መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

@meazahaymanot


"ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት ወስብሕት በሐዋርያት አክሊለ በረከቱ ለያዕቆብ ወትምክህተ ቤቱ ለእስራኤል፡፡"

"በነቢያት በሐዋርያት አንደበት የተመሰገንሽ የያዕቆብ የበረከቱ ዘውድ የእስራኤል ወገን መመኪያ አንቺ ነሽ"
                 መጽሐፈ ሰዓታት

የፌስቡክ ፔጃችን www.fb.me/meazhaimanot ይቀላቀሉን

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

18 Oct, 12:21


http://youtube.com/post/UgkxRoDzJJtb21vCSpGOG_vfC26YjOTJVP1x?si=xDLs-kp5He4m5TQm

ይመልከቱን

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

13 Oct, 16:11


https://youtu.be/NOZ82CWHPp0?si=U_EQiVMgGDHKxQUg

ጸልዩ

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

11 Oct, 11:49


https://youtu.be/NeXqMChlBOY?si=A_9YPJAt4pXqoJy0

ይመልከቱ

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

05 Oct, 07:02


ክቡራን የቻናላችን አባላት በሎጎ ላይ ጥያቄ ካላችሁ የሚመልስላችሁ pdf ነው

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

05 Oct, 05:32


http://youtube.com/post/UgkxQUbhKJLMC_vNKvlXs1ar-wQvsYWtV1P1?si=TdK8TR6VkJ-AZMsW

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

04 Oct, 17:24


ክቡራን የቻናላችን ተከታታዮች እንዴት አመሻችሁ የቀድሞ የገፃችን ሎጎ በይፋ በዚህ መልክ ተቀይሯል

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

04 Oct, 17:23


Channel photo updated

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

03 Oct, 06:11


🕯🌹ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም ፳፫🕯🌹

🕯🌹አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መስከረም ሃያ ሦስት በዚች ቀን ቅዱሳን ጻድቃን መነኰሳት አውናብዮስና እንድርያስ በሰማዕትነት አረፉ ። እሊህ ቅዱሳንም ከልዳ ሀገር ከታላላቆቹ ተወላጆች ናቸው ከታናሽነታቸውም በአምላካዊ ምክር ተስማምተው በሶርያ ውስጥ ከሚገኙ ገዳማት ወዳንዱ ገዳም ሒደው መነኰሳት ሆኑ ።

🕯🌹ዳግመኛም በዚችም ቀን የሰማዕት ኤዎስጣቴዎስ መታሰቢያው ነው በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።

🕯🌹መስከረም ፳፫ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት🕯🌹

🕯ቅዱሳን ጻድቃን አውናብዮስ ወእንድርያስ (ሰማዕታት)
🕯ቅዱስ ጐርጐርዮስ መንክራዊ
🕯ቅድስት ቴክላ ድንግል
🕯ቅዱስ ኤዎስጣቴዎስ ሰማዕት


     🕯🌹ወርኀዊ በዓላት🕯🌹

🕯ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት
🕯ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
🕯ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ሰሎሞን (ንጉሠ እሥራኤል)
🕯አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
🕯ቅዱስ ዳንኤል ነቢይ
🕯አባ ሳሙኤል
🕯አባ ስምዖን
🕯አባ ገብርኤል

🕯🌹በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኩዋ መከራን ብትቀበሉ ብጹዓን ናችሁ ። ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ: አትናወጡም ። ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት ። (፩ኛ ጴጥ.፫ ÷፲፫ )

   ፍኖተ ቅዱሳን ሰንበት ትምህርት ቤት

https://t.me/fkteklehaymanot

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

02 Oct, 19:01


https://youtube.com/shorts/h4qnZsnyv8c?si=WyXmduMYfrl2SB3f

እስከ መጨረሻ እንመልከት

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

01 Oct, 05:45


🕯🌹ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም ፳፩🕯

🕯አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መስከረም ሃያ አንድ በዚች ቀን አምላክን የወለደች የቅድስት ድንግል እምቤታችን ማርያም የበዓሏ መታሰቢያ ነው ። ሁላችንም የአዳም ልጆች እስከ ዓለም ፍጻሜ የበዓሏን መታሰቢያ በየወሩ ልናደርግ ይገባናል የእግዚአብሔር ልጅ ከእርሷ ሰው በመሆኑ ከጠላታችን ሰይጣን እጅ ድኅነታችን በእርሷ ተደርጎልናልና እርሷም ስለእኛ ሁል ጊዜ ትማልዳለችና ።

