሪም 4 ሺህ 935 ጋብቻ መመዝገቡንም ገልጿል። ፍቺን በተመለከተ 4,873 ለመመዝገብ ታቅዶ 3,769 ፍቺ መመዝገብን ተመልክተናል ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር ብልጫ አሳይቷል ተብሏል፡፡ሞትን በተመለከተም 2 ሺህ 917 ተመዝግቧል ተብሏል።

2. የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም አዲስ ሀላፊ ዛሬ ይሾምለታል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ የህዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም እጩ ዋና ዕምባ ጠባቂ፣ ምክትል ዕምባ ጠባቂ እና የዘርፍ እምባ ጠባቂ ሹመቶችን መርምሮ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል። ምክር ቤቱ የከተማ መሬት ይዞታ እና መሬት ነክ ንብረት ምዝገባ ረቂቅ አዋጅን እንደሚያጸድቅም ይጠበቃል።

3. ፎኒክስ የተሰኘው የክሪፕቶ ከረንሲ ኩባንያ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን ገለጸ። ዋና መቀመጫውን የተባበሩት አረብ ኢምሬት ከተማ ዱባይ ያደረገው የክሪፕቶ ከረንሲ ኩብንያ በኢትዮጵያ መሰማራቱን አስታውቋል። ኩባንያው ከኢትዮጵያ ዩ80 ሜጋ ዋት ሀይል ግዢ ስምምነት መፈጸሙን ዘ ናሽናል ጋዜጣ ዘግቧል። ኢትዮጵያ በይፋ የክሪፕቶከረንሲ ግብይትን የከለከለች ቢሆንም የመሰረተ ልማት መስፋፋትን ግን ፈቅዳለች። ባለፉት አንድ ዓመት ውስጥ መሰረታቸውን አሜሪካ፣ ቻይና፣ እና ሌሎች የእስያ ሀገራት ያደረጉ ዓለም አቀፍ የክሪፕቶ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል።

4. በባሕርዳር ጣና ሀይቅ ላይ የሚካሄደው  የታንኳ ቀዘፋ ውድድር ዛሬ ይጀምራል። በባሕርዳር ከተማ ከቀኑ 7 ሠዓት ጀምሮ በጣና ሀይቅ ላይ የታንኳ ቀዘፋ ውድድር፣ የጀልባ ትርዒትና ሽርሽር ይካሄዳል። በጥር ወር በአማራ ክልል የቱሪስት መስኅብ የሆኑ ዝግጅቶች በተለያዩ አካባቢዎች ይደረጋሉ፤ የዛሬው የታንኳ ቀዘፋ ውድድር፣ የጀልባ ትርዒትና ሽርሽርም አንዱ መሆኑን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

5. በውልደት የሚገኝ ዜግነትን የሚከለክለው አዲሱ የፕሬዝዳንት ትራምፕ ህግ ከባድ ተቃውሞ ገጠመው። ህጉ ለወሊድ በሚል ወደ አሜሪካ የሚያቀኑ ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦችን ጨምሮ በርካቶችን የሚነካ ነው። ኤምባሲዎቿን ጨምሮ በአሜሪካ ምድር የሚወለዱ ህጻናት ዜግነት እንዳያገኙም ይከለክላል። ከስደተኛም ይሁን በተለያዩ መንገዶች ወደ አሜሪካ ከገቡ ወላጆች የሚወለዱ ህጻናት የዜግነት መብት እንዳያገኙ የሚያደርግ ነውም ተብሏል። ይህን ተከትሎም የሀገሪቱን 22 ግዛቶች ጨምሮ በርካቶች ተቃውመውታል እንደተቃወሙት ተዘግቧል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #Dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Jan, 14:37


የዕለቱ አበይት ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም

1. ኢትዮጵያ ያለባት አጠቃላይ ዕዳ በ5 ዓመታት ውስጥ በ2 ትሪሊዮን ብር ጨምሯል ተባለ፡፡ አጠቃላይ ዕዳው ከ5 ዓመታት በፊት ከነበረበት 1.9 ትሪሊዮን ብር ወደ 3.9 ትሪሊዮን ብር አድጓል ተብሏል፡፡ የሀገሪቱ አጠቃላይ አመታዊ የሀገር ውስጥና የውጭ የዕዳ ምጣኔ ተንትኖ ያቀረበው የገንዘብ ሚኒስቴር ሪፖርት የአገር ውስጥ ዕዳ የጂዲፒውን 19 በመቶ፤ የውጭ ዕዳው ደግሞ 13.9 በመቶ ድርሻ ስለመውሰዳቸው ይጠቁማል። ሪፖርቱ ባለፉት 5 ዓመታት የታየው የውጭ ምንዛሪ ተመን መዋዠቅ ለዕዳ ግሽበቱ አንድ ምክንያት ስለመሆኑም አመልክቷል።

2. የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) በትግራይ ክልል ከመጪው ሀገራዊ ምርጫ በፊት አስቸኳይ ምርጫ እንዲደረግ ጥሪ አቀረበ፡፡ ኢህአፓ ጥሪ ያቀረበው በክልሉ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ‹‹የትግራይ ህዝብ አሳር ሊያበቃ ይገባል›› ሲል ዛሬ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ/ም ባወጣው መግለጫ ነው፡፡ መግለጫውን የተመለከተ ማብራሪያን ለሚዲያዎች የሰጠው ኢህአፓ የትግራይ ህዝብ በእንደራሴዎቹ እስከሚወከል ድረስ ሁሉንም ፓርቲዎች ያካተተ ምክር ቤት እንዲቋቋም ጥሪ አቅርቧል። የምክር ቤቱ አባል መሆን እንደሚፈልግም ነው ያስታወቀው።


3. የአብን የፓርላማ ተወካዩ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠየቁ፡፡ በየቦታው በመካሄድ ላይ ያሉ ግጭቶች መቆም አለባቸው ያሉት የፓርላማ አባሉ በየቀኑ ውጊያ እየተካሄደ ባለበት ሁኔታ ምክክር ማድረግ አስቸጋሪ ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም ‹‹ለምክክር ቢያንስ ተኩስ አቁም መደረግ››  እንዳለበት ገልጸው ጊዜያዊ ተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠይቀዋል፡፡ ዶ/ር ደሳለኝ  ይህን የጠየቁት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባዘጋጀውና በብሄራዊ መግባባት ላይ አተኩሮ ዛሬ ረቡዕ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ/ም በተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ ነው፡፡

4. የተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎችን የሚያቋርጡ የውሀ ተፋሰሶች የጋራ አጠቃቀምን የተመለከተ ከፍተኛ ምክር ቤት ሊቋቋም ነው፡፡ ምክር ቤቱ ከአንድና ከዚያ በላይ ክልሎችን የሚያቋርጡ 12 የሀገሪቱን የውኃ ተፋሰሶች የሚመለከት ነው የተባለ ሲሆን ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡ ምክር ቤቱን በተመለከተ በቀረበ የማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከትናንት በስቲያ ሰኞ በፓርላማ ህዝባዊ ውይይት መደረጉን የዘገበው ሪፖርተር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምክር ቤቱ ሰብሳቢ፤ 12ቱን ተፋሰሶች የሚጋሩት ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች ደግሞ አባል እንደሚሆኑ ጠቁሟል፡፡

5. አይ.ኤም.ኤፍ መንግሥትን ወቀሰ፡፡ አይ.ኤም.ኤፍ መንግስትን የወቀሰው የሴፍቲ ኔት መርሀግብርን ለማስፋፋት የገባውን ቃል አላከበረም በሚል ነው፡፡ ይህ በመሆኑ በማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ የተጎዱ ወገኖችን በወጉ ለመደጎም ሳይችል ቀርቷል ብሏል፡፡ አይ.ኤም.ኤፍ ይህን ያለው ባሳለፍነው አርብ ሪፎርሙን ለመደገፍ በሚል ለመንግስት ለመስጠት ከተስማማው 3.4 ቢሊዬን ዶላር ብድር ውስጥ 248 ሚሊዮን ዶላሩን ለመልቀቅ መወሰኑን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ነው፡፡


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #Dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Jan, 11:57


ስደተኞችን አሳፍራ የነበረች መርከብ በደረሰባት አደጋ 20 ኢትዮጵያውያን ህይወታቸው አለፈ

ከጅቡቲ የተነሳች ስደተኞችን የጫነች መርከብ የመን አቅራቢያ በደረሰባት የመስጠም አደጋ ቢያንስ 20 ኢትዮጵያውያን ሕይወታቸው ማለፉን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አሳወቀ።

ከአደጋው 15 ኢትዮጵያውያን እና ሁለት የመናውያን የጀልባዋ ቀዛፊ እና ረዳቱ መትረፋቸውም ተገልጿል።

35 ስደተኞችን አሳፍራ ከጅቡቲ የተነሳችው ጀልባ ዱባብ አቅራቢያ ባጋጠማት ብርቱ ነፋስ ለአደጋው መጋለጧን ዓለም አቀፉ ድርጅት አመልክቷል።

በየመናዊ ካፒቴን እና ረዳቱ አማካኝነት ከጅቡቲ የባሕር ጠረፍ ጀልባዋ ስደተኞች አሳፍራ ቅዳሜ ዕለት በምሽት ነበር ጉዞ የጀመረችው።

አደጋው በርካታ ስደተኞች የሚጋፈጡትን አሳዛኝ አደጋ እንደሚያሳይ የገለጸው ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለሕገወጥ ስደት መንስኤ ለሆኑ ችግሮች መፍትሔ እንዲፈልጉ ጥሪውን አቅርቧል።

በርካታ ኢትዮጵያውያን የተሻለ የኑሮ ሁኔታ ፍለጋ በጅቡቲ በኩል ወደ የተለያዩ የአረብ ሃገራት እንደሚሰደዱ በተደጋጋሚ ይነገራል።

ባለፈው ጥቅምት ወርም በተመሳሳይ አደጋ ከጅቡቲ የተነሱ 45 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የተሳፈሩበት ጀልባ በደረሰበት አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ይታወሳል። 

የየመን ባሕር አካባቢ ለስደተኞች አደገኛ ከሆኑ የባሕር መስመሮች አንዱ መሆኑን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አመልክቷል።

ኢትዮጵያውን ስደተኞች ላይ ስለደረሰው አደጋ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተሰማ ነገር የለም።

#DW

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Jan, 11:34


የ80 ዓመት አዛውንትን አስገድዶ የደፈረዉ ተከሳሽ በ10 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ

በጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ በ 80 ዓመት አዛውንት ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በ 10 ዓመት ፅኑ እስራት እንድቀጣ ፍርድቤቱ ወስኗል።

ወንጀሉ የተፈፀመው ህዳር 5 ቀን 2017 ዓ.ም በጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ ሚችሌ ሆለና አከባቢ ስሆን ተከሳሽ ወጣት ቶሎሳ ዘውዴ የተባለው ግለሰብ ከምሽቱ 6 ሰዓት ላይ የ 80 ዓመት አዛውንት ብቻቸውን ሚኖሩበትን መኖሪያ ቤት ሰብሮ በመግባት ድርግቱን መፈፀሙን በክሱ መዝገብ ላይ ተጠቅሷል ።

የወረዳ ፖሊስ ግለሰቡን በቁጥጥር ስር አዉሎ ወንጀሉ መፈፀሙን የሚያስረዱ የሰውና የሠነድ ማስረጃዎችን አደራጅቶ ለዐቃቤ ህግ አቅርቧል ተብሏል።

ዐቃቤ ህግ ፣ ተከሳሹ አዛውንቷ በቤቷ ለብቻ እንደምትኖር አውቀው ቤት ሰብሮ በመግባት መከላከል በማትችልበት ሁኔታ ድርጊቱን እንደፈፀመ የሚያስረዱ ማስረጃዎች አስደግፎ ለዲላ ዙሪያ ወረዳ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ክሱን አቅርቧል።

ዐቃቤ ህግ ያቀረበውን ማስረጃ የተመለከተው የዲላ ዙሪያ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤት ተከሳሽ ወጣት ቶሎሳ ዘውዴ የተባለው ግለሰብ የፈፀመውን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ድርጊት  በምስክር እና በህክምና ማስረጃ በማረጋገጥ ጥር 14  ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሹ በ 10 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ፍርድቤቱ ወስኗል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#Rape #ethiopia #crime

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

13 Jan, 16:00


የዕለቱ አበይት ዜናዎች

አዲስ አበባ፣ ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 05 ቀን 2017 ዓ.ም

1. በሊባኖስ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
በሊባኖስ በአስቸጋሪ ሁኔታ የነበሩ እና ለአደጋ የተጋለጡ 164 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ተመለሾቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን፣ የፌዴራል ፖሊሲ ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቆንስላ ጉዳዬች ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ሲራጅ ረሽድ አቀባባል አድርገውላቸዋል ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

2. የኢትዮ-ጂቡቲ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትርፋማነት መግባቱ ተገለጸ
የኢትዮ-ጂቡት ባቡር መስመር በ2024 የመጨረሻው ሩብ ዓመት ወደ ትርፋማነት መግባቱን የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታከለ ኡማ (ኢ/ር) ገለጹ፡፡
አሁን እያሳየ ያለው ትርፋማነት ድርጅቱ ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ አንስቶ ከፍተኛው መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጠቅሰው፤ ይህ ስኬት ኩባንያውን አትራፊ ለማድረግ የተያዘው የሦስት ዓመት ስትራቴጂያዊ እቅድ እንደሚሳካ ማሳያ ነው ብለዋል።


3. 300 የሰሜን ኮርያ ወታደሮች  በዩክሬን ሲዋጉ መገደላቸዉን ተነገረ

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር እያካሄደችዉ ባለዉ ጦርነት 300 የሚሆኑ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ተገድለዋል ሲል የደቡብ ኮሪያ ህግ አውጪ አስታዉቋል።ከሴኡል ብሔራዊ መረጃ አገልግሎት (ኤንአይኤስ) አጭር መግለጫ በኋላ 300 የሰሜን ኮርያ ወታደሮች መገደላቸዉን እና ወደ 2,700 የሚጠጉ ደግሞ ቁስለኛ ስለመሆናቸዉ የደቡብ ኮሪያ ህግ አውጪ አባል ሊ ሴኦንግ-ኩዌን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ሰኞ ዕለት ተናግረዋል።
የደቡብ ኮሪያ ፖለቲከኛ መግለጫ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ኪየቭ ሁለት የሰሜን ኮሪያ ወታደሮችን መያዟን በመግለጽ ጉዳት የደረሰባቸውን ተዋጊዎች ሲጠየቁ የሚያሳይ ቪዲዮ በለቀቁ ከቀናት በኋላ ነው።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

13 Jan, 13:47


አዲስ አበባ የጦር መሳሪያ በታጠቁ ድሮኖች ትጠበቃለች ተባለ

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአዲ አበባ የታጠቁ ድሮኖችን ለጸጥታ ስራ እንደሚጠቀም አስታውቋል፡፡

የአዲስ አበባ አስተዳደር የከተማዋን ፀጥታ ሁኔታና ትራፊክ ፍሰት ለመቆጣጠር ይሰማራሉ የተባሉ ድሮኖች ቁጥጥር ብቻ ሳይሆን እርምጃም እንደሚወስዱ አስታውቋል።

የትራፊክ ፍሰት እና በበዓላት ወቅት የከተማዋን ጸጥታ ለመቆጣጠር በርካታ ድሮኖች መግባታቸው እና የሚቆጣጠሯቸው ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች ስልጠና አጠናቅቀው በቀጣይ ጥቂት ቀናት ውስጥ ወደ ስራ እንደሚገቡ ተገልጿል፡፡

ድሮኖቹ የከተማዋን ፀጥታ ሁኔታና የትራፊክ ፍሰት ከመቆጣጠር ባሻገር እርምጃም እንደሚወስዱ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ተናግሯል፡፡

በቅርብ ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ የትራፊክ ፍሰትና አጠቃላይ የፀጥታ ሁኔታ እንዲሁም ታላላቅ ፕሮግራሞችን ቁጥጥር ማድረግ የሚችሉ የድሮኖች ስምሪት እንደሚደረግ፣ የፀጥታ ጥምር ግብረ ኃይል ከቀናት በፊት መግለጹ ይታወቃል፡፡

አሁን ላይ በርካታ ድሮኖች አገር ውስጥ መግባታቸውን እና የሚቆጣጠሯቸው ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች ስልጠና አጠናቅቀው በቀጣይ ጥቂት ቀናት ወደ ስራ እንደሚገቡ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ ለመናኸሪያ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

ድሮኖቹ ቀድሞ ስምሪት ተሰጥቷቸው ለዋናው መስሪያ ቤት መረጃ የሚያቀብሉ ሲሆን መረጃ ከመስጠት ባሻገር ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸው አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ፈጣን እርምጃ እንደሚወስዱም አቶ ጄይላን ተናግረዋል፡፡

ድሮኖቹ ከመደበኛ የካሜራ ድሮኖች የተለዩ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊው ለፖሊስ ወንጀል መከላከል፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተሰሩ ናቸውም ብለዋል፡፡    
         
ከዚህ ቀደምም በተለያዩ ህዝባዊ እና ኃይማኖታዊ በዓላት ላይ በድሮኖች የጸጥታ ሁኔታ ክትትል ይደረግ እንደነበር የገለጹት አቶ ጄይላን፣ የተለየ ነገር እንደማይፈጠር እና ህዝብን በማይረብሽ መልኩ ስራው እንደሚከናውን አመላክተዋል፡፡

አዲስ አበባ በተያዘው ጥር ወር ውስጥ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤን ጨምሮ በርካታ ህዝብ የሚሰበሰብባቸው ህዝባዊ በዓላት የሚከበሩበት ወር ነው፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #addisababa #Drones #Police

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

13 Jan, 05:23


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም

1. በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲደረግ ሲወተውቱ የነበሩት አሜሪካዊው ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የ15 ዓመታት እስር እንዲተላለፍባቸው ተጠየቀ። የአሜሪካ ህግ አውጪ ምክር ቤት አባል የነበሩት ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ ከግብጽ ጉቦ መቀበላቸው ተረጋግጧል። ሴናተሩ ከግብጽ ጉቦ የተቀበሉት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ወደ ስምምነት እንድትመጣ ጫና እንዲያደርግ በሚል ነው። ፖለቲከኛው በዚህ ጥፋታቸው የ15 ዓመት እስር እንዲተላለፍባቸው አቀቢ ህጎች ለፍርድ ቤት ጥያቄ አቅርበዋል።

2. ሲዳማ ክልል እንዲሆን ብዙ ዋጋ ብንከፍልም የጠበቅነውን ለውጥ ማየት አልቻልንም ሲሉ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ነዋሪዎች እንዳሉት ሲዳማ ክልል እንዲሆን የህይወት ፣ ንብረት እና አካል ጉዳት ያስተናገድን ቢሆንም አስተዳድሩ በቂ የስራ እድል እየፈጠረ አይደለም፣ ለአገልግሎት ወደ መንግሥት ቢሮዎች ስንሄድም ሙስና እንጠየቃለን፣ የንግድ እንቅስቃሴዎች ተዳክመዋል ሲሉም ነዋሪዎች ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት ግን በዓመት ከ60 ሺህ በላይ የስራ እድል እየፈጠርኩ ነው፣ ህዝባዊ ውይይቶችን እያደረግሁ ነው፣ ዜጎች የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኙ እና ምርታማነት እንዲጨምር ማድረጉን አስታውቋል።የፖለቲካ ፓርቲዎች በበኩላቸው የክልሉ መንግሥት ያስገኛቸው መልካም ውጤቶች ቢኖሩም የመልካም አስተዳድር ችግሮች እንዳሉ ተናግረዋል። ፓርቲዎቹ የሲዳማ ህዝብ ጥያቄ ክልል እንሁን ከሚል ወደ ልማት ጥያቄ ዞሯልም ብለዋል።

3.የናይጀሪያው ፈርስት ባንክ በኢትዮጵያ የመሰማራት ፍላጎት እንዳለው አስታውቋል። ኢትዮጵያ በሯን ለውጭ ባንኮች ክፍት ማድረጓን ተከትሎ የተለያዩ የውጭ ባንኮች እንደሚገቡ በመግለጽ ላይ ናቸው። አሁን ደግሞ የናይጀሪያው ፈርስት ባንክ ኢትዮጵያን ጨምሮ በአንጎላ እና ኮትዲቯር የመስራት ፍላጎት እንዳለው የብንኩ ምክትል ሀላፊ ለአፍሪካን ሪፖርት ተናግረዋል። የኬንያው ኬቢሲ፣ የደቡብ አፍሪካው ስታንዳርድ ባንክ እና ሌሎችም በኢትዮጵያ ፍላጎት ካሳዩ ባንኮች መካከል ዋነኞቹ ናቸው።

4. በአዲስ አበባ ከ41 ባቡሮች የሚሰሩት 16ቱ ብቻ ናቸው ተብሏል።የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ካሉት 41 ባቡሮች ከግማሽ በላይ ያህሉ ስራ እንሳቆሙ አስታውቋል።ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ባቡሮች አገልግሎት የማይሰጡት በብልሽት  ምክንያት ነው ተብሏል።ባቡሮቹ ብልሽት በሚያጋጥማቸው ጊዜ የጥገና ዕቃዎች ገበያ ላይ ባለመኖራቸው ችግሩን ለመፍታት ከአንዱ ባቡር እየተነቀለ ወደ ሌላኛው ሲገጠም እንደነበርም ተገልጿል።


5. በአሜሪካዋ ሎሳንጀለስ ያጋጠመው እሳት አደጋ አሁንም መቆጣጠር አልተቻለም። ከአንድ ሳምንት በላይ የቆየው ይህ አደጋ እስካሁን 16 ሰዎችን ሲገድል፣ ከ100 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን አፈናቅሏል። እንዲሁም አደጋው ከ150 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት ንብረት ያወደመ ሲሆን እሳቱን ለመቆጣጠር ጥረቱ እንደቀጠለ ይገኛል። የእሳት አደጋው ትክክለኛ መነሻ እስካሁን እንዳልታወቀም ሲኤንኤን ዘግቧል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #morningnews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

12 Jan, 19:46


ያልተመዘገቡ ተማሪዎች ፈተና ላይ አይቀመጡም ተባለ

የ2017 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (የ12ኛ ክፍል) ፈተና ምዝገባ እስከ መጪው ማክሰኞ ጥር 6/2017 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ እንደሚጠናቀቅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ።

በተለያየ ምክንያት ያልተመዘገቡ ተማሪዎች ካሉ በቀጣዮቹ ሁለት ቀናት እንዲመዘገቡ ያሳሰበው አገልግሎቱ፤ ያልተመዘገቡ ተማሪዎች ፈተናውን እንደማይፈተኑ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው መልዕክት አስጠንቅቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

12 Jan, 17:57


አርሰናል በማችስተር ዩናይትድ ተሸንፎ ከኤፍኤካፕ ዋንጫ ተሰናበተ።

በኤፍኤካፕ ዋንጫ የተገናኙት አርሰናል እና ማንችስተር ዩናይትድ ያደረጉት ጨዋታ ዩናይትድ አሸንፏል።

ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ ያመሩት ሁለቱ ክለቦች ወደ መለያ እምት አምርተዋል።

የአርሰናሉ ካይ ሀቨርትዝ ፍጹም ቅጣት ምት መሳቱን ተከትሎ ማንችስተር ዩናይትድ ቀጣዩን  ዙር ተቀላቅሏል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

12 Jan, 07:29


በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸነፉ።

በዚህም በሁለቱም ጾታ ከአንደኛ እስከ አስረኛ ድረስ ያለውን ደረጃ በመያዝ በፍጹም የበላይነት ውድድሩን አጠናቀዋል።

ውድድሩን በሴቶች አትሌት በዳቱ ሂርጳ በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ፥ በወንዶች ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በማራቶን የተሳተፈው አትሌት ቡቴ ገመቹ አንደኛ ወጥቷል::

አትሌት ቡቴ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2:04:50 የሆነ ጊዜ የፈጀበት ሲሆን 80 ሺ የአሜሪካን ዶላር ተሸላሚ ሆኗል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

11 Jan, 20:06


ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ተስማሙ

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ተስማምተዋል፡፡

ሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማሻሻል በቁርጠኝነት እንደሚሰሩም አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መንግሥታት የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ማምሻውን አዲስ አበባ ለገቡት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ዛሬ በአዲስ አበባ የጋራ ፍላጎታቸው በሆኑ የተለያዩ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

መሪዎቹ የሀገራቱን ህዝቦች የወንድማማችነት ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችል ውይይት ማድረጋቸውም ተገልጿል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

11 Jan, 15:41


የሶማሊያዉ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ አዲስአበባ ገቡ

የሶማሊያዉ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ አዲስአበባ ገብተዋል።

ጠ/ሚ ዐቢይ በአጭሩ ለፕሬዚዳንቱ የእንኳን ደህና መጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የሶማሊያዉ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ገብታ የነበረዉን የባህር በር ለማግኘት የሚያስችል ስምምነትን ተቀባይነት የሌለዉ መሆኑን በተደጋጋሚ ሲገልጹ የነበረ እና ኢትዮጵያንም በአለማቀፍ መድረኮች ላይ ሲከሱ መቆየታቸው ይታወሳል።

በቅርቡ በአንካራ ቱርክ አሸማጋይነት በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል የተፈጠረውን ዉጥረት ለማርገብ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።

የፕሬዚዳንቱ ጉብኝት እና በአዲስ አበባ ስለሚኖራቸው ቆይታ እስካሁን የተገለጸ ነገር የለም።

#ethiopia #somalia

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

11 Jan, 13:41


መንግሥት የጎዳና ተዳዳሪዎችን በግዴታ ወደ ማጎሪያ ስፍራ እያስገባ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በታኅሣሥ ወር ባደረኳቸው ክትትሎች በአዲስ አበባ ቃሊቲ አካባቢ በሚገኘው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አጠገብ በሰፊ መጋዘን ውስጥ ከጎዳና ላይ የተነሱ በርካታ ሰዎች ተይዘው እንደሚገኙ ገልጿል ።

ኢሰመኮ፣ ሰዎችን የመያዝና ወደ ማቆያ ቦታ የማስገባት ድርጊት መቀጠሉን ተረድቻለሁም ብሏል።

ወደ ማቆያ ማዕከሉ ከገቡት መካከል፣ በተለያዩ አካባቢዎች ወደሚገኙ የእርሻ ጣቢያዎች ተወስደው እንዲሠሩ የተደረጉ እንደሚገኙበት የጠቀሰው ኢሰመኮ፣ ድርጊቱ የሰዎቹን ሰብዓዊ መብቶች የሚጥስ መሆኑን አስታውቋል፡፡

የኢሰመኮ ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሠለ፣ መንግሥት ውሎና አዳራቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ ሰዎችን በግዳጅ ወደ ማቆያ አስገብቶ መያዝ ወይም ያለፍቃዳቸው ወደተለያዩ አካባቢዎች መውሰዱን እንዲያቆም አሳስበዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #Humanrights

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Jan, 17:10


የአቶ ቡልቻ ደመቅሳ የቀብር ስነ-ስርዓት የፊታችን እሁድ ይፈፀማል

የአንጋፋው ፖለቲከኛ እና የምጣኔ ሀብት ባለሙያ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ የቀብር ስነ-ስርዓት በመጪው እሁድ ጥር 4 ቀን 2017 ዓ.ም ይፈፀማል፡፡  

በዕለቱ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ የእርሳቸውን ክብር በሚመጥን መልኩ የአስክሬን ሽኝት እንደሚደረግም ተገልጿል፡፡  

ከሽኝቱ በኋላ የቀብር ስነ-ስርአቱ ቤተሰቦቻቸው፣ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት እሁድ ከቀኑ 7 ሰዓት በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር እንደሚፈፀም ታውቋል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Jan, 17:08


በመዲናዋ የድሮን ስምሪት ሊደረግ ነው

በአዲስ አበባ ከተማ በቅርብ ቀናት የትራፊክ ፍሰትና አጠቃላይ የፀጥታ ሁኔታ እንዲሁም ታላላቅ ፕሮግራሞችን ቁጥጥር ማድረግ የሚችሉ የድሮኖች ስምሪት እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ገለፁ፡፡

የፀጥታ ጥምር ኃይል በአዲስ አበባና ዙሪያዋ ያለውን የፀጥታ ሁኔታን በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መሥሪያ ቤት በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጧል። 

ግምገማውን የመሩት ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የወንጀል መከላከል ሥራችንን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ የሚችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ 

አያይዘውም ከ15 ቀን በፊት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የከተማችን ሰላምና ደህንነት ዘላቂ እንዲሆን የፀጥታ ጥምር ኃይሉ ተቀናጅቶ በመሥራቱ ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ 

በዚህም አሁን ላይ በአዲስ አበባ ምቹ የፀጥታ ሁኔታ ያለበትና በቀጣይ በሀገራችን የሚከበረው የጥምቀት በዓል እና የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ በሰላም እንዲጠናቀቁ ከወዲሁ ይህንን የሚመጥን ዝግጅት መደረጉን ገልፀዋል፡፡


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Jan, 15:44


የዕለቱ አበይት ዜናዎች

አዲስ አበባ፣ ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም

1. ኢትዮጵያ የስቶክ ማርኬት ገበያን ከ50 ዓመት በኋላ ዳግም አስጀመረች::
ኢትዮጵያ በአጼ ሀይለስላሴ አስተዳድር ዘመን የስቶክ ግብይት የሚፈቅድ ስርዓት የነበራት ቢሆንም በደርግ ዘመን ተቋርጦ ነበር፡፡
አሁን ደግሞ ከ50 ዓመት በኋላ ዳግም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ አስጀምረዋል፡፡
በዚህ የግብይት ስርዓት መሰረት ኩባንያዎች አክስዮኖቻቸውን በይፋ ለገዢዎች መሸጥ የጀመሩ ሲሆን ሸማቾች ደግሞ ለሚገዙት አክስዮን ዋስትና የሚሰጥ ተቋምም ወደ ስራ ገብቷል፡፡
ይህን የአክስዮን ግብይት የሚያሳልጡ ሁለት መንግስታዊ ተቋማት የተቋቋሙ ሲሆን የኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት እና የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ነዋዮች ገበያ ናቸው።

2. ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ካምፓላ ገቡ
የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በአፍሪካ ህብረት ልዩ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ በዛሬው ዕለት ዩጋንዳ ካምፓላ ገብተዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ  ኢንተቤ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የሀገሪቱ መከላከያና የአርበኞች ጉዳይ ሚኒስትር ጃኮብ ማርክሰንስ ኦቦት አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን  በቆይታቸው በአፍሪካ አስተማማኝ የግብርናና የምግብ ሥርዓት መገንባት በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው የድህረ ማላቦ አጠቃላይ የአፍሪካ ግብርና ልማት ፕሮግራም አፈጻጸም መድረክ ላይ ይሳተፋሉ።

3. ታግተው የነበሩ 26 ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራዎች ተለቀቁ።
የደቡብ አፍሪቃ ፖሊስ እንዳስታወቀው የጉዞ ሰነድ ያልነበራቸው እና በህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ታግተው የነበሩ 26 ኢትዮጵያዉያንን ማስለቀቁን ገልጿል።
ነጻ የወጡት ኢትዮጵያዉያኑ በጆሃንስበርግ ከተማ ዳርቻ በሚገኝ አንድ ቤት ውስጥ እርቃናቸውን ታግተዉ እንደነበር ዶቸ ቪሌ ዘግቧል።
ነጻ ከወጡት ታጋች  ኢትዮጵያዉያን መካከል የጤና መታወክ የገጠማቸው አስራ አንዱ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።ከዚህ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ጋር በተያያዘ የሀገሪቱ ፖሊስ ሦስት ኢትዮጵያዉያንን በቁጥጥር  ስር ማዋሉን አስታውቋል።
ኢትዮጵያዉያንን ጨምሮ ስራ እና የተሻለ ኑሮ ፍለጋ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞች ከተለያዩ የአፍሪቃ ሀገራት በህገ ወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪቃ እንደሚጓዙ ዘገባው አስታውሷል።

