ታኦዳኮስ @theothokos Channel on Telegram

ታኦዳኮስ

@theothokos


ታኦዶኮስ (ወላዲተ እግዚአብሔር)

ታኦዶኮስ ይሏታል ትርጓሜውም "የአምላክ እናት" ማለት ነው ለዛም ነው ቅድስት ኤልሳቤጥ ☞ በሉቃ 1፥43 ላይ ''የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?'' ያለችው ስለዚህ ብቸኛዋ የአምላክ እናት ስለሆነች "አንዲት" እያልን እንጠራታለን ።

ታኦዳኮስ (Amharic)

ታኦዳኮስ: የዚህን መልእክት በተናገርን ቦታ በካል ስለተጠበቅንልዎት ወራት በተሽከርንህንስ ወያኔይንዚ!

ታኦዳኮስ አባሊኝ፣ ቸስተአብ እና ትራንስምህ ላይ ይህን ጽሑፍ ላይ ያሉትን የአምላክ እናት በአዲስ ቀናል ለመሳሪያ የብርሃንን ትቢያ እና ለእግዚአብሔር ስለሆነች ። ያለችው ስለዚህ ብቸኛዋ፣ የአምላክ እናት ስለሆነች "አንዲት" እያልን እንጠራታለን ።

ታኦዳኮስ

14 Feb, 04:32


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
የካቲት 7 ቀን 2017 ዓ.ም
የሉቃስ ወንጌል ም 19 ቁ 11 - 28
መልካም ዕለተ አርብ !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#friday

ታኦዳኮስ

13 Feb, 13:13


አቤቱ ሙሉ አርገኝ እኔም ሙሉ እሆናለሁ። አቤቱ አንተ አዋቂ ባለይቅርታ ሐኪም ሆይ፣ ቸርነትህን ባርያህ እሻለሁ፡፡ የነፍሴን ቁስል ፈውስ። በዘለዓለማዊው እቅድህ ያለኝን ቦታ አውቅ ዘንድ የልቡናዬን ዐይን አብራ። ምንም ልቤ እና አእምሮዬ ቢታመሙም ጸጋህ ትፈውሳቸው ዘንድ ፍቀድ።

የሰውን የልቡን ሐሳብ ውስጡንም የምትመረምር ላንተ አቤቱ እኔ ምን እላለሁ? አንተ ነፍሴ ውሃን እንዳጣ ምድረ በዳ አንተን እንደተጠማች ልቤም አንተን እንደምትሻ ታውቃለህ። የአንተ ጸጋ የሚወዱህን ሁል ጊዜ ታድናለች፡፡

ሁልጊዜ ትሰማኛለህና አቤቱ አሁን ከጸሎቴ ፊትህን አታዙር። ልቡናዬ አንተን አዳኟን ከእስራቷ አርነትን ትሰጣት ዘንድ ፍጹም እንደምትፈልግህ ታውቃለህና ፊትህን ከእኔ አታዙር።

አቤቱ መራቤን ታጠግብ ዘንድ መጠማቴንም ታረካ ዘንድ ጸጋህን ወደኔ ላክ፥ ባንተ ያለች መረጋጋትን ፍጹም እሻለሁና።

አቤቱ ጌታዬ ሆይ አንተን የሚወድ እውነትህንም የተጠማ ከቶ መች ጠግቦ ይጠግብሃል? አቤቱ ብርሃንን የምትሰጥ ሆይ ልመናዬን ስማ፥ እንደጸሎቴ ጸጋህን ስጠኝ፥ የፍቅርህ ነበልባል በልቤ ይነድ ዘንድ ከጸጋህ አንዲት ጠብታን በልቤ አኑር። እሳት እሾህና ኮሸሽላን እንደሚያነድ እንዲሁ በልቤ ያለውን ክፉ ሐሳብ የጸጋህ እሳት አቃጥሎ ያጥፋልኝ።

አቤቱ የለመንኩህን ሁሉ አትረፍርፈህ ስጠኝ፥ አምላኬ ነህና ለእኔ ለፍጥረትህ፣ ንጉሴም ነህና ለእኔ ለባርያህ ጸጋህን ፍቀድልኝ። እንደ ቸር አባትነትህም አብዝተህ በጸጋህ ባርከኝ።

ማር ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

ታኦዳኮስ

10 Feb, 05:10


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም
የሉቃስ ወንጌል ም 3 ቁ 7 - 18
መልካም ዕለተ ሰኑይ !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#monday

ታኦዳኮስ

09 Feb, 13:00


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ መግለጫ
ሙሉ መልእክት የሚከተለው ነው፡፡

ጥር ፳፱/፳፻፲፯ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተላለፈ የምህላ ሱባዔ፡-
‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ጉባኤውንም አውጁ፤ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ኣምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ (ኢዩ ፩÷፲፬)
    ሁላችንም እንደምናውቀው ያለንበት ዓለም የመከራ ዓለም ነው፣ መከራው በኛ ስሕተትና ክፋት የመጣና እየሆነ ያለ መሆኑም ይታወቃል፤ እኛ የምንፈጽመው ጥቃቅንና ትላልቅ ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን እንደሚያስቈጣ በቅዱስ መጽሐፍ ተረጋግጦ ያደረ ነው፤ ለዚህም ከነነዌ ነዋሪ ሕዝብ የበለጠ ማስረጃ የለንም፤ የነነዌ ከተማ ነዋሪዎች በፈጸሙት ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን አስቈጥተዋል፤ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ቢሆንም እሱ ምሕረቱን ማስቀደም ስለፈለገ በዮናስ በኩል አስጠንቅቆአቸዋል፤ የነነዌ ነዋሪዎችም በዮናስ በኩል የደረሳቸውን የንስሓ ጥሪ ወዲያውኑ ተቀብለው በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት ንስሓ ስለገቡ እግዚአብሔር ፍጹም ይቅርታ አድርጎላቸዋል፤
•  የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን !
እኛ ሰዎች ዛሬም በየሰዓቱ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ አበሳ እንደምንፈጽም ማወቅ ኣለብን፣

ታኦዳኮስ

09 Feb, 13:00


አበሳውና ኃጢኣቱ ሲበዛ እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነውና ወደ ዳኝነት ተግባሩ ይገባል፤ይህ ደግሞ በሰብአ ትካት በሰዶምና በጎሞራ ያስተላለፈውን ዳኝነት ያስታውሰናል፤ አሁን ያለንበት ዘመን ዓመተ ምሕረት በመሆኑ እግዚአብሔር ለጊዜው ቢታገሠንም በኃጢኣታችን የምንጠየቅበት ጊዜ አዘጋጅቶአል፤ ዛሬም ቢሆን የማናስተውለው ሆነን ካልሆነ በስተቀር እግዚአብሔር ተግሣጹን ማስተላለፍ አላቆምም፤ በምድራችን ላይ በምናደርሰው የተዛባ ተግባር በጐርፍ፣ በድርቅ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በአየር መዛባት እየገሠጸን እንደሆነ ማስተዋል አለብን፤
እግዚአብሔር ከጥንቱ ከጠዋቱ ጀምሮ ምድርን እንድንከባከባት፤ እንድናበጃት፣ እንድናጠብቃትና እንድናለማት አዞናል፤ ሆኖም ይህን ትእዛዙን ገሸሽ አድርገን በኬሜካልና በመርዛም ጋዝ ምድርን በመበከል፣ደንዋን በመመጠርና ራቁቷን በማስቀረት በምናደርገው ድርጊት አበሳ እየፈጸምን እንደሆነ ያወቅነው አይመስልም፤ በዚህም ምክንያት በጐርፍ፣ በድርቅ ለሰው ልጆች በማይመች የኣየር ፀባይ ወዘተ . . . ስጋት ውስጥ እየወደቅን ነው፤

   በሌላም በኩል በምናወሳስበው የአስተዳደር ርእዮትና መሳሳብ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና ያላስፈላጊ አደጋ ላይ እንድወድቅ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጠንቅ ሰላም እየደፈረሰ፣ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሃይማኖት ክብርና ልዕልና እየተነካ ራሳችንንም እየጐዳን ነው፤በዚህ ሁሉ ተግባራችን  እግዚአብሔርን እያሳዘንን ነው፤ ይህ ሊገባንና ሊቈረቁረን ይገባል፤
  የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት
ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል፤ ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣የድርቅ መከሠት፣የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . . ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን፤ ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ  ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፤
እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለዓለማችን ይስጠን፤ ምህላችንንም ይቀበልልን፤
   “እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ” ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
ጥር ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ምንጭ:- EOTC Broadcasting Service Agency

ታኦዳኮስ

08 Feb, 03:48


✍️✍️ሐመር መጽሔት በየካቲት ወር እትሟ!  
  ".. እጅግ ብዙ የመከራ ማዕበል ቢጎርፍም ሁልጊዜም አምላኳ ከእርሷ ጋር ስለሆነ ይገፏት ይሆናል እንጂ አትወድቅም "  የካቲት ዕትም በ፳፻፲፯ ዓ.ም መልእክት ዐምድ
 #የኅትመት ዘመን ፦#የካቲት ፳፻፲፯  ዓ.ም
#አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በልማት ተቋማት አስተዳደር  በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት
•  ገጽ ብዛት፦፳፰
   ዋጋ ፦፵ ብር 
•  ሐመር  መጽሔት  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት  ሥርዓትና ትወፊት ጠብቃ በልማት ተቋማት አስተዳደር  በመጽሔት ዝግጅት ክፍል  በየወሩ የምትወጣ መንፈሳዊ መጽሔት ናት፡፡
•  ሐመር መጽሔት ፴፪ኛ ዓመት  ቁጥር ፪  # የካቲት ፳፻፲፯  ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን " # ‹‹  #የአሕዛብን ስድብ አትሸከሚም ››  በሚል ጠንንካራ መልእክት  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  ምእመናን የክፋት ጠማቂዎችን ሤራ በመታገስና በታላቅ ንቃት በመመልከት ትኩረታቸውን በበዓላቸው ላይ፣ ልባቸውንም ከአምላካቸው ጋር በማድረግ በዓሉን በሰላም እንዳሰለፋና ትንኮሳዎቹ ትዕግሥትን የሚፈታተኑ ቢሆንም ‹‹ራሳቸው አምጥተው፣ ራሳቸው በሚያሮጡ›› ተንኮለኞች ሤራ ላለመጠለፍ ያደረጉት ጥንቃቄ የሚያስመሰግን እንደነበረ ።
       በአጠቃላይ ሲታይ ግን እንዲህ ዓይነቱ የክፉዎች መዳፈር ለሀገርም፣ ለመንግሥትም፣ ለቤተ እምነቶች ግንኙነትም አይጠቅምም፡፡ ድፍረቱ ደግሞ በሰዎች ላይ ብቻ ሳይሆን ሁሉን በሚችል አምላክ ላይ የተፈጸመ ደፍረት በመሆኑ ሀገርና ወገንን የሚያስከፍለው  ዋጋ አሁን እየተቀበልን ካለው በላይ እንዳይሆን መጠንቀቅ  እንደሚገባ ሐመር በመልእክት ዐምድ ታስነብባለች።
   

ታኦዳኮስ

08 Feb, 03:48


  .#ዐውደ ስብከት  ሥር” # “በእንተ ጾም ”  በሚል ርእስ  ጾም ማለት ምን ማለት እንደሆነ ፣ጾም በብሉይ ኪዳን ፣ጾም በሐዲስ ኪዳን ፣የጾም አይነቶች ፣የጾም መሠረታዊ ጥቅሞች ፣ዐቢይ ጾምን የምንጾምበት ምክንያት  በስፋት  ታስነብባለች።
  #በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “# “መኑ ይእቲ ዛቲ   ክፍል አንድ " በሚል ዐቢይ ርእስ  እመቤታችን ማን  እንደሆነች፣ የእመቤታችን ከሴቶች መለየት እንዴት እንደሆነ ፤በነገረ ድኅነት የእመቤታችን ድርሻ  የሊቃውንት መጽሐፍ በማጣቀስ ትምህርት ይሰጣል ።

    #ዐቢይ ጉዳይ  ዐምድ  ሥር  ደግሞ “# መከራው እንጂ ፣ለሞት ጣር እንዳይሆን እንሥራ" በሚል ርእስ  የመከራው ዶፍ መገለጫዎችና ማድረግ ያለብን ጉዳዮች በዝርዝር ያሳያል
   •  #ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር  ደግሞ  "#የኦርቶዶክሳዊ ጋብቻ ትምህርት "በሚል ርእስ   ዐቢይ ርእስ  በመልአከ ሰላም  ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው  ስለ ምሥጢረ ተክሊል፣ጋብቻ እንዴት እንደተጀመረ፣የጋብቻ ዓላማው ፣ከመጀመሪያው ጋብቻ ምን እንማራለን? ጋብቻ ብዙኃኑ የሚመኘው ሲሆን እንደምኞቱ ጸሎቱ የደረሰለት ስእለቱ የሰመረለት ስንቱ ይሆን? በሚል ሰፊት ትምህርት  ታሰተምራለች።
   • #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “#ቅዱስ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ፣ወላዴ አእላፍ አበ ብዙኃን" በሚል ርእስ  ስለ ቅዱሱ መጠራት፣ አገልግሎት በስፋትታስቃኛለች ።
   •  #በነገዋ  ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ  ሥር “ መንፈሳውያን ማኅበራት ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን " በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ክፍል ፫   በሚል ርእስ በ፭ መቶ ክፍለ ዘመን፤በዘመነ ላስታና ድኅረ ላስታ ፣ መንፈሳውያን ማኅበራት ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን በ21ኛው ክ/ዘመን ፣መንፈሳውያን ማኅበራት በአሁኑ ዘመን የሚሉ ርእሶች ይዛለች ።
  #በኪነ ጥበብ ዐምድ "#ጥሪ_ክፍል _፪ "በሚል  ታስነብባለች ።
•  #የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ “የማዕረግ ስም አሰጣጥ # ክፍል ፩ " በሚል ርእስ #በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲስ ኪዳን የአንድምታ ትርጓሜ መምህር የሆኑትን #መጋቤ ሐዲስ ስቡሕ አዳምጤን ጋር የተደረገ  ጥያቄና መልስ ይዛለች።  ።
   ሐመር መጽሔት #፴፩ ኛ ዓመት   ቁጥር ፲፪ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ !

magazine @eotcmk.org  #ሐመር #መጽሔት  ዝግጅት  ክፍል

ታኦዳኮስ

08 Feb, 03:48


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም
የዮሐንስ ወንጌል ም 15 ቁ 26 -እስከ ም 16 ፥ 17
መልካም ዕለተ ቀዳሚት ሰንበት !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#saturday

ታኦዳኮስ

07 Feb, 05:04


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም
የሉቃስ ወንጌል ም 23 ቁ 26 - 31
መልካም ዕለተ አርብ !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#friday

ታኦዳኮስ

06 Feb, 04:17


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም
የዮሐንስ ወንጌል ም 1 ቁ 7 - 15
መልካም ዕለተ ሐሙስ !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#thursday

ታኦዳኮስ

06 Feb, 04:17


3. ከድንጋይ ላይ ሁኖ ወርቅ ዘንግ ወርውሮ ያፈለቀው ማየ ጸሎት ማየ ዮርዳኖስ ብሎ የሰየመው
4. ቁመት ጨምራ ከመሬት ተነስታ እንደ ሰው አፍ አውጥታ የመሰከረችው ዋንጫ
5. ጻድቃኑ ይወቅጡበት የነበረ የድንጋይ ሙቀጫ
6. በማኅበራቸው ጊዜ ሲደግሱባቸው የነበሩ የድንጋይ ገበታዎች
7. ከሀገራቸው ከሮም ያመጡት ባለመስታወት ቋሚ ዕፀ መስቀል፡፡
8. ርዕሰ ዮሐንስ የሚባል ነገሥታት ከነዘውዳቸው፥ ጳጳሳት ከነአክሊላቸውና ከነመስቀላቸው በዚያን ጊዜ      የተሳሉበት ስዕል፡፡
9. ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በማህበረ ፃድቃን ዴጌውን ሆኖ ያስተማረበትና የጠመቀበትን በስዕል የሚያሳይ፡፡
10. ይህ ገዳም በአፄ ካሌብ ዘመነ መንግሥት እንደተገደመና ገዳሙ ራሳቸው የገደሙት የራሳቸው መሆኑን በአክሱም መጽሐፍ ክብረ ነገሥት ላይ ተጽፎ ይገኛል፡፡

መልክኦሙ ለጻድቃን ዘዴጎ፤
ሰላም ለዝክረ ስምክሙ ዘሐዋዝ ጥቀ፤
ለዘይሰምእ በእዝኑ ወበኅሊናሁ ጥንቁቀ::
ጻድቃን ዘዴጎ እበይክሙ ተአውቀ፤
እመ በትህትና ማእከሌክሙ ረፈቀ፤
ሊቀ ጠቢባን ክርስቶስ ዘይሜህር ጽድቀ፡፡
(ምንጭ፤ በዋሊ ጉዞ ላይ የገዳሙ አባቶች በቃል ያስረዱን፣ የብሥራት ዕይታ፣ ማኅበረ ዴጎ የምትል ትንሽ መጽሔት)
/#ዋልድባ_ዋሊ/

ታኦዳኮስ

06 Feb, 04:17


#ማኅበረ_ዴጎ (ዶጌ) /#ማኅበረ_ጻድቃናት)፤ #ጥር_29_ቃል_ኪዳን_የተቀበሉበት፤ #ጥር_30_ምስዋሮን_በተባለ_ቦታ_የተሰወሩበት_ዕለት_ነው፡፡
ማኅበረ ዴጎ ማለት የደጋጎች ሀገር ማለት ሲሆን  የተባለበት ምክንያትም ቅዱሳን ስላሉበት ነው፡፡ በ365 ዓ.ም በአስፍሕ ወልደ አብርሃም ንጉሰ ነገሥት ዘኢትዮጵያ  ዘመነ መንግስት ‹‹ ሮምያ›› ከምትባል መንደር የቅዱስ መጽሐፍ ቃል የሆነውን መሠረት አድርገው፤ 1ኛ ‹‹ ስለ ጽድቅ ብለው የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው መንግሥተ ሰማያት የነርሱ ናትና›› ያለውን 2ኛ ‹‹ አባቱንና እናቱን ሚስቱንና ልጆቹን ያልተወ ሊያገለግለኝ አይችልም›› ብሎ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን አንብበው የዚህን ዓለም ጣዕም ጥቅም ንቀው ሃገራቸውን ትተው መንነው ወደ ኢትዮጵያ የመጡ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ነበሩ፡፡
እነዚህም በአኵሱም ከተማ በስተሰሜን በሐውልቱ ጀርባ ቤተ ቀጢን በሚባል ስፍራ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህል እንደ ተቀመጡ በዚያም ምቾትና ድሎት ስለተሰማባቸው ለዚሁ ለዚሁማ ከሀገራችን ለምን ትተን መጣን? ስለዚህ ሱባዔ ገብተን በጾም በጸሎት ተወስነን የምንሄድበትን ቦታ በረከተ ነፍስ የምናገኝበትን ስፍራ እግዚአብሔር እንዲያሳየን እናመልክት ብለው ሱባዔ ገቡ ጾም ያዙ፡፡
ከሱባዔው በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልፃ ግማሾቹን እያንዳንዳቸው የሚኖሩበትን በዓት አመልክታቸው በዚያም በጾምና በጸሎት ፀንተው እንዲኖሩ ነገረቻቸው፡፡
ሦስት ሺህ/3000/ ያህሉ ደግሞ ከላይ ወደጠቀስነው ሄዱ፡፡ ከነርሱ የተቀሩት ደግሞ ወደ ቆየፃ ሓባር፣ ተድባ፣ አኮርየን፣ ተንስሓ፣ ደብረ አንሳ ወደ ተባሉ ቦታዎች ሄደዋል፡፡
ተጨማሪ ሦስት ሺ ደግሞ እዚያ ከነበሩት ጋርም ተደመሩ፡፡ ከዚያም የቅዱስ ጳውሎስና የቅዱስ ዮሐንስ መመሪያ ተከትለው ማለት ‹‹ከሁሉ ፍቅር ይበልጣል›› የሚለውን ጠብቀው በእምነት በፍቅር በአንድነት ፀንተው በየሳምንቱ እሑድ እሑድ ተዝካረ ሰንበትን ጠብቀው ማኅበር መጠጣት ጀመሩ፡፡ የማኅበረ ዴጎ ታሪክም ተቀየረ ፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በአምሳለ ነዳይ ድሀ መስሎ በመካከላቸው ተገኘ፡፡  ከእነርሱ ጋርም አንድ ማኅበርተኛ ሁኖ እንዲታወቅ ጠየቃችው፣ እነርሱም ፈቀዱለት እና አንዱ የማኅበሩ አባል ሆነ፤ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህልም ከነርሱ ጋር ሳይለይ ቆየ፡፡ በዚሁ ጊዜ ‹‹እስቲ ለኔም ተራ ስጡኝ እንደአቅሜ ዝክር ላውጣ፡፡›› አላቸው፡፡ በዚህ ግዜ ግን ድህነቱን አይተው ‹‹አይሆንም አንተ ድሀ ነህ ከኛ ጋር ሁነህ በዓሉን አክብር እንጂ ምን አለህና ነው የምትደግሰው ይቅርብህ›› አሉት፡፡ እርሱም ‹‹አይሆንም ስጡኝ እንጂ›› አላቸው እነርሱም ካልክማ ብለው ቀን ወስነው ሰጡት፡፡ ቀኑም ጥር 29 ነበር፡፡
ከማኅበርተኞቹ መካከል አሳላፊ ወይም ሙሴ  ‹‹ሣይዳ ›› የሚባል ሰው ነበር፡፡ ይህም ሰው እንግዳና ድሀ ሰው ፈጽሞ አይወድም ነበርና ጌታችንም ከማኅበርተኞቹ መካከል ሲገኝ ደሀ መስሎ ስለነበር በጣም ይጠላው ነበር፡፡ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ከነርሱ ጋር ሲቀመጥም አንድ ቀን ስንኳ አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ ሰጥቶት አያውቅም ነበር፡፡ የሆኖ ሆኖ የጌታችን ማኅበር መድረሱ አልቀረም ደረሰ፡፡ እንደማኅበሩ ሥርዐት የወይን ጠጅ የሚጠመቅባቸውን ጋኖች የሚያጥበው ሙሴው /አሳላፊው/ ነው፡፡ ስለሆነም በሥርዐቱ መሠረት ጌታችን ሙሴውን  ጠርቶ ጋኖችን እጠብልኝ አለው፡፡ አሳላፊውም በቁጣ  ‹‹አንተ ቤትህ የማይታወቅ፤ ከየት አምጥተህ ማኅበር ልታደርግ ነው አንተ ብሎ›› በማለት አናንቆ አልታዘዝህም ብሎ ሄደ፡፡ ይህን የተመለከተው ጌታም አንድ እረኛ ጠርቶ ‹‹አንተ ልጅ ከብቶችህን እኔ እጠብቅልሃለሁና በዚህ ውሀ አምጣልኝ›› አለው፡፡ ትንሹ እረኛ ልጅ ገምቦውን ይዞ ትንሽ ወጣ እንዳለ ጌታ ዘወትር በሚቀመጥበት ድንጋይ ላይ ሆኖ ዘንጉን ወደ ልጁ አቅጣጫ ወረወረው፣ ዘንጉንም ከልጁ ፊት ሂዶ ተተከለ፡፡ ልጁንም ጠርቶ ዘንጉንም እንዲነቅለው አዘዘው፡፡ ልጁም እንደታዘዘው ዘንጉንም ቢነቅለው ውሀ ፈለቀ፡፡ ከርሱ ቀድተህ አምጣልኝ አለው፡፡ ልጁም ከዚህ ውሀ ቀድቶ አመጣለት ጋኖቹን አጠባቸው፡፡

በበዓሉ ቀን ማህበርተኞቹ ምን ሊያበላን ነው፣ ምን ሊያጠጣን ነው ሳይሉ ኹሉም ተሰበሰቡ፡፡ ጌታችንም በፊታቸው ጋኖቹን ቢባርካቸው የወይን ጠጅ ሞልተው ተገኙ፡፡

ቀድቶ ቢሰጣቸውና ቢቀምሱትም በጣም ግሩም ጣፋጭ ስለነበር እጅግ አደነቁ፡፡ እነርሱም ጌታን ከጻድቃን አንዱ ስለመሰላቸው ከእግሩ ላይ ወድቀው እስካሁን ድረስ ሳንበድልህ አልቀረንምና ይቅር በለን ብለው ለመኑት፡፡ ተነሱ ብሎ ካስነሳቸው በኋላ እናንተ ምንም አልበደላችሁም የጠየኳችን እድርጋችኋል የበደለኝ ግን አሳላፊው ነው በማለትና አንድም  ቀን ስንኳ አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ አልሰጠኝምና አፈራርዱኝ አላቸው፡፡ ነገር ግን ሙሴው/አሳላፊው/ የማያፍር ደፋርና ርጉም ስለነበር ‹‹ይህ ሰው ጌታችን በልቶ አልበላሁም ፣ ጠጥቶ አልጠጣሁም የሚል ስለሆነና ስለማይጠግብ ነው እንጂ እንዲያውም ለናንተ አንድ አንድ ዋንጫ ሲሰጣችሁ ለእርሱ ሁለት ሁለት ነበር የሚሰጠው ብሎ የሐሰት ቃል መለሰ፡፡

