ዜና ቤተክርስቲያን

@zenatewahedo16


የተለያዩ በቅድስት በቤተክርስቲያን ዙሪያ መነሻ ያደረጉ ዜናዎችን ከቤተክርስቲያን ልሳናት ከሆኑ ምንጮች በማቅርብ መረጃ መለዋወጥ።

ዜና ቤተክርስቲያን

21 Jan, 00:01


https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:58


ማርያም ሆይ፣ አንቺ ብቻ "ልጄ ጌታዬ" ከምትይው፣ አንቺ ብቻ "እናቱ" ከምትባይ፣ "ጌታን ትወልጃለሽ" ስትባዪ "እነሆኝ የጌታ ባሪያ" ባስባለሽ ትህትና ባርኪን። ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ምህረትንና እና ይቅርታን ለምኝልን። ጸሎታችንን አሳርጊልን። 🙏🏿

"አሟሟትሽ በጥር
ነሀሴ መቃብር"

እንኳን አደረሰን!

❤️

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:58


እንኳን ለመስቀሉ ሥር ስጦታችን፣ ለእናታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም፣ ለወላዲተ አምላክ፣ ለኪዳነ ምህረት በዓል በሰላም አደረሰን!

"ኪዳነ ምህረት እመቤት እመቤት
ነይልን ነይልን ካለንበት፤

ከሰማያት በላይ ካለው ከማደሪያሽ
ዝማሬ ከሞላው ከዘላለም ቤትሽ
የምድር ፍጥረታት ማርያም ማርያም ሲሉሽ
የቃል እናት እመቤቴ ነይ በሰረገላሽ"

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:53


ደብረ ታቦር የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ነች፤ ከብሉይና ከሐዲስ ሰብስባለችና፡፡ ከብሉይ ኪዳን ነቢያት ሙሴና ኤልያስን ከሐዲስ ኪዳን ሐዋርያት ጴጥሮስን ያዕቆብን፣ ዮሐንስን ከመምህራቸው ከክርስቶስ ጋር ሰብስባለችና፡፡ ቤተ ክርስቲያን በነቢያትና በሐዋርያት መሠረትነት ላይ ተመሥርታለች “እስመ ተሐነጽክሙ ዲበ መሠረተ ነቢያት ወሐዋርያት እንዘ ክርስቶስ ርዕሰ ማዕዘንተ ሕንጻ” “በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፤ የማዕዘኑም ራስ ደንጋይ ክርስቶስ ነው” እንዲል፡፡
ኤፌ. 2፥20
የታቦር ተራራ
፩. የቤተ ክርስቲያን
፪. የወንጌል
፫. የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው፡፡

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:44


እመቤታችን ሆይ የዐሥራት አገርሽን ኢትዮጵያን አስቢአት፥በረድኤትሽ ጎብኚአት።

የነሐሴ ፮ ምስባክ ዘነግህ፤
“ይትፌሥሓ አድባረ ጽዮን፥
ወይትሓሰያ አዋልደ ይሁዳ፥
በእንተ ፍትሕከ እግዚኦ።”መዝ፡፵፯፥፲፩።

ቅዱስ ዳዊት በመዝሙረ ትንቢት፡-፩ኛ:-“የጽዮን ተራሮች ደስ ይላቸዋል፤(ልዑላኑ ታላላቆቹ ደስ ይላቸዋል)፤” ፪ኛ:-“የይሁዳም ሴቶች ልጆች ሐሴት ያደርጋሉ፤(ትሑታኑ ታናናሾቹ ደስ ይላቸዋል)፤” ፫ኛ:-“አቤቱ ስለ ፍርድህ፤(አሕዛብን ፈርደህ ስላጠፋህ፥ እነርሱን ደግሞ በፍርድህ ስላዳንሃቸው ታላላቆችም ታናናሾችም ደስታን ይጎናጸፋሉ)፤”ብሏል።

ዛሬስ እግዚአብሔር ፈርዶ ኢትዮጵያን እና ቤተ ክርስቲያንን የሚያድናቸው መቼ ነው? ይህ ደሙም እንባውም እየፈሰሰ ያለ ሕዝብ ፍስሐ ወሐሴት የሚያደርገው መቼ ነው? እባክህ እግዚአብሔር ሆይ ስለ ድንግል ማርያም ብለህ ቀኑን ቅርብ አድርገው።
“እንግዲህ እግዚአብሔር በመዓልትና በሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለወዳጆቹ አይፈርድምን? ወይስ ቸል ይላቸዋልን? እላችኋለሁ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል።”ያለ ጌታ እግዚአብሔር ፍርዱ አይዘገይም።ሉቃ:፲፰፥፯። የእግዚአብሔር ቸርነት፥የድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን፥አሜን።

