🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦 @fozuofficial Channel on Telegram

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

@fozuofficial


"በጊዜያቱ እምላለሁ ፤ ሰው ሁሉ በእርግጥ በኪሳራ ውስጥ ነው ፤ እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት ፥ በእውነትም አደራ የተባባሉት ፥ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ"
ሱረቱል ዐስር፦(1፥3)

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦 (Amharic)

አገልግሎት የሚጀመረውና ርዕሶች የሚሰራው የማኅበረሰብን እናስቆጣጠስ እንዳለው በአፍሪማቹ የተሳለው '🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦' ትምህርት እንዲሆኑ የሚመረጡ በተለያዩ ቁስል የተመረጡትን ያለውን የፍላሞች መምሪያ አንቀሳቅስልታለች። የመሪጋችን መዝገብን እና ውበት እንዲሆን በመሆን የሚጨምርና የሚያደምጥ ነገርዎን እንለዋለን። '🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦' ትምህርት በበሽታዎ እንዲሰማና መልካም ምንጮቻችንን እንደህምሪ መሳሪያ አያድርግም። ስለዚህ እንደ '🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦' ትምህርት ስለመጣበቅና ስለማመን እና ሌለ ማስፈርሽን ለማድረግ አስፈላጊ ይሆናል። የእንቅስቃሴ ትምህርት ለመቸም ከፈለገኸን የመሰረተ ስልጠና የሆነው ባለአኳይ ሥራ እንደሆነ ማለት ነው።

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

17 Jan, 14:56


⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው

አስር ( 🔟 )

ጥሩ! በአንድ ሰው ላይ ሁለት ምስክሮች ቢመጡ መግደሉን ለመመስከር ይህ ሰው
ለመግደሉ ሁሉም ማህበረሰብ የግድ በአጠቃላይ መስማማት አለበት! ማለቴ እከሌ እከሌን ገድሎታል ብሎ በእከሌ ላይ ለመመስከር ሁሉም ማህበረሰብ የግድ በአጠቃላይ መስማማት አለበት! ዳኛው አንድም በዲያ (በካሳ ክፍያ) ወይም በቂሷስ (በማመሳሰል እርምጃ) ላይ በአላህ ህግ መዳኘት ግዴታ አለበት፡፡ የአላህን ሸሪዓ ተፈጻሚ ማድረግ አለበት፡፡ ሙብተዲዕን ሙብተዲዕ ከማለት በጣም አደጋ በሆነው በዚህ ጉዳይ ላይ ሁሉም መስማማት መስፈርት ነው!? እነዚህ ሙመይዓ ፣ የባጢል ባለቤቶች ፣ የተንኮል ተጣሪዎች ፣ እንደሚባለው በደፈረሰ ውሃ አዳኝ ናቸው፡፡ ይህን የተበላሽ ንግግራቸውን አትስሙ፡፡ አንድ እውቀት ያለው ዓሊም ሲተች - ባረከሏሁ ፊከ - ይህን ትችት መቀበል ግድ ነው፡፡ አንድ ፍትሀዊ የሆነ ፣ ችሎታ ያለው ዓሊም ከተቃወመ ደግሞ የሁለቱ ንግግር ይጠናል ፣ ትችቱም ውዳሴውም ይታያል፡፡ ትችቱ የተተነተነ እንዲሁም ግልጽ ከሆነ የሚያወድሱት ቁጥራቸው ቢበዛም ፣ ትችቱ ከውዳሴው ይቀደማል፡፡ አንድ ዓሊም አስር ወይም አምሳ አሊሞች - ውጫዊ ገጽታን በማየትና በመልካም በመጠርጠር
ምንም አይነት ማስረጃ ሳይዙ አንድን ግለሰብ ቢያወድሱ -ስለዚህ ሰው የተተነተነ ትችት ይዞ የመጣው ሰው- ማንም ቢቃወምም - ትችቱ ይቀደማል፡፡ ምክንያቱም ተችታ ከእርሱ ጋር ማስረጃ አለ ፤ ማስረጃ ደግሞ ሊቀደም ይገባዋል፡፡ ምድርን የሚሞላ ሰው ቢቃወም ማስረጃን እናስቀድማለን ! ማስረጃው ከእርሱ ጋር ሆኖ የምድር ባለቤቶች ሁሉ ቢቃረኑት ፣ ምንም ይሁን ምን ሀቁ ከእርሱ ጋር ነው፡፡ ጀማዓ ማለት ደግሞ ብቻውን እንኳ ቢሆን በሐቅ ላይ የሆነ ሰው ነው፡፡ አንድ ሰው በሱና ከሆነ ሙብተዲዕ የሆኑ የሁለት ወይም የሶስት ከተማ ሰዎች ቢቃረኑት ሀቁ ከእርሱ ጋር በመሆኑ ፣ ከሌሎች ጋር ያለው ባጢል በመሆኑ መረጃ ይቀደማል፡፡ ሀቅን
ማክበር ግዴታችን ነው ፤ ማስረጃን ማክበር ይገባል፡፡

አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

(قُلْ هَاتُوا۟ بُرْهَٰنَكُمْ إِن كُنتُمْ صَٰدِقِينَ)

“እውነተኞች እንደሆናችሁ አስረጃችሁን አምጡ” በላቸው፡፡ (አል በቀራህ፡111)

(وَإِن تُطِعْ أَكْثَرَ مَن فِي الْأَرْضِ يُضِلُّوكَ عَن سَبِيلِ اللَّهِ ۚ )
   
“በምድርም ካሉት ሰዎች አብዛኞቹን ብትከተል ከአላህ መንገድ ያሳስቱሃል፡፡”
(አል አንዓም፡116)

ማስረጃ አልባ የቁጥር ብዛት ዋጋ አይስሰጠውም፡፡ ትንሽ ቁጥር ካላቸው ውጭ የምድር ሰው በአጠቃላይ በውሸት ቢሰባሰብ ማስረጃ አልባ ከሆኑ ግምት
አይሰጠውም፡፡ አንድ ወይም ትንሽ ቁጥር ያላቸው ሰዎች እንኳ ተቃራኒ ቢሆኑም
ከማስረጃ ጋር እስከሆነ ድረስ ሀቅን በማወቅ ፣ እርሱን አጥብቃችሁ በመያዝና
ሐቅን በመቀበል አላህን ፍሩ አላህን ፍሩ !! አላህ ለሁሉም ሀቁን ይግጠም!”

(شريط المنهج التميعي وقواعده للشيخ
حفظه هللا)                                      

-አሁንም ተጠየቁ፡ “አንድ ግለሰብ ከፊሉ ሙብተዲዕ ፣ ከፊሉ ደግሞ ሙብተዲዕ
አይለውም አንዳንድ ተማሪዎች ሙብተዲዕ ያላሉትን ሰዎች ንግግር ይከተላል፡፡
እርሱን ማውገዝ ይበቃልኛል?”
መልስ፡ “በርካታ ወጣቶች ሀቅን ከማወቃቸው ጋር ይህ በአሁኑ ሰዓት በአካባቢያችን የሚገኝ ፈተና ነው፡፡ ባረከሏሁ ፊከ በእርግጥ ረዘመች! በእርግጥ ረዘመች! አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት ወይም ለመተቸት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት አይደለም፡፡ ይልቁንም ለመተቸትም ይሁን ለማወደስ የአንድ ሰው ንግግር በቂ ነው፡፡
ጀማዓዎች ከተቹት ወይም ሙብተዲዕ ካሉት ሀቅን ለሚፈልግ ሰው በቂው ነው፡፡
ዝንባሌውን የሚከተለው ሰው ከሆነ ግን በሸረሪት ድሮች ይንጠለጠላል እንጅ
አንድም ነገር አይበቃውም፡፡ ሰዎች ይህን ትችት የሚባለውን ነገር አላወቁትም፡፡
ሰዎች ተጠምደዋል፡፡ ሰዎች ይህ ሰው የተተቸ መሆኑን መተቸት የሚገባው
መሆኑንም ተምረዋል ፣ አውቀዋል፡፡ ምክንያቱም ውሸታም በመሆኑ ፣ ዑለሞችን በመዝለፉ ፣ የሰለፎችን መንሐጅና ባለቤቶች በመቃወሙ ፣ የተበላሹ መሰረቶችን በማበጀቱ ፍትሀዊነቱ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ይህን ሁሉ አውቀዋል፡፡ ከምክር በኋላ አይዘንም ይላሉ፡፡ መከሩ ፣ አብራሩ ይህ ሰው እምቢ አለ፡፡ እርሱን ሙብተዲዕ ለማለት ተገደዱ! በዚህ አይነት የቀረ በሸረሪት ድሮች የሚንጠለጠል ሰው ምንድን ነው ምክንያቱ? (ወላሂ እከሌ አወድሶታል!) (ወላሂ በሙብተዲዕነቱ ዑለሞች አልተስማሙም!?) ይላሉ! ሙብተዲዕ ያላሉ ሰዎች በሁለት ይከፈላሉ፡ አንደኛው ያልተማሩ ሰዎች ናቸው ፣ እነርሱም ምክንያት ይሰጣቸዋል፡፡ ሁለተኛው የተማሩ ፣ ለውሸት የሚከላከሉ ናቸው፡፡
ከእነርሱ ዘንድ ያለውን ውሸት ምን እንደሆነ ያውቃሉ ፣ እምቢ ብለው ለዚህ
ሙብተዲዕ መከላከል እንጅ ሌላ አላማ የላቸውም፡፡ እነዚህ ምንም ዋጋ አይሰጣቸውም፡፡ ዝም ባዮች ዝምታቸው መረጃ አይሆናቸውም፡፡ እነዚያ ከሰውዬው ላይ ያሉ ነገሮችን
ሁሉ የተቹ ፣ በሚገባው ያብራሩ መረጃው ከእነርሱ ጋር በመሆኑ ከዚህ በፊት
እንደጠቆምኩት ሐቀኛ ለሆነ ሰው ከአላህ -ዓዘ ወጀለ- ዘንድ ምንም አይነት
ምክንያት የሌላቸው ለሆኑትና በሸረሪት ድሮች ላይ ለሚንጠለጠሉት ሳይሆን (መረጃው ከእነርሱ ጋር የሆነውን) ሐቅን መያዝ ግዴታ አለበት፡፡

✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር)

✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

14 Jan, 07:55


🥳 ☪️ 🥳

🔡🔡አዲስ ዜና...🔡🔡

ዘገየንባችሁ ይቅርታ🌷

የዘገየነው ምክንያቱስ😇?

1ኛ ለሚወጣ ሰዉ ሽልማቱ ከፍ ብሏል።

መቼም የማይለወጥ ለአማኞች መዳኛ ሆኖ በእዝነቱ ነብይ የተላከን የረበል ዓለሚንን ቃል በሽልማት እናበረክታለን 📖📖


ታድያ ማነዉ ይሄን መዳኛ ተሸላሚ የሚሆነው🎈🎈💌?

ቁርኣንን አንብቡ አነሆ ቁርኣን የቂያም ቀን ለሳሒቡ(እሱን ለሚያነበዉ ሰዉ ) አማላጅ ሆኖ ይመጣልና🤲🦋🕊


ተሳተፉ አድድ አድርጉ የጌታቹንም ቃል ተሸለሙ⭐️🏆


2ኛ ለሚወጣ ምርጥዬ የከሰል እጣን ማጬሻ💥🎁

3, የካርድ ሽልማት 100 ወይም ፓኬጅ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

07 Jan, 11:30


⚠️ጌታ ተወለደ

በዚህ ቆሻሻ ቃል ሰማይ እና ምድር አለመለያየታቸው
የላቀውን አምላክ የታጋሽነት ጥግ ትልቅ ማሳያ ነው።

እንጂማ 👉

አምላክ በማህፀን ተወልዶ ያድናል
ለሰው ልጅ መድህን ቤዛ ሆኖ አልፏል።
እያለ እሚዘሙት ሲያሻውም የሚሰክር
ቂላቂል የሰው ፍጡር መቼ ይኖር ነበር።

أبو نحلا


https://t.me/abunehla

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

02 Jan, 15:56


⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው

ክፍል ዘጠኝ (9⃣)

“የተተነተነ ትችትን እንዲሁም አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት
መስፈርት ነው” በማለት ሙመይዓዎች የሚያሰራጩትን ብዥታ ከንቱ የሚያደርግ የሱና ዑለሞች ንግግር የሚወሳበት ርዕስ
1. ሸይኽ አልዓላማ አልሙሐዲስ ሙሐመድ ናሲሩ ዲን አልአልባኒ I “የተተነተነ ትችት ከውዳሴ እንደሚቀደም” ፣ ይህ ህግና መርሆ ደግሞ ከሙሀዲሶች ዘንድ ስምምነት ያለበት መሆኑን በሚከተሉት በሰነዶች እና በመትኖች ላይ ተኽሪጅ ፣ ተህቂቅ እና ከላም በስፋት ባለባቸው በተለይም በ ሲልሲለቲ ሶሂሃ ፣ አድዶዒፋ ፣ ኢርዋእ ፣ ሶሂህ አቢዳውድ ፣ ዶኢፍ አቢዳውድ ፣ እና ሌሎችም ኪታቦች በቋሚነት ጽፈዋል፡፡
- የተተነተነ ትችትን አለመያዝ የጀርህና ተዕዲል እውቀትን ባዶ ማስቀረት እንደሆነ
አልባኒ (አድ' ዶኢፋ 7/293) በተባለው ኪታባቸው ላይ ገልጸዋል፡፡
- “ዋቂዲይ” የተባለውን ግለሰብ በተመለከተ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- እርሱን ታማኝ በማለት ባዘነበሉ ሰዎች አትሸወድ፡፡ ምክንያቱም “የተተነተነ ትችት
ከውዳሴ ይቀደማል” የሚለውን ሙሐዲሶች የተስማሙበትን ህግና መርሆ ተቃርነውታል፡፡ (ሲልሲለቱል አሃዲሲ አድዶኢፋ ወልመውዱዓ (2/146))፤
((አልቃኢደቱ አልሙተፈቅ አለይሃ ኢንደ አልሙሀዲሲን)) በሚባሉ ኪታቦች
ንግግራቸውን ተመልከት፡፡ አሁንም በተጨማሪ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “ትችት ከውዳሴ እንደሚቀደም በሙስጦለህ (በሐዲስ ዕውቀት) ተረጋግጧል በተለይም ከሰበቡ መብራራት ጋር ተቆራኝቶ ከመጣ፡፡” (ኢርዋእ አልገሊል ፊ ተኽሪጅ አሃዲሲ መናሪ አስሰቢል ፡ (1/209)) አልባኒ የዓብደላህ ብን ዓብዲረህማን አጧኢፊይ ታሪክን አስመልክቶ የኑቃዶችን
(የሐዲስ አጣሪዎችን) ንግግር ወስዶ አቅርቧል፡፡ ከዚያም የሚከተለውን
ተናግሯል፡- ከፊሎቹ ታማኝ ነው ብለውታል! ነገር ግን እነዚያ መሪዎች ደካማ ብለው የወሰኑትን ውሳኔ በመቃረኑ እነርሱ ታማኝ ማለታቸው ሚዛን የለውም በተለይም የተተነተነ ትችት ከውዳሴ ይቀደማልና፡፡ (ዶዒፍ አቢ ዳውድ አልኡም (2/70))
- አልባኒ ስለ “ዋቂዲይ” የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “ትችት - በተለይም
የተተነተነ ከሆነ - ከውዳሴ እንደሚቀደም በሐዲስ እውቀት የተረጋገጠ ጉዳይ
ነው፡፡ አንዳንድ ለእርሱ ጎጠኞች የሆኑና ከሀነፍያ የሆኑ ሌሎች ሰዎች ለመጽሐፎቹ
ተቅዲም በማድረጋቸውና ታማኝ በማለታቸው አትሸወድ፡፡ ምክንያቱም እርሱ ከሙሐዲሶች ዘንድ በታወቀው -ግልጽ የሆነው ትችት ከውዳሴ ይቀደማል
ከሚለው- ህግ ጋር ይጋጫል፡፡” (ሲልሲለቱል አሃዲሲ አድዶዒፋ ወልመውዱዓህ ፡ (1/13))
የዚህ አይነት በእርሳቸው ኪታብ I በጣም በርካታ ነው፡፡ ሁሉም መጽሐፎቻቸው
በዚህ ሰለፍይ በሆነ ህግና መርሆ ላይ የተመሰረቱ ናቸው፡፡ ሙመይዓ ካልሆነ በቀር ይህን ህግ የሚተች የለም፡፡
2. ሸይኽ አልዓላማ አልሙሐዲስ ረቢዕ ብን ሀዲ አልመድኸሊ ሸይኽ ረቢዕ አልመድኸሊ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “በአሁኑ ሰዓት በዚህ ፈተና ውስጥ ከአንዳንድ ሰለፍዮች ዘንድ ሳይቀር አስቸጋሪ የሆነው እነርሱን የሚቃረናቸው
አካል ከእርሱ ጋር ማስረጃ ቢኖረው እንኳ “እከሌ ይህን አለ” ፣ “እከሌ ይህን
አለ!”.. የሚለው አመለካከት ነው፡፡ ይህ የጥመት ባለቤቶች መንገድ ነው፡፡ የሰለፎች ጎዳና ሰውየው ደረጃው የፈለገው ቢሆን በዚህ አካሄድ አያምንም፡፡” አንድ ሰው መረጃ በሌለው ንግግር ፈትዋ ቢሰጥ ወይም ቢናገር እርሱን እናከብረዋለን ፣ ምክንያት እና የመሳሰሉ ነገሮችን እንሰጠዋለን እንጅ ንግግሩ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
ነገር ግን ማንኛውም ከረሡል صلى الله عليه وسلم ውጭ ያለ ሰው ንግግሩ ተቀባይነት ሊያገኝ ወይም ሊመለስበት ይችላል፡፡ ከእርሱ ጋር ከአላህ ወይም ከረሡል صلى الله عليه وسلم ማስረጃ ያለውን ሰው ንግግሩ ሊመለስበት አይገባም …” (መጅሙዕ ኢራኢቅ ፡ ገጽ 397)
- ሸይኽ ረቢዕ -ሀፊዞሁሏህ- “የቢድዓ ባለቤቶችን ለመተቸት በዘመኑ ያሉ ሰዎች
መስማማት መስፈርት ነው? ወይስ አንድ ዓሊም ብቻ ይበቃል?” የሚል ጥያቄ
ተጠየቁ፡፡
መልስ፡-“ይህ ቆሻሻ የሆነው ሙመይዕ ህግና መርሆ ነው - ባረከሏሁ ፊኩም -
በየትኛው ዘመን ነው ለዚህ ጉዳይ የዑለሞች ስምምነት መስፈርት የተደረገው? ለዚህ መስፈርት ምንድን ነው መረጃው? በአላህ ኪታብ ውስጥ የሌለ መቶ መስፈርት እንኳ ቢሆን መስፈርቱ ብልሹ ነው፡፡ ኢማም አህመድ ብን ሐንበል I ወይም የህያ ብን መዒን I ሙብተዲዕን ቢተቹ “በዓለም ያለ የሱና መሪ ሁሉ ሙብተዲዕ መሆኑን ሊስማሙበት ግድ ነው እላለሁ!!! ኢማም አህመድ ይህ ሰው ሙብተዲዕ ነው ካሉ ሁሉ ነገር አበቃ ፣ ኢማም አህመድ ይህ ሰው ሙብተዲእዕ ነው ካሉ ሁሉም ሰው ለእርሱ ያስረክባል ፣ ከጀርባው ይጓዛል፡፡ ኢብን መዒን I፡ ይህ ሙብተዲዕ ነው ካለ አንድም ሰው የሚጨቃጨቀው የለም፡፡ ሁሉ መስማማት አለበት የሚለው መስፈርት በማንኛውም ሸሪዓዊ አህካም ሊሆን የማይችል እብለት ነው፡፡

✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር)

✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

30 Dec, 05:32


⭕️ ትውልድን እያደናቀፉ የምን ማሻገር ነው?

" እናሻግራችሁ ሲሉ አንፈልግም እኛው እራሳችን እንሻገራለን ማለት አይከፋም"

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

29 Dec, 16:19


⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው
ክፍል ስምንት (8⃣)

“ያፈነገጠ አላህ እሳት ውስጥ ይከተዋል ፣ ማፈንገጥ ማለት ሐቅን የተቃረነ መሆኑን ተቃራኒዎች አላወቁም፡፡ አንዱ ብቻ ቀርቶ ሁሉም በእርሱ ላይ ቢሆን እነርሱ አፈንጋጭ ናቸው፡፡” በኢማም አህመድ I ዘመን ትንሽ ሰዎች ሲቀሩ ሁሉም አፈንግጦ ነበር፡፡ እነርሱም ጀማዓዎች ሆኑ፡፡ ኢማም አህመድ ብቻውን ነበር ጀማዓ የነበረው፡፡ ያንጊዜ የነበሩ ቃዲዎች ፣ ሙፍቲዎች ፣ መሪዎችና ተከታዮቻቸው አፈንጋጮች ናቸው፡፡ ሰዎች ይህ ነገር ለአቅላቸው ሲከብዳቸው የሚከተለውን ለመሪው ነገሩት፡ “የሙእሚኖች መሪ ሆይ! ቃዲዎችህ ፣ ሀላፊነት የሰጣሀቸው ባለስልጣኖችህ ፣ ፉቀሃዎችህ ፣ ሙፍቲዎችህ ሁሉም በአጠቃላይ ትክክለኛ ሳይሆኑ አህመድ ብቻውን በሀቅ ላይ ይሆናል?” ለዚህ ነገር እውቀቱ አልሰፋውም፡፡ ከረጅም እስር በኋላ በአለንጋና በቅጣት መቅጣት ጀመረ፡፡ ላኢላሃ ኢልለሏህ ሌሊቱን ከትናት ምሽት ጋር ምን አመሳሰለው!! አህለሱና ወልጀማዓዎች ጌታቸውን እስኪገናኙ ድረስ
ቀደምቶቻቸው ባለፉበት ለመጓዝ አስፈሪ መንገድ ነው፡፡ የእነርሱ ምትኮችም
ይጠባበቋታል፡፡

مِنَ الْمُؤْمِنِينَ رِجَالٌ صَدَقُوا مَا عَاهَدُوا اللَّهَ عَلَيْهِ ۖ فَمِنْهُمْ مَنْ قَضَىٰ نَحْبَهُ وَمِنْهُمْ مَنْ يَنْتَظِرُ ۖ وَمَا بَدَّلُوا تَبْدِيلًا ﴿٢٣﴾

ከአማኞቹ በእርሱ ላይ ለአላህ ቃል ኪዳን የገቡበትን በእውነት የፈጸሙ ወንዶች አልሉ፡፡ ከነርሱም ስለቱን የፈጸመ (ለሐይማኖቱ የተገደለ) አልለ ፤ ከነርሱም ገና የሚጠባበቅ አልለ፡፡(የገቡበትንም ቃል) መለወጥንም አልለወጡም፡፡ ”  ( አል አህዛብ፡ 23) ወላሃውለ ወላቁወተን ኢልላ ቢላሂ አልዓልይል ዓዚም ( ኢዕላም አልሙቂዒን ዓን ረቢል ዓለሚን ፡ 3/309-310)
እኔም አልኩ፡ ይህን ጉዳይ  ማለትም “አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው” የሚለው አመለካከት አዲስ ፈሊጥ መሆኑን ወደቀደምቶችም ይሁን ቀጥለው ወደመጡ አህለሱና ዑለሞች ንግግር በመመለስ የተገነዘበ ሰው ፣ ሙመይዓንና በጥቅልም ይሁን በዝርዝር እነርሱ የሚጓዙበትን ቆሻሻ መንሐጅ (ጎዳናቸውን) በአላህ ፈቃድ ይገነዘባል፡፡
- በመቀጠል የሱና ዑለሞችን ንግግር አቀርባለሁ፡፡ በተጨማሪ ሙመይዓዎች
ለፈጠሩት “አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት
ነው” ለሚለው አዲስ መርሆ የሱና ዑለሞች የሰጡትን መልስና የበፊቶችም ይሁኑ የኋለኞቹ አዲስ ሙሙዓዎች የሱና ዑለሞችን መቃረናቸውን ግልጽ አደርጋለሁ፡፡ የሐዲስ እውቀት ሙጀዲድ የሆኑት ሸይኽ አልአላማ አልሙሐዲስ ሙሐመድ ናሲሩ ዲን አልአልባኒ ፣ በትክክል የጀርህና ተዕዲል ሰንደቅ አላማ ተሸካሚ የሆኑት ሸይኽ አልአላማ ረቢዕ አልመድኸሊ ፣ የየመን አገር ሙሐዲስ የሆኑት ሸይኽ ሙቅቢል አልዋዲዒ ፣ የደቡብ ግዛት ሙሐዲስና ሙፍቲ የሆኑት ሸይኽ አህመድ ብን የህያ አንነጅሚ ፣ የኢትዮጵያ ሙፍቲ የሆኑት ሙሐመድ ሸይኽ ሙሐመድ ብን ዓሊ አደም
አልኢትዮጵይ ፣ ሸይኽ አልዓላማ ዑበይድ አልጃቢሪ ፣ አሸይኽ አልዓላማ ሷሊህ
አልፈውዛን እና ሸይኸ አልዓላማ ሙሐመድ ብነ ሀዲ አልመድኸሊ “ተንትኖ የተቸ አወዳሽ ከሆነው ሰው መቀደሙ ግዴታ እንደሆነ” ሁሉም ተስማምተዋል፡፡ “በትችት እና በተብዲዕ ላይ የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው” ማለት በቀደምት ሰለፎች መንሐጅ መሰረት የለውም፡፡ ይልቁንም ፣ ወደ ማስረጃ ፊታቸውን የማያዞሩ ፣ አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው በሚሉ አልዓላማ ተቃራኒ በሀዲስ ዝግጅት
፣ በጀርህ በተዕዲል ሙያ ፣ በአጠቃላይ በሐዲስ ሙያ የሙእሚኖች መሪ የሆኑት
ሙሐመድ ኢብን ኢስማዒል አልቡኻሪ “በተረጋገጠ ማስረጃ ካልሆነ በቀር
የአውሪታው ፍትሀዊነት ውድቅ አይደረግም” በሚለው አመለካከት የሐዲስ ባለቤቶች ስምምነት እንዳላቸው መንቀሉ ተዘግቧል፡፡ ቡኻሪ Iየሚከተለውን ተናግሯል፡- “ኢብራሒም በሸዕብይ ዙሪያ ፣ ሸዕብይ ደግሞ በኢክሪማ ፣ ከእነርሱ በፊት ባሉትም ዙሪያ ተነገረ ተብሎ በሚወራው የአንዳንድ ሰዎች ወሬ እንዲሁም የሰዎችን “ዒርድ” እና “ነፍስ” በሚመለከት የአንዳንድ ሰዎችን ተእዊል (ትንታኔ) በተመለከተ በርካታው ሰው ነጃ (ነጻ) አይወጣም፡፡ በእንደዚህ አይነቱ ነገር የእውቀት ባለቤቶች ፊታቸውን አላዞሩም፡፡ በማስረጃና በማብራሪያ ካልሆነ በቀር ፍትሀዊነታቸው ውድቅ አልተደረገም፡፡ በዚህ ዙሪያ የመጣው ንግግር ብዙ ነው፡፡” (አልቂርአቱ ኸልፈል ኢማም ሊል ቡኻሪ ፡ ገጽ 39)
- ከሙመይዑ ኸድር ከሚሴ ዘንድ ፡ መሰረቱ ሱና ለሆነ ሰው “የፈለጋችሁትን ስሩ በእርግጥ ለእናንተ ምሬያለሁ” እንደተባለው አምሳያ ፣ መሰረቱ ሱና የሆነ ሰው በተረጋገጠ ማስረጃ ቢሆን እንኳ ከሱናነቱ ንቅንቅ አይልም ፣ እንዴውም (እነርሱን ነጻ የሚያደርጉ) ምክንያቶችን ቆጥረን ልንደረድር ይገባል፡፡ ለእርሱ ስንል
መወዛገብ የለብንም!! የሚል አቋም ነው፡፡
ከማህይምነትና ዝንባሌን ከመከተል በአላህ እንጠበቃለን፡፡ መሰረቱ ሱና ሆኖ ግልጽ ከሆነ ቢድዓ ላይ የወደቀ ሰው ምንድን ነው ብይኑ?
ለምሳሌ ቁርኣን ፍጡር ነው ያለ ሰው ፣ ሶሃባን የተቸ ሰው ፣ ለቢድዓ ሰዎች
ጥብቅና የቆመ? ከማስረጃ እና ብዥታን ከማስወገድ ውጭ ሌላ ምክንያት ሰለፎች እንደዚህ ነበሩ? ቁርኣን ፍጡር ነው ብሎ የሚል አስገዳጅ በመጣበት
የፊትና ዘመን የሱናን ሰንደቅ አላማ ተሸካሚ የነበረው ኢማም አህመድ መሰረቱ ሱና የሆነ መሰረቱ ሱና ያልሆነ እያለ ይከፋፍል ነበር? ኢማም አህመድ በቁርኣን ዙሪያ (አቋም ግልጽ ባለማድረግ) የቆመውን የዕቁብ
ብን ሸይባንን ወደመሰረቱ (ሱንይነቱ) ፊቱን ሳያዞር “የዝንባሌ ባለቤት ፣
ሙተበዲዕ” በማለት ነበር የተናገረው፡፡
- ኢብን አልጀውዝይ I የሚከተለውን ተናግሯል፡- ኢማም አቡዓብዲላህ አህመድ
ብን ሀንበል ሱናን በመያዝና ቢድዓን በመከልከል ብርቱ ከመሆኑ የተነሳ ከምርጥ ጀማዓዎች ዘንድ አንዳንድ ሱናን የሚቃረን ነገር ሲከሰት ይናገር ነበር፡፡ ንግግሩ ለዲን ባለው ተቆርቃሪነትና ምክር ተደርጎ ይወሰድ ነበር፡፡ መናቂብ አልኢማም አህመድ ፡ ገጽ ፡235)


✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር)

✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

28 Dec, 05:06


⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው
ክፍል ሰባት (7⃣)

ኡስታዝ ዶክተር አህመድ ባዝሙል የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
“ሀለብይ ከሚያጸድቃቸው ውድቅ ከሆኑ ህግና መርሆዎች መካከል “የተተነተነ
ትችትን መመለስ ፣ ለትችት የኡለሞች ስምምነትን መስፈር ማድረግ” ናቸው፡፡
የሰለፎች መንሐጅ የሆነውን የተተነተነን ትችት (ከውዳሴ ማስቀደም) ፣ የቢድዓና
የዝንባሌ ባለቤቶችን ማኩረፍ የሚያፈርስ እና ዲናቸውን በእነርሱ ላይ ለማምታታት
ሰለፍዮች ሶፍ ውስጥ ቢድዓን እና ሙብተዲዖችን የሚያስገባ በር ለመክፈት አደገኛ
ህግ መሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም፡፡” (ሲያነቱ ሰለፍይ ሚን ወስወሰቲ ወተልቢሳቲ ዓልይ አልሀለብይ ፡ ገጽ 92
ዶክተር አህመድ ባዝሙል)
ዶክተር ዓብዱል ሀሚድ አልሀዷቢ የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
“ይህ- ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነትን መስፈርት ማድረግ - ቀጥተኛ
የሆነውን የዲን መሰረት እርሱም ወላእና በራእን (ለአላህ ብሎ መውደድና
መጥላት) የሚያፈርስ ፍጻሜዋ በተለያየንበት አንዱ ለአንዱ ምክንያት ይስጥ -
ወደሚለው የኢኽዋን መርሆ የሚመለስ- የአህለል አህዋ እና አህለል ቢድዓን ጎዳና
ከጋለቡ የተምይዕ የግርግር ባለቤቶች ካልሆነ በቀር የእውቀት ባለቤቶች የማያውቁት
የሚያስጠላና ውድቅ የሆነ ህግ ነው፡፡ ይህ “ከሌላው ጋር ያለው ውዝግባችን
በመካከላችን ላለው ውዝግብ ምክንያት አይሁን” ከሚለው የሐለብይ ህግ ጋር
ይመሳሰላል፡፡” ሐጅ አትተምይዕ አልኸለፍይ ፡ ገጽ 31-33) አብዱል ሀሚድ አልሀዷቢ ተቅዲም
ኡስታዝ ዶክተር አህመድ ብን ዑመረ ባዝሙል
እኔም አልኩ፡ ይህ ነው የቀድሞዎችም ይሁን አዲሶቹ ሙመይዓዎች በተለየ ሁኔታ
ዘወትር የሚወተውቱት፡፡ በተብዲዕና በትችት እንዲሁም በተተነተነ ትችት ዙሪያ
የማስረጃን አንገብጋቢነት በሙሓዶራቸው ሰምታችኋልን????
ተከልከል!(ነገሩ እንደዚያ አይደለም) ለማንኛውም ውዝግብ እና ልዩነት ከዲን ፣
ከዓቅል እና ከሙሩአ ትንሽ እንኳ ግንዛቤ ላለው ሰው ማስረጃው ዳኛ ከመሆኑ ጋር
እነዚህ ሶስት ሙመይዖች እና በእነርሱ ምህዋር የሚሽከረከሩት አቋም ከመቀየራቸው በፊት “ጀማዓ ማለት ብቻህን እንኳ ብትሆን ሀቅን የገጠመ ነው” የሚለውን የብን መስዑድን  ንግግር ያውቁ ነበር፡፡ “ማስረጃን ያወቀ ካላወቀው ይቀደማል” ፣
“ካራቋች አጽዳቂ ይቀደማል” ፣ “ማስረጃን የሀፈዘ ካላሀፈዘው ይቀደማል” የሚሉ ህጎችንም ያውቁ ነበር፡፡
ኢማም ብን አልቀይም I የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
ኑዓይም ብን ሀማድ የሚከተለውን ተናግሯል፡- “ጀማዓ ሲበላሽ ብቻህን እንኳ ብትሆን ጀማዓው ከመበላሸቱ በፊት በነበረው ሁኔታ ላይ መሆን አለብህ፡፡ ያን ጊዜ አንተ ጀማዓ ነህ” በይሐቅይና ሌሎችም አውስተዋል ከሐዲስ መሪዎች አንዱ የሚከተለውን ተናግሯል -ለእርሱ “ሰዋዱል አዕዞም” (ነጃ የምትወጣዋ ጀማዓ) ተወሳለት- የሚከተለውንም ተናገረ፡- “ሰዋዱል አዕዞም
ምን እንደሆነ ታውቃለህ? እርሱ ሙሐመድ ብን አስለም አጡሲዩ እና ባልደረቦቹ ናቸው፡፡”
“ሰዋዱል አዕዞም” እና ማስረጃ ተደርገው ሲቆጠሩ የነበሩ (የሐቅ) ተቃራኒዎች ሁሉ
ተሰረዙ፡፡ ጀማዓዎች ጁምሁሮች (አብዛኞቹ ዑለሞች) ሆኑ ፣ እነርሱን ለሱና መመዘኛ አደረጓቸው፡፡ (የሐቅ) ባለቤቶች በማነሳቸውና በየዘመኑ ፣ በየከተሞች ብቸኛ በመሆናቸው ምክንያት (ሰዎች) ሱናውን ቢድዓ ፣ መልካሙን መጥፎ አደረጉ፡፡

✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር) ት

✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

27 Dec, 08:35


ድብቁ የሙስሊም እህቶቻችን የእርቃን ፎቶ ንግድ!

