꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂ @eyuelsolomonks Channel on Telegram

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

@eyuelsolomonks


꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂ (Amharic)

ሰላማዊ ምስጢር፣ በቤተክርስቲያን አስተምህሮ አንዳች ነው እና ሰውታም ሰፊውን ነው እና ለሌሎች የምትታይ መረጃዎች የሚመለከተው። ይህ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ የመረጃ መጠን ሲነድም ስለሆነ፣ የአስተምህሮ አጠቃቀም እና መግለጫ እንዲሆን እና እናት ልጅዎትን ለእግዚአብሔር ሲተፋት። ከዚህም፣ በመስሪያ ቤተክርስቲያን በጥናት አንደኛውን የምስራቅ አቅንግቦ ታቅደም። ቤተክርስቲያን አስተምህሮ አስረክቦት ወይም ከተወቅታ እንደሚውል ስለሆነ ልጆቻችን እንኳን ለእግዚአብሔር ሲተፋት አንድ ደቂቃ ክፍል ማድረግ ይችላል።

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

30 Jan, 11:49


  ✥  ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ፡፡” [ዕዝ. ሱቱ. 2:1]                       
በመላእክት ከተማ በራማ ካሉት ሦስት ነገዶች ውስጥ አንዱ ነገድ ሥልጣናት ይባላል፡፡ በሥልጣናት ላይ ከተሾሙ ሊቃነ መላእክት ውስጥ አንዱ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሱርያል ይባላል፡፡ ሱርያል የሚለው ስም በአንዳንድ ድርሳናት ካልሆነ በስተቀር እምብዛም አይታወቅም፡፡ ትርጉሙም ‹‹ዐለቴ እግዚአብሔር ነው›› ማለት ነው፡፡ ሱርያል የቅዱስ ዑራኤል ሌላ ስሙ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያንም በስፋት የሚተወቀው ስም ዑራኤል የሚለው ስም ነው፡፡ [ድርሳነ ዑራኤል 1991 ገጽ 14]

ዑራኤል ማለት “ብርሃነ እግዚአብሔር” ማለት ነው። “ዑራኤል ሥዩም ላዕለ ኵሎሙ ብርሃናት፤ ዑራኤል በብርሃናት ላይ ሁሉ የተሾመ ነው” እንዲሁም “ዑራኤል አሐዱ እመላእክት ቅዱሳን እስመ ዘረዓም ወዘረዓድ፤ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ ዑራኤል በመብረቅና በነጎድጓድ የተሾመ ነው” እንዲል፡፡ [ሄኖክ 6፥2] ከሊቃነ መላእክት አንዱ መሆኑንና ፍርሃት ረዓድ ላለባቸው ረዳታቸው እንደሆነ የመላእክትን ነገር የተናገረ ሄኖክ ነግሮናል፡፡ “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል” በማለት ነቢዩ ዳዊት እንደተናገረ እግዚአብሔርን በሚፈሩና በሚያከብሩት ሰዎች ጭንቀት ጊዜ በመካከላቸው እየተገኘ ያጽናናቸዋል። [መዝ.33፥7]ምሥጢር ይገልጥላቸዋል፤ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይጠብቃቸዋል።

አንድም ዑራኤል የሚለው ስም “ዑር” እና “ኤል” ከሚሉ ኹለት ቃላት የተመሠረተ ነው። ዑራኤል ማለት ትርጉሙ “የብርሃን ጌታ”፣ ”የአምላክ ብርሃን” ማለት (እግዚአብሔር ብርሃን ነው) ማለት ነው። "በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ 7 መላእክትን ዐየሁ" [ራዕ. 8፡2] እንዳለ ሊቃነ መላእክት በቊጥር 7 ናቸው። ቅዱስ ዑራኤልም ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው። በመሆኑም መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። [መ.ሄኖክ. 6፥2] ምስጢረ ሰማይና እውቀትንም ኁሉ ለሄኖክ የገለጸለት የፀሐይን የጨረቃን የከዋክብትንና የሰማይ ሰራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለሄኖክ ነግሮታል። [መ.ሄኖክ 28፥13] “ቅድስት ድንግል ማርያምን፣ ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ የመራ፤ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ በተሰቀለ ጊዜ፣ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ፣ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨ፤ እውቀት ለተሰዎረባቸው ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን ያጠጣ፤ ኢትዮጵያዊውን ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መርካታ ቅዱሳት መጻሕፍትን አንዲደርሱ ያገዘ፣ የረዳና የዕውቀት ጽዋን ያጠጣ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡

የመልአኩ ዓመታዊ ክብረ በዓላት
• ጥር 22 በዓለ ሲመቱ፣
• መጋቢት 27 የጌታችንን ክቡር የሆነ ወርቀ ደሙን ለዓለም የረጨበት ነው፡፡
• ሐምሌ 21 እና 22 ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የእውቀት ጽዋ ያጠጣበት ቀን ነው።

አፈቅሮ ፈድፋደ፡- ዑራኤል ሆይ፣ ከመልኮች ሁሉ ይልቅ ያንተን መልክአ ጸሎት እወዳለሁ፡፡ የመልክህ ስነ ጸዳል በደመ ወልድ እግዚአብሔር የታተመ ነውና፡፡
ዑራኤል ሆይ፣ እግዚአብሔር ኃይሉን የሚገልጽብን መልአከ ብርሃናት አንተ ነህ፡፡ በዕለተ ሥቅለት በደመ ወልድ ዓለምን ለመቀደስ ከሁሉ ይልቅ አንተ ተሰይመሃልና፡፡ ስለክብርህ የሰማይ መላእክት አደነቁ፡፡

ለተፈጥሮትከ፡-
ዑራኤል ሆይ፡- ያለ መናገር በጥንት አርምሞ ከነፋስና ከእሳት ለተፈጠረ ተፈጥሮህ ሰላም እላለሁ፡፡ ዑራኤል ሆይ የተፈጥሮና የይቅርታና የቸርነት ክቡር መልአክ ነህና ስለኛ ስለሰው ልጆች ወደ ልዑል እግዚአብሔር ማልድ አማላጅነትህ ዘወትር ከጥፋት ያድናልና፡፡

ለዝክረ ስምከ፡-
ዑራኤል ሆይ፡- ከማርና ከወተት ይልቅ ለሚጥመው ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ፡፡

ዑራኤል ሆይ፡- ክፍልህ /ክንፍህ/ በደመ ወልድ እግዚአብሔር የተከበረ /የታለለ/ ነውና፡፡ ለዓለሙ ሁሉ መድሃኒት ትሆን ዘንድ ግሩም የሚሆን የእግዚአብሔር ሥልጣን በክብር ከፍ ከፍ አደረገ፡፡ [መልክአ ዑራኤል]

በአምላኩ አማላጅነቱን ኑና ተማጸኑት። በጸሎቱ ለተማጸነ ከአምላኩ በረከትን ምህረትን የሚያሰጥ አዛኝ እርሩህ መልአክ ነው። የቅዱስ ዑራኤል በረከት በኁላችንም ላይ ይደር!! አሜን።

                            ✥••┈••●◉  ✞  ◉●••┈••✥

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

29 Jan, 07:32


ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ

ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በስድሳ አራት ዓመቷ ከሞት ወደ ሕይወት ከመከራ ወደ ደስታ የተሸጋገረችበት ዕለት ነው፡፡

ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ ያሬድም “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ” ትርጉሙ ሞት ለማናኛቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል፡፡ በማለት አደነቀ፡፡ በመሆኑም በዓሉ የወላዲተ አምላክ በዓለ ዕረፍት ከመሆኑ የተነሳ ታላቅ በረከት የሚያስገኝ ስለሆነ በየዓመቱ ይከበራል፡፡
... የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉስድሳ አራት ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ ጥር 21 እሁድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላዕክቱን አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት፡፡ ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁ አለችው፡፡ በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት፡፡ እኚህን ከማርክልኝስ ይሁን አለችው፡፡ ቅድስት ሥጋዋን ከቅድስት ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በዝማሬ መላእክት አሳረጋት፡፡ ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት በደመና ጠቅሶ ካለችበት አድርሶ እመቤታችሁን ቅበሩ አላቸው፡፡ ከመካከላቸው አንዱ ታውፋንያ ዘሎ ያልጋውን ሸንኮር ያዘ፡፡ የታዘዘው መላእክት መጥቶ በሰይፍ ኹለት እጁን ቀጣው፡፡ በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት ድኖለታል፡፡ ከዚህ ቦሃላ ዮሐንስን ጨምሮ ከመካከላቸው ነጥቆ በእጸ ሕይወት ሥር አኑሯታል፡፡

አንድም በዓሉ-፡ እግዚአብሔር ወልድ በሰውነት ተወልዶና ማንነቱ በይፋ ታውቆ በተገለጠበት በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር የ“አስተርእዮ ማርያም” ተብሏል፡፡ አስቀድመው ዐሥራ ኹለቱም ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል ወደ ዓለም ሁሉ ተበትነው ነበርና በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ሁሉም ደመናን ጠቅሰው ወደ ኢየሩሳሌም መጡ፡፡ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ መርቶ አመጣቸው እንጂ ለምን እንደመጡ አያውቁም ነበር፡፡ እመቤታችንም ለምን እንደመጡ ጠየቀቻቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም፡- “ጸጋን የተመላሽ ቅድስት ሆይ! የመምጣታችን ምሥጢርማ እኛ አንቺን እንጠይቅ እንጂ አንቺም እኛን ትጠይቃለሽን? ሁላችንም ለምን እንደመጣን አናውቅም፡፡ ለምሳሌ እኔ አስቀድሜ በአንጾክያ ነበርኩኝ አሁን ግን እነሆ እዚህ ነኝ፡፡ ለምን እንደመጣሁኝ ግን አላውቅም” አላት፡፡ እርሷም ሁሉም በአጠገቧ በተሰበሰቡ ጊዜ የሚሆነውን ነገር አስቀድማ ከልጇ ከወዳጇ አውቃ ተዘጋጅታ ነበርና ለምን እንደመጡ (ዕረፍተ ሥጋዋን ለማየት እንደሆነ) ነገረቻቸው፡፡ ሌሊቱንም በሙሉ በጸሎትና በማኅሌት ደግሞም በዝማሬ ሲያመሰግኑ አደሩ፡፡ ከዚህ በኋላ የተወደደችው እናት በረከቷን አሳድራባቸው በሰላም አንቀላፋች፡፡ ነፍሷም በዐብይ ዕልልታና በታላቅ ምስጋና በመላእክት እጅ ወደ አምላኳ ሄደች፡፡ ኋላ ሐዋርያቱ ዮሐንስን ሲያገኙት፡- “እመቤታችን እንደምን ሆነች?” አሉት፡፡ እርሱም “በገነት በዕጸ ሕይወት ሥር ዐርፋለች” አላቸው፡፡ የቀሩት ሐዋርያት “ዮሐንስ ያን ድንቅ የእግዚአብሔርን ሥራ አይቶ እኛስ ሳናይ እንዴት እንቀራለን?! አቤቱ ለእኛም ቸርነትህን አድርግልን” ብለው በነሐሴ መባቻ በአንድነት ሆነው ወደ ፈጣሪያቸው የሚቀርብ የአንድ ሳምንት ጾምና ጸሎት ጀመሩ፡፡ በኹለተኛው ሱባዔ ማብቂያ ዕለት ነሐሴ 14 ቀን እሑድ የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ መልአኩ ከገነት አምጥቶ ለሐዋርያቱ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ልመናቸው ስለ ተፈጸመላቸው ፈጣሪያቸውን በጸሎት አመስግነው በዚያችው ዕለተ እሑድ ቅዱስ ሥጋዋን ወስደው ቀብረውታል፡፡ እርሷም በሦስተኛው ቀን ነሐሴ 16 ቀን ማክሰኞ ተነሥታለች፡፡ ትንሣኤዋ “ከመ ትንሣኤ ወልዳ- እንደ ልጇ ትንሣኤ” ያሰኘው ይህ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይታ የመነሣቷ እውነታ ነው፡፡

የአዛኚቱ ድንግል አማለጅነትና በረከት አይለየን፡፡ ሁላችንም ባለንበት ይህ ታላቅ በዓሏን እያሰብን ጸልየን የበረከቷ ተካፋዮች እንሆን ዘንድ ልዑል እግዚአብሔር ይርዳን አሜን፡፡ መልካም በዓል!!

