የሾፌሮች አንደበት

@voiceofdrivers


ለአሽከርካሪው መረጃ ማድረስ ድምፅ ሆኖ ማገልገል

የሾፌሮች አንደበት

23 Oct, 05:45


ሰላም ወንድሜ እንዴት ነህ
ዝናቡ እባላለው የተሳቢ ሾፈርነኝ ጅቡቲ ውሰጥ ካሶኒ ግቢ ሰ.ቁ 68540
የባዶ ኮንቴይነር ጌት ፓሰ
የሙሉ ኮንቴይነር ጌት ፓሰ የዶላሬ መግቢያ ካርድ የጅቡቲ መግቢያ ካርድ ሰለጠፋብ ከገኛችሁ በሰልክ ቁ 77543984/0914101169 ደውላችሁ እንድትተበሩኝ በትሕት ና እጠይቃለው

የሾፌሮች አንደበት

18 Oct, 07:22


🔑ይ/ጨፌ ከተማ ክልል ዉስጥ
ወድቆ የተገኘ የመኪና ቁልፍ ነው::
የኔ ነው ባይ ከታች ባለው አድራሻ 🤙ደውሎ🤙 ማግኘት ይችላል...👇👇👇
0916440352
👉 🔑

የሾፌሮች አንደበት

18 Oct, 06:43


ሽፍታ ለመያዝ ያልተገኘ ሚኒሻ መኪና ለመጠበቅ

ከወር በፊት በማኸከላዊ ጎንደር ከጎንደር ሶረቃ መንገድ ላይ የህዝብ Fsr ወንበዴዎች ለማገት ያስቆማሉ ሹፌሩን ሲያሰወረዱት እጂ ፍሬን ባለመያዙ ስትራፕ ያደርግና መኪናው ይወድቃል! እና ሚኒሻ ነን የመንግስት አካል ነን የሚሉት ሰዎች የታገተውን ለማስለቀቅ ሳይሆን የወደቀውን መኪና ለመጠበቅ ለአንድ አዳር 4ዐዐዐ (አራት ሽህ )ብር ይከፈለን ብለውጠይቀው ከዛ ፖሊስ ሽማግሌ ሁኖ በድርድር መኪናው እስኪነሳ የጠበቁበት 25,000 (ሀያ አምስት ሽህ) ብር ተቀብለዋል ::

የታገተውን ሾፌር ለማስለቀቅ የሞከሩት ሆነ የሰሩት ስራ ይለም አጋች ሲያስወርደው የወደቀን መኪና ለመጠበቅ እና ብር ለማግኘት ግን የሚቀድማቸው የለም :: በታች አርማጮ ያላችሁ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች ህግ አስከባሪ ባለሙያዎች ስራችሁን በአግባቡ እየተወጣችሁ አይደለም ::

የሾፌሮች አንደበት

16 Oct, 18:23


ኮድ 3 95661 ታርጋ ሰላገኘዉ የኔ ነው የሚል ካለ ማሰረጃ አቅርቦ መዉሰድ ይችላል አሁን ሰመራ ነኝ 0916038451

የሾፌሮች አንደበት

13 Oct, 11:19


የሚንስትሮች ምክር ቤት የተሻሻለው የመንገድ እና የትራንስፖርት ትራፊ መቆጣበሪያ ነው ::

1 - ተሽከርካሪ በማሽከርከር በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም አሽከርካሪ 1,600 ብር ይቀጣል

2 - በተሽከርካሪ ማንኛውንም አይነት ጥፋት በመፈፀም በሰው አካል ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ያደረሰ ለ 6 ወር መንጃ ፈቃዱ ይታገዳል

3 - በተሽከርካሪ ማንኛውንም አይነት ጥፋት በመፈፀም በሰው አካል ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ያደረሰ ለ 1 አመት መንጃ ፈቃዱ ይታገዳል