ሰሞኑን ከአንድ የስራ ባልደረባዬ ጋር ስናወራ ዲጂታል መፅሄት ላይ የሠፈረ አንድ ጥናታዊ ፅሁፍ ላከልኝ።
ጸሀፊው ምንተስኖት ደስታ ይባላል በሥነ-ሕብረተሰብ (ሶሲዮሎጂ) ከሐረማያ ዩንቨርስቲ የተመረቀ ሲሆን በአሁን ሰዓት በስንቅ ዩዝ ኢኒሼቲቭ ፕሮጀክት ማናጀር ነው ጥናታዊ ፅሁፉም ቴሌግራም ላይ ቻናል ግሩፕ ከፍተው የታዋቂ ሴቶችን ወይንም የድሮ የዝሙት ጓደኞቻቸውን እርቃን ፎቶ እየለቀቁ ብር ስለሚያስከፍሉ የቻናብ ባለቤቶች ያትታል።

ለአንድ እርቃን ፎቶ ከ 3000- 6000 እንደሚያስከፍሉም በጥናታዊ ፅሁፉ ሰፍሯል። እኔን ቀልቤን የሳበኝ እና ከባልደረባዬ የሰማሁት የሙስልም እህቶቻችን ከዚህም በላይ ከፍ ያለ ዋጋ እንዳለው ነው። በእርግጥ ለማመን ቢከብደኝም በገበያው ብዙም ስለማይገኝ ይሁን ለሙስሊም እህቶች ያላቸው መጥፎ እሳቤ በውድ ዋጋ እንደሚቸበቸብ ለዚህ ዋነኛ ተጠቂዎች የአረብ ሀገር እህቶች እና የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እንደሆኑ ነው የሰማሁት።

በእርግጥ ግቢ ውስጥ በነበርንበት ሰአቶችም ይሁን ከግቢ ከወጣን በኋላ አንዳንድ ሽምግልናዎችን ታዝበናል። ከዛም አልፎ ህግ ደረጃ የደረሱም ነበሩ። ሽያጭ ደረጃ ይደርሳል የሚል ምንም አይነት ግምት አልነበረኝም።
በእርግጥ በሰላም ጊዜ ፍቅር ውስጥ በነበሩበት ጊዜ የሚላላኩዋቸው ልቅ ምስሎች ናቸው በኋላ በጠብ ጊዜ ህይወታቸውን የሚያመሰቃቅሉት።

ከሁሉም የከፋው ደግሞ. . .

🔴 እህቶቻችን በማያውቁት መንገድ አብረው ከሚኖሯቸው ሙስሊም ካልሆኑ እህቶች ወይንም ዲናቸውን ጠንቅቀው በማያውቁ ሙስሊም እህቶች ተቀርፀው የሚላኩ ምስሎች ናቸው። በተለይ ሙተነቂብ ሲሆኑ ደግሞ በካሜራ ያድኗቸዋል አሳልፈው ለባዕድ ወንድ ይሰጧቸዋል።

🟢 ይሁን እና ብዙ ኡዝታዞች እና መሻይኾች ይህንን ጉዳይ ዘርዘር አድርገው ህዝበ ሙስሊሙን ቢያነቁበት ባይ ነኝ።

መፅሄቱን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ

👇👇👇👇👇

https://concepthub.net/article/4

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

26 Dec, 19:17


🔷 ለጥንቃቄ

በቴሌግራም መረጃዎች እየተመዘበሩ እንደሆነ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር / ኢንሳ አሳውቋል።

ኢንሳ በዛሬው ዕለት በቴሌግራም መረጃዎች እየተመዘበሩ በመሆኑ ተጠቃሚዎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ሲል አሳስቧል።

ኢንሳ ብዙ የቴሌግራም አካውንቶች በተለያዩ ማስገሪያ (ፊሺንግ ሊንክ) አማካኝነት መረጃዎች እየተመዘበሩ እንደሆነ ገልጷል።

በመሆኑንም ከማንኛውም የቴሌግራም ተጠቃሚ (ከሚያውቁትም ሆነ ከማያውቁት) ግለሰብ ሊንክ ቢላክ መክፈት ተገቢ እንዳልሆነ እና ወዲያውኑ ማጥፋት እንደሚገባ አሳስቧል።

መረጃው የቲክቫህ ኢትዮዽያ ነው ።

https://t.me/bahruteka

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

26 Dec, 13:31


🟢አላህ ይጠብቀን

‏قال الإمام ابن كثير رحمه الله:

والذنوب والمعاصي والشهوات ،

تخذل صاحبها عند الموت مع خذلان الشيطان له“.

📙البداية والنهاية(9/179)

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

26 Dec, 10:09


ስለ ሙመይዓ

ሙብተዲዕን አትናገሩብን።

ለሙብተዲዕ ለስላሳ ለ ሰለፍዮች እሾህ ስለሚሆኑ ሰዎች።

ስለ አልይ ሀለቢ ቃኢዳ።

ሰለፍዮችን ሀዳድይ ስለሚሉ ሰዎች።

ጤፍ እሚቆላ ምላስ ስላለው ሰው።

ሼኽ አቡዘር

📜. https://t.me/abunehla

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

25 Dec, 17:46


⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው
ክፍል ስድስት (6⃣)

ሸይኹ I የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
“ይህ የሙሐዲሶች የጥናት ጭብጥ አይደለም ፣ እንዴውም እርሱ ደካማ
መሆኑን የሚገልጸውን ንግግር ማውሳቱ ግዴታ ነው፡፡ ከዚያም ጀርህን ወይም ተዕዲልን በማስቀደም ዙሪያ ሙሐዲሶች በተናገሩት ንግግር መስራት ግዴታ ነው፡፡ ትክክለኛ አስተውሎት ይኑርህ ፤ የጭፍን ተከታይነት ምርኮኛ አትሁን፡፡ እርሱ የደደቦች ማስረጃ ፣ የአመጸኞች ምርኩዝ ነው፡፡” (በህሩል ሙሒጥ አስሰጃጅ ፊ ሸርህ ሶሂህ አልኢማም ሙስሊም ብን አልሀጃጅ ፡16/677)
ሙሐመድ ሰዒድና ኸድር የተናጋሪውን ንግግር ያውቁ ነበር ፤ መሰረታዊም ይሁን
ቅርንጫፋዊ በሆኑ ጉዳዮች ተግባራዊ ያደርጉትም ነበር፡፡ እርሱም የሚከተለው ንግግር ነው፡-

  وليس كل خلاف جاء معتبرا
إلا خلافاله حظ من النظر                     
ልዩነቱ ሁሉ አይሰጠው ግምት
       ድርሻ ያለው ሲቀር ፣ ልዩ የሆነ ጥናት

- ኢማም አልባኒ I የተተነተነ ትችትን ከውዳሴ ማስቀደምን ለሚቃወሙ ሰዎች
የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
“የዚህን ትልቅ እውቀት ህግና መርሆ  ማለትም ከዑለሞች ዘንድ በታወቀው
መስፈርት ትችትን ከውዳሴ ማስቀደም የሚለውን መርሆ - በመተውና ጠማማ የሆነ አካሄድ በመከተል የዝንባሌ ባለቤቶች የፈለጉትን ሀዲስ ትክክለኛ የፈለጉትን ደግሞ ደካማ ማድረግ ይችላሉ፡፡” አድዶዒፋ : 9/125-130)
- ሙመይዓው ኸድር ከሚሴ ፣ ሙሐመድ ብን ሰዒድ እና ሌሎችም- “የተተነተነ
ትችት ከውዳሴ ማስቀደም” ኡለሞች የተወዛገቡበትና በእርሱም ላይ ተንተርሰን
ውዴታና ጥላቻ የምንመሰርትበት አይደለም!!!” የሚል አመለካከት ስላላቸው ይህ አካሄድ ከእነርሱ ዘንድ የተጣመመ ፣ እንዲሁም ለቢድዓ ፣ ለሽርክ እና ለጥመት ባለቤቶች በር የሚከፍት አይደለም፡፡ ከብዥታ ነጻ ካለመሆን በአላህ እንጠበቃለን፡፡ ይህ መዋዥቅ ከሀዲስ፣ ከሱና ባለቤቶችና ቀደምት ደጋግ ባሮች ከነበሩበት ጎዳና የማፈንገጥ ዋጋ ነው፡፡

✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር)

✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

24 Dec, 06:52


‏قال شيخ الإسلام ابن تيمية رحمه الله:

تظهر الشياطين،

في المواضع التي يختفي فيها،
أثر التوحيد .