ጌታችንም እንግድያስ እኔ የጠጣሁበት ዋንጫ ትቅረብና ትመስክርብኝ አለው፡፡ በዚሁ ተስማምተው አሳላፊው/ሙሴው/ ሄዶ አንድ ሸራፋ ዋንጫ አምጥቶ በዚህ ነበር የሚሰጠውና የሚጠጣው ብሎ አቀረበ፡፡ ዋንጫዋም ከተቀመጠችበት አንድ ክንድ ከስንዝር ተነስታ ጽዋይቱን ስትመሰክር ‹‹ዓለማትን የፈጠረ አምላክ ምስክሬ ነው እኔ የያዝኩትን የወይን ጠጅ ዕቃ ሙሴም በእጆቹ አልያዝኩትም በከንፈሩ አልነካኝም በሌሎቹ ሰዎች እጅ ግን ተይዤ ያየን ነበር›› አለች ያን ጊዜ እንደ ዳታን እና አቤሮን ምድር ተከፈተችና ሙሴውን ከነልጁ ዋጠቻቸው፡፡ 

ማኅበረ ፃድቃንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑ ተረድተው እንደገና ከእግሩ ወድቀው ይቅርታ እንዲያደርግላቸው ለመኑት፡፡ ቀኑም ጥር 29 ነበር፡፡  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይቅርታ ካደረገላቸው በኋላ ስማችሁ የጠራ በስማችሁ ተዝካር ያወጣ በስማችሁ ድሆችን የረዳ፣ ያለበሰ፣ ያጎረሰ፣ የሰጠ፣ የመጸወተ፣ ቤተ ክርስትያናችሁን  የሠራ፥ ያሠራ፣ እሰከ 14 ትውልድ ደረስ ምሬላችኋለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣቸው፡፡ ይህችን ቦታችሁ መጥቶ የሳመ እየሩሳሌም እንደሳመ አድርጌላችኋሁ አላቸው፡፡
በኦሪት ሔኖክ፣ ዕዝራ፣ ኤልያስ፤ በሐዲስ ኪዳንም እነ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድና በየጊዜውም እንደሚሰወሩ ቅዱሳን እንደዚሁም ጌታችን እነዚህን የማኀበረ ዴጎ ጻድቃንንም ከሞት ተሰወሩ ብሎ በበነጋታው ጥር 30 ቀን ሠውሯቸዋል፡፡ በዚህም መሠረት ይህ ታላቅ በዓል ሆኖ ዛሬም በየዓመቱ ጥር 30 ቀን በደማቅ ሁኔታ ሲከበር ይኖራል፣ ይከበራልም፡፡

በገዳመ ዴጎ በዓይን የሚታዩ፥ በእጅ የሚዳሰሱ ተአምራት የታየባቸውና የተደረገባቸው ንዋያት እስካሁንም አሉ፡፡ ወደ አኵሱም ስትሄዱ ታዩት ዘንድ እንጠቁማችሁ፡፡
1. ጌታችን የተቀመጠበትንና የቆመበትን ድንጋይ ከነምልክቱ
2. ምስዋሮም የሚባል ጻድቃኑ የተሰወሩበትን ስፍራ

ታኦዳኮስ

05 Feb, 03:33


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 15 ቁ 22 - 39
መልካም ዕለተ ረቡዕ !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#wednesday

ታኦዳኮስ

01 Feb, 09:23


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም
የሉቃስ ወንጌል ም 18 ቁ 1 - 9
መልካም ዕለተ ቀዳሚት ሰንበት !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#saturday

ታኦዳኮስ

30 Jan, 15:00


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 6 ቁ 5 - 19
መልካም ዕለተ ሐሙስ !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#thursday

ታኦዳኮስ

28 Jan, 22:02


ስጋዋንም ያሳዪት ዘንድ ወደ መቃብርዋ በአደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ስጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ ነገራቸው። ሀዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን እርገቷን ስለ አላዩ እጅግ አዘኑ ስጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኃላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ስጣቸው እነርሱም እስከ ነሀሴ አስራ ስድስት በረስፋ ኖሩ።

የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት አመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሶስት አመት ከሰባት ወር በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት አመት በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት አመት ከሶስት ወር ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት አመት ነው።

የህይወት የድኅነት አለኝታ የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በፀሎቷም ከክፉ ነገር ይጠብቀን፤ በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።

(ስንክሳር ዘተዋሕዶ - #ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)

ታኦዳኮስ

28 Jan, 22:02


#በዓለ_አስተርዕዮ_ማርያም - #ጥር_21
ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በአል መታሰቢያ ነው። ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃበሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም አለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኃላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።

በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦
"ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሩዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሀንስን በዚች ሰአት አምጣው።እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሀዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።

በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሀንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ አለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ህይወት ትሄጂአለሽና። ይህም ስሙ ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኃላ ነው።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላትእግዚአብሄርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።

በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሀዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።

ወዲያውኑ ሁሉም ሀዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት አምላከችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆን ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ አለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት።

በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሀዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኃችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም አለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ።

ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት።

እመቤታችንም ማርያምም ይህን ነገር ከሀዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ።የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።

ፀሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሀዋርያትን እንዲህ አለቻቸው እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረገ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለቸወበት ቤት በቀረብ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።

ከዚህም በኃላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም አላት።

ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሀወሰርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጃዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሀዋርያትን አዘዛቸው።

ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት።

እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።

ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም አለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።

እመቤታችንም ከአረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሄር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።

ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሀዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።

በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።

ሀዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሀዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።

ታኦዳኮስ

25 Jan, 07:36


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
ጥር 17 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 5 ቁ 1 - 17
መልካም ዕለተ ቀዳሚት ሰንበት !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#saturday

ታኦዳኮስ

22 Jan, 05:07


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም
የማርቆስ ወንጌል ም 10 ቁ 29 - 31
መልካም ዕለተ ረቡዕ !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#wednesday

ታኦዳኮስ

20 Jan, 07:25


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
ጥር 12 ቀን 2017 ዓ.ም
የዮሐንስ ወንጌል ም 1 ቁ 44 - ፍጻሜ
መልካም ዕለተ ሰኑይ !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል

ታኦዳኮስ

20 Jan, 07:25


ጌታችን መጻጉዕን የፈወሰበትን፣ አልዓዛርን  ከሞት ያስነሣበትን፣ ዓይን ያበራበትን፣ በአጋንንት እስራት የተያዙትን ነጻ ያወጣበትን፣ ዕለት በክብረ በዓል ደረጃ ሳታከብር የቃናው ተአምር ከጌታችን ንዑሳን በዓላት ውስጥ ተደምሮ እንዲከበር ያደረገችበት ጥልቅ ምሥጢርን ስለያዘና ስላዘለ ነው፡፡ ይህ ሰርግ የሚደረገው  ጌታችን  ከአእላፋት  መላእክቱ  ጋር በሚመጣበት  በዕለተ  ምጽአት  ነው፡፡ ዕለተ  ምጽአት  ሙሽራዪቱ  ቅድስት  ቤተ ክርስቲያን በቅዱሳን ምግባር አጊጣ  የምትታይበት፣ የጽድቅ ዘይት ይዘው መገኘት የቻሉ ልባሞች  ከቤተ  ክርስቲያን ጋር ሰርጉን የሚታደሙበት፣ እንደ ቃናው ደስታ በሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት  መላእከት በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ  በኵራት ማኅበር፥  የሁሉም  ዳኛ ወደሚሆን ወደ  እግዚአብሔር፥  ፍጹማንም ወደ ሆኑት  ወደ ጻድቃን  መንፈሳት የምንደርስበት ዕለት ነው፡፡ (ዕብ.፲፱፥፳፪)

ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ የቃናን ሰርግ ከሰማያዊው ሰርግ ጋር አሰናስሎ ሲያመስግን እንዲህ ይላል፡፡ “ወደ ሰርግ በዓልዋ ዕለት ደስታን ይዘህላት ስለመጣህ ቃና ታመስግንህ! አክብረኸዋልና ሙሽራው የደፋው ዘውድ አንተን ያከብርሃል።  የሙሽራዋ አክሊልም የአንተን ድንቅ ሥራ ያደንቃል፡፡  ቤተ ክርስቲያንህን በሙሽራዋ መስለሃታልና  በቃና  መስታወትነት  ምሳሌዎች ሁሉ ትርጒማቸውን  አገኙ፡፡ የቃናዎቹ እንግዶች ደግሞ አንተ የመረጥሃቸው (ወደ  ሰማያዊው ራት) የጠራሃቸው  ናቸው::  ምጽአትህንም በሰርግ  ቤቱ ደስታ መሰልከው::”

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደ ሙሽራ አጊጣ፣ ለበጉ ሰርግ ያለ እድፍና ያለ ነውር ውብ ሆና ተዘጋጅታ በምትቀርብበት በዚያ ሰማያዊ ሰርግ ለመገኘትና ወደ በጉ ሰርግ ራት ገብተን፣ ካጌጡ ቅዱሳን ጋር ለመቀመጥና ለመብላት የበቃን ያድርገን!

መልካም በዓል!

ምንጭ፡- ትርጓሜ ወንጌል እና “ቃና ዘገሊላ”
በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ

ታኦዳኮስ

20 Jan, 07:25


ቃና ዘገሊላ
እንኳን አደረሳችሁ!

በቤተ ክርስቲያናችን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካደረጋቸው  እጅግ ብዙ ተአምራት መካከል በዓል አድርጋ የምታከብረው የቃና ዘገሊላውን ተአምር ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ተመዝግቦ እናገኘዋለን፡፡  “በሦስተኛውም  ቀን  በገሊላ  ቃና ሰርግ  ነበረ፥  የኢየሱስም  እናት በዚያ  ነበረች፤ ኢየሱስም  ደግሞ  ደቀ  መዛሙርቱም ወደ  ሰርጉ ታደሙ። የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፦ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም” አለችው። ኢየሱስም፦ “አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?  ጊዜዬ  ገና  አልደረሰም”  አላት። እናቱም  “ለአገልጋዮቹ፦   የሚላችሁን  ሁሉ አድርጉ” አለቻቸው። አይሁድም  እንደሚያደርጉት የማንጻት  ልማድ   ስድስት  የድንጋይ  ጋኖች   በዚያ  ተቀምጠው  ነበር፥   እያንዳንዳቸውም  ሁለት ወይም  ሦስት   እንስራ   ይይዙ ነበር። ኢየሱስም፦ “ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው” አላቸው። “እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው” አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።  “አሁን ቀድታችሁ  ለአሳዳሪው  ስጡት”  አላቸው፤  ሰጡትም። አሳዳሪውም  የወይን ጠጅ  የሆነውን  ውኃ  በቀመሰ ጊዜ  ከወዴት  እንደ  መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ ፦ሰው  ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን  የወይን ጠጅ  ያቀርባል፥  ከሰከሩም  በኋላ  መናኛውን፤ አንተስ  መልካሙን  የወይን  ጠጅ  እስከ  አሁን  አቆይተሃል”  አለው። ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።” (ዮሐ.፪፥፩-፲፩)

ታኦዳኮስ

18 Jan, 20:35


#ጌታችን_ለምን_በሌሊት_ተጠመቀ?
በኃጢአት ጨለማ ስለነበረ ሕዝብ የጽድቅ ብርሃን እንዲወጣለትና በጨለማ የሚመስል ኦሪት ይኖር ስለነበረ ለሕዝብ ብርሃን የሆነ ወንጌል መገለጡን ለማሳየት ነው፡፡ ኢሳ.9፥2

አንድም ጌታ ልደቱ፣ ጥምቀቱ፣ ትንሣኤው እንዲሁም ምጽአቱ በሌሊት ነው፡፡ ይኽም የሆነበት ምክንያት፡- ሌሊቱን ተከትሎ የሚመጣው ብርሃን በመሆኑ ከሞት ወደ ሕይወት ከጨለማ ወደ ብርሃን ከሲኦል ወደ ገነት የመሸጋገራችን ምሳሌ ነው፡፡

አንድም መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል የሚወርድ ነውና በጌታ ላይ የወረደው ርግብ እንጂ መንፈስ ቅዱስ አይደለም ባሉ ነበር፡፡ በሌሊት ርግብ የለም ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ይታወቅ ዘንድ፡፡

#መንፈስ_ቅዱስ_ለምን_ጌታ_ከውኃ_ከወጣ_በኋላ_ወረደ?
ሀ. ዮሐንስን ያከብሩት ነበርና መንፈስ ቅዱስ የወረደው ለዮሐንስ እንጂ ለጌታ አይደለም ይሉ ነበርና ምክንያቱን ጌታ ውኃ ውስጥ እያለ ከዮሐንስ አልተለየም ነበርና፡፡
ለ. ውኃን የሚባርክ መልአክ እንዳለ ያውቁ ነበርና ውኃውን ለመባረክ አንጂ ለጌታ አይደለም እንዳይባል፡፡
ሐ. ማረፊያ ያጣች ርግብ በባሕር ስትበር አረፈችበት ይሉ ነበርና ሐሳባቸውን በሙሉ ያጠፋ ዘንድ ከውኃ ውስጥ ከወጣ በኋላ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወረደ፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ታኦዳኮስ

18 Jan, 20:35


#በጥምቀት_ዙሪያ_የሚነሱ_ጥያቄዎች_እና_መልሶቻቸው
#ጌታችን_ለምን_ተጠመቀ?
1. ምሥጢርን ለመግለጥ፡-
ጌታችን በፈለገ ዮርዳኖስ ሲጠመቅ ምስጢረ ሥላሴ ግልፅ ሆኗል፡፡ አብ በደመና “የምወደው የምወልደው ልጄ ይህ ነው” በማለቱ አብ የወልድ አባት መሆኑ ታወቀ፡፡ መንፈስ ቅዱስም የባሕርይ ሕይወቱ መሆኑን ሲያስረዳ በአምሳለ ርግብ በራሱ ላይ ተቀመጠ ወልድም በተለየ አካሉ በዮርዳኖስ ሲጠመቅ ታየ፡፡ ስለዚህ ምሥጢርን ለመግለጥ ስንል የአንድነት የሦስትነት ምስጢር በጐላ ሁኔታ እንዲታወቅ ተጠመቀ ማለት ነው፡፡ /ማቴ. 3፥16/

2. ትንቢቱን ለመፈፀም፡-
በመዝሙር 46/47/፥16 ላይ “አቤቱ ውሆች አዩህ፣ ውሆችም አይተውህ ፈሩ ጥልቆች ተነዋወጡ ውሆችም ጮኹ፡፡” ተብሎ በቅዱስ ዳዊት የተነገረውን ትንቢት ለመፈፀም ተጠመቀ፡፡

3. አርአያ ሊሆነን፡-
ተጠምቆ እንድንጠመቅ አደረገን ሥርዓትን ሠራልን ቀድሞ በአርአያውና በአምሳሉ እንደፈጠረን አሁንም አርአያ ምሳሌ ሆነን፡፡ ለዚህም ነው ምሳሌን ከእኔ ተማሩ ያለን፡፡ /ማቴ 11፥29/ ለትምህርት ለአርአያ /ዮሐ. 13፥1-17/

4. የዕዳ ደብዳቤያችንን ለመደምሰስ፡-
አዳምና ሔዋን ፍዳው በፀናባቸው መከራው በበዛባቸው ጊዜ የሚያቃልልላቸው መስሏቸው ዲያብሎሰ ስመ
ግብርናችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ ባላቸው ጊዜ አዳም ገብሩ ለዲያቢሎስ (አዳም የዲያብሎስ የወንድ አገልጋይ) ሔዋን ዓመቱ ለዲያብሎስ (ሔዋን የዲያብሎስ ሴት አገልጋይ) ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡ ዲያብሎስም ይህንን ደብዳቤ አንዱን በሲኦል አንዱን በዮርዳኖስ አስቀመጠው፡፡ በዮርዳኖስ ያስቀመጠውን ጌታችን ሲጠመቅ እንደሰውነቱ ረግጦ ደምስሶታል፡፡ ይህንን ጽሕፈት ለመደምሰስ ነው ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀው፡፡ ለዚህም ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተፃፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፡፡” ያለው ቆላ 2፥14

#ጌታችን_መች_ተጠመቀ?

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በ5531 ዓመተ ዓለም ዘመነ ሉቃስ ማክሰኞ ጥር 11 ቀን ከሌሊቱ በ10ኛው ሰዓት ነበር፡፡ ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 19 በተጠመቀም ጊዜ ዕድሜው 30 ዓመት ከ13 ቀን ነበር፡፡ /ሉቃ. 3፥23/

#ጌታችን_ስለምን_በ30_ዓመት_ተጠመቀ?
በብሉይ ኪዳን ሥርዓትና ልማድ ካህናት ለቤተ እግዚአብሔር ተልእኮ እና መንፈሳውያን አገልግሎቶች ከ30 ዓመት ዕድሜ በፊት አደባባይ አይወጡም ነበር፡፡ እጅግ አስፈላጊ እንኳ ቢሆን ከ20 እና 25 ዓመት አስቀድሞ ለአገልግሎት መሰየም ልማድ አልነበረም፡፡ የቤተ እግዚአብሔር አገልጋዮች በዕድሜና በዕውቀት የበሰሉ፣ በጠባይና በሥራ ልምድ የተፈተኑ ተልዕኳቸውን በብቃት ለመወጣት በተገልጋዩ ሕዝብ ዘንድ የተመሰከረላቸው መሆን ነበረባቸው፡፡ /ዘፀ. 4፥3፤1ዜና መዋ. 23፥24፤ 1ጢሞ. 3፥6-10/ ያንን ሥርዓት ለመፈጸም ጌታችን የተጠመቀውና ለትምህርተ ወንጌል የተገለጠው በ30 ዓመቱ ነበር፡፡

ዮሐንስ መጥምቅም የጌታን መምጣት ለማወጅ በዮርዳኖስ ይሁዳ ምድረ በዳዎች ወጥቶ የታየው ከ30 ዓመት ዕድሜው በኋላ ነው፡፡ ሌላው ዐቢይ ምክንያት የሰው ሁሉ መጀመሪያ አዳም የ30 ዓመት ጎልማሳ ሆኖ ተፈጥሮ በ40ኛ ቀን ተሰጥቶት ኋላም በኃጢአት ምክንያት ያስወሰደውን ልጅነት ለማስመለስ ነው፡፡

ክርስቶስ የተጠመቀው ክብር ሽቶ ሳይሆን የአብ የባሕርይ ልጅነቱን (የባሕርይ አምላክነቱን) ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ለማስመስከር፣ ውኃውን ለመቀደስ፣ የአዳምን ልጆች የእዳ ደብዳቤ ለመደምሰስና በስህተት የጠፋውን የልጅነት ክብር ለመመለስ ነው፡፡ ጌታ ተጠምቆ ከውኃው ከወጣ በኋላ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ በማረፍ አብ በደመና ‹‹ይህ ልጄ ነው›› ብሎ ሲመሰክርለት ምሥጢረ ሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በጉልህ ተረጋግጧል፡፡ /ማቴ. 3፥16/

#ጌታችን_በዮሐንስ_እጅ_ለምን_ተጠመቀ?

ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ ሲሆን በአገልጋዩ በቅዱስ ዮሐንስ እጅ ይጠመቅ ዘንድ በፍጹም ትሕትና ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ ይህንንም ያደረገልን አብነት ሊሆነን ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታችን ቅዱስ ዮሐንስን ‹‹መጥተህ አጥምቀኝ ›› ብሎት ቢሆን ኖሮ ነገ ነገሥታቱና መኳንንቱ ካህናቱን መጥታችሁ አጥምቁን ባሉ ነበር ስለዚህ እንዲህ እንዳይሆን ነው፡፡ ጌታችን ‹‹ጌታ ስሆን በባርያዬ እጅ እንደተጠመቅሁ እናንተም ወደ ቤተክርስቲያን ሄዳችሁ በካህናት እጅ ተጠመቁ›› ሲል ነው፡፡

ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀው ልጅነትን የምታሰጥ ጥምቀትን ባርኮ ቀድሶ ሊሰጠን እንጂ ክብር እንዲሆነው አይደለም፡፡ ምክንያቱም፡- እርሱ እከብር አይል ክቡር እጸድቅ አይል ጻድቅ ነውና፡፡

#ቅዱስ_ዮሐንስ_ጌታችንን_በማን_ስም_አጠመቀው?

ጌታችን ዮሐንስን አጥምቀኝ ባለው ጊዜ "ሌላውን በአንተ ስም አጠምቃለሁ አንተን በማን ስም ላጥምቅህ? በአብ ስም እንዳላጠምቅህ አብ አባትህ ባንተ ሕልው ነው በወልድ ስም እንዳላጠምቅህ ወልድ አንተ ነህ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንዳላጠምቅህ መንፈስ ቅዱስ ሕይወትህ ባንተ ሕልው ነው ታዲያ በማን ስም ላጥምቅህ?" ብሎ ቢጠይቀው ጌታም ‹‹እንደ መልከጼዴቅ ሥርዓት አንተ የዓለም ካህን ብርሃንን የምትገልጥ የአብ የባሕርይ ልጅ ሆይ ይቅር በለኝ›› ብለህ አጥምቀኝ አለው፡፡

#ዮሐንስ_ጌታን_ሲያጠምቀው_እጁን_ለምን_አልጫነበትም?
- ዮሐንስ በጥምቀት አከበረው /ልዕልና ሰጠው/ እንዳይባል፡፡
- መለኮትን በእጅ መንካት ስለማይቻል

#ጌታችን_ጥምቀቱን_ለምን_በዮርዳኖስ_አደረገው?
በኢየሩሳሌም አካባቢ ብዙ ወንዞች ኩሬዎችና ሐይቆች መኖራቸው የታወቀ ነው፡፡ ጌታ ጥምቀቱን በዮርዳኖስ ያደረገው ስለዚሁ አስቀድሞ የተነገረውን ትንቢት መፈጸሙን ለማረጋገጥ ነው፡፡ ‹‹ባሕር አይታ ሸሸች ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ›› /መዝ.113፥3/ ከዚህም ጋር ከላይ ምንጩ አንድ የሆነው ዮርዳኖስ ዝቅ ብሎ በደሴት ተከፍሎ እንደገና እንደሚገናኝ በግዝረት በቁልፈት (በመገዘርና ባለመገዘር) ተለያይተው የነበሩ ሕዝብና አሕዛብ መላው የአዳም ልጆች በጌታችን ጥምቀት አንድ መሆናቸውን የሚገልጽ ትርጉም አለው፡፡ እስራኤል ዮርዳኖስን ተሻግረው ምደረ ርስት ገብተዋል፡፡ ያመኑ የተጠመቁ ምዕመናንም በጥምቀት ገነት መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉ፡፡ ሌላው በዮርዳኖስ ተጥሎ የነበረውን የዕዳ ደብዳቤ ይደመስስልን ዘንድ /ቈላ. 2፥14/

#ጌታችን_ለምን_በውሃ_ተጠመቀ?
እግዚአብሔር አምላክ በዘመነ ኦሪት ሰብዐ ትካትን በንፍር ውሃ ፈርኦንና ሰራዊቱን በኤርትራ ባሕር ካጠፋ በኋላ ሰዎች ውሃ ለመዓት እንጂ ለምሕረት አልተፈጠረም ይሉ ነበርና ለምሕረት እንደተፈጠረ ለማጠየቅ በውሃ ተጠመቀ ( ዘፍ 7÷17፤ ዘጸ 14÷1-29)

አንድም ውሃ እሳትን ያጠፋል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ከገሃነመ እሳት ትድናላችሁ ሲል ነው፡፡

አንድም ውሃ መልክን ያሳያል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ መልክዓ ሥላሴን የአምላክን ቸርነት ርህራሔ ታያላችሁ ሲል ነው፡፡

አንድም በማር በወተት ቢጠመቅ ኖሮ እነዚህ ለባለጸጎች እንጂ ለድሆች አይገኝም ውሃ ግን በሁሉ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ጥምቀት የታዘዘ ለሁሉ ነው ሲል ነው፡፡

አንድም ማርና ወተት ቢታጠብበት ያቆሽሻል እንጂ አያነጣም ውሃ ግን እድፍን ያስለቅቃል እናንተም በማየ ገቦ ብትጠመቁ ከኃጢአት ትጠራላችሁ ሲል ነው፡፡

አንድም ማርና ወተት ተክል ላይ ቢያፈሱት ያደርቃሉ እንጂ አያለመልሙም ውሃ ግን ያለመልማል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ልምላሜ ሥጋ ወነፍስ ታገኛላችሁ ሲል ነው፡፡ (ዮሐ 19÷35)

ታኦዳኮስ

18 Jan, 04:01


#ከተራና_ባሕረ_ጥምቀት_ጥምቀተ_ባሕር #ታቦታት_ለምን_ከመንበራቸው_ወጥተው_ያድራሉ?
#በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት #ሥርዐተ_ከተራ ……. (#ያንብቡ)

