Mohammedamin Kassaw @mohammadamminkassaw Channel on Telegram

Mohammedamin Kassaw

@mohammadamminkassaw


📌 ከእስልምናና ሙስሊሞች ጋር የተያያዙ ጠቃሚ መረጃዎችን አጋራለሁ::

📌 ለማህበረሰባችን ለውጥ የሚውሉ እይታዎችን አንፀባርቃለሁ::

አስተያየታችሁን @MOHAMMADAMMINM ያድርሱ:: ቻናሉን ለሌሎች በማጋራት ተደራሽ ያድርጉ:: ጀዛኩሙላሁ ኸይረን!

Mohammedamin Kassaw (Amharic)

ሞሃሜዳምን ካሳው ቡኮ አዲሱ ቦታ ነው ከእስልምናና ሙስሊሞች ጋር የተያያዙ ጠቃሚ መረጃዎችን እና ለማህበረሰባችን ለውጥ የሚውሉ እይታዎችን በቀላሉ አድርገናል። የዚህ ቦታ በሞሃሜዳምን ካሳው ላይ ከከፈለው ጥሩ በሽታ የሚገኝ ቢሆን ይመረጣል። እሱም በ@MOHAMMADAMMINM በመካከል ይዘቱን ለሌላው ቡክ በመተግበር የተገኘውን የእውነት ይመሰለናል። እሱ በግንቡ ይህንን በሆነ እና በሆነ ቻናሉ ተመዝግበዋል። ነገር ግን የሚፈልጉ ሰዎች የጀዛኩሙላህ እራሱን ለማዳን እና እንደገና እንዲገደብ ይጋራሉ።

Mohammedamin Kassaw

05 Feb, 06:30


ትራምፕ "አሜሪካ ጋዛን ታስተዳድር!" የሚልን እብደትም ቀልድም የቀላቀለን ንግግር ከደም ወንድሙ ኔትያናሁ ጋር ሆኖ ትላንት ተናግሯል::

የዚህ ሰው እብሪታዊ አካሄድ በቱርክ ሳዑዲ እና ጆርዳን ተቃውሞ ገጥሞታል:: አላህ የመጥፊያውን መንገድ ያመቻችለት!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

04 Feb, 15:44


የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናን (Exit Exam) በመጪው አርብ በጁምዓ ሰዓት ማለትም ከ5:30-8:00 ለመስጠት ያወጣውን ፕሮግራም እንዲቀይር ጠየቀ!

•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ጥር 27 / 2017 ዓ.ል
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

ህብረቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ባስገባው ደብዳቤ ጁምዓ የሙስሊሞች ሳምንታዊ በዓል መሆኑንና ከ5:30-7:30 በሀገር ደረጃ የመንግስት መስሪያ ቤቶች እረፍት መሆናቸውን ጠቅሶ በዚህ ሰዓት የፈተና ፕሮግራም ማውጣት የሙስሊም ተማሪዎችን እሴቶችን እና መብቶችን መጋፋት እንደሆነ ገልፇል:: መሠል ጥፋቶች መደጋገማቸው ሙስሊሙን ተማሪ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያራርቁ በመሆናቸውም ተመሳሳይ ችግሮች በዘላቂነት እንዳይፈጠሩ መስመር እንዲደረገም ጠይቋል::

የደብዳቤው ግልባጭ ለፌደራል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ገብቷል::

©️ EHEMSU

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

04 Feb, 10:46


ለታሪካዊው የAASTU ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ ••• ነጃሺ መስጂድ እንረባረብ!

ዩኒቨርሲቲው ሙስሊሞች አናሳ በሆኑበት አቃቂ ክ/ከተማ በ2004 ዓ.ል ተመሠረተ:: ተማሪዎች በዙሪያ መስጂድ ስላልነበረ በደረሱበት ለመስገድ ጥረት ሲያደርጉ በፌደራል ፖሊስ እየተከለከሉ ግብግብ እየገጠሙ ይሰግዱ ያዙ:: በ2007 ዓ.ል ለመስጂድ ቦታ ይሰጣቸው ዘንድ እስከ ፌደሬሽን ም/ቤት ድረስ ቢሄዱም ሳይሳካ ቀረ:: ከ2008-2010 ዓ.ል ኪራይ ሳይከፍሉ እንዲሰግዱበት ከአንድ አህለል ኸይር በተሰጣቸው ቦታ ይሰግዱና ጀመዓቸውን ያጠናክሩ ያዙ::

በ2010 ዓ.ል የአዲስ አበባ ከተማ ለእምነት ተቋማት ቦታ ለመስጠት መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ የ7000 ሰው ፊርማና የ700 ሰው መታዎቂያ አሰባስበው ለመስጂድ ቦታ ጠየቁ:: ከሁለት አመት ትግል እና ሙከራም 1.249 ሚልዬን ብር ካሳ ከፍለው 3500 ካሬ መሬት ተቀበሉ:: ከተቀበሉም ቡሀላ የአካባቢው ገበሬዎች አናሳጥርም መስጂድ አናሰራም ማለታቸውን ተከትሎ በ30 ፖሊስ ታጅበው በአንድ ቀን ውስጥ አጥረው ጨረሱ:: ገበሬዎቹ ወደ ክስ ቢያመሩም እስከ ሰበር ሰሚ ችሎት ሄደው መስጂዳቸውን አስከበሩ::

ይህ በሙስሊም ተማሪዎች ትግል ለተማሪውና ለማህበረሰቡ የቆመ ብቸኛ መስጂድ አሁን ላይ እገዛችንን ይሻል:: በረንዳ ሰርተው ወለሉን በሲሚንቶ ለመሙላት ጀምረዋል:: ምንጣፍ የለውም:: ከመስጂዱ ውጭ ለማህበረሰቡ እና ለተማሪው የሚያሰማ ድምፅ ማጉያ የለም:: እንደ አጠቃላይ ሙሉ ለሙሉ የተሟላ አገልግሎት ይሰጥ ዘንድ የሁሉም ማህበረሰብ እገዛ ይሻል::

ሁላችሁም የምትችሉትን ALNEJASHI MESJID AND MEDRESA (1000630254427 --- CBE /
0037207820101--- ZAMZAM BANK / 161299456 --- BANK OF ABYSSINIA /
014381320629000 --- AWASH BANK) በማስገባት ታሪካዊውን መስጂድ በመገንባት አስተዋፅዖ አድርጉ:: የምትልኩ Screenshot አድርጋችሁ @MOHAMMADAMMINM ላኩልኝ:: በአካባቢያችሁ ኩፖን መሸጥ የምትችሉ / መስጂድ ላይ ማሠባሰብ የምትችሉም Inbox ላይ አውሩኝ:: በቻልነው አቅም ተረባርበን የአጀሩም የታሪኩም ተካፋይ እንሁን::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

04 Feb, 09:35


3ቱ የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ባለፈው ጥምቀት በታቦት ላይ የተሳለቁ መሆናቸውን ተከትሎ የአምቦ ከተማ ፍ/ቤት ትላንት በዋለው ችሎት የ4 ወር እስር ፈርዶባቸዋል::

•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ይህ እንዲሳካ የቤተክህነቷ ቁርጠኝነትና የሐይማኖት ተቋማት ጉባዔ የተቀላጠፈ እንቅስቃሴ የሚደነቅ ነው::
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

ሆኖም ግን በመጪው አርብ በጁምዓ ሰዓት Exit Exam ሊፈትን ውጥን የያዘውን ት/ሚኒስቴር ማንም አካል አድብ እያለው አይደለም:: በተለያዩ ቦታዎች ከመሳለቅ ባሻገር ግልፅ የሆኑ የሰብዓዊ እና የሐይማኖታዊ መብት ጥሰቶችን በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየፈፀሙ ያሉ አካላት ምንም አይነት እርምጃ ሲወስድባቸው እያየን አይደለም:: ለምን? ከሌሎች መማር ካለፈው መማር ማሰብ ማስተዋል መስራት ያስፈልጋል::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

04 Feb, 07:17


እለታዊ ማስታዎሻ - 347

"وَلْيَعْفُوا وَلْيَصْفَحُوا ۗ أَلَا تُحِبُّونَ أَن يَغْفِرَ اللَّهُ لَكُمْ ۗ وَاللَّهُ غَفُورٌ رَّحِيمٌ

ይቅርታም ያድርጉ፡፡ (ጥፋተኞቹን) ይለፉም፡፡ አላህ ለእናንተ ሊምር አትወዱምን? አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡" [24:22]

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 20:05


ሴኩላር የሆነው ንግድ ባንክ "ሐጀን መብሩር!" የሚል ሚሴጅ ልኮልኛል:: በሌላ አቅጣጫ ደግሞ ሴኩላር የሆነው ትምህርት ሚኒስቴር ከጁምዓ ሶላት የEXIT ተፈታኞችን የሚያፈናቅል ፕሮግራም አውጥቷል:: እና ምን ተሻለ? ያው ሴኩላሪዝምን እንደ ንግድ ባንክ እስኪረዳ ድረስ መታገል ነዋ:: ባንኩ ገንዘብ እና አማራጭ ባይኖርህ አይፈልግህም ነበር:: ትምህርቱም እስኪፈልግህ ድረስ ተማር ••• ታገል ••• ስራ!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 18:59