📙 كتاب النبوات 1019/2

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

24 Dec, 04:04


⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው

ክፍል አምስት  (5⃣)

ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው” የሚለው የሙሐመድ ብን
ሰዒድ የንግግሩ ጭብጥ ሐሳብ ነው፡፡
- በሐበሻ ምድር የሙመይዓ ሰንደቅ አላማ ተሸካሚ የሆነው ኸድር ከሚሴ
የሚከተለውን አመለካከት አረጋግጧል ፡ -
“ከጀርህና ተዕዲል መካከል ኢጅቲሐድይ የሆነ አለ፡፡ ከእርሱ መካከል ኢጅቲሐድይ
ያልሆነም አለ፡፡” በዚህ አነጋገሩ እርስ በርሱ የሚጋጭና ልክ እንደተለመደው የቢድዓ
ባለቤቶች ባህሪ አስገራሚ መዋዥቅ አለው፡፡
የንግግሩ ጭብጥ ሐሳብ፡ ዑለሞች በተተቸና በተወደሰ ግለሰብ ላይ የተወዛገቡ ጊዜ ጉዳዩ
ኢጅቲሐዲይ ይሆናል ፤ በመሆኑም በእርሱ ዙሪያ ማስገደድ የለም፡፡ ለዚህም ምሳሌ
የጠቀሰው የሻፍዕይ ሸይኽ የሆነውን ኢብራሒም ብን አቢ የህያ ነው፡፡ ሻፍዕይ
ታማኝነቱን ሲገልጹ የጀርህና የተዕዲል ዑለሞች ደግሞ ፈተና የተባለ ሁሉ ከእርሱ ላይ
ተሰብስቧል በማለት ትችት አቀረቡ፡፡ ትችቱን እንዲቀበሉ ሻፍዕይን አላስገደዱም፡፡
ኸድር ከሚሴ የሚከተለውን ተናገረ፡ “የተተነተነ ትችት ከውዳሴ መቀደሙ ዑለሞች
የተወዛገቡበት ነው በመሆኑም በእርሱ ላይ ውዴታና ጥላቻ የሚመሰረትበት ጉዳይ
አይደለም፡፡”
ከኸድር ከሚሴ ዘንድ ያለው ጭብጥ ሐሳብ፡ “አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት
የዑለሞች ስምምነት የግድ ነው፡፡ የተተነተነ ትችት ከውዳሴ መቀደሙ ከዑለሞች ዘንድ
ውዝግብ ያለበት ጉዳይ በመሆኑ ሰዎችን በእርሱ ላይ አታስገድዱ !!!” የሚለው
ነው፡፡
ሙሐመድ ሰዒድ እና ኸድር ከሚሴ፡ ሸይኽ ሙሐመድ ብን አደም አልኢትዮጵይ
በጀርህና ተዕዲል ተቃርኖ ዙሪያ ዑለሞች የተናገሯቸውን ንግግሮች እንዳወሱ ጠቅሰዋል፡፡
“ይህ ፣ የተተነተነ ትችት ከውዳሴ መቀደሙ ውዝግብ ያለበት መሆኑ ማስረጃ ነው፡፡”
በማለት ሁለቱ ሙመይዖች ተናገሩ፡፡
እኔም አልኩ፡ ሁለቱ በጀርህና በተዕዲል እንዲሁም በዲኑ ጥልቅ አዋቂ ከሆኑት ዓሊሞች
ዘንድ ባለው ህግና መርሆ የእውቀት ችግር እንዳለባቸው ይጠቁማል፡፡
በዚሁ ኪታብ ሸይኽ ሙሐመድ I ራሳቸው የሚከተለውን ተናግረዋል፡-“ጀርህና ተዕዲል
በተቃረነ ጊዜ ዋጋ ሊሰጠው የሚገባው መሰረት 'የተተነተነ ትችት ከውዳሴ መቀደሙ'
ነው፡፡” (ኢዷህ አስሰቢል ፡ ገጽ 41)
“ዋጋ ሊሰጠው የሚገባው መሰረት” የሚለውን ንግግራቸውን አስተውል፡፡ ይህ ማለት
ከእርሱ ውጭ ያለው ዋጋ የሚሰጠው አይደለም ማለት ነው፡፡
ከሙመይዓ ዘንድ እንዲህ አይነቱ ጭብጥ ሐሳብ ፊት የሚሰጠው አይደለም፡፡
ከእነርሱ ዘንድ አንገብጋቢው ጉዳይ ልዩነት ከተከሰተ እርሱን ማጽደቅ ብቻ ነው!!!
ተናጋሪው ማን እንደሆነ በማይታወቀው ዑለሞች በሚገልጹት (ቂለ) ወይም “ተባለ”
የሚል ቃል ላይ ይደገፋሉ? የተተነተነን ትችት ከውዳሴ ማስቀደም ግዴታ መሆኑን
ከሚገልጹ የሀዲስ ባለቤቶች በዋናነት ከቡኻሪና ሙስሊም መንሐጅ (ጎዳና)
አፈነገጡ፡፡
ሸይኽ ሙሐመድ ብን ዓልይ አደም የተተነተነን ትችት ከውዳሴ ይቀደማል ከሚለው
የሀዲስ ባለቤቶች ጎዳና ያፈነገጠውን ይቃወማሉ፡፡

✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር)

✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

23 Dec, 13:04


🟢 إن الرجال الناظرين الى النساء
مثل الكلاب تطوف باللحمان . . .

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

22 Dec, 21:21


⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው

ክፍል አራት  (4⃣)

ነገር ግን እነርሱ ይህን አጥብቀው አይዙም፡፡ ሀቅ እንዲናገሩ ፣ባጢልን እና ጥመትን እንዲያዋርዱ የሚፈልጉባቸውን ሰዎች ይዋጋሉ፡፡
ከትእቢታቸው ፣ ኩራታቸውና አመጸኝነታቸው መካከል ፡ የሐቅ ባለቤቶች የማስገደጃ
መንገዶች ባለቤት ካለመሆናው ጋር ከእነርሱ ሀቅ መፈለጉን እንደማስገደድ አድርገው
ይመለከቱታል፡፡” የሚከተለውን የሸይኽ ረቢዕ አልመድኸሊ ኪታብ ተመልከት ፡-
እኔም አልኩ፡ በሐዳድያነት ማን ይሆን ሊገለጽ የሚገባው? አንድንም ግለሰብ
ሙብተዲዕ ለማለት ማስረጃን የሚያወሳው ነው? ወይስ ያለምንም ማስረጃ ሰዎችን
በሀዳድያነት የሚፈርጀው?
ድንበር ከማለፍና ከጽንፈኝነት በአላህ እንጠበቃለን!!
- “ጀርህና ተዕዲል -ትችትና ውዳሴ- ኢጅቲሀድይ (የምርምር ነጥብ ነው)”
በማለት ሙሐመድ ብን ሰዒድ አስሲልጢ አረጋግጧል፡፡ በተጨማሪም “ጀርህና
ተዕዲል ከመሰረታዊ ነገሮችም አይደለም፡፡ ነገር ግን ዑለሞች ጀርህና ተዕዲል
በማድረግ ላይ ስምምነት ያደረጉበት ከኢጅቲሀድ ክፍል አለመሆኑ ተለይቶ የሚታይ
ጉዳይ ነው፡፡” በማለት ተናግሯል፡፡
ሙሐመድ ብን ሰዒድ የሚከተለውን ተናግሯል፡ “የተተነተነ ትችት ከውዳሴ መቀደሙ
ዑለሞች የተስማሙበት ሳይሆን የተወዛገቡበት ነው፡፡” ለዚህም “አቡል ሀሰን
አልመእሪቢን ሸይኽ ረቢእ ሙብተዲዕ ሲሉት ሸይኽ ዓብዱል ሙህሲን አልዓባድ
ሙብተዲዕ አላሉትም” የሚል ምሳሌ አውስቷል፡፡ “የፈለገ የሸይኽ ረቢዕን ንግግር
መውስድ ይችላል ፤ የፈለገ ደግሞ የሸይኽ ዓብዱልሙህሲን አልዓባድን ንግግር መያዝ
ይችላል፡፡ በዚህ ላይ ማስገደድ የለም፡፡ ይህ በሰለፍዮች መካከል ለልዩነት ሰበብ ሊሆን
አይገባም!!” በማለት ተናግሯል፡፡

✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር)

✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

22 Dec, 15:27


⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው

ክፍል ሦስት (3)

