የአባቶች ምክር @father_advice Channel on Telegram

የአባቶች ምክር

@father_advice


አስተማሪ የሆኑ የአባቶች ምክሮችን ÷መንፈሳዊ ፁሑፎችን እና ትምህርቶችን የምናጋራበት ቻናል ነው። ሊንኩን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ! የክርስቶስ ሰላም ይብዛላችሁ!

የአባቶች ምክር (Amharic)

የአባቶች ምክር ከሲስትራቲክስ እና ገና ሊንኩን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ። የአባቶች ምክሮችን እና መንፈሳዊ ፅሁፎችን እና ትምህርቶችን የምናጋራበት ቻናል ነው። የአባቶች ምክር አስተማሪ በትግርኛ ብለን የታለበትን ውይይት ፈጥሯል። ትህነጽን እና የልጅነት መሰላላት ከመሆኑ በፊት የክርስቶስ ሰላም ይብዛላችሁ!

የአባቶች ምክር

16 Feb, 05:58


መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊት እጅግ በሚወደው በዮናታን ሞት ምክኒያት ሀዘኑን ሲገልፅ የፍቅራቸውን ሀያልነት ለማሳየት እንዲህ ብሎአል?
"ከሴት ፍቅር ይልቅ ፍቅርህ ለእኔ ግሩም ነው" 1ኛ ሳሙ 1:26

በወንድ እና በሴት መካከል ያለው ፍቅር ከስሜቶች ሁሉ ሀያል ነው ሌሎች ስሜቶች ምንም ሀያል ቢሆኑም እንኳን ይህ ስሜት ግን ከሌሎች በተለየ መልኩ የማይጠፋ ፅኑ እና በሁለቱ የተቃራኒ ፆታዎች ውስጥ የተተከለ ነው
እኛ ልብ ባንለው እንኳን ከመካከላችን ሆኖ ወንዶችን እና ሴቶችን አንዳቸውን ወደ አንዳቸው ይስባል የዚህም ምክኒያት በመጀመርያ ሴት ከወንድ በመገኘቷ እና ከወንድ እና ከሴት ደግሞ ሌሎች ወንዶች እና ሴቶች ስለሚገኙ ነው
John_Chrysostom_commentaries
🌿@father_advice🌿

የአባቶች ምክር

15 Feb, 15:28


+• አንተ ከማን ጋር ትነጋገራለህ? •+
 
አንድ ሕጻን ልጅ ተወልዶ ሲያድግ እናትና አባቱን እጅግ ሊያጓጓቸው ከሚችሉ ነገሮች አንዱ የሕጻኑ አፍ መፍታት ነው፡፡ ምንም ስንኳ በመጀመሪያ እየተኮላተፈ ሲያወራቸው ቃላቶቹ ያልተቀላጠፉ፣ ዐረፍተ ነገሮቹም ያልተሰካኩ ቢሆኑም የእርሱን “እማ” እና “አባ” ማለት ወላጆች ከትልቅ ቁምነገር ቆጥረው በደስታ ይፍለቀለቃሉ፡፡ ሕጻናትም “ውይ አንደበቱ ሲጣፍጥ…” ወይም “ውይ አንደበቷ ማር ማር ይላል” እየተባለላቸው ያድጋሉ፡፡ ሆኖም ግን እድሜ ሲገፋ፣ ክፉ ደጉም ሲታወቅ፣ ብዙዎቻችን ጣፋጭ የነበረው አንደበታችን መበላሸት ይጀምራል፡፡ በደስታ የሚያፍለቀልቁት ቃላቶቻችን በሰዎች ላይ የሐዘን ካባን የሚደርቡ ይሆናሉ፡፡ የሰውን ቅስም በምላሳችን መስበር እንጀምራለን፡፡ ማር የተባለችው አንደበት ሰንብታ እንደ እሬት ትሆናለች፡፡ ታላቁ ቅዱስ ዳዊት ይህንን በመረዳቱ “አቤቱ፣ ለአፌ ጠባቂ አኑር፣ የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ፡፡” (መዝ 141፡3) በማለት ፈጣሪውን ሲማጸን እናገኘዋለን፡፡ የዳዊት ልጅ የሆነው ጠቢቡ ሰለሞንም፤ ልክ እንደ አባቱ የአንደበትን ኃያልነት ስለተገነዘበ “በቃል ብዛት ውስጥ ኃጢአት ሳይኖር አይቀርም፤ ከንፈሩን የሚገታ ግን አስተዋይ ነው፡፡” (ምሳ 10፡19) በማለት ይነግረናል፡፡

አንደበትን መግዛት የሚያስፈልገው ግን ኃጢአትን ላለማብዛት ብቻ አይደለም፡፡ አንዳንዴ የምንናገራቸው ቃላት አድማጭ ከሌላቸውም አባካኝ ላለመሆን የአንደበታችን በር እንቆልፋለን፡፡ አባቶቻችንም ከክፉ ቃላት አንደበታቸውን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን፤ መልካም ቃላቶቻቸውንም ሰሚ ለሆኑ ጆሮዎች ብቻ ያደርጉ የነበረው ለዚያ ነው፡፡ ለዚህ መልካም ምሳሌ የሚሆኑት፤ በረከታቸው ትደርብንና፤ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ናቸው፡፡ እርሳቸው የዝምታ ሕይወትን ከመምረጣቸው በፊት “ከማይሰሙኝ ሰዎች ጋር ከምነጋገር፣ ከሚሰማኝ እግዚአብሔር ጋር ብነጋገር ይሻለኛል፡፡” ስለማለታቸው ይነገራል፡፡ በዚህ የአባታችን ንግግር ውስጥ ትልቅ ጥበብ አለ:: የዝምታ ሕይወትን የመረጡ ቅዱሳን አባቶች እና እናቶች ምንም ስንኳ በሰው ፊት ከመናገር ቢቆጠቡም፤ በፈንታው ግን ሁሌም ከአምላካቸው ጋር የሚነጋገሩ ናቸው፡፡ በእርግጥ ካስተዋልነው አባታችን እውነታቸውን ነው፤ ከእግዚአብሔር በላይ ሰሚ ከወዴት ይገኛል?!

ወንድሜ፤ አንተ ከማን ጋር ትነጋገራለህ? አንቺስ እህቴ፤ ንግግርሽ ከማን ጋር ነው? ጩኸታችንስ የምናቀርበው ወደ ማን ዘንድ ነው? ብዙ ነገሮቻችን ከንቱ እየቀሩ ያሉት ከሚሰማን እግዚአብሔር ይልቅ ሊሰሙን ወደማይፈቅዱ ሰዎች እየጮህን ስለሆነ ይሆን? ሐዘናችን በከንቱ የሚባክንብን እንባችንን በእግዚአብሔር መቅደስ ፊት ከማፍሰስ ይልቅ በሚሳለቁብን ሰዎች ፊት ስለምንዘራው ይሆን? በሕይወታችን ውስጥ ተናግሮ እንዳልተናገረ፣ ጮኾ እንዳልጮኸ፣ አንብቶ እንዳላነባ የምንሆነውስ፤ ከነቢዩ ዳንኤል ጋራ “አምላኬ ሆይ፣ በፊትህ የምንለምን ስለ ብዙ ምሕረትህ ነው እንጂ ስለ ጽድቃችን አይደለምና ጆሮህን አዘንብለህ ስማ፤ ዓይንህን ገልጠህ ጥፋታችንና ስምህ የተጠራባትን ከተማ ተመልከት” (ዳን 9፡18) በማለት ፈንታ እርስ በእርስ ከንቱ ቃላትን በመወራወር ጊዜያችንን ስለምናጠፋ ይሆን?

✍️ Fresenbet G.Y Adhanom
🌿@father_advice🌿

የአባቶች ምክር

15 Feb, 13:52


ጂም ሲሰራ ስቃይ አለው ስቃይ ባይኖረው ድካም አለው እና ጂም የምትሰሩ ሰዎች እረ ይሄን እስፖርት አላቀኝ ትላላችሁ?
ውጋት እስትራፖ እየያዛችሁ ለምንድን ነው የምትሰሩት?
ለውጡን ስለምታስቡ ደስ ብሎአችሁ ነው አይደለምን?
ስጋን እንደሚያጠነክር አምናችሁ ነው የምትሰሩት
ነፍስም የራሷ ማጠንከሪያ አላት
ነፍስን የሚያጠነክራት ነገር መከራ ነው

     አባ ገብረ ኪዳን

“ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር እርሱ ይጸልይ፤
  — ያዕቆብ 5፥13
🌿@father_advice🌿

የአባቶች ምክር

15 Feb, 06:05


“ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤
አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል
ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥
የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።”
— ኢሳይያስ 9፥6
 🌿@father_advice🌿

የአባቶች ምክር

14 Feb, 11:43


+• 20 ወንድማዊ ምክሮች •+

1. ፈገግታ ጌጥ ነውና ከፊትህ ላይ አይለይህ::

2. ብዙ ማውራት ሰውን ያታክታልና በንግግርህ ቁጥብ ሁን::

3. የምትጀምራቸውን ነገሮች ሁሉ በጸሎት ጀምር::

4. ያልተገባ ነገር ተናግረህ ትዝብት ላይ እንዳትወድቅ የማታውቀውን ነገር አላውቅም ለማለት አትፈር::

5. በሁሉ ነገር ላይ አስተያየት ካልሰጠሁ አትበል::

6. በምንም ሁኔታ ውስጥ ብትሆን "እግዚአብሔር ይመስገን" ማለትን አትርሳ::

7. በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ምጽዋትን የምትሰጥ ሁን::

8. ለመቀየም የዘገየህ ይቅር ለማለት የፈጠንክ ሁን::

9. ሕይወትህን በእቅድ ምራ::

10. በጥበብ ማደግ ገደብ የለውምና ትምህርትን በቃኝ አትበል፤ ሊያስተምርህም ፈቃደኛ ከሆነ ሰው ሁሉ ተማር::

11. ውሳኔን ለመስጠት ችኩል አትሁን::

12. በሰው እንዳትናቅ የዋህ ሁን እንጂ ጅል አትሁን:: ሰዎች እንዳይርቁህ ብልጥ ሁን እንጂ ተንኮለኛ አትሁን::

13. በሰዎች ፊት ያለ ፍርሃት እንድትቆም የምትማራቸውን ነገሮች አጥርተህ ተማር::

14. ክርስትና ሕይወት ነውና፤ የምታምነውን በሕይወትህ ለመተግበር የተጋህ ሁን::

15. የሚያስቀይምህን ነገር ልትሠማ ትችላለህና ሰዎች የሚያወሩትን በድብቅ አትስማ::

16. በአመጋገብህ ትዝብት ላይ እንዳትወድቅ ስትመገብ አትስገብገብ::

17. አዳማጭ ከማጣት የቆሰሉ ብዙ ሰዎች አሉና፤ ሰዎች ችግራቸውን ሲያዋዩህ ጆሮ ስጣቸው::

18. ምጽዋት ለጠየቀህ መስጠት ስንኳ ባትችል "እግዚአብሔር ይስጥልኝ" ማለትን አትርሳ::

19. በእንስሳት ላይ ጨካኝ አትሁን::

20. የሰዎችን ሁኔታ የበለጠ ለመረዳት "እኔ በእነርሱ ቦታ ብሆን ምን አደርግ ነበር?" ብለህ ራስህን ጠይቀው::

✍️ Fresenbet G.Y Adhanom
   🌿@father_advice🌿

የአባቶች ምክር

14 Feb, 01:37


የጠፋ በግ አዳምን የፈለገው ባገኘውም ጊዜ
የተሸከመው እውነተኛ ቸር ጠባቂያችን     
          ክ   ር   ስ  ቶ ስ
ሎቱ ስብሐት🙏
     🌿@father_advice🌿

የአባቶች ምክር

14 Feb, 01:27


‹‹ተስፋ ለሕይወታችን አስፈላጊ ነገር ነው:: ሰው ተስፋ ካጣ ሁሉንም ነገር ያጣል። ተስፋ ያጣ ሰው ደግሞ በጭንቀት፣ በስቃይ፣ ግራ በመጋባት፣ ዓላማ በሌለው ጥበቃና በዛለ መንፈስ ውስጥ የወደቀ ስለሚሆን ሰይጣን በመዳፎቹ ውስጥ አስገብቶ መጫወቻ ያደርገዋል፡፡ ይህ በመሆኑም ወደ ተስፋ መቁረጥ የሚመራው ሰይጣን ነው እንላለን፡፡ ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር ልጆች ምን ጊዜም ተስፋ ስላላቸው በማንኛውም ሰዓት የሚኖሩት በተስፋ ነው፡፡

በማንኛውም ሰዓት የሚኖሩት በተስፋ ነው፡፡ በመከራ ጊዜ ተስፋ አላቸው፤ ነገሮች ሲወሳሰቡ ተስፋ አላቸው፤ ከዚህ በተጨማሪ እግዚአብሔር የዘገየ በሚመስልበት ጊዜና ነገሮች ሁሉ ጨለማ በሚመስሉበት ጊዜም ተስፋ ይኖራቸዋል፡፡››

(ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ)

የአባቶች ምክር

13 Feb, 15:45


አቤቱ ንጉሴ ሆይ የራሴን ጥፋት አስመልክተኝ እንጂ
በወንድሜ ላይ እንድፈርድ አታድርገኝ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

የአባቶች ምክር

13 Feb, 10:35


+++ ልሸፈንላችሁ? +++

ሙሴ ከሲና ተራራ ወርዶ ከሕዝቡ ጋር ሲገናኝ የፊቱን ማንጸባረቅ አይተው "ተሸፈንልን" ያሉት ሕዝቡ ናቸው። እርሱ "ከእግዚአብሔር ጋር ስነጋገር ቆይቼ እኮ አሁን መውረዴ ነው? ምነው የፊቴ ብርሃን አስቸገራችሁ? ልሸፈንላችሁ እንዴ?" አላለም። እንዲያውም ቅዱስ መጽሐፍ "ሙሴም ከተራራው በወረደ ጊዜ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለ ተነጋገረ የፊቱ ቁርበት እንዳንጸባረቀ አላወቀም ነበር" ነው የሚለው።(ዘጸ 34፥29) ለቅዱሳን እግዚአብሔር በፊታቸው የሚሥለው የክብር ብርሃን እነርሱን ለሚመለከታቸው እንጂ ለራሳቸው አይታወቃቸውም። እውነተኞቹ ቅዱሳን  "ተሸፈኑልን" የሚባሉ እንጂ "ልሸፈንላችሁ" የሚሉ አይደሉም።

ጥቂት በጎ ሥራ ሠርተህ ጻድቅነትህን በግድ ለማሳየት አትሞክር። ሌሎች ተሸፈንልን ይበሉህ እንጂ፣ አንተ ራስህ "ልሸፈንላችሁ" እያልህ የዋሐንን አታስጨንቅ።

በአገራችን የሚታወቅ ተረት አለ። አንድ ጊዜ ትንኝ በሬ ቀንድ ላይ ቆመችና "ከብጄህ እንደ ሆነ ንገረኝና ልነሣልህ" አለችው። በሬውም "እንኳን ልትከብጅኝ መኖርሽንም አላወቅሁም" አላት።

"ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ሌሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው"   ሉቃስ 18፥9

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

   ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲         ?
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ     ۹ᵉᵘˢⁱᵒⁿ

የአባቶች ምክር

13 Feb, 04:58


እግዚአብሄር እንደሚያኖር ያልዘነጋ
ለመኖር አቅም አያጣም!

የአባቶች ምክር

13 Feb, 03:59


ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥
"...
እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁም፤
እግዚአብሔርም ደግፎኛልና ነቃሁ።

...
ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥
በረከትህም በሕዝብህ ላይ ነው።"

መዝሙረ ዳዊት 3 : 5 - 8

የአባቶች ምክር

12 Feb, 17:45


+• ለትልቅ ሰው እንናገር •+

በዐፄ ቴዎድሮስ ዘመን አንድ ሹም ጥፋት አጠፉና ታሰሩ። እርሳቸው ታስረው እያለ ግን ሚስታቸው ከአሽከራቸው ጋር ግንኙነት ጀመረች። ይህ ወሬ ቀስ ብሎ ከንጉሡ ጆሮ ደረሰ። ንጉሡ “ይህን ሹም አሳስሬ አስደፈርኩት” ብለው በጣም አዘኑ። የታሰሩትንም ሹም አስጠርተው “ሚስትህ ያደረገችውን ነገር ሰምቼ አዝኛለሁ። ፈቃድህ ከሆነ፥ እርሷንም አሽከርህንም ደህና አድርጌ እቀጣልሃለሁ” አሉት። ሹሙ ግን ዝም አሉ። ንጉሡም “ይህንን ጉዳይ ሰምተህ ግን እንዴት አልነገርከኝም?” ብለው ሹሙን ጠየቋቸው። ሹሙም “ለትልቅ ሰው ነግሬያለሁ፥ ንጉሥ ሆይ” አሉ። ንጉሡም ተበሳጭተው “አንተ ትዕቢተኛ፥ ደግሞ ከእኔ ወዲያ ትልቅ ሰው የት አለ?” ሲሉ፥ ሹሙም “ለትልቅ ሰው ለመድኃኔዓለም ነግሬያለሁ፥ ንጉሥ ሆይ” ብለው መለሱ። ዐፄ ቴዎድሮስም “ትልቅ ሰው አልከው?” ብለው ተገረሙ። 

ይህ በሆነ በሦስተኛው ቀን የሹሙ ሚስት እና አሽከር እየተዝናኑ እያለ በጠራራ ፀሐይ የወደቀ መብረቅ ሁለቱንም ገደላቸው። ይህንን የሰሙት ንጉሡም ሹሙን አስጠርተው “በል ወዳጄ፥ ለትልቅ ሰው ነግረህ እኔንም እንዳታስጨርሰኝ ውጣልኝ” ብለው እንዳሰናበቷቸው ይነገራል። 

እኛስ ጉዳያችንን ለማን እንነግር ይሆን? ዕንባችንን በማን ፊት እናፈስ ይሆን? አቤቱታችንን ለማን እናቀርብ ይሆን? ለሰው ከተነገረ ቃል ይልቅ በእግዚአብሔር ፊት የቀረበ ዝምታ፥ በወዳጅ ፊት ከሚቀርብ እልፍ ምሬት ይልቅ በእግዚአብሔር ፊት የፈሰሰ ዘለላ እንባ፥ ለሹማምንት ከሚገባ የአቤቱታ ደብዳቤ ይልቅ ለመድኃኔዓለም የተነገረ አንድ የእውነት ቃል በእጅጉን ይበልጣል። እናቶቻችን ሲጸልዩ “የሚነግሩህን የማትረሳ መድኃኔዓለም” ይላሉ። እውነት አላቸው። ሰው ፈጥኖ ይዘነጋል፥ መድኃኔዓለም ግን የነገሩትን ፈጽሞ አይረሳም።

"አቡነ ዘበሰማያት ሲመታ እንጂ ሲወረወር አይታይም" የሚባለው ሰው የነገሩትን ለሰው መልሶ ሲነግር፥ መድኃኔዓለም ግን ምስጢሩን ጠብቆ ምላሹን ብቻ ስለሚሰጥ ነው። ከሰዎች መፍትሔ በመጠበቅ የባዘንንበት ዘመን ይበቃናል። ዝም ብለን ‘ለትልቅ ሰው’ ብንናገር ይሻለናል።

✍️ Fresenbet G.Y Adhanom 👇
ይህን የወንድማችንን ቻናል ተቀላቀሉ ታተርፉበታላችሁ
የፌስቡክ ገጽ:https://www.facebook.com/fre.asalib

ቴሌግራም: https://t.me/fresenbett

የአባቶች ምክር

12 Feb, 15:37


በእባቡ ፈንታ ገብርኤል ሊናገር ተነሳ..
ሔዋንም ምትክ ማርያም ተነሳች በሃሳቡ ልትስማማ

ሁለት መልእክተኞች ወደ ሁለት ድንግሎች ተላኩ..
ሰይጣን ምስጢርን ለሄዋን በእባቡ በኩል ነገረ..
ጌታም በመልአኩ በኩል የምስራቹን ለእመቤታችን ላከ..

ያዕቆብ ዘስሩግ: on the mother of God [eve’s legacy overturned] 🌿 @Father_advice🌿 

የአባቶች ምክር

12 Feb, 03:15


"ይቅርታ ማድረግ ተሸናፈነት አይደለም አሸናፈው እግዚአብሔር በመስቀል ላይ ሆኖ ይቅርታን ያደረገውም ኃይል አጥቶ አልነበረም፡፡ ሁሉንም ስለ ድፍረታቸውና ንቀታቸው በቅጽበት ሊያጠፋቸው ይቻለው ነበረ እንደ ባብሎን ስዎች ሰቃዮቹን በቋንቋ እንዳይግባቡ ማድረግም ይችል ነበረ፡፡ እርሱ እንኳን. ባያደርገው በድንጋጤና በመደመም ፈዘው የሚመለከቱትን የሰማይ ኃይላት ቅዱሳን መላእክቱን ሊያዛቸው ይችል ነበረ "ወይስ አባቴን እንድለምን እርሱም አሁን ከአሥራ ሁለት ጭፍሮች የሚበዙ መላእክት እንዲሰድልኝ የማይቻል ይመስልሃልን? " ማቴ 26: 53 እንዳለው ወደ አባቱ "ይቅር በላቸው" ብሎ በመለመን ፈንታ ለጥፋት የታዘዙ መላእክትን መጥራት ይችል ነበረ፡፡ በእርግጥ በመስቀሉ ዙሪያ ያሉ ጠላቶቹን ለማጥፋት የመላእክት ጭፍራ አያስፈልግም አንዱ መላአክ ቅዱስ ሚካኤል መቶ ሰማንያ አምስት ሽህ የሰናክሬምን ሠራዊት ሰይፍ እንኳን ሳይመዝዝ በግርማው  ብቻ እንደ ቆሎ አርግፎአቸው  እንደነበር አይረሳም (2ኛ ነገሥ 19:35)የሚካኤል ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ሠራዊተ መላእክቱ በዚያች ዕለት እንዲዘምቱ አልወደደም፡፡ በዚህ ምክንያት ያቺ ዕለት ለመላእክቱ አስጨናቂ ዕለት ነበረች፡፡
            ሕማማት ገፅ 335
🌿 @Father_advice🌿 

የአባቶች ምክር

12 Feb, 03:13


እኔኮ አፌ እንጂ ልቤ ንጹሕ ነው…” የምንል ብዙዎች ነን —ጀብድ እንደኾነ ነገር፤ መርዘኛ ምላስ ከክፉ ልብ ይቀልል ይመስል ነገር።

“እኔ ሲፈጥረኝም መደባበቅ አላውቅም፣ ሲፈጥረኝም
ግልጽ ግልጹን ነው የማወራው” እያልን ሰው የምናቆስል አለን። ግልጽነትን መረን ከመኾን ለመለየት ዕድሜና ብስለት ያልሰጠን —ስናሳዝን።

ሰው ግን በልቡ ከሞላው በቀር በአፉ ሊወጣ የሚችል ምንም ነገር የለም  ከልብ ሞልቶ ከተረፈው አፍ ይናገራልና።”ማቴዎስ 12፥34
እርግጥ ነው አንዳንዴ ሰው በብስጭት ከአፉ ያልተገቡ ቃላት ሊወጡ ይችላሉ። ደጋግሞ ደጋግሞ የታቀደ በሚመስል መልኩ ሰውን የሚሰብር ሰው ግን “እኔም ሰው ነኝ” ብሎ ሊመሳሰል አይችልም።

ይቅርታ” ማጣፊያው ሲያጥረን የምንመዘው ራስን የመከላከያ መሣሪያ አይደለም። “ይቅርታ” ማለት ድጋሚ ያንን ጥፋት ላለማድረግ መወሰን እንጂ፤ “የቀደመ ጥፋቴን እርሱልኝ” የሚል የብልጣ ብልጦች ይግባኝ ሊኾን አይገባም። ብዙዎች ግን ያለ ምንም ማመዛዘን ከአፋቸው አጥንትን የሚሰብር ቃል እያወጡ ደግመው ደግመው “ይቅርታበማለት የቃሉን ጉልበት ይፈትናሉ

ይቅርታ” ማለት ግን “ቀጣይ በደንብ አስቤ አወራለኹ” ማለት ጭምር ነው። ይቅርታ ማለት ግን “ቀጣይ በቂ መረጃ ሳይኖረኝ አላወራም” ማለት ጭምር ነው። ይቅርታ ማለት ግን “የማወራው ነገር የሚያመጣውን ቅጣትና ወቀሳ ሙሉ ለሙሉ እቀበላለኹ” ማለት ነው። ካልኾነ ግን “ይቅርታ” የፍቅር መግለጫ፣ የሕግ ፍጻሜ የኾነውን ያሕል … የክፉ  ሰዎች መሹለኪያ መንገድ  እና የተደጋጋሚ ጥፋቶች ማምለጫ ሆኖ ይቀጥላል።
—————————
ይቅርታ ከብዙ በሽታዎች የሚፈሰው መድኃኒት ነው፡፡ ራሳችንን ከመመረዝ ነጻ ማውጣት የምንችለው በይቅርታ ነው፡፡ ይቅርታ ልክ የተቀደደ ልብስን እንደሚሰፋ የሚያውቅ መርፌ ዓይነት ነው። በየቀኑ የይቅርታን መድኃኒት እየዋጥን መፈወስ ስንችል ለምን ይሆን ራሳችንን የምንመርዘው?
    © አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

"ይቅር ካላልክ ገነትም ይቅርብህ።"
አባ ኤፍሬም አረጋዊ


ከአበው መነኮሳት አንዱን "ትሕትና ምንድር ነው?" ሲሉ ጠየቁት። እርሱም ሲመልስ "የጎዳህ ወንድምህ ወደ አንተ መጥቶ ይቅርታ ሳይጠይቅህ በፊት ይቅር ካልከው እርሱ ትሕትና ነው።" አላቸው።ለካስ ይህም ትሕትና ነው!!!

╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲         ?
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ     ۹ᵉᵘˢⁱᵒⁿ
  

የአባቶች ምክር

11 Feb, 20:13


ሰላም ለሁላችሁ ይሁን!
አቤል አባቱ አዳም በታረደ በግ ምሳሌ መድኃኒት ከሲቲቱ ዘር እንደሚወለድና እንደሚመጣ ሲነግረው አምኖ ከመንጋው ነውር የሌለበትን በግ አቀረበ።
ከአባቱ የሚሰማውን የእግዚአብሔር ቃል አምኖ ስለሚያደርግ የዋህና ቅን መሆን ችሎ ነበር። ቃየን ግን የእግዚአብሔርን ቃል ሊነግረው ከሚችለው አባቱ ይልቅ ራሱንና ክፉ ልቡን ያደምጥ ነበር። ስለዚህ ጥሩ ሰው መሆን አቃተው። በእግዚአብሔር ያልተሰራ ሰው ነውና ቀናተኛና ቁጡ ነበር። ፊቱ ኮስታራም ነበር። መስዋዕቱም አልሰመረለትም። በአባቱ አፍ እግዚአብሔርን መስማትን ቸል ስላለ ተቅበዝባዥ ኮብላይ ሆነ። ነፍሰ ገዳይና በእግዚአብሔር ፊት አጉረምራሚ ሆነ። እግዚአብሔርን መስማትና እንዳለው መኖር ቅንና የዋህ ሰው ያደርጋል

✍️ዘማሪ ቀሲስ አሸናፊገ/ማርያም

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

11 Feb, 17:28


+• አንተ ማለት ለእኛ... •+

ኃጢአታችን ተጽፎ ተደጎሰ። ነውራችን ሞልቶ ፈሰሰ። ክፋታችን ከአጋንንት ባሰ። ደዌያችን ሊቀጥፈን ደረሰ። አሥር ለክተን አንድ መቁረጥ የማይሳካልን፥ መቶ አስበን አንዱ ስንኳ የማይሰምርልን ድውያን ሆንን። ከእኛ ወደ ትፋቱ የሚመለሰው ውሻ፥ ከእኛ ቀና ማለት የማይችለው እሪያ ተሻለ።

በዚህም ሁሉ ውስጥ ግን አንተን ማየት አላቆምንም። ለምን? ምክንያቱም...

አንተ የፍጥረታት ሀለዎታቸው፥ የመነኮሳት ሕይወታቸው፥ የጻድቃን ክብራቸው፥ የሰማእታት መመኪያቸው፥ የምእመናን አርአያቸው፥ የመላእክት ጌታቸው፥ የአጋንንት እሥራቸው፥ የኃጥአን ተስፋቸው ነህ።

ለእኛስ?

ጨለማን የገፈፍክ ብርሃናችን፥ የጥል ግድግዳን ያፈረስክ ኃይላችን፥ ረሃባችንን የምትገታ ምግባችን፥ ጥማችንን የምትቆርጥ መጠጣችን፥ ባለንበት የምታጸናን መልሕቃችን፥
የጥርጣሬን ነፋስ የምትገስጽ ሰላማችን፥ ኃጢአትን ቆርጠህ የምትጥል ሰይፋችን፥ ከደዌ የምትፈውስ መድኃኒታችን ነህ።

✍️ Fresenbet G.Y Adhanom

      🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

10 Feb, 17:31


"ጸሎትን የምንጸልየው እግዚአብሔር የማያውቀው ነገር ኖሮ አይደለም፤ ወደ እርሱ እንድንቀርብ፣ ቀርበን ወዳጆቹ እንድንሆን፣ ዘወትር እንዲረዳን፣ ራሳችንን ዝቅ ለማድረግ፣ ኃጢአታችንንም እንድናሰብ ነው እንጂ።"

ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

🌿 @Father_advice🌿 

የአባቶች ምክር

10 Feb, 12:41


ነገር ሁሉ ያደክማል፤ ሰው ይናገረው ዘንድ አይችልም፤ ዓይን ከማየት አይጠግብም፥ ጆሮም ከመስማት አይሞላም።
የሆነው ነገር እርሱ የሚሆን ነው፥
የተደረገውም ነገር እርሱ የሚደረግ ነው
ከፀሐይም በታች አዲስ ነገር የለም።
መክብብ 1፥8

©ዲ/ን አቤንኤዘር
🌿 @Father_advice🌿 

የአባቶች ምክር

10 Feb, 04:49


ሰው ለመዳን ንስሐ መግባት አለበት

ወደ እግዚአብሄር በንስሐ እንመለስ!
🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  

የአባቶች ምክር

10 Feb, 04:18


ጾመ ነነዌ

የአባቶች ምክር

09 Feb, 17:10


ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ አሁን ላይ ቢኖርና ወደ እኛ መልእክትን ቢጽፍ ምን የሚል ይመስላችኋል..??

በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ በኢትዮጵያ ላለችው የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን.. ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ እና ሰላም ለእናንተ ይሁን..
.
.
.
በመካከላችሁ አንዳንዶች በገድላት ተአምራት ውስጥ የተቀመጠውን ሁሉ ካልተቀበላችሁ በክርስትናችሁ አትቀጥሉም እያሉ ልባችሁን እያወኩ በቃል እንዳናወጧችሁ ሰማን.. የሚያናውጣችሁ ማንም ቢኖር ግን ፍርድን ራሱ ይሸከማል.. የሚያናውጣችሁ ይቆረጥ። እናንተ ግን መዳን የሚገኝበትን ነገር አስቀድማችሁ አውቃችኋልና በእርሱ ጸንታችሁ ኑሩ.. በዛም ላይ ደግሞ በመካከላችሁ ፍቅርን አብዙ.. እንጀራንም(ቅዱስ ቁርባን) ለመቁረስ በተሰበሰባችሁ ጊዜ ከጌታ ሥጋና ደም አትሽሹ..

በእነርዚህ ሁሉ ጽኑ አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል። ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።

@Apostolic_Answers

የአባቶች ምክር

09 Feb, 16:11


ወንድሜ ሆይ እንዲህ ለመሆን ተዘጋጅተሃል ወይ
ጌታ አንተን የሚውጥ ታላቅ ዓሳ ካዘጋጀልህ መፍራት መረበሽ እንዲሁም ማዘን የለብህም
ዮናስ በዓሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ሆኖ እግዚአብሄርን እንዳመሰገነው ሁሉ አንተም ማመስገን መጀመር ይኖርብሃል።
ዓሳው ቢውጥህም ሊጎዳህ እንደማይችል እርግጠኛ ሁን
ከእግዚአብሄር ፈቃድ ውጭ በአጠገብህ ሊደርስ አይችልም ነገር ግን ጊዜው ሲደርስ ቀድሞ ወደ ነበርክበት ደረቅ መሬት እንዲጥልህ ጌታ ያዝዘዋል
እግዚአብሄር የዓሣ ነባሪው ፈጣሪ አይደለምን ሕይወቱና አቅጣጫው የሚወሰነው በእግዚአብሄር እጅ አይደለምን?
ወንድሜ አንተ በመከራ ውስጥ ካለህ የዮናስን ዓሣ ነባሪ አስታውስ ከፍራቻ ትገላገላለህ መከራው እግዚአብሄር ፀጋውን ሊያበዛልህ ስለፈለገ ያዘጋጀው ዓሣ ነባሪ እንደሆነ የምታውቅበት ጊዜ ይመጣል።

       🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

09 Feb, 15:09


+ ጣዕም የሌለው ስብከት +
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ወደ ከተማችን አንድ ሰባኪ ሊሰብክ መጣ ፣ የመጣው ለመስበክ ፈልጎ አልነበረም፡፡ እኛን ለማዳን ጉጉት አድሮበት ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ሊያሰማን ጓጉቶ አልነበረም፡፡ በግድ ተገፍትሮ ፣ ተተፍቶ ፣ ተወርውሮ የመጣ ዓይነት ሰው ነበር፡፡ ወደ መሃል ከተማም አልገባም የከተማችን አንድ ሦስተኛውን ብቻ ከተጓዘ በኋላ ስብከቱን ጀመረ፡፡ የሰበከው ስብከት ሰላምታ የለውም ፣ መግቢያ የለውም ፣ መውጫም የለውም ፣ ማጽናኛም የለውም ፣ ‹ንስሓ ግቡ› የሚል አዋጅ የለውም፡፡ በጩኸት የተናገረው አንድ አስደንጋጭ ዐረፍተ ነገር ብቻ ነበር ‹‹በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች!!›› ከነነዌ ነዋሪዎች አንዱ የነነዌን ታሪክ ቢጽፈው የሚጽፈው እንዲህ ነበር፡፡

የነነዌ ሰዎች እግዚአብሔርን የማያውቁ አሕዛብ ናቸው፡፡ ዮናስ ደግሞ እነርሱ የማያውቁትን አምላክ የሚያመልክ ነቢይ ነው፡፡ ዮናስ ወደ እነርሱ የመጣው የማዳን ተልዕኮ ይዞ አልነበረም፡፡ ወደ አሕዛብ መላኩ አላስደሰተውም፡፡ ዮናስ ወደ ነነዌ የመጣው እንደ ሌላ ሰባኪ በየትኛውም ትራንስፖርት ተጉዞ ሳይሆን በዓሣ አንበሪ ወደ ነነዌ ተተፍቶ ነው፡፡ የተተፋ ሰባኪ እንዴት ደስ ብሎት ይሰብካል? እንኳን ስብከት ይቅርና ማንኛውም ሥራ ያለ ፍላጎት እንዴት ሊሳካ ይችላል? ዮናስ የነነዌ ሕዝብ እንዲድን ፍላጎትም አልነበረውም፡፡ እንዲያውም ከመጀመሪያውም ፍርሃቱ ‹ትጠፋላችሁ› ብሎ ተናግሮ ሳይጠፉ ቢቀሩስ የሚል ነበር፡፡

ዮናስ ወደ ከተማይቱ ዘልቆ ሲገባም በፍላጎት አልሰበከም ፤ የሰበከው ስብከት ተስፋ የሚያስቆርጥ ፣ እንደ ሰይፍ የሚቆራርጥ ነበር፡፡ የነነዌ ሰዎች የማያውቁትን አምላክ እንዲያውቁ ዕድል የሚሠጥ ትምህርት አልተሠጣቸውም፡፡ ዮናስም እንደ ኖኅ ‹ይኼንን ያህል ዘመን ተሠጥቷችኋል ተመለሱ› ብሎ አልሰበከም፡፡ መርከብ ሠርቶ ግቡም አላላቸውም፡፡ ‹በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች› ብሎ ጮኸ፡፡

የነነዌ ሰዎች ግን ‹ማን ነው የሚገለብጣት?› ‹ለምን ትገለበጣለች?› ‹ለመሆኑ አንተ ማን ነህ?› ‹ዝም ብሎ ትገለበጣላችሁ ይባላል? መጀመሪያ ትምህርት አይቀድምም?› አላሉም፡፡ራሳቸውን እንጂ ሰባኪውንና ስብከቱን ለመገምገም ጊዜ አልነበራቸውም፡፡ ‹‹እግዚአብሔርን አመኑ ለጾም አዋጅ ነገሩ ከታላቁ ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ››

አንድ ላይ ኃጢአት መሥራት ቀላል ነው ፤ አንድ ላይ ንስሓ መግባት ግን ይከብዳል፡፡ በሀገር ደረጃ ንስሓ መግባት ግን እጅግ ያስደንቃል፡፡ ‹ነነዌ የምትገለበጥ ከሆነ ሀገር እንቀይር› አላሉም ፤ ሀገር ከመቀየር ይልቅ ራሳቸውን መቀየር እንደሚሻል ተረድተው ነበር፡፡ ሁሉም እኩል ልቡ ተሰበረ ፤ ሁሉም ማቅ ለበሰ፡፡

የሰባኪው ስብከት ጣዕም የለውም ብለው አላማረሩም ፣ ‹ተስፋ የሚሠጥ ስብከት መቼ ሰማን› አላሉም፡፡ ሰባኪው እያዋዛ አላስተማራቸውም ፣ ምሳሌ አልነገራቸውም ፣ ቅኔ አልተቀኘላቸውም ፣ ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ይላል ‹‹የተላከላቸው ጨካኝ ሐኪም ነበር ፤ የያዘው መድኃኒትም የሚያቃጥል ነበር ፤ እንደ ሰይፍ የሚቆራርጥ ቃል ተናገራቸው ፤ እነርሱ ግን አቁስሏቸው ተፈወሱ››

የነነዌ ሰዎች ንስሓ ከላይ እስከታች ነበር፡፡ ነገሥታቱ ሳይቀር ማቅ ለበሱ፡፡ ‹‹ነነዌ ትገለበጣለች› ብሎ ሲናገር ንጉሡ ወታደሮች ልኮ ዮናስን ማሰር ይችል ነበር፡፡ ‹‹ምን በሀገራችን ላይ ታሟርታለህ?›› ብለው አፉን አላፈኑትም፡፡ መፍትሔውን ንገረን ያለውም የለም ፤ ችግሩ እነርሱ ናቸውና መፍትሔውንም ያውቁታል፡፡ ስለዚህ ራሳቸውን መውቀስ ወደዱ፡፡

ሀገሪቱ በአንድ ልብ አለቀሰች፡፡ ንጉሡ ፡- ሰዎችና እንስሶች አንዳች አይቅመሱ! ብሎ አዋጅ አስነገረ፡፡
ከቤተ መንግሥት ጾም የሚታወጅባት ነነዌ እንዴት የታደለች ናት? ‹‹መኳንንቶችሽ ማልደው የሚበሉ አገር ሆይ ወዮልሽ›› ተብሎ ከተጻፈ መኳንንቶችዋ የሚጾሙላት ሀገር እንዴት የታደለች ትሆን? (መክ. 10፡16) መቼም ሕዝብ ብቻ መጾሙ ነገሥታት ቢበሉ የተለመደ ነው፡፡ ነገር ግን እየበሉ የሚጾምን ሕዝብ መምራት እንዴት ይቻላል? ሲጠጡ እያደሩስ ሲጸልይ የሚያድርን ሕዝብ መምራት እንዴት ይቻላል?

ንጉሥሽ ላንቺ ማቅ ለብሶ ያለቀሰልሽ ፣ እንስሳት ሳይቀር የጾሙልሽ ነነዌ ሆይ ምንኛ የታደልሽ ነሽ? ሕዝብሽ ጾም ሲታወጅ የማያላግጡ ፣ ‹እኔ በፈለግሁበት ጊዜ ነው የምጾመው› ብለው የማይመጻደቁ ፣ እንኳን ከቤተ ክህነት ይቅርና ከቤተ መንግሥት የታወጀን ጾም በትሕትና የሚጾሙብሽ ነነዌ ሆይ ምንኛ የታደልሽ ነሽ? የዋሐን ሕጻናትን ጡት ከልክለው የፈጣሪን ርኅሩኅ ልብ የሚያስጨንቁ ፣ እንስሳትን ከውኃ ከልክለው ለምህላ የታጠቁ የነነዌ ሰዎች ምንኛ ድንቅ ናቸው፡፡

ቅዱስ ኤፍሬም ያቺን ከተማ በዓይነ ሕሊናው በጎበኛት ጊዜ እንዲህ ብሏል ፡-
‹‹የንጉሥ ቤት ግብዣ ተቋረጠ ፣ ንጉሥ ማቅ ለበሰ ፤ ንጉሥ ማቅ ከለበሰ ደግሞ የጌጥ ልብስ ይለብሳል፡፡ በዚያን ጊዜ በነነዌ ወርቃችሁን ብትጥሉ ማንም አይሰርቀውም፤ ሀብታችሁ ያለበትን ቤት ክፍት ትታችሁ ብትሔዱ ማንም ዘው ብሎ አይገባም፡፡ ወንዶች ወደ ሴቶች በምኞት አይመለከቱም ፤ ሴቶችም የሚያያቸውን ለመማረክ ጌጦቻቸውን አላደረጉም፡፡ ከልጆቻቸው ጋር አብረው ወደ መቃብር ሊወርዱ ነውና አረጋውያን በላያቸው አመድን ነሰነሱ፡፡ ወላጆች በልጆቻቸው ጥያቄ ተጨነቁ ፤ አብርሃም ልጁ ይስሐቅ ‹የመሥዋዕቱ በግ ወዴት ነው› ሲለው የተጨነቀው ጭንቀት በነነዌ ወላጆች ተደገመ››

ሶርያዊው የበተ መንግሥቱን ሁኔታም እንዲህ ይሥለዋል፡፡

‹‹የነነዌ ንጉሥ ወታደሮቹን ሰብስቦ እንዲህ አላቸውም ፡- ይህ ድል እንደተጎናጸፍንባቸው ውጊያዎቻችን አይደለም ፤ ከባዕድ ሀገር በተሰማው ዜና ኃያላኖቻችን ሳይቀሩ ተብረክርከዋል ፤ አንድ ዕብራዊ መጥቶ በቃሉ አብረከረከን፡፡የጀግኖች እናት ነነዌ አንድን ለብቻው የመጣ ደካማ ሰው ቃል ፈርታለች፡፡
ስለዚህ ወገኖቼ ፤ የማይፈርስ አጥር እንገንባ ፤ ይህች አጥር ንስሓ ናት ፤ ሥውር ጦርነት ታውጆብናልና ራሳችንን ሥውር መሣሪያ እናድርግ!!››

ዮናስ በነነዌ መመለስ ደስ አልተሰኘም ፤ ትንቢቱ ስለማይፈጸምለት ብቻ አይደለም፡፡ ‹‹የእስራኤል ሽማግሌዎች በሚቀማጠሉባት ሰዓት የነነዌ ሽማግሌዎች ሲያለቅሱ አየ ፤ ጽዮን በዝሙት እንደ ሰም ስትቀልጥ ነነዌ ታነባ ነበር›› እስራኤል ከፈጣሪ በራቁበት ሰዓት አሕዛብ የንስሓ ዕንባ ሲታጠቡ ሲያይ ክብር ከእስራኤል መልቀቁን አይቶ ተከፋ፡፡
ዮናስ እስከመጨረሻው ሰዓት የነነዌን መጥፋት ይጠባበቅ ነበር፡፡ ዮናስ ነነዌ የምትገለበጥበትን ቀን ሲቆጥር ነነዌ ደግሞ ኃጢአትዋን ትቆጥር ነበር፡፡

ዮናስ ስለ ነነዌ እንደ ሙሴ ‹እነርሱን ከምታጠፋ እኔን አጥፋኝ› አላለም ፤ በተቃራኒው ‹እነርሱን ካላጠፋህ እኔን አጥፋኝ› እስከማለት ደረሰ፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ነነዌን ወከሎ ነቢዩን እንዲህ ይለዋል ፡-
‹‹አንተ ዕብራዊ ሆይ ሁላችን ብንጠፋ ምን ይጠቅምሃል? አንተ ሰባኪ ሆይ በሁላችን መሞትስ ምን የተሻለ ነገር ይገኛል? የማቴ ልጅ ሆይ ወደ መቃብር በጸጥታ ብንወርድ ምን ታገኛለህ? በቃልህ ፈውሰኸን ልናመሰግንህ ስንመጣ ለምን ታዝናለህ? ዕጣህ ነነዌን ተናግሮ ያጠፋት ከመባል ይልቅ ተናግሮ ያተረፋት መባል ቢሆን አይሻልህም? መላእክት በሰማይ ሲደሰቱ አንተ ለምን ታዝናለህ? ዮናስ ሆይ ከእንግዲህ በስምህ የምትጠራ ናትና ነነዌን አመስግናት››

የአባቶች ምክር

09 Feb, 15:09


በእርግጥም ዮናስ በሽተኛ አክሞ ስለዳነለት የሚበሳጭ ሐኪም ሆነ፡፡ የነነዌ ሰዎች ግን የሰባኪው ማንነት ፣ የስብከቱ ውበት አልባነት ፣ የአነጋገሩ ለዛ ምክንያት ሳይሆናቸው ተስፋ በማይሰጥ ስብከት ተሰብረው ራሳቸውን አዳኑ፡፡ ብዙ ስብከት አልፈለጉም ፤ ክፋትን ለመተው እና ይቅር በለን ለማለት የተሰበረ ልብ እንጂ በእውቀት መሞላት አያስፈልግም፡፡ ኃጢአታችን ከነነዌ ሰዎች ከበለጠ ቆየ ፤ የጋራ ክፋታችንን በጋራ ንስሓ እንጠበው፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

የአባቶች ምክር

09 Feb, 13:35


አንድ ፈላስፋ
"በዛሬዋ ዕለት ጀንበር ወጥታ እስከምትጠልቅ እያንዳንዳቸው በስልሳ ዕንቁ ደቂቃዎች የተንቆጠቆጡ ሁለት ወርቅ ሰዓቶች ጠፍተውብኛል"
አግኝቶ ላመጣልኝ ወሮታውን አልከፍልም ለዝንተ ዓለሙ አምልጠውኛልና ሲል ተናግሯል።

እርስዎስ እስከ ዛሬ ስንት እንቁ ደቂቃዎች በከንቱ እንዳሳለፉ ወይም እንደጠፋብዎት አስበው ያውቃሉ?
ፈልጎ የሚያመጣልዎ የለም አልፈዋልና
ይልቅ አሁን በእጅዎ ያለውን ጊዜ በአግባቡ ይጠቀሙበት
    © ቬነሲያ

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

09 Feb, 08:09


“መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፥
በእርሱም ታመን፥ እርሱም ያደርግልሃል።”
— መዝሙር 37፥5

የአባቶች ምክር

08 Feb, 16:39


የእኔን ስራ ተወው ተግባሬን
  የመስቀሉን ነገር መርሳቴን
  አዚሜን አንስተህ  አንተን ልይህ
  ኢየሱስ ክርስቶስ አምላኬ ነህ

ቸርነትህ ነው የጠበቀኝ እስከ ዛሬ 
ቸርነትህ ነው ያደረሰኝ እስከ ዛሬ 
ላመስግንህ የኔ ጌታ በዝማሬ   
መክሊቴን ቀብሬ ባሳዝንህ
መብራቴንም ይዤ ባልጠብቅህ
በታላቅ ይቅርታ እንዳትረሳኝ
በፍቅር ጎብኝትህ ከሞት አውጣኝ
    ከቤትህ እርቄ መች ጠገብኩኝ
    በረሃብ በእርዛት ተቸገርኩኝ
    አምናለው አምላኬ እንድትምረኝ
    ለይቅርታ  መጣው ተቀበለኝ      
አንዳች እንደሌለኝ  አውቀዋለው
በአንተ ቸርነት ግን እመካለው
የከበደው ሸክሜ ይቀለኛል
ይቅርታ ለባሪያህ ይደርሰኛል
  በመቅደስህ ቆሜ ለመዘመር
  ስራህን ለትውልድ ለመመስከር
  እኔ ማነኝ ብዬ አስባለው
  አምላክ ቸርነትህን አደንቃለው         
በሰው እጅ መመካት አቁሜያለው
እረዳቴ አንተ ነህ አውቀዋለው
አንተ ከጠበከኝ በህይወቴ
ቅጥሬ አይደፈርም መድኃኒቴ
 

የአባቶች ምክር

08 Feb, 15:00


“ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም!
ወደ እናንተ እመጣለሁ።”
— ዮሐንስ 14፥18

የአባቶች ምክር

08 Feb, 13:24


"ለደካሞች ኃይልን ይሰጣል፥ ጉልበት ለሌለውም ብርታትን ይጨምራል። ብላቴናዎች ይደክማሉ ይታክቱማል፥ ጎበዛዝቱም ፈጽሞ ይወድቃሉ፤ እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።" (ኢሳ 40:29-31)

ዳዊት ስለ እርሱ እንዲህ ይላልና፦ ጌታን ሁልጊዜ በፊቴ አየሁት፥ እንዳልታወክ በቀኜ ነውና።
ስለዚህ ልቤን ደስ አለው፥ ልሳኔም ሐሤት አደረገ፥ ደግሞም ሥጋዬ በተስፋ ያድራል፤
ሐዋርያት 2፥25

   🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

08 Feb, 13:04


“ለእግዚአብሔርም ክብርና ምስጋና ከኢየሱስ ክርስቶስ የሚገኝ የጽድቅ ፍሬ ሞልቶባችሁ፥ ለክርስቶስ ቀን ተዘጋጅታችሁ ቅኖችና አለ ነውር እንድትሆኑ
የሚሻለውን ነገር ፈትናችሁ ትወዱ ዘንድ፥
ፍቅራችሁ በእውቀትና በማስተዋል ሁሉ ከፊት ይልቅ እያደገ እንዲበዛ ይህን እጸልያለሁ።”

— ፊልጵስዩስ 1፥9-11

ቅዱስ ጳውሎስ የፍቅር እዳ ዘወትር እዳ እንዲሆን ይመኛል
"እርስ በርሳችን ከመዋደድ በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ "ሮሜ 13፥8
የፍቅር መለኪያው ፍቅርን የትም ቦታ ላይ አለማቆም ነው
''ፍቅራችሁ ከፊት ይልቅ እያደገ እንዲበዛ" በዕውቀትና በማስተዋል ይሁን ይላል
እርሱ ወዳጃችን ብቻ አሊያም ፍቅርን ብቻ አላሞገሰም እንዲህ ዐይነት ነገሮች ከእውቀት የሚመነጩ ናቸውና ይህም ተመሳሳይ ፍቅርን ለሁሉም አትተግብረው
ይህ ስሜትን ከመከተል እንጂ ከፍቅር አይመነጭምና
በእውቀትም ሲል በምክኒያት እና በማስተዋል ማለት ነው
የሚሻለውን ነገር ፈትናችሁ ትወዱ ዘንድ ፍቅራችሁ በዕውቀት እና በማስተዋል ይሁን ለማለት ነው......

የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንዳስተማረው ገፅ28

    🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

07 Feb, 07:19


ቸር እንደ ሆነ ቅመሱ

“እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቅመሱ እዩም በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው ።”
                                 መዝ. 33 ፡ 8 ።

በጣም ደግ የሆኑ ሰዎችን እናውቃለን ። ሰው በልቶ የጠገበ የማይመስላቸው ፣ ያንተ እጅ አያጠግብህም በእኔ እጅ ጉረስ እያሉ በላይ በላዩ የሚያበሉ ሰዎች በዙሪያችን አሉ ። ሰለጠኑ የሚባሉት እንኳን በሰው እጅ ሊጎርሱ የራሳቸውንም እጅ ማመን አቅቷቸው ምግባቸውን ወደ አፋቸው የሚያደርሱት በማንኪያ ፣ በሹካና በቢላዋ ነው ። እንብላ ማለትንም እየረሱ ነው ። ሁሉንም ነገር ስሌት ውስጥ እየከተቱት ነው ። ባልና ሚስትም የየግላቸውን ይከፍሉ ይሆናል እንጂ አንዱ ባንዱ ገንዘብ ማዘዝ አይችልም ። በኅብረት ውስጥ ያለ ግለኝነት እንደ መሰልጠን እየታየ ነው ። ኅብረቱም አይቅርብኝ ፣ ግለኝነቱም አይቅርብኝ እየተባለ ነው ። ቀኑን ሙሉ ጋጋሪ አቁመው እንጀራ የሚያስጋግሩ ፣ የጋገሩትን እንጀራ መንገደኛ በልቶ ካልጨረሰው የሚያዝኑ ፣ እንግዳ መቀበል አገልግሎታቸው የሆኑ ሰዎችን እናውቃለን ። ከቤታቸው ደጃፍ አንድ ጎላ ንፍሮ ቀቅለው መንገደኛ ሁሉ ይበላው ዘንድ በየሰንበቱ የሚያስቀምጡ ቸሮችን አይተናል ። እያዘከሩ ሰው የሚሰበስቡ ፣ ማኅበራዊነትና መንፈሳዊነት እንዳይጠፋ የሚታገሉ ብዙዎች ናቸው ። “እኔ ቤት መጥቶ ሳይበላ ነው የሄደው” በማለት ተቀይመው የሚቀሩ ፣ እንደ እናቱ ባያየኝ ነው ብለው አዝነው የሚጎዱ የዋሃንን በትክክል እናውቃለን ። እነዚህ ደጎች ሳይጎድልባቸው እንደ ሰጡ አልፈዋል ። ስጡ ላለው አምላክ ታዘዋልና ተሰጥቶአቸዋል ። በብዛት ሳይሆን በበረከት መኖር ችለዋል ። ዛሬ ብዙ ገንዘብ አለ ፣ በረከት ግን የለም ። ለድሀ አንሰጥም ፣ ለማንድንበት መድኃኒት ግን ብዙ እናወጣለን  ። እግዚአብሔር ስንሰጥ በጤና እንደሚከፍለን አናውቅም ። እናውቃለን ብለን ሞኝ ሆንን ። የሌሎች የረሀብ ሕመም ሲሰማን የእኛ ሕመም እየተፈወሰ ይመጣል ።

ቸሮች በታኞች አይደሉምሰውን የሚያሰክር መጠጥ ፣ ሱስ የሚጋብዙ እነዚህ ጥይት የሚመጸውቱ ናቸው ። ቸሮች የሚዘሩ ናቸው ። ዘሪ መሬቱን ያውቀዋል ፣ ከርሞ ይመለስበታል ። ዛሬ ይዘራል ፣ ነገ እዚያው ያጭዳል ። ቸሮች አንድን ሰው ካለበት ሁኔታ እልፍ ማድረግ ፣ ከግብ ማድረስ ዓላማቸው ነው ። ቸር ሰው በበረሃ እንደ ተገኘ ውኃ ነው ፣ ያረካል ። ቸሮች ውስጣቸው ሕያው ነው ፣ እንቅስቃሴ ላይ ሲሆን ሊወጣ የሚታገላቸው ኃይል አለ ። ራሳቸውን በጣም ስለማያዩት ፣ የሌሎች ጉድለት ስለሚታያቸው ደስተኞች ናቸው ። ፍቅር ተግባራዊ ሲሆን ቸር ያደርጋል ። ስስታም ፣ ንፉግ ሰው አፍቃሪ አይደለም ። እነዚህ ሁሉ ቸሮች ክፉ ቀንን ያለፍንባቸው ፣ ጨለማችን ላይ ብርሃን ያወጁ ናቸው ። ያለ ደጎች ድጋፍ እዚህ አልደረስንም ። ተቀብለን እንዳልተቀበለ መካድ አይገባንም ። እነዚያን ቸሮች ማመስገን ፣ ዛሬ ተራው የእኛ ከሆነ በችግራቸው መርዳት ይገባናል ።

ቸሮች የእግዚአብሔርን ጠባይ የተካፈሉ ናቸው ። እግዚአብሔርን የሚመስሉ ፣ የሚንሰፈሰፉልን ፣ በረከትን በተርታ የሚያቀርቡልን ፣ ልባቸውም እጃቸውም የተከፈተልን ስጦታዎቻችን ናቸው ። እግዚአብሔርን የምናየው በቸሮች ውስጥ ነው ። ሰው ቅባትና የውበት ዕቃ ሲሸምት ይውላል ፤ እውነተኛ ውበት ግን ቸርነት ነው ። እግዚአብሔር በባሕርይው ቸር ነው ። ቸርነቱን በቃላት መግለጥ ፣ በእውቀት ማስረዳት አይቻልም ። የእግዚአብሔር ቸርነት ከሞት መንጋጋ ያስመልጣል ። ይህን ቸርነት ያልተካፈለ ሰው ፣ እንስሳና እጽዋት የለም ። ቸር አንድ ቀን ከሰዎች ብልጠት የተነሣ ቢስ ይሆናል ። “ቸር ሲያጠቁት ቢስ ይሆናል” እንዲሉ ። እግዚአብሔር ግን እያጠቃነው አሁንም ቸር ነው ።

ነቢዩ በመዝሙሩ፡- “እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቅመሱ እዩም በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው” ይላል ። እግዚአብሔርን ወደ ቤታችን መጋበዝ ፣ እግዚአብሔርን ተሸክሞ ወደ ሰዎች ቤት መሄድ ተገቢ ነው ። መቅመስ ማጣጣም ፣ ለመብላት መዘጋጀት ፣ መሞከር ፣ መለማመድ ነው ። የእግዚአብሔርን ቸርነት መቅመስ አለብን ። ቸርነቱን የሚቀምሱ ቸር ይሆናሉ ። ቀጥሎ፡- “በእርሱ የሚታመን ምስጉን ነው” አለ ። ቸር የማንሆነው ቢጎድልብኝ ብለን ነው ። ቸርነት ግን በእግዚአብሔር በመታመን የሚገኝ ነው ። ስጡ ላለው ቃል ታዝዤ አይጎድልብኝም ብሎ ማመን ይፈልጋልእምነት ልምምድ ነው ። መቅመስ ፣ ማየት ይገባል ። የቸርነት ሕይወት ደስ ያሰኛል ። የተቆለፉ ትልልቅ ቤቶች ፣ ምግብ እየተበላሸ የሚደፋባቸው የባለጠጋ ሳሎኖች ይህን ቸርነት ቢለማመዱ የሞት ጥላ ይገፈፍላቸዋል ። እንዴ በየምሽት በሚሊየን እያወጡ ይጋብዙ የለም ወይ? ቢባል እርሱ ንግድና ጉራ እንጂ ቸርነት አይደለም ። ቸርነት የባለጠጎች ዕዳ ሳይሆን ሁሉም የሰው ልጅ የሚለማመደው ሀብት ነው ። በእጃችን ማጉረስ ባንችል በእጃችን የቆሸሸውን ምስኪን ማጠብ እንችላለን ። የሰውነት ክፍሎቻችን የቸርነት መሣሪያ ናቸው ። ቸርነቱን የምንቀምሰው በጸሎት ነው ። የሚለምኑ ይቀበላሉ ፣ ቸርነቱንም ያያሉ ።

እግዚአብሔር በቸርነቱ የሰጠን ሕይወትን ነው ። የሕይወት ዋጋዋ ስንት ነው ? ያኖረን ቸርነቱ ነው ። እስትንፋሳችን በአፍንጫችን ላይ የተንጠለጠለች ፣ ለመሄድ የተዘጋጀች ናት ። እስትንፋሳችንን በአፍንጫችን ያሳደረልን ፣ ያዋለልን ጌታ ቸር ነው ። ይህን ቸርነቱን ማጣጣም ፣ ማመስገን ፣ መመስከር ይገባል ። በእግዚአብሔር የሚታመን ሰው ቸር ነው ።

እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቅመሱ ።

🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

07 Feb, 06:05


ወንድሜ
አንተ በመከራ ውስጥ ካለህ የዮናስን ዓሣ ነባሪ አስታውስ። ከፍራቻ ትገላገላለህ። መከራው እግዚአብሔር ጸጋውን ሊያበዛልህ ስለፈለገ ያዘጋጀው ዓሣ ነባሪ እንደሆነ የምታውቅበት ጊዜ ይመጣል። የዚህ ዓለም የባሕር ዓሣዎች ብዙ ስለሆኑ ስትዋጥ እንዳይከፋህ መጠንቀቅ ይኖርብሃል። የመጀመሪያው ባህታዊ ጻድቁ አባ ጳውሊ የተናገረውን መዘንጋት የለብህም "ከመከራ መራቅ የሚወድ ከእግዚአብሔር ይርቃል" ብሏል። በእውነት መከራ የጸሎት ትምህርት ቤት ነው። "በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ጮኽሁ እርሱም ሰማኝ። በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ። ቃሌንም አደመጠ" ዮናስ 2፥3

   አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

06 Feb, 17:00


ድንግል ምን መታደል ነው ማርያም ሆይ ጸጋሽ በዛ ወልደሽ ጡት ያጥባሽው ዕጹብ የዓለሙን ቤዛ

የሚያስገርም ጥበብ ነው እጅግ የሚደንቅ ከህሊና በላይ ነው ከአይምሮ ሚረቅ ታላቁን መገለጥ ነው የምናወራው የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ መሆኑ እንዴት ነው

እንዴት ሆኖ እረ እንዴት ተከናወነ ቤቱ መንገድ አምላክ ሰው ሰው አምላክ ሆነ በማህፀንሽ ያደረው ብሩክ ነው ቅዱስ ይገባዋል አምልኮ ስግደት በመንፈስ

አማኑኤል እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ የዓለም ቤዛ ክርስቶስ ባንቺ አደረ ያዳኛችን የበጉ ታላቅ አዳራሽ ሰላም ላንቺ ድንግል ሆይ ጸጋ የተሞላሽ

ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

06 Feb, 07:25


አንተሰ አንተ ክመ
"አንተ ግን ያው አንተ ነህ፥
ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም" መዝ 101፣ 27

እግዚአብሔር በህልውናው ፣ በባሕርይው ፣ በአንድነቱ፣ በሦስትነቱ፣ በመለኮታዊ ግብሩ ጽኑ ነው። በባሕርይው መለወጥ የለበትም። እርሱ ራሱ "እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም" ብሏል ( ሚል.3፥7 )። ብዙ ሰዎችና ሁኔታዎች ደርሰን ስንመለስ፣ ቆይተን ስንመጣ፣ ተኝተን ስንነቃ ከስፍራቸው ይታጣሉ። የቦረቅንበት መንደር  ፣ የሕፃንነታችን መፈንጫ ከዓመታት በኋላ እንዳልነበር ሆኗል:: ያሳደጉን ሽማግሌዎች ፣ ለእኛ መልካም ያደረጉ ደጎች ትዝታቸው እንጂ ህልውናቸው አይገኝም። እነርሱ ከቦታቸው የሉም፣ እኛም አንድ ቀን ከቦታችን እንታጣለን። በአባቶቻችን ዘመን የነበረ ፣ በልጆቻችን ዘመን የሚኖር የሁልጊዜ አዲስ እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ በሚያረጅ ዓለም ውስጥ የሚያጽናናው የእርሱ አዲስነት ብቻ ነው።

ዛሬ በእግር የምንጓዝባቸው፣ በመኪና የምንፈስባቸው ጎዳናዎች አንድ ዘመን የባላባቶች ሳሎን፣ የጎበዞች ማደሪያ ክፍል ነበሩ። ይህ ዓለም የሚገዛው ለለውጥ ሕግ ነው። ለዚህ የለውጥ ሕግ አእምሮአችንን ካላሰናዳን ብዙ ነገሮች ግራ ሊያጋቡን ይችላሉ። የሚሆነው  ሲሆን የነበረ ነው። እግዚአብሔር ግን ሰማይ ዘፋኑ፣ ምድር መከዳው (መደገፊያው) ሆኖ ለዘላለም ይኖራል። የሌለበት ቦታ የለምና የሚታጣበት ስፍራ አይኖርም።

የትላንት መልካችንን ዛሬ እናጣዋለን። ጥቁሩ ፀጉር ሽብቷል ፤ የጠራው ፊታችን ተሸብሽቧል። ለስላሳው እጃችንና ልባችን ሻክሯል። ያ ጽኑ ጉልበት ደክሟል። እንዳለ ያለ እግዚአብሔር ብቻ ነው።

የነበረው እንዳልነበር ለመሆን ይቸኩላል። ሙዝየም የገቡ ቅርሶችና ዐፅሞች በአንድ ዘመን አስፈሪ ነበሩ። ዛሬ ግን መፈራታቸው ወድቆ በመስተዋት ተዘግተው ይጎበኛሉ።  ዓለም ነበር ለመባል ይቸኩላል። እግዚአብሔር ግን ሕያው ነውና ነበር አይስማማውም::

የዛሬ ክፉዎች ትላንት እጃቸውን ቁርጠው የሚሰጡ ደጎች ነበሩ። የእያንዳንዱ ቀን ተግዳሮት ጠባያችንን ሊነጥቀን ይታገለናል። ቁጠኛ የነበሩ አግብተው፣ ወልደው ቀዝቃዛ ሆነዋል። እግዚአብሔር ግን ጠባዩ የማይጨምር የማይቀንስ ጽኑ ነው። የመታመኛ አምላክ የሆነውም በጠባዩ የጸና በመሆኑ ነው።

የጋራ የቃል ኪዳን አገሮችና ጦሮች ፈርሰዋል። አንድነትን አንድ ዓይነት ለማድረግ የፈለጉም ብዝኃነትን ሰርዘዋል፡፡ የራሳቸውን ቋንቋና ባሕል በኃይል ጭነዋል። እግዚአብሔር ግን በማይጨፈለቅ ሦስትነት፣ በማይበታተን አንድነት ለዘላለም ይኖራል ።

ሺህ ዓመት ንገሥ የተባለ ንጉሥም ዓመቶች ያልቁበታል። ብዙ ውጥን የነበራቸው ሊቃውንትም መቃብር ገብተዋል። እግዚአብሔር ግን ዓመቶች አያልቁበት ዘላለማዊ፣ አይለወጥ የሁልጊዜ ያው ነው። የሰዎች መለዋወጥ፣ የሁኔታዎች መደፍረስ ግራ ሲያጋባን "አንተ ግን ያው አንተ ነህ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም" ብለን እንዘምር። እኛ አሮጌና አዲስ ዓመት እንላለን። እግዚአብሔር ግን በዘላለም አዲስነት ይኖራል።

አንተ ያው ስለ ሆነህ የትም ዞረን ስንመጣ እናገኝሃለን። ስንለወጥ ብትለወጥ አናገኝህም ነበር። ታይቶ ለመጥፋት በሚቸኩለው ፣ ሕልም እልም በሆነው ዓለም ከመደናገር ባንተ ድነናል። ክብርና ምስጋና ለአንተ ይሁን
አሜን
🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

05 Feb, 12:05


ዝምታ ራሳችንን የምናይበት ጥሩ መጽሔት(መስታወት) ነው። አብዛኛውን ሰዓት በወሬ ተጠምዶ የሚውል ሰው ራሱን የሚመለከትበት እድል አይኖረውም። በሌሎች ኃጢአት ሲፈርድ፣ ሲተችና ሲያማ ስለሚውል የራሱን ስህተትና ውድቀት ለማወቅ ይቸገራል። ቀኑን ሙሉ እንዲሁ ሲያወራ የሚውል ሰው የሚያሳዝነው ዝም አለማለቱ ብቻ ሳይሆን የሚጠቅም ነገር የማይናገር መሆኑም ጭምር ነው። ነገር ግን ማር ይስሐቅ እንደሚለው "አንድ ሰው ከሰዎች ጋር ብዙ ማውራት ባቆመ ጊዜ ወደ ራሱ ይመለሳል። በእግዚአብሔርም ፊት ምግባሩን ማቅናት ይጀምራል"

የሥጋ አንደበታችንን መቆጣጠርና ዝም ማስባል ስንችል የነፍስ ጆሮአችን ንቁህ መሆን ይጀምራል። ስለዚህም ነፍሳችን ሳይሰለች ከልባችን ደጅ ቆሞ የሚያንኳኳውን የመልካሙን እረኛ ድምጽ ትሰማለች። ደጇንም ከፍታ ታስገባዋለች። ከእርሱም ጋር ለእራት ትሰየማለች።(ራእይ 3፥20) በእውነት ይህ እንደ ምን ያለ መታደል ነው? ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር "የዝምተኛ ሰው ጆሮ የእግዚአብሔርን ድንቆች ትሰማለች" ያለው ለዚህ ይሆን?!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

05 Feb, 04:44


ከፍ ካለው በላይ

የመጣው ሄደ፣ የሄደውም አይመጣም። የነገሠው ተሻረ ፣ የተሻረው ዳግም አይቀባም። የተሞገሰው ተረገመ፣ የተወገዘው ስሙ ያው ሆኖ ቀረ ። ባለ ጠጎች ደኸዩ ፣ አለ የሚባል ጠፍቶ ነበር የሚል ቃል በምድር በረከተ። ጎዳናው ይወስዳል ይመልሳል፣ ሕይወት ግን ያንን ጓደኛ፣ ያንን ውብ ዘመን፣ ያንን ክብር፣ ያንን አንቱታ አትመልስም ። በዘመኑ ታላቁ እስክንድር ዓለም ፈራው ፣ ዛሬ ፈሪዎች አይፈሩትም። እግዚአብሔር ማነው ? ያለው ፈርዖን ሰጠመ ፣ እስካሁን ትንሣኤ አላገኘም ። አውሮፓ ዱር ሳለ ግሪክ አሰለጠነች፣ ዛሬ ግሪክ በዕዳ ተዘፍቃ ብዙ ረዳት ሊያቆማት አልቻለም ። የጰጰሱ ተሳሳቱ ሲባል ይወገዛሉ፣ አስኬማና በትረ ሙሴ መልሱ ይባላሉ ።

ቆንጆዎች ቆንጆ ነበርሁ ሲሉ ማን ያምናቸዋል? ያ ውበት ላይመለስ ጥላሸት ተቀብቷል ። ያ ተክለ ቁመና ፣ ያ እንደ ፀሐይ የሚያበራ ገላ ፣ ያ መሬት ለመርገጥ የሚጸየፍ እግር ዛሬ ጭቃ ላይ ተኝቷል ። ቤቱን ለደቂቃ የማያምነው ለዘላለም ጥሎት ሄዷል። የሚሳሳለትን ንብረት ዛሬ የማያውቀው ሰው ይጫወትበታል ። የሕይወት መንገድ መሄጃ እንጂ መመለሻ የለውም ። እኛ ወደ እነርሱ እንጂ እነርሱ ወደ እኛ አይመጡም። የዓለም ከፍታ በዝቅታ ፣ ዙፋን በመቃብር ፣ ዳኝነት በእስረኛነት ይለወጣል ። ያንተን ልዕልና ፣ አማኑኤል ሆይ ያንተን ክብር ካላሰቡ ልብን ያደክማል

ከፍታህ ዝቅታ የለውም፡፡ ነበረ ተብሎ ታሪክ አይነገርልህም። ሁልጊዜ ያው ነህእንዳንተ የሸመገለ የለም፤ እንዳንተም አዲስ የለም ። መጀመሪያ ላይ ቆመህ መጨረሻውን ታውቃለህ፤ እያወቅህ ግን ዝም ትላለህ። ለድሀው እንጀራ ትሰጣለህ ፣ መልሶ ሲክድህ የሚያማልድ ሰባኪ ትልክበታለህ ። በልካችን አትከፍለንም ፣ በልክህ ታኖረናለህ ። መሰላል ላይ የወጡ ይወርዳሉ። በአየር ላይ የተንሳፈፉ መሬት ይናፍቃሉ ። ከፍ ካሉት በላይ ከፍ ያልከው አንተ ግን በማይነገር ቅድስና ትኖራለህ ። ለጠባይህ ዝቅታ ፣ ለዙፋንህ መናወጥ የለበትም ። የዛሬው አሸናፊ የሁልጊዜ አሸናፊ አይደለም ። የዛሬው ፈራጅ የሁልጊዜ ፈራጅ አይደለም ። የእኔ አምላክ ግን የማለፍን ሥርዓት ድል ትነሣለህ ። ሳትቀበል ትሰጣለህ ። ሳትሾም ትሾማለህ ። አዎ ከፍ ካሉት በላይ ከፍ ብለሃል ። ልዕልናህን ልዕልናህ ያመሰግናል ። በክረምቱ ዝናብ ነጠብጣብ ልክ ብትመሰገን ልክህ አይደለም ።

በምድር ላይ ያንተ ትልቅ ነገር እኛ ነን ። በሰማይና በምድር የእኛ ትልቅ አንተ ሁንልን ! 

           🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

03 Feb, 20:51


ምክኒያት ፈልገን መታረቅ ሲገባን ምክኒያት ፈልገን የምጣላ! የማያጣላ ነገር ቢኖር እንኳ የሚያጣላ ነገር የምንፈልግ
«ይህ የአባቶቻችን የሐዋርያት ትእዛዝ ነው። ሰው በልቦናው ቂምንና በቀልን ቅንዓትንና ጠብን በባልንጀራው ላይ በማንም ላይ ቢሆን አይያዝ።»

" ፍቅራችሁ ያለ ግብዝነት ይሁን። ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ፤
በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤ ሮሜ 12 ፥9 "

🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

03 Feb, 19:54


ድንኳን የሚሆነው ምድራዊ መኖሪያችን ቢፈርስ፥
በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና።”
— 2ኛ ቆሮ 5፥1
🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

03 Feb, 15:09


#እስከማዕዜኑ

የደስታ ቀናት እንደ ሰማይ ሲርቁ…
ክፉ ቀናት እንደ አጀብ ሲከቡን…

የተጠበቀው ቀርቶ የልተጠበቀው ሲሆን…
ሞት አንድ አማራጭ ሆኖ ሲቀርብ…

ውስጣዊ ሰላማችን ሲረበሽ…
እርጋታ ፈጽሞ ሲጠፋ….


…ያን ጊዜ “ጌታ ሆይ እስከመቼ?” እንላለን፡፡ ደግሞም በልጅነት ሰቆቃ በአባቶቻችን አንደበት #እስከማዕዜኑ? እንላለን፡፡

እንባችን እንደ መጠጥ፣ ሀዘናችንም እንደ መብል ይሆንብናል፡፡ የቀናት ጠንሳሽ የሆነው አባታችን እግዚአብሔር ግን “ታገስ፣ የመጠበቅን ፍሬ ትበላለህ” ማለቱን ይቀጥላል፤

እኛም “አምላኬ ሆይ፣ እንዴት ልታገስ? እሰከመቼስ ልጠብቅ?” እንላለን፡፡ ከዚያም ቃሉን ያስታውሰናል፣ የቀደሙ ቅዱሳኑን አብነት ይዘክርልናል፡፡

“እንደ ልጄ እንደ ዳዊት ቀና ሁን፣ እንደ ታላቁ ታጋሽ እንደ ኢዮብ ሁንልኝ፣ የቀጠርኩልህ ቀን ሲደርስ የመከራህን ቀናት አስረሳሃለሁ! እንደ ተወዳጁ ልጄ እንደ ወልድ ትንሳኤህ እስኪገለጥ እርጋታን ገንዘብህ አድርግ!” ይለናል፡፡ በቅዱስ ቃሉ ያባብለናል፡፡

የህማማት ቀናቶቻችን እንደ ግዮን ወንዝ የረዘሙ ሲመስሉ፣ የህዝባችን እፎይታ፣ የሀገራችን ሰላምና መረጋጋት እንደ ጌታችን መምጫ ቀን ሲርቁብን፣ ህይወት ከንቱ መኖርም ምናምንቴ መስሎ ሲታይ… የምድረ በዳው መንከራተት ከንዓናችንን ሊያስረሳን ሲደርስ፣ መራርነት ተስፋችንን ሊያስጥለን ሲተጋ፣ የስጋ ድካም ከዘለዓለማዊው እጣ ፈንታችን ሊያናጥበን ሲል… ያን ጊዜ የታላላቅ አባቶች ምክር፣ የቅዱሳን ጥበብ፣ የታጋሾች ምስክርነት ያስፈልገናል፡፡

© አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
እስከማዕዜኑ

🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

03 Feb, 03:40


" ክርስቶስ በሥጋ መጣ፥
እርሱም ከሁሉ በላይ ሆኖ
ለዘላለም የተባረከ አምላክ ነው፤ አሜን።” — ሮሜ 9፥5
     
      🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

02 Feb, 18:59


ውበት ሐሰት ነውደም ግባትም ከንቱ ነው፤
እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች።”
ምሳ 31፥30

🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

02 Feb, 18:56


+የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም +
(በመምህር ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ )

የአባቶች ምክር

02 Feb, 04:39


ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ለንስሓ ልጁ በሰርጓ ቀን መገኘት ባለመቻሉ የላከላት ደብዳቤ

“ልጄ! ለሰርግሽ የነፍስ አባትሽ እኔ ጐርጐርዮስ ይህን ግጥም ስጦታ አድርጌ ልኬልሻለሁ፡፡ አባት ለሚወዳት ልጁ ሊሰጣት የሚችለው የተሻለው ምክርም ይህ እንደ ኾነ አምናለሁ፡፡

“ኦሎምፒያታ ሆይ፥ እውነተኛ ክርስቲያን ለመኾን ያለሽን ፍላጎት ዐውቃለሁና በደንብ አድምጪኝ! እውነተኛ ክርስቲያን እንዲሁ መኾንን የሚመኝ ብቻ ሳይኾን እንደዚያ ለመኾን ሊጥር ይገባዋል፡፡

“ከኹሉም በላይ፥ እግዚአብሔርን ልታከብሪውና ልትወጂው ይገባሻል፡፡ ከእርሱ ቀጥሎም በቅዱስ ወንጌል እንደ ታዘዘው እንደ ጌታችንና መድኃኒታችን [ኢየሱስ ክርስቶስ] አድርገሽ ባልሽን ልታከብሪውና ልትወጂው ይገባሻል፡፡ ስለዚህ እጠይቅሻለሁ! ጌታዋንና ፈጣሪዋን [ኢየሱስ ክርስቶስን] የማታከብርና የማትወድ ሴት በዚህ መንገድ ባልዋን እንዴት አድርጋ ልታከብረውና ልትወደው ትችላለች?

“በጋብቻሽ ውስጥ የትዳር አጋርሽ ይኾን ዘንድ እግዚአብሔር መርጦ ለሰጠሽ ባል ያለሽ መውደድ፣ ስሜትና ፍቅር እጅግ ኃያል ሊኾን ይገባዋል፡፡ ይህ ሰው አሁን የሕይወትሽ ዓይን፣ የልብሽም ደስታ ነውና፡፡

“እግዚአብሔርን እንደምትወጂው፥ ባልሽንም ያለ ቅድመ ኹኔታ ልታከብሪውና ልትወጂው ይገባሻል፡፡ አንቺ ሴት እንደ ኾንሽና ታላቅ የኾነ ዓላማና ግብ እንዳለሽ፥ ኾኖም ዓላማሽና ግብሽ የቤትሽ ራስ ሊኾን ከሚገባው ባልሽ የተለየ እንደ ኾነ ዕወቂ፤ ተረጂም፡፡ ባንቺ ዕድሜ ላይ ያሉት አንዳንዶች ኹለቱም ፆታዎች እኩል [ራስ ናቸው] ብለው የሚሰብኩትን አትስሚ፤ የጋብቻንም ግዴታ [ወይም ዋና ዓላማ] አስቢ፡፡ እነዚህን ግዴታዎች [ወይም ዓላማዎች] ስታውቂ የቤተሰብሽን ተግባራት ለማከናወን እንደ ምን ያለ ትዕግሥትና ጽናት እንደሚያስፈልግሽ ታውቂያለሽና፡፡ እንደ ሚስት እጅግ ጥንካሬን ገንዘብ የምታደርጊውም በዚህ መንገድ ነው፡፡

“ወንዶች እንዴት በቀላሉ የሚቈጡ መኾናቸውን በርግጥ ልታውቂ ይገባሻል፡፡ አይችሉም፤ ብዙ ጊዜም እንደ በረኻ አንበሳ ይኾናሉ፡፡ እንግዲህ ሚስት ጸንታ ልትቆምና የነፍስ ልዕልናዋን ልታሳይ የሚገባት በዚህች ቅጽበት ነው፡፡ አንበሳን የማስለመድ ሥራ መሥራት አለብሽ፡፡ አንበሳን የሚያስለምድ ሰው አንበሳ ሲያገሳ የሚያደርገው ምንድን ነው? ከየትኛውም ጊዜ በላይ ዝም ጸጥ ይላል፡፡ በጸጥታውና በርጋታውም የአንበሳውን ቊጣ ይቈጣጠራል፡፡ በርጋታና በለሆሳስ ኾኖ ያናግረዋል፤ ይደባብሰዋል፤ በቀስታ ያሻሸዋል፤ በጥቂት በጥቂቱም አንበሳው ቊጣውን ይተዋል፡፡

“ባልሽ ስሕተት ሲሠራ በፍጹም ልትነቅፊው፣ ልትንቂው ወይም ልታስነውሪው አይገባም፡፡ በተመሳሳይ መንገድ አንድ መሥራት ያለበትን ነገር ባይሠራና ከዚሁ የተነሣም ውጤቱ ደስ የማያሰኝ ቢኾን፣ ወይም እጅግ የምትፈልጊውና አግባብ ነው ብለሽ የምታስቢውን ባያደርግ እንኳን ባልሽን መናቅ ከአንቺ ልታርቂ ይገባል፡፡ ክፉዎች አጋንንት ዘወትር ቤታችሁን ለማፍረስና የጥንዶች መንፈሳዊ አንድነትን ለመበተን እንደሚሞክሩ ዕወቂ፡፡”

(ከገብረ እግዚአብሔር ኪደ ከትንሿ ቤተክርስቲያን መጽሐፍ የተወሰደ)
🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

01 Feb, 16:50


ኢትዮጵያ እንደ ርብቃ በሆድዋ ያሉ ልጆችዋ እየተዋጉባት  "እንዲህ ከሆነ ይህ ለእኔ ምኔ ነው?" ብላ እየጮኸች ነው:: ለእናት ልጆችዋ ቢጋደሉላት ምን ይጠቅማታል? ሟቹም ልጅዋ ገዳዩም ልጅዋ ነውና ከመቁሰል በቀር ምንም አታገኝም:: ዳዊት ልጁ አቤሴሎም ሌላ ልጁን አምኖንን በገደለ ጊዜ ያለቀሰውን ለቅሶ ኢትዮጵያ ታለቅሳለች:: በዚህ መካከል ምስኪኑ ወገናችን ይረግፋል:: እጅ እጁን ሲቆርጥ ደስታና ፉከራ የለም:: ብንችል በዚህ ሰዓት በጸጸት እንጸልይ:: ካልቻልን ደግሞ ቢያንስ ዝም እንበል:: የሀገርን ሰላም የምትፈልጉ ሁላችሁ ከሩቅ በለው በለው ማለት ትታችሁ ማረን ማረን በሉ::

በሩቅ ሆነን አይነካንም ብለን እየፎከርን በምስኪኑ ላይ እሳት የምናነድ አንሁን:: በወገን ሞት ተደስተን እንደባዕድ ሀገር ጦርነት የድል ዜማ ብናዜም እግዚአብሔር ከሰማይ ሆኖ ይፈርድብናል::

ከራሳችን በላይ ሌላ ጠላት የለንምና ጌታ ሆይ ከራሳችን አድነን:: ኢትዮጵያ እጅዋን ወደ እግዚአብሔር መዘርጋት ትታ ራስዋ ላይ ቃታ የሳበችበት ዘመን ላይ ደርሰናል:: ጌታ ሆይ በዓይነ ምሕረትህ ተመልክተህ እኛው ያነደድነውን እሳት አብርድልን:: በትግራይ በአማራ በኦሮሚያ ያሉ በዚህ እሳት ዙሪያ የሚማገዱ ወገኖቻችንን ከጥፋት ይጠብቅልን:: በግራም በቀኝም የተሰለፉት በድህነት የሚኖሩ አንድ ውኃ የጠጡ የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው::  አባቶቻቸው ሳይለያዩ አብረው ከብዙ ጠላት ጋር ታግለው ባቆዩአት መሬት ላይ ወንድማማቾች ጦር እየተሳበቁ ነውና በቸርነትህ ልባቸውን አራራ:: ወንድምን ገድሎ እንደ ቃየን ከመቅበዝበዝ በቀር ትርፍ እንደሌለ አሳያቸው:: ጠግቦ በልቶ ሳያድር ተመስገን ማለትን ያልተወ ሕዝብህን ጌታ ሆይ በምሕረትህ አድነው::

(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)

🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

01 Feb, 12:51


ቤትና ባለጠግነት ከአባቶች ዘንድ ይወረሳሉ
አስተዋይ ሚስት ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ናት።
— ምሳሌ 19፥14

  🌿 @Father_advice🌿 
   ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

የአባቶች ምክር

21 Jan, 19:10


አንዱ እንዲህ ይላል
ከአምስት አመት በፊት ጓደኛየ ይሞታል እና ስልኬ ሲጠራ የጓደኛዬ ቁጥር ነበር

አነሳሁትና የ10 አመት ልጅ ነበር ያናገረኝ አጎቴ እንዴት ነህ..? ሳይክል ልትገዛልኝ ትችላለህ? አለኝ እኔም እሺ ግን ታውቀኛለህ እንዴ አልኩት ?
ልጁም አይ አላውቅህም ግን የአባቴና የጓደኛው ፎቶ አለ ፎቶው ላይም ስልክና መልዕክት አለ

የምትፈልጉት ነገር ኑሮ እኔ ከሌለሁ ወደዚህ ስልክ
ደውሉና ጠይቁ ይላል ለዚያ ነው የደወልኩልህ አለኝ
🥺

እንደ አዲስ ቁጭ ብየ ማንባት ጀመርኩ ይህን ያህል ነው ጓደኛየ
በእኔ ላይ እምነት ያለው


''... ባልንጀራንም እንደ ራስ መውደድ በሙሉ ከሚቃጠል መሥዋዕትና ከሌላው መሥዋዕት ሁሉ የሚበልጥ ነው ”
— ማርቆስ 12፥33

🌿 @Father_advice🌿 
            ⌲               
          ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

21 Jan, 14:53


+• ጊዜው ገና ነው •+

አንድ ምንጩ የማይታወቅ አስተማሪ የሆነ አፈ-ታሪክ አለ። በዚህ አፈ-ታሪክ መሠረት፥ ከእለታት በአንዱ ቀን አጋንንት ስብሰባ አደረጉ ይባላል። ይህንን ስብሰባ የጠራው የአጋንንቱ አለቃም “ዓለምን ሁሉ ከእኔ ጋር ለማሰለፍ እፈልጋለሁ። ምን ይደረግ? ማንንስ ልላክ?” ብሎ ጠየቀ። ከሥሩ ያሉትም አንድ በአንድ እየተነሱ አሳቦችን ማቅረብ ጀመሩ። 

አንዱ ተነሳና፥ “እኔን ብትልከኝ፥ ፈጣሪ የለም ብዬ ሰዎችን ማሳመን እችላለሁ!” ብሎ ተናገረ። የአጋንንቱ አለቃ ግን፥ “እርሱ አይሠራም። ብዙዎቹ አያምኑህም። ፈጣሪ እንዳለ ያውቃሉ።” ብሎ መለሰ። 

ሌላኛው ተነሳና፥ “እኔን ከላክኸኝ፥ ገነትም ሆነ ሲኦል የሚባል ቦታ እንደሌለ አሳምናቸዋለሁ!” አለ። የአጋንንቱ አለቃ ግን፥ “እርሱም አይሠራም። ብዙዎቹ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ ያውቃሉ።” ብሎ መለሰ። 

ሌላው ደግሞ ተነሳና፥ “እኔን ላከኝ። ፈጣሪም አለ፥ ገነትም አለ፥ ሲኦልም አለ፤ ነገር ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ ለማሰብ ጊዜው አሁን አይደለም ብዬ አሳምናቸዋለሁ።” አለ። የአጋንንቱ አለቃም ደስ እያለው “ይህ ጥሩ መንገድ ነው!” በማለት አሳቡን ተቀበለና ላከው ይባላል።

ሰይጣን ማዘግየት ጥሩ ስልት መሆኑን ስለሚያውቅ፥ ለማዘግየት ይፋጠናል። በሐዲስ ኪዳን ላይ ቅዱስ ጳውሎስ "ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና፥ እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ፥ ሰይጣን ግን አዘገየን።” (1 ተሰ 2:18) ሲል እናገኘዋለን። ሰይጣን ላያስቀረን ይችላል፥ ግን ቢያንስ ሊያዘገየን ብዙ ይሞክራል።

እርሱ ዓለማዊ ጓዞቻችንን ለአፍታ ስንኳ አውርደን ከእግዚአብሔር ጋር ስላለን ግንኙነት እንድናስብ አይፈልግም። ስለ ጸሎት ብታስብ፥ "አሁን ደክሞሃል። ጊዜው አይደለም። ሌላ ጊዜ ትጸልያለህ" ይልሃል። ለመጾም ብትዘጋጅ "አሁን ጉልበት ስለሚያስፈልግህ ብላ። የምትጾምበት ጊዜ አይደለም፤ ሌላ ጊዜ ትጾማለህ።" ይልሃል። ለመስገድ ብትዘጋጅ "ኧረ ተረጋጋ፤ ጊዜው አይደለም፥ ጾም ሲገባ ትሰግዳለህ" ይልሃል። ንስሃ ልትገባ ብትዘጋጅ "ቆይ እንጂ፥ ዘልለህ ጨርሰህ አንዴ ብትታጠበው አይሻልም?" ለማለት የሚቀድመው የለም። ቅዱስ ቁርባን ልቀበል ነው ካልክ "አንተኮ ገና ነህ፥ ለወደፊት ጣጣህን ስትጨርስ ቀስ ብለህ አመቻችተህ ትቆርባለህ" ብሎ ያዘናጋሃል።

በዚህ ሁሉ መዘግየት ውስጥ መልአከ ሞት መቼ እንደሚመጣ ማን ያውቃል? ለመንፈሳዊ ነገር ስንነሳ፥ ሰይጣን "ጊዜው ገና ነው" ማለቱ አይቀርም። እኛ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል“ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (2ኛ ቆሮ 6፥2) እንደሚል እናስታውስ። ለመዳናችን ቀጥሮ አንስጥ።

✍️ Fresenbet G.Y Adhanom

join👇
🌿 @Father_advice🌿 
            ⌲               
          ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

21 Jan, 10:52


አንድ ሰው አንድ አባት ጋር ሂዶ ብዙ ሀጢአት እንደሰራ ነገራቸውና ሲጨርስ 2 ስገድ አሉት ደስ ብሎት ሄደ

እኒህ አባት የበቁ ስለ ነበሩ እግዚአብሄር በመቅደሱ ተገለጠላቸው እና ምን ሆነው ነው ያጠፋውን የበደለውን እያወቁ 2 ስገድ እንዴት ይሉታል

አምላኬ ሆይ እኔ እንደውም ጨካኝ ነኝ
አንተ ብትሆን ኖሮ እኮ ሀጢአትህ ተሰረየችልህ ዝም ብለህ ሂድ ትለው ነበር አሉት

እግዚአብሔር ታጋሽና ምሕረቱ የበዛ፥ አበሳንና መተላለፍን ይቅር የሚል — ዘኍልቁ 14፥17-18

join👇
@father_advice
            ⌲               
          ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

20 Jan, 05:20


እኛ ስንጨርስ እሱ የሚጀምር አምላክ ስቡሕ ዘተሰብሐ፡፡

በቃና
ሰዎች የተዘጋጁበት ኹሉ አለቀ፡፡ የሰው ዝግጅት ሲያልቅ የማያልቀው የእግዚአብሔር ተአምር ጀመረ፡፡

የማያልቀው ወይን እንዲቀዳ፥ ልጇም ተአምሩን ይጀምር ዘንድ ምክንያት የኾነች "የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፡፡"

አንባቢ ኾይ
ይኽ ታሪክ የአንድ የሰርግ ቤት ታሪክ ብቻ እንዳይመስልኽ፡፡ ይኽ የዐለም ታሪክ ነው፡፡ ስድስቱ ጋኖች ስድስት ሺ ዘመናትን ይወክላሉ፡፡ 5500 ዐመተ ፍዳን ማለት ነው፡፡
በስድስት ሺ የዘመን ጋኖች ውስጥ የነበረው ትንቢትና ተስፋ ሲያልቅ
'እኔ የወይን ግንድ ነኝ' ብሎ የነገረን ጣፋጩ ወይን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም መወለዱን… ያስረዳል፡፡

መ/ር ስሙር አላምረው

join👇
@father_advice
            ⌲               
          ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

20 Jan, 03:56


የፍቅር ወይን እንዳለቀ ከእነርሱ ቀድማ የምታውቀው ድንግል ማርያም ግን ‹‹ፍቅርኬ አልቦሙ›› ‹‹ፍቅር እኮ የላቸውም›› ትላለች፡፡ ልጅዋ ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ በጠብ ውኃ የተሞላውን ቤት ዳግመኛ በወይን ጠጅ ፍቅር ይሞላዋል፡፡
ይኼኛው የወይን ጠጅ ደግሞ እንደበፊቱ ሰው ሠራሽ ወይን የሚያልቅ አይደለም፡፡ ያለፈውን የሚያስንቅ ‹ቀድሞም የፍቅር ወይን አልነበረንም ፤ መናኛ ነበር የያዝነው!› የሚያሰኝ ነው፡፡
ይህን ስንል ግን ባልና ሚስት ራሳቸው ሊያስተካክሏ
ቸው የሚገቡ ጉድለቶቻቸውን ሳያስተካክሉ የእመቤታችንን ምልጃና ተአምር ብቻ ይጠባበቁ ማለታችን አይደለም፡፡ በቃና ምልጃዋ ችግር እንዲፈታ ለአገልጋዮቹ ‹የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ› ብላ ድርሻ ሠጥታ እንደነበር ባለትዳሮችም ሊያደርጉት የሚገባ ነገር አለ፡፡ ትዳራቸው በፍቅር ወይን እንዲሞላ ‹የእኔስ ችግር ምንድር ነው?› ‹የእናቱን አማላጅነት ከጠየቅሁ ከእኔ ምን ማድረግ ይጠበቃል?› ብለው በትሕትና በመታዘዝና ድክመታቸውን በማስተካከል ትዳራቸውን መታደግ አለባቸው፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስን ወደ ጋብቻ ሕይወት መጥራት የሚቻለው ሥጋና ደሙን በመቀበል ነው፡፡ በደቀመዛሙርት የተመሰሉት ካህናትን በንስሓ አባትነት ይዞ ጋብቻን በሥጋ ወደሙ ወስኖ ዘወትር በመንፈሳዊ ሕይወት መንገድ በእግዚአብሔር ቃል ለሚጓዝ ሰው የወይን ጠጁ ዳግም ላያልቅ ይሞላል፡፡
በጋብቻ ሕይወት መንገድ ላይ ላላችሁ ሁሉ የቃናዋ እንግዳ እመቤታችን በአማላጅነቷ ፤ የተወደደ ልጅዋ ደግሞ በአምላካዊ ሥራው በቤታችሁ ተገኝቶ መንፈሳዊውን የፍቅር ወይን ይሙላላችሁ አሜን!

