ቤተ ቅዱስ ሚካኤል @saint_mikael Channel on Telegram

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

@saint_mikael


ለእኛ በ አባታችን ቤት መሆን መልካም ነው

ለማንኛውም ሀሳብ እና አስተያየት
@NAWI21
ይላኩልን

👇👇የYoutube Channel ይቀላቀላሉ👇👇

https://youtube.com/channel/UCqIww_vrxOATvuc5K_EDf1A?sub_confirmation=1

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል (Amharic)

የቤተ ቅዱስ ሚካኤል ታሪኩ የቤቱ እና አባትና እናት እንዲሆኑ የሚፈልገው መፅሀፍ መሠረት በደህንነቱ የይተንን ነገርን ተረትረብ። ቤተ ቅዱስ ሚካኤል ሁላችን የዚህ ሀሳብና አስተያየት የሚያገኙትን መረጃዎችን እና የYoutube ቻንሎ ከፍተኛ ከሆነ እንዲሁም አንዳች በነበሩ የትምህርት ሊያዳምጡ ጀመሩ። በቤተ ቅዱስ ሚካኤል የሚባሉት ገጽታዎችን ለአንዳች የታወቁ መረጃዎችና ተጨማሪ ዘገባችንን ይወከላል። ተጨናንቀው በለስላሊ ፅሁፎቹን በመታሰር ጥይታችንን ይዝናኑ።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

07 Feb, 12:42


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ጾመ ነነዌን አስመልክተው አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል !

ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

ሰኞ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የሚጀመረውን የፈጾመ ነነዌን አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሰላምና የጸሎት አዋጅ መግለጫ ሰጥተዋል።

ሙሉ መልእክቱ እንደሚከተለው ቀርቧል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተላለፈ የምህላ ሱባኤ፡-

‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ጉባኤውንም አውጁ፤ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ኣምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ (ኢዩ ፩÷፲፬)።

ሁላችንም እንደምናውቀው ያለንበት ዓለም የመከራ ዓለም ነው፣ መከራው በኛ ስሕተትና ክፋት የመጣና እየሆነ ያለ መሆኑም ይታወቃል፤ እኛ የምንፈጽመው ጥቃቅንና ትላልቅ ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን እንደሚያስቈጣ በቅዱስ መጽሐፍ ተረጋግጦ ያደረ ነው፤ ለዚህም ከነነዌ ነዋሪ ሕዝብ የበለጠ ማስረጃ የለንም፤ የነነዌ ከተማ ነዋሪዎች በፈጸሙት ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን አስቈጥተዋል፤ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ቢሆንም እሱ ምሕረቱን ማስቀደም ስለፈለገ በዮናስ በኩል አስጠንቅቆአቸዋል፤ የነነዌ ነዋሪዎችም በዮናስ በኩል የደረሳቸውን የንስሓ ጥሪ ወዲያውኑ ተቀብለው በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት ንስሓ ስለገቡ እግዚአብሔር ፍጹም ይቅርታ አድርጎላቸዋል፤

• የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን !

እኛ ሰዎች ዛሬም በየሰዓቱ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ አበሳ እንደምንፈጽም ማወቅ ኣለብን፣ አበሳውና ኃጢኣቱ ሲበዛ እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነውና ወደ ዳኝነት ተግባሩ ይገባል፤ይህ ደግሞ በሰብአ ትካት በሰዶምና በጎሞራ ያስተላለፈውን ዳኝነት ያስታውሰናል፤ አሁን ያለንበት ዘመን ዓመተ ምሕረት በመሆኑ እግዚአብሔር ለጊዜው ቢታገሠንም በኃጢኣታችን የምንጠየቅበት ጊዜ አዘጋጅቶአል፤ ዛሬም ቢሆን የማናስተውለው ሆነን ካልሆነ በስተቀር እግዚአብሔር ተግሣጹን ማስተላለፍ አላቆምም፤ በምድራችን ላይ በምናደርሰው የተዛባ ተግባር በጐርፍ፣ በድርቅ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በአየር መዛባት እየገሠጸን እንደሆነ ማስተዋል አለብን።

እግዚአብሔር ከጥንቱ ከጠዋቱ ጀምሮ ምድርን እንድንከባከባት፤ እንድናበጃት፣ እንድናጠብቃትና እንድናለማት አዞናል፤ ሆኖም ይህን ትእዛዙን ገሸሽ አድርገን በኬሜካልና በመርዛም ጋዝ ምድርን በመበከል፣ደንዋን በመመጠርና ራቁቷን በማስቀረት በምናደርገው ድርጊት አበሳ እየፈጸምን እንደሆነ ያወቅነው አይመስልም፤ በዚህም ምክንያት በጐርፍ፣ በድርቅ ለሰው ልጆች በማይመች የኣየር ፀባይ ወዘተ . . . ስጋት ውስጥ እየወደቅን ነው።

በሌላም በኩል በምናወሳስበው የአስተዳደር ርእዮትና መሳሳብ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና ያላስፈላጊ አደጋ ላይ እንድወድቅ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጠንቅ ሰላም እየደፈረሰ፣ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሃይማኖት ክብርና ልዕልና እየተነካ ራሳችንንም እየጐዳን ነው፤በዚህ ሁሉ ተግባራችን እግዚአብሔርን እያሳዘንን ነው፤ ይህ ሊገባንና ሊቈረቁረን ይገባል፤

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት

ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል፤ ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣የድርቅ መከሠት፣የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . . ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን፤ ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለዓለማችን ይስጠን፤ ምህላችንንም ይቀበልልን።

“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ”

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት

ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

06 Feb, 18:01


ጌታችን "እግድያስ እኔ የጠጣሁበት ዋንጫ ትቅረብና ትመስክርብኝ" አለው። በዚህ ተስማምተው ሙሴው ሄዶ አንድ ሽራፊ ዋንጫ አምጥቶ "በዚህ ነበር የሚሰጠውና የሚጠጣው" ብሎ አቀረበ። ዋንጫዋም ከተቀመጠችበት አንድ ክንድ ከስንዝር ተነስታ "ዓለማትን የፈጠረ አምላክ ምስክሬ ነው እኔ የያዝኩትን የወይን ጠጅ ዕቃ ሙሴም በእጆቹ አልያዘኝም በከንፈሩ አልካኝም በሌሎች ሰዎች እጅ ግን ተይዤ ያየን ነበር" አለች። ያን ጊዜ ሰውም እንስሳትም እፀዋትም ሁሉ ፆራ (ተሸክማ) የምትሔድ ሙሴን ልትጾር (ልትሸከመው) አልቻለችም። እንደ ዳታ አቤሮን ምድር ተከፍታ ከነልጁ ጋር ዋጠቻቸው። ማኅበረ ጻድቃንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ተረድተው እንደገና ከእግሩ ወድቀው ይቅርታ እንዲያደርግላቸው ለመኑት ቀኑም ጥር29 ነበር። ጌታችን ኢየሱስ ክስቶስ ይቅርታ ካደረገላቸው በኋላ "ስማችሁን የጠራ በስማችሁ ተዝካር ያወጣ በስማችሁ ድሆችን የረዳ፣ ያለበሰ፣ ያጎረሰ፣ የሰጠ፣ የመፀወተ፣ ቤተ ክርስትያኖች ሆነ የሠራ ያሠራ፣ እስከ14 ትውልድ ድረስ ምሬላችኋለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣቸው። ይህችን ቦታችሁ መጥቶ የሳመ ኢየሩሳሌም እንደሳመ አድርጌላችኋለሁ" አላቸው።

በኦሪት ኄኖክና፣ ዕዝራና ኤልያስ በሐዲስ ኪዳን እነ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድና በየጊዜው የሚሰወሩ ቅዱሳን ግልጽ ነውና እንዚሁም ጌታችን እነዚህ የማኅበረ ደጔ ጻድቃንም ከሞት ተሰወሩ ብሎ በበነገታው ጥር30 ቀን ሠውሮአቸዋል። በዚህም መሠረት ይህ ታላቅ በዓል ሆኖ ዛሬም በየዓመቱ ጥር30 ሲከበር ይኖራል። በገዳሙ ውስጥ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው የተፈጸመውን ነገር በውል የሚያስረዱ በዐይን የሚታዩ በእጅ የሚዳሰሱ በጌታችን ተአምራት የተደረገባቸው ቅርሶች በክብር ተጠብቀው ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ፡-

1.ክንድ ከስንዝር ወደላይ ተነሥታ በሰው አንደበት በመመስከር ጌታችን በእርሷ እንዳልጠጣባት የመሰከረችው ዋንጫ (ጽዋ)

2.ጌታችን የተቀመጠባትና ያስተማረባት ድንጋይ ከነምልክቷ።

3.ምስዋሮም የሚባል ጻድድቃኑ የተሰወሩበትን ሥፍራ።

4.ጌታችን ከድንጋይዋ ላይ ሁኖ ወርቅ ዘንጉን ወርውሮ ያፈለቀውና "ማየ ዮርዳኖስ" ይሁን ብሎ የሰየመው ጠበል።

4.ቅዱሳኑ ሲወቅጡበት የነበረው የድንጋይ ሙቀጫ።

5.በማህበራቸው ጊዜ ሲደግሱባቸው የነበሩ የድንጋይ ገበታዎች።

7.ቅዱሳኑ ከሀገራቸው ከሮም ያመጡት ባለመስታወት ቋሚ ዕፀ መስቀል።

8.ርዕሰ ዮሐንስ የሚባል ነገሥታት ከነዘውዳቸው ጳጳሳት ከነአክሊላቸውና ከነመስቀላቸው በዚያን ጊዜ የተሳሉበት ሥዕል።

9.ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በማኅበረ ጻድቃን ዴጔ ሆኖ ያስተማረበትና የጠመቀበትን በሥዕል የሚያሳይ።

10.ይህ ገዳሙ በዐፄ ካሌብ ዘመነ መንግሥት እንደተገደመና የገደሙትም ራሳቸው መሆኑን በአክሱም መጽሐፍ ክብረ ነገሥት ላይ ተጽፎ እንደሚገኝ በታሪኩ ተረጋግጦ ተላልፎልናል፡፡ ምንጭ፦ የማኅበረ ጻድቃን ዴጔ ጥንታዊ ገዳም ታሪክ ባጭሉ ከሚለው መጽሐፍ።

                          

                              
#የከበሩ_ቅዱሳን_ደናግል_ጲስጢስ_አላጲስና_አጋጲስ_እናቸው_ቅድስት_ሶፍያ፦ እናታቸው ከአንጾኪያ ከከበሩ ወገኖች ውስጥ ናት። እነዚህንም ሦስት ልጆች በወለደቻቸው ጊዜ በእሊህ ስሞች ጠራቻቸው ትርጓሜያቸውም ሃይማኖት ተስፋ ፍቅር ነው የራሷም ስም ትርጓሜ ጥበብ ማለት ነው። ጥቂትም በአደጉ ጊዜ ወደ ሮሜ ከተማ ወስዳ በጎ አምልኮን እግዚአብሔርን መፍራትን የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት አስተማራቻቸው በከሀዲውም የሮሜ ንጉሥ በአርያኖስ ዘንድ ወሬያቸው ተሰማ ወደ ርሱም ያመጡአቸው ዘንድ አዘዘና አመጡአቸው እናታቸውም በማስተማር ትመክራቸውና ታጸናቸው ነበር። እንዲህም ትላቸዋለች "ልጆቼ ተጠበቁ የዚህን የኃላፊውን ዓለም ክብር በማየት ልባችሁ እንዳይደክምና ከዘላለማዊ ክብር እንዳትርቁ ከሙሽራው ከክርስቶስ ጋር ሁናችሁ ወደ ሰማያዊ ሠርግ እንድትገቡ ጠንክሩ"። ዕድሜያቸውም የታላቂቱ ዐሥራ ሁለት የሁለተኛዪቱ ዐሥር የሦስተኛዪቱ ዘጠኝ ነው።

እናታቸው ወደ ንጉሥ በአቀረበቻቸው ጊዜ ታላቂቱን ጲስጢስን "እኔን ስሚ ከቤተ መንግሥቴ ታላላቆች ለአንዱ አጋባሻለሁ ብዙ ስጦታም እሰጥሻለሁ ለአጵሎን ስገጂ" አላት። እርሷም እርሱንና የረከሱ አማልክቶቹን ሰደበች እርሱም ተቆጥቶ በብረት ዘንጎች እንዲደበደቧት ጡቶቿንም እንዲቆርጡ እሳትንም ከብረት ምጣድ በታች በማንደድ ባሩድ፣ ሙጫ፣ ሰሊጥን በውስጡ አድርገው እጅግ አፍልተው ወደዚያ ይጨምሩዋት ዘንድ አዘዘ። በጨመሩዋትም ጊዜ እየፀለየች በብረት ምጣዱ ውስጥ ቆመች ከቶ እሳት አልነካትም። የምጣዱም ግለት ጸጥ ብሎ እንደ ጥዋት ጊዜ ጤዛ ቀዝቅዛ ሆነ ከዚያ ያሉ ሰዎችም አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑት ብዙዎችም በክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ራሶቻቸውንም ቈርጡዋቸውና በሰማዕትነት ሞቱ።

ከዚህም በኋላ የቅድስት ጲስጢስን ራስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ምስክርነቷንም ፈጽማ የምስክርነት አክሊልን ተቀበለች እናቷም ሥጋዋን አንሥታ ወሰደች። ዳግመኛም ሁለተኛዋን አላጲስን አቀረቧትና ደበደቧት ጽኑዕ ግርፋትንም ገረፏት ከጋለ ብረት ምጣድ ውስጥ ጨመርዋት በዚያንም ጊዜ ቀዝቅዞ እንደ ጥዋት ጤዛ ሆነ ንጉሡም ከዚያም እንዲአወጧትና ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ምስክርነቷንም አድርሳ በመንግሥተ ሰማያት የሕይወት አክሊልን ተቀበለች እናቷም ሥጋዋን ወሰደች።

ቅድስት ሶፍያም ከሥቃይ የተነሣ እንዳትደነግጥ ስለ ልጅዋ ስለ አጋጲስ ትፈራ ነበር ታጽናናትና እንድትታገሥ ታደርጋት ነበር በዚያንም ጊዜ ወስደው ከመንኰራኩር ውስጥ ጨመርዋት እግዚአብሔርም መልአኩን ልኮ ያንን መንኰራኲር ሰበረው እርሷም በደኅና ወጣች ዳግመኛም እሳትን አድደው ከውስጡ እንዲጥሏት አዘዘ እርሷም ፊቷን በመስቀል ምልክት አማትባ ወደሚነደው እሳቱ ተወርውራ ገባች በዚያንም ጊዜ እሳቱ እንደ ጥዋት ውርጭ የቀዘቀዘ ሆነ ከዚያ ያሉትም ሰዎች ብርሃን የለበሱ ሁለት ሰዎች ከነጫጭ ልብሶች ጋር ሲጋርዷዋት አይተው እጅግ አደነቁ ብዙዎችም በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ራሶቻቸውንም ቆርጠዋቸው በሰማዕትነት ሞቱ ያቺንም የዘጠኝ ዓመት ልጅ የከበረች አጋጲስን ራሷን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ። ምስክርነቷንም ፈጸመች ሁሉም የማያልፍ የማይጠፋ ሰማያዊ መንግሥትን ወረሱ።

የከበረች ሶፍያም የሦስት ልጆቿን ሥጋቸውን ወስዳ ገነዘቻቸው ወደ ከተማውም ውጭ አድርሳ በዚያ ቀበረቻቸው በሦስተኛውም ቀን ወደ መቃብራቸው ሔዳ አለቀሰች ነፍሷንም ይወስድ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነች ልመናዋንም ተቀብሎ ነፍሷን ወሰደ ምእመናን ሰዎችም መጥተው ገንዘው ከልጆቿ ጋር ቀበሩዋት። በከሀዲው ንጉሥ ላይ ግን እግዚአብሔር ጭንቅ የሆነ ደዌ ላከ ዐይኖቹም ፈረጡ ዐጥንቶቹም እስከማሚታዩ ሥጋው ሁሉ ተሠነጣጠቀ እጆቹም ተቆራረጡ ከእርሱም ደምና መግል ፈሰሰ ትልም ይወድቅ ነበር ሁለመናውም ተበላሽቶ በክፉ ሞት ሞተ። ስለ እነዚያ ደናግል ጌታ ተቀበቅሎታልና። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ደናግላን ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

06 Feb, 18:01


"በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

            #ጥር ፴ (30) ቀን።

እንኳን #ለማኅበረ_ዴጔ_ለሦስት_ሺህ_ጻድቃን እንደ ቅዱሳን ኄኖክና ዕዝራ ከዚህ ዓለም ከሞት ለተሰወሩበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው፣ ለከበሩ ደናግል #ለቅድስት_ሶፍያ_ልጆች ለቅድሳት #ለጲስጢስ_ለአላጲስና_ለአጋጲስ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ ስሙ መርቅያኖስ ለሚባል ለጣዖት ለሚሰግድ ለሮሜ ንጉሥ ልጅ ለከበረች #ለቅድስት_ኦርኒ ሰማዕትነት ለተቀበለችበት ለዕረፍቷ በዓል፣ ለከበረች #ቅድስት_ጤቅላ ከእርሷ ጋር ከሚኖሩ አራት ደናግል ጋር ፎላ በሚባል ኃጥእ ቄስ እጅ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና ተጋዳይ ለሆነ ለመነኰስ ለከበረ #አባ_አክርስጥሮስ ለዕረፍት በዓልና ለመለኮትን ነገር ለሚናገር ለቅዱስ ጎርጎርዮስ ለመታሰቢያ በዓሉ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክድርያ አገር አርባ ሰባተኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_ሚናስ ዕረፍትና #ከቅድስት_ኦርኒ_ማኅበር ከሆኑ #ከዐሥራ_ሦስት_ሺህ_ሰዎች በሰማዕትነት  ከዐረፉ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።  
 
                      
                           
#ማኅበረ_ዴጔ፦ ማለት የደጋጎች አገር ማለት ነው። የደጋጎች አገር የተባለበት ምክንያት ብዙ ሺህ ቅዱሳን ተሰብስበው ስለሚኖሩበት ነው፡፡ ገዳሙ የሚገኘው በትግራይ ክልል በአክሱም አውራጃ ከአክሱም ከተማ ወደ ደቡብ ምዕራብ በሚወስደው መንገድ ዐሥራ ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ ነው፡፡ ከገዳሙ ተያይዞ የተላከልን ዘገባ እንደሚያስረዳው ቤተ ክርስትያኑ በ39ዓ.ም እንተተተከለ በግልፅ ያስረዳል። ይኸውም መጽሐፈ ሱባኤ በተባለው በመሪ ኤ.ኤም የተዘጋጀው መጽሐፍ ከምዕራፍ 11 በገጽ 132 ላይ አቴዥን ሕንደቼ ንግሥት ነገሥታት ዘኢትዮጵያ ሆና በነገሠች በ39ዓ.ም በአንደኛው ዓመተ መንግሥትዋ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በ40ዓ.ም ማኅበረ ጻድቃን ዴጔ ገብቶ ሲያስተምርና ሲያጠምቅ ሰምታ መኳንንትና መሳፍንትን አሰከትላ መርዌ ወረደች ይላል።

በዚህም ንግሥቲቱ ቅዱስ ማቴዎስ አግኝታ "ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር አብ የባሕሪ ልጅ መሆኑ አውቃለሁ ይሁን እንጂ ዳግመኛ ከእግዚአብሔር ከድንግል ማርያም መወለዱን አላውቅም ነበር አሁን ግን በትምህርትህ መንፈስ ቅዱስ ስለ ገለጸልኝ አጥምቀኝ" አለችው። ቅዱስ ማቴዎስም ንግሥቲቱን ካጠመቀ በኋላ ቀጥሎ መኳንንቱን፣ መሳፍንቱን የጦር ሠራዊቱን ሁሉ አጥምቋቸዋል ይላል፡፡ አያይዞም ንግሥቲቱ ቅዱስ ማቴዎስን ይዛው ወደ አክሱም ተመለሰች፣ ልጆችዋንና ቤተሰቦችዋንም አስጠመቀች እንዲሁም አክሎስ የሚባል ባልዋም አምኖ ተጠመቀ። ቅዱስ ማቴዎስ ከዚህ በፊት የነባቡና የናግራንን ህዞቦች አጥምቆ ከዚህም በኋላ የጻድቃንን ዴጔ ማህበር አቋቁሞ በጌታችን ስም በየወሩ በ29ቀን እየተሰበሰቡ ጽዋ እንዲጠጡ አድርጓቸው ወደ ኢየሩሳሌም ሄዷል፡፡

በ365ዓ.ም በአስፍሕ ወልደ አብርሃም ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ዘመነ መንግሥት "ሮምያ" ከምትባል መንደር ቅዱሳን "ስለ ጽድቅ ብለው የሚሰደዱ ብፁአን ናቸው መንግሥተ ሰማያት የነርሱ ናትና" ያለውን ዳግመኛም "አባቱንና እናቱን ሚስቱንና ልጆቹን ያልተወ ሊያገለግለኝ አይችልም" ብሎ ጌታችን የተናገረውን አስበው ቅዱሳን የዚህም ዓለም ጣዕም ጥቅም ንቀው አገራቸውን ትተው መንነው ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ነበሩ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን በአክሱም ከተማ በስተሰሜን በሐውልቱ ጀርባ ቤተ ቀጠንት በሚባል ስፍራ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህል እንደ ተቀመጡ በዚያም ምቾትና ድሎት ስለተሰማባቸው "ለዚህ ለዚህማ አገራችንን ለምን ትተን መጣን? ስለዚህ ሱባዔ ገብተን በጾም በጸሎት ተወስነን የምንሄድበትን ቦታ በረከተ ነፍስ የምናገኝበትን ስፍራ እግዚአብሔር እንዲያሳየን እናመልክት" ብለው ሱባዔ ገቡ ጾም ያዙ፡፡ ከሱባዔውም በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጻላቸው ግማሾቹን እያንዳንዳቸው የሚኖሩበትን በዓት አመልክታቸው፣ በዚያም በጾምና በጸሎት ጸንተው እንዲኖሩ ነገረቻቸው፡፡ ሦስት ሺህ ያህሉን ደግሞ ከላይ ወደጠቀስነው ሥፍ ሄዱ፡፡ ከእነርሱ የተቀሩት ደግሞ ወደ ቆየፃ ሓባር፣ ተድባ፣ አኮርየን፣ ተንስሓ፣ ደብረ አንሳ ወደ ተባሉ ቦታዎች ሄደዋል፡፡ ተጨማሪ ሦስት ሺህ የሚሆኑት ደግሞ እዚያ ከነበሩት ጋር ተደመሩ፡፡

ከዚህም በኋላ እነዚህ ቅዱሳን "ከሁሉ ፍቅር ይበልጣል" የሚለውን ጠብቀው በእምነት በፍቅር በአንድነት ጸንተው በየሣምንቱ እሁድ እሁድ ተዝካረ ሰንበትን ጠብቀው ማኅበር ሲጠጡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅራቸው አይቶ በአምሳለ ነዳይ ደሀ መስሎ በመካከላቸው ተገኘ። ከነርሱ ጋርም አንድ ማኅበርተኛ ሁኖ እንዲታወቅ ጠየቃቸው፤ እነርሱም ፈቀዱለት አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህልም ከነርሱ ጋር ሳይለይ ቆየ በዚሁ ጊዜ "ለእኔም ተራ ስጡኝ እንደ አቅሜ ዝክር ላውጣ"አላቸው። እነርሱም ግን "አይሆንም አንተ ደሀ ነህ ከኛ ጋር ሁነህ በዓሉን አክብር እንጂ ምን አለህ እና ነውን" አሉት፣ እርሱም "አይሆንም ስጡኝ እንጅ አላቸው" እርሱም ካልክማ ብለው ቀን ወስነው ሰጡት ቀኑም ጥር29 ነበር። ከማኅበርተኞቹ መካከል "ሣይዳን" የሚባል ሰው ነበር፡፡ ይህም አሳላፊ ወይም ሙሴ ማለት ነው። ይህም ሰው እንግዳና ድሀ ሰው ፈጽሞ አይወድም ነበር፣ ጌታችንም ከማኅበርተኞቹ መካከል ሲገኝ ደሀ መስሎ ስለ ነበር በጣም ይጠላው ነበር።

አንድ ዓመት ከስድስት ወር ከነርሱ ጋር ሲቀመጥም አንድ ቀን ስኳን አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ ሰጥቶት አያውቅም ነበር፣ ሆኖም የጌታችን ማኅበር ደረሰ፣ እንደ ማኅበሩ ሥርዓት አሳላፊው ጠርቶ "ጋኖችን እጠብልኝ አለው" አሳላፊው "ቤትህ የማይታወቅ ከየት አምጥተህ ማኅበር ልታደርግ ነው" ብሎ አናንቆ ተመለከተው ጌታም አንድ እረኛ ጠርቶ "አንተ ልጅ ከብቶችህን እኔ እጠብቅልሃለሁና ውኃ አምጣልኝ" አለው፣ ልጁም ገምቦውን ይዞ ትንሽ ወጣ እንዳለ ጌታ ዘወትር ከሚቀመጥበት ድንጋይ ላይ ሆኖ ዘንጉን ወደ ልጁ አቅጣጫ ወረወረው፣ ዘንጉንም ከልጁ ፊት ሂዶ ተተከለ ልጁንም ጠርቶ ዘንጉንም ንቀለው አለው ልጁም ዘንጉን ቢነቅለው ውኃ ፈለቀ "ከርሱ ቀድተህ አምጣልኝ" አለው። ልጁም ከዚህ ውሃ ቀድቶ አመጣለት ጌታም ልጁ ባመጣው ውኃ ጋኖቹ ቀድቶ አጠባቸው፣ በበዓሉ ቀን ማኅበርተኞቹ ምን ሊያበላን ነው ምን ሊያጠጣን ነው ሳይሉ ሁሉም ተሰበሰቡ ጌታችንም በፊታቸው ጋኖቹን ቢባርካቸው የወይን ጠጅ ሞልተው ተገኙ። ቀድቶ ቢሰጣቸውና ቢቀምሱትም በጣም ግሩም ጣፍጭ ስለነበር እጅግ አደነቁ፣ እነርሱም ጌታችን ከጻድቃን አንዱ ስለመሰላቸው ከእግሩ ላይ ወድቀው "እስካሁን ድረስ ሳንበድልህ አልቀረንምና ይቅር በለን" ብለው ለመኑት ተነሡ ብሎ ካስነሳቸው በኋላ "እናንተ አልበደላችሁም፡ በደለኝ አሳላፊያችሁ ነው አንድ ቀን ስንኳ አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ አልሰጠኝምና አፋራርዱኝ" አላቸው። ነገር ግን ሙሴው የማያፍር ደፋርና ርጉም ስለነበር ሲጠይቁት "ይህ ሰው ጌታችንን በልቶ አልበላውም ጠጥቶ አልጠጣሁም የሚል ስለሆነና ስለማይጠግብ ነው እንጂ እንዲያውም ለናንተ አንድ አንድ ዋንጫ ሲሰጣችሁ ለእርሱ ሁለት ሁለት ነበር የሚሰጠው" ብሎ የሐሰት ቃል መለሰ።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

06 Feb, 18:01


እርሱም "ከአባቶችህ ጋር ትኖር ዘንድ ወደ ገዳምህ ተመለስ" የሚል ቃል መጣ፡፡ በተመለሰም ጊዜ አቡነ አክርስጥሮስ በሰላም ዐረፈ፡፡

                             
#ሰማዕቷ_ቅድስት_ጤቅላ፡- ጤቅላ ማለት "ልጅ፣ ለግላጋ" ማለት ነው፡፡ ቅድስት ጤቅላና ከእርሷ ጋር የነበሩ አራት ደናግል ጥር 30 ቀን ፎላ በሚባል ኃጥእ ቄስ እጅ ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ፡፡ ይህም ፎላ የተባለ ቄስ በአመጽ የሰበሰበው ብዙ ገንዘብ እንዳለው በከሃዲው መኰንን ዘንድ ነገሩበት፡፡ ስለዚህም መኮንኑ ገንዘቡን ሁሉ እንዲወርሱ አዘዘ፡፡ ፎላም ወደ መኰንኑ ዘንድ በመሄድ ገንዘቡን ይመልስለት ዘንድ ቢለምነው እምቢ አለው፡፡ ከሃዲው መኰንንም ስለ እነቅድስት ጤቅላ የምግባር የሃይማኖታቸውን ዜናቸውን በሰማ ጊዜ ወደ እርሱ እንዲያመጧቸው አዘዘና አስመጣቸው፡፡ ጌታችንን አስክዶ እምነታቸው አውጥቶ ለጣዖት እንዲገዙ ግድ አላቸው፡፡ እነርሱ ግን በእምነታቸው በጸኑ ጊዜ መኰንኑ ፎላንን ጠርቶ "እነዚህ ደናግል ለፀሐይ ይሰግዱ ዘንድ እነርሱን ብትሸግልልኝ ገንዘብህን መልሼ እሰጥሃለሁ" አለው፡፡ ፎላንም እነ ቅድስት ጤቅላን ይሸነግላቸው ጀመረ፡፡ ደናግሉም "አንተ የሰይጣን ልጅ የክብር ባለቤት ክርስቶስን እንክው ዘንድ እንዴት ትፈትነናለህ? አንተ ቀድሞ መምህራችን የነበርክ ስትሆን" ብለው ዘለፉት፡፡
መኰንኑም ይህን ቃላቸውን ከአንደበታቸው በሰማ ጊዜ በጅራፍ ጽኑ ግርፋትን አስገረፋቸው፡፡ እነዚህ ቅዱሳት ደናግል ግን ስለ ጌታችን ይመሰክሩ ነበር እንጂ ምንም አልፈሩም ነበር፡፡ መኰንኑም ፎላንን "የበከተ ብትበላ ደምንም ብትጠጣ ገንዘብህን እመልስልሃለሁ" ባለው ጊዜ እንዳለው አደረገ፡፡ ዳግመኛም "እነዚህን ደናግል ብትገድላቸው ገንዘብህን እመልስልሃለሁ" አለው፡፡ ፎላም ይህን በሰማ ጊዜ እንደ አስቆሮቱ ይሁዳ ልቡ በገንዘብ ፍቅር ተነድፏልና ልቡናውን አጽንቶ ቅዱሳት ደናግሉን ሊገድላቸው ሄደ፡፡ እነርሱም እንዲህ አሉት፡- "ከሃዲ ሆይ የመድኃኒታችንን የክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን በእጅህ ታቀበን አልነበረምን? ስለ ገንዘብ ፍቅር ብለህ እኛን የክርስቶስን በጎች ልታርድ መጣህን?" እያሉ በገሠጹት ጊዜ ሰልፍ እንደተማረ አርበኛ ሰው ሆኖ በሰይፍ ራስ ራሶቻቸውን ቆረጣቸው፡፡ መኰንኑም የፎላንን ብላሽነትና ድንቁርናውን አይቶ ወዲያው በሰይፍ ገደለው፡፡ ፎላም ገንዘቡን፣ ሃይማኖቱንና ነፍሱን አጣ፡፡ የእነዚህም ቅዱሳት ደናግል ስማቸው መሪ የሆነቻቸው ጤቅላ፣ ማርያ፣ ማርታ፣ አመታ፣ አበያ ሲሆን ጥር 30 ቀን ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጽመው የክብር አክሊልን ተቀዳጅተዋል፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን በአባ ጎርጎርዮስና አቡነ አክርስጥሮስ በቅድስት ጤቅላ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር30 ስንክሳር።

                             
                            
#የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወይወስዱ ለንጉሥ ደናግል ድኅሬሃ። ወቢጻሂ ይወስዱ ለከ። ወይወስድዎን በትፍሥሕት ወበኃሤት"። መዝ 44፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 5፥1-7፣ 1ኛ ጴጥ 5፥2-5 እና የሐዋ ሥራ 9፥37-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 23፥26-32። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታች የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የማኅበረ ጻድቃን (ዴጔ) በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

06 Feb, 18:01


                            
#ታላቋ_ሰማዕት_ቅድስት_ኦርኒ፡- ይኽችም ቅድስት ስሙ መርቅያኖስ የሚባል ለጣዖት የሚሰግድ የሮሙ ንጉሥ ልጅ ናት፡፡ እናቷ ግን ክርስቲያናዊት ናት፡፡ ንጉሡ አባቷም እልፍኝ አሠርቶላት በወርቅና በብር አስጊጦ ከ12 ደናግል ጠባቂዎች ጋር ወደዚያ አስገባት፡፡ ከዚያም ልጁ ኦርኒና ደናግሉ ይሰግዱላቸው ዘንድ 17 ጣዖታትን አመጣላቸው፡፡ ቅድስት ኦርኒም ሰባት ዓመት በዚያ ስትቆይ ወደ እግዚአብሔር ከመጸለይ አላቋረጠችም ነበር፡፡

ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ዐይኖቿን አቅንታ ስትጸልይ በአፏ የዘይት ቅጠል የያዘች ርግብን አየች፡፡ ርብቧም ቅጠሉን ከማዕዷ ላይ ጥላው ወጣች፡፡ ዳግመኛም ወደ ቅድስት ኦርኒ ወደ ምዕራብ ስትመለከት በአፉ ከይሲ የያዘ ቁራ መጥቶ በመዕዷ ላይ ጥሎት ሄደ፡፡ መምህሯም በመጣ ጊዜ ያየችውን ራእይ ነገረችው፡፡ እርሱም ሲተረጉምላት "ርግብ የጥበብ ነገር ነው፣ የዘይቱም ቅርንጫፍ በጥምቀት የሚገኝ ክብር ነው፣ ቁራውም ንጉሥ ነው፣ ከይሲውም መከራ ነው፣ አንቺም በርቺ ጠንክሪ በክርስቶስ ስም መከራ ትቀበይ ዘንድ አለሽና የሕይወትንም አክሊል ትቀበያለሽ" አላት፡፡