4. ምክንያቱ ባልታወቀ እሳት ቃጠሎ የሰብል ክምር ወደመ።
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በዋድላ ወረዳ 11 ቀበሌዎች ጥር 1/2017 ዓ.ም በደረሰው “ምክንያቱ ባልታወቀ” የእሳት ቃጠሎ የ154 አርሶ አደሮች የሰብል ክምር መቃጠሉ ተገልጿል፡፡
የዋድላ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ሙሉየ ረታ 4 ሺህ 560 ኩንታል የሚሆን 152 ክምር ላይ የደረሰው ቃጠሎ ጉዳት ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት ጠቁመዋል፡፡


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Jan, 15:13


ምክንያቱ ባልታወቀ እሳት ቃጠሎ የሰብል ክምር ወደመ።

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በዋድላ ወረዳ 11 ቀበሌዎች ጥር 1/2017 ዓ.ም በደረሰው “ምክንያቱ ባልታወቀ” የእሳት ቃጠሎ የ154 አርሶ አደሮች የሰብል ክምር መቃጠሉ ተገልጿል፡፡

የዋድላ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ሙሉየ ረታ 4 ሺህ 560 ኩንታል የሚሆን 152 ክምር ላይ የደረሰው ቃጠሎ ጉዳት ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት ጠቁመዋል፡፡

በዚህ ቀበሌ ብቻ የ52 አርሶ አደሮች የሰብል ክምር ሙሉ በሙሉ ሲቃጠል በቤተሰብ ደረጃም ከ260 በላይ የቤተሰብ አባላት ጦም ለማደርና ልመና ለመውጣት እንደሚገደዱ የአካባቢው የህብረተሰብ ክፍሎች ተናግረዋል።

የዋድላ ወረዳ የአደጋ መከላከል እና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ጽሕፈት ቤት ቡድን መሪ ምትኩ ሞላ በበኩላቸው እስካሁን ባለው መረጃ 770 የሚሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች የጉዳቱ ሰለባ መሆናቸውን መግለጻቸውን አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘግቧል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Jan, 15:00


ታግተው የነበሩ 26 ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራዎች ተለቀቁ

በደቡብ አፍሪካ ይኖሩ የነበሩ 26 ኢትዮጵያዊያን በህገ ወጥ አዘዋዋሪዎች ታግተው ነበር ተብሏል።

የደቡብ አፍሪቃ ፖሊስ እንዳስታወቀው የጉዞ ሰነድ ያልነበራቸው እና በህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ታግተው የነበሩ 26 ኢትዮጵያዉያንን ማስለቀቁን ገልጿል።

ነጻ የወጡት ኢትዮጵያዉያኑ በጆሃንስበርግ ከተማ ዳርቻ በሚገኝ አንድ ቤት ውስጥ እርቃናቸውን ታግተዉ እንደነበር ዶቸ ቪሌ ዘግቧል።

የደቡብ አፍሪቃ ፖሊስ የቅድመ ወንጀል መከላከል ክፍል እንዳለው ፖሊስ ታጋቾች ወደነበሩበት ህንጻ በደረሰበት ወቅት ታግተው ከነበሩ ሰዎች በተጨማሪ 30 ያህል ሰዎች መስኮት ሰብረው ሳያመልጡ አልቀረም።

ፖሊስ ታጋቾችን ለማስለቀቅ የአካባቢው ነዋሪዎች ያልተለመደ እንቅስቃሴ መመልከታቸውን ተከትሎ ጥቆማ ከሰጡ በኋላ እርምጃ መውሰዱን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘገባ ያመለክታል።

ታጋቾቹ ለምን ያህል ጊዜ ታግተው እንደነበሩ አልተገለጸም ። ነገር ግን ነጻ ከወጡት ታጋች  ኢትዮጵያዉያን መካከል የጤና መታወክ የገጠማቸው አስራ አንዱ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።ከዚህ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ጋር በተያያዘ የሀገሪቱ ፖሊስ ሦስት ኢትዮጵያዉያንን በቁጥጥር  ስር ማዋሉን አስታውቋል።

ባለፈው የነሐሴ ወር 2016 በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 80 ሰነድ አልባ ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች ማስለቀቁን የጠቀሰው የሀገሪቱ ፖሊስ በወቅቱ ታጋቾቹ ያለ በቂ ምግብ እና ዉሃ ኢሰብአዊ በሆነ መንገድ ታጉረው እንደነበር አስታውሷል።

ኢትዮጵያዉያንን ጨምሮ ስራ እና የተሻለ ኑሮ ፍለጋ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞች ከተለያዩ የአፍሪቃ ሀገራት በህገ ወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪቃ እንደሚጓዙ ዘገባው አስታውሷል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Jan, 14:36


ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ካምፓላ ገቡ

የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በአፍሪካ ህብረት ልዩ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ በዛሬው ዕለት ዩጋንዳ ካምፓላ ገብተዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ  ኢንተቤ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የሀገሪቱ መከላከያና የአርበኞች ጉዳይ ሚኒስትር ጃኮብ ማርክሰንስ ኦቦት አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን  በቆይታቸው በአፍሪካ አስተማማኝ የግብርናና የምግብ ሥርዓት መገንባት በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው የድህረ ማላቦ አጠቃላይ የአፍሪካ ግብርና ልማት ፕሮግራም አፈጻጸም መድረክ ላይ ይሳተፋሉ፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Jan, 14:27


ኢትዮጵያ የስቶክ ማርኬት ገበያን ከ50 ዓመት በኋላ ዳግም አስጀመረች

ኢትዮጵያ በአጼ ሀይለስላሴ አስተዳድር ዘመን የስቶክ ግብይት የሚፈቅድ ስርዓት የነበራት ቢሆንም በደርግ ዘመን ተቋርጦ ነበር፡፡

አሁን ደግሞ ከ50 ዓመት በኋላ የስቶክ ግብይትን ዳግም ያስጀመረች ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ አስጀምረዋል፡፡

በዚህ የግብይት ስርዓት መሰረት ኩባንያዎች አክስዮኖቻቸውን በይፋ ለገዢዎች መሸጥ የጀመሩ ሲሆን ሸማቾች ደግሞ ለሚገዙት አክስዮን ዋስትና የሚሰጥ ተቋምም ወደ ስራ ገብቷል፡፡

ይህን የአክስዮን ግብይት የሚያሳልጡ ሁለት መንግስታዊ ተቋማት የተቋቋሙ ሲሆን የኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት እና የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ነዋዮች ገበያ ናቸው፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Jan, 10:27


ትናንት ምሽት በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የታዩት ቁስ አካላት ተፈጥሯዊ ወይም ሰው ሰራሽ ቁስ አካል ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል፡፡

ትናንት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸው ይታወቃል፡፡

በኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የአስትሮኖሚና አስትሮ ፊዝክስ ተመራማሪ ገመቹ ሙለታ (ዶ/ር) ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ትናንት ምሽት ሰማይ ላይ ሲንቀሳቀስ የታየው ተቀጣጣይ ቁስ አካል በሁለት መንገድ ሊገመት ይችላል፡፡

አንደኛው መላምት ተፈጥሯዊ የሰማይ አካል ሊሆን እንደሚችል እና ሌላኛው ደግሞ ሰው ሰራሽ ቁስ አካል ሊሆን እንደሚችል አስረድተዋል፡፡

እነዚህ ቁሶች በመሬት ስበት ውስጥ ሲገቡ በከባቢ አየር ሰበቃ ምክንያት እንደሚቃጠሉ የሚናገሩት ተመራማሪው በዚህ ወቅትም ቃጠሎው እንደሚታይ አስረድተዋል፡፡
አስትሮይድን ጨምሮ ሌሎች ተፈጥሯዊ የሰማይ አካላት የሚባሉት በብዛት በማርስና በጁፒተር መካከል እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡

እነዚህ አካላትም ልክ እንደ መሬት ጸሃይን ይዞራሉ፤ በዚህ ወቅትም በአጋጣሚ በመሬት ስበት ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉና በዚህ ወቅትም በመሬት ከባቢ አየር ሰበቃ ምክንያት ውጫዊ አካላቸው ይቃጠልና እሳት እንደሚታይ ተናግረዋል፡፡
ውስጣዊ አካላቸው ደግሞ በብረት ወይም ሲልኬት የተሞላ በመሆኑ መሬት ላይ ሊደርስ እንደሚችል ጠቅሰዋል፡፡

ሰው ሰራሽ አካል ከሆነ ደግሞ ህዋ ላይ የሚንቀሳቀሱ ነገሮች ሊኖሩ ስለሚችሉ ወደ ከባቢ አየር ውስጥ ሲገቡ የመቃጠል እና ተሰባብሮ የመውረድ ምልክቶችን እንደሚያሳዩ አስገንዝበዋል፡፡
ስለሆነም ክስተቱ በቤተ ሙከራ ተጠንቶ ወይም በባለሞያዎች በዘርፉ መሳሪያ ታይቶ እስካልተረጋገጠ ድረስ አስትሮይድ ነው ወይም ሰው ሰራሽ አካል ነው ብሎ መደምደም እንደማይቻል አስረድተዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

10 Jan, 04:44


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

አዲስ አበባ፣ ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም

1. ትናንት ምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገራችን ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸው ተገልጿል። የኢትዮጵያ  ስፔስ ሳይንስ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ስብስቦቹ የጠፈር ፍርስራሾች አልያም የሚቲዮር አለቶች ሊሆኑ ይችላሉ ብሏልይ። ስብስቡ ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ እንደነበረም ለማወቅ ተችሏል ብሏል። የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት ያስችለን ዘንድ ሁኔታውን በቅርበት እያጣራን ነው ያለው ተቋሙ ወቅታዊ መረጃዎች እንደሚያደርስም አስታውቋል።


2. በዝነኛው የኢትዮጵያ ሙዚቀኛው ማህሙድ አህመድ የህይወት ታሪክ ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገው መጽሀፍ ተመርቋል። በርካታ እንግዶች በተገኙበት በዚህ መጽሀፍ ምረቃ ስነ ስርዓት ላይ የሙዚቀኛው የሙያ አጋሮች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ ነጋዴዎች እና በርካታ ተጽእኖ ፈጣሪ ሰዎች ተገኝተዋል። ንብ ባንክ በ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የመጽሀፉን  ሕትመት ስፖንሰር ማድረጉም ተገልጿል። ተጨማሪ መጽሐፍ ከገዙት መካከልም አቶ ሳሙኤል ታፈሰ የሰንሻይን ሪል ስቴት ባለቤት 100 መጽሐፍትን በ500 ሺ ብር ገዙ ገዝተዋል። መጽሀፉ የክቡር ዶክተር አርቲስት መሀሙድ አህመድ
ላለፉት 63 ዓመታት በሙዚቃው ዓለም ያሳለፋቸዉን ውጣ ውረዶች ፣ የቤተሰብ የኋላ ታሪክና የወዳጅ ጓደኞቹን እንዲሁም የሙያ ባልደረባዎቹን ምስክርነት አካቶ ይዟል። የሕይወት ታሪክ መፅሐፉ በጋዜጠኛና ደራሲ ወሰን ደበበ ማንደፍሮ ተዘጋጅቷል።

3. የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ቅንጡ አፖርታማዎችን ሊገነባ ነው ይፋ አድርጓል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የሚመራው የጫካ ፕሮጀክት አረንጓዴ ልማት ፕሮግራም የቅንጦት ቤቶች ግንባታ በኦቪድ ሪልስቴት እንደሚያከናውን ተሰምቷል።ሪልስቴቱ የጫካ ፕሮጀክት የመኖሪያ አፖርትመንት ማስጀመሪያና የሽያጭ ቢሮ ምርቃት ፕሮግራም አካሂዷል።ኦቪድ ሪልስቴት መካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ያማከለ የቤቶች ግንባታ ያከናውን እንደነበር ዋና ሥራ አስፈፃሚው ዮናስ ታደሰ አስታውሰው ይህኛው ግን የቅንጦት አፖርትመንት መሆኑን ገልፀዋል።የቅንጦት መኖሪያ መንደሩ የገበያ ማዕከል፣ ዘመናዊ ሆስፒታሎች፣ ፖርኮች፣ የመኪና ማቆሚያዎች፣ ሞሎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ እና የህፃናት ማቆያ ይኖሩታል ብለዋል።መኖሪያ ቤቶቹ ከ60 ካሬ ጀምሮ ከአንድ እስከ ሦስት መኝታ ቤት የሚኖራቸውና በአጠቃላይ 9 ነጥብ 46 ሄክታር ላይ የሚያርፍ መንደር ነው ተብሏል።ከእንጦጦ ተነስቶ በየካ አባዶ ሲሲዲ የሚያገናኝ አስፋልት እንደሚዘረጋለትም ተገልጿል።

4. ሩሲያ 1 ሺህ 630 ሜትሪክ ቶን ስንዴ ለኢትዮጵያ ድጋፍ አደረገች። የሩሲያ መንግስት ከ 160 ሺህ በላይ ለሚደርሱ ስደተኞች የሚዉል ስንዴ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት የዓለም ምግብ ፕሮግራም በጋምቤላ ክልል ለሚገኙ ስደተኞች እያደረገ ያለዉን ድጋፍ እንዲያጠናክር ያደርገዋል የተባለዉን 1 ሺህ 630 ሜትሪክ ቶን ስንዴ ከሩሲያ መንግስት ተሰጥቶታል ።
በአዳማ በሚገኘዉ (ደብሊው ኤፍ ፒ) የሎጀስቲክስ ማዕከል በተካሄደው ርክክብ በጋምቤላ ክልል ለሚገኙ 163,240 ስደተኞች የሚደርስ መሆኑ ተጠቁሟል።

5. በአሜሪካዋ ሎስአንጀለስ ያጋጠመው የእሳት አደጋ አሁንም መቆጣጠር አልተቻለም። ዝነኛ እና ቅንጡ ቤቶችን ሳይቀር እያወደመ ያለው ይህን እሳት አደጋ ለመቆጣጠር ጎረቤት ሀገር የሆነችው ካናዳም እየረዳች ትገኛለች። ተመራጩ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የከተማዋ ከንቲባ ስልጣን እንዲለቁ ጠይቀዋል

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #morningnews #dailynews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

09 Jan, 15:07


የዕለቱ አበይት ዜናዎች

አዲስ አበባ፣ ኢትዮ ነጋሪ፣ ጥር 1 ቀን 2017 ዓ.ም

1. ፓርላማው የንብረት ማስመለስ አዋጅን አጸደቀ::
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው14ኛ መደበኛ ስብሰባው የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል።
አዋጁ በሕገ-ወጥ መንገድ የተፈራን ንብረት ማስመለስ የሚያስችሉና የሕግ-ተጠያቂነትን የሚያስከትሉ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዕጸገነት መንግስቱ በረቂቅ አዋጁ የተደረጉ ማስተካከያዎችና የተጨመሩ አንቀጾችን አስመልክተው ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

2. በትግራይ ክልል ባለሃብቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ
በትግራይ ክልል በተለያዩ የግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ለመሰማራት መሬት ወስደው ወደ ልማት ያልገቡ 24 ባለሃብቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ፡፡
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የመሬትና ማዕድን ቢሮ  ሃላፊ አቶ ካልአዩ ገብረህይወት ለኢዜአ እንደገለፁት እርምጃው የተሰጣቸውን መሬት ከማስመለስ ጀምሮ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እስከ መስጠት የደረሰ ነው፡፡
ከባለሃብቶቹ መካከል አራቱ ምንም ዓይነት ልማት ያልጀመሩ እና ለሌላ አከራይተው በመገኘታቸው የወሰዱትን መሬት ሙሉ በሙሉ እንዲመልሱ መደረጉን ተናግረዋል።
በሌሎች 20 ባለሃብቶች ላይ ደግሞ ለ6 ወራት የሚቆይ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው አቶ ካልአዩ ገልጸዋል።

3. በርዕደ መሬቱ ትምህርት ቤቶች ላይ ጉዳት ደረሰ
በአፋር ክልል ጋቢ ዞን እየተከሰተ ባለው ተከታታይ ርዕደ መሬት በሶስት ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 37 ትምህርት ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ሃላፊ አቶ አብዱ ሀሰን ያዮ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለፁት በጉዳቱ ሙሉ በሙሉ የወደሙ እና በከፊል ጉዳት የደረሰባቸው ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን ገልፀዋል፡፡
16 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ጉዳት ሲደርስባቸው 21 ትምህርት ቤቶች ደግም ከፊል ጉዳት እንደደረሰባቸው ሃላፊው ገልጸዋል።

4. በአሜሪካ ሎሳንጀለስ የተከሰተው ሰደድ እሳት ወደ ሆሊውድ ኮረብታዎች እየተስፋፋ መሆኑ ተገለጸ
ሰደድ እሳቱ ከ10 ሄክታር ተነስቶ በከተማዋ ባለው ከፍተኛ አውሎ ንፋስ ምክንያት 80 ኪሎሜትር በሰዓት በፍጥነት በመጓዝ በከፍተኛ ሁኔታ መዛመቱ ተገልጿል።
ከ100 ሺ በላይ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ ታዘዋል።
ሎስአንጀለስ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር የምትገኝ ሲሆን፣ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጆ ባደን ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚውል የፌደራል በጀት ማፅደቃቸውም ተጠቁሟል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

09 Jan, 12:09


ፓርላማው የንብረት ማስመለስ አዋጅን አጸደቀ::


የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስትና የህዝብ ንብረትን ለማስመለስ የነበረውን የሕግ ክፍተት የሚሞላ የንብረት ማስመለስ አዋጅን አጽቋል።

ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው14ኛ መደበኛ ስብሰባው የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል።

አዋጁ በሕገ-ወጥ መንገድ የተፈራን ንብረት ማስመለስ የሚያስችሉና የሕግ-ተጠያቂነትን የሚያስከትሉ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዕጸገነት መንግስቱ በረቂቅ አዋጁ የተደረጉ ማስተካከያዎችና የተጨመሩ አንቀጾችን አስመልክተው ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

ቋሚ ኮሚቴው በአዋጁ ላይ በአስረጅ፣ በህዝብና የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት ግብዓት እንደሰበሰበ ገልጸዋል።

የንብረት ማስመለስ አዋጅ የመንግስትና የህዝብ ንብረትን ለማስመለስ የነበረውን የሕግ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ አስረድተዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

25 Dec, 17:03


የዕረቡ ታህሳስ 16/ 2017 ዓ.ም ዋና ዋና መረጃዎች

- የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼኽ ሞሐመድ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አስመራ መግባታቸው ተገለጸ። የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስቴር የማነ ገብረመስቀል በኤክስ ገጻቸው እንዳስታወቁት ዛሬ ታኅሣሥ 16/2017 ዓ. ም. የሶማሊያው ፕሬዝዳንት አስመራ ሲገቡ በፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። መሪዎቹ "የሁለትዮሽ ግንኙነትን ስለማጠናከር እንዲሁም የጋራ ጠቀሜታ ስላላቸው ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ይወያያሉ" ሲሉም አቶ የማነ ገልጸዋል። የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼኽ ሞሐመድ ወደ አስመራ ከማቅናታቸው ከሁለት ቀናት በፊት አገራቸው የኢትዮጵያ ወታደሮች ድንበር ጥሰው የሶማሊያ ጦር ላይ "ጥቃት ሰንዝረዋል" ብላ መክሰሷ ይታወሳል።

- በሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ሳቢያ 110 ሺህ ወገኖች አስቸኳይ የሰብዓዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን የክልሉ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ፕሮግራም ማስተባበሪያ ኮሚሽን አስታወቀ። ነዋሪዎች ላይ ጉዳት የደረሰው በአልሚ ምግብና በመድሀኒት አቅርቦት ችግር ምክንያት ነው ሲል ኮሚሽኑ ገልጿል። በዞንና ወረዳው የተጎጂን ሁኔታ የመለየት፣ መረጃውን ለፌደራል አደጋ ስጋት ስራ አመራርና ለአጋር አካላት የማሳወቅና የሚያስፈልገውን የድጋፍ መጠን የመለየት ሥራ ተሰርቶ በተለያዩ አካላት ድጋፍ እንዲቀርብ መደረጉን ም/ኮሚሽነሯ ገልጸዋል። በUSAID በኩል የሚተላለፉ የደጋፊ ምግቦችን በወቅቱ ባለማድረስ በመጣ ክፍተት ችግሩ መከሰቱን ኮሚሽኑ አሳውቋል።በክልሉ ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ተጨማሪ አልሚ ምግብ ማድረስ አለመቻሉ ተጠቁሟል። በአንዳንድ ቦታዎች ዝርፊያ መፈጸሙን እና ዜጎች በዚህ ምክንያት ለችግር መዳረጋቸውም ተጠቅሷል።

- አራት የስኳር ፋብሪካዎች ከክረምት ጥገና በኋላ መደበኛ ስኳር የማምረት ስራቸውን መጀመራቸው ተጠቆመ። ከ2016 ዓ.ም የክረምት ወራት መግባት ጋር ተያይዞ አጠቃላይ የጥገና ሥራ ሲያከናውኑ የቆዩት አራት ስኳር ፋብሪካዎች መደበኛ የማምረት ሥራቸውን መጀመራቸውን የኢትዮጵያ የስኳር ኢንደስትሪ ግሩፕ አስታወቀ። ስኳር ማምረት የጀመሩት ፋብሪካዎች ወንጂ ሸዋ፣ መተሐራ፣ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3/1 እና ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 መሆናቸውም ተገልጿል፤ የፊንጫ ስኳር ፋብሪካም የክረምት ወራት አጠቃላይ የጥገና ሥራውን አጠናቆ ወደ ኦፕሬሽን እየገባ መሆኑ ተጠቁሟል።

- ኢራን በሶሪያ ውስጥ ቀውስ እና ትርምስ ከመፍጠር እንድትቆጠብ የሶሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሳድ ሀሰን አስጠነቀቁ፡፡ አዲስ እየተቋቋመ በሚገኘው የሽግግር መንግስት ውስጥ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት አሳድ ሶሪያውንያን የተሻለ የፖለቲካ ስርአትን እና ሀገርን ለመገንባት ጥረት ላይ ናቸው ብለዋል፡፡ ሚኒስትሩ በይፋዊ የኤክስ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት የሶሪያውያን ዜጎች ፍላጎት እና ሉዐላዊነት እንዲከበር ጠይቀዋል፡፡

- ሳኡዲ አረቢያ በመጠናቀቅ ላይ በሚገኘው የፈረንጆቹ 2024 አመት በሞት የቀጣቻቸው ሰዎች ቁጥር በአስርተ አመታት ውስጥ ከፍተኛው እንደሆነ ተነግሯል፡፡ በ2024 በሞት የቀጣቻቸው 330 ሰዎች ቁጥር ከባለፈው አመት አንጻር ሲወዳደር በእጥፍ የጨመረ ሲሆን በአስርት አመታት ውስጥ ደግሞ ከፍተኛው ነው ተብሏል፡፡ በተለያዩ ሰብአዊ መብት ተሟጋቾች የወጣው እና ሮይተርስ አረጋግጨዋለሁ ባለው መረጃ ሀገሪቱ በ2022- 196 ሰዎች በሞት የቀጣች ሲሆን በ2023 ደግሞ 172 ሰዎች ተቀጥተዋል፡፡ በዚህኛው አመት በተፈጸሙ የሞት ቅጣቶች ውስጥ ከፍተኛ ወንጀል ያልፈጸሙ እና መንግስትን የሚቃወሙ ቁጥራቸው 150 የሚጠጉ ዜጎች ጭምር ሰለባ እንደሆኑ የመብት ተሟጋቾች ይናገራሉ፡፡


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

25 Dec, 14:19


በኢትዮጵያ የስራ ማቆም አድማ ሊደረግ እንደሚችል ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አባል ማህበራት የሰራተኞች ጥያቄ ካልተመለሱ  ስራ የማቆም አድማና ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ሲል አስጠንቅቋል፡፡

ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል በመንግስት እንዲወሰንና ከደመወዝ ላይ የሚቆረጠው ከፍተኛ_ግብር እንዲቀንስ መንግስት በተደጋጋሚ ቢጠየቅም እስካሁን ምላሽ አልሰጠም ተብሏል፡፡

በመሆኑም ከዚህ በኋላ ሰራተኞች ወደ ስራ ማቆም አድማና ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያመሩ እንደሚችሉ ማህበራቱ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን የኢትዮጵያን ሰራተኞች ይወክላሉ ከሚባሉት አባላቱ ጋር ባሳለፍነው ሳምንት አድርጎት በነበረው ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ አባላቱ በሰራተኞች ጥቅም ዙሪያ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ተጨማሪ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://bit.ly/3Bzf5Vh

#ethiopia #CETU #Minimumwage

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

25 Dec, 09:29


የመንገደኞች አውሮፕላን ተከስክሶ የ42 ሰዎች ህይወት አለፈ

አደጋው የተከሰተው ንብረትነቱ የአዛርባጂያን አየር መንገድ የሆነ አውሮፕላን ወደ ሩሲያ በመብረር ላይ እያለ ነው።

አውሮፕላኑ በገጠመው የቴክኒክ ችግር ምክንያት በካዛኪስቷኗ አክታው በምትባል ቦታ ለማረፍ ሲሞክር ተከስክሷል።

በዚህ አውሮፕላን ላይ 67 መንገደኞች እና የበረራ አስተናጋጆች ተሳፍረው የነበረ ሲሆን 42ቱ ህይወታቸው አልፏል ተብሏል።

የአደጋው መንስኤ እስካሁን ያልታወቀ ሲሆን ምርመራዎች እየተካሄዱ ነው።

የካዛኪስታን መንግሥት በአደጋው የቆሰሉ መንገደኞችን ህይወት ለመታደግ የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።

#Azerbaijan #planecrash #Aktau #Kazakhstan

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

25 Dec, 04:48


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

አዲስ አበባ፣ ኢትዮ ነጋሪ፣ ታህሳስ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

1. በኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት ህክምና የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ከ400 ሺሕ በላይ መድረሱ ተገልጿል። ሰዎች ከሞቱ በኋላ ኩላሊት እንዲለግሱ የሚፈቅደው የሕግ ማዕቀፍ ሀሳቡ ከዓመታት በፊት በረቂቅ ደረጃ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በቅርቡ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ መቅረቡን የኩላሊት ሕመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት አስታውቋል።ሰው በሕይወት እያለ ወዶና ፈቅዶ በመስማማት ሕይወቱ ካለፈ በኋላ ኩላሊቱ እንዲወሰድ የሚፈቅደው የሕግ ማዕቀፍ ለብዙ ጊዜ ይፀድቃል ተብሎ ሲጠበቅ ነበር። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዚህ ረቂቅ ህግ ዙሪያ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ከተባሉ አካላት ጋር እየተወያየበት ይገኛል። ረቂቅ አዋጁ ሌሎች የሰውነት አካላት ልገሳ፣ መዳን በማይችል ህመም የተያዙ ሰዎች በፈቃዳቸው በህክምና የታገዘ ሞት እንዲሞቱ፣ የዘር ፍሬ ልገሳ እና ሌሎችም ጉዳዮችን ይዟል።

2. ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ወራት ከቡና ንግድ 800 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች ተባለ። የቡና እና ሻይ ልማት ባለስልጣን እንዳለው ከሆነ ባለፉት አምስት ወራት 178 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጪ ተልኮ 797 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል። ኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት ከቡና ንግድ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት እቅድ ይዛለች።

3. በአዲስ አበባ የመኪና ነሸጫ ዋጋ ቅናሽ አሳየ። በአዲስ አበባ በተለያዩ ምክንያቶች በተለይም በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል ተብሏል። ፊደል ፖስት እንደዘገበው ከሆነ የኢትዮጵያ ባንኮች ለመኪና እና ለቤት ግዢ እየሰጡ ብድር አለመስጠታቸው ፣ የኤሌትሪክ መኪኖች ግዢ  ፍላጎት መጨመር ፣ የነዳጅ ዋጋ መጨመር ፣ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ የሰው  ንብረት የመግዛት አቅም መዳከም የኮሮላ እና ቪትዝ መኪኖችን ገዢ በከፊል የቀነሰ ሲሆን ይሄም ዋጋቸው  ላይ ተፅእኖ አሳድሯል። ሱዝኪ ዲዛየርን ጨምሮ ኮሮላ እና ቪትዝ ላይ በአማካኝ በአራት መቶ ሺ ብር  ቀንሷል። ሞዴላቸው  ቪትዝ ከአንድ ነጥብ አራት እስከ አንድ ነጥብ ሰባት ኮሮላ መኪና ደግሞ ከአንድ ነጥብ ስምንት እስከ ሁለት ነጥብ ሁለት ሚልየን ብር እየተሸጡ ይገኛል።

4. አሜሪካ ከዓለም ጤና ድርጅት ልትወጣ ትችላለች ተብሏል። የተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሽግግር ቡድን አባላት አሜሪካን ከአለም ጤና ድርጅት አባልነት ለማስወጣት እቅድ እያዘጋጁ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ሮይተርስ እንደዘገበው ከሆነ ፕሬዝዳንት በመጀመርያ ቀን የስልጣን ቆይታቸው ከሚያስተላልፏቸው ቁልፍ የፖሊስ ውሳኔዎች መካከል ከድርጅቱ አባልነት መውጣት አንዱ ሊሆን ይችላል፡፡የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ግዙፉ የጤና ኤጄንሲ ወረርሽኞችን እና ሌሎች አለምአቀፋዊ የጤና ቀውሶችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ዋሽንግተንን በማግለል ተወቅሷል። በተጨማሪም በመሰል አለም አቀፋዊ የጤና ጉዳዮች ከአሜሪካ ይልቅ ወደ ቻይና አድልቷል በሚልም በትራምፕ የሽግግር ቡድን ውንጀላ ቀርቦበታል፡፡

#ethiopia #morningnews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Dec, 16:15


የማክሰኞ ታህሳስ 15/ 2017 ዓ.ም ዋና ዋና መረጃዎች

- የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ኃይሎች በሶማሊያ ጦር ላይ ጥቃት አድርሰዋል ሲል ያቀረበውን ክስ የኢትዮጵያ መንግሥት አስተባበለ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማክሰኞ ታኅሣሥ 15/2017 ዓ. ም. ባወጣው መግለጫ፣ "የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሶማሊያዋ ከተማ ዱሎው ለተፈጠረ ክስተት የኢትዮጵያ ወታደሮችን መክሰሱ ኢትዮጵያን አሳስቧታል" ብሏል። የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰኞ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ዱሎው በተባለችው የጁባላንድ ከተማ "የኢትዮጵያ ኃይሎች ጥቃት ፈጽመዋል" ሲል ከሷል። የኢትዮጵያ መንግሥት በምላሹ "የተስተካከለውን የሶማሊያና የኢትዮጵያ ግንኙነት ማወክ በሚፈልጉ ኃይሎች የተፈጠረ ክስተት ነው" ብሏል። የኢትዮጵያ መንግሥት "ሦስተኛ ወገን" ያላቸው አካላት "የአፍሪካን ቀንድ ለመናጥ ቆርጠው የተነሱ የቀጣናው ሰላም አደፍራሾች" ናቸው ሲል ገልጿል።