(ቃና ዘገሊላ ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ)
  🌿 @Father_advice🌿 
  

የአባቶች ምክር

20 Jan, 03:56


{ትዳርና የወይን ጠጅ}>>
(በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)

ጌታችን በሰርጋቸው ላይ የተገኘላቸው የቃና ዘገሊላዎቹ ሙሽራና ሙሽሪት እንደማንኛውም ሙሽሮች ሁሉ አቅማቸው የፈቀደውን ያህል ለሰርጋቸው ሲዘጋጁ ሰንብተዋል፡፡ እንደባሕላቸው ስለሚለብሱት ልብስ፣ ስለሚደግሱት ድግስ፣ ስለሚጠሩአቸው እንግዶች ብዛት፣  ስለሚቀርበው ምግብ፣ ስለሚጠጣው የወይን ጠጅ ከዘመድ ወዳጆቻቸው ጋር ሲደክሙ ከርመዋል፡፡ በሰርግ ዕለት ግን የሚያጋጥም ነገር አይታወቅምና ብዙ እንግዳ ይሸኛል የተባለው የወይን ጠጅ ሳይታሰብ አለቀ… የማይሽር ቁስል የሚጥልባቸውን፣ የሰው መተረቻ የሚያደርጋቸውን ይህን ክስተት ግን እነርሱ ሳይሰሙ በሰርጉ ቤት የነበረችው እመቤታችን በምልጃዋ ፈታችው፡፡ ለተወደደ ልጅዋ ነግራ የጎደለውን አስሞልታ ባማረ ሁኔታ ዳረቻቸው፡፡ የጠሩት የሰማይና የምድር ንጉሥ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ውኃን ወይን ጠጅ አድርጎ አከበራቸው፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ ውኃና የወይን ጠጅ ከጠብና ከፍቅር ጋር ተያይዘው ሲነገሩ እናገኛለን፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን ስለ ፍቅር ሲናገር ወይን ጠጅን በንጽጽር ያነሣል ‹‹ፍቅርህ ከወይን ጠጅ ይልቅ መልካም ነው!›› ‹‹ፍቅርሽ ከወይን ጠጅ ይልቅ እንዴት ይሻላል!›› ‹‹ከወይን ጠጅ ይልቅ ፍቅርህን እናስባለን›› ‹‹ወደ ወይን ጠጁም ቤት አገባኝ፥ በእኔ ላይ ያለው ዓላማውም ፍቅር ነው።›› እያለ ማለት ነው፡፡ (መኃ.፩፥፪፣፬፤፪፥፬፤፬፥፲) በአንጻሩ ስለ ጠብ ሲያነሣ ደግሞ ውኃን ያነሣል፡፡ ‹‹ብዙ ውኃ ፍቅርን ያጠፋት ዘንድ አይችልም›› ‹‹የጠብ መጀመሪያ እንደ ውኃ አፈሳሰስ ነው›› ‹‹በዝናብ ቀን የሚያንጠባጥብ ቤትና ጠበኛ ሴት አንድ ናቸው›› ብሏል፡፡ (መኃ.፰፥፯፤ምሳ.፲፯፥፲፬፤፳፯፥፲፭) በአጠቃላይ በመጽሐፍ ቅዱሳዊ አተረጓጎም ውኃ የጠብ ምሳሌ ሲሆን ወይን ጠጅ ደግሞ የፍቅር ምሳሌ ነው፡፡
በቃና ዘገሊላ ሰርግ ቤት በመጀመሪያ የወይን ጠጅ ተጠምቆ ዝግጁ ሆኖ ነበረ፡፡ ይህ የወይን ጠጅ የጠማቂ ባለሙያ የተጠበበበት ነበር፡፡ ሙሽሮቹ ያላቸው ወይን ጠጅ ሰርጉን እንደሚያዘልቃቸው ተማምነው የነበረ ቢሆንም ወይኑ ግን ባልጠበቁት ፍጥነት አለቀ፡፡ ከዚያ በኋላ በዚያ ሰርግ ቤት ለሚመጣ እንግዳ ሊቀርብ የሚችለው ብቸኛ መጠጥ ውኃ ብቻ ነበር፡፡ ለሙሽሮቹ የተሻለ የሚሆንላቸው ከዚያች ደቂቃ ጀምሮ ሌላ እንግዳ ጨርሶ ባይመጣ ነው፡፡ ወይን ጠጅ በሚጠጣበት ሰርግ ቤት ውኃ ከሚጠጣ ለእንግዳውም ባይመጣ ይሻለዋል፡፡
በሁሉም የትዳር ሕይወት ውስጥ በወይን ጠጅ የተመሰለው ፍቅር መጀመሪያ ይኖራል፡፡ መጠኑ ይለያይ እንጂ ሁሉም ማለት ባይቻልም ባለትዳሮች በአመዛኙ ከጋብቻ በፊት ቢያንስ ወደ ጋብቻ እንዲያመሩ ምክንያት ሊሆን የቻለ ፍቅር ይኖራቸዋል፡፡ ብዙዎች የቃና ሙሽሮች በወይን ጠጃቸው እንደተማመኑ ሁሉ በፍቅራቸው ዘላቂነት እርግጠኞች ነበሩ፡፡ ከጋብቻ በፊት የነበራቸው ፍቅር ከጋብቻ በኋላ አብሯቸው እንደሚዘልቅ ተማምነው ነበር፡፡ አንዳንድ ጥንዶች እንደውም በፍቅራቸው ዘላቂነት ላይ ካላቸው እርግጠኝነት የተነሣ ሌሎች ባለትዳሮች ሲጣሉ ሲያዩና ሲሰሙ ‹ሰው እንዴት ይጣላል? እንደኛ ስላልተፋቀሩ ነው!› ብለው ይፈርዳሉ፡፡ ‹የፈለገ ነገር ቢከሰት እኛ መቼም እንዲህ አንሆንም!› ብለው ይዝታሉ፡፡
በሰርግ ሰሞንና በመጀመሪያዎቹ የጋብቻ ወራት ባልና ሚስት በፍቅር ወይን የተሞሉ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የጫጉላ እርከን (Honeymoon stage) ላይ እያሉ ሁሉም ነገር ደስታና ሰላምን የተሞላ ሊሆን ይችላል፡፡ እንደቃናው ሰርግ ቤትም ይህ የፍቅር ወይን በልበ ሙሉነት ሲቀዳ ይቆያል፡፡ ሆኖም ሰው የጠመቀው ወይን ማለቁ እንደማይቀር በጋብቻ ሕይወትም እንዲሁ በወይን የተመሰለው ፍቅር እያለቀ እያለቀ መምጣቱ አይቀርም፡፡ ከዚያ በኋላ በዚያ ጋብቻ ላይ ሊገኝ የሚችለው ውኃ ይሆናል፡፡ ባል ለሚስቱ ፍቅር የተባለውን ወይን ማቅረብ ሲሳነው፣ ሚስትም እንዲሁ ወይን ማምጣት ሲያቅታት አንዳቸው በአንዳቸው ሁኔታ እየተበሳጩ ይሔዳሉ፡፡ ወይን ከሌለ ደግሞ እንደ መፍትሔ ቆጥረው አንዳቸው ለአንዳቸው የሚያቀርቡት ውኃን ይሆናል፡፡ ውኃ ደግሞ ከላይ በመጽሐፉ እንዳየነው የማያቋርጥ ጠብ ነው፡፡ ባል ለሚስቱ ሚስት ለባልዋ እንደ ውኃ የቀዘቀዙ ይሆናሉ፡፡ እርስዋ ‹‹እውነት ግን ይኼንን ሰው ነበር ባል ብዬ የተቀበልሁት?›› ብላ ትብከነከናለች፡፡ እርሱም ‹‹ምን ነክቶኝ ነበር?›› እያለ ይቆጫል፡፡ ወደ ቤታቸው የሚመጣ ሰውም ፊት ሊያቀርቡት የሚችሉት ወይን የላቸውም፡፡ የመጣ ሰው የሚያየው ጠባቸውን ብቻ ስለሚሆን የእንግዳ አለመምጣት ለሁለቱም የተሻለ ይሆናል፡፡ ያያቸው ሰው እርስ በእርሳቸው ያላቸውን ጥላቻ ሲመለከት ‹‹እነዚህ ሰዎች አስቀድሞስ እንዴት ተፋቅረው ሊጋቡ ቻሉ? የለም ቀድሞውኑም ፍቅር ባይኖራቸው ነው!›› ብሎ ይደመድማል፡፡ ልክ ነው ወይን አልቆ ውኃ ሲቀርብ በዚያ ቤት ወይን ኖሮ የሚያውቅ አይመስልም፡፡
በእንዲህ ዓይነት ኑሮ የሚሠቃዩ ብዙዎች ናቸው፡፡ ባልጠበቁት ሁኔታ የፍቅር ወይን አልቆባቸው የጠብ ውኃን መጋት የለመዱ፣ የተጋቡበትን ቀን የሚራገሙ፣ ጋብቻን ለማንም ሰው የማይመክሩ ፣ ባላገቡ ሰዎች ዕድል የሚቀኑ ፣ ፍቺ እንዳይፈጽሙ ፈርተው ልጆቻቸውን ላለመበተን ብለው አብረው የሚኖሩ፣ ባልና ሚስት ሆነው አልጋ ለይተው የሚተኙ፣ ሰላምታ እንኳን የማይሠጣጡ ወይን ጠጅ አልቆባቸው ቤታቸው በጠብ ውኃ ጎርፍ የተሞላባቸው እጅግ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ለዚህ ችግር መፍትሔ ፍለጋ ብዙዎች ይደክማሉ፡፡ ችግራቸውን ሊፈቱላቸው ለማይችሉ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው የወይናቸውን ማለቅ ተናግረው መዘባበቻ ሆነው የቀሩ ብዙዎች ናቸው፡፡
መፍትሔ ይሆናል ብለው በራሳቸው መንገድ ሔደው ሌላ ድጋሚ ሊያልቅ የሚችል በሰው ጥበብ የተጠመቀ የወይን ጠጅ ሊያመጡ ሞክረው ባጭር ጊዜ ያለቀባቸውም ብዙዎች ናቸው፡፡ መፍትሔው ግን በዚሁ በቃና ዘገሊላ ሰርግ ቤት ታሪክ ላይ ተቀምጧል፡፡ ችግሩ መፈታት የሚችለው በዚያ ሰርግ ቤት በተፈታበት መንገድ ብቻ ነው፡፡ የቃና ወይን ጠጅ ሲያልቅ አይታ ‹‹ወይን እኮ የላቸውም›› ብላ ለምና ያስሞላችው ወላዲተ አምላክ በባለ ትዳሮች መካከል ካለች ችግሩ ያለጥርጥር ይፈታል፡፡ ስም ለሚያጠፉ ለሰዎች በመንገር ጊዜ ማጥፋት አያስፈልግም፡፡ በቃና ዘገሊላ እንዳደረገችው ድንግል ማርያም በባለ ትዳሮችም ቤት ገብታ ‹‹ፍቅር እኮ የላቸውም›› ትላለች፡፡
አንዳንድ ባለ ትዳሮች በጋብቻቸው ውስጥ ወይን መጉደሉን እንደ ቃና ዘገሊላዎቹ ሙሸሮች ፈጽመው አያውቁም፡፡
በየጊዜው አስታራቂ ከመካከላቸው እየገባ ሊያስማማቸው ሲሞክር የጠባቸው መንሥኤ ከድሮም አብሯቸው የኖረ ተራ ምክንያት ይሆናል፡፡ የማያጣላው አጣልቷቸው በውኃ ቀጠነ ሲነታረኩ ይገኛሉ፡፡ በተደጋጋሚ ሽምግልና እየታረቁም እንኳን ሰላም አያገኙም፡፡ ‹‹እስቲ ምን አዲስ ነገር ተገኘና ነው ዛሬ ተነሥተሽ እንዲህ የምትዪኝ›› ‹‹ዛሬ ነው ወይ ይኼ ነገር የታየህ›› እየተባባሉ በማያጠግብ ምክንያት መናቆራቸው ለሁለቱም ግራ ይገባቸዋል፡፡ ያልተረዱት ነገር ግን አለ፡፡ በየሰበቡ እንዲጣሉ የሚያደርጋቸው ፍቅራቸው ማለቁ ነው፡፡

የአባቶች ምክር

18 Jan, 21:20


ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።
አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና።
እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ።
ገላትያ 3፥27_29


በዓለም ዙሪያ የምትገኙ በክርስቶስ ክርስቲያን የተሰኛችሁ ሁሉ
እንኳን አደረሳችሁ!

የአባቶች ምክር

18 Jan, 21:16


† ዮርዳኖስ †

★ ወንዞች ማርና ወተት ሆኑ ማለት ምን ማለት ነው?★

ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዶኖስ ወንዝ በተጠመቀ ጊዜ ወንዞች ማርና ወተት ሆኑ ብለው ሊቃውንት በትርጓሜ መጻሕፍት የጻፋልን ለምንድነው ብለን መጻሕፍት በጥንቃቄ ማየት ያስፈልጋል።

ጥንት በዘመነ ኦሪት በሰዎች ኃጢአትና በደል ምክንያት እግዚአብሔር በውሃ ይቀጣቸው ነበር።ለምሳሌ በነብዩ በኤልሳዕ ዘመን ሕዝበ እስራኤል እግዚአብሔርን ሲበድሉ ውሃቸውን ለደዌ እንዲሆንባቸው አድርጎት ነበር ፤ ከውሃው የጠጡ ሁሉ ክፋኛ ይታመሙ ነበር ሴቶች ይጨነግፋ ነበር ፣ወላዷን መኻን ያደርጋት ነበር።በኋላ ነቢዩ ኤልሳዕ ከምንጩ ሄዶ ጸልዮበት ጨው ቢጨምርበት ውሃው ተፈውሷል።2ነገሥት 2፥19

በዘመነ ሙሴ ደግሞ ግብጻውያን በእግዚአብሔር ላይ ሲያምፁና በደላቸው እጅግ ሲበዛ ውሃቸውን ሁሉ ደም አድርጎባቸው ነበር።ከብዙ ጭንቀትና ስቃይ በኋላ ሙሴ በጸሎት ውሃቸውን ፈውሶታል።ዘፀአት 7 ፥14

በኖኅ ዘመን የሰው ልጅ ክፋት በምድር ላይ እጅግ ሲበዛ እግዚአብሔር ምድርን በጥፋት ውሃ አጥለቅልቆ ብዙዎችን ቀጥቷል።

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ከባሕርይ አባቱ ከአብከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስና ከራሱ ጋር ለማስታረቅ ሰው ሆኖ በዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ ግን በውሃ ይመጣ የነበረው መርገምና ቅጣት ሁሉ ቀረ ፣ውሃን ለምሕረት ለይቅርታ መገለጫ አድርጎ ተጠመቀበት።ለዚህ ነው ሊቃውንት ጌታ ሲጠመቅ ውኆች ማርና ወተት ሆኑ ያሉት ይህ ማለት የውሃ መርዝነት፣ደምነት፣ንፍር ሆኖ ማቃጠል ቀረ ለማለት ነው እንጂ የከብት ወተትና የንብ ማር ሆነ ለማለት አይደለም።እንዲህ ዓይነት አተረጓጎም Alligorical expression ይባላል ።

ደግሞ ልናስተውለው የሚገባው በጥማችን ሰዓት ውሃ ከማርና ከወተት ይበልጥ ያረካናል።ውሃ በጠማን ሰዓት ጥማችንን የሚያረካልን ራሱ ቀዝቃዛ ውሃ ነው የዛኔ ውሃ  እንደ ማርና ወተት እጅግ አስደሳች መጠጥ ሆኖ እናገኘዋለን።ስለዚህ የሊቃውንቱ ሐሳብ ይህንን ለመግለጽ የተጻፈ ነው።
join👇
@father_advice
 ⌲               
          ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

18 Jan, 20:38


+ አንዲት ዘለላ እንባ😢 +

አባ አንቶኒ ኮኒያሪስ የተሰኙ የግሪክ ኦርቶዶክስ ካህን በጻፉት "ፊሎካሊያ: የኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት ቅዱስ መጽሐፍ" (Philokalia: The Bible of Orthodox Spirituality) በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ
ለማስተማሪያነት ያሰፈሩት እንዲህ የሚል አንድ ጥንታዊ አፈታሪክ አለ

እግዚአብሔር ከዕለታት በአንዱ ቀን ቅዱሳን መላእክቱን "ወደ ምድር ወርዳችሁ ከሁሉ ይልቅ እጅግ ብርቅዬ የሆነውን ነገር ይዛችሁልኝ ኑ" ብሎ ያዛቸዋል::

አንድ መልአክ ሌላ ሰው ለማዳን ብሎ ራሱን መስዋእት ያድረገን ሰው የደም ጠብታን ይዞ ተመለሰ:: እግዚአብሔርም "መልአክ ሆይ ፥ በእርግጥ ይህ በእኔ ዓይን እጅግ የተወደደ ነው:: በዓለም ያለው እጅግ ብርቅዬ ነገር ግን አይደለም::" አለው::

ሌላኛው መልአክ ደግሞ ሌሎችን ስታስታምም በያዛት በሽታ ምክንያት ያረፈችን የአንዲት ነርስ የመጨረሻ እስትንፋስ ይዞ መጣ:: እግዚአብሔርም "መልአክ ሆይ ፥ በእርግጥ ስለሌሎች የሚከፈል መስዋእትነት በእኔ ዓይን እጅግ ታላቅ ዋጋ አለው:: ሆኖም ግን በዓለም ያለው እጅግ ብርቅዬው ነገር ይህ አይደለም" አለው::

በመጨረሻም አንድ መልአክ ንስሃ ገብቶ ወደ እግዚአብሔር የተመለሰን ኃጢአተኛ አንድ ዘለላ እንባ ይዞ መጣ:: እግዚአብሔርም "መልአክ ሆይ ፥ በዓለም ላይ ያለውን እጅግ ብርቅዬ ነገር አመጣህ - ይኸውም የገነትን በር የሚከፍት የንስሃ እንባ ነው!" በማለት ተናገረ::

ቸሩ መድኃኔዓለም ለምህረት ይኾንልን ዘንድ ከሚፈሰው እንባ አንዷን የእንባ ዘለላ ይቀበልልን ? እርሱ እንደ ቸርነቱ ያድርግልን! ሐዋርያው "ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ" (ፊል 4፡4) ብሎናልና፤ ሁኔታ ሳይገድበን እናመሰግንሃለን! እንዘምርልሃለንም!

  🌿 @Father_advice🌿 
  

የአባቶች ምክር

18 Jan, 19:43


ለሌሎች ይደርስ ዘንድ ሼር ያድርጉ

ይህቺን ቻናል ተቀላቀሉና ከስንክሳሩ የተወሰዱና በስንክሳሩ ያልተካተቱ የቅዱሳንን ታሪክ እያነበብን ከሕይወታቸው እንማር

መዓዛ ቅዱሳን

https://t.me/meaza_kidusan12

የአባቶች ምክር

17 Jan, 12:53


ሰው አያከብርህም?

ሰው ሲሰድብህ ትናደዳለህ? የሚያዋርድ እና አንገት የሚያስደፋ ነገር ቢያደርግብህስ በቁጣ ትገነፍላለህ? ግን አንድ ጊዜ ቆም ብለህ እስኪ ራስህን ጠይቅ? ከአንተ በላይ አንተን የሰደበ፣ ከአንተ በላይ አንተን ያዋረደ እና አንገት የሚያስደፋ ነገር ያደረገብህ አለ? ከአንተ በላይ አንተነትህን ዋጋ ቢስ ያደረገ ማን ነው? አንተ አይደለህ?

አንተው መልስ!

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚለው
ለሰው ጠላቱ ማንም አይደለም ራሱ ነው። የሕይወትን ዛፍ ቸል ብሎ ወደ እጸ በለስ የሚሮጠው፣ የብርሃኑን ልብሱን ጥሎ ቅጠል ማገልደም የሚያምረው፣ ከወንድሙ ጋር በሰላም ከመኖር ይልቅ ደሙን አፍስሶ ሲቅበዘበዝ መኖር የሚመርጠው ሰው ራሱ ነው።

ሌላውን ከመውቀስህ በፊት መጀመሪያ አንተ ራስህን ታከብራለህ? በአንተ ዘንድ የአንተነትህ ዋጋው ስንት ነው? ከልብስ ይልቅ ሰውነትህን ከመብልስ በፊት ነፍስህን ታስቀድማለህ? አንተ ራስህን በክፋት እና በበደል እንዲህ እያጎሳቆልክ “ማንም አያከብረኝም” እንዴት ትላለህ?

ዲያቆን አቤል ካሣሁን
🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

17 Jan, 04:04


አንድ ድንጋይ ወደ መስታወት ቢወረወር መስታወቱን ይሰብረዋል
ወደ አንድ ተራራ ቢወረወር ግን ተራራውን ያሳድገዋል; አንተም እንደ ተራራው ሁን እንጂ እንደ መስታወቱ አትሁን!”

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

16 Jan, 09:46


+• የቀስት ጸሎቶች •+

የጊዜ ባለቤት ለሆነው ፈጣሪያችን "ጊዜ አጣሁ" ማለት ከጀመርን ሰንበትበት ብለናል:: የፈጣሪን በረከት መንዝረን ስናበቃ ለእርሱ የሚሆኑ ሽርፍራፊ ደቂቃዎችን ለመመደብ እናመነታለን:: አባቶቻችን እና እናቶቻችን "ጸልዩ! ኧረ ተዉ ጸልዩ!" ብለው ለዘመናት ወተወቱ:: ይህ ምክራቸው ግን ፍጹም ሰሚ አጣ:: በጊዜ ያልተካንነውን ጸሎት ሁሉም ጭንቅ ሲሆን በወከባው መሃል ለመጸለይ ብንፈልግም ተሳነን:: "ሠርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ" እንደሚባለው ሠርግ የተባለ ሞት ደርሶ ስንኳ በርበሬ መቀንጥሱን አልቻልንም:: በተጋድሎው እጅግ ደክመን በመንፈሳዊው ውጊያው ላይ ሰይጣን ሙትና ቁስለኛ እያደረግን አለን::

ከትእዛዛቱ ምን ያህል እንደራቅን የምናውቀው "ሳታቋርጡ ጸልዩ" (1 ተሰ 5:17) መባላችንን ስናስታውስ ነው:: ጸሎቱ እንዳይቋረጥ የታዘዘው ውጊያውም ስለማያቋርጥ ነው:: ሰይጣን ድካም የሌለበት፣ እንቅልፍ የማያስፈልገው፣ ተስፋ የማይቆርጥ እና የብዙ ሺህ ዓመታት የሥራ ልምድ ያለው ከይሲ ነው:: የእኛን የሰዎችን ሁኔታ በሚገባ ስለተገነዘበም ቀጥታ ከመግጠም ይልቅ እንደ ደፈጣ ተዋጊ እየተደበቀ፣ እያዘናጋ እና እያደባ ያጠቃናል:: "የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ።" (ኤፌ 6:11) የሚለው ቃል አንድም ሳይቀር ያሉንን መንፈሳዊ ትጥቆች ሁሉ ታጥቀን እንድንነሳ የሚያሳስብ ነው:: ይህ የውጊያውን ብርቱነት በአጽንኦት ያስታውሰናል::

የጥንቶቹ ብርቱ አባቶች እና እናቶች ሰይጣንን እያቆሰሉ ድል ከነሱበት መሣሪያ አንዱ የቀስት ጸሎት ነው:: የቀስት ጸሎት ማለት ከመንፈሳዊ መጻሕፍትም ሆነ ከራሳችን ሊገኙ የሚችሉ አጭር እና በተመስጦ የሚባሉ አጫጭር ጸሎቶች መጠሪያ ነው:: በተለይም ደግሞ የምንኩስና ተጋድሎ በተፋፋመበት የግብጽ በረሃ ከጥንት አንስቶ የዚህ አይነት ጸሎቶች ጥቅም ላይ ይውሉ እንደነበር የሚያሳዩ ማስረጃዎች አሉ:: አባ ፖላሞን ከርሱ በቀደሙ ብርቱዎች ትምህርት ላይ ተመስርቶ አባ ጳጉሚስን ሲያስተምረው "ሳናቋርጥ እንድንጸልይ ታዝዘናልና፤ አጫጭር ጸሎቶቹን ሳንቆጥር ልንጸልይ ይገባናል" ብሎት ነበር:: ታላቁ ቅዱስ ወግሪስም "አጭር የተመስጦ ጸሎቶችን ተጠቀሙ" በማለት የሚመክር ሲሆን የእነዚህ ጸሎቶች ኃያልነትም ይታይ ዘንድ ቅዱስ ዮሐንስ ዘአስቄጥስ  አጭርና በተመስጦ የሚባሉት ጸሎቶቹ ሰይጣንን ሲያቆስሉት በራዕይ ተመልክቶ ነበር::

ከእነዚህ የቀስት ጸሎቶች መካከል "ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ማረኝ" የሚለው ጸሎት ተወዳጅነትን ያተረፈ ነው:: ይህ ጸሎት በተለያየ አይነት ሁኔታ ለዘመናት አገልግሎት ላይ ውሏል:: በሀገራችንም "እግዚኦ ማሐረነ ክርስቶስ" (አቤቱ ክርስቶስ ሆይ ማረን) በሚለው ይታወቃል:: እንዲህ አይነት ጸሎቶች በሀገራችን የምንኩስና ታሪክ ውስጥ እንደነበሩ ማሳያ ከሚሆኑት አንዱ ደግሞ ቅዱስ አቡነ ሃብተማርያም ናቸው:: የታላቁ አቡነ ሃብተማርያም ገድል እንደሚነግረን ከሆን አባታችን ይህንን ጸሎት ከሰሙበት ጊዜ ጀምሮ ዘወትር እየደጋገሙ ይጸልዩት ነበር:: ዛሬም ድረስ ከመነኮሳት እስከ ምእመናን ድረስ ተወዳጅ ጸሎት ሆኖ እንደቀጠለ ነው::

የቀስት ጸሎቶች ሰይጣንን እረፍት ይነሱታል:: የእኛን ኅሊና ደግሞ ሁሌም ከፈጣሪ በማገናኘት "አልእሉ አልባቢክሙ" (ልቡናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ) የሚለውን ሰማያዊ ትእዛዝ ፈጻሚ ያደርጉናል:: የጸሎት መጽሐፍ መጨበጥ በማንችልባቸው ጊዜያት ሁሉ ከፈጣሪ የምንገናኝባቸው ድልድዮች ናቸው:: ከእነዚህ አጫጭር ጸሎቶች መካከል የተወሰኑትን እንመልከት:-

* ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ማረኝ

* አቤቱ ንጹህ ልብን ፍጠርልኝ፤ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ (መዝ 50:10)

* አቤቱ ጌታዬና ንጉሤ ሆይ፤ ለባልንጀሮቼ ክፉ ያለማሰብን እና የራሴን ኃጢአቶች የማየት ጸጋ ስጠኝ (ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ)

* አቤቱ፥ እኔን ለማዳን ተመልከት፤ አቤቱ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን። (መዝ 70:1)

* ጌታ ሆይ፤ እንደ ፈቃድህ እና እንደ እውቀትህ ማረኝ! (ቅዱስ መቃርዮስ)

* ጌታ ሆይ እርዳኝ!

የሚከተሉት ደግሞ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከደረሳቸው የሃያ አራት ሰዓት አጫጭር ጸሎቶች መካከል የተመረጡ ናቸው:-

* አቤቱ ጌታ ሆይ፤ ከዘለዓለማዊ ስቃይ አድነኝ!

* እቤቱ ጌታ ሆይ፤ ከፈተና ሁሉ አድነኝ!

* አቤቱ ጌታ ሆይ፤ አትተወኝ!

* አቤቱ ጌታ ሆይ፤ ትሕትናን፣ ንጽሕናን እና መታዘዝን ስጠኝ::

* አቤቱ ጌታ ሆይ፤ ስምህን አመሰግን ዘንድ ጸጋህን ላክልኝ::

* አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፤ በሕይወት መጽሐፍ ስሜን ጻፈው፤ መጨረሻዬንም አሳምርልኝ::

በእነዚህ እና መሠል ጸሎቶች ሕይወታችንን እናስጊጥ:: ለመጸለይ የግድ ሰዓት መጠበቅም ሆነ የጸሎት መጽሐፍ መጨበጥ የለብንም:: ልባችን ያረፈበትን አንድ አጭር ጸሎት (ወይም እንዳለንበት ሁኔታ ተስማሚ የሆነውን አጭር ጸሎት) የእግር ጉዞ ስናደርግ፣ በመኪና ስንሄድ፣ ስንቀመጥም ሆነ ስንተኛ በውስጣችን እየደጋገምን እንጸልይ::

ጸሎት የሁሉ ነገር መክፈቻ ቁልፍ መሆኗን አንዘንጋ!

✍️ Fresenbet G.Y Adhanom
  🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ 

የአባቶች ምክር

16 Jan, 04:50


ዘግይተህ አይደለም እኔ ቸኩዬ ነው
በነጋ በጠባ ስምህን ማማርረው
የሚያስፈልገኝን አንተ ቀድመህ አዉቀህ
ሁሉንም በጊዜው ታደርግልኛለህ

  🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

16 Jan, 04:37


በፈርኦን ዱላ እስራኤል ግብፅ መኖሪያቸው እንዳልሆነች ተገነዘቡ
እግዚአብሄር ምቾትን በመንሳት የእኛ ካልሆነው ሰፈር ያስወጣናል
ሁለተኛ በሰማይ ያለውን የቃል ኪዳን አምላክ
አስታውሱ
ክፉዎች ደጉን አምላክ እንድንጠራው ያደርጉናል

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

15 Jan, 14:00


"ዘወትር ጸልይ እግዚአብሄር
ጸሎተኛውን ሰው ይወዳልና
ለእርሱም ለጋስ ነውና"

ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

15 Jan, 09:33


በተናገርኳቸው ቃላቶች ብዙ ጊዜ ተፀፅቻለሁ
ነገር ግን በዝምታየ ተጸጽቼ አላውቅም


አባ አርሳኒዎስ

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

15 Jan, 09:22


ስለ ጋብቻ

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ

የአባቶች ምክር

15 Jan, 07:43


አንድ መነኩሴ ታላቁን ቅዱስ አባ እንጦንዮስን
እድን ዘንድ ምን ማድረግ አለብኝ ?
በማለት ይጠይቀዋል
አረጋዊው አባታችን አባ እንጦንስም እንዲህ ሲል መለሰለት
በራስህ ጽድቅ አትታመን
ስላለፈው ነገር አትጨነቅ
እና ምላስህንና ሆድህን ገድብ


🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
                         ⌲               
                       ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

10 Jan, 13:20


+ ወደ ሄሮድስ እንዳትመለሱ +

የአባቶች ምክር

10 Jan, 13:20


+ ወደ ሄሮድስ እንዳትመለሱ +

ሰብአ ሰገል ወደ ሄሮድስ ሔደው ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ጠየቁ:: ከዚያም በኮከብ ተመርተው ወደ ክርስቶስ ደረሱ:: ሔደውም ሰገዱለት:: እጅ መንሻም አቀረቡ::

ከዚያ በኋላ ግን "ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ" ማቴ. 2:12

ይህ መልእክት የተነገራቸው ስለ ሁለት ነገር ነው:: የመጀመሪያው ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ስለሚፈልግ ለሄሮድስ መረጃ እንዳይሠጡ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ እየመሰከሩ የመጡበትን መንገድ ትተው አየነው እያሉ በሌላ መንገድ እንዲመሰክሩና የሕፃኑ ንጉሥ ዝና እንዲሰፋ ወንጌል እንዲስፋፋ ነበር::

መልአኩ ወደ ሄሮድስ አትመለሱ አለ እንጂ "ሄሮድስ ሊገድለው ነው" አላላቸውም:: ምክንያቱም ይህን ዜና ቢሰሙ ጦር ይዘው የመጡ ነገሥታት ናቸውና "እኛ እያለን እስቲ ይሞክረን" ብለው ውጊያ ሊያነሡ ይችሉ ነበር:: የሰላም አለቃ የተባለው ህፃኑ ክርስቶስም የውጊያ መነሻ ይሆን ነበር:: ክርስቶስ ግን የምትዋጋለት ሳይሆን የሚዋጋልህ አልፎም የሚወጋልህ አምላክ ነው::

በዚህ መሠረት ሰብአ ሰገል
"ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ"

ወዳጄ ክርስቶስን ሳታገኝ በፊት ሄሮድስ ጋር ብትሔድ ችግር የለውም:: ክርስቶስን ካገኘህ በኋላ ግን ወደ ሄሮድስ መመለስ ኪሳራ ነው:: እንደ ሰብአ ሰገል ለጌታ እጅ መንሻ አቅርበህ ፣ ዘምረህ ፣ የከንፈር መሥዋዕት አቅርበህ ነፍስህ መድኃኒትዋን አግኝታ ከተደሰተች በኋላ ሕይወት እንዴት ይቀጥላል?

ወደ ሄሮድስ ልትመለስ ይሆን? እንዳታደርገው! ሄሮድስ ጋር ያለው ኃጢአት ነው:: ሄሮድስ ጋር ያለው ክፋት ነው:: እመነኝ እንደ ሰብአ ሰገል ጌታህን ካገኘህ ወዲህ ወደ ሄሮድስ አትመለስ!

ወዴት ልሒድ ካልከኝ መልሱ እዚያው ላይ አለ :-

"በሌላ መንገድ ወደ ሀገራቸው ሔዱ"

እስቲ ሌላ መንገድ ሞክር! ትናንት ያልኖርክበትን ዓይነት ኑሮ ፣ ትናንት ያልሞከርከው የንስሐ መንገድ እስቲ ዛሬ ሒድበት! ሌላ መንገድ አልነግርህም "መንገድም ሕይወትም እውነትም እኔ ነኝ" ያለህ መድኃኔዓለም ክርስቶስ እርሱ ነው:: በእኔ ኑሩ እንዳለ በእርሱ ኑር:: አደራ ወደ ሄሮድስ እንዳትመለስ!

ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ (የመቄዶንያ አምባሳደር)
ጥር 2 2017


ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!
8161 ላይ OK ብለው በመላክ መቄዶንያን ይርዱ!
መቄዶንያን ይጎብኙ!

ማስታወሻ :- የልደቴን ቀን አስመልክታችሁ ብዙ ምርቃትና መልካም ምኞት ላዘነባችሁልኝ ሁሉ ለእኔ የተመኛችሁትን ሁሉ ለእናንተ እጥፍ ድርብ ያድርግላችሁ:: ከመቼውም ጊዜ በላይ የሚያስፈልገኝ ጸሎታችሁ ነውና ተክለ ማርያም ብላችሁ አስቡኝ::

የልደት ሥጦታ ልሥጥህ ካላችሁ ደግሞ 8161 ላይ OK ብለው በመላክ መቄዶንያን ይርዱልኝ::


    🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥     

የአባቶች ምክር

10 Jan, 05:23


ትንቢተ ኢሳይያስ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አሁን ስለ ወዳጄና ስለ ወይን ቦታው ለወዳጄ ቅኔ እቀኛለሁ። ለወዳጄ በፍሬያማው ኮረብታ ላይ የወይን ቦታ ነበረው።
² በዙሪያው ቈፈረ፥ ድንጋዮችንም ለቅሞ አወጣ፥ ምርጥ የሆነውንም አረግ ተከለበት፥ በመካከሉም ግንብ ሠራ፥ ደግሞም የመጥመቂያ ጕድጓድ ማሰበት፤ ወይንንም ያፈራ ዘንድ ተማመነ፥ ዳሩ ግን ሆምጣጣ ፍሬ አፈራ።
³ አሁንም እናንተ በኢየሩሳሌም የምትኖሩ የይሁዳ ሰዎች ሆይ፥ በእኔና በወይኑ ቦታዬ መካከል እስኪ ፍረዱ።
⁴ ለወይኔ ያላደረግሁለት፥ ከዚህ ሌላ አደርግለት ዘንድ የሚገባኝ ምንድር ነው? ወይንን ያፈራል ብዬ ስትማመን ስለ ምን ሆምጣጣ ፍሬ አፈራ?
አሁንም በወይኔ ላይ የማደርገውን እነግራችኋለሁ፤ አጥሩን እነቅላለሁ፥ ለማሰማርያም ይሆናል፤ ቅጥሩንም አፈርሳለሁ፥ ለመራገጫም ይሆናል።
⁶ ባድማ አደርገዋለሁ፤ አይቈረጥም፥ አይኰተኰትም፤ ኵርንችትና እሾህ ይበቅልበታል፤ ዝናብንም እንዳያዘንቡበት ዳመናዎችን አዝዛለሁ።

የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔር ወይን ቦታ እርሱ የእስራኤል ቤት ነው፥ የደስታውም አትክልት የይሁዳ ሰዎች ናቸው፤ ፍርድን ተስፋ ያደርግ ነበር፥ እነሆም ደም ማፍሰስ ሆነ፤ ጽድቅንም ይተማመን ነበር፥ እነሆም፥ ጩኸት ሆነ።

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥     

የአባቶች ምክር

09 Jan, 18:11


ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካርኃያል አምላክየዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።”
— ኢሳይያስ 9፥6

    🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥     

የአባቶች ምክር

09 Jan, 17:03


+ ሸክላ ሠሪ +

በድሮ ዘመን ነው - መምህር አልዓዛር የተሰኙ አንድ የአይሁድ መምህር በአህያቸው ላይ ኾነው ከትምህርት ቤታቸው ወደ ሰፈራቸው እየተመለሱ ነው። በእለቱ በዛ ያለ የእግዚአብሔር ቃል ስላጠኑ ቀናቸው ብሩህ ኾኖላቸው ፊታቸው ፈካ ብሏል። በጉዞ ላይ እያሉ ግን አንድ ሰው ቀረበና፡ “መምህር ሆይ፥ ሰላም ለእርስዎ ይኹን!” ብሎ ሰላምታ ሰጣቸው። ከአህያቸው ላይ ሆነው ቁልቁል አዩትና ፊታቸው ጠቆረ። “አንተ የማትረባ! መልክህ ምንድር ነው? ለምንድር ነው እንዲህ መልከ ጥፉ የኾንከው? የአንተ አካባቢ ሰዎች ሁሉ እንዳንተው መልከ ጥፉ ናቸው እንዴ?” አሉት። ይህም ሰው “እርሱን አላውቅም። ባይኾን የሠራኝን ሄደው ‘የሠራኸው ሸክላ እንዴት መልከ ጥፉ ነው!’ ብለው ይንገሩት።” አላቸው።

መምህር አልዓዛርም ሰውየውን በመልኩ ብቻ ክፉ ንግግር እንደተናገሩት አስተዋሉና ከአህያቸው ወረዱ፤ በፊቱም ተደፍተው “እባክህ ይቅር በለኝ” ብለው ለመኑት። እርሱ ግን “እርስዎ ሄደው ለሠራኝ ‘የሠራኸው ሸክላ መልከ ጥፉ ነው!’ ብለው እስካልነገሩት ድረስ ይቅርታ አላደርግልዎትም አላቸው።

መምህር አልዓዛር ሰውየውን እየተከተሉ ይቅርታ እየጠየቁት ከሰፈራቸው ደረሱ። የሰፈሩ ሰው ኹሉም እየወጣ “እንኳን ደህና መጡ፥ መምህር ሆይ” እያሉ ሰላምታ ይሰጡዋቸው ጀመር። ሰውየውም “ማንን ነው መምህር ሆይ የምትሉት?” ብሎ ጠየቀ። ሰዎቹም “እርሳቸውን ነዋ! ታላቅ የኦሪት መምህር ናቸውኮ!” ብለው መለሱለት። እርሱም “እርሳቸው የኦሪት መምህር ከኾኑ፥ እንግዲያውስ ለዘለዓለም በእስራኤል ምድር እንደ እርሳቸው አይነት መምህር አይኑር!” ብሎ ተናገረ። የሰፈራቸው ሰዎችም ደንግጠው ለምን እንዲህ እንዳለ ጠየቁት፤ እርሱም የተፈጠረውን ነገራቸው። ሰዎቹም በማዘን “ቢሆንም ይቅርታ ጠይቀዋል፤ ስለዚህ ይቅር በላቸው። እርሳቸው ታላቅ የኦሪት ምሁር ናቸው።” አሉት። ሰውየውም “ከአሁን በኋላ እንዲህ አይነት ነገር እንደማያደርጉ ቃል ከገቡ፥ ለእናንተ ስል ይቅርታ አደርጋላቸዋለሁ።” በማለት ለመምህሩ ይቅርታ አደረገላቸው።

በእድሜ ዘመናችንሲያስጠላስታስጠላ’ ብለን ያሸማቀቅናቸው ምን ያህል ይኾኑ? ለአንዳንድ ሰው ምርቃት እስኪመስል ድረስ እነዚህ ቃላት ከአንደበቱ አይለዩትምእግዚአብሔር አስውቦ የሠራውን ሸክላ ለመንቀፍ የበቃነው፥ እኛም ‘ሸክላነታችንን’ ስለምንረሳ ነው። ሸክላነቱን ያልረሳው የዘለሰኛ ገጣሚ፦

እዚያ ዳር ያለች ሸክላ ሠሪ፥ ድሃ ናት አሉ ጦም አዳሪ
ማን አስተማራት ጥበቡን፥ ገል ዐፈር መኾኑን!’

… ብሎ አዚሞ ነበር። አንዳንዴ ኹሉ ሲሰምርልን ሥልጣን የሚሻር፥ ሀብት የሚጠፋ፥ መልክ የሚጠወልግ አይመስለንም። አንዳንዶች ጸጉራቸው መመለጥ ሲጀምር ‘ጸጉርኮ ባዳ ነው’ ይላሉ። ጸጉር ብቻ ሳይሆን አሉን የምንላቸው ሁሉ ባዳ ናቸው። በዚህ ሁሉ ውስጥ ጸንቶ የሚቀረው ‘ሸክላነታችን’ ነው፤ እርሱም ወደ መጣንበት ዐፈር እስክንመለስ ድረስ።

ሁላችንም ከአፈር የተሰራን ሸክላ ነንና፤ ሸክላውን በመልኩ ስንሳደብ፥ ሸክላ ሰሪውን እየነቀፍን መኾኑን አንርሳ!

