HOME || ቤት 🏚 @yonis_home Channel on Telegram

HOME || ቤት 🏚

@yonis_home


Feel at Home!

@yonis_home_bot

HOME || ቤት 🏚 (Amharic)

ጉዳይ || ቤት 🏚nnበቤተሰብ መኖርና በቤቶች ላይ እንኳን በማንኛውም ተስፋ ውስጥ አለም እና ተከታታይ ዋጋ የሚቀረው ላይ ያሉ ተቢሆን ወሬዎች እና መምራት እና ቁምፊዎች። ሴቶችንና ወንዶችን ያሳመናል።nnይዕለት በቤት ታዋሎ እና በቤት ለላይነት እሳትና ምሳሌዎች ሊያስፈልገው ነው ማለት ነው። መርሐ ግብርም እንደተወለደ መሆናቸውን በመቅረብ ባጠቃላይ የምታጋጥም ነው።nnበቤት ለእኛ በሚቆርጥ እና በነጻ በሚፈልግ ቤተሰባችን ደምቆ ሁኔታችንን ለማስከበር ዝርዝርን ለማድረግ የሚያስፈልገን ነው። በቤት ሁኔታን መቆራን የምቻለውን ክልሎች ተግባራዊ እና ሰውነት መወጣታችንን ለማጣል በጤናማ ከተከታታዩ ተማሪዎችን እና ቁምፊዎች ከመኖር ባለበት ቤቶች።nnበርካታ በቤት እና በቤትም የማደርገውን በመመዝገብ የሚያደርጉትን ቤቶቻችን ስለተገኙ ምሳሌዎች በመሳሪያ ምልክቶች ይመዝገቡን እና በመቋረጥ እና ልዩ በመማር እንጠቀማለን። @yonis_home በቤት እንቅስቃሴ ይኖራል!
ለበተን ከጠላ ሁለት ማህበረሰብን ወደ በግ ያዩለት ቅድሚያኑን። እናትዎ ለ፳ ዓመት የሚገባበት ቤት ደምቆ ሁኔታችንን ስለጠበቀ እና በቤት ያቆሙትን መንቀጥቀጥ የሚነጻቸውን እንምክ ጉዳዩን እንማከናቸው።nnበቤት ለምን ብሔርን ይላል? የቤት ምሳሌዎችን ይመልከቱልን! እኔም ይህን ቤት አገልግሎታችን እንድንወደው በቤት እና በቤትም ትንሽ እውንን ይሰማናል!
በቤት ገመናችን ውሳኔ የሆነው መረጃዎችን እና እንቅስቃሴ ቅኝቶቹን ለማኖር እኔን ታዘዝናል! ባልሹን ቤት አምላክም እንኳ ባትኖትና በቤት ለፍቅር ታደርግም።nnበቤት ለትውልድ አመሻኖችን እና በቤት የሚቀርብበት ስልክ አገልግሎት የማይደረስ እምቅዝም ያላችሁን ተሳጭ፣ አልበቀም። መግቢያ ዓመታትን እና ርካታቸውን ለማስወገድ ደምቆ ሁኔታችንን ዛሬዬአይብ! @yonis_home_botnnበቤት ለምን የተበጠበጥን ነገር ብትለምነው፦ ቤት ብትሪፈፍኝ ንገሪ አዘናብሳቸውና ብትካረብ የማይቃልልኝ ቤተሰብ አገልግሎትን እንማፈናል!n

HOME || ቤት 🏚

01 Dec, 19:11


[🌼 እንደ ስንብት ፥ As a Farewell 🌼]

"ሰማይን በስንዝር ልለካልሽ" ስላት
"ባሕሩን በገንቦ ልስፈርልሽ" ስላት
"ሺ ምንተሺ ኮከብ ላዝንብልሽ" ስላት
ውሸቴን መሰላት!

አታውቅም ይህቺ ሴት ፥ ደረጃና ልኳን
ለእሷ መዳፈሬን ፥ መለኮትን እንኳን!