- ኢትዮጵያ ከአጎዋ ተጠቃሚ ሀገራት ዝርዝር ውስጥ በድጋሚ አለመካተቷ ተገለጸ። ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ነጻ የንግድ ስምምነት አጎዋ በድጋሚ ተጠቃሚ ለመሆን ያደረገችው ጥረት አለመሳካቱ ተገለጸ። የዩናይትድ ስቴት የንግድ ተወካዮች ምክር ቤት ከአጎዋ ተጠቃሚ የሚሆኑ 32 ሀገራትን ስም ዝርዝር ታህሳስ 12 ቀን 2017 ዓ.ም ይፋ ያደረገ ሲሆን ኢትዮጵያ ከተዘረዘሩት ሀገራት ውስጥ አልተካተተችም። ባሳለፍነው አመት ሐምሌ ወር ላይ የአሜሪካ የንግድ ተወካይ ቢሮ ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ለአጎዋ ብቁ መሆን አለመሆኗን ለመለየት ውይይት ያደረጉ ቢሆንም ተጠቃሚነቷ እንዲነሳ የሚያደርገው ውሳኔ አሁንም እንዲቀጥል ተደርጓል። ከሶስት አመታት በፊት በትግራይ የተካሄደውን ጦርነት ተከትሎ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ግሮውዝ ኦፖርቹኒቲ አክት (አጎዋ) የቀረጥና ታሪፍ ነፃ መብት መሰረዛቸውን ጥር 2014 ዓ.ም ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።

- ሐረሪ ክልል ውስጥ ለዘጠኝ ቀናት የተዘጉ 43 የባንክ ቅርጫፎች እንዲከፈቱ ማኅበሩ ጠየቀ። ሐረሪ ክልል ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ባንኮች 43 ቅርንጫፎች ለኮሪደር ልማት እንዲያዋጡ ተጠየቅን ያሉትን 2 ሚሊዮን ብር ባለመክፈላቸው ባንኮቹ ከተዘጉ ዘጠኝ ቀናት እንዳለፋቸው የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር አስታወቀ። የባንኮች ማኅበሩ ዋና ጸሐፊ አቶ ደምሰው ካሳ፣ አንዳንዶቹ ባንኮች ግንባታቸው ባልተጠናቀቀ ሕንፃ ውስጥ መሥራታቸው እንደ ምንክኒያት ቢነገራቸውም፣ ዋናው ጉዳይ ግን ገንዘብ ባለማዋጣታቸው ነው ብለዋል።

- በሶሪያ በሀማ ከተማ አቅራቢያ በአደባባይ ላይ የተቀመጠ የገና ዛፍ መቃጠሉን ተከትሎ የክርስትና እምነት ተከታዮች ለተቃውሞ አደባባይ ወጥተዋል፡፡ በርካታ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሚኖሩበት ሱካለቢያ በተባለ ማዕከላዊ የሶሪያ ከተማ የበዓሉን መቃረብ ተከትሎ የተሰቀለው የገና ዛፍ ፊቱን በጭንብል በሸፈነ ታጣቂ በእሳት ሲቀጣጠል በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ታይቷል፡፡ ፕሬዝዳንት በሽር አል አሳድን ከስልጣን ያስወገደውን ውጊያ የመራው አማጺ ቡድን ቃጠሎውን የፈጸሙት ሰዎች የውጭ ተዋጊዎች መሆናቸውን በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እና ዛፉ በፍጥነት እንደሚጠገን ተናግሯል።
በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች ድርጊቱ በተፈጸመበት ሱካለቢያ እና ሌሎች የሶሪያ አካባቢዎች በመውጣት አዲሱ አስተዳደር ለአናሳ የማህበረሰብ ክፍሎች ጥበቃ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር የሐማስ የፖለቲካ ክንፍ መሪ ኢስማኢል ሀኒዬ ባለፈው ሐምሌ ቴህራን ውስጥ በእስራኤል መገደላቸውን አመኑ። ሚኒስትሩ እስራኤል ካትዝ በኢራን የሚደገፉ የሁቲ መሪዎችን ዒላማ እንደሚያደርጉ በሰጡት መግለጫ ወቅት ነው ይህን ያሉት። የሁቲ አማፂያን እስራኤል ላይ የድሮን እና የሚሳዔል ጥቃት እያደረሱ ይገኛሉ። ሀኒዬ በኢራን መዲና ቴህራን በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው ሳሉ ነው የተገደሉት። እስራኤል ግድያውን መፈፀሟን ባታምንም ብዙዎች ግን ከጥቃቱ ጀርባ እጇ አለበት ሲሉ ቆይተዋል። እስራኤል የሁቲ አማፂያን ላይ "ከፍተኛ እርምጃ" ትወስዳለች፤ የቡድኑ መሪዎችን ጭንቅላት "ትቀላለች" ሲሉ ካትዝ ተናግረዋል።
"ልክ ሀኒዬን እንዳደረግነው፣ [ያህያ] ሲንዋርን፣ እና [ሐሰን] ናስራላሕን በቴህራን፣ ጋዛ እና ሊባኖስ እንዳደረግነው በተመሳሳይ በሆዴይዳ እና ሰንዓ እናደርጋለን" ብለዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Dec, 11:44


ኢትዮጵያ በሶማሊያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች

የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ትናንት ባወጣው መግለጫ ወታደሮች ጌዶ ግዛት ልዩ ቦታው ዶሎ ላይ ጥቃት ፈጽመዋል ሲል መክሰሱ ይታወሳል።

ጥቃቱ የሶማሊያን የጸጥታ ሀይሎች እና ንጹሀን ዜጎች ላይ ትኩረቱን አድርጓልም ሲል አክሏል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ በሶማሊያ የቀረበው ክስ ሀሰተኛ መሆኑን አስታውቋል።

ሶማሊያ በኢትዮጵያ ላይ ያቀረበችው ክስ ሁለቱ ሀገራት በቅርቡ በአንካራ የተስማሙትን ስምምነት እንዳይተገበር በሚፈልጉ አካላት ግፊት የተደረገ ነውም ተብሏል።

የግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ወደ ካይሮ ካቀኑት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በጋራ ባወጡት መግለጫ ግብጽ የሰላም አስከባሪ ጦር ወደ ሞቃዲሾ እንደምትልክ፣ ከቀይ ባህር ጋር የማይዋሰን ሀገር በአካባቢው መንቀሳቀስ እንደማይችል ተናግረዋል፡፡

#ethiopia #somalia #Egypt

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Dec, 09:43


የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች በማይቀበሉ ትምህርት ቤቶች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በተለይም አንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች ለመቀበል ፍቃደኛ እንዳልሆኑ ገልጿል።

ማንኛውም ትምህርት ቤት እነዚህን ልጆች ታሳቢ ያደረገ የመማሪያ ክፍል እና የትምህርት ስርዓት የመዘርጋት ግዴታ አለበት ተብሏል።

አካቶ ትምህርት በሀገሪቱ ተግባራዊ እየተደረገ ነው ቢባልም ልጆቹን ትምህርት ቤት ከማስገባት ውጪ ትምህርቱና የትምህርት ክፍሎቹ እነሱን ታሳቢ ያደረጉ እንዳልሆኑ የፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ሥራ አስኪያጅ ሸዋጌጥ ክብረት አስረድተዋል ሲል አራዳ ኤፍ ኤም ዘግቧል። 

ከዚህ ባሻገር ምን ያህል የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ልጆች ከትምህርት ገበታ ቀርተዋል የሚለው ጉዳይ እንኳን፥ ጥናት ያልተደረገበት እና ቁጥራዊ መረጃ የሌለው መሆኑንም አስረድተዋል።

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Dec, 04:48


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ ታህሳስ 15 ቀን 2017 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ

1. ኢትዮጵያ ከአግዋ እድል መሰረዟ በ2025 እንደሚቀጥል ተገልጿል። በደቡብ አፍሪካ በተካሄደ የሰላም ስምምነት አማካኝነት የቆመው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነትን ታሳቢ ምክንያት አሜሪካ ኢትዮጵያ ከአግዋ እድል መታገዷ ይታወሳል። ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈጽሟል፣ ጉዳዩም ለአሜሪካ ብሔራዊ ጥቅም አስጊ ነው በሚል በኢትዮጵያ ላይ ከሶስት ዓመት በፊት የተላለፈው ይህ እገዳ እንዲነሳ ያደረገችው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል። ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ባይደን የአግዋ እድል አሁን እየተጠቀሙ ያሉት 32 ሀገራት ባሉበት እንዲቀጥሉ ውሳኔ አሳልፈዋል ተብሏል። ይህን ተከትሎም ኢትዮጵያ በ2025 ዓመትም ከአግዋ እድል ውጪ መሆኗ ተረጋግጧል።

2. ወደ አዲስ አበባ እና ካይሮ የዲፕሎማሲ ልዑኮቿን ከላከች በኋላ የተለያየ አቋም ያላቸው ሁለት መግለጫዎችን አውጥታለች። በውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ የተመራው እና ወደ ግብጽ ያመራው የሶማሊያ ልዑክ ኢትዮጵያን በመክሰስ የጋራ መግለጫ አውጥተዋል። ከቀይ ባህር ጋር የማይዋሰኑ ሀገራት እንዲንቀሳቀሱ ሊፈቀድላቸው አይገባም የሚል ጭብጥ ያለው መግለጫ ያወጡት ሁለቱ ሀገራት ኢትዮጵያን በተዘዋዋሪ ለማስፈራራት ሞክረዋል። እንዲሁም ሶማሊያ በውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዴኤታው የተመራው ልዑክ ደግሞ በአዲስ አበባ ባደረገው ቆይታ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ተወያይቷል ተብሏል። የኢትዮጵያ ወታደሮች በሶማሊያዋ ጌዶ ግዛት ልዩ ቦታው ዶሎ ላይ ጥቃት ፈጽመዋል ሲል ከሷል። ጥቃቱ የሶማሊያን የጸጥታ ሀይሎች እና ንጹሀን ዜጎች ላይ ትኩረቱን አድርጓልም ተብሏል። የሶማሊያ ሁለት መግለጫዎች በቱርክ ፕሬዝዳንት ኤርዶሀን አደራዳሪነት ግንኙነታቸውን ዳግም ለማስተካከል ተስማምተዋል በተባለበት ማግስት ነው። ኢትዮጵያ እስካሁን በካይሮ እና በሞቃዲሾ ስለተሰጡት ሁለት መግለጫዎች ምላሽ አልሰጠችም።

3. ባንድ ቀን ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ በመተሀራ አካባቢ በድጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አጋጥሟል። የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ትናንት ምሽት 4:41 ላይ ከመተሐራ 13 ኪሎ ሜትር ርቀት የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር ገልጿል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶችን የሚከታተለው ተቋሙ መሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.9 የተመዘገበ ጠቅሶ ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ ተሰምቷል።

4. ኢትዮጵያ በባሮ ወንዝ ላይ የተጀመረውን አልዌሮ ግድብን ዳግም ስራ ልታስጀምር እንቅስቃሴ መጀመሯ ተገልጿል። በቀድሞ የሶቭየት ህብረት እርዳታ የተጀመረው ይህ ግድብ በጋምቤላ የሚገኝ ሲሆን አንድ ሚሊዮን ሄክታር መሬት የማልማት እቅድ ነበረው ተብሏል። በደርግ አስተዳድር ወቅት የተጀመረው የዚህ ግድብ ግንባታ ኢህአዴግ ስልጣን በሀይል መቆጣጠሩን ተከትሎ ስራው ቆሞ ቆይቷል። የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ባለስልጣን ይህን ግድብ ማጠናቀቅ እና ዳግን ወደ ስራ ለማስገባት ስራ መጀመሩን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

5. ሰሜን ኮሪያ ተጨማሪ ወታደሮች እና የጦር መሳሪያ ወደ ሩሲያ ልትልክ መሆኗን ባላንጣዋ ደቡብ ኮሪያ ገልጻለች።ሰሜን ኮሪያ ሞስኮ በዩክሬን ላይ የምታደርገውን ጦርነት ለመደገፍ ተጨማሪ ወታደሮችን እና ወታደራዊ መሳሪያዎችን ምናልባትም አጥፍቶ ጠፊ ድሮኖችን ጨምሮ ወደ ሩሲያ ልታሰማራ እየተዘጋጀች ይመስላል ሲል የደቡብ ኮሪያ ጦር ሃይሎች አስታዉቋል።ግምገማው የተደረገው ሰሜን ኮሪያ ከዩክሬን ጋር በምታደርገው ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮቿን ለሩሲያ እንዲዋጉ አድርጋለች ተብሎ በሚታመንበት ወቅት ሲሆን የሟች የሰሜን ወታደሮች ቁጥር ወደ 1,100 እንደሚደርስ የደቡብ የስለላ ድርጅት ገልጿል።

#ethiopia #morningnews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Dec, 16:24


የሰኞ ታህሳስ 14/ 2017 ዓ.ም ዋና ዋና መረጃዎች

- የአንካራ ስምምነትን ተከትሎ የ ሶማሊያ ልዑካን ቡድን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ_አበባ ይገባል። በሶማሊያ የውጭ ጉዳይና አለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አሊ ኦማር የተመራ የሶማሊያ ፌዴራል መንግስት የልዑካን ቡድን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ እንደሚገባ ተገለፀ። ጉብኝቱ በአንካራው ስምምነት መሰረት ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ሲል የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።የልዑካን ቡድኑ በጋራ ጥቅም እና ትብብር ላይ የተመሰረተ አጋርነት ለመፍጠር የለውጥ ዕድሎችን በማሰስ ላይ እንደሚያተኩር ተጠቁሟል።

- አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የቆየችውን የአፍሪካ ከታሪፍ ነፃ ዕድል ወይም አጎዋ እገዳን ዘንድሮም አራዝሜዋለሁ ብላለች። የአሜሪካን ንግድ ሥራ የሚመራውና የአሜሪካ ንግድ ተወካይ የሚባለው ቢሮ የሀገራትን ወቅታዊ ሁኔታ አቅርቦ ካስገመገመ በኋላ ነው በኢትዮጵያ ከሰብዓዊ መብት አያያዝ ጋር በተያያዘ የተጣለው የአጎዋ ማዕቀብ እንዲራዘም የተወሰነው። የዚሁ የንግድ ተወካይ ቢሮ ባለፈው ነሐሴ ወር ለፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የግምገማ ሪፖርቱን ካቀረበ በኋላ ፕሬዝዳንቱ የእገዳውን መራዘም በፊርማቸው አፅድቀውታል። ባይደን በፊርማቸው ስላፀደቁትም በ2024 ሀገራት በ2025 ለውጥ ሳይኖር እንዳለ ይቀጥላሉ ተብሏል።

- በአዲስ አበባ በስድስት ክፍለ ከተሞች የሥምና ንብረት ዝውውር ታገደ። በአዲስ አበባ ከተማ ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራ ሲባል ለቀጣይ 5 ወራት በስድስት ክፍለ ከተሞች እና በተመረጡ ወረዳዎች የሥምና ንብረት ዝውውር መታገዱን የከተማዋ መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጄንሲ አስታውቋል። ኤጄንሲው ከመሬት ይዞታ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ ለዚህም ዘመናዊ ሁለገብ ካዳስተር ግንባታ ስርዓት በመዲናዋ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ሥራ መጀመሩን አመልክቷል፡፡ አሁን ላይ ከአዲስ አበባ ጠቅላላ የቆዳ ስፋት ውስጥ 54 በመቶ ለሚሆነው የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራ መሰራቱን ገልጿል።

- ሰሜን ኮሪያ በዩክሬን ውጊያ እያካሄደች ላለችው ሩሲያ ተጨማሪ ወታደሮች እና ድሮኖች ልትልክ መሆኑን የሚያሳይ ምልክት ማግኘቱን የደቡብ ኮሪያ ጦር በዛሬው እለት አስታውቋል። ጦር እንደገለጸው ሰሜን ኮሪያ 240 ኤምኤም የተባለ በአንድ ጊዜ በርካታ ሮኬቶችን ማስወንጨፊያዎችን፣ ራሱ መተኮስ የሚችል 170 ኤምኤም የጦር መሳሪዎችን መስጠቷን እና ወደ ሩሲያ የሚላኩ ራሳቸው የሚያጠፉ ወይም 'ሱሳይድ ድሮኞች' ለማምረት ስትዘጋጅ ታይታለች። "ሱሳይድ ድሮኖችን ማምረት መሪው ኪም ትኩረት ካደረጉባቸው ተግባራት ውስጥ አንዱ ነው" ያለው ጦሩ ሰሜን ኮሪያ ድሮኖቹን ለሩሲያ የመስጠት ሀሳብ እንዳላት ገልጿል።

- ትራምፕ ቲክቶክ አሜሪካ ውስጥ የተወሰነ ጊዜ ሳይዘጋ እንዲቆይ ማድረግ አስፈላጊ ሊሆን እንደሚችል ገለጹ። የምርጫ ቅስቀሳ በሚያካሂዱበት ወቅት በቲክቶክ በቢሊዮን የሚቆጠር እይታ ማግኘታቸውን የገለጹት ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ሳይዘጋ ለተወሰነ ጊዜ እንዲቆይ እንደሚፈልጉ በትናንትናው እለት ተናግረዋል። የአሜሪካ ሴኔት ባለፈው ሚያዝያ ወር ቲክቶክ የብሔራዊ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በመጥቀስ ነበር ንብረትነቱ የቻይናው ባይቲዳንስ የሆነውን መተግበሪያ በአሜሪካ ውስጥ እንዲሸጥ ወይም አንዲታገድ የወሰነው።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Dec, 08:05


የስም እና ንብረት ዝውውር ታገደ

በአዲስ አበባ በስድስት ክፍለ ከተሞች የስምና ንብረት ዝውውር ታገደ

በአዲስ አበባ ከተማ ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራ ሲባል ለቀጣይ 5 ወራት በስድስት ክፍለ ከተሞች እና በተመረጡ ወረዳዎች የስምና ንብረት ዝውውር ታግዷል።

የከተማዋ መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጄንሲ እንዳስታወቀው ከመሬት ይዞታ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ ነው።

ለዚህም ዘመናዊ ሁለገብ ካዳስተር ግንባታ ስርዓት በመዲናዋ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ሥራ መጀመሩን አመልክቷል፡፡

አሁን ላይ ከአዲስ አበባ ጠቅላላ የቆዳ ስፋት ውስጥ 54 በመቶ ለሚሆነው የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራ መሰራቱ ተጠቁሟል።

በተያዘው በጀት ዓመት ለመጨረሻ ጊዜ በ136 ቀጠናዎች የሚገኙ ይዞታዎችን አረጋግጦ ለመመዝገብ እየተሰራ ነው ተብሏል።

በዚህ መሠረትም የይዞታ ማረጋገጥ ስራው በተመረጡ ስድስት ክፍለ ከተሞች በቀጣይ አምስት ወራት ውስጥ እንደሚከናወን ተጠቅሷል።

ክፍለ ከተሞችም የካ፣ ለሚ ኩራ፣ አቃቂ ቃሊቲ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ፣ቦሌ እና ኮልፌ ቀራኒዮ መሆናቸው ተመላክቷል።

ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራው ሲባልም ምዝባ በሚካሄድባቸው የክ/ከተሞቹ ወረዳዎች እስከ ቀጣዩ ሚያዝያ ወር ድረስ የስምና ንብረት ዝውውር መታገዱ ተገልጿል።

ባለይዞታዎች ከታሕሣሥ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 ቀናት የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ እንዲያቀርቡም ጥሪ ቀርቧል።

#ethiopia #morningnews #addisababa

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Dec, 05:10


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

1. የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ700 ሚሊዮን ዶላር ብድር አጸደቀ። ባንኩ ብድሩን ለኢትዮጵያ የፈቀደው የፋይናንስ ስርዓትን ለማዘመን እንደሆነ አስታውቋል። ገንዘቡ በተለይም በኢትዮጵያ ጠንካራ የገንዘብ ቁጥጥር ማድረግ የሚያስችሉ አሰራሮችን ለመዘርጋት ይውላልም ተብሏል። የገንዘብ ድጋፉ በቀጥታ ብሔራዊ ባንክ፣ ንግድ ባንክ እና ልማት ባንክ ያላቸውን የፋይናንስ ቁጥጥር ስርዓቶችን እንዲያሻሽሉ ያግዛል ሲል የዓለም ባንክ ባወጣው መግለጫ ላይ ጠቅሷል።

2. የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአንድ ሳምንት በፊት ከቦይንግ የተረከበው ግዙፍ አውሮፕላን እክል ገጠመው። አየር መንገዱ በፈረንጆቹ ታህሳስ 12 ቀን 2024 ቦይንግ 777-300ER የተሰኘ አውሮፕላን ከቦይንግ ተረክቦ ነበር። ቦይንግ ኩባንያ መሰል አውሮፕላኖችን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲያስረክብ በሁለት ዓመት ውስጥ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜው ነው። ይሁንና ይህ አውሮፕላን ከሰሞኑ ወደ ዱባይ እየበረረ እያለ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ምክንያት ወደ ቦሌ ኤርፖርት ተመልሶ እንዲያርፍ ተደርጓል። አውሮፕላኑ ለ20 ደቂቃ በረራ ካደረገ በኋላ አብራሪው በእቃ መጫኛው ውስጥ ችግር እንዳጋጠመው አዲስ አበባ ላሉት ለአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ከተናገረ በኋላ እንዲያርፍ መደረጉን ዘ አቪዬሽን ሄራልድ ዘግቧል። አውሮፕላኑ ያጋጠመው የቴክኒክ ችግር ዙሪያ እየተካሄደ ያለው ምርመራ እንዳልተቋጨም ተገልጿል።


3. የኤርትራ ጦር በትግራይ ክልል 23 ትምህርት ቤቶችን ተቆጣጥሯል ተብሏል። በትግራይ ክልል ኢሮብ ወረዳ ስር ካሉት ትምህርት ቤቶች ውስጥ 23ቱ አሁንም በኤርትራ ጦር ቁጥጥር ስር እንደሆኑ ተገልጿል። የወረዳው ትምህርት ፅሕፈት ቤት እንደገለጸው በወረዳው ውስጥ ካሉ 47 ትምህርት ቤቶች 23 ሙሉ በሙሉ በኤርትራ ወታደሮች ቁጥጥር ስር እንደሚገኙ ገልጿል። በ23 ትምህርት ሲማሩ የነበሩት 7300 ተማሪዎች ላለፉት አራት ዓመታት በምን አይነት ሁኔታ እንደሚገኙ ማወቅ እንዳልቻለም ጽህፈት ቤቱ ለትግራይ ቴሌቪዥን ተናግሯል።

4. በአፋር ክልል አዋሽ ከተማ አቅራቢያ 4.6 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አጋጥሟል። አደጋው ሲያጋጥም ይህ የመጀመሪያው ባይሆንም ዛሬ ከሌሊቱ 8:40 ላይ መጠነኛ መንቀጥቀጥ አደጋ እንዳጋጠመ ዓለም አቀፉ የጂኦሎጂ ጥናት ማዕከል አስታውቋል።

5. በሞዛምቢክ ባጋጠመ አውሎ ነፋስ ቀላቅሎ በጣለ ከባድ ዝናብ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 94 ደርሷል። ደቡብ አፍሪካዊቷ ሀገር ሞዛምቢክ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት እየተጎዱ ካሉ ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ናት። በቅርቡ በተካሄደ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ አለመረጋጋት ውስጥ የቆየችው ሞዛምቢክ ቺዶ በተሰኘው ከባድ አውሎ ነፋስ ምክንያት የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችልም ተሰግቷል።


#ethiopia #morningnews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Dec, 16:01


ማንችስተር ዩናይትድ በበርንማውዝ ተሸነፈ

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድ ከበርንማውዝ ተጫውተዋል።

በርንማውዝ በውጤት ቀውስ ውስጥ ያለው ዩናይትድን በሁይጅሰን፣ክሉይቨርት እና ሴሜኒዮ ጎሎች ድል ቀንቶታል።

ቼልሲ በበኩሉ በጉዲሰን ፓርክ ስታዲየም ከኤቨርተን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 0ለ0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል።

ከደቂቃዎች በኋላ የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ከቶትንሀም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#football #premierleague

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Dec, 11:49


አትሌት ስለሺ ስህን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ

አትሌት ደራርቱ ከፓሪስ ኦሎምፒክ ጋር በተያያዘ ስልጣን መልቀቋ ይታወሳል።

በ28ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ለቀጣይ አራት አመት ፌዴሬሽኑን በፕሬዝዳንት ለመምራት ምርጫ እየተከናወነ ይገኛል፡፡

በዚህም ከኦሮሚያ ክልል የተወከሉት አትሌት ስለሺ ስህን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#Ethiopia #athletics

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

21 Dec, 16:36


የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን  ለይፋዊ ሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ፡፡

ፕሬዚዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ  አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ማክሮን በፈረንሳይ የገንዘብ እና ቴክኒክ ድጋፍ የታደሰው ብሔራዊ ቤተ መንግስትን እንደሚመርቁ ይጠበቃል።

ከአምስት ዓመት በኋላ ወደ አዲስ አበባ የተመለሱት ፕሬዝዳንት ማክሮን ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ስምምነቶችን እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

#ethiopia #dailynews #emanuelmacron #France

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

20 Dec, 17:35


የአርብ ታህሳስ 11/ 2017 ዓ.ም ዋና ዋና መረጃዎች

- አሜሪካ በሰሜን ወሎ ቡግና ወረዳ ለተከሰተው ድርቅ እና የምግብ እጥረት ምግብ እየተላከ መሆኑን አስታወቀች ። አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ የተከሰተውን ድርቅ እና የምግብ እጥረት ተከትሎ እርዳታ ወደ ስፍራው እየተላከ መሆኑን አስታውቋል። ኤምባሲው በኦፊሴላዊ የፌስቡክ ገፁ እንዳስታወቀው በወረዳው ድርቅ እንደተከሰተ ከሰሞኑ እየወጡ ያሉ ሪፖርቶች ላይ ክትትል አድርጓል። "የኢትዮጵያ ህዝብን ለመደገፍ አጋሮቻችን ምግብ እና አልሚ ምግቦችን ወደተጠቁት ስፍራዎች እየላኩ ነው" ያለው ኤምባሲው ሁኔታውን በቀጣይም በመከታተል ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚሰራ አስታውቋል።

- በኤሌክተሪክ ፍጆታ እና በልዩ ልዩ ክፍያዎች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ተደረገ። ከ200 ኪሎ ዋት ሠዓት በላይ በሚጠቀሙ ደንበኞች የፍጆታ ሂሳብ ላይ እና አዲስ ደንበኛ ማገናኘትን ጨምሮ ደንበኞች በሚፈፅሟቸው ልዩ ልዩ የአገልግሎት ክፍያዎች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡የገንዘብ ሚኒስቴር ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የሚሆነውን የመኖሪያ ቤት የኤሌክትሪክ ኃይልና የውኃ ፍጆታ መጠን ለመወሰን ባወጣው አዋጅ መመሪያ መሠረት ክፍያው ከመስከረም ወር ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉን ነው አገልግሎቱ ያስታወቀው፡ በመመሪያው መሰረትም ከአገልግሎታችን ተጠቃሚ ደንበኞች ከወርሀዊ የፍጆታ ሂሳብ ጋር ተጨምሮ እንዲከፍሉ በማድረግ የተሰበሰበው ገንዘብ በየወሩ ለገቢዎች ሚኒስቴር ገቢ እንደሚያደርግም ነው የገለጸው፡፡

- በሐረር ከተማ የታሸጉ 35 የባንክ ቅርንጫፎች አገልግሎት ወደ መስጠት እንዲመለሱ ለሀረሪ ክልል አቤቱታ ቀረበ። የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር በሐረር ከተማ የታሸጉ 35 የባንክ ቅርንጫፎች ተከፍተው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ እንዲደረግ ለሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቤቱታ አቀረበ። የክልሉ መንግስት ቅርንጫፎቹ የታሸጉት “ግንባታቸው ባላለቁ ህንጻዎች አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ ነው” ቢልም፤ ማህበሩ ግን ከሌሎች የንግድ ድርጅቶች በተለየ መልኩ እርምጃው በእነርሱ ላይ መወሰዱ ለክልሉ የኮሪደር ልማት የተጠየቀው መዋጮ ተግባራዊ ባለመደረጉ ምክንያት የተፈጸመ እንደሆነ “ከድምዳሜ ላይ እንዲደርስ” እንዳደረገው ገልጿል።

- ሶማሊያ የኢትዮጵያ ወታደሮች በህብረቱ ልዑክ ውስጥ የመካተታቸውን ጉዳይ “መልሳ ለማጤን” ዝግጁ መኾኗን አስታወቀች። የሶማሊያ መንግሥት የኢትዮጵያ ወታደሮች በአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ውስጥ መካተታቸውን በተመለከተ “መልሶ ለማጤን” ዝግጁ መኾኑን አስታወቀ።የሶማሊያ መንግሥት ለልዑኩ ኅይል ከሚያዋጡት ሀገራት ማለትም ዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ጂቡቲ እና ቡሩንዲ ወታደሮችን ማግኘቱን እና መደልደሉን ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ አንድ ከፍተኛ የሶማሊያ መንግሥት ባለሥልጣን እንደነገሩት ቪኦኤ በዘገባው አስታውቋል።

- የፕሬዝደንት ጆ ባይደን አስተዳደር ከፍተኛ ባለስልጣን በሀያት ታህሪር አል ሻም(ኤችቲኤስ) ከሚመሩት የሶሪያ ባለስልጣናት ጋር ለመመከር በዛሬው እለት ደማስቆ መሆናቸውን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አስታውቋል። የአሜሪካ የመካከለኛው ምስራቅ ዋነኛ ዲፕሎማት ባርባራ ሊፍ፣ የሆስቴጅ ጉዳይ ፕሬዝደንታዊ ተወካይ ሮገር ካርስቴንስ፣ በቅርቡ የሶሪያን ጉዳይ እንዲከታተሉ የተሾሙት ከፍተኛ አማካሪ ዳኒኤል ሩቢንስተን ሶሪያን ለረጅም ጊዜ የመራው በሽር አላሳድ በተቃዋሚ ታጣቂዎች ከስልጣን ከተገረሰሰ በኋላ ደማስቆን የጎበኙ የመጀመሪያዎቹ ዲፕሎማቶች ሆነዋል። ይህ ጉብኝት የተካሄደው ምዕራባውያን ሀገራት ቀስ በቀስ በራቸውን እየከፈቱ እና በቡድኑ ላይ የተጣለውን የሽብርተኝነት ፍረጃ ስለማንሳት ወይም ስላለማንሳት እየተወያዩ ባለበት ወቅት ነው። የአሜሪካ የሉእካን ቡደን ጉብኝት ቡድኑ በቅርቡ ከፈረንሳይ እና እንግሊዝ ጋር ግንኙነት ማድረጉን ተከትሎ የመጣ ነው።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

20 Dec, 13:43


በሐረር ከተማ 35 የባንክ ቅርንጫፎች ለኮሪደር ልማት ገንዘብ አላዋጣችሁም በሚል ታሸጉ

የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር በሐረር ከተማ የታሸጉ 35 የባንክ ቅርንጫፎች ተከፍተው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ እንዲደረግ ለሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቤቱታ አቅርቧል።