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

28 Jan, 05:47


https://youtu.be/CICragXPeDg?feature=shared

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

26 Jan, 22:21


በዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ዘመንም ቢሆን በጥንታዊ ታሪክ እንደተገለጸው በዶዎሮ ክፍለ ሀገር አርዌ በድላይ የተባለ የአረመኔዎች መሪ የነበረ ብዙ ወታደሮች ሰብስቦ ዘርዓ ያዕቆብን ሊወጋው ተነሥ። ዓፄ ዘርአ ያዕቆብም የቅዱስ ጊዮርጊስን ጽላት ይዞ ሠራዊቱን አስከትቶ ዘመተና ጠላቱን ድል መቶ ተመለሰ። ይህንንም የዘርዓ ያዕቆብ ጸሐፊ ትእዛዝ የነበረው መርቆርዮስ ከዘርዓ ያዕቆብ ታሪክ ጋር መዝግቦታል። ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ነገሥታት በሚዝምቱበት ታላላቅ ዘመቻዎች ሁሉ የቅዱስ ጊዮርጊስን ጽላት ትተው አይንቀሳቀሱም ነበር። ይህንን እውነት ለማረጋገጥ ቢፈለግ በዐድዋ ላይ ከኢጣልያ ጦር ጋር በተደረገው ውግያ ማለትም የአድዋ ጦርነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ያደረገው ታአምራዊ ተሳትፎ ኢትዮጵያን በዓለም ታሪክ በጦር ኃይል ፲ጊዜ እጥፍ የሚበልጣትን አገር አሸንፋ ታዋቂ የነፃነት አገር እንድትባል ያደረጋትን ታሪክ መመልከት ይበቃል። ይህም ዳግማዊ ዓፄ ምኒሊክ ወደ ዐድዋ ሲዘምቱ በአራዳ ገነተ ጽጌ ቤተ ክርስቲያን የሚገኘውን የቅዱስ ጊዮርጊስን ጽላት አስይዘው ዘመቱ። ጦርነቱም እንደተጀመረ ቅዱስ ጊዮርጊስ የእርዳታ እጁን ዘረጋ በዛም ጊዜ ብዙ የጠላት ሠራዊት አለቀ። ጠላትም እንደመሰከረው አንድ በነጭ ፈረስ ላይ የተቀመጠ ጅግና ነው የፈጀን ብለዋል በወቅቱ የነበረ አንድ የኢጣልይ ጋዜጠኛ ወደ አገሩ ባስተላለፈው ዘገባ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ሠራዊት ጎን ተሠልፎ የኢጣሊያን ሠራዊት አርበደበደው የምንዋጋው ከሰው ጋር ብቻ ሳይሆን ከእግዚአብሔርም ጋር ሰለሆነ በጦርነት ድል ልንመታ ችለናል ሲል አስተላልፏል። በዚህም የተነሣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነቱን ፈጥኖ ደራሽነቱን ስለት ሰሚነቱን አማላጅነቱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን ስለሚያምኑበትና ስለሚወዱት ጽላቱ በተተከለበት ቤተ ክርስቲያኑ በተሠራበት በዓሉ በሚከበርበት ስሙ በሚጠራበት ሥፍራ ኁሉ እየተገኙ በጸሎትና በምስጋና ያስቡታል።

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

26 Jan, 22:20


ቅዱስ ጊዮርጊስ (ሰማዕት)
ቅዱስ ጊዮርጊስ አባቱ አንስጣቴዎስ (ዘሮንቶስ) ይባላል። እናቱም ቴዎብስታ ትባላለች የዘር ሐረግዋም ከፍልስጥኤም ወገን ነው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ጥር ፪ ቀን ፪፻፸፯ ዓም ተወለደ የተወለደባትም ቦታ ቀጰዶቅያ ትባላለች።

ቅዱስ ጊዮርጊስ የሰማዕታት አለቃ, ታላቁ ሰማዕት ...
ቀጰዶቅያም በትንሹ ምሥራቃዊ እስያ(እንደዛሬ አጠራር መካከለኛው ምሥራቅ) ትገኛለች ከሮም ገናና መንግሥት በፊት በፋርስ መንግሥት ሥር ነበረች። ጊዮርጊስም የፋርስ ሰማዕት የሚባለው በዚህ ምክኒያት እንደሆነ ይነገራል ይህችኑ ሀገር ግሪኮችና ሮማውያን በቀኝግዛት ይዘዋት እንደ ነበር ታሪክ ያብራራል። በዚህ አኳኋን አንዳንድ ሰዎች ቅዱስ ጊዮርጊስን የግሪክ ተወላጅ ነው ሲሉ ሎችም ደግሞ የሮማ ተወላጅ ነው ይላሉ ጥቂቶችም የእንግሊዝ ዜጋ ነው ይላሉ ለዚህ ሁሉ ከአፈ ታሪክ በስተቀር ብዙ ጊዜ ተመራምሮ እስካሁን ድረስ በቂ ማስረጃ አልተገኘም። ከዚህም የተነሳ ጊዮርጊስ የዚህ ሀገር ተወላጅ የዚያኝው ሀገር ዜጋ ነው የሚል አነጋገር ቢሰጥ አያስደንቅም ምክኒያቱም የሥራ ሰውንና ጅግናን ማንም ሰው የሱ ዜጋ እንዲሆን ሰለሚፈልግ ነው።

ይሁን እንጂ በዚያን ዘመን ወታደርነት ተፈላጊ ሙያ ስለነበር ቅዱስ ጊዮርጊስም ወታደር ሆኖ ብዙ ጀብዱ ፈፅሟል በወጣትነቱም የውትድርናን ሥራ እንደሠራ በግሪክና በኮብትና በሶርያ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ተጽፏል ይልቁንም በመጽሐፈ ስንክሳርና በራሱ ገድል ተብራርቶ ይገኛል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ለጥቂት ጊዜ በወታደርነት ከሠራ በኋላ የክርስቶስ ወታደር ሆኖ ቤተ ክርስቲያንን ያገለግል ጀመረ።

• ቅዱስ ጊዮርጊስ በድዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግሥት
በድዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግሥት ስለ ክርስትና ሃይማኖት ብዙ ተጋድሎ አድርጓል። ወንጌልንም አስተምሮ ያላመኑ ሰዎችን ወደ ክርስትና እምነት መልሷል ገድሉ እንደሚለው ቢሩታይትን የተባለችውን ልጃገረድ ድራጎን ለተባለው አውሬ ግብር እንድትሆን ቀርባ ሳለች ዘንዶውን በጦር ወግቶ ገድሎ እሷን ከመበላት አድኗታል። ይህንንም ዘንዶ ሰዎች ሁሉ አምላክ አድርገው ስለሚያመልኩት በተወሰነ ጊዜ አንዳንድ ከወንድም ከሴትም ወጣት እየመለመሉ ያቀርቡለት ነበር። አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ተንታኞች ግን በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ታሪክ አንዲት ልጃገረድን ከድራጎን እንዳዳነ የተመዘገበውን ጽሑፍ ልዩ ትርጉም ሰጥተውታል። አባባላቸውም በዘመነ ሰማዕታት ፪፻፹ ዓ/ም-፫፻፭ ዓ/ም ድረስ በክርስቲያን ሴቶች ልጆች ላይ ብዙ ግፍ ይፈፀም ነበር። ከዚያም የተነሣ አንድ ግፈኛ መኮንን በአንዲት ልጃገረድ ላይ ግፍ ሊፈፅምባት ሲሞክር ጊዮርጊስ ደርሶ ገድሎ ልጃገረዲቷን ከሞት አዳናት። ይህም ታሪክ በምሳሌያዊ አነጋገር ቀረበ ነገር ግን ከጊዮርጊስ ሥዕል ጋር የሚታየው ድራጎን በዓለም ላይ የሌለ አውሬ ነው ተብሎ ተገምቷል በግልጽ አነጋገር ዮሐንስ በራእዩ እንዳየው ዘንዶ ምሳሌያዊ መልክ ነው ማለታቸው ነው። ይህንን አባባል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ብቻ ሳትሆን የግብፅ የአርመን የሶርያ የግሪክ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ይቃወሙታል።

ቅዲስ ጊዮርጊስ ድራጎኑን ከገደለ በኋላ ሥራው ባገር ሁሉ ታወቀ በዚያም ዘመን ክርስቲያኖች በየቀኑ እየተገደሉ በየሜዳው ይጣሉ ስለነበር በፈረሱ ጭኖ እየወሰደ እንዲቀበሩ ያደርግ ነበር። በሕይወት ያሉትንም እየተዘዋወረ ያጽናናቸውና በእምነታቸው እንዲተጉ ወንጌልን ያስተምራቸው ነበር። በተጨማሪም የግፍ ሞት ከሚፈፀምበት አደባባይ የደከሙትን ሽማግሌዎችንና አሮጊቶችን እንዳይፈጁ በፈረስ ወደ ሌላ ሥፍራ ያሸሻቸው ነበር ፈረሰኛው ጊዮርጊስ የሚሰኘውም በዚህ ምክንያት ነው።

ስለ ክርስትና እምነት የተጻፉት የቤተክርስቲያን ንዋየ ቅዱሳትንም በየዋሻው መሬት እየቆፈረ ደብቆ በመቅበር ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፉ አድርጓል በጠቅላላ በተፈጥሮና በትምህርት ችሎታ በእግዚአብሔር ጸጋ መንፈስ ቅዱስ የተመላ ሰው ስለነበር ስለ እውነት ስለ ኢየሱስ ፍቅር ስለ ሰላም ስለ እኩልነት ስለ ፍትህ ተጋድሏል ይህም ሁሉ በቤተክርስቲያን ስጦታዊ ታሪክ ወርቃዊ ስጦታ ታእምራዊ ሰማዕት ተብሏል። በርግጥም ስለ እውነት ስለ ሰላም የሚመሰክር ሰው ተአምረኛው ሊያሰኘው ይገባል።

ይህም መንፈሳዊ ተጋድሎው ከ፪፻፷-፫፻፵ ዓ/ም የነበረው የቤተክርስቲያን አባት የሆነው አውሳብዮስ ዘቂሣርያ ቅዱስ ጊዮርጊስን ብርቱና ጠንካራ ሰማዕት እንደሆነ መስክሯል የአውሳብዮስ መጽሐፍ ፰-፲። ቅዱስ ጊዮርጊስ ብዙ ዘመን ስለ እምነቱ ስለ ሀገሩ ነፃነት ስለ እኩልነት ስለ ሰላም ስለ ፍትህ ስለ ወንጌል መስፋፋት ስለ ቤተክርስቲያን ዕድገት ታማኝ ምስክርነትን በየአድባባይ እየመሰከረ ለሰባት ዓመታት ያህል እየታሰረ እየተሰቃየ እየተገረፈና እየተወገረ ጽኑ ተጋድሎ ከፈፀመ በኋላ የመንፈስ ዐርበኝ እንደመሆኑ መጠን የመከራውን ሸለቆ ተሻግሮ ከሕይወት ወደብ ደርሶ ምእመናን እየተያዙ በሚገደሉበት በዱዲያኖስ ዘመን መንግሥት በ፫፻፫ ዓ/ም ሚያዝያ ፳፫ ቀን ልዳ በሚባለው ሀገር በሰማዕትንት ዐረፈ በዚህም ብዙ የታሪክ ጸሐፊዎች ተስማምተውበታል። ስለ ዜና ቅድስናው ከላይ በተገለፀው መሠረት ቅዱስነቱ ወይም ቅድስና ያለ ሥራ ሊሰጥ ባለመቻሉ ከነአውሳቢዮስ ዘመን ጀምሮ የቅዱስ ጊዮርጊስ የሥራ ታሪክ ጥናት ተጀመረ። ቅዱስ የተባለውን ስም ለማግኘት በሥራና በአካሄድ ክርስቶስን መምሰል እንደሱ ሌላውን ማገልገልና ለራስ ሳይሆን ሰለ ሌላው መኖር ያሻል ስለ ሌላው ተላልፎ መሞት መከራን መቀበል መሰቀልንም መሸከም በሰው ፊት መመስከርና ራስን መካድ ያስፈልጋል።