✍️ Fresenbet G.Y Adhanom
     🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  
       ⌲               
      ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

09 Jan, 04:40


እምነ እናታችን

በስድስተኛው ወር መልአኩ ገብርኤል ወዳንቺ ተላከ ። ከስድስት ወር በፊት የዮሐንስን መወለድ ሊያበሥር ወደ ዘካርያስ ሂዶ ነበር ። ንጉሥ በሚያልፍበት ጎዳና ከመንፈቅ በፊት መልእክተኛ ይሄዳል ። የጠመመውን እያቀና ፣ የጎበጠውን እያስተኛ ፣ የጎደለውን እየሞላ ፣ የሻከረውን እያለሰለሰ የንጉሡን መንገድ ያቀናል ። ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅም በሥጋ ልደት ልጅሽን ስድስት ወር ይበልጣል ። እርሱ ለመልእክተኛነት ብቻ ተወልዷል ። ጧሪ ፣ ቀባሪ ለመሆን ፣ ባለትዳር ባለሀብት ለመሆን አልተወለደም ። እርሱ መንገድ ጠራጊ ነው ። የሰውን ልብ ማቅናት ጎዳና ከማቅናት ይበልጣል ። ሰው ሲሞሉት የሚጎድል ፣ ሲያለሰልሱት የሚሻክር ፣ ሲያቅፉት የሚገፈትር ፣ አበባ ሲሰጡት አፈር የሚበትን ነው ። ስለ ወዳጅ እሬት ይላሳልና ዮሐንስ ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ከባዱን ጉዞ ተጋጠመው ። እርሱ ለእስራኤል ብቻ ሳይሆን ለኤዶማውያን ለሄሮድስ ቤተሰብ ቅድስና የሚጨነቅ ፣ የነገሥታትን መንፈሳዊ ውበት የሚናፍቅ ነበር ። እርሱ እንደሚሰብከው ቃል ሰይፍ ነው ። ለመያዝ አይመችም ። ስለ አሕዛብ መሞትም የሚጨነቅ ፣ በግፍ ስለሞተው ሹም ሲከራከር በግፍ የሞተ ነው ። እርሱ በአጥቢያ የማያለቅስ የሁሉን ሕመም የራሱ ለማድረግ መንፈሳዊ ስፋት የተሰጠው ነው ።

እርሱ የሚወረስ ሀብት ፣ የሚጠፋ ስም የለውምና ስለ እውነት ከማንም መጣላትን አልፈራም ። ለእውነት ዋጋ እየከፈለ እንጂ እውነትን እየሠዋ ማንንም መወዳጀት አልፈለገም ። እምነ እናታችን ማርያም ሆይ እርሱም የአክስትሽ ልጅ ወንድምሽ ነው ። ልጅሽ አምላክ ፣ አክስትሽ ቅድስት ኤልሳቤጥ ፣ የአክስትሽ ባል ሊቀ ካህናት ፣ የአክስትሽ ልጅ መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ መንፈሳዊ ዘመድ የበዛልሽ እናታችን ነሽ ።

ስለ ሰው መዳን መልአኩ አንቺን ደስ ይበልሽ አለሽ ። ስለ ግል ጥቅም እንጂ ስለመላው ዓለም በረከት የሚደሰት ጥቂት ነው ። አንቺ ግን የሰው መዳን ይናፍቅሻልና መዳንም በአንዱ በእግዚአብሔር ነውና ደስ ይበልሽ ተባልሽ ። የአንቺ ደስታ ዓለም በእርሱ እንዲድን ፣ ዓለምም በልጅሽ እንዲያምን ነው ። ስለ ፀሐይ የማናመሰግነው ፣ ስለሚነፍሰው አየር ስብሐት ለእግዚአብሔር የማንለው የግል ስላልሆኑ ነው ። እናታችን ሆይ ስለ ጽድቅ ፀሐይ ክርስቶስ ደስ ይበልሽ ተባልሽ ። የግል ኑሮ የሌለሽ ሕይወትሽን ለእግዚአብሔር የሰጠሸ ነሽና ። የምናከብርሽ ክርስቶስን ንቀን ፣ የምንወድሽ አማኑኤልን ጠልተን አይደለም ። እርሱን ስለምናከብር እናከብርሻለን ፣ እርሱን ስለምንወድ እንወድሻለን ። ሁሉ በክርስቶስ ይወደዳሉ ፣ እርሱ ግን ስለ ራሱ ይወደዳል ። ነቢያትን ብንወድ ስለ እርሱ ትንቢት ተናገሩ ብለን ነው ፣ ሐዋርያትን ብንወድ ስለ እርሱ ሰበኩ ብለን ነው ።
ሰማዕታትን ብንወድ ስለ እርሱ ሞቱ ብለን ነው ፣
ደናግላንን ብንወድ ስለ እርሱ ኖሩ ብለን ነው ።

አንቺን ብንወድሽ እውነተኛውን የጽድቅ መብል ፣ እውተኛውን የጽድቅ መጠጥ ወለድሽ ብለን ነው ። “ኦ ማርያም በእንተዝ ናፈቅረኪ ወናዐብየኪ እስመ ወለድኪ ለነ መብልዐ ጽድቅ ዘበአማን ወስቴ ሕይወት ዘበአማን ።”

እምነ መንገዱ ረጅም ቢሆንም ደስታን ይዞ ማደር ፣ የምሥራችን ሰምቶ መቀዝቀዝ አይገባምና ወደ ተራራማው አገር ገሰገስሽ ። ቅዱስ ገብርኤል ከስድስት ወር በፊት በይሁዳ ኢየሩሳሌም ተላከ ፣ አሁን ደግሞ በገሊላ ናዝሬት ተገኘ ። የጸሎት መልስ በጸሎት ማማው ላይ ይመጣል ። ዘካርያስ በመቅደሱ ፣ አንቺም በትጋት ስፍራሽ የምሥራች መጣላችሁ ። ሔዋን ከስፍራዋ ብትታጣ ስፍራዋን አጣች ። ስለ ኤልሳቤጥ መፅነስ ብትሰሚ “ካረጁ ልጅ ምን ሊሠራ ነው?” አላልሽም ። የአብርሃም አምላክ ዛሬም በሥራ ላይ ነው ብለሽ ገሰገስሽ ። ትልቁ እግዚአብሔር ታናናሾችን አይንቅም ብለሽ ለማወደስ ተነሣሽ ። ደስታ ኃይል ይሆናልና በመቶ ኪሎ ሜትሮች ተጓዝሽ ። እግዚአብሔርን የያዘ አይፈራምና ያንን አስጊ መንገድ ብቻሽን አቋረጥሽ ። ባንቺም የሆነውን ፣ በኤልሳቤጥም የሆነውን የሰው አስረጂነት አይገልጠውምና በጊዜው ይገለጥለት ብለሽ አገልጋይሽ ዮሴፍን ዝም አልሽው ። እንደ ሰው ልማድ እጮኛ ተብሎ ቢጠራም አንቺ ግን አብ ለልጁ ማደሪያነት አጭቶሻል ። ባንቺ የሆነውን ሥጋውያን አይረዱትምና ዮሴፍ መጋረጃ ሁኖ ተሹሟል።

ተራራማውን አገር እንዴት ወጣሽ ? በሰው ደስታ ለመደሰት ይህ ሁሉ ፍጥነት የፍቅር እናት መሆን ነው ። ሴቶች
ለሐሜት ሳይሆን ነገረ እግዚአብሔርን ለመነጋገር እንደሚገናኙ አንቺ ምስክር ነሽ !
አንቺም የፀነስሽው የዓለም ቤዛ ፣ ኤልሳቤጥም የፀነሰችው የእግዚአብሔር አገልጋይ ነው ። ስለ ዓለም ጥቅም መደሰት መንፈሳዊነት ነው ። ልጅን ለግል ጥቅም ሳይሆን ለዓለም በረከት እንዲሆን መመኘት ትልቅነት ነው ። ባንቺ የሆነውን ተአምር በጥቂት መረዳት የምትችል ኤልሳቤጥ ናት ። ተአምርን ተአምር ከሆነላቸው ጋር ማውራት ዋጋ አለው ። ዕንቈን እሪያ ፊት ቢጥሉት ይረግጠዋል ፣ ይጫወትበታል እንጂ አያጌጥበትም ፤ ዋጋውን አያውቀውምና ። ዋጋን ከሚያውቁ ጋር ተአምራትን ማውራት ደስታ ይሰጣል ። እምነ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነውና ሰው አጠገብሽ አለመኖሩ አላስጨነቀሽም ። የአማኑኤል እናቱ ለእኔ እኅቴ ልትሆኚ አይቻልም ። ለዮሐንስ ወንጌላዊ እነኋት እናትህ በማለት ልጅሽ ልጅ ሰጥቶሻል ። እኔም እምነ ጽዮን እልሻለሁ ። ትውልድ ነኝና ብፅዕት ነሽ እላለሁ ። ኃጢአት ያደከመን ፣ የደሙን ዋጋ ያላወቅን ልጆችሽ ከባለ ቅኔው ጋር እንዲህ እንልሻለን፡-

“እመቤቴ ማርያም ጠጅ እያማረሽ ፣
ማር አትይውም ወይ ? ሲቆርጥ ልጅሽ።”


     🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ 

የአባቶች ምክር

09 Jan, 04:00


"ኃጢአት የሌለበት ከጸለየ
ኃጢአተኞች እንዴት አብልጠው
መጸለይ ይገባቸዋል።"

ቅዱስ ቆጵሮስ ዘቅርጣግ
  🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  

የአባቶች ምክር

08 Jan, 18:30


በዓመት ለተወሰኑ ቀናት ከእያንዳንዱ የአገሪቱ ዜጋ ጋር የሚገናኝና ጥያቄዎቻቸውን በግለሰብ ደረጃ የሚመልስ መንግሥት ቢገኝ ምን ያህል ሊወደድ እንደሚችል አስቡት?  ሕዝቡም በዚህ ደረጃ ቅርብ ሆኖ የሚጨነቅለትና ጥያቄዎቹን የሚሰማለት ደግ ንጉሥ በማግኘቱ ይህን ባሰበ ቁጥር አንዳች የደስታና የኩራት ስሜት ሰውነቱን ውርር ሳያደርገው አይቀርም።

ሰማይና ምድርን የፈጠረው፣ ዓለሙን የሚመግብና የሚያስተዳድረው ታላቁ ንጉሥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር እንድንገናኝና ጥያቄዎቻችንን እንድናቀርብ በዓመት ውስጥ ምን ያህል ጊዜ ሰጠን? ምድራውያን ነገሥታት ቢገዙ የሚታየውን ዓለም ያውም ደግሞ በተራራ እና በወንዝ ተቆራርሶ፣ በግዛት ታጥሮ የተሰጣቸውን ኩርማን መሬትና በዚያ የሚኖሩትን ሕዝብ ነው። እንዲህም ሆኖ ግን ሥራ ስለሚበዛባቸው ከጊዜያቸው አጣበው በዓመት አንድ ወይም ሁለት ቀን እያንዳንዱን ዜጋ ቢያገኙ እጅግ ታላቅ ጀብዱ ሆኖ ይነገርላቸዋል።

በእውነት እንደ እግዚአብሔር ያለ "ሥራ ብዙ" ማን ነው? መድኃኒታችን በወንጌል "አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል፡ እኔም ደግሞ እሠራለሁ" እንዳለ እርሱ እኮ የሚታየውንና የማይታየውን ዓለም ሲያስተዳድር ዕረፍት አያውቅም፤ ድካምም የለበትም።(ዮሐ 5፥17) ይሁን እንጂ ከእኛ ጋር ለመገናኘት ግን የወር ወይም የቀናት ቀጠሮ አይሰጠንም። ዛሬስ አይታሰብም ባይሆን ነገ ሞክሩ ብሎ አይመልሰንም። ወደ እርሱ የሚመጡትን ሁሉ ለመቀበል እጆቹ ዘወትር የተዘረጉ ናቸው። "ትናንት አላናገርኩህም? ዛሬ ምን ቀረህ?" ብሎ አያሳቅቅም፤ አይሰለችም። በዚህ ቀንና በዚህ ሰዓት ብቻ እገኛለሁ አይልም። ብንችል ሳናቋርጥ አብረነው ብንሆንና ብናነጋግረው ደስ ይለዋል።(1ኛ ተሰ 5፥17) በእርሱም ዘንድ የተቆለፈ በር የለም። እንደውም ወደ ልባችን እልፍኝ እስክናስገባው ከውጭ ሆኖ እኛን ደጅ ይጠናል። ያንኳኳል፤ ክፈቱልኝ ይላል።(ራእይ 3፥20) ሲከፈትለትም ምስኪኑን ቤት አይቶ አይጸየፍም። የልባችንን እልፍኝ ያሰናዳዋል። ለእራትም አብሮን ይቀመጣል።

ታዲያ እንዲህ ያለ ቸር ጌታ እያለን እንዴት ዝም ይባላል? እንግዲህስ ከተኛንበት የስንፍና አልጋ እንነሣ። ንጉሡን እናነጋግረው። ወደ እርሱ ስላቀረበን እናመስግነው፣ የልባችንንም ኃዘን እንንገረው።

ተንሥኡ ለጸሎት!

"በማታና በጥዋት በቀትርም እናገራለሁ...ቃሌንም ይሰማኛል" መዝ 55፥17

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
     🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ 

የአባቶች ምክር

08 Jan, 14:25


ጌታ ሆይ ብዙ የታመሙ ወገኖች አሉን በደዌ ዳኛ
በአልጋ ቁራኛ የተያዙ በአጋንንት እስራት ተይዘው የሚሰቃዩ

ጌታ ሆይ በሽታቸው ለነጋዲዎች ለጨካኞች የሃብት ማገኛ መንገድ የሆነባቸው ብዙዎች አሉ
አቤቱ ጌታ ሆይ ቁስለ ስጋቸውን ቁስለ ነፍሳቸውን
አንተ ቸር ጌታ ፈውስ
በጸሎታችሁ አስቡን የሚሉንን
አንተ ቸር ጌታ በማታልፈው ርስትህ አስባቸው ከሚያገኛቸው ምድራዊ ፈተና ሁሉ አንተ ማዕዶት ሁናቸው
እነዚህን ባሪያዎችን በሰማያዊና በምድራዊ በረከትህ ባርካቸው
ቅዱስ ፓትሪያሊክህን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን
ቀሳውስት ዲያቆናትን አንባቢ መዘምራንን ደናግል መነኮሳትን
ስምህን ተሸክመው የሚዞሩትን ወንጌላውያን
ሰባኪዎችን
በጣዕመ ዜማ አንተን የሚሰብኩህን መዘምራንን ሁሉ
አቤቱ ጠብቅልን
አብዛልን በስምህ የሚታመኑ ህዝቦችህን ሁሉ አቤቱ አስበን🙏
ጌታ ሆይ በፊትህ በቆምን ጊዜ እንድናስባቸው ያዘዙን
ታመው እንደሆነ ይፈወሱ ደክመው እንደሆነ ይበርቱ
አዝነው እንደሆነ ይፅናኑ ተሰደው እንደሆነ ይመለሱ
ጌታ ሆይ እኛ ደካሞቹን በጸሎታችሁ አስቡን ብለውናልና አንተ ብርቱ አምላክ ጸሎታቸውን ሰምተህ አድናቸው
ክብርና ምስጋና ለአንተ ይሁን አሜን!

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  

የአባቶች ምክር

08 Jan, 04:38


ምዕመናን ሲጠፉስ???

ዲ/ን ሄኖክ ሃይሌ

የአባቶች ምክር

07 Jan, 17:07


"መዋደድ ክብርን መንካት የለበትም
ክብር ደግሞ ፍቅርን ማስቀረት የለበትም"
እግዚአብሄር ያን ያህል የከበረ ሲሆን ግን
ዝቅ ብሎ የሚወድ አምላክ ነው
ከድሃ ቤት የሚገባ የእኛን ስጋ የለበሰ
በእኛ ቃል የተናገረ
ነው
             አባ ገብረ ኪዳን

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  

የአባቶች ምክር

07 Jan, 08:47


‹‹ኦ አንትሙ ሕዝበ ክርስቲያን እለ ተጋባእክሙ በዛቲ ዕለት ከማሁ ያስተጋባእክሙ በደብረ ጽዮን ቅድስት ወበኢየሩሳሌም አግዐዚት በሰማያት᎓᎓››
የክርስቲያን ወገኖች በዚች ዕለት እንደተሰበሰባችሁ፤ ነጻ በምታወጣ በደብረ ጽዮን በመንግሥተ ሰማያት ይሰብስባችሁ።

መልካም የልደት በዓል!

   🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  

የአባቶች ምክር

07 Jan, 02:54


ሉቃስ 2
¹ በዚያም ወራት ዓለሙ ሁሉ እንዲጻፍ ከአውግስጦስ ቄሣር ትእዛዝ ወጣች።
² ቄሬኔዎስ በሶርያ አገር ገዥ በነበረ ጊዜ ይህ የመጀመሪያ ጽሕፈት ሆነ።
³ ሁሉም እያንዳንዱ ይጻፍ ዘንድ ወደ ከተማው ሄደ።
⁴-⁵ ዮሴፍም ደግሞ ከዳዊት ቤትና ወገን ስለ ነበረ ከገሊላ ከናዝሬት ከተማ ተነሥቶ ቤተ ልሔም ወደምትባል ወደ ዳዊት ከተማ ወደ ይሁዳ፥ ፀንሳ ከነበረች ከእጮኛው ከማርያም ጋር ይጻፍ ዘንድ ወጣ።
በዚያም ሳሉ የመውለጃዋ ወራት ደረሰ፥
⁷ የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥ በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው በግርግም አስተኛችው።
⁸ በዚያም ምድር መንጋቸውን በሌሊት ሲጠብቁ በሜዳ ያደሩ እረኞች ነበሩ።
⁹ እነሆም፥ የጌታ መልአክ ወደ እነርሱ ቀረበ የጌታ ክብርም በዙሪያቸው አበራ፥ ታላቅ ፍርሃትም ፈሩ።
¹⁰ መልአኩም እንዲህ አላቸው፦ እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ
¹¹ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።
¹² ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ።
¹³ ድንገትም ብዙ የሰማይ ሠራዊት ከመልአኩ ጋር ነበሩ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ፦
¹⁴ ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።
¹⁵ መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ፥ እረኞቹ እርስ በርሳቸው፦ እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ ተባባሉ።
¹⁶ ፈጥነውም መጡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ።
¹⁷ አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ።
¹⁸ የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሩአቸው ነገር አደነቁ፤
¹⁹ ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር።

የአባቶች ምክር

06 Jan, 18:42


ለህዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ የምስራች

ሉቃስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ መልአኩም እንዲህ አላቸው፦ እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤
¹¹ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።
¹² ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ።
¹³ ድንገትም ብዙ የሰማይ ሠራዊት ከመልአኩ ጋር ነበሩ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ፦
¹⁴ ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።

እንኳን አደረሳችሁ!

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥  

የአባቶች ምክር

06 Jan, 16:04


"የጌታ ልደት በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ"

ቀዳማዊ አምላክ ዛሬ ተወለደ፤ ጥንቱን ገንዘቡ ባይደለ ባህርይ ተገኝ፤ እርሱ ቀዳማዊ አምላክ ነው፤ ሰው በመሆኑም ከባህርይው አልተለወጠም፡፡ የመለኮቱ መገኝትም ከእመቤታችን ከተወለደ ወዲህ አይደለም፤ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ዓለም ሳይፈጠር የነበረ ጥበብ ነው እንጂ፤ የማይታመም እርሱ ከባህርይ መለኮቱ ሳይለወጥ ሕማም የሚስማማውን ስጋን ተዋሃደ፡፡ ዳግመኛም በልዑል ዙፋን ላይ ተቀምጦ ያለ እርሱ በበረት ተጣለ ስጋ ሳይሆን የነበረ የማይዳሰስ ወልድ ዋህድ ዛሬ ስጋን በመዋሃድ ተዳሰሰ፤ ሃጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱ በጨርቅ ተጠቀለለ፡፡

መፅሃፍ እንዲህ አለ፦ ብልህ ሽክላ ሰሪ የሚሰራውን የለዘበ ጭቃ በአገኝ ጊዜ ከእርሱ መልካም እቃ እንዲሰራ እንደዚሁ ጌታችን የዚህችን ድንግል ንፁህ ስጋዋን ንፅህት ነፍሷን ባገኘ ጊዜ ነፍስ ያለችውን ስጋ ሊዋሃደው ፈጠረ፡፡ እንደወደደ ከድንግል ነፍስን ስጋን ፈጥሮ ለበሰ እርሱንም ተዋህዶ ዛሬ ተወለደ ሕፀፅ ያለበት ነው ብሎ ባህርያችንን አልተወውም ፤ ስጋን በተዋህዶ ጊዜ ቃል ከምላቱ አልተወሰነም፤ ስጋ የፈጣሪ አካል ባህርይ በሆነ ጊዜ ፍፁም አምላክነትን አገኝ እንጂ፡፡ ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? ከዘመን አስቀድሞ የነበረ እርሱ ትንሽ ህፃን ሆኗልና፡፡

እኔ ፈፅሜ አደንቃለሁ፤ ከሰማየ ሰማያት በላይ የሚሆን በዘላለማዊ ዙፋን የሚኖር እርሱ በበረት ተጣለ ከስጋዌ አስቀድሞ አይዳሰስ የነበረ አንዱ እርሱ በምድራውያን እጅ ተዳሰሰ ሃጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱን በጨርቅ ጠቀለሉት፤ ይህን ወዷልና፡፡ ክብሩ ተለይቶት የነበረ ስጋን ክቡር አምላክ ሊያደርገው፤ የፀጋ ገዥነትን አጥቶ የነበረ ስጋንም የባህርይ ገዥ ሊያደርገው ወደደ፤ አዳም ከእኛ እንዳንዱ ሆነ ያለውንም ሰው በመሆን ሊገልጠው ወደደ፡፡

     🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ 

የአባቶች ምክር

06 Jan, 14:06


የአዕላፋት ዝማሬ ቀጥታ ስርጭት
https://www.youtube.com/live/t2M4jDPcH6E?si=sLgeQsFgycymbRTb

የአባቶች ምክር

05 Jan, 17:24


አዳም ከጎኑ ያለ እናት ሔዋንን አስገኘ ፣ አንቺ ያለ አባት ክርስቶስን ወለድሽ ።
ሴቶች ሁሉ ስሙንና ጾታውን የማያውቁትን ልጅ ይፀንሳሉ ። አንቺ ግን ስሙንም ፣ ፆታውንም የምታውቂውን ፀነስሽ ። ስሙም ኢየሱስ ይባላል ።
ከዘላለም በሥላሴ መንግሥት ያለ እና የነበረ የሚኖር ፣ በቅዱስ ገብርኤል ላንቺ የተገለጠ ድንቅ ስም ነው ።
የተመረጥሽ እመቤት ማርያም ሆይ ! ሔዋን በገነት ወደቀች ። አንቺ ግን በምድር ላይ በሃይማኖት ጸናሽ ።
ሔዋን የቀዳማዊ አዳም እንቅፋት ሆነች ፣ አንቺ ግን የዳግማዊ አዳም አገልጋይ ሆንሽ ።
አዳም ጌትነትን ሽቶ ወደቀ ፣ ክርስቶስ በትሑት ሥጋ ተገልጦ አዳነ ። ከፍታን የሚመርጡ ይዋረዳሉ ። መጨረሻው ላይ የቆሙ ያላቸው መንገድ ወደ መጀመሪያው መውረድ ነው ። አዳምም ወደ መጣበት አፈር ተመለሰ ። ጽርሐ አርያምን በጉልበት ተመኘ ፣ መኖሪያው መቃብር ሆነ ።

የዘላለም ተራሮችን ያቋረጡ እግሮች መሄድ የማይችሉ የሕፃን አእጋር ሁነው ተገለጡ ። አዳምን የሠሩ እጆች በሠሩት ፍጥረት ተገፉ ። ለድሆች አንደበት የሆነው ፣ ሄሮድስ ሲያሳድደው መናገር የማይችል ሕፃን ሁኖ ተሰደደ ። በበጉ ራስ ላይ ሊቀ ካህኑ እጁን ይጭናል ። አሁን ግን በጉም ካህኑም ራሱ የሆነው ክርስቶስ በፈቃዱ ሊሞት ከድንግል ተወለደ ። በግ ሁኖ የመጣው ክርስቶስ በበጎች ማደሪያ በበረት ተወለደ ። እረኛው ለእረኞች ተገለጠ ።
ክብርና ምስጋና በደሙ ፈሳሽነት ከሀጢአታችን ላነፃን ከሞት ወደ ሕይወት ላሸጋገረን ለጌታችን ለመድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ይሁን!
የበጉ እናት ማርያም ሆይ “የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤” — ሉቃስ 1፥48
ብለሽ የለምን እኔም ትውልድ ነኝ ብፅዕት እልሻለሁ

@father_advice

የአባቶች ምክር

05 Jan, 07:01


“እንጀራህን በውኃ ፊት ላይ ጣለው፥ ከብዙ ቀን በኋላ ታገኛዋለህና።”
  — መክብብ 11፥1

ከውሃ ላይ የጣሉት እንጀራ አይታይም
ምፅዋታችሁ በስውር  ይሁን
ከብዙ ጊዜ ቡሃላ ታገኙታላችሁ

ማቴዎስ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ለሰዎች ትታዩ ዘንድ ምጽዋታችሁን በፊታቸው እንዳታደርጉ ተጠንቀቁ፤ ያለዚያ በሰማያት ባለው አባታችሁ ዘንድ ዋጋ የላችሁም።
² እንግዲህ ምጽዋት ስታደርግ፥ ግብዞች በሰው ዘንድ ሊከበሩ በምኩራብ በመንገድም እንደሚያደርጉ በፊትህ መለከት አታስነፋ፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።
³-⁴ አንተ ግን ምጽዋት ስታደርግ ምጽዋትህ በስውር እንዲሆን ቀኝህ የምትሠራውን ግራህ አትወቅ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።

  🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ 

የአባቶች ምክር

05 Jan, 06:17


#እጠበኝ_ቆሽሻለሁ

እጠበኝ ቆሽሻለሁ አምላኬ በድያለሁ
ያለ እናት ያሳደከኝ ያለ አባት የጠበከኝ
ያን ሁሉ ዛሬ ረሳሁ እጠበኝ ቆሽሻለሁ

ከድንኳኑ ብታስገባኝ ሞገስ ስጥተህ
የአፍኒንን ምግባር ይዤ አስቀየምኩህ
ቅብዓ ሜሮን ያተምክበት ልጅነቴ
እንዳይጎድፍ ጠብቅልኝ ቸር አባቴ
#አዝ
ኃይል አኑረህ እንደ ሶምሶን በፀጉሬ
ጎልያድን አስጥለክኝ በጠጠሬ
አቅም ቢያንስኝ ለሥጋ ጦር ተሽንፌ
ደጅህ መጣሁ የዕንባ መባ በአይኔ አቅፌ
#አዝ
እንዳትረሳኝ በመዳፍህ ቀርፀኸኛል
እንዳተወኝ ያለመጠን ወደኸኛል
ባትሰነዝር ልትቀጣኝ በሞት በትር
የትግስትህ ሰሌዳ ነው የኔ ክብር
#አዝ
በከንፈሬ ጥበብ ፅፌ ቅኔ ቢፈስ
በመታበይ አሳዘንኩት ያንተን መንፈስ
ፍቅር ሰተህ በእቅፍህ ስር ያሳደከኝ
እባክህን በበደሌ አትቅስፈኝ

መዝሙር
ሊቀመዘምራን ዲያቆን
ቴዎድሮስ ዮሴፍ
      🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

05 Jan, 05:14


መዝሙር 51

¹ አቤቱ፥ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ🙏
እንደ ምሕረትህም ብዛት መተላለፌን ደምስስ።
² ከበደሌ ፈጽሞ እጠበኝ፥ ከኃጢአቴም አንጻኝ፤
³ እኔ መተላለፌን አውቃለሁናኃጢአቴም ሁልጊዜ በፊቴ ነውና።
⁴ አንተን ብቻ በደልሁ፥ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ፥ በነገርህም ትጸድቅ ዘንድ በፍርድህም ንጹሕ ትሆን ዘንድ።
⁵ እነሆ፥ በዓመፃ ተፀነስሁ፥ እናቴም በኃጢአት ወለደችኝ።
⁶ እነሆ፥ እውነትን ወደድህ፤ የማይታይ ስውር ጥበብን አስታወቅኸኝ።
በሂሶጵ እርጨኝ፥ እነጻማለሁ፤ እጠበኝ፥ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።
⁸ ሐሤትንና ደስታን አሰማኝ፥ የሰበርሃቸውም አጥንቶቼ ደስ ይላቸዋል።
ከኃጢአቴ ፊትህን መልስ፥ በደሌንም ሁሉ ደምስስልኝ
¹⁰ አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።
¹¹ ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ።
¹² የማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ።
¹³ ለሕግ ተላላፎች መንገድህን አስተምራለሁ፥ ኃጢአተኞችም ወደ አንተ ይመለሳሉ።
¹⁴ የመድኃኒቴ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፥ ከደም አድነኝ፥ አንደበቴም በአንተ ጽድቅ ትደሰታለች።
¹⁵ አቤቱ፥ ከንፈሮቼን ክፈት፥ አፌም ምስጋናህን ያወራል።
¹⁶ መሥዋዕትን ብትወድድስ በሰጠሁህ ነበር የሚቃጠለውም መሥዋዕት ደስ አያሰኝህም።
¹⁷ የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥😔 የተሰበረውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።
¹⁸ አቤቱ፥ በውዴታህ ጽዮንን አሰማምራት፤ የኢየሩሳሌምንም ቅጽሮች ሥራ።
¹⁹ የጽድቁን መሥዋዕት መባውንም የሚቃጠለውንም መሥዋዕት በወደድህ ጊዜ፥ ያን ጊዜ በመሠዊያህ ላይ ፍሪዳዎችን ይሠዋሉ።

   🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

የአባቶች ምክር

05 Jan, 03:18


      ክርስትና የሚኖር ሕይወት ነው
ክርስቶስን ለብሰን በሕይወታችን እንዲገለጥ
ልባችን ይሻል ሰዎችም ከቃል ስብከት በላይ የክርስቶስን ቃል የሚኖርላቸው ሰው ይሻሉ::በክርስቶስ ኢየሱስ የተቃኜ መንፈሳዊ  ህይወት ስብከት ነው
ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት።”  — ሮሜ 13፥14

እርሱ እኮ ክርስቲያን ስለ ሆነ ይህን አያደርግም
እርሷ እኮ ክርስቲያን ስለ ሆነች ይህን አታደርግም
ተብለን ሰማያዊ አባታችንን የምናስደስተው መቼ ነው?

መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።”
  — ማቴዎስ 5፥16

ክርስቲያን ማለት በክርስቶስ ክርስቲያን የተሰኜ የክርስቶስ ኢየሱስ ተከታይ ማለት ነው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታይ የሆነው ቅዱስ ጳውሎስ ክርስቶስን የለበሰ ብእሴ እግዚአብሄር  ነበርና እንዲህ ይለናል

“እኔ ክርስቶስን እንደምመስል ''እናንተም'' እኔን ምሰሉ።”
  — 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥1

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

የአባቶች ምክር

04 Jan, 05:58


የተሳሳቱ ሃሳቦች
ሰው በመንፈሱ በስጋው በነፍሱ  በህሊናው በስሜቱና በሁለንተናው ንፁህ ሆኖ ሊኖር ይገባል አንተን የማያስደስት ማንኛውም ዓይነት ሃሳብ ከእኛ ይራቅ🙏 እንዲህ ብለን ወደ እግዚአብሄር እንፀልያለን በጸሎታችንም ውስጥም አንተ ነፍሳችንን ስጋችንን መንፈሳችንንና ሃሳባችንን አንፃው እንላለን
በህሊና ውስጥ የሚመላለሱ የተሳሳቱ ሃሳቦች ቁጣ ብቀላ ትዕቢት ኩራት ከንቱ ውዳሴ የቁም ቅዥት የምቀኝነት ሃሳቦች ቅናት ዓለማዊ ምኞቶች ዝሙት ርኩሰትና እነዚህ እና የመሳሰሉት ናቸው
ስለ ሆነም ክፉ ሃሳብ መንፈሳዊ ሞትን ስለሚያመጣብን ትዝታው በሕሊናችን ውስጥ ሊኖር አይገባውም

©ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ (መንፈሳዊ ውጊያዎች መፅሐፍ)

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

የአባቶች ምክር

03 Jan, 18:39


አባ መቃሪ በአንድ ወቅት ስለ ትሕትና ሲያስተምር ‹አንድ ባለጠጋ የነበረ ንጉሥ ያለውን ሀብት በአደራ መልክ ከአንድ ደሃ ዘንድ ቢያኖር ፤ ያ ደሃ በእነዚያ ብሮች እና ወርቆች ሊመካ ይችላልን? እንደ ራሱ ንብረትስ በመቁጠር የባለቤትነት ስሜት ሊሰማው ይገባል?› ሲል ይጠይቃል፡፡ በዚህ ቅዱስ አባት ምሳሌ መሠረት ያ ባለጠጋ ንጉሥ እግዚአብሔር ነው፡፡ አደራ ተቀባዩ ነዳይ ደግሞ እኛ ነን፡፡ አደራውም በእጃችን ያሉ በጎ ነገሮች ሁሉ ናቸው፡፡ ያሉንን መልካም ነገሮች እንደ ራስ ንብረት መቁጠርና በሌላው ላይ መኩራራት አደራ ተቀባይነትን እንደ መርሳት ነው፡፡ ሰው ባልፈጠረው በጎነት እንዴት ይኩራራል?


ዲያቆን አቤል ካሳሁን
  🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥   

የአባቶች ምክር

03 Jan, 12:55


ወደ ፈተናም አታግባን

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥   

የአባቶች ምክር

03 Jan, 05:03


ኒቆዲሞስ በሌሊት እየሄደ ከክርስቶስ ሲማር የነበረው በቀን ከክርስቶስ ጋር መታየት ስለሚያሳፍረው ነበር ክርስቶስም ይህን እያወቀ ተቀብሎ አስተምሮታል
እኛም የፈለገ አሳፋሪ ስራን ብንሰራ ክርስቶስ መቼም
አያፍርብንም እና እስከነ ድካማችን ወደ ክርስቶስ እንመለስ
©ሄኖክ ኃይሌ
    🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥   

የአባቶች ምክር

02 Jan, 18:17


እኛ ለባልንጀሮቻችን ምቹ ጊዜ የምንፈልግላቸው ነን ወይስ የምንፈልግባቸው?
የምንፈልግላቸው ከሆነ ልንጠቅማቸው የጎደላቸውን አይተን ልንሞላላቸው ምቹ ጊዜን እንፈልጋለን።

የምንፈልግባቸው ከሆነ ግን ድክመታቸውንና ስሐተታቸውን ዘግበን በዚህ ለመጣል አሳልፈን ለመስጠት ምቹ ጊዜን የምንፈልግ ይሁዳዎች ነን።
ወዳጅ ስትሆን ወዳጅህ የደከመበትን የጎደለበትን የተቸገረበትን ጎን እንደምቹ አጋጣሚ ተጠቅመህ የምትጎዳ ይሁዳ ሳትሆን ይህን የወዳጅህን የጉድለት ወቅት እንደምቹ ጊዜ ተጠቅመህ የምትረዳ የምትጠግን የምትሞላ ደግ ወዳጅ ትሆናለህ። ይሁዳ ግን ምቹ ጊዜን ወዳጁ ክርስቶስን አሳልፎ ለመስጠት ይጠባበቅ የነበረ ሰው ነበር።
more.............
🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

02 Jan, 18:16


ምቹ ጊዜ ለወዳጅ

"ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ አሳልፎ ሊሰጠው ምቹ ጊዜ ይሻ ነበር።"

ወዳጅን ለማንሳት ምቹ ጊዜን መፈለግ የደግ ወዳጅ ጠባይ ነው። ወዳጅን ለመጣል ምቹ ጊዜን መፈለግ ግን ይሁዳነት(የአስቆሮቱ) ነው።

ይሁዳ ምቹ ጊዜን ወዳጁን አሳልፎ ለመስጠት ለሕማምና ለሞት ለመዳረግ ይፈልግ የነበረ ወዳጅ ነው። ወዳጄ አንዳንዶች የስልጣን ጊዜአቸውን በጎ ለማድረግ ትውልድን ለማትረፍ ምቹ ጊዜ አድርገው የሚጠቀሙ አሉ አንዳንዶች ደግሞ ገንዘብ ሲኖራቸው ያን እንደምቹ አጋጣሚ አድርገው በገንዘባቸው ለተቸገረ የሚረዱ ትውልድ የሚያንጽ ሥራ በመሥራትት የሚጠቅሙ ይኖራሉ። እውቀታቸውን ጉልበታቸውን በምቹ ጊዜ ለምቹ ነገር የሚያውሉ በርካቶች ናቸው።

አንዳንዶች ደግሞ ስልጣናቸውን እንደምቹ ጊዜ ተጠቅመው ለበቀል ለጥፋት ሊጠቀሙ ይችላሉ። ይሁዳ ይጠብቀው የነበረው የጌታን ብቻ መሆን ነበር። ልክ እንደ ይሁዳ የሰውን ብቻ መሆን እንደመልካም አጋጣሚ ለክፋት የሚጠቀሙም የይሁዳ ወንድሞች ናቸው።

እኛ ለባልንጀሮቻችን ምቹ ጊዜ የምንፈልግላቸው ነን ወይስ የምንፈልግባቸው?
የምንፈልግላቸው ከሆነ ልንጠቅማቸው የጎደላቸውን አይተን ልንሞላላቸው ምቹ ጊዜን እንፈልጋለን።

የምንፈልግባቸው ከሆነ ግን ድክመታቸውንና ስሐተታቸውን ዘግበን በዚህ ለመጣል አሳልፈን ለመስጠት ምቹ ጊዜን የምንፈልግ ይሁዳዎች ነን።

ወዳጅ ስትሆን ወዳጅህ የደከመበትን የጎደለበትን የተቸገረበትን ጎን እንደምቹ አጋጣሚ ተጠቅመህ የምትጎዳ ይሁዳ ሳትሆን ይህን የወዳጅህን የጉድለት ወቅት እንደምቹ ጊዜ ተጠቅመህ የምትረዳ የምትጠግን የምትሞላ ደግ ወዳጅ ትሆናለህ። ይሁዳ ግን ምቹ ጊዜን ወዳጁ ክርስቶስን አሳልፎ ለመስጠት ይጠባበቅ የነበረ ሰው ነበር።

ማቴዎስ 26
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ "በዚያን ጊዜ የአስቆሮቱ ይሁዳ የሚባለው ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ወደ ካህናት አለቆች ሄዶ።
¹⁵ ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ? እነርሱም ሠላሳ ብር መዘኑለት።
¹⁶ ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ አሳልፎ ሊሰጠው ምቹ ጊዜ ይሻ ነበር።

© ባሮክ
🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥     

የአባቶች ምክር

02 Jan, 02:51


+++ የጀማሪ ጠባይ +++

መንፈሳዊ ሕይወትን ገና ስትጀምረው ለፍጹምነት ጥቂት የቀረህ ያህል ይሰማሃል። አንተ ጋር ያለው ደስታ እና ሰላም ሌሎች ጋር የሌለ ይመስልሃል። በዚህች ሁከት በሞላባት ዓለም አንተ ብቻ ክርስቶስን እንዳገኘኸው ታስባለህ። የቀረው ሕዝበ አዳም እንዲሁ በከንቱ ሲርመሰመስ የሚውል ባካና ሆኖ ይታይሃል። ታዝንለታለህ፣ አይይይ ይህ ኃጢአተኛ ሕዝብ ምን ይሻለዋል? ትላለህ።

የእውነተኛ መንፈሳዊ እድገት መገለጫ ግን ይህ አይደለም። ሰው ወደ እግዚአብሔር እየቀረበ ሲመጣ ከሌላው ሰው ይልቅ የራሱ ጉድለት ይታየዋል። መንፈሳዊነት የሚገልጥልህ ሰዎችን ተመልክተህ የምትፈርድበትን ውጫዊ ዓይንህን ሳይሆን ራስህን አይተህ የምትወቅስበት የውስጥ ዓይንህን ነው። መንፈሳዊ ሕይወትህ ሲጎመራ "አይ ሰው" ሳይሆን "አይ እኔ!" ያሰኝሃል። አባ ማቴዎስም እንዲህ ይላል "ሰው የበለጠ ወደ እግዚአብሔር ሲቀርብ ይበልጥ ኃጢአተኛ መሆኑ እየታየው ይመጣል። ነቢዩ ኢሳይያስ እግዚአብሔርን ካየ በኋላ ከንፈሮቼ የረከሱብኝና የጠፋሁ ሰው ነኝ እንዳለ።"

ከብቃት ደርሰህ መላእክት ሲወጡና ሲወርዱ ቢታዩህ እንኳን ሁሉ እንዳንተ ስለሚመስልህ እንደ ዮሐንስ ሐጺር "ሚካኤል ይበልጣል ወይስ ገብርኤል?"  እያልህ ከአጠገብህ የቆመውን ትጠይቃለህ እንጂ "አይይ አንተ እንኳን ገና አልበቃህም። ብዙ ይቀርሃል" ብለህ ወዳጅህን አታናንቅም። ይልቅ "ለእኔ ብቻ ገልጦ ለሌላው እንዲሰውር የሚያደርገው ምንም ቁም ነገር የለኝም" በማለት ከወንድምህ የተሻልህ እንዳልሆንክ በፍጹም ልብህ ታምናለህ።

ለመንፈሳዊ ሕይወት አዲስ ስትሆን ገና ጥቂት ጸልየህ፣ ጥቂት ጾመህ፣ ጥቂት መጽውተህ ሳለ ግን ሩጫህን ወደ መጨረሱ የተቃረብህ ይመስልሃል። ጉዞህን በግማሽ እርምጃ ከመጀመርህ ከፍጻሜው ላይ የደረስህ ያህል ይሰማሃል። "እኔን ምሰሉ" ማለት ያምርሃል። ነገር ግን መንፈሳዊ ሕይወት የቱንም ያህል ብትሮጥበት ሁል ጊዜ እንደ ጀማሪ የሚያደርግ ረጅም ጎዳና ነው። ሰማንያ ዓመት በገዳም ሲጋደል የነበረው አባ ሲሶይ ነፍሱ ከሥጋው ልትለይ በቀረበች ጊዜ ብዙ መነኮሳት በአልጋው ዙሪያ ከበውት ሳለ ቅዱሱ "አምላኬ ሆይ፣ እባክህ ለንስሐ የሚሆን ጥቂት ጊዜን ስጠኝ?" እያለ በልቅሶ ሲማጸን ሰሙት። በዚህ የተገረሙት መነኮሳቱ አባ ሲሶይን "አባታችን አንተ እድሜ ልክህን በንስሐ የኖርህ መምህረ ንስሐ ሆነህ ሳለ እንዴት አሁን ጥቂት የንስሐ ጊዜን ትለምናለህ?" ቢሉት፣ ቅዱሱም "ልጆቼ ይህን መንፈሳዊ ጥበብ (ንስሐን) ገና አሁን መጀመሬ ነው" አላቸው።

ጌታ ሆይ መንፈሳዊ ሕይወት እኖር ዘንድ አስጀምረኝ፤ ገና ጀማሪ ሳለሁ ደርሻለሁ ከማለትም ሰውረኝ። እንድቆም አትፍቀድልኝ፤ ወደ አንተ ሳበኝ፣ አሳድገኝ።

ዲያቆን አቤል ካሳሁን

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥     

የአባቶች ምክር

01 Jan, 04:32


ጠቃሚ ምክር!

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ

👉 "ለደካሞች ትጉላቸው " ብሎ በተናገረው መሠረት ምንጊዜም የሰዎችን ሞራልና መንፈስ ለመጠበቅ እንሞክር።

👉[1ኛ ተሰ 5*14]  አንድን ሰው ሲቆጡት፤ ሲወቅሱትና ፤ትህትናን ሲነፍጉት ብትመለከቱት እርሱን ከጎናችሁ አድርጋችሁ የሚገባውን በእርሱ ስም ተናገሩለት።

👉 በእርግጥም ይህ ሰው ይህንን ታላቅ ሥራችሁን በእድሜው ዘመን ሙሉ አይረሳውም።
👉 ይህ ማለት ደግሞ በፍቅርና በቸርነት በተሞሉ ታላላቅ ልቦናዎች መንፈሳቸው ለደከመ ሰዎች የተደረገ ታላቅ ሥራ ነው።
👉 በኃጢአት የተተበተበ አንድ ሰው ብታገኙ ከዚህ ነፃ አውጡት እንጂ አትገስጹት።

  👉በአንድ ወቅት አንድ ወጣት ልጅ የገባበት ውኃ ሊያሰጥመው ሲል ራሱን ለማዳን በመፍጨርጨር ላይ ሳለ በዚያ የሚያልፍ አንድ ሰው "ልጄ ሆይ ዋና ሳትችል እንዴት እዚህ ባሕር ውስጥ ልትገባ ቻልክ! ?" እያለ ሲቆጣው ልጁ "በእርግጥ ተሳስቻለሁ ወደዚህ ባሕር የገባሁበትን ምክንያት እንድነግርህ ግን በመጀመሪያ ከሞት አድነኝ " ብሎ መልሶለታል።

👉 እናንተም ልክ እንደዚህ ሰውዬ መሆን የለባችሁም። ማንንም ሰው ሲወድቅ ብትመለከቱት አትገስጹት ይልቁንም። ተስፋ ስጡት።

👉" እኔ ብዙ ጠቃሚ ምክሮች መክሬሃለሁ አንተ ግን አልተጠቀምክባቸውም ስለዚህ ከባድ መከራ ቢደርስብህ አይቆጨኝም " ብለን አንናገር።
  👉 የሐዋርያው ቃል በንቃት አድምጡ። "...... ለደካሞች ትጉላቸው ሰውን ሁሉ ታገሱ" [1ኛ ተሰ 5*14] ።

👉ሥሩን የሰደደ ኃጢአትን ነቅሎ ለመጣል ጊዜና ትዕግስት ስለሚጠይቅ እግዚአብሔር እንደነዚህ ያሉትን ደካሞች በጸጋው እስኪጎበኛቸው ነጻ እስኪያወጣቸው ድረስ ትዕግስት አድርጉላቸው።
አንተም

👉 ተፈጥሮህ ከእነርሱ ጋር ተመሳሳይ ስለሆነ ከዚህ የሚከተለውን የሐዋርያውን ቃል ዘወትር ከፊትህ አስቀድም።

👉 " ከእነርሱ ጋር እንደ ታሰረ ሆናችሁ እስሮችን አስቡ የተጨነቁትን ደግሞ ራሳችሁ ደግሞ በሥጋ እንዳለ ሆናችሁ አስቡ ።[ዕብ 12*3] ።

  👉የእግዚአብሔርን ሕዝብ ተስፋ ለማስቆረጥ የተጉትን ሰዎች እግዚአብሔር ወደ ተስፋይቱ ምድር እንዲገቡ አልፈቀደላቸውም።

👉እግዚአብሔር ሕዝቡን ".....በኃይል ከእኛ ይበረታሉና በዚህ ሕዝብ ላይ መውጣት አንችልም...... ያየናቸው ሰዎች ሁሉ ረጃጅም ሰዎች ናቸው. .... እኛም በዓይናችን ግምት እንደ አንበጣዎች ነበርን " በማለት ሊያዳክሙት የነበሩትን ሰዎች ገድቧቸዋል ። [ዘኁ13*31-33]።
👉  እናንተ ግን አንድ ሰው ኃጢአተኛ ወይም ደካማ ቢሆንም እንኳ በሕይወቱ ውስጥ መልካም ጎኑን በመፈለግ አውጥታችሁ እነዚያ ባሕርያቱን አሞግሱለት።

👉 ኢየሱስ ክርስቶስ ለሳምራዊቷ ሴት ያደረገው እንደዚህ ነው። " ባል የለኝም በማለትሽ መልካም ተናገርሽ. ..."በዚህ እውነት ተናገርሽ "[ዮሐ 4*17እና 18]

👉 ።ይህ ውዳሴ ሴቲቱ ኃጢአቷን እንድትናዘዝ ስላደረጋት ለንስሓ ትበቃ ዘንድ ጌታ አሸንፏታል።

👉አንዱ ሰው ሌላው ሸክሙን በሚያቀሉለት በቅዱሳት መጻሕፍት ታሪኮች ሲበረታታ ሌላው ደግሞ ስለ እግዚአብሔር ጸጋና ሥራ ሲነገረው ይበረታታል።

👉ከዚህ ሌላ ስህተቶቹን ሁሉ በመርሳት የሚበረታታ ሰው ይኖራል።
👉 ለተፈጸመ ስህተት ሁሉ ቁጣን ማቅረብ ግን ወደ ተስፋ መቁረጥ ያደርሳል።

  ©አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥     

የአባቶች ምክር

31 Dec, 05:15


+++ሳያቋርጡ የመጸለይ ጥበብ+++

የሰው ልጅ በዚህች ምድር ላይ ሲኖር ለቅጽበትም ቢሆን አእምሮው ሊረሳውና ሊያቋርጠው የማይችለው ነገር ምን እንደሆነ አስባችሁት ታውቃላችሁ? ሰውነቱ በእንቅልፍ ተሸንፎ እንኳን ቢተኛም እያንቀላፋ አስታውሶ የሚያደርገው ክንውን የትኛው እንደሆነ አስተውላችኋል? እንደው አይሆንም እንጂ ሆኖለት ለደቂቃዎች ሰውነቱ ይህንን ተግባር በመርሳት ባያከናውነው ሕልውናው አጠያያቂ ሁኔታ ውስጥ ይወድቃል፡፡ ይህ ሰውነታችን ልምድ ያደረገውና ለአፍታ እንኳን መቋረጥ የማይፈልገው ተግባር አየር ማስገባትና ማስወጣት ወይም መተንፈስ ነው፡፡

ለዚህ ጽሑፍ ይህን የተፈጥሮ እውነት እንደ መነሻ የተጠቀምነው ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ጸሎትን እንደ ነፍስ እስትንፋስ ይቆጥሯታል፡፡ አየር ያጠረው ወይም ወደ ሰውነቱ የማያስገባ ሰው በሕይወት የመቆየት ዕድሉ ጠባብ እንደሆነ ፤ እንዲሁ ከጸሎት የተለየች ነፍስም ወደ ሞት መንደር የመውረዷ ነገር የሚያጠራጥር አይደለም፡፡ ነፍሳችን ሕያዊት የምትሰኘው በአረጋዊ መንፈሳዊ መጽሐፍ ላይ  ‹የነፍሴ ነፍሷ› ተብሎ ከተጠራው መንፈስ ቅዱስ ጋር በጸሎት ትስስርን ስትመሰርት ነው፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙም እንደሚያስተምረው ሰው ከእስትንፋሱ የበለጠ ዘወትር ፈጣሪውን በጸሎት ሊያስታውስ ይገባዋል፡፡

ጸሎት ማለት ምን ማለት ነው? ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱ ሊቃውንት በፍትሕ  መንፈሳዊ አንቀጽ 14 ላይ ‹ጸሎትስ ሰው ከልዑል እግዚአብሔር ጋር የሚነጋገራት ነገር ናት› ሲሉ የጸሎትን ትርጉም ይነግሩናል፡፡ እግዚአብሔር የሰው ልጆችን በልዩ ልዩ አይነት መንገድ ሊያናግራቸው ይችላል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ በራእይ በመገለጥ ወይም ቅዱስ ዳዊት ‹እግዚአብሔር ለሕዝቡ በመጽሐፍ ይነግራቸዋል› ሲል እንደ ዘመረው በመጽሐፍ በኩል ማናገር ተጠቃሾቹ ናቸው፡፡ የሰው ልጆች ደግሞ ከፈጣሪያቸው ጋር የሚነጋገሩት ጸሎት በተባለ ድልድይ አማካኝነት ያነጋግሩታል፡፡

መተንፈስ ለሥጋዊው አካላችን የዕለት ተዕለት የማይቋረጥ ሥራው እንደሆነ ሁሉ የነፍስ እስትንፋስ የተባለች ጸሎትም ለክርስቲያን የየዕለት መንፈሳዊ ተግባር ናት፡፡ ለዚህም ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹ሳታቋርጡ ጸልዩ› በማለት የሚመክረን (1ኛ ተሰ 5፡17)፡፡

በሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ሶርያዊው አባ ይስሐቅ (ማር ይስሐቅ) ቅዱሳን ምንም ዓይናቸው በእንቅልፍ ሽፋሽፍት ቢያዝ እንኳን ነፍሳቸው ግን ከእግዚአብሔር ጋር በሚደረግ የማይቋረጥ ንግግር (ጸሎት) ውስጥ ስለምትገኝ ተኝተውም ቢሆን ጸሎትን እንደማያስታጉሉ ይናገራል፡፡ እኛ በዓለም የምንኖር ግን የሥጋ ድካም ስላለብን ቀኑንም ፣ማታውንም በጸሎት የማሳለፍ ብርታቱ የለንም፡፡ በመሆኑም ‹ሳታቋርጡ ጸልዩ› የሚለው የሐዋርያው ትዕዛዝ ይከብድብናል፡፡

በዚህም ምክንያት እንደ እኛ ሥጋ ለባሽ የሆኑ አባቶቻችን ይህን ድካማችንን አይተው ቀኑን ሁሉ በጸሎት ማሳለፍ ባትችሉ እንኳን ቢያንስ በቀን ሰባት ጊዜ እግዚአብሔርን ስለ እውነተኛ ፍርዱ አመስግኑት ሲሉ ሰባት የጸሎት ጊዜያቶች ወስነውልናል (መዝ 119፡164)፡፡

ይህ ሁሉ ሲሆን ግን አሁንም ከፈጣሪው ጋር ቀኑን ሙሉ በጸሎት የማሳለፍ ጽኑዕ ፍላጎት ላለው ክርስቲያን አባቶች የሚያስተምሩት ሌላ ‹ሳያቋርጡ የመጸለይ ጥበብ› አለ፡፡ ይህንን ጥበብ የምናገኘው ቅዱስ ጰላድዮስ (St. Palladius) የተባለው አባት ባሰባሰበውና የብዙ አባቶችን ዜና ሕይወት ይዞ በሚገኘው ‹መጽሐፈ ገነት› ላይ ነው፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው ፡-

በአንድ ወቅት አባ ሉቅዮስን (Abba Lucius) ለማየት የመጡ ጥቂት መነኮሳት እንዲህ አሉት ‹በእጃችን ምንም አይነት ሥራን አንሠራም፡፡ የቅዱስ ጳውሎስን ትዕዛዝ በማክበር ሳናቋርጥ እንጸልያለን እንጂ!›፡፡ አረጋዊው መነኩሴ አባ ሉቅዮስም ‹አትመገቡም? ወይም አትተኙምን?› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ እነርሱም ‹አዎን! እንተኛለን ፤ እንመገባለን› ሲሉ መለሱ፡፡ አባ ሉቅዮስም ‹ወንድሞቼ ይቅርታ አድርጉልኝና የምትሉትን ነገር (ሳያቋርጡ መጸለይን) እየፈጸማችሁ አይመስለኝም፡፡ ስለዚህ በእጆቼ ሥራን እየሠራሁ እንዴት ሳላቋርጥ እንደምጸልይ አሳያችኋለሁ፡፡ ዘወትር ጠዋት በእግዚአብሔር እርዳታ የዘንባባ ዛፍ ቅሪቶችን እሰበስብና እነርሱን ሽጬ አሥራ ስድስት ሳንቲሞችን አገኛለሁ፡፡ ከዚያም ሁለቱን ሳንቲሞች ከቤቴ በር ደጃፍ ላይ አስቀምጥና በቀረው ምግብ እገዛበታለሁ፡፡ የገዛሁትንም ምግብ ተመግቤ ስተኛ ፤ ያ ከቤቴ ደጃፍ ላይ ሁለቱን ሳንቲሞች የወሰደው ነዳይ ደግሞ ስለ እኔ ይጸልያል፡፡ እንዲህ እያደረግሁ በእግዚአብሔር ረድዔት ሳላቋርጥ እጸልያለሁ› በማለት ልምዱን አካፈላቸው፡፡   

ስለዚህ አንድ ክርስቲያን ከጸሎት ጋር በቀን ማከናወን ያለበትን ሥራ ሥርቶ ከጨረሰ በኋላ አመሻሽ ላይ ከሚያገኘው ትርፍ ለነዳይ ቢመጸውት ብዙውን ሰዓት በእንቅልፍ የሚያሳልፍበትን ሌሊት በምጽዋት እያካካሰ ሳያቋርጥ ሊጸል ይችላል ማለት ነው፡፡
ሳናቋርጥ እንጸልይ!!!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
    🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

30 Dec, 15:41


ሀጢአት ሳልሰራ አውለኝ ብላችሁ ጸልያችሁ ታውቃላችሁ?..