ታክሲ ውስጥ ከሹፌር አልፎ ትራፊክ ፖሊስ ከሚሰማበት ሬንጅ እየጮሃችሁ ፖለቲካዊ ቤተሰባዊ ጓደኛዊ ፍቅራዊ ወሬዎችን የምታወሩ ሰዎች ግን ••• አድቡ ••• ወይንም ከማውራታችሁ በፊት ራሳችሁን አዳምጡ ••• አንዳንድ የሚወጡ ቃላት ደግሞ የሚያሳቅቁ አይነት ናቸውና ጠንቀቅ በሉ ••• ህዝብ ይታዘባል ••• ይፈርዳል ••• ይሳቀቃል ••• ጆሮውን ይታመማል ••• ይታዘባል:: ታክሲ ደግሞ በራሷ "የትም ብትሆን አላህን ፍራ!" የሚል ጥቅስ ከፊት ለፊት ትለጥፋለችና አላህን እንፍራ ••• ታክሲም ውስጥ ብንሆን ••• አደብ ያሻል::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 18:45


BTW "ከእርሷ ጋር ትዳር መስርቼ አንድ ቀንም ቢሆን ከኖርኩ ብሞት እንኳ አይቆጨኝም!" ያለው ልጅ ከእርሷ ውጭ አግብቶ መኖር ከጀመረ አንድ አመት አልፎታል:: ከእርሱ ጋር በትዳር 1 ቀን እንኳ ከኖርኩ ዱንያ ቢበቃኝም አልፀፀትም!" ያለችው ልጅም ከእርሱ ውጭ አግብታ መኖር ከጀመረች አንድ አመት አልፏታል::

ነሲባችን ከየትኛው ጋር እንደሚገጥም አይታወቅም:: የአላህን ቀደር እየወደዱ መሶበር ብቻ ነው የሚያወጣው:: 18ን በ1 እና በ2 ያለፋችሁ ሶብሩ:: አለም ሰፊ ነች ••• ህይዎትም እንደዚያው::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 17:08


"የእስልምና መልዕክት እንዲሰራጭ እንዲስፋፋ ለሌሎች እንዲዳረስ እርስዎ ምን አበርክተዋል?" የሚልን ርዕስ ከአንድ በራሪ ወረቀት ላይ አነበብኩ:: እስቲ ራሳችንን እንጠይቅ ••• ምን አበርክተናል? በእኛ ሰበብ ስንት ሰው እስልምናን ተቀበለ? በእኛ ሰበብ ስንት ሰው ወደ እስልምና ተሳበ? በእኛ ሰበብ ስንት ሰው ወደ ተውሒድ መጣ? በእኛ ሰበብ ስንት ሰው ከሽርክ ራቀ? በእኛ ሰበብ ስንት ሰው ስነ- ምግባሩ ተቀና? ወይንስ እያበላሸን ነው?

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 15:33


አሁን አይደል እንዴ የሚገባኝ! የሆነች ሱቅ የእለቱ የወርቅ ዋጋ ብላ በግራም ከፋፍላ ዋጋውን አስቀምጣለች:: እኔ ሞኙ እንዴት ወርቅ እዚህ ሸጥ ውስጥ ይሸጣል? እንዴትስ በዚህ ልክ ረከሰ? ወይንስ ምንድን ነው?" እያልኩ እብሰለሰልላችሗለሁ:: ለካስ ወርቅ ብለው የጠሩት ጫትን ነው:: ሳልገዛ አትሉም¡ ከባድ ነው ብቻ! ጫትን ወርቁ አድርጎ የሚኖር ትውልድ ••• ያሳዝናል ብቻ! ሰው ግን እንዴት ከፍሎ ይደነዝዛል?

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 11:43


አህመድ አሸርዕ ሶሪያን ወደቀድሞው ገናናነቷ ለመመለስ መንገድ የጀመረ ይመስላል:: የበሻርን የግፍ አገዛዝ መንግሎ ከጣለ ቡሃላ ሀገሩን ሰላማዊ ለማድረግ ብሎም የተሰበረውን ለመጠገን የጎደለውን ለመሙላት ከተለያዩ ሀገራት መሪዎች ጋር ውይይት እያደረገ ነው:: ሳዑዲ ሄዶ ከቢን ሰልማን ጋር ከተወያየ ቡሃላም ለዑምራ ወደ መካ አቅንቷል::

አላህ ይወደደው ••• መሠል ወንዶችን ያብዛልን!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 11:16


በቅድመ 1966 ዓ.ል የነበሩ አባቶቻችን ስለ ጁምዓ ቀን የነበራቸው ጥያቄ ከስራ ውጭ እንዲሆን አልያም ከ5:30 - 9:00 ክፍት እንዲሆን ነበር:: የዚያኔ ባይሳካም ጥረታቸው ፍሬ አፍርቶ በ1985 ዓ.ል በሽግግር መንግስቱ ከ5:30 - 7:30 ከስራ ውጭ ይሁን የሚል ተወሰነ:: ሆኖም ግን በሕግ ፀና የተባለውን መብት ከ32 አመታት ቡሃላ ጥሶ ት/ሚኒስቴር በጁምዓው ቀን ከ5:30-8:00 ሰዓት ፈተና ካልፈተንኩ እያለ ነው::

ይህ ትውልድ መሠል ጥፋቶችን ችላ ብሎ የሚያልፍ ከሆነ በአባቶቹ ትግል ላይ አፈር ከመነስነሱም ባሻገር ሀላፊነቱን በራሱ እጅ መቅበርም ነው:: በቃ ሊባል ይገባል:: በቃን እስኪሉ ድረስ!

©️ EHEMSU

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 09:15


እንዲህ ተጨንቀው ስልክ ይዘው ለመግባት ከሚታትሩ እንዲሁ ተጨንቀው ቢያነቡ የተሻለ አያመጡም? ዛሬ ለExit ስልክ ይዘው ሲገቡ የተያዙ ናቸው አሉ:: አስተግፊሩላህ!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 06:55


159 የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሒጃባቸው ምክንያት ከትምህርት ውጪ ከተደረጉ 3 ወራት አለፉ።  እስላም ጠሎቹ የአክሱም ከተማ  ትምህርት ቢሮ ኋላፊዎች እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኋላፊዎች 159 ሴቶች ከትምህርት ውጪ ሲደረጉ የትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ የሴቶች እና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እስካሁን ምንም አላሉም። በዚህም ምክንያት ትምህርት ቤቶቹ ትክክል እንደሆኑ እንዲሰማቸው ወይም ማንም ተጠያቂ እንደማያደርጋቸው እንዲሰማቸው አድርጓል። ለዚህም ሁለቱ የፌደራል ተቋማት ተጠያቂዎች ናቸው። የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደርም በቃሉ አልተገኘም። የነደብረፅን ቡድንም ጉዳዩ የፖለቲካ መጠቀሚያ አድርጎታል። የፌደራሉ መጅሊስም እነዚህን ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸውን ለመመለስ ደብዳቤ ከመፃፍ የዘለለ ጠንካራ ስራ አለመስራቱ ያሳዝናል።  ብዙ አክቲቪስቶችኡስታዞችታዋቂ ሰዎች ለእነዚህ ሴቶች ድምፅ ከመሆን ምን እንዳገዳቸውም ግራ የሚያጋባ ነው።  እንዴት 159 ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ተደርገው መፍትሔ ዝም ይባላል?

©️ Mohammadawol Hagos

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 06:38


ት/ሚኒስቴር Exit Examን በጁምዓው ከ5:30 - 8:00 ለመስጠት እንደወጠነ ነው:: እዚህጋ ጥያቄ አለን ••• የሚፈተን ሙስሊም ተማሪ የላቸውም? ወይንስ ጁምዓ ለሙስሊም ምን ማለት እንደሆነ አያውቁም? ወይንስ በጁምዓ ቀን ከ5:30 - 7:30 የመንግስት ስራ ዝግ እንደሆነ አያውቁም? ወይንስ ምንም ቢፃፍ ምንም ቢሆን ሙስሊሙ ተማሪ ከትምህርቱ እና ከጁምዓው መምረጥ አለበት?

