የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት @fra_haymanot16 Channel on Telegram

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

@fra_haymanot16


መዝሙር ጥናት
አጫጭር ኮርሶች
የቤተክርስቲያን ስርዓት አጠባበቅ
ጥያቄ እና መልስ
የተለያዩ የሰ/ቤት ጉባኤዎች ያገኙበታል
ሰንበት ትምህርትቤት እናት ናት
join&share
ቻናላችንን ይቀላቀሉ

@fra_haymanot16
group

t.me/fra_haymanot_16
ጥያቄ፣ሀሳብ እና አሐስተያየት ካሎት

@yoniyekidye

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት (Amharic)

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት በአማርኛ "ፍቅር እና እውነት" ተብለው ታወቀናል ፡፡ አጠቃላይ ያህዌው አስፈላጊ መሆኑን ለመከላከል አስተያየቁ። ወይም እርስዎ አቅርቦ እንደሆነ እርሱ እናቱና ችግር ሲሆን አሁን እንደሚከበርኩ እርሱን በመከበሩ ለማድረግ እዚህ ላይን ይመዝገብ። ይሁኑ፣ የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት ከተለያዩ የሰዎች ጉባኤዎች ጋር እና ባንዳማስ ለሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት ለመመዝገብ ምን ብሎአል ፡፡ የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤትን በጥንቃቄ እና መልስ ለመረዳት ለእርሱ በጥናት ያግኙ።

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

25 Jun, 06:44


ክብሬ_ነው

ክብሬ ነው ክብርህን መናገሬ
ፅድቄ ነው ፍቅርህ መመስከሬ
ጌታዬ አምላኬ እልሃለሁ (2)
ስጠራህ ሳመልክህ እኖራለሁ (2)

አይቼ የእጅህን ታምራት
ሰምቼ የቃልህን ትምርት
ሆኛለሁ ምስክር ላዳኝነትህ
ስጋን ተዋህደህ ለኛ መገለጥህ (2)

ተከተልኩ ሁሉን ነገር ንቄ
መድኃኒት መሆንክን አውቄ
ከመልካሟ ቤትህ ተጠልያለሁ
የእጅህን በረከት ካንተ እጠግባለሁ (2)

እርፍ ይዤ ላላርስ ወደኅውላ
እያየው መረቤን ስትሞላ
እመካብሃለሁ ባንተ መድህኔ
አምላኬ ነህና የምትራራ ለኔ
አባቴ ነህና የምታስብ ለኔ

ቸርነት ምረት ከበዛልኝ
ለስምህ ውዳሴ ቅኔ አለኝ
ክብሬና ሞገሴ አንተ ነህ ጌታ
ተመስገን (2) ጠዋትና ማታ (2)

share & join
group

https://t.me/fra_haymanot_16
channal

@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት

@yoniyekidye

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

25 Jun, 06:31


🕊      እንኳን አደረሳችሁ !    🕊

         [    ጾመ ሐዋርያት !    ]

†   🕊              †                🕊   †

[  ክፍል አንድ  ]

በስመ አብ ፥ ወወልድ ፥ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን።

በየአመቱ በዕለተ ሰኑይ ብቻ [ ሰኞ ቀን ብቻ ] የሚጀምሩ ሦስት አጽዋማት አሉ፡፡ እነርሱም ዓቢይ ጾም፣ ጾመ ነነዌ እና ጾመ ሐዋርያት ናቸው፡፡ እነዚህአጽዋማት ምን ጊዜም ቅበላቸው እሁድ ሲሆንየሚገቡት ደግሞ ሰኞ ቀን ነው፡፡ በየትኛውም ዓመት ይህን ዕለት አይለቁም፡፡

ስለዚህ የ፳፻፲፭ [2015] ዓ.ም ጾመ ሐዋርያት ዛሬ ሰኞ ግንቦት ፳፰ [28] ገብቷል፡፡ ቤተ  ክርስቲያናችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በየግላችንም ያጋጠሙንን መንፈሳዊና ሥጋዊ ውጊያዎች በማሰብ ድል የምናደርግበትን ኃይል ፈጣሪያችን ይሰጠን ጾሙን ከወትሮው በበለጠ ጥንቃቄ ልንጾመው ይገባናል፡፡

የጾሙን ታላቅነት ተረድተን እንድንጾመው የትመጣውን ፣ ትንቢቱን ፣ ምሳሌውንና ምሥጢሩን መረዳት አጋዥ ስለሚሆነን አስቀድመን ስለጾሙ እንማር ዘንድ በአጭሩ ቀርቧል !