ቅዱስ ጊዮርጊስም ይህን ሁሉ ተግባር ሠርቶ በመገኘቱ ብዙ ምስክር ተገኝቶለት በ፮ኛው መቶ ዘመን በደቡብ ሶርያ በምትገኘው አድራ ወይም (ይድራስ) በተባለች ቤተክርስቲያን ተሰብስበው የቤተክርስቲያን አባቶች እውነተኛ ሰማዕትነቱንና ቅድስናውን በጉባኤ አጽድቀው ውሳኔውን ለሕዝብ አስተላልፈዋል። በ፩ሺህ፺፮ ዓ/ም ደግሞ በአንጾኪያ በተደረገው የሃይማኖት ጦርንት በራዕይ እንደታየ ተረጋግጦ ስመ ገናና መሆን ጀመረ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ደሞ ማርያም ልጇን እየሱስ ክርስቶስን ይዛ በምትታይበት ስዕል ሥር "አክሊለ ፅጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀፀላ መንግሥቱ አንቲ ሁሉ ታስግዲ ሎቱ ወለኪሰ ይሰግድ ውእቱ" ተብሎ ይጻፋል።

•ቅዱስ ጊዮርጊስ በኢትዮጵያ
ወደ ኢትዮጵያ ጽላቱ የገባው ብ፲፫ኛው ክፍለ ዘመን በዐፄ ዐምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት እንደነበር ከክብረ ነገሥት መረዳት ይቻላል። በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳም ውስጥ ብዙ ዐመታት የኖሩ አባ ልዑለ ቃል የተባሉ መነኩሴ ከሶርያ ደብረ ይድራስ ከሚባለው ገዳም የቅዱስ ጊዮርጊስን ጽላት ከገድሉ ጋር አምጥተው ለዐፄ አምደ ጽዮን አስረከቡ ዐፄውም ቤተ ክርስቲያን አሠራለት ገድሉም ከዐረብኛ ወደ ግእዝ ተተርጎመ። ዐምደ ጽዮንም የጊዮርጊስን ጽላት አስይዞ ከጠላቶቹ ጋር በመግጠም ዐሥር ታላላቅ ዘመቻዎችን በድል አድርጊንት ተወቷል። ከአንዳንድ የታሪክ ዘጋቢዎች እንደተገለጸው ዐፄ አምደ ጽዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ አማላጄና ረዳቴ ስለሆነ አረመኔዎች ድል ሊያደርጉኝ አይችሉም እያለ በቅዱስ ጊዮርጊስ አማላጅነትና ረዳትነት አብዝቶ ያምን ነበር።

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

17 Jan, 14:40


꧁༒ ቃል ከሰማይ ለመናገር በመጣ ጊዜ እሳት ባሕሩን ከበበው ༒꧂

እንኩዋን አደረሳችሁ!

https://youtu.be/MalZqxlM9Mo?si=S9fWZvqr8FT9xdiE

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

17 Jan, 09:57


ስለ ጥምቀት ታሪክና ምስጢር በብሉይ ኪዳን
አብርሃም ለዐምስቱ ነገሥተ ሰይሞ ረድቶ አራቱን ነገሥተ ኮሎዶጎምርን ወግቶ ድል ነሥቶ ሲመለስ ኃይል ቢሰማው ልጅኀን ከሰማየ ሰማያት ይወርዳል ከድንግል ማርያም ይወለዳል ብለህ ነበር፤ ከዚኽ ዘመን ደርሼ፤ የቃሉን ትምህርት የእጅን ታምራት አያለሁን? ይቀርብኛል ብሎ ጸለየ፡፡ ከጌታም ከማረከው ከዐሥር አንዱን ይዘኽ ዬርዳኖስን ተሻግረኽ ከመልከጼዴቅ ዘንድ ድረስና አምሳሉን ታያለህ እንጂ ከዘመኑስ አትደርስም አለው፡፡ መልከ ጼዴቅንም አብርሃም ይመጣልሃልና ኀብስተ አኮቴትን፤ ጽዋዓ በረከትን ሰጠው አለው መልከ ጼዴቅም ቡሩኩ ቅዱሱ ለእግዚአብሔር÷ የእግዚአብሔር ወዳጅ ብሎ ሰጠው [ዘፍ 14:17-18]፡፡ አብርሃም ኀብስቱንም በልቶ ወይኑን ጠጥቶ፤ ከዐሥር አንዱን ሰጠው፡- ዬርዳኖስ የጥምቀት፤ አብርሃም የምእመናን፤ መልከ ጼዴቅ የካህናት፤ ኀብስተ አኰቴቅ ጽዋዓ በረከት የሥጋው የደሙ አምሳል ነው፤ አብርሃም ዬርዳኖስን ባይሻገር መልከ ጼዴቅን ባላወቀውም ነበር ምዕመናንም ባይጠመቁ ሥልጣነ ክህነትም ባላወቁ ነበርና ሥልጣነ ክህነትን ለማሳወቅ በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡                                                           
                                                             
አብርሃም ለመልከ ጼዴቅ አብርሃም ዮርዳኖስን ተሻግሮ ባይኄድ መልከ ጼዴቅን ባላወቀውም ነበር፡፡ [እንዳለ ቄርሎስ]
ኢዬብም ደዌ ሥጋ ታም ሳለ÷ ከጌታዬ ከፈጣሪዬ የሚያወቃቅሰኝ ጽኑ ዳኛ÷ የውል ሽማግሌ አይገኝም እንጂ ባይገኝስ በጥሬ ዱቄት ባንድ ኹለት በተከፈልኹት ነበር አለ ጌታም ከአምላክ መዋቀስ÷ ትችላለህን? መወቃቀስስ ይቅርና ምድርን በምን ላይ ዘርግቻታለሁ፤ አቁሜያታለሁ መጠኗስ ምን ያህል ነው ቢለው አቤቱ እንዲህማ ካልከኝ አፌን በእጄ እይዛለሁ እንጂ አለው ፡፡ [ኢዮብ 38 ÷4] ተሰዓሎ እግዚአብሔር በደመና ወበዓውሎ ….. ጌታም የኢዮብን ትሕትና ዓይቶ በዮርዳኖስ ታጠብ አለው ቢታጠብ ከደዌ ተፈወሰ፡፡ ዮርዳኖስ የጥምቀት ኢዮብ የምዕመናን ደዌው የመርገመ ሥጋ የመርገመ ነፍስ አምሳል ነው፡፡ 

ኢያሱ ለእሥራኤል ምድረ ርስትን ለማካፈል ሲኄድ ዮርደኖስ ምልቶ አገኘው ከዳር ቆም ቢጸልይ ጌታ ካህናቱን ታቦትን ተሸክማችሁ ቁሙ በላቸው አለው፡፡ ተሸክመው ቢቆሙ የላዩ ወደላይ የታቹ ወደታች የሦስት ቀን መንገድ ሸሸ፡፡ ወተገብሩ ኰሉ ሕዝብ አዲወ ዮርዳኖስ ዬርዳኖስን ለመሻገር ኹሉም አንድ ኹነው ገቡ እንዲል ዐሥራ ኹለቱ ነገደ እሥራኤል ዐሥራ ኹለቱ ድንጋይ ይዘው ተሻገሩ ካህናቱ አንዱ እግራቸው ከውስጥ አንዱ እግራቸው ከዳር ሳለ ውሃው አለበሳቸው፡፡ ወተጠምቃ እገሪሆሙ ለካህናት- የካህናቱ እግሮች ተጠመቁ እንዲል ]መጽሐፈ ኢያሱ 4÷1-19] ኢያሱም ለእሥራኤል ምድረ ርስትን አካፈላቸው ÷ ዮርዳኖስ የጥምቀት÷ ኢያሱ የምዕመናን÷ ዐሥራ ኹለቱን ድንጋይ የዐሥራ ኹለቱ ሐዋርያት ምድረ ርስት የመንግሥተ ሰማያት አምሳል ነው፡፡ 

ኤልያስም ዬርዳኖስን ሲሻገር ተማሪዋቹ ተከተሉት፤ ተመለሱ አላቸው፡፡ ኤልሳዕ ግን መድረሻህን ሳላይ እንዳልመለስ ሕያው እግዚአብሔር ያውቅብኛል አለው፡፡ ኹለቱ ሲኄዱ ዬርዳኖስን ሞልቶ አገኙት፡፡ ኤልያስም መጠምጠሚያውን/መቀነቱን/ እንደ መስቀል አድርጎ ቢመታው ተከፍሎላቸው ተሻገሩ፡፡ የምትወደውን ነገር ለምነኝና ተመለስ ቢለው÷ በአንተ አድሮ ያለው መንፈስ ቅዱስ እጽፍ ድርብ ኹኖ ይደርብህ በለኝ አለው፡፡ ድንቅ ነገር ለመንከኝሳ ብሎ ይደርብህ አለው፡፡ አፍራሰ እሳት ሠረገላተ-እሳት መጡለት በነዚህ ሁኖ ወደ ገነት ሲያርግ÷ አባቴ ልጅህን ለምን ጥለኸኝ ትኄዳለህ ብሎ ቢያለቅስበት ዕርገቴን ብታምን ፈጣሪዬ ይደርብህ ባታምን ይቀርብህ ብሎ ሐሜለቱን ጥሎለት ዓረገ፡፡ [መጽ. ነገሥ ካልዕ 2÷8-15] ዮርዳኖስ የጥምቀት÷ ኤልሳዕ የምእመናን÷ ሐሜለቱ የመስቀል÷ ገነት የመንግሥተ ሰማያት አምሳል ነው፡፡ ኤልሳዕም መምህሩን ሸኝቶ ቢመለስ ዮርዳኖስን ሞልቶ አገኘው ኤልያስ ሲያደርግ ዓይቶ ኹለት ጊዜ ቢመታው እምቢ አለው፤ በሶስተኛው ኢሀሎኑ ዝየ አምላከ ኤልያስ- የኤልያሰ አምላክ እዚህ የለም? ብሎ ቢመታው ተከፍሎለት ተሻገረ፡፡ [ነገሥት ካልዕ.2÷14] ደግሞም ደቂቀ ቤቴልን ሲያስተምር ጸበበነ ማኀደር- ቦታ ጠበበን ቢሉት ዕንጨት ቆርጣችኹ ሰፊ ቤት ሥሩ አላቸው÷ ረድኤት እንድትሆነን አንተም አብረኸን ውረድ አሉ፡፡ በጽንፈ ዮርዳኖስ ኾኖ ዕንጨት ሲያስቆርጥ ከተማሮቹ አንዱ የተዋሰው መሳር ወልቆ ቢጥልበት ሞሳሩን ይዞት ወጣ፡፡ ወቀረፈ ኤልሳዕ  ቅርፍተ ዕፀ……. ከእንጨትም ቅርፊት ቀርፎ በዚያ ጣለው፤ ብረቱም ተንሳፈፈ፡፡ እርሱም÷ እነሆ÷ ምሳርህ ውሰደው አለ እጁንም ዘርግቶ ወሰደው፡፡ [ነገሥተ ካልዕ 6÷1-7] ኤልሳዕ የእግዚአብሔር አብ÷ ቅርፍተ ዕፅ የእግዚአብሔር ወልድ÷ ምሳሩ የአዳም÷ ባሕሩ የገሃነመ እሳት አምሳል ነው፡፡ መጥለቅ የማይገባውን ምሳር ይዞት እንደወጣ÷ ሞት የማይገባው ክርስቶስ ሞቶ ሞት የሚገባውን አዳምን ከነልጆቹ ለማዳን በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡ 

ንእማን ሶሪያዊም ለምጽ ቢወጣበት ከደዌዬ ቢፈውሰኝ ብሎ ወርቅ ይዞ ወደ ኤልሳዕ ሲኄድ÷ በዬርዳኖስ ታጠብ ብሎ ከመንገድ ስለ ላከበት÷ ነቢየ እግዚአብሔር ሲባል በቃሉ ጸለዩ በእጁ ዳሶ ይፈውሰል ብዬ ነበር እንጂ የውሃ ውሃ ምን አለኝ እንዲሉ÷ የውሃ ውሃማ የሀገሬ ውሀዎች ባብና ፋርፋ ምን አሉኝ ብሎ ወደ ሀገሩ ሊኄድ ሠረገላውን መለሰ፡፡ ሰዎቹ ግን ቢኾን ትፈወሳለህ÷ ባይሆን የአገርህ መንገድ ይቀርብሃል ታጠብ አሉት ቢታጠብ ተፈወሰ፡፡ ወርቁን ግምጃውን ወስዶ ኤልሳዕን እነሆ ዋጋህን ተቀበለኝ ቢለው የእግዚአብሔርን ጸጋ ለወርቅ÷ ለብር እሸጠዋለኹን? አልቀበልም አለው፡፡ [ነገ ካልዕ 5 ÷6 – 8] ዮርዳኖስ የጥምቀት ÷ ንእማን የምዕነመናን÷ ለምጹ የመርገመ ሥጋ የመርገመ ነፍስ አምሳል ነው፡፡ ይኽን ኹሉ ለመፈጸም በዬርዳኖስ ተጠመቀ፡፡ 