ዘላቂ መፍትሔ ያሻል ••• ይህ የመጀmeሪያ ስህተታቸው አይደለም ••• የሪሜዲያል ተማሪዎችን ፈተና ከዒድ ጋር አድርገው ብዙ ተማሪ ላይ ተፅዕኖ መፍጠራቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው::

©️ EHEMSU

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 04:44


እለታዊ ማስታዎሻ - 346

"لَوْ أَنزَلْنَا هَٰذَا الْقُرْآنَ عَلَىٰ جَبَلٍ لَّرَأَيْتَهُ خَاشِعًا مُّتَصَدِّعًا مِّنْ خَشْيَةِ اللَّهِ ۚ وَتِلْكَ الْأَمْثَالُ نَضْرِبُهَا لِلنَّاسِ لَعَلَّهُمْ يَتَفَكَّرُونَ

ይህንን ቁርኣን በተራራ ላይ ባወረድነው ኖሮ ከአላህ ፍራቻ (የተነሳ) ተዋራጅ ተሰንጣቂ ኾኖ  ባየኸው ነበር፡፡ ይህችንም ምሳሌ ይገመግሙ ዘንድ ለሰዎች እንገልፃለን፡፡" [59:21]

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

03 Feb, 04:35


"የአላህን ውሳኔ አምኖ እንደመቀበል ደስታን የሚሰጥ ምን አለ?"

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 20:06


የትምህርት ሚኒስቴር Exit Examን በጁምዓ ሰዓት አድርጓል!

ጁምዓ ቀን በመንግስት መስሪያ ቤቶች ደረጃ ከ5:30 - 7:30 ለስግደት በሚል ዝግ እንደሆነ ይታወቃል:: የፌደራል መጅሊስ በቅርቡ በሰጠው ፈታዋም የጁምዓ ሶላት የደረሰበት ማንኛውም ሙስሊም ወደ መስጂድ ሄዶ መስገድ ግዴታው እንደሆነ አሳውቋል:: ሆኖም የትምህርት ሚኒስቴር የመውጪያ ፈተናን በመጪው ጁምዓ ከ5:30 - 8:00 ለመስጠት ፕሮግራም አውጥቶ ሙስሊም ተማሪዎችን ከጁምዓ ሶላትና ከፈተናቸው እንዲመርጡ የሚያስገድድ ሁኔታ ፈጥሯል:: ይህ ሀገራችንን የምትመራበትን መመሪያ መጣስ ብሎም የሙስሊም ተማሪዎችን መብት መዳፈር ነው::

በትምህርትም ሆነ በፈተና ፕሮግራም ከትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ ከዩኒቨርሲቲዎች ወይንም ከበታች ትምህርት ቤቶች በተደጋጋሚ የሚፈፀሙ የመብት ጥሰቶች በዘላቂነት ሊፈቱ ይገባል:: ካላንደር ከሌላቸው ወይንም ስለሙስሊሙ መሠረታዊ መብቶች እውቀቱ ከሌላቸው እንዲያውቁ ይደረጉ:: እየረሱ ወይንም ሆን ብለው እያበላሹ ከሆነ ደግሞ መንግስት ብዙም የማይረሳና የማያበላሽ ሰው በቦታው ላይ ያስቀምጥ::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 18:46


አማርኛ ምንም የማይችል ጓደኛዬ በሰሞኑ "በትንሹም ቢሆን ጥቂት ቃላትን እየለመድኩ ነው!" አለኝ:: ምን ምን ቻልክ እስካሁን ስለው "ድንች በእንቁላል ••• ቡና በወተት!" እና መሠል ቃላትን ብሎኝ እርፍ:: ከለመዱስ አይቀር እንደዚህ ነው ጃል¡ ሆድ ከሀገር ይሰፋል!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 18:14


ዲፓርትመንት ለምትመርጡ ጥቂት ምክር:-

  ይጠቅማል አይጠቅምም የሚል አማራጭ ውስጥ የሚገባበት ዲፓርትመንት ይኖራል ብዬ አላስብም:: የትኛው ዲፓርትመንት ውስጥ ብገባ ራሴንና ሀገሬን እጠቅማለሁ የሚለው ጥያቄም more or less ከየትኛው ዲፓርትመንት ጋር ዝንባሌዬ ይሄዳል በሚለው ይወሰናል:: ከዚያ ውጭ socialም ሆነ Natural ከዲኦሎጂ እስከ ኢቲኖግራፊ ብሎም ኢንጂነሪንግ ወ ሜዲስን የማይቀይር የማይለውጥ ብሎም ለገበያ የማይቀርብ ዲፓርትመንት የለም::

   ዋናው ቁምነገሩ ዲፓርትመንቶቹን በምን ያክል ደረጃ እናውቃቸዋለን የሚለው ነው:: ሲቀጥልም በምን መልኩ እናጠናቸዋለን or ግንኙነታችን በምን መልኩ ይሆናል የሚለው ነው:: ኢኮኖሚክስን ስታጠኑ ልክ እንደ እሸቱ ጮሌ ለመሆን or ለመብለጥ ከሆነ ብዙ ታተርፋላችሁ:: ኡማውንም ትጠቅማላችሁ:: ባይሎጂን ስታጠኑ እንደ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ለመሆን or ለመብለጥ ከሆነ ኡማውንም ሆነ እራሳችሁን አብዝታችሁ ትጠቅማላችሁ:: ሜዲስንን ስታጠኑ ልክ እንደ ፕሮፌሰር ጀማል አብዱልቃዲር ለመሆን or ለመብለጥ ከሆነ በዙሪያችሁ ያለን ሁሉ አብዝታችሁ ትጠቅማላችሁ::

  ከዚያ ውጭ ግን የፈለገ ብልጭልጭ ዲፓርትመንት ብትገቡ ካልሰራችሁበት አይሰራላችሁም:: ከዚያ ውጪ ግን ፖለቲካ: ታሪክ: ሕግ: ኢኮኖሚክስ: ማኔጅመንት: ኢኮኖሚክስ: አካውንቲንግ: ሎጅስቲክስ: BIS: ሜዲስን: ቬተርናርይ ሜዲስን: ኢንጂነሪንግ: ኮምፒውተር ሳይንስ: ጂኦሎጂ: ጂኦግራፊ: ቋንቋ ብሎም ያልጠቀስኳቸው የትምህርት ክፍሎች ውስጥ ገብታችሁ ልዩ ሰው ከሆናችሁ ልዩ የሆነን አበርክቶ ለኡማው ማበርከት ትችላላችሁ:: ኡማችን በሁሉም ዘርፍ ያለው ሰው ውስን ነው:: በሁሉም ዘርፍ ገብቶ ማገልገል ይቻላል::

አላህ ሁላችንንም ባለንበት ያበርታን!
ጠቅመን የምንጠቅምም ያድርገን!!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 17:00


ግቢ ውስጥ ቴንሽን ውስጥ ከሚከቱ ነገሮች መካከል "ሌክቸር እከሌኮ ከC በላይ አይሰጥም:: ባለፈው አመት D እና F ነው ያለበሳቸው::" አይነት ፕሮፓጋንዳዎች ናቸው:: በተለይም ፍሬሽ ስንሆን መደንገጥም ያጋጥማል:: የሆነ ጊዜ እንደዚህ የሚታማ ሌክቸር Exam ሊፈትነን ከክላስ ስገባ ተማሪው ደንዝዞ አጊኝቼ ቀረብ ብዬ "ምነው?" ስላቸው "ቲቸርኮ ከC በላይ አይሰጥም ብለዋል!" ብለውኝ ተገርሜ "ከሰራሁ ደግሞ ለምን አይሰጥም? አትፍሩ!" ብዬ አልፌያቸው ነበር:: ውጤት ሲመጣ ግን የብዙሐኑ C ቤት ሆኖ የእኔ A minus ነበር:: ቡሃላ ሲገባኝ አዕምሯቸውን በዚያ ልክ አሳምነውት ገብተው ስለነበር ሊሰሩ እንዳልቻሉ ነው::

እናማ ••• በመጀመሪያ አላህን ከዚያም ንባባችሁን እንጅ ሌላ ቅብርጥስጥስ እንዳትሰሙ:: በቢስሚላህ ስሩት ••• A ማለቴ A Plus ይመጣል::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 16:54


ነገ Final Exam የምትወስዱ የAAUም ሆነ የሌላ ግቢ Freshers:- ከሁሉ በፊት ብዙ ነገር አልፋችሁ ለዚህ ባበቃችሁ አምላካችሁ አላህ ላይ መተማመናችሁን አድርጉ:: በፈተና ሰዓት ፈፅሞ መጨናነቅ እንዳይኖር:: ከፈተና ክፍል ገብታችሁ "አላነበብኩም እኮ!" የሚል እሳቤ ውስጥ እንዳትገቡ:: Just ፈተናውን እንዴት ልስራ የሚለው ላይ ብቻ ትኩረት አድርጉ:: በተዓውዝ እና በቢስሚላህ ጀምሩት:: ተወኩላችሁን በአላህ ላይ አድርጉ:: then በአላህ ፈቃድ የሚጠቅማችሁ ውጤት ይመጣል:: ከዚያ ባሻገር መኮረጅ ማስኮረጅ መስረቅ ማሰረቅ እንደ ሙስሊም እርም ናቸውና ፈፅሞ እንዳትሞክሯቸው:: ለሌሎችም መልዕክቱን አድርሱ::

መልካም ፈተና ••• መልካም ውጤት ••• መልካም ዲፓርትመንት!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 15:37


የዛሬው የቁርዓን ውድድር ወደ 60 ሀገራት የላክናቸው አምባሳደሮች ከሰሩት ዲፕሎማሲ በላይ አሳክቷል ቢባል ማጋነን አይሆንም:: ዛሬ ከ60 በላይ ሀገራት ሐበሻ ሐበሻ ሲሉ ነው የሚውሉት:: this is what we call diplomacy. ይህን ያዘጋጁ ሰዎች ትልቅ ክብር ይገባቸዋል::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 14:39


የቁርዓን ውድድሩ መሳካቱ ድል ቢሆንም ••• ክፍተቶች ነበሩ!