ጾመ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ዕድሜያቸው ለጾም የደረሱ ምእመናን በሙሉ እንዲጾሙአቸው ካወጀቻቸው ሰባት የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጌታችንና በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አንደበት ቀን የተቀጠረለት ፣ ትንቢት የተነገረለትና ምሳሌ የተመሰለለት ጾምመሆኑ ከአጽዋማት ሁሉ ለየት ያደርገዋል፡፡

ጌታችን ስለዚህ ጾም ትንቢት በመናገር ፣ ምሳሌ በመመሰል ሰፊ ትምህርት የሰጠው ፈሪሳውያን ወደ እርሱ ቀርበው " ደቀ መዛሙርትህ የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው ? " ብለው በጠየቁት ጊዜ ነው፡፡ እርሱም ሲመልስ እንዲህ አላቸው ፦ " ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገርግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል ፤ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም ፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና ፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም ፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል ፤ የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡" [ ማቴ.፱፥፲፬ ]

በዚህ የጌታችን መልስ ውስጥ "ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡" የሚል ስለ ጾመ ሐዋርያት የተነገረ የትንቢት ቃል እናገኛለን፡፡ ይህ አምላካዊ ቃል ጾሙ ስለሚጀመርበት ወራት ቀጠሮ ይሰጣል፡፡ ያም ጊዜ ሙሽራው ከእነርሱ ከተወሰደ በኋላ ያለው ጊዜ ነው፡፡ "ሙሽራው ከተወሰደ" በኋላ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ማለት ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ የሚጀምረው በዚህ ቃል ምክንያት ነው፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊትና መጽሐፍቅዱሳዊ መሆኗን ይመሠክራል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡ ወለወላዲቱ ድንግል ፡ ወለመስቀሉ ክቡር፡፡


share & join
group

https://t.me/fra_haymanot_16
channal

@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት

@yoniyekidye

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

13 May, 18:04


https://www.tiktok.com/@frahaymanot1/photo/7368535313666346245?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7367679555300050437

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

13 May, 17:06


አይቀርም አይቀርም አይቀርም እንዴት ይቀራል

ታላይ መንፈሳዊ ጉባዬ በሆለታ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን የፍሬ ሀይማኖ ሰንበት ት/ቤት 41ኛ ዓመት በማስመልከት የተዘጋጀ ጉባኤ ታላላቅ መምህራን አባቶች፣ሰባኪያን እና ዘማሪዎች ስለሚገኙ እርሶም የበረከቱ ተካፋይ ይሁን እያለች ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ታሳስባለተ
"ኑ በእግዚአብሄር ደስ ይበለን"መዝ 95:1
share & join
group

https://t.me/fra_haymanot_16፡
channal

@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት

@yoniyekidye

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

12 May, 09:59


💛 ዳግም ትንሳኤ 💛
እንኳን ለዳግም ትንሳኤ
በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!
share & join
group

https://t.me/fra_haymanot_16
channal

@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት

@yoniyekidye

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

06 May, 08:04


አይቀርም በሆለታ መንበረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ልደትሽ ልደታችነው እያልን በልደቷ ዋዜማ ማለትም በ30 ታላቅ የአእላፍ ዝማሬ በመዘጋጀቱ የተዋህዶ ልጆች የሆናቹ በሙላ ላልሰማ በማሰማት እና በቦታው ተገኝተን ለእናታችን ምስጋና እናቅርብ

share & join
group

https://t.me/fra_haymanot_16
channal

@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት

@yoniyekidye

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

05 May, 12:20


ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም
ተነስቷል በዚህ የለም😍

share & join
group

https://t.me/fra_haymanot_16
channal

@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት

@yoniyekidye

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

03 May, 18:49


ቀዳም ስዑር
ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ
የጌታችንን መከራ በማሰብ
በፆም ታስባ ስለምትውል
የተሻረች ቅዳሜ ተብላ ተሰይማለች።

share & join
group

https://t.me/fra_haymanot_16
channal

@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

03 May, 04:31


🕊    †    ሰሙነ ሕማማት   †    🕊

▬▬▬▬▬▬  †  ▬▬▬▬▬▬

         [    አርብ   ]