4 - በተሽከርካሪ ማንኛውንም አይነት ጥፋት በመፈፀም በሰው ሞት ያደረሰ ለ 1 አመት መንጃ ፈቃዱ ይታገዳል

5 - ግልፅ የሆነ ደምብ ወይም መመሪያ በመተላለፍ 2 እና ከዛ በላይ የሞት ጉዳት ያደረሰ 1 አመት ከ6 ወር ይታገዳል

ሌሎች ህጎችን ከፎቶው ያንብቡ

የሾፌሮች አንደበት

13 Oct, 07:27


አማራ ክልል ጎጃም ፍኖተ ሰላም
በመንገድ ክልከላው የተነሳ ቁመን ነበር ፍኖተ ሰላም ከተማ ላይ ከተማው መሀል ጦርነት ነበር ሰው ከቤቱ ሁሉ አይወጣም ነበር አሁን ሲረጋጋ ስራ አትጀምሩም ብለው ታርጋ ወሰዱብን ለማን አቤት እንበል ይላሉ አሽከርካሪዎች ::

ፍኖተ ሰላም ከተማ ያላችሁ አመራሮች ለራሳችሁ በመንገድ ለመሄድ አይደለም ደጂ ወጠህ ለመቀመጥ ፈርተህ ቤትህን ቆልፈህ ተደብቃችሁ ከርማችሁ ዛሬ ሲረጋጋ ብቅ ብላችሁ ልቅጣ የምትሉ በምን ሞራላችሁ ነው ::

ተው እንጂ ጦርነት በነበረበት ጥይት በሚዘንብበት እናንተ ፈርታችሁ ቤታችሁ ባልወጣችሁበት ተደብቃችሁ ከርማችሁ እንዴት ነው አሁን ካልቀጣን ማለት የጀምራችሁ እስኪ ያለምንም የመከላከያ አጀብ ዛሬ ወደ ባህር ዳር ሂዱ ኧር ባህር ዳር ሩቅ ነው ቡሬ ሂዱ ::

ብር ለመሰብሰብ ሰበብ ማብዛት አያስፈልግም በጦርነት መሀል እናንተ አልጋ ስር ተጋድማችሁ ሾፌር እንዲንቀሳቀስ ማሰባችሁ ነውረኝነት ነው :: እናንተ በሚዘጋ መንገድ በጦርነት መሀል ደፍራችሁ ነድታችሁ አሳዩን እንከተላችሁ አልጋ ስር ከትመህ ከርመህ አቧራህን የሸረሪት ድርህን አራግፈህ ወጠህ ካልቀጣው ማለት ያሳፍራል ::

መንገድ በክልከላ ሲዘጋ ለምን የእጀባ ስራ አትሰሩን ? አታደርጉትማ አጂበህ ለማሳለፍ አይደለም አስፖልት አቋርጠህ በእግርህ ለማለፍ ጋቢተከናንበህ ራስክን ቀይረህ እየሄድክ ሾፌርን ለማንገራገር መድፈር ትልቅ ነውር ነው::

ተው እንጂ ህዝብ በሰላም ወጦ የሚገባበት ሾፌር ከቦታ ቦታ በሰላም ተንቀሳቅሶ የሚሰራበት ሰላማዊ ሁኔታ ማመቻቸት የእናንተ ስራ መሆኑን እረስታችሁ ነው: : ህግ ቢኖር ሰላም ባለማስፈናችሁ መንገዶችን ከስጋት ነፃ ባለማድረጋችሁ እናንተ ነበር ከስልጣን መነሳት በህግ መጠየቅ የነበረባችሁ ጭራሽ እናንተ ከሳሽ ሁናችሁ ትመጡ አታፍሩም ::

የሾፌሮች አንደበት

12 Oct, 19:01


ነገ በ03/02/2017 ከጠዋቱ 12 ሰአት ጀምሮ ቡራዮ እና ሰበታ የኢሬቻ በአል ይከበራል በዛ በኩል የምትወጡ ሆነ የምትመጡ አገባባችሁን አወጣጣችሁን ይህንን ፕሮግራም ግምት ውስጥ ያስገባ ይሁን እንዳትጉላሉ ::