የአባቶች ምክር

30 Dec, 11:35


የሴት ልጅ የእርሷነቷና የከበረ ማንነቷ መገለጫ ከላይ
በገፅታዋ የሚታየው ስጋዊ አካሏ ሳይሆን

ከውስጥ ያለውና በዐይነ ርግብ የተሸፈነው
ብርታትና ጥንካሬዋ ነው


ቅዱስ ጎርጎርዮስ

    🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

30 Dec, 06:00


“ወደ ባልንጀራህ ቤት እግር አታብዛ፤ ታሰለቸውና ይጠላሃል።”
  — ምሳሌ 25፥17
       🌿 @father_advice 🌿

የአባቶች ምክር

29 Dec, 18:58


ትርጓሜ ወንጌል ኢትዮጵያ😔

ማቴዎስ 24
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው
⁷ ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ
በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤
እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።
⁹ በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችኋል ይገድሉአችሁማል፥ ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።
¹⁰ በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ፤
¹¹ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤
¹² ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች።
እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።”

     🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡      
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ 

ጸልዩ በእንተ ሀገሪትነ ኢትዮጵያ 🙏

የአባቶች ምክር

29 Dec, 14:07


“ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል?”
— 1ኛ ዮሐንስ 4፥20

   🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥     

የአባቶች ምክር

29 Dec, 13:09


ክፋትን_ከአንተ_አርቃት

"ሰይጣን ክርስቶስ በልብህ ውስጥ ያለ መሆን አለመሆኑን ያውቃል፡፡ ይኸውም ስትቆጣ ወይም ስትጮህ ወይም የማይረቡ ከንቱ ነገሮችን ስትናገር ሲያይህ ጠላት በአንተ ዘንድ እግዚአብሔር እንደሌለ ያውቃል ያን ጊዜ በውስጥህም በውጭህም ያለውን ሳይቀር ይገዛል ፤ መዝጊያ እንደሌለው ቤት እንደ ክፉ ሌባ ይገባና ውስጥህን ይበረብረዋል፡፡"

© ቅዱስ_ ባስልዮስ

      🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

29 Dec, 08:32


ሰካራሙ መነኩሴ

በአቶስ ተራራ ላይ በካሬስ የሚኖር አንድ መነኩሴ ነበር።  በየቀኑ ይጠጣ ነበር፣ ከዚያም በመነኮሳትና በመንፈሳዊ ተጓዦች(pilgrims) ላይ ችግር ይፈጥራል....ይኽንን እያደረገ ሰነባበተ...በገዳሙ የሚኖሩ መነኮሳት በሙሉ በሰካራምነቱ ስለሚያውቁት "ሰካራሙ መነኩሴ" በሚል ነበር የሚያውቁት...ከጥቂት ጊዜ በኋላ ይኽ መነኩሴ አረፈ።

👉በሞተም ጊዜ ከመነኮሳት መካከል የተወሰኑት ወደ አባ ፓይሲየስ ዘአቶናዊው ፈጥነው ሄዱና በደስታ ሆነው የገዳሙ ችግር አሁን ማብቃቱን ነገሩት(ሰካራሙ በመሞቱ)።

አባ ፓይሲየስ ስለ መነኩሴው ሞት አስቀድሞ ያውቅ ነበር፤ የመላእክት ጭፍሮችም የመነኩሴውን ነፍስ ለማግኘት ሲመጡ አይቶ ነበር። እነዚያም መነኮሳትና መንፈሳዊያን ተጓዦቹ ግራ በመጋባት በመሆንና አባ ፓይሲየስ ለመልካሙ ዜናቸው በሰጠው ምላሽ ሲናደዱ፣ ቅዱስ ፓሲዮስ የሚከተለውን ነገራቸው፡-

"ይህ መነኩሴ በታናሿ እስያ ነው ከእልቂቱ
(Holocaust) በፊት ብዙም ሳይቆይ የተወለደው።  ወላጆቹ ልጃቸውን ብቻውን መተው ስላልፈለጉ አዝመራውን ለመሰብሰብ(harvest) ሲሔዱ ይወስዱት ነበር፤ በዚኽም ልጃቸው እንዳያለቅስ እና እንዳይያዙ ወተቱ ላይ ጠንካራ የአልኮል መጠጥ ጨምረው እንቅልፍ እንዲተኛ በተደጋጋሚ ያደርጉት ነበር።  በዚህም ምክንያት ይኽ መነኩሴ የአልኮል ሱሰኛ ሆነ...ሐኪሞችም ቤተሰብ እንዳይመሰርት  ስለመከሩት፣ ወደ አቶስ ተራራ(Mount Athos) በመምጣት መነኩሴ ሆነ።  ሰካራም መሆኑንም ለአንድ ሽማግሌ ካህን ተናዘዘ።  ሽማግሌው ካህንም በየቀኑ እንዲሰግድ አዘዘው እና ወደ ቅድስተ ቅዱሳን የአምላክ እናት ድንግል ማርያም(Theotokos) እንዲጸልይ እናም ቀስ በቀስ መጠጥ እንዲቀንስ እንድትረዳው እንዲጠይቃት እንዲለምናትም ነገሩት...ይኽንንም በብዙ ጥረት ማድረጉን ቀጠለ። 

ከአንድ አመት ተከታታይ ተጋድሎ እና ንስሃ በኋላ በየቀኑ የሚጠጣውን 20 መጠጥ ወደ 19 ዝቅ ማድረግ ቻለ። ትግሉ ቀጠለ እና ከዛ ሁሉ መንፈሳዊ ጦርነት ዓመታት በኋላ መነኩሴው በቀን የሚጠጣው ከ2-3 ጊዜ ብቻ ነበር። ለዓመታት ሰዎች እንደ ሰካራም መነኩሴ እና ችግር ፈጣሪ ያውቁታል <ነገር ግን እግዚአብሔር እንደ አንድ ተዋጊ ስሜቱን ለማሸነፍ በታላቅ ቅንዓት ሲታገል ተመለከተ።> በዚኽም በከበሩ መላእክት ነፍሱ ታጅባ ሔደች" አላቸው።

ይኽንን የሰሙት መነኮሳቱ እና መንፈሳዊያን ተጓዦቹም ምን ያኽል በሰው ድካም ሲፈርዱ እንደነበር አውቀው ተጸጸቱ🙏ለዚህም ነው ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ "ኃጢአት ሲሠራ ባየኸው ወንድም ላይ አትፍረድ፥ አንተ ግልጽ የወጣ ኃጢአቱን እንጅ በስውር ለካህን የሚነግረውን ንስሐ አታውቅምና። ስለዚህ የራስህን ድካም ተመልከት።" ያለው🙏🙏🙏

በአንዳች ነገር ላለመፍረድ ሞክሩ
እንኳን ባላያችሁት ባያችሁትም



🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

28 Dec, 15:38


የሚናገሩትን ልትመርጥላቸው አትችልም
ምን መስማት እንዳለብህ ግን መምረጥ ትችላለህ።

ምን መጻፍ እንዳለባቸው ወስነህ መስጠት አትችልም የሚያጠፋህን ሳይሆን ግን የሚያንጽህን መርጠህ የማንበብ መብቱ ያንተ ነው።

መስማት ስለቻልን ብቻ ሁሉን የምንሰማ አንሁን መናገር ስለቻልንም ብቻ አፍራሹንም አጥፊውንም አንናገር። የተበከለ ምግብ ቀርቦልን እንደማንበላ ሁሉ የተበከሉ ንግግሮችን እንጠየፍ። የቆሸሸ ምግብ ለጤና ጠንቅ እንደሆነ ሁሉ ጤናማ ቃል የሌለባቸውም ንግግሮች ጦማሮች/ጽሑፎች/ ለአመለካከት ጠንቅ ናቸው። ስለሆነም ስንበላ ብቻ ሳይሆን ስናነብ እንምረጥ ስንጠጣ ብቻ ሳይሆን ስንሰማም እንጠንቀቅ።

የበላነው በሥጋነት የጠጣነው በደምነት ውሕደት እንደሚገነባን ሁሉ ያነበብነው አመለካከትን የምንሰማው ርዕዮትን ይገነባል። ሰው ለአካላዊ ጤንነቱ ጤናማ የአመጋገብ ስርአት መከተል ወሳኝ እንደሆነ ሁሉ ለጤናማ አመለካከት ጤናማ አሰማም ያሻል።

ምክንያቱም ዓይኑ ጤናማ ካልሆነች ሰው አፍአዊ ዕይታው ላይ ተጽእኖ እንደሚኖረው ሁሉ ውሳጣዊ ምልከታውም ከታወረ ዕይታው ሁሉ የታመመ ነው የሚሆነው። እርሱ የሚከሰተው ደግሞ በአፍራሽ ንግግሮች ነውና ምን እየሰማን እንዳለን እንጠንቀቅ ጆሮአችንን መርጠን እንስጥ።

©ባሮክ

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

27 Dec, 18:45


ከምንባብ በፊት የሚፀለይ ፀሎት በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ።

ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በዚህ በምድር በምኖርበት ዘመን ሁሉ ቃልህን አንብቤ ፈቃድህን እረዳ ዘንድ የልቡናዬን አይኖች አብራልኝ።
የሕግጋትን ምስጢር ከእኔ አትሰውር ይልቁኑ የትዕዛዛትህን መልዕክታት ተረድቼ በሕግህ እደነቅ ዘንድ የልቡናዬን አይኖች አብራልኝ።በመፅሀፍ ውስጥ የተሰወረውን የአንተን ጥበብ ግለፅልኝ።
ጌታዬ ሆይ በአንተ የእውቀት ብርሀንነት ለልቡናዬ ማስተዋልን ትሰጥ ዘንድ ተስፋዬ በአንተ ላይ ነው።
በቅዱስ መፅሀፍ በሰፈሩት መልዕክታትህ ደስ እሰኝ ዘንድ ተስፋዬን በአንተ ላይ አኑራለሁ፤ቅዱስ በሆነው መፅሀፍህ ውስጥ የማነባቸው የቅዱሳኖችህ ህይወትና ትምህርት እኔን ወደ ኃጢአት የሚመሩኝ አይደሉም፤ይልቁኑ ለንስሐ፣ለአእምሮ ብሩህነት፣ለነፍሴ ድኅነት እንዲሁም የርስትህ ወራሽ እንድሆን የሚያበቁኝ ናቸው እንጂ።በጨለማ ላሉት ብርሀን የሆንህና በአንተ መልካም ስራ እንዲሰሩ ከፀጋህ ያደልካቸው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ከዘለዓለም እስከ ዘለአለም ክብር ምስጋና ላንተ ይሁን..... አሜን።

  🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

27 Dec, 13:31


"ሥጋችን ምግብ ሲያጣ እንደሚደክም ሁሉ ነፍስም ምግቧን የእግዚአብሔርን ቃል ስታጣ ትደክማለች።"

ብጹዕ አቡነ ሽኖዳ
   🌿 @Father_advice🌿 

የአባቶች ምክር

27 Dec, 08:48


አንደበቱን የሚጠብቅ ሕይወቱን ይጠብቃል፤ አፉ እንዳመጣለት የሚናገር ግን ይጠፋል።”
ምሳሌ 13 : 3

የአባቶች ምክር

27 Dec, 03:41


#መጽሐፍ_ቅዱስ

በአንድ ተራራማ ስፍራ እርሻ በማረስ ከልጅ ልጁ ጋር የሚኖር አንድ ሽማግሌ ነበር፡፡ ይህ ሽማግሌ ዘወትር ፀሐይ ብርሃኗን ስትፈነጥቅ እየተነሳ መጽሐፍ ቅዱስን ያነባል፡፡ የልጅ ልጁ የአያቱን ተግባር ይከታተል ስለነበር እሱም ያያቱን ፈለግ በመከተል ጠዋት ጠዋት እየተነሳ መጽሐፍ ቅዱን ማንበብ ጀመረ፡፡

አንደ ቀን ታድያ አያቱን “አባባ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ እየሞከርኩ ነበር፡፡ ነገር ግን ልረዳው አልቻልኩም ደግሞም አንብቤ እንደጨረስኩ ወዲያውኑ እረሳዋለሁ እናም እንድረዳውና እንዳልረሳው ምን ማደረግ አለብኝ?” ሲል ጠየቀ፡፡

ሽማግሌው ምንም ድምጽ ሳያሰሙ “ከሰሉን ወደ ምድጃው ጨመሩና እንካ ይሄን የከሰል ቅርጫት ይዘህ ወንዝ ውረድና ውሃ ይዘህልኝ ተመለስ” አሉት፡፡ ልጁ ትዛዙን ለመፈጸም ወደወንዝ ወርዶ ውሃውን ይዞ ሊመለስ ቢመክርም ቅርጫቱ ውሃውን እያንጠባጠበ ቤት ከመድረሱ በፊት ፈሶ አለቀበት፡፡ ሽማግሌው የልጁን ሁኔታ እያስተዋሉ “አሁን ለሁለተኛ ጊዜ ይዘህ ስትመጣ ግን ፈጠን ፈጠን ብለህ ተመለስ ብለው” ድጋሜ ላኩት፡፡ አሁንም ልጁ እንደተነገረው በፍጥነት ውሃውን ቀድቶ ሊመለስ ቢሞክርም ቤቱ ሳይደርስ ውሃው ፈሶ አለቀበት፡፡ አያቱንም “በቅርጫት ውሃ ማምጣት ስለማይቻል ሌላ መያዥ ይስጡኝና ላምጣ” ሲል ጠየቀ፡፡ ሽማግሌ አያቱም “እኔ የምፈልገው የቅርጫት ውሃ ነው፡፡ ጠንክረህ ባለመሞከርህ ነው ፈሶ ያለቀብህ” በማለት እንደገና ላኩት፡፡ በዚህ ጊዜ ልጁ በቅርጫት ውሃን ማምጣት እንደማይቻል ቢያውቅም ለአያቱ ታዛዥነቱን ለማሳየት ከበፊቱ ፈጥኖ ለማምጣት ሲሞክር ውሃው ፈሶ ስላለቀበት ባዶውን ቅርጫት እያሳየ “ተመልከት አባባ! እዲሁ ነው የምደክመው እንጅ እኮ ጥቅም የለውም” አለ፡፡

ከዚህ ጊዜ ምልልስ በኋላ ሽማግሌው “እስኪ ቅርጫቱን ተመልከተው” አሉት፡፡ ልጁ ቅርጫቱን ሲመለከት ከዚህ በፊት የማያውቀው ቅርጫት ይመስል ቅርጫቱ የተለየ ሆነበት የከሰል መያዣ እያለ በጅጉ የቆሸሸ ነበር፡፡ አሁን ግን ሙልጭ ብሎ ጸድቷል፡፡ ውስጡን ሲመለከተው ከመንጻቱ የተነሳ የበፊቱ ቅርጫት አልመስለው አለ፡፡

ስለዚህ ልጄ መጽሐፍ ቅዱስን ስታነብ የሚሆነው እንደ እርሱ ነው፡፡ ላትረዳው ትችል ይሆናል ወይም ደግሞ ያነበብከውን ሁሉንም ነገር ላታስታውሰው ትችል ይሆናል ዳሩ ግን ባነበብክ ቁጥር ለውጨኛው የሚተርፍ ውስጣዊ ንጽህና እያመጣህ መሆኑን አትዘንጋ የመንፈስ ሥራ እንደዚህ ነው በማለት አስተማሩት፡፡

   🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

26 Dec, 18:53


💎በአንተ ያለን እምነት እና ለአንተ ያለን ፍቅር💎

እርሱን ውዴ የምትል ነፍስ በፍቅሩ እሳት የምትነድ ማንነት ለክፉ ሃሳብም ግብርም አትሰጥምና ሰይጣን ይሰለጥንባት ዘንድ አይችልም።

ክርስቶስን እጅግ ስናፈቅር ሰይጣን ይፈራል ክፉ የመናፍስት ሰራዊት ይቀርቡን ዘንድ አይቻላቸውም። በእርሱ ያለን እምነት አሸናፊዎች ሲያደርገን ለእርሱ ያለን ፍቅር አስፈሪዎች ያደርገናል። ሰይጣን ምን ያስፈራዋል ቢባል ክርስቶስን በፍጹም ልብ በፍጹም ነፍስ በፍጹም ኃይሉ የሚወድ ሰው መልሱ ነው።

🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥     
        ⌲               
       ˢʰᵃʳᵉ   

የአባቶች ምክር

26 Dec, 12:48


ወዴት ነህ ?

ወዴት ነህ ? ብለህ አዳምን የፈለግህ ፣ ያለበትን እያወቅህ ያለበትን ያሳወቅህ ፣ በቃል ብቻ ሳይሆን በለቢሰ ሥጋ ወዴት ነህ ? ብለህ የፈለግህ ፣ ከገነት ጫካ እስከ ቀራንዮ የጠፋውን ያሰስህ እኛም በተራችን እንጠይቅህ ወዴት ነህ ?

ለመቆምም ለመሄድም ስንፈራ ፣ ለመግጠምም ለመለያየትም ስንሰጋ ፣ ለመጀመርም ለመጨረስም ስንንቀጠቀጥ ፣ መንፈስህ የራቀን ይመስለናል ። እባክህ ወዴት ነህ ? ገጻችን ሲጠቁር ፣ የልጅ አዋቂው ፊት ትካዜ ሲይዘው ፣ የመኖር መላ ጠፍቶ ሞት እንደ መፍትሔ ሲፈለግ ፣ ድሀ ያለችውን ሲነጠቅ ፣ የፈሩት እየደረሰ ፣ የጠሉት ሲወርስ ምነው አንድዬ ጨከነብን ይሉሃል ። እባክህ ራስህን ግለጥ ፤ ወዴት ነህ ? ሳትለየን የተለየኸን ፣ አጠገባችን እያለህ የራቅኸን መስሎ ሲሰማን ወዴት ነህ ? ብለን በተራችን እንጠይቅሃለን ።

መልሱ ጥያቄ ከሆነብን ጥያቄው ምን ሊመስል ነው ? ሽማግሌው በሰላም ማረፍ ፣ ሬሳው አፈር መልበስ ፣ የወጣው መግባት ፣ የተማረው ማምረት ፣ የሠራው ማግኘት ሲሳነው ወዴት ነህ? እንልሃለን ፣ ለመብላት ይከፍለው የሌለው በሰው እጅ ታግቶ ለመኖር ሲከፍል ፣ ፈጥሮ ላልፈጠረ ተወን እንዳትባል እባክህ ወዴት ነህ ? ዓለም ሰላም ሆኖ እኛ ብቻ የታወክን መስሎ ይሰማናልና እባክህ እንፈልግህ ወዴት ነህ ?

የክፋት አማካሪዎች ምድሩን ሞልተውታል ። ገላጋይ ጠፍቶ ቤተሰብ ያልቃል ። ጌታ ሆይ እባክህን አይቴ ውእቱ አምላኮሙ ከመ ኢይበሉነ...። ጸሎታችንን ስማን
አሸናፊ በሌለበት ወንድማማች ይዋደቃል ። ከሚደነቅ ወደሚያደቅ ምዕራፍ ስንሸጋገር ፣ ቀኛችን ግራ ሁኖ ግራ ሲያጋባን ወዴት ነህ ? እንልሃለን ። የጠፋውን አዳም ፈልገህ ያገኘኸው ፣ የጠፋብንን እውነት ፈልገን እስክናገኘው እርዳን ። እየጸለይን ካለመሰማት ፣ ስምህን እየጠራን ከመለያየት እባክህ አድነን ። አሁንም በቀረችው ትንሽዋ አቅማችን ወዴት ነህ ? እንልሃለን ። ስለ ድሆች እንባ አለሁ በለን ።

   🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

26 Dec, 07:43


ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ3ኛው ክፍለ ዘመን የነበረ አንድ የሚያስገርመኝ ዜኖ የሚባል ፈላስፋ ነበር። ይህም ሰው ከዕለታት በአንዱ ቀን ከትምህርት ቤት ወደ ቤቱ ሲመለስ ድንገት ወደቀና ጣቱ ክፉኛ ተጎዳ። ከዚያም ከወደቀበት ሳይነሣ በእጆቹ መሬቱን እየመታ “እየመጣሁ ነውና እኔን ለመጥራት መድከምህ ከንቱ ነው” ሲል የአንድ ባለ ቅኔን ንግግር ተናግሮ እዚያው ራሱን አፍኖ ገደለ።
ይኸው ፈላስፋ ደግሞ የሚያደንቃቸው አትላንቲክ ውቅያኖስ አካባቢ የሚኖሩ Celts የሚባሉ ወገኖችም ነበሩ። እነዚህ ሰዎች ሞትን መፍራትን እንደ ትልቅ ውርደት አድርገው ስለሚቆጥሩ ትልልቅ ጥፋት የሚያመጡ ነገሮችን ሳይቀር ፊት ለፊት ይጋፈጡ ነበር። ለምሳሌ ቤቱ ሊያፈርስ ቢያዘምባቸው ወይም ግድግዳው ሊናድ ቢንደረደርባቸው ሮጠው ከዚህ አደጋ ለማምለጥ አይሞክሩም። በውቅያኖስም ውስጥ ሆነው ማዕበል ቢቀሰቀስ ወደ ኋላ አያፈገፍጉም። እንዲያውም ወጀቡ እስኪያልፍ ባሉበት ሳይንቀሳቀሱ ይቆማሉ። ሞትን ፈርተው ሸሹ እንዳይባሉ እነዚህን አስፈሪ ነገሮች ያደርጋሉ።
ሕይወት እግዚአብሔር የሰጠን ትልቁ ስጦታ ነው። እርሱ በቀጠረው ጊዜ እስኪጠራን ድረስ አለመታገስ የዚህን ስጦታ ዋጋ አለመረዳት ነው። እውነተኛ ጀብድ በዚህ አስቸጋሪ ዓለም ሊያጋጥሙ የሚችሉትን ፈተናዎች ሁሉ ታግሎ ለማሸነፍ እስከ መጨረሻዋ ሕቅታ ድረስ መፋለም እንጂ ቀድሞ ሩጫ ማቋረጥ አይደለም። አንድ ክርስቲያን ሞትን እንደማይፈራ ማሳየት ያለበት “ሕያው የሚያደርገውን” የክርስቶስን ሥጋ እና ደም በመቀበል እንጂ ራሱን ለሞት በማጋለጥ መሆን የለበትም።
“ማምሻም ዕድሜ ነው” እንደሚባለው አይደለም በወጣትነት በሽምግልና ዘመን የቀረች ጥቂት ቀን እንኳ ታሳሳለች። ምክንያቱም ከመሰንበት ንስሐ መግባት፣ መጸጸት፣ መመለስ፣ የኋላውን ትቶ የፊትን ለመያዝ መዘርጋት አለና።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን

የአባቶች ምክር

26 Dec, 06:24


ዕብራውያን 4
¹² የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤
¹³ እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም።
¹⁴ እንግዲህ በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፥
ጸንተን ሃይማኖታችንን እንጠብቅ።

  🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥     

የአባቶች ምክር

26 Dec, 04:01


"ሕፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሠጥቶናል ስሙም
ድንቅ!
መካር ኃያል አምላክ
የዘላለም አባት
የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል" ኢሳ.6:9

      🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

25 Dec, 05:49


እንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን፥ እንደ ሰው ወግና እንደ ዓለማዊ እንደ መጀመሪያ ትምህርት ባለ በፍልስፍና በከንቱም መታለል ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠበቁ።”
— ቆላስይስ 2፥8

🌿 @Father_advice🌿 
  ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

24 Dec, 19:13


እግዚአብሔርን አመስግኑት
ስራህ ግሩም ድንቅ ነው በሉት / 2 /

ሰማይን ያለ ምሰሶ 
ምድርንም ያለ መሠረት
ያጸናው እርሱ ነው 
ሥራህ ድንቅ ነው በሉት
more...................
🌿 @Father_advice🌿 
    ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
       ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
      ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌‌‌

የአባቶች ምክር

24 Dec, 17:24


ልጄ_ሆይ

ሁኔታዎች የከበዱ ሲመስልህ እነዚህን አስታውስ!

1) እግዚአብሔር ካንተ ጋር እንደነበረ

2) አሁንም ካንተ ጋር እንዳለ

3) ሁልጊዜም ካንተ ጋር እንደሚሆን

©አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
    🌿 @Father_advice🌿 
             ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
                 ❍ᅠ    ⎙ᅠ  ⌲     ♡          
             ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ˡᶦᵏᵉ   ‌‌

የአባቶች ምክር

24 Dec, 10:02


ስለዚህ ዘወትር እግዚአብሔርን አመስግን፡፡
ብትታመምም እግዚአብሔርን አመስግን፤
ሀብት ንብረት ብታጣም አመስግን፤
በሐሰት ቢከሱህም አመስግን፡፡

እንደ ነገርኩህ ተጎጂዎቹ ክፉ ተቀባዮች ሳይሆኑ
             ክፉ አድራሾች ናቸውና፡፡"

©ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
  🌿 @Father_advice🌿 
             ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
                 ❍ㅤ    ⎙ㅤ  ⌲     ♡          
             ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ  ˡᶦᵏᵉ   

የአባቶች ምክር

24 Dec, 07:25


እግዚአብሔር የሚከብርበት ክርስቲያናዊ ጋብቻ የሚከተሉት አምስት ባሕርያት ይኖሩታል።

1) የእግዚአብሔር ቃል የኑሮአቸው መመሪያ ነው። « ሕግህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴ ብርሃን ነው»  በማለት መዝሙረኛው እንደተናገረው ክርስቲያዊ ቤተሰብም በቃሉ በመመራት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ያከናውናል። መዝ 119:105።

2) ጸሎት የሕይወታቸው መሠረት ነው።  «እውነት እላችኋለሁ ማንም ያለው ነገር እንዲደረግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር ይህን ተራራ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል።ስለዚህ እላችኋለሁ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል።» በማለት ጌታ እንዳስተማረን ክርስቲያናዊ ቤተሰብ  የማይቻለውን ለእግዚአብሔር እያቅረበ የእግዚአብሔርን ጸጋ ይቀበላል። ማር 11:23-24።

3) ፍቅር የቤታቸው ቋንቋ ነው። « በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደ ሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜ አለሁ።» በማለት ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው የክርስቲያናዊ ሕይወታችን ዋና አምድ ፍቅር ነው። በባልና በሚስት መካከል ሊኖረው የሚገባውም ፍቅር በሁኔታዎችና በጥቅም ላይ የተመሠረተ ፍቅር ሳይሆን መሥዋዕታዊ ፍቅር ነው። 1 ቆሮ 13፥1።

4) መደማመመጥ የዕለት ምግባቸው ነው። «የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን የሚፈሩ እርስ በእርሳቸው ተነጋገሩ እግዚአብሔርም አደመጠ ሰማም» በማለት ነቢዩ እንደተናገረው ( ሚልክያስ 3:16 በመደማመጥ ውስጥ ፍቅር ይዳብራል። የተሰበረ ይጠገናል የታመመ ይፈወሳል። እግዚአብሔር ጸሎትን ይሰማል። «ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ ጸሎታችሁ እንዳይከለከል አብረው ደግሞ የሕይወትን ጸጋ እንደሚወርሱ አድርጋችሁ አክብሩአቸው።» 1 ጴጥሮስ 3:7።

5) ደስታ ውበታቸው ነው። የእግዚአብሔር ቃል «ምንጭህ ቡሩክ ይሁን ከጕብዝናህም ሚስት ጋር ደስ ይበልህ።እንደ ተወደደች ዋላ እንደ ተዋበችም ሚዳቋ ጡትዋ ሁልጊዜ ታርካህ በፍቅርዋም ሁልጊዜ ጥገብ። » ምሳሌ 5:18-19። ይላል።  እግዚአብሔር የከበረበት ቤተሰብ ደስተኛ ፈገግተኛና ለዛ ያለው ቤተሰብ ነው።

© መ/ር አቤል ተፈራ

       🌿 @Father_advice🌿 
             ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
                 ❍ㅤ    ⎙ㅤ  ⌲     ♡          
             ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ  ˡᶦᵏᵉ   

የአባቶች ምክር

23 Dec, 18:06


''በከፍተኛ ቁጣ የተሞላ ሰው ራሱን ይገድላል። ይህ ሰው ለስህተት ተጠያቂ የሆነና ደካማ ጤንነት ያለው ሰው ነው። ጢስ ንቦችን ከቀፎአቸው እንደሚያስወጣቸው ቁጣም እውቀትን ከልብ ያስወጣል።''
                     ቅዱስ ኤፍሬም

     🌿 @Father_advice🌿 
             ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
                 ❍ㅤ    ⎙ㅤ  ⌲     ♡          
             ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ  ˡᶦᵏᵉ   

የአባቶች ምክር

23 Dec, 14:22


📚ብሒለ አበው

ከንስሐ አባትህ ጋር ስትሆን ጥያቄህን እንጂ ውሳኔህን አታቅርብላቸው በልብህ ካሰብከው ጋር እንዲስማሙ ሳይሆን በሀሳብ ላይ ሀሳባቸውን ምክራቸውን እንዲሰጡህ አድርግ።
         ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሣዊ


ክርስቲያን ወንድምህን በፍቅር ባየኀው ጊዜ እግዚአብሔርን ማየትህ ነው።
       ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ


ፍቅር በእውነት ሰማያዊ ኅብስትና የአእምሮ ምግብ ነው።
       ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ


እኛ ወደ እርሱ መውጣት ሲያቅተን እርሱ ወደ እኛ ወረደ።
       ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሣዊ


ፍቅርን ገንዘብ ያደረገ ሰው ሁልጊዜ ክርስቶስን ይመገበዋል።
           ማር ይስሐቅ


      🌿 @Father_advice🌿 
             ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
                 ❍ㅤ    ⎙ㅤ  ⌲     ♡          
             ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ  ˡᶦᵏᵉ   

የአባቶች ምክር

23 Dec, 11:26


መዝሙር ትዘምራላችሁ?

አንድ ክርስቲያን መዝሙር ትዘምራለህ ተብሎ ቢጠየቅ መልሱ አዎ ነው የሚሆነው መቼ ሲባል ደግሞ
ሰንበት ተማሪዎች በማህበር እንዘምራለን የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችም በማህበር እንዘምራለን ማህበረ ምዕመናንም በጉባኤ ፊት እግዚአብሄርን በዝማሬ እናመሰግናለን ብለን እንመልሳለን!
በግል የጸሎት ህይወታችንም በዝማሬ ብንተጋ እጅግ ማትረፊያ ነው መዝሙር በማህበር መልካም እንደ ሆነ ሁሉ በግል የጸሎት ህይወታችን እጅግ መልካም ነው
ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ ዘምሩ ለንጉስነ ዘምሩ

መዝሙር ማምለኪያ ነው
መዝሙር ጸሎት ነው
መዝሙር ምስጋና ነው
መዝሙር የአመስጋኝነት ህይወት መገለጫ ነው

በማህበር ፊት ለመዘመር ፀጋው ያለው ሰው ያስፈልጋል
በጌታ ፊት ለመዘመር ግን የሪትም ህግን አይጠይቅም
የድምፅ ማማርንም አይጠይቅም መኮላተፋችንን ሊሰማ ይጠብቀናል
እንዘምር

በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤”
— ኤፌሶን 5፥19

“የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤ በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ፤ በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤”
— ቆላስይስ 3፥16

  🌿 @Father_advice🌿 
             ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
      ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
                 ❍ㅤ    ⎙ㅤ  ⌲     ♡          
             ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ  ˡᶦᵏᵉ   

የአባቶች ምክር

07 Dec, 13:49


1ኛ ጢሞቴዎስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ፤
¹⁶ ስለዚህ ግን፥ የዘላለምን ሕይወት ለማግኘት በእርሱ ያምኑ ዘንድ ላላቸው ሰዎች ምሳሌ እንድሆን፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ዋና በምሆን በእኔ ላይ ትዕግስቱን ሁሉ ያሳይ ዘንድ፥ ምህረትን አገኘሁ።
¹⁷ ብቻውን አምላክ ለሚሆን ለማይጠፋው ለማይታየውም ለዘመናት ንጉሥ ምስጋናና ክብር እስከ ዘላለም ድረስ ይሁን፤ አሜን።

የአባቶች ምክር

06 Dec, 13:39


የዓለምን ሕይወት የሚለውጥ ዜና

የአባቶች ምክር

06 Dec, 10:30


እግዚአብሔር መልካም ነው

     "እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል ::" (ናሆ  ፩ ፥ ፯)
        
ያለው ማማሩ ፣ ... እያሉ እንደ ዋዛ የሚናገሩ ሰዎች አሉ። ያለው ሰው ሁሉም ነገሩ ያምራል። ሰውዬው ባለ ጠጋ ነው ፣ ቆንጆ ሴት ያዘ ። አንድ ቀንም "ቆንጆ ነኝ ወይ እቱ?" ብሎ ቢጠይቃት "ጌታዬ የባለጠጋ አስቀያሚ የለውም" አለችው ይባላል። ባለጠጋ በመንገድ ቢወድቅ የሚደግፈው ብዙ ነው ፣ ንግግሩ ቢሰበር የሚጠግንለት፣ እንዲህ ያሉት እንዲህ ለማለት ፈልገው ነው በማለት የቃል ወጌሻዎች ይሰለፉለታል። አንድ ምስኪን ሰባኪ የቃል ስህተት ሲያሰማ ሁሉም ተሳስተሃል ፣ ውጉዝ ነህ ሊለው ይጣደፋል። ተራራ የሚያህል ስህተት የሚናገሩ ትልልቅ የሚባሉ ሰዎች ብቅ ሲሉ ቃላቸውን የሚጠግን ወጌሻ ቊጥር የለውም። ለማለት የፈለጉት እንዲህ ነው፣ ከዐውዱ ተገንጥሎ ታይቶባቸዋል በማለት በከንቱ እሪ ይሉላቸዋል። እርሳቸው መልስ ስጡልኝ አላሉም። ላለው ቅንጭብ ያረግዳል ይባላል። እንኳን ሰዉ ቀጤማውም ልጎዝጎዝልህ ይለዋል።  ደሀው ግን በመንገድ ሲወድቅ በሞትኩት ከሚለው ምነው ሞቶ ባረፈው የሚለው ብዙ ነው። በቃሉ ሲሰበርም አፍ አፉን የሚለው ምነው ዝም ብትል ብሎ የሚመክረው ሁሉም ነው።

ክፉ ቀን አይምጣ ወዳጅ እንዳላጣ ይባላል። ክፉ ቀኖች ነፋስ ገለባን እንደሚበትን ወዳጆችን ይበትናሉ ። ደጉ ሰው ክፉ ይሆንብናል። መንገድ ሲያገኘን ተወርውሮ የሚያቅፈን መንገድ አሳብሮ ይሸሸናል። የተከፈቱ በሮች ዝግ ይሆኑብናል። ለልመናና ለእርዳታ የመጣን መስሏቸው ሰዎች ይሰለቹናል። እኔም ችግር አለብኝ ምን ላድርግህ በማለት በልቡ የሚያማን ይኖራል። በመከራ ቀን መልካም ሰው ማግኘት ውድ ነው።

ጴጥሮስ በሰላም ቀን ተገኘ ፣ በክፉ ቀን ከዳ። የቀሬናው ስምዖን ግን በግብዣው አልነበረም፣ በመከራ ቀን ግን መስቀል አጋዥ ሆነ ። በመከራ ቀን እግዚአብሔር ሰው ይሰጣል። ለቀኑ በልኩ የተሰፉ ሰዎችን ያመጣል። በመከራ ቀን የሚገኙ ሰዎች ጠባይ የመጀመሪያው በመከራ ማለፋቸው ነው። የሌሎችን መከራ ሲያዩና ሲሰሙ ያለፉበትን የጭንቅ ጊዜ ያስታወሳሉ። መከራን ከመከረኛ ጋር ማውራት ጥሩ ነው ይባላል። እነዚህ ሰዎች ካነበቡት ብቻ ሳይሆን ከኖሩትም ይመክራሉ። አብሮነታቸው ፣ አይዞህ ባይነታቸው ልብን ይደግፋል። በመከራ ቀን የሚገኙ ጨዋ አስተዳደግ ያላቸው፣ የታረሙ  ሰዎች ናቸው ።  በመልካም ቀን ሁሉ ይገኛል፣  በክፉ ቀን አለሁ የሚሉ ሰዎች ክርስቶስን በምድር ላይ የሚያሳዩን ናቸው።

መከረኞች በመከራቸው ቀን መልካሞችን አያገኙም። የወደቀ ዛፍ ምሳር ይበዛበታል እንዲሉ የሚፈርድባቸው ፣ በቁስል ላይ ጥዝጣዜ የሚያወርድባቸው ክፉ ሰው ይገጥማቸዋል። እግዚአብሔር ግን በመከራ ቀን መልካም ነው። ብቻችንን አይተወንም፣ እሰይ ተቀጡ አይለንም። በብሉይም በሐዲስም ያለው አገልግሎት ተመሳሳይነት አለው። ከመከራ በፊት የማስጠንቀቅ፣ መከራ ሲመጣ የማጽናናት ፣ ከመከራ በኋላ የማበረታታት አገልግሎት ይደረጋል:: እግዚአብሔር በመከራ ዘመን አጽናኝ አገልጋዮችን ይልክልናል። እነ ኤርምያስ፣ እነ ሕዝቅኤል ፣ እነ ዳንኤል የማጽናናት አገልግሎት ሲያከናውኑ ነበር። እግዚአብሔር ያጽናናል፣ የኀዘን ማቅን እየቀደደ የደስታ መጎናጸፊያን ይደርባል።

"እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤" እግዚአብሔር ይህን ቃል የተናገረው በነቢዩ በናሆም በኩል ነው። ናሆም ማለት የስሙ ትርጓሜ መጽናናት ማለት ነው። ይህ መልእክት የተላለፈው ከእስራኤል ውጭ ላሉት ለነነዌ ሕዝቦች ነው ። በዮናስ አገልግሎት ንስሐ የገባችው ነነዌ መልሳ በኃጢአት ጭቃ ላይ እየተንከባለለች ነበር። በዚህ ጊዜ ዳግመኛ ነቢዩ ናሆም ተላከ። የሚመጣውን ፍርድ  አመለከተ ። አሁንም በፍርዱ ውስጥ ምሕረት አለውና  ወደ እርሱ ቢመጡ እንደሚቀበላቸው ተናገረ። ምክንያቱም እግዚአብሔር መልካም ነውና።

መልካም ማለት ሁልጊዜ በጎ የሚያስብ ፣ በሌለንበት እንኳ ስለ እኛ ጥሩ የሚናገር፣ ብንራቆት የሚሸፍነን ፣ ብንወድቅ የሚያነሣን፣ የመጽናናት ቃል ለእኛ ያለው፣ በክፉ ቀን የማይከፋብን፣ በትላንቱ የማይለካን፣ ተስፋ የሚሰጠን፣ ዝቅ ብሎ ከውድቀት የሚያነሣን ፣  እጆቹን ለምሕረት የዘረጋልን፣ ቆርሶ የሚያጎርሰን፣ ቀዶ የሚያለብሰን ነው ። የሰው መለኪያው ክፉ  ቀን ነው ። እግዚአብሔር በክፉ ቀን የሚገኝ አምላክ ነው። መልካምነቱን ጊዜ አያሸንፈውም። መልካምነቱም የባሕርይ ገንዘቡ ነው። ከመፍረድ ማዳን የሚወድ ነው። አይታዘበንም፣ ተስፋ ያደርገናል። በእኛም ደስ ይለዋል ።

መከራ አሳዳጅ ነው። በመከራ ውስጥ ያለ ሰው ሰማይና ምድር አልደብቅህ የሚሉት ተንከራታች ነው ። ተናግሮ አይረካም፣ ሄዶ አያርፍም። መፍትሔ አለ በተባለ ስፍራ ፊት ለፊት ቆሞ ወረፋ የሚጠብቅ ነው። ሌሊት እንቅልፍ፣ ቀን ዕረፍት የለውም። ሕሊና ይከሰዋል፣ ወዳጅ ይፈርድበታል። ያጽናናቸው ሰዎች ያቆስሉታል። እግዚአብሔር ግን በመከራ ቀን መሸሸጊያ ነው ። ይደብቃል፣ ይሰውራል፣ ገዳዩን ያሳልፋል። እስራኤልን በቤት ሸሽጎ ቀሳፊውን መልአክ አሳለፈላቸው። የእግዚአብሔር ምሽግነት አይደፈርም። አምባው አይፈርስም። መሸሸጊያ ዋሻ፣ ለጠላት አሳልፎ የማይሰጥ፣ መማጸኛ ከተማ ፣ ከሞት ማምለጫ እግዚአብሔር ነው። ይህን መጽናናት የላከው ለነነዌ ሰዎች ነው። ለሁሉ ቃል ያለው አምላክ ስሙ የተመሰገነ ይሁን !

"የሚታመኑትንም ያውቃል" ይላል። በመከራ ቀን ብዙ ሙከራዎች አሉ። የምናውቃቸው ሰዎች፣ ስልክ ቁጥሮች፣ ባለ ሥልጣናት ... ይሞከራሉ። አንዳቸውም አለሁ አይሉም። ያላስቀደምነው እግዚአብሔር ግን ቀድሞ ይደርስልናል። በመከራ ዘመን በእግዚአብሔር መታመን ይገባል። ተራራውን ሳይሆን በተራራው ራስ ላይ የነገሠውን አምላክ ማሰብ ልብን ያበረታል። እግዚአብሔር እነማን እንደሚታመኑት የሚፈትነው በመከራ ቀን ነው፡፡ ለጥቂት ጊዜ ብፈተንም አምላኬ ድል ይሰጠኛል። ወደ እርሱ ባለቅስ መልስ ይሆነኛል፡ በሱባዔ ባስሰው ይገኝልኛል፣ ብጠራው አቤት ይለኛል ብለው የሚታመኑበትን ያውቃል።

መከራ ዝቅ ሊያደርጋችሁ ፣ ወዳጅ ሊያሳጣችሁ ቆርጦ ቢነሣ እግዚአብሔር መልካም ነው። በጥይት እሩምታ፣ በገዳይ ማሳደድ ውስጥ ክፍት የነበረው የወዳጅ በር ቢዘጋባችሁ እግዚአብሔር መሸሸጊያ ነው። በእርሱ ለሚታመኑት ዕውቅናና ድል ይሰጣል። እንደ ነነዌ የወደቃችሁ ብትሆኑ እግዚአብሔር ለእናንተ ቃል አለውና በርቱ ! ቀኑ ጎርፍ ቢሆንባችሁ ከብርሃን ፈጥኖ ሊያድናችሁ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ነው። የተመሰቃቀለ የመሰላችሁን ነገር ባለሙያው ጌታ ያስተካክለዋል። እሾሁን ነቅሎ ዕረፍት ይሰጣችኋል።

ምስጋና ለአንድ አምላክ ለእግዚአብሔር ይሁን!