ቅድስት ኦርኒ ዕድሜዋ ከፍ ሲል ወላጆቿ ከታላላቅ ወገን ለሆነ ለከበረ ሰው ሊድሯት አሰቡ እርሷ ግን "ሰባት ቀን ታገሱኝ" አለችና ወደ ፈቀደው መንገድ እንዲመራት እግዚአብሔርን በጸሎት ጠየቀች፡፡ በዚህም ጊዜ የታዘዘ መልአክ መጥቶ "ኦርኒ ሆይ በርቺ፣ ኃይልንም ልበሺ፣ ሐዋርያው ጢሞቴዎስ ወዳንቺ መጥቶ የወንጌልን ትእዛዝ ያስተምርሻል፣ ያጠምቅሻል" አላት፡፡ ወዲያውም ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስ መጥቶ የቤቷን ግድግዳ ሰንጥቆ ገብቶ ሁሉንም ነገር አስተማራት፡፡ ከቆመበትም መሬት ውኃ አፍልቆ በውኃው ላይ ጸልዮ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃትና ከእርሷ ዘንድ ሄደ፡፡

ከዚህም በኋላ ቅድስት ኦርኒ ተነሥታ የአባቷን ጣዖቶች ሰባበረቻቸው፡፡ አባቷም መጥቶ ይህን ባየ ጊዜ በንዴት ወዲያው ሊድራት ሞከረ፡፡ እርሷ ግን "እኔስ ለሰማያዊው ሙሽራ ለክርስቶስ ተጠርቻለሁ፣ በስሙም ተጠምቄያለሁ" አለችው፡፡ ንጉሡ አበቷም የቅድስት ኦርኒ ንግግር በሰማ ጊዜ ታላቅ ቁጣን ተሞልቶ ከእልፍኟ እየጎተተ አወረዳት፡፡ ክርስቲያናዊት እናቷም ይህንን ስታይ እያለቀሰች በራሷ ላይ አመድ ነሰነሰች፡፡ አባቷም ታስረው ይቀለቡ የነበሩ 4 ኃያላን ፈረሶችን አምጥቶ የቅድስት ኦርኒን ፀጉር ከጅራታቸው ጋር አሥሮ እንዲጎትቷትና ሰውነቷ ተቆራርጦ እንዲያልቅ ፈረሶቹን አስሮጣቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አንዱ ፈረስ ሲሮጥ ሰንሰለቱን በጥሶ ሲያመልጥ የንጉሡን ቀኝ እጅ ቆረጠውና አባቷ ወዲያው ሞተ፡፡ የከበረች ቅድስት ኦርኒ ግን ተነሥታ ጸሎት በማድረግ ንጉሥ አባቷን ከሞት አስነሣችው፡፡ የተቆረጠ እጁንም እንደቀድሞው አድርጋ መለሰችለት፡፡ ሕዝቡም ይህንን ድንቅ ተአምር አይተው ከንጉሡ አባቷ ጋር በጌታችን አምነው ተጠመቁ፡፡ በዚህም የቅድስት ኦርኒ ተአምር ምክንያት የተጠመቁት ሰዎች ቁጥር ከሰላሳ ሺህ በላይ ነው፡፡

ንጉሥ ዳኬዎስም ይህን ተአምርና የቅድስት ኦርኒ ዜና ስለሰማ ወደዚያች አገር ገባ፡፡ የከበረች ቅድስት ኦርኒንም ይዞ በራሷ ፀጉር ሰቀላትና አሠቃያት፡፡ ዳግመኛም መርዛማ እባቦችና ጊንጦች ወደተሞሉበት ጉድጓድ ውስጥ ጨመራት፣ ነገር ግን መርዛማ እባቦቹና ጊንጦቹ በእግዚአብሔር ኃይል ሁሉም ወዲያው ሞቱ፡፡ ዳግመኛም ንጉሥ ዳኬዎስ በመጋዝ ይሰነጥቋት ዘንድ አዘዘ፤ እንዳዘዘውም ሊያደርጉባት ሲሉ መጋዙ ተሰበረ፡፡ ንጉሡም ወዲያው በሞት ተቀሰፈ፡፡ የዳኬዎስ ልጅም ይህን ሰምቶ በታላቅ ሆኖ መጣና አገሪቱን ከበባት፡፡ ቅድስት ኦርኒንም ይዞ የተሳሉ ወስፌዎችን በእጆቿና በእግሮቿ እንዲሰገሰጉ አደረገ፡፡ በጀርባዋም ላይ አሸዋ የተመላ ዳውላ አድርገው ከአራት ፈረሶች ላይ አስረው ሥጋዋ ተበጣጥሶ እስኪጠፋ ድረስ ፈረሶቹን አስሮጧቸው፡፡ በዚህም አልቻሏትም፤ የታዘዘ መልአክ መጥቶ እርሷ ከፈወሳት በኋላ የዳኬዎስን ልጅ በጦር ወግቶ ገደለው፡፡

የከበረች ቅድስት ኦርኒም ሃይማኖትን እያስተማረች፣ ድውያንን እየፈወሰች፣ ሙታንን እያስነሣች በታላቅ አገልግሎት ተቀመጠች፡፡ ከዚህም በኋላ 4ኛ ንጉሠሥ መጣና የእርሷን ዜና ሰምቶ ወደ እርሱ አስመጣት፡፡ ለጣዖትም እንድትሰግድ ባስገደዳት ጊዜ ጣዖቱቹንና እርሱን ረገመቻው፡፡ ንጉሡም በዚህ ተናዶ ከእሳት ውስጥ ጨመራት፡፡ እርሷም ከእሳቱ ውስጥ ሆና ስትጸልይ የታዘዘ መልአክ መጥቶ እሳቱን አቀዝቅዞ በሰላም አወጣት፡፡ ከእሳቱም ከወጣች በኋላ የንጉሡን ጣዖታት ዳግመኛ ዘለፈች፡፡ ንጉሡም በእርሷ ላይ የተፈጸመውን ታላቅ ተአምር አይቶ ቤታችን አመነ፡፡ አምስተኛውም የፋርስ ንጉሥ በመጣ ጊዜ ቅድስት ኦርኒን ይዞ በእጁ በያዘው ጦር ወጋትና ሞተች፡፡ የታዘዘ መልአክም መጥቶ ከሞት አስነሣትና ዳግመኛ በጌታችን ስም ማስተማር ጀመረች፡፡ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ተነጥቃ ወጣች፡፡ ማኅበርተኞቿ የሆኑ 13 ሺህ ሰዎች በዚሁ ዕለት በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ኦርኒ በጸሎቷ ይማረን በከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

                           
#የመለኮትን_ነገር_የሚናገር_አቡነ_ጎርጎርዮስ፡- በሌላም በኩል "ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ" እየተባለም ይጠራል፡፡ ሀገሩ ቂሳርያ ነው፡፡ በመጀመሪያ የሕግ ባለሙያ የነበረ ሲሆን በኋላ ግን የቍስጥንጥንያ ሊቀጳጳስ ሆኖ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በሐዋርያነት አገልግሏል፡፡ በደራሲነቱ ምድራውያን መላእክት ከተሰኙት ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ነው፡፡ የአምላክን ሰው መሆንና ምሥጢረ ሥላሴን እጅግ አስፍቶና አራቆ ያስተማረ ከመሆኑም በላይ ‹‹ዳግማዊ ዮሐንስ ነባቤ መነኮት›› ተብሎ እስኪጠራ ድረስ በነገረ መለኮት የተራቀቀ ታላቅ ሊቅ መምህር ነው፡፡ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙን የማይጠቅስ መጽሐፍና መምህር የለም፡፡ ሃይማኖተ አበው አጥብቆ የሚጠራው የቤተ ክርስቲያናችን መመኪያ ነው፡፡ የአርመንን ኦርቶዶክስ ያቀና ሲሆን መንበሩን የኖኅ መርከብ ባረፈችበት አራራት ተራራ ላይ ነው የሠራው፡፡

                           
#አቡነ_አክርስጥሮስ፡- ይኽም ቅዱስ አባት በዮርዳኖስ በረሃ የሚኖር ታላቅ ተጋዳይ ነው፡፡ ከመነኮሳቱም አንዱ በፊቱ እየሰገደ ሥራውን ይገልጥለት ዘንድ በእግዚአብሔር ስም አማለው፡፡ ሽማግሌው አክርስጥሮስም እንዲህ ብሎ መለሰለት፡- "ልጄ ሆይ! ጎልማሳ ሆኜ ሳለ በመነኰስኩ ጊዜ በዚያ እጸልይ ዘንድ በሌሊት ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ መቅደስ እሄድ ነበር፡፡ 12 ደረጃዎችም አሏት፣ በእንዳንዱ ደረጃ መቶ መቶ ስግደቶቸን እሰግዳለሁ፡፡ ደወልንም በሚደውሉ ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመግባት ከወንደሞች ጋር የማኅበሩን የጸሎት ሥርዓት እፈጽማለሁ፣ እንዲህም በማድረግ 10 ዓመት ኖርኩ፡፡
ከሌሊቶቹም በአንዲቱ የተለመደ ጸሎቴን ከፈጸምኩ በኋላ ልቡናዬ በተመስጦ ተማረከ፡፡ ነጫጭ ልብሶችን የለበሱ ሁለት ሰዎች መቅረዞችን ሲያበሩ እኩሌቶቹ ሲበሩ እኩሌቶቹ ሲጠፉ አየሁ፡፡ እኔም "ይህ ሥራ ምንድነው?" አልኳቸው፡፡ እነዚያም አባቶች "ባልጀራውን የሚወድ መቅረዙ ይበራለታል" አሉኝ፡፡ እኔም ደግሙ "መቅረዜ የትኛው ነው?" አልኳቸው፡፡ እነርሱም "ሂድ ከወንድሞችህ ጋር ተፋቀር፣ እኛ እናበራልሃለን" አሉኝ፡፡ በነቃሁም ጊዜ ማንንም አላገኘሁም" ብሎ ለጠየቀው መነኮስ ነገረው፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ አክርስጥሮስ ብቻውን ወደ ደብረ ሲና ሄዶ በዚያ እየተጋደለ 50 ዓመት ኖረ፡፡ ወደ

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

05 Feb, 16:22


"በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ  አሜን"።

            #ጥር ፳፱ 29 ቀን

እንኳን #ጌታችን_አምላካች_መድኀኒታችን_ኢየሱስ ክርስቶስ በአካል ተገልጦ በደሃ ሰው ተመስሎ ከማኅበረ ዴጔ ጋር በመካከላቸውም ተገኝቶ የጽዋ ማኅበር እየጠጣ ተራው ደርሶ ተዓምር አድርጎ አምላክነቱ ለገለጠበት ቀን ለመታሰቢያ በዓል፣  የስሟ ትርጓሜ መጻተኛ ለሆነ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ በራእይ ለተገለጠላትና ከከበሩ ነገሥታት ወገን ለሆነችው ዓለምን ንቃ በመመንኰስ በምትተኛ ጊዜ ያለ ምንጣፍ በምድር ላይ እየተኛችና ጥሬ ባቄላን ብቻ እየተመገበች በታላቅ ተጋድሎ ለኖረችው ለከበረች #ቅድስት_አክሳኒ ለዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ፣ ተጋዳይ ለሆነ በበረሃ ውስጥ የሞተ ሰው ራስ ቅል አግኝተው የራስ ቅሉን ላነጋገሩና ሥራውን መርምረው ለተረዱ በኋላም አማልደውት ምሕረትን ላሰጡት #አባ_እስጢፍኖስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከድንግል እመቤታችን ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከተወለደበት #ከልደቱ_በዓለ_ወልድ_ወራዊ መታሰቢያ፣ ከመስተጋድል ከከበረ #ሰማዕት_ከሰርያኮስ ከመታሰቢያው፣ ከሮሜ ሰዎች ውስጥ #ከንጹሐት_ሴቶች ከመታሰቢያቸው፣ #ከፊልንማ_ከኢያልኒ_ከሰረባሞኒና_ከቃውት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
                         

                           
#ቅድስት_አክሳኒ፦ ይችም ቅድስት የስሟ ትርጓሜ መጻተኛ ለማለት ነው። እርሷም ከሮሜ አገር ለከበሩ ሰዎች ልጅ ናት ወላጆቿም ከርሷ በቀር ልጅ የላቸውም እርሷም የምትጋደል ሆነች በቀንና በሌሊትም ትጾማለች ትጸልያለች በሮሜ አገር ወዳለ የደናግል ገዳም በመሔድ ከእርሳቸው ጋር ታገለግላለች ትጸልያለች በሮሜ አገር ወዳለ የደናግል ገዳም በመሔድ ከእሳቸው ጋር ትጋደላለች ከአባቷ ቤት የሚያመጡላትን ምግብ ለድኆችና ለምስኪኖች ሰጥታ እርሷ ከደናግል ምግብ ትመገባለች የደናግል መነኵሳይትንም ገድል አዘውትራ ታነባለች ከእርሳቸውም ጋር አንድ ያደርጋት ዘንድ እግዚአብሔርን አብዝታ ትለምን ነበር።

ከዚህም በኋላ ወላጆቿ ሊአገቧት አስበው ከሮሜ አገር ታላላቆች ለአንዱ አጭዋት የወርቅ ልብሶችን ከወርቅና ከብር የተሠሩ የከበሩ ሽልማቶችንና ጌጦችንም አዘጋጁላት። የጋብቻውም ቀን ሲደርስ እናቷን "እናቴ ሆይ በምታጋቡኝ ጊዜ ወደ ደናግል መሔድ አይቻለኝም እኔ ዛሬ ሔጄ በረከታቸውን ተቀብዬ ሰላምታ ሰጥቻቸው ፈጥኜ መመለስ እሻለሁ" አለቻት። እናቷም የነገሥታት የሆነ የወርቅ ልብሶችን አልብሳ ሴቶች አገልጋዮችን ከእርሷ ጋር አድርጋ አሰናበተቻት።

እርሷም ግን ወደ ባሕር ወደብ ተጉዟ መርከብንም አግኝታ ተሳፈረችና ወደ ቆጵሮስ ደሴት ሔደች። ወደ ከበረ ኤጲፋንዮስም ደርሳ ኀሳቧን ሁሉ አስረዳችው የከበረ ኤጲፋንዮስም ወደ እስክንድርያ አገር ሰደዳት ወደዚያም በደረሰች ጊዜ በሕልሟ የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ተገልጾ ስሙን ነገራትና የምትሠራውን ሁሉ አስተማራት። በማግሥቱም ወደ ሊቀ ጳጳስት ቴዎፍሎስ ገባች የራሷንም ጠጉር ተላጭታ የምንኵሴና ልብስን ለበሰች ከርሷ ጋር ያሉ ሽልማቶችንና ጌጦችን የወርቅ ልብሶችንም ሸጠችና በሰማዕታት መጀመሪያ በከበረ እስጢፋኖስ ስም ቤተ ክርስቲያን ሠራች አባ ቴዎፍሎስም ብዙዎች ደናግል መነኰሳይትን ሰበሰበላትና በዚያ ገዳም ከርሷ ጋር የሚኖሩ ሆኑ።

ይቺም ቅድስት አክሳኒ ታላቅ ተጋድሎን ጀመረች እርሷ ከጥሬ ባቄላ በቀር በእሳት ያበሰሉትን አትቀምስና በምትተኛም ጊዜ ያለ ምንጣፍ በምድር ላይ ትተኛ ነበር እንዲህም እየተጋደለች ሃያ ዓመት ያህል ከዚያም የሚበዛ ኖረች ከዚህም በኋላ ጥቂት ታመመችና ዐረፈች። ልዑል እግዚአብሔር የሰጣትን ልዕልና ሊገልጥ ወደደ። በአረፈችበትም ዕለት ሰዎች በቀትር ጊዜ የብርሃን መስቀል በሰማይ ውስጥ አዩ ብርሃኑም የፀሐይን ብርሃን ሸፍኖ ነበር የሚያበሩ ከዋክብትም አክሊላትም በዙሪያው ሁነው ሥጋዋን ከደናግል ሥጋ ጋር አስከ አኖሩ ድረስ የሚያበሩ ሆኑ ከዚያም በኋላ ተሠወረ ይህም ስርሷ እንደተገለጠ ሕዝቡ አወቁ።

በዚያንም ጊዜ እነዚህ ሁለት አገልጋዮቿ የዚችን ቅድስት አክሳኒ ከመጀመሪያው እስከ ዕረፍቷ ያለ ገድሏን ለሊቀ ጳጳሳቱና ለሕዝቡ ሁሉ ስማቸውን ለውጣ እኅቶቿ እንዳለቻቸው እርሷንም እመቤታችን ማለት ሳይሆን እኅታችን እንዲሏት ምሥጢሯንም ሁሉ እንዲሠውሩ እንዳማለቻቸው ተናገሩ። ሊቀ ጳጳሳቱና ሕዝቡም ሁሉ አደነቁ ገድሏንም እስከመጨረሻው ጻፉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት አክሳኒ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።

                          
#አባ_እስጢፋኖስ፦ ይህም ቅዱስ ቅዱሳን ገዳማውያንን በመፈለግ በበረሀ ውስጥ ሲዞር የወደቀች የሰው ራስ አገኘ እርሷም ሥጋ የልላት ዐጥንት ብቻ ናት። ሥራዋንም ያስረዳው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነ በዚያንም ጊዜ ከዚያች ራስ ውስጥ እንዲህ የሚል ቃል ወጣ "እኔ በብዝበዛ ጭምር የማተርፍ ነጋዴ ነበርኩ መመጽወትንም አላውቅም በእኔ ዘንድ ሩቅ ወደ ሆነ አገር ስጓዝ ውኃ ወደ ሌለበት በረሀ ደረስኩ የቀን ሐሩርም በጸና ጊዜ ግመሎቼ ሞቱ ባሮቼም ሸሹ ብቻዬንም ቀረሁ። በሦስተኛውም ቀን ዐይኖቼ ከበዱኝ እንደፋጨትም ያለ ሰማሁ ያንጊዜ ነፍሴ ወጣች እንደሥራዬም ቅጣቴን ልቀበል ወደ ሥቃይ ቦታ ወሰዱኝ አንተም በለመንክ ጊዜ ሥራዬን እነግርህ ዘንድ ወዳንተ አመጡኝ አሁንም ወደ ሥቃይ ቦታ እንዳይመልሱኝ እግዚአብሔርን ስለ እኔ ምሕረትን ትለምነው ዘንድ እማልድሃለሁ" አለው።

ቅዱስም ወደ እግዚአብሔር ስርሱ ለመነለት በዚያንም ጊዜ ስለ አንተ ምሬዋለሁ የሚል ቃልን ሰማ ይህንንም ሰምቶ ወደ በዓቱ ሔደ እስከ ዐረፈ ድረስም እያለቀሰና ደረቱን እየደቃ ኖረ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ እስጢፋኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 29 ስንክሳር።

                            
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለ ኃይል። ወብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ"። መዝ 109፥3 ወይም መዝ 38፥12-13።የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 12፥16-40 ወይም ዮሐ1፥7-15።

                            
የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እስመ ፈላሲ አነ ውስተ ምድር። ወነግድ ከመ ኵሉ አበውየ። ስሐተኒ ከመ አፅርፍ"። መዝ 38፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ  3፥14-1ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 1፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥12-17። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1፥7-15። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው።  መልካም የጌታችንን በማኅበረ ዶጌ ያደረገ የተአምር በዐል፣ የአቡነ ታዴዎስ፣ የአቡነ ማትያስና የአቡነ ገብረ ናዝራዊ  የዕረፍታቸው በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
  

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

04 Feb, 16:35


ዮሴፍም ከዋሻ ገብቶ በሰባት ቀን እየጾመና እየጸለየ በገድል ተጠምዶ ሃያ ስምንት ዓመት ያህል ኖረ ከዚህም በኋላ ዕረፍቱ እንደቀረበ በአወቀ ጊዜ የቅዱስ ጊዮርጊስ ወደሆነች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ በቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ፊት ቁሞ ወደ ተወዳጅ ልጅዋ ትማልድለት ዘንድ ለመናት ከሥዕሉ ውስጥም እንዲህ አለችው "ዮሴፍ ሆይ በሦስተኛው ቀን በሦስት ሰዓት ወደኔ ትመጣለህና ደስ ይበልህ" በዚያችም ዕለት ጥር 28 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ዮሴፍ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

                          
"#ሰላም_ለቀሌምንጦስ_ዘተበፅዐ_ትግሥቱ። በዐውደ ምኵናን ኃምስቱ። በብዙኅ ኵነኔ እምድኅረ ኰነንዎ ሎቱ። #እግዚአብሔር አስተቀጸሎ ህየንተ ፍሉሕ ሩጸቱ። #ከመ_ጊዮርጊስ_በአክሊል_ሰብዓቱ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር_28።

                           
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወይኤምሮ ፍኖተ ለልቡባን። ኵሉ ፍኖቱ ለእግዚአብሔር ሣህል ወጽድቅ። ለእለ የኀሡ ሕጎ ወስምዖ። መዝ 24፥9። የሚነበበው ወንጌል ማር 10፥1-13።

                           
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወአዝነመ ሎሙ መና ይብልዑ። ወወሀቦሙ ኅብስተ ሰማይ። ወኅብስተ መላእክቲሁ በልዑ እጓለ እመሕያው"። መዝ 77፥24-25 ወይም መዝ መዝ 64፥4-5።
የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥8-17፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-ፍ.ም፣ የሐዋ ሥራ 2፥32-40። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 15፥32-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የአምላካችን የቅዱስ አማኑኤል በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

04 Feb, 16:35


"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

             #ጥር ፳፰ (28) ቀን።

እንኳን #ለአምላካች_ለቅዱስ_አማኑኤል ተአምራት አድርጎ አምስት እንጀራንና ሁለት ዓሣን አበርክቶ ሕፃናትና ሴቶች ሳይቆጠሩ አምስት ሺህ (አምስት የገብያ ሕዝብ ለመገበበት (ላጠገበበት) ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል፣ ኪራኮስ ከሚባል አገር ስሟ አክሮስያ የምትባል ለመበለት ልጅ ሰባት ጊዜ ታላላቅ አሠቃቂ መከራዎችን በመቀበል ሰማዕትነቱን ለፈጸመው ለከበረ #ለቅዱስ_ቀሌምንጦስ ለዕረፍቱ በዓል፣ ፍዩም ከሚባል ሀገር ለሆነ ሰይጣን ይዞ በራሱ ጠጉር አሥሮ ለቀጣው ለከበረ መነኰስ #ለአባ_አካውህ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና፣ ለከበረ ለአይሁዳዊ ለማኅው ልጅ እመቤታችን ከእሳት ውስጥ አውጥታ ላዳነችው በዕረፍቱም ጊዜ "በሦስተኛው ቀን በሦስት ሰዓት ወደኔ ትመጣለህና ደስ ይበልህ" ላለችው #ለቅዱስ_ዮሴፍ ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ ሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱስ_አባ_አካውህ_ማኅበር ከስምንት መቶ ሰማዕታት፣ ከአባቶቻችን #ከቅዱሳን_አብርሃም_ከይስሐቅና_ከያዕቆብ፣ #ከሠልስቱ_ደቂቅና_ከታቤላ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

                             
#ሰማዕቱ_ቅዱስ_ቀሌምንጦስ፦ ይህም ቅዱስ ኪራስ ከሚባል አገር ስሟ አክሮስያ የምትባል የመበለት ልጅ ነው። ሰማዕት የሆነው በገላትያ ነገሥታት በአርያኖስና በሉቅዮስ ዘመን ነው ከታናሽነቱም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሥርዓቷንና ሕጓንም እናቱ አስተማረችው ዕድሜውም ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲሆነው በጾምና በጸሎት መጋደል ጀመረ አገልግሎትንም አበዛ በእሳት የበሰለ ሥጋም ቢሆን አይበላም ነበር። እንደ ሠለስቱ ደቂቅ ጥሬ ባቄላ የሚመገብ ሆነ እንጂ ዲቁናም ተሾመ ጥበብና እውቀትም ተጨመረለት።

ወሬውም በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ በተሰማ ጊዜ ወደርሱ አስቀርቦ ብዙ ሸነገለው ለርሱም ልጁ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ትእዛዙንም ባልሰማ ጊዜ ታላቅ ሥቃይን አሠቃየው እግዚአብሔርም አጸናው ያለ ጉዳትም በጤንነት አስነሣው ከሀድያንን አሳፈራቸው። በዚያንም ጊዜ የምስክርነቱ ተጋድሎ በዲዮቅልጥያኖስ እጅ ሰባት እስቲደርስ አንድ ተብሎ ተቈጠረለት።

ማሠቃየቱንም በደከመ ጊዜ ዲዮቅልጥያኖስ ወደ ሮሜ ንጉሥ ላከው እንዲህም ብሎ ጻፈ "ይህ መሠርይ ከቶ እንደርሱ ያለ መሠርይ አላየሁም ለአማልክትም ይሠዋ ዘንድ ምናልባት ልቡን መመለስ። ብትችል እነሆ ወዳንተ ላክሁት"። ወደ ሮሜው ንጉሥም በደረሰ ጊዜ የወርቅ ልብሶችን አመጡለት እነርሱም ወደ ልብሶች አልተመለከተም ንጉሡም በእርሱ ላይ ተቆጣ ቊጣውንም አልፈራም በዚያንም ጊዜ በመንኰራኵር ታላቅ ሥቃይን አሠቃየው ገረፈውም ሕዋሳቱን አስቆራረጠ እግዚአብሔርም እንደ ቀድሞው ያለ ጥፋት በጤንነት አስነሣው ይህም ሁለተኛ ምስክርነት ነው። ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ወደ ኒቆምድያ ከተማ ወደ መክስምያኖስ ላከው በዚያም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃዩት ጌታችንም እንደቀድሞው በጤንነት አስነሥቶት ጠላቶቹን አሳፈራቸው ይህም ሦስተኛ ምስክርነት ነው።

ከዚህም በኋላ ወደ አደገባት ወደ ኪራስ ከተማ መለሱት በዚያም አሠቃዩት ጌታችንም በጤንነት ያለሥቃይ አስነሣው ይህም አራተኛ ምስክነት ነው። ዳግመኛም ወደ መክስምኖስ መለሱት በዚያም ቅዱስ ከልከላዎስንና ብዙ ሰማዕታትን አግኝቶ እርስ በርሳቸው ተጽናኑ የከበረ ቀሌምንጦስንም ጽኑ ሥቃይን አሠቃዩት ጌታችንም እንደቀድሞው አዳነው ይህም አምስተኛ ምስክርነቱ ነው።

ከዚህም በኋላ ወደ መኰንን ሉቅዮስ ወሰዱትና በዚያ አሠቃዩት ጌታችንም አዳነው ይህም ስድስተኛው ምስክርነት ነው። ሰባተኛውም ምስክርነት ብዙ ከአሠቃዩ በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጡ ሶፍያ የምትባል አማኒት ሴት መጥታ የቅዱሱን ሥጋ ወስዳ ገንዛ ቀበረች። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ቀሌምንጦስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

                           
#አባ_አካውህ፦ ይህም ቅዱስ ፍዩም ከሚባል አገር ነው በምንኵስናም ታላቅ ተጋድሎን ሲጋደል የኖረ ነው ሰይጣንም ተገልጦ መጣበት ቅዱስ አካውህም ሰይጣንን ይዞ በራሱ ጠጉር አሠረውና ሊቀጣው ጀመረ። ሰይጣንም "ትለቀኝ ዘንድ በክርስቶስ መከራዎች አምልሃለሁ" ብሎ ጮኸ በዚያንም ጊዜ ሰደደው እንደ ጢስም ተበተነ።

ከዚህም በኋላ በስደት ወራት ወደ ከሀድያን አደባባይ ሔደና "እኔ ክርስቲያን ነኝ" ብሎ ጮኸ ከሀድያንም ጽኑ ሥቃይን አሠቃይተው ጥር28 ቀን ራሱን በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አካውህ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

                             
#የከበረ_አይሁዳዊ°የማኅው_ልጅ_ቅዱስ_ዮሴፍ፦ ይህም ቅዱስ እስራኤላዊ ነው የአይሁድንም ሃይማኖት እየተማረ አደገ መጻሕፍቶቻቸውንም ተማረ። በአንዲትም ዕለት እየተማሩ ሳለ የክርስቲያንን ልጆች አያቸው ከእርሳቸውም ጋር ትደምረው ዘንድ እናቱን ለመናት። በደመረችውም ጊዜ የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ሁሉ ተማረ የክርስቶስ ሃይማኖት ፍቅርም በልቡ አደረ ከዚህም በኋላ የቤተ ክርስቲያንን ሕግ ከሚወድና ከሚጠብቅ ከአንድ ክርስቲያናዊ ወጣት ጋር ተገናኘ እርሱም በቊርባን ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን ወሰደው ዮሴፍም ሥጋውንና ደሙን ተቀበለ። በማግሥቱም አናጒንስጢሶችና መዘምራን ከዮሴፍ ጋር ተሰበሰቡ ልብሶቻቸውንም እንደ ድንኳንና እንደ መጋረጃ አምሳል በመሥራት ከቤታቸው ዳቦ አመጡ በጨዋታ መልክ ከውስጣቸው ሊቀ ጳጳሳትን ኤጲስቆጶሳትን ሾሙና የቊርባን ሥርዓት ሠሩ ወደሚያስተምራቸውም መምህር ቤት ሔደው ይበሉ ይጠጡ ነበር እንዲህም እያደረጉ ኖሩ።

የዮሴፍ አባት በሰማ ጊዜ ቊጣን ተመልቶ ልጁን የግንግሪት አሠረው በውጡ እሳትን የተመላ ጒድጓድ ወዳለበት ወህኒ ወስዶ ጨመረውና በላዩ የእቶኑን በር ዘጋበት የእግዚአብሔርም መልአክ እሳቱን አቀዘቀዘው እናቱ ግን ልጅዋን በአጣችው ጊዜ በመጮህ አለቀሰች የምታደርገውንም አጣች። ከሰባት ቀኖችም በኋላ የዮሴፍን ወሬ ወደ እሳት እንደተጨመረ ባልጀሮቹ ሰምተው በመጮህ እያለቀሱ ስሙንም እየጠሩ መጡ ዮሴፍም ከውስጥ እንዲህ ሲል መለሰላቸው "በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት በእመቤቴ ማርያም ርዳታ እኔ በሕይወት አለሁና ወንድሞቼ አታልቅሱ እርሷም ከእሳቱ በልብሷ ሸፍና አድናኛለችና" ይህንን በሰሙ ጊዜ ለሊቀ ጳጳሳቱ ነገሩት። እርሱም ወዲያውኑ ተነሣ ከካህናቱ ጋር ወንጌልን መስቀልንና ማዕጠንቶችን ይዘው ሔዱ ወደ እቶኑም በደረሱ ጊዜ ጸሎትን አድርገው ዮሴፍን ከማሠሪያው ፈትተው አወጡት። አባቱ ማኅውም በሰማ ጊዜ መጥቶ ከሊቀ ጳጳሳቱ እግር በታች ወድቆ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ የክርስትና ጥምቀትንም ያጠምቀው ዘንድ ለመነውና ከቤተ ሰቦቹ ሁሉ ጋር አጠመቀው።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

23 Jan, 02:15


ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta):
"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

              #ጥር ፲፭ (15) ቀን።

እንኳን #ለከበረ_ሕፃን በሦስት ዓመቱ ተጋድሎውን ለፈጸመ #ለቅዱስ_ቂርቆስ_ለዕረፍቱ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል፣ #ለቅዱስ_ቂርቆስ_ማኅበር_ለዐሥራ_አንድ_ሽህ_አራት_ሰዎች_ሰማዕትነት ለተበቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና ለሐናንያ ልጅ ለዕውተኛ ነቢይ #ለቅዱስ_አብድዩ ለዕረፍት በዓል። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ በሶርያ አገር ያሉ የክርስቲያን ወገኖች #ለቅዱስ_ጎርጎርዮስ የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል ከመያከብሩት፣ #ከጴጥሮስ_ከሶፍያ_ከአድምራና_ከይስሐቅ ከዕረፍታቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
                                                           
                           
# ሕፃኑ_ቅዱስ_ቂርቆስ፦ በዚያንም ወራት የክብር ባለቤት የሆነ ክርስቶስን በሚያምኑ የክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራና ስደት ሆነ። ስሟ ኢየሉጣ የሚባል አንዲት ሴት ነበረች እርሷም ከታናሽነቷ ጀምራ ደግ ናት ስደትም እንደሆነ በሰማች ጊዜ መኰንኑን ከመፍራት የተነሣ ሕፃኗን ይዛ ከሮሜ ከተማ ተሰዳ የኪልቅያ አውራጃ ከሆነ ከጠርሴስ ደርሳ ከዚያም በአገሮች ውስጥ እየተዘዋወረች ተቀመጠች። ወደዚያች አገርም ያ ከእርሱ የሸሸችው መኰንን እለእስክድሮስ መጣ ጭፍሮቹም ክርስቲያኖችን ፈለጓቸው። ይቺንም ቅድስት ኢየሉጣን አግኝተው ያዝዋትና ወደ መኰንኑ አደረሷት የክርስቲያን ወገንም እንደሆነች ነገሩት።