• ውጥኑ ወራት ቢያልፉትም እርስ በዕርስ ባለ አለመግባባት ይሁን በሌላ ምክንያት የሚገባውን ያክል ማስታዎቂያ አልተሰራለትም:: ሀገርን የሚወክል ፕሮግራም ተዘጋጅቶ በጥቃቅን ክፍተቶች ወደሗላ ማፈግፈግ ትልቁን ምስል አለመመልከት ነውና ትኩረት ያልሰጠ/እንዲሰጥ ያላደረገ አካል ሁሉ የውድቀቱ ተቋዳሽ ነው:: በዚህም ሆነ በሌላ ምክንያት at the end በሚልዬኖች የሚቆጠረው የአዲሳባ ሙስሊም 30ሺህ የሚይዘውን የአዲሳባ እስታዲዬም ግማሽ ያክል እንኳ መሙላት አልቻለም:: ለወደፊቱ ቢታሰብበት ጥሩ ነው::

• ከመጀመሪያው ጀምሮ እንደተገለፀው 800 / 400 ብር መግቢያ በተለይም ለመድረሳ እና ለአስኮላ ተማሪዎች ከውድም በላይ ነው:: እስከመጨረሻው ድረስ ግግም ብሎ ክፍያ መጠየቁ ከግማሽ በላይ ወንበር ባዶ እንዲሆን አድርጎታል:: በዚህ ውስጥ ፕሮግራሙም ሆነ ሽልማቱ ዶላራዊ መሆኑን ማሰብ ቢገባንም ህዝባችን የዶላር ህይዎትን አይችል ብሎ በቀን ሁለት/አንድ ጊዜ የሚበላ መሆኑ መታሰብ አለበት::

• ፕሮግራም 2:00 ይጀመራል ተብሎ 6:00 መጀመሩ ትዝብት ላይ ይጥላል:: ረጃጅም የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክቶች: የምርጫ ቅስቀሳ የሚመስሉ መንግስት ተኮር መልዕክቶች እንዲሁም አንዳንድ መዘግየቶች ጊዜውን ከመግፋታቸው ባሻገር የተለያየ የፖለቲካ አመለካከት ይዞ የሚታደምን አካል የተለዬ ምልከታ እና ጥርጣሬ እንዲኖረው ያደርጋል::

• መንግስት ሁኔታዎችን አመቻችቶ ፕሮግራሙ እንዲዘጋጅ አስተዋፅዖ ማድረጉ የሚያስመሰግን ቢሆንም ሀላፊነቱን ከመወጣቱ ባሻገር የተለዬ ውለታ እንደዋለልን ተደርጎ መታሰብ የለበትም:: ለተለዬ ምክንያት መሠል መልዕክቶች የሚተላለፉ ከሆነም ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በቅርብ ጊዜያት እየደረሱበት ያሉት መገፋቶች እንደሌሉ አድርጎ ማቅረብ ደግሞ አግባብነት የለውም:: በቅርብ ጊዜ እንኳ በሸገር ሲቲ የፈረሱ መስጂዶች ጉዳይ: የአክሱም እና የዲላ ሙስሊም ተማሪዎችን ጉዳይ ማየት እንችላለን::

■ የሚሰራ መሳሳቱ ••• በስራ ውስጥ ክፍተቱ መፈጠሩ ተፈጥሯዊ ነውና ክፍተቶቹ ከተጠገኑ ለወደፊቱ ለውጥ ያመጣሉ:: ግን ከሁሉም በላይ ••• የአለም ህዝብ እያየ እስቲዲዬም የሚሞላ ሙስሊም አለመኖሩ ትልቅ shame ነው:: አላህ የተሻለ እና ያማረ ነገር የምንሰራበትን ጉልበት እና ብልሐት ይስጠን::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 14:24


የቁርዓን ውድድሩ እንደ ኢትዮጵያ ሙስሊም ትልቅ ድል ነው!

• ታሪክን ወደሗላ ስንቃኝ እንኳን የቁርዓን ድግስ ተደግሶ በአደባባይ ዝግጅት ሊሰናዳ አይደለም ሙስሊም ሆኖ መኖር እንኳ ቅንጦት የሆነበት ሰዓት ነበር:: ከዚያ ባሻገር የየዘመኑ ጀግኖች እየታገሉ የትግሉንም ዱላ ለተተኪው ትውልድ እያስረከቡ መሻሻሎች ቀን በቀን ተተካክቶ ሲያልፍ ተሻሽለው ከዚህ ደርሰዋል:: በቀላሉ የኢድ ሶላትን በአደባባይ በስታዲየም ማክበር የተቻለው ከዛሬ 32 አመታት በፊት በ1985 ዓ.ል ነበር:: አሁን የአላህ ፍቃዱ ሆኖ በ2ተኛ ዙር የቁርዓን ውድድር በዚያው ስታዲዬም ተዘጋጀ::

• ዝግጅቱ ከ60 በላይ ሀገራት የተውጣጡ ሙስሊም ወንድሞቻችንን ወደ ማዕድ ያመጣ ያቀራረበ ያዋደደ መሆኑ ደግሞ ትልቅ እምርታ ነው:: የአረብ እና የሙስሊም ጥላቻ ተዘርቶ ባፈራባት ሀገር ውስጥ የመላው አለም አረቦች እና ሙስሊሞች ወኪሎች ከኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ጋር ተሰባስበው የአላህን ቃል ማንበባቸው ትልቅ ድል ነው::

• ከዚያ ባሻገር ይህንን ፕሮግራም ወኪሎቻቸውን የላኩ ሀገራት ሁሉ መመልከታቸው አይቀሬ መሆኑ ስለ ኢትዮጵያና ሙስሊም ዜጎቿ አዎንታዊ የሆነ ምስል በመላው አለም መሠራጨቱ አይቀሬ ነው:: ይህ ደግሞ ፈርጀ- ብዙ ጥቅሞች አሉት::

አልሐምዱሊላህ ••• ስለተዘጋጀ ••• ስለታደምን ••• ስለተሳካ ••• ውጤት ስላመጣ ••• በስም የምናውቃቸውን ታሪካዊ ሀገራት ወኪሎች በአካል ስላሳየን:: የከንዓን አንበሶችን ከፍልስጤም ••• የፋቲሁ ሙሐመድን ልጆች ከኢስታንቡል ••• የኡመር ሙኽታርን የልጅ ልጆች ከትሪፖሊ ••• የበግዳድን ፍሬዎች ከኢራቅ ••• የሰልማኑል ፋሪስን ወዳጆች ከኢራን ••• የሰንዓ ከዋክብትን ከየመን ••• የደማሲቆ ልጆችን ከሶሪያ ••• በመላው አለም የሚገኙ ሙስሊሞችን በሐበሻ ምድር በአንድ ጥላ ስር ስላሰባሰበ ••• ምስጋና ይገባው:: ስለእውነት ትልቅ ድል ነው ••• ላሳኩት ሁሉ ክብር ይገባ::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 14:08


ይህ ብላቴና ኢራቅን ወክሎ የተወዳደረው ነው:: አላህ ያሳድገው!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 13:57


የአለም-አቀፉ የቁርዓንና አዛን ውድድር አሸናፊዎች የሚከተለውን ይመስላሉ:-

በቁርአን ሒፍዝ በወንዶች፦
1ኛ. መሐመድ ፉአድ አሕዋጂ የመን፣ 2ኛ.ዩሱፍ አሺ ኳታር፣
3ኛ.መሐመድ ፏአድ ከአሜሪካ አሸናፊ ሆነዋል።

በሴቶች ቁርአን ሂፍዝ፦
1ኛ.ሩቀያ ሷሊህ ከየመን ፣
2ኛ.ነሲም ጀናውጂ ከአልጄሪያ
3ኛ. ቀመራ ወሊዩ መሐመድ ከኢትዮጵያ አሸናፊ ሆነዋል።

በአዛን ውድድር፦
1.መሐመድ አቡበክር ከኢንዶኔዥያ
2.ዑመር ዱራን ከቱርኪዬ
3.ጅብሪል አደም ከኢትዮጵያ በመውጣት ተሸላሚ ሆነዋል።

በቁርአን አቀራር(በቲላዋ) ዘርፍ በወንዶች 1.አብዱረዛቅ አልሸሃዊ ከግብፅ
2.ከራር ለይስ ኢራቅ
3.አንጀድ ከምዳን የመን አሸናፊ ሆነዋል።