የምታድን እርሷን እናቱን ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን ።🙏

🕯 ዳግመኛም በዚችም ቀን ሃይማኖታቸው የቀና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት ጳጳሳት ስብሰባ በኒቅያ ከተማ ተደረገ በረከታቸው ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።🙏

🕯🌹መስከረም ፳፩ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

🕯ቅድስት ግሼን ደብረ ከርቤ
🕯ብዙኃን ማርያም
🕯"፫፲፰ቱ" ቅዱሳን ሊቃውንት
🕯ቅዱስ ቆዽርያኖስ ሰማዕት
🕯ቅድስት ዮስቴና ድንግል
🕯ቅዱስ ጢባርዮስ ሐዋርያ

🕯🌹ወርኀዊ በዓላት

🕯ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም ወላዲተ አምላክ
🕯አበው ጎርጎርዮሳት
🕯አቡነ ምዕመነ ድንግል
🕯አቡነ አምደ ሥላሴ
🕯አባ አሮን ሶርያዊ
🕯አባ መርትያኖስ ጻድቅ

🕯🌹እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል ። ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ይላል ። እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ ። ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ። ከእናንተም ይሸሻል ። ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ። ወደ እናንተም ይቀርባል ። (ያዕ ፬÷፮)

🕯🌹 ለእግዚአብሔር መሆን ስጋና ይሁን እኛንም በቄዱሳኑ ጸሎት የሚሉ ማረን በቃልኪዳናቸውም ይጠብቀን ለዘላለሙ አሜን። 🙏🙏

🌹ፍኖተ ቅዱሳን ሰንበት ትምህርት ቤት

https://t.me/fkteklehaymanot

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

29 Sep, 08:22


መላአኩ ቅዱስ ገብርኤል
መስከረም 19#
ገድል ድርሳን ስንክሳር




የመላአኩ ቅዱስ ገብረርኤል ምልጃ ጠብቃዉ አይለየን

🕯🕯🕯🕯🕯

=========

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

26 Sep, 09:53


https://t.me/fkteklehaymanot

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

26 Sep, 04:31


ኢየሩሳሌም በየጊዜው ከጦርነት ከምርኮ ያላረፈች ሃገር በመሆኗ ቅዱስ መስቀልን በአሕዛብ እጅ እየተማረከ ቅዱስ ካንዱ ወዳንዱ መዘዋወሩ አልቀረም ነበር፡፡ የክርስቲያን ነገሥታትም በዚህ ነገር እየተናደዱ እየተቆጡ ጦራቸውን መስቀል ወደ ሔደበት ቦታ ሁሉ ከማዝመት አልተገዙም፡፡ ከዚህም በዋናነት የሚጠቀሰው የሮም ንጉሥ ሕርቃል ነው፡፡ ሕርቃል በተንባላት ተማርኮ ወደ ፋርስ /ኢራቅ/ የሔደውን መስቀል በጦርነት አስመልሷል፡፡ የመስቀል ዘመቻና ጦርነት እየተባለ ብዙ ክርስቲያን ደም ፈሶበታል፡፡

ደመራ
ደመረ፣ ጨመረ፣ አንድ አደረገ፤ ከሚለው የግእዝ ቃል የተወረሰ ሲሆን መቀላቀልን፣ መገናኘትን፣ መሰብሰብን፣ መጣመርን፣ መዋሐድን በአጠቃላይ ሱታፌን፣ አንድነትን እና ኅብረትን ያመለክታል፡፡ የጌታችን ቅዱስ መስቀል በማያምኑበት አይሁድ ለሦስት መቶ ዓመታት ያህል እንዳይገኝ ተደርጎ ከተቀበረ በኋላ በዕሌኒ ንግሥት ፍለጋ በደመራው የዕጣን ጢስ ስግደት የተደበቀበት ስፍራ ተለይቶ መስከረም 17 ቀን ቁፋሮ ተጀምሮ መጋቢት 10 ቀን ከተቀበረበት ወጥቷል፡፡ ቅዱስ መስቀሉ በተገኘበት ቦታም በንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዕብነ መሠረት ተቀምጦ መስከረም 16 ቀን ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል፤ ስለሆነም ደመራ ዕንጨቶች የሚደመሩበት የበዓለ መስቀል ዋዜማ ነው፡፡