አወይ የእኔ ብጤ ፥ ሞኝ አፍቃሪ መሆን
የወደደ ጉንዳን ፥ "ልጣል" ይላል ዝሆን!
ዝሆንን እንኳ አንዴ ፥ ይጥሉት ይሆናል
ተነስቶ ሲመጣ ፥ ግን እንዴት ይዳናል?



እኔና ወይኔ ላይ ፥ ስካር የለው ስልጣን
ስበላም በገደብ ፥ አያውቀኝም ቁንጣን
በልኬ እንዳልበላሁ ፥ በልኬ እንዳልጠጣሁ
መጥኖ ማፍቀሪያ ፥ ልብ ምነው አጣሁ?



ምድርን ተሸክሟል ፥ አትላስ ያ ገርጋራ
በዕውቀቱም° አዝሏል ፥ ምድርን ካትላስ ጋራ

ይኸው እኔም አለሁ...
ከሁለቱም በላይ ፥ ደክሜና ዝዬ
እሷን ከፍቅሯ ጋር ፥ ተሸክሜ አዝዬ!



የቆጠርኩት ሀሁ ፥ የገለጥኩት መጣፍ
የቤተስኪያን አፀድ ፥ የጸሎቴ ምንጣፍ
እሷ ፊት ሲቆሙ ፥ አይገዳደሯት
ጭራሽ አበረቷት ፥ ጭራሽ አደደሯት!

የመረሳት ልጅ ሆንኩ ፥ የመገፋት ወንድም
ምነው አይቆርጥ ልቤ ፥ እግሬ አይራመድም?
ጸሎቴ አይሰማም ፥ አይሰምርም ስለቴ?
ቆርጦ ጣለኝ መቁረጥ ፥ የት ሄደ ብስለቴ?
"ሙት" እንኳን ብትለኝ ፥ አላስብ ሁለቴ!
እሷን የጊዜ ገድ ፥ ሲያሳምር ሲኩላት
ስንቴ እየተነሳሁ ፥ ስንትዜ ሞትኩላት?



ያጣሁኝ ይመስል ፥ ሸክም ባይነት ባይነት
አሻፈረኝም ብዬ ፥ በእምቢ ባይነት
ጠርጣራ ልቤ ላይ ፥ እንዳልተሸከምኳት
ስዝል ራቀችኝ ፥ ሲደክመኝ ደከምኳት!



"እለቅ" ሲልኝ እንጂ
"ባክን" ሲለኝ እንጂ
የመከነ ፈንጂ
ሁን ሲለኝ ነው እንጂ
ልክ እንደ ልጥ ዘገር
እንደው ያለነገር
የነፍሴ ነበልባል ፥ አልተንቀለቀለም
አለቅኩ እንደ ላምባ ፥ ነጠፍኩ እንደ ቀለም!



ፍዝ ኩራዝ ተግ ይላል ፥ ላምባ ሲንቆረቆር
ስብራት ይገጥማል ፥ ይድናል ቆረቆር
በደል ይሠረያል ፥ ይካሳል በእጥፍ
ግን ምን ያድርጉታል ፥ ሰው ነፍሱ ሲነጥፍ?

ቢላ ቢዶለዱም ፥ መቁረጡንም ቢተው
ያስቀጠቅጡታል ፥ ለአንጥረኛ ሰጥተው
ሸማውን ላጣቢ
ገንዘብ ለቆጣቢ
ባደራ ይሰጣል
ያደፈ ይነጣል
ጎፈር ያድርጉታል ፥ ጨብራራን ከርክመው
ምን መላ አለው ለሰው ፥ ሰው መሆን ሲደክመው?

በእሷው ዝዬ ብታይ ፥ እሷው ሳቀችብኝ
እንደህል እንደ ውኃ ፥ ነፍሴ አለቀችብኝ!