የሾፌሮች አንደበት

12 Oct, 09:47


ይህ እግረኛ መንገድ ባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 04 ነው እንደሚታየው እግረኛው መጦ መጦ ጫፍ ላይ ክፍቱን የተተወ ትልቅ የውሀ መተላለፊያ ቦይ ነው :: አይነ ስውሮች በእድሜ የገፉ እናት አባቶች ነፍሰ ጡሮች ህፃናት ሌሎችም ሳያዩት ድንገት ቢገቡበት ሊከሰት የሚችለውን ማሰብ አይከብድም ::

ባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከዋና ከንቲባ ቢሮ በ150 ሜትር በማይሞላ ርቀት ላይ የሚገኝን እንዲህ ያለ አደጋን ሊያስከትል ህይወትን ሊቀጥፍ አካልን ሊያጎል የሚችልን ቦታ በአፋጣኝ በመዝጋት ጉዳት ከማድረሱ በፊት እርምት ልትወስዱበት ይገባል ::

የሾፌሮች አንደበት

11 Oct, 16:00


ጥንቃቄ
ከጥቁር ውሃ ሻሸመኔ መሄጃ እስከ ቶጋ ካምፕ ድረስ ያለው መንገድ ጥገና እየተደረገለት ስለሆነ በተለይ በምሽት ለምታሽከረክሩ ጥንቃቄ እንድታደርጉ ጥገናው በተወሰነ መልኩ በምሽትም እየሰሩ ስለሆነ::

የሾፌሮች አንደበት

11 Oct, 03:23


ጂቡቲ ላላችሁ ጉዞ ለማድረግ የተዘጋጃችሁ ገርሀቡስ ውሀ ሞልቶ መንገድ ተዘግቶ ቁመናል ባላችሁበት ሁናችሁ መንገዱ ክፍት እስኪሆን ጠብቃችሁ ተንቀሳቀሱ የሚል መልህክት ደርሶናል ::

01/02/2017 ከጥዋቱ 12:20

የሾፌሮች አንደበት

10 Oct, 13:04


ይህንን የመኪና ታርጋ ቁጥር A52665 የጣለ ወይም የጠፋበት አሽከርካሪ በ 0927942537 ደዉሎ መዉሠድ ይችላል።

የሾፌሮች አንደበት

10 Oct, 12:18


በአማራ ክልል ተጥሎ የነበረው የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ እቀባ ከነገ 01/02/2017 ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ ተነስቷል የሚል መረጃ ደርሶናል አጣሩ ::

የሾፌሮች አንደበት

10 Oct, 04:27


ራስክን በራስህ ማስከበር በምትችለው ጉዳይ ሁሉ አታልቅስ ::

ብዙዎች አሽከርካሪዎች በውስጥ መተሐራ የመኪና ማሳደርያ 400 ብር ክፈሉ ተባልነ አልከፍልም ስንል በሚኒሻ ተደበደብነ ተንገላታነ የሚል መረጃ አድርሳችሁን እኛም በ3 ቀን የማሳደሪያ ሂሳቡን አስተካክሉ የሚል ጥሪ አቅርበን ነበር የተሰጠ ምላሽ የተቀነሳ ገንዘብም የለም ::

ምክራችን በሁሉ አታልቅስ ነው :: መተሀራ በማደርህ 400 ብር ክፈል በመባልህ ቅር ካለህ በግዴታ እደር ብሎ የሚያስግድድህ የለም :: ስለዚህ በራስህ ፍላጎት ሄደህ ቆመህ ለሚደርስብህ ነገር ተወቃሹ ራስህ ነህ :: መተሐራ በማደርህ 400 ብር በመክፈልህ ቅር ከተሰኘህ መፍትሄው አለማደር ብቻ ነው ::

በራሳችን እጂ ያለውን ራስን የማስከበር ሂደት እና መብት በመጠቀም በደልን ሆነ የተጋነነ ክፍያን ማስቆም እየቻልን ሌላን መውቀስ ሆነ ማለቃቀስ ነውር ነው :: ራስክን ውቀስ ራስክን ክሰስ ::