መልካም የደመራና የመስቀል በዓል ይሁንላችሁ

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

26 Sep, 04:31


በዓለ መስቀል

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ዐበይት እና ንዑሳን በዓላት መካከል አንዱ በዓለ መስቀል ነው፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በወርኃ መስከረም ብቻ በዓለ መስቀልን አራት ጊዜ ታከብራለች፡፡ የመጀመሪያው ምክንያተ ክብረ በዓል፣ በኢትዮጵያ ነግሦ የነበረው ዓፄ ዳዊት ከግብፅ ንጉሥና ሊቃነጳጳሳት የተላከለትን በቅዱስ ሉቃስ እጅ የተሳለችውን ስዕለ ማርያምን፣ በወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የተሳለውን ኩርዓተ ርእሱን ፣ ሌሎች ንዋያተ ቅድሳትን እና የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ግማደ መስቀል የግብፅ እና ኢትዮጵያ ድንበር ከነበረችው አስዋን ከተባለችው ቦታ ተረክቧል፡፡

ንጉሡ የያዘውን በረከት ወደኢትዮጵያ ሳያደርስ ስናር በተባለው ቦታ ዐረፈ፡፡ ከጊዜ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዳግማዊ ቆስጠንጢኖስ የተባለው ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ተቀብሎ በደብረ ብርሃን፣ በየረር፣ በመናገሻ እና በልዩ ልዩ ተራራማ ቦታዎች ሲዘዋወር ቆይቶ “መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ አኑር” የሚል ራእይ ተገልጦለት ቅዱስ መስቀሉን በወሎ ክፍለ ሀገር በአምባሰል አውራጃ በግሸን ደብረ ከርቤ አስቀምጦታል፡፡ መጋቢት ዐሥር ቀን ደብረ ብርሃን ሲገባ ብርሃን ስለወረደና ዐፄ ዳዊት ከግብፃውያን ጳጳሳት እና ንጉሥ እጅ መስቀሉን የተረከቡበትን ቀን በማዘከር የአድባራት እና የገዳማት ሊቃውንት ልብሰ ተክህኖአቸውን ለብሰው የብር መቋሚያ እና ጸናጽል ይዘው ወደ ነገሥታቱ ሔደው ተቀጸል ጽጌ እያሉ እያሸበሸቡ ጸሎተ ወንጌል ያደርሱ ስለነበር መስከረም ዐሥር ቀን የዓፄ መስቀል በዓል ተብሎ ይከበራል
መስቀሉ እንዴት ተገኘ?