መኰንኑም "ሴትዮ ተናገሪ ከወዴት ሕዝብ ወገን ነሽ ነገድሽ ምንድን ነው አገርሽስ ወዴት ነው" አላት። የከበረች ኢየሉጣም እንዲህ ብላ መለሰችለት "የአንጌቤን ሰው ለሆንኩ ለእኔ ወገኖቼ ኤሳውሮሳውያን ናቸው እኔም በአንተ ምክንያት ሸሽቼ ነበር እነሆ ዛሬ ግን በእጅህ ውስጥ ነኝ" አለችው። መኰንኑም "በእጄ ውስጥ እንደተገኘሽ ታውቂያለሽን" አላት "አሁንም የሚሻልሽን ምረጪ ስምሽንም ተናገሪ እኔንም እሺ በይኝና ለአማልክት ሠዊ" የከበረች ኢየሉጣም አለችው "ለረከሱ አማልክት እኔ አልሠዋም" አለችው መኰንኑም "ስምሽን ስጪ ተናገሪ" አላት እርሷም "የኔ ስም ክርስቲያን መባል ነው" አለችው። መኰንኑም "ይህስ ስንፍና ነው የሚጠቅምሽ አይደለም እንዳትሞቺ ስምሽን ስጪ ተናገሪ" አላት። የከበረች ኢየሉጣም "የኔ ስም ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞት የሚሽረው በሰዎች ዘንድ የምጠራበትን ከፈለግህ ስሜ ኢየሉጣ ነው" ብላ መለሰችለት። መኰንኑም "ጽኑ የሆኑ ሥቃዮችን በላይሽ ሳያመጡ ተነሥተሽ መሥዋዕትን ለአማልክት አቅርቢ" አላት። የከበረች ኢየሉጣም "ዕውነት ነገርን ለመሥራት የምትሻ ከሆነ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነ ሕፃን ልጅ ይፈልጉ ዘንድ ወደ አገሩ መንደር ላክ ወዳንተም ያምጡትና የምንገዛለትንና የምናመልከውን እርሱ ይነገረን" አለችው።

ያን ጊዜም የሦስት ዓመት ልጅ ይፈልጉ ዘንድ መኰንኑ ወታደሮችን ላከ የአገር ሰዎችም ልጆቻቸውን ሠውረዋልና አላገኙም ከዚያም ከከተማው ቅጽር ውጭ በፀሐይ መውጫ ወዳለው በረሀ በኩል ወጡ የቅድስት ኢየሉጣንም ልጅ አገኙት ይህ ሕፃን "የስንት ዓመት ልጅ ነው" ብለው ስለርሱ ጠየቁ ሰዎችም "ይህ ሕፃን የሦስት ዓመት ሲሆን የክርስቲያናዊት መበለት ልጅ ነው" አሏቸው። ያንንም ሕፃን ይዘው ወደ መኰንኑ ወሰዱት መኰንኑም መልኩ የሚያምርና ደም ግባት ያለው እንደሆነ በአየ ጊዜ "ደስ የምትል ደስተኛ ሕፃን ሰላምታ ይገባሃል" አለው። ሕፃኑም "እኔን ደስተኛ ማለትህ መልካም ተናገርክ ላንተ ግን ደስታ የለህም እግዚአብሔር ለዝንጉዎች ደስታ የላቸውም ብሏልና ብሎ መለሰለት መኰንኑም ሕፃኑን "ሳልጠይቅህ ይህን ያህል ትመልስልኛለህን" አለው። ሕፃኑም "ገና ከዚህ የሚበዛ ነገርን እመልስልሃለሁ" አለው።

መኰንኑም "ስምኽ ማነው” ብሎ በጠየቀው ጊዜ "ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ሕፃን ስሜ ክርስቲያን መባል ነው" ብሎ መለሰለት። መኰንኑም "ዳግመኛ እንዳትሞት ስምህን ንገረኝ" አለው የከበረ ሕፃንም "ስሜ ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞክሼ ስም የምትሻ ከሆነ እናቴ የሰየመችኝ ቂርቆስ ነው" በማለት መለሰለት፡፡ መኰንኑም ሕፃን ቂርቆስን "እሺ በለኝና እሾምሃለሁ በብዙ ወርቅና ብርም አከብርሃለሁ" አለው። ሕፃኑም "የሰይጣ መልእክተኛ ለዕውነትም ጠላቷ የሆንክ ከእኔ ራቅ" አለው። መኰንኑም ሰምቶ ተቆጣ ደሙ እንደ ውኃ እስከሚፈስ ቆዳውን እንዲጨምቁትና እንዲግፉት አዘዘ። የከበረች ኢየሉጣሜ የልጅዋን ትዕግሥት በአየች ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነችው።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ "ጨውና ሰናፍጭ አምጡ አለ። የሁለቱንም አፍንጮቻቸውን ከፍተው ያንን ጨውና ሰናፍጭ እንዲጨምሩባቸው አዘዘ ያን ጊዜ ሕፃኑ "ትእዛዝህ ለጒረሮዬ ጣፋጭ ሆነ ከማርና ከስኳርም ለአፌ ጣመኝ" ብሎ ጮኸ። ሁለተኛም መኰንኑ እንዲህ ብሎ አዘዘ የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች አምጡ ሰባቱን በእናቱ አካላት ውስጥ ጨምሩ በሕፃኑም ሁለት ጆሮዎቹ ሁለት በዐይኖቹ ሁለት በአፉና በአፍንጫው አንድ በልቡ ጨምሩ እንዲህ ሲጨመርበት ጆሮዎቹ እንዲአሩ ዐይኖቹም ይጠፋ ዘንድ አንደበቱም ይቃጠል ዘንድ ወደ ልቡም ጽኑ ሕማም ገብቶ እርሱ ከዚህ ዓለም በሞት እንዲለይ ለእናቱም እንዲሁ አድርጉ ችንካሮችም በቅዱሳኑ በሥጋቸው ሁሉ ተጨመሩ። የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ትእዛዝ የብረቶቹ ግለት ጠፍቶ እንደ በረዶ ቀዘቀዘ ጤነኞችም ሆኑ መኰንኑም "ወደ ወህኒ ወስዳችሁ በዚያ አሥራችሁ ዝጉባቸው" አለ።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ "የሥቃይ መሣሪያን ይሠራ ዘንድ እንዳዝዘው ብረትን የሚያቀልጥ ሰው አምጡልኝ" አለ። በአመጡለትም ጊዜ ሰይጣን ወደ መኰንኑ ልብ ገብቶ አንደበቱን ዘጋውና መናገር ተሳነው ሕፃኑ ፈጥኖ አክሊልን ለመቀበል እንደሚተጋ ሰይጣን ስለ አወቀ ስለዚህ ዘጋው።

ከዚህም በኋላ ሕፃኑ ሠራተኛውን ጠርቶ "እኔንና እናቴን የሚያሠቃዩ በትን የሥቃይ መሣሪያ መሥራት ትችላለህ ይህ መኰንን ግን ምንም የሚያውቀው ነገር የለም" አለው። ሠራተኛውም እንደምትሻው በል ንገረኝ እምታዝዘኝ እኔ መሥራት እችላለሁ" አለው። ሕፃኑም ቅዱስ ቂርቆስ እያዘዘው...። ብረት ሠሪውም ሰምቶ እጅግ አደነቀ የሚረዱትንም ከአገር ውስጥ መቶ ሠራተኞችን ሰብስቦ መሥራት ጀምረ በአርባ ቀንም ጨረሰ።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ እለእሰሰክድሮስ ቂርቆስንና እናቱን ወደ አደባባይ ያመጡአቸው ዘንድ አዘዘ ያን ጊዜ አንደበቱ ተፈትቶ ነበርና እንዲህ አለ "ሕፃኑንና እናቱን ከቆዳቸው ጋር ራሳቸውን ላጩአቸውና በላያቸው የእሳት ፍሞችን ጨምሩ እርር ብለው እንዲቃጠሉ ዳግመኛም አራት ችንካሮችን ከትከሻዎቹ እስከ ተረከዙ ድረስ እንዲተክሉበት አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ ሥቃዩን ከርሱ አራቀ። ዳግመኛም ከጥዋት እስከ ማታ ከሥቃይ መሣሪያዎች ውስጥ ጨምረው አዋሏቸው ግን ማሠቃየት ተሳናቸው።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

23 Jan, 02:15


ከዚህም በኋላ ከማምጠቂያው ውስጥ ጨምረው መገዙአቸውና አመድ እስከሆኑ ከቅባትና ከጨው ጋር በብረት ምጣድ ውስጥ ቆሉአቸው ጌታችንም አስነሥቶ አዳናቸው። ወደ መኰንኑም በገቡ ጊዜ እንዲህ አላቸው "በእውነት ከሙታን ተለይታችሁ የተነሣችሁ ከሆነ ይህ ጫማዬ በእግሬ ወጥቶ እንደ ቀድሞው ሕያው እንዲሆን አድርጉ ሕፃን ቂርቆስም በጸለየ ጊዜ ያ ጫማ ታላቅ በሬ ሆነ ከአንገቱም ፍየል ወጣ። በዚያንም ሰዓት ለዐሥራ አንድ ሽህ አራት ሰዎች በሬውንና ፍየሉን አርደው ምሳ እንዲአደርጉላቸው መኰንኑ አዘዘ እንዲህም አለ ይህ "በቅቷቸው ከጠገቡ ከዚህም ሌላ ምግብ ካልፈለጉ የተሠራው ሁሉ ዕውነተኛ ነዋሪ ነው"።

ከዚህም በኋላ አርደው ምሳ አደረጉላቸውና ከፍየሉ ሥጋ ስድስት እንቅብ ከበሬው ሥጋ አራት እንቅብ አተረፉ መኰንኑም የተረፈውን ሥጋ አይቶ ወደ ባሕር እንዲጥሉት አዘዘ። መኰንኑም ቢያፍር የሕፃኑን ምላስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ምላሱን መለሰለት ዳግመኛም በታላቅ ጋን ውኃ አፍልተው ሕፃን ቂርቆስንና እናቱን ኢየሉጣን ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ እናቱም አይታ ፈራች። ልጅዋም ወደ እግዚአብሔር በጸለየላት ጊዜ አምላካዊ ኃይልን አሳደረባትና ከልጅዋ ጋር ወደ ጋኑ ገባች። እንደ ውርጭም ቀዝቃዛ ሆነ ደግሞም በውስጡ መንኲራኵር ወዳለበት የብረት ምጣድ እንዲጨምሩአቸውና ሥጋቸው እስከሚቦጫጨቅ እንዲስቡአቸው አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም በሕይወት አወጣቸው።

መኰንኑም እነርሱን ማሸነፍ በተሳነው ጊዜ ቸብቸቧቸውን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ በዚያን ጊዜ ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወረደ ሕፃን ቅዱስ ቂርቆስንም "የምትሻውን ለምነኝ" አለው። ሕፃኑም "ሥጋዬ በምድር አይቀበር ስሜን ለሚጠራ መታሰቢያዬን ለሚያደርግ ቤተ ክርስቲያኔን ለሚሠራ የተጋድሎዬን መጽሐፍ ለሚጽፍና ለሚያጽፍ ወይም ለሚያነበው ለቤተ ክርስቲያኔ መባ ለሚያገባ በውስጧም ለሚጸልይ ለሁሉም ፍላጎታቸውን ስጣቸው ኃጢአታቸውንም ይቅር በል ስሜም በሚጠራበት በዚያች ቦታ የከብት ዕልቂት አይምጣ በሰውም ላይ አባር ቸነፈር በእህልም ላይ ድርቅ የውኃም ማነስ አይሁን"።

መድኃኒታችንም "የለመንከኝ ሁሉ አስጥሃለሁ አንተም በቀኜ ትኖራለህ ሥጋህንም ኤልያስ በዐረገበት ሠረገላ ውስጥ አኖራለሁ" አለው ሕፃን ቂርቆስ በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ ብሎት ጌታችንን አመሰገነው። ከዚህም በኋላ በሌሊቱ እኩሌታም ከእናቱ ጋር አንገቱን ተቆረጠ መድኃኒታችንም በማይጠፋ አክሊል ጋረደው ነፍሶቻቸውንም በታላቅ ክብር ከእርሱ ጋር አሳረገ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ቂርቂቆስና በእናቱ ቅድስት ኢየሉጣ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

                             
#ነቢዩ_ቅዱስ_አብድዩ፦ ይህም ነቢይ የሐናንያ ልጅ ነው በንጉሥ ኢዮሳፍጥም ዘመን ትንቢት ተናገረ እግዚአብሔርም ስለ ትንሣኤና ስለ ፍርድ ቀን በቃሉ ነገረው። ሁለተኛም ከእስራኤል ልጆች የሚሆነውን ከአሕዛብም ለቀሩት አጸናቸው አብዝቶ መከራቸውም ገሠጻቸውም።

ይህም ንጉሥ አካዝያስ ይጠሩት ዘንድ ወደ ኤልያስ ከላከቸው ሦስተኛ መስፍን ነው ከእርሱ አስቀድመው የመጡ እነዚያን ሁለት መስፍኖች በኤልያስ ቃል አሳት ከሰማይ ወርዳ ከእነርሳቸው ጋር ካሉ ወታደሮች ጋር በላቻቸው። ይህ ግን ወደ ኤልያስ በመጣ ጊዜ በፊቱ ተንበርክኮ ሰግዶ ተገዛለት እንዲህም አለው "የእግዚአብሔር ሰው ተገዛሁልህ የእሊህ የባሮችህ ሰውነትና የኔ ሰውነት በፊትህ ትክበር" በእግዚአብሔር ነቢይ ላይ ፈጽሞ አልታበየምና ነቢዩ ኤልያስም ራራለት ወርዶም ከርሱ ጋር ወደ ንጉሡ ሔደ።

ይህም አብድዩ ከምድራዊ ንጉሥ አገልግሎት የኤልያስ አገልግሎት እንደምትበልጥ የኤልያስ አገልግሎት ለሰማያዊ ንጉሥ አገልግሎት ታደርሳለችና ይህን በልቡ ዐወቀ ስለዚህ ምድራውያን ነገሥታትን ማገልገል ትቶ ነቢዩ ኤልያስን ተከትሎ አገለገለው በላዩም ከእግዚአብሔር ሀብተ ትንቢት አደረበትና ትንቢትን የሚናገር ሆነ የትንቢቱም ወራት ሃያ ዓመት ነው ከጌታችን ሥጋዌ በፊት በዘጠኝ መቶ ዓመት በሰላም በፍቅር አንድነትም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ነቢያት ሁሉ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 15 ስንክሳር።
                                                    

                           
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም። ወከዐዉ ደሞሙ ከመ ማይ ዐውዳ ለኢየሩሳሌም። ወኃጥኡ ዘይቀብሮሙ። መዝ 78፥2-3።

                          
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "አኅለፍከነ ማእከለ እሳት ወማይ። ወአውጻእከነ ውስተ ዕረፍት። እበውእ ቤተከ ምስለ መባእየ"። መዝ 65፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 12፥1-11፣ 1ኛ ጴጥ 4፥11-15 እና የሐዋ ሥራ 16፥14-19። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ቂርቆስ የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

19 Jan, 20:02


“ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።”
ዮሐንስ 2፥11

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

19 Jan, 16:36


ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta):
"በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

             #ጥር ፲፪ (12) ቀን።

እንኳን #ለጌታችን_ለአምላካችን_ለመድኃኒታችን #ለኢየሱስ_ክርስቶስ ለንዑስ በዓል ለሆነው #በቃና_ዘገሊላ_በሠርግ_ቤት_ተገኝቶ_የመጀመርያውን_ተአምር_ላደረገበት መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል፣ #ለመላእክት_አለቃ_ለቅዱስ_ሚካኤል እስራኤል ወደ ተባለ #ቅዱስ_ያዕቆብ_ለተላከበት ከወንድሙ ከኤሳው ፈርቶ ሳለ ላዳነበት ለወራዊ በዓሉ፣ ለታላቁ ሰማዕት ለምሥራቅ ሰው ጽኑዕ ኃይለኛ ለሆነ #ለቅዱስ_ቴዎድሮስ_በናድሌዎስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍት በዓልና #ለቅዱስ_ይስሐቅም ልጅ #ለቅዱስ_ያዕቆብ_ለልደቱ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱስ_ቴዎድሮስ_ማኅበር_ለውንድዮስና_ኒቆሮስንና_ከሁለት_መቶ ኃምሳ _ሠራዊት_ሰማዕታት፣ #ከቅዱሳን_ከሰማዕቱ_ከየዩልያኖስና ከመነኵሴው #ከአባ_ዳንኤል ከመታሰቢያቸው፣ #ከቃሮስና_ከሰሚኖስ ከመታሰቢያቸው፣ #ከአባ_ነካሮ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።   

                            

                         
በዚችም ቀን #የክብር_ባለቤት_ጌታችንና_ፈጣሪያችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_የገሊላ_ክፍል_በሆነች_በቃና_በሠርግ_ቤት _ሠራው_የተአምራቱ_መታሰቢያ ይደረግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሠሩ። ቅዱስ ወንጌል እንደ ተናገረ ይህች የተአምራቱ መጀመሪያ ናት ውኃውን ለውጦ መዓዛው የሚጥም ጣፋጭ ወይን አድርጎታልና።

በዚህም አሳዳሪው ምስክር ሆነ ሙሽራውን በጠራው ጊዜ "ሰው ሁሉ መልካሙን ጠጅ አስቀድሞ ያጠጣል ከሰከሩም በኋኋ ዝቅተኛውን ያጠጣል። አንተ ግን የተሻለውን ጠጅ ወደ ኋላ አቆይተህ አጠጣህ" አለው። ጌትነቱንም ገለጠ ደቀ መዛሙርቱም አመኑበት። ለርሱም ከቸር አባቱ መሐሪና ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።                     
                                  

                           
በዚች ቀን #የከበረ_መልአክ_የመላእክት_አለቃ #የቅዱስ_ሚካኤል_የበዓሉ_መታሰቢያ_ነው በዚች ቀን #እስራኤል_ወደ_ተባለ_ያዕቆብ_እግዚአብሔር ልኮታልና ከወንድሙ ከኤሳወሰም ፈርቶ ሳለ አዳነው። ዮርዳኖስንም አሻግሮት ወደ እናቱ ወንድም ወደ ላባ ሔደ። እርሱም ሁለቱን ልጆቹን ልያና ራኄልን አጋባው ከዚህም በኋላ ከብዙ ገንዘብና ልጆቹ ጋር መንገዱን እየጠረገና እያቀና በሰላም በጤና ወደ አገሩ መለሰው ወንድሙ ኤሳውም በፍቅር በሰላም ተቀበለው ስለዚህም የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ሆነ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

                         

                          
#ቅዱስ_ቴዎድሮስ_በናድሌዎስ፦ ይህም ታላቅ ተጋዳይ ከአንጾኪያ አገር ሰዎች ከመንግሥት ወገን ነው። የአባቱ ስም ሲድራኮስ ይባላል ለንጉሥም የጭፍራ አለቃ ነው የእናቱም ስም በጥርቃ ይባላል ትርጓሜውም እመቤት ማለት ነው።

ንጉሥ ኑማርያኖስም በጦርነት ውስጥ በሞተ ጊዜ ልጁ ዮስጦስም በጦርነት ውስጥ ነበር መንግሥትም ያለ ንጉሥ ነበረች የቴዎድሮስ አባት ሲድራኮስና ፋሲለደስ ዲዮቅልጥያኖስ ነግሦ ሃይማኖቱን እስከ ካደ ድረስ የመንግሥቱን አስተዳደር ይመሩ ነበር። እርሱም ዲዮቅልጥያኖስ አስቀድሞ ከላይኛው ግብጽ የሆነ የዮስጦስ እኅት የንጉሥ ኑማርዮስ ልጅ ሚስት ሆነችውና አነገሠችው።

ቅዱስ ቴዎድሮስ በአደገ ጊዜ በጦርነት ውስጥ ፈጽሞ ኃይለኛ ሆነ እርሱ ቅዱስ ቴዎድሮስ በሚሔድበት ጦርነት ሁሉ ጠላቶቹን ድል አድርጎ ያሳድዳቸዋል የፋርስ ሰዎችም ቴዎድሮስ ወደ እናንተ መጣ ሲሏቸው ልባቸው ይሰበራል ይገዙለታልም ከእርሱም ወስጥ "ቴዎድሮስ የሮማውን አምላክ ነው" የሚሉ አሉ።

የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም በጦርነት ቦታ ቡናቢስ በሚባል ወንዝ አጠገብ ሳለ ስሙ ለውንድዮስ የሚባል ወዳጁም ሳለ ከዚህም በኋላ በአንዲት ሌሊት ራእይን አየ ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ መሰላል አለ። በላዩም ታላቅ ዙፋን ጌታችን ተቀምጧል በዙሪያውም የብዙ ብዙ አእላፍ መላእክት ያመሰግናሉ ከበታቹም ታላቅ ከይሲ ነበር በዙፋኑ ላይ የተቀመጠውም ቴዎድሮስም "አቤቱ አንተ ማነህ" አለ ጌታችንም "እኔ የአብ አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ ለአንተም ስለ ስሜ ደምህ ይፈስ ዘንድ አለህ" አለው። በዚያንም ጊዜ ከቆሙት አንዱ ወሰደውና በእሳት ባሕር ሦስት ጊዜ አጠመቀው ሁለመናውም በመንበሩ ዙሪያ እንደቆሙት ሆነ። ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ጌታችንን ከወዳጄ ከለውንድዮስ መለየት አልሻም" አለው። ጌታም እንዲህ ብሎ መለሰለት እርሱ ብቻ አይደለም ለቊዝ ሠራዊት መኰንን የሆነ ኒቆሮስም ነው እንጂ።

ከዚህም በኋላ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ አየ እነዚያ መላእክትም ለውንድዮስንና ኒቆሮስን አመጠቋቸው ከእሳት ባሕር ውስጥ አጠመቋቸውና እነርሱን ለቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሰጡት ከእንቅልፋም በነቃ ጊዜ ራእይን እንዳየ ለለውንድንስ ነገረው ፈጽሞ ደስ ብሏቸው እርስ በርሳቸው ተሳሳሙ።

ከዚህም በኋላ የቊዝ የሠራዊት አለቃ ኒቆሮስ ወዳለበት የእግዚአብሔር ኃይል ተሸከመቻቸው እርሱም በደስታ ተቀብሎ አስቀድሞ እንደሚያውቃቸው አቅፎ ሳማቸው እነርሱም እንዳዩት ያንን ራእይ ነገራቸው እጅግም አደነቁ ኒቆሮስም ቴዎድሮስ በናድሌዎስን "እኔንና ወንድሜ ለወንድዮስን ለአንተ በእጅህ እንደሰጡን ወንድሜ ሆይ ዕወቅ" አለው።

ከዚህም በኋላ በዚያን ጊዜ ወደ ሠራዊቶቻቸው መጡ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ ደማቸውን ሊአፈሱ ተስማሙ። ከንጉሠ ቊዝ እንዴት ዕርቅ እንዳደረገ ሊጠይቀው ያን ጊዜ ንጉሥ ወደ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ላከ ዲዮቅልጥያኖስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ክዶ ጣዖታትን በአመለከ ጊዜ ስለዚህ የቊዝ ሰዎች እጅግ ደስ ብሏቸወልና።

የከበረ ቴዎድሮስ በናድልዮስም ሠራዊቱን "ነፍሱን ከሰይፍ ሊያድን የሚወድ ወደ ፈለገው ይሒድ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ግን መጋደልን የሚሻ ከእኛ ጋር ይኑር" አላቸው። ሁሉም በታላቅ ድምፅ "አንተ የምትሞትበትን ሞት እኛ ካንተ ጋራ እንሞታለን አምላክህም አምላካችን ነው" ብለው ጮኹ የተመሰገነ ቴዎድሮስም ዳግመኛ "ነገራችሁ እውነት ከሆነ ሁላችሁም ወደዚህ ወንዝ ወርዳችሁ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሦስት ጊዜ ተጠመቁ" አላቸው።

በዚያንም ጊዜ ልብሳቸውን አውልቀው ወደ ወንዙ ወርደው ተጠመቁ ከውኃውም ሲወጡ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃልን ሰሙ "ምስክሮቼ በርቱ ጽኑ አሸናፊዎችም ሁኑ እኔ ከእንተ ጋር እኖራለሁና"። የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ወደ አንጾኪያ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ ጊዜ ሠራዊቱን ከከተማ ውጭ ትቶ ከሁለቱ ወዳጆቹ ከለውንድዮስና ከኒቆሮስ ጋር ገባ ንጉሥም በክብር ተቀብሎ  ስለ ጦርነት ወሬ ስለ ሠራዊቱም ጠየቀው እነርሱም የሆነውን ሁሉ ነገረው።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

19 Jan, 16:36


ከዚህም በኋላ ለአጵሎን ስለ መስገድ አወሳ የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ንጉሡን ገሠጸው ዘለፈውም እንዲሁም ወዳጆቹ ለውንድዮስና ኒቆሮስ ንጉሡን ረገሙት እርሱም ተቆጣ ለውንድዮስንና ኒቆሮስን ወደ ሚዶን አገር ወስደው በዚያ ያሠቃዩአቸው ዘንድ አዘዘ። ኒቆሮስን የፋርስ አገር የሠራዊት አለቃ መኰንን ስለነበረ ከፋርስ ሰዎች የተነሣ ዲዮቅልጥያኖስ ፈርቷልና በዚያም ለውንድዮስና ኒቆሮስን በአሠቃዩአቸው ጊዜ በዚች ቀን ጥር ዐሥራ ሁለት የሰማዕትነት አክሊል ተቀበሉ።

የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎን ግን ከሞል በሚባል ታላቅ እንጨት ላይ አስተኝተው ቊጥራቸው መቶ ኅምሳ ሦስት በሆነ በረጃጅም የብረት ችንካሮች እንዲቸነክሩት አዘዘ። እግዚአብሔርም መልአኩን ቅዱስ ሚካልን ወደርሱ ልኮ በመከራው ሁሉ አጸናው። በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸለትና "የመረጥኩ ቴዎድሮስ  ሆይ ሰላም ይሁንልህ ይህን ሁሉ መከራ ስለ ስሜ ታግሠሃልና ብፁዕ ነህ ይህን ከሀዲ ንጉሥ ታሳፍረው ዘንድ እሊህን ብረቶች ከሥጋህ ውስጥ አውጥቼ እንዳድንህ ትሻለህ" አለው። ቴዎድሮስ  በናድሌዎስ ጌታችንን "እንግዲህስ ስለ ከበረ ስምህ መሞት ይሻለኛል" አለው።

ሁለተኛም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ወዳጄ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሆይ እነሆ ሦስት አክሊላትን አዘጋጅቼልሃለሁ አንደኛው ስለ ድንግልናህ ሁለተኛው የዚህን ዓለም ክብር ትተህ መከራ ስለመቀበልህ ሦስተኛው ስለ ስሜ ደምህን ስለ አፈሰስክ ነው" አለው። "እኔም ቃል ኪዳንን ሰጠሁህ ስምህን ለሚጠራና መታሰቢያህን ለሚያደርግ በሁሉ ቦታ ከመከራው ሁሉ አድነው ዘንድ፤ ለድኆችም ምጽዋት የሰጠውን፤ ስለ አንተ በቤተ ክርስቲያንህንም የሠራውን ሁሉንም ኃጢአቱን ይቅር ብዬ መንግሥተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ"። ጌታችንም ይህን ቃል ኪዳን ከሰጠው በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ ቴዎድሮስም ሦስቱን አክሊሎች ሲሰጡት ሦስትን መላእክት አየ በዚያንም ጊዜ የከበረች ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ።

ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ከዐረፈ በኋላ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ለጣዖታት ያስግዱአቸው ዘንድ ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ ሠራዊት የጣዖታቱን ካህናት ላከ ሁሉተኛም ንጉሥን የሚወድ ለአማልክት ይስገድ እያለ የሚዞር ዓዋጅ ነጋሪ አዘዘ። የቴዎድሮስ በናድሌዎስ  ሠራዊትም "የነገሥታት ንጉሥ የጌቶች ጌታ ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም" ብለው ሁሉም ጮኹ ንጉሡም ሰምቶ ራሶቻቸውን በሰይፍ ይቆርጧቸው ዘንድ አዘዘ። ቊጥራቸውም ሁለት መቶ ኃምሳ እልፍ ሆነ ለሰማዕታት ራሶች ላይ አክሊልን የሚያኖሩ ብርሃናውያን መላክት አየሩን መሉት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስና በሰማዕታት ሁሉ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

                              
                           ✝️ ✝️ ✝️
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን። መዝ 83፥6-7። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 1፥1-12።

                           ✝️ ✝️ ✝️
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወምስካይነ አምላኩ ለያዕቆብ። ንዑ ትርአዩ ግብሮ ለእግዚአብሔር። ዘገብረ መንክረ በዲበ ምድር"። መዝ 45፥7-8። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 9፥1-17፣ ይሁ 1፥9-14 እና የሐዋ ሥራ 10፥34-39። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1፥44-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ኤጲፋንዮስ። መልካም የቃና ዘገሊላና የቅዱስ ሚካኤል በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።                                                  

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

18 Jan, 19:19


"በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

             #ጥር ፲፩ (11) ቀን።

እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ_ለብርሃነ_ጥምቀቱ_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከፋርስ አገር ሰዎች ወገን ከሆነ #ከከበረ_ቅዱስ_እንጣልዮስ በሰማዕትነት ከዐረፈ፣ #ከከበሩ_አዮስጦስና_ከፋይዮስ ዕረፍት፣ ከከበረ ተጋዳይ #ከአባ_ወቅሪስ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                          
                              
                            
በዚች ቀን #የክብር_ባለቤት_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ከአጥማቂው_ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘንድ_በዮርዳኖስ ወንዝ ውኃ ተጠመቀ። ይችም ዕለት በዮናኒ ቋንቋ ኤጲፋንያ ትባላለች ትርጓሜውም መለኮት የተገለጠበት ማለት ነው ልዩ የሆነች የሦስትነቱ ምሥጢር ገልጦባታልና አብ ከሰማይ ሁኖ የምወደው በርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት እያለ ሲመሰክር ወልድም በዮርዳኖስ ወንዝ ቁሞ ሳለ መንፈስ ቅዱስም በነጭ ርግብ አምሳል በወልድ ራስ ላይ ሲቀመጥ ይህ አጥማቂው ዮሐንስ እንደመሰከረ። እንዳህ ሲል "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠምቆ ከውኃ በወጣ ጊዜ ወዲያኑ ሰማይ ተከፈተ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በጌታችን ራስ ላይ ተቀምጠ ከሰማይም እንዲህ የሚል ቃል መጣ "ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ነው እርሱንም ስሙት"።

በዚች ዕለት ጌታችን ራሱን ገልጦአልና ከዚህ በፊት ሠላሳ ዓመት ያህል ራሱን አልገለጠም ነበር ግን በዚች ዕለት ለእስራኤል ልጆች ራሱን ገለጠ እነሆ "የእግዚአብሔር በግ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ" ብሎ መጥምቁ ዮሐንስ እንደገለጠው የከበረ ወንጌል ምስክር ሆነ። "እኔ አላውቅውም ነበር ነገር ግን እስራኤል ያውቁት ዘንድ በውኃ ላጠምቅ ስለዚህ መጣሁ" አለ።

በዚህም በዓል የእግዚአብሔር ልጅ የክርስቶስ የጌትነቱ ክብር ተገልጧል እርሱም የዓለሙን ሁሉ ኃጢአት ለማስወገድ የሚሠዋ የእግዚአብሔር አማናዊ በግ ነው። ስለዚህም ይህ በዓል በክርስቲያን ወገኖች ሁሉ ዘንድ የከበረና ከፍ ከፍ ያለ ሆነ በርሱም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጥምቀቱ በአበረው ውኃ ይነጹበታል የተቀበሉትንም ንጹሕና ጠብቀው ቢኖሩ በውስጡ የኃጢአታቸውን ሥርየት ያገኛሉ።

ስለዚህም ከክፉ ነገር ሁሉ ተጠብቀን የፈጠሪያችንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የቸርነቱን ብዛት ልመናመሰግን ይገባናል እርሱ ስለ እኛ ሰው ሁኖ ከኃጢአታችን አድኖናልና። ለእርሱም ከቸር አባቱ ሕይወት ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ክብር ምስጋና ስግደትም ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር11 ስንክሳር።

                          
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ባሕርኒ ርእየት ወጐየት። ወዮርዳኖስኒ ገብአ ድኅሬሁ። አድባር አንፈርዐፁ ከመ ሐራጊት። መዝ113፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ማቴ3፥13-ፍ.ም።

                           
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ርእዩከ ማያት እግዝኦ። ርእዩከ ማያት ወፈርሁ። ደንገፁ ቀላያተ ማያት ወደምፀ ማያቲሆሙ"። መዝ 76፥16። የሚነበቡት መልዕክታት ቲቶ 3፥4-8፣ 1ኛ 5፥5-13 እና የሐዋ ሥራ 10፥34-39። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 3፥21-38። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የብርሃነ ጥምቀቱ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።  

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

17 Jan, 16:44


"በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

             #ጥር ፲ (10) ቀን።

እንኳን #ለገሀድ (ጋድ) ጾመ፣ #ለከተራ_በዓልና #ለአባ_ታውብንጦ ለዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡ፦  #ከሰማዕት_ከጠምያኒ_ከኪናርያና #ከንግሥት_በጥሪቃ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
                            