መተሐራ ኬላ ዘግታ በግድ ቁም አላለችህም በቃ እኔ 400 ነው የማስከፍል ስትፈልግ ቁም ሳትፈልግ እለፍ እና ሂድ ብላሀለች ያንተ ምርጫ ቆሞ ማደር ከሆነ ክፈል የተጠየከውን አታልቅስ አይ ይህ አልከፍልም ውድ ነው ካልክ አልፈህ በመሄድ መብትህን አስከብር ::

አንተ ካልቆምክ የሚጠብቀው መኪና የሚጨምረው ዋጋም አይኖርም :: መነሻህን አስተካክል መድረሻህን አመቻች ይሄው ነው ::

የሾፌሮች አንደበት

09 Oct, 13:01


ለኢፌድሬ የሀገር መከላከያ ሰራዊት
ለኢትዮጽያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን
ወደን ሳይሆን ተገደን በቆምንበት ልትጠይቁን አይገባም ::

አሽከርካሪው በሀገሪቱ በተለዩ አካባቢዎች ዘርፈ ብዙ ችግሮች እያስተናገደ ከዛሬ ነገ ይሻል ይሆና በሚል ተስፋ ግፍን እየተቀበለ ስራውን በመስራት ላይ ይገኛል :: ከእለት ስራው ባለፈ በግዳጂ ተግባር ላይ በመስማራት ግልጋሎትን በመስጠት የበኩሉን የሚወጣ እየተወጣም ያለ መሆኑ ይታወቃል ::

ከቅርብ ጊዜ በሀገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የመንገድ መዘጋት ክልከላወችም ሲከሰቱ መንገድ እስኪከፈት በየቦታው በመቆም ለከፋ ኢኮኖሚያዊ ችግር ለእንግልት ይዳረጋል :: ሾፌር ወዶ ሳይሆን ተገዶ በክልከላ በቆመበት ሂደት የመንግስት የፀጥታ ሀይሎች ለምን ቆማችሁ ባመለት የሚያደርሱት ማስፈራራት እና እንግልት አሳፋሪ እና ነውረኝነት የተሞላበት ተግባር ነው ለእኛ ::

በመጀመሪያ እገዳ በተጣለባቸው የእንቅስቃሴ ገደብ በተቀመጠባቸው መንገዶች ሲያሽከረክር ንብረቶች ለውድመት ሾፌሮች እስከ ሞት ለደረሰ ጉዳት ማስተናገዳቸው በሚታወቅበት ሂደት ለምን ቆምክ ብሎ ለመውቀስ መቅረብ ተገቢነት የሌለው ሀላፊነት የጎደለው ተግባር ነው ::

ዛሬ በወልድያ እና በደብረ ብርሀን ከተሞች በመንገድ የእንቅስቃሴ ክልከላ ምክንያት ሳምንት ለሚደርስ ቀናት የቆሙ መኪኖች ክልከላ በመነሳቱ ለመጓዝ ሲነሱ የመንግስት የፌደራል ፖሊስ እና የመከላከያ አካላት ያስቆማችሁ መጦ ያስወጣችሁ በማለት ከከተማ እንዳይወጡ ማገዳቸውን መረጃ ደርሶናል ::

👉ሾፌር በየመንገዱ በዘራፊዎች ሲዘረፍ በአጋቾች ሲታገት በወንበዴዎች ውድ ህይወቱን ሲነጠቅ ቀርቦ ህግን ለማስከበር ፍትህን ለማንበር አጋችን ለማስለቀቅ በዳይን በህግ ለመጠየቅ በደልን ለማስቀረት የማይሰራ የማይራመድ ህግ አስከባሪ በምን ሞራሉ ነው ሾፌር ላይ በትሩን ሊያነሳ አትሄድም ብሎ መንገድ ሊዘጋስ የሚደፍረው ??