▬▬▬▬▬▬  †  ▬▬▬▬▬▬

†   የስቅለት ዓርብ ይባላል   †

ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና [ ማቴ ፳፯፥፴፭ ] የስቅለት ዓርብ ይባላል።

†   መልካሙ ዓርብ ይባላል   †

ከጌታ ስቅለት በፊት በተለይም በሮማውያን ህግ የወንጀለኛ መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል ጌታችን በደሙ ቀድሶ የምህረት ፣ የሕይወት አርማ ፣ የዲያቢሎስ ድል መንሻ ስላደረገው ፤ በሞቱ መልካሙን ሕይወት ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ይባላል።

▬▬▬▬▬▬  †  ▬▬▬▬▬▬
share & join
group

https://t.me/fra_haymanot_16
channal

@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት

@yoniyekidye

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

02 May, 05:11


[    ዘሐሙስ   ]

▬▬▬▬▬▬  †  ▬▬▬▬▬▬

[ †  ጸሎተ ሐሙስ ይባላል  † ]

ጌታችን ለአይሁድ ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ ሲጸልይ በማደሩ [ ማቴ ፳፮፥፴፮ ] ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም [ ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ] ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል።

[ †  የምስጢር ቀን ይባላል   † ]

ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምስጢር [ ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ ] በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምስጢር ቀን ይባላል።

[ †  የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል  † ]

መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድኅነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ [ ሉቃ ፳፪፥፳ ] የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።

[ † የነጻነት ሐሙስ ይባላል  † ]

ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነም [ ዮሐ ፲፭፥ ፲፭ ] የነጻነት ሐሙስ ይባላል።

▬▬▬▬▬▬  †  ▬▬▬▬▬▬
share & join
group

https://t.me/fra_haymanot_16
channal

@fra_haymanot16
ለ ሐሳብ እና አስተያየት

@yoniyekidye

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

28 Apr, 17:29


የሰሙነ ህማማት ሳምንት
እሁድ: ሆሳዕና
ሰኞ:መርገመ በለስ
ማግሰኞ: ዕለተ ጥያቄ
ረቡ: ምክረ አይሁድ
ሐሙስ:ፀሎተ ሐሙስ
አርብ: እለተ ስቅለት
ቅዳሜ: ቀዳም ሰዑር

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

27 Apr, 18:56


ሆሳህና
ይህ የስምንተኛው ሳምንት ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት በነቢዩ በዘካርያስ ላይ የተጻፈው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያይቷ እና በውርንጭላይቷ ላይ ተቀምጦ ሆሳህና በአርያም ሆሳህና ለዳዊት ልጅ ተብ እየተመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ መግባቱ የሚተሰብበት ዕለት ነው፡፡
ሆሳህና ማለት ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

26 Mar, 04:16


መዝሙር
ስብከት
የተለያዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መረጃዎች ያገኙበታል
ኦርቶዶክስ የአለም ሁሉ መዳኛ ናት
Join&share
ቻናላችንን ለመቀላቀል

@gebreal_abate
.group
@likee_melaek

ጥያቄ፣ሀሳብ እና አሐስተያየት ካሎት
@kedus_gebreal_bot

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

06 Feb, 20:02


📕ቁርባን በቅዱሳት መጻሕፍት

🗓 ክፍል አንድ

"ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፡- እንካችሁ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። ጽዋም አንሥቶ አመስግኖ ሰጣቸው እንዲህም አለ፡- ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ ይህ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው። ' ( ማቴ. 26:26-28 )