የአባቶች ምክር

06 Dec, 03:14


የእግዚአብሔር ፍቅር በልብህ ውስጥ ጠልቆ ከገባ ድካምህ ይጠፋል ።

ከእግዚአብሔርና ከትእዛዛቱ የበለጠ ኃጢአትን የምትወድ ከሆነ ደካማ ትሆናለህ ። ነገር ግን ፍቅሩ ወደ ልብህ ከገባ በውስጥህ ያለውን የኃጢአት ፍቅር አውጥቶ ይጥለዋል ። ስለሆነም ማንኛውንም ዓይነት ፈተና ለመቃወም ብርቱ ትሆናለህ ።

"ንስሓ ማለት ፍላጎትን በፍላጎት መቀየር ማለት ነው ።" ይህ ማለት የእግዚአብሔር ፍቅር የአለምን ፍቅር ይተካል ማለት ነው ። ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር የሚመሩህን ማንኛውም አይነት መንፈሳዊ መንገዶች ሁሉ ተከተል ። ከዚህ በተጨማሪ እግዚአብሔርን ከሚወዱት ጋር ተባበር ! እርሱን ስለ ወደዱት ሰዎች የተጻፈውንም አንብብ ! በመጨረሻም ምሳሌያቸውን ተከተል ።

አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

የአባቶች ምክር

05 Dec, 17:00


"You have one soul; if you gain it, you have gained everything, if you lose it, you have lost everything"

+ Pope Shenouda +


"አንድ ነፍስ አለህ ፤ ካገኘኸው ሁሉንም አተረፍክ ፣ ካጣኸው ሁሉንም አጥተሃል"

+ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሽኖዳ

የአባቶች ምክር

04 Dec, 18:41


ስለዚህ እንደ ቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 10፥12

የአባቶች ምክር

04 Dec, 04:46


ስለ መተላለፋችን ምንም ዓይነት ቅጣት የማንቀበል ብንሆን ኖሮ እግዚአብሔር ኅሊናን የሚያህል ፈራጅ ዳኛ በውስጣችን አይፈጥርም ነበር፡፡”

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
🌿 @Father_advice🌿 

የአባቶች ምክር

03 Dec, 11:02


__ ምን ያህል ድሆች ነን!?_

አንድ ባለጸጋ አባት ልጁ ድሆች ምን የመሰለ ኑሮ ይኖሩ እንደሁ ያውቅ ዘንድ ወደ ድሀው ገበሬ ሰፈር ወሰደው፡፡ በአንድ የድሃ ገበሬ ቤትም አንድ ቀንን አሳለፈው ወደቤታቸው ተመለሱ፡፡ ወደ  ቤታቸው  እየተመለሱ በመንገድ ላይ ሳሉም አባት ልጁን ምን ያህል ድሃ እንደሆኑና በድህነት እንደሚኖሩ አየህ አደል!? ምን ተማርክ? ሲል ጠየቀው፡፡
ልጅ ያየውንና የተማረውን እንዲ ሲል ገለጸው፡፡ “እኛ እንድ ውሻ አለን እነሱ ግን አራት ውሾች አሏቸው፤ እኛ የታጠረ የመዋኛ ገንዳ አለን እንሱ ግን ወንዞችና ሐይቆች አሏቸው፤ እኛ ማታ ማታ የምንጠቀምበት አምፖል አለን እነሱ ግን ሰማይ ሙሉ ከዋከብት አሏቸው፤ እኛ ምግብ ገዝተን እናገኛለን እንሱ ግን ከማሳቸው ያበቅላሉ፤ እኛ እራሳችንን ለመከላከል አጥር ሰርተናል እነሱ ግን አጥር ሳይሆን  ወዳጆችና ጓደኞች አሏቸው፤እኛ ኢንሳይክሎፒዲያ አለን እነሱ ግን  መጽሐፍ ቅዱስ አላቸው፡፡ እናም አባየ ከኛ በጣም የላቁ ባለጸጎች ናቸው፡፡ እኛ ምን ያህል ድሀዎች እንደሆንን ስላሳየኸኝ አመሰግናለሁ” አለው ይባላል፡፡

ባለጸጎች እንድንሆን የሚያደርገን የሰበሰብነው ቁሳቁስ አይደለም የሚለውን መልዕክት ይነግረናል፡፡ በመንፈስ ድሃ ሁኖ ቁስን ቢሰበስቡት ከሸክም ውጭ ምን ፋይዳ አለውና፡፡ ገንዘብ ብቻውን ባለጸጋ አያደርግንም፡፡  በገንዘቡ አማካኝነት የምንፈጥረው እሴት ጭምር እንጅ፡፡ ስለዚህ በቁሶች የተዋጥን ሰዎች ከሌሎች ጋር ስንኖር ምን አትርፎልናል!? እያለንስ ምን ያህል ድሆች ሁነናል!? እሚለውን እንድናስብ ያስታውሰናል፡፡


"ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም የምትል ስለ ሆንህ፥ ጐስቋላና ምስኪንም ድሀም ዕውርም የተራቆትህም መሆንህን ስለማታውቅ፥ . . . ወርቅ፥ . . . ነጭ ልብስን፥ እንድታይም ዓይኖችህን
የምትኳለውን ኵል ከእኔ ትገዛ ዘንድ እመክርሃለሁ።"

ራእይ 3፥17-18
“እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ፤ ማንም ድምፄን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ፥ ወደ እርሱ እገባለሁ ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል።”
  — ራእይ 3፥20
  @Father_advice
 

የአባቶች ምክር

03 Dec, 09:53


ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ በለስን የቆረጠው ከአምላኩ ጋር የነበረውን ንግግር (ጸሎቱን) በማቋረጡ ነው። ይኸውም አዳምን ጠርቶ "ወዴት ነህ?" ባለው በፈላጊው ድምጽ ተረጋግጧል።

©ዲያቆን አቤል ካሳሁን 👉 https://t.me/Dnabel/1539
🌿 @Father_advice🌿 

የአባቶች ምክር

02 Dec, 13:38


በሕይወት ውስጥ መጀመሪያ ከፊት የሚመጡት ሰዎች "ሔዋንህ" ወይም "አዳምሽ" ላይሆኑ ይችላሉ።
ልክ አዳም ከተፈጠረ በኋላ መጀመሪያ በእርሱ ፊት እንስሳትን እንዳገኘ እና ለእነርሱም የሚገባቸውን ስም እየሰጠ እንዳሰናበታቸው፣ አንተም አንዳንዴ በኑሮህ ቀድመህ የምታገኛቸው አካላት "ጎረቤት፣ የሥራ ባልደረባ፣ ጓደኛ" እያልክ ስም የምታወጣላቸው ብቻ ይሆናሉ። ለምን? "እንደ አንተ ያሉ (የሚመቹ) ረዳቶች" አይደሉማ። አዳም ለእንስሳት፣ ለሰማይ ወፎችና ለምድር አራዊት ሁሉ ስም ካወጣላቸው በኋላ መጽሐፉ "ለአዳም እንደ እርሱ ያለ ረዳት አልተገኘለትም ነበር" ይላል።(ዘፍ 2፥20)

አዳም እንደ እርሱ ያለ ረዳት ከእንስሳቱ መካከል ፈልጎ በማጣቱ "በቃ የምን መኩራት ነው? ያሉት እነዚህ ስለሆኑ እኔን ባትመስል እንኳ ትንሽ ለእኔ የቀረበችውን ብመርጥ ይሻላል" አላለም።  ከሌሎች ይልቅ በአካላዊ ቁመና ለእርሱ የምትቀርበውን ትልቅ ጦጣ (Chimpanzee) መርጦም ወደ ፈጣሪው በመውሰድ "እባክህ ጌታዬ፣ ለአንተ የሚሳንህ የለምና ትንሽ ጸጉሯን ብትቀንስ፣ ጅሯቷን ብታጠፋ እና ፊቷ አካባቢ ማስተካከያ ብታደርግላት እንደ እኔ ያለ ረዳት ትሆናለች" ብሎ ሲማጸን አናገኝም። ይህን ቢያደርግ ኖሮ አሁን የአዳምን ታሪክ የምናነብ ሰዎች ሁሉ በችኮላው እየተገረምን እንስቅበት ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ከጥቂት ቀን በኋላ አጥንቷ ከአጥንቱ፣ ሥጋዋ ከሥጋው የተፈጠረ ሔዋን የተባለች እጅግ ውብ ሚስት እንደሰጠው ስለምናውቅ። 

ከአንተ ጋር በሃይማኖት፣ በአመለካከትና ይህን በመሳሰሉት ነገሮች ጨርሳ ልትገጥም የማትችል የማትመችህን ረዳት "ለአንተ ምን ይሳንሃል? አስተካክልልኝ" እያልክ ለምን ትታገላለህ። በፍጹም ስለማይሆንሽ ሰው ለምን የmodification ጥያቄ ታቀርቢያለሽ? ጥቂት ጊዜ ከታገስህ እግዚአብሔር ለአንተ የምትመችህን (compatible) ረዳት ያመጣልሃል። አሁን ግን ፊት ለፊት ያገኘሃት ጥሩ የሥራ ባልደረባ ወይም ጓደኛ እንጂ የምትመች ረዳትህ አይደለችም።

በሕይወት ውስጥ ቀድሞ የመጣ ሁሉ ባል ወይም ሚስት አይሆንም። መጽሐፍ ቅዱስም "ቢቻላችሁስ... ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ" ይላል እንጂ "ከሁሉ ጋር ተጋቡ" አላለንም።(ሮሜ 12፥18)
©ዲያቆን አቤል ካሳሁን
የመ/ር ዲ/ን አቤል ካሳሁንን ቻናል ብትቀላቀሉ ታተርፋላችሁ!
👉 https://t.me/Dnabel/1354
       join👇
🌿
@Father_advice🌿 

የአባቶች ምክር

02 Dec, 04:55


👬 ሁለቱ ጓዋደኛሞች👬

ሁለት የሚዋደዱ ጓደኛሞች በረሃ ውስጥ እየተጓዙ እያሉ ድንገት አለመግባባት ተፈጠረና አንደኛው አንደኛውን በጥፊ👋 ይመታዋል፡

የተመታው ጥፊው ቢያመውም ምንም ሳይናገር ዝም አለና አሸዋው ላይ  ዛሬ የምወደው ጓደኛየ በጥፊ መታኝ ብሎ ፃፈ፡

ከዛም እየተጓዙ እያሉ ትልቅ ባህር ያለበት ወንዝ ያገኙና መታጠብ ፈልገው ይገባሉ እየዋኙ እያሉ ያ በጥፊ የተመታው ልጅ ይሰምጣል በዚህ ስዓት ጓደኛው እንደምንም ብሎ ሂወቱን ያተርፈዋል፡

ከሞት የተረፈው ልጅ ቋጥኝ ድንጋይ ፈልጎ እድንጋዩ ላይ እየፈለፈለ ዛሬ የምወደው ጓደኛየ ሂወቴን አተረፈኝ ብሎ ፃፈ፡

ጓደኛውም ገርሞት ቅድም በጥፊ ስመታህ አሸዋ ላይ ፃፍክ አሁን ከሞት ሳተርፍህ ደግሞ እድንጋይ ላይ ለምን እንደዚህ አደረክ አለው...

ጓደኛውም እንዲህ አለው የምንወዳቸው ሰዎች ሲበድሉን በደላችንን የይቅርታ እና የምህረት ንፋስ እንዲያጠፋው አሸዋ ላይ መፃፍ አለብን ጡሩ ነገር ሲያደርጉልን ግን ውለታቸውን እንዳንረሳ ሁሌም እንድናስታውሰው እድንጋይ ላይ መፃፍ አለብን አለው።

መልካም ቀን

የአባቶች ምክር

01 Dec, 17:41


ፀሎት! (አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ)
🌿 @Father_advice🌿 
                                 ♡ ㅤ⌲       
                                 ˡᶦᵏᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

01 Dec, 17:23


"ኑ ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ"
(ብፁእ አቡነ ሺኖዳ)

ኑ ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ ፤ ኑ በፀሎት ወደአምላክ ቅረቡ ፤ በፀሎት ማለት እንዴትነው?
ይህስ የልባችሁን ምስጢር ሁሉ ሳትደብቁ እርሱ እግዚአብሄር
እንደሚያስፈልጋችሁ መናገር ማለት ነው ፤ እንዲህም በሉ ፦ “ጌታ ሆይ ወደ አንተ መምጣት እፈልጋለሁ ፡ ጌታ ሆይ ካንተ ተለይቼ እኔ ምንም ነኝ ፡ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ህይወቴን አጣሁ ፤ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ደስታየን ሁሉ አጣሁ ጌታ ሆይ እኔ አንተን ያጣሁ እለት ህይወቴ ትርጉም አልባ ሆነ ፤ ጌታ ሆይ እኔ አንተን
ያጣሁ እለት ህይወቴ ጣእም አልባ ሆነ” በሉ ፤ ዳግምም ከእግዚአብሄር እግር ስር ተደፍታችሁ እንዲህ በሉት፦ “ አምላኬ ሆይ ፦ ወደ አንተ መመለስ እፈልጋለሁ ፤ ነገር
ግን ጠላቶቼ ከእኔ በእጅጉ የሚበልጡ ናቸው ፤ ነፍሴንም አምላክሽ አያድኑሽም የሚሏት ብዙ ናቸው” ፡፡

ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ ፤ “ ጌታ ሆይ ታደገኝ ወደ አንተ የምመለስበትን መንገድ ምራኝ” በሉት ፤ ለአምላካችሁ ንገሩት ፦
ካንተ ከተለየሁ ወዲህ አቅሜ ሁሉ ተዳክሟልና ጌታ ሆይ ልዩ ሃይልህን ላክልኝ ፡ ወዳንተ የምመለስበትን ልዩ ርዳታህን ስጠኝ ፤” በማለት፡፡ ብዙ ሰወች በመደጋገም “ወደ
እግዚአብሄር የምመለሰው እንዴት ነው ?” ይላሉ፡፡ ከእግዚአብሄር እግር በታች
ራሳችሁን ጣሉ ፡ እንዲህም በሉት ፦ “ ጌታ ሆይ ሳትባርከኝ አልለቅህም ፡ ወዳንተ አቅርበኝ ፡ ከልጆችህ እንደአንዱ አድርገኝ ፡ ሃጢአቴን ብቻ ይቅር እንድትልልኝ አልሻም ፡
ይልቁንም ከሃጢአት ፍቅር ትለየኝ ዘንድ ጭምር እንጂ
፡”በሉት ፦ ዳግምም “ ጌታ ሆይ
የሃጢአት ፍቅር ልቤን ተቆጣጥሮታልና ይህን ካላስወገድኩ
ወዳንተ መቅረብ አይቻለኝም ፡ ጌታ ሆይ የሃጢአትን ፍቅር ከልቤ ላይ ንቀል ፡” በሉት ዳግምም እንዲህ
በሉት ፦ ”ጌታ ሆይ ከሃጢአቴ ነፅቼ ወዳንተ መምጣት እንደምን ይቻለኛል? ይልቁንስ መጀመሪያ አንተ ናልኝ ሃጢአቴንም ደምስስ
እንጂ “
እንዲህም በሉት ፦ “ በራሴማ
ሃጢአትን ማስወገድ ብችል ወዳንተ መቼ መመለስ ያቅተኝ ነበር? እኔ ግን አንተ ከሃጢአቴ እንድታርቀኝ እወዳለሁ ፡ ጌታ ሆይ ፦ ሃይልህን እንድትሰጠኝ እፈልጋለሁ”በሉት፡፡
እመኑኝ የምወዳችሁ ልጆቼ ፦ ትክክለኛዋን ፀሎት ያወቃት እርሱ ትክክለኛዋንም ንስሃን
የሚያውቅ እርሱ ነው ፤ ማር ይስሃቅ እንደተናገረው “ንስሃ ከፀሎት ውጭ እንደሚገኝ የሚያስብ ሰው እርሱ በዲያቢሎስ የተታለለ ነው” ምክንያቱም በፀሎት ወደ
እግዚአብሄር የምትመለሱበትን ሃይልን ታገኛላችሁና፡፡ ስለሆነም ከየትኛውም ስራ ይልቅ
ራሳችሁን ለፀሎት አስገድዱ ፤ ምክንያቱም በፀሎት አማካኝነት በእናንተና
በእግዚአብሄር መካከል ያለውን ግድግዳ አስወግዳችሁ እንደገና ወደእርሱ ትመለሱ
ዘንድ ይቻላችኅልና ፤ በጣም ብዙ ሰወች ከፀሎት ይልቅ ለአገልግሎት መትጋታቸው የሚገርም ነው ወይንም ከፀሎት ይልቅ በንባብ የሚተጉትም እንደዚያው ወይንም ከፀሎት ይልቅ በተመስጦ የሚተጉትም እንደዚያው ወይንም ከፀሎት ይልቅ በመንፈሳዊ ስብሰባወች ለመታደም የሚተጉትም እንደዚያው ፤ ለዚህ እኮ ነው ከእግዚአብሄር ጋር
ባላቸው ግንኙነት የማይሳካላቸው ፤ ይፀልያሉ ያነባሉ ደግሞም ስብሰባወችን ይታደማሉ
በዚህ ሁሉ ሰአት ከእግዚአብሄር ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም ፤ ምንም አይነት
ግንኙነት ፡፡
ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ ፤ ወደእግዚአብሄር ተመለሱና ከእርሱ ውሰዱ  ስለዚህ ልጆቼ  ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ"

© አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

የአባቶች ምክር

01 Dec, 15:59


ፊልጵስዩስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር፤
⁴ እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ።
በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።
⁶ እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥
ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥
⁸ በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ።
⁹ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤
¹⁰ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥
¹¹ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።
¹² ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ እንደ ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ፤

የአባቶች ምክር

01 Dec, 12:51


የተወለድነው በሌሎች ሰዎች እርዳታ ነው፡፡
🔷 ስማችንን የተቀበልነው ሌሎች ሰዎች ባወጡልን መሰረት ነው፡፡
የገቢ ምንጫችን የሚመጣው ከሌሎች ሰዎች ነው፡፡
🔷ክብርና እውቅና የሚሰጡን ሌሎች ሰዎች ናቸው፡፡
ገላችንን ለመጀመሪያ ጊዜ ያጠቡን ሌሎች ሰዎች ናቸው፣ ለመጨረሻ ጊዜ የሚያጥቡንም ሌሎች ሰዎች ናቸው፡፡
🔷 ከዚህ አለም ስንሰናበት ቤታችንና ንብረታችን በሌሎች ሰዎች ይወሰዳል፡፡
እጃችንን ይዘው በመደገፍ መራመድ ያስለመዱን ሌሎች ሰዎች ናቸው፣ በመጨረሻም እጃችንን ይዘው በመደገፍ የሚያራምዱን ሌሎች ሰዎች ናቸው፡፡
🔷 በመወለዳችን ምክንያት በደስታ የደገሱና የበሉት ሌሎች ሰዎች፣ ስንሞትም በኃዘን የሚደግሱና የቀብር ስርአታችን የሚከናወነው በሌሎች ሰዎች ነው፡፡

🔑ይህ ሁሉ እውነታ እያለ “ነኝ” እና “አለኝ” በምንለው ነገር የምንመካበት ጉዳይ አይገባኝም፡፡ እስቲ ያወሳሰብናትን ሕይወትን ቀለል እናድርጋትና ለመከባበርና ለመዋደድ ቅድሚያን በመስጠት እንኑር፡፡
©socal media

የአባቶች ምክር

30 Nov, 17:56


"ለእግዚአብሔር የችግርህን ታላቅነት አትንገረው፤ ለችግርህ ግን የእግዚአብሔርን ታለቅነት ንገረው።"

join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

30 Nov, 12:37


ሙሴ የያዘውን በትር የግብፅ ጠንቋዮች ይዘውት ነበር::ሁለቱም እባብ ሆነ ልዩነቱን ግን የሙሴ በትር የአስማተኞቹን ዕባብ ውጣ አሳየች:: "ያም በትር ነው ይሄም በትር ነው" ካልከኝ ፈርዖን ይታዘብሃል:: ጌታ የለበሰውም ቀሚስ ነው ፤ ሕዝቡ የለበሱትም ቀሚስ ነው:: በሕዝብ መካከል እንደ እባብ እየተሳበች በብዙ ቀሚሶች እየተዳሰሰች መጥታ የመሲሑን ቀሚስ ስትነካ ደምዋ ቀጥ ላለላት ሴት "ቀሚስ ቀሚስ ነው" በላትና ትመልስልህ::

አዎ ዳጎንም ታቦተ ጽዮንም የተቀረጸ ምስል ናቸው:: ነገር ግን ታቦት የእግዚአብሔር ዙፋን ሲሆን ጣዖት ግን በእሳታዊ ዙፋኑ ፊት እንድ ማገዶ የሚሰባበር እንጨት ነው፡፡ ታቦትን ከጣዖት ጋር ከመመደብ ይሠውረን:: አንድም ታቦት ሰውነታችንን ከዳጎን ኃጢአት ጋር ከማስቀመጥ ይሠውረን::

‘ብርሃን ከጨለማ ምን ኅብረት አለው? ክርስቶስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስም ከጣዖት ጋር ምን መጋጠም አለው’ 2ቆሮ. 6፡14-16

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ኅዳር 21 2017 ዓ.ም.

የአባቶች ምክር

30 Nov, 12:37


+ ታቦትን ከጣዖት ጋር አታስቀምጡ +

እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ አለው ፦ በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ። አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም››(ዘጸ. 20፡4)

ይህንን ትእዛዝ በእሳት ቀለም የጻፈበት ድንጋይ ሳይደርቅ እግዚአብሔር ለሙሴ ሌላ ትእዛዝ አዘዘው ፦ ‘ሁለት ኪሩቤል ከተቀጠቀጠ ወርቅ ሥራ’ (ዘጸ. 25፡18) እግዚአብሔር ለሙሴ ምን እያለው ነው? ‘የተቀረጸ ምስል ለአንተ አታድርግ’ ካለው መልሶ የሁለት ኪሩቤል ‘የተቀረጸ ምስል ማሠራቱ ለምንድን ነው?’ መርቅያን የተባለው ጸረ ብሉይ ኪዳን የነበረ ውጉዝ ይህንን ተቃርኖ በመጥቀስ የብሉይ ኪዳኑ እግዚአብሔርን ክብር ይግባውና ‘በሃሳቡ እንደሚወላውል’ አድርጎ ሐሰትን ተናግሯል፡፡ እውን እግዚአብሔር ‘የተቀረጸ ምስል አታድርግ’ ያለውን የራሱን ቃል ‘ታቦት ሥራ ፣ ኪሩቤልን ቅረጽ’ ሲል እየጣሰው ይሆን?

ታሪኩ በዚህ አላበቃም ፤ እስራኤላውያን ‘የወርቅ ጥጃ ምስል’ ሰርተው ሲያመልኩ እግዚአብሔር አይቶ ቁጣው ነደደ ፤ ቀሠፋቸውም፡፡ (ዘጸ. 32፡4) ቆይቶ ደግሞ ‘እግዚአብሔርም ሙሴን፦ እባብን ሠርተህ በዓላማ ላይ ስቀል የተነደፈውም ሁሉ ሲያያት በሕይወት ይኖራል አለው’ (ዘኁ. 21፡8) ነገሩ እንዴት ነው? ከወርቅ ጥጃ መሥራት ጥፋት ከሆነ ከነሐስ እባብ መሥራት እንዴት ልክ ሊሆን ይችላል?

ሳዊሮስ ዘገብሎን የእባቡን ምስል አስመልክቶ ሙሴን እንዲህ ሲል ይጠይቀዋል፡፡ ‘የተረገመ ሥዕል በመከራ ለተናወጠ ሕዝብ እንዴት ድኅነትን ሊያመጣ ይችላል? የተነደፋችሁ ሁላችሁ አንጋጥጣችሁ ወደ ሰማይ ወደ እግዝዚአብሔር ተመልከቱ ወይም ወደ መገናኛው ድንኳን ተመልከቱና ትድናላችሁ’ ቢል አይሻለውም ነበር? ከምድርም ፣ ከሰማይም የተቀረጸ ምስል አታድርግ ያለ ሙሴ ስለምን ይህንን አደረገ? እጅግ የታመንከው የእግዚአብሔር አገልጋይ ሙሴ ሆይ የከለከልከውን ነገር ራስህ እየሠራህ ነውን? ‘የተቀረጸ ነገር አታድርግ’ ያልህ አንተ ፣ የጥጃ ምስል የሰባበርህ አንተ የናስ እባብን እንዴት ሠራህ? ያውም በምሥጢር ሳይሆን በገሐድ ነበረ!’ (Severian Bishop of Gabala , Homily on the Serpent pg 56)

ነገሩ ወዲህ ነው ፤ በመጀመሪያ ወደ ማብራሪያው ሳንሔድ ‘የተቀረጸ ምስል ለአንተ አታድርግ’ የሚለው ትእዛዝ ራሱ የተጻፈው በተቀረጸ ምስል ላይ መሆኑን በማስተዋል እንጀምር፡፡ ትእዛዛቱ የተጻፉት ከድንጋይ በተቀረጸ ጽላት ላይ ሲሆን የሚቀመጡት ደግሞ ከግራር እንጨት ተሠርቶ በወርቅ በተለበጠና ከወርቅ ተቀጥቅጠው የተሠሩ ኪሩቤል ያሉበት ታቦት ውስጥ ነበር፡፡ ስለዚህ የተቀረጸ ምስል ለአንተ አታድርግ የሚለውን ቃል እያነበብን ያለነው ከተቀረጸ ምስል ውስጥ ባገኘው በተቀረጸ ሰሌዳ ላይ የመሆኑን ምፀት (irony) እንደ ዋዛ አናልፈውም፡፡ ቃሉ የተጻፈበት ፊደልም ቢሆን ሌላው በጣት የተቀረጸ ነገር መሆኑም የሚዘነጋ ነገር አይደለም፡፡

እግዚአብሔር ‘የተቀረጽ ምስል ለአንተ አታድርግ’ ብሎ ያዘዘውን ትእዛዝ ግን ብዙዎች ከምስሉ ጀምረው አነበቡት እንጂ ቃሉ የሚጀምረው ‘ከእኔ በቀር ሌላ አማልክት አይሁኑልህ’ በሚል ነው፡፡ ይህም ማለት ‘ሌላ አምላክ አለ ብለህ አትመን ፤ ይህንን አምነህም የተቀረጸ ምስል ለአንተ አታድርግ ፣ አትስገድላቸው አታምልካቸውም’ ብሎ ከጣዖት አምልኮ እንድንርቅ ያዘዘው ትእዛዝ ነው፡፡ በራሱ ፈቃድ እንዲሠሩ ያዘዛቸው ሁለቱ ኪሩቤልም ‘በእግዚአብሔር ሥዕል የተሣሉ’ (ይሣሉ ብሎ ያሣላቸው) ሲሆኑ አምላክ ናቸው ተብለው ሊመለኩ አይደለምና የላይኛው ትእዛዝ እነርሱን አይመለከትም፡፡ የናሱን እባብም ኃይሉን ሊገልጥበት ወድዶ አሠራው እንጂ ይመለክ ብሎ አላሠራውም፡፡ በኋላ ዘመን የናሱን እባብ እንደ አምላክ ቆጥረው ከሐውልቶች መካከል አቁመው ያመለኩትን ደግሞ ራሱ እንዲሰባበርባቸው አድርጓል፡፡ (2 ነገሥ. 18፡4)

ይህ ሁሉ የሚያሳየን የተቀረጸ ምስል ሁሉ ጣዖት እንዳልሆነ ፤ በተመሳሳይ እንጨት ፣ በተመሳሳይ ወርቅ ቢሠራ እንኳን የተሠራበት ዓላማ እንደሚለየው ፣ እግዚአብሔርን ለማምለክ የተሠራ ታቦት እግዚአብሔርን ለመተካት ከተሠራ ጣዖት ጋር ልዩነት እንዳለው ነው፡፡

የታቦትንና የጣዖትን ልዩነት በተመለከተ የፍልስጤም ሰዎችን ያህል ግን እውቀት ያለው ያለ አይመስልም፡፡ ፍዳቸውን አይተው ታቦትን ከጣዖት የለዩ እነሱ ናቸው፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው ፦

በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በእግዚአብሔር ታቦት ፊት ብዙዎች በግንባራቸው ተደፍተው ስለመስገዳቸውተጽፎአል:: መስፍኑ ኢያሱ በእግዚአብሔር ታቦት ፊትሰግዶአል:: የእስራኤል ሽማግሌዎችም ሙሉ ቀን በታቦቱፊት ወድቀው ምሕረት ለምነዋል:: (ኢያ. 7:6) በታቦት ፊት ከሰገዱ ሁሉ ግን እጅግ በጣም የሚያስደንቀውከፍልስጤማውያን ዘንድ የታየው ሰጋጅ ብቻ ነው::

ዳጎን ይባላል:: ዳጎን ሰው አይደለም:: ደህና አናጢ እጅ የገባ የፍልስጤማውያን ዛፍ ነው፡፡ ፍልስጤማውያን ከእንጨት ጠርበው ያቆሙት ሰው ሠራሽ አምላክ ነው::አይሰማም አይለማም:: አይበላም አይጠጣም::። ለክብሩ መቅደስ ተሠርቶለት ሰዎች በስሙ እየተሰየሙለት (አብደናጎ ገብረ ዳጎን ማለት ነው እንዲል) ይኖራል::

ዳጎን ተንቀሳቅሶ ባያውቅም ታቦተ ጽዮን ተማርካ አጠገቡ ስትመጣ ግን ተንቀሳቀሰ:: ፍልስጤማውያን ዳጎንን ከታቦተ ጽዮን ጋር እኩል አድርገው አስቀመጡት::በማግሥቱ ሲመጡ ግን ሌላ ነገር ጠበቃቸው:: ‘እነሆም፥ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በምድር ላይ በግምባሩ ወድቆ ነበር ፤ ዳጎንንም አንሥተው ወደ ስፍራው መለሱት" 1ኛ ሳሙ.5:3

አይሰሜ አይለሜው ዳጎን በታሪኩ ቁምነገር ሠርቶ አያውቅም ነበር:: በታቦተ ጽዮን ፊት ሰግዶ ማደሩ ግን ብቸኛው ቁምነገሩ ነው:: ታቦትን ከጣዖት እኩል አድርገው ለሚያስቡ እና ጎን ለጎን ላስቀመጡት የአዛጦን ሰዎች"የእግዚአብሔር ታቦት ይኼ ነው እኔ ግን ጣዖት ነኝ" ብሎበተግባር አሳያቸው:: ለእርሱ ሲሰግዱ ለነበሩት ሰዎች ስግደት የሚገባው በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት እንደሆነ ሰግዶ አሳያቸው:: በእውነት ዓይን እያለው የማያየው ፣ ጆሮ እያለውየማይሰማው ጣዖት እንኩዋን የገባው እውነት ከብዙዎች ተሰውሮ ታቦትን ጣዖት ሲሉ ማየት ያሳዝናል::

"ታቦትን ጣዖት ስትሉ እኛ እንደሰማን ፍልስጤማውያን እንዳይሰሙ፣ ዳጎን እንዳይሰማችሁ” ያሰኛል:: የአዛጦን መቅደስ ታቦት ገብቶበት እንኳን አልተቀደሰም:: የእግዚአብሔር ታቦት ደግሞ ጣዖት ቤት ገብቶ አልረከሰም:: ታቦት ቢማረክ ቢሸጥ ቢለወጥ ታቦትነቱን አያስቀረውም:: እግዚአብሔርም ኃይል የለውም አይባልም:: ልብ አድርጉ ይህ ሁሉ ታሪክ የሚሆነው የእንስሳ ደም ይረጭበት በነበረው በኦሪት ታቦት ላይ ነው::የክርስቶስ ደም የሚፈስስበት ሥጋው የሚፈተትበት አልፋና ኦሜጋ የሚል ስሙ የሚጻፍበት የሐዲስ ኪዳኑ የመሠዊያ ታቦትማ ምንኛ እጥፍ ክብር ይገባው ይሆን? ዳጎን ለዚያኛው ታቦት ከወደቀ ለዚህኛው የቁርባን ጠረጴዛ እንዴት ይሰባበር ይሆን?

ታቦትን ከጣዖት አጠገብ የማስቀመጥ “ፍልስጤማዊ አባዜ” ያለበት ሰው ግን ይህን ለመረዳት ይቸገራል:: "ዳጎንም እንጨት ታቦተ ጽዮንም እንጨት" ይልሃል:: ሁለቱም እንጨት ነው ነገር ግን ታቦተ ጽዮን እግዚአብሔር ያደረባት ስትሆን ዳጎን ሰይጣን የሰፈረበት ነው:: "የአሕዛብ አማልክት ሁሉ አጋንንት ናቸውና" መዝ. 96:5

የአባቶች ምክር

30 Nov, 06:40


ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን ሶበ ተዘከርናሃ ለጽዮን 
ውስተ አፍላገ ባቢሎን  ህየ ነበርነ ወበከይነ

¹ በባቢሎን ወንዞች አጠገብ በዚያ ተቀመጥን፤ ጽዮንንም ባሰብናት ጊዜ አለቀስን።
² በአኻያ ዛፎችዋ ላይ መሰንቆቻችንን ሰቀልን።
³ የማረኩን በዚያ የዝማሬን ቃል ፈለጉብን፥ የወሰዱንም፦ የጽዮንን ዝማሬ ዘምሩልን አሉን።

መዝሙር 137
join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝


እንኳን አደረሳችሁ

የአባቶች ምክር

29 Nov, 17:34


"የተሳሳተ እምነት ይዘን መልካም ህይወትን ብንኖር ምንም ጥቅም የለውም። ልክ እንደዛውም ቀጥተኛዋን ሃይማኖት ይዘን የኀጢአት ኑሮ ብንኖር ምንም ፋይዳ የለውም። እምነት ብቻ ለመዳን በቂ አይምሰለን ንፁህ ህይወትም አስፈላጊና ወሳኝ ነው።"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

29 Nov, 16:05


“ትዕግሥተኛ ሰው ከኃያል ሰው ይሻላል፥
በመንፈሱም ላይ የሚገዛ ከተማ ከሚወስድ ይበልጣል።”
— ምሳሌ 16፥32

የአባቶች ምክር

28 Nov, 16:33


ወንድሞቼ ሆይ፡- ሃይማኖት ቀላል ቅድስና ወይም እርግማን አይደለም! ወይም ደግሞ ቀላል ትእዛዝ ወይም ክለከላ አሊያም ተራ ሕግ ወይም ጸጋ አይደለም፤በሚቻለው ሁሉ ለእግዚአብሔርና ለሰዎች የሚሆን ፍቅር እንጂ።

ከዚህ ፍቅር የሚመነጨውም ሁሉ መልካም ነገር ነው፡፡ እግዚአብሔርንና ሰዎችን የማትወዱ ከሆናችሁ የተፈለገውን ያህል ብትጸልዩ ወይም ብትጾሙ ወይም ብታነቡ ወይም በተመስጦ ብትቆዩ ወይም አሥራት ብታወጡ ወይም ብታገለግሉ ወይም ብትሰብኩ የሃይማኖት ሰዎች ልትሆኑ አትችሉም፡፡

እግዚአብሔር የሚፈልገው ፍቅርን እንጂ ቀላል ተግባራትን አይደለም፡፡ . . . እግዚአብሔር ከእናንተ የሚፈልገው እርሱ እናንተን እንደ ወደዳችሁ እናንተም እርሱን እንድትወዱት ነው፡፡

አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

             join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

28 Nov, 06:11


የክርስቲያኖች ሀይል🙏

✍️ አሁን ባለንበት ዘመን ትልቅ ኃይል አላቸው የምንላቸው ብዙ ነገሮች አሉ። እንዲሁም በጦርነት ዓለም በዋነኝነት ከሚጠቀሱት ትልቅ ኃይል መካከል Nuclear Bomb ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ ሲነግረን፦
ያዕቆብ 5
¹⁷ ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥
¹⁸ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች።


ከጸሎት ውጪ ሰማይ የሚከፍት ሰማይ የሚዘጋ ምንም ኃይል አላየንም።

ስለዚህ ከNuclear Bomb እና ከሌሎች ኃይሎች የጠነከረ ታላቅ ኃይል አለ እርሱም ጸሎት ነው!

ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤።”
— ማቴዎስ 26፥41
ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።”
  — ማቴዎስ 7፥7
አምናችሁም በጸሎት የምትለምኑትን ሁሉ ትቀበላላችሁ ።”
  — ማቴዎስ 21፥22
“ማናቸውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለሁ።”
— ዮሐንስ 14፥14

join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

27 Nov, 13:03


“መታዘዛችሁም በተፈጸመች ጊዜ
አለመታዘዝን ሁሉ ልንበቀል ተዘጋጅተናል።”
— 2ኛ ቆሮ 10፥6

በመታዘዝ አለመታዘዝን እንበቀል🙏

የአባቶች ምክር

27 Nov, 05:20


🕊 ቢቻላችሁ ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ 🕊

ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ።” ሮሜ. 12፡18 ። ሐዋርያው “ቢቻላችሁስ” አለ ። ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም መኖር ከባድ ነውና ። ቢቻለን ከሁሉም ነገድ ከሁሉም ሃይማኖት ጋር በሰላም መኖር ይገባናልምድር የሁሉም እንጂ የአንድ ሃይማኖትና የአንድ ወገን አይደለችምና ። ለሁሉም እንደ ሥራው የሚፈርድ አምላክ አለና ሳንፈራረድ ከሁሉም ጋር በሰላም መኖር መታደል ነውበዚህ ምድር ላይ ልከኛ ነዋሪ የሚባለው ከሰዎች ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያሳምር ነው ከሰዎች ጋር የዝምድና ፣ የሃይማኖት ፣ የጓደኝነት ፣ የሥራ ባልደረባነት ፣ የነጻነት ትግል ፣ የአገር ፍቅር ሊያገናኘን ይችላል ። መቼም ሃይማኖት ላለው ሰው ከዝምድና ሁሉ የሚበልጠው በክርስቶስ ያወቁት ወንድምና እኅት ነው ። ምድራዊ ዝምድና ሁሉ መቃብር ይገታዋል ። በክርስቶስ መዛመድ ግን ከሞትም ባሻገር የሚዘልቅ ነው ። በኖርኩበት ዘመን መንፈሳዊ ዝምድናን የሚያከብር ብዙ አላየሁም ። የሥጋ አባቱን ምሥጢር ደብቆ የሃይማኖት አባቱን እንከን በአደባባይ የሚያወራ ብዙ ነው ። የሥጋ ወንድሙ ቢበድለው ይቅር እያለ የሃይማኖት ወንድሙን ግን ጠልቶ የሚቀር አያሌ ነው ። የእግዚአብሔር ፈቃድ ሰው ከሰው ጋር እንዲኖር ነው ። ከሌላው ጋር ለማበር ሰው መሆን በቂ ነው ። በሽታው ሲመጣ ጥቁርና ነጩን በአንድነት ይፈጀዋል ። በአንድ ዓይነት በሽታ እየታመምን በአንድ ዓይነት ፍቅር መኖር አለመቻል ያሳዝናል  ።

join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

26 Nov, 20:03


✞ አኑሮኛል ቸርነትህ ✞

አኑሮኛል ቸርነትህ ልክ የሌለው ደግነትህ(2)
እንዳንተ አይነት ከዬት ይገኛል
ሁሉም ነገር ትዝ ይለኛል(2)

more...........

                   join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

26 Nov, 19:57


✞ አኑሮኛል ቸርነትህ ✞

አኑሮኛል ቸርነትህ ልክ የሌለው ደግነትህ(2)
እንዳንተ አይነት ከዬት ይገኛል
ሁሉም ነገር ትዝ ይለኛል(2)

        
ያቺ ፈዋሽ አዳኝ እጅህ
ዛሬም ለኔ ተሰርግታ
በሐጢያት ርቄ እንዳልጓዝ
አስረህኛል በውለታ
ደግሞስ ህይወት ምርጫ ቢሆን
ካንተ ወደማን ይኬዳል

         አባቴ ፍቅርህ እኮ
        ጌታዬ ፍቅርህ እኮ
         አለምን ያስክዳል

        
ሞቸ ነበር ተቀብሬ
ጌታ ወደ እኔ ባትመጣ
አንተ ሞቴን ባትሞትልኝ
ወዴት ነበር የእኔ እጣ
ከንቱ ነበር ማንነቴ
ተሽናፊ ለዚች ዓለም
     ግን አንተ የያዝከው
       አባቴ የያዝከው
      ይኖራል ዘላለም

              
መቅደስህን ተጠግቼ
አይቻለሁ ብዙ ነገር
በልቤ ውስጥ ያስቀመጥኩት
እንዲህ ለሰው ማይነገር
ግን የሆነው ሁሉም
ሆኖ የለም ዛሬ ያላረፈ
       የመከራው እሳት
       የፈተናው  እሳት  
      ባንተ እየታለፈ


አይጠፋኝም ያ ፈገግታ
ልጅ ብለህ ያሳየህኝ
አመፅኛ መጥፎም ሆኜ
በትክሻህ ላይ ያኖርከኝ
እንዲህም አይነት ወዳጅ አለ
እየጠሉት የሚያፈቅር

         ስሙም ኢየሱስ ነው(2)
        የፅድቃችን ሚስጥር

        
ስነፈርቅ ሳለቅስብህ እሺ
እያልከኝ ሁሉም ሆነ
ማይሆንለት ነገር የለም  
ለካስ ባንተ የታመነ
መቸኮሌ መጣደፌ
አምላኬ ሆይ በከንቱ ነው
    መፈፅሙ ላይቀር(2)
        ጌታዬ አንተ ያልከው


join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

26 Nov, 15:14


ጸሎቴን ቶሎ አይሰማኝም ያልነው አምላክ
ሀጢአት ስንሰራ ቶሎ ያልቀጣን አምላክ ነው!

                   join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

26 Nov, 06:53


ወደ ሰማይ የወጣ የወረደስ ማን ነው?
ነፋስንስ በእጁ የጨበጠ ማን ነው?
ውኃንስ በልብሱ የቋጠረ ማን ነው?
የምድርን ዳርቻ ሁሉ ያጸና ማን ነው?
ይህን ታውቅ እንደ ሆንህ፥
ስሙ ማን የልጁስ ስም ማን ነው?”
— ምሳሌ 30፥4

                   join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

 
 ✍️✍️ ✍️✍️ ✍️✍️

የአባቶች ምክር

26 Nov, 03:55


ሰው ያለው ሰው ምንኛ ሙሉ ነው!
አጥሩ በእግዚአብሄር የተሸፈነለት
ቢያወራ አዳማጭ ያለው
ቢያለቅስ እንባ አባሽ
ቢጎድል የሚሞላ
የሚልወዳጅ ማገኜት ለካ
ከእግዚአብሄር ትልቁን ስጦታ እንደ መቀበል ነወ
join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

 
 

የአባቶች ምክር

25 Nov, 04:52


#ልጄ_ሆይ፦

ሕይወት አጭር ናት!
የሁሉም ሰው ትርፍ ትዝታ መሆን ነው።


ስለዚህ፦

👉ቅናትን
👉ምቀኝነትን
👉ተንኮልን
👉ኩራትን
👉ንቀትን እና
👉ከሰዎች መቆራረጥን

አስወግድ!!

ትምህርተ_ሺኖዳ መጽሐፍ
አቡነ_ሺኖዳ_መልስ_አላቸው መጽሐፍ

join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

24 Nov, 17:42


መታመኛ አምላክ

"በአንተ ታምናለችና በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ።" ኢሳ. 26፥3

የሚታመኑ ሰዎች በማጣት ከትዳር የዘገዩ፣ ከራእይ የቀሩ፣ ከፍቅር የጎደሉ ፣ ከሥራ ዓለም የወጡ፣ ከአገልግሎት የተፈናቀሉ፣ ከጅምራቸው የተመለሱ ሰዎች እንዳሉ እንሰማለን። ስለ መከዳታቸው ሲነግሩን ስለ መክዳታቸው ግን ነግረውን አያውቁም። አንተ እኮ ልጅ ነህ ብለው  የጠዋቱን የሚያወሩን ትሞታለህና በሥርዓት ኑር ብለው ግን አያወሩንም። የሚታመን ቢገኝ ብቸኝነት ይገሠጻል፣ ሀብት ይደረጃል ፣ የአንድ አሳቢ የአንድ በሬ ሳቢ እንዲሉ አንድ ሰው ብቻውን ብዙ ነገር ማከናወን ይከብደዋል። አንድ ሰው ሁለት እጅ ቢኖረውም አንድ ነው። በአንዱ ነገር ብርቱ ቢሆን በብዙ ነገር ደካማ ነው። ታማኝ ሰው ግን በጎደለው አጥር ፣ ሙሉ ሆኖ ይቆማል። ሙሽራው ለፎቶ ብሎ ሙሽራይቷን ብድግ አድርጎ ሊያቅፋት ሲል ሱሪው ተተረተረ ፣ በጣም ደነገጠ፣ ሙሽራይት ድርቅ ብላ ቀረች፤ እርሱም የሚገባበት ጠፋው፣ በአዳራሹ ያለው ተጋባዥ የሚለው አጣ ፣ ግማሹ ሳቀ ። አንድ ሚዜ ግን ፈጠን አለና ኮቱን አወለቀ። ሙሽራውን ለመሸፈን ፈጠነ። ታማኝ ሰው ሲራቆቱ የሚሸፍን ነው።

ሰውዬው ሲራቆት የቅርብ ቢሆኑም አብረውት ደንግጠው የሚቆሙ ሰዎች አሉ። አጠገባቸው ካለው ሰው ጋር ለሐሜት የሚፈጥኑም አሉ። ለዓለም ለማሳየት ስልኩን የሚያወጣም አለ። ከዚያ መሐል አንድ ታማኝ ይገኛል። እርሱ ተራቁቶ ወዳጁን ያለብሳል። ቤተ ክርስቲያን ባሳለፈችው ታሪክ ወንድሙን የሚያጋልጥ ወንድም አልገጠማትም። እንደውም የወንድማቸውን ኃጢአት የራሳቸው አድርገው እኔ ልወቀስ ልከሰስ የሚሉ ከባቴ አበሳነትን ጉድን ሸፋኝነትን የተለማመዱ አባቶችን አፍርታለች። ስለ ራሱ ኃጢአት ኃላፊነት የሚወስድ በጠፋበት ዓለም የወንድሙን ኃጢአት የራሱ አድርጎ ወንድሙን ለንስሐ የሚያበቃ የክርስትና ታሪክ አለን። ታማኝ ሰው የወንድሙን ዕራቁትነት የሚሸፍን ነው። ዛሬ በደጉ ቀን ለክፉ ቀን ይሆነኛል ብለው የወንድማቸውን አበሳ መዝግበው የሚያስቀምጡ ምስኪኖች ሰዎች አሉ። አበሳ ያለበት በሌላው አበሳ እንዴት ፈራጅ ይሆናል?

ታማኝ ሰው ትዳሩን እስከ ሞት ድረስ በመሥዋዕትነት ያቆያል። የተደረገለትን በጎ ነገር አይረሳም። ለሰዎች ውለታ ክብር ይሰጣል። ታማኝ ሰው ያገኘ ራእዩን ያሳልጣል፤ መንገዱን ያረዝማል። በዓለም ላይ ሕዝብ በሌለበት ንጉሥ  የለም። ተመልካች ባይኖርም ሯጭ አይኖርም ነበር ። አጋዥ ከተገኘ ሥራ ይቀላል። አብሮ የሚበላ ሰው ካለ ምግብ ይሠራል፤ ይበላል። አብሮ የሚጓዝ ከተገኘ መንገድ አያደክምም።

የሚታመኑበት፣ ልብ የሚጥሉበት ፣ ለአደራ የሚበቃ፣ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው እየጠፋ ነው። ሰው ቢታጣ እግዚአብሔር አለ። በእግዚአብሔር መታመን የሰላም መሠረት ነው። በቁማቸው ጨርሰው ስሞት ልጆቼ ምን ይሆናሉ ? ብለው የሚጨነቁ ሰዎች አሉ። በእግዚአብሔር የታመኑ ግን ልጆቼ በእኔ በኩል ቢመጡም የእኔ አይደሉም ብለው ያርፋሉ። መጀመር የሚፈሩ እግዚአብሔር ያስፈጽመኛል ብለው ታምነው ይነሣሉ ። ሰው በሌለበት ማገልገል ከባድ ነው፣ ሕዝቡ አይሰማም ብለው የሚፈሩ በእግዚአብሔር ታምነው የቃሉን ዘር ይዘራሉ።

በእግዚአብሔር የሚደገፉ አይናወጡም። ወንበር ላይ ስንቀመጥ፣ ምሰሶ ስንደገፍ አይጥለንም ብለን ታመነን ነው። እግዚአብሔርን የወንበርና የምሰሶ ያህል መታመን ብዙ ጊዜ ያቅተናል። አይጥለኝም አይተወኝም ብሎ በእግዚአብሔር መተማመን የልብን ሰላም ይጠብቃል። እርሱን መደገፍም ማዕበላዊ ቀኖችን ያሻግራል።

ውድ ወዳጆች ሰላም የመታመን ውጤት ነው! በእግዚአብሔር የታመኑ ልባቸው በማዕበል ከመናወጥ ይድናል። ሰው የሦስት ነገሮች ውቅር ነው። የትላንት፣ የዛሬ፣ የነገ ። በእግዚአብሔር መታመን ትላንትን ይክሳል፣ ዛሬን ያሠራል፣ ነገን ያስውባል።

ምስጋና ለእግዚአብሔር ይሁን!
 