የእሷ ገመምተኛ ፥ የማልቆርጥ ወላዋይ
በከንቱ ጩኸቴ ፥ እላለሁ እንጂ "ዋይ"
እሷ እንደኹ አይገርማት ፥ ሞቴንም ናቀችው
ቯለሰች °° በጣሬ ፥ ዕምባዬን ሳቀችው!



እንድድናት ታመምኩ
እንድትይዘኝ ዘመምኩ
በእሷው እንዳልመጣ ፥ ሕመም በሽታዬ
አንድ "ይማርህ" አጣች ፥ ለሺ እንጥሽታዬ?



ቧልቴ ወጋወጌ ፥ የአንደበቴ ፌዝ
እሷን ማሳቅ ከብዶት ፥ አጥሮት ለዛና ወዝ
እንዲያው ስድከመከም ፥ እንዲያው ስወዘወዝ

ይኸው አንድ ዘዴ ፥ ይኸው አንድ መላ
ቀልድ አደረኩላት ፥ ሕይወቴን በሞላ!

ይሄን ተመልክታ
ፈክታ ተንከትክታ
ስቃ ስታበቃ
ጥላኝ ሄደች በቃ?

ሁሌ እንድትስቀኝ ፥ ከፊቷ ባልርቅም
የተደገመ ቀልድ ፥ ለካ አያስቅም!
ሳቅ የተለበጠ ፥ ሺ ዕምባ ቀፍቅፌ
ብቻዬን ቀረኹኝ ፥ ቀልድ ሕይወት ታቅፌ!



ግን ይሁን!
መቀበል ነው እንጂ ፥ የሕይወት አሰስ
ዳኛውን ለራሱ ፥ ምን ይረባል መክሰስ?
ምን ያመጣል ልቤ ፥ ቢያዝን ቢበሳጭስ?
ወዳልፈለገው ነው ፥ ሰውና የእጣን ጭስ!



ባት[]ሚኝም ስሚኝ...
ባት[]ሚኝም ስሚኝ...

መልኩን አሳምሮ ፥ ቢኮፈስ ቢኮራ
ከ"እኝክ - እንትፍ" ዕጣ ፥ አያመልጥ ሸንኮራ
እኔም እንደዚያ ነኝ ፥ አገዳና ቅንጥሽ
ካፍሽ ብውል እንኳን ፥ ችዬ ማልዋጥሽ
መሆኔን አውቃለሁ ፥ ጣፋጭ ግን አላቂ
ስትጎርሺኝ አልቅሰሽ ፥ ስትተፊኝ ግን ሳቂ!

መተፋቱ ላይቀር ፥ መስቲካ ታኝኮ
ምንምሽ ነኝ እኔ ፥ ምንምሽ ነኝኮ!

፨ ፨ ፨

°° ቯለሰች - "ቯልስ ደነሰች" የሚለውን ቃል የሚተካ የቃላተ-ፈጠራ ሙከራ

HOME || ቤት 🏚

22 Nov, 20:10


"እንገናኝ" ስትለኝ "እምቢየው - Insecure ነኝ" ስል ከርሜ ከስንት ልመና በኋላ እሺ ብያት ዴት ከወጣን በኋላ "አንድ የማወቀው የጣሊያን ቤት አለ። ሞሶሎኒያቸው በጣም አሪፍ ነው። ላፎንቴናቸውማ OMG you have no idea! እሱን መሞከር አለብሽ" ብያት ፈረንጅ የሚበዛበት ሬስቶራንት ከወሰድኳት በኋላ ለእኔ አፒታይዘር ቺክን ሳላድና ሚኒስሮ በስቴክ ከአሩስቶ ጋር፣ የሚጠጣ ነገር ደግሞ ሞሂቶ፤ ለእሷ half toasted corn with pumpkin soup (የበቆሎ ቂጣ በዱባ መረቅ)፤ ዲዘርት ደግሞ ለእኔ ቴራሚሶ ለእሷ ደግሞ ቴሊታቢስ አዘን ከበላን በኋላ ቢል 2.3 ሚሊየን ዶላር ሲመጣ ንፍጤን ልናፈጥ በሚል ሰበብ ሽንት ቤት ሄጄ mirror ሰልፊ ተነስቼ "Having a quality time with myself!" በሚል caption ፑስት!