👉በክልከላ የተዘጋን መንገድ ሳያስከፍት ከተማ ተቀምጦ ወጦ የመንገዶን ደህንነት ሳያስጠብቅ በክልከላ መሀከል በሚሄዱት ላይ የሚወሰድን እርምጃ ቆሞ በሚመለከትበት ሂደት በምን አግባብ ነው በመቆማችን ልትወቅሱን የምትቀርቡ??

👉የመኪኖች መቆም ቢያሳስባችሁ ኑ እኛ አጂበን እናሳልፋችሁ ትሉ ነበር አጂባችሁ ለማሳለፍ ሳትሞክሩ እንዴት ብትሳሳት ነው ምስኪንን ክልከላ ጥሶ ቢሄድ ህይወቱን ሊከፍል የሚችል ሾፌርን ያገደህ መጦ ያስወጣህ የምትሉት ??

ጉልበታችሁን ጉልበት በሚጠይቅበት ሜዳ ላይ አውሉት ማንም እየተነሳ ሲዘርፈው ሲያግተው ሲገለው የማትደርሱለት በደሉን የማታስቆሙለት ሾፌር ላይ አታውሉት ::

ሾፌርን ለምን ቆምክ ብሎ የመክሰስ የመውቀስ ሞራል በፍፁም ሊኖራችሁ አይገባም የሚነዳበትን መንገድ ሰላም ማድረግ በሰላም ሰርቶ ወጥቶ ነድቶ የሚሄድበትን መስመር ማስከበር የእናንተ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን አትርሱ :: ያን ሳታደርጉ ወቀሳ ሆነ ክስ አግባብነት የለውም ::

ህግን ባላስከበራችሁበት ሾፌር ቢሄድ ህይወቱን ሊያጣ በሚችልበት ሂደት ለምን አልሄድክም ተብሎ መውቀስ ሆነ መክሰስ አይቻልም :: እኛ 24 ሰአት ብንሰራ ነበር ምርጫችን ግን በየት መንገድ በምን ሰላም :: ሰላም አስከብሩ መንገዶችን ከስጋት ነፃ አድርጉና መቆም እንደምንጠየፍ እናሳያችሁ ::

የሾፌሮች አንደበት

09 Oct, 11:17


ጂቡቲ ላይ ይህንን ቁልፍ ያቀኘ

የጅቡቲ ሰልክ +25377663270
የኢትዮጵያ 0901002444

የሾፌሮች አንደበት

09 Oct, 06:37


ዛሬ ማለትም በ 29/011 2017 ወልደያ ላይ በእንቅስቃሴ እገዳ ምክንያት ቆመው የነበሩ የጭነት መኪኖች ወዴትም አትወጡም በማለት የፌደራል ፖሊሶች አስቁመውናል ሰንጠይቃቸው ያስቆመህ ይምጣና ይስደድህ የሚል መልስ ሰጠውናል ሲሉ መልህክት እድርሰውናል ::

ሾፌር ክልከላ ባለባቸው ሲያሽከረክር እርምጃ ሲወሰድበት ቀርባችሁ ለማትረፍ በማትሞክሩበት ሂደት እንዴት በምን ሞራል ነው ያስቆመህ ያስለቅቅህ ልትሉስ የደፈራችሁ ?

የመኪኖቹ መቆም ካሳሰባችሁ ለምን እያጀባችሁ እንዲጓዙ ያላደረጋችሁ እናንተ የፈራችሁትን መንገድ ሾፌር በምን ድፍረቱ እንዲሄድበት ፈለጋችሁ ???

ወልድያ ያላችሁ ህግ አስከባሪዎች ሾፌሮችን አትንቀሳቀሱም የምትሉ የፌደራል ፖሊሶች ልታፍሩ ይገባል ::

የሾፌሮች አንደበት

08 Oct, 04:40


ይህ መንጃፈቃድ የጠፋው በዚህ ይደውል 0920641134 ጌቱ

የሾፌሮች አንደበት

08 Oct, 04:38


የት እንቁም ??
ከተማ ውስጥ ገብቶ ቆሞ በመገኘት 10,000 ብር እንዴት ያስቀጣል ??