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:35


‹‹ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ፣ ተፈሥሒ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር፡- ምልእተ ጸጋ ሆይ ደስ ይበልሽ፤ በእግዚአብሔ ዘንድ ሞገስን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ››
(ሉቃ. 1÷28-30")

እንኳን ለጾመ ፍልሰታ አደረሰን!
#ፍልሰታ #ማርያም
በዚህች ጾም ጊዜ ፈቅዶላችሁ በማስቀደስ የምታሳልፉ አልያም ሳትችሉ በሥራና ትምህርት እያሰባችኋት የምታሳልፉ መልካሙን ጊዜ እየተመኘን ባላችሁበት ቦታ ቀጥታ የሚሰራጩ መርሀግብሮችን ተከታተሉ።

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:29


እንኳን አደረሳችሁ
ጻዲቁ አቡነ ሐብተ ማርያም ሆይ እኛ ልጆችህን ከክፉ ሁሉ ጠብቀን ወጥቶ ከመቅሰፍት ሰዉረን

እናት ሀገራችንን ኢትዮጵያን በተሰጠህ ቃል ኪዳን ጠብቅልን

ከድንገተኛ ሞት ሰዉረን አሜን!!!

የጻድቁ አቡነ ሀብተ ማርያም በረከቱና ረድኤቱ አይለየን።

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:25


ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ

እንኳን ለሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ወርሃዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን !!!

⛪️ ገና ከልጅነቱ ጀምሮ በክርስትና ስርዓት ያደገው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ፳ ዓመት እድሜው የንጉሥ ዱድያኖስ ወታደር ሆኖ ሹመትን ሊቀበል ወደ ንጉሡ ሄደ

⛪️ ንጉሡም ክርስቲያኖችን ለጣኦት ካልሰገዳችሁ ብሎ ሲያሰቃይ አይቶ ንጉሡን ተቃወመ፣ ማዕረጉንም ተወ

⛪️ ለክርስቶስም ታምኖ የጣኦት አሰራርን መቃወም ጀመረ፤ ያለውንም ንብረት ሸጦ ለድሆች አካፈለ

⛪️ ዓለማዊውን መንግሥት ንቆ ለክርስቶስ በተገዛው በቅዱስ ጊዮርጊስ ድርጊት የተበሳጨው ንጉሥም ሊያባብለው ሞከረ፤ ግን አልተሳካለትም

⛪️ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስም እስከ ሰማዕትነት ጊዜው ድረስ በአምላኩ ታምኖ ጣኦት አምላኪዎችን እየተቃወመ አምላኩም በርሱ ድንቅ እያደረገ ኖረ

የትውልድ ዘመን ጥር ፪ ፪፻፸፭ /275/

የትውልድ ቦታ ቀጰዶቂያ

የአባት ስም አንስጣስዮስ

የእናት ስም ቴዎብስታ

ሥራ ክርስቲያን፣ ሰማዕት

የንግሥ በዓል ሚያዝያ ፳፫

ታዋቂ ገዳም ደብረ ጽጌ ቅዱስ
ጊዮርጊስ ቤ/ያን

የእረፍት ቀን ሚያዝያ ፳፫

የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎትና በረከት ከእኛ ጋር ይሁን። ምልጃው ዘወትር አይለየን።

#አንዲት_ቤተክርስቲያን
#አንድ_ሲኖዶስ
#አንድ_ፓትርያርክ
#አንዲት_ጥምቀት
#ተዋህዶ
#orthodoxchurch
#ኢትዮጵያ

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:23


እንኳን አደረሳችሁ ከቅዱስ ኡራኤል ከቅዱስ ሉቃስ ከቅዱስ ያዕቆብ ምስራቃዊ ርድኤት በረከት ይክፈለን በምልጃቸው ይጠብቁን አሜን::

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:18


ጸሎታችሁን ቅዱስ ገብርኤል ይስማ!

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:18


ህጻን ወእሙ ክልኤሆሙ ፈጸሙ ገድሎሙ!

የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት፣ የቅድስት ኢየሉጣ እና የቅዱስ ቂርቆስ ጸሎታቸው፣ ምልጃቸው ይጠብቀን፡፡ 🙏🙏🙏

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:16


ሰላም ለእስትንፋስኪ ዘመዓዛሁ ሕይወት
ከመ መዓዛ ዕፅ ኅሩይ ዘውስተ ገነት
ማርያም ድንግል ቤተ ቅድሳት
ጽንሕኒ ውስተ ሠናይ ወሰውርኒ እሞት
በአክናፍኪ ርግብየ ኅሪት ❤️ 🙏🏿

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:09


ጠብቆ አሳድጎ ከልጅነቴ
አባት እየሆነኝ ሚካኤል አባቴ
ይለይብኛል ሚካኤል ይለይብኛል
በክንፋ ሸፍኖ በቤቱ አሳድጎኛል
#ቅዱስ ሚካኤል አባቴ
እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን
ቅዱስ ሚካኤል ከክፋ ነገር ይጠብቀን።
1️⃣2️⃣

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 22:02


👉ዛሬ ሐምሌ 7 ቅድስት ሥላሴ ለአብርሃም የተገለጡበት የይስሐቅንም መወለድ የአበሠሩበት፡ በቤቱም የተስተናገዱበት ዕለት ነው፡፡ እንኳን አደረሳችሁ "ሀገራችንን ከጥፋት፡ህዝባችንን ከስደት ከሞት ይታደጉልን።🙏🥰

ቅድስት ሥላሴ በዕለተ ቀናቸው ያላሰብነውን ደስታ ይስጡን፡ መልካም እለተ ሰንበት ይሁንልን።🙏

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 21:31


በዓለ ጰራቅሊጦስ፤

ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ይህቺን ቅድስት ዕለት የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን ናት ብሏታል። እውነት ነው፥ቤተ ክርስቲያን በቀራንዮ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ላይ ስትመሠረት ተፀነሰች፥ የጰራቅሊጦስ ዕለት ተወለደች፥ምክንያቱም በዚያች ዕለት ሁሉም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ተሰጥቶአት ምሉዐ ጸጋ ሆናለችና ነው።ይህንንም በጥምቀት ለተወለዱ፥በሜሮን ለከበሩ፥በሥጋ ወደሙ ለታተሙ ልጆቿ ስታድል ትኖራለች።

የተሰጠንን ጸጋ ያጽናልን፥በጸጋ ላይ ጸጋ ይጨምርልን።

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 21:26


#ከድርሳነ #ሚካኤል #ዘሰኔ

በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነን በባሕርይ በህልውና አንድ አምላክ ብለን ክብር ምስጋና ይግባውና በዛሬው ዕለት እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤልን በወገኖቹ በመላእክት ሁሉ ላይ ከክብሩና ከገናንነቱ ጋራ እንደሾመው እንናገራለን።

ንዑድ ክቡር የሚሆን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል ተአምራቱ ብዙ የብዙ ብዙ ነውና ስለዚህ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በየወሩ በአሥራ ሁለት ቀን እናከብር ዘንድ አዘውናል ጸሎቱና በረከቱ ከኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።

ምንጭ፦
ድርሳነ ሚካኤል ዘሰኔ ቁጥር 133-134

"ይህም የከበረ መልአክ ክብር ይግባውና በጌታችን ፊት ስለ ሰው ልጆችና ስለ ፍጥረትም ሁሉ ይለምናል ይማልዳልም"
- ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ ቁጥር ፲

👉"ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል" ዳን. 12፥1

👉"ማኑሄም የእግዚአብሔርን መልአክ፦ ነገርህ በደረሰ ጊዜ እንድናከብርህ ስምህ ማን ነው? አለው። የእግዚአብሔርም መልአክ። ስሜ ድንቅ ነውና ለምን ትጠይቃለህ? አለው።" መሳ. 13፥17-18

👉"ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ" ዘፍ. 48፥16

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 21:18


ለበዓለ ዕርገቱ እንኳን አደረሳችሁ
+++++
"ወበዕርገቱ ጼሐ ለነ ፍኖተ ሰማያት ወአርኀወ ለነ ኆኀተ ሰማይ::"

ትርጉም፦
"በዕርገቱም የሰማያትን ጎዳና ጠረገልን የሰማይንም ደጅ ከፈተልን::" (ድርሳነ ማሕየዊ)
++++

"ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ። በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤ ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ። ወደ ምሄድበትም ታውቃላችሁ፥ መንገዱንም ታውቃላችሁ።"
(ዮሐ. 14፥1)

ዜና ቤተክርስቲያን

20 Jan, 21:13


ከበዓታ ለማርያም በረከት ረድኤት ይክፈለን።

ከቤተ መንግሥቱ ግቢ ውስጥ ያለሽ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም:-ለሀገራችን ቅን መሪ፥ለቤተ ክርስቲ ያናችን ቅን አገልጋይ አድዪን።በአማላጅነትሽ ኢትዮጵያ አገራችንን፥ተዋህዶ ሃይማኖታችንን ከነደደ እሳት አውጪልን፥የመከራውን ዘመን አሳጥሪልን።

1,560

subscribers

293

photos

16

videos