#MenInWomenField
#ወንዶችበሴቶችዘርፍ

HOME || ቤት 🏚

04 Nov, 15:55


[📸: እኔው ወንድማችሁ! 😅]

HOME || ቤት 🏚

04 Nov, 15:53


ማንን ነው የምታገለው? የፈጠረኝን? የፈጠርኩትን? ወይስ ራሴን? አላውቅም! ባውቅም የሚረባኝ አይመስለኝም። ለምን እታገላለሁ? ለማሸነፍ? የማሸነፍ ጥቅም ምንድነው? የአሸናፊነት ጉሮ ወሸባ?

አንዳንዴ - አንዳንዴ ብቻ ሳይሆን ብዙ ጊዜ - ታግለው ቢያሸንፉትም የኋሊት ተጉዘው የማያስመልሱት እልፍ ኪሳራ አለ። ትላንቴን በምን ዓይነት ገመድ የፊጥኝ አስሬ ብጎትተው ይመለሳል? ያስለቀሰኝን ታግዬ ብጥለው ፈስሶ ለባከነ እምባዬ መታሰቢያው ምንድነው? የፈሰሰን እምባ ምገው ወደ ከረጢቱ አይመልሱት ነገር! እንደ ጠመዥ ቆሎ ለተመነዠገ ባካና ወጣትነቴ፣ ለባከነ ልጅነቴ፣ በዋል ለፈሰሰ ጉብዝናዬ ስርየታቸው ምንድነው? ለማንስ "ያንት ያለህ" ይባላል?

ስለ ሕይወት እተክዛለሁ፤ ስለ እኔነቴ እቃትታለሁ። የሚጠቁምበት አጥቶ ተንከርፍፎ ለቀረው ለሌባ ጣቴ አዝንለታለሁ። የሚሰድበውን ላጣ የይሉኝታና የወግ ፋሻ ለሸበበው ለመሀል ጣቴ በኃዘን ከንፈሬን እመጥጣለሁ። ለቀለበት-አልቦው ቀለበት ጣቴ እብሰከሰካለሁ። ጥሏን ሳታውቅ እርቅ ለምትቃርም ትንሿ ጣቴስ?

"እየኖርኩት ያለሁት ኑሮ የማን ነው?" እላለሁ። ሕይወት ያሳረፈችብኝን ሰንበሮቼን እቆጥራለሁ፤ ብጉሮቼን እዳብሳለሁ። ጣቶቼን ባቀመቀመው ጢሜ መሀከል አርመሰምሳለሁ። "ማን ነኝ ግን?" ብዬ እጠይቃለሁ።

በጠራቢ እጅ እንደዋለ ሀውልት ነኝ ፥ መጠረቡ ባይከፋኝም ከሀውልቱ ድፍን ዓለት ላይ ተጠርበው ከሚጣሉት ረብ የለሽ ጠጠሮች መሀከል መሆኔ ብቻ ይከፋኛል - በስሱ ይከፋኛል - በስሱ ብቻ ሳይሆን በአያሌው ይከፋኛል።

የሕይወት ጉድፍ ከመሆን በላይ ምን ያማል? ገና ለጋ ሳለን ተላምጠን የተተፋን ቅንጥሾች እንሆን? ፍሬ ነን ወይስ ገለባ? እያንገዋለለ በዋለበት ሁሉ የሚጥለን ራስ ወዳድ ንፋስ ለገለባነታችን ምስክር አይሆንብንም?