#ከተራ_፤ ከተረ (ዘጋ፣ አቆመ፣ አገደ፣ ከለከለ) ካለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ውሃን መከተር ወይም ውሃ መገደብ (መዝጋት፥ ማቆም፥ ማገድ፥ ማጠር፥ ዙሪያውን መያዝ፥ መክበብ፥ መከልከል) ማለት ነው፡፡
#ከተራ_ለምን_ተባለ?
በጥምቀት በዓል ዋዜማ በጥር 10 ቀን ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውሃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ወይም ጉድጓድ ተቆፍሮ፤ ድንኳን ይተክላል፥ ዳስ ሲጣል ይውላል (ምክንያቱም ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናምና የበረዶ ወራት ስለሆነ ቅዝቃዜውም በወንዞች አጠገብ ስለሚያይል በባሕረ ዮርዳኖስ፥ በዕደ ዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ ሰዎች ድንኳን ተክለው፥ ዳስ ጥለው ያድሩ ስለነበረ ነው)፡፡ ነገር ግን በዚህ ወቅት የምንጮች ውሃ ደካማ በመሆኑ ውሃው እንዲጠራቀም ወንዶች ጉድጓድ እየቆፈሩ፥ ሴቶች ውኃ በእንስራ እየቀዱ ከወንዞችና ከምንጮች ውኃውን ይከትራሉ፥ ይገደባሉ (አሁን በከተሞች ሰው ሰራሽ ግድብ ይገደባል)፡፡ የምዕመናኑ አብዛኛው ስራ ውሃውን መከተርና መገደብ በመሆኑ ዕለቱ #ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
#አንድም በኢያሱ መሪነት እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ባሕር ሲሻገሩ ታቦቱን ያከበሩ (የያዙ) ካህናት ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ከወንዙ መሃል ቆመው ነበር ውኃውም እንደ ባሕረ ኤርትራ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ቆሞ ነበርና ይህንንም ለማስታወስ ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡
#አንድም ጌታችን በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የላይኛው ሸሽቶ እንደ ክምር ተቆልሏል (ከአዳም ጀምሮ እስከ መድኅን መወለድ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ተቋርጦ ለመቅረቱ፥ ከአበው ወደ ውሉድ ላለመተላለፉ ምሳሌ)፤ የታችኛውም ወደ ታች ሸሽቶ በመድረቁ (የአዳም ኀጢአት ከሥሩ እንደተነቀለ ዛፍ ሆና ለመውደቋ ምሳሌ) ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡
፠ውኃ የሚከተርበት ቦታ ‹‹#ባሕረ_ጥምቀት(#ጥምቀተ_ባሕር_››) (#የታቦት_ማደሪያ) እየተባለ ይጠራል፡፡ ውኃው የሚከተረውም በማግስቱ ጥር 11 ቀን ለሚከበረው የጥምቀት በዓል መጠመቂያና የጥምቀትን በዓል ለማክበር እንዲሆን ነው፡፡ ሌሊት ማኅሌት ተቁሞ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ፥ ጠዋት ጸሎት ተደርሶ የሚጠመቅ ሕፃን ካለ እዚያው ውስጥ ይጠመቃል፡፡ ጐበዛዝትም ለቡራኬ ይዋኙበታል ምዕመናንም እንዲሁ ለቡራኬ ይረጩታል፡፡ ያ ስፍራ በዘልማድ ጥምቀተ ባሕር ተብሎ ይጠራል፡፡
#ሥርዐተ_ከተራ
፠ ታቦተ ሕግ ይዞ መጓዝና ወደ ወንዝ መውረድ የተጀመረው በአሮን ልጅ በአልዓዛር ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ቀድሞ በሙሴ ኋላ በኢያሱ መሪነትም ታቦተ ሕጉን ይዘው የዮርዳኖስን ባሕር መሻገራቸውንም ልብ ይሏል፡፡ የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁት ጊዜ ከስፍራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት፡፡ /ኢያ.3፥3/ እንዲል፡፡
፠ የከተራ ዕለት ድንኳኑ ተተክሎ፥ ዳሱ ተጥሎና ውሃው ተከትሮ ሁሉም ነገር ከተስተካከለ በኋላ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ የደወል ድምፅ እንደተሰማ ከልጅ እስከ አዋቂ በነቂስ ተወጥቶ በዐፀደ ቤተ ክርስቲያንና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች ይሰበሰባሉ፤ የየአድባራቱና የገዳማቱ ታቦት በካህናት አማካይነት በወርቅና በብር በተንቈጠቆጠ መጐናጸፊያ እየተሸፈኑ በታቦት ጉዞ (በዝግታ) ወደ ጥምቀተ ባሕሩ ይጓዛሉ፡፡ በዚህም ጊዜ፤
*ባለ መስቀል መፆር ሰንደቅ ዓለማና ዓርማ የያዘው ግን ከሁሉም ፊት ፊት እያለ ቀድሞ ይሄዳል፡፡
*የወርቅ (ወርቀዘቦ) ካባና ላንቃ የለበሱና ጥላ የያዙት ቀሳውስትና መነኰሳት ከታቦቱ ጐን፤
*መስቀልና ጽንሐሕ የያዙት ከታቦቱ በፊት ማዕጠንት እያጠኑ ይሄዳሉ፡፡
*እንደ ቀሳውስቱ ተመሳሳይ ልብስ ተክህኖ የለበሱት ዲያቆናት ጥላ፣ ድባብ፣ መስቀልና ቃጭል ይዘው እያቃጨሉ ከቀሳውስቱ በፊት በመሆን ያጅቧቸዋል፡፡
*ወደ ባሕረ ጥምቀቱም ሲወረድ ካባ ላንቃ፥ ጥንግ ድርብ በለበሱ፥ የብር፣ የነሐስ፣ የወርቅ መቋሚያና ጽናጽል በያዙ በማኅሌታውያን መዘምራን ደባትር ሃሌታ፣ በሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ዝማሬና ሽብሸባ፣ በወጣት መዘምራን ደስታ፣ በወንዶች ሆታ፣ በሴቶች እልልታ ዲያቆናቱን ቀድመው እያጀቡ ይሄዳሉ፡፡
*የደብር አለቆችና አበው ካህናት ታቦቱን ተከትለው ይጓዛሉ፡፡
*ሕዝቡም ደግሞ ‹‹#ለጥምቀት_ያልሆነ_ቀሚስ_ይበጣጠስ›› እንዲሉ እንደየችሎታው ያለውን ልብስ (ጃኖ፣ ለምድ፣ በርኖስና የመሳሰለውን) ለብሶና አጊጦ፥ የጀብዱነት ሽልማት ያለው በሽልማቱ አጊጦ፥ ሽማግሌዎችና የጐበዝ አለቃዎችን በማስቀደም ታቦቱን በመከተል በስተኋላ ይሄዳሉ፡፡
**ነገር ግን ሴቶችና ልጆች እንደፈለጋቸው ከፊትም ከኋላም ሆነው ይሄዳሉ፡፡
ባሕረ ጥምቀትም እንደደረሱ ታቦቱ በድንኳን አጠገብ ቆሞ የዓመቱ #ተረኛ_ደብር (#የምራት_ባለተረኛ) “#ወረደ_ወልድ_እምሰማያት_ውስተ_ምጥምቃት_፤ #በፍሥሓ_ወበሰላም” (እግዚአብሔር ወልድ በሰላምና በደስታ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከሰማያት ወደ መጠመቂያው ወረደ) የሚለው #ሰላም ተመርቶ በአግባቡ ከተለዘበ በኋላ ጸሎት ተድርጐ ሲያልቅ ታቦቱ ወደ ድንኳኑ ይገባል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ግሱን ለመቃኘትና ለማሸብሸብ፣ ማኅሌት ለመቆም፣ ቅዳሴ ለመቀደስና ሌላውንም ሥርዐት ለመፈጸም ኃላፊነት ያለባቸው ተረኛ ደብር (የምራት ባለተረኞች) ሲሆኑ ለቀጣዩ (ለከርሞ) ዓመት ተረኞች የሚሆኑና በአሁኑ ዓመት የምራት ባለተረኞችን የሚረዱት ገዳማትና አድባራት ደግሞ ‹‹#አንሺዎች_›› ይባላሉ፡፡
የከተራ ዕለት የየአጥቢያው ሕዝብ በየዓመቱ ተራ እየገባ ራት ከየአካባቢው ስለሚያመጣ ያ ሲበላና ሲጠጣ ከቆየ በኋላ ወዲያው የሌሊቱ ጸሎት(ስብሐተ ማኅሌቱ) በተረኛው ደብር ካህናት ተጀምሮ አገልግሎቱ መላ ሌሊቱን ሲካሄድ ያድራል (እንደ ቀጨኔ ባሉ ታላላቅና የሊቃውንት መፍለቂያ አድባራት ተረኛ ቢሆኑም /በጥምቀተ ባሕሩና በቤተ ክርስቲያናቸው ጭምር/ ባይሆኑም በቤተ ክርስቲያናቸው ማኅሌቱን ቆመውና ቅዳሴውን ቀድሰው ያድራሉ)፡፡ ቅዳሴው የሚቀደሰው ከሌሊቱ 7-9 ሰዐት ነው፡፡ በዚያን ዕለት ምሽት ፈቃደኛ የሆኑ ሽማግሌዎችና ወጣቶች፣ ባልቴቶችና ኮረዳዎች ሕፃናትም ጭምር እዚያው በጥምቀተ ባሕሩ ዙሪያ ስለሚያድሩ እንደ የዕድሜ ደረጃቸው ማለ#ከተራና_ባሕረ_ጥምቀት_ጥምቀተ_ባሕር #ታቦታት_ለምን_ከመንበራቸው_ወጥተው_ያድራሉ?
#በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት #ሥርዐተ_ከተራ ……. (#ያንብቡ)
#ከተራ_፤ ከተረ (ዘጋ፣ አቆመ፣ አገደ፣ ከለከለ) ካለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ውሃን መከተር ወይም ውሃ መገደብ (መዝጋት፥ ማቆም፥ ማገድ፥ ማጠር፥ ዙሪያውን መያዝ፥ መክበብ፥ መከልከል) ማለት ነው፡፡
#ከተራ_ለምን_ተባለ?

በጥምቀት በዓል ዋዜማ በጥር 10 ቀን ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውሃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ወይም ጉድጓድ ተቆፍሮ፤ ድንኳን ይተክላል፥ ዳስ ሲጣል ይውላል (ምክንያቱም ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናምና የበረዶ ወራት ስለሆነ ቅዝቃዜውም በወንዞች አጠገብ ስለሚያይል በባሕረ ዮርዳኖስ፥ በዕደ ዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ ሰዎች ድንኳን ተክለው፥ ዳስ ጥለው ያድሩ ስለነበረ ነው)፡፡ ነገር ግን በዚህ ወቅት የምንጮች ውሃ ደካማ በመሆኑ ውሃው እንዲጠራቀም ወንዶች ጉድጓድ እየቆፈሩ፥ ሴቶች ውኃ

ታኦዳኮስ

18 Jan, 04:01


በእንስራ እየቀዱ ከወንዞችና ከምንጮች ውኃውን ይከትራሉ፥ ይገደባሉ (አሁን በከተሞች ሰው ሰራሽ ግድብ ይገደባል)፡፡ የምዕመናኑ አብዛኛው ስራ ውሃውን መከተርና መገደብ በመሆኑ ዕለቱ #ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
#አንድም በኢያሱ መሪነት እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ባሕር ሲሻገሩ ታቦቱን ያከበሩ (የያዙ) ካህናት ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ከወንዙ መሃል ቆመው ነበር ውኃውም እንደ ባሕረ ኤርትራ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ቆሞ ነበርና ይህንንም ለማስታወስ ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡
#አንድም ጌታችን በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የላይኛው ሸሽቶ እንደ ክምር ተቆልሏል (ከአዳም ጀምሮ እስከ መድኅን መወለድ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ተቋርጦ ለመቅረቱ፥ ከአበው ወደ ውሉድ ላለመተላለፉ ምሳሌ)፤ የታችኛውም ወደ ታች ሸሽቶ በመድረቁ (የአዳም ኀጢአት ከሥሩ እንደተነቀለ ዛፍ ሆና ለመውደቋ ምሳሌ) ከተራ እየተባለ ይጠራል፡፡
፠ውኃ የሚከተርበት ቦታ ‹‹#ባሕረ_ጥምቀት(#ጥምቀተ_ባሕር_››) (#የታቦት_ማደሪያ) እየተባለ ይጠራል፡፡ ውኃው የሚከተረውም በማግስቱ ጥር 11 ቀን ለሚከበረው የጥምቀት በዓል መጠመቂያና የጥምቀትን በዓል ለማክበር እንዲሆን ነው፡፡ ሌሊት ማኅሌት ተቁሞ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ፥ ጠዋት ጸሎት ተደርሶ የሚጠመቅ ሕፃን ካለ እዚያው ውስጥ ይጠመቃል፡፡ ጐበዛዝትም ለቡራኬ ይዋኙበታል ምዕመናንም እንዲሁ ለቡራኬ ይረጩታል፡፡ ያ ስፍራ በዘልማድ ጥምቀተ ባሕር ተብሎ ይጠራል፡፡
#ሥርዐተ_ከተራ
፠ ታቦተ ሕግ ይዞ መጓዝና ወደ ወንዝ መውረድ የተጀመረው በአሮን ልጅ በአልዓዛር ጊዜ ነው፡፡ ነገር ግን ቀድሞ በሙሴ ኋላ በኢያሱ መሪነትም ታቦተ ሕጉን ይዘው የዮርዳኖስን ባሕር መሻገራቸውንም ልብ ይሏል፡፡ የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁት ጊዜ ከስፍራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት፡፡ /ኢያ.3፥3/ እንዲል፡፡
፠ የከተራ ዕለት ድንኳኑ ተተክሎ፥ ዳሱ ተጥሎና ውሃው ተከትሮ ሁሉም ነገር ከተስተካከለ በኋላ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ የደወል ድምፅ እንደተሰማ ከልጅ እስከ አዋቂ በነቂስ ተወጥቶ በዐፀደ ቤተ ክርስቲያንና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች ይሰበሰባሉ፤ የየአድባራቱና የገዳማቱ ታቦት በካህናት አማካይነት በወርቅና በብር በተንቈጠቆጠ መጐናጸፊያ እየተሸፈኑ በታቦት ጉዞ (በዝግታ) ወደ ጥምቀተ ባሕሩ ይጓዛሉ፡፡ በዚህም ጊዜ፤
*ባለ መስቀል መፆር ሰንደቅ ዓለማና ዓርማ የያዘው ግን ከሁሉም ፊት ፊት እያለ ቀድሞ ይሄዳል፡፡
*የወርቅ (ወርቀዘቦ) ካባና ላንቃ የለበሱና ጥላ የያዙት ቀሳውስትና መነኰሳት ከታቦቱ ጐን፤
*መስቀልና ጽንሐሕ የያዙት ከታቦቱ በፊት ማዕጠንት እያጠኑ ይሄዳሉ፡፡
*እንደ ቀሳውስቱ ተመሳሳይ ልብስ ተክህኖ የለበሱት ዲያቆናት ጥላ፣ ድባብ፣ መስቀልና ቃጭል ይዘው እያቃጨሉ ከቀሳውስቱ በፊት በመሆን ያጅቧቸዋል፡፡
*ወደ ባሕረ ጥምቀቱም ሲወረድ ካባ ላንቃ፥ ጥንግ ድርብ በለበሱ፥ የብር፣ የነሐስ፣ የወርቅ መቋሚያና ጽናጽል በያዙ በማኅሌታውያን መዘምራን ደባትር ሃሌታ፣ በሰ/ት/ቤት ተማሪዎች ዝማሬና ሽብሸባ፣ በወጣት መዘምራን ደስታ፣ በወንዶች ሆታ፣ በሴቶች እልልታ ዲያቆናቱን ቀድመው እያጀቡ ይሄዳሉ፡፡
*የደብር አለቆችና አበው ካህናት ታቦቱን ተከትለው ይጓዛሉ፡፡
*ሕዝቡም ደግሞ ‹‹#ለጥምቀት_ያልሆነ_ቀሚስ_ይበጣጠስ›› እንዲሉ እንደየችሎታው ያለውን ልብስ (ጃኖ፣ ለምድ፣ በርኖስና የመሳሰለውን) ለብሶና አጊጦ፥ የጀብዱነት ሽልማት ያለው በሽልማቱ አጊጦ፥ ሽማግሌዎችና የጐበዝ አለቃዎችን በማስቀደም ታቦቱን በመከተል በስተኋላ ይሄዳሉ፡፡
**ነገር ግን ሴቶችና ልጆች እንደፈለጋቸው ከፊትም ከኋላም ሆነው ይሄዳሉ፡፡
ባሕረ ጥምቀትም እንደደረሱ ታቦቱ በድንኳን አጠገብ ቆሞ የዓመቱ #ተረኛ_ደብር (#የምራት_ባለተረኛ) “#ወረደ_ወልድ_እምሰማያት_ውስተ_ምጥምቃት_፤ #በፍሥሓ_ወበሰላም” (እግዚአብሔር ወልድ በሰላምና በደስታ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከሰማያት ወደ መጠመቂያው ወረደ) የሚለው #ሰላም ተመርቶ በአግባቡ ከተለዘበ በኋላ ጸሎት ተድርጐ ሲያልቅ ታቦቱ ወደ ድንኳኑ ይገባል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ ግሱን ለመቃኘትና ለማሸብሸብ፣ ማኅሌት ለመቆም፣ ቅዳሴ ለመቀደስና ሌላውንም ሥርዐት ለመፈጸም ኃላፊነት ያለባቸው ተረኛ ደብር (የምራት ባለተረኞች) ሲሆኑ ለቀጣዩ (ለከርሞ) ዓመት ተረኞች የሚሆኑና በአሁኑ ዓመት የምራት ባለተረኞችን የሚረዱት ገዳማትና አድባራት ደግሞ ‹‹#አንሺዎች_›› ይባላሉ፡፡
የከተራ ዕለት የየአጥቢያው ሕዝብ በየዓመቱ ተራ እየገባ ራት ከየአካባቢው ስለሚያመጣ ያ ሲበላና ሲጠጣ ከቆየ በኋላ ወዲያው የሌሊቱ ጸሎት(ስብሐተ ማኅሌቱ) በተረኛው ደብር ካህናት ተጀምሮ አገልግሎቱ መላ ሌሊቱን ሲካሄድ ያድራል (እንደ ቀጨኔ ባሉ ታላላቅና የሊቃውንት መፍለቂያ አድባራት ተረኛ ቢሆኑም /በጥምቀተ ባሕሩና በቤተ ክርስቲያናቸው ጭምር/ ባይሆኑም በቤተ ክርስቲያናቸው ማኅሌቱን ቆመውና ቅዳሴውን ቀድሰው ያድራሉ)፡፡ ቅዳሴው የሚቀደሰው ከሌሊቱ 7-9 ሰዐት ነው፡፡ በዚያን ዕለት ምሽት ፈቃደኛ የሆኑ ሽማግሌዎችና ወጣቶች፣ ባልቴቶችና ኮረዳዎች ሕፃናትም ጭምር እዚያው በጥምቀተ ባሕሩ ዙሪያ ስለሚያድሩ እንደ የዕድሜ ደረጃቸው ማለትም በልጅነት ዕድሜ ላይ ያሉት በሀገር ባህል ዜማ ሲያመሰግኑ ፥ እናቶችም ታቦቱን የሚያሞግስ ግጥም እየገጠሙ ሲያመሰግኑ ያድራሉ፡፡ በከተሞች ደግሞ ስበከተ ወንጌልና መዝሙር ሲዘመር ያድራል፡፡
#በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት_አላቸው_እነዚሁም_፤
#ታቦቱ_የጌታችን ምሳሌ
#ታቦቱን_አክብሮ_ይዞ_የሚሄደው_ካህን_የቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_ምሳሌ
#ባሕረ_ጥምቀቱ_የዮርዳኖስ_ወንዝ_ምሳሌ
#ታቦታቱን_አጅበው_የሚሄዱት_ምዕመናን_ወደ_ቅዱስ_ዮሐንስ_እየመጡ_የንስሐ_ጥምቀት_ሲጠመቁ_የነበሩ_ሰዎች_ምሳሌ
#ታቦታቱ_በከተራ_ዕለት_ከመንበራቸው_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_መውረዳቸው_መድኀኔ_ዓለም_ክርስቶስ_በእደ_ዮሐንስ_በፈለገ_ዮርዳኖስ_ለመጠመቅ_ከገሊላ_ወደ_ዮርዳኖስ_ከማታው_ጀምሮ_መውረዱንና_ተራውን_ሲጠብቅ_አድሮ_መጠመቁን_ያጠይቃል፡፡ ‹‹ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡›› /ማቴ፡ 3፥13/
#ጥምቀቱ_የሞቱ፤ አርአያ፤ የመቃብሩ አምሳል ነው፡
ትም በልጅነት ዕድሜ ላይ ያሉት በሀገር ባህል ዜማ ሲያመሰግኑ ፥ እናቶችም ታቦቱን የሚያሞግስ ግጥም እየገጠሙ ሲያመሰግኑ ያድራሉ፡፡ በከተሞች ደግሞ ስበከተ ወንጌልና መዝሙር ሲዘመር ያድራል፡፡
#በከተራ_ዕለት_የሚከናወኑ_ድርጊቶች_ምሳሌነት_አላቸው_እነዚሁም_፤
#ታቦቱ_የጌታችን ምሳሌ
#ታቦቱን_አክብሮ_ይዞ_የሚሄደው_ካህን_የቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ_ምሳሌ
#ባሕረ_ጥምቀቱ_የዮርዳኖስ_ወንዝ_ምሳሌ
#ታቦታቱን_አጅበው_የሚሄዱት_ምዕመናን_ወደ_ቅዱስ_ዮሐንስ_እየመጡ_የንስሐ_ጥምቀት_ሲጠመቁ_የነበሩ_ሰዎች_ምሳሌ
#ታቦታቱ_በከተራ_ዕለት_ከመንበራቸው_ወደ_ጥምቀተ_ባሕር_መውረዳቸው_መድኀኔ_ዓለም_ክርስቶስ_በእደ_ዮሐንስ_በፈለገ_ዮርዳኖስ_ለመጠመቅ_ከገሊላ_ወደ_ዮርዳኖስ_ከማታው_ጀምሮ_መውረዱንና_ተራውን_ሲጠብቅ_አድሮ_መጠመቁን_ያጠይቃል፡፡ ‹‹ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡›› /ማቴ፡ 3፥13/
#ጥምቀቱ_የሞቱ፤ አርአያ፤ የመቃብሩ አምሳል ነው፡

/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/

ታኦዳኮስ

06 Jan, 07:46


ከግርግሙ ማን ይቀራል?