                           
#በዚች_ዕለት_ምንም_ምን_መብልን_ሳይቀምሱ #ምእመናን_ሁሉ_እስከ_ምሽት_ይጾሙ ዘንድ ከእኛ አስቀድመው የነበሩ ታላላቅ ሊቃውንት የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሥርዓትን ሠሩ በምሽትም ቢሆን በታላቁ ጾም ከሚበላው በቀር ጥሉላትን እንዳይቀምሱ። በዚች ዕለት ምእመናን እስከ ምሽት እንደመጾሙን ያዘዙበት ምክንያቱ ይህ ነው የልደትና የጥምቀት በዓል በዓል በረቡዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን በበዓለ ኃምሳ የሚበላውን የጥሉላት መብል በጥዋት በመብላት ምእመናን ሁሉ በዓሉን እንዲአከብሩ የከበሩ አባቶቻችን ሐዋርያት አዝዘዋል እሊህ ሁለቱ የእግዚአብሔር ታላላቅ በዓላቶቹ ናቸውና።

እኛ በዚህ በኅላፊው ዓለም ተድላ ደስታ ደስ የሚለን ለሌሎች እንዳይመስላቸው እንደ አይሁድና እንደ አረማውያን በዓል በመብልና በመጠጥ ብቻ እንዳናደርግ ስለዚህ ከልደትና ከጥምቀት በዓል በዋዜማ ያሉትን ሁለቱን ዕለታት እንድንጾም አዘዙን የልደትና የጥምቀት በዓል በረቡዕና በዓርብ ላይ በሚሆን ጊዜ በረቡዕና በዓርብ ፈንታ እንድንጾማቸው ይገባልና በዚህም ሁለት ሥራ ይፈጸምልናል የጾም ሥራና የበዓል ማክበር ሥራ ነው። እንዲሁም በግብፃውያን አብያተ ክርስቲያን የተሠራ ነው።

በይረሙን በእሑድ ወይም በአይሁድ ሰንበት ቀን ቢሆን ይህም ጌታ የተገለጸበት ጥር ዐሥራ ቀን ነው በዋዜማው ዐርብ እስከ ምሽት ይጹሙ አስቀድመን እንደተናገርን ጥሉላት አይብሉ የልደትና የጥምቀት በዓልም ሰኞ ቀን ቢሆን በሰንበት ቀን ይጾም ዘንድ አይቻልም ነገር ግን ጥሉላትን ከመብላት ይጠበቁ።

በጥምቀትም ዕለት ከእኵለ ሌሊት በፊት ተነሥተው በውኃው ላይ ይጸልዩና ይጠመቁ ሕፃናትም በሚጠመቁ ጊዜ በውኃ እንዳይገድፉ ካህናቱም ከመንጋቱ በፊት ቀድሰው ቊርባኑን ያሳርጉ እጅግም ማልደው በጥዋት ከቤተ ክርስቲያን ይውጡ በከበረ ሥርዓታቸው ጌቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘዙ።

የመለካውያን ወገኖች ግን የልደትና የጥምቀት ዋዜማ በቅዳሜ ቀን ወይም በእሑድ ቀን ቢሆን በሦስት ሰዓት ይቀድሳሉ ከወደዱም የተባረከ ኅብስት ተመግበው ውኃ ይጠጣሉ ከዚህም በኋላ ካህናቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሁነው በየሰዓቱ በመጸለይ ለበዓሉ የሚገባውን የነቢያትን ትንቢቶች ያነባሉ በዚያች ቀን በምሽት ይኸውም ጥር ዐሥር ነው በውኃው ላይ ይጸልያሉ ይህም አባቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘዙት አልሆነም። እርሳቸው የኤጲፋንያን በዓል እንዲአክብሩ አዘዋል ይኸውም መድኃኒታችን የተገለጠበት ካኑን በሚባል በሮም ሁለተኛ ወር በሰባት ይህ ጥር ዐሥራ አንድ ቀን ነው።

መለካውያን ግን የከበሩ አባቶች የቤተ ክርስቲያን መምህራን ያዘዙትን ይተላለፋሉ በልደትና በጥምቀት በዓል ዓርብም ረብዕም ቢሆን አስቀድመው በርሱ ፈንታ ሳይጾሙ በጥዋት ተነሥተው ይበላሉና። እኛንም ከበደላችን ያነጻን ዘንድ በዮርዳኖስም ወንዝ እንደ ተገለጸ የጌትነቱን ክብር በልቡናችን ይገልጥልን ዘንድ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው ጌትነት ክብር ስግደት ለእርሱ ይገባልና ከቸር አባቱ ጋር ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን።

                             
#አባ_ታውብንጦስ፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ አባ ታኡና በሚባል በሮሜው ሊቀ ጳጳሳት ቤት አደገ እርሱም የምንኵስናን ልብስ አለበሰው። መንፈሳዊ ዕውቀትና ኃይል እንደተሰጠው አይቶ ከእስክንድርያ አገር ውጭ ስሙ ጤናዲራን በሚባል ቦታ ኤጲስቆጶስነት ሹሞ የገዳም አበ ምኔት አደረገው ከእርሱ ሥር ያሉ መነኰሳትም ሰባት መቶ ናቸው።

ከዚህም በኋላ ከእርሱ ጋር ላሉ መነኰሳት አለቃ የሆነ ኤጲስቆጶስ ታውብንጦስ ከከሀዲ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ስለሆነው ሁከት በሰማ ጊዜ ሸሽቶ ወደ ደብረ ሲሐት ገዳም ሒዶ እግዚአብሔርን ከምትፈራ ከአንዲት ድንግል ዘንድ ተቀመጠ። በእርሷ ቤትም ብዙ ዘመናት ኖረ በመጀመሪያ ወደርሷ በገባ ጊዜ ግን ንጉሡን ስለ መፍራት ጣዖትን ስታመልክ አገኛትና የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስን ወደ ማመን መለሳት።

ከዚያም ተርኑጥና መርኑስ ወደ ሚባሉ ገዳማት ሔደ የአብያተ ክርስቲያናትን ወሬ ይሰማ ዘንድ ፈልጎ በጾም በጸሎት ሌሊትም በመትጋት እያገለገለ በአንዲት ገዳም ውስጥ ሁለት ሦስት ቀን ተሠውሮ ያድር ነበር። የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ በላዩ እንዳደረ እግዚአብሔርም በእጆቹ ድንቆች ተአምራቶችን እንዳደረገ ከወንበዴዎችና ከዓመፀኞች ብዙዎችን መነኰሳትን አድርጎ ለክርስቶስ ወደ መገዛት እስከ መላሳቸው ድረስ መነኰሳቱ ሁሉ መሰከሩለት።

ከዚህም በኋላ ፈጽሞ በአረጀ ጊዜ የሚሞትበትን ቀን ዐወቀ ልጆቹንም የክርስቶስ በሆነች በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ ትእዛዙንም እንዲጠብቁ አስተማራቸው ወዲያውኑ ጥር10 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ታውብጦስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር10 ስንክሳር።

                          
"#ሰላም_እብል_ለጾመ_ዕለት_ዋሕድ። #ዘስሙ_ገሀድ። መምህራነ ሥርዓት አቀሙ ለዘይመጽእ ትውልድ። እመባልዕት ጥሉላት ወእምነ ቅሡም ማዕድ። አንስት ይትሀረማ ወይጹሙ ዕድ። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር_10።

                         
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ለበስኩ ሠቀ ወኮንክዎሙ ነገረ። ላዕሌየ ይዛውዑ እለ ይነብሩ ውስተ አናቅጽ። ወኪያየ የኀልዩ እለ ይሰትዩ ወይነ"። መዝ68፥11-12። የሚነበበው ወንጌል ማር 1፥1-9።

                         
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ሣህል ወርትዕ ተራከባ። ጽድቅ ወሰላም ተሰዐማ። ርትዕሰ እምድር ሠረፀት"። መዝ 84፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 3፥20-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 4፥14-18 እና የሐዋ ሥራ 13፥24-30። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 3፥1-13። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የጾም ቀንና የከተራ በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

14 Jan, 18:59


"በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

                 #ጥር ፯ (7) ቀን።

እንኳን #ለአጋዕዝተ_ዓለም_ለቅድስት_ሥላሴ የሰናዖር (የባቢሎንን) ቋንቋቸው ለደባለቁበትና የሠሩት ግንብ ላፈረሱበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል (ታሪኩ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ዘፍ11፥1-9)፣ ታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስን የክርስትና ጥምቀት ላጠመቀው ለሮሜ አገር ሊቀ ጳጳስ ለከበረ አባት #ለአቡነ_ሶል_ጴጥሮስ ለዕረፍት በዓልና ለታላቁ አባት #ለቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ ለመታሰቢያው  በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከሰሎሞን፣ #ከጎርጎርዮስ_ከማርቆስ_ከአትያኖስ_ከሉያ፣ #ከመልይን_ከሱስዮስና_ከማርትይ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
                                                  
                            
#የሮሜ_አገር_ሊቀ_ጳጳስ_አባ_ሶል_ጴጥሮስ፦ ይህንንም አባት ስለ ተጋድሎው ገናናነት ስለ አገልግሎቱም ስለ ትሩፋቱ ስለ አዋቂነቱና ስለ ደግነቱ ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ መልጥያኖስ ከዐረፈ በኋላ መርጠው ሊቀ ጵጵስና በሮሜ አገር ላይ ሾሙት። በሐዋርያት አለቃ በጴጥሮስ ወንበር በተቀመጠ ጊዜ የዕሊኒ ልጅ የሆነ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስን የክርስትና ጥምቀትን አጠመቀው ከከሀድያን ጋር ስለሚያደርገው ጦርነት ምክንያት ገና አልተጠመቀም ነበርና የጣዖታትንም ቤቶች አፍርሶ የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት ሠራላቸው።

የዚህም አባት ሶል ጴጥሮስ ገድሉ እጅግ ብሩህ የሆነ ነው እርሱ ሁል ጊዜ ሕዝቡን ያስተምራቸዋልና ከልቡናቸውም ከሰይጣን የሆነ ጥርጥርንና ክፉ ሐሳብን ያርቃል። ከእነርሳቸው ሥውር የሆነውንም የመጻሕፍት ምሥጢር ተርጒሞ ያስገነዘባቸው። አይሁድንና ዮናናውያንን ሁል ጊዜ ይከራከራቸው ነበር ከእርሳቸውም ብዙዎችን መልሶ ወደ ቀናች ሃይማኖት አስገባቸው የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው ስሙም በምእመናን ዘንድ ፈጽሞ የሚያስፈራ ሆነ። እግዚአብሔርን ስለ ማወቅና ስለ ወልደ እግዚአብሔር ሰው መሆን ብዙ ድርሳናትን ደረሰ።

በተሾመ በሰባተኛውም ዓመት ስለ አርዮስ በኒቅያ ከተማ ሃይማኖታቸው የቀና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት የከበሩ አባቶች የአንድነት ስብሰባ ሆነ ይህም አባት ሶል ጴጥሮስ ከእርሳቸው አንዱ ነበር አርዮስንም ከተከታዮቹ ጋር ረገመው አውግዞም ለየው። በሹመቱም ዐሥራ አንድ ዓመት ኖረ መልካም ተጋድሎን ፈጽሞ እግዚአብሔርንም አገልግሎ ጥር7 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ሶል ጴጥሮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር7 ስንክሳር።
                           

                         
"#ሰላም_ለከ_ጴጥሮስ_ሶል። መጥምቀ #ቈስጠንጢኖስ ንጉሥ ከሣቴ መስቀል። መዋዕለ ዕብሬትከ ኮነ ዕብሬተ ርትዕ ወሣህል። እስመ ተቀጥቀጠ ዳጎል ወወድቀ ቤል። በከመ ቀዳሜ ኢሳይያስ ይብል"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር_7።

                           
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ሣህሉ ለእግዚአብሔር መልአ ምድረ። ወበቃለ ለእግዚአብሔር ፀንዐ ሰማያት። ወእስትንፋሰ አፉሁ ኵሉ ኃይሎሙ"። መዝ 32፥5-6። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 28፥16-20።

                           
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቅ ዓረብ። ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ። ወኵሎ አሚረ ይድኅርዎ"። መዝ 71፥15። የሚነበቡት መልዕክታት ቈላ 2፥10-16፣ 1ኛ ዮሐ 2፥25-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 22፥7-22። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 2፥21-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የቅድስት ሥላሴ በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።  

      
                               

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

14 Jan, 09:54


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ስድስት በህዚች ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ ፈጸመ ልሳነ ዕፍረት ሐዋርያው ጳውሎስ ጌታ ክርስቶስ በሥጋው ግዝረትን ተቀበለ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ ብሎ እንደተናገረ።

ለብዙዎችም ጌታችን ወደ ቤተ ግዝረት እንዳልገባና እንዳልተገረዘ ይመስላቸው ነበር እነርሱ እንዳሰቡት ሁኖ ቢሆን ኑሮ አይሁድ ታላቅ ምክንያትን የሚያገኙ በሆኑ ነበር ጌታችን ግን የግዝረትን ሕግ ፈጸመ ለእኛ በግዝረት ፈንታ የክርስትና ጥምቀትን ሰጠን የፋሲካውንም ቂጣ በላ በእርሱም ፈንታ ሥጋውንና ደሙን ሰጠን።

የከበረ ወንጌል ስምንተኛው ቀን በተፈጸመ ጊዜም ሕፃኑን ሊገዝሩት ወሰዱት ሳትፀንሰው መልአኩ እንዳወጣለት ስሙን ኢየሱስ አሉት እንዳለ ንጽሕት ድንግል እመቤታችን ማርያም ጻድቅ አረጋዊ ዮሴፍን እንደ ሕጉ ልጄን እንዲገርዘውና ስሙንም እንድንሰይመው ብልህ የሆነ ገራዥ ሰው አምጣልኝ አለችው። ዮሴፍም ሔዶ የሚገርዝ ባለሙያ አመጣ ያ ባለሙያም ሕፃኑን ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በእናቱ በንጽሕት ድንግል ማርያም ክንድ ላይ አየው እንድገርዘው ሕፃኑን በጥንቃቄ ያዙት አላቸው።

ሕፃን ጌታ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው ባለሙያ ገራዥ ሆይ ደሜ ሳይፈስ ትገርዘኝ ዘንድ ትችላለህን በዚያች ዕለት ካልሆነ በቀር ደሜ አይፈስምና ጐኔን በጦር ሲወጉኝ ያን ጊዜ ውኃና ደም ይፈሳል ለአዳምና ለሚያምኑ ልጆቹ መድኃኒት ይሆናል።

የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ያ ባለሙያ በሰማ ጊዜ አደነቀ ዕቃውንም ሰብስቦ ተነሥቶ ከሕፃኑ ጌታ እግር በታች ሰገደ ያንጊዜም ምላጮቹ በእጆቹ ላይ ቀልጠው እንደ ውኃ ሆኑ የከበረች ድንግል እመቤታችንን ማርያምን ከሴቶች ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ የማሕፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው ይህ ልጅሽ ስለርሱ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት የሕያው አምላክ ልጅ ነው አላት።

ሕፃኑም ለዚያ ባለሙያ ዳግመኛ መልሶ እንዲህ አለው እኔ ነኝ ትገዝረኛለህን ወይስ ተውክ ወይም ያባቶቼ አባቶች እንዳደረጉ እኔ ላድርግ ያም ባለሙያ የአባቶችህ አባቶች እነማን ናቸው አለው ሕፃን ጌታችንም አብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብ የሕዝቡ ሁሉ አባቶች የሆኑ ናቸው ለእነርሱም ይህ ግዝረት አስቀድሞ ከአባቴ ዘንድ ተሰጣቸው ባለሙያውም እኔ ከአንተ ጋር እናገር ዘንድ አልችልም በአንተ ህልውና መንፈስ ቅዱስ አለና አለው።

በዚያንም ጊዜ ሕፃኑ ጌታችን ዐይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ አባት ሆይ ለአብርሃም ለይስሐቅ ለያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሃቸው ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ አለ። ያን ጊዜ ያለ ሰው እጅ በሕፃኑ ሥጋ ላይ ግዝረት ተገለጠች። ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማሕፀን እንደ መውጣቱ የጌታችን ግዝረቱ የማይመረመር ሆነ እንዲሁ ወደ ሐዋርያት በተዘጋ አዳራሽ መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እንዲሁ እንደ ፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ።

አዳምንና ልጆቹን ያድናቸው ዘንድ በፈቃዱ ከጐኑ በመስቀል ላይ የሚፈሰው ደምና ውኃ ካልሆነ በቀር ብዙም ሆነ ጥቂት ሊሆን አይችልም እርሱ በፈቃዱ ሕጉ እንዲፈጸም አስቀድሞ አዘዘ እንጂ።

ያም ባለሙያው ገራዥ ይህን ተአምር ባየ ጊዜ የሕፃኑንም ነገር በሰማ ጊዜ እጅግ አደነቀ የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግር በታች ሦስት ጊዜ ሰገደና በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ አለው። ከዚህም በኋላ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተአምራቱ ያየውንና የሰማውን እየተናገረ ወደ ቦታው ሔደ።

ለእርሱም ለጌታችን ከቸር አባቱ ጋራ ማሕየዊ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋራ ክብር ምስጋና ስግደትም ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን።

ከወርኀ ጥር ስንክሳር የተወሰደ

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

11 Jan, 19:15


"በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

             #ጥር ፬ (4) ቀን።

እንኳን #ለከበረና_ለተመሰገነ ለታላቁ #ለወንጌላዊው_ለአቡቀለምሲስ_ለቦኤኔርጌስ፣ #ለታኦሎጎስ_ለድንግላዊው_ለቊጹረ_ገጽ፣ #ለፍቊረ_እግዚእ_ለሐዋርያው_ለቅዱስ_ዮሐንስ_ወልደ_ነጐድጓድ_ለፍልሰቱ (ከሞት ለተሰወረበት) ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦# ከከበረ_ከጊዮርጊስ ከሊቀ ጳጳሳት #ከማርቴና_ከሰማዕት_ታኦድራ_ከአባ_ሊቃኖስና #ቀውስጦስ_ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                              
                            

                             
#ወንጌላዊው_ቅዱስ_ዮሐንስ፦ ለዚህም ቅዱስ ወደ እስያ አገር ይሔድ ዘንድ ዕጣው በወጣ ጊዜ እጅግ አዝኖ አለቀስ እነርሱ ክፉዎች ከሀዲዎች ልባቸው የደነደነ መሆናቸውን አውቋልና ግን ጌታችን ኃይልን መጽናናትን አግኝቶ ከደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስ ጋር ወጥቶ ወደ ክፍሉ ሔደ። ወደ ኤፌሶንም ሊሔድ ወዶ በመርከብ ላይ ተሳፈረ መርከቡም ተሰበረ እየአንዳንዱ በመርከብ ስባሪ ሠሌዳ ላይ ተንጠለጠለ ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስንም የባሕሩ ማዕበል ወደአንዲት ደሴት አደረው ቅዱስ ዮሐንስ ግን በባሕሩ ማዕበል መካከል አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ኖረ።

ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስ ወዳለበት ወደ የብስ ባሕሩ ተፋው ስለ መገናኘታቸውም እግዚአብሔርን አመሰገኑት በዚያን ጊዜም ተነሥተው ወደ ኤፌሶን ከተማ ገቡ ግን በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሰብኩ ዘንድ አልተቻላቸውም እነዚያ  ያገር ሰዎች እጅግ የከፉ ናቸውና። ስለዚህም ምክንያት ፈጥረው ዮሐንስ ሮምና ለምትባል ሴት የውሽባ ቤት እሳትን የሚያነድ ሆነ ረድኡ አብርኮሮስም አጣቢ ሆነ ያች ሴትም እጅግ ታሠቃያቸው ነበር መጻተኞችም ስለሆኑ ታጐሳቁላቸዋለች ትደበድባቸዋለች ትረግማቸዋለች ባሮቿም እንደሆኑ ጽፈውላታልና ከእርሷ ባሮች አደረገቻቸው በዚህ በታላቅ ጒስቊልና ውስጥ ኖሩ።

ከዚህም በኋላ በአንዲት ዕለት ይታጠብ ዘንድ የአገረ ገዥው ልጅ ገባ በዚያም የውሽባ ቤት ከተሠራ ጀምሮ የሰይጣን ኃይል አለ የመኰንኑም ልጅ አንቆ ገደለው በዚያንም ጊዜ የአገር ሰዎች ለዚያ ለሞተው ሊያለቅሱለት ተሰበሰቡ የከበረ ዮሐንስም እርሳቸው ጋር መጥቶ እንደ ሰው ሁሉ ሊያይ በዚያ ቆመ። ሮምናም በአየችው ጊዜ ረገመችው "አንተ በጌታዬ ልጅ ሞት ደስ ብሎህ ልትዝትብኝ መጣህ" አለችው ቅዱሱ ግን በቅንነት "አይዞሽ አትዘኝ" አላት ይህንንም ብሎ ወደ ሞተው ቀረብ ብሎ በመስቀል ምልክት አማተበበት በፊቱም ላይ እፍ አለበት። በዚያንም ጊዜ ያ የሞተው ድኖ ተነሣ የአገር ሰዎችም ደነገጡ ሮምናም "ወዮልኝ እግዚአብሔር የሚሉት አምላክ አንተ ነህን? አለች። እርሱም "አይደለሁም እኔ አገልጋይ ሐዋርያው ነኝ እንጂ" አላት በእነርሱ ላይ የሠራችውን በደል ሁሉ ይቅር ይሏት ዘንድ መሪር ልቅሶ በማልቀስ ሐዋርያትን ለመነቻቸው እነርሱም አረጋጓት አጽናኗትም።

ከአገሩም ሰዎች ብዙዎቹ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው በፊታቸውም ብዙዎች የሆኑ ድንቆች ተአምራትን አደረገ ይህንንም አይተው የአገሩ ሰዎች ሁሉም በጌታችን አመኑ። ከጣዖታቱ አገልጋዮች በቀር እነርሱም ሰይጣን በእርሱ ላይ ስለሚያነሣቸው ሊገድሉት ይሹ ነበር ነገር ግን ምርጦቹን እግዚአብሔር ጠበቃቸው። የከበረ ዮሐንስም ሁሉንም እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ እስከመለሳቸው ድረስ ታላቅ ድካምና ጭንቅ የሆነ መከራ ደረሰበት። የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ልቡናቸው ደንዳናነት ጣዖታትን ስለመውደዳቸውም ስለ እነርሱ መስክሮአል። እርሱም ቅዱስ ዮሐንስ በታላቅ ድካም ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው። ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶሳትን፣ ቀሳውስትን፣ ዲያቆናትን ሾመላቸው። ከዚህም በኋኋ ከእስያ በዙርያዋ ወዳሉ አገሮች ሁሉ ወጥቶ አስተማረ እግዚአብሔርንም ወደማወቅ መለሰላቸው።

ይህም የከበረ የተመሰገነ ቅዱስ ዮሐንስ በዚህ ዓለም ዘጠና ዓመት ኖረ እጅግም ሸመገለ ግን እንደ ባልጀሮቹ ሐዋርያት በሰይፍ ሞትን አልቀመሰም። ስለ ድንግልናውና ስለ ንጽሕናው ይህ ሆነ ሁሉም በክብር ይስተካከሉ ዘንድ እርሱም ወንጌልን ቀለምሲስ የሚባለውን ራእይ ሦስት መልክታትን የጻፈ ነው። ራት ሲበሉ በጌታ ኢየሱስ አጠገብ የተቀመጠውና "የሚያሲዝህ አቤቱ ማነው?" ያለው ይህ እርሱ ነው። ጌታችንም በተሰቀለ ጊዜ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር በመስቀሉ አጠገብ የቆመ እናቱንም "እነሆ ልጅሽ ያላት" እርሱን ደቀ መዝሙሩንም "እነኋት እናትህ" ያለው ነው።

ቅዱስ ጴጥሮስም እርሱን ሲከተለው በአየው ጊዜ ስርሱ ጌታ ኢየሱስን "አቤቱ ይህስ እንዴት ነው?" ብሎ የተናገረ ጌታ ኢየሱስም "እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ከወደድኩ አንተ ምን አለህ አንተ ግን ተከተለኝ ያለለት" ይህ ነው።

የተመሰገነ ቅዱስ ዮሐንስም ከዚህ ዓለም የሚወጣበት ሰዓት እንደ ቀረበ በአወቀ ጊዜ ሕዝቡን ጠራቸው ጸሎትንም ጸለየና ኅብስቱን ባርኮ ቆረሰ ይህም የጌታችን ሥጋውንና ደሙን ሰጣቸው በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አዘዛቸው ባረካቸው አጽናናቸውም።

ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስን ከወንድሞችም ሌሎች ሁለቱን መቆፈሪያ ይዘው ይከተሉት ዘንድ አዘዘ። ከኤፊሶንም ከተማ ወጭ ወጣ ጒድጓድ እንዲቆፍሩም አዘዘ ከውስጥዋም ወርዶ ቆመ ልብሱንም አስወገደ ከአንድ የበፍታ ቀሚስ በቀር አላስቀረም። እጆቹንም አንሥቶ ጸለየና ወደ ከተማ ይመለሱ ዘንድ አሰናበታቸው በክርስቶስም ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ለሕዝቡ ይነግሩአቸው ዘንድ አዘዛቸው በጎ ሥራዎችንም ይሠሩ ዘንድ ጌታችን ለሁሉም እንደ ሥራው ይከፍለው ዘንድ አለውና።

ሁለተኛም እንዲህ አላቸው "እኔ ከሁላችሁም ደም ንጹሕ ነኝ ከእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ ሳልነግራችሁ የተውኩት ምንም ምን የለምና እናንተም ከእንዲህ ከቶ ፊቶን አታዩኝም"። ይህንንም በተናገረ ጊዜ አለቀሱ እጆቹንና እግሮቹን ስመው በጒድጓዱ ውስጥ ትተውት ወደ መንደር ተመለሱና የሆነውን ሁሉ ለሰዎች ነገሩዋቸው ሁሉም ደንግጠው መጡ ግን ልብስና ጨማ እንጂ መቃብሩን አላገኙም እጅግም አደነቁ ደቀ መዝሙሩ ዮሐንስን በዚህ በጎ ዕረፍት ያሳረፈው እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ አባት በሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 4 ስንክሳር።

                           
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ"። ወእስከ አፅናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ18፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 4፥17-ፍ.ም።


                          
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወበኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አዕርክቲከ እግዚኦ። ወፈድፋደ ፀንዑ እምቀደምቶሙ። እኌልቆሙ እምኆፃ ይበዝኁ"። መዝ 138፥17-18። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 6፥1-11፣ 1ኛ ዮሐ 1፥1-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 4፥8-24። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 21፥20-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ነው። መልካም የሐዋርያው የቅዱስ ዮሐንስ የስዋሬ  በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
 

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

11 Jan, 17:02


" በትግራይ ክልል የምትገኙ የሃይማኖት አባቶች መበደላችሁን እናውቃለን ፣ በኀዘናችሁ ሰዓት አብረን መቆም ባለመቻላችን ማዘናችሁም እርግጥና ተገቢ ነው። ነገር ግን ሁሉም ነገር የሚካሰው በእርቅ ሲሆን እኛ የገፋነውን እርቅ ዓለም ሊቀበለው ስለማይችል፤ በእጃችንም የያዝነው መስቀለ ክርስቶስ የሰላም ዓርማ ነውና ልባችሁን ለሰላም፣ ለአንድነት እንድታዘጋጁ እንጠይቃለን " -  ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ  ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

@tikvahethiopia

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

08 Jan, 18:41


"በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

#የተባረከ_የጥር_ወር_የመዓልቱ_ሰዓት_ዐሥር ነው ከእንግዲህ ይጨመርለታል።

              #ጥር ፩ (1) ቀን።

እንኳን #ለሊቀ_ዲያቆናት_ለቀዳሜ_ሰማዕት #ለቅዱስ_እስጢፋኖስ_ለልደቱና_ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና #ከሶርያ_አገር_ለሆነ በከሀዲው መክስምኖስ ዘመነ መንግስት ሰማዕትነት ለተበቀበለ #ለቅዱስ_ለውንድዮስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክድርያ ስልሳ ዘጠነኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_መቃርስ ዕረፍት፣ #ከከበሩ_ከአክሚም_ሰማዕታት የምስክርነታቸውን ተጋድሎ ከፈጸሙ ስማቸው #ቅዱሳን_ዲዮስቆሮስና_ሰከላብዮስ ዕረፍት፣ በዲዮቅልጥያኖስ እጅ ሰማዕትነት ከተቀበሉ ቊጥራቸው #ከካህናት_ስምትት_መቶ፣ #ከዲያቆናት_መቶ_ሠላሳ_ከመምህራን_ኃምሳ፣ #ከሦስት_ከቤተ_ክርስቲያን_ሹማምንት_ከሰማንያ_መሳፍንት_ከሠላሳ_ሁለት_ንፍቅ_ዲያቆናትና_ከመቶ_ኃምሳ_ሕዝባውያን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

                              
                          
                         
#ቀዳሜ_ሰማዕታት_ቅዱስ_እስጢፋኖስ፦ ለዚህም ለከበረ እስጢፋኖስ እግዚአብሔር ኃይልን ጸጋ የተመላ ሰው እንደነበረና በሕዝቡም መካከል ታላላቅ ተአምራትንና ድንቅ ሥራን ይሠራ እንደነበረ የሐዋርያት ሥራ የተባለ መጽሐፍ ስለርሱ ምስክር ሆነ። ከዚህም በኋላ አይሁድ ቀኑበት የሐሰት ምስክሮች የሚሆኑ ሰዎችንም አስነሡበት "ይህን ሰው በሙሴና በእግዚአብሔር  ላይ የስድብ ቃልን ሲናገር ሰምተነዋል እንዲሉ ሐሰትን አስተማሩአቸው። ሕዝቡንና ሽማግሌዎችን ጸሐፊዎችንም አነሣሡአቸው አዳርሱን ብለው ከበው እየጐተቱ ወደ ሸንጎ ወሰዱት።

የሐሰት ምስክሮችንም አቆሙበት እነርሱ ይህ ሰው በቤተ መቅደስ ላይ በኦሪትም ላይ ስድብን ሲናገር ተው ብንለው እምቢ አለ። "የናዝሬቱ ኢየሱስ ቤተ መቅደሳችሁን ያፈርሰዋል ሙሴ የሰጣችሁን ኦሪታችሁንም ይሽራል" ሲል ሰምተነዋል አሉ። በአደባባይ ተቀምጠው የነበሩት ሁሉ ተመለከቱት ፊቱም የእግዚአብሔርን መልአክ ፊት ሁኖ አዩት። ሊቀ ካህናቱም "እውነት ነውና እንዲህ አልክ" አለው። እርሱም እንዲህ አለ "ወንድሞቻችንና አባቶቻችን ስሙ ወደ ካራን ከመምጣቱ አስቀድሞ በሶርያ ወንዞች መካከል ሳለ ለአባታችን ለአብርሃም የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ተገለጠለት። ካአገርህ ውጣ ከዘመዶችህም ተለይ እኔ ወደማሳይህ አገርም ና" አለው።

"ከዚህም በኋላ ከከላውዴዎን ወጥቶ በካራን ተቀመጠ አባቱም ከሞተ በኋላ ዛሬ እናንተ ወደ አላችሁባት ወደዚች አገር አመጣው። ከዚህም በኋላ የግዝረትን ሥርዓት ሰጠው ይስሐቅም በወለደው ጊዜ በስምንተኛው ቀን ገዘረው እንዲሁ ይስሐቅም ያዕቆብን ገዘረው ያዕቆብም ዐሥራ ሁለቱን ነገድ አባቶች ገዘረ። የቀድሙ አባቶቻችንም በዮሴፍ ላይ ቀንተው ወደ ግብጽ አገር ሸጡት እግዚአብሔር ግን አክብሮት ነበር። ከመከራው ሁሉ አዳነው በግብጽ ንጉሥ በፈርዖን ፊትም ዕውቀትን መወደድን ሰጠው በግብጽ አገር ሁሉና በቤቱ ሁሉ ላይ ሾመው"። ነገርም በማስረዘም በሰሎሞን እጅ እስከተሠራችው ቤተ መቅደስ ያለውን ተረከላቸው።

ከዚህም በኋላ ድምፁን ከፍ ከፍ አድርጎ "እናንተም እንደአባቶቻችሁ ዘወትር መንፈስ ቅዱስን የምታሳዝኑት ዐይነ ልቡናችሁ የታወረ ዕዝነ ልቡናችሁ የደነቈረ አንገተ ደንዳኖች" አላቸው። "አባቶቻችሁ ከነቢያት ያላሳደዱት ያልገደሉት ማን አለ እናንተ ክዳችሁ የገደላችሁትን ገደላችኋቸው። በመላእክት ሥርዓት ኦሪት ተቀብላችሁ አልጠበቃችሁም"።

ይህንንም ሰምተው ተበሳጩ ልባቸውም ተናደደ ተነሠሣ ጥርሳቸውንም አፋጩበት። በቅዱስ እስጢፋኖስም መንፈስ ቅዱስ አደረበት ሰማይም ተከፍቶ ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ የእግዚአብሔርን ክብር አየ። "እነሆ ሰማይ ተከፍቶ የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ አያለሁ" አለ።

ዶሮአቸውን ይዘው በታላቅ ድምፅ ጮኹ በአንድነትም ከበው ጐተቱት። እየጐተቱም ከከተማ ወደ ውጭ አውጥተው በደንጊያ ወግረው ገደሉት የገድሉትም ሰዎች ልብሳቸውን ሳውል ለሚባል ጐልማሳ ልጅ ያስጠብቁ ነበር። "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል" እያለ ሲጸልይ እስጢፋኖስን በደንጊያ ወገሩት።