የአባቶች ምክር

24 Nov, 13:44


ኤፌሶን 6
¹⁰ በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ።
¹¹ የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ
የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ።
¹² መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።
¹³ ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ።
¹⁴-¹⁵ እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤
¹⁶ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤
¹⁷ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው።
¹⁸ በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤
¹⁹ ደግሞ የወንጌልን ምሥጢር በግልጥ እንዳስታውቅ አፌን በመክፈት ቃል ይሰጠኝ ዘንድ ስለ እኔ ለምኑ፤
🌿@father_advice🌿

የአባቶች ምክር

23 Nov, 16:39


አመነታለሁ

ጌታዬ ሆይ! በውስጤ ነው የምወድህ ? በላይኛው እንቅስቃሴዬ ብዬ አመነታለሁ ። ለራሴ ጸጋን እየጠቀስኩ ሰዎች ግን በሕግ መጠየቅ አለባቸው ብዬ አስባለሁ ፣ በኦሪት ነኝ ወይስ በሐዲስ ብዬ የራሴን አድራሻ ለማወቅ አመነታለሁ ። ጽድቅን ለአንድ ጊዜ ፣ ኃጢአትን በተደጋጋሚ ስመርጥ ከእውነት የምወደው የቱን ነው? ብዬ አመነታለሁ ። ከቤትህም አልቀርም ፣ ከዓለምም አልታጣምና “የቱን ልያዝ ?” ብዬ በአንዱ ሰውነቴ ለሁለት ጌታ ማደር ፣ እንደ አክርማ መሰንጠቅ ፣ አንተንና ሰይጣንን ማስታረቅ ያምረኛል ። የሌሎችን ስህተት በአጉሊ መነጽር እያየሁ የራሴን ግን ላለማመን “ዓይኔን ግንባር ያድርገው” ብዬ እምላለሁ ፣ ይህን ባሰብሁ ጊዜ እውነተኛ ነኝ ወይ ? ብዬ አመነታለሁ ።
🌿@father_advice🌿
የተሰጠኝን ዘንግቼ ያልተሰጠኝን ስሻ ፣ የራሴን ትቼ የሌሎችን ጸጋ ስጋፋ ፣ በመንፈስህ መመራቴን አመነታለሁ ። በአገሬ ለመኖር “ሰዉና አየር ንብረቱ..” ስል በሰው አገር ለመኖር “ንጽሕናውና ነጻነቱ” እያልሁ አመነታለሁ ። ሁለት ነገር እያባረርሁ አንዱንም አጣለሁ ። የተፈቀደልኝን ቀን ፣ የመደሰት መብቴን አሳልፌ እሰጣለሁ ። ሁለት መልካም ነገሮችን አንዳንዴም ደግነትና ክፋትን ለመምረጥ አመነታለሁ ። እፈልጋለሁ ግን አልፈልግም ፣ ከራሴ ጋር ስብሰባ እቀመጣለሁ ግን አልወስንም ። ልቤ ይሞቃል ፣ ላደርግ ስነሣ መልሶ ይበርዳል ። አመነታለሁ ። ካንተ ጋር ልኖር ፣ ወደ ሰማይ ልመጣ እሻለሁ ፣ ያለበስኳቸውን ጨርቆች አስብና እንደገና በዚህ መኖርን እፈልጋለሁ ። አንደኛው ልቤ ባሕታዊ ፣ ሁለተኛው ልቤ ዓለማዊ ይሆንብኛል ። በአንድ ጊዜ ጽርሐ አርያም ወዲያው እንጦሮጦስ እገኛለሁ ። “ማረኝ” እያልኩህ “አትማራቸው” እላለሁ ። አመነታለሁ ፣ የማን ወገን እንደምሆን እጨነቃለሁ ። የዚያኛው ድግስ ጮማ ብርንዶ ቢኖረውስ? ይህኛው እልበት ፣ ሽሮ ቢሆንስ ? እያልሁ በመንታ መንገድ ላይ ቆሜ ሰዓቱን አሳልፋለሁ ።

ደግነትን እመርጥና ውጤቱ ቢዘገይስ? ክፋት ይሻላል ፣ አሳማውን በልቶ መቀደስ ይቻላል እላለሁ ። ለእምነት የተሰጠውን ንስሐ ለብልጠት እጠቀምበታለሁ ። መድኃኒት አለና በሽታ ቢይዘኝ እላለሁ ። ደግሞም ጭቃ ከነካኝ አይቀር ብጨማለቅስ ? እላለሁ ፣ ከኃጢአተኝነት ወደ ሰይጣንነት ለመሄድ እቆርጣለሁ ። የሰማሁት ቃልህ “ተው” ሲለኝ ፣ ልቤ “ግፋ” ሲለኝ በእነዚህ ሁለት አሳቦች አመነታለሁ ። ንጉሥ የወደደው ጣዖት የታቦት ያህል ነው ብዬ ከኤልያስ አክአብን መርጬ ፣ ማወቄን ባለማወቅ ለውጬ ፣ የዝናብ አምላክ “በኣል ነው” ብዬ ልጠፋ እሰናዳለሁ ። ጥሩ አማኝ ወይም የለየለት ከሀዲ አልሆንሁም ። ጌታ ሆይ አመነታለሁ።

ልቤ ከአንደኛው ሸለቆ ጥግ ወደ ሁለተኛው ጽንፍ ሲላጋ ፣ ተቀምጬ መሮጥ ፣ ተኝቶ መብረር ሥራዬ ሆኖአል ። የተፈጥሮ ስጦታ እያልሁ ስናገር ያንተን ሰጪነት መካዴ ነው ፣ እግዚአብሔር ብዬ ከምናገር “ፈጣሪ ይባርክህ” ብል ሁሉም ይወደኛል ብዬ ስምህን እዘላለሁ ። ዘላለምንም ዘመንንም ለማትረፍ እታገላለሁ ፣ አዎ አመነታለሁ ። ልበ ሙሉ ከሀዲ ለመሆን “ምነው ቃሉን ባልሰማሁ” እያልሁ እመኛለሁ ። አውቆ እንዳላወቀ ሰው መኖርን እናፍቃለሁ ። የበጋ መብረቅ ክፉዎችን ሲቆርጥ ያን ጊዜ ደግሞ “ወደ ወጣሁበት ቤቴ ልመለስ” ብዬ እገሰግሳለሁ ። ትክክልም ስህተትም አይደለም ብሎ ባለመናገር ዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ በመጠቀም ካለውም ከሚመጣውም ጋር ጓድ ለመሆን አሰላለሁ ። ፍርድን ትቼ ፍርሃትን እዛመዳለሁ ። ሳልኖር ለመሞት እሰጋለሁ ። አዎ አመነታለሁ ። የሥነ ምግብ ባለሙያዎች እንደሚመክሩኝ ለመኖር አስብና መልሼ ቀለል አድርጎ መኖርን እፈልጋለሁ ። ስፖርት ለቀኑ ጤንነት እንጂ ለዕድሜማ ሰጪው አንተ ብቻ መሆንህን እዘነጋለሁ ። ጥሩ የሚንቀሳቀሰው ልቡ ቀጥ ሲል “የቱ ነው ለዓለም የሚሻለው ?” እያልሁ አመነታለሁ ። ምዕራባዊነትን ከዘመናዊነት ጋር ሳምታታው ፤ ዘመናዊነት መሰልጠን ፣ ምዕራባዊነት ሌላ ባህል መሆኑን ስዘነጋው የቱን ልምረጥ ብዬ አመነታለሁ ።

የሚያመነታ ገንዘብ ቢኖረው አይገዛ ፣ እግር ቢኖረው አይራመድ ፣ ሃይማኖት ቢኖረው አያመልክ ፣ ፍቅር ቢኖረው አብሮ አይዘልቅ ፣ ቤት ቢኖረው አያርፍ ፤ ስቁል ልብ ፣ ከርታታ መንፈስ አለው ። ጌታዬ ሆይ የወንጌልህን ቃል ለመስማትም ለመኖርም ጨካኝ መሆን እሻለሁ ። በቍርጥ እንዳዳንኸኝ ፣ በቍርጥ ልከተልህ እመኛለሁ ። በአብርሃም ድንኳን እንደ ተገኘህ ፣ በድንኳን ሰውነቴ ፣ በሚነዋወፀው አካላቴ ተገኝና በአማን ይስሐቅ ይሁንልኝ ።
     አሜን🙏
🌿@father_advice🌿

የአባቶች ምክር

23 Nov, 16:16


አትጨነቁ
Don't worry

መ/ር ሳሙኤል አስረስ
@Father_advice

የአባቶች ምክር

23 Nov, 15:56


"ዘኢያደሉ"
ስለ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የተዘመረ አዲስ መዝሙር
በማኅበረ ፍኖተ አፈወርቅ የተዘጋጀ
በኢቲ አርት ሚዲያ (ETart)
ማክሰኞ ኅዳር 17/2017 ዓም ይለቀቃል።

ሼር በማድረግ ለሌሎች ያድርሱ

የአባቶች ምክር

23 Nov, 07:56


ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤”
— ቲቶ 2፥12-13

የአባቶች ምክር

23 Nov, 03:13


በአገልግሎታችሁ ምንም ፈተና ካልገጠማችሁ!
ሰይጣን ንቋችኋል ማለት ነው

ዲ/ን ሄኖክ ሀይሌ

የአባቶች ምክር

22 Nov, 17:09


"…ምክራቸውን " ጥልቅ " አድርገው ከእግዚአብሔር ለሚሰውሩ፥ ሥራቸውንም በጨለማ ውስጥ አድርገው ማን ያየናል? ወይስ ማን ያውቀናል? ለሚሉ ወዮላቸው !
ኢሳ 29፥15

የአባቶች ምክር

22 Nov, 06:40


ብቻ እናንተ ጸሎት ጀምሩ እንጂ
ብቻ እናንተ የእግዚአብሄርን ስም ጥሩት እንጂ
ሰው የገለጠውን ቁስላችሁን መድኃኔዓለም ይሸፍነዋል

የአባቶች ምክር

21 Nov, 14:21


ልብ ያለው ልብ ብሎ ያስተውል"!!!
~
አትመኝ እንደ አዳም የዲያቢሎስ ባርያ ትሆናለህ፡፡ ዘፍጥ 3፥1-8

አትቅና፦እንደ ቃኤል ወንድምህን ትገላለህ፡፡ዘፍጥ 4÷1-8 y2

አትስከር፦አእምሮ አሳጥቶ የማይገባ ስራ ትሰራለህ፡፡ዘፍጥ 19÷30-38

አለምን አትመልከት፦እንደ ሎጥ ሚስት የጨው ዐምድ ሆነህ ትቀራለህ፡፡ ዘፍጥ 19÷22-23

በአባትህ አትሳቅ፦እንደ ካም ትረገማለህ/በአንተ መተላለፍ ልጆችህን ትጎዳለህና/፡፡ዘፍጥ 9÷20

እልከኛ አትሁን፦ እንደ ፈርፆን ትሰጥማለህ፡፡ዘፀ 14÷28

በሀሰት አትመስክር፦እንደ ሐማ ባዘጋጀኸው ጉርጓድ ትገባለህ፡፡ መጽ አስቴ 7÷1

ትዕቢተኛ አትሁን፦እንደ ሰናክሬም ትወድቃለህ፡፡2ነገ 19÷35

ክፉ ባልንጀራን አትያዝ እንደ እንደ ሳምሶን በጠላትህ እጅ ትወድቃለህ፡፡ መጽ.መሳ 16÷15 y2

አትዘሙት፦እንደ ሰሎሞን አምላክህን አስረስቶ ጣፆትን እንድታመልክ ያደርግሀል፡፡ 1ነገ 11÷1-8

ስልጣንን አትውደድ፦ እንደ አቤሴሎም በአባትህ ላይ ትነሳለህ፡፡ 2ነገ ሳሙ 15÷13-17

ገንዘብን አትውደድ፦እንደ ይሁዳ ጌታን ያስክድሀል ፡፡ ማቴ 26÷ 14÷16
join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

20 Nov, 18:31


ሚካኤ🕊
“ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም።”
— ዳንኤል 10፥21

“የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤
— ዳንኤል 10፥13

በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤ ሕዝብም ከሆነ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል፤ በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል።”
— ዳንኤል 12፥1

“በሰማይም ሰልፍ ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉ። ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ፥ አልቻላቸውምም፥”
— ራእይ 12፥7

ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?”
— ዕብራውያን 1፥14

ሚካኤል ብሒል መኑ ከመ እግዚአብሄር

join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

የአባቶች ምክር

20 Nov, 12:39


እግዚአብሔር ትዕግሥተኛ፥ ኃይሉም ታላቅ ነው፥ በደለኛውንም፦ ንጹሕ ነህ አይልም፤ እግዚአብሔር በወጀብና በዐውሎ ነፋስ ውስጥ መንገድ አለው፥ ደመናም የእግሩ ትቢያ ነው።”
  — ናሆም 1፥3

የአባቶች ምክር

19 Nov, 12:13


የምክር ቃል ከቅዱስ ኤፍሬም!!

   ✝️  የበደሉንን ይቅር ማለት መሸነፍ ሳይሆን ፍቅርን ማስተማር ነውከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡ የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህን ኃጢአት አትግለጥ፡፡
የባልጀራህን ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በሌሎች ላይ አትፍረድ ገዢያቸው አይደለህምና፡፡

✝️ ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡ ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡ ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡ ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱ ልክ በእሳት ፊት እንደ ወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡

✝️ ቅዱስ፣ ጥንቁቅ፣ ግልጽና ብልህ ሁን፡፡ እርጋታን የተላበሰ ሰብእና ይኑርህ፡፡ ደስተኛ ሁን፤ ሰላምታህ በፈገግታ የታጀበ ንጹሕ ይሁን፡፡ ንግግርህ የታረመ አጭርና በጨው እንደ ተቀመመ ጣፋጭ ይሁን፡፡ቃላቶችህ የተመጠኑና ጤናማዎች ሁሉም የሚረዳቸው ይሁኑ፡፡ የጓደኛህን ምስጢር አትግለጥ፤ ለሚወዱህ ሁሉ የታመንክ ሁን፡፡
ወደ ጭቅጭቅና ንትርክ ከመግባት ራስህን ጠብቅ፡፡ የሚሰሙህ ሁሉ እንዳይጠሉህ ወደ ጠብ አትግባ፡፡
┈•┈••●◉ ✞ ◉●••┈

            join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

   ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲         
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ    
@fatheradvice_bot

የአባቶች ምክር

18 Nov, 16:14


ምንም እንኳን ስለታሪኩ እውነተኛነት አንዳንዶች ቢጠራጠሩና እንደ አፈ-ታሪክ ቢቆጥሩትም፣ ስለጥንቱ የማሰዶኒያ (መቀዶኒያ) ገዢ እና የጦር አዛዥ አሌክሳንደረ (Alexander the Great) እንዲህ የሚል ታሪክ እንደተጻፈ ይነገራል፡፡

ይህ አለም ያወቀውና ያደነቀው ታላቅ ሰው በመጨረሻዎቹ ሰዓታት ጊዜ በሞት አፋፍ ላይ ሆኖ እንዲህ አለ ይባላል፡ “ሶስት ትእዛዞች አሉኝ፡-

1) አስከሬኔን መሸከም ያለባቸው የግል ሃኪሞቼ ብቻ ናቸው፤

2) ወደ መቃብር የምሄድበት መንገድ በወርቅ፣ በብር እና በዕንቁዎች የተሞላ መሆን አለበት፤

3) እጆቼ ከሬሳ ሣጥኑ ላይ ተንጠልጥለው መተው አለባቸው።

በአሌክሳንደር ዙሪያ የነበሩና ይህንን ትእዛዙን የሰሙ ሁሉ ግራ ሲጋቡ የቅርብ ጀረናሎቹ ቀረብ ብለው እነዚህ ሶስት ትእዛዞች ለምን ያን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ጠየቁት፡፡ መልሱ እንደሚከተለው ነበር፡፡

1. ሐኪሞች በመጨረሻ አቅመ ቢስ እንደሆኑና እኛን ከሞት መዳን እንደማይችሉ ሰዎች እንዲያውቁ እመኛለሁ።

2. ሰዎች ሀብትን ለማሳደድ ሲሉ የሚያጠፉት ጊዜ እጅግ ውድ ጊዜያቸው መሆኑን እንዲያውቁ እመኛለሁ።

3. እንዲሁም፣ ሁላችንም ባዶ እጃችንን ወደዚህ ዓለም እንደመጣን እና ሁላችንም በተመሳሳይ መንገድ ባዶ እጃችንን እንደምንሄድ ሰዎች ሁሉ እንዲያውቁ እመኛለሁ።

የአባቶች ምክር

17 Nov, 18:27


መልእክት ከርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

የተወደዳችሁ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን በያላችሁበት ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።

አሐቲ ድንግል ከታተመችበት ጊዜ ጀምሮ መጽሐፉን ለማግኘት በምታደርጉት ርብርብ ለእመቤታችን ያላችሁን ፍቅርና ለኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ያላችሁን ቅናት አሳይታችኁናል። በመሆኑም መጽሐፉ በተፈለገው ቁጥር መጠን መድረስ ባለመቻሉ አንዳንድ ሰዎች ከዋጋው በላይ እንደሚሸጡት ከወንድሞቻችንና እኅቶቻችን ጥቆማ ደርሶናል። በመሆኑም መጽሐፉ እየታተመ ስለሆነ ከዋጋው በላይ በመግዛት እንዳትጎዱ ለመጠቆም እንወዳለን።

የአባቶች ምክር

17 Nov, 17:37


እኔኮ አፌ እንጂ ልቤ ንጹሕ ነው…” የምንል ብዙዎች ነን —ጀብድ እንደኾነ ነገር፤ መርዘኛ ምላስ ከክፉ ልብ ይቀልል ይመስል ነገር።

“እኔ ሲፈጥረኝም መደባበቅ አላውቅም፣ ሲፈጥረኝም
ግልጽ ግልጹን ነው የማወራው” እያልን ሰው የምናቆስል አለን። ግልጽነትን መረን ከመኾን ለመለየት ዕድሜና ብስለት ያልሰጠን —ስናሳዝን።

ሰው ግን በልቡ ከሞላው በቀር በአፉ ሊወጣ የሚችል ምንም ነገር የለም ከልብ ሞልቶ ከተረፈው አፍ ይናገራልና።”ማቴዎስ 12፥34
እርግጥ ነው አንዳንዴ ሰው በብስጭት ከአፉ ያልተገቡ ቃላት ሊወጡ ይችላሉ። ደጋግሞ ደጋግሞ የታቀደ በሚመስል መልኩ ሰውን የሚሰብር ሰው ግን “እኔም ሰው ነኝ” ብሎ ሊመሳሰል አይችልም።

ይቅርታ” ማጣፊያው ሲያጥረን የምንመዘው ራስን የመከላከያ መሣሪያ አይደለም። ይቅርታ” ማለት ድጋሚ ያንን ጥፋት ላለማድረግ መወሰን እንጂ፤ “የቀደመ ጥፋቴን እርሱልኝ” የሚል የብልጣ ብልጦች ይግባኝ ሊኾን አይገባም። ብዙዎች ግን ያለ ምንም ማመዛዘን ከአፋቸው አጥንትን የሚሰብር ቃል እያወጡ ደግመው ደግመው “ይቅርታበማለት የቃሉን ጉልበት ይፈትናሉ

ይቅርታ” ማለት ግን “ቀጣይ በደንብ አስቤ አወራለኹ” ማለት ጭምር ነው። ይቅርታ ማለት ግን “ቀጣይ በቂ መረጃ ሳይኖረኝ አላወራም” ማለት ጭምር ነው። ይቅርታ ማለት ግን “የማወራው ነገር የሚያመጣውን ቅጣትና ወቀሳ ሙሉ ለሙሉ እቀበላለኹ” ማለት ነው። ካልኾነ ግን “ይቅርታ” የፍቅር መግለጫ፣ የሕግ ፍጻሜ የኾነውን ያሕል … የክፉ ሰዎች መሹለኪያ መንገድ እና የተደጋጋሚ ጥፋቶች ማምለጫ ሆኖ ይቀጥላል።
—————————
join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

   ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲         ?
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ ۹ᵉᵘˢⁱᵒⁿ
  

የአባቶች ምክር

17 Nov, 08:15


እኛ እያንዳንዱ የተቆለፈ በር ሺህ መክፈቻ ቁልፎች አሉት ብለን እንናገራለንእግዚአብሔር ግን ሁሉንም የተዘጉ ደጃፎች ወይም መዝጊያዎች መክፈት ይችላል ። ሁሉም ጨለማ በብርሃን ይተካል እያንዳንዱ ጥያቄም መፍትሄ ወይም መፍትሔዎች ይኖሩታል ። እግዚአብሔር እያንዳንዱን መከራ መቆጣጠር ይቻለዋል ከመራራው ጣፋጭን ከበላተኛውም የሚበላ ማውጣት የሚቻለው እግዚአብሔር ለችግሮቻችን በሙሉ መፍትሔ አለው ።

አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

የአባቶች ምክር

16 Nov, 11:40


@Father_advice

የአባቶች ምክር

16 Nov, 09:03


እናንተ ብትሆኑስ!?
‹‹ ስለ ወንድሙ መዳን የማይደክም ድኗል ብዬ አላምንም፡፡››
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

የአባቶች ምክር

16 Nov, 05:39


መልካም ነህ ብልህ ይህም ያንስብሀል

ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን

የአባቶች ምክር

16 Nov, 05:36


መልካም ነህ ብልህ ይህም ያንስብሀል
ታላቅ ነህ ብልህ ይህም ያንስብሀል
ቅዱስ ነህ ብልህ ይህም ያንስብሀል
ልዩ ነህ ብልህ ይህም ያንስብሀል
አንደበቴ በሺህ ቃላት
ማዳንህን ቢናገር
መች ይበቃል መች ይበቃል
እንዲያው ልብን ያስደንቃል

የአባቶች ምክር

16 Nov, 05:12


"አቤቱ የዕውቀት ዓይኖችን ስጠን፤ ዘወትር አንተን ያዩ ዘንድ ጆሮዐችንም ያንተን ቃል ብቻ ይሰሙ ዘንድ።"

(ቅዳሴ እግዚዕ - የጌታ ቅዳሴ)

የአባቶች ምክር

15 Nov, 20:07


❤️ልብ❤️ ሲባል
አእምሮን /ዳን 4፥16/ አሳብን /ማር 2፥6/ ፈቃድን ማር 3፥5 እና ስሜትን ሉቃ 24፥32 ያመለክታል❣️

ልብ የሕይወት መውጫ ነው ምሳ 4፥ 23
ልብ የማንነታችን መለኪያ ነው 1ሳሙ 16፥9 መዝ 50፥7
ልብ አፍ ለሚናገረው ምንጭ ነው ማቴ12፥35

የምናደርጋቸው ነገሮች ሚዛን የሚደፉት ከልብ ስናደርጋቸው ነው

❣️ይቅርታችን ከልብ ማቴ 48፥35
❣️ስጦታችን ከልብ  2ኛ ቆሮ 9፥7
❣️መለወጣችን ከልብ  ሮሜ 12፥2
❣️ማየታችን ከልብ ኤፌ 1፥18
❣️አምልኳችን ከልብ  ያዕ 1፥26
❣️መሰበካችን ከልብ ሐዋ 2፥37
❣️ፍቅራችን ከልብ ሮሜ 12፥9 1ጴጥ1፥22
❣️ መመለሳችን ከልብ ሉቃ 15፥17
❣️ማመናችን ከልብ ሐዋ 8፥37  ሮሜ 10፥9
❣️ምስጋናችን ከልብ 1ኛ ጴጥ 3፥15
❣️ ደስታችን ከልብ ማቴ 15፥15

የአባቶች ምክር

15 Nov, 13:48


ሱስ

╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝
                                      ♡ ㅤ⌲       
                                     ˡᶦᵏᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

11 Nov, 16:20


ዓለም ከንቱ

ዓለም ከንቱ ባትሆን፣ አብባ ባትረግፍ ፣ ታይታ ባትጠፋ ይቆጭ ነበር ። እነዚያን ወገኖቻችንን ለምን ሞቱ ? ብለን አዝነን ባላባራን ነበር ። ዓለም ከንቱ መሆንዋ ሰማይን እንድንናፍቅ አደረገን።

አዲስ ነገር በዓለም ላይ የለም። ሊድርህ የመጣው ሰው ሊቀብርህ ይሰበሰባል። ስትዳርም ያንተን ድግስ አትበላውም፣ ስትሞትም በስምህ የተደገሰውን አትቀምሰውም። የሕይወትህ መግቢያና መውጫ የዓለም ጉዞህ ተመሳሳይ ነው። ሙሉ በሙሉ ፈቃዱ የእግዚአብሔር ሆኖ ተወልደሃል፣ ሙሉ በሙሉ ፈቃዱ የእግዚአብሔር ሆኖ በሞት ትወሰዳለህ። ስትወለድ ምጥ ነበረ፣ ስትሞትም ጣር አለ። ስትወለድ ሰዎች ተሰብስበው ማርያም ፣ ማርያም ይሉ ነበር። ስትሞትም ሰዎች ተሰብስበው በሰላም ያሳርፈው እያሉ ይለምኑልሃል። ስትወለድ እትብቱን ይቆርጡልሃል፣ ያን ቀን እናትህ ስለቱን አትይዘውም፤ ስትሞትም ይገንዙሃል፣ አሁንም እናትህ አትቀርብህም። ስትወለድ ወንድ ተወለደ ብለው ጥይት ይተኩሳሉ፣ ስትሞትም ኧረ ጀግናው ሄደ እያሉ ጥይት እንደ በቆሎ ያረግፋሉ።

ስትወለድ አታውቅም ነበር፣ ስትሞትም ምን እየተከናወነ እንዳለ አታውቅም። ስትወለድ እንኳን ማርያም ማረችሽ ያሏት እናትህን ስትሞት እግዚአብሔር ያጽናሸ  ይሉአታል። ስትወለድ ለራስህ ታለቅስ ነበር፣ ስትሞት ሌሎች ላንተ ያለቅሳሉ። ስትወለድ ዛሬ የምትጋደልለትን ቋንቋ አታውቅም ነበር፣ ስትሞትም ቀድሞ አንደበትህ ይያዛል። ስትወለድ ሰዎች ከመሬት አንሥተው ተሸክመውሃል፣ ስትሞትም ሰዎች ተሽክመው ወደ መቃብር ይወስዱሃል። ስትወለድ ማንንም የማትጎዳ ምስኪን ነበርህ፣ ስትሞትም ማንንም የማትጎዳ ምስኪን ትሆናለህ።የተቀየሙህም ይቅር ይሉሃል። ሙት አይወቀስ ድንጋይ አይነከስ ብለው ስላንተ ደግ ደጉን ብቻ ያወራሉ። ስትወለድ ዕራቁትህን ነበር ፣ ስትሞትም ዕራቁትህን  ትሄዳለህ። ስትወለድ ወደ ሐሰተኛው ዓለም መጣህ፣ ስትሞት ወደ እውነተኛው ዓለም ትሄዳለህ።

ስትወለድ ወላጆችህ አያውቁህም ነበር፣ ስትሞት እንሸኝህ ብለው አይከተሉህም። ስትወለድ አምባሳደር ሆነህ መጥተሃል፣ ስትሞት ወደ አገርህ ተጠርተሃል። ስትወለድ ከልደትህ በፊት የሚያውቅህ እግዚአብሔር ነበረ፣ ስትሞትም ሰማይን የሚያወርስህ እርሱ ብቻ ነው። ስትወለድ ራስህን አትከላከልም ነበር፣ ስትሞትም ቢያቃጥሉህ እንኳ አትቆጣም። ስትወለድ ዓይኖችህ ሰው አይገላምጡም ነበር፣ ስትሞትም ማንንም አትበድልም። ስትወለድ ያንተ ያልሆነ ቤት ገባህ፣ ስትሞት ያንተን ንብረት ለቀሪው ትተህ ትሄዳለህ። ስትወለድ በትንሽ ጨርቅ ተጠቅልለህ ነበር፣ ስትሞትም በትንሽ ሳጥን አሸገው ከቤትህ ያወጡዋል። ስትወለድ ካህናት ሊያጠምቁህ ይጠብቁ ነበር፣ ስትሞትም ሊጸልዩልህ ይመጣሉ ። ስትወለድ ያዩህ ሞትህን ሲሰሙ ያዝናሉ።

ልደትህ ሞትህን ያያል፣ ሞትህ ልደትህን ያስታውሳል። ከተወለድህ ቀን አንሥቶ ወደ ሞት እየተጓዝህ ነው። የልደት ቀንህን ስታከብር ዕድሜህ የተጨመረበት ብቻ ሳይሆን ዕድሜህ የተቀነሰበትን በዓል እያከበርህ ነው።

አንተ ወገኔ !
ሁሉን ትትህ ትሄዳለህና በሁሉም ነገር አትጨነቅ። ዓለምን ከኋላህ ፣ ክርስቶስን ከፊትህ አድርገህ ትሄዳለህና ሌላውን ቀምተህ አዳሪ አትሁን። ሌላውን እየቀብርህ አንተ የምትቀር መስሎህ አትስገብገብ ። ለማትኖርበት ዓለም ሰብስበህ ወደምትኖርበት ሰማይ ባዶ እጅህን እንዳትሄድ ተጠንቀቅ። ዘመኑ አልቋልና ወደ ጌታህ ዕቅፍ ለመግባት በንስሐ ለሥጋ ወደሙ ፍጠን!

join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

   ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

11 Nov, 12:59


"መላእክትን ማየት ትልቅ ተአምራት አይደለም፥
የራስን ስህተት መመልከት ግን ተአምር ነው
።'
ቅዱስ አባ እንጦንስ

“ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም።”
— 1ኛ ዮሐንስ 1፥8

የአባቶች ምክር

11 Nov, 10:35


አይሰለቸኝም ከቶ ውዳሴ መዝሙር ቅኔ፣
ብዙ ነው ያደረገልኝ እግዚአብሔር በዘመኔ
more...
ዘማሪ እዝራ ሀይለ ሚካኤል

የአባቶች ምክር

11 Nov, 10:23


💠 አይሰለቸኝም ከቶ 💠

አይሰለቸኝም ከቶ ውዳሴ መዝሙር ቅኔ፣
ብዙ ነው ያደረገልኝ እግዚአብሔር በዘመኔ።


ቸርነትና ፍቅሩን ያላራቀ ከባሪያው
በለመለመ ስፍራ በጎቹን የሚያሠማራው
ታላቅ ነው የእኛ ንጉሥ ታላቅ ነው የእኛ ጌታ
መጽሐፉን የዘረጋ ማሕተሙን የፈታ።
             
አንገቱን ፍጹም ደፍቶ ቀና እንድል አድርጎኛል
እየቃተተ ሞቶ በሕይወት አቁሞኛል
አልችልም የእርሱን ፍቅር መዘርዘርና ማውራት
ውለታውን ለመግለጥ የለኝም ብርቱ ቃላት።

የአንተ ክንድ የማይንደው ተራራ ጋራ የለም
ወጥቻለው ከጥልቁ ታላቅ ነህ ዘለዓለም
የተከፈተ ደጃፍ ሠጥተኸኛል ከፊቴ
ተመስገን ክበርልኝ ንገሥልኝ አባቴ።
                
ለይተህ የጠራኸኝ ያበዛህልኝ ጸጋ
ትዝታዬ ነህ ጌታ ሲመሽና ሲነጋ
ወዳጅ እና ዘመዴ ብዬ ስጠራህ ልኑር
ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ለወጠኝ የአንተ ፍቅር።

          join👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

   ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

11 Nov, 07:59


" እምነት ባሕርን ከፍሎ ያሻግራል በበረሃ መካከል ከሚገኝ አለትም ውኃ አፍልቆ ያጠጣል:: ለዚህ ነው መጽሀፍ ቅዱስ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል የሚለው:: "
ብጹዕ አቡነ ሺኖዳ

ይቀላቀሉ👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

   ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

11 Nov, 07:40


አርዮስፋጎስ

ይህ የቴሌግራም ቻናል በወልድያ ደብረ ሲና ተክለሃይማኖት ቤ/ያን የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ መምህርና የሀገረስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ሃላፊ የሆኑት የመጋቤ ሐዲስ ኤርምያስ አዳነ ነው።
➛ አርዮስፋጎስ ማለት ፦ግሪካዊ ቃል ሲሆን ለሕዝብ ይፋ የሆነ የምርምር አደባባይ ማለት ነው።
➛ ቻናሉ በመንፈሳዊ ምርምር እንጅ በሥጋዊ ምርምር ልንረዳቸው የማንችል ጥልቅ የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች፣
➛ ስብከቶች እና ጽሑፎች የሚለቀቁበት እንዲሁም
➛ ሌሎች ተከታታይ ትምህርቶችን የሚያስተምሩበት የቴሌግራም ቻናል ነውና ይቀላቀሉ ሌሎችንም ይጋብዙ ዘንድ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።

https://t.me/Ariosfagos1271

https://t.me/Ariosfagos1271

የአባቶች ምክር

11 Nov, 05:40


እኔን ደካማውን
እኔ ደካማውን ቀኝህ እያገዘኝ
እኔን ሀጥያተኛውን ክንድህ እየረዳኝ
ሳትቆጥረው በደሌን ከፊትህ አቆምከኝ
ገመናየን ከድነህ በከፍታ አዋልከኝ

ቀኝህ ባታግዘኝ ባትረዳኝ መድህኔ
ማነው ሰው እያለ ይቆም ነበር ጎኔ
መታያ ሆነኸኝ ከፍ ያለ ሰገነት
ሁሌም እደምቃለሁ በእጅህ በረከት
  እልፍ አየበደልኩኝ በእልፍ ምህረት
  ፊቴን እያዞርኩኝ ሳይጠላኝ ያንተ ፊት
  አብዝቼ ስርቅህ አጥበቀህ ቀረብከኝ
  የማፍቀርህ ጥጉ መውደድህ አኖረኝ


የደማስቆ ብርሀን ህይወቴን ቀይሮት
ግብሬ መሰደድ ነው ለስምህም መሞት
አዳፋው ቀፀላ ዛሬ መች ታሰበ
ቤቴ ደምቆ ዋለ ፍቅር አሰያነበበ
   እልፍ አየበደልኩኝ.....

ከበደሌ ማይርቅ በስጋ ምኞቱ
ፅድቅን እየሸሸሁ ብውል ከጥፋቱ
አቤት የኔ ጌታ አቤሰ ያንተ ፀጋ
ሁሌም ያኖረኛል ሌቱን እያነጋ
   እልፍ አየበደልኩኝ .....

ይቀላቀሉ👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

   ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

10 Nov, 17:48


በቸርነት በይቅርታው አሰበን
በፍቅሩና በምሕረቱ ጎበኘን
አምላካችን በሞቱ ወደደን


ተነጥቆ ሰላም እረፍታችን
ላያድን ላይፈውስ ጽድቃችን
ተጥለን ስንኖር በሞት
በደምህ ወጣን አርነት
በደምህ ወጣን ነጻነት

የጭንቀት የመከራ አመት
ተረሳ በኢየሱስ ሞት
በፍጹም ፍቅሩ ወደደን
በሞቱ ከሞት አዳነን

ህዝቡን ሲያስጨንቅ የነበረ
የጠላት ክንዱ ተሰበረ
ማልቀስ ቀረልን መቅበዝበዝ
ገነት ገብተናል በእርሱ ወዝ
ገነትን ወረስን በእርሱ ወዝ

ሰማይና ምድር ተስማሙ
ታጥበዋልና በደሙ
ነፃነት አዋጅ ተሰማ
አዜምን የጽድቁን ዜማ
ዘመርን የጽድቅ ዜማ

#ዘማሪ_ዲ/ን_አቤል_መክብብ
        ይቀላቀሉ👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

   ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

10 Nov, 17:28


1ኛ ጢሞቴዎስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³-⁴ ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ
ይህ ነው።

አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤
ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤
⁷ እኔም ለዚህ ነገር አዋጅ ነጋሪና ሐዋርያ በእምነትና በእውነትም የአሕዛብ አስተማሪ ለመሆን ተሾምሁ፤ እውነት እናገራለሁ፤ አልዋሽም።
⁸ እንግዲህ ወንዶች በስፍራ ሁሉ አለ ቍጣና አለ ክፉ አሳብ የተቀደሱትን እጆች እያነሱ እንዲጸልዩ እፈቅዳለሁ።
⁹-¹⁰ እንዲሁም ደግሞ ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእፍረትና ራሳቸውን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸልሙ፤ እግዚአብሔርን እንፈራለን ለሚሉት ሴቶች እንደሚገባ፥ መልካም በማድረግ እንጂ በሽሩባና በወርቅ ወይም በዕንቍ ወይም ዋጋው እጅግ በከበረ ልብስ አይሸለሙ


ይቀላቀሉ👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

   ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

10 Nov, 07:26


የታማኝነት አበባ
.......

በድሮ ዘመን አንድ ልዑል የንግስና ዘውዱን ከመድፋቱ በፊት ሚስት እንዲያገባ የሚያስገድድ ባህል ነበር፡፡ እናም የንግስና ዘውዱን ለመድፋት የተቃረበ አንድ ልኡል ታማኝና ሚስት የምትሆነው ሴት ማግኘት ፈለገና በመላ ሀገሪቱ አዋጅ አስነግሮ ወጣት ሴቶችን ለማወዳደር ሰበሰበ፡፡

በዛች ሀገር ውስጥ የምትኖር የአንዲት አገልጋይ ሴት ልጅ ነበረች፡፡ ልጅቱም ልዑሉን አጥብቃ ታፈቅረው ነበር፡፡ እናም ይቺ ልጅ ውድድሩን እንደሰማች ከመላ ግዛቲቱ ተሰባስበው የልኡሉ ሚስት ለመሆን ከሚፎካከሩት መካከል አንዷ ለመሆን ወሰነች፡፡ ነገር ግን አገልጋይ እናቷ "ተይ ወደ ቤተ-መንግስት ገብተሽ አትወዳደሪ፤ ከመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ቆነጃጅትና ሀብታም ሴቶች ናቸው የሚመጡት፡፡ ሞራልሽን ይነኩታል፡፡ ተይ ልጄ እሱን ማግባት አትችይም አንቺ ደሀ ነሽ" አለቻት፡፡ ልጅቷ ግን አሻፈረኝ አለች፡፡

"ከእነዛ ሁሉ ቆነጃጅትና ሀብታም ሴቶች እኔን እንደማይመርጥ አቃለው፤ ነገር ግን ቢያንስ ለመጨረሻ ግዜ ከእሱ ጋር ማውራት እችላለው፡፡" ብላ ወደ ውድድሩ ገባች፡፡ በቀጣዩ ቀን ሁሉም ቆነጃጅቶች በቤተ-መንግስት ተሰበሰቡ፡፡ ከደሀዋ ወጣት ሴት በስተቀር ሁሉም በሚያማምሩ ልብሶችና ጌጣጌጦች ተውበው ነበር፡፡

በመቀጠል ልኡሉ "ለሁላችሁም የአበባ ዘር እሰጣችኀለው፤ ከ6 ወር በኀላ በጣም የሚያምር አበባ አሳድጋ ያመጣችልኝ ሴት ሚስቴ ትሆናለች" አለ፡፡ ሁሉም ሴቶች የሚተክሉትን የአበባ ዘር ወሰዱ፤ ደሀዋ ወጣትም እንደዛው፡፡ ወጣቷ ዘሩን በአበባ መትከያ ውስጥ ከተከለችው 3ወራት አለፈ፤ ነገር ግን አበባው ሊበቅል አልቻለም፡፡ በጣም ተረበሸች፡፡ የግብርና ባለሙያዎችን አማከረች፡፡ ነገር ግን አበባው ሊበቅል አልቻለም፡፡

6ኛው ወር ደረሰና ሴቶቹ ሁሉ ዳግም በቤተ-መንግስት ተሰበሰቡ፡፡ ከደሀዋ ልጅ በስተቀር ሁሉም በአበባ መትከያ ባዶ ማሰሮ የሚያማምሩ አበቦችን ይዘዋል፡፡ ደሀዋ ልጅ ደሞ የአበባ መትከያውን ብቻ ይዛለች፡፡ በመቀጠል ልኡል ውሳኔውን አስተላለፈ፡፡

"ሚስቴ የምትሆነውን ሴት መርጫለው፡፡ የአበባ መትከያ ብቻ የያዘችው ወጣት ሚስቴ ትሆናለች" አለ፡፡ ሁሉም ሴቶች "እኛ የተጠየቅነውን አበባ ይዘን መተን እሷ ባዶ እጇን እንዴት ትመረጣለች?" እያሉ አጉተመተሙ።

ልዑሉ ቀጠለና "ከመካከላችሁ አበባውን ለማብቀል በትክክልም የጣረች እና ለንግስነት ዙፋኑ የምትመጥን እሷ ናት ከስድስት ወር በፊት የሰጠኋችሁ የአበባ ዘሮች የመከኑ ናቸው። በምንም አይነት ሊበቅሉ አይችሉም። ሁላችሁም ግን ከየት እንደሆነ ባላቅም አበባ ይዛችሁ መጣችሁ፡፡ ይቺ ሴት ግን የታማኝነት አበባን ነው ይዛ የመጣችው " አለ፡፡

ብዙ ግዜ የሆነ ነገር ለማግኘት በጣም ከመጓጓታችን የተነሳ አብዛኞቻችን እውነታውን በሀሰት እንቀይራለን፡፡ ነገር ግን እውነት እና ታማኝነት ሁሌም ቢሆን ፍሬያቸው ጣፋጭ ነው፡፡
"በጥቂቱ የታመነ በብዙ ይሾማል”— ማቴዎስ 25፥23
ታማኝ ሁኑ!

ይቀላቀሉ👇
╔═F══════════A══╗
💚🌿
@Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝

   ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
  ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

10 Nov, 04:36


"በሰው ላይ በአመፃ የምትነሣሣ ከሆነ በእግዚአብሔር ላይ እንደተነሣሣህ ቁጠረው፡፡ ለባልንጀራህ አክብሮትን የቸርኸው ከሆነ እንሆ እግዚአብሔርን አከበርኽ።"

#ቅዱስ_ኤፍሬም

የአባቶች ምክር

09 Nov, 15:17


ሥራ ሰለሌለኝ እጮኛዬን ላጣት ነው

በአቤል ተፈራ በላይ

https://t.me/Abelltefera

      ✦_  @father_advice  _✦
     ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
     ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

09 Nov, 08:47


ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ ወላጆች የሌላቸውን ልጆች ባልቴቶችንም በመከራቸው መጠየቅ፥ በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው።”
— ያዕቆብ 1፥27

✍🏽"ክርስቶስን በቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ወድቆ በሚለምነው ነዳይ ውስጥ ካላገኘኸው ውስጥ ገብተህ በመንበሩ ላይ ባለው ጽዋ ላይ አታገኘውም።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

የአባቶች ምክር

09 Nov, 04:16


መንጋቱ ላይቀር አትዘኑ ትካዜ ማብዛት ማንንም አልበጀም
ለእናንተ ያለው የትም አይሄድም
እግዚአብሄር በህይወታችሁ የተከለውን ማንም አረም ነው ብሎ መንቀል አይችልም
አይዞህ ወንድሜ አንገት ላቀረቀርከው🚶‍♂️
እየራበሽ ልጄን ላልሽው እናት
ቀን ለጨለመብሽ የእናቴ ልጅ
የማያልፍ የለም!
ታሪክ ይቀይራል መድሐኔዓለም
ብዙ ነገዎች ትላንትና ሆነዋልና
ቢጨልም ይነጋል!
©Abenezer

                           ✦_  @father_advice  _✦
                           ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
                          ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

08 Nov, 09:39


ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ አለ

"እኔ የምናገረውን ሰዎች ምን ያህል በተሳሳተ መንገድ እንደሚተረጉሙት ባውቅ ኑሮ አልናገርም ነበር።"
🤐

የአባቶች ምክር

08 Nov, 09:30


አንድ ቀን ሁሉም ሰራተኞች ወደ ቢሮ ሲደርሱ እንድ ጎላ ተደርጎ የተፃፈ ማስታወቂያ ተለጥፎ አዩ ፡፡ “በዚህ ኩባንያ ውስጥ እድገትዎን የሚያደናቅፈው ሰው በትላንትናው ዕለት ከዚህ አለም በሞት ስለተለየ በመሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ተዘጋጅቷልና መጥተው ይሰናበቱት ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን" የሚል

መጀመሪያ ላይ ሁሉም በሞተው የሥራ ባልደረባ ሐዘን ገብቷቸው ነበር ፣ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን የባልደረቦቹን እና የድርጅቱን እድገት የሚያደናቅፍ ያ ሰው ማን እንደሆነ ለማወቅ መጓጓት ጀመሩ፡፡
በአዳራሹ ውስጥ በርካታ ሰው ስለነበር ደንብ አስከባሪ ጥበቃ በክፍሉ ውስጥ ያለውን ሕዝብ እንዲቆጣጠሩ ትእዛዝ ተሰጣቸው። አዳራሽ ውስጥ ያለው ሰው እየጨመረ በመጣ ቁጥር የሟቹን ነገር ተረስቶ እድገታቸውን ያስተጓጎለው ሰው በሞሞቱ ደስታ ይሰማቸው ነበር፡፡ ብዙዎቹም እያጉረመሩሙ መደሰታቸውን ይገልጻሉ፡፡ ሰዎች ወደ ሬሳ ሳጥኑ በቀረቡ ቁጥር ደስታቸው እየጨመረ መጣ፡፡ በዛው መጠን ማን እንደሆነ የማወቅ ጉጉታቸው አየለ፡፡ “እድገቴን የሚያደናቅፈው ይህ ሰው ማነው? እንኳንም ሞተ! አሁን ቶሎ አድጋለው” ብለው የሚያስቡ በርካቶች ነበሩ፡፡ አስተናባሪዎች፤ ሰራተኞች አንድ በአንድ ወደ የሬሳ ሳጥኑ እንዲጠጉ እና ወደ ውስጥ እንዲያዩ አደረጉ፡፡ ሳጥኑ ውስ ያለውን ነገር ሲመለከቱ ግን በሙሉ ድንገት ዝም አሉ። በሬሳ ሳጥኑ ውስጥ የጠበቁት ሬሳ አልነበረም። በምትኩ የራሳቸውን ምስል መልሶ የሚያሳያቸው መስታዎት ነበር የተቀመጠው።
ከመስተዋቱ አጠገብ “በእድገትዎ ላይ ገደብ የማድረግ ችሎታ ያለው አንድ ሰው ብቻ ነው ፡፡ እርሱም ራስዎ ነዎት” የሚል መልእክትም በጉልህ ይታያል። ያኔ ሁሉም ሰው ወደ ልቡ ተመልሶ ስራውን በአግባቡ ይሰራ ጀመር...
***
በህይወታችን ውስጥ ለውጥ ሊያመጡ የምንችለው ራሳችን ብቻ ነን፡፡ በደስታ እና በስኬታችንም ላይ ተጽዕኖ ልናሳርፍ የምንችለው እኛው ነን። ለእኛ ከእኛ በቀር ረዳት ከየት ሊመጣል ይችላል።

አለቃችን ስለተቀየረ ፣ ጓደኞች ስለለወጥን፣ መስሪያ ቤት ስለቀየርን፣ ሕይወታችን ላይ ለውጥ አይመጣም። ራሳችንን በለወጥን ጊዜ ግን ሁሉም ለውጥ ይከሰታል።

                           ✦_  @father_advice  _✦
                           ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
                          ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

08 Nov, 08:22


አውግስጢኖስ
"የአንድ ሰው መንፈሳዊነት ተገልጦ የሚታየው ስህተት የፈፀመውን ወንድም በሚይዘበት መንገድ ነው"የሚል አባባል አለው።

                           ✦_  @father_advice  _✦
                           ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
                          ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

07 Nov, 16:53


👆👆👆 ጠቃሚ ምክር!