ትንቢቱን ያናገረ ምሳሌውን ያስመሰለ እሱ ባወቀ ዓይደለምን? ምስጢሩ እንደ ምንድር ነው? ቢሉ፡- አዳምና ሔዋን ከገነት ወጥተው በደብር ቅዱስ ሳሉ ጋትርኤል የተባለ ዲያብሎስ የጨለማ መጋረጃ ጋርዶ ስቃይ አጸናባቸው÷ ወዲያው ምትሐቱን ጥቂት ብርሃን አስመስሎ ቢያሳያቸው አንተ ባለ ብርሃን ይህን ጨለማ አርቅልን አሉት፡፡ ስመ ግብርናታችሁን ጽፋችሁ ስጡኝና ላርቅላችሁ ቢላቸው በመከራ ያሉ ናቸውና ይሁንብን ጻፍብን አሉት፡፡ በብራና ብጽፈው ይደመሰሳል÷ በእንጨት ብጽፈው ይበሰብሳል ብሎ አዳም ገብሩ ሔዋን ዓመቱ ለዲያብሎስ ብሎ በኹለት ዕብነ ሩካም ቀርጾ አንዱን በዬርዳኖስ አንዱን በሲዖል መካከል ጥሎት ነበርና የአዳምንና የሔዋንን ስመግብርናት በኪደተ ግብሩ ለማጥፋት በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡ ወደምሰሶ ለነ መጽሐፈ ዕዳኑ የዕዳ ደብዳቤዎቻችንን አጠፋልን እንዳለ [ቅዱስ ጳውሎስ ቆላ .2÷14] 

ለፍጥረታት ኹሉ ገዥ ለአብ ምስጋና ለመንግሥትና ለነገሥታት ጌታ ለወልድም ስግደት ልብንና ኩላሊትን ለሚመረምር ለመንፈስ ቅዱስ አኰቴት ይገባል እንበል ለዘለዓለም አሜን!

መልካም የጥምቀት በዓል ይሁንላችሁ!                                                      

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

17 Jan, 09:39


የአንድነትና  የሦስትነት መገለጥ እንዴት ነበር
ጌታ ተጠምቆ ከውሃው ከወጣ በኋላ መንፈስ ቅዱሰ በርግብ አምሳለ ወርዶ ከራሱ ላይ ተቀመጠ፡፡ አወራረዱ እንደምን ነው ቢሉ አነድ ክነፍን ወደ ሰማይ ÷ አነድ ክንፍ ን ወደ ምድር አድርጎ ወርደል የአብ ሕይወት የወለድ ሕይወት ነኝ ሲል በርግብ አምሳል መውረዱ ሰለምን ነው ቢሉ÷ ርግብ የዋህ ናት÷ መንፈስ ቅዱስም በየዋሃን ሰዎች ያድራልና፡፡ ርግብ በኖኀ ጊዜ ኀፀ ማየ አይህ ነትገ ማየ አይሕ ስትለ ቆጽለ ዕፀዘፍትን ይዛ ተገኝታለች፡፡ [ዘፍ.8÷8-12]

መንፈስ ቅዱስም ሐፀ ማየ ኃጢአተ ነትገ ማየ መርገም አያለ ተስፍ መስቀል ያበሥራልና፡፡ መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ [ማቴ.16÷24]፡፡  ስለዚኽ ነገር በርግበ አምሳል ወረዶ አማናዊ ርግብ አለመኾኑ በምን ይታወቃል? ቢሉ ጌታ የተጠመቀ በዐሥረኛው ሰዓት ሌሊት ነው፡፡ በዚያን ጊዜ ተሕዋስያን ከቦታቸዉ አይናወጹምና በዚኽ ታዉቋል፡፡ በዚኽ ጊዜ አብ በደመና ሁኖ ዝንቱ ውአቱ ወለድየ ዘአፈቅር- ለመሥወዕት የፈቀድሁት በርሱ ህለው ሁኜ የምመለክበት ልጄ ይኽ ነው አለ፡፡[ማቴ.3÷17]፡፡ አንድ አካል አንድ ባሕርይ አድርጎ ዝንቱ ይኽ ልጄ ነው አለ÷ በዚኽ አድሮ ያለ ልጄ ነው አላለም አንድ አካል አንድ ባሕሪይ አርጎ ይህ ልጄ ነው አለ÷ እንጂ [እንዳለ ቄርሎስ] የአብ ምስክርነት የመንፈስ ቅዱስ መውረድ ከውሃው ከወጣ በኋላ ነው፡፡ ወልድ በክበብ ትስብዕት በጽንፈ ዩርዳኖስ ቁሞ ሲታይ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ከራሱ ላይ ሲቀመጥ አብ በአየር ሆኖ ሲመስክር የአንድነት የሦስትነት ምሰጢር ተገለጠ፡፡ ይኽ የአንድነትና የሦስት ምስጢር በምስጢረ ሥላሴ አስተምሮ ላይ ርቀታቸውን ሲገልጽ ሥላሴ በአካል ሦስት ናቸው፤ ለሥልጣናቸውም ወሰን መጨረሻ የለውም ካልን፤ ሰው አብሮ በተቀመጠ ጊዜ ፈቅ በልልኝ አታስጨንቀኝ ብሎ ይከላከላል፤ በሥላሴ እንዴት ነው ቢሉ? ሰው ግዙፍ ነውና ይከላከል፤ ሥላሴ ግን ረቂቃን ናቸውና አይከላከሉም፡፡ መከላከልስ እንደሌለባቸው ምሳሌ ያስረዳል፤ በመዓልት ብርሃንና ሙቀት ነፋስ ሦስት ፍጥረታት መልተው ይውላሉ፤ ብርሃኑ ሲኄድ ሲሠራበት ይውላል፡፡ ሙቀትንና ረፋስን ፈቅ በሉልኝ አይላቸውም፡፡ ነፋስም ዛፍን ሲያናውጽ ይውላል ሙቀትንና ብርሃንን ፈቅ በሉልኝ አይላቸውም፡፡ ሙቀትም የበረደውን ሲያሞቅ የረጠበውን ሲያደርቅ ይውላል፤ ብርሃንና ነፋስን ፈቅ በሉለኝ አይላቸውም፡፡ እሊህስ እንኳን ረቂቃን ነን ብለው አይከላከሉም፡፡ ከእሊህ ይልቅ ሥላሴ ይረቃሉና መከላከል የለባቸውም፡፡ 

ከኹሉም መላእክት ይረቃሉ ከአካላቸወም ርቀት የሕሊናቸው ርቀት ይበልጣል÷ ይኽ የሕሊናቸው ርቀት በሥላሴ  አካል ርቀት አንጻር እንደተራራ ገዝፎ ይታያል፡፡ በሥላሴ ርቀት የመንፈሳውያን መላእክት ርቀት አደን ግዙፍ ሥጋ ነው፡፡ [እንዳለ አረጋዉ መንፈሳዊ፡፡] በዚኽም በዕለተ ጥምቀት ሦስትነታቸውም በግልጽ የታየበትና የተገለጸበት ዕለት ነው፡፡ አብ በደመና ውስጥ ወልድ ሥጋንና መለኮትን አዋሕዶ በመጥምቁ ዮሐንስ አጠገብ በመቆም መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወደ ምድር/በወልድ/ላይ በማረፍ ታይቷል፡፡ በዚኽ ዕለትም የሥላሴ በአካል ሦስት መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡ አካሉ ግን የማይመረመር ምሉዕ ስፍሕ ረቂቅ ነው፡፡ እርሱ ራሱ ቢያውቀው እንጂ ሌላ አያውቅም፡፡ ፍጥረት ሁሉ በሱፊት በቅጠል ላይ እንዳረፈች ጠልና እንደ ወርቅ ሚዛን ማቅኛ ነው ብሎ ኢሳያስ እንደተናገረ፡፡ በዕለተ ጥምቀት በሦስትነት መታየታቸው ግን ፡- አብ በተለየ አካሉ ልብ ነው፤ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ልባቸው አብ ነው፡፡ ሌላ ልብ የላቸውም፡፡ ለባውያን መባላቸው በአብ ልብነት ነው፡፡ ወልድም በተለየ አካሉ ቃል ነው፤ ለአብ ለመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ወልድ ነው፤ ሌላ ቃል የላቸውም፡፡ ነባብያን መባላቸው በወልድ ቃልነት ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በተለየ አካሉ እስትንፋስ /ሕይወት /ነው ለአብ ለወልድ ሕይወታቸው መንፈስ ቅዱስ ነው ሌላ ሕይወት የላቸውም ሕያዋን መባላቸው በመንፈስ ቅዱስ ሕይወትነት ነው፡፡ 

አብ ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ ልባቸው ነው፡፡ ወልድም ለአብና ለመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም ለአብና ለወልድ ሕይወታቸው ነው፡፡ [እንዳለ አቡሊድስ] ሦስቱም በአብ ልብነት አስበው በወልድ ቃልነት ተናግረው በመንፈስ ቅዱስ ሕይወትነት ሕያዋን ሁነው ይኖራሉ፡፡ በአብ ልብነት በወልድ ቃልነት በመንፈስ ቅዱስ ሕይወትነት እናምናለን [እንዳለ ሳዊሮስ] አብ በሰማይ ወልድ በምድር መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ሆኖ ሦስትነት ይገለጽ እንጂ በሦስትነት አንድነት በአንድነት ሦስትነት አለ ብለን እናምናለን፡፡ ይህም እንዳለና እንዲታወቅ በምስጢረ ጥምቀት ዕለት ተገልጾልናል፡፡

ይቆየን
ቀጣይ ➥

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

17 Jan, 09:37


ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለስርየተ ኀጢአት - ኀጢአትን ለማስተሰረይ በምንጠመቃት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን፡፡  ✞          
[ሃይማኖተ አበው ዘሠለስቱ ምእት] 

ጥምቀት ማለት በምስጢረ ሥላሴና በምስጢረ ሥጋዌ ለሚያምን ሰው ኹሉ የተሰጠ የኃጢአት መደምሰሻና ከእግዚአብሔር የጸጋ ልደትን መቀበያ ነው፡፡ ጥምቀት የኃጢአት መደምሰሻ እንደሚኾንም እግዚአብሔር አስቀድሞ በነቢያት ትንቢት አናግሯል ...የጠራ ውሃ አፈስባችኋለሁ ትጠሩማለችሁ ከርኩሰታችሁም ሁሉ አነጻችኋለሁ፡፡ በማለት ተናግሯል፡፡ [ሕዝ. 36÷25] በመቀጠልም መልሶ ይምረናል ኃጢአታችንንም ያጠፋል ኃጢአታቸው ኹሉ ወደ ጥልቅ ባሕር ትጥላለኽ ማለት ኃጢአታቸውን በጥምቀ ታስተሰርያለህ/ትደመስሳለህ/ [ሚክ. 7÷19] 

ጌታም እውነት እውነት እልኻለሁ ማንም ከውሃና ከመንፈስ ቅዱስ ያልተወለደ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ይገባ ዘንድ አይችልም፡፡ [ዮሐ.3÷5] እንግዲህ ኂዱና አሕዛብን ኹሉ አስተምሩ አጥምቋቸውም በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ፤ [ማቴ. 28÷19] ያመነ የተጠመቀ ይድናል ያላመነ ግን ይፈረድበታል፡፡ [ማር.16÷16] ተብሎ ተጽፏል፡፡ 