የምድር ነገሥታት ሰማያዊውን ንጉሥ ለማምለክ ሊመጡ ይገባል። ወታደሮችም ሠራዊትን ሁሉ በአፉ እስትንፋስ ያጸናውን ጌታ ለማገልገል ሊቀርቡ ያስፈልጋል። ሴቶችም ኀዘናቸውን ወደ ደስታ ይለውጥ ዘንድ ከሴት የተወለደውን ያዩ ዘንድ ሊመጡ ይገባል። ሕፃናትም ከሚጠቡ እና ከሕፃናት አፍ ምስጋናን ያዘጋጅ ዘንድ ሕፃን የሆነውን ይመለከቱ ዘንድ ሊመጡ ያስፈልጋል። እረኞችም ነፍሱን ስለ በጎቹ የሚያኖር መልካሙን እረኛ ለማየት ይመጡ ዘንድ ይገባል። ባሮችም የባርነት ቀንበራቸውን ሰብሮ በነጻነት ያከብራቸው ዘንድ የባሪያውን መልክ የነሣውን ሕፃን ያዩ ዘንድ መምጣት ይገባቸዋል። ዓሣ አጥማጆቹም የቃሉን መረብ አስይዞ ሰው አጥማጅ የሚያደርጋቸውን ወንድ ልጅ ለማየት ይቀርቡ ዘንድ ይገባቸዋል። ቀረጥ ሰብሳቢዎችም ከቀራጮች መካከል ወንጌላዊ አድርጎ የሚመርጠውን ጌታ ለማየት ሊመጡ ይገባቸዋል። ዘማውያን ቅዱሳት እግሮቹን በዘማውያን እንባ እንዲታጠብ የሚሰጠውን የፍቅር አምላክ ለማየት ይቀርቡ ዘንድ ይገባል። ኃጥአን ሁሉ የዓለምን ኃጢአት የሚሸከመውን የእግዚአብሔር በግ ለማየት ሊመጡ ይገባል።

#ዛሬ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት በአእላፋት ዝማሬ እንገናኝ!

https://t.me/Dnabel

ታኦዳኮስ

28 Dec, 09:15


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐሥራ ዘጠኝ ቀን በዚህች ዕለት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ውስጥ ያዳነበት ዕለት ነው ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን መላእክት ፣ በጻድቃን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።

ታኦዳኮስ

28 Dec, 09:15


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
ታኅሣሥ 19 ቀን 2017 ዓ.ም
የሉቃስ ወንጌል ም 1 ቁ 11 - 21
መልካም ዕለተ ቀዳሚት ሰንበት !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#saturday

ታኦዳኮስ

28 Dec, 09:15


ከአሥርቱ መዓርጋተ መላእክት ውስጥ አንደኞቹ አርባብ ይሰኛሉ። ረበበ ማለት ጋረደ፣ ሸፈነ ማለት ሲሆን አርባብ ማለት የሚጋርዱ፣ የሚሸፍኑ የሚል ትርጉምን ይሰጣል፡፡ እነዚህም መላእክት የእግዚአብሔርን መንበር በክንፎቻቸው ስለሚሸፍኑ እና ስለሚጋርዱ ይህን ስያሜ አግኝተዋል። ዳግመኛም ዘወትር ከሚወረወረው የሰይጣን ፍላጻ (ጦር) ያመልጡ ዘንድ ለሰው ልጆች ሁሉ ሽፋን ከለላ ስለሚሆኑ ስለዚህ አገልግሎታቸው አርባብ/"የሚጋርዱ" ተብለው ይጠራሉ። የእነዚህም የመላእክት ሠራዊት አለቃቸው ሠለስቱ ደቂቅን ሰይጣን በናቡከደነጾር ልብ አድሮ ካነደደው እሳት ጋርዶ፣ ሸፍኖ ያዳናቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡

ቅዱስ ገብርኤል በተለይ ልጅ ወደሚወልዱ ደጋግ ቅዱሳን አበው እና ቅዱሳት እማት ‹አብሣሬ ጽንስ›/‹ጽንስን የሚያበሥር› ሆኖ በመላክ በተደጋጋሚ በመጽሐፍ ስሙ የተጠቀሰ መልአክ ነው፡፡ ለማኑሄ እና ለሚስቱ ሶምሶን የተባለ ኃያል ሰው እንደሚወልዱ፣ ለሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ዮሐንስ መጥምቅን የመሰለ ደገኛ ልጅ እንደሚወልድ፣ ክብር ይግባትና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ በማኅጸኗ እንደሚቀረጽ ያበሠረ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነውና ‹መልአከ መበሥር› በመባል ይጠራል፡፡(መሳ 13፥4 ፣ሉቃ 1፥13 ፣ሉቃ 1፥26)

በተጨማሪም አዲስ እና ደስ የሚያሰኘውን የአምላክን መወለድ ዜና ብሥራትም በመናገሩ እና በሐዲስ ኪዳንም ስሙ ተደጋግሞ በመነሣቱ ምክንያት ‹መጋቤ ሐዲስ› በመባል ይታወቃል፡፡ ለብፁዕ ዳንኤልም ዕውቀት እና ማስተዋል የሰጠው ጥበብንም ያስተማረው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል መሆኑን ይኸው ነቢይ በመጽሐፉ ምስክርነትን ይሰጣል፡፡(ዳን 8፥15)

የአምላክን ሰው ሆኖ ወደዚህች ምድር መምጣት ያበሰረው ቅዱስ ገብርኤል እንደሆነ ሁሉ ፤ ‹ልደት እና ዕርገት በአንድ መልአክ ተበሠሩ› በሚለው በቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ ትምህርት ደግሞ የአምላክን ወደ ሰማይ ማረግም ለሰማያውያን መላእክት ‹መኳንንት ደጆቻችሁን ክፈቱ› ሲል ዳግመኛ ያበሠረው ይኸው መልአክ መሆኑ ተጠቅሶ እናገኛለን፡፡

እንኳን አደረሳችሁ!!!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]

ታኦዳኮስ

14 Dec, 08:35


•  ሐመር  መጽሔት  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት  ሥርዓትና ትወፊት ጠብቃ በልማት ተቋማት አስተዳደር  በመጽሔት ዝግጅት ክፍል  በየወሩ የምትወጣ መንፈሳዊ መጽሔት ናት፡፡
•  ሐመር መጽሔት ፴፩ ኛ ዓመት  ቁጥር ፲፪  # ታኀሣሥ ፳፻፲፯  ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን " #ይእዜኒ ለሰላም ንትልዋ መድኃኒነ ተወልደ ነዋ” (ቅዱስ.ያሬድ)  "በሚል ዐቢይ መልእክት   ያለንበት ዘመን ግን “የዓባይን ልጅ ውኃ ጠማው” እንደሚባለው የሰላም አምላክ ደሙን ያፈሰሰላት፣ሥጋውን የቆረሰላት፣ የሕይወት ዋጋ የከፈለላት፣ሁል ጊዜ “ጸልዩ በእንተ ሰላም፤ ስለ ሰላም ጸልዩ”እያለች የምትጽልይ፣ስለ ሀገር፣ ስለ ሠራዊት፣ ስለ ሕዝብ የምትለምን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በውስጥም በውጭም ሰላም አጥታ እየታወከች ፤ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከአባቶች በኩል “መምህር ወመገሥጽ ዘኢያደሉ ለገጽ” በመሆን ለማንም ሳይወግኑ ማንንም  ሳይፈሩና ሳያፍሩ የሚመከረውን መምከር የሚገሠጸውን መገሠጽ የውስጥ መለያየትንም በመፍታት በአንድነት  ለሰላም እንዲቆሙላት  እንደምትጠበቅ ፣በዓለ ልደት የተጣሉት የታረቁበት፣ የተለያዩት አንድ የሆኑበት፣ ሰላም የተሰበከበት   እንደሆነ ሐመር በመልእክት ዐምድ ታስነብባለች።
   
  .#ዐውደ ስብከት  ሥር” # “ናሁ ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ”  በሚል ርእስ  ይህ ትንቢት በብሉይ ኪዳን ስለ እመቤታችንና ስለክርስቶስ በአንድነት
ከተነገሩ ደረቅ (ቀጥተኛ) ትንቢቶች መካከል አንዱ መሆኑን ፣የእመቤታችን ሕይወት ሰለእኛ ምን እንደሚያስተምረን  ታስነብባለች።
  #በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “# “ቃል ሥጋ ሆነ” (ዮሐ.፩፥፲፬)  ክፍል አንድ " በሚል ዐቢይ ርእስ በመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው  ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ "በመጀመሪያ ቃል ነበረ "በማለት  ወንጌሉን የመጻፉን ምክንያት በጥልቀት  ቀርቦበታል።ቃል ሥጋ የሆነው እንደሆነ በዝርዝር ተዳሶበታል፤ድንግል ማርያም እንዴት ኢየሱስን ክርስቶስን እንደወለደችው የሊቃውንት መጽሐፍ በማጣቀስ ትምህርት ይሰጣል ።

    #ዐቢይ ጉዳይ  ዐምድ  ሥር  ደግሞ “# የቅዳሴ አገልግሎትና ምሥጢሩ" በሚል ርእስ  በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ የተሠራ  ጥናታዊ ጽሑፍ (Investigative Reporting) ላይ ትኩረት ያደረገ  ስለ ቅዳሴ በዝርዝር ያሳያል
   •  #ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር  ደግሞ  "#ኦርቶዶክሳዊ የልጆች አስተዳደግ "በሚል ርእስ  አንድ ነገር መፍትሔ መነሻው በተከሰተው ችግር ላይ ያለን ግንዛቤ እና ከዚያ ችግር ለመውጣት የሚነሣ የልቡና ቁጭት  እንደሆነ ያሳያል ።የልጆች ማንነት ፤የልጆች እና የወላጅ /አሳዳጊ/ ግንኙነት ምን መምሰል እንዳለበት ፤ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብን በመገንባት አርአያ መሆን እንደሚገባ  በአጠቃላይ ልጅን በመንፈሳዊ ዕውቀት፣በሥነ ምግባርና በኢትዮጵያዊ ባሕል ቀርጾ ማሳደግን የመሰለ ወላጅ ለልጁ የሚመኘው ተግባር ያለ አይመስለኝም።"በማለት ትኩረት ለልጆች መስጠት እንደሚገባ በአጽንዖት ታሰተምራለች።
   • #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “#የስደተኞች መጠጊያ ጁባ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን " በሚል ርእስ  የአመሠራረት  ሁኔታውን ፣ ያሉን መልካም  ዕድሎችና ተሞክሮዎች ታስቃኛለች ።
   •  #በነገዋ  ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ  ሥር “ መንፈሳውያን ማኅበራት ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን" በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ክፍል አንድ  በሚል ርእስ ስለ መንፈሳዊ ማኅበራት ምንነትና አመሠራረት ጥናት ተኮር ጹሑፍ ይዛለች ።ስፍር ቁጥር የሌላቸው፣ ህልውናቸው በምንና እንዴት እንደሆነ ለመረዳት አሰቸጋሪ የሆነ፣ የሚሠሩት ሥራም ሆነ የሚፈጽሙት
ተልእኮ ተለይቶ የማይታወቅ በርካታ ማኅበራት ያሳያል ።
  #በኪነ ጥበብ ዐምድ "# በፍላጻ የተወጋ ልብ  ክፍል _፪ "በሚል  ታስነብባለች ።ዲያቆን ጴጥሮስ በሚል የአንድ ቅን ወንድማችን ታሪክ ታስነብባለች። የሚገርም እጅግ የሚመስጥ ታሪክ ይዛለች።በተለይም የሐረማያ ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች እና ደቡብ ኢትዮጵያ ያላችሁ ከገጸ ባሕርይው ተነስታችሁ ዲ/ን ጴጥሮስ ማን እንደሆነ ትረዳለች ።በእርግጠኝነት በዕንባ ይኽን ኪነ ጥበብ ታነቡታላችሁ ።(ገጽ_፳፫)
•  #የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ “በዐልና አከባበሩ- # ክፍል ፩ " በሚል ርእስ #“በዓልንና የበዓል  አከባበርን” በተመለከተ የሚነሡ ጥያቄዎችን መሠረት በማድረግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ  ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የትምህርትና ማሠልጠኛ መምሪያ ዋና ኃላፊ የሆኑትን መጋቤ ሐዲስ ኀይለ እግዚእ አሰፋ ጋር የተደረገ  ጥያቄና መልስ ይዛለች  ።
  
   ሐመር መጽሔት #፴፩ ኛ ዓመት   ቁጥር ፲፪ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ !

magazine @eotcmk.org  #ሐመር #መጽሔት  ዝግጅት  ክፍል

ታኦዳኮስ

14 Dec, 08:35


✍️✍️ሐመር መጽሔት በታኅሣሥ ወር እትሟ!

✍️".. ጉዳዩን ከአንዱ ወደ ሌላው መግፋት ሳይሆን ሁሉም የየድርሻውን ወስዶ፣ ሁሉም የሚጠበቅበትን ተግባር በአግባቡ አከናውኖ ሁሉም ሰላምን ተከትሏት..) #ሐመር #መጽሔት ታኀሣሥ በ፳፻፲፯ ዓ.ም መልእክት ዐምድ  ✍️      
                      ༺ ༻ 
  #የኅትመት ዘመን ፦# # ታኀሣሥ ፳፻፲፯  ዓ.ም
#አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በልማት ተቋማት አስተዳደር  በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት
•  ገጽ ብዛት፦፳፰
   ዋጋ ፦፵ ብር 

ታኦዳኮስ

12 Dec, 07:54


በዓታ ለማርያም
ታኅሣሥ በባተ በሦስተኛው ቀን የሚታሰበውና የሚከበረው በዓል ‹‹በዓታ ለማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡ ከእናቷ ከቅድስት ሐና እና ከአባቷ ቅዱስ ኢያቄም በስዕለት የተወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዕለት የከበረ እንደመሆኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ታከብረዋለች፡፡
በዓት ቃሉ የግእዝ ሲሆን ቤት ማለት ነው፡፡ ደጋጎቹ የእግዚአብሔር ሰዎች ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ልጅ አጥተው ለብዙ ዘመናት ከመኖራቸው የተነሣ በኀዘን ፈጣሪያቸውን ሲማጸኑ ቃል በመግባት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ዓመት ሲሆናት በእግዚአብሔር ቤት ትኖርና ታገለገል ዘንድ በቤተ ክርስቲያን እንድትኖር ስለሰጧት በዓሉም ስያሜውን በዚያ መሠረት አግቷል፡፡
በዚያን ጊዜም በቤተ ክርስቲያን ያገለግል የነበረው ካህኑ ዘካርያስ ስዕለታቸውን አስተውሶ ቅድስት ድንግል ማርያምን ሊቀበላት ሲቀርብ እንደ ፀሐይ የምታበራ ሕፃን ሆና አገኛት፤ በመገረምና በመጨነቅም ከወላጆቿ ጋር ምን ሊመግቧት እንደሚችሉ በመጨነቅ ላይ ሳሉ ሕዝቡ በተሰበሰበበት መካከል መልአኩ ፋኑኤል ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ይዞ ከሰማይ ወረደ፡፡ ካህኑ ዘካርያስም ለእርሱ የመጣ መና መስሎት ሲቀረብ ወደ ላይ ተመለሰበት፡፡ በዚያ የተሰበሰቡት ሰዎችም እያንዳንዳቸው ቢሞክሩ በተመሳሳይ መልኩ ተመልሶ ወደ ላይ ራቀባቸው፡፡ ‹‹ምን አልባት ለእንግዶች የመጣ ሀብት እንደሆነ›› ብለው ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም እንዲቀርቡ ቢደረግም ለእነርሱም ራቀባቸው፡፡ ካህኑ ዘካርያስም ቅድስት ሐናን ‹‹እግዚአብሔር የሚያደርገውን የሚያውቅ የለምና ልጅቷን ትተሸ ወደዚህ ነይ›› አላት፤ ሆኖም ግን ቅድስት ማርያም እናቷ ትታት ስትሄድ መከተል ጀመረች፤ ምርርም ብላ አለቀሰች፡፡

ታኦዳኮስ

12 Dec, 07:54


በዚህም ጊዜ መልአኩ ፋኑኤል ወደ እርሷ ቀርቦ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ መገባት፤ ከዚያም በክብር ዐረገ፤ ሊቀ ካህናቱና ሕዝቡም ‹‹የምግቧ ነገር ከተያዘልን በቤት እግዚአብሔር ትኑር›› ብለው ወደ ቤተ መቅደስ አስገቧት፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ሰማያዊ ኅብስትና መጠጥ እየተመገበች  በቤተ መቅደስ  ለ፲፪ ዓመታትም ኖራለች፡፡
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ በረከቷ ይደርብን፤አሜን! 
ምንጭ፡- ነገረ ማርያም

ታኦዳኮስ

12 Dec, 07:54


"ማርያም ሆይ፣ የሐናን ጡት እየጠባሽ ወደ ቤተ መቅደስ በገባሽ ጊዜ ያገኘሽ ያለ እናት ማደግ ያሳዝነኛል፤ ዳግመኛም በደመና የሚጫን የእሳት አበባ የለበሰ ፋኑኤል እንደ አባት ከመላእክት ጋር መናን እየመገበሽ በቅድስና የማደግሽ ምሥጢር ያስደስተኛል"

አባ ጽጌ ድንግል

እንኳን ለእመቤታችን ወደ መቅደስ የመግባት በዓል በሰላም አደረሰን!!!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

ታኦዳኮስ

03 Dec, 03:32


††† ኅዳር 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1."24ቱ" ቅዱሳን ካህናተ ሰማይ (ሱራፌል)
2.ቅዱስ አዝቂር ሰማዕት
3."48" ሰማዕታት (ማሕበሩ)
4.አባ ዮሴፍ ዘሃገረ ጻን
5.ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጥዑመ ዜና
6.ቅዱስ ኪርያቅ ሰማዕት††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (መምሕረ ትሩፋት)
2.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
3.አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ ዘክብራን
4.ቅዱስ አጋቢጦስ (ጻድቅ ኤጲስቆጶስ)
5.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
6.ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም (ኢትዮጵያዊ)
7.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ

††† "በዙፋኑ ዙሪያም ሃያ አራት ዙፋኖች ነበሩ:: በዙፋኖቹም ላይ ነጭ ልብስ ለብሰው: በራሳቸውም የወርቅ አክሊል ደፍተው ሃያ አራት ሽማግሌዎች ተቀምጠው ነበር:: ከዙፋኑም መብረቅና ድምጽ: ነጐድጓድም ይወጣል:: በዙፋኑም ፊት ሰባት የእሳት መብራቶች ይበሩ ነበር:: እነርሱም ሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስት ናቸው::" †††
(ራዕይ ፬፥፬)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

https://t.me/zikirekdusn

ታኦዳኮስ

03 Dec, 03:32


††† ❇️እንኳን ለ24ቱ ቅዱሳን ካህናተ ሰማይ እና ቅዱስ አዝቂር ሰማዕት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ †††

††† እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክትን ሲፈጥራቸው በነገድ መቶ (100): በክፍለ ነገድ አሥር (10) አድርጓቸዋል:: አቀማመጣቸውንም በሦስት ሰማያትና በ10 ከተሞች (ዓለማት) አድርጓል::

††† መላእክት ያሉባቸው ከተሞች ከታች ወደ ላይ "ኤረር: ራማና ኢዮር" ይባላሉ:: አሥሩ ክፍለ ነገድ ደግሞ ከነ አለቆቻቸው ይህንን ይመስላሉ:-
1."አጋእዝት" (የቀድሞ አለቃቸው ሳጥናኤል: አሁን የተረፉት በቅዱስ ሚካኤል ሥር ናቸው)
2."ኪሩቤል" (አለቃቸው ኪሩብ)
3."ሱራፌል" (አለቃቸው ሱራፊ)
4."ኃይላት" (አለቃቸው ሚካኤል)
5."አርባብ" (አለቃቸው ገብርኤል)
6."መናብርት" (አለቃቸው ሩፋኤል)
7."ስልጣናት" (አለቃቸው ሱርያል)
8."መኳንንት" (አለቃቸው ሰዳካኤል)
9."ሊቃናት" (አለቃቸው ሰላታኤል)
10."መላእክት" (አለቃቸው አናንኤል) ናቸው::

††† ከእነዚህም:-
*አጋእዝት: *ኪሩቤል *ሱራፌልና *ኃይላት መኖሪያቸው በኢዮር (በ3ኛው ሰማይ) ነው::
*አርባብ: *መናብርትና *ስልጣናት ቤታቸው ራማ (2ኛው ሰማይ) ነው::
*መኳንንት: *ሊቃናትና *መላእክት ደግሞ የሚኖሩት በኤረር (በ1ኛው) ሰማይ ነው::

መላእክት ተፈጥሯቸው እምኀበ አልቦ ኀበ ቦ ነው:: አይራቡም: አይጠሙም: አይዋለዱም: አይሞቱም:: ተፈጥሯቸውም ረቂቅ ነው:: ተግባራቸውም ዘወትር "ቅዱስ: ቅዱስ: ቅዱስ" እያሉ ፈጣሪያቸውን ማመስገን ነው:: ምግባቸውም ይሔው ነው::

ዕረፍት ብሎ ነገርን አያውቁም:: "አኮቴቶሙ ዕረፍቶሙ: ወዕረፍቶሙ አኮቴቶሙ" እንዲል:: በተጨማሪም መልአክ ማለት ተላላኪ (አገልጋይ) ነውና ከፈጣሪ ወደ ሰው ልጆች ለምሕረትም: ለመዓትም ይላካሉ::

ምሕረትን ያወርዳሉ:: ልመናን ያሳርጋሉ:: ቅጡ ሲባሉም ይቀጣሉ:: ስነ ፍጥረት (አራቱ ወቅቶች) እንዳይዛቡ ይጠብቃሉ::
*ዘወትርም ስለ ሰው ልጆች ያማልዳሉ:: (ዘካ. 1:12)
*ምሥጢርን ይገልጣሉ:: (ዳን. 9:21)
*ይረዳሉ:: (ኢያ. 5:13)
*እንዳንሰናከል ይጠብቃሉ:: (መዝ. 90:11)
*ያድናሉ:: (መዝ. 33:7)
*ስግደት ይገባቸዋል:: (መሳ. 13:20, ኢያ. 5:13, ራዕ. 22:8)
*በፍርድ ቀንም ኃጥአንን ከጻድቃን ይለያሉ:: (ማቴ. 25:31)
*በአጠቃላይ ለሰው ልጆች ሕይወትና ድኅነት ሲባል ከፈጣሪያቸው የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ሲጠብቁና ፈቃዱን ሲፈጽሙ ይኖራሉ::

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚህች ዕለት የሃያ አራቱን ቅዱሳን ካህናተ ሰማይን መታሰቢያ ታደርጋለች:: እኒህ ቅዱሳን መላእክት በነገድ 10 ሲሆኑ መጠሪያቸው "ሱራፌል" : መኖሪያቸውም በኢዮር ነው:: ነገር ግን ሃያ አራቱ አለቆቻቸው ተመርጠው በመሪያቸው በቅዱስ ሱራፊ አለቅነት በጽርሐ አርያም ያገለግላሉ::

በቀናች ሃይማኖት ትምሕርት ሁሉም ቅዱሳን መላእክት ለእግዚአብሔር ቅርብ ቢሆኑም: በነጠላ የቅዱስ ሚካኤልን ያህል: በነገድ ደግሞ የኪሩቤል (አራቱ እንስሳ) እና የሱራፌልን (ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ) ያህል ቅርብ የለም::

††† ሃያ አራቱ ቅዱሳን ካህናት ሥራቸው:-
1.እንደ ሞገድ ከአንደበታቸው ምስጋና እየወጣ: ጧት ማታ ፈጣሪያቸውን ይቀድሱታል:: (ኢሳ. 6:1, ራዕይ 4:11, 5:11)

2.የሥላሴን መንበር ያለ ማቋረጥ ያጥናሉ:: (ራዕይ 5:8)

3.የሰው ልጆችን: በተለይም የቅዱሳንን ጸሎት በማዕጠንታቸው ያሳርጋሉ:: (ራዕይ 8:3)

4.የረከሱትን ይቀድሳሉ:: (ኢሳ. 6:6)

5.ዘወትርም ለሰው ልጆች ምሕረትን ሲለምኑ ይኖራሉ:: (ዘካ. 1:12)

ስለ እነዚህ ቅዱሳን ካህናት (ሱራፌል) ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ ብዙ ይላል:: ለምሳሌ:- ዐቢይ ነቢይ ወልዑለ ቃል ኢሳይያስ ፈጣሪው ተቀይሞት በነበረበትና ዖዝያን በሞተበት ወራት: ግሩማን ሆነው ሥላሴን "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ" እያሉ ዙሪያውን ከበው ሲያመሰግኑ ሰምቷል::

ከእነርሱም አንዱ (ሱራፊ) መጥቶ በጉጠት እሳት ከንፈሩን ዳስሶ ከለምጹ አንጽቶታል:: (ኢሳ. 6:1) አቡቀለምሲስ የተባለ ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ በግርማ: በአምሳለ አረጋዊ ተመልክቷቸዋል:: (ራዕይ 4:4)

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን የመሰሉ ቅዱሳን ሊቃውንት ደግሞ በጣዕመ ምስጋናቸው ሲገልጿቸው:-
"ካህናተ ሰማይ ቅውማን በዐውዱ::
አክሊላቲሆሙ ያወርዱ::
ቅድመ መንበሩ እንዘ ይሰግዱ::
ይርዕዱ::
ከመ ኢይዝብጦሙ ሶበ ይበርቅ ነዱ::" ብለዋል:: (መጽሐፈ ሰዓታት)
ትርጉሙም "በፈጣሪ መንበር ዙሪያ የሚቆሙ የሰማይ ካህናት አክሊለ ክብራቸውን አውርደው በመንበሩ ፊት ይሰግዳሉ:: መብረቀ መለኮቱ በተገለጠ ጊዜም በፍርሃት ይንቀጠቀጣሉ::" ነው:: ግሩም ባሕርየ ሥላሴን ሊቋቋመው የሚችል ፍጡር የለምና::

ቅዱሳን ካህናተ ሰማይ በምስጋናቸው: በማዕጠንታቸውና በምልጃቸው ክቡራን ናቸውና ዘወትር ልናከብራቸው ይገባናል:: የረከሰ ማንነታችንን ይቀድሱ ዘንድ: በምልጃቸውም ዘንድ እንድንታሰብ: ጸሎታችንንም ያሳርጉልን ዘንድ እንለምናቸው::

††† ኅዳር 24 ቀን ዓመታዊ በዓላቸው ነው ማለት በየወሩ በ24 ወርኀዊ በዓላቸው መሆኑን ያሳያልና ዘወትር ልናስባቸው ይገባል::

በተለይ ያዘነን ልብ ደስ ያሰኛሉና እንደ ሊቃውንት እንዲህ ብለን እንጠራቸዋለን::
"ሰላም ለክሙ ካህናተ ሕጉ ወትዕዛዙ::
ለእግዚአብሔር ቃል ዘጶዴሬ ሥጋ አራዙ::
እምነቅዐ አፉክሙ ሐሴት ዘኢይነጽፍ ዉሒዙ::
ኪያየ ኅዙነ ወትኩዘ ልብ ናዝዙ::
ወበክንፍክሙ ብርሃናዊ ዐውድየ ሐውዙ::" (አርኬ ዘኅዳር 24)

††† ቅዱስ አዝቂር ካህን †††

††† ከዜና ካህናት ወደ ዜና ካህናት እንለፍ:: ቅዱስ አዝቂርን የመሰሉ ካህናት ምንም ሥጋ ለባሽ ቢሆኑም ሥልጣናቸውና ግብራቸው ሰማያዊ ነውና መላእክትን ይመስላሉ:: አንድም በስልጣናቸው ከመላእክት ይበልጣሉ::