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ለደካሞች ትጉላቸው " ብሎ በተናገረው መሠረት ምንጊዜም የሰዎችን ሞራልና መንፈስ ለመጠበቅ እንሞክር። [1ኛ ተሰ 5*14] አንድን ሰው ሲቆጡት፤ ሲወቅሱትና ፤ትህትናን ሲነፍጉት ብትመለከቱት እርሱን ከጎናችሁ አድርጋችሁ የሚገባውን በእርሱ ስም ተናገሩለት። በእርግጥም ይህ ሰው ይህንን ታላቅ ሥራችሁን በእድሜው ዘመን ሙሉ አይረሳውም። ይህ ማለት ደግሞ በፍቅርና በቸርነት በተሞሉ ታታላላቅ ልቦናዎች መንፈሳቸው ለደከመ ሰዎች የተደረገ ታላቅ ሥራ ነው። በኃጢአት የተተበተበ አንድ ሰው ብታገኙ ከዚህ ነፃ አውጡት እንጂ አትገስጹት።

በአንድ ወቅት አንድ ወጣት ልጅ የገባበት ውኃ ሊያሰጥመው ሲል ራሱን ለማዳን በመፍጨርጨር ላይ ሳለ በዚያ የሚያልፍ አንድ ሰው "ልጄ ሆይ ዋና ሳትችል እንዴት እዚህ ባሕር ውስጥ ልትገባ ቻልክ! ?" እያለ ሲቆጣው ልጁ "በእርግጥ ተሳስቻለሁ ወደዚህ ባሕር የገባሁበትን ምክንያት እንድነግርህ ግን በመጀመሪያ ከሞት አድነኝ " ብሎ መልሶለታል። እናንተም ልክ እንደዚህ ሰውዬ መሆን የለባችሁም። ማንንም ሰው ሲወድቅ ብትመለከቱት አትገስጹት ይልቁንም። ተስፋ ስጡት። " እኔ ብዙ ጠቃሚ ምክሮች መክሬሃለሁ አንተ ግን አልተጠቀምክባቸውም ስለዚህ ከባድ መከራ ቢደርስብህ አይቆጨኝም " ብለን አንናገር።

የሐዋርያው ቃል በንቃት አድምጡ። "...... ለደካሞች ትጉላቸው ሰውን ሁሉ ታገሱ" [1ኛ ተሰ 5*14] ። ሥሩን የሰደደ ኃጢአትን ነቅሎ ለመጣል ጊዜና ትዕግስት ስለሚጠይቅ እግዚአብሔር እንደነዚህ ያሉትን ደካሞች በጸጋው እስኪጎበኛቸው ነጻ እስኪያወጣቸው ድረስ ትዕግስት አድርጉላቸው። አንተም ተፈጥሮህ ከእነርሱ ጋር ተመሳሳይ ስለሆነ ከዚህ የሚከተለውን የሐዋርያውን ቃል ዘወትር ከፊትህ አስቀድም። " ከእነርሱ ጋር እንደ ታሰረ ሆናችሁ እስሮችን አስቡ የተጨነቁትን ደግሞ ራሳችሁ ደግሞ በሥጋ እንዳለ ሆናችሁ አስቡ ።[ዕብ 12*3] ።
#የእግዚአብሔርን_ሕዝብ_ተስፋ_ለማስቆረጥ_የተጉትን_ሰዎች_እግዚአብሔር_ወደ_ተስፋይቱ_ምድር_እንዲገቡ_አልፈቀደላቸውም።
እግዚአብሔር ሕዝቡን ".....በኃይል ከእኛ ይበረታሉና በዚህ ሕዝብ ላይ መውጣት አንችልም...... ያየናቸው ሰዎች ሁሉ ረጃጅም ሰዎች ናቸው. .... እኛም በዓይናችን ግምት እንደ አንበጣዎች ነበርን " በማለት ሊያዳክሙት የነበሩትን ሰዎች ገድቧቸዋል ። [ዘኁ13*31-33]።
እናንተ ግን አንድ ሰው ኃጢአተኛ ወይም ደካማ ቢሆንም እንኳ በሕይወቱ ውስጥ መልካም ጎኑን በመፈለግ አውጥታችሁ እነዚያ ባሕርያቱን አሞግሱለት። ኢየሱስ ክርስቶስ ለሳምራዊቷ ሴት ያደረገው እንደዚህ ነው። " ባል የለኝም በማለትሽ መልካም ተናገርሽ. ..."በዚህ እውነት ተናገርሽ "[ዮሐ 4*17እና 18] ።ይህ ውዳሴ ሴቲቱ ኃጢአቷን እንድትናዘዝ ስላደረጋት ለንስሓ ትበቃ ዘንድ ጌታ አሸንፏታል። አንዱ ሰው ሌላው ሸክሙን በሚያቀሉለት በቅዱሳት መጻሕፍት ታሪኮች ሲበረታታ ሌላው ደግሞ ስለ እግዚአብሔር ጸጋና ሥራ ሲነገረው ይበረታታል። ከዚህ ሌላ ስህተቶቹን ሁሉ በመርሳት የሚበረታታ ሰው ይኖራል። ለተፈጸመ ስህተት ሁሉ ቁጣን ማቅረብ ግን ወደ ተስፋ መቁረጥ ያደርሳል።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ እንዳስተማሩት! !
                           ✦_  @father_advice  _✦
                           ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
                          ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

07 Nov, 06:54


"ላለማመን እንጂ ለማመን በዙሪያችን ብዙ ምስክሮች አሉልን!"
         (ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ )

  | ዐይነ ሥውሩ ቅዱስ ዲዲሞስ በአንድ ወቅት የእግዚአብሔርን መኖር የሚክዱ ተመራማሪዎች የራሳቸውን እውቀት መነሻ በማድረግ የእግዚአብሔርን አለመኖር ከነገሩት በኋላ <እስኪ አንተ እግዚአብሔር መኖሩን በተጨባጭ አስረዳን?> ሲሉ ጠየቁት።

ቅዱስ ዲዲሞስ ተመራማሪዎቹ ጭልጥ ብለው መሳሳታቸውን ቢያውቅም በጥሞና ያዳምጣቸው ነበር እንጂ አልተበሳጨም።

ለጠየቁት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት "ምሽት ተመልሳችሁ ኑ" አላቸው።

እነርሱም የቀጠሮአቸውን ሰዓት አክብረው ምሽት ተመልሰው መጡ።

ቅዱስ ዲዲሞስም "እስኪ ወደላይ አንጋጣችሁ የሰማዩን ገጽታ ተመልከቱ" አላቸው።

እነርሱም እንዳላቸው ሰማዩን ተመለከቱ።

እርሱም "በሰማይ ላይ ምን ምን ይታያችኋል?" አለ።

እነርሱም "ከዋክብት" ብለው መለሱለት።

እርሱም "በስጋዊ አይናችሁ የማየት ችሎታ እነዚህን ክዋክብት በቀን ማየት ትችላላችሁን?" አላቸው።

እነርሱም "አንችልም" አሉት።

እርሱም "ለምን ማየት ያቅታችኋል?" ሲል ጥያቄውን በጥያቄ ደገመላቸው።

እነርሱም "ምክንያቱም ከዋክብትን ለማየት የግድ መምሸት አለበት" አሉት።

እርሱም "በእርግጥ ትክክል ናችሁ የመለሳችሁት ምላሽ ትክክል ነው። ይሁን እንጂ በተፈጥሮ እንደምናውቀው የተሰወረውን ነገር ለማግኘት ብርሃን ያስፈልጋል። እነዚህን የምታዩአቸው ከዋክብት ለማየት ግን ብርሃን ሳይሆን ጨለማ ሊኖር የግድ ነው። እንደዚሁ ሁሉ እግዚአብሔርንም ለማየት ቁሳዊ ነገርን ማየት በሚቻልበት በሳይንስ መሳሪያና ፍልስፍና ሳይሆን በእምነት ብቻ ማረጋገጥ እንደሚቻል ልነግራችሁ እወዳለሁ።" በማለት አስረዳቸው።

ከዚያም እርሱ በተራው "በሰማያት ገጽታ ላይ ከዋክብት እንደሚታዩ ነግራችሁኛል። ይሁን እንጂ እኔ አይነ ሥውር ስለሆንኩ በምን ታረጋግጥሉኛላችሁ?" ሲል አዲስ የጥያቄ ርእስ ከፈተላቸዉ።

እነርሱም ግራ ተጋብተው ምላሽ አጡ እና ከመናገር ይልቅ ዝምታን መረጡ።

እርሱ ግን የእኔ አይነ ስውርነት የከዋክብቱን አለመኖር አያረጋግጥም፤ እኔ አየሁም አላየሁም ከዋክብቱ ዘወትር አሉ። እኔም ምንም ዐይነ ሥውር ብሆንም እንኳን ከዋክብቱን ሳልመለከት እናንተ አይታችሁ በነገራችሁኝ ምስክርነት ብቻ የከዋክብቱን መኖር አምኜ ተቀብየዋለሁ አላቸው። እኔ አንዳች ከዋክብት ሳልመለከት የከዋክብቱን መኖር እንዳመንኩ እናንተም በሥጋዊ አይናችሁ ባትመለከቱም እንኳን በእምነት እግዚአብሔር መኖሩን አታምኑምን? ብታምኑ መልካም ነው።" ሲል በትሕትና ጠየቃቸው።

እነርሱም በጥያቄ መልክ ያቀረበላቸውን አስተሳሰቡን እና ምስክርነቱንም ተቀብለው የእግዚአብሔርን መኖር በእምነት አረጋገጥን አሉት።

በዚህ የክርክርና የውይይት ሁኔታ ዐይነ ሥውሩ ቅዱስ ዲዲሞስ (በትሕትናውና በድክመቱ) የተናገሩትን አድምጦ የእነርሱን ዕውቀታቸውንና አስተሳሰባቸውን ተጠቅሞ ክብራቸውን ሳይጋፋ የእግዚአብሔርን መኖር በማሳመን ረታቸው።

ክርክራቸውም በዚህ ተደመደመ።

ምንጭ ፦
በአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ በእንግሊዝኛ "CALMNESS" በሚል ተጽፎ በመምሕር ሰለሞን በቀለ "የሕይወት መንገድ" በሚል በአማርኛ ከተተረጎመ መጽሐፍ የተወሰደ
                           ✦_  @father_advice  _✦
                           ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
                          ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

07 Nov, 06:48


የ፮ እሁድ ማኅሌተ ጽጌ በሊቀ መዘምራን ተስፋ ጽዮን

https://youtu.be/7NvahZyM3pU?si=gJwwP02gLIy6aLhG&sfnsn=mo

የአባቶች ምክር

06 Nov, 16:43


ግትርነት ውስጥ ምህረት የለም!!

ከክርስቶስ ልደት በፊት በ60 ዓ.ዓ የኖረው ጠቢቡ #ሲሴሮ ስለቁጣ ሲናገር ፦ << በንግሥና ዙፋን ተቀምጦ በቁጣ ቀንበር ስር እንደሚሰቃይ ንጉስ የሚያሳዝን የለም።>> ይላል፡፡

ንጉስ ግኔስ ፒሶ ፦ ቁጡ ፣ ግትር እና ማስተዋል የጎደለው ንጉስ ነበር ። #ፒሶ :: አንድ ቀን አንድ ወታደር ለአሰሳ ከወጣበት ሲመለስ አብሮት የወጣውን የመቶ አለቃ ትቶት ብቻውን ይመለሳል ። ይህን የሰማው #ንጉስ ፒሶ ወታደሩ እንዲገደል ትእዛዝ ሰጠ ። ለሞት ፍርዱም ምክንያት ፦ " ወታደሩ መቶ አለቃውን ገድሎት ሊሆን ይችላል ፤ ባይገድለውም ደግሞ አለቃው ትቶ መምጣቱ በራሱ ብቻ ያስገድለዋል " የሚል ነበር ።
ሞት የተፈረደበትን ወታደር የሚገድል ሌላ ወታደር ታዘዘና ወደ አንድ ከፍታ ይዞት ይወጣና ሰይፉን መምዘዝ ሲጀምር። መቶ አለቃው ድንገት ከተፍ ይላል ። ገዳዩ እና ተገዳዩ በዚህ ደስ ተሰኝተው ከመቶ አለቃው ጋር ሦስቱም ወደ ቤተ መንግስቱ ይመጣሉ ። ይህን ጊዜ በቤተ መንግስቱ ደስታ ይሆናል ። ነገር ግን #ፒሶ ሶስቱን ወታደሮች በአንድ ላይ ሲመለከት በቁጣ ነደደ ። ወዲያው ሦስቱም እንዲገደሉ ትእዛዝ ሰጠ።

የፒሶ ምክንያት ደግሞ ፦
<<የመጀመሪያው እንዲሞት እስቀድሜ ስለፈረድኩበት ይሞታል
ሁለተኛው ወታደሩን እንዲገድል ትእዛዝ ከሰጠሁት በኃላ ትእዛዜን ባለመፈፀሙ ይሞታል ፣
ሦስተኛው የመቶ አለቃ ደግሞ ለወታደሩ መሞት ምክንያት ስለሆነ እሱም ይሞታል>> በማለት ፈረደ ።

#ግትርነት_ውስጥ_ምህረት_የለም!!!
እኔ ያልኩት ብቻ ይሆናል ከሚል ግትርነት ራቅ አንዳንዴ መሸነፍ መልካም ነውና!

    ✦_  @father_advice  _✦
     ♡ ㅤ    ❍ㅤ     ⎙ㅤ   ⌲            
   ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

06 Nov, 14:17


በብዙ መከራና ፈተና ሆኖ እግዚአብሄር ያውቃል ማለት
ከብዙ መከራና ስቃይ ይሰውራል
ልመርቃችሁ
ጸሎቴን ሰማኝ
እንባየ ታበሰ ለማለት ያብቃችሁ

የአባቶች ምክር

06 Nov, 07:25


ዮሐንስ 21
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ ስምዖን ጴጥሮስ፦ ዓሣ ላጠምድ እሄዳለሁ አላቸው። እነርሱም፦ እኛም ከአንተ ጋር እንመጣለን አሉት። ወጥተውም ወደ ታንኳይቱ ገቡ በዚያችም ሌሊት ምንም አላጠመዱም።
⁴ በነጋም ጊዜ ኢየሱስ በባሕር ዳር ቆመ፤ ደቀ መዛሙርቱ ግን ኢየሱስ መሆኑን አላወቁም።
⁵ ኢየሱስም፦ ልጆች ሆይ፥ አንዳች የሚበላ አላችሁን? አላቸው። የለንም ብለው መለሱለት
⁶ እርሱም፦ መረቡን በታንኳይቱ በስተ ቀኝ ጣሉት ታገኙማላችሁ አላቸው። ስለዚህ ጣሉት፤ በዚህም ጊዜ ከዓሣው ብዛት የተነሣ ሊጐትቱት አቃታቸው።

አንድ ቀን እግዚአብሄር የጠየከውን ሲሰጥህ/ሽ ጌታ ሆይ
ይህ ከጠየኩህ በላይ ነው መረቤ መሸከም አቃተት! ብለህ/ሽ እግዚአብሄርን ታመስግናለህ/ታመሰግኚአለሽ !🙏

የአባቶች ምክር

06 Nov, 06:12


ጌታዬ ሆነ ደም ግባት አልባ፣
ጀርባዉ በጅራፍ ስለእኔ ደማ፣
የእኔን መገረፍ እርሱ ተገርፎ፣
ክብር አለበሰኝ እርሱ ተገፎ፣ ( ×፪ )

የአባቶች ምክር

06 Nov, 06:10


ኢሳይያስ 53
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል?
² በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል፤ መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።
³ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።
⁴ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው።
⁵ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
⁶ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።
⁷ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።
⁸ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?
⁹ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ፤ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም ነበር።

ጌታዬ ሆነ ደም ግባት አልባ፣
ጀርባዉ በጅራፍ ስለእኔ ደማ፣
የእኔን መገረፍ እርሱ ተገርፎ፣
ክብር አለበሰኝ እርሱ ተገፎ፣ ( ×፪ )

በሀሰት ሸንጎ ወጥመድ ተጠምዶ
ጌታ ተያዘ ሕይወቴን ፈቅዶ
ክፉዎች ቢያዩት እንደ ወንበዴ
ለእኔ ግን ሆኗል መውጫ መንገዴ ( ×፪ )

     ታስረሃል ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
     ታስረኃል ስለኔ ኢየሱስ መድኅኔ
አገቱኒ ከለባት ብዙኀን
ወአኀዙኒ ማኅበሮሙ ለእኩያን
አገቱኒ ከለባት ብዙኀን

ሲዘብቱበት ምራቅ ሲተፉ
የማይደፈር ደፍረው ሲዘልፉ
በከበቡት ፊት ቃል ከለከለ
እኔ እንድናገር እርሱ ዝም አለ ( ×፪ )

     ታርደሃል ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
     ታርደሃል ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ

ቀነዉኒ እደውየ ወእገርየ
ወኈለቁ ኩሎ አዕጽምትየ
ቀነዉኒ እደውየ ወእገርየ

ሕይወት መንጭቷል ተወግቶ ጎኑ
ለከሳሾቹ ተርፏል ማዳኑ
እጅ እግሩን ሚስማር ሲቸነክርው
የሞትን እሾህ ከኔ ነቀለው ( ×፪ )

     ተወጋ ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
     ተወጋ ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ

ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልዕየ
ወአስተዩኒ ብሒዓ ለጽምዕየ
ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልዕየ

እርቃኑን ሆኖ ፈተለው ልብሴን
አንዲሁ ወዶኝ ጠጣ ኾምጣጤ
በምሕረቱ ጠል ነፍሴን አርክቶ
አለመለመኝ እርሱ ተጠምቶ ( ×፪
)
    ተጠማ ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
    ተጠማ ስለእኔ ኢየሱስ መድኅ

የአባቶች ምክር

06 Nov, 03:43


መርዓዊ ሰማያዊ መርዓዊ ሰማያዊ
ለእመገብረ በዓል በዓል 
መድኃኔዓለም ነው የሰማይ ሙሽር
ከሰርጉ ለመግባት ተነሱ በተራ

የሾህ አክሊል ደፍቶ የተሞሸረው
ቤተክርስቲያንን በደሙ የዋጀው
እየሱስ ክርስቶስ እርሱ ነው ሙሽራ
በመስቀሉ ብርሀን ለሁሉ ያበራ
.................... እዝ .....................

ሚዜው ደስ ብሎታል መጥምቁ ዮሐንስ
ሙሽራዋን ይዞ ወደ ራሷ ሲደርስ
ደቀ መዛሙርቱ አልቻሉም ሊያዝኑ
ከሙሽራው ጋራ አብረው ስለሆኑ


..................... አዝ ....................
ከማሰሮው ጋራ ዘይት እንዳትረሱ
ይመጣል በድንገት ሙሽራው ንጉሱ
ቢዘገይም እንኳን አይቀርም ይመጣል
ወደ ሰማዩ ስር ኑ .. ግቡ ይለናል
..................... አዝ ....................
አእላፍ መልዕክት በሰማይ ቤት ሁሉ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ሀያል ነህ እያሉ
የቃናዋ እንግዳ ድንግል ማርያም
በሰርጉ ቤት አለች ከ መድኃኔዓለም
..................... አዝ ....................
መርዓዊ ሰማያዊ መርዓዊ ሰማያዊ
ለእመገብረ በዓል በዓል..
መድኃኔ  ዓለም ነው የሰማይ ሙሽር
ከሰርጉ ለመግባት ተነሱ በተራ

........  share ... join

የአባቶች ምክር

05 Nov, 13:18


ሰውን ወዳጁና ሩህርሁ እግዚአብሔር

ሰው ጨካኝ ሲሆን እግዚአብሔር ግን ሁሉን የሚወድ ቸርና ርህርህ ነው፡፡ ለዚህም ነው ንጉስ ዳዊት ከሦስቱ ቅጣቶች መካከል አንዱን እንዲመርጥና አማራጩ ሲቀርብለት የተናገረው ቃል ድንቅ ነው፡፡ " ምህርቱ ብዙ ነውና በእግዚአብሔር እጅ እንውደቅ በሰው እጅ ግን አልውደቅ፡፡" 2ኛ ሳሙ 24 ፥ 14፡፡ ጻድቁ እዮብም በሦስቱ ባልደረበቹ እጅ በወደቀ ጊዜና እነርሱም እርሱን መውቀሳቸውን ባላቋረጡ ጊዜ እንዲህ ነበር ያላቸው ፡- "ነፍሴን የምትነዘንዙ በቃልስ የምታደቅቁኝ እስከ መቼ ነው? ይኸውም ስትሰድቡኝ አሥር ጊዜ ነው፡፡" ኢዮ 19 ፥ 2 - 3፡፡ #እግዚአብሔር ግን ከሰው በእጅጉ በተለየ መልኩ መሐሪና ርህርህ መሆኑን በሚከተሉት ውስጥ እንመለከታለን፡፡

#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ

የአባቶች ምክር

04 Nov, 10:17


ያንን ድሃ ስንት ጊዜ ወደክ ብለው ጠየቁት
አንድ ጊዜ በጠላቶቼ ሺ ጊዜ በወዳጆቼ ብሎ መለሰላቸው
ታዲያ ምን አተረፍክ ብለው ቢጠይቁት
እግዚአብሄርን
አላቸው

የአባቶች ምክር

04 Nov, 09:49


"ስለራስህ ተስፋ ከመቁረጥ ተጠንቀቅ
በራስህ ሳይሆን በእግዚአብሔር እንድትታመን ታዝዘሃል።"
        /አውግስጢኖስ/

የአባቶች ምክር

03 Nov, 16:56


❤️ዮሐንስ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤
² በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው።
³ ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል።
⁴ የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤
⁵ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና።
⁶ ኢየሱስ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ እነርሱ ግን የነገራቸው ምን እንደ ሆነ አላስተዋሉም።
⁷ ኢየሱስም ደግሞ አላቸው፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እኔ የበጎች በር ነኝ።
⁸ ከእኔ በፊት የመጡ ሁሉ ሌቦችና ወንበዴዎች ናቸው፤ ዳሩ ግን በጎቹ አልሰሙአቸውም።
በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማርያም ያገኛል።
¹⁰ ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።
¹¹ መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።
¹² እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል በጎቹንም ይበትናቸዋል።
¹³ ሞያተኛ ስለ ሆነ ለበጎቹም ስለማይገደው ሞያተኛው ይሸሻል።
¹⁴-¹⁵ መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች ያውቁኛል፤ ነፍሴንም ስለ በጎች አኖራለሁ።
¹⁶ ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።

የአባቶች ምክር

03 Nov, 11:46


ጌታ ሆይ
እየሄድኩ የምመጣው
እየጠፋሁ ብቅ የምለው
ካንተ ውጭ መኖር ስለማልችል ነው🥺

የአባቶች ምክር

03 Nov, 04:39


#ስትፈራ_ስትጨነቅ_ይህን_አስታውስ!

እግዚአብሔር
-ኃይልን
-ፍቅርን
-ራስን መግዛትን እንጂ

- ፍርሃትን አልሰጠህም!!
በርታ!!


#ትምህርተ_ሺኖዳ መጽሐፍ

የአባቶች ምክር

03 Nov, 03:43


እግዚአብሄር ከእንቅልፍህ እንድትነሳ ከረዳህ አሁንም
በአንተ ላይ እቅድ አለው ማለት ነው።

የአባቶች ምክር

02 Nov, 20:21


በእኔ ቢጠቁር ሰማይ

በእኔ ቢጠቁርም ሰማይ
በእኔ ቢጠልቅም ፀሐይ
በነፋሳት የማይጠፋ ፋኖሴ
ኢየሱስ ነው የመኖር እስትንፋሴ

እርሱን ታምኜ እወጣለሁ
እርሱን ታምኜ እገባለሁ
ድብቅ ሰራዊት አለው ለእኔ
የሚጠብቀኝ በዘመኔ
እግዚአብሔር ለእኔ ብርሃኔ ነው
የሚያስደነግጠኝ የሚያስፈራኝ ማነው

ሰው አልባ ሁኜ በስደት
ወዳጄ የሆነኝ የእኔ አባት
ክርስቶስ ለእኔ ሕይወቴ ነው
እርሱን ታምኜ እኖራለሁ
የለም የሚያስፈራኝ በዘመኔ
ብርሃን ነውና እግዚአብሔር ለእኔ

መች ይሰጠኛል ለጠላት
አይሰለጥንም በእኔ ሞት
የሚጠብቀኝ ጌታ ነው
የትኛው ጠላት ሊደፍረው
በቤቴ መቃን ላይ ደም ይታያል
እኔን ከእግዚአብሔር ከቶ ማን ይለያል

ይኸው አቆመኝ በመቅደሱ
እየጠበቀ በመንፈሱ
እኔን ሊያከብር ራሱን ሰጥቶ
ግዝቶኛል ጌታ ሞቴን ሙቶ
ይገዛ ለስሙ ስጋ መንፈሴ
በእርሱ ነውና ለዛሬ መድረሴ

በዓለም ሳለሁ የዓለም
ብርሃን ነኝ። ዮሐ 9፥5

ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ

@father_advice
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯

የአባቶች ምክር

02 Nov, 19:27


#በርባን_እኔ_ነኝ

በርባን ይፈታ በርባን ይፈታ
ይሰቀል ጌታ ይሰቀል ጌታ

የሚለው ጩኸት ሆነ መዳኛዬ
በርባን እኔ ነኝ ማረኝ ጌታዬ
በአንተ መታሰር እስሬ ተፈቶ
በአንተ መጎተት ቀንበሬ ላልቶ
ነፃ የወጣሁ ሀጢያተኛ
እኔ ነኝ የአለም ክፉ ወንጀለኛ
አንተ ተጠልተህ የተወደድኩት
አንተ ተዋርደህ የተከበርኩት
በርባን እኔ ውለታ ቢሷ
የዋልክልኝን ሁሌ ምረሳ

ዘውድ እንድቀዳጅ እሾኽ ደፍተሃል
ለነፃነቴ ተቸንክረሀል
እኔ ግን ተመለስኩ ወደ ሀጢአቴ
መች ተወኝ እና በርባርነቴ

join👇
https://t.me/kebelayhungtmoch

የአባቶች ምክር

02 Nov, 16:03


“ንብ የምትሞተው መቼ ነው?”
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)

የጥበበኛ ነፍስ መገለጫዋ ይሄ ነውና ሁል ጊዜ የምታመሰግኑ ሁኑ፡፡ ክፉ ደረሰባችሁን? ይህስ እናንተ ከፈቀዳችሁ ክፉ አይደለም፡፡ ሁል ጊዜ አመስግኑ፤ ክፉ የሆነባችሁም መልካም ይሆንላችኋል፡፡ ከተወደደው ኢዮብ ጋር ሆናችሁ “የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን” እያላችሁ አመስግኑ /ኢዮብ.1፥21/፡፡

እስኪ ንገሩኝ! ደረሰብኝ የምትሉት ክፉ ነገር ምንድነው? በሽታ ነውን? ታድያ ይሄ እኮ አዲስ ነገር አይደለም፡፡ ምክንያቱም ሥጋችን መዋቲና ለስቃይ የተጋለጠ ነውና፡፡ሀብት ንብረት ማግኘት አለብኝ የሚል መሻት ነውን? ታድያ ይሄ እኮ ምግኘት የሚቻል ነው፤ ካገኙት በኋላ ግን መልሶ የሚጠፋና በዚህ ዓለም ብቻ የሚቀር ነው፡፡ ከወንድሞች የሚደርስ ሐሜትና የሐሰት ወቀሳ ነውን? ታድያ ተጐጂዎቹ’ኮ የሚያሙንና በሐሰት የሚመሰክሩብን እንጂ እኛው አይደለንም፡፡ “ኃጢአት የምትሠራ ነፍስ ትሞታለች” እንዲል ተጐጂዎቹ ይህን ኃጢአት የሚሠሩት እንጂ እኛው አይደለንም /ሕዝ.18፥4/፡፡ ተጐጂው ምንም በደል ሳይኖርበት ክፉ የሚደርስበት ሰው ሳይሆን ክፉ የሚያደርሰው ሰው ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ ምውት በሆነ ሰው ልትቆጡ አይገባም፤ ከዚያ ይልቅ ከሞት ይድን ዘንድ ልትጸልዩለት ይገባል፡፡

ንብ መቼ እንደምትሞት አይታችሁ ታውቃላችሁን? የምትሞተው ሌላውን ስትናደፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር በዚህች ፍጥረት በወንድሞቻችን ላይ ልንቆጣ እንዳይገባ ያስተምረናል፡፡ እኛው የምንቆጣ (የምንናደፍ) ከሆነ ግን ቀድመን የምንሞተው እኛው ነን፡፡ ስንቈጣቸው የጎዳናቸው ይመስለን ይሆናል፤ ነገር ግን እንደዚያች ንብ ተጐጂዎቹ እኛው ነን፡፡

የአባቶች ምክር

02 Nov, 09:54


"ብዙ ጊዜ ሰዎች ብልህ ነን እያሉ ይሳሳታሉ። ነገር ግን ብልህ የሚባሉት ብዙ የተማሩና ብዙ ያነበቡ ብዙ የሚናገሩ ብቻ አይደሉም። ይልቁንም ጠቢባን የሚባሉት ጥብብት መጥበቢት ብልህ ነፍስ ያላቸው፤ የእግዚአብሔርንና የሰይጣንን ለይተው ለእግዚአብሔር ሆነው የሚኖሩ ናቸው። ፍጹም ምልዓተ ኃጢአትንና ከጦር ይልቅ የሚወጉ የኃጢአት እሾሀቸውን የነቀሉ ናቸው ጠቢባን።

ጠቢባንስ እግዚአብሔርን ያለጥርጥር በሙሉ ልብ የሚያምኑት፤ አምነውም እንደ ፈቃዱ የተከተሉት፤ በክንፈ ጸጋ ተመስጠው ከልብ በሚወጣ ውዳሴ ከእርሱ ጋር ተዋሕደው የሚኖሩ ናቸው። የነፍሳቸውን ረብሕ ጥቅም አውቀው ዕለት ዕለት ያንን የሚለማመዱ በእውነት ጠቢባን እነዚህ ናቸው።"

(ቅዱስ አባ እንጦንስ)

የአባቶች ምክር

02 Nov, 09:10


ዝምታ🤐!

አንዳንድ ጊዜ ዝምታ ከቃላት ይልቅ ውጤታማ፣ ይበልጥ ተገቢና እጅግ ጠቃሚም ነው። ወይም ደግሞ ቢያንስ - ቢያንስ ተናግሮ ከሚመጣ ጉዳት ይልቅ ሳይናገሩ የሚመጣ ጉዳት ይሻላል። በዝምታ ውስጥ ጥበብና ጥንካሬ ከመኖራቸው በተጨማሪ ክብርና ሞገስም አሉ፡፡

አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር ይናገር ዘንድ እኛ ዝም እንላለን፣እኛ ልንናገር ከምንወደው ከማንኛውም ነገር የበለጠ የእግዚአብሔር ቃል እጅግ ኃያል ነውና። መጽሐፍ ቅዱስ ይህን አስመልክቶ የተናገረው ቃል ምንኛ ድንቅ ነው! «እግዚአብሔር ስለ እናንተ ይዋጋል፤እናንተም ዝም ትላላችሁ. . » ዘጸ 14፥14።

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጲላጦስ ፊት በዝምታ ቆይቷል። በዚያን ጊዜ እርሱ አፉን አልከፈተም ራሱንም አልተከላከለም። ጌታ ዝምታን በመረጠ ጊዜ ጲላጦስ «ይህን ጻድቅ ሰው የምወነጅልበት ምንም ዓይነት ምክንያት አላገኘሁም» በማለት ተናግሮ ነበር፡፡

ዝምታ ትርፍ አስገኚ ይሁን እንጂ የተወሰነ መመሪያ አይደለም፡፡ ወርቃማው መመሪያ፡- ሰው ሊናገር የሚገባው በትክክለኛው ጊዜ መሆኑና ዝም ማለት የሚገባውም ዝም ማለት በሚገባው ትክክለኛ ጊዜ መሆኑ ነው።

ሰው ዝም ሲል ልቡ ከእግዚአብሔር ጋር እንዲነጋገር ስለሚፈቅድ በእርሱ ፈንታ ጌታው እንዲናገር ይጠይቃል ማለት ነው፡፡

(አቡነ ሽኖዳ ሣልሳዊ - የሕይወት ልምድ ገጽ 14 - በአያሌው ዘኢየሱስ የተተረጎመ)

የአባቶች ምክር

01 Nov, 19:20


ኤፌሶን 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ
እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።

¹⁸-¹⁹ ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤
²⁰-²¹ ክርስቶስንም ከሙታን ሲያስነሣው ከአለቅነትና ከሥልጣንም ከኃይልም ከጌትነትም ሁሉ በላይና በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ሊመጣ ባለው ዓለም ደግሞ ከሚጠራው ስም ሁሉ በላይ በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው በክርስቶስ ባደረገው ሥራ የብርታቱ ጉልበት ይታያል፤
²² ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛለት ከሁሉ በላይም ራስ እንዲሆን ለቤተ ክርስቲያን ሰጠው።

የአባቶች ምክር

31 Oct, 12:26


ምን አልባት ይሄን ሁሉ የተፈተንኩት
እግዚአብሄር ተማምኖብኝ ቢሆንስ

ሰይጣን በፊቱ ቁሞ እስቲ የሰጠኸውን ልንጠቀውና እንደማያመልክህ ታየዋለህ ብሎ በእኔ ተወራርዶ ቢሆንስ

እግዚአብሄር ምንም ብትነጥቀው ከእኔ ከአባቱ አይሼሽም ብሎ ተማምኖብኝ ቢሆንስ
ይሄን ሁሉ የተፈተንኩት

ገጣሚ ኤልያስ ሽታሁን
መፅሐፈ ኢዮብ 1፥6.......

የአባቶች ምክር

23 Oct, 09:57


ዘጸአት ነው

ዘጸአት ነው ለሕዝቡ፣
በደም ታሥሯል ወጀቡ፣
ጽኑ ክብርን ያየነው፣
ኢየሱስን ይዘን ነው፣
ክርስቶስን ለብሰን ነው።

በዘማሪ ገብረ ዮሐንስ ገብረ ጻድቅ

የአባቶች ምክር

23 Oct, 09:57


ዘፀአት ነው ለህዝቡ በደም ታስሯል ወጀቡ
ጽኑ ክብርን ያየነው ኢየሱስን ይዘን ነው
ክርስቶስን ለብሰን ነው (2)

🌿🕊🌿🕊🌿🕊

የግብፁ ፈርዖን በግፍ ሲያስጨንቀን
ክቡደ መዝራይት ሙሴ ተነሳና ከራምሴ
መንጋውን ይዞ ወጣ እየቀና በኀቅለ ቃዴስ በሲና

ያ መንፈሳዊ መጠጥ ያ መንፈሳዊ መብል
ክርስቶስ ነበር እኛን የሚከተል

🌿🕊🌿🕊🌿🕊

በራፍዴም እዳንቀር ተወልን ምስክር
በእያሱ ወልደ ነዌ እያዳነን ከአርዌ
ከነአን ሔደ ከፊት እየመራን
ስሙ መድኀኒት ሆነን

እስራኤል ዘነፍስ ነን ድል ባደረገው ጌታ
ኢያሪኮ ሲዖል ፈርሷል በእልልታ

🌿🕊🌿🕊🌿🕊

በፋርስ ነገሥታት ወድቆብን ባርነት
በኤርሚያስ የለወዝ በትር እየታየን በምስጢር
እንደ ብረት አምድ ቅጥር አድርጎን
የእሳቱን ወጀብ አለፍን

በምልክት በራዕይ ተስሎ በሰማይ
ማምለጫችን ሆነ በጎለጎታ ላይ

🌿🕊🌿🕊🌿🕊

ከጠላታችን መዳፍ መከራ ቢወነጨፍ
የጠበቅነው መሲህ ደርሷል
ሸክማችንም ተራግፏል
የመቤዠት ቀን ቀርቦ ዘፀአት ጠቅለን ወጣን ከሞት

በደሙ አጊጠናል እርስቱን እንወርሳለን
በጽዮን ተራራ ለበጉ እየዘመርን

የአባቶች ምክር

23 Oct, 05:34


"ይህንን ካስታወስክ በሰው መፍረድ ታቆማለህ ።
ይሁዳ ሐዋርያ ነበር።
ከጌታ ቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ ነፍሰ ገዳይ ነበር
"

አባ ዮሐንስ ዘሰዋሰው


“ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ቀራጮችና ጋለሞቶች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በመግባት ይቀድሙአችኋል።”
— ማቴዎስ 21፥31ዐ

የአባቶች ምክር

22 Oct, 18:29


“እግዚአብሔር ይማረን ይባርከንም፥ ፊቱንም በላያችን ያብራ፤”
— መዝሙር

   ✦•✥•  @father_advice •✥•✦   
  ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
           ❍ㅤ    ⎙ㅤ  ⌲     ♡          
     ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ   ˢʰᵃʳᵉ  ˡᶦᵏᵉ   

 
4444........

የአባቶች ምክር

22 Oct, 18:10


ሁሌም እግዚአብሄር
የመጀመርያ ምርጫችን ይሁን


እግዚአብሄር አማራጫችን አይደለም የመጀመርያ ምርጫችን ነው

የአባቶች ምክር

22 Oct, 13:36


ከቅዱሱ ስፍራ ከቤተክርስቲያን በቅዳሴው፣ በትምህርቱ፣ ሚስጥራቱን ሁላ ተሳትፋችሁም ሆነ  የግል ጸሎት አድርጋችሁ እንዲሁ በጎ ነገር ሰርታችሁ  ስትጨርሱ ውስጣችሁን የደስታ፣ የእረፍት፣ የተስፋ፣ አንዳች ስሜት በውስጣችሁ ከተሰማችሁ እርሱ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ  አስተውሉ ።

#ብጹዕ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
╔═F══════════A══╗
💚🌿 @Father_advice🌿  💚
╚═F══════════A══╝
                                            ♡ ㅤ⌲       
                                            ˡᶦᵏᵉ   ˢʰᵃʳᵉ

የአባቶች ምክር

22 Oct, 08:53


መምህር ኢዮብ
😔!

የአባቶች ምክር

22 Oct, 06:30


ምድራዊው ሙሽራ ሰማያዊውን ሙሽራ ወደ ሰርጉ ጋበዘው። በሰርጉ እንዲገኝ የተጋበዘው እርሱ በመንግሥቱ ቤቶችን የሚያዘጋጅላቸው ነው።

እርሱ ከነበሩት ሕዝብ ጋር ተጋባዥ ነበር እነርሱን በመልክ መስሏቸዋልና። ነገር ግን ድንቅ የሆነ ተዓምር በማድረግ በባሕሪይው ከእነርሱ የተለየ እንደሆነ አሳያቸው። ምንም እንኳን ገፅታው እነርሱን ቢመስልም በተዓምሩ ግን ከእነርሱ እጅጉን የሚልቅ አምላክ መሆኑን አሳያቸው።

እርሱ ቃል ሳይናገር ውሃውን ከሌሎች ወይን ይልቅ ምርጥ ወይን አድርጎ ቀየረው። በዚህም የወይን አስገኚ ማን እንደሆነ መርምረው አገኙት፣ በተዓምሩ  ደስ ተሰኙ። ምንም እንኳ እንደ እንግዳ ተጋባዥ ቢሆንም የሰርጉ ጌታ እርሱ እንደሆነ ለማሳየት እንዲህ አደረገ። ጉድለታችንን የሚሞላ እርሱ መሆኑን ሊያሳየን ስለፈለገም የአሳላፊዎቹን ጉድለት በመሙላት ገለጠው። 

[ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ - ዲያቴሳሮን ]

የአባቶች ምክር

21 Oct, 16:14


በነገራችን ላይ "እሷ እኮ በጣም ሐሜተኛ ናት"
ማለትም ሐሜት ነው
" ባልንጀራውን በቀስታ የሚያማን እርሱን አሳደድሁ " መዝ 101፦5

የአባቶች ምክር

21 Oct, 06:00


"የማምነውና ተስፋ የማደርገው በምትሐት ወይም በማስመሰል ሳይሆን ስለ እኔ በእውነት ሰው በሆነውና በሞተው በኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ "

ቅዱስ አግናጥዮስ

የአባቶች ምክር

20 Oct, 18:32


ለምንድን ነው ሰው ያሰበውን ሳይሆን ያላሰበውን ሰው የሚያገባው?

የአባቶች ምክር

20 Oct, 16:26


ውድ ወንድሜ

እንዲያልፍህ የተፃፈ አያገኝህም
አግኝቶ እንዲያስተምርህም የተፃፈ አያልፍህም
ስለዚህ

አትጨነቅ

የአባቶች ምክር

20 Oct, 03:33


ፍቅር ብዙ ጥፋቶችን ይቅር ይላል
ጥላቻ ግን የሌሉ ጥፋቶችን እንኳን ሊኖሩ ይችላሉ
እያለ ያስባል።

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ

የአባቶች ምክር

19 Oct, 17:48


አንድ ሰው መጥቶ ለአንድ ቅዱስ አባት ጥያቄ አቀረበለት

"ተአምር መሥራት እፈልጋለሁ ፣ እንዴት ላድርግ?"
ቅዱሱ አባት መለሰለት

"አንድን ሰው ወንጌል እንዲያነብ ካስተማርከው ዓይን አበራህ ማለት ነው

ድሆችን እንዲረዳ ካስተማርከው ሽባውን አዳንክ ማለት ነው

ወደ ቤተ ክርስቲያን መሔድ እንዲችል ካደረግህ አንካሳውን ፈውሰሃል

ሙት ማንሣት ከፈለግህ ደግሞ ንስሓ እንዲገባ አድርገው ያኔ የሞተ ሰውን አስነሥተሃል ማለት ነው
በል ሒድና ተአምር ሥራ!"

⛪️⛪️⛪️⛪️

ለልጆቻችን ክርስቶስ ማን እንደሆነ እኛ ካልነገርናቸው ዓለም ክርስቶስ ያልሆነውን ሁሉ ይነግራቸዋል።

⛪️⛪️⛪️⛪️

"ፍቅር እንዴት መቆጣት እንዳለበት አያውቅም"
ቅዱስ ማር ይስሐቅ

⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️

ኃጢአተኞች በሌላ ኃጢአተኛ ላይ ከእነርሱ ለየት ያለ ኃጢአት ስለ ሠራ ይፈርዱበታል ፣ ወይም ተመሳሳይ ኃጢአት ቢሠራም ይፈርዱበታል።
⛪️⛪️⛪️⛪️

“የሚጾሙ የሚጸልዩና የሚተጉ ድቃቂ ሳንቲም እስካላስወጣቸው ድረስ በምንም ነገር ላይ የሚገኙ በችግር ላይ የሚሰቃዩትን ግን ዞር ብለው የማያዩ ብዙ ሰዎችን አውቃለሁ" ቅዱስ ባስልዮስ

⛪️⛪️⛪️⛪️

"እኛ መነኮሳት ነን:: እኛ የሠለጠንነው ሰዎችን ለመግደል ሳይሆን ምኞታችንን ለመግደል ነው" አባ ጴኤሜን

★ ★ ★
አባታችን ሆይ እንዴት ትላለህ?

እንደ ልጅ ካልኖርህ እንዴት "አባት" ትለዋለህ?
ሌላውን ጠልተህ ራስ ወዳድ ከሆንክ እንዴት አባት "አችን" ብለህ በአንድነት ትጠራዋለህ?
ምድራዊ ነገር ብቻ እያሰብህ እንዴት "በሰማያት የምትኖር" ትለዋለህ?
ልብህ ከእርሱ ርቆ በአንደበትህ ብቻ እየጠራኸው "ስምህ ይቀደስ" እንዴት ትለዋለህ?
ሥጋዊና መንፈሳዊውን እየቀላቀልህ "መንግሥትህ ትምጣ" ለምን ትለዋለህ?
መከራን በጸጋ የማትቀበል ከሆነ "ፈቃድህ ይሁን" ለምን ትላለህ?
ለራስህ ሆድ እንጂ ለተራቡት ግድ የማይሰጥህ ከሆነ ለምን "እንጀራችንን ሥጠን" ትላለህ?
በወንድምህ ላይ ቂም ይዘህ "እኛም የበደሉልን ይቅር እንደምንል" እንዴት ትላለህ?
የኃጢአትን አጋጣሚዎች ሳትሸሽ "ወደ ፈተና አታግባን" እንዴት ትላለህ?
ክፉን ለመቃወም አንዳች ሳታደርግ "ከክፉ አድነን" እንዴት ትላለህ?
ጸሎቱን ከልብህ ሳትሰማውስ እንዴት አሜን ትላለህ?

ምንጭ: Orthodox Notes (ON)
ትርጉም: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

የአባቶች ምክር

18 Oct, 16:11


አንድ ጊዜ መነኮሳት ስለ አንድ መነኩሴ እያመሰገኑ ለአባ እንጦንስ ነገሩት ያ መነኩሴም በመጣ ጊዜ ምስጋና የሚቀበለውን ያህል ሲሰድቡት ምን ያህል እንደሚታገስ ለማረጋገጥ በክፉ ቃል ተናገረው

መነኩሴው ግን አብዝቶ ተቀየመ በዚህ ጊዜ አባ እንጦንስ
"አንተ ከውጭ በልዩ ልዩ ጌጥ የተዋበ ውስጡን ግን ሌቦች የዘረፉት
መንደር ትመስላለህ" አለው!


እኔ ሀጢአተኛ ነኝ እያልን በሰዎች በመሐል ትሁት ለመምሰል እንጥር ይሆናል፣እውነተኛ ትህትና ሰዎች ስለ እኛ ክፉ በሚናገሩበት ጊዜ እና እኛን የሚያናድድ ነገር በሚተገብሩት ጊዜ በምናሳየው ሁናቴ ይታወቃል

         መተውን እንልመድ!

የአባቶች ምክር

17 Oct, 21:35


“እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።”
— ማቴዎስ 7፥1-2

“አትፍረዱ አይፈረድባችሁምም፤ አትኰንኑ አትኰነኑምም። ይቅር በሉ ይቅርም ትባላላችሁ።”
— ሉቃስ 6፥37

“በእምነት የደከመውንም ተቀበሉት፥ በአሳቡም ላይ አትፍረዱ።”
— ሮሜ 14፥1



አትፍረዱ

የአባቶች ምክር

16 Oct, 14:49


የባንክ accountsሽ ውስጥ 10ሺ እንኳን ብር ሳይኖር መኪና የሌለው ወንድ አላገባም አትበይ የምታገቢው ድህነትሽን ለማራገፍ አይደለም። መጀመሪያ ራስሽን ቻይ! ይሄ የጥገኝነትሽ መንፈስ ብር ያለው ክፋ ሰው ጋር ሳይጥልሽ አይቀርም እና ተጠንቀቂ/ቅ

© social media

7,233

subscribers

676

photos

84

videos