ፀሐይ በጠለቀች ቁጥር ላባከንኩት ቀኔ የንስሓ እንባ በጉንጮቼ ላይ እዘራለሁ። ያለፈኝን የዳዊት ልጅ "እባክህ አትለፈኝ!" እለዋለሁ። ሟቹ እንደሆነ ረፍዶበታል - ለገዳዬ እማልዳለሁ።

አሁንም ለተላለፍኩት ልጅነቴ አርባ እሰግዳለሁ፤ የኋሊት እያማተርኩ እጅ እነሳዋለሁ። "አንተ ከልጆች መካከል የተባረክ ነህ!" እለዋለሁ። የምጠላው ወዳጄን - የምወደው ጠላቴን - ራሴን - "በመንግሥቴ በመጣሁ ጊዜ እንዳስብህ፤ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ!" እለዋለሁ።

HOME || ቤት 🏚

02 Nov, 12:26


አይ የአዲስ አበባ ካፌዎች 🤦‍♂️

ገና ገብተህ አንድ ሁለት ሰዓት ከመቀመጥህ ያቁነጠንጣቸዋል። ጠረጴዛውን ዐስሬ ይወለውሉታል፣ ወንበሮቹን ያስተካክላሉ፣ ስኳር ዕቃውን ያነሳሉ፣ ያስቀምጣሉ። ደግሞ ሰው የሚበዛበት ካፌ ቢሆን እሺ። ባዶ ወንበር ታቅፈው እኮ ነው የሚውሉት።

የእኔዪቱማ በፋራ ሙድ እንዳልገባው ሰው ስገግምባት ደጋሚ መጥታ "ምን ልታዘዝ?" ውይ እናትዬ አሁን ቡና አጠጣሽኝ፣ ነገር አበላሽኝ እኮ!

ገና እስከ ማታ አንድ ሰዓት ነው የምቀመጠው። እስኪ አፍ አውጥተሽ "ውጣ!" ትዪኝ እንደሆነ እናያለን። ሲጀመር የመጣሁት እኮ የቀጠነ ቡና ለመጠጣት አይደለም የእኔ እናት! ተቀምጬ ሥራዬን ለመሥራት ነው።

👎

HOME || ቤት 🏚

22 Oct, 19:16


እኔ...
የውስጤን ችዬ ፥ የማላብራራ
አፈ-ላሁጫ ፥ ልበ-ጨብራራ
አምላክ ላይ እንኳን ፥ ጅንን ቀብራራ
ሟች የነበርኩኝ ፥ እግዜር ባይራራ!

እኔ...
ስንኩል መልከ-አምላክ ፥ መንፈሰ-ክልስ
ነፍሱ ሸካራ ፥ ምላሱ ልስልስ
ድቅል ተክል ነኝ ፥ ስንዴና እንክርዳድ
የተዘራ አብቃይ ፥ የሆዴ ሁዳድ!

እኔ...
ለሥጋ ታጋይ ፥ ለቅንጥብጣቢ
ገላው ቆሽሾ ፥ ስሙን አጣቢ
ሕይወት ትርዒት ፥ ኑሮም ድራማ
ሲገበርለት ፥ ጀማው ከራማ

የሙጥኝ ብዬ ፥ ያዳም ከል ቅርሴን
እንኳን ወዳጄን ፥ እንኳን ራሴን
አምላኬን እንኳን ፥ ምንኛ አለፋሁ
ስጠፋ አገኘኝ ፥ ሲያገኘኝ ጠፋሁ!

አትራራልኝም ፥ ዓለም አጅሪት
ክብ ሆኖብኛል ፥ ሕይወት አዙሪት
ኢያሪኮዬን ዛሬም ፥ ልዙረው
ትላንቴን አይደል ፥ ነገ ምኖረው?

ባሮጌ አንቀልባ ፥ ነፍሴን አዝያት
ሾልካ ጭቃ ላይ ፥ ስትወድቅ እያት
ቀኔ ሲጓደል ፥ ሲርቀኝ ቆሌ
"ሆሳዕና" ነው ፥ ኦሜጋ ቃሌ
"አሁን አድን" ነው ፥ ፍጻሜ ቃሌ!