ከእግዚአብሔር መወለዳችን የእግዚአብሔርን ርስት መንግሥት ሰማይን ለመውረስ ነው፤ መንግሥት ሰማይንም በጥምቀት ልንገባባት እንደምንችል ጌታችን በዚኽ ትምህርቱ እንደገለጸልን አውቀን መኖር ይገባናል፡፡ ይኽም የጌታ ትምህርት ስለጥምቀት ለነቢያት ትንቢት መፈጸሚያ ለሐዋርያት ትምህርት መምሪያ ነው፡፡ ምነው ጌታ ፈጣሪ እግዚእ ሲሆን ወደ ትሑት ዮሐንስ ኄደ ቢሉ ሥጋ መልበሱ ለትሕትና ነውና፡፡ በዚያውም ላይ ነገሥታት መኳንንት ቀሳውስትን መጥታችሁ አጥምቁን አቊርቡን ባሉ ነበርና፤ እኔ የሰማይ የምድርም ንጉሥ ስሆን ኄጄ ተጠምቄ ያለሁና እናንተም ኂዳችሁ በቀሳውስት እጅ ተጠመቁ ቊረቡ ሲል ነው፡፡ ጌታ መጠመቁ ብዙ ምስጢር አለው፡፡ መጀመሪያው ምክንያት አቤቱ ውኖች ዓዩኽ ተጨነቁም ቀላዬችም ተንቀጠቀጡ ተብሎ ትንቢት ተነግሮለት ነበር ይኽን ትንቢት ለመፈጸም ተጠመቀ፡፡ [መዝ. 77÷16] እንደ ትንቢቱም ቃል ጌታ ሊጠመቅ በገባበት ግዜ የዬርዳኖስ ውሃ ከመካከሉ ተከፍሎ ወደ ኋላው ሸሽቷል እሳትም እንዳነደዱበት ሁኖ ፈልቷል፡፡ ፈልሑ ማያት ዲበ ርእሱ - ውኖች በራሱ ላይ ፈሉ [እንዳለ ቅዱስ ያሬድ] 

የዬሐንስንም ምስክርነት ለማስረዳት ነው፡፡ ዮሐንስ ከእኔ በፊት የነበረ ከእኔ የሚበልጥ ከእኔ በኋላ ይመጣል፤ ብሎ በቃል መስክሮለት ነበረና ለሕዝቡ ተገልጾ እንዲታይ እንዲታወቅ ነው፡፡ ይኽም ሊታወቅ የተገለጠበት ዕለት ኤጲፋንያ ተብሏል፡፡ ኤጲፋንያ የፅርዕ /የግሪክ/ ቋንቋ /ቃል/ ሲኾን በግእዝ አስተርእዬ ተብሏል፡፡ በዐማርኛ መታየት መገለጽ ማለት ነው፡፡ መጠመቁን የፈቀደበት ምክንያት ሲገልጽ ግን በጥምቀቱ ውኖችን ሊቀድስልን አምናችሁ ብትጠመቁ ከኃጢአት መንጻትን ከመንፈስ ቅዱስ ልደትን ታገኛላችሁ ብሎ ሲያስተምረን ነው፡፡ [ሃይ. አበ. ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ]፡፡ ኀጢአት ኑሮበት ንጹሕ ሊኾን የተጠመቀ አይደለም በንጹሕ ከሱ ጋራ አንድነትን ይሰጠን ዘንድ ነው እንጂ፡፡ ……[ሃይ. አበ. ዘጎርጎርዮስ] 

ኹሉን ማድረግ የሚችል ጌታ በማር በወተት ያልተጠመቀ በውሃ የተጠመቀ ስለምን ነው ቢሉ ማር ወተት ለባለጸጋ እንጂ ለደሀ አይገኝምና ጥምቀትን ለሁሉ በሚገኝ በውሃ አድርጎ እንደሰጠን ሊያጠይቅ ነው፡፡ ዳግመኛ ማር ወተት ለተክል ቢያጠጧቸው ቢያደርቁ እንጂ አያለመልሙም÷ ውሃ ግን ያለመልማልና በውሃ ብትጠመቁ ልምላሜ ነፍስ ታገኛላችሁ ሲል ነው፡፡ ማር ወተት መልክአ ገጽ አያሳዩም÷ ውሃ ግን መልክአ ገጽ ያሳያልና በውሃ ብትጠመቁ መልክአ ሥላሴ ይሳልባችኋል ሲል ነው ማር ወተት ልብስ ያሳድፋል እንጂ አያነጻም÷ ውሃ ግን ያነጻልና በውሃ ብትጠመቁ ንጽሐ ነፍስ ታገኛላችሁ ሲል ነው፡፡ ዳግመኛም ውሃ ካለበት ዘንድ ተሐዋስያን አያገኙም ማር ወተት ባሉበት ግን ተሐዋስያን አይለዩምና አጋንንትም ወደ ጥሙቀን እንዳይቀርቡ ከኢጥሙቃን እንዳይለዩ ሲያጠይቅ ነው፡፡ ዳግመኛም ማር ወተት ቢፈሱ ከቅርብ ይቀራሉ እንጂ ከሩቅ አይደርሱም፡፡ ውሃ ግን እሩቅ ይደርሳልና ጥምቀትም ጽንፍ እስከ ጽንፍ እንደደረሰ ለማጠየቅ ነው፡፡ ዳግመኛም አቤቱ ማየት ዓዩህ አይተውህም ሸሹ ያለው ትንቢት እንደ ደረሰ እንደ ተፈጸመ ለማጠየቅ ነው፡፡ [መዝ. 76÷16] ፈርኦንን ከነሠራዊቱ በውሃ አጥፍቶት ነበርና ዲያብሎስንም ከነሠራዊቱ በጥምቀት ለማጥፋት ነው በፈርኦንም አድሮ የነበረ ሰይጣን በዚያው በኩል ወደ ሲኦል እንደ ወረደ በቁራኝነትም የነበሩ አጋንንት በጥምቀት ድል ይነሣሉ ሲል ነው፡፡ በዕለተ ኀሙስ ለታውጽእ ባሕር ባለ ጊዜ በደመ ነፍስ ሕያዋን የሚኾኑ ፍጥረታት ተገኝተዋል ከነዚኹም በዚያው ጸንተው የሚኖሩ ወጥተው የኄዱ÷ አንድ ጊዜ ከባሕር ጸንተው የሚኖሩ አሉ። [ዘፍ.1÷10፣ ዘጾ. 14 ÷26-31]

ዮሐንስም ሎሌ ከጌታው ይኄዳል እንጂ ጌታ ከሎሌው ሊጠመቅ ይኄዳልን? እንደዚኹስ ኹሉ እኔ ካንተ ዘንድ ለመጠመቅ እመጣለኹ እንጂ አንተ ከኔ ዘንድ ለመጠመቅ ትመጣለኽን? ብሎ አይኾንም አለው፡፡ ኀድግ ምዕረሰ አንድ ግዜስ ተው አለው አንድ ጊዜስ ተው ማለቱ ጌታ ሲጠመቅ ዮሐንሰ ሲያጠምቅ አይኖርምና፡፡ እስመ ከመዝ ተድላ ለነ÷ ይኽ ለኛ ተድላ ደስታችን ነውና÷ አንተ እኔን አጥምቀኽ መጥምቀ መለኮት እየተባልኽ ልዕልናኽ ሲነገር ይኖራል፡፡ እኔም ባንተ እጅ ተጠምቄ በባሪያው እጅ ተጠመቀ እየተባለ ትሕትናዬ ሲነገር ይኖራልና ይኽ ለእኛ ተድላ ደስታችን ነው፡፡ [ማቴ. 3÷15 መዝ. 110÷4]  ዮሐንስም ሌላውን በእንተ ስምከ አጠምቃለሁ አንተን ምን እያልኩ አጠምቅሃለሁ አለው፡፡ ጌታም ወልዱ ለቡሩክ ከሣቴ ብርሃን ተሣሃለነ፡፡ የብርሃን የዕውቀት ባለቤት የወንጌል መምህር የአብ የባሕርይ ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ይቅር በለን፡፡ ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘየ አትት  ኃጢአተ ዓለም ፡፡  
                                                          
የዓለሙን ኃጢአት ለማስተሥረይ የመጣ  የእግዚአበሔር መሥዋዕቱ እነኾ እያልክ አጥቀኝ አለው [ዩሐ. 1÷30] ይኽን ተባብለው ኹለቱ እጅ ለእጅ ተያይዘው ወደ ባሕሩ ገቡ÷ በዚኽ ጊዜ እጁን አልጫነበትም ከራሱ ላይ ረቦቆሞ ወፈልሑ ማየት ከመዘእምአፍላግ እንዲል፤ ውሃው እየተመላለሰ ሦስት ጊዜ አልብሶት ወረደ ÷ እጁን ከራሱ ላይ ረቦ መቶሙ ስለምን ነው ቢሉ ሊቀ ካህናታችሁ ይኽ ነው የቀድሞ መሥዋዕታችሁ አለፈ ፤ እንግዲኽ ወዲኽ መሥዋዕታችሁ ይኽ ነው ብሎ በጣት ጠቅሶ እንደማሳየት ያለ ነው፡፡ መጠመቁም ለኛ አብነት ለመኾን ÷ጥምቀትን ብርህት ጽድልት ለማድረግ ለጥምቀት ኃይል ለመስጠት ነው፡፡ እኛም ኃይል መንፈሳዊ በየጊዜው እንዲጨመርልን እሱን አብነት አድርገን እንጠመቃለን፡፡ 

ይቆየን...
ቀጣይ ➥

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

15 Jan, 10:25


እንኩዋን አደረሳችሁ!

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

13 Jan, 18:42


✧°༺༻°✧ የጥር 6 ግዝረትና በዓላት ✧°༺༻°✧

ግዝረት ከጌታችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው፡፡ በተጨማሪም ይህ ቀን ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ዕረገተ ኤልያስ፤ ዕረፍተ ኖኅ፤ ልደተ ቅድስት አርሴማ፤ ዕረፍተ ዐቢይ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፤ አቡነ ኖኅ አባ ሙሴ ገዳማዊ፤ አባ ወርክያኖስ እና ወአባ ሙሴን በዓላት ታከብራለች፡፡

ከእናቱና ከደቀመዛሙርቱ ጋር በሰርግ ቤት የተገኙበት ቃና ዘገሊላ፣ በአርባ ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ የገባበትና አረጋዊ ስምዖንን የሰላሳ ዓመት ጎልማሳ የሆነበት “ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ ዐይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና” በማለት የተናገረበት ልደተ ስምዖን ከንዑሳን በዓላት ይመደባሉ፡፡ ክብር ምስጋና ይድረሰውና የጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ግዝረት በየዓመቱ ጥር ፮ ቀን ይውላል።

ልሳነ ዕፍረት ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋው ግዝረትን ተቀበለ፡፡ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ፤›› በማለት እንደ ተናገረው [ሮሜ.፲፭፥፰]፣ የክብር ባለቤት መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ ፈጽሟል፡፡ በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ በስምንተኛው ቀን እንደ ኦሪቱ ሥርዓት ግዝረት ይፈጸምለት ዘንድ ሕፃኑ ጌታችንን ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡ ስሙም ገና በሥጋ ሳይፀነስ የእግዚአብሔር መልአክ ባወጣለት ስም ‹‹ኢየሱስ›› ተብሎ ተጠራ [ሉቃ.፪፥፳፩-፳፬]፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ሲገረዝ የሊቀ ካህን ልጅ ነው ብለው ሊገርዙት ወደ እርሱ መጡ፡፡ ጌታችን ግን ወደ ምድር የመጣው ለትሕትና ነው እንጂ ለልዕልና አይደለምና ወሰዱት አለ [ትርጓሜ ወንጌለ ሉቃስ]፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም አረጋዊው ዮሴፍን ‹‹እንደ ሕጉ ልጄን እንዲገርዘውና ስሙንም እንድንሰይመው ብልህ የኾነ ገራዥ ሰው አምጣልኝ፤›› አለችው፡፡ ጻድቁ ዮሴፍም እንዳዘዘችው የሚገርዝ ባለሙያ ይዞ መጣ፡፡ ባለሙያውም በእናቱ በንጽሕት ድንግል ማርያም ክንድ ላይ ሕፃኑ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ባየው ጊዜ ‹‹እንድገርዘው በጥንቃቄ ያዙት›› አላቸው፡፡ ጌታ ኢየሱስም ‹‹ባለሙያ ገራዥ ሆይ! ደሜ ሳይፈስ ልትገርዘኝ ትችላለህን? በዕለተ ዓርብ በመስቀል ስሰቀል ካልኾነ በስተቀር ደሜ አይፈስምና፡፡ ጐኔን በጦር ሲወጉኝ ያን ጊዜ ውኀና ደም ይፈሳል፡፡ ይኸውም ለአዳምና ለሚያምኑ ልጆቹ መድኀኒት ይኾናል፤›› አለው፡፡