ዘለፍለፍ ባለ ጊዜም ድምፁን ከፍ አድርጎ "አቤቱ ይህን ኃጢአታቸውን ይቅር በላቸው በደልም አታድርግባቸው" ይህንንም ብሎ ዐረፈ። ደጋግ ሰዎችም መጥተው የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ ወስደው ቀበሩት ታላቅ ልቅሶም አለቀሱለት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ሐዋርያና ሰማዕት በሆነ በቅዱስ እስጢፋኖስ  አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

                           
#ሰማዕቱ_ቅዱስ_ለውንድዮስ፦ የዚህም ቅዱስ ዜና እግዚአብሔርን የሚያመልክ ተጋዳይ እንደሆነ ንጉሥ መክስምያኖስ በሰማ ጊዜ ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሃይማኖቱንም ትቶ አማልክቶቹን ያመልክለት ዘንድ ብዙ ገንዘብ አቀረበለትና ይሸነግለው ጀመረ የከበረ ቅዱስ ለውንድዮስ ግን ዘበተበት ስጦታውንም  በማቃለል ክብሩን አጐሳቈለ የረከሱ አማልክቶቹንም ረገመ።

ያን ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ በመንኰራኵር ውስጥ ሰቅለው ጽኑዕ የሆነ ሥቃይን እንዲ አሠቃዩት አዘዘ። ንጉሥ እንዳዘዘ አደረጉበት የክብር ባለቤት ጌታችን ግን ያለ ጥፋት በጤና አወጣው። ዳግመኛም በብረት ዘንጎች ይደበድቡት ዘንድ ቅባትና ስብንም በታላቅ ድስት አፍልተው ቅዱስ ለውንድዮስን ከውስጡ ይጨምሩት ዘንድ አዘዘ ይህን ሁሉ ሥቃይንም አሠቃዩት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያጸናውና ያስታግሠው ያለ ጉዳትም በጤና ያስነሣው ነበር።

ማሠቃየቱንም በደከመው ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ከሥጋውም ድንቆች የሆኑ ብዙዎች ተአምራቶች ተገለጹ ዜናውም በሶርያ አገር ሁሉ ተሰማ አብያተ ክርስቲያናትና ገዳማት ተሠሩለት ከገዳማቱም በአንዲቱ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት የሆነው የከበረ ሳዊሮስ በሕፃንነቱ ተጠመቀባት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ለውንድዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

                          
#የከበሩ_የአክሚም_ሰማዕታት_ቅዱሳን_ዲዮስቆሮስና_ሰከላብዮስ፦ እክሚም በሚባል አገር ሹም የሆነ አንድ ሰው ነበር በወርቅ በብር ባለጸጋ ነው ስሙም አልሰመማልዮስ ይባላል ስማቸው ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ የሚባል ሁለት ልጆቹን ወለደ እነርሱም ከመጾምና ከመጸለይ ጋር እግዚአብሔርን በመፈራት አደጉ። አባታቸው በሞተ ጊዜ ምንኵስናን ተመኙ የእግዚአብሔርም መልአክ ተገልጦላቸው ወደ ገዳማዊ አባ ሙሴ ገዳም እንደመሔዱ አዘዛቸው ሒደውም በዚያ መነኰሱ ድንቆች ተአምራቶችንም እያደረጉ በብዙ ተጋድሎ ኖሩ። ከጥቂት ወራትም በኋላም ዲዮስቆሮስ ቅስና ሰከላብዮስም ዲቁና ተሾሙ። ዲዮቅልጥያኖስም የክብር ባለቤት ክርስቶስን በካደው ጊዜ ለጣዖታት የማይሰግዱ ክርስቲያኖችን ሁሉ ይገድል ዘንድ የእንዴናው ገዥ አርያኖስን አዘዘው።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

08 Jan, 18:41


አርያኖስም አክሚም ከተማ በደረሰ ጊዜ ኤጲስቆጶስን አባ ብኑድያኖስን ያዘውና አሥሮ ወደ አገር ውስጥ ገባ። የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤልም ለዲዮሰሰቆሮስና ለሰከላብዮስ ተገለጸላቸው ወደ መኰንኑም ሒደው የምስክርነት አክሊልን እንዲቀበሉ ነገራቸው እነርሱም ታኅሣሥ ሃያ ስምንት ቀን  ሃያ አራት መነኰሳት ሁነው ሔዱ። ወደ አክሚም ከተማም ሲደርሱ በመድኃኒታችን ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የከበረ የልደትን በዓል ለማክበርና ስለ ከበረ ስሙም ይሞቱ ዘንድ የክርስቲያን ወገኖችን ከሴቶቻቸውና ከልጆቻቸው ጋር ተሰብስበው አገኙአቸው ኤጲስቆጶሱ አባ ብኑድያኖስም ከእርሳቸው ጋር ገባ። በማግሥቱም አባ ብኑድያኖስ ቀደሰ አግዮስ ወደሚባለው በደረሰ ጊዜ መላእክት እንዲህ ብለው በታላቅ ድምጽ አመሰገኑ "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር አሸናፊ ፍጹም የጌትነትህ ምስጋና በሰማይና በምድር የመላ ነው"። ያን ጊዜ መድኃኒታችንን በመሠዊያው ታቦት ላይ ተቀምጦ መላእክትም በዙሪያው ቁመው ቊርባኑን እያነሣ በካህኑ እጅ ላይ በማድረግ የተሰበሰቡትን ሲያቆርባቸው ቅዱሳኑ አዩት።

በዚያንም ጊዜ መኰንኑ አርያኖስ ደረሰ ተቆጥቶም ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ስማቸው ብሕዋፋና ውኒን የሚባሉ ሁለት የአገር አለቆችን ይዞ ራሳቸውን በሰይፍ ቆረጠ ከእነርሱም በኋላ ዲያቆናትን ንፍቀ ዲያቆናትን መዘምራንን የቤተ ክርስቲያን ሹሞች ደማቸው ከቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ወጥቶ ሃያ ክንድ ያህል እስቲጎርፍ ሴቶችና ልጆችንም ሳያስቀር አረዳቸው።

ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶሱን አባ ብኑድያስን ዲዮስቆሮስን ሰከላብዮስን ከእርሳቸውም ጋር ያሉ መነኰሳትን ከእርሱ ጋር ወሰዳቸው ለጣዖትም ይሰግዱ ዘንድ ሸነገላቸው እምቢ በአሉትም ጊዜ ዐጥንቶቻቸው እስከሚለያዩ ድረስ ይደበድቧቸው ዘንድ አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጾላቸው አዳናቸው የአርያኖስም የጭፍሮቹ ታላላቆች ኮርዮንና ፊልሞና ከጭፍሮችም አርባ ሰዎች ይህን ድንቅ ተአምር አይተው በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ወደ እሳት ማንደጃም እንዲጥሏቸው አዘዘ። ተጋድሏቸውንም ታኅሣሥ ሠላሳ ቀን ፈጸሙ ከተሰበሰቡትም ውስጥ ብዙዎች የሚያስገድዳቸው ሳይኖር በእውነተኛ አምላክ በክርስቶስ እናምናለን እያሉ ወደ እሳቱ ማንደጃ ራሳቸውን ወረወሩ ምስክርነታቸውንም እንደዚህ ፈጸሙ።

ከዚህም በኋላ ጥር አንድ ቀን ቅዱሳን ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ ታሥረው ሳሉ የመላእክት አለቃ ቅዱሰሰ ሚካኤል ተገለጠላቸውና ምስክርነታቸውን እንደመፈጽሙ አበረታቸው በነጋም ጊዜ ለአማልክት ስለ መስገድ አርያኖስ ተናገራቸው አይሆንም በአሉትም ጊዜ የዲዮስቆሮስን ዐይኖቹን ያወልቁ ዘንድ አዘዘ ቅዱሱም የወለቁ ዐይኖቹን አንሥቶ ወደ ቦታቸው መለሳቸው መኰንኑ ሉክዮስ አይቶ ከሠራዊቱ ጋር በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ ወደ እሳትም ወርውረዋቸው ምስክርነታቸውንም ፈጸሙ።

ከዚህም በኋላ የከበሩ ሰማዕታትን ይገደሏቸው ዘንድ አርያኖስ አዘዘ ሲጸልዩም የክብር ባሌበት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠላቸው ስማቸውን ለሚጠረሠ መታሰቢያቸውንም ለሚያደርግ ገድላቸውንም ለሚጽፍ ከቅዱሳን አንድነት ይቈጥረው ዘንድ ቃል ኪዳን ሰጣቸው። ከዚህም በኋላ ወታደሩ ቀርቦ የቅዱስ ዲዮስቆሮስን ራሱ ቆረጠ ሰከላብዮስንም ከወገቡ ላይ ቆረጡት ሃያ አራቱን መንኰሳትም ከቁመታቸው ሠነጠቋቸው በዚች በጥር አንድ ቀን ተቆረጡ ከዘመዶቻቸው የሆነ ሳሙኤልም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በከበረች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቀበራቸው በአገረ አክሚም የተገደሉ ሰማዕታትም ቊጥራቸው ስምንት ሺህ አንድ መቶ አርባ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሁሉ ቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር1 ስንክሳር።

                        
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ። በ­ቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ78፥10-11። የሚነበበው ወንጌል ማር13፥9-23።

                           
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እስመ በጻሕኮ በበረከት ሠናይ። ወአንበረከ አክሊለ ዲበ ርእሱ ዘእምዕንቊ ክቡር። ሐይወ ሰአለከ ወወሀብኮ"። መዝ 20፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥32-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 7፥51-58። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 21፥33-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የብርሃነ ልደቱ ሰሞን፣ የቅዱስ እስጢፋኖስ የልደትና የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

07 Jan, 15:49


የአእላፋት ዝማሬ ለፓሪስ ኦሎምፒክ ጸያፍ ትርዒት ምላሽ ሠጠ
| ጃንደረባው ሚድያ | ታኅሣሥ 2017 |
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

የ2017 ዓ.ም. የአእላፋት ዝማሬ ላይ "የገና መልእክት ከኢትዮጵያውያ ሰዎች ወደ ኦሎምፒከኞች" (A Christmas Message from Myriads to Olympiads) በሚል ርእስ የሁለት ደቂቃ አኒሜሽን ታየ:: የዚህ መልእክትም ዋነኛ ሃሳብ ከአራት ወራት በፊት በፓሪስ ኦሎምፒክ መክፈቻ ላይ የጸሎተ ሐሙስ ሥዕል ላይ ጸያፍ መልእክቶችን በማስተላለፍ የተደረገውን ተሳልቆ ለጸሎተ ሐሙስ ሥዕልና ለከበረው የክርስቶስ ደም ክብር የምትሠጠው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ምን ያህል እንዳስቆጣ ለማሳየት ነው:: "እነርሱ በስሙ ሲዘብቱ ኢትዮጵያ ግን ዳግመኛ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች" (When they mock his name in vain, Ethiopia lifts her hands to God again) የሚል መልእክት ያለው ይህ ቪድዮ የፓሪስ ኦሎምፒክ አዘጋጆችን ድርጊት በክርስቶስ ላይ የጥላቻ ጦር ከሰበቀው ከንጉሥ ሔሮድስ ድርጊት ጋር በማመሳሰል የተሠራ መሆኑን የአኒሜሽኑ ዳይሬክተር ወ/ሪት ቅድስት ፍስሓ ገልጻለች::

"ዓለም አቀፍ መክፈቻ ሥነ ሥርዓቶችና ምርቃቶች በተካሔዱ ቁጥር በክርስትና መቀለድና ሰይጣናዊ ትርዒቶችን ማሳየት እየተለመደ መጥቶአል" ያሉት የአኒሜሽኑ ክሪኤቲቭ ዳይሬክተር ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ በበኩላቸው "ዓለም አቀፍ ሚድያዎች ከፍተኛ ሽፋን እየሠጡት ባለው በአእላፋት ዝማሬ ላይ ለዓለም አቀፉ ተመልካች የሚሆን መልእክት ለማስተላለፍ አጋጣሚውን ተጠቅመንበታል" ብለዋል::

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

04 Dec, 18:58


"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

           #ኅዳር ፳፮ (26) ቀን።

እንኳን #ለአገረ_ናግራን_ሰማዕታትና ለአባታቸው #ለቅዱስ_ኂሩት ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው መታሰቢያቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱስ_ቢላርያኖስ ከሚስቱ #ኪልቅያና_ከእኅቱ_ታቱስብያ በሰማዕትነት ከዐረፉ፣ ከደሴተ ሰንሲላ ኤጲስቆጶስ #ከአባ_ጎርጎርዮስ፣ #ከጌልዮስ_ከምክዋስና_ከማርልዮስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

                          
#የዕለቱ_እስመ_ለዓለም_ምሕረቱ፦ "ኦ ዓባይ ሀገር ሀገረ ናግራን ከዋክብትኪ ብሩሃን ወዕፀውኪ ፍሱሐን ወካህናትኪኒ ነባብያን ወዲያቆናትኪኒ ላእካን ወሕዝብኪኒ መሐይምናን እለ ተጠምቁ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን"። ትርጉም፦ ከፍ ያለች የናግራን ከተማ ሆይ ከዋክብቶችሽ ብሩሃን ናቸው ካህናቶችሽ የተማሩ ናቸው ዲያቆናቶሽም ተላላኪዎች ናቸው ሕዝቦችሽም አምነው በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተጠመቁ ናቸው። ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።

                         
#የአገረ_ናግራን_ሰማዕታት አባታቸውም #ቅዱስ_ኂሩት፦ ይህም ዮስጢኖስ ለቊስጥንጥንያ በነገሠ በአምስተኛው ዓመት ለኢየሩሳሌም አባ ዮሐንስ ለእስክንድርያ አባ ጢሞቴዎስ ለቊስንጥንጥንያም አባ ጢሞቴዎስ ለአንጾኪያ አባ አውፍራስዮስ ሊቃነ ጳጳሳት ሁነው ሳለ በኢትዮጵያም ጻድቁ ካሌብ ነግሦ ሳለ በዚያን ወራት ለአይሁድ ስሙ ፊንሐስ የሚባል አይሁዳዊ ነገሠ።

በመጀመርያ ግን ሳባ የተባለች አገር በኢትዮጵያ ነገሥታት እጅ ውስጥ ነበረች የሮም ነገሥታት አስባስያኖስና ጥጦስ ከኢየሩሳሌም አይሁድን በአሳደዷቸው ጊዜ ይቺን ሳባን አይሁድ ወረሷት። በውስጧም በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑ ብዙዎች ክርስቲያኖች በሚኖሩባት ታላቅ ከተማ አለች ይህም የተረገመ አይሁዳዊ ፊንሐስ ሊአጠፋት በመጣ ጊዜ የዚችን የከበረች አገር በመስቀል ምልክት በዙሪያዋ ያለ ቅጽርዋን በበሮቿና በግንብ አጥርዋ ላይ ያሉ ብዙ አርበኞች ሠራዊትን አይቶ በምንም ምክንያት ሊገባባት ስለአልተቻለው ተቆጣ። እግዚአብሔር አጽንቷታልና ነገር ግን በውጭ ያገኛቸውን ገበሬዎች ገደለ ታናናሾችንም ማርኮ ለባሮቹ ሰጣቸው።

ይህም ዲያብሎስን የሚመስለው አይሁዳዊ የኦሪትና የነቢያት ፈጣሪ በሆነ በእግዚአብሔር ስም እየማለ በተንኰል መልእክትን ላከ እንዲህም አላቸው "እኔ ከእናንተ ጋር ጠብ አልሻም ከአገር ሰው አንዱን እንኳ ማጥፋት አልፈልግም ነገር ግን የከተማዋን አሠራርዋን አደባባዮቿን ገበያዎቿን ማየት እሻለሁ" ለአገር ሰዎችም የተናገረው እውነት መስላቸው። የካዕቢ ልጅ አባት ኂሩት "ይህን አይሁዳዊ አትመኑት ሐሰተኛ ነውና ደጁንም አትክፈቱለት" አላቸው አባት ኂሩትንም አልሰሙትም ደጁንም ከፈቱለትና ሰዎች ገንዘባቸውን እንዲዘርፋአቸው አዘዘ። ሁለተኛም ነባልባሉ ወደ አየር እስቲደርስ እሳትን አንድደው የአገሪቱን ኤጲስቆጶስ አባ ጳውሎስን እንዲአመጡት አዘዘ እርሱ እንደ ሞተም በነገሩት ጊዜ ዐፅሙን ከመቃብር አውጥቶ አቃጠለው።

ከዚህም በኋላ ቀሳውስትን ዲያቆናትን መነኰሳትን፣ አንባቢዎችንና መዘምራኑን በቀንና በሌሊት መጻሕፍትን በማንበብ የሚተጉትን ሰበሰበ እነርሱንም ከእሳት ውስጥ ጨመራቸው ቊጥራቸው አራት ሺህ ሃያ ሰባት ነፍስ ሆነ ክርስቲያኖችን በዚህ ሊአስፈራራቸው አስቧልና። ዳግመኛም የብረት ዛንጅር በቅዱስ አባት ኂሩት አንገት ውስጥ እንዲአስገቡ እጆቹንና እግሮቹንም እንዲአሥሩት አዘዘ ታላላቆችንና የአገሩን መኳንንትንም እንዲአሥሩአቸው ክርስቶስን የማይክደው ሁሉ እንዲህ ተሠቃይቶ በክፋ አሟሟት ይሞታል የሚል ዐዋጅ ነጋሪ እየጮኸ በከተማው ውስጥ እንዲአዞቸው አዘዘ።

ቅዱሳን ክርስቲያን ወገኖች በሰሙ ጊዜ እንዲህ እያሉ ጮኹ "እኛ ያመንበትንና በስሙ የተጠመቅንበትን ክብር ይግባውና ክርስቶስን አንክደውም ይህ ርጉም አይሁዳዊም ሰምቶ ወንዶችና ሴቶችን ወጣቶችንና ሕፃናትን ሽማግሎችን ሁሉንም እንዲገድሉ አዘዘና ገደሉአቸው ቊራቸውም አራት ሺህ ሁለት መቶ ኃምሳ ሁለት ነፍስ ሆነ።

ከዚህም በኋላ የቅዱስ ኂሩትን ሚስት ቅድስት ድማህን ከሁለት ሴቶች ልጆቿ ጋር ያዟት እነርሱም በቤታቸው መስኮት ከሚገባው በቀር ፀሐይ ያልነካቸው ናቸው ደርሰውም በአይሁዳዊ ንጉሥ ፊት በቆሙ ጊዜ እርሱም ሃይማኖታቸውን ያስክዳቸው ዘንድ በብዙ ተንኮል ሊሸነግራቸው ጀመረ እምቢ ባሉትም ጊዜ የራሳቸውን መሸፈኛ እንዲገልጧቸው አዘዘ የአገር ሴቶችም እስከ ሚያለቅሱ ድረስ ከልጆቿም የምታንስ አንዲቱ ዕድሜዋ ዐሥራ ሁለት ዓመት የሆነ ከንጉሡ ፊት ላይ ምራቋን ተፋችበት። ወታደሩም አይቶ ሰይፋን መዝዞ አንገቷን ቆረጠ የእኅቷንም አንገት ቆረጠ። ድማህ የልጆቿን ደም እንዲአጠጧት አዘዘ እርሷም ቀምሳ "የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አመሰግንሃለሁ እንደቊርባን መሥዋዕት የሆነውን የልጆቼን ደም እኔ ባሪያህ እንድቀምስ አድርገሃልና" አለች። በዚያንም ጊዜ ርሷንም በሰይፍ አንገቷን እንዲቆርጡ ዳግመኛ አዘዘ ተጋድሎአቸውንም ፈጸሙ።

ከዚህም በኋላ ቅዱስ ኂሩትን ከአሥር ቤት እንዲአመጡት ንጉሥ አዘዘ ከርሱም ጋር አንድ ሺህ አርባ እሥረኞች ሰዎች አሉ ሃይማኖቱንም ይተው ዘንድ አስገደደው። ቅዱስ ኂሩትም ንጉሡን እንዲህ አለው "ክብር ይግባውና ጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን እያመለክሁት ስኖር ሰባ ስምንት ዓመት ሆነኝ እስከ አራት ትውልድ ለማየትም ደርሼአለሁ ዛሬም ስለ ከበረ ስሙ ምስክር ሁኜ ስሞት እጅግ ደስ ይለኛል። እኔኮ አስቀድሜ መሐላህን እንዳያምኑ ለወገኖቼ ነግሬአቸው ነበር አንተ ሐሰተኛ ነህና ነገር ግን ይህ ሁሉ በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው የሆነው ለዚህም ተጋድሎ ላደረሰኝ ለእርሱ ምስጋና ይሁን" ንጉሡም ይህን ሰምቶ ተቆጣ ወደ ወንዝም ወስደው በዚያ አንገቱን እንዲቆርጡት አዘዘ።

ቅዱስ አባት ኂሩትም በሰማ ጊዜ ደሰሰ አለው የሮምንና የኢትዮጵያን መንግሥት ያጸና ዘንድ የተረገመ አይሁዳዊውን መንግሥት ያጠፋ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ሕዝቡንም ባረካቸው። ከእርሳቸው ጋር በሰላምታ ተሰናበታቸው ከዚህም በኋላ የቅዱሳኑን ራሶቻቸውን ቆረጧቸው በዚያም የአምስት ዓመት ልጅ ያላት አንዲት ክርስቲያን ሴት ነበረች ከቅዱሳን ደም ወስዳ ተቀባች ልጅዋንም ቀባችው ወታደሮችም አይተው ከእሳት ጨመርዋት ልጅዋን ግን አይሁድ ወደእነርሱ ወስደው ወደ ንጉሥን አቀረቡት ንጉሡም "እኔን ትወዳለህ? ወይስ ክርስቶስ የሚሉትን?" አለው ሕፃኑም "እኔስ የእጁ ሥራ ነኝና ክርስቶስን እወደዋለሁ ይልቅስ ልቀቀኝ ወደ እናቴ ልሒድ" አለው በከለከለውም ጊዜ እግሩን ነከሰው አምልጦም ሩጦ ከእሳቱ ውስጥ ገባ። ሁለተኛም የዐሥር ወር ሕፃን እንደተሸከመች አንዲትን ሴት አመጧት እርሷም "ልጄ ሆይ ላዝንልህ አልቻልኩም" አለችው ያ ሕፃንም "እናቴ ሆይ በፍጥነት ወደ ዘላለም ሕይወት እንሒድ ይቺን እሳት ከዛሬ በቀር አናያትምና" አላት በዚያንም ጊዜ ከልጅዋ ጋር ወደ እሳት ውስጥ ተወረወረች።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

04 Dec, 18:58


የክርስቲያን ወገኖችም ይህን አይተው እኩሌቶቹ ወደ እሳት እኩሌቶቹም ወደ ሰይፍ ተቀዳደሙ የአይሁድ ጉባኤ ዕጹብ ዕጹብ ብለው እስኪያደንቁ ድረስ ከዚህም በኋላ እሳቱ በሰማይ ውስጥ መልቶ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ታየ። የአይሁድ ንጉሥ ፊንሐስም ወደአገሩ በሔደ ጊዜ ወደ ነገሥታቱ ሁሉ በኃይሉ እየተመካ ላከባቸው የሮሜ ንጉሥ ዮስጢኖስም ሰምቶ ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ ጢሞቴዎስ ላከ በአገረ ናግራን ለሚኖሩ የክርስቲያን ወገኖች ደማቸውን ይበቀል ዘንድ ለኢትዮጵያ ንጉሥ ለካሌብ መልእክት እንዲልክ ነው።

የኢትዮጵያ ንጉሥ ካሌብም መልእክት በደረሰው ጊዜ ፈጥኖ ተነሣ በዋሻ ከሚኖር ከአባ ጰንጠሌዎን በረከትን ተቀብሎ ከብዙ ሠራዊት ጋር በመርከቦች ተጭኖ ሔደ በደረሰም ጊዜ የሳባን ንጉሥ የፊንሐስን አገር አጠፋ ሰውም ሆነ እንስሳም ሆነ ሸሽቶ የሚያመልጥ እንኳ ምንም ምን ሳይቀር አጠፋቸው የናግራንን ከተማ ሕንፃዋን አደሰ የሰማዕታትንም መታሰቢያ አቆመ። ከዚህም በኋላ ወደ ሮሜ ንጉሥ ዮስጢኖስ ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጢሞቴዎስ የምሥራች ላከ እነርሱም ሰምተው እጅግ ደስ አላቸው እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ በናግራን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 26 ስንክሳር።

                             
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አድኅነኒ እግዚኦ እምፀርየ። ወአንግፈኒ እምእለ ቆሙ ላዕሌየ። ወባልሐኒ እምገበርተ ዐመፃ"። መዝ 58፥1-2። የሚነበበው ወንጌል  ሉቃ 21፥12-21

                             
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እስመ ተዘከረ ዘይትኃሠሥ ደሞሙ። ወኢረስዐ አውያቶሙ ለነዳያን። ተሣሃለኒ እግዚኦ ወርኢ ዘከመ የሐመኒ ጸላእትየ"። መዝ 9፥12-13 ወይም መዝ 115፥15-16። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 6፥1-12 ፣ 1ኛ ጴጥ 5፥7-9 እና የሐዋ ሥራ 20፥28-31። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 21፥12-21። የሚቀደሰው የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው። መልካም የአቡነ ሀብተ ማርያም፣ የአቡነ ኢየሱስ ሞዐ የዕረፍት በዓል፤ የአቡነ ሰላማ የልደት በዓል፣ የናግራ ሰማዕታት መታሰቢያ በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

02 Dec, 20:50


"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"

          #ኅዳር ፳፬ (24) ቀን።

እንኳን #ለኢትዮጵያኑ_ጻድቃን ለታላቁ አባት #ለሐዲስ_ሐዋርያ_ለአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ሃያ አምስተኛ ሆነው አብራው #ከሃያ_አራቱ_ካህናተ_ሰማይ_ጋር_የቅድስት_ሥላሴ_ዙፍን_ላጠኑበት በዓልና #ለአቡነ_ዜና_ማርቆስ #በቅዱስ_ማርቆስ_አብሳሪነት_ለተወለዱበት (ለልደታቸው) በዓላቸው በሰላም አደረሰን።

                              
#አቡነ_ተክለ_ሃይማኖትም_ከሃያ_አራቱ_ካህናተ_ሰማይ_ጋር_የቅድስት_ሥላሴን_መንበር_እንዳጠኑ፡- አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ መጥተው በሐይቁ ዳር ቆመው ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦላቸው ነው በእግሩ በውኃው ላይ እየሄደ እያሳያቸው ተከትለውት እንዲሄዱ የነገራቸው። አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትም መልአኩን ተከትለው ሐይቁን በእግራቸው ተራምደው ተሻግረው አቡነ ኢየሱስ ሞዐን አገኟቸው፡፡ እርሳቸውም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ እርሳቸው እየመጡ እንደሆነ በመንፈስ ዐውቀው ነበርና ሲያገኟቸው በጣም ተደስተው ከተቀበሏቸው በኋላ አመነኩሰዋቸዋል፡፡

ከዚህም በኋላ አባታችን በዚያው በሐይቅ በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ አክፍሎትንም በየሳምንቱ ያከፍላሉ፣ ከእሁድና ከቅዳሜ በቀር ምንም አይቀምሱም ነበር፡፡ በእነዚህም ዕለት የአጃ ቂጣ ወይም የዱር ቅጠል ይመጉ ነበር፡፡ ወዛቸው እንደ ውኃ ፈስሶ ምድሪቷን እስኪያርሳት ድረስ እስከ 70 ሺህ ስግደትንም በመስገድ ራሳቸውን እጅግ አደከሙ፡፡ በእነደዚህ ዓይነቱ ተጋድሎ ላይ ሳሉ ነው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ድንገት ነጥቆ ወስዶ ከሥሉስ ቅዱስ ዙፋን ፊት ያቆማቸው፡፡ ከዚህ በኋላ ስለሆነው ነገር ራሳቸው አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሲናገሩ "…ከዚህ በኋላ መልአኩ ወደ ሰማይ አውጥቶ ከመጋረጃው ውስጥ አስገብቶ ከሥላሴ ዙፋን ፊት አቆመኝና ሰገድኩለት፡፡ ከዚያ አስቀድሞ በማላውቀው በሌላ ምስጋና አመሰገንኩት፡፡ "ተክለ ሃይማኖት ክፍልህ ከ24ቱ ካህናቶቼ ጋር ይሁን" የሚል ቃል ከዙፋኑ ውስጥ ወጣ፡፡ የወርቅ ጽና አምጥተው ሰጡኝና ከእነርሱ ጋር አንድነት አጠንሁ፡፡ ምስጋናዬ ከምስጋናቸው ጋር ልብሴም እንደልብሳቸው ሆነ፡፡ ፈጣሪዬንም በሦስትነቱ ተገልጦ አየሁት፡፡ በጸሎትህ የሚታመን ሰው ሁሉ ስለአንተ ይድናል አለኝ….." ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ምዕራፍ 43።

                           
#አቡነ_ዜና_ማርቆስ_በወንጌላዊ_በቅዱስ_ማርቆስ ብሥራት_እንደተወለዱ፡- አባታችን ዜና ማርቆስ ሀገራቸው ጽላልሽ አውራጃ ምድረ ዞረሬ ሲሆን ትውልዳቸው ከነገደ ሌዊና ከእስራኤል ነገሥት ወገን ነው፡፡ ወላጆቻቸው ልጅ በማጣት ሲያዝኑ አንድ ዕለት ሐዋርያውና ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወደ እናታቸው ማርያም ዘመዳ ሌሊት መጥቶ "ገድሉና ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ የመላ ጻድቅ ልጅ እንደምትወልድ አበሠራት፡፡ ለአባቱ ለቀሲስ ዮሐንስም እንዲሁ ተገልጦለት "ሚስትህ ማርያም ዘመዳ የካቲት 24 ፀንሳ ኅዳር 24 ቀን ይኸውም በካህናተ ሰማይ በዓል ቀን ትወልዳለች፣ ስሙም ዜና ማርቆስ ይባላል" በማለት ብሥራቱን ነግሮታል፡፡

በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ብሥራት መሠረት አባታችን ዜና ማርቆስ በዚህች ዕለት ኅዳር 24 ቀን በተወለዱ ጊዜ ቅዱስ ዑራኤልና ቅዱስ ሩፋኤል የብርሃን ልብስ አልብሰው በክንፋቸው ሲጋርዱአቸው ለሰዎች ሁሉ ታይቷል፡፡ የአቡነ ሳሙኤል ዘወገግ አባት ቅዱስ እንድርያስና የአቡነ ተክለሃይማኖት አባት ቅዱስ ጸጋ ዘአብ እስኪደነቁ ድረስ ይህን በዓይናቸው ተመልክተዋል፡፡ ሁለቱ መላእክትም አቡነ ዜና ማርቆስን ከእናታቸው ዕቅፍ ወስደው ወደ ሐዋርያው ማርቆስ መቃብር ወስደው ለማርቆስና ለቅዱሳን ጳጳሳት አስባርከዋቸው መልሰው ለእናታቸው ሰጧቸው፣ እናታቸው ግን ይህን አታውቅም ነበር፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን በእግራቸው ቆመው "አንድ አምላክ ለሆኑ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ እሰግዳለሁ" ብለው ሦስት ጊዜ አምላካቸውን አመስግነው ሰግደዋል፡፡ ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።         

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

29 Nov, 20:59


"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

        #ኅዳር ፳፩ (21) ቀን።

እንኳን #ለእናታች_ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም_ታቦተ_ጽዮን የፊልስጥኤማውያን ጣዖት ዳጎንን ለሰባበረችበት (ታሪኩ በመጽሐፍ ቅዱስ # 1ኛሳሙ 5)፣ #ወደ_ኢትዮጵያ_ገብታ_አክሱም ለመጀመርያ ጊዜ ለከበረችበትና ታቦተ ጽዮን ከነበረችበት ድንኳን ወጥታ ማንም ካህን ሳይሸከማት #በተአምራት_አብርሃና_አጽብሓ ወዳሠሩላት ቤተ መቅደስ ራሷ በመንፈስ ቅዱስ ገብታ ለተገኘች ለዓመታዊ መታሰቢያ በዓልና ለኢትዮጽያዊው ጻድቅ #ለአቡነ_ተወልደ_መድኅን ለበዓላቸው መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሮሜ አገር ከሆነ ተአምራት ከሚያደርግ (ከገባሬ መንክራት) #ከቅዱስ_ጎርጎርዮስ ዕረፍት፣ ከእስክድርያ ሃምሳ አራተኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_ቆዝሞስ ዕረፍት ከእስሙናይ አገር ሰማዕታት #ከእልፍዮስ_ከዘኬዎስ_ከሮማኖስ፣_ከዮሐንስ፣ #ከፊቅጦርና_ይስሐቅ ከመታሰቢያቸው፣ ከብርሌና ከብርጭቆ ሠሪዎች ልጅ ከሆነ ከአስዩጥ ሀገር #ከቅዱስ_አባት_ከአባ_ዮሐንስ_ዕረፍትና፣ ጫብሬ ከምትባል ከአገር ድልበት #ከቅድስት_ዲቦራ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

                                                    
                             
በዚች ቀን #የእመቤታችን_የቅድስት_ድንግል_ማርያም_የበዓልዋ_መታሰቢ ነው። በጸሎቷ የሚገኝ በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።

                             
                           
#የሮሜ_አገር_የሆነ_ገባሬ_መንክራት #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት የቀናች ሃይማኖትንም ተምሮ እውነተኛ ክርስቲያን ሆነ። ከዚህም በኋላ የዚህን ዓለም ኃላፊነት የማታልፍ የመንግሥተ ሰማያትንም ኑሮ አሰበ ኀሳቡንም ሁሉ ስለ ነፍሱ ድኅነት አደረገ።