ከዚያም ኢብኑ ሙነወር በሸይኽ ዓብዱል ሐሚድ እና አብረዋቸው ባሉት ላይ ሐዳድያ
እንደሆኑ ፣ በቀድሞው ሀዳድያ እና በሸይኽ ዓብዱል ሐሚድ እንዲሁም አብረዋቸው
ባሉት መካከል ያለው ልዩነት ጊዜ ብቻ እንደሆነ ፍርድ ሰጠ፡፡
እኔም አልኩ፡ ስለእነርሱ ሐዳድይነት እውነተኛ ከሆንክ ፣ ከአንተ ጎን እንድንቆምና
ከአንተ ጋር ያለውን ሐቅ እንድንረዳ ለምን ማስረጃዎችህን አታወሳም? ከሸይኽ
ዓብዱልሐሚድና ከሸይኽ ሐሰን ገላው ዘንድ ያለው የሀዳድያ ባህሪ ምንድን ነው?
ከሩቁም ከቅርቡም የሚታወቀው ሁለቱ ሸይኾች ሀዳድያን በመዋጋትና ከእነርሱም
በማስጠንቀቅ ነው፡፡
- ምናልባት እነርሱን በሀዳድያነት መግለጽህ ኤልያስን ሙብተዲዕ ስላሉ ሊሆን
ይችላል፡፡ በዚህ ላይ ማስረጃቸውን አውስተዋል፡፡ ልክ እንደዚሁ ሁለት መቶ
ከሚሆኑ አምሳያዎችህ እነርሱ በጣም አዋቂዎች ናቸው፡፡ ኤልያስን ሙብተዲዕ
በማለት አንድንም አላስገደዱም፡፡ ነገር ግን -ሸይኽ ረቢዕ አልመድኸሊ
እንደተናገሩት- ሙመይዓህ ስለስሜት ተከታዮችና ጠማማ ሰዎች እውነታውን
እንዲናገሩ ሲፈለግባቸው ያለቃቅሳሉ ፣ “እከሌን ሙብተዲዕ ካላላችሁ እያሉ
አስገደዱን ፣ ጫና ፈጠሩብን ፣ …”. ይላሉ፡፡
ፍጻሜውን አላህ ያሳምርለት ሂዝብያዎችን ጠንቅቆ የሚያውቀው ሸይኽ ረቢዕ
አልመድኸሊ የሚከተለውን ተናግሯል፡- “በነፍሳቸው እንዲሁም በጥመት ባለቤቶች
ላይ የሚገባቸውን ፍርድ እንዲሰጡ ፣ ሀቅ እንዲናገሩ ፣ በመልካም እንዲያዙ ፣
ከመጥፎ እንዲከለክሉ ኢስላማዊ መሰረቶች ታስገድዳቸዋለች ፣ ግዴታ
ታደርግባቸዋለች፡፡

✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር)

✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

20 Dec, 14:10


⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው

ክፍል ሁለት  (2⃣)

“የተተነተነ ትችት ከውዳሴ መቀደሙ ውዝግብ ያለበት ጉዳይ ነው፡፡ በእርሱ ላይ
ተንተርሶ ውዴታና ጥላቻ አይመሰረትም” የሚል አመለካከት ከሙመይዕ ዘንድ አለ፡፡
“የኤልያስ መሰረቶች ሱንይ ናቸው ፣ በመሆኑም በዑለሞች አጠቃላይ ስምምነት
ካልሆነ በቀር (ከሱንይነቱ) አይነቃነቅም!!!” ይህ ነው የሙመይዓ እርግጠኛው
መንሐጅ (ጎዳና)፡፡ በእነርሱ የተንኮል ወጥመድ ከመጠለፍ ሰላም ልትሆን ዘንድ ይህን
ጉዳይ በደንብ ተገንዘብ፡፡
- “ጀርህና ተዕዲል ኢጅቲሐዲይ ነው ፤ በእርሱ ዙሪያ መገደድ የለም” በማለት
ኢብን ሙነወር አረጋግጧል፡፡ እንዴውም በዚህ ዙሪያ ሙሓዶራ (የትምህርት
ፕሮግራም) አካሄዷል፡፡ መገደድ የሌለ መሆኑን ሲገልጽ አንድም በዚህ ርእሰ￾ጉዳይ አትሰማም ፣ ልክ እንደ ኹጥበቱል ሀጃ (የንግግር መክፈቻ) የሚከተለውን
የተናገረ ቢሆን እንጅ ፡-
“ሸይኽ ፉላን እከሌን ሙብተዲዕ ብሎታል ፣ እከሌ ደግሞ ሙብተዲዕ አላለውም ፣
እሽ ወደርሱ ልታስጠጉት ነው? ሸይኽ ፉላን ሙብተዲዕ የተባለውን ሰው
አወድሶታል እሽ ወደርሱ ልታስጠጉት ነው? ሸይኽ ፉላን እከሌን በተመለከተ
እንዲህ ብሏል ሸይኽ እከሌ ደግሞ ተቃርኖታል …”
ይህ አካሄድ የጥመት ባለቤቶች መንገድ እንደሆነ ሸይኽ ረቢዕ ተናግረዋል፡፡ በአላህ
ፈቃድ ንግግራቸው በቅርብ ይመጣል፡፡
ከኢብን ሙነወር ንግግሮች ጭብጥ መልዕክት የሚከተለው ይገኝበታል፡- “አንድን ሰው
ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው፡፡ ምክንያቱም ዑለሞች እከሌን
ሙብተዲዕ በማለት ዙሪያ ካልተስማሙ ሰዎችን አታስገድዱ ፣ እኔም ግድ አይለኝም….

✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር)

✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

12 Dec, 04:08


አንተ ቁርኣንን ሐፍዘህ ሙራጃዐዉን የተዉክ ሰዉ ሆይ! ሐፍዘህ ስለረሳከዉ ቁርኣን ተጠያቂ ነክ።......ያለ ህመም፣ያለእርጅና ከሆነ የረሳከዉ ዋ! ጥፋትክ!
አትነሳም ወይ? ለስፖርት፣ለጥናት እና ለተለያዩ ነገሮች ግዜ ሰጥተህ ለሙራጀዐ ሲሆን ከበደህ? ....

አንተ ወጣት ተጠንቀቅ፣እወቅም! ቁርኣንን የያዘ ከስሜት ዝንባሌ ይጠበቃል።


@umu_elham

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

25 Nov, 18:23


‏قال الشيخ ربيع المدخلي:

أما منهج السلف
فواضح غاية الوضوح كامل كل الكمال شامل كل الشمول لأنه مُستمَُدٌ من كتاب الله وسنة رسوله صلى الله عليه وسلم ومما دَوَّنه علماء السنة من القرون الأولى إلى هذا العصر يؤكد اللاحق منهم ماقرره السابق.

المجموع ج١١/ص٢٤٨

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

24 Nov, 04:58


🔸ثلاثٌ مِنَ الصَّبْرِ

صَحّ عَنِ الإمامِ سُفيانَ الثّوريِّ عَنْ بعضِ أصْحابِه قالَ:"يُقالُ:

ثَلاثٌ مِنَ الصَّبْرِ:

ألَّا تُحَدِّثَ بِمَوْجِعِكَ،
ولا بِمُصيبَتِكِ،
ولا تُزَكِّي نفسَك.

📙 إخرجَهُ عبدالرّزّاق في(التّفسير)(١/ ٢٧٧)و-مِنْ طَريقه- ابنُ جريرٍ في(جامع البيان)(١٣/ ٤١)


https://t.me/abunehla

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

13 Nov, 14:35


🔴መድኸሊ አትሁን ወይ ጃሚይ አትሁን ለሚሉ . . .

በዳዕዋ ላይ ስመጥር ከሆኑ ጠንካራ ዑለሞች ውስጥ . . .

ሼኽ አብዱልሙህሲን አል- አባድ ፣ ፈዲለቲ ሼኽ ረቢዕ ቢን ሀዲ ፣ ፈዲለቲ ሼኽ ሷሊህ አሱሀይሚ ፣ ፈዲለቲ ሼኽ መሀመድ አማን አልጃሚ እነዚህ ዑለሞች ጠንካራ ተጋድሎ አድርገዋል ወደ አላህ በኢኽላስ በመጣራት ይህ ቀጥተኛን ዳዕዋ አስበውትም ይሁን ሳያስቡትለ ማጣመም በሚፈልጉ አካሎሽች ላይ ረድ በማድረግ ብዙ ትግል አድርገዋል። እነዚህ ዑለሞች እውቀት ያላቸው የሰዎችን ንግግር በትዕግስት በማገናዘብ መልካሙን ከመጥፎ የመለየት ችሎታ ያላቸው ናቸው።
ስለዚህ አስተምህሮታቸው ካሴቶቻቸው ሊሰራጩ ከነሱ ሰዎች ሊጠቀሙ ይገባል።

ድምፁን ለማግኘት 👇👇

🎙ሼኽ ሷሊህ አልፈውዛን ሀፊዘሁሏህ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

12 Nov, 06:07


‏قال تعالى(واشكروا لي ولا تكفرون)
قال جمع من السلف: الشكر تركُ المعصية.
وقال بعضهم :الشكر أن لا يُستعان على المعاصي بشيء من نعمه .

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

30 Oct, 03:38


🟢ፊትና የሚከሰተው . . .

ሸይኹል ኢስላም አቡ አል-አባስ ኢብኑ ተይሚያህ -አላህ ይዘንላቸው እንዲህ ብለዋል፡-

ፊትና አላህ ያዘዘውን ነገር በተወ ሰው ላይ እንጂ አይከሰትም።

በእርግጥ ጥራት የተገባው ጌታ በትዕግስት እና በእውነተኝነት አዟል።

ፊትናም ወይ እውነተኝነትን አሊያም ትዕግስት በሌለው ሰው ላይ ነው የሚከሰተው።

📚【አልስቲቃማ (39/1)】

‏قال شيخ الإسلام أبو العباس ابن تيمية - رحمه الله:

وَلَا تقع فتْنَة إِلَّا

من ترك مَا أَمر الله بِهِ ،

فَإِنَّهُ سُبْحَانَهُ أَمر بِالْحَقِّ وَأمر بِالصبرِ ،

فالفتنة إِمَّا من ترك الْحق

وَإِمَّا من ترك الصَّبْر .