"ካህናትየ ይቤሎሙ::
ወእምኩሉ ፈድፋደ አክበሮሙ::
ዘኢተገብረ ለመላእክት ተገብረ ለካህናት::"

ትርጉም "አገልጋዮቼ አላቸው::
ከሁሉ በላይ አከበራቸው::
ለመላእክት ያልተደረገ ለካህናት ተደረገ::" እንዳለ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ:: (መጽሐፈ ቅዳሴ)

ቅዱስ አዝቂርም የናግራን (አሁን የመን) ክርስቲያን ሲሆን በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን በንጹሕ የክህነት አገልግሎቱ ሰውንም: ክርስቶስንም ደስ ያሰኘ አባት ነው:: አሕዛብን: አረማውያንን ሁሉ ድል ነስቶ መንጋውን ጠብቋል:: በቁጥርም አብዝቷል::

ገርፈው ቢያስሩት በቃሉ ስልጣን የብረት በሮችን ከፍቶ አሕዛብን ሲያጠምቅ ተገኝቷል:: ሊገድሉት ሲወስዱት በየመንገዱ ይሰብክ ነበር:: ገዳዮቹ በርሃ ላይ ውኃ ጥም እንዳይገድላቸውም በአንዲት ገበታ ላይ ዝናም አዝንሞ 700 ወታደሮች ከነ ፈረሶቻቸው አጥግቧል::

በመጨረሻም አይሁድ በድንጋይ ሲወግሩት ድንጋዮቹ እየተመለሱ አናት አናታቸውን ብሏቸዋል:: ያን ጊዜ በብስጭት አንገቱን ቆርጠውታል:: አብረውም ቅዱስ ኪርያቅ ወዳጁንና 48 ተከታዮቹን ሰይፈዋል::

††† አምላከ ቅዱሳን ካህናተ ሰማይ ከምስጋናቸው ሐሴትን: ከማዕጠንታቸው በጐ መዓዛን ያውርድልን:: በረከታቸውንም ያብዛልን::

ታኦዳኮስ

26 Nov, 03:37


ወላጆቿም ግድ ብለው ስዕለ ክርስቶስ የተባለ የሱስንዮስን የጦር መሪ አጋቧት:: እስከ 24 ዓመቷም ልጆችን ወለደች:: በዚህ ሁሉ ጊዜ የጾምና የጸሎት ሰው ነበረች:: አፄ ሱስንዮስ ተዋሕዶን ክዶ ካቶሊክ በሆነ ጊዜ ባሏ ወደ ንጉሡ እምነት ገባ::በዚህ ስታዝን ይባስ ብሎ ጠዳ ላይ የአቡነ ስምዓን (ዻዻሱን) ልብስ ግዳይ ይዞ ቀረበ:: እርሷም ልቧ ቆረጠ:: ፈጣሪ 3ቱን ልጆቿን አከታትሎ ወሰደ:: ደስ ብሏት ጠፍታ ሳጋ (ዛሬ ገዳሟ ያለበት) ገባች:: ቀጥላም መነኮሰች::

ከዚህ በሁዋላ እየዞረች መናፍቃን ስታሳፍር: ሕዝቡን ስታጸና ዓመታት አለፉ:: በሷ ስብከትም ብዙ መነኮሳትና ምዕመናን ሰማዕት ሆኑ:: እሷም በየገዳማቱ ተንከራተተች:: በደዌ ተሰቃየች:: በንጉሡ ተይዛ 2 ጊዜ ወደ በርሃ ተሰደደች::

ፋሲል ነግሶ: ሃይማኖት ተመልሶ ሃገር ሲረጋጋ ወደ ምጽሊ: ከዚያም ወደ መንዞ መጥታ ገዳም መሥርታ: መናንያንን ሰብስባ: ስታጽናና ኑራለች:: በተወለደች በ50 ዓመቷም በ1630ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ዐርፋ ተቀብራለች:: የተጋድሎ ዘመኗም 26 ዓመታት ናቸው:: ቅድስት ወለተ ዼጥሮስ ሰማዕትም ጻድቅም ናት::

††† የጥቡዓን አምላክ የሊቁን ምሥጢር: የቅድስቷን መጨከን: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

††† ኅዳር 17 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ (ፍልሠቱ)
2.ቅድስት ወለተ ዼጥሮስ ኢትዮዽያዊት
3.አባ ሲኖዳ (ዘደብረ ጽሙና - ጐጃም)
4.ጻድቃን እለ ወጺፍ
5.ቅዱሳን አብርሃምና ሐሪክ
6.ቅድስት ወለተ ዻውሎስና ወለተ ክርስቶስ

††† ወርኀዊ በዓላት
1.እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት
2.ያዕቆብ ሐዋርያ
3.መክሲሞስና ዱማቴዎስ
4.አባ ገሪማ
5.አባ ዸላሞን
6.አባ ለትጹን
7.ቅዱስ ኤዺፋንዮስ

††† "በድካምና በጥረት: ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት: በራብና በጥም: ብዙ ጊዜም በመጦም: በብርድና በራቁትነት ነበርሁ . . . የቀረውን ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው::" †††
(2ቆሮ. 11:23)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

ታኦዳኮስ

26 Nov, 03:37


††† እንኳን ለዓለም ሁሉ መምሕር ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እና ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ለቤተ ክርስቲያን የብርሃን ምሰሶ ስለሆነላት ስለ ታላቁ ሐዋርያዊ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? እንደ እኔ ያለ ኃጥእ: ለባሴ ሥጋና ገባሬ ንስሃ ስለሱ ሊናገር አይቻለውምና:: አባቶቻችን እንደ ነገሩን ስለ አፈ ወርቅ ለመናገር አፈ ወርቅ መሆን ያስፈልጋል:: እስኪ በቅዱሱ አባት ምልጃ ጥቂት ልሞክር::

††† ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ማን ነው?

††† ነገዱ ከሶርያ: የተወለደው በ347 ዓ/ም በእስክንድርያ ሲሆን አባቱ አስፋኒዶስ እናቱ ደግሞ አትናስያ ይባላሉ:: እነርሱ ደግ ቢሆኑ ይህንን እንቁ ልጅ እግዚአብሔር ሰጣቸው:: ዮሐንስ ለክርስቲያን እንደሚገባ በትምሕርትና በጥበብ አደገ:: ገና በሕጻንነቱ ወደ ግሪክ ሔዶ የዘመኑን ሳይንስ (ፍልስፍና) ከአፉ እስከ ገደፉ ተምሮ ተመልሷል::

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን ለየት ከሚያደርጉት ነገሮችም አንዱ ይሔው ነው:: በዘመናዊም ሆነ በመንፈሳዊ ትምሕርት ይህ ቀረህ የማይሉት ሊቅ የሆነው ገና በ15 ዓመቱ ነበር:: በ2 ወገን የተሳለ ሰይፍ በመሆኑ ስንኩዋን በሕይወተ ሥጋ እያለ ዛሬም ለንፉቃን ትልቅ የራስ ምታት ነው::

ቅዱሱ ገና በ16 ዓመቱ ሃብት: ንብረት: ውበት: ክብርና እውቀት የሞላለት ቢሆንም ያለውን ሁሉ ለነዳያን ሰጥቶ መጻሕፍትን ብቻ ሰብስቦ ከባልንጀራው ቅዱስ ባስልዮስ ጋር በርሃ ገባ:: ሰውነቱን በጾምና በጸሎት እየቀጣ በበርሃ ሲኖር ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ወደ እርሱ መጡ:: ሊቀ ሐዋርያት የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ ስልጣን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ሰጥተው ተሰወሩት::

ከዚህች እለት በሁዋላ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ባሕረ ምስጢራት ሆነ:: ብሉይ ከሐዲስ: ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ራዕየ ዮሐንስ ድረስ በአንድምታ ትርጉዋሜ ተነተናቸው:: በተለይ ሐዲስ ኪዳንን እየመላለሰ አመሰጠረው:: ቅዱስ ሕሊናው ሳይታክት: ንጹሕ እጆቹ ሳይዝሉ የጻፋቸው ድርሳናት: መልዕክታትና ትርጉዋሜያት ቢቆጠሩ አሥር ሺህ ሞሉ:: በእውነት ለዚህ አንክሮ ይገባል! የሚገርመው ይህን ሁሉ ሲሰራ እድሜው ገና ለጋ: ማዕርጉም ዲቁና ነበር::

ከዚህ በሁዋላ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ቅስና ተሹሞ በስብከተ ወንጌል ብዙ ቦታዎችን አዳረሰ:: በቅድስናው ወደውታልና የቁስጥንጥንያ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት:: አፈ ወርቅ ሲናገርም ሆነ ሲያስተምር እንኩዋን የሚያወራ ኮሽ የሚል የለም:: ከጣዕመ ትምሕርቱ የተነሳ ሕዝቡ በተደሞ ይሰሙት ነበር:: ሲያስተምር ምድራዊው ሰው ይቅርና ልዑላኑ መላእክት ተሰብስበው ያደንቁት ነበር:: አንዴም እመቤታችን በሕዝብ መካከል አፈ ወርቅ ብላ ጠርታዋለች:: ለዛም ነው አፈ ወርቅ የሚባለው:: ቅዱሱ በሥልጣነ ቃሉ መልዐከ ሞትን ገስፆ 10 ዓመት አቁሞታል::

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለሰው ፊት አያደላም:: በርሱ ዘንድ ንጉሥና ደሃ ነዳይ እኩል ነው:: ለሞት ያበቃውም ይሔው ነበር:: ምክንያቱም የወቅቱ ንግስት አውዶክስያ ያንዲት ድሃ መበለትን መሬት ቀምታ አልመልስም በማለቷ መክሮ አወገዛት:: እርሷ ግን ከኃጥአንና መናፍቃን ጋር መክራ 2 ጊዜ አጋዘችው:: በተሰደደበት ሃገር ፍሬ አፍርቶ: አስተምሮና አሳምኖ በ407 ዓ/ም አርፏል:: ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ሳይጠግቡት እንደናፈቁት በ60 ዓመቱ አጡት:: በወቅቱ ታላቅ ሐዘንና ለቅሶ ተደረገ::

አንድ ቀን የዘመኑ ደግ ንጉሥ አርቃድዮስ ግብር አገባ:: (ግብዣ አዘጋጀ) በዚያች ሌሊት ደግሞ ቅዱሱ ሊቅ ታጥቆ ሲጸልይ ሳለ: አባ ማርዳሪ የሚባል ጻድቅ ደግሞ 12ቱ ሊቃነ መላእክት (እነ ቅዱስ ሚካኤል) ከሰማይ በግርማ ሲወርዱ ተመለከተ::

ደንግጦ "ወዴት ናችሁ ጌቶቼ" ቢላቸው "ቁስጥንጥንያ: ወደ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንሔዳለን:: እርሱ እመቤታችንን እንደሚያመሰግናት ጌታ ነግሮናልና" አሉት:: "እባካችሁ እኔም የአፈ ወርቅ ምስጋናው እንዲገለጥልኝ መርቁኝ" አላቸው:: ሊቃነ መላእክቱም መርቀውት ጐዳናቸውን ቀጠሉ::

በማግስቱ በቤተ መንግስት ውስጥ ሊቃውንቱ: መሳፍንቱ: ዻዻሳቱ: ሕዝቡ ሁሉ ተሰብስበው ከድግሱ በሉ:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ግን በመንበሩ ተቀምጦ ነበር እንጂ አልበላም:: ድግሱ ሲጠናቀቅ ንጉሡ አርቃድዮስ ሊቁን "ጥያቄ አለኝ" ብሎ በጉባኤ መካከል ጠየቀው::

"ምነው ወንጌላዊ ማቴዎስ 'ኢያዕመራ ዮሴፍ እስከ አመ ወለደት ወለደ ዘበኩራ - የበኩር ልጇን እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም' ማለቱ (ማቴ. 1:25) ስለ ምን ነው?" ቢለው ቅዱሱ ተነስቶ: በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ይተረጉምለት ጀመር::

"ድንግል ማርያም ንጹሕ ብርሌን ትመስላለች:: ብርሌ የተለያየ ቀለም ያለው ፈሳሽ ቢያስገቡበት ቀለሙ አብሮ ይቀያየራል:: እመቤታችንም ጌታን ጸንሳለችና ሕብረ መለኮቱ ሲለዋወጥ መልኩዋ አብሮ ሲለዋወጥ እያየ ዮሴፍ ይደነግጥ ነበር::

'እርሷ ማን ናት? በማሕጸኗ ያለውስ ማን ነው?' እያለ ይጨነቅ ነበር:: ጌታን ከወለደች በሁዋላ ግን አንድ ሕብረ መልክ ሆናለችና:: አስቀድሞ ማን እንደ ነበረች አላወቀም::

አሁን ግን እርሷም ወላዲተ አምላክ: ልጇም አምላክ ዘበአማን መሆኗን አወቀ ማለት ነው" እያለ ሲተረጉም ሰምተው ሁሉም ሲያደንቁ: በዚያ የነበረች ስዕለ አድኅኖ "አፈ ወርቅ! ልሳነ ወርቅ! አፈ በረከት!" ስትል ተናገረች::

ያን ጊዜ አርቃድዮስ የወርቅ ልሳን በሊቁና በስዕሏ ላይ አደረገ:: አፈ ወርቅ ግን ባጭር ታጥቆ "እሰግድ ለኪ! እሰግድ ለኪ! ወእዌድሰኪ . . ." ብሎ ዛሬ በተአምረ ማርያም የምናውቀውን ምስጋና ሰተት አድርጐ አደረሰላት:: ይህንን ምስጋናም ሊቃነ መላእክቱ ሰምተው እያደነቁ ወደ ሰማይ ወጥተዋል::

ሊቁ ባረፈ በ35 ዓመቱ በትንሹ ቴዎዶስዮስ ዘመን: በዚህ ቀን ሥጋው ፈልሷል:: ወደ ቁስጥንጥንያ ሲደርስም ከናፍቆት የተነሳ ታላቅ ዝማሬና እንባ ተደርጉዋል:: አፈ ወርቅም ቀና ብሎ ሕዝቡን ባርኩዋል::

††† ቅዱሱ ሲጠራ እንዲሕ ነው:-
*ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
*አፈ በረከት
*አፈ መዐር (ማር)
*አፈ ሶከር (ስኩዋር)
*አፈ አፈው (ሽቱ)
*ልሳነ ወርቅ
*የዓለም ሁሉ መምሕር
*ርዕሰ ሊቃውንት
*ዓምደ ብርሃን (የብርሃን ምሰሶ)
*ሐዲስ ዳንኤል
*ሊቀ ዻዻሳት ዘበርትዕ (እውነተኛው)
*መምሕር ወመገስጽ ዘኢያደሉ ለገጽ
*ጥዑመ ቃል - - -

††† ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ኢትዮጵያዊት †††

††† ቆራጧ እናታችን ቅድስት ወለተ ዼጥሮስ ለእኛ ለኢትዮዽያውያን የተዋሕዶ አማኞች ሞገሳችን ናት:: እጅግ የሚደነቅ መንፈሳዊ አርበኝነትን በካቶሊኮች ላይ አሳይታለችና::

ቅድስት ወለተ ዼጥሮስ የተወለደችው በ16ኛው መቶ ክ/ዘመን በምሥራቅ ኢትዮዽያ ዳውሮ አካባቢ ነው:: ወላጆቿ ባሕር አሰግድና ክርስቶስ ዕበያ ይባላሉ:: ክርስትናን በሚገባ አጥንታ አድጋ: በወላጆቿ ፈቃድ በሥርዓቱ ባል አገባች:: ግን ወዲያው አፄ ያዕቆብ ገደሉባት::

ታኦዳኮስ

26 Nov, 03:26


የጸሎት ማስተካከያዎች

1, ጸሎተ ሃይማኖት ላይ

ከአብ ጋር የሚስተካከል
ከአብ ጋር የሚካከል ✔️ ( እኩል መሆንን ያሳያል)

2, የቅዳሜ ውዳሴ ማርያም ላይ
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ የውዳሴ ማርያም ደራሲ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በሰባቱ ዕለታት እየተገለጠችለት በሰባቱ ዕለታት ከፋፍሎ ምስጋናዋን አዘጋጅቷል። ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በዕለት በዕለት ብቻ የተከፈለውን ውዳሴ ማርያም ሰአሊ ለነ ቅድስት (ቅድስት ሆይ ለምኝልን) በማለት በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የእድሜ ዘመን በ64 ከፍሎታል። የእያንዳንዱ ቀን ውዳሴ ማርያም ቆጥረው ቢደምሩት 64 ይሆናል። ይኸውም የሰኞ 9 ፣ የማግሰኞ 15 ፣ የረቡዕ 8 ፣ የሐሙስ 7 ፣ የዓርብ 6 ፣ የቅዳሜ 10 ፣ የእሑድ 9 ነው።

በአንዳንድ የአማርኛ ውዳሴ ማርያም መጻሕፍት ላይ ይኽ ተዛብቷል። በቅዳሜ ውዳሴ ማርያም ላይ ለብቻቸው በቅድስት ሆይ ተከፍለው መቀመጥ የነበረባቸውን የመጀመሪያዎቹን ሁለቱን ክፍሎች በአንድ አስቀምጠዋቸዋል  (በአንድ ቅድስት ሆይ ለምኝልን) ፤ እንዲህ በመኾኑ ብዛቱ 63 ይሆናል

ትክክለኛ መሆን ያለበት ግን
'' ንጽሕት ነሽ ብርህትም ነሽ ጌታን በመኻል እጅሽ የያዝሽው ሆይ በሁሉ የተቀደስሽ ነሽ ፤ ፍጥረት ሁሉ ቅድስት ሆይ ለምኝልን ብለው እየጮኹ ከአንቺ ጋር ደስ ይላቸዋል ''
ካለ በኋላ '' ቅድስት ሆይ ለምኝልን'' መግባት አለበት።

'' ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ( ብሎ ጀምሮ )..... ወደ አባቱ ወደ እግዚአብሔርም አቀረበን ፤ ቅድስት ሆይ ለምኝልን ''

ሁለቱም ጋር ቅድስት ሆይ ለምኝልን በማስገባት እናስተካክል።

3,  ይዌድስዋ ላይ

እንዴት ከድሀ ቤት አደረ እንደ ምስኪን የሚለውን አንድ ላይ እናንብብ። ከሰማያት ወርዶ የሚለውን ለብቻው እናንብብ ፤ከሰማይ የወረደ ምስኪን የለምና

4, ይዌድስዋ ላይ

ይህ እንዴት ይሆንልኛል ካለ በኋላ ወንድ አላውቅም (ወንድ ስለማላውቅ) የሚለውን በግዕዝ ቃል ተጠቅሞ '' እንዘ ኢየአምር ብእሴ'' ይላሴ መጽሐፉ ፤  አላውቅም ለማለት '' ኢ '' አፍራሽ ስለሆነች  እንዘ የአምር ሳይሆን ኢየአምር ብለን እናስተካክል።

እንዘ የአምር ብእሴ
እንዘ ኢየአምር ብእሴ ✔️

ታኦዳኮስ

26 Nov, 03:26


ዕለት ዕለት ስለምናደርጋቸው ከማወቅ እንጀምር
ከትላንት ዘግይተናል ከነገ ግን አናረፍድም
መልካም ፆም

ታኦዳኮስ

23 Nov, 13:53


✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ኅዳር ፲፭ (15) ❖

+"+ ቅዱስ ሚናስ ምዕመን ሰማዕት +"+

=>ቅዱስ ሚናስ (ማር ሚና) በምድረ ግብጽ ተወዳጅ
ከሆኑ ሰማዕታት ዋነኛው ነው:: ልክ በሃገራችን ቅዱስ
ጊዮርጊስ ልዩ ቦታ እንዳለው ሁሉ ግብፃውያን ማር
ሚናስን ጠርተው አይጠግቡትም::

+ምክንያቱም ከታላላቅ ሰማዕታት አንዱ በመሆኑና ዛሬም
ድረስ ለጆሮና ለዐይን ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ስለሚሠራ
ነው:: በተለይ ለታመመ: ለደከመና ለተጨነቀ ፈጥኖ
ደራሽ: ባለ በጐ መድኃኒት ፈዋሽና አማላጅ ነው::

+"ግብጽ ውስጥ ቅዱሱን የማያውቅ ሰው ካገኛችሁ
እርሱ ኦርርቶዶክሳዊ አይደለም ማለት ነው" ሲባልም
ሰምተናል:: በነገራችን ላይ ለቅዱሳን ተገቢውን ክብር
በመስጠት: ታሪካቸውን በመጻፍ: በማጥናት: በመጽሔት:
በፊልምና በመሳሰሉት ለሕዝብ በማስተዋወቅ
ግብጻውያኑ ከእኛ ብዙ ርቀት ሒደዋል:: ዛሬ እንኩዋ
የምንጠቀምበትን ስንክሳር 80 ከመቶ እጁን ያዘጋጁት
እነርሱ ናቸው::

+አባቶቻችንና እናቶቻችን ኢትዮዽያውያን ቅዱሳን ግን
አብዛኞቹ ተረስተው ቀርተዋል:: መጽሐፈ ገድላቸውንም
ብል በልቶታል:: ዛሬም የቤት ሥራው የእኛ ብቻ ነው::

+ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ ሚናስ (ትርጉሙ ታማኝና ቡሩክ ማለት ነው):-

*በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረ የደጋግ ክርስቲያኖች
ልጅ::
*በልጅነቱ የቅድስና ሕይወትን ያጣጣመ::
*በዘመኑ ሰው እጅግ ተወዳጅ የነበረ::
*ሃብትን: ክብርን: ሥልጣንን ንቆ በጾምና በጸሎት
የተወሰነ::
*በመጨረሻም በክርስቶስ ስላመነ አላውያን የገደሉት
ሰማዕት ነው::

+እርሱ ሰማዕት ከሆነ ከበርካታ ዘመናት በሁዋላ
ምዕመናን ክቡር አካሉን ፈልገው ያጡታል::
የሚገለጥበት ጊዜ ሲደርስ ግን እርሱ የተቀበረበት ምድረ
በዳ የበጐችና የእረኞች መዋያ ነበርና ተአምራትን
አደረገ::

+አንድ እረኛ በጐቹ ድውያን ሆኑበት:: በዚያ ሰሞን
ከቅዱሱ መቃብር ላይ ጸበል ፈልቆ ነበርና እረኛው ተርታ
ውሃ ነው ብሎ በጎቹን ሲያጠጣቸው አንዱ ድውይ በግ
ወደ ጸበሉ በመዘፈቁ ዳነ::

+በዚህ የተገረመው እረኛ ሁሉንም የታመሙ በጐቹን
አምጥቶ ነከራቸው:: እነርሱም ተፈወሱ:: ይህ ዜና
በምድረ ግብፅ ሲሰማ ድውያን ሁሉ እየመጡ ይፈወሱ
ገቡ:: ግን እነሱም ሆነ እረኛው ምክንያቱን ማወቅ
አልቻሉም:: ነገሩ በሮም ንጉሥ ዘንድ ሲሰማ ሴት ልጁን
ከሠራዊቱ ጋር ላካት::

ምክንያቱም እርሷ ከብዙ ዘመን ጀምራ መጻጉዕ ነበረችና
ፈውስን አጥታ ነበር::

+መጥታ ተጠመቀች: ፈጥናም ተፈወሰች:: እርሷ ግን
እንደ ሌሎች ያዳናትን ማንነት ሳታውቅ መሔድ
አልፈለገችምና ሱባዔ ገባች:: ቅዱስ ሚናስ በሌሊት
ራዕይ መጥቶ ሥጋው እንዳለ ነገራት:: እርሷም መሬቱን
አስቆፍራ የቅዱሱን አካል በክብር አስወጣች::

+ከዚያም በንጉሡ ትዕዛዝ ምድረ በዳው ከተማ
እንዲሆን ተቀየረ:: ስሙም "መርዩጥ" ተባለ:: ጸበሉ
የነበረበት ቦታም ላይ የማር ሚናስ ቤተ ክርስቲያን
ታንጾበት ቅዳሴ ቤ ተከብሯል::

+"+ ቅዱስ ቂርቆስ ሕጻን +"+

=>ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ካሏት ዐበይት ሰማዕታት አንዱ
ቅዱስ ቂርቆስ ነው:: በተለይ በዘመነ ሰማዕታት ተነስተው
እንደ ከዋክብት ካበሩትም አንዱ ነው:: ቅዱስ ወንጌል
እንዲህ ይላል:- "መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን
ያፈራል::" (ማቴ. 7:17)

+መልካም ዛፍ ቅድስት ኢየሉጣ መልካም ፍሬ ብጹዕ
ቂርቆስን አፍርታ ተገኝታለችና ክብር ይገባታል:: ቡርክተ
ማሕጸንም እንላታለን:: የተባረከ ማሕጸኗ የተባረከ ልጅን
ለ9 ወር ተሸክሟልና::

+በዚያ ክርስቲያን መሆን መከራ በነበረበት ዘመን ይህንን
ደግ ሕጻን እርሷን መስሎ: እርሷንም አህሎ እንዲገኝ
አስችላለችና:: አበው በትውፊት እንዳቆዩልን ከሆነ
በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በዚህች ቀን እናታችን ቅድስት
ኢየለጡ ብጹዕ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስን ወልዳለች::

+ፈጣሪ ቢያቆየን የሰማዕትነት ዜናቸውን ጥር 15 ቀን
የምንመለከት ነንና የዚያ ሰው እንዲለን እንማጸነዋለን::

=>አምላከ ሰማዕታት በምሕረቱ ይማረን:: በይቅርታው
ኃጢአታችን ይተውልን:: ከበረከተ ሰማዕታትም ይክፈለን::

=>ኅዳር 15 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ሚናስ ሰማዕት
2.ልደተ ቅዱስ ቂርቆስ
3.ብጽዕት ኢየሉጣ
4.አባ ሚናስ ዳግማይ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (አፈ በረከት)
2.ቅድስት እንባ መሪና
3.ቅድስት ክርስጢና

=>+"+ አሁንስ ይላል እግዚአብሔር:: በፍጹም ልባችሁ
በጾምም: በለቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ:: ልባችሁን
እንጂ ልብሳችሁን አትቅደዱ:: አምላካችሁም
እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ: ቁጣው የዘገየ: ምሕረቱም
የበዛ: ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ:: +"+ (ኢዩ. 2:12)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/zikirekdusn

ታኦዳኮስ

15 Nov, 09:44


እመቤታችን ቅድስት ማርያም ከጌታችን ኢየሱስ ጋር ከመሰደዷ አስቀድሞ ነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹ወይወርድ እግዚእነ ውስተ ምድረ ግብጽ እንዘ ይጼዐን ዲበ ደመና ቀሊል፤ ጌታችን በፈጣን ደመና (በእመቤታችን ጀርባ) ተጭኖ ወደ ግብጽ ይወርዳል›› ተብሎም በተናገረው መሠረት ትንቢቱ ተፈጽሟል፡፡ (ኢሳ. ፲፱፥፩)

ጌታችን ኢየሱስ  በደብረ ቁስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቱን ሰበሰባቸው፤ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንንም አክብሮ የቁርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ሰጥቷቸዋል፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከጌታችን ኢየሱስ ጋር በቁስቋም ተራራ ስድስት ወራትን ያረፈች ሲሆን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅዳር ፮  የእነርሱን ስደትና ወደ ሀገራቸው እስራኤል መመለሳቸውን በማስታወስ ታከብራለች፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!!