የዚያችም አገር ኤጲስቆጶስ በኤጲስቆጶስነት ሥራ ይረዳው ዘንድ ለመነው እርሱ ግን አልፈቀደም ከውዳሴ ከንቱ የሚሸሽ ሁኗልና ወደ ገዳምም ገብቶ ጽኑዕ የሆነ ተጋድሎንም መጋደል ጀመረ። የዚችም አገር ኤጲስቆጶስ በዐረፈ ጊዜ ኤጲስቆጶስ የሚያደርጉት ፈልገው አጡ ስለዚህም ተሰብስበው ሳሉ የመለኮትንም ነገር የሚናገር ጎርጎርዮስ ከእርሳቸው ጋር ሳለ ገዳማዊ ጎርጎርዮስን ፈልጋችሁ በእናንተ ላይ ሹሙት የሚል ቃል ከሰማይ ወደ እነርሱ መጣ። በበረሀም ውስጥ በፈለጉት ጊዜ አላገኙትም እየፈለጉትም ብዙ ቀን ኖሩ እርሱ ግን በአቅራቢያቸው ይኖር ነበር። ባላገኙትም ጊዜ በአንድ ምክር ተስማምተው በሌለበት ወንጌል ይዘው በላያቸው ኤጲስቆጶስነት ሾሙት ስሙንም የመለኮትን ነገር በሚናገር በጎርጎርዮስ ስም ጎርጎርዮስ ብለው ሰየሙት።

ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለቅዱስ ጎርጎርዮስ ተገልጦ "ተነሥተህ ወደ እነርሱ ሒድ እነሆ በላያቸው ኤጲስቆጶስነት ሹመውልሃልና ይህም ከእግዚአብሔር የሆነ ነው" አለው። ያን ጊዜም ወደ እነርሱ ወረደ የአምላክን ትእዛዝ መተላለፍ ፈርቷልና በአዩትም ጊዜ ወጥተው በታላቅ ክብር ተቀበሉት የሹመቱንም ሥርዓት ፈጸሙ። እግዚአብሔርም ቊጥር የሌላቸው ብዙዎች ተአምራትን በእጆቹ ገለጠ ስለዚህ ገባሬ መንክራት ጎርጎርዮስ ተብሎ ተጠራ።

ከብዙዎች ተአምራቱም አንዲቱ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ ከእርሷም ብዙ ዓሣዎችን የሚያጠምዱባት ታናሽ ባሕር ነበረቻቸው አንዱም አንዱ የኔ ናት በማለት እርስ በርሳቸው ተጣሉ ስለዚችም ባሕር በመካከላቸው ይፈርድ ዘንድ ወደ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ለመሔድ ተስማሙ እርሱም ከሁለት ተካፈሉ ብሎ አዘዛቸው እንዳዘዛቸውም ባልተስማሙ ጊዜ ስለዚች ባሕር እግዚአብሔርን ለመነው በዚያንም ጊዜ ባሕሪቱ ደርቃ የምትታረስ ምድር ሆነች ስለሚደረጉ ድንቆች ተአምራቴ ዜናው በሁሉ አገር ተሰማ በጎ አገልግሎቱንም ከፈጸመ በኋላ በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ቅዱስ አባት በገባሬ መክራት ጎርጎርዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

                            
#የብርሌና_የብልጭቆ_ሠሪዎች_ልጅ #አባ_ዮሐንስ፦ ይህንም ቅዱስ በወለዱት ጊዜ በበጎ ተግሣጽ አሳደገውታል የጥርብ ሥራንም አስተማሩት ከጥቂት ዘመናትም በኋላ አባቱና እናቱ ዐረፉ። ያን ጊዜ ወደ ቅዱስ ኢስድሮስና ወደ አባ ባይሞን ዘንድ ሒዶ መነኰሰ በጾምና በጸሎት በገድል ሁሉ ተጠምዶ ተጋደለ ዜናውም በራቀ ገዳማት ሁሉ ተሰማ።

ከዚህም በኋላ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጠለት ወደ አገሩ ሒዶ ወገኖቹን የጽድቅን ጎዳና ይመራቸው ዘንድ አዘዘው። ቅዱስ ቊርባንንም ሳይቀበል ከበዓቱ የማይወጣ ሆነ። በአንዲት ዕለትም ሁለት ቅዱሳን አረጋውያን አባ አብዢልና አባ ብሶይ ወደርሱ መጡ ገና ወደርሱ ሳይቀርቡ ከሩቅ ሳለ ስማቸውን በመጥራት ሳያውቃቸው አባቶቼ ለመምጣታችሁ ሰላምታ ይገባል ብሎ ተናገረ እጅግም አደነቁት አባ ሲኖዳም ከግብጽ አገር እየመጣ ብዙ ጊዜ ይጎበኘው ነበር።

የከዳተኞችም ጠብ በግብጽ አገር ላይ በተነሳ ጊዜ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ የላከው የጦር መኰንን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ መጣ። በጸሎቱም ይረዳው ዘንድ ለመነው ቅዱስ ዮሐንስም መስቀሉን አንሥቶ መኰንኑን "አይዞህ አትዘን አንተ ጠላቶችህን ድል ታደርጋለህና"፧ አለው እንደ ቃሉም ሆነ። ዳግመኛም በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ላይ ጠላት በተነሣበት ጊዜ ወደ ቅዱስ ዮሐንስ ላከ እርሱም "አትዘን ጠላትህን ታሸንፋለህ" አለው ያን ጊዜም ጠላቶቹን አሸነፈ።

ከዚህም በኋላ በእነዚያ ወራት ንጉሥ ቴዎዶስዮስ የርኵሰትን ሥራ ስለ ሠሩ የአስዩጥን ሰዎች እንዲገድላቸው ሀገራቸውንም እንዲአጠፉ አዘዘ። ንጉሡም የላከው መኰንን ሳይደርስ የእግዚአብሔር መልአክ ይህን ነገር ለአባ ዮሐንስ አሳወቀው የአገርም ሰዎች የንጉሡን ትእዛዝ በሰሙ ጊዜ ወደ አባ ዮሐንስ ገዳም ወጥተው ስለ መጥፋታቸው በፊቱ አለቀሱ አባ ዮሐንስም "አትጨነቁ አይዟችሁ እግዚአብሔር ያድናችኋላና" አላቸው። መኰንኑም በመጣ ጊዜ ከእርሱ በረከትን ይቀበል ዘንድ ወደ አባ ዮሐንስ ደረሰ አባ ዮሐንስም ንጉሡ ያዘወውን ሁሉ ነገረው መኰንኑም ሰምቶ ደነገጠ ለቅድስናውም ተገዢ ሆነ ለመኰንኑም ርኵስ መንፈስ ያደረበት የዐሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ነበረው ያድንለት ዘንድ ቅዱስ ዮሐንስን ለመነው በዚያንም ጊዜ ዘይትን ቀብቶ አዳነው።

ከዚህም በኋላ የአስዩጥ ሰዎችን መገደላቸውን እንዲተው ወደ ንጉሥ ይጽፍለት ዘንድ መኰንኑን አባ ዮሐንስ ለመነው መኰንኑም ጽፎ ለአባ ዮሐንስ ሰጠው አባ ዮሐንስም ተቀብሎ ወደ ዋሻው ገባ ወደ ጌታችንም ጸለየ ብርህት ደመናም መጣች ተሸክማም ወደ ንጉሡ አደሰገችው ያን ጊዜም ንጉሥ ከማዕድ ላይ ነበረ ያንንም ደብዳቤ ከወደላይ ጣለለት ንጉሡም አንሥቶ በአነበበው ጊዜ ከመኰንኑ የተጻፈ እንደሆነ በመካከላቸው በአለ ምልክት ተሸፎ አገኘው የተጻፈውም ቃሉ ስለ አባ ዮሐንስ ልመና ሀገሪቱን ማጥፋትን እንዲተው የሚል ነበር ቀና ባለ ጊዜም ደመና አየ ንጉሡም አደነቀ።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

29 Nov, 20:59


ከዚህም በኋላ አገሪቱን ማጥፋትን ስለ አባ ዮሐንስ ይተው ዘንድ መልሱን ለመኰንኑ ንጉሡ ጽፎ ደብዳቤዋን ወደ ደመናው ወረወራት የተሰበሰቡትም እያዩ እጅ ተቀበለችውና ወደ ደመናው ገባች ወዲያውኑ አባ ዮሐንስ በዚያች ደመና ወደበዓቱ ተመለሰና በማግሥቱ ያቺን ደብዳቤ ለመኰንኑ ሰጠው በላይዋም የንጉሡ ፊርማውና ማኅተሙ አለ በአያትና በአነበባት ጊዜ ደነገጠ አደነቀም ስለ አገሪቱ ድኅነትም እግዚአብሔርን እያመሰገነ ወደ አገሩ ተመለሰ። የንጉግሥ ዘመድ የሆነች የከበረች ሴት ዜናውን በሰማች ጊዜ ከደዌዋ ይፈውሳት ዘንድ ወደርሱ መጣች በጸሎቱም ተፈወሰች።

ከዚህም በኋላ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ በሞተ ጊዜ መናፍቁ መርቅያን ነገሠ። ቅዱስ አባ ዲዮስቆሮስንም አሠቃየው። የቀናች ሃይማኖትን ስለመለወጡ አባ ዮሐንስ እየዘለፈና እየረገመው ወደ ርሱ ደብዳቤ ላከ ከጥቂት ወራትም በኋላ እግዚአብሔር ቀሠፈው። ለእርሱም ዕድሜው መቶ ሃያ አምስት ዓመት ሲሆነው ዕረፍቱ እንደደረሰ አወቀ እየጸለየም ግምባሩን በምድር አስነክቶ ሰገደ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ ከመቃብሩም ቊጥር የሌላቸው ድንቆች የሆነ ብዙዎች ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 21 ስንክሳር።

                               

                            
"#ሰላም_ለኪ_ማርያም_እምነ። ዘሰመናይናኪ ጸወነ። ሶበ እምርኁቅ ርእየ ዘጽላሎትኪ ስነ። ለቢሶ ዳዊት ልብሰ ክብር ዘየሐይድ ዐይነ። ቅድመ ታቦተ ሕግ ኀለየ ወዓዲ ዘፈነ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የኅዳር _21።

                             
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ዕግትዋ ለጽዮን ወሕቀፍዋ። ወተናገሩ በውስተ ማኅፈዲሃ። ደዩ ልበክሙ ውስተ ኃይላ"።  መዝ 47፥12። የሚነበበው ወንጌል  ማቴ 23፥1-ፍ.ም።

                              
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እስመ ሐረያ እግዚአብሔር ለጽዮን። ወአብደራ ከመ ትኩኖ ማኅደሮ። ዛት ይዕቲ ምዕራፍየ ለዓለም"።  መዝ 131፥13-14። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 6፥12-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 2፥5-11 እና የሐዋ ሥራ 7፥44-59። የሚነበበው ወንጌል # ማቴ 21፥42-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የጽዮን ማርያም በዓልና የጾም ጊዜ ። ለሁላችንም ይሁንልን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

25 Nov, 19:57


"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

            #ኅዳር ፲፯ (17) ቀን።

እንኳን #ለዓለም_ሁሉ_መምህር ለቊስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳስ #ለቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ_ለሥጋው_ለፈለሰበት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቡሩክ #አብርሃምና_ከሚስቱ_ሐሪክ_ከወጺፍ_ጻድቃን ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


                         
#የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ_የሥጋው_ፍልሰት፦ ይህም እንዲህ ነው መበለቲቱን ቦታዋን በግፍ ነጥቃታለችና እርሱም እንድትመስላት ቢያዛት ስለአልሰማችው ስለ መበለቲቱ ቦታ ቅዱስ ዮሐንስ ንግሥት አውዶክስያን በአወገዛት ጊዜ በእርሱ ላይ ተቆጣች ሰይጣንም በልቧ አደረና ስለ ክፉ ሥራቸውና ስለ በደላቸው አውግዞ የለያቸውን ኤጲስቆጶሳት በእርሱ ላይ ሰበሰበች። እርሱንም ስለ መሰደዱ ከእርሷ ጋር ተስማምተው አድራኮስ ወደምትባል ደሴት አጋዘችው በዚያም ጥቂት ዓመታት ኑሮ ወደ መንበረ ሢመቱ ተመለሰ።

ከዚህም በኋላ ዳግመኛ መናፍቃን የሆነ ኤጲስ ቆጶሳትን ሰበሰበችና ወደ አርማንያ አጋዙት ከዚያም በረሀ ወደሆነ ሩቅ አገር ሰደዱትና በዚያ ዐረፈ። የአርቃዴዎስም ልጅ ታናሹ ቴዎዶስዮስ በነገሠ ጊዜ መልክተኞችን ልኮ የቅዱስ ዮሐንስን ሥጋ ብዙ በመዘመርና በማመስገን በታላቅ ክብር ወደ ቊስጥንጥንያ አፍልሶ አስመጣው ይህም ከዕረፍቱ በኋላበሠላሳ አምስት ዓመት ነው።

በሌላ በቅብጢ መጽሐፍ በግንቦት ወር ሃያ ሁለት ቀን እንደ ደረሰ ይነገራል በሮሜውያን መጽሐፍ ግን በየካቲት ወር ሃያ ሁለት ቀን ተባለ የዕንቊ ፈርጾች ባሉት የዕብነ በረድ ሳጥን ውስጥ አድርገው ወደ ቤተ መቅደስ አስገቡት ከሥጋውም ታላላቅ የሆነ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።

ሁለተኛም የእስክንድርያ ግጻዌና የአገረ ቅብጥ ኤጲስቆጶስ አባ ዮሐንስ የጻፈው ግጻዌ የመለካውያንም ግጻዌ በዚች በኅዳር ዐሥራ ሰባት ቀን ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንዳረፈባት ተባበሩ። ሁለተኛም ደግሞ የመለካውያን ግጻዌ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ዐይሉል በሚባል ወር በዐሥራ አራት እንዳረፈ ይናገራል ይህም በመድኃኒታችን በመስቀል በዓል መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን ነው። ስለዚህም ራሱን ለማሰሰቻል ወደ ኅዳር ዐሥራ ሰባት ቀን ለወጡት።

የቀደሙ መጻሕፍት ግን ዕረፍቱን ግንቦት ዐሥራ ሁለት ቀን እንደሆነ ያወሳሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ቅዱስ በከበረ አባት በዮሐንስ አወ ወርቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦የኅዳር 17 ስንክሳር።

                            
#የዕለቱ_ምስባክ፦ "እግዚአብሔር ያፈቅሮሙ ለጻድቃን። እግዚአብሔር የዐቅቦሙ ለፈላስያን። ወይትዌከፎሙ ለዕቤራት ወለእጓለ ማውታ"። መዝ 145፥8-9። የሚነበቡት መልዕክታት ፊሊ 1፥12-19፣ 1ኛ ጴጥ 2፥10-18 እና የሐዋ ሥራ 16፥14-25 የሚነበበው ወንጌል ማቴ10፥16- ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅድስት ወለተ ጴጥሮስና የአቡነ ሲኖዳ የዕረፍታቸው በዓልና የነቢያት (የገና) ጾም ጊዜና ለሁላችንም ይሁንልን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

20 Nov, 19:14


"በስመ አብ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

          #ኅዳር ፲፪ (12) ቀን።

እንኳን #ለሰው_ወገን_ለሚያዝንና_ለሚራራ በእግዚአብሔር ጌትነት ፊት ሁልጊዜ በመቆም ለፍጥረት ሁሉ ለሚማልድ #ለመላእክት_አለቃ_ለቅዱስ_ሚካኤል_እስራኤልን_ከግብፅ_ባርነት ሲወጡ ከሊቀ ነቢያት ሙሴ ጋር በሆነ ሕዝብ በመንዳቸው ሁሉ እየመራ የኤርትራ ባሕር ለከፈለበት፣ #ለነዌ_ልጅ_ለነቢዩ_ለቅዱስ_ኢያሱ ለተገለጠለት፣ #ዱራታዎስና_ሚስቱን_ቴዎብስታ_ለረዳበት_ዓመታዊ_በዓልና #ለኢትዮያዊው_ንጉሥ #ለጻድቁ_ለዐፄ_በእደ_ማርያም_ለዕረፍቱ መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከመጥምቀ_መለኮት_ቅዱስ_ዮሐንስ ራሱ በደብረ ማህው ከታየችበት፣ ከእስክድርያ ስልሳ ሦስተኛ ሊቀ ጳጳስ ከቅዱስ አባት #ከአባ_ፊላታዎስ ዕረፍት ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
                                                  

                             
በዚች ቀን #ለሰው_ወገን_የሚያዝንና_የሚራራ #በእግዚአብሔር_ጌትነት_ዙፋን_ፊት_ሁልጊዜ በመቆም #ለፍጥረቱ_ሁሉ_የሚማልድ_የመላእክት_አለቃ በሰማያትም ለሚኖሩ ኃይሎች ሁሉ አለቃቸው ለሆነ #ለቅዱስ_ሚካኤል_የበዓሉ መታሰቢያ ነው።

ይህም በንጉሥ ጭፍራ አምሳል በታላቅ ክብር ሁኖ የነዌ ልጅ ኢያሱ ያየው ነው "ከእኛ ሰዎች ወገን ነህን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ?" አለው። "እኔስ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ነኝ አሁንም ወዳንተ መጥቻለሁ" አለው። ኢያሱም ወደ ምድር በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደለትና "በእኔ በባሪያህ ዘንድ ምን አቁሞሃል?" አለው። የእግዚአብሔር የሠራዊቱም አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ኢያሱን "የቆምክባት ምድር የከበረች ቦታ ናትና ጫማህን ከእግርህ አውልቅ" አለው ኢያሱም  እንዳለው አደረገ። እግዚአብሔርም ኢያሱን እንዲህ አለው "በውስጧ ያለውን ንጉሷን ከኃያላኑና ከአርበኞቹ ጋር በእጃችሁ ኢያሪኮን እነሆ አስገባታለሁ"።

ይህም የከበረ መልአክ ከቅዱሳን ሰማዕታት ጋር በመሆን ገድላቸውን እስከ ሚፈጽሙ የሚያጽናቸውና የሚያስታግሣቸው ነው። ስለዚህም ስለ ልዕልናውና ስለ አማላጅነቱ በየወሩ በዐሥራ ሁለት ቀን ለመታሰቢያው በዓል ተሠራለት እርሱ ስለ እኛ የምድሩን ፍሬ ይባልክልን ዘንድ ዝናሙንም በጊዜው እንዲወርድልን የወንዙንም ውኃ እንዲመላልን ነፋሱንም የምሕረት ነፋስ እንዲአደርግልን ሁሉንም የተስተካከለ እንዲአደርግልን ወደ እግዚአብሔር በጸሎት ይማልድልናልና።

                           
#ቅዱስ_ሚካኤል_ያደረገው_ተአምር_ይህ_ነው፦ እንዲህም ሆነ እግዚአብሔር ወዳጅ የሆነ ስሙ ዱራታዎስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ የሚስቱም ስም ቴዎብስታ ነው እነርሱም ሁልጊዜ ያለ ማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢ ያደርጉ ነበር ከዚህም በኋላ በአገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ ለዚህም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉት አጡ ዱራታዎስም ሽጦ ለበዓሉ መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ የእርሱን ልብስና የሚስቱን ልብስ ይዞ ወጥቶ ሔደ። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም በታላቅ መኰንን አምሳል ለዱራታዎስ ተገለጠለት ወደ ባለ በጎች ሒዶ በእርሱ ዋስትና በአንድ ዲናር አንድ በግ እንዲወስድ ሁለተኛም ወደ ዓሣ አጥማጅ ሒዶ አንድ ዓሣ እንዲወስድ ግን መልአኩ ወደ ቤቱ ሳይደርስ የዓሣውን ሆድ እንዳይቀድ ወደ ባለ ሥንዴም እንዲሔድና የሚሻውን እንዲሁ በርሱ ዋስትና እንዲወስድ አዘዘው ዱራታዎስም ቅዱስ ሚካኤል እንዳዘዘው አደረገ። ወደ ቤቱም በተመለሰ ጊዜ በረከትን ሁሉ ቤቱ ተመልቶ አገኘው። እጅግም አደነቀ የዚህንም የከበረ መልአክ የበዓሉን መታሰቢያ እንዳስለመደ አደረገ። የተራቡ ድኆችን ሁሉንም ጠርቶ መገባቸውና ወደየቤታቸው አሰናበታቸው።

ከዚህም በኋላ ለዱራታዎስና ለሚስቱ ቅዱስ ሚካኤል ሁለተኛ ተገለጠላቸው። ዱራታዎስንም የዓሣውን ሆድ እንዲሠነጥቅ አዘዘው። በሠነጠቀውም ጊዜ ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር በዓሣው ሆድ ተገኘ። ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስንና ቴዎብስታን እንዲህ አላቸው "ከዚህ ዲናር ወስዳችሁ ለባለ በጉ ለባለ ዓሣውና ለባለ ሥንዴው ዕዳችሁን ክፈሉ የቀረውም ለፍላጎታችሁ ይሁናችሁ እግዚአብሔር አስቧችኋልና በጎ ሥራችሁን መሥዋዕታችሁንና ምጽዋታችሁን አስቦ በዚህ ዓለም አሳመረላችሁ። በኋለኛውም መንግሥተ ሰማያትን አዘጋጅቶላችኋል" አላቸው።

እነርሱም ሲሰሙ ስለዚህ ነገር ደነገጡ እርሱም "ከመከራችሁ ሁሉ ያዳንኳችሁ የመላእክት አለቃ እኔ ሚካኤል ነኝ መሥዋዕታችሁና ምጽዋታችሁን ወደ እግዚአብሔር ፊት ያሳረግሁ እኔ ነኝ አሁንም በዚህ ዓለም ከበጎ ነገር እንድታጡ አላደርጋችሁም" አላቸው። ይህንንም ብሎ ወደ ሰማያት ወጣ። እነርሱም ሰገዱለት ተአምራቱም የማይቈጠር ብዙ ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ መልአክ በቅዱስ ሚካኤል ጸሎትና አማላጅነት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

                            
#አባ_ፊላታዎስ፦ በእስክንድርያ ከተሾሙ ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ስልሳ ሦስተኛ ነው። በሹመቱ ወራት የኢትዮጵያ ንጉሥ ወደ ኖባ ንጉሥ ወደ ጊዮርጊስ እንዲህ ብሎ የመልክት ደብዳቤ ጻፈ "ወንድሜ ሆይ ከሊቀ ጳጳሳት ቆዝሞስ ጊዜ ጀምሮ ለረጅም ጊዜ ጳጳስ ስለ ሌለን እኛ በታላቅ ችግር ውስጥ እንዳለን ዕወቅ። ይህም የሆነው ተንኰለኛው ሚናስ በተንኰልና በሐሰት ነገር የከበረ ጳጳሳችንን ጴጥሮስን ከሹመቱ ወንበር እንዲሰደድ ስለ አደረገው ነው። ስለዚህ አምስት ጳጳሳት እስቲአልፉ ለአገራችን ጳጳስ አልተላከም። አሁንም ስለ እግዚአብሔር ብለህ ስለ ቀናች ሃይማኖትም በድካም ከእኛ ጋር አንድ በመሆን ስለእኛ ወደ ግብጽ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ቅዱስ ፊላታዎስ ጳጳስ ይልክልን ዘንድ ከራስህ ደብዳቤ እንድትጽፍለት እለምንሃለሁ" የሚል ነበር።

በዚያንም ጊዜ የኖባ ንጉሥ ጊዮርጊስ ለኢትዮጵያ አገር ጳጳስን ይሾምላቸው ዘንድ የልመና ደብዳቤ ወደ አባ ፊላታዎስ ጻፈ ይህ ቅዱስ ፊላታዎስም ልመናውን ተቀብሎ ከአስቄጥስ ገዳም ስሙ ዳንኤል የሚባል አንድ ጻድቅ መነኰስ አስመጣ እርሱን ጵጵስና ሹሞ ወደ ኢትዮጵያ አገር ላከው ወደ እነርሱም በደረሰ ጊዜ የኢትዮጵያ ሰዎች በታላቅ ደስታ ተቀበሉት። በዚህም አባት ፊላታዎስ ዘመን ብዙ ተአምራት ተገልጠዋል ኅዳር 12 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ፊላታዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 12 ስንክሳር።

                            

                          
#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እግዚኦ በኃይልከ ይትፌሣሕ ንጉሥ። ወብዙኀ ይትሐሠይ በአድኅኖትከ። ፍትወተ ነፍሱ ወሀብኮ"። መዝ 20፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ19፥11-28።

                           
#የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ዘነፈቃ ለባሕረ ኤርትራ ወከፈላ። እስመ ለዓለም ምሕረቱ። ወአውፆኦሙ ለእስራኤል እንተ ማዕከላ"። መዝ 135፥14-15 ወይም መዝ 33፥7-8። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 9፥17-24  ይሁ 1፥9-14 እና የሐዋ ሥራ 20፥28-31። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥15-21 ። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ያዕቆብ ነው። መልካም የቅዱስ ሚካኤል በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
  

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

09 Nov, 18:43


🌹ተፈጸመ ማኅሌተ ጽጌ🌹
            ፮ኛ ሳምንት

ተፈጸመ ማሕሌተ ጽጌ
ተፈጸመ ማሕሌተ ጽጌ ሥሙር{፪×}
ንግሥተ ሰማይ{፫×} ወምድር{፬×}
ትርጉምየሰማይና ምድር ንግሥት የሆንሽ እመቤታችን ሆይ የአንቺ መዝሙር ተፈጸመ።

ምንጭ፦
ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት

መልካም አዳር

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

06 Nov, 18:30


🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹

          🌹 #ጥቅምት ፳፰ (28) ቀን።

🌹 እንኳን #ለቅዱስ_አማኑኤል_ዓመታዊ_በዓል፣ #አባቱ_ኖኅ_እግዚአብሔር_የያፌትን_አገር_ያስፋለት ብሎ ለመረቀው #ለቅዱስ_ያፌት_ለመታሰቢያ_በዓሉ፣ #ለቅዱሳን_ሰማዕታት_ለመርትያኖስና_ለመርቆሬዎስ ለዕረፍታቸው በዓል፣ እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከአባ_መቅብዩ፣ #ከአባቶቻችንም_ከቅዱሳን_ከአብርሃም_ከይስሐቅና_ከያዕቆብ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

                      
                  
                           
🌹 #ቅዱሳን_ሰማዕታት_መርትያኖስና_መርቆሬዎስ፦ እሊህም ለቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት ለአባ ጳውሎስ ደመ መዛሙርቱ ናቸው ይህም እንዲህ ነው አርዮሳዊ የሆነው ሁለተኛው ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ አባ ጳውሎስን በተጣላው ጊዜ ወደ አርማንያ አጋዘውና በዚያም በሥውር አሥር ቤት ውስጥ አንቀው እንዲገድሉት አደረገ እሊህ ቅዱሳን መርትያኖስና መርቆሬዎስ ግን የዕረፍቱን ቀን ገድሉንም ጻፉ አርዮሳዊውያን ንጉሥ ረገሙት።

🌹 አንድ ክፉ ሰውም ወደ ንጉሡ ሒዶ እነርሱ እንደረገሙት ወነጀላቸው ንጉሡም ያን ጊዜ ከአታክልት ቦታዎች በአንዲቱ ቦታ ተቀምጦ ሳለ ወታደሮች ልኮ ወደርሱ አስቀረባቸው በሰይፍም እንዲገድሏቸው አዝዞ ገደሏቸው በዚያም በገደሏቸው ቦታ ቀበሩአቸው እስከ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ዘመንም በዚያ ቦታ ኖሩ እርሱም ዜናቸውን በሰማ ጊዜ መልእክተኞችን ልኮ ሥጋቸውን ወደ ቊስጥንጥንያ በክብር አስመጣ ያመረች ቤተ ክርስቲያንንም ሠርቶላቸው ሥጋቸውን በውስጧ አኖረ በዚችም ቀን ጥቅምት 28 በዓልን አደረገላቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ቅዱሳን ሰማዕታት መርትያኖስና መርቆሬዎስ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥቅምት28 ስንክሳር።
                         
                              
🌹 #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ትውልደ ጻድቃን ይትባረኩ። ክቡር ወብዕል ውስተ ቤቱ። ወጽድቁኒ ይነብር ለዓለም"። መዝ 111፥12-13 ወይም መዝ 71፥15። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 6፥9-15፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥12-17።  የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 20፥36-41። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ አማኑኤል በዓል፣ የአቡነ ይምአታ የዕረፍት በዓልና የጽጌ ጾም ለሁላችንም ይሁንልን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

26 Oct, 19:03


ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta):
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹

           🌹 #ጥቅምት ፲፯ (17) ቀን።

🌹 እንኳን #ለዲያቆናት_አለቃ ለሰማዕታት መጀመሪያ ለሆነ #ለቅዱስ_እስጢፋኖስ_ለሢመቱ_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።


                          
🌹 #የዚህ_ሳምንት_የዕለቱ_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፭ "#ጳጳሳት_ቀሳውስት_ወዲያቆናት ሊቃነ ካህናት ሥዩማነ ቤተ ክርስቲያን እለ ሎሙ ሕግ ወሎሙ ሥርዓት #ብፁዕ_እስጢፋኖስ_ምስለ_ኵሎሙ_ቅዱሳን ለከ የዓርጉ ስብሐት #እግዚኣ_ለሰንበት አሠርጎካ ለምድር #በሥነ_ጽጌያት_ወሠራዕከ_ሰንበት_ለሰብእ_ዕረፍተ ወብውህ ለከ ትኅድግ ኃጢአተ ረቢ ንብለከ ረቢ ሊቅ ነአምን ብከ። ትርጉም፦ ሕግና ሥርዓት ያላቸው የካህናት አለቆች የቤተ ክርስቲያን ሹማምንት፣ #ዲያቆናት፣_ቀሳውስትና_ጳጳሳት_ቅዱስ_እስጢፋኖስ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ምስጋናን ያሳርጉልሃል፣ #የሰንበት_ጌታ_ምድርን_በአበቦች_ውበት አስጌጥካት፣ #ለሰው_ዕረፍትን_ሰንበትን_ሠራኽ ኃጢአትን ትተውለት ዘንድ መምህር እንልሃለን፣ ሊቅ መምህር ሆይ እናምንብሃለን። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።

                       
                                                 
                           
🌹 #ቀዳሜ_ሰማዕት_ቅዱስ_እስጢፋኖስ፦ እስጢፋኖስ ማለት "መደብ" ማለት ሲሆን በግሪክ ቋንቋ "አክሊል" ማለት ነው፡፡ በግብሩ የቀን ሃሩር የሌሊት ቁር የማይለውጠው፣ መብራት ማለት ነው፡፡ ትውልዱ ከነገደ ብንያም ሲሆን አባቱ ስምዖን እናቱ ሐና ይባላሉ፡፡ እነርሱም እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከነቢያትና ከጻድቃን ወገን ናቸው፡፡ በመጀመሪያ ሁለት ወንድ ልጆችን ወለዱ፡፡ አንዱ ይሁዳ ሲባል ሁለተኛውም ቅዱስ እስጢፋኖስ (አስተፓኖስ) ነው፡፡

🌹 ቅዱስ እስጢፋኖስ የተወለደው ጥር 1 ቀን በእስራኤል ሃገር ውስጥ ልዩ ስሟ ሐኖስ በተባለች ቦት ነው፡፡ የተወለደውም በስለት ነው፡፡ እርሱም ከመጥምቁ ዮሐንስ እግር ሥር በመሆን ተምሯል፡፡ በኋላም ወደ ቅዱሳን ሐዋርያት በመሄድ ይላላካቸውና ያገለግላቸው ነበር፡፡ በኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን ከተሾሙት ከ7ቱ ዲያቆናት አንዱ ሲሆን የዲያቆናት አለቃ እርሱ ነው፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ወንጌልን በማስተማሩና ብዙዎችን ክርስቶስን ወደማመን ስለመለሳቸው ክፉዎች አይሁድ በጠላልትነት ተነስተውበት ጥር 1 ቀን በ34 ዓ.ም ከጌታችን ቀጥሎ ከምእመናን ወገን የመከራውን ገፈት ስለተቀበለ (በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ስላረፈ) "ቀዳሜ ሰማዕት" ተሰኘ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ "ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ" እየተባለ ይጠራል፡፡ ይኸውም የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያት በሰባቱ ዲያቆናት ላይ አለቃ አድርገው በሾሙት ጊዜ የተሰጠው ስያሜ ነው።

🌹 የመጀመሪያ ክርስቲያኖች የአማኞች ቊጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በሄደ ጊዜ የማኅበራዊው ኑሮ አስተዳደር ማለትም የምግብንና የመሳሰሉትን ቁሳቁሶች (ገንዘብም ጭምሮ) በትክክልና በእኩልነት የማከፋፈሉ ሥራ በሐዋርያት ዘንድ አስቸጋሪ ሆኖ ተገኘ፡፡ እነርሱም ደግሞ ዋና ተግባር አድርገው በትጋት ለመያዝ የፈለጉት ማስተማርን ነበር፡፡ ስለዚህም አማኞችን ሁሉ ሰብስበው ከመካከላቸው
በመልካም ጠባያቸው የተመሰገኑ በመንፈስ ቅዱስና በጥበብ የተሞሉ ሰባት ሰዎችን እንዲመርጡ አሳስቧቸው፡፡ አማኞችንም ነገሩ አስደስቷቸው ሰባት ሰዎችን መረጡ፡፡ እነርሱም፡- ቅዱስ እስጢፋኖስ (ዕረፍቱ ጥር 1)፣ ቅዱስ ጵሮኮሮስ (ሰኔ 8)፣ ቅዱስ ጢሞና (ሚያዝያ 16)፣ ቅዱስ ፊልጶስ (ጥቅምት 14)፣ ቅዱስ ጰርሜና (መስከረም 1)፣ ቅዱስ ኒቃሮና (3 ጊዜ ሞቶ የተነሣ)፣ ቅዱስ ኒቆላዎስ (ሚያዝያ 15) ናቸው፡፡ ሐዋ 6፡5፡፡