••• የተወዳደሩት ሁሉ አሸናፊዎች ናቸው:: ያዘጋጁት ሁሉ አሸናፊዎች ናቸው:: የታደሙት ሁሉ አሸናፊዎች ናቸው:: ተደጋግሞ የሚዘጋጅ ደጋግመን የምንታደም ያድርገን::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 12:58


ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን! በቅርቡ ተመርቆ የወጣውና በ6ኪሎ ጀመዓ ሲንቀሳቀስ የምናውቀው የወንድማችን ፍሮምሳ አለማየሁ እናት ወደ አኼራ ሄደዋል። አላህ ነፍሷን በጀነት ይቀበል። ለእርሱ እና ለመላ ቤተሰቡም መፅናናትን ይወፍቅ።

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 12:07


የምወዳቸው የየመኖች ተወካይ ከመድረክ ተሰይሟል። የመጨረሻው ተወዳዳሪ ነው።

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 11:51


አልጀሪያዊው ሸይኽ ፕሮፌሰር ከማል ስለ ኢትዮጵያ የሚከተለውን ብሏል:-

"ሐበሻ አሐዱን አሐድ በማለት በአረቢያ በረሐ ላይ የፅናትን ጥግ ያሳየው ቢላል ሀገር ነች። የኢስላም ቀደምት ብርቅዬ ወጣቶችን እየተሳደዱ ባለበት ወቅት 'በሀገሬ በሰላም ኑሩ!' ያለው የፍትሐዊው ንጉስ ነጃሺ ሀገር ነች። ከአሚና እቅፍ ተቀብላ ነቢን ተንከባክባ ያሳደገችው ኡሙ አይመን በረካ ሀገር ነች። ወደ ሐበሻ ሂዱ!' ብለው ነቢ ሲያዙ የአላህ ምርጫ መሆኑ እርግጥ ነው። የፍትሐዊው ንጉስ ሀገር የሰላም ሀገር ነች። ከመካ ቀጥሎ ቁርዓን የተነበበባት ሀገር ነች። የሐበሻ ትክክለኛ መልኳ የዛሬው ነው። ቁርዓን ወዳድ ሰው አስተናጋጅ ህዝብ ናችሁ።"

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 10:30


የቢላል ልጅ ሐበሻን ወክሎ በሐበሻ ምድር የአዛን ድምፅ እያሰማ ነው:: ምንኛ ያማረ ድምፅ ነው በአላህ?!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 09:55


ዶላርን ማለቴ አሜሪካን ወክሎ የሚወዳደረው ከመድረክ ተሰይሟል፡፡

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

02 Feb, 09:24


ከሊብያ ከኡመር ሙኽታር ሀገር የመጣው ቃሪዕ ከመድረክ ተሰይሟል፡፡

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

20 Jan, 11:54


እውን ኒቃብ የደህንነት ስጋት ይሆናል?

የአንድን ሐይማኖት ተከታይ ሐይማኖታዊ ልብስ የደህንነት ስጋት ብሎ መግለፅ ከጥላቻ የሚመነጭ እምነቱን እና አማኙን የሚያንቋሽሽ መሆኑ የሚታወቅ እና የሚያስጠይቅ ቢሆንም ምን ያክል አመክንዮን የተከተለ እና ያልተከተሉ መሆኑን ለመረዳት ያክል የሚከተሉትን ምክንያቶች እንመልከት::

1ኛ:- አሁን ላይ ኒቃብን የደህንነት ስጋት በማለት ሙስሊሙን ከመሳደብ አልፈው ኒቃቢስቶቹን የሚያንገላቱት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ሆኑ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ወይም ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ባለፉት አመታት ውስጥ ኒቃብ ሲለበስባቸው ነበር:: እዚህ ጋር የሚነሳው ጥያቄ ኒቃብ የደህንነት ስጋት ከሆነ ባለፉት አመታት ውስጥ በእነዚህ ተቋማት ውስጥ በኒቃብ ሳብያ ምን አይነት የደህንነት ስጋት ተፈጠረ? መልስ ምንም ሆኖ ጥያቄው ደግሞ ካለፉት ዘመናት የተለዬ ነገር በዚህ ሰዓት ምን ተፈጠረ? የትላንቷ እና የአሁኗ ኢትዮጵያ ምን ልዩነት አላቸው? ዩኒቨርሲቲዎቹስ ምን የተለዬ ነገር አመጡ?

2ኛ:- ከተቋማቱ ባሻገር ወይንም ከተቋማቱ ቅጥር ግቢ ውጭ ኒቃብ ለባሾች በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ:: እናም ታዲያ በጊዜ ሂደት መንግስት ኒቃብ ለባሾች ለሀገሪቱ ደህንነት ስጋት ናቸውና ለብሰው መንቀሳቀስ አይችሉም ሊል ነው? ወይንስ ዩኒቨርሲቲዎች ከሀገራችን ቦታዎች በተለዬ መልኩ ኒቃብ ሲነሳ የተለየ የሆኑ የደህንነት ስጋት ይጋረጥባቸዋል?

3ኛ:- ሰው በኒቃብ መልኩን ሸፍኖ ያልሆነ ነገር ይዞ ይገባል የሚል ስጋት ከሆነ ያላቸው ሌሎች ሰዎችስ በሌላ መንገድ ሸፍነው ይዘው ይገቡ የል? እናስ እነርሱም በተመሳሳይ ያንን ነገር እንዲያስወግዱ ይጠየቁ ይሆን? ለአብነት ሜካፕ ተቀብተው ማንነታቸው የሚቀይሩ ሴቶች አሉ:: እናስ ሜካፓችሁን ካላስወገዳችሁ አትገቡም ሊባሉ ነው? በሱሪው ኪስ የማይፈቀድ ነገር ደብቆ የሚገባ አለ:: ሱሪህን አውልቅ ሊባል ነው?

  እንደ አጠቃላይ የደህንነት ስጋት የሚለው ምክንያት ስድብ ከመሆኑም ባሻገር ከLogic የራቀ ምክንያት ነው:: ድንበር ያለፈ ጥላቻ እና ንቀትን ከማሳየት የዘለለ አይደለም:: ሊታረሙ ይገባል::

©️ EHEMSU

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

20 Jan, 11:31


By the way at this time i am feeling an earth quake shaking my bed and a chair at al-aqsa mesjid.

አላህ በቃ ይበለው ••• ይታረቀን!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

20 Jan, 10:54


ቆይ ግን ••• ስለ ደህንነት አንስተው ኒቃብን ለመከልከል የሚሞክሩ ሰዎች ለደህንነት ከተጨነቁ ከኒቃብ ይልቅ ሜካፕ ስጋት አይሆንም? ኒቃብ ለባሾችን እንኳ ገለጥ አድርገው ከመታዎቂያቸው ጋር ማመሳሰል ይችላሉ ••• ባለ አምስት ኪሎግራም ሜካፓሟን ከመታዎቂያዋ ጋር እንዴት ነው የሚያመሳስሉት? የእውነት አይችሉም ••• ከሜካፕ እና ከሜካፕ ቡሃላ ያለ ምስል የሁለት ፕላኔት ፍጥረት እስኪመስሉ ድረስ ይለያያልኮ:: ብቻ ግን ••• ሰዎቹ አጀንዳቸው ሌላ ነው::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

20 Jan, 10:45


"ኒቃብ ለደህንነት ስጋት ስለሆነ መልበስ አይቻልም!" - ዲላ ዩኒቨርሲቲ

ላለፉት 3 አመታት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በነፃነት ይለበስ የነበረውን ኒቃብ ያለ ሕግ እና መመሪያ ከወር በፊት ከልክሎ የነበረው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከሙስሊም ተማሪዎች ጋር ግብግብ ውስጥ እንደነበር ይታወቃል:: በሰሞኑም ለብሳችሁ አትገቡም በማለቱ ሙስሊም ተማሪዎች ከግቢ ውጭ ከመስጂድ ማደራቸው ይታወሳል::

የተፈጠረውን ችግር ለመፍታትም በዛሬው እለት ከሙስሊም ተማሪዎች ተወካዮች ጋር ውይይት ያደረገው የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር "ኒቃብ ለደህንነት ስጋት ስለሆነ በግቢ ውስጥ ለብሶ መግባትም ሆነ መንቀሳቀስ አይቻልም!" የሚል መልስ እንደሰጣቸው ተማሪዎች አሳውቀዋል::

በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ተጨባጭ ያልሆነ እና እምነቱን የሚዳፈር ምክንያት በማቅረብ የሚደረግ የመብት ጥሰት መቆም እንዳለበት:: ኒቃብንም ሆነ የትኛውንም ኢስላማዊ አለባበስ የደህንነት ስጋት አድርጎ ማሰብም ሆነ ማቅረብ ሀይማኖቱን ከማንቋሸሽ ተለይቶ አይታይም:: ኒቃብ በሐይማኖት እንዲለበስ የታዘዘ የእምነት ልብስ ሲሆን በሕግ ደግሞ የማይከለከል የነፃነት መገለጫ ነው::

በአላህ ፈቃድ መሠል ጥላቻ ተኮር የመብት ጭቆናዎች በዚህ ትውልድ ታሪክ ይሆናሉ ••• ነፃነት በትግል እንጅ በነፃ አይገኝም!