አይሁድ መድኃኔዓለም እውር አበራ፣ ለምጽ አነጻ፣ አጋንንት አወጣ፣ ሙታንን አስነሳ፣ በሽተኞችን ፈወሰ፣ ብለው በሰይጣናዊ ቅንዓት ሰቅለው ከገደሉት በኋላ ከሙታን ተለይቶ መነሳቱ ሲገርማቸው የተሰቀለበት ቅዱስ መስቀል ዕውር ሲያበራ፣ ሙት ሲያስነሳ፣ ልዩ ልዩ ደዌያትን ሲፈውስ አይተው የክርስቶስ መስቀል እንዲቀበርና ደብዛው እንዲጠፋ 300 ዓመታት ያህል በከርሠ ምድር ቀበሩት፡፡ አይሁድ የክርስቶስን መስቀል ለማጥፋት በጉድጓድ ጥለው የኢየሩሳሌም ነዋሪ ሁሉ ጉድፍ እንዲጥሉበት አደረጉ፡፡ ማንኛውም ቤተሰብ የቤቱን ጥራጊ እያመጣ መቃብሩ ላይ እንዲቆለል ተደረጎ ጥራጊ ሲጣልበት በመኖሩ ቦታው ኮረብታ ሆኖ ነበር፡፡ ምንም እንኳ ለማውጣት ባይችሉ ክርስቲያኖቹ ቦታውን ያውቁት ነበር፡፡ ከጊዜ በኋላ ጀኔራሎች በአስቫስያንና ጥጦስ ወረራ በ70 ዓ.ም ክርስቲያኖቹ ኢየሩሳሌምን ለቀው ስለወጡ መስቀሉ የተቀበረበት ቦታ ወዴት እንደሆነ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ዕሌኒ ንግሥት ልጇ ቆስጠንጢኖስ የክርስትና እምነት ፍቅርና ተቆርቋሪነቱ ቢኖረውም ገና አልተጠመቀም ነበርና አምኖ ተጠምቆ ወደ ክርስትና ሃይማኖት የገባልኝ እንደሆነ ወደ ኢየሩሳሌም ሄጄ የፈረሱትን አብያተ ክርስቲያናት አሳንፃለህ የተቀበረውን ቅዱስ መስቀሉን ፍለጋ አስፈላጊውን ሁሉ ራሴ አሟላለሁ ስትል ብፅዕት አድርጋ ስለነበር በአራተኛው መ/ክ/ዘ 337 ዓ.ም ከብዙ ሠራዊት እና መኳንንት ጋር ሆና ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች፡፡

ልጅዋ ቆስጠንጢኖስ ቅዱስ መስቀልን ከተቀበረበት ለማውጣት አስቦ ስለነበር እናቱ ከመንፈሳዊ ሃሳቡ ጋር በመተባበሩዋና ቅዱስ መስቀልን ለማስወጣት የነበሩትን ብፅዓት ለመፈጸም በማሰብ ተደሰቱ፡፡ አስቀድማ ሂዳ መስቀል ያለበትን ስፍራ እንድታጠና ሠራዊት ገንዘብ አሲዞ ላካት ዕሌኒም ኢየሩሳሌም ደርሳ ኮረብታ የሆነውን ሁሉ ብታስቆፍርም መስቀሉ ያለበትን ማግኘት አልቻለችም፡፡ የአይሁድ ሕዝብ ሁሉ የጎልጎታን ተራራ እንዲጠርጉ አዘዘች፡፡ በምንም ሁኔታ መስቀሉ ሊገኝ አልቻለም፡፡ ከነሐሴ ወር ጀምራ ምሕላ ያዘች፣ ሱባኤ ገባች፡፡ ጊዮርጊስ ወልድ አሚድ ዕሌኒ ንግሥት ወደ ኢየሩሳሌም ሄዳ ኤጲስ ቆጶስ አባ መቃርስን አገኘችውና መስቀሉ የተቀበረበት ስፍራ ጠየቀችው አባ መቃርስም ከሃዲዎቹ በላይ ብዙ አፈር አፍሰውበታል አፈሩም ትልቅ ተራራ አስከ መሆን ደርሷል ብሎ አስረዳት ይላል፡፡ ኪራኮስ የተባለም ሽማግሌ ወደ ንግሥቲቱ ቀርቦ መስቀሉ ያለበት ስፍራ ቀራንዮ መሆኑን አባቴ ነግሮኛል ተራራው ያ ነው፡፡ ብሎ ጎልጎታን አመልክቷል፡፡ በያዘችው ሱባኤ መልአከ እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ መስቀሉን በእጣን ጢስ ታገኚዋለሽ ብሎ ነግሮአት ስለነበር ኅሊናዋ አልተጠራጠረም፡፡