ምንጭ፤ ድርሳነ ማርያም (ትርጉም ፳፻፫ ዓ.ም)
              ስንክሳር ዘወርኃ ኅዳር

ታኦዳኮስ

15 Nov, 09:44


ደብረ ቁስቋም

ኅዳር ፮ ቀን የአርያም ንግሥት፣ የፍጥረታት ሁሉ እመቤት፣ የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይዛ አረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍንና ቅድስት ሰሎሜን አስከትላ ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት የስደት እና የመከራ ዓመታት በኋላ በስተደቡብ የምትገኘው ደብረ ቁስቋም ላይ ያረፉችበት ዕለት ይከበራል፡፡

ደብረ ቁስቋም በደቡብ ግብጽ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ይህ ተራራ የተቀደሰ ተራራ ስለመሆኑ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ታኦፊሎጎስ በድርሳነ ማርያም ‹‹ይህም ከሀገሮቹ ሁሉ ተራሮች የሚበልጥ (የተለየ) ከፍ ያለ ተራራ ነው፡፡ በውስጡ ቅዱስ አግዚአብሔር ያድራል፡፡ ይህንን ተራራ የእግዚአብሔር ልጅ ወዶታል፤ አክብሮታልምና፤ ከዓለም ሀገሮች ሁሉ ከተቀደሰች እናቱ ጋር አድሮባታልና፡፡ ከመላእክት ቤት ያድር ዘንድ አልወደደም፤ ቢታንያንም አልመረጠም፡፡ ከተራራው ላይ ባለች ገዳም ቤት ውስጥ አደረ እንጂ፤ ነቢዩ ዳዊት የጽዮንን ተራራ ወደደ፤ በአርያምም መቅደሱን ሠራ እንዳለ፡፡››

በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ ሄሮድስ ክርስቶስን ለመግደል በፈለገ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለአረጋዊው ዮሴፍ በሕልሙ ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ›› ባለው መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ (ማቴ. ፪፥፲፫-፲፭)

በስደቱም ጣዖታተ ግብጽ እየተሰባበሩ ሲወድቁ፤ በእነርሱም አድረው ሰውን ሲያስቱ የነበሩ አጋንንትም ሲሸሹ ታይተዋል፤ ደግሞም ጌታችን ዳግማዊ አዳም ነውና በምክረ ከይሲ (ዲያብሎስ) ምክንያት ተሰዶ የነበረው ቀዳማዊ አዳምን ለመካስ ተሰደደ፤ በዚህም አጋንንትን ከሰው ልቡና አውጥቶ አሳደደ፡፡

ታኦዳኮስ

21 Oct, 06:23


"እግዚአብሔር አምላክ የለመኑትን አይነሳምና ሁላችሁም ስለ ሀገር ሰላም፣ስለ ቤተክርስቲያን አንድነት፣ስለ ሕዝብ ደህንነትና አብሮነት ጸልዩ፤"

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት

ታኦዳኮስ

12 Oct, 15:58


የምንጸልየው እግዚአብሔር ምን ማድረግ እንዳለበት ለመንገር ሳይሆን እግዚአብሔር ምን ማድረግ እንዳለብን እንዲነግረን ነው።
        ቅዱስ አውግስጢኖስ

ታኦዳኮስ

09 Oct, 09:39


ሐመር መጽሔት ፴፩ ኛ ዓመት ቁጥር -፲ ጥቅምት ፳፻፲ ፯ ዓ.ም በመልዕክት ዐምድ "#የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ነባራዊ ሁኔታ የሚረዳ፣ ከሥጋትም የሚታደግ ትውልድ እናፍራ "በሚለል ዐቢይ ርእስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ የደረሰባትን ፈተና ሁሉ እያለፈች ዛሬ ላይ የደረሰችው ከእግዚአብሔር ጥበቃ ጋር የዘመኑን ፍልስፍና ተረድተውና ዘመኑን ዋጅተው ሃይማኖትን ከሥነ ምግባር ጋር አዋሕደው ይዘው ጠላት ዲያብሎስ የሚዋጉ ጠንካራ አባቶች ስለነበሯት ነው፡፡ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካትና ለህልውናዋ የሚተጋ፣ ሁለንተናዊ ዕድገትን የተላበሰ ትውልድ ለማፍራት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሁሉ መሥራትም ጊዜ የማይሰጠው ተግባር መሆኑን መረዳት ይገባል። በማኅበረ ቅዱሳን ፲፮ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተስተዋለውን የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያ ኃላፊዎች ተሳትፎ በማጠንከር እና የየማዕከላቱ ተወካዮች በተለያየ ችግር ውስጥ ሁነው ሳላ ስለ አገልግሎት ለመመካከር ብዙ ነገሮችን ተቋቁመው መምጣታቸው፣ለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በመናበብ ማገልገል ከማኅበረ ቅዱሳን የሚጠበቅ ተግባር ነው ። ማኅበረ ቅዱሳን እንደ ቤተ ክርስቲያን ልጅነቱ ከአባቶቹ መመሪያ እየተቀበለ ለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት መጠናከርና ተደራሽነት እያደረገ ያለውን ጥረት ከአሁኑ በተጠናከረና ዘመኑን በዋጀ መልኩ ማከናወን ይጠበቅበታል።"በማለት ታስነብባለች።

.#ዐውደ ስብከት ሥር” #ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊት ” በሚል ርእስ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊነት ማለት ሰፊ ጽንሰ ሐሳብ ያለው ከመሆኑ የተነሣ በአጭር ዐረፍተ ነገር ለመግለጽ አስቸጋሪ እንደሆነ ያሳያል ። ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን አንዲት፣ ጋራ ተራራ፣ ድንበር ወሰን፣ ቋንቋ፣ ዘርና ቀለም የማይገድባት ዓለም ዐቀፋዊት፣ ሐዋርያዊት፣ ጥንታዊት፣ ሰላማዊት፣ እና ርትዕት ናት፡፡ “ኦርቶዶክሳዊ ተዋሕዶ” ነት ከዓለም ፈጣሪና መጋቢ ከልዑል እግዚአብሔር እና ካከበራቸው ቅዱሳን ጋር አሁን በረድኤት ኋላም በመንግሥተ ሰማያት በክብር መንግሥቱ አብሮ መኖር ማለት መሆኑን ያሳያል።

#በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “# "ዘመነ ጽጌ " በሚል ዐቢይ ርእስ በመልአከ ሰላም ቀሲስ #ደጀኔ ሺፈራው #የደንቨር ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ይህን ወቅት(ዘመነ ጽጌን) ቤተ ክርስቲያን:-እመቤታችንን በምድር አንድም በአበባ፥ተወዳጅ ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስንም በአበባ አንድም በፍሬ እየመሰለች ዘመነ ስደታቸውን በየዓመቱ በማኅሌት፥ በቅዳሴ በመዝሙርና በትምህርት በልዩ ኹኔታ ታስበዋለች።የሚፈጸመውም አገልግሎት ለጊዜው ዘመነ ጽጌ ምነው ባላለቀ የሚያሰኝ፥ ለፍጻሜው ደግሞ የከርሞው መቼ በደረሰ የሚያስብል አገልግሎት እንዳላት ያስተምራሉ ።
#ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ሥር ደግሞ “#ለመማከር ተሰበሰቡ "በሚል ዐቢይ ርእስ ብፁዓን አባቶችም ከሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ የሚቀርበው ሪፖርት ምን ያህል በአደራ የተቀበሏቸውን የክርስቶስን ግልገሎች ጠቦቶችንና፣ በጎችን የማገልገል ጉዳይ ሆኖ ቀርቧል የሚለውን ነጥብ ይፈትሻሉ፡፡ ከዚህ ያፈነገጠ ሪፖርት፣ ዕቅድ፣ ውሳኔና አቋም ሁሉ ብፁዓን አባቶች የሚመሯትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን እንደማይመለከት በግልጽ ያሳያሉ፡፡ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሪፖርትም ለዚህ በአደራ የተሰጣቸውን ከባድ ኃላፊነት መወጣት የሚያስችል ምላሽ የሚሰጥ መሆን ይገባዋል፡፡ በዚህ ጉባኤ ከሚገኙት የሪፖርት ምላሽ ተነስተው አባቶቻችን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን አጀንዳ ይቀርጻሉ፡፡

አገልጋዮች ለአገልግሎታቸው ምን ዓይነት ማነቆዎች አጋጠሟቸው? የትኞቹስ ቀኖናዊ መፍትሔ የሚፈልጉ ናቸው? የትኞቹ በጸሎት የሚፈቱ ናቸው? የትኞቹ በምክርና ተግሣጽ የሚፈቱ ናቸው? …ወዘተ ብሎ በዓይነትና በመልክ አቅጣጫ ይሰጣል፡፡
• #ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር ደግሞ "#ጭንቀት ክፍል_ ፩ "በሚል ርእስ መጋቤ ሐዲስ #አእምሮ ደምሴ #የኳታር ጸርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የብሉያትና የሐዲሳት ትርጓሜ መ/ር ደግሞ ሥጋዊ ጭንቀት፦ከልብ የሚመነጭ በሕሊና የሚወጣና የሚወርድ ፣በረቂቁ አእምሯችን የሚመላለስ ፣ በሐሳብ መሥመር የሚንቀሳቀስ፣ በሕሊና ቦይ የሚፈስ፣ ለጉዳት የሚያጋልጥ ነው። ጭንቀት፦ ክብደቱና ቅለቱ ይለያያል እንጂ በሁሉም ሰው ላይ የሚታይና የሚገለጽ ነው።ጭነቀትት ፦ መጠኑ ከሚገባው በላይ እየጨመረ ከሄደ ሰውነትን የሚያዛባ፣ አእምሮን የሚያቀውስ፣ ሕሊናን የሚያዘነጋ፣ ራስን እስከመጣል የሚያደርስ፣ ከቤተሰብ፣ ከትዳር፣ ከጓደኛ፣ ከጎረቤት፣ ከማኀበራዊ ኑሮ የሚለይ ፣ በብቸኝነት መኖርን እንዲመርጡ የሚያደርግ፣ ከፍ ሲልም ተስፋ እስከ መቁረጥ የሚያደርስ አደገኛ እንደሆነ በጹሑፋቸው ይጠቁማሉ። ስማችን፣ አለባበሳችን፣ ኦርቶዶክሳዊ ሆኖ ነገር ግን ከኦርቶዶክሳዊነት ውጭ በሆነ እሳቤ ብዙ ጉድለቶች እንዳሉብን ያሳያሉ ።
• #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “#የምሥራቅ አፍሪካ ፈርጥ #ናይሮቢ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን " በሚል ርእስ በኬንያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለመመሥረቱ ምክንያቶችና የአመሠራረት ሁኔታውን ፣የናይሮቢ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን የስብከተ ወንጌል እንቅስቃሴ ፣ በአብነት ትምህርት ፣ የደብሯን የሰበካ ጉባኤ የልማት እንቅስቃሴ ፤በሰንበት ትምህርት ቤት እና በየዘመናቱ የነበሩ ተግዳሮቶች ፣ወቅታዊጉዳዩች፣ የናይሮቢ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያንን ልዩ የሚያደርጉት ጉዳዮችን ፣-በደብሩ የሚገኙት የሰበካ ጉባኤ አባላት ፣የሰንበት ት/ቤት አባላትና በማኀበረ ቅዱሳን የኬንያ ማእከል አባላት በፍጹም አንድነት ያለ ምንም ልዩነት አገልግሎት የሚሰጥበት ቤተ ክርስቲያን ነው፡፣ የናይሮቢ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን መልካም አጋጣሚዎችን ታስቃኛለች ።
• #በነገዋ ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ ሥር "ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን የስብከተ ወንጌል ሚና _ክፍል ፪ " በሚል ስብከተ ወንጌላችን ተደራሽ እንዲሆን ምን መደረግ እንዳለበት የተወሰኑ ነጥቦችን ያነሳል ።ተልዕኮ ተኮር የስብከት ዘዴን መከተል ፤የቋንቋ እንቅፋትን ማስወገድ፣ በቦታ ያልተገደደበ አገልግሎት መስጠት ይገባናል ።
#በኪነ ጥበብ ዐምድ "# ትንሣኤ_፪ "በሚል ታስነብባለች ።
• # በጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምዳችን “ወርኃ ጽጌን ክፍል -፩ ” በተመለከተ የሚነሡ ጥያቄዎችን መሠረት አድርገን ምላሽ ይሰጡን ዘንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል የሆኑትን መጋቤ ሐዲስ #ተስፋ ሚካኤል ታከለ ጋር የተደረገውን ምልልስ ይዛለች ።
ሐመር መጽሔት #፴፩ ኛ ዓመት ቁጥር ፲ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ !

magazine @eotcmk.org #ሐመር #መጽሔት ዝግጅት ክፍል

ታኦዳኮስ

09 Oct, 09:39


ሐመር መጽሔት በጥቅምት ወር እትሟ!

✍️".....በዚህ ዓመት  ምን ያህል ገንዘብ ፈሰስ አደረገ ከሚለው ይልቅ በዚህ ዓመት ስንት ነፍስ በንስሓ አተረፍን? ስንት የሥላሴ ልጆችን በጥምቀት አፈራን  ወይም ቅድስት  ቤተ ክርስቲያን ስንት ኢአማንያንን በጥምቀት ወለደች??  ...."✍️ #ሐመር #መጽሔት ዐቢይ ጉዳይ ጥቅምት  ፳፻፲፯ ዓ.ም  )
                      ༺ ༻ 
#የኅትመት ዘመን ፦#ጥቅምት ፳፻፲፯ ዓ.ም ቁ.፲ 
#አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በልማት ተቋማት አስተዳደር  በመጽሔት ዝግጅት ክፍል #በየወሩ የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት
•  ገጽ ብዛት፦፳፰
   ዋጋ ፦፵ ብር 
•  ሐመር  መጽሔት  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት  ሥርዓትና ትወፊት ጠብቃ በልማት ተቋማት አስተዳደር  በመጽሔት ዝግጅት ክፍል  በየወሩ የምትወጣ መንፈሳዊ መጽሔት ናት፡፡

ታኦዳኮስ

10 Sep, 16:27


እንኳን ለአዲሱ ለዘመነ ማቴዎስ በሰላም በጤና አደረሰን!!

አዲሱ ዓመት ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር የተሰጠን ሌላ አዲስ ዕድል ነው። አማኑኤል ከእኛ ጋር ለመሆን የእኛን ሥጋ ተዋሕዷል። አምላክነቱ ሳያሳስበው የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አድርጉዋል። በደሃ ቤት አድሯል፣ በበረት ተወልዷል፣ ከብርድ መከለያ ጨርቅን ፈልጓል፣ ፍጥረትን የሚመግብ እርሱ ከእናቱ የድንግልናዋን ወተት ለምኖ አልቅሷል፣ እንደ ሕፃናት በጉልበቱ ድኋል፣ ለእናቱ እየታዘዛት ጥቂት በጥቂት አድጓል። ከአደገም በኋላ ራሱን የሚሰውርበት ጎጆ ሳይኖረው በተራራ ተንከራቷል፣ ተርቧል፣ ከኃጢአተኞች በደረሰበት ተቃውሞ ተሰድቧል፣ ተገፍቷል። ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ሆኗል።

ከእኛ ጋር ለመሆን ብቻ ሳይሆን በእኛ ውስጥ ለመኖር ደግሞ በዕለተ አርብ በመስቀል ተሰቅሎ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ተሰጥቶናል። እኛስ ወደ እርሱ ሊያቀርበን ይህን ሁሉ ከሆነልን አምላክ ጋር ለመኖር ምን አደረግን? ለእርሱ ብለን ክፋትን አወገዝን? የተሸከምነውን ኃጢአት በንስሐ አራገፍን? ሥጋ ወደሙን ተቀበልን? 

ከእግዲህስ በኃጢአት ያረጀ ማንነታችንን እንተው። አዲሱን ዓመት  "ማለዳ ማለዳ አዲስ" ከሆነው ፈጣሪያችን ጋር ለመኖር ለራሳችን ብሩህ ተስፋ እንሰንቅ። እስኪ አምና ወድቀን ከተሰበርንበት የዘር፣ የጥላቻ ጉድጓድ ወጥተን ዘንድሮን ተዋድደን፣ ተፋቅረን በሰላም እንኑር። እስኪ ደግሞ ወደ ሰላማዊ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀርበን ይህችን ዓመት በሰላም ጀምረን እንፈጽማት።

መልካም አዲስ ዓመት!!!

ታኦዳኮስ

08 Sep, 11:57


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!
ጳጕሜን 3 ቀን 2016 ዓ.ም
የሉቃስ ወንጌል ም 17 ቁ 11 - 37
መልካም ዕለተ ሰንበት !

#ethiopianorthodoxtewahedochurch #የዕለቱ_ወንጌል
#tewahedomediacenter#sunday

ታኦዳኮስ

08 Sep, 11:56


ኢየሱስ ክርስቶስ:
ለሚጠራው ስሙ ጣፋጭ ነው።
ለሚበላው የሕይወት እንጀራ ነው።
ለሚጠጣው የመድኃኒት ጽዋ ነው።

ታኦዳኮስ

07 Sep, 21:11


🕊እንኳን አደረሳችኹ ወርኃ ጳጒሜን በሰላም ያስፈጽመን የንስሐ ልብ ይሰጠን::

🕊"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"    /ማቴ ፫:፫/

💥ስለ ንስሐ💥

ከቅዱስ ሙሴ ጸሊም የምንማራቸው 7 ነገሮች።

፩, 🌿ቅዱስ አብርሃምን መምሰል( ፈጣሪውን ተመራምሮ አገኘ)::

፪,  🌿ዓለምንና የዓለምን ነገሮች መታው።

፫, 🌿የንስሐ ሕይወት( ንስሐን በትጋት መፈጸም)።

፬, 🌿መታዘዝ (የሚታዘዘውን ሳያጓድል መስራትን)።

፭, 🌿ለሌሎች መኖርን።

፮, 🌿በሰው አለመፍረድን።

፯, 🌿ትሕትናን።
          

🌿ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!


1,💥ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡

2,💥ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡

3, 💥በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡

4,💥የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው

4 ነገሮችን በደንብ ልብ እንበል!
    1, አላማ

    2 ,እምነት

    3,ጥረት

    4 ጥንቃቄ

❇️9ኙ የቅድስና መንገዶች❇️

💥ሃይማኖት
💥ጾም
💥ጸሎት
💥ስግደት
💥ምጽዋት
💥ፍቅር
💥ትህትና
💥ትዕግስት
💥የዋህነት

እነዚኽን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።

🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት
🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)


🔗https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

ታኦዳኮስ

07 Sep, 21:11


እንኳን አደረሳችሁ !

ጳጒሜን ፫፦

አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ዝክረ ስሞሙ ሕይወት፤
ወሩፋኤል መልአክ ፈዋሴ ቁስሉ ለጦቢት፤
ለሰራጵዮን ወጦብያ ወለሣራ ማኅቶት፤
መልከ ጼዴቅ ሊቀ ካህናት ንጉሠ ሳሌም ኅሪት፤
ዘርዓያዕቆብ ጻድቅ ንጉሠ አዜብ አግዓዚት፤
ዮሐንስ ወአኖሬዎስ ወቴዎፍሎስ ሊቀ ጳጳሳት

ታኦዳኮስ

07 Sep, 21:11


††† እንኳን ለርኅወተ ሰማይ: ለቅዱስ ሩፋኤል: መልከ ጼዴቅ: ዘርዓ ያዕቆብና ሰራጵዮን ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ርኅወተ ሰማይ †††

††† ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት: አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት: ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ዕለት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ-ሰማይ የሚከፈትባት ቀን::" ትባላለች::

አሁን በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም:: የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት ያለ ከልካይ የሚያሳርጉበት: አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንዲህ ተባለ እንጂ::

እመቤታችን ድንግል ማርያም ለአጼ ናዖድ እንደ ነገረቻቸው በዚህች ዕለት ሁሉም ቅዱሳን ስለሚታሰቡ: የእግዚአብሔር የምሕረት መዝገቡ ስለሚከፈት: ዕለቷን ክብርት ያሰኛታል:: በቅዱስ ሩፋኤል አበጋዝነት (መሪነት) በዚህች ዕለት ለዓመት የሚበቃ ምሕረት ይገኛል::

ስለዚህም አባቶቻችን በዚህች ሌሊት ሦስት መቶ ስልሳ አምስት አቡነ ዘበሰማያትን ሲጸልዩ ያድራሉ:: በሌላ ወገን ደግሞ የጌታ ዳግም ምጽዓቱ መታሰቢያ እንደ መሆኗ ትልቅ ትኩረትም ይሰጣታል::
ቸሩ ጌታችን ከተከፈተች ገነት ከተነጠፈች ዕረፍት ሁላችንንም ያድርሰን::

††† ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት †††

††† ቅዱስ ሩፋኤል በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት በደረጃው ሦስተኛ ነው:: በመጀመሪያዋ ዕለተ ፍጥረት እግዚአብሔር መቶ ነገደ መላእክትን ፈጥሮ በአሥር ከተማ ሲያኖራቸው የቅዱስ ሩፋኤል ዕድል ፈንታው ራማ ሆነች::

በዚያም "መናብርት" ተብለው ለሚጠሩ አሥሩ ነገድ አለቃ (መሪ) ሆኖ በፈጣሪው ተሹሟል:: በኋላም "መጋብያን" በሚባሉ በሃያ ሦስቱ ነገድ ላይ ሹሞታል:: ይህች ዕለትም በዓለ ሲመቱ ናት::

አንድ ቀን ጌታችን ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ ሐዋርያቱ ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲያስተዋውቃቸው ለመኑት:: ጌታም ሦስቱን ሊቃናት (ሚካኤል: ገብርኤል እና ሩፋኤል) ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው::

ቀጥሎም ቅዱስ ሩፋኤልን "ክብርህን ንገራቸው::" አለው:: እርሱም ለጌታ ሰግዶ ለሐዋርያት ብዙ ምሥጢር ነገራቸው:: በተለይ ስሙን ለሚጠሩ: መታሰቢያውን ለሚያከብሩ የሚደረገውን ጸጋ አብራርቶላቸው ዐረገ::

በመጽሐፈ ጦቢት ላይ ተጽፎ እንደምናገኘው ቅዱሱ መልአክ ሰው (አዛርያን) መስሎ: ጦብያን ለትዳር አብቅቶ: ሣራን አስማንድዮስ ከሚባል ሰይጣን አድኖ: የጦቢትን ዓይን አብርቷል:: በገድላተ ቅዱሳን እንደምናየውም ለብዙ ቅዱሳን ረዳታቸው ሆኖ ገድላቸውን አስፈጽሟል::