©️ EHEMSU

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

20 Jan, 10:27


ባሌ ••• አለችው ••• ወዬ ብሎ ሲያዳምጣት ••• አሁን ለወደፊት ላም ገዝቼ ተንከባክቤያት ••• ጥጃ ወልዳ ••• ጥጃዋንም ከመደባችን አጠገብ ችካል ቸክዬ አስራታለሁ ••• አለች:: ባልም ኮስተር ብሎ "ከእኔ መደብማ የአንቺ ጥጃ አትታሰርም!" አለ:: እርሷም በስጨትጨት ብላ "ምን ማለትህ ነው? መደቡ የጋራ ነው:: አስራለሁኝ::" አለች:: በዚህም ተጣሉ:: ተጨቃጨቁ:: በመጨረሻም ንዴቱን መቆጣጠር ያቃተው ባል በሙቀጫ ግልገል አፋንጫዋን ብሎ ገደላት::

ተመልከቱ ••• ላሟ ሳትገዛ ጥጃዋም ሳትወለድ ከመደቡም ሳትታሰር ••• አሰራለሁ አታስሪም በሚል ጭቅጭቅ የሚስት ህይዎት ጠፋ:: አብዛኛውንም ጥል እና ጭቅጭቅ ካየነው ከዚህ አያልፍም:: ሀ ብለን መንገድ ሳንጀምር ፐ ደርሰን በሀሳብ እንቧቀሳለን:: መንገዱም ሳይገባደድ ጉዞው ይቋጫል:: ሰውም ይበታተናል:: የብዙሐኑ ችግር ይህ ነው:: መንገድን አጥርቶ መጓዝ ጥሩ ቢሆንም በማይመስሉ ነገሮች ተጨቃጭቆ ከመንገድ ውጭ መሆን ግን ሞኝነት ነው::

የቃል ፍች:- መደብን ለመርሳት የሚጣጣር ካለ መደብ ማለት በድንጋይ እና ጭቃ የሚሰራ አልጋ መሳይ ከፍ ያለ መተኛ ቦታ ነው::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

20 Jan, 09:43


እንዲህ አምረው ካደጉ ••• መጪው ትውልድ ከዛሬ ባማረ መልኩ ይገነባል ይሆናልም ••• ማሻ አላህ!

ግን እኛስ መች ይሆን የምንወልደው?🙊

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

20 Jan, 09:38


በእጅ ሰጥቶ በእግር መፈለግ!" እንዲል አበው በአሁን ዘመን ከማበደር ይልቅ ያበደሩትን መቀበል ከብዷል:: አብዛኛውን ጊዜ አበዳሪ ያበደረውን ሲጠይቅ ሊበደር ደጅ የሚጠና ያክል ይመስላል:: ተበዳሪም ከመንቀባረሩ የተነሳ ስልክ ማንሳትና ቴክስት መመለስን እርም ይላል:: ይህ ሁሉንም ሰው ባይወክል እንኳ አብዛኛውን ይገልፃል:: እናማ ••• በድንገት የምትበደሩ ሰዎች በቃላችሁ መሠረት መልሱ:: የምታበድሩ ሰዎች ደግሞ 50 በ50 አውፍ እንዳላችሁ አስባችሁ ይሁን:: አለዚያ ገንዘብ ዝምድናን ጓደኝነትንና ወዳጅነትን እየቆራረጠ ነው::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

20 Jan, 08:52


"እናገረዋለው ያበጠው ይፈንዳ
ፂም አወራረዱ ልክ እንደአልቃይዳ
"
.
አንዲት አዝማሪ አባይ ቲቪ ባስተላለፈው ዝግጅት ከእንግዶች አንዱን (ምስሉ ላይ የሚታየውን) የገለፀችበት ነው ...
.
እናውቃለን ኮማሪ ቤት ይቅርና ስልጣን የያዙት ፅንፈኞች ራሱ ከዚህ የተሻለ አስተሳሰብ የላቸውም ... ነገር ግን እንዴት Abbay TV እንዲህ ሙስሊሙን በሙሉ በሽብርተኝነት የሚፈርጅ አባባል ያሰራጫል? ምን አይነት ንቀት ነው?
.
እንዲህ ባሉ ሙስሊሙን በሽብርተኝነት በሚፈርጁ ሚድያዎች ማስታወቂያ የምታስነግሩ ነጋዴዎችስ መቼ ነው አራጆቻችንን ከመደገፍ የምትታቀቡት?
ነው ወይስ የናንተንም ምርት እርም ማለት አለብን?

©️ Bin Ali

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

20 Jan, 08:40


ሐማስ የእስራኤል እስረኞችን ሲያስረክብ የሚያሳይ ቪድዮ ነው ••• እስረኛኮ አይመስሉም ቢላህ!

አላህስ "ምግብንም ከመውደዳቸው ጋር ለድኻ: ለየቲምም: ለምርኮኛም ለእስረኛም ያበላሉ::" [አል_ኢንሳን: 8] ያለው ለዚህ አይደል?

ይህችን አለምኮ ብዙ ነገር አስተማሩ ••• ፍልስጤማውያን!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

20 Jan, 06:03


እለታዊ ማስታዎሻ - 337

"وَلْيَعْفُوا وَلْيَصْفَحُوا ۗ أَلَا تُحِبُّونَ أَن يَغْفِرَ اللَّهُ لَكُمْ ۗ وَاللَّهُ غَفُورٌ رَّحِيمٌ

ይቅርታም ያድርጉ፡፡ (ጥፋተኞቹን) ይለፉም፡፡ አላህ ለእናንተ ሊምር አትወዱምን አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡" [24:22]

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

19 Jan, 22:11


አንዳንድ ሆድ አለ ••• ሌት ከየትም ምግብ እንደማታገኝ ሲገባው ደጋግሞ የሚያንቋርር ••• ምግብ ተትረፍርፎ ሲቀርብልህ ደግሞ በቃኝ ብሎ የሚነፋፋ ••• አስመሳይ ::

አንዳንድ ልብም አለ ••• እንደማይወዱት እርግጠኛ ለሆነባቸው ነገሮች ደጋግሞ የሚመታ ••• ደጋግመው ለሚመቱለት አካላት ደግሞ ድንጋይ ሆኖ የሚያልፍ ••• እድለ ቢስ ::

ሆድ ብዙ ያስናግራልና ዝም ልበል!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

19 Jan, 21:02


አንዳንድ ስጦታዎች በመከራ ታሽገው ይመጣሉ!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

19 Jan, 20:57


"አልሐምዱሊላህ ታቦቱ በሰላም ገባ!"

የዚህን አባባል ስረ- መሠረት ወንድማችን አብዱልጀሊል ሸህ ዓሊ ካሳ ተምኔታዊት ደሴት ሲል በፃፈው መፅሐፍ ላይ በገፅ 260 እንደሚከተለው ይገልፃል:-

"ከዚህ አባባል ጀርባ ያለው ነገር ምንድነው? አልሃምዱሊላህ ታቦቱ በሰላም ገባ የተባለው ታቦታት ለክብረ በዓላት ሲወጡ በአካባቢያችን ደም ካላየሁ ታቦቱ አልገባም አለ በሚል አባባል ጎረምሶች የሚፈጥሩትን ድብደብና ደም መፋሰስ የሚያመጣውን ጦስ ቀላል ባለመሆኑ ሙስሊሙ "አልሃምዱሊላህ ታቦቱ በሰላም ገባ" ለማለት የተጠቀመበት ነው።"

ከዚህም ባሻገር ባለፉት ጊዜያቶች የራጉኤል ታቦት በአንዋር ሲያልፍ "መስጂዱ ካልፈረሰ አልሄድም አለ!" እየተባለ ብዙ ፈተናዎች ይነሱ ነበር:: ደሴም በሸዋበር መስጂድ ሲያልፍ "ሸዋበር ካልፈረሰ አልሄድም አለ!" ተብሎ አተካሮ ይነሳ ነበር:: በነዚህ መሐል የመስጂድ ኢማሞች እየተጠሩ "እንግዲያውስ ለእኛ ልቀቁልንና አለመሄዱን እናረጋግጥ!" እያሉ ••• ይህም ሲባል "አይ! ታቦቱ እምነታችንን ለመፈተሽ ነበር!" እንሂድ እያሉ ብዙ ጊዜያት አልፏል::