የመላእኩንና የሽማግሌውን ቃል መሠረት አድርጋ በምድረ ይሁዳና ኢየሩሳሌም የነበሩትን ሕዝብ በጎልጎታ የሚደመር እንጨት እየያዛችሁ ኑ ብላ አዘዘቻቸው፡፡ መስከረም 16 ቀን ከየመንደራቸው እንጨት እየያዙ በጎለጎታ ተራራ ልይ ተደመሩ፡፡ ተደመሩትም እንጨቶች በእሳት አስለኮሰች፡፡ ብዙ ጊዜም የዕጣኑ ጢስ በተአምራት ከላይ ወደ ታች ተመልሶ መስቀሉ በተቀበረበት ሥፍራ ላይ ተተክሎ ታየ፡፡ የኢትዮጵያ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዕጣን የመስቀልን ሥፍራ አመለከተ፣ ጢስም ለመስቀሉ ሰገደ እያለ የዘመረው ለዚህ ነው፡፡ /ምዕራፍ ዘአርያም/ ንግሥት ዕሌኒ የዕጣን ጢስ ያመለከተውን ስፍራ ወዲያው መስከረም 16 ቀን ማስቆፈር ጀመረች፡፡ በብዙ ድካም በብዙ ጥረት በተፋጠነ ቁፋሮ መስቀሉ መጋቢት 10 ቀን ተገኘ
ንግሥት ዕሌኒ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀልና ሁለቱ ወንወበዴዎች ጥጦስና ዳክርስ የተሰቀሉባቸው መስቀሎች በተገኘ ጊዜ ከእነዚህ ሁለቱ መስቀሎች ጌታችን የተሰቀለበት ቅዱስ መስቀል በምንአውቀዋለሁ ብላ ለኤጲስ ቆጶስ አባ መቃርስን ጠየቀችው አባ መቃርስም የጌታ መስቀል እንደ ልማዱ ሙት ላይ ሲያኖሩት ሙት ያስነሳልና በዚህ ለይተሽ ታውዋለሽ ብሎ ምልክት ነገራት፡፡ ወዲያው የጌታ መስቀል ሙት ላይ ቢያኖሩት ሙት ማስነሳቱ፣ ደዌ ቢያቀርቡለት ፈወሰ፡፡ ይህ የጌታችን የኢየሱስ መስቀል ብለው አመኑ፡፡ መስቀል እንዲው ችቦ አብርተው አበባ ይዘው እንዲህ አበራ፣ እንዲህም አበበ አብቦም ፍሬ ክብርን አፈራ እያሉ አሸበሸቡ፡፡

የምስራችንም የቆስጠንጢኖስ ዙፋን እስከነበረበት ቆስጠንጢንያ ድረስ አስተላለፈ፡፡ ከኢየሩሳሌም እስከ ቆስጠንጢኖስ ድረስ አስተላለፈ፡፡ ከኢየሩሳሌም እስከ ቆስጠንጢኖስ ድረስ የነበሩ ሕዝቦች ችቦ በማብራት በየደጁ ተሰብስቦ የደመራ እሳት ወጋገን በማሳየት አበባ ይዞ በመዘመር እልል በማለት ደስታውን በሕብረት ገለጡ፡፡

ዕሌኒ ንግሥት የጌታን መስቀል በማግኘቷ ስለተደሰተች ጌታ በተወለደበት ቤቴልሔም ጌታ በተቀበረበት ጎለጎታ ላይ አብያተ ክርስቲያናት ማሳነጽ ጀመረች፡፡ በዕንቍ በወርቅ በብር አስጌጠች አሠራች፡፡ ቆስጠንጢኖስም በገንዘብና በንዋየ ቅድሳት ረዳት፡፡ ቅዳሴ ቤተክርስቲያኑ መስከረም 17 ቀን የእስክንድርያ፣ የአንጾኪያ፣ የቆስጥንጥንያ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ኤጵስ ቆጶሳት መጥተው በዋዜማው መስቀል 16 ቀን ባረኩ፡፡ ቅዳሴ ቤቱንም አከበሩ፡፡ መስቀል ጥንዓ ይዘው ቅዱሳት መካናት ሁሉ ዞሩ ሥርዓተ ዑደት አደረጉ፡፡ የዕጣን ጢስ አመልክቶ ቁፈራ የተጀመረበትና ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት አንድ ዕለት ሆነ በዚህም ዕለት ሆነ በዚያም ዕለት የዓለም ሕዝብ ክርስቲያን በኢየሩሳሌም
እየተሰበሰቡ በዓሉን በድምቀት ያከብሩት ነበር፡፡ ይህም መስቀል በኢየሩሳሌም ካስቀመጠችው በኋላ ዘረፉና ምርኮ አጋጥሟታል፡፡