የክብር ባለቤት ጌታችን የተናገረውን ይህን ቃል ባለሙያው በሰማ ጊዜም አደነቀ፡፡ ዕቃውንም ሰብስቦ ተነሣና ከጌታችን እግር በታች ወድቆ ሰገደ፡፡ ያንጊዜም ምላጮቹ በእጁ ላይ እንዳሉ እንደ ውኀ ቀለጡ፡፡ ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንም ‹‹ከሴቶች ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ፡፡ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፡፡ ይህ ልጅሽ ስለ እርሱ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት የሕያው አምላክ ልጅ ነው፤›› አላት፡፡

ጌታችንም ባለሙያውን ‹‹እኔ ነኝ! ትገዝረኛለህን ወይስ ተውክ? ወይስ የአባቶቼ አባቶች እንዳደረጉ ላድርግ?›› አለው፡፡ ባለሙያውም መልሶ ‹‹የአባቶችህ አባቶች እነማን ናቸው?›› ሲል ጠየቀው፡፡ ጌታችንም አብርሃም፣ ይስሐቅ፣ ያዕቆብ የሕዝቡ ዅሉ አባት እንደ ኾኑ ካስገነዘበው በኋላ ‹‹ለእነርሱም ይህ ግዝረት አስቀድሞ ከአባቴ ዘንድ ተሰጣቸው›› በማለት የግዝረትን ሕግ አስረዳው፡፡ ባለሙያውም ይህን ምሥጢር ሲሰማ ‹‹እኔ ከአንተ ጋር እነጋገር ዘንድ አልችልም፡፡ በአንተ ህልውና መንፈስ ቅዱስ አለና፤›› ብሎ የኢየሱስ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክነት መሰከረ፡፡

በዚህ ጊዜ ጌታችን ዐይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ ‹‹አባት ሆይ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ፣ ለያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሃቸው፤ ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ›› አለ፡፡ ያንጊዜም ያለ ሰው እጅ በጌታችን ላይ ግዝረት ተገለጠ (የግዝረት ምልክት ታየ)፡፡ ከዚህ ላይ ጌታችን ወደ አባቱ ወደ እግዚአብሔር አብ ልመና ማድረሱ የለበሰው ሥጋ የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ መኾኑንና ጸሎት ማቅረብ የሚስማማው ሥጋን መልበሱን ለማጠየቅ ነው እንጂ በእርሱና በአብ መካከል ልዩነት ኖሮ አይደለም፡፡

ጌታችን ድንግልናዋን ሳያጠፋ ከድንግል ማኅፀን እንደ መውጣቱ ግዝረቱም አይመረመርም፡፡ በተዘጋ ቤት ወደ ሐዋርያት እንደ ገባና እንደ ወጣ ዅሉ እርሱ በሚያውቀው ረቂቅ ጥበብ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቈረጥ፣ ምንም ደም ሳይፈሰው መገረዙ ተገለጠ፡፡

ገራዡም የጌታችንን ቃል ከመስማቱ ባሻገር በሥጋው ላይ የተደረገውን ተአምር ባየ ጊዜ እጅግ አደነቀ፡፡ ከክብር ባለቤት ከጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግር በታች ወድቆም ሦስት ጊዜ ሰገደና ‹‹በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ፣ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ!›› በማለት በክርስቶስ አምላክነት አመነ፡፡ ከዚህ በኋላ ያየውንና የሰማውን ዅሉ እየመሰከረ ወደ ቦታው ተመለሰ፡፡

በዚህች ዕለት ‹‹መሲሑን ሳታይ አትሞትም›› ተብሎ የተነገረለት፤ በንጉሥ በጥሊሞስ መራጭነት መጻሕፍተ ብሉያትን ከዕብራይስጥ ወደ ጽርዕ(ግሪክ) ቋንቋ ከመለሱ ሰባው ሊቃናት አንዱ የኾነውና ትንቢተ ኢሳይያስን ወደ ጽርዕ ቋንቋ የመለሰው ነቢዩ ስምዖን ጌታችንን በታቀፈው ጊዜ ከሽምግልናው ታድሷል፤ የእግዚአብሔርን ማዳን በማየቱና በተደረገለት ድንቅ ተአምር በመደሰቱም ‹‹አቤቱ ባሪያህን ዛሬ አሰናብተው›› እያለ እግዚአብሔርን ተማጽኗል፡፡

በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶም የክርስቶስን የዓለም ቤዛነትና ክርስቶስ በሥጋው በሚቀበለው መከራ እመቤታችን መራራ ኀዘን እንደሚደርስባት፤ እንደዚሁም ጌታችን ለሚያምኑበት ድኅነትን፣ ለሚክዱት ደግሞ ሞትን የሚያመጣ አምላክ እንደ ኾነ የሚያስገነዝብ ትንቢት ተናግሯል [ሉቃ.፪፥፳፭-፴፭]፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ነቢዪት ሐናም በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝታ የክርስቶስን ሥራ እያደነቀች ቸርነቱን ለሕዝቡ ዅሉ መስክራለች [ሉቃ.፪፥፴፮-፴፱]፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

09 Jan, 14:16


የቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ሥጋ መለወጫ
በዚችም ዕለት የቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆን እና የቀዳማዊት ክርስቲያን ሰማዕት ሥጋ የተቀየረበትን ቀን ቤተ ክርስቲያን ታከብራለች። በኢየሩሳሌም በሰማዕትነት ካረፈ በኋላ አንዳንድ ምእመናን ንጹሕ ሥጋውን ወስደው በኢየሩሳሌም አቅራቢያ በምትገኝ ገማልያል በምትባል መንደር ቀበሩት። ለሦስት መቶ ዓመታት ያህል አስከሬኑ የት እንዳለ አይታወቅም ነበር።

ከዚያም ቅዱስ እስጢፋኖስ ሉክያኖስ ለሚባል ካህን ተገለጠለት። ስሙንና አስከሬኑ የተቀበረበትን ነገረው። ካህኑም ወደ የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ ወደ ቅዱስ ዮሐንስ ሄዶ ራእዩን ነገረው። ኤጲስ ቆጶሱም ተነሥቶ ሌሎች ሁለት ጳጳሳትንና የቤተ ክርስቲያንን ሰዎች ይዞ አስከሬኑ ወዳለበት ሄደ።  በተጠቀሰው ስፍራም ቈፈሩ፥ ታላቅም መናወጥ ሆነ፥ የቅዱስ ሥጋም ያለበት የሬሳ ሳጥን ታየ። ወደ ኢየሩሳሌምም እስኪደርሱ ድረስ በታላቅ ክብር ተሸከሙት።

ከዚህም በኋላ የቁስጥንጥንያ ተወላጅ የሆነው እስክንድር የሚባል አንድ ሰው በኢየሩሳሌም ለቅዱስ እስጢፋኖስ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ሠራለት ሥጋውንም በውስጡ አኖረ።

ከዐምስት ዓመታት በኋላ እስክንድር ሄዶ ሚስቱ በቅዱስ እስጢፋኖስ ታቦት አጠገብ ቀበረችው። ከስምንት ዓመታት በኋላ የአሌክሳንደር ሚስት ወደ ቁስጥንጥንያ ለመመለስ ወሰነ እና የባሏን አስከሬን ከእሷ ጋር ለመውሰድ ፈለገች። ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥታ የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ የባሏ ታቦት መስሎት ያለበትን ታቦት ወሰደች። እሷም ወደ ቁስጥንጥንያ በመርከብ ተሳፍራለች። በጉዞው መሀል ከሬሳ ሣጥን ውስጥ የዝማሬና የምስጋና ድምፅ ሰማች። እሷም በመደነቅ የሬሳ ሳጥኑን መረመረች።  እሷም የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋ ያለበት የሬሳ ሣጥን እንደሆነና ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንደሆነ ተረዳች። ጌታን አመሰገነች እና ወደ ቁስጥንጥንያ እስክትደርስ ድረስ መንገዷን ቀጠለች።

በዚያም ወደ ታላቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ሄዳ የሆነውን ነገር ነገረችው። ንጉሠ ነገሥቱ፣ ፓትርያርኩ፣ ጳጳሳቱ፣ ካህናቱና የከተማው ሕዝብ ታቦቱን በትከሻቸው ተሸከሙ። በመንገዳቸው ላይ በድንገት ሰልፉ ቆሞ “የቅዱሱን ሥጋ እዚህ ማኖር ተገቢ ነው” የሚል ታላቅ ድምፅ ሰሙ።

 ንጉሠ ነገሥቱም በዚያ ቦታ ለቅዱሳኑ ቤተ ክርስቲያን እንዲሠራላቸው አዘዘ፤ በዚያም ንዋየ ቅድሳቱን አኖሩ።

 የጸሎቱ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን።

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

08 Jan, 10:00


እስጢፋኖስ (በግሪክ: Στέφανος ሲነበብ ፡ Stéphanos ስቴፋኖስ፤ በዕብራይስጥ ፡ הקדוש סטפנוס ፤ በእንግሊዘኛ ፡ Stephen ሲነበብ ፡ ስቴፈን) በሕገ ወንጌል (በክርስትና) የመጀመሪያው ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳሚው ሰማዕት ይህ ቅዱስ ነው።

የተወለደው በ፩ኛው ክፍለ ዘመን፤ የትውልድ ቦታ ኢየሩሳሌም፤ የእናት ስም ማርያም፤
የአባት ስም ስምዖን፤ የሚከበረው በመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ሥንክሳር፤
በዓለ ንግሥ ሲመቱ ጥቅምት ፲፭ ቀን፤ ዕረፍቱ ጥር ፩ ቀን፤ ፍልሰቱ መስከረም ፲፯ ቀን፤ በግብፅ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን ቶቢ ፩ ቀን፤ በምዕራባውያን ዲሴምበር ፳፮ ቀን፤
ያረፈበት ቀን ጥር ፩ ቀን በመናፍቃን በድንጋይ ተወግሮ ነው።

ቅዱሱ በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን አስገራሚ ማንነት ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር። ይህም በወጣትነት ያለፈችው ሕይወቱ ስትሠራ የነበረው ታላቅ መንፈሳዊ ሥራ ይመሠክራል።

ከቅዱስ ዮሐንስ መጥምቁ ጋር

በወቅቱ ደግሞ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ የንስሐ ጥምቀትን እየሰበከ መምጣቱን የተመለከተ ቅዱስ እስጢፋኖስ ነገሩን መረመረ። ከእግዚአብሔር ሆኖ ቢያገኘው የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆነ። ለስድስት ወራትም በትጋት ቅዱስ ዮሐንስን አገለገለ። ለስድስት ወራት ከቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ ከተማረ በኋላ ለስም አጠራሩ ስግደት ይድረሰውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠመቀ። በወቅቱ የተደረገውን ታላቅ ተአምር ልብ ያለው ቅዱስ እስጢፋኖስ መምህሩን ቅዱስ ዮሐንስን እንዲያስረዳው ጠየቀው። "ከእኔ ይልቅ ከፈጣሪው አንደበት ይስማው።" በሚል ላከው። ቅዱሱም ከጌታ ዘንድ ሔዶ እጅ ነስቶ ተማረ። [ሉቃ. ፯፥፲፰] በዚያውም የጌታ ደቀ መዝሙር ሆኖ ቀረ።

ከጌታችን ዕርገት በኋላ

ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በኋላ ለአንድ ዓመት ያህል ስምንት ሺውን ማኅበር እየመራ ወንጌልን እየሰበከ ቢጋደል ኦሪት "እጠፋ እጠፋ" አለች። በዚህ ጊዜ "ክርስትናን ለማጥፋት መፍትሔው ቅዱስ እስጢፋኖስን መግደል ነው" ብለው አይሁድ በማመናቸው አልቀረም ገደሉት። እርሱ ግን ፊቱ እንደ እግዚአብሔር መልአክ እያበራ ፈጣሪውን በብዙ ነገር መሰለው። በመጨረሻውም ስለ እነሱ ምሕረትን እየለመነ በድንጋይ ወገሩት። ደቀ መዝሙርቱም ታላቅ ለቅሶን እያለቀሱ ቀበሩት።

ይቆየን...