እነሆ ዛሬ ይህ ታሪክ ሆኗል ••• በአባቶቻችን ትግል እና ጥረት በሰዎች አዕምሮ ውስጥ ተስላ የነበረችው ተምኔታዊት ደሴት ብን ብላ ጠፍታለች:: የመቻል ጊዜም አልፎ የመከባበር በር በጥቂቱም ቢሆን ተከፍቷል:: በአላህ ፈቃድ በቀጣይም ሙሉ መከባበር የሚኖርባትን ኢትዮጵያ እናይ ይሆናል::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

19 Jan, 20:19


ETV ታቦቱ አማኑኤል በመሄድ ታማሚዎችን ጎብኝቶ አለፈ እያለን ነው

ዝምምም ሳይሻል አይቀርም!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

19 Jan, 20:10


የትግራይ መጅሊስ በመቋለ ከተማ ለማክሰኞ ሊያደርግ ላሰበው ሰላማዊ ተቃውሞ ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ ገልፇል::

•••ተምሳሌትነት ያለውን እንቅስቃሴ ከትግራዋይ እህት ወንድሞች አባት እናቶች እያየን ነው::

ትግራይ ላይ ለሒጃብ ሲባል ታስረዋል:: ለሒጃብ ሲባል ተደብድበዋል:: ለሒጃብ ሲባል ከትምህርት ርቀዋል:: ለሒጃብ ሲባል ለአመታት ተተብተቦ የነበረውንና አይነኬ የሚባለውን ጨቋኝ ቢሮክራሲ ተጋፍጠዋል:: ሒጃብ ክብር ነውና ከዚህም በላይ ግድ ነው:: ሒጃብ ነፃነት ነውና ብዙ ይከፈልለታል:: ይህንን ትግራዋዮች በተግባር ነግረውናል:: እንማር ይሆን?

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

19 Jan, 19:03


"የቻለ ያግባ ያልቻለ ይፁም!"

እናማ ነገ ሰኞ ነው ••• እየፆማችሁ (የምትችሉ እያገባችሁ)

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

19 Jan, 18:07


ዲላ በሁሉም ካምፓስ ዛሬ ገብተዋል!

ኒቃብን ከልክሎ ተማሪዎችን አላስገባም ያለው ዲላ ዩኒቨርሲቲን በመቃወም አንገባም ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች ከኒቃቢስት እህቶቻቸው ጋር ገብተዋል::

ነፃነት በነፃነት አይገኝም! ኢንሻ አላህ ••• ነገ ከግቢው ጋር ውይይት ይኖራቸዋል:: በአላህ ፈቃድም መብታቸውን ያስከብራሉ::

©️ EHEMSU

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

19 Jan, 17:14


ከ471 የትግል ጊዜያት ቡሃላ አቡ-ዑበይዳህ ልብ በሚደርስ ቃሉ መልዕክቱን አድርሷል!

ከድንቅ ህዝብ የተገኘ ድንቅ ሰው ••• አቡ-ኡበይዳህ!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

19 Jan, 16:23


ከቀኝ አክራሪ የእስራኤል ካቢኔ አባላት ዋነኛውና የጸጥታ ሚኒስትር የሆነው ቤን ጋቪር እንዲህ ይላል:-

"ከሰላም ስምምነቱ በኋላ በጋዛና west bank ያለውን የደስታ ጭፈራ ስናይ የጦርነቱ ሰለባ( በጣም የተጎዳው) ማን እንደሆነ ተገነዘብ::"

በውርደት ላይ ውርደትን በሽንፈት ላይ ሽንፈትን ይጨምርላቸው!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

19 Jan, 16:05


ጥቆማ!

የሳኡዲ አረቢያ ኤምባሲ የባህል ዘርፍ 2ተኛ ዙር ሀገር አቀፍ የወንዶች እና የሴቶች ሀዲስ ሂፍዝ ዉድድር አዘጋጅቷል። በዚህኛው ዙር ለውድድር የቀረበው ኪታብ በሰሚር ኢብኑ አሚር አልዙሀይሪ አርትኦት የተዘጋጀው የኢብኑ ሀጀር አል አስቀላኒ ቡሉገ-ል-መራም ሚን አዲለቲ-ል-አህካም ነው።

📌 የመፅሐፉ PDF: https://down.ketabpedia.com/files/bkb/bkb-ha1853-ketabpedia.com.pdf

📌 የመወዳደሪያ ደረጃዎች (አንድ ሰው በአንድ ደረጃ ብቻ ነው መወዳደር የሚችለው)
1. 1 - 57 ያሉ ሀዲሶችን መሐፈዝ
2. 1 - 108 ያሉ ሀዲሶችን መሐፈዝ
3. 1 - 150 ያሉ ሀዲሶችን መሐፈዝ
4. 1 - 203 ያሉ ሀዲሶችን መሀፈዝ

📌 ለውድድሩ መስፈርቶች
1. ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ መሆን፤
2. እድሜ ከ 40 አመት በታች መሆን፤
3. በፈተናው ቀን፣ ሰዓት እና ቦታ መገኘት መቻል፤
4. የምግብ፣ የማደሪያ፣ የትራንስፖርትና ማንኛውም ወጪ በራሳቸው መሸፈን መቻል፤


📌 ለመመዝገብ በዋትስአፕ ቁጥር:-
- ለወንዶች +251928933333
- ለሴቶች +251945777744
+251945777755

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 21:05


እዚሁ ኢትዮጵያ ወንዶ የሚባል ወረዳ ሰደድ እሳት አመሻሹን እንደተከሰተ ተገልፇል::

ያስፈራል ••• በእዝነቱ ይታረቀን!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 20:32


ይህ ሰው ካህሳይ ይባላል:: የአክሱም ሙስሊም ተማሪዎችን እያወናበደ ያለ መምህር የሚልን ስም የያዘ የክፋት መምህር:: ሙስሊም ተማሪዎችን የሚከለክል መመሪያ ት/ቤታችሁ ከጥቅምት ጀምሮ ለምን አወጣ ተብሎ ሲጠየቅ "ፀጉራቸውን የሚገላለጡት ተማሪዎች ፀጉራቸውን ከሚሸፍኑት ጋር አንማርም!" ስላሉ ነው አለ::

ማለቱን አይሉም ••• ግን ቢሉስ ••• ሀገር አንድን አካል ብቻ መምሰል አለባት ማለት ነው? ወይ ደግሞ በዚህች ሀገር ውስጥ እምነቴ ብሎ ክብርን መጠበቅ አይፈቀድም ነው?

ግን ምንድን ነው የተማረው በአላህ?

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 20:04


ኒቃብ ህልውና ነው!

ኒቃብ ሲነሳ አጀንዳዎችን መዝዞ ኒቃብን ትንሽ አጀንዳ ለማስመሰል የሚሞክር አካል ካለ እርሱ ምስጥ ነው:: የኒቃብ ጥያቄ ሲነሳ የኡማው ክብር እና የሴት ልጁ ህልውና የማይታየው ሰው Short-sighted ከመባል አያልፍም::

እስልምና ለሚስቱ ሲል የተጋደለ ብሎ ከሸሂድነት ጎራ ይመድባል:: ለክብሩ ሲል ነፍሱን የሰጠንም ሸሒድ ያደርጋል::

እዚህጋ በምንም መልኩ በምንም ምክንያት ከትግል መስመር የሚሸሽ ሰው ክብር የሚባለውን ቀይ መስመር እየተላለፈ መሆኑን ይወቀው:: ከዚያ ደግሞ ኒቃብን አልፈው --- ሴት ልጁንም አልፈው --- በራሱ ክብር እና ህይዎት ሲመጡበት ራሱን መች እንዳዋረድ በግልፅ ይገባዋል::

ኒቃብ ሕልውና ነው ••• ከደማችሁ ጋር አዋህዱት!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 18:54


ዲላ ዩኒቨርሲቲ ••• ተጨማሪ!

ኦዳያ ካምፓስ ያሉትን ተማሪዎች ቢያስገቧቸውም በዋናው ግቢ (agri campus) ያሉትን ግን ሒጃብ ካልወለቀ አትገቡም ብለዋቸው ሁሉም ተማሪዎች ተመልሰው ከመስጂድ አድረዋል:: የሚገርመው በዋናው ግቢ ያሉት አውልቁ ያሉት even ማስክን ነው::

ያሳዝናል ••• ክብርህን ካላወለቅክ ብሎ ተማሪውን ከግቢ ውጭ የሚያሳደር የልሕቀት ማዕከል ተፈጥሯል:: ግን እንደው ምንድን ነው የሚያስምሩት? የተማሩትስ ምን ይሆን?

ብቻ ••• ነፃነት በነፃ አይገኝም!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 18:16


ዲላ ኒቃቢስቶቹ ለዛሬ ገብተዋል!

ዩኒቨርሲቲው አይገቡም ብሎ ቢከለክልም የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች "ኒቃቢስቶች ካልገቡ አንገባም!" በማለት አብረዋቸው እስከ ምሽት 3:00 ቆይተው ገብተዋል::

መሠል ችግሮች በዘላቂነት እንዲፈቱ ችግር ፈጣሪዎችም ለፍትሕ እንዲቀርቡ ሁሉም አካል ተረባርቦ መስራት ይጠበቅበታል::

ነፃነት በትግል እንጅ በነፃ አይገኝም!

