ሼፉ ቁጥር ፩
"…ቀሲስ ነዋይ ግን ከምር በጣም ተሳስተሃልና ታረም። ደግሞም አትሟገተኝ። እኔ ቀደም ብዬ ከብፁዕነታቸው ስለተማርኩ ነው ሳልመን በሁለት ዓይነት ነው የሚሠራው ያልኩህ። አንተ እንጂ አንተ ካላወቅክ አላወቅኩም ይባላል እንጂ ስለ ምግብ አሠራር በዚህ መልኩ ልትከራከረኝ አይገባም። ቀሲስ ሱራፌል እንኳ አምሶሪ እኔ እንጀራ በሽሮ ብቻ ነው የማውቀው ማለቱ አቅሙን ዐውቆ ለመማር ዝግጁ መሆኑን ነው የሚያሳየው። ቀሲስ ሳሙኤል ድሮም የበሰለ መብላት እንጂ በምግብ አሠራር ላይ አልሟገትም ማለቱን ልታደንቅለት ይገባል። እናም ልብህን እልኸኛ አታድርግ፣ የምግብ አሠራር ለመማር እኮ እንደ እኔ በጣም ትእግስተኛ መሆንን ይጠይቃል። ከፈለግክ ቀሲስ ልዑልን ስለ እኔ ጠይቀው። ይነግርሃል።
"…ደግሞ ስለ ዋልድባ ቋርፍ የነገርኩህ ስለ አሜሪካ አባቶች አይደለም። አሜሪካ ቋርፍ ይበላ ቢባልስ ከየት መጥቶ ይበላል…? አንዳንዴ ሊብራል ዲሞክራት መሆን አለብን እንዴ? ብሎ ሱሬ የሚናገረው ባይገባኝም ሊብራል ግን ምድነው ቀሲስ? የሱሬ እንግሊዝኛ እኮ ለእኔ ከበድ፣ ጠጠር ነው የሚልብኝ።
"…ቀሲስ አሁን እኔ ልተኛ ነው። አንተ ጋር ግን ገና እየመሸ ስለሆነ የሰለሞን ዓሣን አሠራርን በደንብ ተመልከት። ከዚያ ነገ ስለ አበላሉ፣ ስለ አስተኛኘኩ፣ ስለ አፍ አከፋፈቱ፣ ስለ ገበታ ላይ ለምግብ እንደተራበ ሰው መስገብገቡ ከፈለግክ እንከራከራለን። ጳጳሳት በዚህ መልኩ ተስገብግበው ይበላሉ ወይ? አጎራረሳቸውስ እንደ ጎረምሳ መሆን አለበት ወይ? በአፋቸው፣ በጎንጫቸው ምግብ ሞልተው፣ እምጫ፣ እምጫ፣ እምጫ እያሉ እያኘኩ ማውራት ለተመልካች ይደብራል አይደብርም የሚለውን ነገ መከራከር እንችላለን። ዛሬ ግን የሰለሞን ዓሣ አሠራርን ልብ ብለህ ተመልከት። ከዳቤ እና ከቋርፍ ጋር ግን ማነጻፃሩ ነውር ይመስለኛል።
Guten Appetit.