📚【 الاستقامة(٣٩/١) 】

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

18 Oct, 07:42


🟢አላመቱ ኢብኑ ረጀብ ረሂመሁሏህ እንዲህ አሉ :

በላጩ ሰደቃ :

አላዋቂዎችን ማስተማር

ወይንም :

የዘነጉ ሰዎችን ማንቃት ነው።

መጀሙዑ ረሳኢል (186/1)

‏قال العلامة ابن رجب رحمه الله:

أفضل الصدقة:

تعليم جاهل،

أو ،

إيقاظ غافل.

📙مجموع الرسائل (186/1)

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

18 Oct, 06:28


አፉ ተለጉሞ ዲንን ለሚንዱ
አንዱ በዓቂዳ ሌላው በመውሊዱ
ለጥፋት አብረው ችለው ሲረዳዱ
ዛሬ በሀቅ መንገድ እውቀት ቢያሰናዱ
አስታወከው ክፋት የቋጠረው ሆዱ‼️

https://t.me/abunehla

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

12 Oct, 09:13


በሰለፍያ ዳዕዋ ጩኸት የሚረበሽ ሸይጧን ወይ ሙብተዲዕ ነው እንግዲህ ከሁለት አንዱ ናችሁ ምርጫው ለእናንተ ነው!

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

08 Oct, 05:33


🟢ብቻህን ሁነህ ነፍስህን ተሳሰብ ...

ከጌታህ ጋር ለብቻ ሆነህ ነፍስህን ለመተሳሰብ እና ለማስተንተን ከወቅትህ ቀንሰህ እራስህን መነጠል (ገለል) ማድረግ  ምንም ቅሮት የሌለው ጉዳይ ነው።

ለዓቅመ አዳም ከደረስክበት ጊዜ ድረስ ጀምሮ የሰራከው ሁሉ ተቆጥሯል አንተ ግን ረስተክዋል። እያንዳንዱ መጥፎ ስራህ ባንተ ላይ ኮፒ ተደርጓል ፣ መዝገብህ ላይ ተፅፏል ፣ ስለሱም ትጠየቅበታለህ አላህ ካልማረልህ ትቀጣበታለህ‼️

ከእርሱ የት ነው የምታመልጠው

አብዘሀኛው ስራህ ደግሞ ተውበት ያላደረግክበት ነው። ብዙ ያሳለፍካቸው ነገሮች ላይ አስተንትን
🔘 ለአቅመ አዳም ከደረስክ ጊዜ ጀምሮ።
🔘ተጠያቂ መሆን ከጀመርክ ጊዜ ጀምሮ።
🔘 መዝጋቢዎቹ ባንተ መልካም ስራ እና መጥፎ ስራ መዝገብ ላይ መመዝገብ ከጀመሩበት ቀን ጀምረህ‼️
በአንተ ላይ መመዝገብ ከጀመሩበት ቀን ጀምረህ አስተንትን‼️

ትጠየቅበታለህ‼️ ይሄ ሁሉ ፊትህ ይቀረብልሀል። ወይ በቀኝህ ወይ በግራህ በጀርባ በኩል ትቀበላለህ‼️ አላህ ይጠብቀን እና።

ነገር ግን ወደፊት ታየዋለህ‼️

ድምፁን ለማድመጥ ስሙን ይጫኑ👇👇👇

🎙በሼኽ ሙሀመድ ሰዒድ ረስላን (ዶ/ር)  
  
    ሀፊዘሁሏህ

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

06 Oct, 08:10


ይህ App በማታ ስልክ ለምታዘወትሩ . . .

🟢የስልካችንን ስክሪን ሙሉ ወደ night mode ይቀይርልናል

🟢ስናነብ ምቾት እንዲሰማን

🟢የአይናችን ጤንነት ለመጠበቅ
    ይጠቅማል

       ተጠቀሙበት !!

https://t.me/abunehla

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

02 Oct, 06:52


የእይታ መዘዝ. . .

🟢አል-አላማ ቢን ዘይድ እንዲህ አሉ፡-

በሴት ቀሚስ ላይ እይታህን አታስከትል!

መመልከት በልብ ውስጥ ሻህዋን (ስሜትን) ይፈጥራልና።

📙ዙህድ ኢማም አህመድ (311)።

‏عن العلاء بن زياد قال:

لا تتبع بصرك رداء المرأة ،

فإن النظر يجعل شهوة في القلب .

📙الزهد للإمام أحمد ( 311 ) .

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

30 Sep, 02:32


🟢ደስተኛ ህይወት...

ሸይኽ ሙሐመድ ቢን ሳሊህ አል-ዑሰይሚን ረሒመሁሏህ እንዲህ አሉ፡-

ደስተኛ ፣ የምታረካ እና ዘላቂ ሕይወት ፣
ከሞት በኋላ ያለው ሕይወት ነው።
የዱንያ ህይወትን በተመለከተ የቱንም ያህል በጥሩ ሁኔታ ብትኖር ጠፊ ናት።

📙 ሸርህ ሪያድ አል-ሷሊሂን (3/364)

‏قال الشيخ محمد بن صالح  العثيمين  رحمه الله:

العيشة الهنية الراضية الباقية،

هو عيش الآخرة،

أما ‌ الدنيا فإنه مهما طاب عيشها، فمآلها للفناء.

📙 شرح رياض الصَّالِحين (٣/٣٦٤)

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

19 Sep, 10:50


💡M/Barumsa Qur’aanaa fi Tajwiidaa Nuurayin💡
––––––––––––––––––––––––––––––––––––––––––
Dhaabbanni keenya karaa onlaayiniitiin, aliifa irraa eegalee hanga sadarkaa hifzii gahutti barattoota galmeessee, barsiisota shamaraa dandeettii gahaa qabaniin haala gaariin barsiisuu irratti argama. Dhaabbata keenya wanti adda godhu shamarran qofaan barsiisuu isaati. Isinis daddaffiin galmaayaa.

🧭 Akaakuu Barnootaa Kennaman 🧭
––––––––––––––––––––––––––––––––––––––––––
🌸 Qaaidatu-Nuuraaniyyaa, ji’a 3 keessatti
🌸 Qur’aana ijaan tajwiida wajjiin, ji’a 8 keessatti
🌸 Hifzii Qur’aanaa muraaja’aa gahaa wajjiin, waggaaf ji’a 3 hanga ji’a 6tti
🌸 Kitaabban gaggabaaboo, ji’a 3 keessatti

🧭 Karaa Barnoonni Ittiin Kennamu 🧭
––––––––––––––––––––––––––––––––––––––––––
● Barattuun takka eega galmoofte booda, barsiistuu isiif ramadame wajjiin karaa:
🌸 Imoo
🌸 Telegram
🌸 Zoom
🌸 WhatsApp tiin
        kallattiin (live) haala mijataa ta’een baratti

👉 Barumsi Yeroo Kam Kennama?
––––––––––––––––––––––––––––––––––––––––––
● Torbaanitti guyyaa 5 (Roobii-Dilbataa)
● Barattuun sa’aa isii mijatutti

📞 Galmaayuuf 👇👇


☎️+251947311878

           @Lemizgeba

🎙 M/Barumsa Qur’aanaa fi Tajwiidaa Nuurayin 🎙
Kaayyoon keenya dubartoota barnoota diiniitiin duroomsuudha.

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

16 Sep, 22:42


ስትወርድ ግብዣ ከየት እንደሚመጣልህ ልብ በል ከሁሉ በላይ የሚገርመው የነ ለሰለፍያ ነው የሚሰሩት ባይ ሞጋቾች እና አጨብጫቢዎች ናቸው‼️

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

14 Sep, 06:29


የመውሊድ አከባበርን አስመልክተው ዑለሞች የተናገሩት!

🗣️ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን حفظه اللّٰه

🗣️ሸይኽ ኢብኑ ባዝ  رحمه اللّٰه

🗣️ሼይኽ ሷሊህ አል ሉሃይዳን رحمه اللّٰه

🗣️ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን رحمه اللّٰه


https://t.me/abunehla

🇸🇦 ውበት በኒቃብ 🇸🇦

14 Sep, 06:28


የመውሊድ አከባበርን አስመልክተው ዑለሞች የተናገሩት!

🗣️ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን حفظه اللّٰه

🗣️ሸይኽ ኢብኑ ባዝ  رحمه اللّٰه

🗣️ሼይኽ ሷሊህ አል ሉሃይዳን رحمه اللّٰه

🗣️ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን رحمه اللّٰه


https://t.me/abunehla

1,201

subscribers

808

photos

85

videos