ታሪክ እንደሚለው ይህች ቀን ለቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱም ናት:: በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በቅዱስ ቴዎፍሎስ ዘእስክንድርያ አማካኝነት ቤቱ ታንጿል:: የሚገርመው ደግሞ የታነጸው በዓሣ አንበሪ ጀርባ: ደሴት ላይ ነው:: በመልአኩ አጋዥነትም ለሦስት መቶ ዓመታት አገልግሏል::

††† ቅዱስ ሩፋኤል
¤መስተፍስሒ (ልቡናን ደስ የሚያሰኝ)
¤አቃቤ ሥራይ (ባለ መድኃኒት ፈዋሽ)
¤መዝገበ ጸሎት (የጸሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው)
¤ሊቀ መናብርት (በዙፋን ላይ በክብር የሚቀመጡ መላእክት መሪ)
¤ፈታሔ ማኅጸን (የሰውንም ሆነ የእንስሳትን ማኅጸን የሚፈታ)
¤መወልድ (አዋላጅ: ምጥን የሚያቀል) ይባላል::
"ለሰብእ ወለእንስሳ ፈታሔ ማኅጸኖሙ አንተ" እንዲል::

††† ቅዱስ መልከ ጼዴቅ †††

††† ካህኑ መልከ ጼዴቅን ቅዱስ ጳውሎስ "የትውልድ ቁጥር የለውም: ለዘመኑም ጥንትና ፍጻሜ የለውም::" ይለዋል:: (ዕብ.7:3) ሐዋርያው ይህንን ያለው ለወልደ እግዚአብሔር ምሳሌ ሲያደርገው እንጂ ትውልዱ ከነገደ ካም ነው:: ወላጆቹም "ሚልኪ እና ሰሊማ" ይባላሉ::

ገና ከእናቱ ማኅጸን የተመረጠው ቅዱሱ "ካህነ ዓለም: ንጉሠ ሳሌም" ይባላል:: የዛሬ አምስት ሺ አምስት መቶ ዓመት አካባቢ ሴም ባኖረበት ቦታ (በደብረ ቀራንዮ) ለዘላለም ይኖራል:: ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከሰው ወገን እጅግ ክቡርም ነው::

††† አፄ ዘርዓ ያዕቆብ †††

††† ሃይማኖቱ የቀና ኢትዮጵያዊው ንጉሥ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በኢትዮጵያ በነገሠባቸው ሠላሳ አራት ዓመታት (ከ1426 እስከ 1460 ዓ/ም) ብዙ በጐ ነገሮችን ሠርቷል:: ላለፉት ሰባ ዓመታት ግን አንዳንድ ጥቃቅን ሰብአዊ ስህተቶችን እየነቀሱ ተሐድሶዎቹ ስሙን ሲያጠፉት ኑረዋል::

ዛሬ ዛሬ ደግሞ የእኛ ቤት ሰዎችም ተቀላቅለዋቸዋል::
እነርሱ ያሉትን ይበሉ እንጂ ለእኛ ግን ዘርዓ ያዕቆብ ማለት:-
1.ጣዖት አምልኮን ከሃገራችን ለማጥፋት ብዙ ሺህ ካህናትን አሰልጥኖ አሰማርቷል::
2.የኑፋቄ ችግሮችን ለመቅረፍ ጉባኤያትን አዘጋጅቷል::
3.ከአሥራ አንድ ያላነሱ መጻሕፍትን በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ደርሶ ለአገልግሎት አብቅቷል::
4.ብዙ መጻሕፍትን ከውጪ አስመጥቶ አስተርጉሟል (በተለይ ተአምረ ማርያምን)
5.ሰው ሁሉ ለእመ ብርሃንና ለመስቀሉ ፍቅር እንዲገዛ ጥረት አድርጓል
6.እመቤታችንን በፍጹም ልቡ ከመውደዱ የተነሳ ዛሬ ድረስ በሃገራችን ድንግል ማርያም "የዘርዓ ያዕቆብ እመቤት" እየተባለች ትጠራለች::
7.ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን አንጾ: ብዙ ሥርዓቶችም በሊቃውንት እንዲሠሩ አድርጐ: ሌሎች ብዙ በጐ ተግባራትንም ፈጽሞ በዚህች ቀን ዐርፏል::
ቤተ ክርስቲያን ስለውለታቸው ዘርዓ ያዕቆብን: እናታቸው ጽዮን ሞገሳን እና አባታቸው ዳዊትን በክብር ታስባለች::

††† ቅዱስ ሰራጵዮን ዘሰንዱን †††

††† ይህ ቅዱስ እጅግ የበዛ ሃብቱን ለነዳያን አካፍሎ: ወደ ሌላ ሃገር ሔዶ ለባርነት ተሽጧል:: በተሸጠበት ሃገርም በጸሎት ተግቶ ከክህደት ወደ ሃይማኖት መልሷቸዋል:: ክብሩን ሲያውቁበትም በተመሳሳይ ወደ ሌላ ሃገር ሒዶ አሕዛብን አድኗል:: በፍጻሜው ወደ በርሃ ገብቶ በተጋድሎ ኑሮ በዚህች ቀን ዐርፏል::

††† አምላከ ቅዱሳን የወዳጆቹን ሁሉ በረከትና ጸጋ ያብዛልን:: ለዓለምም ሰላሙን ይዘዝልን::

††† ጳጉሜን 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ርኅወተ ሰማይ (የሰማይ መከፈት)
2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት
3.ቅዱስ መልከ ጼዴቅ ካህን
4.አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ንጉሥ (የእመቤታችን ወዳጅ)
5.ቅዱስ ሰራጵዮን ዘሰንዱን
6.ቅዱስ አኖሬዎስ
7.ቅዱስ ቴዎፍሎስ
8.አባ ዮሐንስ
9.ቅዱስ ጦቢት
10.ቅዱሳን ጦብያና ሣራ

††† ወርኀዊ በዓላት
(የለም)

††† "እውነት እውነት እላችኋለሁ:: ሰማይ ሲከፈት: የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ::" †††
(ዮሐ. ፩፥፶፪)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

ታኦዳኮስ

07 Sep, 14:27


††† እንኳን ለቅዱስ ቲቶ ሐዋርያ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ቲቶ ሐዋርያ †††

††† የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ቅዱስ ቲቶ ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ሲሆን በተወሰነ መንገድም ቢሆን የተዘነጋ ሐዋርያ አይደለም:: በተለይ ደግሞ ቅዱስ ጳውሎስ ከጻፋቸው አሥራ አራት መልእክታት መካከል አንዷ የተላከችው ለዚህ ቅዱስ በመሆኗ ታሪኩ እንኳ ባይነገር ስሙ አይረሳም:: ቅዱስ ጳውሎስም በመልዕክታቱ በጐ ስሙን እየደጋገመ ያነሳዋል::

ለመሆኑ ሐዋርያው ቅዱስ ቲቶ ማን ነው?
ቅዱስ ቲቶ የተወለደው በ1ኛው መቶ ክ/ዘመን እስያ ውስጥ: ቀርጤስ በምትባል ከተማ ነው:: የዘር ሐረጉ ከእሥራኤልም: ከጽርእም (ግሪክ ለማለት ነው::) ይወለዳል:: አካባቢው አምልኮተ እግዚአብሔር የጠፋበት ስለሆነ እሱም: ቤተሰቦቹም የሚያመልኩት ከዋክብትን ነበር::

መዳን በእውቀት ይመስላቸው ስለ ነበር የአካባቢው ሰዎች የግሪክን ፍልስፍና ጠንክረው ይማሩ ነበር:: ቅዱስ ቲቶም በወጣትነቱ ወደ ት/ቤት ገብቶ የግሪክን ፍልሥፍናና የዮናናውያንን ጥበበ ሥጋ ተማረ:: በጥቂት ጊዜም የሁሉ የበላይ ሆነ::

ቅዱሱ በወቅቱ ምንም እውነተኛውን ፈጣሪ አያምልክ እንጂ በጠባዩ እጅግ ቅንና ደግ ነበር:: ምክንያቱን ሳያውቀው ለእኔ ቢጤዎች ያበላ: ያጠጣ: ይንከባከባቸውም ነበር:: እግዚአብሔር ግን የዚህ ቅን ሰው በጐነቱ እንዲሁ እንዲቀር አልወደደምና አንድ ቀን በራዕይ ተገለጠለት::

በራዕይም አንድ ምንነቱን ያልተረዳው ነገር "ቲቶ ሆይ! ስለ ነፍስህ ድኅነት ተጋደል:: ይህ ዓለም ኃላፊ ነው::" ሲለው ሰማ:: ከእንቅልፉ ነቅቶ በእጅጉ ደነገጠ:: የሚያደርገውንም አጣ:: ያናገራቸው ሁሉ ምንም ሊገባቸው አልቻለም::

ለተወሰነ ጊዜም ለጉዳዩ ምላሽ ሳያገኝለት በልቡ እየተመላለሰ ኖረ:: ድንገት ግን በዚያ ሰሞን ከወደ ኢየሩሳሌም አዲስ ዜና ተሰማ:: "ክርስቶስ የሚሉት ኢየሱስ: እርሱም የባሕርይ አምላክ የሆነ ወደ ምድር ወርዶ: ስለ እግዚአብሔር መንግስትም እየሰበከ ነው::" ሲሉ ለቲቶ ነገሩት::

"ሌላስ ምን አያችሁ?" አላቸው:: "በእጆቹ ድውያን ይፈወሳሉ:: ሙታን ይነሳሉ:: እውራን ያያሉ:: ለምጻሞች ይነጻሉ:: ሌሎች ብዙ ተአምራትም እየተደረጉ ነው::" አሉት:: የወቅቱ የሃገረ አክራጥስ መኮንን ፈላስፋ ነበርና ስለ ክርስቶስ ሲሰማ ሊመራመር ወደደ::

እርሱ መሔድ ስላልተቻለው "ብልህ ጥበበኛ ሰው ፈልጉልኝ::" ብሎ ተከታዮችን ቢልካቸው ከቲቶ የተሻለ በአካባቢው አልነበረምና እርሱኑ አመጡት:: መኮንኑ ቲቶን "ነገሩ ትክክል ወይም ስሕተት መሆኑን በጥልቅ መርምረህ ምላሽ አምጣልኝ::" ብሎ ላከው::

ቅዱስ ቲቶም ፈጥኖ ተነስቶ ወደ ኢየሩሳሌም ገሰገሰ:: ወደ ከተማዋ እንደገባም ጌታችንን አፈላልጐ አገኘው::
1.ጌታችን ክርስቶስ በሥልጣነ ቃሉ ደዌያትን ሲያርቅ: አጋንንትን ሲያሳድዳቸው ተመልክቶ ይህ ሥራ የፍጡር እንዳልሆነ ተረዳ::
2.ጌታችን የሚያስተምረው ትምሕርት ከግሪክ ፍልሥፍና እጅግ ርቆና መጥቆ አገኘው:: የግሪክ ፍልሥፍና መነሻውም ሆነ መድረሻው ሥጋዊ ነው:: ጌታ ግን በጣዕመ ቃሉ የሚያስተምረው ሰማያዊ: በዚያ ላይ ዘላለማዊ የሆነ ትምሕርት ነው:: በራዕይ "ስለ ነፍስህ ተጋደል::" ያለው ምሥጢር አሁን ተተረጐመለት::

በዚህ ምክንያትም ጊዜ አላጠፋም:: ወዲያውኑ አምኖ ተከታዩ ሆነ:: ጌታም ከሰባ ሁለቱ አርድእት ደመረው:: የአክራጥስ መኮንን "ምነው ዘገየህ?" ቢለው ያየውን ሁሉ ጽፎ: እንደማይመለስም አክሎ ደብዳቤ ላከለት::

ከዚህ በኋላ ቅዱስ ቲቶ ከጌታችን እግር ለሦስት ዓመታት ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ: በመላው እስያ ለስምንት ዓመታት ወንጌልን ሰብኳል:: ቅዱስ ጳውሎስ ባመነ ጊዜ ደግሞ የእርሱ ደቀ መዝሙር ሆኖ ለሃያ አምስት ዓመታት አስተምሯል::

ቅዱስ ጳውሎስ ሰማዕት ከሆነ በኋላ ደግሞ ወደ አክራጥስ ተመልሶ: ሕዝቡን አሳምኖና አጥምቆ: ቤተ ክርስቲያንን አንጿል:: ዕድሜው በደረሰ ጊዜም መምሕራንን: ካህናትን ሹሞላቸው: ባርኳቸውም በዚህች ቀን ዐርፏል::

††† አምላከ ቅዱስ ቲቶ መልካሙን የሕይወት ምሥጢር ይግለጽልን:: ከሐዋርያውም በረከቱን ያድለን::

††† ጳጉሜን 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ቲቶ ሐዋርያ (ከሰባ ሁለቱ አርድእት)

††† ወርኀዊ በዓላት
(የለም)

††† "የእግዚአብሔር ባሪያና የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ. . . መድኃኒታችን እግዚአብሔር እንዳዘዘ: ለእኔ አደራ በተሰጠኝ ስብከት ቃሉን ገለጠ: በሃይማኖት ኅብረት እውነተኛ ለሚሆን ልጄ ቲቶ::
ከእግዚአብሔርም አብ: ከመድኃኒታችንም ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ምሕረት: ሰላምም ይሁን::" †††
(ቲቶ. ፩፥፩)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

ታኦዳኮስ

07 Sep, 14:27


༺ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ስያሜና ትርጓሜ ༻ ༒ ኦርቶዶክስ ( 𝙊𝙍𝙏𝙃𝙊𝘿𝙊𝙓 )
“ኦርቶዶክስ” የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን “ኦርቶ” እና “ዶክስ” ከሚሉት ኹለት ቃላት ነው፡፡ ትርጉማቸውም ኦርቶ ማለት ቀጥተኛ፣ ትክክለኛ ማለት ሲሆን፤ ዶክስ ማለት ደግሞ የተመሰገነች እምነት/ሃይማኖት ማለት ነው፡፡ በአንድነት ሲሆኑ ኦርቶዶክስ ማለት ቀጥተኛ፣ ትክክለኛ፣ የተመሰገነች እምነት/ሃይማኖት ማለት ነው፡፡ The word "𝗢𝗿𝘁𝗵𝗼𝗱𝗼𝘅" takes its meaning from the Greek words orthos ('right') and doxa ('belief'). Hence the word 𝗢𝗿𝘁𝗵𝗼𝗱𝗼𝘅 means correct belief or right thinking. (Orthodoxy (from Greek: ὀρθοδοξία, orthodoxía, 'righteous/correct opinion') is adherence to correct or accepted creeds, especially in religion). የእንግሊዝኛው "right" አንድም ትክክል አንድም ቀኝ ማለት ነው። የቀናች የሚለው ቀኝ ከሚለው ይወጣል።

ኦርቶዶክስ የሚለው ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ አገልግሎት ላይ የዋለው በ325 ዓ.ም በኒቅያ ጉባዔ ነው፡፡ በኒቅያ “ወልድ ፍጡር ነው” የሚለውን የአርዮስን የክህደት ትምህርት ለማውገዝና ሃይማኖታቸውን ለማፅናት የተሰበሰቡ ሃይማኖታቸው የቀና 318ቱ ሊቃውንት ይህን ቃል የተጠቀሙት ሐዋርያት ያስተማሯት ሃይማኖት ቀጥተኛና ትክክለኛ ናት ለማለት ነው፡፡ ሌሎች እንደ አርዮስ ክህደት ያሉት በየዘመኑ የሚነሱት ልዩ ልዩ አዳዲስ ትምህርቶች የምንፍቅና መሆናቸውን ለማረጋገጥ ይህችን ሃይማኖት ኦርቶዶክስ ብለዋታል፡፡

በዘመናችን የቋንቋ አጠቃቀምም ኦርቶዶክሳዊ መንገድ(𝗢𝗿𝘁𝗵𝗼𝗱𝗼𝘅) ማለት ቀጥተኛ (የተለመደ የታወቀ) የችግር አፈታት ሲሆን፤ ኢ-ኦርቶዶክሳዊ (unorthodox) ማለት ደግሞ ከተለመደው ከታወቀው ወጣ ያለ የችግር አፈታት ማለት ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ይህን ቃል አንዳንዶች ግትርነትን ወይም ለለውጥ ያልተዘጋጀ የሚለውን ለመግለፅም ሲጠቀሙበት ይታያል፡፡ ይህ ግን በሂደት የመጣ የትርጉም መዛባት ተደርጎ ሊወስድ ይችላል፡፡

༒ ተዋሕዶ (𝗠𝗶𝗮𝗽𝗵𝘆𝘀𝗶𝘁𝗲 )
ተዋሕዶ የሚለው ቃል ከልሣነ ግእዝ የመነጨ ቃል ነው፡፡ ትርጒሙም “አንድ ሆኑ” ማለት ነው። በዚህ ትርጉም ውስጥ አንድ የሆኑት መለኮታዊና ሰብዓዊ ባሕርይ (መለኮትና ትስብዕት) ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት የተዋሕዶ ትርጓሜ በአጭሩ “ወልድ ዋሕድ” የሚለው ነው፡፡ ክርስቶስ ሰው የሆነው ያለሚጠት (ያለ መመለስ)፣ ያለ ውላጤ (ያለ መለወጥ)፣ ያለ ቱሳሔ (ያለ መቀላቀል)፣ ያለ ትድምርት (ያለ መደመር)፣ ያለ ቡዓዴ (ያለ መለያየት)፣ ያለ ኅድረት (ያለ ማደር)፣ እንበለ ተጋውሮ(ያለ መጎራበት)፣ እንበለ ፍልጠት (ያለ መለያየት) ነው፡፡ ክርስቶስ ከኹለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ፣ ከኹለት አካል አንድ አካል የሆነው በተዋህዶ ነው፡፡ ስለዚህ ተዋሕዶ የሚለው ቃል ክርስቶስ ሰው የሆነበትን ምስጢር የሚገልፅ ታላቅ ቃል ነው፡፡ ክርስቶስ ሰው የሆነው በ ተ ዋ ሕ ዶ ነው!
( The word 𝙈𝙞𝙖𝙥𝙝𝙮𝙨𝙞𝙩𝙚 derives from the Ancient Greek μία (mía, "one") plus φύσις (phúsis, "nature, substance"). 𝙈𝙞𝙖𝙥𝙝𝙮𝙨𝙞𝙩𝙚 teaching is based on Cyril of Alexandria's (Saint Pope Kyrillos VI of Alexandra's coptic church) formula μία φύσις τοῦ θεοῦ λόγου σεσαρκωμένη, meaning "one physis of the Word of God made flesh" (or "... of God the Word made flesh").

༒ ቃል ሥጋ የሆነው፤ ያለ ቱሳሔ ነው፤
ቱሳሔ ማለት: ቅልቅል የተቀላቀለ ማለት ነው፤ ይኸውም እንደ ማር እና እንደ ውኃ እንደ ወተት እና እንደ ቡና ነው፤ ማር እና ውኃ ቢቀላቀሉ ስም ማዕከላዊ መልክ ማዕከላዊ ጣዕመ ማዕከላዊ ይገኝባቸዋል።

ስም ማዕከላዊ የሚባለው የዕለቱ ብርዝ የሰነበተው ጠጅ ይባላል እንጂ ከቀደሙት ስሞች በአንዱ ወኃ ወይም ማር ተብለው አይጠሩም።

መልክ ማዕከላዊ የሚባለው ብርዙ ወይም ጠጁ እንደ ማር አይነጣም ወይም እንደ ውኃ አይጠቁርም ማዕከላዊ መልክ ይይዛል።

ጣዕም ማዕከላዊ የሚባለው ደግሞ እንደ ማር ሳይከብድ እንደ ውኃም ሳይቀል መካከለኛ ጣዕም ይኖረዋል።

ወተት እና ቡናም ሲቀላቀሉ እንዲሁ ናቸው፤ እንደ ወተት ያልነጣ እንደ ቡናም ያልጠቆረ ማዕከላዊ መልክ ያመጣሉ፤ ጣዕማቸውም ከሁለቱም ወስዶ ማዕከላዊ ይሆናል፤ ስማቸውም በማዕከላዊ ስም «ማኪያቶ» ቢባል እንጂ በቀደመ ስም ቡና ወይም ወተት ተብለው አይጠሩም።

ቃል ሥጋ የሆነው እንዲህ አይደለም፤ እንዲህ ቢሆን ኖሮ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክም የሰው ልጅም ተብሎ አይጠራም ነበር፤ ነገር ግን ሰው ከሆነ በኋላ «የሰው ልጅ» ተብሎ ተጠርቷል። [ማቴ 16፥13]

ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደግሞ «የእግዚአብሔር ልጅ (የአብ ልጅ ወልድ) እንደመጣ እውነተኛም የሆነውን እግዚአብሔርን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደሰጠን እናውቃለን፤... እርሱም እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው» ብሎታል። [1ኛ ዮሐ 5፥20]

ይህንን በተመለከተ ቅዱስ ቄርሎስ «መለኮትና ትስብእት እርስ በርሳቸው ሳይቀላቀሉ መለየት በሌለበት ተዋሕዶ ፈጽመው አንድ ሆኑ» ብሏል። [ሃይማኖተ አበው 73፥30]

አምላክ ሰው የመሆን ምስጢር ውስጥ ሥጋ እና መለኮት ተቀላቅለው ያስገኙት ሦስተኛ አካል ወይም ባሕርይ የለም፡፡ ሥጋ ሥጋዊ ባሕርዩን ሳይለቅ መለኮትም መለኮታዊ ባሕርዩን ሳያጣ በመጠባበቅ አንድ ሆነዋል፡፡
ይቆየን...

ታኦዳኮስ

06 Sep, 09:15


✞ ንስሐችንን ማዘግየት

እያንዳንዱ የሕይወታችን ገጽታ በክርስቶስ ላይ ያለን እምነት ነጸብራቅ መሆን አለበት፣ ነገር ግን ይህንን እንደ እውነታ በመኖር ሙሉ በሙሉ እንወድቃለን። እራሳችንን እና ከሌሎች ጋር ያለንን ግንኙነት በቅርበት ለመመልከት እንቸገራለን። በራሳችን ውስጥ መለወጥ ከሚያስፈልገው ነገር ለመራቅ እየፈቀድን ሌሎችን በመፍረድ፣ በእነሱ ላይ ስህተት እየፈለግን በቀላሉ ወደ ወጥመድ ውስጥ እንገባለን።

በሌሎች ውድቀት ላይ በማተኮር የራሳችንን የንስሐ ቀን እናራዝማለን። ወደ ኋላ እየተጓዝን ነው። ደረጃ በደረጃ ከጌታ መንገድ እናፈገፍጋለን። እውነተኛ መንፈሳዊ እድገትን እናስወግዳለን፣ ከራሳችን ፈቃድ ጋር ተጣብቀን እና የራሳችንን ኢጎን ከፍ እናደርጋለን። ክብራችንን ለመጠበቅ አጥብቀን እየሞከርን ርስታችንን እንሰዋለን።

ክርስቶስን በአርአያችን አናከብርም ፍቅሩን እና ጽድቁንም በሕይወታችን አናንጸባርቅም። ራስን መመርመር በጣም አስቸጋሪው ተግባር ነው እና ግድየለሽነት እውነተኛ ጠላት ነው። ስለዚህ በምድረ በዳ እንደሚሄዱ ወደ ጌታችን እንዘረጋለን እና እንጮኻለን።

* እግዚአብሔር ሆይ ማረኝ

ታኦዳኮስ

06 Sep, 08:51


꧁༒꧂ ኃጢአት እንደሠራህ ይሰማሃል? ꧁༒꧂

ኃጢአት እንደሠራህ ካልተሰማህ እንዴት ንስሐ ትገባለህ?
ለራስህ ታማኝ ነህ?
ራስህን በትእዛዙ ላይ ትለካለህ?
ራስህን ከቅዱሳን ጋር ታወዳድራለህ?
በራስህ ውስጥ የእውነተኛ ክርስቲያን ባሕርያትን ታያለህ?
በራስህ ረክተሃል?
አሁን ያለህ ሕይወት ለመንግሥተ ሰማያት ብቁ አድርጎሃል?
መንፈሳዊ አባት አለህ?
የሚመራህ ሰው አለ?