🌹 እነዚህንም ቅዱሳን በከበሩ ሐዋርያት ፊት ባቆሟአቸው ጊዜ ጸልየው እጃቸውን በራሳቸው ላይ ጭነው ሾሟቸው፡፡ በከበሩ ሐዋርያት ጫንቃ ላይ ተጭኖ የነበረው ከባድ ሸክም ባሎቻቸው የሞቱባቸውን ሴቶችና ወላጆቻቸው የሞቱባቸውን ደሀ አደጎች በመርዳት ችግሮቻቸውን አቃለሉላቸው፡፡በከበሩ ሐዋርያት ከተመረጡት ሰባቱ ዲያቆናት መካከል ሊቀ ዲያቆናት ተደረጎ የተመረጠው ቅዱስ እስጢፋኖስ ሲሆን ሌሎቹም ዲያቆናት እስከ ሕይወታቸው ፍጻሜ ወንጌልን በማስተማርና የመጀመሪያ ክርስቲያኖች በማስተዳደር በጽናት ተጋድለዋል፡፡ እነዚህም ሰባቱ ዲያቆናት ከአባቶቻቸው ከከበሩ ሐዋርያት አይተው የእነርሱንም መንፈስ ተቀብለው ያልተማሩ አህዛብን ልቡናቸውን ለመስበርና የእግዚአብሔርን ኃይልነት ተረድተው እንዲገነዘቡ በማሰብ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደርጉ ነበር፡፡

🌹 ከእነርሱም ውስጥ በዋነኛነት ቅዱስ እስጢፋኖስ በአህዛብ ፊት ያደረጋቸው ተአምራት እጅግ ድንቅ ናቸው፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ በአህዛብ መካከል ቆሞ ሲያስተምር ከቆየ በኋላ አንድ አንደበቱ ዲዳ የሆነ ሰው አጠገቡ ቢመጣ በጆሮው የሕይወት እስትንፋስ እፍ ቢልበት መስማት የማይችለው መስማት ቻለ፡፡ በዚህም ጣኦት አምላኪው ናኦስ እና ተከታዮቹ ሁሉ ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ተመለሱ፡፡ ጣኦት አምላኪው ናኦስ በድርጊቱ በጣም ከመናደዱ የተነሣ በአጠገቡ የቆመውን በሬ ጠንቋዩ ናኦስ በጆሮው እፍ ብሎ ቢተነፍስበት በሬው በምትሃት ለሁለት ተሰንጥቆ በመሞቱ ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ የተመለሱት በናኦስ ምትሃታዊ ድርጊት በመሳባቸው እንደገና ወደ ናኦስ ተመለሱ፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስም በዚህ ጊዜ የአህዛብ ልቡና ወላዋይ እንዳይሆንና እንዳይጠፉም በማሰብ ናኦስ እፍ ብሎ ለሁለት ሰንጥቆ የገደለውን በሬ መልሶ በሕይወት እንዲያስነሣው ናኦስን ጠየቀው፡፡ ነገር ግን ናኦስ ያንን ማድረግ አልቻለም፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ እስጢፋኖስ "ናኦስ ዳግመኛ ሕይወት ዘርቶ ማስነሣት ካልቻለ ነገሩ ሐሰተኛ ነው ማለት ነው፣ እኔ ግን በእግዚአብሔር ኃይልና ድንቅ ሥራ ይህን ለሁለት ተሰንጥቆ የሞተውን በሬ ዳግመኛ ሕይወት ዘርቶ እንዲነሣ አደርገዋለሁ" በማለት ወደ እግዚአብሔር ከጸለየ በኋላ በሬውን አስነሣው፡፡ ይህንንም ተአምር አድርጎ በማስተማር ልቦናቸው ወላውሎ ወደ ናኦስ የተመለሱትን አህዛብ ገንዘቡ እንዲሆኑ በእግዚአብሔር ኃይልነት እንዲያምኑ አድርጓል፡፡ ናኦስ በአልሸነፍ ባይነትና በአጋንንት ረዳትነት ራሱን ወደ ላይ
እንዲንሣፈፍ አድርጎ በአየር ላይ ቢወጣ ቅዱስ እስጢፋኖስ የእግዚአብሔርን ተአምር በማሳየት በትዕግስት ጠብቆ በአጋንንት ረዳትነት ወደ ላይ የተነሳውን ናኦስ በትምዕርተ መስቀል ቢያማትብበት ይዘውት የነበሩት አጋንንት ሁሉ ለቀውት ሲበተኑ ናኦስም ምድር ደርሶ ተንኮታኩቶ በመውደቁ በጣኦት አምላኪነት የነበሩ ሁሉ ዳግም ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ተመልሰዋል፡፡

🌹 የሰማዕታት መጀመሪያ የሆነው ቅዱስ እስጢፋኖስ በትምህርቱና በተአምራቱ ብዙዎችን ወደቀናች ሃይማኖት ስለመለሰ ክፉዎች አይሁድ ቀኑበትና የሐሰት ምስክር አዘጋጁበት፡፡ "በእግዚአብሔርና በሙሴ ላይ የስድብን ቃል ሲናገር ሰምተነዋል" ብለው በሐሰት ከሰሱትና በሸንጎአቸው አቆሙት፡፡ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስም ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ጌታችን ያለውን ሁሉንም እየጠቀሰ የሃይማኖትን ነገር አስተማራቸው፡፡ ነቢያትን ስለማሳደዳቸውና ስለመግደላቸው እየወቀሰ ሲናገራቸው በትምህርቱ ተናደው ጆሮአቸውን ይዘው በመጮህ በድንጋይ ወግረው ይገድሉት ዘንድ እየጎተቱ ከከተማው ውጭ አወጡት፡፡

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

26 Oct, 19:03


🌹 ቅዱሱም በድንጋይ ወግረው ሲገድሉት ከጌታችን የተማረውን "አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይህን ኃጢአት አትቁጠርባቸው" እያለ ስለ ገዳዮቹ ምሕረትን ይለምን ነበር፡፡ ሰማይም ተከፍቶ የእግዚአብሔርን ክብር ተመለከተ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ይኸውም የቀድሞው ሳውል ቅዱስ እስጢፋኖስን በድንጋይ ሲወግሩት የገዳዮቹን ልብስ ይጠብቅና ድንጋይ ያቀብል ነበር፡፡ "የሰማዕትህንም የእስጢፋኖስን ደም ባፈሰሱ ጊዜ፥ ራሴ ደግሞ በአጠገባቸው ስቆም ተስማምቼ የገዳዮችን ልብስ እጠብቅ ነበር አልሁ" ብሎ ራሱ ቅዱስ ጳውሎስ መስክሯል፡፡ ሐዋ 22፥20፡፡

🌹 የቅዱስ እስጢፋኖስ መምህር የነበረው ምሑረ ኦሪቱ ገማልያልና ልጁ አቢብ በእስጢፋኖስ ትምህርትና የሞቱ ሰዎች የሰጡትን ምስክርነት አይተው ከይሁዲነት ተመልሰው በክርስቶስ አምነው ተጠምቀዋል፡፡ ስለ ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡- "እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር፡፡ የነፃ አውጪዎች ከተባለችው ምኵራብም ከቀሬናና ከእስክንድርያም ሰዎች ከኪልቅያና ከእስያም ከነበሩት አንዳንዶቹ ተነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር፤ ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም፡፡ በዚያን ጊዜ በሙሴ ላይ በእግዚአብሔርም ላይ የስድብን ነገር ሲናገር ሰምተነዋል የሚሉ ሰዎችን አስነሡ፡፡ ቀርበውም ያዙት ወደ ሸንጎም አመጡትና "ይህ ሰው በዚህ በተቀደሰው ስፍራ በሕግም ላይ የስድብን ነገር ለመናገር አይተውም፤ ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ ያፈርሰዋል ሙሴም ያስተላለፈልንን ሥርዓት ይለውጣል ሲል ሰምተነዋልና" የሚሉ የሐሰት ምስክሮችን አቆሙ፡፡ በሸንጎም የተቀመጡት ሁሉ ትኵር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት"፡፡ የሐዋ ሥራ 6፥8-15፡፡

🌹 የአይሁድ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ ያቀረቡት የክሳቸው ምክንያት ጌታችንን ከከሰሱት ክስ ጋር በሁለት ነጥቦች ይመሳሰላል፡፡ የመጀመሪያው ክሳቸው "የሙሴን ሕግ ሽሯል" የሚል ነው፡፡ "የሙሴን ሕግ በመሻር ኦሪት አትጠቅምም አትመግብም አታድንም፤ ሐዲስ ኪዳን (ወንጌል) ግን ትመግባለች ታድናለች" ብሏል ብለው ከሰሱት፡፡ የሐዋ ሥራ 6፥13፡፡ ሁለተኛው ክሳቸው "እግዚአብሔርንም ይሰድባል" የሚል ነው፡፡ የሐዋ ሥራ 7፥50፡፡ አይሁድም የቅዱስ እስጢፋኖስን የወንጌል ቃል ንግግሮች በእግዚአብሔር ላይ እንደተሰነዘሩ ስድቦች በመቁጠር ነበር የወነጀሉት፡፡ የኦሪት የካህናት አለቃውም ቅዱስ እስጢፋኖስ ለተከሰሰበት መልስ ይሰጥ ዘንድ ሲጠይቀው እርሱ ግን ለተከሰሰበት መልስ ከመስጠት ይልቅ ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ድረስ ያለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ጽሑፍ በዝርዝር በሚገባ ተረከላቸው።

🌹 ቅዱስ እስጢፋኖስም እንዲህ አላቸው፡- "ከነቢያትስ አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን ነው? የጻድቁንም መምጣት አስቀድሞ የተናገሩትን ገደሉአቸው፤ በመላእክት ሥርዓት ሕግን ተቀብላችሁ ያልጠበቃችሁት እናንተም አሁን እርሱን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት ገደላችሁትም፡፡ ይህንም በሰሙ ጊዜ በልባቸው በጣም ተቈጡ ጥርሳቸውንም አፋጩበት፡፡መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፡፡ እነሆ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ፡፡ በታላቅ ድምፅም እየጮኹ ጆሮአቸውን ደፈኑ፣ በአንድ ልብ ሆነውም ወደ እርሱ ሮጡ፤ ከከተማም ወደ ውጭ አውጥተው ወገሩት፡፡ ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ፡፡ እስጢፋኖስም "ጌታ ኢየሱስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል" ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር፡፡ ተንበርክኮም "ጌታ ሆይ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው" ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፡፡ ይህንም ብሎ አንቀላፋ፡፡ ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር፡፡ የሐዋ ሥራ 7፥52-60፡፡

🌹 ቅዱስ እስጢፋኖስ ስለንጽሕናው ስለድንግልናው፣ ስለሰማዕትነቱ ስለተጋድሎው እና ስለስብከቱ ስለተአምራቱ ሦስቱ አክሊላት ተቀዳጅቷል፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ አምላኩን ክርስቶስን በብዙ ነገር መስሏል፡፡ በመጨረሻዋ የመሞቻው ሰዓት ላይ እንኳን ሆኖ አምላኩን አብነት አድርጎ ተገኝቷል፡፡ ጌታችን "ነፍሴን ተቀበላት" እንዳለ ሁሉ ቅዱስ እስጢፋኖስም "አቤቱ ጌታ ሆይ ነፍሴን ተቀበላት" ብሏል፡፡ ጌታችን "አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው" እንዳለ እስጢፋኖስም "ጌታ ሆይ ይህን ኃጥአት አትቁጠርባቸው የሚያደርጉትን አያውቁምና" በማለት ለገዳዩቹ ምሕረትን ለምኗል፡፡ በጌታችን ጸሎት እነ ፊያታዊ ዘየማንን ጨምሮ እልፍ ነፍሳት ወደ ንስሐ ተመልሰው ገነት መንግስተ ሰማያትን እንደወረሱ ሁሉ በቅዱስ እስጢፋኖስም ጸሎት ብዙ ነፍሳት ድነው ገነት መንግስተ ሰማያትን ወርሰዋል፡፡

🌹 የጌታችን ቅዱስ መስቀል እልፍ ሙታንን ያስነሣ ድውያንን ይፈውስ እንደነበር ሁሉ የቅዱስ እስጢፋኖስም ዐፅም ሙታንን ያስነሣ ድውያንን ይፈውስ ነበር፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ የተወገረበት ድንጋይ ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ታንጸውበታል፡፡የቅዱስ እስጢፋኖስ ልደቱና ዕረፍቱ ጥር 1 ቀን ነው፡፡ መእመናንም ሥጋውን ወስደው በክብር ቀበሩት፡፡ ጥቅምት 17 የተሾመበት ነው፡፡ መስከረም 15 ቀን ፍልሰተ ሥጋው ነው፡፡ የቅዱስ እስጢፋኖስ ቅዱስ ዐፅሙ ሙትን ያስነሣ ድውይን ይፈውስ ነበርና አይሁድ በቅናት ተነሥተው እንደ ጌታችን ቅዱስ መስቀል የቅዱስ እስጢፋኖስን ዐፅም አርቀው በመቆፈር ቀብረው በላዩም ቆሻሻ በመጣል ለ300 ዓመታት ያህል ተቀብሮ ኖሮ በመጨረሻ በፈቃደ እግዚአብሔር እንደ ቅዱስ መስቀሉ ተቆፍሮ በመውጣት መስከረም 15 ቀን ቅዱስ ዐፅሙ ወጥቶ በክብር በስሙ በታነጸው ቤተ ክርስቲያን በክብር ተቀምጧል፡፡

🌹 ይኸውም የሆነው እንዲህ ነው፡- ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ካረፈ ከ300 ዓመት በላይ በሆነ ጊዜ ጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ሲነገሥና ሃይማኖትን በመላው ዓለም አቀና፡፡ ተዘግተው የነበሩ ገዳማትና አብያተ ክርስያናት ተከፈቱ፡፡ በዚህም ወቅት የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋው በሚገኝበት በኢየሩሳሌም አካባቢ ሉክያኖስ ለሚባል ሰው ቅዱስ እስጢፋኖስ በራእይ ተገለጠለትና "እኔ እስጢፋኖስ ነኝ፣ ሥጋዬ በዚህ ቦታ ተቀብሯል" በማለት ሥጋውን ያወጡ ዘንድ አዘዘው፡፡ ሉክያኖስም ለኢየሩሳሌሙ ኤጰስ ቆጶስ ሄዶ ነገረውና ወደ ቦታው ሄደው ሲቆፍሩ ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነና ሳጥኑ ተገኘ፡፡ ከሳጥኑ እጅግ ደስ የሚል በዓዛ ወጣ፡፡ በዚያ ቦታም ቅዱሳን መላእክት ሲያመሰግኑ ተሰሙ፡፡ ኤጲስ ቆጶሳቱና ካህናቱም የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ በክብር በታላቅ ዝማሬ ወስደው አስቀመጡት።

🌹 ከዚህም በኋላ እንዲህ ሆነ፡- በኢየሩሳሌም የሚኖር የቁስጥንጥንያ ተወላጅ የሆነ ስሙ እለእስክንድሮስ የሚባል ሰው ነበር፡፡ እርሱም ለቅዱስ እስጢፋኖስ ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ሠርቶለት ሥጋውን አፍልሰው በዚያ በክብር አኖሩት፡፡ ከ5 ዓመት በኋላም እለእስክንድሮስ ዐረፈና ሚስቱ በቅዱስ እስጢፋኖስ አስክሬን ጎን ቀበረችው፡፡ ከሌሎች ከ5 ዓመቶችም በኋላ ሚስቱ የባሏን አስክሬን ወደ ቊስጥንጥንያ አገር ይዛ ልትሄድ አስባ ወደ መቃብሩ ስትሄድ የባሏን አስክሬን የወሰደች መስሏት በእግዚአብሔር ፈቃድ የቅዱስ እስጢፋኖስን ሣጥን ወስዳ እስከ አስቃላን ከተማ ድረስ ተሸከመችውና በመርከብ ተሳፍራ ወደ ቁስጥንጥንያ ሄደች።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

26 Oct, 19:03


🌹 የእለእስክንድሮስም ሚስት በመርከብ ስትጓዝ ጣዕም ያለው የመላእክትን ዝማሬ ሰማች፡፡ ልታየውም በተነሣች ጊዜ ሣጥኑ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋ ያለበት መሆኑን ዐወቀቸ፡፡ ወደ ኢየሩሳሌምም ለመመለስ አልተቻላትም ይልቁንም ይህ እንዲሆን የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ዐውቃ ለዚህ ክብር ስላበቃት አመሰገነች፡፡ ቊስጥንጥንያም እንደደረሰች ለሊቀ ጳጳሱ በእግዚአብሔር ፈቃድ የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ ይዛ እንደመጣች ላከችበት፡፡ ካህናቱና ሕዝቡም ሁሉ በታላቅ ደስታ ወጥተው በክብር ተቀበሏት፡፡ ከሥጋውም ብዙ ተአምራት ተገልጠው ታዩ፡፡

🌹 ከዚህም በኋላ ሥጋውን በበቅሎ ጭነው ሲጓዙ  ቊስጣንጢኖስ ከሚባል ቦታ ሲደርሱ የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ የያዘችው በቅሎ አልንቀሳቀስ አለች፡፡ እግዚአብሔር የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋው በዚህ ቦታ እንዲኖር የፈቀደ መሆኑን ዐወቁ፡፡ ሥጋውን የተጫነው በቅሎም በሰው አንደበት "የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ በዚህ ሊያኖሩ ይገባል" ብሎ ተናገረ፡፡ ይህንንም ያዩና የሰሙ ሁሉ እጅግ አደነቁ፡፡ የበለዓምን አህያ ያናገረ አምላክ አሁንም የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ የተሸከመችውን በቅሎ እንዳናገራት ዐውቀው ደስ አላቸው፡፡የሀገሪቱም ንጉሥ በቦታው ላይ ውብ ቤተ ክርስቲያን ሠርተውለት ሥጋውን በውስጧ በክብር አኖሩ፡፡ ከሥጋውም ብዙ አስገራሚ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ ከቅዱስ እስጢፋኖስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከቱ ያሳትፈን በጸሎቱ ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱስ ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደና ከገድላት አንደበት።

                      
                            
🌹 "#ሰላም_ለእስጢፋኖስ_እንተ_ነጸረ_በዐይኑ። እንዘ ወልድ ይነብር ለአብ ውስተ የማኑ። ከመ ኖትያዊ ጠቢብ ኃዳፌ ሐመር በኪኑ። ባሕረ መጻሕፍት አመ ጸበተት ልሳኑ። ተቃውሞቶ መዋግድ ስእኑ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥቅምት_17።

                            
🌹 #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አሐተ ሰአልክዎ ለእግዚአብሔር ወኪያሃ አኀሥሥ። ከመ እኅድር ቤቶ ለእግዚአብሔር በኵሉ መዋዕለ ሕይወትየ። ወከመ ያርእየኒ ዘያሠምሮ ለእግዚአብሔር"። መዝ 26፥4-5። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1፥35-41።

                           
🌹 #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወጽንሐሐኒ ኢትሠምር። መሥዋዕቱ ለእግዚአብሔር መንፈስ የዋህ። ልበ ትሑተ ወየዋሃ ኢይሜንን እግዚአብሔር"። መዝ 50፥16-17 ወይም መዝ 50፥10። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 1፥3-15፣ 1ኛ 5፥2-5 እና የሐዋ ሥራ 7፥54-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 21፥1-7። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ እስጢፋስ የሢመት በዓል፣ የማኅሌተ ጽጌ አራተኛ ሳምንት (ሰንበት)ና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

26 Oct, 16:32


🌹ማኅሌተ ጽጌ🌹
፬ኛ ሳምንት
ምንጭ፦
ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት

መልካም አዳር

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

23 Oct, 18:44


ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta):
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹

           🌹 #ጥቅምት ፲፬ (14) ቀን።

🌹 እንኳን #ከዘጠኙ_ቅዱሳን_አንዱ ለሆኑት #ለአባ_ዘሚካኤል በሚሰሩት ስራቸው አረጋዊ ለተባሉት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_አረጋዊ ከዚህ ዓለም ከሞት ለተሰወሩበት ቀን ለመታሰቢያ በዓል፣ ለቊስጥንጥንያ ንጉሥ ለቴዎዶስዮስ ልጅ ለሙሽራወ #ለቅዱስ_ለገብረ_ክርስቶስና ከሮሜ ሀገር ለሆነ ለእግዚአብሔር ሰው #ለቅዱስ_ሙሴ_ለዕረፍታቸው ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከመራክዋና ከእርሱ ጋር ካሉ ሰማዕታት፣ #ከድማቴዎስና_ከምራይስ #ከአራት_መቶ_ሠላሳ_አንድ_ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

                                                
                            
🌹 #አባ_ዘሚካኤል_አቡነ አረጋዊ፦ እኚህ አባት ከ9 ቅዱሳን አባቶች አንዱ ሲሆኑ አባታቸው ይስሐቅ የሮም ንጉሥ ነበሩ፡፡ እናታቸው ንግሥት እደና ይባሉ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ዘሚካኤል ነው፡፡ ጥበብ መንፈሳ ሲማሩ አድገው ወደ እስክንድርያ ገዳም ገቡ፡፡ አበምኔቱ አባ ጳኵሚስ በፈቃደ እግዚአብሔር የመጡ መሆናቸውን አውቀው መዓረገ ምንኵስና ሰጥተዋቸዋል፡፡

🌹 የንጉሣዊ የቅንጦት ኑሮ ንቀው ትተው ገዳም ገብተው በምንኵስና ተወስነዋል፡፡ አባታችን በተጋድሏቸውም ከአባ እንጦንስ፣ ከአባ ጳውሊ እና ከአባ መቃርስ ቀጥሎ በአራተኛ ማዕረግ አበ መነኰሳት ሆነው ተመርጠዋል።

🌹 በገዳመ ዳውናስ 7 ዓመት ከቆዩ በኋላ ወደ ሮም ተመልሰው ሲያስተምሩ የሀገራችን ኢትዮጵያን ዜና ሰምተው ለመምጣት በ480 ዓ.ም ከአባ ፍሬምናጦስ በኋላ መንገድ ጀመሩ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በክንፉ ተሸክሞ አክሱም አድርሷቸዋል፡፡ ተመልሰውም ሄደው ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ  መስክረዋል፡፡ "ሐዋርያ ሳይላክላት በሃይማኖት በምግባር ጸንታ ትኖራለች" ብለው ለሰባቱ ዘመዶቻቸው አበው መነኰሳት ነገሯቸው፡፡ ስምንቱም ጓዛቸውን ጠቅልለው በሮም ነግሦ የነበሩ ይስሐቅን (አባ ገሪማን) ጨምረው ንጉሥ አልአሜዳ በነገሠ በአምስተኛ ዓመት ማለትም በ480 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ዘጠኝ ሆነው መጥተዋል፡፡

🌹 አባ አረጋዊ እናታቸው ቅድስት እድናን ደቀ መዝሙራቸውን ማትያስን አስከትለው እግረ መንገዳቸውን እያስተማሩና ድውያንን እየፈወሱ ደብረ ዳሞ ደረሰዋል፡፡ ከእግረ ደብር ሆነው አሁን "ይህን ተራራ በምን ልወጣው እችላለሁ" እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ በንግግሩ ሐሰት የሌለበት አምላካችን በነቢዩ ዳዊት ላይ አድሮ በመዝ 90፥11-16 ላይ "በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ"። እንዳለው የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስደሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ ቅዱስ ሚካኤል ሰይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ከተራራው አናት አድርሷቸዋል፡፡

🌹 ወዲያው ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው አመስግነዋል፡፡ ቦታውም ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሏል፡፡ በዚያ ዕለት ግማሽ ህብስት በልተው ጠገቡ፤ ከዚያ በኋላ ግን ምድራዊ ሕብስት አልተመገቡም፡፡ በሰንበተ ክርስታያን ከቅዳሴ በኋላ ሕብስተ ሰማያዊ እያመጡላቸው ይመገቡ ነበር እንጂ፡፡ ኋላም ዜና ጽድቃቸውን ሰምተው ከስድስት ሺህ ያላነሱ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበውላቸዋል፡፡

🌹 ስለ አባታች አቡነ አረጋዊ መሰወር፦ የእርግና ዘመኑ ደረሰ ዘጠና ዘጠኝ ዓመት ሆነው። በነጋም ጊዜ ቆሞ ሲለምንና ጸሎትም ሲያደርግ ተመለከተው በምን ጊዜ ወይም ሰዓት ከነሱ እንደሚሠወር ደቀ መዝሙሩ አባ ማትያስ ይጠባበቅ ወይም በልቡ ያስቡ ነበርና።

🌹 ጸሎት ያደርግ ዘንድ ቀድሞ ወደነበረበት ተመልሶ ገባ ወይም ሄደ። ዳግመኛም ሦስት ሰዓት በሆነ ጊዜ ተመልሶ መጣ ነገር ግን ከበዓቱ በደረሰ ጊዜ አላገኘውም እሱ ተሠውሯልና። በዚያም ከመቋሚያና ከመስቀል በስተቀር ምንም ያገኘው ነገር የለም ይህንኑም ለወንድምቹ ነገራቸው። እነርሱም ጮሁ ዋይ ዋይም አሉ እሱንም ያገኙ እየመሰላቸው መስቀሉንና መቋሚያውን ተሸክመው በመሳም መሪር ዕንባን አለቀሱ።

🌹 ኀዘናቸውንና ልቅሶአቸውን ከፈጸሙ በኋላ ከእግዚአብሔር ዘንድ ለክቡር አባታችን አቡነ አረጋዊ የተሰጠውን ቃል ኪዳን ደቀ መዝሙሩ አባ ማትያስ  "ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁ" ብሎ ቃልኪዳን እንደሰጠው፡፡ "በስምህ የተማጸነውን እስከ ዐሥራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ" ብሎ ተስፋ እደነገራቸው፡፡ ነገራቸው ወንድሞቹም ይህን በሰሙ ጊዜ ፈጽመው ተደሰቱ ኀዘናቸውም ወደ ደስታ ተለወጠ ስለዚህም እግዚአብሔር አመሰገኑት።

🌹 በዚያን ጊዜ ቀለምና ብራና አዘጋጅተው ማትያስና ዮሴፍ እየነገሯቸው ለልጅ ልጅ መታሰቢ ሆኖ ይኖር ዘንድ የገድሉንና የቃል ኪዳኑን መጽሐፍ ጻፈ።

🌹 ከዚህም በኋላ በመነኰሳት ሥርዓት ማኅበር ሥርዓት ማኅበር ይኖሩ ዘንድ የሠራላቸውን ሥርዓት አሰቡ በሥርዓት ይመራቸው ዘንድ አባታቸው አረጋዊ ለሰጣቸው ለመንፈሳዊ አባታቸው ለአባ ማትያስም ራሳቸውን ዝቅ አደረጉ ሃሳባቸውንም የአባታቸው የአረጋዊዊን መታሰቢያ ወደማድረግ ተመለሱ።

🌹 ክብር አባታችን አቡነ አሰጋዊ የተሠወረበት ቀን በኢትዮጵያ ወር አቆጣጠር በጥቅምት ዐሥራ ዐራት ቀን በዕብራውያን ደግሞ በታስሪን ዐሥራ አንድ ቀን በኢትዮጵያዊው ንጉሥ በዐፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት ነው። ከአባታች ከአቡነ አረጋዊ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ አረጋዊ።

                        
                             
🌹 #የቊስጥንጥንያ_ንጉሥ_የቴዎዶስዮስ ልጅ መሽራው #ቅዱስ_ገብረ_ክርስቶስ፦ ይህም ቴዎዶስዮስ እግዚአብሔርን የሚፈራ ነው ሚስቱም በጎ የምትሠራ እግዚአብሔርንም የምትፈራ ናት ስሟም መርኬዛ ነው። እነርሱም ልጅ ስለሌላቸው ያዝኑ ነበር ወደ ኢየሩሳሌምም ሒደው ስእለትን ተሳሉ ቸር መሐሪ ወደሆነ እግዚአብሔርም ለመኑ እርሱም ልመናቸውን ተቀበሎ ይህን ያማረ ልጅ ሰጣቸው ስሙንም "አብደልመሲህ" ብለው ሰየሙት ትርጓሜውም "ገብረ ክርስቶስ" ማለት ነው ። የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ የሥጋዊንም ትምህርት አስተማሩት ።

🌹 አድጎ በጕለመሰም ጊዜ የሮሜውን ንጉሥ ልጅ አጭተው እንደ ሥርዓቱ አጋቡት ከሌሊቱ እኩሌታም በሆነ ጊዜ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ተነሥቶ ወደሙሽራዪቱ ገባ እጅዋንም ይዞ ከእርስዋ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ። ከዚያም የሃይማኖት ጸሎት በአንድ አምላክ እናምናለን የሚለውን እስከ መጨረሻ ጸለየ የተሞሸረበትንም ልብስ ከላዩ አውልቆ የግምጃ ልብስን ለበሰ ወደ ሙሽሪቷም ሒዶ ራስዋን ሳማት እንዲህም እያለ ተሰናበታት "እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ይኑር ከሰይጣን ሥራ ሁሉ ያድንሽ"። እርሷም አልቅሳ "ጌታዬ ወዴት ትሔዳለህ ለማንስ ትተወኛለህ" አለችው እርሱም "በእግዚአብሔር ዘንድ እተውሻለሁ እኔም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን ልከተለው እሔዳለሁ የአባቴ መንግሥት አላፊ ነውና አንቺም መሐላሽን አስቢ" አላት ያን ጊዜ መሐላዋን አስባ ዝም አለች።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

23 Oct, 18:44


🌹 ለሠርጉም የታደሙት ሁሉ እንደተኙ በሌሊት ወጥቶ ሔደ ወደ ባሕርም ዳርቻ ደርሶ በመርከብ የሚጓዙ መንገደኞችን አገኘ የዓመት መንገድ ወደሚሆን አርማንያም እስከሚደርስ ከእነርሱ ጋር ተጓዘ። ነግቶ ወደ ሠርጉ አዳራሽ አባትና እናቱ በገቡ ጊዜ ሙሽራውን ልጃቸውን አላገኙትም ሙሽሪትንም "ልጃችን ወዴት አለ?" ብለው ጠየቋት እርሷም እንዲህ አለቻቸው። "በሌሊት ወደ እኔ ገባ መሐላን አማለኝ ከእኔ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ ራሴንም ስሞኝ ከእኔ ዘንድ ወጣ እኔም እያለቀስኩ ብቻዬን አደርኩ" ነገርዋንም ሰምተው ወድቀው በመጮህ ታላቅ ልቅሶን አለቀሱ ።

🌹 በዚያችም ጊዜ በሀገሮች ውስጥ ሁሉ ልጁን ገብረ ክርስቶስን ይፈልጉት ዘንድ ንጉሡ አምስት መቶ አገልጋዮቹን ላከ ለድኆችና ለምስኪኖችም ምጽዋት አድርገው የሚሰጥዋቸውን ብዙ ገንዘብን ሰጣቸው።
ገብረ ክርስቶስ ግን በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም በአርማንም አገር በተሠራች በአንዲት ቤተ ክርስቲያን ደጅ የሚኖር ሆነ። አባቱ የላካቸውም ሁለቱ አገልጋዮች ከዚያ ደርሰው ስለርሱ መረመሩ ግን ወሬውን ማግኘት ተሳናቸው ለድኆችም ምጽዋትን ሰጡ እርሱም ከድኆችም ጋር ምጽዋትን ተቀበለ።

🌹 በዚያም ዐሥራ አምስት ዓመት ከኖረ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለአንድ ቄስ ተገለጸችለት ቦታውንም አመልክታ እንዲህ አለችው። "የእግዚአብሔር ሰው ገብረ ክርስቶስን ይዘህ ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ አስገባው ከውጭ አትተወው" ቄሱም እመቤታችን እዳዘዘችው አደረገ።

🌹 ከዚህም በኋላ የተመሰገነ ገብረ ክርስቶስ በሌሊት ተነሣ ከእመቤታችንም ሥዕል ፊት ቁም ጸለየ እንዲህም አላት "እመቤቴ ሆይ የተሠወረ ሥራዬን አንቺ ለምን ገለጥሽ አሁንም ወደሚሻለኝ ምሪኝ" ይህንንም ብሎ የእመቤታችንን ሥዕሏን ተሳልሞ በሌሊት ወጥቶ ወደ ባሕሩ ወደብ ደረሰ ወደሌላ ሀገርም ሊሔድ ወዶ በመርከብ ተሳፈረ። ግን በእግዚአብሔር ፈቃድ ከአባቱ አገር ደረሰ የአባቱና የእናቱም ባሮች እየናቁትና እየሰደቡት በአባቱ ደጅ ዐሥራ አምስት ዓመት ኖረ። ሲገቡና ሲወጡም ሽታው እንዳያስጨንቀን "ይህን ምስኪን አስወግዱልን" ይላሉ ወጭትና ድስትም አጥበው በላዩ ይደፉበታል ውሾችም እንዲናከሱበትና እንዲበሉት የሥጋ ትርፍራፊ ይጥሉበታል ውሾች ግን ቁስሉን ይልሱለት ነበር እንደዚህም አብዝተው አሠቃዪት ።