የክልሉ መንግስት ቅርንጫፎቹ የታሸጉት “ግንባታቸው ባላለቁ ህንጻዎች አገልግሎት እየሰጡ በመሆኑ ነው” ቢልም፤ ማህበሩ ግን ከሌሎች የንግድ ድርጅቶች በተለየ መልኩ እርምጃው በእነርሱ ላይ መወሰዱ ለክልሉ የኮሪደር ልማት የተጠየቀው መዋጮ ተግባራዊ ባለመደረጉ ምክንያት የተፈጸመ እንደሆነ “ከድምዳሜ ላይ እንዲደርስ” እንዳደረገው ገልጿል ሲል ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

በሀረሪ ክልል የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ባንኮች የሁለት ሚሊዮን ብር “ድጋፍ” እንዲያደርጉ በደብዳቤ የተጠየቁት የዛሬ ሶስት ሳምንት ገደማ ነበር።

ደብዳቤውን ለባንክ ቅርንጫፎች የጻፈው የሀረሪ ክልል የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ፤ የገንዘብ መጠኑን በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ገቢ እንዲያደርጉ ቀነ ገደብ ሰጥቷቸውም ነበር።

ሃያ ስድስት ባንኮችን በአባልነት ያቀፈው የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር፤ ከትላንት በስቲያ ለሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በጻፈው ደብዳቤ፤ የባንክ ቅርንጫፎች የተጠየቁትን ያህል የገንዘብ መጠን በመዋጮ መልክ ለመክፈል “ስልጣን እንደሌላቸው” ገልጿል።

ተጨማሪ ያንብቡ https://ethionegariamharic.com/2024/12/20/ethiopia-seals-35-bank-branches-in-harar-city/

#dailynews #ethiopia #Hararcity #banking

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

20 Dec, 09:23


አቶ ካሳሁን ፎሎ በድጋሚ የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አካሂዷል፡፡

(ኢሠማኮ) በአዲስ አበባ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ኮንፌዴሬሽኑን የቀጣዮቹ 5 ዓመታት አመራሮችን መርጧል፡፡

በዚህም ላለፉት ዓመታት ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለሶስተኛ ጊዜ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋ፡፡

ኮንፌዴሬሽኑ አቶ ድሪብሳ ለገሰ እና አቶ አብዱልሐኪም ሙሰማ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ እንደመረጠም ሰምተናል፡፡

አቶ ካሳሁን ከምርጫው በኋላ ባደረጉት ንግግር በሀላፊነት የሚቀጥሉት ለመጨረሻ ጊዜ እንደሆነ በጉባኤው ላይ ገልጸዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ አክለውም መንግሥት ለሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን በድጋሚ ጠይቀዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ https://bit.ly/4fvRP8v

#ethiopia #cetu #tradeunion

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

20 Dec, 06:22


ቴክኖ አዳዲስ በኤአይ የታገዙ የቴክኖሎጂ ምርቶቹን ይፋ አደረገ

አዲሱ የቴክኖ ኤአይ አጋዥ ቴክኖሎጂ የዕለት ተዕለት ኑሮን በእጅጉ ከማቅለሉም በላይ ቋንቋን ከመተርጎም አንስቶ ፎቶን በራሱ አቅም ኤዲት ማድረግ፣ የተለያዩ ድምጾችን ወደ ፅሁፍ መቀየር እና መሰል ተያያዥ ስራዎች በቀላሉ እና በፍጥነት ለመከወን የሚያስችል አጋዥ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ቴከኖሎጂን ተካቶለታል፡፡

መርሐግብሩን የቴክኖ ኢትዮጵያ ብራንድ ማናጀር አቶ አሊክ ባደረጉት የመከፈቻ ንግግር በይፋ የተከፈተ ሲሆን ቴክኖ ኢትዮጵያ በሀገራችን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ላይ ቁልፍ ሚናን እየተጫወተ እንደሚገኝ በዚህም ከፍተኛ ኩራት እንደሚሰማው የገለፁ ሲሆን አከለውም ቴከኖ ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለህብረተሰቡ ተደራሽ መሆኑን እንዲሁም ማህበረሰቡ አለም ከደረሰበት ቴክኖሎጂ እኩል እንዲራመድ መትጋቱን እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

በመድረኩ የቴኖሎጂ ኤክስፐርቱ ሰለሞን ካሳ ስለ አዳዲሶቹ የፋንተም V2 ታጣፊ ስልኮች ከቴክኖ ኤ አይ ጋር አጣምረው ስለመጡት ቴክኖሎጂ በምስል የታግዘ ሰፊ ማብራሪያ ለታዳሚው አቅርቧል።

የዝግጅቱ  ታዳሚዎች የቴክኖ ኤአይ እና አዲሶቹ የፋንተም V2 ታጣፊ ስልኮችን በቅርበት የመመልከት ዕድል እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡

በመርሐግብሩ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የቴከኖ ኢትዮጵያ ሃላፊዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተውበታል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Tiktok:- https://www.tiktok.com/@ethionegari?_t=ZM-8sMnSHUu9QL&_r=1

#ethiopia #dailynews #AI #Tecno

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

20 Dec, 05:32


የማለዳ አንኳር ዜናዎች

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ ታህሳስ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

1. ስድስት የፖሉቲካ ፓርቲዎች ብልጽግና መሩ መንግሥት ኢትዮጵያን ወደ ከባድ ምስቅልቅል ችግሮች እያስገባት ነው ሲል ከሷል። የስድስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ህብረት የሆነው ኮከስ ብልፅግና መሩ መንግስት ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ኢትዮጵያ በጦርነት፣ በኑሮ ውድነት፣ በኢኮኖሚ ድቀት፣ ሆን ብሎ ማፈናቀል እና ሌሎች በርካት ችግሮችን በህዝብ ላይ አድርሷል ሲል ከሷል።  "ፖለቲካችን የተለመደውን የአፈናና አግላይነት፣ የአንድ ፓርቲ የበላይነትና ጠቅላይነት አጠናክሮ ቀጥሏል" ኮከሱ " የፖለቲካ ፓርቲዎች ከአጃቢነት፣ ህዝብ ከአገልጋይነት ያለፈ የፖለቲካ መብታቸውን የማንሳት ህገመንግስታዊ መብት ተነፍጓቸው በወንጀል ተቆጥሮባቸው ፀጥ-ለጥ ብለው እንዲገዙ ተፈርዶባቸው በከፍተኛ ድብርት ውስጥ ናቸው ሲልም በመግለጫው ላይ ጠቅሷል።

2. በኢትዮጵያ በየዓመቱ 30 ሺህ ህጻናት ከነርቭ ዘንግ ችግር ጋር እንደሚወለዱ ተገልጿል። በኢትዮጵያ በየአመቱ ከሚፀነሱ ህጻናት መካከል 30 ሺህ የሚሆኑት ከነርቭ ዘንግ ክፍተትና  ከጭንቅላት ውሀ ክምችት  ጋር አብረው እንደሚወለዱ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። የሰሜንና የደቡብ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ይበልጥ ለችግሩ ተጋላጭ መሆናቸዉንም ሚንስቴሩ ገልጿል። የችግሩ መንስኤዎች በርካታ ቢሆኑም የፎሊክ አሲድ እጥረት ዋነኛነት  መንስኤ ነው ተብሏል።

3. የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ለ10 የመድኃኒት ምርቶች የመድኃኒት ደህንነት ማስጠንቀቂያ ሰጠ። በኢትዮጵያ ገበያ የሚዘዋወሩ አሥር የፀረ ወባ መድሐኒቶች ዝቅተኛ የጥራት መመዘኛዎችን ሳያሟሉ መገኘታቸውን ባለ ስልጣኑ አስታውቋል። ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ እና ባለድርሻ አካላት በማንኛውም መልኩ መጠቀማቸውን እንዲያቆሙ ጥሪ አቅርቧል። ዝቅተኛ ጥራት አላቸው የተባሉት መድሀኒቶችን እና እርምጃ የተወሰደባቸውን ተቋማት ከመግለጽ ተቆጥቧል።

4. የሶማሊያ መንግሥት የኢትዮጵያ ወታደሮች በአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ውስጥ ልታካትት እንደምትችል ፍንጭ ሰጠች። አንድ የሶማሊያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን ለቪኦኤ እንዳሉት" የሶማሊያ መንግሥት ለልዑኩ ኅይል ከሚያዋጡት ሀገራት ዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ጂቡቲ እና ቡሩንዲ ወታደሮችን አግኝቶ ደልድሏል" ብለዋል። ኢትዮጵያ እና ሱማሊያ አንዳቸው የሌላውን ሉዐላዊነት፣ እንዲሁም የግዛት አንድነት እንደሚያከብሩ አንካራ፣ ቱርክ ላይ ባለፈው ሳምንት ስምምነት መፈጸማቸውን ገልጸዋል። ስምምነቱ በመፈጸሙም ሶማሊያ የኢትዮጵያ ወታደሮች በአዲሱ ልዑክ ውስጥ የመካተታቸውን ጉዳይ " እንደገና እንደምታጤን ባለስልጣኑ ተናግረዋል።

5. የሩሲያ ጦር ቁልፍ ተብላ በምትጠራው ፖክሮቭስክ ከተማን ለመቆጣጠር ጫፍ ላይ መድረሱ ተገልጿል። የሩሲያ ጦር ፖክሮቭስክ ከተማን ለመቆጣጠር በሁለት ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ አስገብቷል ተብሏል።ከተማዋ የዩክሬን ጦር ቁልፍ የሎጅስቲክስ እና ወታደራዊ አመራር መስጫ ማዕከል ሆና ስታገለግል ቆይታለች።ዩክሬን ከተማዋን ላለመነጠቅ ስትል በሌሎች ግምባሮች ያሉ ወታደሮቿን በማንሳት ወደ ምስራቅ ግምባር እያሰፈረች እንደሆነ ተገልጿል።

#ethiopia #morningnews

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

19 Dec, 17:57


የሐሙስ ታህሳስ 10/ 2017 ዓ.ም ዋና ዋና መረጃዎች

- የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አመራሩ ጃዋር መሐመድ 'አልጸጸትም' በሚል ርዕስ ሐሙስ፣ ታህሳስ 10/ 2017 ዓ.ም በናይሮቢ ሊያስመርቀው የነበረው መጽሐፍ ከተለያዩ አካላት በደረሱ ማስፈራሪያዎች እና ዛቻዎች ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉን የቢቢሲ ምንጭ ገለጹ። ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እኚሁ ምንጭ ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት መጽሐፉ የሚመረቅበት ናይሮቢ የሚገኘው የኬንያታ ዓለም አቀፍ የስብሰባ ማዕከል መሆኑ ከታወቀ በኋላ የተለያዩ ማስፈራሪያዎች ደርሰዋል ብለዋል። ዛቻው ማዕከሉን ለሚያስተዳደሩት አካላት በመድረሱ ምርቃቱ መሰረዙን ገልጸዋል። ፖለቲከኛው ጃዋር መሐመድ በኬንያ መዲና ናይሮቢ ዛሬ ሐሙስ ታሕሳስ 10 2017 ዓ.ም. ሊካሄድ የነበረው የመፅሐፍ ምርቃት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ አስታውቋል። ጃዋር በፌስቡክ ገጹ ላይ "በተሳታፊዎች ብዛት እና በደህንነት ስጋት" ምክንያት የምረቃ አዳራሹ አስተዳደር ላልተወሰነ ጊዜ ማስተላለፉን ገልጾ በቅርብ ቀን ተቀያሪ ቦታ እናሳውቃለን ብሏል።

- በአማራ ክልል "በመንግሥት ተጠርቷል" በተባለ ሰልፍ ላይ በ3 ከተሞች በተፈጸሙ የቦምብ ጥቃቶች የሰው ህይወት ማለፉ ተገለጸ። በአማራ ክልል “በመንግሥት አስተባባሪነት” ትናንት ታህሳስ 9 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሄድ በተባለ ሰልፍ ላይ በባሕር_ዳር፣ ወልዲያና ደብረ_ብርሃን ከተሞች “በተፈጸሙ የቦምብ ጥቃቶች የአንድ ሰው ህይወት ማልፉንና ሰልፈኞች መቁሰላቸው” ተገልጿል።

- በኢትዮጵያ በሰብአዊ መብት ጥሰት የተጠረጠሩ ባለስልጣናትን ከስልጣን እንዲነሱ አሜሪካዊቷ አምባሳደር ጠየቁ። የኢትዮጵያ ባለስልጣናት የሀገሪቱ የሽግግር የፍትህ ሂደት አካል በመሆን በሰብአዊ መብት ጥሰት የተሳተፉና ተጠርጥረው ጉዳያቸው በፍርድ ሂደት ላይ የሚገኙ ወታደራዊ አባላትን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ የሀላፊነት ቦታዎች የሚገኙ ባለስልጣናትን ከስልጣን እንዲያነሱ ሲሉ በቅርቡ በኢትዮጵያ ጉብኝት ያካሄዱት #በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአለም አቀፍ የወንጀል ፍትህ አምባሳደር ቤትዝ ቫን ስካክ አሳሰቡ። በተጨማሪም አምባሳደር ቤትዝ የሀገሪቱ መንግስት ለተፈጸሙ ግፎች እና በደሎች እውቅና ሊሰጥ ይገባል ሲሉ አሳሰቡ። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሲቪክ ማህበራት ምህዳሩ እንደጠበበ ተረድተናል ሲሉ ቅሬታቸውን የገለጹት አምባሳደር በአማራ እና ኦሮምያ ክልሎች እየተፈጸሙ ስላሉ አሰቃቂ ተግባራት የሚወጡ ዘገባዎችንም እየተከታተልን ነው ብለዋል።

- ምዕራባውያን ሚሳኤሉን መቋቋም የሚያስችል ቴክኖሎጂ እንዳላቸው እርግጠኞች ከሆኑ በፈለጉት ኢላማ ላይ መሞከር እንደሚችሉ ፑቲን ተናግረዋል። ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በቅርብ ጊዜ በዩክሬን ላይ ያስወነጨፉትን “የኦሬሽኒክ” የባለስቲክ ሀይፐር ሶኒክ ሚሳኤል አስመልክቶ አነጋጋሪ ሀሳብ ሰንዝረዋል፡፡ ፑቲን “ምዕራባውያን እና አሜሪካ የኦሬሽኒክ ሚሳኤልን መቋቋም የሚችል የአየር መቃወሚያ ካላቸው በመረጡት ኢላማ ላይ ሙከራ ማድረግ ይችላሉ” ብለዋል፡፡ በአሜሪካ የሚሳኤል መከላከያ ስርአቶች የሚጠበቅ የትኛውም ኢላማ ተመርጦ የኦሬሽኒክ ሚሳኤልን መቋቋም መቻሉን ለማረጋገጥ ሙከራ ማድረግ ይችላሉ ነው ያሉት፡፡

- በዩክሬን ጦርነት ለሩሲያ ወግነው ከሚዋጉት መካከል ቢያንስ 100 የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች መገደላቸውን የደቡብ ኮሪያ የፓርላማ አባል ገለጹ።
ፓርላማው በአገሪቱ ብሔራዊ መረጃ አገልግሎት ማብራሪያ ከተሰጠው በኋላ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ሊ ሱንግ ኳን ተጨማሪ 1 ሺህ ወታደሮች ቆስለዋል ብለዋል። ከተገደሉት መካከል ከፍተኛ መኮንኖች እንደሚገኙበት ተናግረው የወታደሮቹ ግድያ ስለ አካባቢው በቂ ግንዛቤ አለመኖር እንዲሁም ከሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት ጋር በተያያዘ ሊገለጽ ይችላል ብለዋል። በጦርነቱ የተገደሉ ሰሜን ኮሪያውያን ወታደሮች ሪፖርት ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ የሆነው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ነው። በጥቅምት ወር ሰሜን ኮሪያ 10 ሺህ ወታደሯቿን ሩሲያን ለማገዝ መላኳ ተገልጿል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Nov, 15:14


የቅዳሜ ህዳር 14/ 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

ዛሬ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አለልቱ ወረዳ በደረሰው የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ታውቋል። አደጋው ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ የሚጓዝ የሕዝብ ማመላለሻ በተቃራኒ አቅጣጫ ሲጓዝ ከነበረ ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው። የዞኑ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሥራ ሒደት ሃላፊ አቶ ሰለሞን ዘውዴ በአደጋው እስካሁን የ11 ሰዎች ሕይወት አልፏል ብለዋል። በተጨማሪም በ40 ሰዎች ላይ ከባድ እና 11 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።

በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል ውክልና አለመስጠቱን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ። ለሥራ ዜጎችን እንልካለን በማለት የማጭበርበር ድርጊት የሚፈጽሙ አካላትን የሕግ ተጠያቂ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝም ገልጿል። ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፤ ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎችን በማሰራጨት ህብረተሰቡን ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት እየዳረጉ መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ሳርማሌ ወረዳ ከፍላጎታቸው ውጪ ያለአግባብ ደሞዛቸው መቆረጡን የተቃወሙ ከ60 በላይ የሚሆኑ መምህራን መታሰራቸው ተገለጸ። የመምህራኑ ደመወዝ ከነሐሴ 2016 ዓ.ም ጀምሮ መቆረጥ መጀመሩን እና እንዲመለስላቸው ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ አለማግኘታቸውን ተከትሎ የሥራ ማቆም አድማ ማድረጋቸውን የታሳሪ መምህራን ቤተሰቦች ለቪኦኤ አስታውቀዋል።
በወረዳው መምህር የሆኑት አቶ ወረደ ዋኪሶ በበኩላቸው መምህራኑ ከደመወዛቸው ላይ እስከ 25 በመቶ ያለአግባብ መቆረጡን አስረድተዋል። በዚህም ምክንያት መምህራኑ አቤቱታቸውን በመምህራን ማሕበር አማካኝነት ለወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት እና ለወረዳው አስተዳደር ቢያቀርቡም "የምታመጡት ነገር የለም፤ እኛ የላክናቸው ካድሬዎች አስማምተው በመጡት መሰረት ነው ደመወዛችሁን የቆረጥነው።" የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ወለድ እና የአገልግሎት ዋጋ ማሻሻያ ሊያደረግ ነው። ባንኩ የአገልግሎት ክፍያ ማሻሻያ በሚያደርግበት ወቅት ለደንበኞቹ ቀደም ብሎ እንደሚያሳውቅ ገልጿል፡፡ ይህን ተከትሎም ባንኩ በሚሰጣቸው የብድር፣ የቅርንጫፍ እና የዲጂታል እንዲሁም በዓለም አቀፍ የባንክ አገልግሎቶች ላይ በቅርቡ የብድር ወለድ እና የአገልግሎት ዋጋ ማሻሻያ ሊያደርግ መሆኑን ነው ያስታወቀው፡፡

እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ባለፉት 48 ሰአታት በፈጸመችው የአየር ጥቃት 120 ፍልስጤማውያን መገደላቸው ተነገረ፡፡ በሰሜናዊው ጋዛ በሚገኝ ሆስፒታል በደረሰው ጥቃት ከሞቱት ሰዎች ባለፈ የህክምና ሰራተኞች መቁሰላቸው እና የህክምና መሳሪያዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የፍልስጤም የህክምና ባለስልጣናት ገልጸዋል፡፡ ከሟቾቹ መካከል በጋዛ ከተማ ዜይቱን በተባለ አካባቢ የሚኖሩ ሰባት የአንድ ቤትሰብ አባላት የሚገኙበት ሲሆን የተቀሩት በማዕከላዊ እና ደቡባዊ ጋዛ በተፈጸመ ጥቃት የሞቱ ናቸው፡፡

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አዲሱን “የኦሬሽኒክ” ባለስቲክ ሚሳኤል በጅምላ እንዲመረት ትዕዛዝ መስጠታቸውን ገለጹ፡፡ ሚሳይሉ በጅምላ እንዲመረት የታዘዘው በዚህ ሳምንት በዩክሬን ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በውጊያ ጥቅም ላይ ከዋለ በኋላ ነው። በክሬምሊን ከመከላከያ ሚኒስቴር አመራር እና ከመከላከያ ኢንዱስትሪ ተወካዮች ጋር በተደረገው ስብሰባ ላይ ፑቲን እንደተናገሩት “የኦሬሽኒክ” ሚሳኤል ስርዓት የሩሲያ የቅርብ ጊዜ ወታደራዊ ግስጋሴዎች ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ወቅታዊ የሩሲያ የመከላከያ ፍላጎትን ለማሟላት የተሰራ ነው የተባለው ሚሳይል በከፍተኛ የሃይፐርሶኒክ ቴክኖሎጂ እና በዘመናዊ ቁሳቁሶች ላይ ተመስርቶ የተመረተ መሆኑን አብራርተዋል፡፡


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Nov, 07:41


አዲስ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

በተለያዩ የስራ መስኮች የወጡ የNGO ስራዎችን በዝርዝር ለመመልከት እና ለማመልከት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://ethionegari.com/2024/11/22/latest-ngo-job-opportunities-in-ethiopia-6/

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Nov, 15:10


የአርብ ህዳር 13/ 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

የሲቪል ማህበረስበ ድርጅቶች ባለስልጣን“የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል” (CARD) እና “ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” (AHRE)ን አግዷል። ባለሥልጣኑ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እና በዚህ ሳምንት ለድርጅቶቹ በተናጠል በላከው ደብዳቤ፣ ድርጅቶቹ ከማንኛውም እንቅስቃሴ መታገዳቸውን አስታውቋል ሲል ዋዜማ ሬዲዮ ዘግቧል። ለእገዳው የሰጠው ምክንያት “ከፖለቲካ ገለልተኛ ሆኖ መሥራት ሲገባው ከዓላማው ውጭ በመንቀሳቀስ የአገርና የህዝብ ጥቅምን የሚጎዱ ተግባራት ላይ በመሰማራቱ ከባድ የህግ ጥሰት መፈጸሙን ማረጋገጥ ተችሏል” የሚል ነው። የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከሉ በበኩሉ “ከዓላማው ውጪ ምንም ዓይነት ተግባራት ላይ እንደማይሳተፍ እና በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ፍጹም ገለልተኛ ተቋም መሆኑን” አጽንዖት ሰጥቷል። 


የተለያዩ የደህንነት መስፈርቶችን ባላሟሉ ተቋማት ከ10 ሺሕ ብር የገንዘብ መቀጮ ጀምሮ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችለውና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የተዘጋጀው መመሪያ መጽደቁ ተሰምቷል፡፡
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የአደጋ መከላከል ቁጥጥር ፍተሻና ብቃት ማረጋገጥ ስርዓት መመርያ ቁጥር 163/2017ን ያጸደቀ ሲሆን፤ መመርያውን ተግባራዊ በማያደርጉ ተቋማት ላይም ከገንዘብ ቅጣት ጀምሮ ንግድ ፍቃድን እንዲታገድ ፈቃዱን ለሰጠው አካል እስከማሳወቅ የሚደርስ እርምጃን ማካተቱ ተገልጿል፡፡


የሚኒስትሮች ምክር ቤት 581.98 ቢሊየን ብር ተጨማሪ በጀት በማጽደቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መራ። የተጨማሪ በጀት እና የወጪ አሸፋፈን ማስተካከያው የተሻሻለውን የ2017-2021 የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ማዕቀፍ ማስፈጸም በሚያስችል መልኩ የመንግስት የፋይናንስ አቅምና ተጠባቂ ገቢዎችን ታሳቢ በማድረግ እንዲሁም የተጨማሪ በጀት ታሳቢዎችንና የወጭ ታሳቢዎችን ግምት ውስጥ በማስገባት መዘጋጀቱን ከጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ይህም የ2017 ዓ.ም አጠቃላይ በጀት ከ1.5 ትሪሊየን ብር በላይ እንደሚያደርገው ተመላክቷል።

ፕሬዚዳንት ፑቲን ማስጠንቀቂያውን የሰጡት ዩክሬን ከኔቶ አባል ሀገራት እና አሜሪካ በታጠቀቻቸው የረጅም ርቀት ሚሳኤሎች ሩሲያ ላይ ጥቃት መፈፀሟን ተከትሎ ነው፡፡ ጥቃቱን አስመልክቶ ፑቲን በሰጡት መግለጫ ÷ አሜሪካ፣ ብሪታኒያ እና ፈረንሳይ አርሚ ታክቲካል በተባለው ዘመናዊ ሚሳኤል ሩሲያ ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡ ሩሲያ አዲስ የስትራቴጂክ ሚሳኤሎችን በመጠቀም የአፀፋ ምላሽ መስጠቷን እና በአፀፋ ጥቃቱ የሩሲያ ባላስቲክ ሚሳኤል የዩክሬን የጦር መሰረተ ልማቶችን ኢላማ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በእርሳቸው እና በቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት ላይ የጦር ወንጀሎች የእስር ማዘዣ እንዲወጣ ያስተላለፈውን ውሳኔ “ፀረ-ሴማዊ” ሲሉ አውግዘዋል። “በሲቪሎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለማስወገድ የምንችለውን ሁሉ እያደረግንም ነው” አይሲሲ “በውሸት ሰላማዊ ሰዎች ላይ አነጣጥረዋል” በሚል እየከሰሳቸው መሆኑን ተናግረዋል። አይሲሲ ለሐማሱ አዛዥ መሐመድ ዴይፍም የእስር ማዘዣ አውጥቷል። እስራኤል ግን አዛዡ በጋዛ ውስጥ በሐምሌ ወር መገደሉን ተናግራለች። የአይሲሲ ዳኞች ሦስቱ ሰዎች በእስራኤል እና በሐማስ መካከል እየተደረገ በሚገኘው ጦርነት ለፈጸሙት ጥፋት “የወንጀል ተጠያቂነት” መኖሩን ለማመን “በቂ ምክንያቶች” እንዳሉ ተናግረዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በእስራኤል ባለሥልጣናት ላይ የአይሲሲ ያስተላለፈውን ውሳኔ “አሳፋሪ” ብለውታል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Nov, 13:43


መንግሥት ሁለት የሰብአዊ መብት ድርጅቶችን አገደ

የሲቪል ማህበረስበ ድርጅቶች ባለስልጣን በሰብአዊ መብት ሥራዎች ታዋቂ የሆኑ ድርጅቶችን እንዳሸገ ተገልጿል፡፡

ከታገዱት ድርጅቶች መካከልም “የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል” (CARD) እና “ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” (AHRE) ይገኙበታል።

ባለሥልጣኑ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እና በዚህ ሳምንት ለድርጅቶቹ በተናጠል በላከው ደብዳቤ፣ ድርጅቶቹ ከማንኛውም እንቅስቃሴ መታገዳቸውን አስታውቋል ሲል ዋዜማ ሬዲዮ ዘግቧል።

ለእገዳው የሰጠው ምክንያት “ከፖለቲካ ገለልተኛ ሆኖ መሥራት ሲገባው ከዓላማው ውጭ በመንቀሳቀስ የአገርና የህዝብ ጥቅምን የሚጎዱ ተግባራት ላይ በመሰማራቱ ከባድ የህግ ጥሰት መፈጸሙን ማረጋገጥ ተችሏል” የሚል ነው።

ከሁለቱ የሰብዓዊ ድርጅቶች በተጨማሪ ሌሎችም እንደታገዱ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።

ተጨማሪ ያንብቡ https://bit.ly/4gikCyf

#Ethiopia #humanrights

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Nov, 12:42


በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በጎጃም የተወሰኑ አካባቢዎች ሃይል ተቋረጠ

ከባህርዳር ዳንግላ በተዘረጋው 66 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት ከዛሬ ኅዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋት ጀምሮ በአዊ፣ቻግኒ እና ግልገል በለስ ከተሞች የኃይል አቅርቦት መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Nov, 10:52


አዲስ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

SOS Children’s Village በተለያዩ የስራ መስኮች አዲስ ሰራተኞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ አውጥቷል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለማመልከት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://ethionegari.com/2024/11/22/exciting-career-opportunities-at-sos-childrens-villages-ethiopia/

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

21 Nov, 15:18


የሐሙስ ህዳር 12 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

- የኦሮሚያ ከልል መንግስት እና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ “በፋኖ ታጣቂዎች” የ17 አመት ወጣት ላይ ተፈጽሟል የተባለውን አሰቃቂ ድርጊት በተናጠል ባወጡት መግለጫ አወገዙ። የኦሮሚያ ክልል ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ ዛሬ ህዳር 12/2017 በሰጡት መግለጫ “የጽንፈኛ የፋኖ አካላት ድርጊቱ ለብሄር ብሄረሰቦች እና ለኦሮሞ ዝህብ ያላቸውን ንቀት የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን የሚያስብ አዕምሮ እንደሌላቸውና ነገን የማያውቁ እራስ ወዳድ መሆናቸውን በተጨባጭ አሳይቷል” ብለዋል። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር በበኩሉ ባወጣው መግለጫ፤ “በፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግስት ኃይሎች በህዝባችን ላይ እየተፈጸመ ያለው አሰቃቂ ግድያ ከባድ የጦር ወንጀል ነው” ብሏል። ፓርቲው በመግለጫው በተፈጸመው የጭካኔ ግድያ ከፋኖ ታጣቂዎች በተጨማሪ መንግስትን ከሷል።

- በዛሬው ዕለት የመጀመሪያው ዙር የ መቀለ የተሓድሶ ስልጠና ማዕከል የሚገቡ 320 የትግራይ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች የነፍስ ወከፍ እና የቡድን የጦር መሳሪያ ትጥቃቸውን ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ማስረከባቸው የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል። በርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ላይም የብሔራዊ ተሃድሶ ምክትል ኮሚሽነርና የመከላከያ ሰራዊት ተወካይ ብርጋዴር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያ፣ የመከላከያ ሠራዊት ወታደራዊ መኮንኖች፣ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነሮች፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ተወካዮች፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ የአውሮፓ ሕብረት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ሌሎች ተባባሪ አካላት ተገኝተዋል።

- የኢትዮጵያ ወታደሮች ጁባላንድ ግዛት ዶሎ አየር ማረፊያ ላይ ስድስት የሱማሊያ ወታደሮችን እንዳሠሩ የአገሪቱ ዜና ምንጮች መዘገባቸው ተመልክቷል። ከሞቃዲሾ የተነሱት ወታደሮች በታሠሩበት ወቅት ሲቪል ለብሰው እንደነበር ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ወታደሮቹ ታሠሩ የተባለው፣ የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት ጁባላንድ በቅርቡ ልታካሂደው ያሰበችውን ምርጫ ኃይል በመጠቀም ለማስተጓጎል እንዳቀደ እየተነገረ ባለበት ወቅት ላይ ነው።

- ሩሲያ ዛሬ [ሐሙስ] ጠዋት ላይ ከደቡባዊ ከተማዋ አስትራክሃን አህጉር አቋራጭ ባሊስቲክ ሚሳኤል (አይሲቢኤም) የተባለውን ረጅም ርቀት ሚሳዔል መተኮሷን የዩክሬን አየር ኃይል አስታወቀ። አየር ኃይሉ እንዳለው በተለያዩ ዓይነት ሚሳዔሎች በተፈፀመው ጥቃት ዲኒፕሮ ክልል ዒላማ ተደርጋለች። የክልሉ ኃላፊ በተፈፀመው በዚህ ጥቃት የደረሰው ጉዳት በውል ባይታወቅም ቢያንስ 15 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል። ከተጎዱት መካከል የ16 እና የ17 ዓመት ታዳጊዎች እንደሚገኙበት ጠቅሰው ዘጠኝ ሰዎች በሆስፒታል ሕክምና እየተደረገላቸው እንደሆነ፤ ነገር ግን ስላሉበት ሁኔታ አለመታወቁን የክልሉ ኃላፊ ሴሪይ ሊይሳክ ገልጸዋል።

- ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የእስር ትዕዛዝ ወጣባቸው። መቀመጫውን ጀኔቭ ስዊዘርላንድ ያደረገው ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል ፍርድ ቤት በሁለቱም አመራሮች ላይ የእስር ማዘዣ አውጥቷል። የእስር ማዘዣው በጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ፣ መከላከያ ሚንስትር ዮአቭ ጋላንት እና በሐማስ ኮማንደር መሀመድ አልማስሪ ላይ ወጥቷል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል። እስራኤል ከዚህ በፊት የአይሲሲን የእስር ማዘዣ ሊያወጣ እንደሚችል በተገለጸበት ወቅት ጉዳዩን ተቃውማ ነበር።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

21 Nov, 09:38


በትግራይ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የመስፈታት ስራ ተጀመረ

በዛሬው ዕለት የመጀመሪያው ዙር የመቀለ የተሓድሶ ስልጠና ማዕከል የሚገቡ 320 የትግራይ ክልል የቀድሞ ታጣቂዎች የነፍስ ወከፍ እና የቡድን የጦር መሳሪያ ትጥቃቸውን ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ማስረከባቸው የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

በርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ላይም የብሔራዊ ተሃድሶ ምክትል ኮሚሽነርና የመከላከያ ሰራዊት ተወካይ ብርጋዴር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያ፣ የመከላከያ ሠራዊት ወታደራዊ መኮንኖች፣ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነሮች፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ተወካዮች፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ የአውሮፓ ሕብረት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ሌሎች ተባባሪ አካላት ተገኝተዋል።

የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፤ በትግራይ ክልል መቀሌ፣ እዳጋ ሀሙስ እና ዓድዋ በተዘጋጁ ሶስት ማዕከላት በሚቀጥሉት አራት ወራት 75 ሺህ የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ በማስፈታት በዘላቂነት የማቋቋምና ወደ ማህበረሰቡ የመቀላቀል ስራ እንደሚከናወን አስታውቀዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

21 Nov, 09:13


የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍ አገልግሎት የዓመቱ ምርጥ አየርመንገድ ሽልማትን አገኘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በግብጽ፣ካይሮ በተካሄደው 56ተኛው የAFRAA (የአፍሪካ አየር መንገዶች ማኅበር) አጠቃላይ ስብሰባ በዓለም አቀፍ አገልግሎት የዓመቱ ምርጥ አየርመንገድ (Airline of the Year - Global Operations) በመባል ሽልማቱን ማግኘቱን ገልጿል።

አየር መንገዱ ሽልማቱን ለስምንተኛ ግዜ መቀዳጀቱንም አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

20 Nov, 15:08


የዕረቡ ህዳር 11 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

- የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ክልሎች 371 ሺህ 971 የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ ተቀላቅለው በዘላቂነት ለማቋቋም መለየታቸውንም አስታውቋል። መንግስት በመደበው 1 ቢሊዮን ብር እና ከአጋሮች በተገኘ 60 ሚሊዮን ዶላር በመጀመሪያው ምዕራፍ በትግራይ ክልል የሚገኙ 75 ሺህ የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታትና በዘላቂነት የማቋቋም ስራ ይጀመራል ብለዋል። በክልሉ በመቀሌ፣ እዳጋሀሙስ እና አድዋ ሶስት ማዕከላት ተለይተዋል ያሉት ኮሚሽነሩ በመቀሌ ማዕከል በዚህ ሳምንት 320 የቀድሞ ታጣቂዎችን መቀበል እንጀምራለን ብለዋል።

- የናይጄሪያ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኢትዮጵያ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት በዕስር ላይ የሚገኙ ከ270 በላይ የሚሆኑ ናይጄሪያውያን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የናይጄሪያ ዳያስፖራ ኮሚሽን ሁኔታዎችን እንዲያመቻቹ ውሳኔ አስተላልፈ። ውሳኔው የተላለፈው ኢትዮጵያ በበጀት እጥረት ምክንያት ዕስረኞቹን ማቆየት የማትችል መሆኑን ማሳወቋን ተከትሎ ነው። ሄነሪ አንያዉ፣ ሌኦናርድ ኦካፎር እና ማዷግዉ የተባሉ ሶስት አቤቱታ ከስገቡ በኋላ የናይጄሪያ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማስተላለፉን ፒፕልስ ጋዜጣ ዘግቧል።

- የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ያሳለፈውን የቪዛ እገዳ ለማንሳት የተግባር እንቅስቃሴ እንዲያደርግ ተጠየቀ።የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በስብሰባ ላይ “የአውሮፓ ሕብረት ከአሁን በፊት በኢትዮጵያውያን ላይ ያሳለፈውን የቪዛ እገዳ ለማንሳት የተግባር እንቅስቃሴ ማድረግ ይገባዋል” ሲሉ ማሳሰባቸውን ከሚኒስቴሩ ገልጿል። መካከል ኢትዮጵያውያን ከአንድ ጊዜ በላይ ወደ አውሮፓ ህብረት አባል አገራት ገብተው መውጣት የሚችሉበት ቪዛ (multiple entry) ማግኘት አይችሉም የሚለው ይገኝበታል።

- እስራኤል በሐማስ ለታገቱባት እያንዳንዱ ዜጎች አምስት ሚሊዮን ዶላር እከፍላለሁ አለች፡፡ ባለፉት ጊዜያትም ከታገቱት 250 ዜጎች ውስጥ 34ቱ መሞታቸው ሲረጋገጥ 97ቱ አሁንም በሐማስ እገታ ስር መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ በፍልስጥሟ ኔትዛሪም ሆነው ባደረጉት ንግግር የታገቱ እስራኤላዊያንን ለማስለቀቅ 5 ሚሊዮን ዶላር ለመክፈል ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡ የእስራኤል ጦር ታጋቾችን ከነ ህይወታቸው አልያም አስከሬናቸውን ስለቀቅ ጥቃቱን እንደሚቀጥልም ተገልጿል፡፡

- በዩክሬን ያለው የአሜሪካ ኢምባሲ በሩሲያ ጥቃት ምክንያት ተዘጋ። ሁለቱም ሀገራት ከምድር ጦር ባለፈ የአየር ላይ ጥቃቶችን በስፋት እየተጠቀሙ ሲሆን በኪቭ ያለው የአሜሪካ ኢምባሲ ለአንድ ቀን እንደሚዘጋ አስታውቋል፡፡ ኢምባሲው ባወጣው ማስጠንቀቂያ መሰረት የኢምባሲው ሰራተኞች በያሉበት ሆነው ራሳቸውን ከአየር ላይ ጥቃቶች እንዲጠብቁም አሳስቧል፡፡ ሩሲያ በዛሬ ዕለት የአየር ላይ ጥቃት እንደምታደርስ መረጃ ደርሶኛል የሚለው ኢምባሲው አሜሪካዊያን የአደጋ ማስጠንቀቂያ ደወል ሲሰሙ ወደ ተሸለ ቦታ እንዲጠለሉ ብሏል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

20 Nov, 11:52


በኢትዮጵያ በዕስር ላይ የሚገኙ ከ270 በላይ ናይጄሪያውያን እንዲመለሱ የአገሪቱ ፍርድ ቤት ወሰነ

የናይጄሪያ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኢትዮጵያ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት በዕስር ላይ የሚገኙ ከ270 በላይ የሚሆኑ ናይጄሪያውያን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የናይጄሪያ ዳያስፖራ ኮሚሽን ሁኔታዎችን እንዲያመቻቹ ውሳኔ አስተላልፈ።

ውሳኔው የተላለፈው ኢትዮጵያ በበጀት እጥረት ምክንያት ዕስረኞቹን ማቆየት የማትችል መሆኑን ማሳወቋን ተከትሎ ነው።

ሄነሪ አንያዉ፣ ሌኦናርድ ኦካፎር እና ማዷግዉ የተባሉ ሶስት አቤቱታ ከስገቡ በኋላ የናይጄሪያ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማስተላለፉን ፒፕልስ ጋዜጣ ዘግቧል።

ዕስረኞቹ የታሰሩት ለምን እንደሆነ እንደማያውቁ እና በችሎት የመቅረብ እድል መነፈጋቸውም ተገልጿል። በተጨማሪም “ከቤተሰቦቻቸው ጋር ግንኙነት እንዳይኖራቸው ተከልክለው ቤተሰቦቻቸው እንደሞቱ አድርገው እንዲያስቡ ተደርገዋል" ተብሏል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

20 Nov, 08:47


75 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎች ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ሊመለሱ ነው ተባለ

የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን እንዳስታወቀው በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ተሳትፎ ከነበራቸው 274 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው እንደሚመልስ አስታውቋል፡፡

ከዚህ ውስጥም በመጀመሪያው ምዕራፍ 75ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞቢላይዝ የማድረግ ስራውን በነገው እለት በይፋ እንደሚጀመር ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡

ኮሚሽኑ ፕሮግራምና ፕሮጀክቶች በመቅረጽ ከሰባት ክልሎች ከ371 ሺህ በላይ የቀድሞ ተዋጊዎችን ከ760 ሚሊየን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በሁለት ዓመታት ውስጥ የዲሞቢላይዜሽንና መልሶ ማቋቋም ስራውን ለመጨረስ የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል።

ህዳር 12ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮም ለመጀመሪያው ዙር ተዋጊዎች ብተና ማስፈጸሚያ ሀብት መንግስትና ከለጋሾች ማግኘት ተችሏል ተብሏል፡፡

መንግስት ኮሚሽኑ ስራ ሲጀምር 1 ቢሊዮን ብር የተለገሰ ሲሆን በተጨማሪም ከ7 ሀገራት 60 ሚሊየን ዶላር መገኘቱ ተገልጿል።

በድጋፍ የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ህብረት የገንዘብ እና የቁስ ድጋፍ ማድረጋቸው ሲገለጽ 12 የሚጠጉ ሀገራት ደግሞ በቀጣይ ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡

ኮሚሽኑ በቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ስራው ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ መስተዳድር እና ከሚመለከታቸው የፌዴራል ተቋማት ጋር በመሆን የተሃድሶ ፕሮግራም ተሳታፊዎችን መለየት የተቻለ ሲሆን ሶስት ማዕከላትንም በመለየት የመረከብና የመጠገን ስራዎች ተሰርተዋል፡፡

መቀሌ ፣ እዳጋ ሀሙስ እና አድዋ የመጀመሪያ ዙር ተዋጊዎች ስልጣና የሚወስዱባቸው አካባቢዎች ናቸው ተብሏል።

በመጀመሪያ ዙር ወደ ስልጠና ካምፖች የሚገቡ 75 ሺህ ታጣቂዎች በአራት ወራት ለማጠናቀቅ እቅድ መያዙን ኮሚሽኑ ገልጿል።

የተሃድሶ ስልጠና ሰነዶች ዝግጅትና የአሰልጣኞች ስልጠና፤ የመመዝገቢያ ሶፍትዌር ማበልጸግ የማዕከላት ርክክብና ጥገና እንዲሁም አስፈላጊ የሎጅስቲክስ ግጞዥና አቅርቦት ተካሂዷልም ተብሏል፡፡

በዚህ መሰረት የተሃድሶ ፕሮግራም ተሳታፊዎች ወደ ማዕከላት ሲገቡ የስድስት ቀናት የተሃድሶ ቆይታ ይኖራቸዋል።

በቆይታቸውም የዲጅታል ምዝገባና ማረጋገጥ፣ የስነ ልቦና እና የተሃድሶ ስልጠና ይወስዳሉ ተብሏል፡፡

የተሃድሶ ፕሮግራም ተሳታፊዎች ወደ ማህበረሰቡ ሲመለሱ ለመሠረታዊ ፍጆታ እንዳይቸገሩ የመልሶ ማቀላቀል ክፍያ ተሰጥቷቸው ወደ ማህበረሰቡ እንደሚሸኙም ተገልጿል፡፡


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

20 Nov, 04:08


አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ የሮጠበት ማልያ በ2400 ዶላር ተሸጠ

በበርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ስኬታማ አትሌት የሆነው ሀይሌ ገብረስላሴ የሮጠበት አንድ ማልያ በ2 ሺህ 400 ዶላር ተሸጧል፡፡

በአዲስ አበባ በተካሄደ በዚህ ጨረታ ላይ የቀረበው ይህ ማልያ አትሌት ሀይሌ በ1992 በደቡብ ኮሪያ ሴኡል ከተማ በተካሄደው የ10 ሺህ ሜትር ውድድርን ያሸነፈበት ማልያ ነበር፡፡

ይህ ውድድር ለአትሌት ሀይሌ ገብረ ስላሴ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የጀመረበት ወቅት እንደነበርም ተገልጿል፡፡

የታላቁ ሩጫ መስራች እና ባለቤት አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ ለጨረታ ቀርቦ 2 ሺሕ 400 ዶላር የተሸጠው ማልያ የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን ለማጠናከር ይውላልም ተብሏል፡፡

በጨረታው የታላቁ ሩጫ ባዘጋጀው የእራት ግብዣ ፕሮግራም ላይ የኃይሌ ገ/ሥላሴ የሮጠበት ማልያ፤ በእንግሊዛዊ ተጋባዥ እንግዳ አሸንፏል።

ተጨማሪ ያንብቡ https://bit.ly/4fTp5XJ

#Ethiopia #athletics

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

19 Nov, 15:03


የማክሰኞ ህዳር 10 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

የአዲስ አበባ ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ አቶ ሰይድ አሊ የተባሉ የምክር ቤት አባልን ያለመከሰስ መብት ማንሳቱ ተገልጿል። አቶ ሰይድ አሊ ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው መሆኑ ተጠቁሟል።የምክር ቤት አባሉ ከዚህ በፊት የኮሪደር ልማት ፕሮጀክትን ሽፋን በማድረግ ያለአግባብ "ስድስት የመኖሪያ እና አንድ የንግድ ቤት በማፍረስ ቦታው ለግለ አፓርትመንት ገንቢ ባለሀብት ተላልፎ እንዲሰጥ” በማድረግ መጠርጠራቸውን አመልክቷል።

በትግራይ ክልል የማዕከላዊ ዞን አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን መዓሾ ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች በተፈጸመባቸው ‘የግድያ ሙከራ’ መትረፋቸውን ተናገሩ። አስተዳዳሪው እሁድ ኅዳር 8/2017 ዓ.ም. ከሰአት በኋላ በሥራ ምክንያት ከ አክሱም ወደ መቀለ ከተማ በመጓዝ ላይ እያሉ ጥቃቱ እንደተፈጸመባቸው ለቢቢሲ ትግርኛ ገልጸዋል።ድርጊቱ በእርሳቸው ላይ ያነጣጠረ “የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸው ሊሆን እንደሚችል” የተናገሩት አቶ ሰለሞን በእርሳቸው ላይም ሆነ አብሯቸው በመኪናው ውስጥ የነበሩት የግል ጠባቂያቸው እና ሹፌራቸው ምንም ዓይነት ጉዳት ባይደርስባቸውም፣ መኪናቸው አራት ቦታ በጥይት እንደተመታ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል አጀንዳ እና ተሳታፊዎችን ለመለየት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን እገዛ እንደሚፈልግ ገለጸ።
የተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በበኩላቸው “[አስቻይ] ሁኔታ ለመፍጠር ጠንካራ ሥራ በጋራ ተቀናጅተን እንሠራለን። ከክልሉም ጋር እንመካከራለን” ብለዋል። ይህ የተባለው ኮሚሽኑ ዛሬ ማክሰኞ ኅዳር 10/2017 ዓ.ም. የአፈጻጸም ሪፖርቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበበት ወቅት ነው።

የሶማሊላንድ ተቃዋሚ ፓርቲ የሆነው የዋዳኒ ፓርቲ መሪ የሆኑት አብዲራህማን ሞሀመድ አብዲላሂ (ሲሮ) የወቅቱን የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቤሂ አብዲን አሸንፈዋል።የሶማሊላንድ ምርጫ ኮሚሽን የዋዳኒ ፓርቲ እጩ አብዲራህማን መሀመድ አብዲላሂ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸውን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ አብዲራህማን ሥድስተኛው የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት ይሆናሉ ተብሏል።በሶማሊላንድ ባሳለፍነው ሳምንት ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ.ም የተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የሶማሊላንድ ብሔራዊ ምርጫ ኮሚሽን "ግልጸኝነት የተሞላበት የመራጮች ምዝገባ እና የእጩዎች ማቅረቢያ ሂደትን አካሂዷል።" በሚል ከዓለም አቀፍ አጋሮች አድናቆት ተችሮታል።

የዘንድሮው ጉባኤ 2030 600 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎችን ከድህነት ለማውጣት ስትራቴጂ የሚነደፍበት ነው ተብሏልየአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለአለም ባንክ በአለም አቀፍ ልማት ትብብር ፈንድ በኩል ለድሀ ሀገራት የሚከፋፈል 4 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ለመስጠት ቃል መግባታቸው ተነግሯል፡፡ በብራዚል ሪዮዲጂኔሮ እየተካሄደ በሚገኘው የዘንድሮ የቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ከሌሎች የአለም መሪዎች ጋር እየመከሩ የሚገኙት ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ድህነት ቅነሳ እና ርሀብን ማስወገድ ላይ አባላቱ በቅርበት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

19 Nov, 14:24


በትግራይ ክልል የማዕከላዊ ዞን አስተዳዳሪ በታጣቂዎች ‘የግድያ ሙከራ’ እንደተደረገባቸው ተናገሩ

በትግራይ ክልል የማዕከላዊ ዞን አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን መዓሾ ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች በተፈጸመባቸው ‘የግድያ ሙከራ’ መትረፋቸውን ተናገሩ።

አስተዳዳሪው እሁድ ኅዳር 8/2017 ዓ.ም. ከሰአት በኋላ በሥራ ምክንያት ከአክሱም ወደ መቀለ ከተማ በመጓዝ ላይ እያሉ ጥቃቱ እንደተፈጸመባቸው ለቢቢሲ ትግርኛ ገልጸዋል።

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የክልሉ ማዕከላዊ ዞን አስተዳዳሪ ሆነው የተሾሙት አቶ ሰለሞን ላይ የተፈጸመውን የግድያ ሙከራ በተመለከተ እስካሁን ድረስ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ የለም።

ድርጊቱ በእርሳቸው ላይ ያነጣጠረ “የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸው ሊሆን እንደሚችል” የተናገሩት አቶ ሰለሞን በእርሳቸው ላይም ሆነ አብሯቸው በመኪናው ውስጥ የነበሩት የግል ጠባቂያቸው እና ሹፌራቸው ምንም ዓይነት ጉዳት ባይደርስባቸውም፣ መኪናቸው አራት ቦታ በጥይት እንደተመታ አረጋግጠዋል።

አቶ ሰለሞን በማዕከላዊ ዞን ያለውን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተም በአሁኑ ወቅት እጅግ አስቸጋሪ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን እና በበርካታ ሰዎች ላይ ጥቃት እና ግድያዎችም እንደሚፈጸሙ አመልክተዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

19 Nov, 12:35


አዲስ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

ዳሸን ባንክ በተለያዩ የስራ መስኮች አዲስ ሰራተኞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ አውጥቷል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለማመልከት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://ethionegari.com/2024/11/19/dashen-bank-wants-to-hire-the-following-positions/

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

19 Nov, 09:50


የሶማሊላንድ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ አብዲራህማን ሞሀመድ ሥድስተኛው የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

የሶማሊላንድ ተቃዋሚ ፓርቲ የሆነው የዋዳኒ ፓርቲ መሪ የሆኑት አብዲራህማን ሞሀመድ አብዲላሂ (ሲሮ) የወቅቱን የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቤሂ አብዲን ማሸነፋቸውን ሆርን ዲፕሎማት ዘግቧል።

የሶማሊላንድ ምርጫ ኮሚሽን የዋዳኒ ፓርቲ እጩ አብዲራህማን መሀመድ አብዲላሂ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸውን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ አብዲራህማን ሥድስተኛው የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት ይሆናሉ ተብሏል።

በሶማሊላንድ ባሳለፍነው ሳምንት ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ.ም የተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የሶማሊላንድ ብሔራዊ ምርጫ ኮሚሽን "ግልጸኝነት የተሞላበት የመራጮች ምዝገባ እና የእጩዎች ማቅረቢያ ሂደትን አካሂዷል።" በሚል ከዓለም አቀፍ አጋሮች አድናቆት ተችሮታል።

ኢትዮጵያ በበኩሏ የሶማሌላንድ የምርጫ ኮሚሽን ነጻ እና ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄዱን አድንቃ "ሂደቱ የሶማሊላንድን የአስተዳደር እና የዲሞክራሲ ስርዓት ብስለት የሚያንፀባርቅ ነው" ስትል መግለጿ ይታወሳል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

18 Nov, 15:07


የሰኞ ህዳር 9 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከኤርትራ ጋር ሰላም መፍጠር እንደሚፈልጉ እና ዳግም ከኤርትራ ጋር ጦርነት ስለመግጠም ማውራት እንደማያስፈልግ አስታወቁ። አቶ ጌታቸው ከድርድሩ በፊት ግን ኤርትራ ለተፈጸሙ ጥፋቶች ሃላፊነት መውሰድ እንደሚገባ አመላክተዋል፤ “በሰላማዊ ሰዎች እና በሴቶች ላይ ጥቃት የፈጸሙት መያዝ አለባቸው” ሲሉ ጠቁመዋል። ስለፕሪቶርያው ስምምነት በጋዜጣው የተጠየቁት አቶ ጌታቸው “በርካታ ጦርነቱ እንዲቀጥል ለማድረግ ግፊት የሚፈጥሩ ሁኔታዎች ቢኖሩም በበርካታ የትግራይ ግዛቶች ላይ ጦርነት እንዳይኖር አድርጓል፣ የጥይት ድምጽ አስቁሟል” ሲሉ በመግለጽ ጠቃሚ ውጤት አስገኝቷል ብለዋል።

ሳዑዲ አረቢያ በፈረንጆቹ 2024 ዓ/ም 7 ኢትዮጵያውያን ጨምሮ ከ100 በላይ የውጪ ዜጎች በሞት ቀጣች መቅጣቷን የአገሪቱን ዜና ወኪሎች ጠቅሶ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል። ከሰባቱ ኢትዮጵያውያን በተጨማሪ የሞት ቀጣት ተፈጻሚ ከተደረገባቸው የውጭ ዜጎት መካከል 1 ኤርትራዊ፣ 3 ሱዳናውያን፣ 10 ናይጄሪያውያን፣ 9 ግብጻውያን፣ 21 ፓኪስታናውያን፣ 20 የመኒ፣ 14 ሶርያውያን ይገኙበታል።በዘገባው መሰረት በውጪ ዜጎች ላይ ተግባራዊ የሚሆነው የሞት ቅጣት ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ምክንያት ነው።

የቀድሞ ገዢው ፓርቲ ንብረት የሆኑት ዋልታ አዲስ ሚዲያንና ፋና ሚዲያ ኮርፖሬት (ራዲዮ ፋናን) በአንድ አጠቃሎ “ጠንካራ ሚዲያ” ለማድረግ በመንግስት አካላት ሲደረግ የነበረው ሂደት ተገባዶ ርክክብና ሽግግር እየተከናወነ መሆኑ ተሰምቷል። ካለፈው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ የማዋሀድ ስራው የተጀመረ ሲሆን የሁለቱን ሚዲያዎች አዲስ ጥምረት በቦርድ ስብሳቢነት እንዲመሩ የጠቅላይ ሚንስትሩ አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተመድበዋል። በስራ አስፈፃሚነት ደግሞ የራዲዮ ፋና ስራ አስኪያጅ አድማሱ ዳምጠው እንዲቀጥሉ ተወስኗል። ሌሎች የበታች አመራሮችን የመመደብ ስራ በዚህ ሳምንት የሚቀጥል ሲሆን የዋልታ ሚዲያ ስራ አስፈፃሚ የነበሩት አቶ መሀመድ ሀሰን እስካሁን አልተመደቡም።

ሰሜን ኮርያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን የሀገሪቱ ጦር የውጊያ አቅሙን እንዲያሳድግ አሳሰቡ፡፡ 
በፒዮንግያንግ በተካሄደው የሻለቃ አዛዦች እና የፖለቲካ አስልጣኞች ኮንፈረንስ ላይ ባደረጉት ንግግር የሀገሪቱ ጦር ሀይል ጦርነትን መቋቋም እንዲችል፤ የፖለቲካ እና ወታደራዊ ጥንካሬን እንዲያጎለብት እና የውጊያ ቅልጥፍናን እንዲያሳድግ ጠይቀዋል። “ደቡብ ኮርያን ጨምሮ አሜሪካ እና አጋሮቿ ከሰሜን ኮርያ ጋር ያላቸው ወታደራዊ ፍጥጫ በታሪክ አስከፊ ደረጃ ላይ ደርሷል፤ ይህም የሰሜን ኮርያን ልሳነ ምድር ትልቁ የፍልሚያ ቦታ አድርጎታል” ያሉት ኪም፤ በሁሉም ወታደራዊ ዘርፍ ወሳኝ ለውጦችን ለማምጣት ሁሉም ርብርብ እንዲያደርጉ መጠየቃቸውን የሀገሪቱ ቴሌቪዥን ኬሲኤንኤ ዘግቧል፡፡

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ዩክሬን የአሜሪካን የረዥም ርቀት ሚሳኤሎች ተጠቅማ ሩሲያ ውስጥ ዒላማዎችን እንድትመታ መፍቀዳቸው ሩሲያን ውስጥ ቁጣ ቀሰቀሰ። የሩሲያ መንግሥት ጋዜጣ የሆነው ሮስያስካያ ጋዜት “ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በጣም የሚያስቆጣ እና ያልታሰበ ውሳኔ ላይ ደርሰዋል። ይህም ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል” ሲል አስነብቧል። ሩሲያዊው የሕዝብ እንደራሴ እና ለክሬምሊን ቅርብ የሆነው የሊበራል ዴሞክራሲ ፓርቲ ኃላፊ ሊዮኒድ ስላትስኪ ውሳኔው “ወደ ከፍተኛ ግጭት ያመራል” ብለዋል። ሩሲያዊው ሴናተር ቭላድሚር ዳባሮቭ “ወደ ሦስተኛው የዓለም ጦርነት የሚያስገባ” ሲሉ ውሳኔውን ኮንነዋል። ለክሬምሊን ቅርብ የሆነው ድረ ገጽ ኮምሶሞልካያ ፕራቭዳ “ይጠበቅ የነበረ ውጥረት ማባባስ” ሲል አስተያየት ሰጥቷል። የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እስካሁን ምንም አላሉም።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

18 Nov, 14:26


ኢትዮጵያ በሶስት ወራት ውስጥ ከ87 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገራት መላኳ ተገለጸ

የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል የሶስት ወራት እቅድ አፈጻጸማቸውን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበዋል፡፡

ሚኒስትሯ በዚህ ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ 140 ሺህ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ ለመላክ ታቅዶ ነበር ብለዋል፡፡

የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በዘንድሮ በጀት ዓመት 700 ሺህ ኢትዮጵያውያንን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ ለመላክ እቅድ እንደነበረውም ሚኒስትሯ አክለዋል፡፡

ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት 332 ሺህ ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ መላካቸውም ተገልጿል።

ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች የተላከባቸው ሀገራት ስድስት የመካከለኛው ምስራቅ እና ሁለት የአውሮፓ ሀገራት ናቸው።

ተጨማሪ ያንብቡ https://bit.ly/3OeRZpn

#Ethiopia #jobsearch

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

16 Nov, 15:16


የህዳር 7 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ችግርን በጠመንጃ ለመፍታት ለሚሞክሩ አካላት መንግስት ሕግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። በተለይ በአማራ ክልልና በኦሮሚያ ክልል ፅንፈኛ ኃይሎች ህፃናት እንዳይከተቡ፣ ወጣቶች ስራ አጥ እንዲሆኑና ልማት እንዳይረጋገጥ እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።

በቋሚ ደመወዝ ለሚተዳደሩ ሰራተኞች የሥራ ግብር መቀነስን ጨምሮ ሌሎች እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድን በደብዳቤ መጠየቃቸውን የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ ገለጹ። አቶ ካሣሁን እንደገለጹት የብር የመግዛት አቅም መዳከም ጋር ተያይዞ ቋሚ ደመወዝ የሚያገኙ ሰራተኞች ለከፍተኛ የኑሮ ፈተና እየተዳረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል። በመሆኑም የሥራ ግብር መቀነስን ጨምሮ ሌሎች የኑሮ ፈተናውን ሊያቀሉ የሚችሉ ኢኮኖሚያዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠቅላይ ሚንስትሩን በድጋሚ በደብዳቤ መጠየቃቸውን አመላክተዋል።

እስራኤል በሰሜን ምስራቅ ሊባኖስ የአደጋ ጊዜ ምላሽ ማዕከል ላይ በፈጸመችው ጥቃት 15 የነፍስ አድን ሰራተኞች መገደላቸውን የአገሪቱ ባለስልጣናት አስታወቁ።ሐሙስ፣ ኅዳር 6/ 2017 ዓ.ም በማዕከሉ ላይ የተፈጸመው ይህ ጥቃት በጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው ምላሽ እየሰጡ በነበሩ የነፍስ አድን ሰራተኞች ላይ የደረሰ የከፋ ጥቃት ተብሏል።በዱሪስ ከተማ በተፈጸመው ጥቃት ከሊባኖስ መንግሥት ጋር አብሮ የሚሰራው የሲቪል መከላከያ ኤጀንሲ ህንጻ ወድሟል። በዚህ ጥቃት በከተማዋ የኤጀንሲው ኃላፊ ቢላል ራድ መገደላቸውን የግዛቲቷ አስተዳደር ባቺር ክሆድር ገልጸዋል። የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር “አረመኔያዊ” ሲል በፈረጀው በዚህ ጥቃት ላይ የእስራኤል ጦር ምንም አይነት መግለጫ አልሰጠም።

የዩናይትድ ኪንግደም ግዛት የዩክሬን ስደተኞችን በቤታቸው ተቀብለው ለሚያስጠልሉ በጎ ፈቃደኛ ቤተሰቦች 600 ፓውንድ ወይም 93 ሺህ ብር በየወሩ መውሰድ ይችላሉ አለች። ይህ ክፍያ ቤተሰቦቹ እያደረጉት ላለው በጎ ተግባር “ለማመስገን” እንደሆነ ግዛቲቷ ገልጻለች። ኤልምብሪጅ ቦሮው የተሰኘችው ግዛት አስተዳደር ቤታቸውን ከፍተው ዩክሬናውያንን እየተቀበሉ ላሉ ቤተሰቦች ገንዘብ መስጠት የጀመረው ከምስጋናው በተጨማሪ የኑሮ ውድነቱንም ከግምት ውስጥ በማስገባት መሆኑን አክሏል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

15 Nov, 15:04


የህዳር 6 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎና ሰሜን ሸዋ ዞኖች የሚገኙ መምህራን የጸጥታ ችግር ወደአለባቸውና ወደተመደቡባቸው የገጠር ት/ቤቶች ሄደው ሥራ እንዲጀምሩ በአካባቢው ባለሥልጣናት አስገዳጅ መመሪያ እንደወጣባቸው ገለጸዋል። መምህራኑ የተመደቡባቸው ቀበሌዎች በፌደራል መንግሥቱ እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከፍተኛ ግጭት የሚካሄድባቸው በመኾናቸው ለደህንነታቸው እንደሚሰጉ ተናግረዋል፡፡ እንዳይቀሩ ደግሞ ወደምድብ ቦታቸው ካልሄዱ ደሞዝ እንደማይከፈላቸው እንደተነገራቸው ገልጸዋል ሲል ቪኦኤ ዘግቧል።

በሶማሊያ ከሚሰማራው አዲሱ የአፍሪካ ኅብረት የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ ውጪ መደረጓ የተገለጸው ኢትዮጵያ አልሻባብን በማዳከም ተግባር እንደምትቀጥልበት አስታወቀች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ኢትዮጵያ የሶማሊያውን ታጣቂ ቡድን አልሻባብን ለማሽመድመድ ለዘመናት ያደረገችው ዘመቻ እንደሚቀጥል የተናገሩት ሐሙስ ኅዳር 5/2017 ዓ.ም. ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ነው። አምባሳደሩ “አልሻባብ ብሔራዊ ደኅንነታችን ላይ ስጋት የማይሆንበት ደረጃ እስኪደርስ እንዲሁም እስካሁን የተመዘገቡ ድሎች እንዳይቀለበሱ አልሻባብን ለማዳከም የተሰሩ ወሳኝ ሥራዎች በማንኛውም መንገድ ይቀጥላሉ” ብለዋል።

በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዞኖች ትናንት ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ/ም የተካሄዱት የሰላም ጥሪ ሰልፎች “በመንግስት የተመቻቹ ናቸው” መባሉን የክልሉ መንግስት “ከእውነት የራቀ” ሲል አስተባበለ። የኦሮሚያ ክልል መንግስት ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ “ህዝቡ ሰላምን ከመጠማቱ የተነሳ የወጣውን ሰላማዊ ሰልፍ በመንግስት አስተባባሪነት እንደተካሄደ ለማሳየት መሞከር ከእውነታ የራቀና የህዝቡን ቁስል በእንጨት መንካት እንደሆነ የሚታሰብ ነው” ብሏል። መግለጫው የወጣው በክልሉ የተካሄደውን ሰልፍ አስመልክቶ ከመንግስት ጋር ለአመታት የትጥቅ ግጭት በማካሄድ ላይ ያለው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት እና እንደ ጀዋር መሐመድ ያሉ ፖለቲከኞች በመንግስት ላይ ትችት መሰንዘራቸውን ተከትሎ ነው።

የሱዳን ጊዜያዊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት አሊ የሱፍ "በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ ውሳኔ ያላገኙ እና ያልተፈቱ ልዩነቶች ወደ ጦርነት ሊያመሩ ይችላሉ" ሲሉ የሰጡትን አስተያየት ተከትሎ ኢትዮጵያ የሱዳንን አምባሳደር ረቡዕ ዕለት ጠርታ ማነጋገሯን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል። ሚንስትሩ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙርያ የሚደረጉ ድርድሮች የማይሳኩ ከሆነ ሱዳን ከግብፅ ጋር ልትሰለፍ እንደምትችል ገልፀው ጦርነት የሶስቱንም ሀገራት የውሃ ተጠቃሚነት መብት የሚያረጋግጥ አማራጭ መሆኑን አስታውቀዋል።የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጉዳዩ ደስ አለመሰኘቱን ገልጾ በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት መግለጻቸውን ዘገባው አመልክቷል።

እስራኤል ባለፈው ዓመት 90 በመቶ የሚሆነው፣ 1.9 ሚሊዮን በጋዛ የሚኖሩ ፍልስጤማውያንን ከቀያቸውን ለቀው እንዲፈናቀሉ አድርጋለች ሲል ሂውማን ራይትሰ ዋች አስታወቋል።እስራኤል በሙሉ ከበባ ውስጥ ያስገባቻት ጋዛ 79 በመቶ የሚሆነው መሬቷም እስራኤል የማፈናቀል ትዕዛዝ ቁጥጥር ስር ያደረገችው እንደሆነ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገልጿል። እስራኤል በበኩሏ “በሂውማን ራይትስ ዋች ሪፖርት ከወጣው በተጻራሪ እስራኤል ጥረቷ የሃማስን የሽብር አቅም በማውደም ላይ ብቻ ያተኮረ እንጂ በጋዛ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ አይደለም” ሲሉ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኦረን ማርሞርስቴይን በኤክስ ገጻቸው አስፍረዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

15 Nov, 14:00


ኢትዮጵያ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙርያ በተሰጠ አስተያየት ምክንያት የሱዳን አምባሳደርን ጠርታ አነጋገረች!