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

05 Jan, 23:44


የቀጠለ ክፍል

✤• ፲፩ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ

“ኦ ጥቀ ዕጹብ ሰኪበ መላኬ ኲሉ ዓለም በውስተ ጎል፤ ጎል ተለዐለ እምኑኀ አርያም፤ ወሰፍሐ እምአጽናፈ ምድር ... (በበረት ውስጥ የዓለም ገዢ መተኛት እጅግ ድንቅ ነው፤ በረት ከጽርሐ አርያም ይልቅ ረዘመ፤ ከምድር ዳርቻም ሰፋ፤ ሕዝቅኤል ካየው ሠረገላ፤ ዳንኤልም ካየው ኪሩባዊ ዙፋን በረት በለጠ) [ሕዝ. 1፥18፤ ዳን. 7፥9፤]

በረት ነባቢ ለኾነ መሥዋዕት መሻተቻ መንበርን ኾነ፤ ይኸውም የቅድስቲቱ እንቦሳ ልጅ ንጹሕ በግ ነው፤ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው፤ ወሰነውም፤ በረት ተመሰገነ፤ የኀያላን ጌታ በውስጡ ስለተኛ ... በረት ተመሰገነ፤ ምድርን በውሃ ላይ ያጸና ርሱ ስለተጠጋበት፤ ድንግልም ትጉሃን ሰራዊትን አስገለገለቻቸው፤ በኪሩቤል በኪሩቤል ዐድሮ የሚኖር ጌታ በማሕፀኗ ስለ ዐደረ፤ በረት ኪሩቤል እንደሚሸከሙት ዙፋን ኾነ ... ዮሴፍና ሰሎሜ በወዲኽና በወዲያ፤ ላምና አህያም በበረቱ ጐንና ጐን በአራቱ ማዕዘን ናቸው፤

በሰማይ ሥርዐት ጐኖች አራቱ እንስሳት እንደሚኖሩት፤ የሰማይ ሥርዐት በምድር ላይ ተሠራ፤ ቤተልሔምም እንደ ሰማይ ተመሰለች፤ በሚጠልቅ ፀሓይም ፈንታ፤ በቅዱሳን ላይ ዘወትር የሚያበራ፤ ኅልፈት ጥልቀት የሌለበት አማናዊ ፀሓይ ኢየሱስ ክርስቶስ በውስጧ ወጣ፤ ከብርሃኑ ጒድለት መምላትን የሚያፈራርቅ በጨረቃ ፈንታ የድንግልናዋ ምስጋና ዘወትር የማይጐድልና በኹሉ የመላ በዕብራይስጥ ሚርያም የተባለች የተመረጠች ድንግል ማርያም ተገለጠች፤ በከዋክብት ፈንታም የብርሃን መላእክት ታዩ ይላል።

“ህየ አብ ዘእንበለ እም ወበዝየ እም ዘእንበለ አብ ምድራዊ ህየ ገብርኤል ይቀውም በፍርሀት ወበዝየ ገብርኤል ያበሥር በትፍሥሕት…” (በዚያ ያለ እናት አባት አለው [መዝ. 2፥7፤ ዳን. 7፥13] በዚኽም ያለምድራዊ አባት እናት አለችው [ሉቃ. 2፥7]፤ በዚያ ገብርኤል በፍርሀት ይቆማል [ሉቃ. 1፥19] በዚኽም ገብርኤል በሐሤት የምሥራችን ይናገራል [ሉቃ. 1፥26]፤ በዚያ በጽርሐ አርያም የሚደነቅ ከማይታይ አብ የመወለድ ምስጋና አለው በዚኽም በቤተልሔም ከድንግል መወለድ ምስጋና አለው [ሉቃ. 2፥1]፤ በዚያ ከሰማያውያን ካህናት በወርቅ ማዕጠንት የዕጣኑን መዐዛ ይቀበላል [ራእ. 8፥3] በዚኽም ወርቅንና ከርቤን ዕጣንንም ከሰብአ ሰገል ተቀበለ [ማቴ. 2፥12]፤ በዚያ ኪሩቤልና ሱራፌል ከግርማው የተነሣ ይንቀጠቀጣሉ።

በዚኽም ማርያም ዐቀፈችው ሰሎሜም አገለገለችው፤ በዚያ የመብረቅ ብልጭልጭታ በፊቱ ይገለባበጣሉ የእሳትም ወላፈን ከአዳራሹ ይወጣል [ሕዝ. 1፥13] በዚኽም አህያና ላም በትንፋሻቸው አሟሟቁት [ኢሳ. 1፥3]፤ በዚያ የእሳት ዙፋን አለ በዚኽም የደንጊያ በረት አለ፤ በዚያ የእብነ በረድ የሰማይ ንጣፍ አለ በዚኽም የላሞች መጠጊያ በረት አለ፤ በዚያ የትጉሃን ሥፍራ በሰማያት ያለች ኢየሩሳሌም አለችው በዚኽም የእንስሳት ጠባቂዎች ማደሪያ በኣት አለው [ሉቃ. 2፥7]፤ በዚያ ርዝማኔ የማይታወቅ የዳንኤል ብሉየ መዋዕል አባት አለው [ዳን. 7:13]

በዚኽም የዓመቶቹ ቊጥር በሰው ልጅ ዐቅም መጠን የኾነ ሽማግሌ ዮሴፍ ተሸከመው ... የአምላክን ልጅ ሰው መኾኑን በዓል እናድርግ የተሸከመችውን ማሕፀን እናመስግን፤ ላቀፉት ጉልበቶች እንስገድ፤ ላሳደጉት ጡቶች እንዘምር፤ የዳሰሱትን እጆች እናመስግን፤ ለሳሙት ከንፈሮች እናሸብሽብ፤ ከእረኞች ጋር ምስጋናን እናቅርብ፤ ከሰብአ ሰገልም ጋር እጅ እንንሣ፤ እንደ ዮሴፍ እናድንቅ እንደ ሰሎሜም እናገልግል በተኛበት በረት እንስገድ፤ በተጠቀለለበት በረት እንበርከክ፤ ለእግዚአብሔር በሰማያት ምስጋና ይኹን በምድርም ሰውን ለወደደ እንበል [ሉቃ. 2፥14]

እንኩዋን አደረሳችሁ መልካም በዓል 

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

05 Jan, 16:14


ከላይ የቀጠላ

➥3. ሙሴ ይጠፋ ዘንድ ሕጻናት ሲያስገድል የነበረው ሰይጣን አሁንም ሕያው የሆነው ይሞት ዘንድ ወንድ ልጆችን ያስገድላል፡፡ ሰይጣን ወደ ይሁዳ ስለወጣ ወደ ግብጽ ብሸሽ ይሻለኛል፤ አዳኙን የሚያድነው /ሰይጣን/ ግራ ይጋባ ዘንድ፡፡

➥4. ሄዋን በድንግልናዋ ጊዜ የሃፍረትን ቅጠሎች ለበሰች፤ እናትህ ግን በድንግልናዋ ጊዜ ለሁሉ የሚበቃ የክብር ልብስ ለበሰች፡፡

➥5. በህሊናዋ እና በልቧ አንተ ያለህ ያቺ እናትህ የተባረከች ናት፡፡ ለአንተ ለንጉሱ ልጅ ቤተ መንግሥት፤ ለአንተ ለሊቀ ካህናቱም ቅድስተ ቅዱሳን ሆናለችና፡፡

በእንተ ልደት /መዝሙር 18/
. ሰዎች «ፀሐይ» ብለው በሚጠሩት ንጉሥ /አውግስጦስ ቄሳር/ ዘመን ጌታ በእስራኤላውያን መካከል አበራ፤ የእውነተኛው ብርሃን መንግስትም ተመሠረተ፤ እርሱ በምድር ንጉስ በሰማይ ደግሞ ልጅ ነውና፤ የተመሰገነ ይሁን፡፡

. ግብር ለመሰብሰብ ሰዎችን በመዘገበው / በጻፈው/ ንጉስ ዘመን መድኃኒታችን ሰዎችን በሕይወት መጽሐፍ ይጽፍ ይመዘግብ ዘንድ ተወለደ፡፡

. በዚህ ምድር ሰላሳ ዓመታት ያህል በድህነት ቆየ፡፡ ወንድሞቼ ለእነዚህ ለጌታ ዓመታት ሁሉንም ዓይነት ምሥጋና እናቅርብ፡፡ ልደቱ የተመሰገነ ይሁን፡፡

በእንተ ልደት /11ኛ መዝሙር/
. ጌታ ሆይ፣ እናትህን እንዴት ብሎ /ምን ብሎ መጥራት እንዳለበት የሚያውቅ ማንም የለም፡፡ «ድንግል» ብሎ እንዳይጠራት ልጅ አላት፤ «ያገባች» እንዳይላትም ማንም / በግብር/ ያወቃት የለም፡፡ ነገር ግን እናትህ እንዲህ ልትገለጽ የማትችል ከሆነች፣ አንተን ሊገልጽህ /ሊያውቅህ/ የሚችል ማን ነው? ሁሉ ነገር በፊትህ ቀላል ለሆነው ለሁሉም ጌታ ለአንተ ምሥጋና ይገባል፡፡

. እርሷ ብቻዋን እናትህ ነች፤ ከሁሉም / ከክርስቲያኖች ሁሉ ጋር ደግሞ እህትህ ነች፡፡ እርሷ ለአንተ እናትም እህትም ነች፡፡ ከእነዚያ ከንጹሐን ደናግል ጋርም ሙሽራህ ነች፡፡ የእናትህ ውበቷ ሆይ፣ አንተ በሁሉ ነገር ከፍ ከፍ አድርገሃታል፡፡

. እመቤታችን በአንተ ምክንያት ያገቡ ሴቶች ያሏቸውን ነገሮች ሁሉ ማለትም፤ ያለ ዘርአ ብእሲ መጽነስን፣ ከተለመደው መንገድ ውጪ በጡቶቿ ወተትን፣ አግኝታለች፡፡ ደረቂቱ ምድር /Parched earth/ በድንገት የወተት ምንጭ አድርገሃታል።

. እናትህ እጅግ አስደናቂ ነች፤ ጌታ ወደ እርሷ ገባና አገልጋይ ሆነ፤ መናገር የሚችል ሆኖ ገብቶ በእርሷ ውስጥ ዝም አለ፤ የሁሉ እረኛ ሆኖ ገብቶ በእርሷ ውስጥ በግ ሆነ፤ እያለቀሰም ወጣ።

. የእናትህ ማኅፀን ሥርዓትን ሁሉ ሻረ፤ ሁሉን ያዘጋጀው /ሁሉ በእርሱ የሆነው/ ሀብታም ሆኖ ገባበት፤ ድሃ ሆኖም ወጣ፡፡ ከፍ ከፍ ያለ ሆኖም ገባና ትሁት ሆኖ ወጣ፡፡

. ኃይለኛ ተዋጊ ሆኖ ገብቶ በእርሷ ማኅፀን ፍርሃትን ለበሰ፤ የሁሉ መጋቢ ሆኖ ገብቶ ረሃብን ተቀበለ፡፡ ለሁሉም መጠጥን የሚሰጥ ሆኖ ገብቶ ጥምን ተቀበለ፡፡ ለሁሉ ልብስን የሚሰጠው ከእርሷ ማኅፀን ራቁቱን ሆኖ ተወለደ፡፡

✤• ፬ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ
በፈቃደ አቡሁ ወረደ፣ ኀበ ማርያም ተአንገደ፤ በድንግልናሃ ንጹሕ እግዚአብሔር ተወልደ። በጎለ እንስሳ ተወድየ፣ አምኃ ንግሡ ተወፈየ፤ ወከመ ሕጻናት በከየ፣ እንዘ ይስእል እምአጥባተ እሙ ሲሳየ። (በአባቱ ፈቃድ ወረደ፣ በማርያም ዘንድ፣ እንግዳ ሆነ፣ እግዚአብሔር በንጹሕ ድንግልናዋ ተወለደ። በእንስሳት በረት ተጨመረ፣ የንግሡንም እጅ መንሻ፡ ተቀበለ፣ ከእናቱ ጡቶች ምግብን እየለመነ እንደ ሕጻናት አለቀሰ።) [ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ]