©️ EHEMSU

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 17:51


ነገረ ኒቃብ ••• በዲላ ዩኒቨርሲቲ!

ከአንድ ወር በፊት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አገልግሎት እና የደህንነት ክፍል ሀላፊ የሙስሊም ተማሪዎችን ተወካዮች ጠርተው "ከአሁን ቡሃላ ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብን ለብሰው መግባትም ሆነ መንቀሳቀስ አይችሉም!" ብለው ነበር:: ተወካዮቹም አይሆንም መብታችን ነው በማለታቸው ሳቢያ በታህሳስ 9 ለሚመለከታቸው የዩኒቨርሲቲው አካላት ሁሉ ደብዳቤ አስገቡ:: የደብዳቤውን መግባት ተከትሎም ዩኒቨርሲቲው "ጉዳዩን ወደ ሕግ ክፍል መርቸዋለሁ:: ውሳኔ ጠብቁ:: እስከዚያ ግን ይልበሱ::" የሚልን መልስ ሰጠ::

ሆኖም አልፎ አልፎ ክልከላ እና ትንኮሳ ማካሄዳቸውን ተከትሎ የጌዴኦ ዞን መጅሊስ ጉዳዩን በመቃወም ለዩኒቨርሲቲው በጥር 5 ከአምስት ቀናት በፊት ደብዳቤ አስገባ:: ይህንንም ተከትሎ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ተማሪዎች እንወያይ የሚል ጥያቄን ሲያቀርቡለት "እሺ! እደውላለሁ!" የሚል መልስን በመስጠት ዛሬ ደረሰ::

ሆኖም በዛሬው እለት ተማሪዎችን ሳያማክሩ "ኒቃብ ተለብሶ መግባት አይቻልም!" ብለው ከልክለዋል:: ተማሪዎች እስካሁንም ከመስጂድ ናቸው:: በሕገ- ወጥነታቸው ይቀጥሉበት እንደሆነ የሚታይ ይሆናል::

ፍትሕ ለኒቃቢስቶች!
ፍትሕ ለሙስሊም ተማሪዎች!!
ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!!


©️ EHEMSU

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 17:36


ዲላ ዩኒቨርሲቲ ኒቃብ ለባሽ ተማሪዎች እንዳይገቡ ከልክሏል!

  ከዚህ በፊት ዩኒቨርሲቲው በትዕዛዝ ደረጃ እንዳትለብሱ ብሎ ተማሪዎች ከሕግ ውጭ ነው በማለታቸው ሳቢያ ለውይይት ቀጠሮ ቢሰጣቸውም ተማሪዎችን ሳያወያይ በዛሬው እለት መግባት አትችሉም ብሎ ከልክሏቸዋል:: ተማሪዎቹም በአሁን ሰዓት ከግቢ ውጭ ናቸው::

©️ EHEMSU

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 16:16


መቱ በደሌ ••• ተደገመ!

ዛሬ የWelcome ፕሮግራም አዘጋጅተው ደስታቸውን ገልፀዋል:: ኒቃቢስቶችም በዝተዋል ብለዋል:: ከዚያ ባሻገር የኦርቶዶክስ ወገኖቻችንም ከዚህ በፊት ይከለከሉት የነበረውን ነጠላ በእነርሱ ሳቢያ ለብሰው በነፃነት መንቀሳቀስ እንደጀመሩ ነግረውናል::

አልሐምዱሊላህ ••• ፍትሕ የሁላችንም ነች!

NB:- በደሌ ላይ በቅርብ ለአመታት ሲከለከል የነበረውን ኒቃብ ታግለው አስከብረዋል::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 16:06


በሮች ሁሉ የተዘጉ ቢመስል እንኳ መውጫ በርን ፈልግ ••• አንድ ይኖራል:: መንገዶች ሁሉ የጠፉ ቢመስልም መጓዣ መንገድን ፈልግ ••• በእርግጥ አንድ ይኖራል:: ከፍ ለማለት የምትጨብጠው ገመድ የጠፋ ቢመስል እንኳ ፈልግ ••• የእውነት አንድ አይጠፋም:: there is always a way habibi.

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 15:26


ለእኔም ሆነ ለሌሎች ወዳጆቻችሁ ቁርዓንም ሆነ ሌላ ስጦታ መስጠት ከፈለጋችሁ በተመጣጣኝ ዋጋ አለን ብለዋል::

ቻናላቸውን https://t.me/collection34 ተቀላቀሉ:: ስጦታም ተሰጣጡ::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 14:11


ለፈጣን መልሳችሁ አመሠገንኩ ••• የነበሩት አለቁ:: በአላህ ፈቃድ በሌላ ዙር እንገናኝ ይሆናል::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 12:18


አልገደሉትም አልሰቀሉትም - ዘመቻ 2!

እስልምናን ማጥናት ለሚፈልጉ የሌላ እምነት ተከታይ ተማሪዎች ቅን ልቦች በሰጡት ልገሳ እስካሁን የኡስታዝ ወሒድን "አልሰቀሉትም አልገደሉትም!" መፅሐፍ በተለያዩ የሀገራችን ዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ ተማሪዎች ይደርስ ዘንድ 13 መፅሐፍትን ሰጥተናል:: አሁንም ጥቂት መፅሐፎች አሉና የሚያነቡ እስልምናን ማወቅ የሚፈልጉ ተማሪዎች ካሉ inbox ላይ @MOHAMMADAMMINM አሳውቁኝ::

ጭማሬ:- በመሠል ኸይር ስራ ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ኸይር ፈላጊ ወዳጆቼ ካላችሁም inbox ላይ አሳውቁኝ::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 10:51


ጥምቀት ነው ••• ተማሪዎች ስትንቀሳቀሱ መታዎቂያ መያዝ አትርሱ ••• ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው Videoዎች በቅርብ ካሉ ወደ ሚስጢር ቦታ አዛውሯቸው ••• በዓሉ እስኪያልፍ ጥንቃቄ አይለያችሁ::

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 09:47


ሰለመች!

በአዲስ አበባ ት/ቤቶች በነበረው የኒቃብ ክልከላ "ኒቃብ ለምን ተከለከለ? ኒቃብ ምንድን ነው? እስልምናስ ምንድን ነው?" በሚል ተገፋፍታ እስልምናን ማጥናት የጀመረች ተማሪ የሆነች እህት ትላንት እስልምናን ተቀበለች::

እስልምናን ለማጥፋት ሲሞክሩ ለሌሎች የእስልምናን በር ይከፍታሉ ••• አልሐምዱሊላህ ••• አላህ ፅናቱን ይስጣት!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 07:57


"ተንኮል እና ሸር ለጤናም ለሪዝቅም ጠንቅ ነው!"

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 07:41


"ዙልም የመከራ እናቱም አባቱም ነው።" - KH Abate

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 07:37


እናት አባቱን ጠርቶ "ልጃችሁን ልገድል ነውና ኑ እዩ!" በማለት ገደለው:: ይህ ተቀርፆ ያየነው ነው:: ያልተቀረፀስ ምን ያክል ይሆን? ይህ በአንድ ቦታ የተከሰተ የሚከሰት ሳይሆን በሀገራችን የተለያዩ ቦታዎች እየተከሰተ ያለ ነው:: መተዛዘን ጠፍቷል:: ጭካኔ ነግሷል:: ጭካኔም እንደ ፅድቅ ተቆጥሮ በጀብደኝነት ይሰራጫል::

እና በዚህ ልክ ሆነን መሬት ብትውጠንስ ምን ይደንቃል? አላህስ እሳት ቢያዘንብበን ምን ይገርማል? አላህ መልካም ሰሪዎችን ያብዛ:: መጥፎዎቹን ይቅጣ::

ያሰላሙ:- ሰላምን ስጠን!

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 07:05


በሰቆጣ ከአንድ ግለሰብ የተገኙ የውሐ ቆጣሪ እና መክፈቻዎች ናቸው:: አሳዶ ይሰርቃል ይላል ዜናው::

••• ኑሮ ከፍቷል:: እና ደግሞ ካምፓስም ሻወሩ ሁላ መክፈቻ የሌለው መሰል መቅሰፍት አጋጥሞት ይሆን? በተለይ FBEዎች ....?

@MohammadamminKassaw

Mohammedamin Kassaw

18 Jan, 04:13


እለታዊ ማስታዎሻ - 336

"وَقَالُوا الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي أَذْهَبَ عَنَّا الْحَزَنَ ۖ إِنَّ رَبَّنَا لَغَفُورٌ شَكُورٌ

ይላሉም «ምስጋና ለእዚያ ከእኛ ላይ ሐዘንን ላስወገደልን አላህ ይገባው፡፡ ጌታችን በጣም መሓሪ አመስጋኝ ነውና፡፡" [35:34]

@MohammadamminKassaw

1,274

subscribers

2,218

photos

215

videos