የሱዳን ጊዜያዊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት አሊ የሱፍ "በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ ውሳኔ ያላገኙ እና ያልተፈቱ ልዩነቶች ወደ ጦርነት ሊያመሩ ይችላሉ" ሲሉ የሰጡትን አስተያየት ተከትሎ ኢትዮጵያ የሱዳንን አምባሳደር ረቡዕ ዕለት ጠርታ ማነጋገሯን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል።

ሚንስትሩ በቅርቡ በቴሌቭዥን ቀርበው ባደረጉት ቃለ ምልልስ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙርያ የሚደረጉ ድርድሮች የማይሳኩ ከሆነ ሱዳን ከግብፅ ጋር ልትሰለፍ እንደምትችል ገልፀው ጦርነት የሶስቱንም ሀገራት የውሃ ተጠቃሚነት መብት የሚያረጋግጥ አማራጭ መሆኑን አስታውቀዋል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሱዳን አምባሳደር አልዘይን ኢብራሂም ጋር ባደረገው ውይይት በጉዳዩ ደስ አለመሰኘቱን ገልጾ በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት መግለጻቸውን ዘገባው አመልክቷል።የሱዳን ጊዜያዊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት አሊ የሱፍ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ ሊሰጡ በቅርቡ ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ እንደሚችሉ የዲፕሎማቲክ ምንጮች ጠቁመዋል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የሆኑት አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ትናንት ህዳር 5 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር ያላትን “የዳበረ እና ስትራቴጂካዊ” ግንኙነት በመጥቀስ የህዳሴ ግድብ ጉዳይን በውይይት ለመፍታት ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።አክለውም ኢትዮጵያ ላለፉት 13 ዓመታት ካካበተችው ልምድ ግድቡ በታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ላይ ጉዳት እንደሌለው የሚያረጋግጥ መሆኑንና ይልቁኑ ቀጠናዊ ትብብርን እንደሚያጠናክር አጽንኦት ሰጥተዋል።

ምንጭ - ቪኦኤ

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

15 Nov, 12:14


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ‘ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ’ ሽልማትን አገኘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2024 የቢዝነስ ተጓዦች ሽልማት ውድድር ‘ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ’ በመባል መሸለሙን ገለጿል።

አየር መንገዱ ሽልማቱን ለተከታታይ አምስተኛ አመት ማግኘቱን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

14 Nov, 15:04


የህዳር 5 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

- የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ “የዜጎችን ህይወት የመጠበቅ ሃላፊነት ያለበት መንግሥት ቢሆንም በሚያሰማራቸው የጸጥታ ሃይሎችና የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ጭምር የዜጎች ህይወት በበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች እንደቅጠል እያረገፈ ይገኛል” ብሏል፡፡ኢሕአፓ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ህገመንግሥቱን የመንግሥት አካላት ራሳቸው ካላከበሩት እንዴት ሊያስከብሩት ይችላሉ “በንጹሀን ዜጎች ላይ የሚደረጉት ግድያዎች ይቁሙ” ሲል አሳስቧል፡፡

- በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ ኦቦራ በተሰኘ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ከ130 በላይ ሰላማዊ ሰዎች “ከኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አባላት ጋር ቤተሰባዊ ግንኙነት አላችሁ” በሚል ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ከሰባት ወራት በላይ ታስረው እንደሚገኙ የታሳሪ ቤተሰቦች ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጸዋል።

- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ላኪዎች ያመነጩትን የውጭ ምንዛሬ 50 በመቶ ወዲያውኑ በመሸጥ ቀሪውን 50 በመቶ ላልተወሰነ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለ አካውንታቸው ማስቀመጥ የሚችሉበት አሰራር ከዛሬ ህዳር 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ አስታወቀ። በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፊት ከነበረበት 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር በአሁኑ ወቅት 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የባንኩ ገዥ ማሞ ምህረቱ ገለጸዋል።

- በአምስተርዳም የማካቢ ቴል አቪቭ ደጋፊዎች ጥቃት ከደረሰባቸው በኋላ በፈረንሳይ እና እስራኤል ብሔራዊ ቡድኖች መካከል የሚደረገውን ጨዋታ ለመጠበቅ በሺህዎች የሚቆጠሩ ፖሊሶች በፓሪስ ተሰማርተዋል። የፓሪስ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ላውረንት ኑኔዝ እንዳስታወቁት 4 ሺህ ፖሊሶች ከተማዋን ሲቃኙ ይውላሉ፤ 2 ሺህ 500 የሚሆኑት ደግሞ በስታድ ደ ፍራንስ ስታዲየምና በህዝብ ትራንስፖርት መስጫዎች ይሰማራሉ። 1 ሺህ 600 የግል የደህንነት ባለሙያዎች እና የጸረ ሽብር ፖሊስ አባላት ደግሞ በስታዲየሙ ውስጥ የእስራኤል ተጫዋቾች እና ደጋፊዎችን በንቃት ይጠብቃሉ ነው ያሉት ኑኔዝ።

- ራስ ገዟ ሶማሊላንድ በትናንትናው እለት ያካሄደችው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን አስታወቀች።ከ1 ሚሊየን በላይ ሰዎች በ2 ሺህ የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ድምጻቸውን ሰጥተው ከምሽት ጀምሮ ቆጠራ መጀመሩን የሶማሊላንድ ምርጫ ኮሚሽን ገልጿል።የፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ውጤት ህዳር 12 2017 በይፋ እንደሚገለጽም ነው የኮሚሽኑ ሊቀመንበር ሙሴ ሃሰን ዩሱፍ የተናገሩት።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

14 Nov, 06:07


የአበረታች ቅመምችን የተጠቀሙ ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከማንኛውም ስፖርታዊ ውድድሮች ታገዱ

የአለም አትሌቲክስ እና ብሔራዊ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን የአበረታች ቅመምች ህግ ጥሰት በፈፀሙ አትሌቶች ላይ የቅጣት ውሳኔ ማስተላለፉ ተገልጿል።

የቅጣት ውሳኔው ከተላለፈባቸው አትሌቶች መካከል አትሌት ሳሙኤል አባተ ዘለቀ ፣ አትሌት ፀሐይ ገመቹ በያን እና አትሌት ህብስት ጥላሁን አስረስ ሲሆኑ የአበረታች ቅመሞች ህግ ጥሰት መፈጸማቸው ተረጋግጧል ተብሏል።

ጥሰቱን ተከትሎም አትሌት ሳሙኤል አባተ ዘለቀ የካቲት 2015 ዓ.ም በተካሄደው ምርመራ ኢፒኦ የተባለውን የተከለከለ ንጥረ ነገር መጠቀሙ ተረጋግጧል፡፡

በዚህም መሰረት አትሌት ሳሙኤል አባተ ለ2 ዓመታት ማለትም እስከ ሚያዝያ 2018 ዓ.ም ድረስ በማንኛውም የስፖርት ውድድር እንዳይሳተፍ ቅጣት ተጥሎበታል፡፡

አትሌት ፀሐይ ገመቹ በያን በተደረገላት የአትሌት ባይሎጂካል ፖስፖርት (ABP) ምርመራ አበረታች ቅመም መጠቀሟ የተረጋገጠባት ሌላኛዋ ኢትዮጵያ አትሌት ስትሆን ለአራት ዓመታት እገዳ ተጥሎባታል ተብሏል፡፡

አትሌቷ ከህዳር 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ህዳር 2019 ዓ.ም ድረስ ለአራት በማንኛውም የስፖርት ውድድር እንዳትሳተፍ ቅጣት እንደተጣለባት ውሳኔውን ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

እንዲሁም አትሌት ህብስት ጥላሁን አስረስ ቻይና ሀገር ውስጥ በነበረው ውድድር ላይ በተካሄደው ምርመራ ትሪያምሲቦሎን አሴቶናይድ የተባለውን በውድድር ወቅት የተከለከለ ንጥረ ነገር መጠቀሟ በመረጋገጡ ለ2 ዓመታት በማንኛውም የስፖርት ውድድር እንዳትሳተፍ ቅጣት ተጥሎባታል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

13 Nov, 15:24


የህዳር 4 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

- በፍራንኮ ቫሉታ ከውጭ የሚገቡ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች በመደበኛ የንግድ ባንኮች የመተማመኛ ሰነድ (ኤል ሲ) አማካኝነት እንዲገቡ መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ገለጹ፡፡ አቶ አህመድ የፍራንኮ ቫሉታ ባልተገባ መንገድ ለጥቁር ገበያ በመጋለጡ በውጭ ምንዛሬ ላይ ጫና በማሳደር ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ አመዝኗል ብለዋል፡፡ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራው በመደበኛውና በትይዩ ገበያው መካከል ያለውን የውጭ ምንዛሬ ተመን ተቀራራቢ በማድረጉ የፍራንኮ ቫሉታ እንዲነሳ መደረጉንም ገልጸዋል፡፡

- በኢትዮጵያ የሚኖሩ ኤርትራውያን ወደ ሌሎች ሀገራት ለመሄድ ሲፈልጉ የመውጫ ቪዛ ለማስመታት እስከ 4ሺህ ዶላር የሚደርስ የተጋነነ ክፍያ እየተጠየቁ መሆናቸውን ገልጸዋል። የክፍያው ምክንያት ግልፅ እንዳልኾነና ወጥነትም እንደሌለው የተናገሩት ኤርትራውያኑ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የክፍያውን መጠን ዳግም እንዲመለከተው መጠየቃቸውን የአሜሪካ ድምጽ ዘግቧል። የኢሚግሬሽና ዜግነት አገልግሎት በበኩሉ፣ እየተጠየቀ ያለው ክፍያ፣ ለመውጫ ቪዛ ሳይሆን፣ በሕገወጥ መንገድ ለቆዩበት ጊዜ የሚወሰን ቅጣት ነው ማለቱን ዘገባው አመላክቷል፡፡

- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዘንድሮ በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ውስጥ የሰበሰበው ገቢ፤ በእቅድ ይዞት ከነበረው በ10 ቢሊየን ብር ያነሰ መሆኑን ገለጸ። በዚህ ጊዜ ውስጥ ከውጭ እርዳታ እና ብድር የተገኘው ገቢም፤ ከታቀደው ከግማሽ በታች መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል።በከተማይቱ እየተተገበሩ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቁ ሆነው ሳለ፤ በበጀት ዓመቱ ሶስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ መቀነሱ “ትኩረት የሚያሻው” መሆኑ ተገልጿል ሲል ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

- ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደራቸውን የሚቀላቀሉ ሹመኞችን እያስታወቁ ነው። የጽሕህት ቤት ኃላፊ፣ የድንበር ኃላፊ፣ የተባበሩት መንግሥታት የአሜሪካ አምባሳደርን እና የአካባቢ ጥበቃ ኤጀንሲ ኃላፊ ሚሆኑት ግለሰቦችን ይፋ አድርገዋል። የምርጫ ቅስቀሳቸውን የመሩት ሱዚ ዊልስ የመጀመሪያዋ ሴት የጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል። የመጀመሪያው የትራምፕ የሥልጣን ዘመን ከጎናቸው ነበሩት ቶም ሆማን ደግሞ ከድንበር እና ከስደት ጋር በተያያዘ ጉዳይ ላይ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ። ፕሬዝዳንቱ አራት ሺህ የሚጠጉ ፖለቲካዊ ሹመቶችን የመስጠት ኃላፊነት አለባቸው።

- የእስራኤል ጦር 14 ሺህ የሀማስ እና 2550 የሄዝቦላ ተዋጊዎችን መግደሉን አስታውቋል። ሄዝቦላህ እና ሀማስ በእስራኤል ላይ አዲስ ጥቃት የመክፈት አቅማቸው በእጅጉ መቀነሱን አሜሪካ አስታወቀች። እስራኤል በሊባኖስ እና ጋዛ ባካሄደችው ወታደራዊ ዘመቻ እና የአየር ጥቃት ሀማስ እና ሄዝቦላህ በሀገሪቱ ላይ ዳግም ጥቃት የማድረስ አቅማቸውን እንደቀነሰው አሜሪካ ገልጻለች፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

13 Nov, 14:23


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሦስት ሶስት ወራት ውስጥ የሰበሰበው ገቢ፤ በእቅድ ይዞት ከነበረው በ10 ቢሊየን ብር ያነሰ መሆኑ ተገለፀ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዘንድሮ በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ውስጥ የሰበሰበው ገቢ፤ በእቅድ ይዞት ከነበረው በ10 ቢሊየን ብር ያነሰ መሆኑን ገለጸ።

በዚህ ጊዜ ውስጥ ከውጭ እርዳታ እና ብድር የተገኘው ገቢም፤ ከታቀደው ከግማሽ በታች መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል።

በከተማይቱ እየተተገበሩ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቁ ሆነው ሳለ፤ በበጀት ዓመቱ ሶስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ መቀነሱ “ትኩረት የሚያሻው” መሆኑ ተገልጿል።

ይህ የተገለጸው፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 በጀት አመት አንደኛ የሩብ አመት የስራ አፈጻጸሙን ትላንት ማክሰኞ ህዳር 3፤ 2017 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የመሰብሰቢያ አዳራሽ በገመገመበት ወቅት ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዘንድሮ በጀት አመት ለመሰብሰብ ያቀደው ጠቅላላ የገቢ መጠን 230 ቢሊየን ብር ነው።

የከተማ አስተዳደሩ ይህን ገንዘብ የሚሰበስበው፤ ክታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች፣ ከማዘጋጃ ቤት ገቢዎች፣ ከመንገድ ፈንድ እንዲሁም ከውጭ እርዳታ እና ብድር እንደሆነ በዘንድሮ በጀት አዋጅ ላይ ሰፍሯል።

ምንጭ - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

13 Nov, 13:39


ፍራንኮ ቫሉታ በውጭ ምንዛሬ ላይ ጫና በማሳደር ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ አመዝኗል ተባለ

የፍራንኮ ቫሉታ ባልተገባ መንገድ ለጥቁር ገበያ በመጋለጡ በውጭ ምንዛሬ ላይ ጫና በማሳደር ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ አመዝኗል ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ተናግረዋል፡፡

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራው በመደበኛውና በትይዩ ገበያው መካከል ያለውን የውጭ ምንዛሬ ተመን ተቀራራቢ በማድረጉ የፍራንኮ ቫሉታ እንዲነሳ መደረጉን ገልጸዋል፡፡

መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ውስጥ የማስገባት ውሳኔ ሙሉ በሙሉ እንዲቆም መደረጉንም ተናግረዋል፡፡

በሂደት ላይ ያሉ ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች በሁለት ሳምንታት ውስጥ እንዲገቡ እንደሚደረግም አስታውቀዋል፡፡

በውሳኔው መሰረትም ከውጭ የሚመጡ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች በንግድ ባንኮች የመተማመኛ ሰነድ ብቻ እንዲገቡ መወሰኑንና ይህም ወደ ተግባር መግባቱን አረጋግጠዋል፡፡

የንግድ ባንኮች ለመረሰታዊ ሸቀጦች የሚሆን በቂ የውጭ ምንዛሪ ክምችት እንዳላቸው ጠቅሰው÷ ባንኮች ለሸቀጦች ትኩረት ሰጥተው የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት እንዲያሻሽሉ ይደረጋል ነው ያሉት፡፡

መንግሥት የመሰረታዊ ሸቀጦችን አቅርቦትና ዋጋ በማረጋጋት የፖሊሲ ርምጃው ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚያደርግም አመላክተዋል፡፡

መንግስት በወሰዳቸው የቁጥጥርና የፖሊሲ ርምጃዎች በትይዩ ገበያውና በመደበኛ ገበያው መካከል ያለው ልዩነት መጥበቡንም አስድተዋል፡፡

በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራው የውጭ ምንዛሪ ተመን መዋዠቅ አላጋጠመም ያሉት ሚኒስትሩ÷ በቀጣይም በብሔራዊ ባንክ በኩል የተጠናከረ ክትትል ይደረጋል ብለዋል ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

12 Nov, 15:08


የህዳር 3 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

አዲሱ የኢትዮጵያ ሚዲያ ህግ ማሻሻያ ከሚዲያ እና ህግ ባለሙያዎች ማህበራት ተቃውሞ ገጥሞታል። 14 የጋዜጠኞች፣ ህግ እና ሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ማህበራት በጋራ ባወጡት መግለጫ የሚዲያ ህግ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የሕዝብንም ሆነ የባለድርሻ አካላትን ድምፅ በተገቢ ያላካተተ ነው ሲሉ ተችተዋል፡፡ የሚዲያ ህግ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ሁሉን ያሳተፈ ውይይት በአስቸኳይ እንዲደረግበትም ተጠይቋል፡፡

በትግራይ ሰላም እና ጸጥታ እንዲሰፍን ድጋፍ እናደርጋለን ሲሉ ክልሉን የጎበኙ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ የእንግሊዝ፣ ጀርመን እና ኔዘርላንድ አምባሳደሮች አስታወቀ‍ዋል።
አምባሳደሮቹ በክልሉ ደጉዓ ተምቤን ወረዳ የጎበኙ ሲሆን ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን ተጠቁሟል። አቶ ጌታቸው ለአምባሳደሮቹ የአውሮፓ ህብረትና ሌሎች ሀገራት ለትግራይ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መጠየቃቸው ተመላክቷል።።

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር፣ የዩኒቨርሲቲ መምህራን የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታና ነጻ ህክምና እንዲያገኙ ለመንግሥት ጥያቄ አቀረቧል። ማህበሩ ለትምህርት ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ፣ እንደሌሎች የመንግሥት ሠራተኞች ሁሉ፣ መምህራንም የበረሃና የውርጭ አበል እንዲከፈላቸውም ጠይቋል፡፡

የሳዑዲ ልዑል አልጋ ወራሽ መሐመድ ቢን ሰልማን እስራኤል በጋዛ ‘የዘር ጭፍጨፋ’ እየፈጸመች ነው ብለዋል። ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ በአደባባይ እስራኤል ላይ የሰላ ትችት ያሰሙት ልዑል አልጋ ወራሹ የእስራኤልን ድርጊት ኮንነዋል።የሙስሊምና አረብ አገራት መሪዎች ጉባዔ ላይ እስራኤል በሊባኖስና በኢራን የፈጸመችውንም ጥቃት አውግዘዋል።በሪያድና ቴህራን መካከል ያለው ግንኙነት እየተሻሻለ መሆኑን በሚጠቁም ሁኔታ እስራኤል ኢራን ላይ የምታደርሰውን ጥቃት በተመለከተም ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።

የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ድንበር በመጣስ በምዕራብ ሩሲያ ጥቃት እየፈጸመ ያለው የዩክሬን ጦር አሁን ላይ ከ50ሺ ወታደሮች ጋር ሊዋጋ መሆኑን ገልጸዋል። ዘለንስኪ በሰጡት እለታዊ መግለጫ እንደተናገሩት ዘመቻው ሞስሶ በዩክሬን ውስጥ ያላትን የማጥቃት አቅም ቀንሷታል። ፕሬዝደንቱ የጥቃቱ አላማ ይህ መሆኑን ለረጅም ጊዜ ሲገልጹ ቢቆዩም የተወሰኑ ምዕራባውያን አጋሮቻቸው ግን በጥርጣሬ እየተመለከቱት ነው።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

12 Nov, 11:03


አዲስ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

በተለያዩ የስራ መስኮች የወጡ የNGO ስራዎችን በዝርዝር ለመመልከት እና ለማመልከት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://ethionegari.com/2024/11/12/latest-ngo-job-openings-in-ethiopia-2/

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

12 Nov, 08:31


አዲሱ የኢትዮጵያ ሚዲያ ህግ ማሻሻያ ከሚዲያ እና ህግ ባለሙያዎች ማህበራት ተቃውሞ ገጠመው

የሚዲያ ህግ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ሁሉን ያሳተፈ ውይይት በአስቸኳይ እንዲደረግበት  ተጠይቋል፡፡

ከአንድ ወር በፊት በስራ ላይ ያለው የሚዲያ ህግ እንዲሻሻል ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡ ይታወሳል፡፡

ይህ ረቂቅ አዋጅ በቂ የባለድርሻ አካላት ውይይት ሳይደረግበት ወደ ቋሚ ኮሚቴ መመራቱ ትክክል እንዳልሆነ በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የጋዜጠኞች፣ ህግ እና ሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ማህበራት ተችተዋል፡፡

14 የጋዜጠኞች፣ ህግ እና ሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ማህበራት በጋራ ባወጡት መግለጫ የሚዲያ ህግ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የሕዝብንም ሆነ የባለድርሻ አካላትን ድምፅ በተገቢ ያላካተተ ነው ሲሉ ተችተዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ https://bit.ly/3O0JD4O

#ethiopia #media #Journalism #medialaw

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

11 Nov, 15:01


የህዳር 2 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና ዜናዎች

- በሰሜን ወሎ ዞን የቆቦ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ደርቤ በለጠ በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት ተገድለዋል። እንዲሁም በስፍራው የነበሩ 4 ሰዎች ቆስለዋል ተብሏል። የጥቃቱ ፈጻሚዎች የ"ፋኖ" ታጣቂዎች መሆናቸውን አንድ ነዋሪ ለአዲስ ስታንዳርድ ገልጸው፤ ከእሳቸው በተጨማሪ የቆቦ ከተማ የመሬት ደስክ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ የነበሩት ዶ/ር አዲሱ ወዳጆ እግራቸው አከባቢ በጥይት ተመተው መቁሰላቸውን ተናግረዋል።

- ከአፍሪካ ሀገራት ተወጣጥቶ በቀጣይ ተልዕኮ ተሰጥቶት በሶማሊያ ከሚሰፍረው የሰላም አስከባሪ ጦር ውስጥ የኢትዮጵያ ሰራዊት እንደማይሳተፍ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱልቃድር ሞሃመድ ኑር አስታወቀዋል። የአፍሪካ ህብረት በበኩሉ የሶማሊያ ድጋፍና ማረጋጋት ተልዕኮ ( AWSSOM) ን የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ በአዲሱ የሰላም አስከባሪ ሃይል ላይ የሶማሊያን ሉዓላዊነት የሚያከብሩ አገራት ብቻ ይሳተፉ የሚል ውሳኔ አስተላልፏል።

- በዶ/ር ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው እና በነሃሴ ወር ጉባኤ ያካሄደው የህወሓት ቡድን በጊዜያዊ አስተዳደሩ ላይ ይፋዊ የመፈንቅለ መንግስት እያካሄደ ነው ሲል ትላንት ህዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም የጊዜያዊ አስተዳደሩ ባወጣው መግለጫ አስታወቋል።“ይህ ቡድን የመንግስት ስራዎችን ከማደናቀፍ አልፎ ይፋዊ የመፈንቅለ መንግስትን ወደ መፈፀምና ፍፁም ስርዓት አልበኝት ወደ ማስፋፋት ተሸጋግሯል” ብሏል።

- ትራምፕ እና ፑቲን በስልክ ተወያዩ የሚለው መረጃ ሀሰት ነው ሲል ክሬሚሊን አስተባብሏል። ተመድ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በትላንትናው ዕለት በስልክ ተወያይተዋል የሚል ዘገባ ወጥቶ ነበር።የስልክ ውይይቱ በዩክሬን ላይ ያተኮረ መሆኑን ትራምፕ ፑቲን የዩክሬንን ጦርነት ከማባባስ እንዲቆጠቡ ማሳሰባቸውን የሚል ነበር ዘገባው።በዛሬው ዕለት ሁለቱ መሪዎች መወያየታቸውን የሚጠቅሱ ዘገባዎች በሮይተርስ እና ዋሽግተን ፖስት ከተሰራጨ በኋላ ክሪምሊን መረጃው ሀሰት ነው ሲል አስተባብሏል፡፡

- የሩሲያ እና የዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ ሁለቱም አገራት ግዙፍ የተባለውን የሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮን) ጥቃት ፈጽመዋል። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር በስድስት ክልሎች 84 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖች ማክሸፉን ገልጿል። አንዳንዶቹ ሞስኮ ዒላማ ያደረጉ እንደነበር ተገልጿል። በዚህም ምክንያት ከዋና ከተማዋ ዋና ዋና ሦስት አውሮፕላን ማረፊያዎች የሚነሱ እና የሚያርፉ በረራዎች እንዲቀየሩ ተገደዋል። የዩክሬን አየር ኃይል በበኩሉ ሩሲያ ቅዳሜ ምሽት 145 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ወደ ሁሉም የአገሪቱ ክፍል መላኳን እና አብዛኞቹ መመታታቸውን አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

11 Nov, 08:21


የአፍሪካ ህብረት በአዲሱ የሰላም አስከባሪ ሃይል ላይ የሶማሊያን ሉዓላዊነት የሚያከብሩ አገራት ብቻ እንደሚሳተፉ ገለፀ

የአፍሪካ ህብረት (ATMIS)ን በሚተካው የአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ድጋፍና ማረጋጋት ተልዕኮ ( AWSSOM) ን የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ በአዲሱ የሰላም አስከባሪ ሃይል ላይ የሶማሊያን ሉዓላዊነት የሚያከብሩ አገራት ብቻ ይሳተፉ የሚል ውሳኔ አስተላልፏል።

የኅብረቱ ሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ በቀጣይ በሶማሊያ ለሚሰማራው የአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ድጋፍና ማረጋጋት ተልዕኮ (AUSSOM) ወታደሮችን ለማዋጣት ዝግጁ መሆናቸውን ከገለጹ የአፍሪካ አገሮች ጋር ምክክር እንዲያደርግ መመርያ መስጠቱን አስታውቋል።

ኅብረቱ በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን፣ በውሳኔውም በሁለቱ አገሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት በአስቸኳይ ሰላማዊ መፍትሔ እንዲያገኝ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ከሚመለከታቸው የአኅጉሪቱ የኢኮኖሚ ማኅበረሰቦች፣ ቀጣናዊ ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እንዲሠሩ አቅጣጫ አስቀምጧል። 

የሶማሊያ መከላከያ ሚኒስትር አብዱልቃድር መሀመድ ኑር ኢትዮጵያ በመጪው ጥር 2025 በሚጀመረው የአፍሪካ ህብረት ድጋፍ ተልዕኮ (#AUSSOM) ውስጥ አትሳተፍም ሲሉ ቅዳሜ እለት መናገራቸው ይታወሳል።


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

09 Nov, 16:33


የጥቅምት 30 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና መረጃዎች

- የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በእጣ እና በጨረታ ተላልፈው ነዋሪ ያልገባባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች እስከ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ድረስ የቤት ባለቤቶቹ የማይገቡበት ከሆነ ውል የሚቋረጥ መሆኑን የገለፀ ቢሆንም ዛሬ በሰጠዉ ማስጠንቀቂያ ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ህዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም. ማራዘሙን አስታውቋል።

- የተፈቀደው የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ ክፍያ ዘግይቷል፥ ቀርቷል የሚሉ ሃሳቦች አሳሳች ናቸው ሲሉ የሲቪል ሰርቪስ ኮምሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ገልፀዋል።ኮሚሽነሩ “የገንዘብ ሚኒስቴር የተጨማሪ ክፍያ በጀቱን ለሚመለከታቸው ተቋማት ፈቅዷል። በእኛ መስሪያ ቤትም በኩል የተስተካከለውን የጥቅምት ወር ደመወዝ ተከፍሏል። ሌሎችም እንደዚሁ የከፈሉ አሉ። የቀሩት ደግሞ የማጥራት ሥራ እየሰሩ ሊሆን ይችላል። እነዚያም ዝግጅታቸውን ሲያጠናቅቁ የተስተካከለው የጥቅምት ወር ክፍያ ታሳቢ በማድረግ የሚከፍሉ ይሆናል” ብለዋል።