🌹 ከዚህም በኋላ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ለመነ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለአባቴና ለእናቴ ባሮች በደል እንዳይሆንባቸው ወዳንተ ውሰደኝ"። በዚያንም ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው። ከዚህም በኋላ ገድሉን ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ጻፈ በእጁም ጨብጧት ጥቅምት 14 ቀን ዐረፈ።

🌹 በእሑድ ቀንም ሕዝቡ ሁሉና ካህናቱ ከሊቀ ጳጳሳቱ ጋር በቅዳሴ ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሳሉ "የእግዚአብሔርን ሰው በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ቤት ፈልጉት" የሚል ቃል ከሰማይ ሰሙ በዚያን ጊዜ ሔደው በአረፈበት ቦታ አገኙት። በእጁም ውስጥ የተጨበጠ ክርታስን አዩ ሊወስዷትም ሽተው መውሰድ ተሳናቸው ።

በአንድነትም በጸለዩ ጊዜ እጁ ተፈትታ ወስደው አነበቧት አባትና እናቱም ልጃቸው እንደሆነ አወቁ ታላቅ ጩኸትም ሆነ መሪር ልቅሶንም አለቀሱ አክብረውም ቀበሩት መቃብሩም በሽተኞችን ሁሉ በመፈወስ ድንቆች የሆኑ ብዙ ተአምራትን የሚያደርግ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

                           
🌹 #ከሮሜ_ሀገር_የሆነ_የከበረ_የእግዚአብሔር ሰው #ቅዱስ_ሙሴ፦ የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አውፊምያኖስ የእናቱ አግልያስ ነው እነርሱም እግዚአብዘሔርን የሚፈሩ እጅግም ባለጸጎች ናቸው። አብዝተውም ይመጸውታሉ ሁልጊዜም ይጸልያሉ እስከ ዘጠኝ ሰዓትም ይጾማሉ ድኆችንና ችግረኞችንም ሳይይዙ አይበሉም።

🌹 ነገር ግን ልጆች የሏቸውም ነበር የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ የተባረከ ልጅን ይሰጣቸው ዘንድ እግዚአብሔርን ይለምኑት ነበር ጌታችንም ልመናቸውን ተቀብሎ ይህን መልኩ እጅግ ያማረ የከበረና የተባረከ ልጅን ሰጣቸው በወለዱትም ጊዜ በርሱ ደስ ብሏቸው ለድኆችና ለምስኪኖች ታላቅ ምሳ አደረጉ ስሙንም ሙሴ ብለው ሰየሙት ትርጓሜውም የእግዚአብሔር ሰው ማለት ነው ስለእርሱ እግዚአብሔር ልመናቸውን ሰምቷልና።

🌹 ከዚህም በኋላ ሙሴን በመልካም አስተዳደግ አሳደጉት መንፈሳዊና ሥጋዊ ትምህርትን ጥበብን ሁሉ አስተማሩት። አድጎም በጎለመሰ ጊዜ አባቱ አውፊምያኖስ ሚስቱ አግልያስን "እነሆ ልጃችን ሙሴ አደገ ሚስትን ልናጋባውና በጋብቻውም ደስ ሊለን ለእኛ ይገባናል" አላት። የሙሴ እናት አግልያስም ሰምታ በዚህ ነገር ደስ አላት ከሮሜ አገር ታላላቆች ሰዎች ወገንም መልኳ እጅግ ያማረ አንዲት ብላቴና አጋቡት። ታላቅ ሠርግንም በማዘጋጀት ሸልመው አስጊጠው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በጋብቻ ሥርዓት አክሊላትን አቀዳጇቸው። ከዚህ በኋላ ሥጋውንና ደሙንም ተቀብለው ወደሚሠረጉበት ቤት ገቡ።

🌹 ከዚህም በኋላ በማግሥቱ አውፊምያኖስ ሚዜውን ጠርቶ እንዲህ አለው ሙሽራው ወደ ሙሽሪቷ ገብቶ የጋብቻውን ሕግ እንዲፈጽም ንገረው ያ ሚዜውም በነገረው ጊዜ ወደ ሙሽራዪቷ ገባ ድንቅ የሆነ ውበቷንና ደም ግባቷን ተመለከተ በልቡም አስቦ እንዲህ አለ "ይህ ሁሉ ውበትና ደም ግባት አላፊ ጠፊ አይደለምን"። ይህንንም ብሎ ወደ ሰማያዊት መንግሥቱ የሚደርስበትን መንገድ እንዲመራው እግዚአብሔርን ለመነው። ሙሽራዪቱንም እንዲህ አላት "የተባረክሽ እኅቴ ሰላም ይሁንልሽ የእግዚአብሔርም ፍቅር አንድነት ከአንቺ ጋር ይኑር ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ እስከምንገናኝ ደኅና ሁኚ"። ይህንንም በሚላት ጊዜ ልብሶቹን አውልቆ ሰጥቷት ከእርሷ ዘንድ ወጣ የተሞሸረበትንም ልብስ ለውጦ ከባሕር ዳርቻ እስከሚደርስ መንገዱን ተጓዘ። ልብሶቹንም ሁሉ ሽጦ ለድኆችና ለችግረኞች ምጽዋትን ሰጠ እርሱም ጨርቅ በመልበስ እንደ ድኃ ሁኖ ቁራሽ እንጀራ እየለመነ በየጥቂቱ እየተመገበ እስከ ሀገረ ሮሀ ድረስ ሔደ።

🌹 ከዚያም በደረሰ ጊዜ ወደቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ ለሮሀ ንጉሥ ለአቃርዮስ በስብከቱ ወራት የተላከለትን ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሥዕልና የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕል አግኝቶ ከሥዕሎቹ ተሳልሞ በረከትን ተቀበለ ወደ ልዑል እግዚአብሔርም ፈጽሞ እያመሰገነ ጸለየ። ወጥቶም ኑሮውን ከድኆችና ከምስኪኖች ጋር አደረገ።

🌹 ከዚህም በኋላ መጸለይና መጾምን ጀመረ እስከ ምሽትም ይጾማል በቀንና በሌሊትም ጸሎቱን አያቋርጥም ምጽዋትንም ከድኆች ጋር ተቀብሎ እርሱ መልሶ ለሌሎች ይሰጣል። በዚያቺም ዕለት በነጋ ጊዜ ወደ ሠርጉ አዳራሽ አባትና እናቱ ሲገቡ ሙሽራው ልጃቸው ሙሴ በጫጉላው ቤት እንደ ሌለ ሰሙ ደስታቸውም ወደ ኀዘን የሠርጉም ዘፈን ወደ ልቅሶ ወደ ዋይታ ተለወጠ።

🌹 ከዚህም በኋላ አውፊምያኖስ ባሮቹን ጠርቶ ብዙ ገንዘብን ሰጣቸው እንዲህም አላቸው "ልጄን እስከምታገኙት ድረስ ሁለት ሁለት እየሆናችሁ ወደ ሀገሩ ሁሉ ሒዱ ለድኆችና ለችግረኞች ምጽዋትን ስጡአቸው"። እነርሱም በሀገሩ ሁሉ ተበታተኑ። ከአባቱ አገልጋዮችም ሁለቱ አገኙት ግን አላወቁትም ምጽዋትንም ከድኆች ጋር ሰጡት ቅዱስ ሙሴም አውቋቸው እንዲህ ብሎ አመሰገነ "ጌታዬ ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ስለ አንተ ፍቅር ከአባቴ ባሮች እጅ ምጽዋትን እቀበል ዘንድ ለዚህ ታላቅ ክብር አድለህኛልና

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

23 Oct, 18:44


🌹 ከዚህም በኋላ ሥጋውን በታላቋ በሐዋርያት ጴጥሮስና ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን አኖሩ ከሥጋውም ብዙ ድንቆች ተአምራት ተደረጉ ዕውሮች አይተዋልና ሐንካሶችም ቀንተው ይሔዳሉና ደንቆሮዎችም ይሰማሉና ለምጻሞችም ይነጻሉና አጋንንት ያደሩባቸውም ይወጡላቸዋልና ሁሉም ካለባቸው ደዌ ይድናሉና። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሙሴ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥቅምት 14 ስንክሳር።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

23 Oct, 18:44


አመሰግንሃለሁ"። የአባቱ አገልጋዮችም ብዙ ወራት በሁሉ አገሮች ሲዞሩ ኑረው ወደ አውፊምያኖስ ጌታቸው ተመለሱ። የእግዚአብሔር ሰው ቅዱስ ሙሴም ከሰንበት ቀኖች በቀር እህልን የማይቀምስ እስቲሆን ድረስ ተጋድሎውን በመጨመር በየሁለትና በየሦስት ቀኖች የሚጾም ሆነ።

🌹 ከዚህም በኋላ እመቤታችን የከበረች ድንግል ማርያም ከዚያች ቤተ ክርስቲያን ካህናት ውስጥ ለአንድ ደግ ጻድቅ ቄስ ተገልጻ እንዲህ አለቸው "በጥዋት ወደ ቤተ ክርስቲያን ውጭ ውጣ ከምሰሶ አጠገብ ብቻውን ቁሞ የሚጸልይ ሰው ታገኛለህ የእግዚአብሔር ሰው ሆይ ወደ ቤተ ክርስቲያን ግባ በለው በውጭ አትተወው ጾሙ ጸሎቱ በእግዚአብሔር ፊት መዓዛው ጣፋጭ እንደሆነ ዕጣን ተቀባይነትን አግኝቷልና"። ሲነጋም ያ ቄስ ወደ ቅዱስ ሙሴ ሒዶ "የእግዚአብሔር ሰው ሆይ ወደ ቤተ ክርስቲያን ግባ" አለው ሙሴም "አባቴ ሆይ በከበረ ቦታ ላይ መቆም የማይገባኝ ኃጢአተኛ ነኝና ተወኝ" አለው ቄሱም "ወደ ቤተ መቅደስ አስገባህ ዘንድ ከቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ወዳንተ ተልኬአለሁ" ብሎ መለሰለት ወደ ቤተ መቅደስም ያስገባው ዘንድ እንዳዘዘችው ነገረው ከዚህም በኋላ አስገባው።

🌹 ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር ሰው ሙሴ ወደ ሀገረ ጠርሴስ ይሔድ ዘንድ አስቦ እርሷም የሐዋርያው ጳውሎስ አገር ናት እንዲህም አለ "እስከ ዕለተ ሞቴ በውስጥዋ እኖራለሁ ሥጋው ምንም በሮሜ አገር የሚኖር ቢሆንም የትውልድ አገሩ ናትና በረከትን እቀበላለሁ" ብሎ ነው።

🌹 በሌሊትም ወጥቶ ወደ ባሕር ዳርቻ ሔደ ወደ ጠርሴስም ይሔድ ዘንድ በመርከብ ተጫነ በባሕር መካከልም ታላቅ ነፋስ ተነሣባቸው ባሕሩም ከነፋሱ ኃይል የተነሣ ታወከ ወደየትም እንደሚሔዱ አያውቁም ነበር ቀኑ ጨልሞባቸዋልና ስለ ነፍሳቸውም ድኅነት ወደ እግዚአብሔር ለመኑ በዚያንም ጊዜ ባሕሩ ጸጥ ብሎ ታላቅ ደስታ ሆነ ብርሃንም ታየ ወደ ሮሜ ሀገር ወደብም እንደ ደረሱ አወቁ።

🌹 ቅዱስ ሙሴም ተነሥቶ በመርከብ ውስጥ ያሉትን በሰላምታ ተሰናብቷቸው ጉዞውን ጀመረ በልቡም እንዲህ አለ "ይህ ሁሉ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሆነ እንግዲህ እስከ ዕለተ ሞቴ ራሴን ለማንም እንዳልገልጥ ሕያው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን የሚያውቀኝ የለምና በአባቴ ደጅ እኖራለሁ" ይህንንም ብሎ ወደ አባቱ ቤት ተጓዘ። በመንገድም ላይ አባቱን ተገናኘው ብዙ ሰውም ተከትሎት ነበር የእግዚአብሔር ሰው ሙሴም ቀረብ ብሎ አባቱ የተቀመጠበትን ፈረስ ልጓሙን ያዘ እንዲህም አለው "እግዚአብሔር የባረከህ ያከበረህ አንተ ደግ ሰው እግዚአብሔርም ኃጢአትህን ይቅር ይበልህ የልብህንም ልመና ይስጥህ እኔም መጻተኛ ድኃ ሰው እንደ ሆንኩ እወቅ ለመጻተኛነቴና ለችግረኛነቴ የምትራራ ሁነህ ከማዕድህ ፍርፋሪ ልትመግበኝ ከወደድህ መኖሪያዬን በቤትህ አንጻር በደጃፍህ አድርግልኝ ዋጋህንም የሚሰጥህ እግዚአብሔር ነውና"።በዚያንም ጊዜ አውፊምያኖስ የልጁ የሙሴን ስደት አስታውሶ በተቃጠለ ልብ አለቀሰ መኖሪያውንም በቤቱ ደጅ እንዲሠሩለት አዘዘለት። ሁለተኛም ከአገልጋዮቹ አንዱን በሚያሻው ነገር ሁሉ እንዲአገለግለው አዘዘው።

🌹 የእግዚአብሔር ሰው ሙሴም ያን የሚያገለግለውን "ወንድሜ ሆይ ከሰንበት ቀኖች በቀር መብልና መጠጥ እንዳታመጣልኝ እለምንሃለሁ ይኸውም ከቁርባን በኋላ ግማሽ እንጀራና የጽዋ ውኃ ብቻ ነው" አለው። በጾምና በጸሎትም እየተጋደለ በዚያ በአባቱ ደጅ ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖረ።

🌹 ሰውን የሚወድ ቸር ጌታችን ኢየሱስ ከዚህ ዓለም ድካም ሊአሳርፈው ወዶ ተገለጠለት እንዲህም አለው "የመረጥሁህ አንተ ብፁዕ ነህ አንተ ፈቃዴን ፈጽመሃልና በዚህ ዓለም ከደስታ ኃዘንን ከብልጽግና ድኅነትን መርጠሃልና እኔም የማይጠፋ ብልጽግናን እሰጥሃለሁ ዳግመኛም ስምህን የሚጠራ መታሰቢያህንም ለሚያደርግ የተራበውን ለሚያጠግብ የተጠማውን ለሚያጠጣ የተራቈተውን ለሚያለብስ ገድልህንም ለሚጽፍ ወይም ለሚያጽፍ ስለ ስምህ በጎ ሥራ ሁሉ ለሚሠራ ቃል ኪዳንን ሰጠሁህ። በሰማያዊት መንግሥትም በጎ ዋጋን እሰጠዋለሁ ተጠራጣሪ ካልሆነ በዚህ ዓለምም እጠብቀዋለሁ ከበጎ ነገር ሁሉ ምንም አላሳጣውም። አሁንም ከአራት ቀን በኋላ እወስድሃለሁ ምርጦቼ ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት ከአሉበትም አኖርሃለሁ" ይህንንም ብሎ ከእርሱ ዘንድ ወደ ሰማይ በታላቅ ክብር ዐረገ።

🌹 ቅዱስ ሙሴም ከእግዚአብሔር ዘንድ ይህን ጸጋ በተሰጠ ጊዜ እጅግ ደስ አለው ያን የሚያገለግለውንም ወንድሜ ሆይ እንግዲህ "ስለ እኔ ከመድከም ታርፋለህና ወረቀትና ቀለም አምጣልኝ" አለው። ያ አገልጋይም ከአነጋገሩ የተነሣ አድንቆ ወረቀቱንና ቀለሙን አመጣለት የከበረ የእግዚአብሔር ሰው ሙሴም ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ገድሉን ሁሉ ጻፈ በአራተኛውም ቀን ያቺን የጻፋትን መጽሐፍ በእጁ ጨበጣት በእሑድ ቀንም በሰላም ዐረፈ። መላእክት "ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት ለሚያገለግሉት የዘላለም ተድላ ደስታ ለሚሰጥ ለነበረና ለሚኖር ፈጣሪያችን ምስጋና ይሁን" እያሉ ነፍሱን ተቀበሏት። ሕዝቡም ሁሉ በቅዳሴ ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተሰብስበው እያሉ ከመሠዊያው በላይ "የጌታቸውን ሕጎቹንና ሥርዓቱን የሚያደርጉ ደጎች አገልጋዮች ባሮች የተመሰገኑ ናቸው እነርሱ ወደ ዘላለም ተድላ ደስታ ይገባሉና" የሚል ቃልን ሲጮህ ሰሙ ።

🌹 ሊቀ ጳጳሳቱና ኤጲስቆጶሳቱ ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ሕዝብም ሁሉ በሰሙ ጊዜ በላያቸው ታላቅ ፍርሀት ወደቀባቸው። የቅዳሴውም ሥርዓት ከተፈጸመ በኋላ ይህን ምሥጢር ይገልጽላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ በመጸለይ ማለዱ በዚያንም ጊዜ "የእግዚአብሔርን ሰው በአውፊምያኖስ ቤት ፈልጉት እነሆ እርሱ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጥቷልና" የሚል ቃልን ሰሙ። ሊቀ ጳጳሳቱም ይህን ነገር ሰምቶ አውፊምያኖስን ጠራውና "ይህ ታላቅ ጸጋ በቤትህ ውስጥ ሲኖር በሕይወቱ ሳለ እንድንጎበኘው በረከቱንም እንድንቀበል ለምን አልነገርከንም" አለው አውፊምያኖስም እንዲህ ብሎ መለሰ "ክቡር አባት ሆይ ቅድስናህ ይመስክር ይህን የሚመስል በቤቴ ውስጥ እንዳለ አላወቅሁም"።

🌹 በዚያንም ጊዜ ሊቀ ጳጳሳቱ ከሁሉ ካህናትና ሕዝብ ጋር ተነሥቶ ወደ አውፊምያኖስ ቤት ሔደ የከበረ የእግዚአብሔር ሰው ሙሴንም በዐረፈበት ቦታ አገኙት ክርታሱም በእጁ ውስጥ ነው ሊቀ ጳጳሳቱም ያቺን ክርታስ አንሥቶ "የእግዚአብሔር ሰው ሙሴ የአውፊምያኖስ ልጅ እናቱም አግልያስ" እስከሚለው ስሙ እስቲደርስ በሕዝቡ ሁሉ ፊት አነበባት። እናትና አባቱም በሰሙ ጊዜ ደነገጡ መራር ልቅሶንም አለቀሱ ቤተሰቦቻቸውም ሁሉ ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ አጽናንቶ ጸጥ አደረጋቸው።

🌹 በዚያንም ጊዜ ሊቀ ጳጳሳቱ የሐር ልብስ አስመጥቶ በክብር ገነዘው ወደ ቤተ ክርስቲያንም ወስደው ከሥጋው እስከሚባረኩ በቤተ መቅደስ አኖሩት። ካህናቱና ሕዝቡ ሁሉ ከዚህም በኋላ ብዙ በሽተኞች ዕውሮች ሐንካሶች ደንቆሮዎች ዲዳዎች መጥተው ከሥጋው በተሳለሙ ጊዜ ሁሉም ከደዌያቸው ዳኑ በዚያችም ቀን ታላቅ ደስታ ሆነ። ሕዝቡም በበዙ ጊዜ የልጁን የሙሴን ሥጋ ከዐልጋው ላይ እንዳይጥሉት አውፊምያኖስ ፈራ ብዙ ገንዘብም አምጥተው ይበትኑ ዘንድ አገልጋዮቹን አዘዛቸው። ሥጋውን ትተው ወደ ተበተነው ገንዘብ ይሔዳሉ ብሎ አስቦ ነበር ግን ከቶ አንድ እንኳ ወደ ገንዘብ የሔደ የለም።

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

22 Oct, 07:28


ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ክፉ ድርጊት እየተፈጸመ ያለው በእኛው ልጆች በኢትዮጵያውያን መሆኑ ነው፤ ስለሆነም በከተማም፣ በጫካም፣ በገጠርም በየትኛውም ስፍራ የምትገኙ ልጆቻችን ምንም ይሁን ምን ሀገርንና ሕዝብን ከመጉዳት ተቆጠቡ፡፡ በተለይም ከቤተ ክርስቲያንና ከሀገር እንደዚሁም ሕዝቡን ከሚያገለግሉ ካህናትና ሲቪል ሰራተኞች እባካችሁ እጃችሁን አንሡ፤ ቤተ ክርስቲያን እኮ የእናንተና የሕዝቡ ሁሉ እናት ናት፤ በእናታችሁ ላይ መጨከንን እንዴት ተለማመዳችሁት? አሁንም ንስሐ ግቡ ያለፈው ይበቃል፡፡ ልብ በሉ ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት አይበጅም፤ ሰውን መጉዳትና እግዚአብሔርን መዳፈር አቁሙ፤ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሥርዓተ አምልኮም ያለቦታው አታውሉ፤ ጥያቄአችሁን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዕድል ስጡ፡፡ በእግዚአብሔር ስም ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንና ልጆቻችን የምናስተላፈው ወቅታዊ መልእክታችን ይህ ነው፡፡

በመጨረሻም
በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎትና የስራ አፈጻጸም ላይ ለመምከርና ለመወሰን ኃላፊነት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት መደበኛና ዓመታዊ ጉባኤውን የጀመረ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናበስራለን፡፡
እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ!
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን::

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ፤

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

22 Oct, 07:28


"አሁን የምንገኝበት ዘመን የጸላኤ ሠናያት መንፈስ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ከምንም ጊዜ በበለጠ ጦሩን ሰብቆ የተነሣበት ጊዜ ነው።" ቅዱስ ፓትርያርኩ

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጀመረ !

ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

የጥቅምት 2017 ዓ.ም ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ በቅዱስ ፓትርያርኩ መልእክት ተከፍቷል።

የቅዱስነታቸው ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ቀርቧል

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

• ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጐጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
• ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፤

ዓመቱን ጠብቆ ስለ አጠቃላይ ተልእኮአችን ለመወያየት በዚህ ጉባኤ የሰበሰበን አምላካችን ስሙ የተመሰገነ ይሁን፤

“ወይእዜኒ ግብኡ ኀበ ኖላዊሃ ወዓቃቢሃ ለነፍስክሙ፤ አሁንም ወደ እረኛችሁና ወደ ነፍሳችሁ ጠባቂ ተመለሱ” (1 ጴጥ 2÷!5)

ሁሉን የሚችል አምላካችን እግዚአብሔር በፍቅሩና በፍቅሩ መነሻነት ብቻ ፍጥረታትን በሙሉ እንደፈጠረ ቅዱስ መጽሐፍ ያስተምረናል፤ ከፈጠረም በኋላ የክብሩ ተሳታፊ እንዲሆኑ ወዶ ክብሩን አድሎአቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ለፍጡራኑ ካደላቸው ነገሮች አንዱ በየዓይነታቸው ጠባቂና መሪ እያደረገ በፍጡራን ላይ ፍጡራንን መሾሙ ነው፤ ይህ ስጦታ በሰማይም ሆነ በምድር ላሉ ፍጥረታት የተሰጠ የሱታፌ መለኮት ስጦታ ነው፡፡

ይህም በመሆኑ ሁሉም ፍጡራን አራዊትም ሆኑ እንስሳት ይብዛም ይነስ ጠባቂና መሪ እንዳላቸው እናስተውላለን፤ በተለይም የፍጥረታት ቁንጮ የሆኑ መላእክትና ሰዎች መሪና ሹም እንዳሏቸው የማንክደው ሓቅ ነው፡፡ ቅዱስ መጽሓፍም ይህንን ደጋግሞ ያስረዳል፤ የእነዚህ ሁሉ ላዕላዊ ጠባቂና መሪ ደግሞ እግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በፍጡራን ላይ ፍጡራንን ጠባቂዎች አድርጎ ሲሾም ፍጡራንን የክብሩ ተሳታፊ ለማድረግ እንጂ የእሱ ጥበቃ አንሶ ወይም ድጋፍ ሽቶ አይደለም፡፡ ስለሆነም ፍጹምና ላዕላዊ የሆነ ጥበቃው ሁሉንም ያካለለ ነውና ከእሱ ቊጥጥርና ጥበቃ ውጭ አንድም ነገር እንደሌለ የምንስተው አይደለም ፡፡

• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
• የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!

በአምሳለ እግዚአብሔር በተፈጠረውና በክብር መልዕልተ ፍጡራን በሆነው ሰው ላይ በዚህ ዓለም የተሾሙ ሁለት አካላት አሉ፤ እነሱም የመንፈስና የዓለም መሪዎች ናቸው፡፡ በተለይም የመንፈስ መሪዎችና ጠባቂዎች የተባሉት በመንፈስ ቅዱስ ተሹመን በዚህ ክርስቶሳዊ ጉባኤ የተሰበሰብነው እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ነን፡፡

ይህ ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚገኙና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን መሪና ጠባቂ ነው፤ ከዚያም ባሻገር እንደ ቃሉ እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ቃሉን በመስበክ ፍጥረተ ሰብእን በሙሉ የመጥራት ተልእኮ ለእኛ የተሰጠ የቤት ስራ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ የተሰጠን ኃላፊነት እጅግ በጣም ታላቅ እንደመሆኑ የሚጠበቅብን ውጤትም በዚያው ልክ ትልቅ ነው፤ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይፈለግበታል ያለው የጌታችን አስተምህሮም ይህንን ያስታውሰናል፡፡

ሁላችን እንደምንገነዘበው አሁን የምንገኝበት ዘመን የጸላኤ ሠናያት መንፈስ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ከምንም ጊዜ በበለጠ ጦሩን ሰብቆ የተነሣበት ጊዜ ነው፤ አሁን ያለው ዓለም በሀገራችንም ሆነ በሌላው ክፍለ ዓለም ላሉ ኦርቶዶክሳውያን ከባድ ፈተና ደቅኖብናል፡፡ ክፉው መንፈስ የሰውን አእምሮ በማዛባት ምእመናንን በቅዱስ መጽሐፍና በሕገ ተፈጥሮ ከተመደበላቸው የጋብቻ ሕግ በማስወጣት እንስሳት እንኳ የማይፈጽሙት ነውረ ኃጢአት እንዲፈጽሙ በመገፋፋት ላይ ይገኛል፡፡ በአማንያን ልጆቻችን ላይም በረቀቀ ስልት ግድያ፣ እገታ፣ አፈና፣ የመብት ተጽዕኖ እና አድልዎ በማድረግ እንደዚሁም በአስመሳይ ስብከትና አምልኮ ጣዖትን በማለማመድ ሕዝቡ ሳይገባውና ሳይጠነቀቅ ከእግዚአብሔር መንግሥት እንዲወጣ እያደረገ ነው፡፡

• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
• የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!

ክፉው መንፈስ በተራቀቀና በተራዘመ ስልት ሊውጠን በተነሣ ልክ እኛም ከእሱ እጥፍ በሆነ መለኮታዊ ኃይል ልንመክተው ካልቻልን በፈጣሪም ሆነ በትውልድ እንደዚሁም በታሪክ ፊት በኃላፊነት መጠየቃችን አይቀርም፡፡ መከላከል የምንችለውም ችግሩን በውል ከመረዳት አንሥቶ ሕዝቡን በደምብ በማስተማርና በመጠበቅ እንደዚሁም ለመሪነታችን ዕንቅፋት ከሚሆኑን ዓለማዊ ነገሮች ራሳችንን በማራቅ ነው፡፡ ሕዝቡም በዚህ ዙሪያ ሊያደምጠንና ሊከተለን የሚችለው መስለን ሳይሆን ሆነን ስንገኝለት ነው፡፡ ሕዝቡ ሊከተለን የሚችለው እሱን በብቃት ለመጠበቅ ዓቅሙም ተነሣሽነቱም ቁርጠኝነቱም እንዳለን ሲመለከት፣ እንደዚሁም ከዕለት ተዕለት ተግባራችንና አኗኗራችን የሚያየው ተጨባጭ እውነታ ኅሊናውን ሲረታ እንደሆነ አንርሳ፡፡

የምናስተምረው ሌላ የምንሰራው ሌላ ከሆነ ግን ከሕዝቡ አእምሮ መውጣታችን እንደማይቀር መገንዘብ አለብን፤ በመሆኑም በሰብእናችን፣ በአስተዳደራችን፣ በአመራራችንና በጥበቃችን ሁሉ እንደቃሉና እንደቃሉ ብቻ ለመፈጸም መትጋትና በቁርጥ መነሣት ጊዜው አሁን ነው እንላለን፡፡ ይህ ሲሆን በምእመናንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት አስተማማኝና እንከን የለሽ ይሆናል፤ ይህ ከሆነ እውነትም የመሪነት፣ የእረኝነትና የመልካም ተምሳሌነት ኃላፊነታችንን በትክክል ተወጥተናል ማለት እንችላለን፡፡

• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
• የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!

የሰው ልጆች በዚህ ዓለም ሲኖሩ የተሟላ ሰላምና ጣዕመ ሕይወት ሊኖራቸው የሚችለው በመንፈሳዊ ኑሮአቸው የተሻለ ነገር ስላገኙ ብቻ አይደለም፡፡ ሰዎች ከሥጋዊ ክዋኔም ጭምር የተፈጠሩ እንጂ እንደመላእክት ሥጋ የሌላቸው መንፈስ ስላይደሉ ለኑሮአቸውና ለሥጋዊ ክዋኔአቸው የሚሆን ነገር ያስፈልጋቸዋል፡፡ በዚህም ዓለማዊው አስተዳደር የተመቻቸ መደላድል ሊፈጥርላቸው ግድ ነው፤ ዓለማዊው አስተዳደርም የመለኮትን ተልእኮ ለመፈጸም የተሾመ ሹመኛ እንደመሆኑ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በትክልል መምራት ይጠበቅበታል፡፡ ምንም ቢሆን የተቀበለው ኃላፊነት የእግዚአብሔር ነውና በሚሰራው ሁሉ በሿሚው አምላክ ከመጠየቅ አያመልጥም፡፡
እኛም በዚህ ዓለም የእግዚአብሔር ወኪሎች ስለሆንን ቢሰሙንም ባይሰሙንም ዓለማውያን ሹማምንትን የማስተማርና የመምከር ኃላፊነት አለብን፡፡ ይህ የሁለታችን ኃላፊነት እንደ እግዚብሔር ፈቃድ ስንፈጽም የሕዝብ ሰላምና በረከት፣ ፍቅና አንድነት፣ ዕድገትና ልማት በአስተማማኝ ሁኔታ ይረጋገጣል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን እየሆነ ያለው ይህ አይደለም፤ አለመግባባት በዝቶአል፣ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቶአል፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡ ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቶአል፤ ይህ ለአንድ ሀገር ወይም ሕዝብ የውድቀት ምክንያት ከሚሆን በቀር ከቶውኑም የዕድገት ምልክት ሊሆን አይችልም፡፡

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

19 Oct, 18:07


🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹

🌹 እንኳን #ለዘመነ_ለማኅሌተ_ጽጌ_ለሦስተኛ_ሳምንት ለዕለተ እሑድ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

                          
🌹 #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ ፫ "#ወመኑ_መሐሪ_ዘከማከ፤ ምስለ #ኖኅ_ኪዳነ ዘአቀምከ #ለደቂቀ_እስራኤል መና ዘአውረድከ፤ አዝ፣ #ወበጽጌያት_ምድረ_አሠርጎከ ወሥነ ገዳምኒ ምስለ ቅዱሳኒከ፤ አዝ፣ ወከመ ወሬዛ ኀየል መላትሒሁ ጒርዔሁ መዐርዒር አምሳሉ ዘወይጠል፤ አዝ፣ ሰማየ ወምድረ ዘአንተ ፈጠርከ #ፀሐየ_ወወርኃ_ዘአስተዋደድከ፤ አዝ፣ በከዋክብት ሰማየ ዘከለልከ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ አዝ፣ #ቀደሳ_ወአክበራ_አዕበያ_ለሰንበት ወአልዓላ እምኲሉ ዕለት ወመኑ መሐሪ ዘከማከ ወኲሉ ይሴፎ ኪያከ"። ትርጉም፦ #እንደ_አንተ_ያለ_ይቅር ባይ ማነው? #ከኖኅ_ጋር_ቃል_ኪዳንን ያቆምህ (ያጸናህ)፤ #ለእስራኤል_ልጆች_መናን_ያወረድህ፤ #በአበቦች_ውበት_ምድርን_ያስጌጥክ፣ የገዳምን ውበት ከቅዱሳንህ ጋር ነው አስጌጥክ እንደ ኃይለኛ ጎልማሳ እንደ ዋሊያ ጉረሮው ጣፋጭ ነው ሰማይና ምድርን የፈጠርህ፣ #ፀሐይና_ጨረቃን_ያስማማህ፣ በከዋክብት ሰማይን የጋረድክ፣ በአበቦችን አሳየ፣ ቁጥር የሌለው ብዙ አበቦችን አሳይ፣ ለሕዝብህ በረከትን ስጥ፣ #ሰንበትን_ቀደሳት_አከበራት_ከዕለታት_ሁሉ_ከፍ ከፍ አደረጋት እንዳንተ ያለ ይቅር ባይ ማነው ሁሉ አንተን ተስፋ ያደርጋል። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።

                            
🌹 #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ። ወይበዝኅ ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ። ትኩላን እሙንቱ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር"። መዝ 91፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 10፥1-14፣ ራዕ ዮሐ 14፥1-6 እና የሐዋ ሥራ 4፥19-31። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 12፥1-32። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም ለቅዱስ ሰርጊስ፣ አባ አውማንዮስ የዕረፍት በዓል፣ የማኅሌተ ጽጌ ሦስተኛ ሳምንትና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

https://t.me/saint_mikael

2,872

subscribers

2,870

photos

39

videos