አባ አሞጽ “የንስሐ ስድስት መንገዶች አሉ፡-
ኃጢአትን ማውገዝና መተው፣
በጸጸት መናዘዝ፣
የሌሎችን ኃጢአት ይቅር ማለት፣
በደለኞች ከመፍረድ መቆጠብ እና ልብን መያዝ” ብሏል።
"ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን እውነትም በእኛ ውስጥ የለም።" [1ኛ ዮሐንስ 1:8]

መልካም የጳጉሜን ወር ይሁንልን🥰

ታኦዳኮስ

06 Sep, 08:51


➽ በተጨማሪም ከዘላለማዊ ሕይወት ጋር በተገናኘ ከሚነሱ አስተምህሮዎች መካከል አንዱ የሆነውን እና ከዳግማዊ ምጽአቱ አስቀድሞ ክርስቶስ ከቅዱሳኑ ጋር ለአንድ ሺህ ዓመት በምድር ይነግሳል የሚለውን ‘የሺህ ዓመት-Millennialism’ አስተምህሮ ይዳስሳል።የአስተምህሮው መነሻ፣ ይህንን አስተምህሮ የሚቀበሉ አባቶች፣ ቅድመ ምጽአት ሺህ ዓመትና ድኅረ ምጽአት ሺህ ዓመት ምንድን ናቸው? እነ አባ ጊዮርጊስ ሳይቀር በድርሳኖቻቸው የሚያነሱት ምሳሐ ደብረ ጽዮንስ ምንድን ነው? የሚለውን ከገለጸ በሗላ በርግጥ በራእየ ዮሐንስ የተገለጸው ሺህ ዓመት የሚለው ትርጉም ምንድን ነው? የሚለውንና ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን የሺህ ዓመት አስተምህሮን ለምን እንደማትቀበለው በዝርዝር ይመልስልናል።

➽ ይህ ምዕራፍ በኢትዮጵያውያን ኅሊና ዘንድ ያለውንና በእያንዳንዱ መጥፎ ገጠመኝ ሳይቀር ‘አይ ስምንተኛው ሺህ’ የሚባልለትን ስምንተኛው ሺህን በትቂቱ ካነሳ በሗላ apokatastasis የሚባለውን ሁሉም ሰውና የወደቁ መላእክት ሳይቀሩ ከመጨረሻው ፍርድ በሗላ ድኅነት ያገኛሉ_ፍጥረት ሁሉ ከውድቀት በፊት ወደነበረበት ደረጃ ይመለሳል የሚለውን አስተምህሮ ምንነት፣መነሻና ኢ_ኦርቶዶክሳዊነት ገልጾልን ምዕራፉን ያጠናቅቃል።
➽ የመጽሐፉ የአምስቱ ምዕራፍ ማጠቃለያ በአንዲት ገጽ በአንዲት የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ተጠቃሏል።እንዲህ በሚል።
“...ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም::” (1ኛ ዮሐ 3፥2)

📋 በመጨረሻም መጽሐፉ “ነገረ ሞት በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርት “ በሚል በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ ‘ጉባኤ ደቂቀ አበው’ መርሐ ግብር ላይ በአዘጋጁ የቀረበ ጥሩ ጥናታዊና ትምህርታዊ ጽሑፍ አካቶ አቅርቧል።
—---------------------------------------------------------------------------
“ ክርስቶስ ሆይ በጌትነትና በምስጋና በመጣህ ጊዜ አገልጋዮችህ እኛን ተድላ ደስታ ወዳለበት ዐደባባይ ጥራን፤በአዲስ ልብስ አጊጠን ከአንተ ጋር በዚያ እንመላለስ ዘንድ፡፡” መልክአ ኢየሱስ
—-------------------------------------------------------------------------
እስመ ኵሉ እምኔሁ ወኵሉ በእንቲአሁ ወኵሉ ቦቱ ወሎቱ ሰብሃት ለዓለመ ዓለም አሜን:-ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።
÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷
ጳጉሜን 1፡ 2016 ዓመተ ምሕረት

ታኦዳኮስ

06 Sep, 08:51


➽ በሌላ በኩል ደግሞ አንዳንድ ጊዜ በዚህ ዓለም ስንኖር ስለሞት እያሰቡ መተከዝ፣ ማዘን፣ መጨነቅ በዚህ እንድንኖር የፈቀደልንን የደስታ ዓለም የፈጠረን አምላክ ማሳዘን አይሆንም ወይ? የሚል ሊኖር ይችል ይሆናል። ሞትን አላስብም ብሎ ሰው ራሱን ለማታለል ቢሞክር እንኳ ከሞትና ሞትን አስቦ አለመዘጋጀቱ ከሚያስከትለው ጥያቄና ፍርድ ነጻ መሆን አይችልም። በኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ተዘክሮተ ሞት ወይንም ሞትን ማሰብ መሠረታዊ ጉዳይ ነው።ለምን ያልን እንደሆነ ከኃጢአት እና ፈቃደ ሥጋው ከሚያመጣቸው ፍትወታት ጋር ለሚያደርገው ብርቱ ትግል የዘወትር ብርታቱ ስለሆነች ነው። ይወርሳት ዘንድ ያለችውን፣ተስፋም ለሚያደርጋት መንግስተ እግዚአብሔር ለመዘጋጀትና እሷንም ለማግኘት የሚሸጋገርባት ድልድዩ ስለሆነች ዘወትር ሞትን እናስበዋለን። ምዕራፍ አንድ ይህን እና የመሳሰሉ የነገረ ሞት ጉዳዮችን ካብራራልን በሗላ ሞት በአበው አስተምህሮ ምን እንደሚመስል በአጭሩ ዳስሶልን ምዕራፉን ይቋጫል።

➹ ማስታወሻ:-
[ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ስለሆኑት ስለሞትና ሕይወት በሰፊው ለመረዳት “ፍካሬ ሞት ወሕይወት” የሚለውን የመምህር ቃኘው ወልዴን መጽሐፍ መመልከቱ በእጅጉ ይጠቅማልና እንዲመለከቱት እንመክራለን ።]

🔸ምዕራፍ ሁለት🔸
➽ በኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ትምህርትና ሥርዓተ አምልኮ በስፋት ከሚሰበኩ ርዕሰ ጉዳዮች አንዱ የጌታችን ዳግም ለፍርድ የመምጣቱ ነገር ነው። ቅዳሴያችንና ጸሎቶቻችን ደጋግመው ያነሱታል። ቀዳማዊ ምጽአቱ በትሕትና ለአድኅኖተ ዓለም ሲሆን ለደቀመዛሙርቱ እንደነገራቸው ዳግም ምጽአቱ ግን በግርማ መለኮት ለፍርድና ይህችን ዓለም እንደ ድንኳን ጠቅልሎ ለማሳለፍ የሚመጣበት ነው።የዚህ መጽሐፍ ሁለተኛው ምዕራፍ ስለዳግም ምጽአት ያብራራልናል።

➽ ምዕራፉ ዳግም ምጽአት በክርስትና ውስጥ ያለውን ቦታ በመግለጽ ይጀምርና በመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ በብሉይም፣በሐዲስም የተገለጠበትን መንገድ በማተት የጌታ ዳግም መምጣት ምልክቶችን አንድ በአንድ ያብራራልናል።በዚህም ተደጋግሞ ስለሚነሳው ሐሳዊ መሲህ(ሐሰተኛው ክርስቶስ) ማንነትና ምንነት ይገልጽልናል።ቀጥሎም ስለመነጠቅ ምንነት እና በኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን እንዴት እንደሚታይና መነጠቅን ለምን እንደማንቀበለው ያቀርብልናል። ከዚያም ጌታችን አምላካችን እንዴት ይመጣል? ለሚለው የሚመለሱ በግርማ መለኮትና በክበበ ትስብእት የሚሉ ነገሮች ምንነታቸውን ያቀርብና የአበውን ትምህርት ስለዳግም ምጽአተ ክርስቶስና ዳግም ምጽአቱ በሥርዓተ አምልኮ በምን ሁኔታ እንደሚገለጥ ያቀርብልንንና ምዕራፉን ያጠናቅቃል።

🔸ምዕራፍ ሦስት🔸
➽ ሦሥተኛው ምዕራፍ ነገረ ትንሣኤ ሙታንን ይዳስሳል።የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ የሆነው የቅዳሴ ትርጓሜ መጽሐፍ ሕይወትን በተመለከተ ሲገልጽ ሦሥት አይነት ሕይወት አለ ይላል።እነዚህም ሕይወት መልአካዊ፣ሕይወት እንስሳዊና ሕይወት ሰብአዊ ናቸው ። ይህንን ሲያብራሩም ሕይወት እንስሳዊ ደመ ነፍሳዊ ሲሆን በተፈጥሮ ወይንም በልደት ይሰጣቸውና በሚሞቱበት ጊዜ ተነስቶባቸው(ተወስዶባቸው) በዚያው እንደተነሳ የሚቀር ሕይወት ነው ይላሉ። ሕይወት መልአካዊ በተፈጥሮ የሚሰጥ፣እንደተሰጠ የሚቀርና የማይነሳ ሕይወት ነው።ሕይወት ሰብአዊ በተፈጥሮ ይሰጠናል በሞት ይነሳል(ይወሰዳል)፣በትንሣኤ ዘጉባኤ የሚመለስ ሕይወት ነው።በክርስትና እምነት ሰው ከሞተ ከፈረሰና ከበሰበሰ በሗላ አካሉ ከነፍሱ ጋር በመዋሐድ ይነሳል ብለን እናምናለን። ስለዚህም ምዕራፉ ትንሣኤ ዘጉባኤ ጊዜ የሚፈርስ የሚበሰብስ ሥጋችን በኃይለ እግዚአብሔር እንዴት እንደሚነሳ ይገልጻል።

➽ ምዕራፉ ለሰው ልጆች ሁሉ ትንሣኤና የክርስትና ማዕከል የሆነውን የጌታችንን ትንሣኤ ልዩ መሆን፣በኩረ ትንሣኤ መሆን፣ጌታ ከሙታን ለመነሳቱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎችን እንዲሁም ስለሙታን ትንሣኤ የጌታችን ትምህርት ምን እንደሚመስል ከገለጠልን በሗላ ትምህርተ ትንሣኤ ሙታን በሁለቱ ኪዳናት እግዚአብሔር እንዴት እንደገለጠልን ያብራራል።ከዚያም ነገረ ትንሣኤን ማለትም ትንሣኤ ልቡናን፣ ትንሣኤ ነፍስን፣፣ትንሣኤ ዘጉባኤን ፣ በትንሣኤ ዘጉባኤ አካላዊ ትንሣኤ እንዴት እንደሚነሳ፣ ሥጋ ወይም አካል የእግዚአብሔርን መንግስት አይወርስም ስለሚሉ ሰዎች፣የሰው አካል ከትንሣኤ በሗላ ምን ይመስላል? የሚለውን ካብራራልን በሗላ ነገረ ትንሣኤ ሙታን በቀደሙት የቤተክርስቲያን አበው እንዴት እንደተብራራ በመጠኑ ገልጾልን ምዕራፉን ይደመድማል።

🔸ምዕራፍ አራት🔸
➽ አራተኛው ምዕራፍ በጎቹና ፍየሎቹ፣ስንዴዎቹና እንክርዳዶቹ ስለሚለዩበት ስለመጨረሳው ፍርድ ያብራራል።የቤተክርስቲያን የነገረ ሃይማኖት ምንጭ እና እስትንፋሰ አምላካውያት በሆኑት በዐሥራው ቅዱሳት መጻሕፍት(ብሉይ ኪዳንና ሐዲስ ኪዳን) ስለዘላለማዊ ፍርድ እግዚአብሔር በአፈ ቅዱሳን በኩል ምን ብሎ ነገረን፣ ከመጨረሻው ፍርድ ጋር በተገናኘ የተነሳው የፎጢኖስ ክህደት፣ ጊዜያዊ ፍርድ(partial Judgment) ስለሚባለው ነገር፣ በመጨረሻው ፍርድ የሚፈረድባቸው እነማን ናቸው?እና የመጨረሻው ፍርድን ተገቢነት ፣ የሚፈርደው ማነው? ፍርድስ የሚተላለፈው በማን ላይ ነው? እነዚህንና የመሳሰሉትን ያብራራልናል።

➽ ምዕራፉ በተጨማሪም ከፍርድ በሗላ ስለሚኖሩ ሁኔታዎች ለምሳሌ ገነት፣ሲኦል፣ መንግስተ ሰማይ፣ገሃነም ስለመሳሰሉት እነዚህን በተመለከተ የቤተክርስቲያን ትምህርት፣ የሊቃውንት ልዩ ልዩ አመለካከቶች እና የሚነሱ ክርክሮችን ይዳስሳል።ለምሳሌ ገነትና ሲኦል የተለዩ መካናት ናቸው? ወይስ ሁኔታዎች ናቸው? መካነ ኃጥአን የሚባል አለ? የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮችን ይዳስስልናል። ሲኦልስ የተለየ የስቃይ ቦታ ነው ወይስ ሌላ ከእግዚአብሔርና ከፍቅሩ ውጭ መሆን? ነው ወይስ ሌላ? ገሃነምስ? የዘላለም የስቃይ ቦታ ወይስ ሌላ? እሳቱ የማይጠፋ ትሉ የማያንቀላፋ የሚለውስ ምንድን ነው? ወዘተ በእነዚህ ርዕሶች የተለያዩ ሊቃውንትን አተያይ ያቀርብልናል። በመጨረሻም መንጽሔ እሳት(Purgatory) የሚለው በካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ያለውና ሙሉ በሙሉ ንጹሕ ሳይሆኑ ወይንም ለሰሩት ጥቃቅን ኃጢአቶች ሥርየት ሳያገኙ የሞቱ ሰዎች ከኃጢአታቸው ነጻ የሚሆኑበት ስፍራ አለ የሚለው አስተምህሯቸው ምንድን ነው? ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንስ ትምህርቱን የማትቀበልባቸው ምክንያቶች ምንድን ናቸው? የሚለውን አቅርቦልን የአበው አስተምህሮ ስለመጪረሻው ፍርድ ምን ብለው እንዳስተማሩ መጠነኛ ዳሰሳ አቅርቦልን ምዕራፉ ይጠናቀቃል።

🔸ምዕራፍ አምስት🔸
➽ የመጨረሻውና አምስተኛው ምዕራፍ ኅልፈተ ዓለምና ዘላለማዊ መንግስትን ይዳስሳል።የዓለም ኅልፈት የማያሳስበውና ሰው ያለ አይመስልም።ጉዳዩ ደቀመዛሙርቱንም አሳስቧቸው የዓለም ፍጻሜ መቼ ይሆናል? ሲሉ ክርስቶስን ጠይቀውታል። ለመሆኑ የዓለም ፍጻሜ መቼ ይሆናል? ዓለምስ እንዴት ነው የምታልፈው? ከዓለም ኅልፈት በሗላ የምንወርሰው ‘አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር’ የተባሉትስ ምንድን ናቸው? አዲስ ሰማይ ምንድን ነው? አዲስ ምድር ሲባልስ ምንድን ነው? አዲስ ያሰኘው ምኑ ነው? የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮችን በአጭሩ ያብራራልናል።

ታኦዳኮስ

06 Sep, 08:51


🗒 የመጽሐፍ ጥቆማ 🗒
➾ የመጽሐፉ ርዕስ:- ኅልቀተ ዓለም: የኦርቶዶክሳዊ ነገረ ፍጻሜ ዘመን አስተምህሮ
➾ የመጽሐፉ አዘጋጅ፦ ቀሲስ አሉላ ለማ
➾ የመጽሐፉ ይዘት:-ኦርቶዶክሳዊ ነገረ ሃይማኖት
➾ የመጽሐፉ የገጽ ብዛት:- 235
➾ የመጽሐፉ የምዕራፍ ብዛት:- አምስት
➾ የህትመትዓመት:-፩ኛ ዕትም 2009 ዓ.ም፥፪ኛ ዕትም 2016 ዓ.ም
➾ የተጠቀማቸው ዋቢ ድርሳናት ብዛት፦ 49
➾የመጽሐፉ የሽፋን ዋጋ፦ 400 ETB

📗 መግቢያ 📗

➽ በኢትዮጰያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዐቢይ ጾም እኩሌታ(ደብረ ዘይት)፣በመጋቢት 29 ፡ እና በወርኃ ጳጉሜጊዜያት በተለየ ሁኔታ በቤተክርስቲያን ጸሎታት ፣ ምንባባት ፣ ዝማሬ፣ ቅዳሴና ሥርዓተ አምልኮ ሚዘከር ፣የሚመሰጠር ፣የሚተረጎምና የሚዜም ርዕሰ ጉዳይ ነው ነገረ ኅልቀተ ዓለም (Eschatology)። የዚህ ሳምንት የመጽሐፍ ጥቆማየም ወቅቱ እርሱም ወርኃ ጳጉሜ በቤተክርስቲያናችን ሥርዓተ አምልኮና አገልግሎቶች አንዱ የዓለም ፍጻሜና የክርስቶስ ዳግም ምጽዓት የሚወሳበትና የሚዘከርበት ወቅት ስለሆነ ከወቅቱ ጋር የተስማማ መጽሐፍ ለመጠቆም ወደድሁ።

➽ የትምህርተ ሃይማኖታችን አንዱ ክፍል ነው። በነገረ መለኮት ትምህርት ነገረ ኅልፈተ ዓለምና ተያያዥ ጉዳዮችን የምንማርበት አንዱ የነገረ ሃይማኖት ዘርፍ ነው Eschatology:: በቤተክርስቲያናችን አእማደ ምሥጢራት ተብለው ከሚጠቀሱትም አንዱ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ይህንን ርዕሰ ጉዳይ ይዳስሳል።በርግጥም በሰው አእምሮ ከመረዳት በላይ የሆነ የነገረ ሃይማኖት ትምህርት ስለሆነ ምሥጢር መባል የተገባው ነው። አንድ ክርስቲያን ዘወትር በሚጸልየው ጸሎተ ሃይማኖት በተባለው የሃይማኖት መግለጫም <<....ዳግመ ይመጽዕ በስብሐት ይኵንን ሕያዋነ ወሙታነ ወአልቦ ማኅለቅት ለመንግስቱ….ወንሴፎ ትንሣኤ ሙታን ሕይወተ ዘይመጽዕ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም >> ብለን የምናምነውን እንጸልያለን። የምንጸልየውንም እናምነዋለን።የሥርዓተ አምልኳችን ማዕከል የሆነው ቅዳሴያችን ደጋግሞ ያነሳሳዋል።

➽ በክርስቲያኖች ሕይወትና በአጠቃላይ በኦርቶዶክሳዊ ክርስትያኖች ሕይወት ትልቅ ትርጉም ያለው ነው ፍጻሜ ዓለምንና ፍጻሜ ዓለምን የተመለከተው ጉዳይ። ገና ወደፊት የሚፈጸም ምሥጢር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለብዙ ግላዊ አስተያየት (Speculations) የተጋለጠም ይመስላል። ሐሳውያን ነቢያትና ባሕታውያን ለሚፈልጉት ነገር(ቢዝነስም ይሁን ለሌላ) ምዕመኑን ከሚያስፈራሩበትና ከሚስቡበት ርዕሰ ጉዳይ አንዱ ነው። በእኛ ማኅበረሰብ ዘንድ ደግሞ ነገሩ ትንሽ ለየት ባለ መልኩ እንደ ስምንተኛው ሺ የመሳሰሉ ሀቲቶች የማኅበረሰቡ ንግርቶች ተደጋግመው ይጠቀሳሉ። .በሌላ መልኩ እንደ ሺ ዓመት መንግስት ፣ መነጠቅ፣ ምሳሐ ደብረ ጽዮን፣ Universal Salvation የመሳሰሉ የሊቃውንት አተያዮችና ሀሳቦችም የሚነሱበትና ከኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ አንጻር የሚታዩበት ክፍለ ትምህርትም ነው።

➽ ከዚህ ሁሉ አንጻር አንድ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን በቅዱሳት መጻሕፍት የተገለጠውንና በቅዱሳን አበው በመንፈስ ቅዱስ አብርኆት የተብራራውን እውነተኛውን ትርጓሜ መረዳትና ማወቅ የተገባና ራስንም ሌሎችንም ለመጠበቅና ለማዳን በእጅጉ ይጠቅማል። ይህ ኅልቀተ ዓለም የተሰኘው መጽሐፍም ነገረ ኅልቀተ ዓለምን በተመለከተ የሚነሱ ሀሳቦችን፣ አስተያየቶችን፣ ጥያቄዎችን ከኦርቶዶክሳዊ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ አንጻር ለማብራራት የሚሞክር መጽሐፍ ነውና ሊነበብ የሚገባው ነውና እንዲነበብ እንመክራለን። ጸሐፊውም ይህንን መጽሐፍ ስላበረከቱልን እናመሰግናቸዋለን::
➹ ማስታወሻ:- [ነገረ ኅልቀተ ዓለምንና ነገረ ምጽዓትን በተመለከተ ተጨማሪ ሰፊ ግንዛቤ ለማግኘት <ምጽዓተ ክርስቶስ> የተሰኘውን የመምህር ሣሙኤል ፈቃዱን መጽሐፍ መመልከት እጅግ ጠቃሚ ነው]።

📗 የመጽሐፉ ዓላማና አስፈላጊነት 📗
➽ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ሞትን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊ አረዳድ እንዲኖረን ያስችላል።
➽ ኅልቀተ ዓለምን በተመለከተ የኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን ትምህርት ያስተዋውቃል።
➽ በአንዳንድ ርዕሰ ጉዳዮች ሊቃውንት የተለያየ አመለካከት ስላላቸው ቤተክርስቲያን የምትቀበላቸውን አስተምሮዎች ለማሳወቅና የብሔራዊ ሊቃውንትንም አመለካከት በተወሰነ መልኩ ለማየት ይጠቅማል።
➽ በዚህ ሩጫና መባከን በበዛበት ፣ ትኩረት በሚያሳጣ ዓለም ስለዘለዓለማዊ ሕይወት በማሰብ መንፈሳዊ ሕይወታችንን ለማስተካከል ይረዳል።
➽ ቤተክርስቲያን የምታስተምረውን ትክክለኛውን የነገረ ኅልቀተ ዓለም ትምህርት በመረዳት ሰውነትንና ሕይወትን ለወዲያው ዓለም ድልው አድርጎ ለመኖር ይጠቅማል።

📗 የምዕራፋቱ መሠረታዊ ጭብጥ 📗

🔸ምዕራፍ አንድ🔸
➽ ውሎ ውሎ ከቤት ኑሮ ኑሮ ከሞት እንላለን በብሒላችን። ዘወትር እንደጥላ ይከተለናል።ለሰው ልጅ የማይቀር እጣ ፋንታና ሰውን አንድ የሚያደርግ እውነታ ነው። ለሺዎች ዓመታት የሕይወት አንድ እውነታ ቢሆንም ሰው አሁንም መቀበል የሚከብደው እውነታ ቢኖር ሞት ይሉትን ኃይል ነው። “ሁሉም ሰው እንደሚሞት ያውቀዋል፣ ነገር ግን ይህን እውነት አይቀበለውም።” እንዲል ሞሬ ስካዋርትዝ። ለመሆኑ ሞት ምንድን ነው? ሞትን መቀበል ለምን ያቅተናል? በተለይ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች እንዴት ነው መረዳት ያለብን? ስንት ዓይነት ሞት አለ? ሞት ራሱን የቻለ ሕልውና ያለው አካል ነውን? ወይስ ሌላ? ሞትን ማን እና ምን አመጣው? ለሞት ተጠያቂው ማነው? ሞት የሕይወትን ትርጉም እንዴትና እስከምን ይወስናል? ሞትስ ለምን እንፈራለን? መጽሐፍ ቅዱስስ ስለሞት ምን ይላል? ሞትና ነጻ ፈቃድ ምን አይነት ግንኙነት አላቸው? ነፍስ ከሥጋ ከተለየች በሗላ ምን ትሆናለች? የራሷ ሕልውና ይኖራታል? ወይስ እንዴት ትኖራለች? ለሞቱ ክርስቲያኖች ጸሎተ ፍትሐት ለምን ይደረጋል? ከሞት በሗላ ያለው ሕይወትስ ምን ይመስላል? የዚህ መጽሐፍ የመጀመሪያው ምዕራፍ ይህንን በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ እጅግ ትልቅ ቦታ የሚሰጠውን ነገረ ሞትን በማነሳሳት እነዚህንና ሌሎች ጥያቄዎችን ይመልሳል።

➽ ብዙ ጊዜ በተግባር የምናየው የክርስቲያኖች የሞት አረዳድ የተንሸዋረረ እና ከሌሎች በክርስትና ተስፋ ከማይኖሩ እንኳ የከፋ ሆኖ ይታያል። ወዲህ የሕይወት መደምደሚያ፣መፈጸሚያ፣ማለቂያ አድርጎ ከሞት በሗላ ሕይወት የሌለ የሚያስመስል አረዳዳድ እናስተውላለን። ሰው ሲሞትብንም ሀዘናችን መራር ይሆንና እግዚአብሔር ጋር እስከ መጣላትና እሱ ላይ እስከማጉረምረም እንደርሳለን። አንድ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ሞትን እንዴት ነው ሊረዳው የሚገባው? የሚለው ጉዳይ መሠረታዊ ነገር ነው።ሞትና ኃይሉ በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተሻረ እና በክርስቶስ ሞትም መቃብር ለዘለዓለም ሕይወት የምንወለድበት ማኅፀን ወደ መሆን ትርጉሙ ቢቀየርም አሁንም ሞት ላይ ያለን ተግባራዊ መረዳታችን ከዚህ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤ የተዛነፈ መሆኑ ያሳስባል።ቅዱስ አትናቴዎስ በሐዲስ ኪዳን ሞት ጥፍሩና ጥርሱ እንደወላለቀና ኃይሉን እንዳጣ አንበሳ ነው የሚለንም ለዚህ ነው።ሰማዕታት ለሽልማት በቀይ ምንጣፍ የተጠሩ ይመስል ለሞት የተሽቀዳደሙትና የሚፋጠኑት የሞትን ኦርቶዶክሳዊ አረዳድ ገንዘብ ስላደረጉ ነው። ይህ ምዕራፍ የሞትን ምንነት በኦርቶዶክሳዊ ቅኝት ለመረዳት ከሞት ጋር ተያያዥ የሆነ ርዕሶችን ይዳስስልናል።