- የትግራይ ክልል የመምህራን ማህበር የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር እና የፌደራል መንግስቱ ለ17 ወራት ለክልሉ መምህራን መከፈል የነበረበትን ደመወዝ ባለመክፈላቸው ክስ መስርቷል። የማህበሩ ጠበቃ የሆኑት አቶ ዳዊት ገብረሚካኤል "ክስ ከተመሰረተባቸው መካከል የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የክልሉ ትምህርት እና ፋይናንስ ቢሮዎች ይገኙበታል፣ ክሱም የፌደራል መንግስት ለመምህራን የላከውን የአምስት ወር ደሞዝ ለሌላ አገልግሎት በማዛወራቸው የተሰጣቸውን ስልጣን ያለአግባብ ተጠቅመዋል” የሚል ነው ሲሉ ገልጸዋል። በተጨማሪ የፌዴራል መንግስት ደግሞ “የ12 ወራት ደሞዝ ባለመልቀቁ ነው ክሱ የተመሰረተው" ሲሉ አቶ ዳዊት አስረድተዋል፡፡

- የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ቢሮ በስድስት ወር ውስጥ ብቻ በጋዛ ጦርነት ከተገደሉት መካከል 70 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች እና ሕጻናት መሆናቸው ማረጋገጡን ጠቅሶ አውግዟል። ኤጀንሲው የሟቾች ቁጥሩ እንዲህ በከፍተኛ ሁሌታ ሊያሻቅብ የቻለው እስራኤል ሕዝብ በሚበዛባቸው አካባቢዎች ሰፊ ጉዳት የሚያደርስ የጦር መሳሪያ በመጠቀሟ እንዲሁም የተወሰኑ ሞቶች ደግሞ የፍልስጤም ታጣቂ ቡድኖች የሚያስወነጭፏቸው መሳርያዎች ላይ ባጋጠመ ችግር በደረሱ ፍንዳታዎች ሊሆን እንደሚችል አስታውቋል።

- የአሜሪካ መንግሥት ዶናልድ ትራምፕ ቀጣዩ ፕሬዝዳንት ሆነው ከመመረጣቸው በፊት ኢራን ለመግደል አሲራለች ካለው ጋር በተያያዘ ተሳታፊ ተብሎ የተጠረጠረ አፍጋኒስታናዊ ላይ ክስ መስረተ። የፍትህ ሚኒስቴር አርብ ዕለት ትራምፕን ለመግደል “እቅድ የማቅረብ” ኃላፊነት ተሰጥቶት ተሳትፏል ሲል በወነጀለው የ51 ዓመቱ ፋርሃድ ሻኬሪ ላይ የመሰረተውን ክስ ይፋ አድርጓል። የአሜሪካ መንግሥት ሻኬሪ በቁጥጥር ስር አለመዋሉን ገልጾ፣ ኢራን ውስጥ ይኖራል ተብሎ እንደሚታመን ገልጿል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

09 Nov, 11:31


ባለቤቶች ያልገቡባቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዉላቸዉን ለማቋረጥ የወጣው ማስጠንቀቂያ ለአንድ ወር መራዘሙ ተገለፀ

በእጣ የተላለፉ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ ነዋሪ ባለመግባቱ ምክንያት የተለያዩ ህገ ወጥ ተግባራት እየተፈፀመባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን አስታዉቆ እንደነበር ይታወቃል ።

በዚህም በእጣ እና በጨረታ ተላልፈው ነዋሪ ያልገባባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች እስከ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ድረስ የቤት ባለቤቶቹ የማይገቡበት ከሆነ ውል የሚቋረጥ መሆኑን የገለፀ ቢሆንም ዛሬ በሰጠዉ ማስጠንቀቂያ ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ህዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም. ማራዘሙን ነዉ ያስታወቀው።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

08 Nov, 15:28


የጥቅምት 29 / 2017 ዓ.ም ዋና ዋና መረጃዎች

- የገንዘብ ሚኒስቴር ዛሬ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና ለጉምሩክ ኮሚሽን በፃፈው ደብዳቤ ፍራንኮ ቫሉታ ከዛሬ ጀምሮ መከልከሉን ጠቅሷል፡፡ በደብዳቤውም ከዚህ ቀደም በፍራንኮ ቫሉታ ሸቀጦችን ከውጪ ያዘዙ ካሉ ከዛሬ ጀምሮ በ2 ሳምንት ጊዜ ውስጥ ግዢ የተፈፀመባቸው ህጋዊ ሰነዶችን ለጉምሩክ ኮሚሽን በማቅረብ ተቀባይነት አቅርበው የንግድ ሸቀጦቹ ወደ ሀገር እንዲገቡ ይደረጋል፡፡

- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር መገር ወረዳ ከነገ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታውቋል። በዞኑ እኖር ኤነር መገር ወረዳ ስር ያሉ ቆሴ ከተማ፣ ባረዋ እና ደያስ ቀበሌያት ከሌሊቱ 12 እስከ ምሽት 12 ሰዓት ብቻ እንቅስቀሴ የሚደረግ መሆኑን የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ ተናግረዋል።

- በ2017 ዓ.ም. ብቻ ባጋጠሙ 127 አደጋዎች 93 ነጥብ 6 ሚልዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን እና የ22 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ ከደረሱት አደጋዎች 117ቱ በአዲስ አበባ ቀሪዎቹ 10 አደጋዎች ደግሞ በሸገር ከተማ ያገጠሙ ስለመሆናቸው ተነግሯል፡፡ ካጋጠሙት አደጋዎች መካከል 63ቱ የእሳት ቃጠሎ፣ 28ቱ የጎርፍ፣ 18ቱ የንግድ ቤቶች ቃጠሎዎች ሲሆኑ 64ቱ ደግሞ ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች ናቸው ተብሏል።

- ትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳቸው ኃላፊ የነበሩትን ሱዛን ሳመርል ዋይልስ ጥር ወር ለሚረከቡት ዋይት ሐውስ የጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው እንዲያገለግሉ መርጠዋቸዋል። የ67 ዓመቷ ሱዛን ዋይልስ የመጀመሪያዋ የዋይት ሐውስ የጽህፈት ቤት ኃላፊ በመሆን ታሪክ ሠርተዋል። ከጥር 12 በኋላ በይፋ ፕሬዚዳንት ሆነው አገሪቷን የሚመሩት ትራምፕ የውጭ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ እና የመከላከያ ሚኒስትርን ጨምሮ 15 ከፍተኛ የሪፐብሊካን ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚዎቻቸውን ለመምረጥ የሽግግር ቡድናቸው ሥራውን ጀምሯል።

- የእስራኤል ፓርላማ መንግስት በሽብር ክስ የተፈረደባቸው ሰዎች ቤተሰቦችን ከሀገሪቱ እንዲያስወጣ የሚፈቅድ ህግ አጸደቀ። ህጉ የሽብር ተግባር በመፈጸም አልያም በማበራታታት ጥፋተኛ ሆኖ የተገኘው አካል ወላጆች፣ እህትና ወንድሞች እንዲሁም ልጆች ከሀገር ይባረራሉ ይላል።እስራኤላውያንም ጭምር የዚህ ህግ ሰለባ መሆናቸው ቢገለጽም በዋናነት ፍልስጤማውያን እና አረብ እስራኤላውያን ላይ ያነጣጠረ ነው በሚል ተቃውሞ እየቀረበበት ነው።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

07 Nov, 15:00


የጥቅምት 28 / 2017 ዓ.ም አጫጭር መረጃዎች:-

- የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ለሁሉም የክፍያ አገልግሎት ሰጪዎች የዲጂታል ክፍያ በQR ኮድ ከህዳር 22 ቀን 2017 ጀምሮ ተግባራዊ እንደያደርጉ ትዕዛዝ ሰጥቷል። ይህ ኢት ኪውአር ኮድ (EthQR Code) የተሰኘው አሠራር ዓለምአቀፍ የአሠራር ልምዶችን መሠረት ያደረገ፣ የክፍያም ሆነ የግብይት ተዋናያንን ሙሉ መረጃ የሚይዝ ነገር ግን ከተወሰኑ አስፈላጊ መረጃዎች በቀር ሌሎቹን በምሥጢር የሚጠብቅ ሥርዓት መሆኑ ተገልጿል።

- የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ለአንድ ወር በዘለቀ ግዜ በአማራ ክልል በሺዎች የሚቆጠሩ የክልሉን ነዋሪዎች በዘፈቀደ ለእስር ዳርገዋል፣ ይህ ተግባርም ሊቆም ይገባዋል ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል አሳስቧል።በክልሉ ከሀገሪቱ የመከላከያ ሰራዊት እና ከክልሉ የጸጥታ ሀይሎች የተዋቀረ ግብረሀይል “ህግ የማስከበር፣ ክልሉን የማረጋጋት እና ሰላም የማስፈን” በሚል በሺዎች የሚቆጠሩ የክልሉን ነዋሪዎች ለእስር ዳርገዋል ሲል ኮንኗል።

- ከተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ከ297 ሚሊዮን ብር በላይ እና 151 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ሃብት ታግዶ የወንጀል ምርመራ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የኦዲት ግኝት የባለድርሻ አካላት የትብብር ፎረም አመለከቷል። እንዲሁም 46 መኖሪያ ቤቶች እና አንድ ሕንጻ፣ 86 ተሽከርካሪዎች፣ ሁለት ነጥብ አምስት ሚሊዮን የሚያወጣ የአክሲዮን ብር ዋጋ ያለው፣ 81 ሺህ ገደማ ካሬ የመሬት ይዞታዎች እግድ እንደወጣባቸው ተመልክቷል።

- የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በመንግስት ኃይሎች የሚፈፀም ግድያ፣ እገታ እና ያለ ፍርድቤት ትዕዛዝ እስር መቀጠሉን አስታውቋል። የፌዴራል መንግስት እና የሚመለከታቸው የክልል መንግስታት የግዛት ወሰናቸው ባሉባቸው አካባቢዎች የሚፈጸሙ ግድያ፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመት፣ የእገታ እና ህገወጥ እስር እንዲያስቆሙ እና ድርጊት ፈጻሚዎችን በሕግ ተጠያቂ እንዲያደርጉ ኢሰመጉ አሳስቧል።

- የሩሲያ ጦር ከዩክሬን በዶኔትስክ ክልል የሚገኙት አንቶኒቭካ እና ማክሲምቪካ የተሰኙ መንደሮችን ተቆጣጥረናል ማለቱን አናዶሉ ዘግቧል።እንደዘገባው ከሆነ የሩሲያ ደቡባዊ እና ምስራቃዊ ጦር አባላት ሁለቱን መንደሮች ተቆጣጥሯል።ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ የሩሲያ ጦር 648 አውሮፕላን፣ 283 ሂልኮፕተር፣ ከ35 ሺህ በላይ ድሮን፣ 585 የአየር መቃወሚያ እና ሌሎች የውጊያ መሳሪያዎችን አውድሟል ብሏል።ይሁንና ዩክሬን እስካሁን በሩሲያ ጦር ተይዘዋል ስለተባሉት መንደሮች እና ሌሎች ጉዳቶች ዙሪያ እስካሁን ምላሽ አልሰጠችም።

- እስራኤል በምስራቃዊ ሊባኖስ በፈጸመችው የአየር ጥቃት በጥቂቱ የ40 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።በባካ እና ባልቤክ ግዛቶች በተፈጸሙት ጥቃቶች ከ53 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውንም ነው የገለጸው።የእስራኤል ጦር በበኩሉ ጄቶቹ ጥቃቱን ያደረሱት በባልቤክ አካባቢ በሚንቀሳቀሱ የሄዝቦላህ ታጣቂዎች ላይ መሆኑንና በጥብቅ የደህንነት መረጃዎች ተመርኩዘው ጥቃቱን ማድረሳቸውን ገልጿል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

07 Nov, 12:16


ብሔራዊ ባንክ የዲጂታል ክፍያ በኪውአር (QR) ኮድ እንዲሆን ትዕዛዝ ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ለሁሉም የክፍያ አገልግሎት ሰጪዎች የዲጂታል ክፍያ በQR ኮድ ከህዳር 22 ቀን 2017 ጀምሮ ተግባራዊ እንደያደርጉ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

አዲሱ መመሪያ ከጥሬ ገንዘብ ንክኪ ነጻ የሆነውን የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት በኢትዮጵያ ለማጎልበት እየተሰራ ያለውን ስራ ለማጠናከር እንደሚያግዝ እና የዲጂታል ግብይትን እየለመደ ያለውን ማህበረሰብ በይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል፡፡

እንዲሁም ይህ ኢት ኪውአር ኮድ (EthQR Code) የሚል ሥያሜ የሚኖረው አሠራር ዓለምአቀፍ የአሠራር ልምዶችን መሠረት ያደረገ፣ የክፍያም ሆነ የግብይት ተዋናያንን ሙሉ መረጃ የሚይዝ ነገር ግን ከተወሰኑ አስፈላጊ መረጃዎች በቀር ሌሎቹን በምሥጢር የሚጠብቅ ሥርዓት መሆኑ ተገልጿል።

ባንኩ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የዲጂታል ክፍያ አገልግሎትና ግብይት የጥሬ ገንዘብን ዝውውር የሚቀንስ ከመሆኑም በላይ፣ ሕብረተሰቡ ለሥርቆት፣ በእጁ ያለው ገንዘቡም ለእርጅና እንዳይጋለጥ፤ ከባንክ ውጭ የሚዘዋወር የገንዘብ መጠን እንዲቀንስ፣ ብሎም በአገር አቀፍ ደረጃ ገንዘቡን ለማሳተም የሚወጣ ወጪን እንዳይጨምር ለማድረግ ይረዳል ብሏል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

07 Nov, 10:42


በአማራ ክልል ሰዎች በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ኢሰመጎ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች እየተፈፀሙ ነው ስላላቸው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በጥቅምት 27 2017 ዓ.ም ጋዜጣዊ መግለጫ አውጥቷል።

ኢሰመጉ በመግለጫው ጥቅምት 17/2017 ዓ/ም በአማራ ክልል ከግጭቱ ጋር ተያይዞ በአዊ ብሔረሰብ ዞን አረጋውያንን ጨምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች በተለምዶ ፋኖ በመባል
የሚታወቀው ቡድን ደጋፊ ናችሁ በሚል ከህግ አግባብ ውጭ ግድያ እንደተፈፀመባቸው ገልጿል።

በክልሉ በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች ተፈፀመ በተባለ ጥቃት አንዲት ሴት መገደሏን እና በተለምዶ ፋኖ ተብሎ በሚጠራው ሀይል ሁለት ሰዎች መገደላቸው ተጠቁሟል።

እንዲሁም በክልሉ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚደረግ እስር መቀጠሉን እና የሚያዙ ሰዎች ፍርድ ቤት እየቀረቡ አለመሆኑን ኢሰመጉ አስታውቋል።

በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ሸዋ ዞን አዋሳኝ ድንበሮች ጥቅምት 20/2017 ዓ.ም በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ አካላት ተፈፀመ በተባለ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በህፃናት፣ ሴቶች፣ እና አረጋውያን ላይ ሞት ፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት መድረሱን ኢሰመጉ ገልጿል።

በተጨማሪም በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ገዳ አረቦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሀጂ አህመድ መስጅድ ኢማም የነበሩት ሼህ አህመድ መኪ ከ12 ቤተሰቦቻቸው ጋር በታጠቁ አካላት ታግተው ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም በአጋቾች ግድያ እንደተፈፀመባቸው ተጠቁሟል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማ ከሰኔ 2016 አ.ም ጀምሮ በተለያዩ አካባቢ የሚኖሩ በርካታ ሰዎች ብሔርን መሰረት በማድረግ ያለ ፍርድቤት ትዕዛዝ መያዛቸውን እና መግለጫው እስከወጣበት ዕለት ፍርድ ቤት አለመቅረባቸው ተገልጿል።

እንዲሁም በቤኒሻንጉልጉሙዝ መተከል ዞን ከጥቅምት 12 2017 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተይዘው እንደሚገኙ እና ኢሰመጉ መገለጫውን እስካወጣበት ሰዓት ድረስ ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውን ገልጿል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

07 Nov, 09:44


እነ ጆን ዳንኤል የወንጀል ድርጊቱን አልፈጸምንም በማለት የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጡ

ዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል)፣ አማኑኤል መውጫ፣ ናትናኤል ወንድወሰን፣ ኤልያስ ድሪባ፣ ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ የተባሉ ስድስት ተከሳሾች የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነትን አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል በሚል የቀረበባቸው ክስ ላይ የወንጀል ድርጊት እንዳልፈጸሙ ጠቅሰው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ልዩ ልዩ ከባድ ወንጀል ችሎት ዛሬ ቀርበው የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ ከአንድ ወር በፊት አውሮፕላንን ያለአግባብ መያዝ ወንጀል፣ የመንግስት ሰራተኛ የስራ ግዴታውን እንዳይፈጽም መቃወምና አለመታዘዝ ወንጀል ክስ እንዲሁም በ1ኛ ተከሳሽ ብቻ ደግሞ የአየር መንገዱን መልካም ስም ለሚያጎድፍ በተንቀሳቃሽ ምስል በኮምፒውተር ስርዓት አማካኝነት ማሰራጨት ወንጀል የሚል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

ተከሳሾቹ የክስ ዝርዝር ከደረሳቸው በኋላ ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ በተሰጠ ትዕዛዝ መሰረት ከማረሚያ ቤት ቀርበው ጉዳያቸውን ተከታትለዋል።

የተከሳሾች ጠበቆች የክስ ዝርዝሩ እንዲሻሻል የመጀመሪያ ደረጃ የክስ መቃወሚያ ሲያቀርቡ፤ ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ደግሞ የክስ ዝርዝሩ ሊሻሻል አይገባም የሚል መልስ በጽሁፍ ሰጥቷል፡፡

ፍርድ ቤቱ የቀረበውን የክስ መቃወሚያ እና የዐቃቤ ሕግ መልስን መርምሮ በዛሬ ቀጠሮ ተከሳሾቹ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ፍሬ ነገር ወደ ፊት በማስረጃ የሚጣራ መሆኑን ጠቅሶ ውድቅ አድርጎታል።

ከዚህም በኋላ ተከሳሾቹ በክሱ ዝርዝር የተገለጸውን የወንጀል ድርጊት ሰለመፈጸም አለመፈጸማቸው በፍርድ ቤቱ በቀረበላቸው ጥያቄ መሰረት "የወንጀል ድርጊቱን አልፈጸምንም " በማለት የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ለወንጀሉ መፈጸም ያስረዱልኛል ያላቸው ምስክሮች ቃል እንዲሰማለት በጠየቀው ተለዋጭ ቀጠሮ መሰረት የምስክር ቃል ለመስማት ለሁለት ቀን ማለትም ለሕዳር 18 እና ለሕዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ምንጭ- FBC

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

06 Nov, 13:07


ሶማሊላንድ ለሰላማዊ ምርጫ ዝግጁ መሆኗን አስታወቀች

የጸጥታ ስጋቶችን ለመከላከል አለም አቀፍ ድጋፍ ጠይቃለች።

የሶማሌላንድ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር በመጪው ህዳር 13 ለሚካሄደው የፕሬዚዳንታዊ እና የፓርቲ ምርጫ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጧል።

የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዶ/ር ኢሳ ካይድ በሀርጌሳ ለአለም አቀፍ ተወካዮች በብሄራዊ ምርጫ ኮሚሽን የወሰዳቸው እርምጃዎች "የመራጮች ምዝገባን ማረጋገጥ፣ የእጩዎችን ጥቆማ ማጠናቀቅ፣ የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት እና የአለም አቀፍ ታዛቢዎችን እውቅና መስጠት" የሚሉትን ርምጃዎች አብራርተዋል።

ሚኒስቴሩ በቅርቡ በቆሪሉጉድ ከሞጋዲሹ ጋር ግንኙነት አላቸው በተባለው የጸጥታ ስጋቶች የሶማሊላንድ መረጋጋት ላይ ስጋት አድሮባቸዋል ብሏል።

ሚኒስቴሩ የአገሪቱን ሉዓላዊነት የመጠበቅ መብት እንዳላት አፅንዖት የሰጠው ሚኒስቴሩ፣ የቀጣናውን ሰላም የሚያደፈርሱ ድርጊቶች አለም አቀፍ ድጋፍና ውግዘት እንዲደረግ ጠይቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

06 Nov, 11:15


የሪፐብሊካን ፓርቲ ዕጩው ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ አሸነፉ

የሪፕብሊካኑ ተወካይ ዶናልድ ትራምፕ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን በማሸነፋቸው 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት በመሆን ወደ ዋይት ሃውስ የሚመለሱ ይሆናል።

በፍሎሪዳ የሪፐብሊካን ደጋፊዎች በተሰበሰቡበት ትራምፕ “አስደናቂ ድል” ሲሉ ተደምጠዋል።

ትራምፕ ምርጫውን ለማሸነፍ ከሚያስፈለገው 270 ድምጽ ከ279 በላይ ያገኙ ሲሆን ካማላ ሃሪስ በበኩላቸው 223 በላይ ድምጽ ማግኘታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

ካማላ ሃሪስ ከምርጫ ውጤት ይፋ መሆን በኋላ ተዘጋጅቶ የነበረው ድግስም መሰረዙን ዘገባው አመላክቷል።

ውጤቱን ተከትሎ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለዶናልድ ትራምፕ የእንኳን ደስ አለህ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “በእርስዎ የስልጣን ዘመን የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር በጋራ እንሰራለን” ብለዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

06 Nov, 08:39


በርካታ መሪዎች ዶናልድ ትራምፕን እንኳን ደስ አለዎት እያሉ ነው

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት እየተገባደደ ሲሆን ዶናልድ ትራምፕ ካማላ ሀሪስን 267 ለ224 ድምጽ እየመሩ ነው።

ይህን ተከትሎ የፈረንሳይ፣ እስራኤል ፣ ሀንጋሪ እና ኢትዮጵያ መሪዎች እንኳን ደስ አለዎት ሲሉ ለዶናልድ ትራምፕ የደስታ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በቀጣዮቹ ሰዓታት ውስጥ የአሜሪካ ምርጫ ኮሚሽን የዶናልድ ትራምፕን አሸናፊነት እንደሚያውጅ ይጠበቃል።

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

05 Nov, 07:22


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን ተረከበ

ጥቅምት 26 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን በፈረንሳይ ቱሉዝ በተካሄደ ስነስርዓት ከኤርባስ ኩባንያ መረከቡን አስታውቋል፡፡

በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጀነራል ይልማ መርዳሳ ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና የኤርባስ ኩባንያ የስራ ሀላፊዎች መገኘታቸው ተመላክቷል፡፡

ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተረከበው ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን ዛሬ አዲስ አበባ እንደሚገባም ተመላክቷል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

05 Nov, 06:53


አሜሪካ በአማራ ክልል በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት አሳስቦኛል አለች

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ጋር በስልክ ማውራታቸው ተሰምቷል።

“በኢትዮጵያ በመካሄድ ላይ ያሉ የእርስ በርስ ግጭቶች እልባት እንዲያገኙ የፖለቲካ ውይይት ወሳኝነት አለው” ሲሉ አንቶኒ ብሊንከን ከጠ/ሚኒስትር አብይ ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት ወቅት መናገራቸው የመስሪያ ቤታቸው መግለጫ አመላክቷል።

አሜሪካ “በአማራ ክልል በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት ያሳስባታል” ሲሉ መናገራቸውን መግለጫው አካቷል።

አንቶኒ ብሊንከን ከጠ/ሚኒስትር አብይ ጋር በስልክ ያወሩት በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት ዙሪያ እንደነበር ጸ/ቤታቸው ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

አንቶኒ ብሊንከን “ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነቱ ተግባራዊ እንዲደረግ ለምታደርገው ጥረት ሀገራቸው እገዛ ለማድረግ ዝግጁ ናት” ሲሉ መናገራቸውን መግለጫው ጠቁሟል።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ጠ/ሚኒሰትር አብይ በአፍሪካ ቀንድ እየተካረረ በመጣው ውጥረት ዙሪያም መምከራቸውንም የመስሪያ ቤታቸው ቃል አቀባይ ቢሮ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

05 Nov, 05:44


አዲስ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

ዳሸን ባንክ በተለያዩ የስራ መስኮች አዲስ ሰራተኞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ አውጥቷል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለማመልከት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://ethionegari.com/2024/11/05/vacancy-announcement-banking-jobs-at-dashen-bank/

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

https://ethionegari.com/2024/11/05/vacancy-announcement-banking-jobs-at-dashen-bank/

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

05 Nov, 05:21


የመንግስት ሰረተኞች የደመወዝ ጭማሪ ተራዘመ

በዚህ ወር ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ_ጭማሪ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል

መንግሥት ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ያለው የመንግሥት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪ፣ በዚህ ወር ተግባራዊ አለመሆኑን ተሰምቷል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ መንግሥት ሠራተኞች በተወሰኑ ወረዳዎች ከሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን እና ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል።

ቢሮው፣ ለከተማ አስተዳደሩ የመንግሥት ሰራተኞች ጭማሪው የሚከፈልበት ጊዜ የተራዘመው የሰራተኞችን መረጃ ለማደራጀት ጊዜ ስለሚያስፈልግ ነው የሚል ምላሽ ሰጥቷል ።

ሆኖም ሰራተኞቹ ቢሮው እስካሁን ምን ያህል የመንግስት ሰራተኛ እንዳለ እና ሌሎች ከደሞዝ ጋር የተያያዙ መረጃዎችን አያውቅም ወይ? የሚል ጥያቄ ማንሳታቸው ተሰምቷል ።

ሰራተኞቹ እስካሁን የተጨመረላቸውን ደሞዝ የሚገልጽ ይፋዊ ደብዳቤ አልደረሳቸውም።
በተጨማሪም ከተማ አስተዳደሩ አዲስ የመዋቅር ማሻሻያ አደረጃጀት ጥናት አድርገው የብቃት መመዘኛ ፈተና ለሰጡት ተቋማት ሰራተኞች የደሞዝ ጭማሪው ይዘገያል ተብሏል።

ጭማሪው የሚዘገየው ተቋማቱ የሰራተኞችን የሥራ ደረጃ ምደባ ገና ስላልጨረሱ ነው ተብሏል። 

ከተማ አስተዳደሩ በመጀመሪያው ዙር የብቃት ምዘና ፈተና የተሰጠው ለቤቶች ልማት አስተዳደር ጽህፈት ቤት፣ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽህፈት ቤት፣ የሥራ ኢንተርፕራይዝ ኢንዱስትሪ ልማት ፅሕፈት ቤት፣ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ፅሕፈት ቤት፣ ኅብረት ሥራ ፅሕፈት ቤት እና የመሬት ልማት አስተዳደር ፅሕፈት ቤት መሆኑ ይታወሳል።
በክልሎች እንዲሁም የፌደራል የፋይናንስ ተቋማት እስካሁን ስለደሞዝ ጭማሪው የደረሰን መመሪያ የለም በማለት የዚህን ወር ደሞዝ በነባሩ ደመወዝ እየከፈሉ ይገኛሉ።

የፋይናንስ ቢሮዎቹ ደሞዝ ጭማሪው ተግባራዊ የሚደረግ ከሆነ ከጥቅምት ወር ጀምሮ ያለው ወደፊት ሊከፈል ይችላል የሚል ምላሽ እንደሰጧቸውም የጠየቅናቸው የመንግሥት ሠራተኞች ነግረውናል።

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሚኖሩ አንድ የመንግሥት ሰራተኛ ነባሩ የጥቅምት ወር ደሞዝ እንደተከፈላቸው ገልጸው፣ ጭማሪው የሰራተኞች መረጃ ወደ ዞን ተልኮ ክልል ከደረሰ በኋላ ኅዳር ላይ ሊመጣ ይችላል የሚል ግምት እንዳላቸው ነግረውናል።

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ በጀቱን ለክልሎች ልከናል በማለት ክፍያ ያልተፈጸመው ክልሎች የሚያጣሩት ነገር ኖሯቸው ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል። 

ከጥቅምት ጀምሮ ያለውን የደሞዝ ጭማሪም ወደፊት ሊከፍሉ እንደሚችሉም ተናግረዋል።

የገንዘብ ሚንስትር አህመድ ሽዴ ጥቅምት 09/2017 ዓ. ም ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ አዲሱ የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ገልጸው ነበር።

ሚንስትሩ፣ የደመወዝ ጭማሪውን ተግባራዊ ለማድረግ የገንዘብ ሚንስቴር እና ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኹሉንም ቅድመ ዝግጅቶች አድርገዋል ብለውም ነበር።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በተመሳሳይ ባለፈው ሳምንት ለሕዝብ እንደራሴዎች በሰጡት ማብራሪያ ለደሞዝ ጭማሪው 91 ቢሊዮን ብር ስለተመደበ ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ማለታቸው ይታወሳል።

ምንጭ ዋዜማ ሬዲዮ

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

04 Nov, 12:48


የREMEDIALፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆነ

በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የREMEDIAL ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ተደርጓል።

ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ተማሪዎች ምደባቸውን ፦

በWebsite: https://placement.ethernet.edu.et 

በTelegram: https://t.me/moestudentbot ላይ መመልከት እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ተማሪዎች ተቋማት በሚያስተላልፉት ጥሪ  መሰረት የREMEDIAL ፕሮግራሙን እንዲከታተሉ ብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑንም አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

04 Nov, 08:32


ሶማሊያ የኢትዮጵያን ኤምባሲ ከፕሬዝዳንቱ ቅጥር ግቢ ልታስወጣ መሆኑን ገለጸች

በሶማሊያ ፕሬዝዳንት ቅጥር ግቢ (ቤተመንግስት) ውስጥ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በቅርቡ ወደ ሌላ ቦታ ለማዘዋወር መታቀዱን የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አህመድ ሞአሊን ፊቂ አስታወቁ።

ኤምባሲው ከዚህ ቀደም ወደ ነበረበት ቦታው እንዲመለስ ይደረጋል ሲሉ ሚኒስትሩ ጥቅምት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ለሀገሪቱ ጋዜጠኞች በሰጡተ መግለጫ መጠቆማቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ሚኒስትሩ በጋዜጣዊ መግለጫቸው “በፕሬዝዳንታቸው ቅጥር ግቢ ውስጥ የውጭ ሀገር ኤምባሲ መገኘቱ አግባብነት የለውም” የሚል ስሜት በበርካታ ሶማሊያውያን ዘንድ መኖሩን ጠቅሰው “ሶማሊያውን እያሰሙት ያለውን ቅሬታ መቀበል ተገቢ ነው” ሲሉ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወደ ቀድሞ ቦታው እንዲመለስ የሚደረግበትን ምክንያት አስቀምጠዋል።

“ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ይገኝበት የነበረው አከባቢ በአሁኑ ሰአት ምንም አይነት ጥቅም እየሰጠ አይደለም፣ እሱን አድሰን ኤምባሲው ወደዚያው እንዲዛወር እናደርጋለን” ሲሉም አስታውቀዋል።

በተጨማሪም ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ካልሆነ ግን በተመሳሳይ “በአዲሰ አበባ የሚገኘውን የሶማሊያ ኤምባሲ በኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ግቢ ውስጥ እንዲሆን የሚል ጥያቄ እናቀርባለን” ሲሉም ገልጸዋል።

የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መግለጫ በሀገራቱ መካከል እየተካረረ የመጣውን ልዩነት የሚያንጸባርቅ ነው ሲሉ መገናኛ ብዙሃኑ በዘገባዎቻቸው አትተዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

04 Nov, 06:50


አዲስ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

Save The Children በተለያዩ የስራ መስኮች አዲስ ሰራተኞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ አውጥቷል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለማመልከት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://ethionegari.com/2024/11/04/new-ngo-job-opportunities-in-ethiopia-2/

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

02 Nov, 13:56


ኢትዮጵያ ሞቶ የተገኘ አስከሬንን ለምርምር መጠቀም እንዲቻል የሚፈቅድ ህግ አዘጋጀች

ከሁለት ሳምንት በፊት የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡ ይታወሳል፡፡

ይህ ረቂቅ ከያዛቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የአስከሬን አያያዝ እና ዝውውር ጉዳይ አንዱ ሲሆን በርካታ ጉዳዮችን ደንግጓል፡፡

ከነዚህ መካከልም በህግ ሥልጣን ከተሰጠው አካል ካልፈቀደ በስተቀር የሰው አካል ክፍልን፣ አስክሬንን ወይም አጽምን ወደ ሐገር ውስጥ ማስገባት ወይም ከሐገር ማስወጣትን ይከለክላል፡፡

እንዲሁም አስከሬንን ለማስተማሪያነት ወይም ለምርምር ማዘጋጀት የሚችለው አግባብነት ባለው አካል የተመረጠ የጤና ተቋም ነው እንደሆነም በረቂቅ አዋጁ ላይ ተጠቅሷል፡፡

ተጨማሪ ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://bit.ly/4faWCwB

#ethiopia #health

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

02 Nov, 09:29


አቶ ጌታቸው ረዳ ኃላፊነታቸውን አስረከቡ

አቶ ጌታቸው ረዳ ኃላፊነታቸውን በጊዜያዊነት አስረክበዋል ተብሏል።

አቶ ጌታቸው ስልጣናቸው ያስረከቡት ለምክትላቸው ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ በውክልና መሆኑ ታውቋል።

አቶ ጌታቸው ለህክምና ወደ ውጭ ሊሄዱ በመሆኑ ነው ስልጣናቸውን በውክልና ያስተላለፉት ተብሏል።

ይሁንና አቶ ጌታቸው ለህክምና ወደየትኛው ሀገር እንደሚያቀኑ አልተጠቀሰም።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

01 Nov, 12:01


የሪሚዲያል ፕሮግራም አልተቋረጠም - ትምህርት ሚኒስቴር

የተማሪዎች አቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ተቋርጧል በሚል በማህበራዊ ሚዲያ ሐሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈትነው የማለፊያ ነጥብ ያላመጡ ተማሪዎች አቅማቸውን በማሻሻል ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዲገቡና ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ እየተደረገ እንደሚገኝም አስታውሷል።

ይሁንና ሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ትምህርት ሚኒስቴር የሪሚዲያል ፕሮግራም በበጀት ዕጥረት መቋረጡን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ መሰረተ ቢስ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ ገልጿል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

01 Nov, 10:54


በመሬት መንሸራተት አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ጫሬ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሥድስት ሰዎች ህይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ትናንት ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ዛሬ ጠዋት 2:00 ላይ የመሬት መንሸራተት መከሰቱን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

በአደጋው ህይወታቸውን ያጡት ሰዎች የሁለት ቤተሰብ አባላት ሲሆን ከአንደኛው ቤተሰብ አራት እንዲሁም ከሌላኛው ቤተሰብ ሁለት ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ተገልጿል ሲል ኤፍ ቢ ሲ ዘገቧል፡፡

በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋም ሁለት ቤት መውደሙ የተገለጸ ሲሆን የነፍስ አድን ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉንና እስከ አሁንም 1 አስከሬን ተገኝቷል ተብሏል፡፡

በአካባቢው አሁንም መሬቱ እየተናደ መሆኑ እና የውኃ ሙላት (ጎርፍ) መኖሩ የነፍስ አድን ሥራውን በሚፈለገው ልክ እንዳይሆን እንዳደረገው ተመላክቷል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

01 Nov, 10:39


አዲስ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

በተለያዩ የስራ መስኮች የወጡ የNGO ስራዎችን በዝርዝር ለመመልከት እና ለማመልከት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://ethionegari.com/2024/11/01/latest-ngo-job-opportunities-in-ethiopia-5/

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

https://ethionegari.com/2024/11/01/latest-ngo-job-opportunities-in-ethiopia-5/

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

01 Nov, 09:21


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በባንኮች እርስ በርሳቸው የሚበዳደሩበት የገንዘብ ገበያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባንኮች እርስ በርሳቸው የሚበዳደሩበትን የገንዘብ የግብይት ሥርዓት መፍቀዱን አስታውቋል።

ብሔራዊ ባንኩ ዛሬ ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት መጀመር ንግድ ባንኮች የዕለት- ተዕለት የገንዘብ ፍሰታቸውን በአግባቡ እንዲያስተዳድሩ ያግዛቸዋል ብሏል።

ንግድ ባንኮች ብድር መበደር ወይም ማበደር የሚችሉት ላንድ ቀን ወይም ለሰባት ቀናት ለሚከፈል ገንዘብ ብቻ እንደኾነ ተጠቁሟል።

ይህም ባንኮች የአጭር ጊዜ የገንዘብ ጉድለትን በመሸፈን ወይም ትርፍ ገንዘብን ለሌሎች ባንኮች በማበደር የገንዘብ ፍሰትን በብቃት እንዲያስተዳደሩ ያስችላቸዋል ተብሏል።

በተጨማሪም በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ የግብይት መድረክ ላይ ብቻ እንዲከናወን የተፈቀደ ሲሆን ግብይቱ ላይ ለመሳተፍም ሁሉም የንግድ ባንኮች ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፍቃድ ማግኘት እና የሚጠበቅባቸውን መስፈርቶች ማሟላት እንደሚገባቸው ተመላክቷል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

31 Oct, 13:21


የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤርትራ የአየር ክልል እንዳይበር ተከልክሏል በሚል የተሰራጨው መረጃ ሃሰት ነው -የኢትዮጵያ አየር መንገድ

በዛሬው ዕለት በአንዳንድ የማህበራዊ ትስስር ገፆች የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤርትራ የአየር ክልል እንዳይበር ተከልክሏል የሚል መረጃ እያሰራጩ መሆኑን ተመልክተናል ብሏል አየር መንገዱ።

ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኤርትራን አየር ክልል እንዲጠቀም ከኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ፈቃድ የተሰጠው እና የኤርትራ አየር ክልልን ለመደበኛ በረራ እየተጠቀመ መሆኑን እረጋግጦ በማህበራዊ ትስስር ገፆች የተገለፀው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን አየር መንገዱ አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

31 Oct, 10:32


ኮሪደር የፈረሰውን ማፍረስ ነው - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ

"ኮሪደር የፈረሰውን ማፍረስ ነው ላስቲክ እና ጭቃ ፈረሰ ምትሉ ሰዎች መጀመሪያም አልነበረም" ሲሉ ጠ/ሚ ዐቢይ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ወቅት ተናግረዋል።

ጠ/ሚ ዐቢይ አክለውም ኢትዮጵያ ውስጥ ሶስት ሾተላዮች ያሉብን ይመስለኛል ብለዋል።

አንደኛው እያፈረሱ መስራት ነው ይህም ሲባል የኮሪደር ልማትን ማለት አይደለም ኮሪደር የፈረሰውን ማፍረስ ነው ላስቲክ እና ጭቃ ፈረሰ ምትሉ ሰዎች ከጅምሩም ያልነበረ ነው ሲሉ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል፡፡

ሁለተኛው በእድል እና በጊዜ መቀለድ ነው ያሉ ሲሆን በተገኘው እድ መጠቀም እንጂ እድልን ማባከን እና ካለፈ በኋላ ጸጸት ዋጋ እንደሌለው ገልጸዋል፡፡

በሶስተኛነት ደግሞ ካለፈ በኳላ መቆዘም እንደሀገር የሚታይ ሾተላይ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "አለም እያደነቀ ያለውን የኮሪደር ልማት መንቀፍ እኔ አላደረኩትም ከሚል እሳቤ የመጣ ነው" ብለዋል፡፡

እንደዚህ አይነት እሳቤ በብዙ እየጎዳን ስለሆነ አርቀን ወደ ፊት ብንሄድ ይሻላልም ብለዋል፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

31 Oct, 08:15


አንዳንድ ኤምባሲዎች የኢትዮጵያን ሀብት እየዘረፉ ማሸሽ ቋሚ ሥራቸው አድርገውታል - ዐቢይ አህመድ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የስራ ዘመኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 3ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ባለበት ወቅት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህጋዊና በጥቁር ገበያው መካከል ያለው የምንዛሬ ልዩነት እንዲጠብ የተሰራው ሥራ ወጣታማ ሆኖ ልዩነቱ ወደ አምስት በመቶ መውረዱን ተናግረዋል።

ይሁንና አሁንም የውጭ ምንዛሬ ገበያው ላይ የሚደረጉ አሻጥሮች እንዳልተቀረፉ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በተለይ ኤምባሲዎችን በዚህ ውስጥ ጠቅሰዋል።

አንዳንድ ኤምባሲዎች ዶላር መመንዘርና የኢትዮጵያን ሀብት እየዘረፉ ማሸሽ ቋሚ ሥራቸው አድርገውታል ሲሉም ወቅሰዋል።

እነዚህን ኤምባሲዎች እስካሁን በትዕግሥት እያለፍናቸው ነው፣ ነገር ግን ከዚህ ድርጊታቸው ካልተቆጠቡ ርምጃ ይወሰድባቸዋል ብለዋል።

ይሁንና ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ሀብት ይዘርፋሉ ያሏቸውን ኤምባሲዎች በስም አልጠቀሱም።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

30 Oct, 17:23


እስከ 6ኛ ክፍል ድረስ ያሉ ተማሪዎችን በውጤታቸው ደረጃ መስጠትን ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ

ኢትዮጵያ የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅን ለማሻሻል ያለመ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅታለች፡፡

ይህ ረቂ አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ በትናንትናው ዕለት ቀርቧል፡፡
ምክር ቤቱም ይህን ረቂቅ አዋጅ ተጨማሪ ውይይቶች እና ሌሎች ግብዓቶች እንዲታከሉበት በሚል ለዝርዝር እይታ ወደ ቋሚ ኮሚቴ መርቷል፡፡

ይህ ረቂቅ አዋጅ እንደሚለው ከሆነ ተማሪዎች ስለ ሚማሯቸው ቋንቋዎች፣ ስርዓት ትምህርት ዝግጅት፣ መምህራን ቅጥር፣ ተማሪዎች ምዘና፣ ትምህርት ጥራት ማስጠበቂያ መንገዶች እና ሌሎችንም ጉዳዮች ይዟል፡፡

ቋንቋዎችን አስመልክቶ በረቂቅ አዋጁ ላይ እንደተቀመጠው የአፍ መፍቻ ቋንቋ እንደ ትምህርት አይነትነት እና እንደ ማስተማሪያ ቋንቋነት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ የሚሰጥ ሆኖ እንደ ትምህርት አይነትነት እና እንደ ማስተማሪያ ቋንቋነት መሰጠቱ የሚያበቃበትን የክፍል ደረጃ ክልሎች ይወስናሉ ብሏል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ https://bit.ly/3YKejNY

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#ethiopia #Education

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

30 Oct, 17:07


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምርጡ የአፍሪካ አየር መንገድ በመባል ተሸለመ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመታዊው APEX Passenger Choice Awards 2025፣ ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ “Best Overall in Africa award” በሚል ተሸልሟል፡፡

አየር መንገዱ በዚህ የሽልማት አሰጣጥ መርሓ ግብር ላይ በምርጥ የበረራ ላይ መስተንግዶ፣ በምርጥ የበረራ ላይ መዝናኛ አገልግሎት፣ በምርጥ የበረራ ላይ የምግብ እና መጠጥ አገልግሎት፣ በምርጥ የአውሮፕላን ውስጥ መቀመጫ ምቾት እንዲሁም በምርጥ የበረራ ላይ ገመድ አልባ ኢንተርኔት አገልግሎት ዘርፎች ከአፍሪካ ምርጡ አየር መንገድ በመሆን ተሸልሟል።

ይህ በ “Airline Passenger Experience Association” (APEX) የመንገደኞችን ድምፅ መሰረት በማድረግ ለአየር መንገዶች ዕውቅና የሚሰጥበት መድረክ በአቪዬሽን ኢንደስትሪው ትልቅ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሽልማቶች አንዱ ሲሆን በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ አየር መንገዶች ለሚያቀርቡት የላቀ የደንበኞች አገልግሎት ዕውቅና የሚሰጥበት መሆኑን የአየር መንገዱ መረጃ ያመለክታል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

30 Oct, 13:03


በመገናኛ ብዙሃን ማሻሻያ ህግ ላይ የቀረበው ረቂቅ በፓርላማ አባላት ዘንድ ጥያቄ አስነሳ

አዲሱ ረቂቅ አዋጅ የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተርን የመመልመል ሥልጣን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲሆን የሚደነግግ እና ሌሎችንም በ2013 ዓ.ም የወጡ አዋጆችን የሚሽር ነው።

በ2013 ዓ.ም. ፀድቆ በሥራ ላይ ባለው አዋጅ የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዕጬ ዋና ዳይሬክተር በመገናኛ ብዙኃን ቦርድ ተመልምሎ፣ በመንግሥት አቅራቢነት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚሰየም ተደንግጓል፡፡

ይሁንና በሥራ ላይ ባለው አዋጅ የተካተተው የቦርድ አባላት ስብጥር፣ ከባለሥልጣኑ የቁጥጥር ሚና ጋር በተያያዘ የጥቅም ግጭቶች የሚፈጥር ሆኖ መገኘቱ እንደ ክፍተት መታየቱን ሪፖርተር ዘግቧል።

ይሁንና ማክሰኞ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. በተካሄደው የህዝብተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ከገለልተኝነት አንፃር በምክር ቤቱ አባላት ጥያቄ ተነስቶበታል።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አባል አወቀ አዘምየ (ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት፣ በሥራ ላይ ባለው አዋጅ የቦርድ አባላት ከሚመረጡባቸው መሥፈርቶች አንዱ የፖለቲካ ፓርቲ አባል ወይም ተቀጣሪ ያልሆኑ በሚል የተቀመጠ ቢሆንም፣ በቀረበው ረቂቅ ሕግ ግን ይህ መሥፈርት ለምን ተሻሻለ ሲሉ ጥያቄ ማቅረባቸውን ሪፖርተር ዘግቧል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

30 Oct, 11:16


የአቦል አዳዲስ ይዘቶች ማስተዋወቂያ እና የአፋፍ ቴሌኖቬላ ማጠናቀቂያ ልዩ ዝግጅት ተካሄደ

ሕንድ ለ20 የፊልም ሙያተኞች የስኮላርሽፕ እድል ሰጥታለች

“የአቦል አዳዲስ ይዘቶች ማስተዋወቂያና የአፋፍ ቴሌኖቬላ ማጠናቀቂያ” ልዩ በአዲስ አበባ በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት አዳራሽ (ወመዘክር) ተካሂዷል፡፡

በዚህ መድረክ ላይ ታዋቂ የፊልም ባለሙያዎች፣ ተወናዮች፣ የመንግስት ተቋማት ሃለፊዎች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልመህዲ በፕሮግራሙ ላይ ባደረጉት ንግግር "ዲኤስቲቪ በኢትዮጵያ የፊልም ጥበብ እንዲጎለብት በፋይናንስና በስርጭት እያደረገ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው። በርካቶች የፊልም ጥበብ ባለሙያዎች ይህንን በመጠቀም እየተንቀሳቀሱ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም ለዚህ ማሳያ የሆነው " አፋፍ ተከታታይ ድራማ በፕሮዳክሽን ጥራትም በይዘትም ምሳሌ በሚሆን መልኩ ተዘጋጅቶ ሲቀርብ ነበር" ብለዋል።

በስኬት በመጠናቀቁም የይዘት ባለቤቱን ዲኤስቲቪ አቦል ቴሌቪዥንና አዘጋጁን ሚካኤል ሚሊዮንን ( ሰውኛ ፕሮዳክሽን ) እና አባላቱን እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ https://bit.ly/3UsRmw2


ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

30 Oct, 08:32


በዎላይታ ዞን በከፍተኛ መጠን በጣለው ዝናብ በተከሰተው የመሬት ናዳ የሰባት ሰዎች ህይወት አለፈ

በዚሁ በትላንትናው ዕለት ማታ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በካዎ ኮይሻ ወረዳ 01 ቀበሌ የአንድ ቤተሰብ አባለት በሙሉ እና ሌሎች ላይ አደጋ ደርሷል።

በዎላይታ ዞን በካዎ ኮይሻ ወረዳ በኮይሻ ላሾ ቀበሌ ሞግሳ ቀጠና በተከሰተው መሬት ናዳ 4 ሰውና በ01 ቀበሌ 3 ሰው አጠቃላይ የ7 ሰው ሕይወት አልፏል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Oct, 12:57


አዲስ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

በተለያዩ የስራ መስኮች የወጡ የNGO ስራዎችን በዝርዝር ለመመልከት እና ለማመልከት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://ethionegari.com/2024/10/24/latest-ngo-jobs-in-ethiopia-10/

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

24 Oct, 12:31


የዩንቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ

በ2016 ዓ. ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈትነው 50 ከመቶ ውጤት እና ከዛ በላይ ያመጡ ተማሪዎች የዩንቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆኗል።

ትምህርት ሚንስቴር እንዳስታወቀው ተማሪዎች የተመደቡበትን ዩንቨርስቲ በሚንስቴሩ ድረገጽ ላይ ማየት ይችላሉ ብሏል።

የዩንቨርስቲ ለውጥ እንደማይቻልም ሚንስቴሩ አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#Universityplacement #ethiopia

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

23 Oct, 09:26


ኢትዮጵያ በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ከአፍሪካ 7ኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠች

ኢትዮጵያ ወደ 24.83 ሚሊዮን የሚጠጉ አካውንቶች ይዛ በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ከአፍሪካ 7ኛዋ ትልቅ ሀገር ሆናለች።

103 ሚሊዮን የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ያሏት ናይጄሪያ በቀዳሚነት ተቀምጣለች።

ከናይጄሪያ በመቀጠል ግብፅ ስትሆን 82.01 ሚሊዮን የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች አሏት።

ደቡብ አፍሪካ 45.34 ሚሊዮን ተጠቃሚዎችን በማግኘት በሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Oct, 14:29


የእሳት አደጋውን ተገ አድርገው የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 33 ተጠርጣሪዎች ተያዙ
          
ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ/ም ምሽት በመርካቶ ሸማ ተራ የተከሰተውን የእሳት አደጋ እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 33 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል።

ከአደጋው ጋር በተያያዘ በ7 ሰዎች ቀላል በሁለት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት  መድረሱንም ገልጿል፡፡     

የአደጋውን መንስኤ ለማጣራት የአዲስ አበባ ፖሊስ ከፌዴራል ፖሊስ የፎረንሲክ ምርመራ ቡድን ጋር በመቀናጀት ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Oct, 08:10


አዲስ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

በተለያዩ የስራ መስኮች የወጡ የNGO ስራዎችን በዝርዝር ለመመልከት እና ለማመልከት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://ethionegari.com/2024/10/22/latest-ngo-jobs-in-ethiopia-9/

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

22 Oct, 07:57


ምርጫ ቦርድ የአገልግሎት ክፍያ ተመን ላይ ጭማሪ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሙሉ ዕወቅና ለመስጠት ሲያስከፍል የነበረው 200 ብር ቢሆንም ከትናንት ጀምሮ ግን 30ሺህ ብር ማድረጉን አስታወቀ፡፡

በመቶኛ ሲሰላ - ከ150% በላይ ነው፡፡

ቦርዱ ባወጣው መግለጫ ለሀገር አቀፍና ለክልላዊ ፓርቲ ጊዜያዊ የምስክር ወረቀት ለማግኘት ያስከፍል የነበረው 100 ብር ሲሆን ከትናንት ጀምሮ ግን በአንድ መቶ ሀምሳ ዕጥፍ (150%) ጨምሮ 15ሺህ ብር አድርሶታል፡፡

የሙሉ ዕወቅና ክፍያ 200 ብር ሆኖ እስከትናንትናው ዕለት ድረስ ቢቆይም እዚህም ላይ የ150% ጭማሪ በማድረግ ቦርዱ 30ሺህ ብር አስግብቶታል፡፡ 30 ብር የነበረው የሰነድ ማሻሻያ ክፍያ ደግሞ በአንድ መቶ ስድሳ ስድስት ነጥብ ስድስት በመቶ (166.6%) አሻቅቦ 5ሺህ ብር ሆኗል፡፡

ቦርዱ ለዚህ ጭማሪው በየጊዜው መሻሻል እንደሚያስፈልግ በማመኔ ነው ይበል እንጂ ዝርዝር ጉዳዮቹን አልገለጸም፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

21 Oct, 20:51


የእሳት አደጋውን መቆጣጠር ተችሏል - አዳነች አቤቤ

መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በፌስቡክ ገፃቸው አስፍረዋል።

የእሳት አደጋዉን በቁጥጥር ስር በማዋል ርብርብ  ላደረጉ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።

በንብረት ላይ የደረሰው ጉዳትና መንስኤዉን በማጣራት ቀጣይ ለህብረተሰቡ እንደሚገለፅም ከንቲባዋ ጠቁመዋል።

ምሽት 1 ሰአት ገደማ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ከ4 ሰአት በላይ ጊዜ የወሰደ ሲሆን ይህም የሆነው በአከባቢው የመንገድና ሌሎች አመቺ ያልሆኑ ጉዳዮች ምክንያት ነው ተብሏል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

21 Oct, 17:05


የራይድ ታክሲ ተጠቃሚ በመምሰል ሾፌሮችን ሲገድሉ የነበሩ አራት ግለሰቦች በሞት ተቀጡ

የታክሲ ኮንትራት በመጥራት ሹፌሮችን በመግደል ተሽከርካሪ ሲሰርቁ የነበሩ አራት ግለሰቦች በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ ተላልፎባቸዋል።

በተለያዩ ጊዜያት አሽከርካሪዎችን  ራቅ ወዳለ ስፍራ እየወሰዱ በመግደል ተሽከርካሪዎችን ሲሰርቁ የነበሩ አራት ግለሰቦች በቁጥጥር  ስር ውለው በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ ተላልፎባቸዋል።

በአዲስ አበባ ገላን ክፍለ ከተማ፣ በሳሪስ እንዲሁም በቢሾፍቱ መኖሪያቸውን ያደረጉት ቴዎድሮስ ብርሃኔ እና  እዩኤል ቴዎድሮስ እንዲሁም በሌላ በኩል ተፈሪ ተስፋዬ እና ዩሃንስ አረፋ  የተባሉት ግለሰቦች  ከአዲስ አበባ ቢሾፍቱ በመመላለስ ድርጊቱን ሲፈጽሙ እንደነበር  የሸገር ከተማ አስተዳደር  ዓቃቢ ህግ ጽ/ቤት የተለያዩ ወንጀሎች ምርመራ ዓቃቢ ህግ አቶ ሚዴቅሳ አጋሩ  ተናግረዋል።

አራት ግለሰቦች ከግል ተበዳዮች በኮንትራት በመውሰድ ከዋናው መንገድ ውጪ በማስውጣት የአሽከርካሪዎቹን ህይወት በማጣፋት ተሽከርካሪዎቹን ይዞ በመሰወር  ለተለያዩ ጋራዦች እና  ግለሰቦች በመሸጥ ድርጊቱን ሲፈጽሙ እንደነበር ተገልጿል።

ተጨማሪ ያንብቡ:- https://bit.ly/3Y95f3w

#ethiopia #Deathpenality

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

21 Oct, 12:57


የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ምደባ በቅርቡ ይገለፃል- ትምህርት ሚኒስቴር

በርካታ ጥያቄ እየቀረበበት የሚገኘው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምደባ ጉዳይ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ምላሽ ሰጥቷል።

ሚኒስቴሩ በኦፊሻል የፌስ ቡክ ገፁ ላይ ባወጣው መረጃ "በ2016 የ12ኛ ክፍል  ሀገር አቀፍ ፈተና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ምደባ በቅርቡ ይገለፃል " ብሏል።

ይህንን በመገንዘብ ተማሪዎች በትዕግስት እንዲጠባበቁ ሚኒስቴሩ ጥሪ አቅርቧል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

21 Oct, 07:57


ኦብነግ ከሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ራሱን አገለለ

የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር ድርጅት አሳታፊነትና ግልጸኝነት ስላላየሁበት ከአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተሳታፊነት እራሴን አግልያለሁ ሲል ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

በሱማሌ ክልል የገዢው ፓርቲ መዋቅር ተሳታፊዎችን የሚለይበትና የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ድምጽ የሚያፍንበት ህገ-ወጥ አሰራር መዘርጋቱን የሚገልጸው ፓርቲው በዚህ ሂደት ውስጥ በምክክር መሳተፍ ረብ የለሽ ነው ሲልም ገልጾታል፡፡

ይህ አግላይ አሰራር አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተቋቋመበትን አላማ የሚጥስ ነው ሲልም በምክክር ኮሚሽኑ ሂደት ላይ ጥያቄ አንስቷል፡፡

ፓርቲው ከሱማሌ ክልል ውጪ በአማራና ኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳሱ የታጠቁ ሃይሎች ባልተሳተፉበት ሁኔታ እንዴት የምክክር ሂደቱ ሊሳካ ይችላል ሲልም በጥያቄ መልስ አንስቷል፡፡

በቀጣይም ሁሉን አቀፍ የድርድር መድረክ እስካልተዘጋጀ ድረስ በዚህ ሂደት ውስጥ መሳተፍ እንደማይችልም ጠቁሟል፡፡

ኦብነግ በ2010 ዓ.ም ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴን ለማድረግ ከፌዴራሉ መንግስት ጋር ስምምነት አድርጎ መግባቱ አይዘነጋም፡፡

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

19 Oct, 17:38


የጥቅምት ወር የደመወዝ ክፍያ በአዲሱ ስኬል እንደሚሆን ተገለፀ

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የጥቅምት ወር የደመወዝ ክፍያ በአዲሱ በተሻሻለው የደመወዝ ስኬል መሰረት መሆን ይጀምራል ብለዋል።

ለዚህም በቂ ዝግጅት ከመደረጉ በላይ የአፈፃፀም መመሪያ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

አዲሱ የደመወዝ ስኬል በሁሉም ክልሎች ተግባራዊ እንደሚሆን ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

19 Oct, 16:32


በመቄዶኒያ አረጋዊያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ድርጅት የእሳት አደጋ ደረሰ

በአዲስ አበባ አያት በሚገኘው የመቄዶኒያ አረጋዊያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ድርጅት፣ ዛሬ ከሰዓት  በኋላ የእሳት አደጋ ማጋጠሙ ተሰምቷል፡፡

አዲስ በመጠናቀቅ ላይ በሚገኘው ህንፃ ስር ተነስቶ ነበር የተባለው የእሳት አደጋ፣ ስላደረሰው የጉዳት መጠን እስካሁን የተገለፀ ነገር የለም።

የእሳት አደጋው ከአንድ ሰዓት በላይ በፈጀ ጥረት፣ በቁጥጥር ስር መዋሉም ተነግሯል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

19 Oct, 16:21


አዲስ የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች

በተለያዩ የስራ መስኮች የወጡ የNGO ስራዎችን በዝርዝር ለመመልከት እና ለማመልከት ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ

https://ethionegari.com/2024/10/19/care-ethiopia-latest-ngo-job-openings/

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

19 Oct, 16:08


በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር የዩናይትድ ብሬንትፎርድን አሸነፈ

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ስምንተኛ ስምንት በመካሄድ ላይ ሲሆን ማንችስተር ዩናይትድ በሜዳው ከብሬንትፎርድን አስተናግዷል።

2ለ1 በተጠናቀቀው በዚህ ጨዋታ አሊሀንድሮ በጋርናቾ እና ራስሙንድ ሆይሉንድ ጎሎችን ለማንችስተር አስቆጥረዋል።

የአርሰናል እና በርንማውዝ ጨዋታ ከቀዲቃዎች በኋላ ይካሄዳል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

#football

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

18 Oct, 15:10


በጫሞ ሀይቅ ላይ በደረሰ የጀልባ አደጋ 14 ሰዎች የገቡበት አልታወቀም

አደጋው የደረሰው ትላንት ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ነው።

ከኮሬ ዞን አቡሎ አርፋጮ ከሚባል አካባቢ ሙዝ ጭኖ ሲመለስ የነበረ ጀልባ ጫሞ ሐይቅ ሰምጦ ከተሳፈሩ  16 ሰዎች ውስጥ ሁለቱ መገኘታቸውን የጋሞ ዞን  ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሕዝብ ግንኙት እና ገጽታ ግንባታ ድቪዥን  ኃላፊ ኮማንደር ረታ ተክሉ፣ በጀልባው ላይ ከነበሩ 16 ሰዎች ሁለቱ በጀርካን ላይ ተንሳፈው የተረፉ ሲሆን 14ቱ ባለመገኘታቸው ፖሊስ በፍለጋ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

የጀልባዋ ተሳፋሪዎች በሙሉ ሙዝ ለመጫን ከአርባምንጭ ዙሪያ አካባቢ የሄዱ ናቸው።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook  https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

18 Oct, 12:41


በኢትዮጵያ ከሞቱ ሰዎች ኩላሊት እንዲለገስ የሚፈቅድ ህግ እንዲዘጋጅ ተጠየቀ

ኩላሊት ከሞተ ሰው እንዲወሰድ የሚፈቅድ ረቂቅ ህግ ከስድስት ዓመት በፊት የተዘጋጀ ቢሆንም እስካሁን መልስ እንዳላገኘ የኩላሊት ህመምተኞች ማህበር ተናግሯል፡፡

የኩላሊት ንቅለ ተከላ ለማድረግ የኩላሊት ልገሳን ከቤተሰብ ውጭ እንዲለገስ የማይፈቅደው የኢትዮጵያ የጤና ህግ  እንዲሻሻል ቢጠየቅም መልስ አለማግኘቱ ችግር እንደሆነ ተነግሯል።

በቅርቡ በተወካዮች ምክር ቤት የጤና ህጎች ረቂቅ አዋጅ መቅረቡ የሚታወስ ሲሆን ስለ ኩላሊት ልገሳ የሚያወራው ህግ ግን እስካሁን እንዳልቀረበ  በኩላሊት ተካሚዎች ማህበር በጎ አድራጎት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን አሰፋ ገልጸዋል።

ተጨማሪ ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://bit.ly/3BNWVil


#ethiopia #Kidneyhealth #organtransplant

Ethio Negari ኢትዮ ነጋሪ

18 Oct, 08:21


ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ሚንስትር ሆነው ተሾሙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥተዋል።

በዚሁ መሰረት ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ሚንስትር፣ ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ የቱሪዝም ሚንስቴር ሚንስትር፣ ወ/ሮ ሃና አርአያስላሴ፦ የፍትህ ሚንስቴር ሚንስትር ሆነው ተሾመዋል።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

�Telegram https://t.me/EthioNegarii

�Twitter https://twitter.com/EthioNegari

� YouTube https://youtube.com/channel/UCxywavkb3e3K7BY3BEh2piQ

Facebook https://www.facebook.com/EthioNegarii/

Website https://ethionegari.com/

LinkedIn https://www.linkedin.com/company/ethio-negari