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

24 Sep, 14:56


https://youtu.be/SC_hUYx0nKI?si=udJGNb4xawuF5hyz

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

22 Sep, 18:54


ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን እንዴት አመሻችሁ ከማኅበሩ ጋር ማገልገል የሚፈልግ በposteru lay balew link በውስጥ ያውሩን

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

22 Sep, 15:51


በአንድ ወቅት አንድ መንፈሳዊ አባት ከነበሩበት ቦታ ወደ በረሃ መሰደድ ግድ ሆነባቸው። ከቅዱስ መጽሐፋቸው ሌላ ሦስት ነገሮች ነበሯቸው።

እነሱም፦ ቅዱስ መጽሐፉን በጨለማ ወቅት ለማንበብ የሚጠቅማቸው ኩራዝ ፣ጎህ ከመቅደዱ በፊት ከእንቅልፍ የሚቀሰቅሳቸው አንድ አውራ ዶሮ እና ለመጓጓዣነት የሚገለገሉበት አንድ አህያ ነበሩ።

አንድ ቀን ምሽት ከጉዞ የተነሣ በጣም ስለ ደከሙ እኚህ መንፈሳዊ አባት ወደ አንድ መንደር ቀርበው ማደሪያ ቢጠይቁም መንደርተኛው ፈቃደኛ ባለመሆኑ ማንም አላሳደራቸውም። ስለዚህም ከመንደሩ አቅራቢያ አንድ ጉድጓድ ያገኙና በዚያ ውስጥ ገብቶ ለማደር በመወሰን ገብተው አደሩ። እንደ ወትሮው ቅዱስ መጽሐፋቸውን ለማንበብ ኩራዛቸውን ቢለኩሱትም የነበረው ብርቱ ነፋስ አጠፋባቸው።

ስለዚህም ለመተኛት ጋደም እንዳሉ ተኩላ መጥቶ አውራ ዶሮዋቸውን፣ አንበሳም አህያቸውን በሉባቸው። የተደራረበ ጉዳት ስለደረሰባቸው ሽማግሌው እርዳታን በመሻት ወደዚያ መንደር ቢመለሱ ዘራፊ ሽፍታዎች የመንደሩን ነዋሪዎች በሙሉ ገድለው ንብረት ዘርፈው ዖና መንደር ሆኖ አገኙት።

ሽማግሌው ይህን ሁሉ ባጤኑ ጊዜ እግዚአብሔር ምን ያህል መልካም ነገርን እንዳደረገላቸው አስተዋሉ። በዚያች ምሽት በመንደርተኞቹ በአንዱ ቤት ቢያድሩ ኖሮ የዘራፊዎች ሰለባ ሆነው ሊገደሉ በቻሉ ነበር። ቀንዲላቸውንም ነፋስ ባያጠፋው የብርሃኑ ወጋገን እዚህ ጋር ሰው አለ በማለት ለሽፍታዎቹ ያሳብቅ ነበር። አውራ ዶሮአቸውና አህያቸውም ባይበሉ ኖሮ ከሽፍታዎቹ ተደብቀው ማደር ባልቻሉ ነበር።” እግዚአብሔር ከክፉ ነገሮች ውስጥ መልካም ነገር ማውጣት የሚችል አምላክ ነው።"

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ስለዚህ እንዲህ በሉ፦ "የሚደርስብኝ ፤ የሚገጥመኝ ፈተናና መከራ ሁሉ አምላኬ ሆይ ለበጎ ታደርግልኛለህና አመሰግንሐለሁ" አሜን

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

19 Sep, 16:38


ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን የመዓዛ ሃይማኖት ቻናል  አባላቶች እንዴት  ናችሁ ይኸን ቪዲዮ ያለየ ካለ ለ 4ደቂቃ በቅንነት ቢያይና አገልግሎቱን ቢደግፍ መልካም ነው

ሼር በማድረግ እናዳርስ

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

18 Sep, 20:28


https://youtube.com/shorts/iuWDPJmSRIc?feature=share

እስከ መጨረሻ ይመልከቱ

መዓዛ ሃይማኖት በጎ አድራጎትና ጉዞ ማህበር

18 Sep, 10:33


https://youtube.com/shorts/NVKb2A13DdE?si=BJDpiuSOVZoi6LkC

3 ደቂቃ

4,239

subscribers

992

photos

24

videos