አሁን አድነኝ...
በጆችህ ልዋል ፥ ሁነኝ ጠራቢ
አንፀኝ ጌታ ፥ አድነኝ ረቢ
አድክመኝ ላለም ፥ ቆሜ ላለክልክ
አሳደህ ያዘኝ ፥ በሽሽቴ ልክ

አሁን አድነኝ...
ፈውሰኝ ረቢ ፥ እስቲ ላገግም
ዕምባዬን አብስ ፥ አላልቅስ ዳግም
መሮጥ ቢያቅተኝ ፥ በስሱ ላዝግም

አሁን አድነኝ...
ይደገፍ በጅህ ፥ መንገዳገዴ
ዋጀው ዕድሌን ፥ ይግደድህ ገዴ
በእቶን አባብለኝ ፥ አልሁን ለጋ
ሞት ደጃፍ አልሂድ ፥ ሕይወት ፍለጋ!

አሁን አድነኝ...
ይፋፋም እንጂ ፥ ሕቅ እንቅ ትግል
ሥጋና ነፍሴን ፥ አላሸማግል
እንኳን ገላዬ ፥ ሃሳቤ አይዘሙት
ዓለም ትሙተኝ ፥ ለዓለም ልሙት!

አሁን አድነኝ...
ክንፌን ስበረው ፥ ይብቃ መክነፌ
ሥጋ ይሸነፍ ፥ በመሸነፌ
ዓለም ትርበድበድ ፥ በመርበድበዴ
እነሆኝ ፊትህ ፥ መንታ ወንበዴ
ነፍሴን በግራ ፥ ሥጋዬን በቀኝ
እመስቀልህ ጎን ፥ ባክህ ጠርንቀኝ!
ምኞት ሹክሹክታው ፥ ሲነዘንዘኝ
በፍቅርህ ገድለህ ፥ እስቲ ገንዘኝ!

አሁን አድነኝ...
ምኞት ሲንጣት ፥ ሲያርገፈግፋት
መልሳት ነፍሴን ፥ ልቤን ደግፋት
በብሉይ ፍቅር ፥ በአዲስ ኪዳን
ለመኖር ልሙት ፥ ለመሞት ልዳን!

HOME || ቤት 🏚

02 Oct, 15:01


ያው ስልኬ እየለየላት ስለሆነ ሰሞኑን ቁጭ ብዬ ፋይሎቼን backup ሳደርግ ነበር። ልክ እንደዚህ ያሉ ለሦስት ዓመት የጻፍኳቸውን Nonsense የሆኑ ጽሑፎቸ፣ ብሶቶች፣ ያልተላኩ ቴክስቶች፣ የማያስቁ ቀልዶች እያየሁ ስፍታታ ነበር።

አንዳንዶቹ ያስቃሉ፣ አንዳንዶቹ አለማሳቃቸው ያስቃል፣ አንዳንዶቹ ያናድዳሉ፣ አንዳንድቹ ምንም ትርጉም የላቸውም፣ አንዳንዶቹ ለማን እንደሆኑ እንኳን የማላስታውሳቸው ቴክስቶች ናቸው፣ አንዳንዶቹ ደግሞ በጊዜው የነበርኩበትን ስሜት ያስታውሳሉ፣ አንዳንድቹ ስጽፋቸው የነበርኩበትን ቅጽበት ጥርት አድርገው ያሳታውሱኛል። ብቻ ደስ ይላል ሁሉንም አልፈው ወደ ኋላ መለስ ብለው ሲያዩት። እና ዝም ብዬ ላካፍላችሁ ፈለግኩ። They will be deleted soon, I guess!

መልካም ምሽት!
😎

HOME || ቤት 🏚

02 Oct, 15:01


The most random thing in the whole universe is my notepad, I must say!
😂

HOME || ቤት 🏚

02 Oct, 15:01


The Randomness is so funny!

😂

HOME || ቤት 🏚

02 Oct, 15:01


ብድሩን መልሼ ይሆን?

😂