💦ብሉይ ኪዳን

እግዚአብሔር የቃል ኪዳን ልጆቹን ያሳድጋል
ኢየሱስ የቅዱስ ቁርባንን ዋና ዋና የክርስቲያን ሃይማኖት ሥነ ስርዓት አስተዋወቀ። በብሉይ ኪዳን ዘመን አልነበረም። ይሁን እንጂ የሰማዩ አባታችን እንድንቀበለው ቀስ በቀስ አዘጋጀን። እነዚህ የብሉይ ኪዳን ዘገባዎች የቅዱስ ቁርባን ቅድመ-ምሳሌዎችን ይገልጻሉ።ስለዚህ ከብሉይ ኪዳን ምሳሌዎች ተነስተን ወደ ሐዲስ ኪዳን እንሄድ አለን

💦አቤል
የክርስቶስ ሥጋ እና ደሙ የቅዱስ ቁርባን የመጀመሪያ ጥላ የአዳም እና የሔዋን ታናሽ ልጅ አቤል ነበር። ቃየን መልካሙን እረኛ አቤልን ገደለው። ጌታ ቃየንን፣ ዘፍ 4፡10 “የወንድምህ የደም ድምፅ ከምድር ወደ እኔ ይጮኻል” ብሎታል። የዕብራውያን መጽሐፍ፣ ዕብ 12፡24 ያስታውሰናል “…[የክርስቶስ]  ከአቤል ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር መርጨት ደም ደርሳችኃል”።

💦መልከ ጼዴቅ
መልከ ጼዴቅ ክርስቶስን አስቀድሞ አቅርቧል(በዚያን ጊዜ በዓለም ሁሉ ባሉ ክርስቲያኖች ለእግዚአሔር የሚቀርበው መስዋዕት አስቀድሞ ተገለጠ)ከክስተቱ ከረጅም ጊዜ በኋላ ይህ መስዋዕት ገና በሥጋ ሊመጣ ባለው በክርስቶስ እንደሚፈጸም በነቢዩ ተናግሯል። አብራም ኮሎዶጎመርን ድል አድርጎ ሲመለስ፣ ዘፍ 14፡18 “የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅ እንጀራና የወይን ጠጅ አወጣ፤ እርሱም የልዑል እግዚአብሔር ካህን ነበረ…” በማለት አብራም በዚያን ጊዜ የልዑል እግዚአብሔር ካህን በሆነው በመልከ ጼዴቅ በግልጥ ተባርኮ ነበር። . የዕብራውያን መጽሐፍ ይነግረናል ዕብ 7፡2 "[መልከ ጼዴቅ] በመጀመሪያ ስሙ የጽድቅ ንጉሥ ነው ከዚያም በኋላ የሳሌም ንጉሥ ነው እርሱም የሰላም ንጉሥ ነው። አባትና እናት የትውልድም ቍጥር የሉትም፥ ለሕይወትም መጀመሪያና መጨረሻ የለውም፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ልጅ ተመስሎ ለዘላለም ካህን ሆኖ ይኖራል።
ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ይልቅ የልዑል እግዚአብሔር ካህን ማን ነው?ለእግዚአብሔር አብ መስዋዕት አቀረበ መልከ ጼዴቅም ያቀረበውን ያንኑ እንጀራንና ወይንን እርሱም ሥጋውንና ደሙን አቀረበ?

💦ሙሴ
ሙሴ የመጀመሪያው የእስራኤል ካህን በሲና ተራራ ሥር ለተሰበሰቡት ስድስት መቶ ሺህ የእስራኤል ሕዝብ ሁሉ ኦሪትን አንብብ።የታረደውን የበሬ ደም በሕዝቡ ላይ ረጨ።፡ ዘጸ 24፡8 እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ያደረገው ቃል ኪዳን ደም እነሆ አለ። ኢየሱስ በመጨረሻው እራት ላይ፣ ማቴ 26፡28 “ይህ የቃል ኪዳኑ ደሜ ነው” ብሏል።
ዘፀአት 34:29 ሙሴ ከሲና ተራራ በወረደ ጊዜ ከተራራው ሲወርድ ሁለቱን የምስክር ጽላቶች በእጁ ይዞ... ከእግዚአብሔር ጋር ይነጋገር ነበርና የፊቱ ቁርበት አበራ... በፊቱም መጋረጃ አደረገ።
ኢየሱስ በእንጀራና በወይን መልክ ተሸፍኖ ወደ እኛ ይመጣል።በኃጢአት ከጨለመችው የራሳችን ነፍሳችን ጋር ሲነጻጸር እጅግ የላቀውን የሙሉ ክብሩን ድንቅ ብርሃን መቋቋም አንችልም።።