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጂመንት ያለ በቂ ግንዛቤ ጥናት እና እውቀት ያወጣው የትራፊክ እንቅስቃሴ የሰአት ገደብ እና የመቆሚያ ቦታ ክልከላ ትልቅ የሚባል ችግርን የሚፈጥር ሾፌሩን የሚያማርር እና የሚመዘብር ሆኖ እያየን ነው ::

ይህ ቅጣት የተቀጡት ተክለሀይማኖት ጀርባ ትንሿ መስጊድ ፔፕሲ ላይ ካለ ፖርኪንግ ግቢ እና ውጭ ላይ ህጋዊ የፖርኪንግ ቦታ ላይ በቆሙበት መርካቶ ለመጫን ሁሌም ተራ ታይዞ በሚጠበቅበት ቦታ ላይ ነው ::

የቅጣቱ ምክንያት ምን ይላል በተከለከለ ሰአት ወደ ከተማ ውስጥ ገብቶ በመቆም ይላል ህጉ በዋና መንገዶች ላይ ቆሞ መገኘት ነበት ሲያወጡ የተናገሩት እዚህ ላይ 10,000 ብር ሲቀጡት ባስቀመጡት የቅጣት ምክንያት ከተማ ውስጥ ገብቶ ቆሞ በመገኘት ይላል ጎበዝ ከተማ ውስጥ በጭራሽ መግባት ተከልክሏል እንዴ??

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ማኔጂመንት በዘፈቀደ ሾፌርን ሊመዘብር ሊያማርር አይገባም መቆም በሚከለክሉ ቦታዎች መቆም የሚከለክሉ ምልክቶችን በመትከል መከላከል እንጂ ሙሉ ከተማ ውስጥ የሚቆምን በመቅጣት ማንገላታት ህጋዊ የውንብድና ተግባር ነው ::

ከተማ ውስጥ ገብቶ በመቆም የሚል ቅጣት ምን የሚሉት ቅጣት ነው ? ከተማ ውስጥ ገብቶ መቆም መቸ ተከለከለ??

በዋና መንገዶች መቆም ክልክል ነው የሚል ህግ ነበር አወጣን ያላችሁ ዋና መንገድ የትኞቹ ናቸው ዘርዝሩልን ??

ሌላው የትራፊክ ህግ በአለም አቀፍ የመንገድ ዳር ምልክት ነው የሚመራ የሚሰራ እናንተ የሚከለክል ምልክት ሳትተክሉ ዝም ብላችሁ መቆም ክልክል ነው እያላችሁ ህዝብን የምትዘርፉበት ሂደት የተቋሙን የአመራር ክሽፈት የአሰራር ድቀት አመላካች ነው ::

የሾፌሮች አንደበት

07 Oct, 17:11


አያችሁ 20,000 ብር ከምስኪን ሾፌር
ይህ የአዲስ አበባ የትራፊክ ማኔጂመንት ቢሮ ውስጥ ተቀምጦ ህግ እያለ ነባራዊ ሁኔታውን ተግዳሮት ያላገናዘበ ያለ በቂ ጥናት በማውጣት ሾፌርን ለምሬት ላቡን አፍስሶ ያገኘውን ጥሪት ለመብላት የተሰማራ መስሪያ ቤት ነው ::

ይህ ሾፌር ሳሪስ አቦ ከዋና ቀለበት በመውጣት ለመቆም 5 ደቂቃ ከሰአት ገደቡ በማለፉ ነው ሳሪስ አቦ ላይ 20,000 ብር የተቀጣ

ቆይ በመንገድ መዘጋጋት ዋና መንገድ ላይ እያለ የሰአት ገደቡ የሞላበት የት ይቁም ?? ህጉ ሲወጣ ይህንን ግምት ውስጥ አስገብቷል???

ሰአት ሲሞላባቸው መኪኖች ወጠው የሚቆሙባቸው የፖርኪንግ ቦታዎችን አዘጋጂታችኋልን ?? ንገሩን