💦መከሩ
በጥንቷ እስራኤል የፀደይ መከር እህል ወይም ስንዴ ያቀፈ ነበር። ዳቦ ለረጅም ጊዜ የፀደይ መከር ምልክት ነው. የበልግ መከር በአብዛኛው ወይን እና ወይራ ነበር። የወይን ወይን እና የወይራ ዘይት የበልግ መከር ምልክቶች ነበሩ። ዳቦ እና ወይን. ዘሌ 23፡12-13 " ነውር የሌለበትን የአንድ ዓመት ተባት የበግ ጠቦት የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር ታቀርባላችሁ። ከእርሱም ጋር የእህል ቍርባን ከመስፈሪያው ሁለት እጅ ሁለት በዘይት የተለወሰ መልካም ዱቄት ይሁን። ከእርሱ ጋር ያለው የመጠጥ ቍርባን የወይን ጠጅ ይሁን። ካህናት በዘይት ይቀባሉ። ኦሪት ኅብስትንና ወይንን፣ ካህኑንም ከበጉ መሥዋዕት ጋር አንድ ያደርጋል።

💦የድንኳን መስዋዕት
💧የመገኘት እንጀራ
የመገኘት ኅብስት፣ በጥንታዊው ድንኳን እና በኋላ በቤተ መቅደሱ፣ 1 ነገ 7፡48 ኢየሱስን በቅዱስ ቁርባን ተመስሏል።
በማደሪያው ድንኳን ውስጥ እግዚአብሔር ሙሴን ዘጸ 25፡8 "በመካከላቸው አድር ዘንድ መቅደስ ይሥሩልኝ" ብሎ አዘዘው። በመቅደሱ፣ በቃል ኪዳኑ ታቦት ውስጥ፣ እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ ብሎ ነገረው፣ ዘጸ 25፡22 “በዚያም ከአንተ ጋር እገናኛለሁ ከስርየት መክደኛውም በላይ በምስክሩ ታቦት ላይ ባሉት በሁለቱ ኪሩቤል መካከል ሆኜ አገኛለሁ። ከአንተ ጋር... እግዚአብሔር አክሎ፣ ዘጸ 25፡30 “የመሥዋዕቱን እንጀራ ሁልጊዜ በፊቴ በገበታው ላይ አድርግ። ኢየሱስ ማቴ 28፡20 "እኔ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ" ብሎናል ።
ካህኑ አቢሜሌክ ይህን የተቀደሰ እንጀራ ለዳዊት ሰጠው። 1ኛ ሳሙ 21፡6 ካህኑም የተቀደሰውን ኅብስት ሰጠው፤ በዚያም ከበፊቱ እንጀራ በቀር እንጀራ አልነበረምና። ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ሁሉ እንደሆነ አስተምሮናል። ማቴዎስ 12:1 ፡— በዚያን ጊዜ ኢየሱስ በሰንበት በእርሻ አለፈ፤ ደቀ መዛሙርቱም ተራቡ፥ እሸትም ይቀጥፉ ይበሉም ጀመር።… ዳዊትም በተራበ ጊዜ ከእርሱም ጋር የነበሩት አደረጉ፤ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ የመገኘትንም እንጀራ እንደ በላ... እላችኋለሁ፥ ከመቅደስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።
ኢየሱስ ከመቅደስ የሚበልጠውን አሳይቶናል። ሉቃስ 22፡19 “እንጀራም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና፡— ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት፡ አላቸው።

፡ Share & join

channel
@gebreal_abate

Group
@likee_melaek

📩 @kedus_gebreal_bot

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

06 Feb, 16:13


፡ Share & join

channel
@gebreal_abate

Group
@likee_melaek

📩 @kedus_gebreal_bot

የሆ/ደ/ገ/ፍሬ ሀይማኖት ሰ/ት/ቤት

20 Jan, 19:09


፡ Share & join

channel
@gebreal_abate

Group
@likee_melaek

📩 @kedus_gebreal_bot

1,083

subscribers

366

photos

57

videos