• ፭ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
The nativity of Christ is the birthday of the whole human race - የክርስቶስ ልደት የመላው ሰው የልደት ቀን ነው ሲል መስክሯል (Hyman of praise to the mother of God)፡፡

✤• ፮ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? ከዘመን አስቀድሞ የነበረው እርሱ ሕፃን ኾኗልና። እኔ ፈጽሜ አደንቃለሁ፡፡ ከሰማየ ሰማያት በላይ የሚኾን፣ በዘለዓለማዊ ዙፋን የሚኖር እርሱ በበረት ተጣለ፡፡ ከሥጋዌ አስቀድሞ አይዳሰስ የነበረ አንዱ እርሱ በምድራውያን እጅ ተዳሰሰ፡፡ ኀጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱን በጨርቅ ጠቀለሉት። ይህን ወዷልና፤ [ሃይማኖተ አበው ዘዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ 66፥17]።

✤• ፯ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ
ርሱ እሳትን ለብሷል፤ በመጠቅለያ ጨርቅም ተጠቅልሏል፤ ግን ደግሞ ከመታወቅ በላይ ነው፤ በዙፋን ላይ ተቀምጧል እንዲኹም በግርግም ተኝቷል፤ ግን ደግሞ አይመረመርም በኪሩቤል ዠርባ ላይ ተቀምጧል እንዲኹም ጉልበቶች ተሸክመውታል፤ እናም በዚያ ምክንያት ርሱ ታላቅ ነው፤ ርሱ የተፈጠሩ ፍጥረታትን ያላውሳቸዋል እንዲኹም ርሱ አካለ ሥጋን ተውሕዷል እናም እነርሱ ድንቁን ይናገራሉ፤ ርሱ ወገኖችን ያኖራቸዋል ርሱ እንዲኹም ወተት ይጠባል፤ ርሱን ይረዳው ያውቀው ዘንድ ማን ይችላል?፤ ርሱ ዝናብን ያዘንባል፤ ርሱ ደግሞ ጡት ይጠባል፤ እናም ድንቁን ተመልከቱ ርሱ ልዑል እና አስፈሪ ነው፤ ርሱም የሚቀኝለት ነው፤ እነሆ ድንቁ፤ ሰማይ ለርሱ እጅግ ያንሰዋል እናም ርሱ መኖሪያን ፈለገ፤ እነሆ እንዴት ያለ ጸጋ ነው! ሱራፌል ራሳቸውን ይሸፍናሉ (ይጋርዳሉ)፤ ዮሴፍ ይሰግዳል አንዳች ድንቅ በዚኽ አለና፤ ሥልጣናት ተዘርግተዋል ሰዎችም ደካሞች ናቸው፤ ያስተውል ዘንድ ግን ማን ይችላል?” [ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ፤ ድርሳን በእንተ ልደተ እግዚእ]

✤• ፰ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘ ኒውስ
ከእስራኤል ፈጣሪ በቀር ሰው እንዳልገባበት ነብዩ ሕዝቅኤል እንዳያት ኆኅተ ማኅተመ ድንግልናዋ ሳይለወጥ በኅቱም ድንግልና ተፀንሶ ተወለደ፡፡

እናንተ አላዋቂዎች የድንግል ማርያም መፅነሷን መውለዷን እንደ ሴቶች አታስመስሉ፡፡ ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም ይህ ነገር ሊነገርባት አይገባም፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ያለዘርዐ ብዕሲ ፀንሳ ምጥ ሳይሰማት ወለደችው እንጂ፡፡

✤• ፱ ቅዱስ ቴዎዶጦስ
ወልድ ዋሕድ ከአብ መወለዱ እንዴት እንደሆነ ከቅድስት ድንግልም መወለዱ እንዴት እንደሆነ አትጠይቀኝ፡፡ እርሱ በባሕርዩ ከአብ ተወልዷልና ለራሱ በአደረገው ተዋሕዶም ከድንግል ተወልዷልና አምላክ ነው ሰውም ነው፡፡

✤• ፲ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ
አብ ጥንት ፍፃሜ የሌለው ቃልን ዓለምን ከመፍጠሩ አስቀድሞ ወለደው፡፡ በኋላ ዘመንም በግብረ መንፈስ ቅዱስ ንጽሕይት ከምትሆን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ተወለደ።

ይቆየን... ይቀጥላል

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

05 Jan, 15:57


✤✤✤ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በቅዱሳን ድርሳናት ✤✤✤
ቅዱሳን አባቶች ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በድርሳናቸው፣ በመዝሙራቸው፣ በድንጋጌያቸው በመሳሰሉት... ያልዘከሩበት የለም። የእነዚህ ቅዱሳን አባቶች ድርሰቶች ምስጢረ ሥጋዌንና እንዲህ ያሉትን ድንቅ ነገሮች አጉልተው በማሳየት ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡ ከእነዚህም መካከል ስለ በዓለ ልደቱ ካሰፈሩት አባቶች መካከል 1 1ዱን እንጠቅሳለን። 

✤• ፩ ቅዱስ ቻርለስ ዘእስክንድርያ
"O my beloved, ye God-fearing people, open ye the ears of your hearts. (የምወድዳችሁ እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሕዝቦች ሆይ የልቡናችሁን ዦሮዎች ከፍታችሁ የሴቶችን ሁሉ ንግሥት፣ በርሷም ውስጥ የአብ ልጅ በታላቅ ክብር የኖረ የእውነተኛዋን ሙሽራ የእግዚአብሔርን እናት ክብሯን ስሙ፤ መጥቶ በማሕፀኗ ለዘጠኝ ወራት ኖረ ስለእኛ መዳን በቤተ ልሔም ውስጥ ወለደችው በመናኛ የመታቀፊያ ኩታ ጨርቅ ጠቀለለችው፤ በከብቶች ማደሪያ በረት ውስጥ አኖረችው፤ እንስሳትም ርሱን ተመልክተው ዐውቀውት ተገዙለት (እስትንፋሳቸውን ገበሩለት) [ሉቃ. 2፥6]፤

ቅድስት ድንግል ማርያምም የቀኝ ክንዶቿን ዘርግታ በእጆቿ አንሥታ በግራ ክንዶቿ ውስጥም እንዲያርፍ አደረገችው፤ አንገቶቿን ሳታዞር በመቅረቷም ጸጉሮቿ በላዩ ላይ እንዲያርፉ ኾኑ፤ ልክ የባሕርይ አባቱ እንዳደረገው ርሷም አፉን ስማ በጉልበቶቿ ላይ አሳረፈቻቸው፤ ዐይኖቹን ወደ ፊቷ አዞራቸው እጆቹንም ዘርግቶ ጡቶቿን በመሳብ ከመና ይልቅ በጣም ጣፋጭ የነበረውን ወተቷን ባፉ ውስጥ ጨመራቸው፤ ጣእሙም ከኖኅ የመሥዋዕት ሽታ ጣዕም የበለጠ ለርሱ ጣፋጭ ነበረ [ዘፍ. 8፥20] ከንጹሓት ጡቶች ወተትን እየጠባ “የእኔ እናት" ብሎ ይጠራል ... እግዚአብሔር ማርያምን "እናቴ" እያለ በመጣራት ሲስማት ኑና ተመልከቱ፤ ርሷም ኹልጊዜ እየሳመች “ጌታዬና ልጄ" እያለች ትጠራዋለች፤ ታመልከዋለች፤ ጡቶቿንም ስትመግበው ራሷን ለክብሩ ወደርሱ ታስጎነብሳለች፤ ርሱም እንደ ዐምድ ሲቆም “ጌታዬ እና ልጄ" በማለት ታመልከዋለች)

✤• ፪ ቅዱስ ያሬድ
ቅዱስ ያሬድ በስደስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኖረ ኢትዮጵያዊ የነገረ መለኮት ሊቅ እና የዜማ ደራሲ ነው፡፡ ቤተክርስቲያናችን ዛሬም ድረስ ለአገልግሎት የምትጠቀምባቸውን የአገልግሎት መጻሕፍት በአብዛኛው ያዘጋጀው እርሱ ነው፡፡ ዓመቱን ሙሉ ላሉት በዓላት እና አጽዋማት በቀኑና በጊዜያት ምስጋና የሚቀርብባቸውን መጻሕፍት እና ዜማ ደርሷል፡፡ ከእነዚህ መጻሕፍት መካከል ዋነኛው ድጓ የተባለው መጽሐፍ ነው፡፡ ቀጥሎ በዚህ መጽሐፍ ልደትን አስመልክቶ ያቀረባቸው ምስጋናዎች ቀርበዋል፡፡
➥• እምርሁቅ ብሔር አምጽኡ ሎቱ እምሃቡ ወርቀ ከርቤ ወሰሂነ፤ አስከበቶ እሙ ውስተ ጎለ እብን፤ ከደነቶ እሙ ቆጽለ በለሶን፤ ወትቤሎ ስሙ መድኃኔ ዓለም (ስብአ ሰገል ከሩቅ ሀገር እጅ መንሻውን ወርቅ፣ ከርቤ እና እጣን አመጡለት፡፡ እናቱ በድንጋይ በተሰራ ግርግም ላይ አስተኛቸው የበለስ ቅጠልም አለበሰችው ስሙንም መድኃኔ ዓለም አለችው፡፡)
➥• ነያ ዜና ንዜኑ ለዘየአምን፤ እስመ ተወልደ ለክሙ ዮም ምደኅን፣ አምላክ ዘይሠሪ ኀጢአተ ዓለም (እነሆ ለሚያምን ሰው የምሰራችን እንናገራለን፤ ዛሬ የዓለምን ኀጢአት ይቅር የሚል /የሚያጠፋ/ መድኃኒትና አምላክ ተወልዶላችኋል) • በጎል ሰከበ፤ በአጽርቅት ተጠብለለ፤ ውስተ ማኀጸነ ድንግል ኀደረ፤ ዮም ተወልደ እግዚእ ወመድኀን ቤዛ ኩሉ ዓለም (በግርግም ተኛ፤ በጨርቅም ተጠቀለለ በድንግል ማርያም ማኅፀን አደረ፤ የዓለም መድኃኒት ጌታ ዛሬ ተወለደ፡፡)
➥• ዮም በርህ ሠረቀ ለነ፤ ሰማይ ወምድር ዘኢያገምሮ ማኀጸነ ድንግል ጾሮ፤ እንዘ አምላክ ውእቱ ኀደረ ወተገምረ። (ዛሬ ብርሃን ወጣ፤ ሰማይና ምድር የማይችለውን የድንግል ማኅፀን ተሸከመው፤ አምላክ ሲሆን በማኅፀን አደረ፡፡)
➥• ዮም ፍስሃ ኮነ በዛቲ ዕለት፤ ተቤዘነ ኩልነ ዘእም ድንግል በዓልነ ዮም እሃውየ፤ ለነ ሣህልነ ዮም ተወልደ ለነ መድኃኒተ ነፍስነ፡፡ (ዛሬ በዚህች ዕለት ደሰታ ሆነ፤ ከእመቤታችን /በተወለደው/ ኹላችንም ተቤዥን፤ ወንድሞቼ ዛሬ በዓላችን ነው፤ ዛሬ ለኛ የይቅርታችን ዕለት ነው፤ የነፍሳችን መድኃኒት ዛሬ ተወለደ፡፡)
➥• ዮምሰ አሃውየ ሠረቀ ለነ ብርሃን፤ ዮም ተወልደ ክርስቶስ እምድንግል፤ ዮም፤ ዮም ዮም ይትፌስሐ አድባረ ጽዮን፡፡ (ወንድሞቼ ዛሬ ብርሃን ወጣልን፤ ዛሬ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም ተወለደ፤ ዛሬ ዛሬ ዛሬ የጽዮን ተራራዎች ደስ ይበላቸው)
➥• ዮም እግዚአ ሰማያት ወምድር በጎል ሰከበ እሳት በአጽርቅት ተጠብለለ፤ ሀሊቦ ጠበወ፤ ዮም ዘይፀወርዎ ሱራፌል በክንፍ በከርሥ ተፀወሩ፤ ዘያሌዕሎ ለማዕበለ ባሕር ሐሊበ ጠበወ፤ ኢንክል ከቢቦቶ፣ በአርምሞ ናዕኩቶ፤ ንስግድ ሎቱ ለ ክርስቶስ (ዛሬ የሰማይና የምድር ጌታ በግርግም ተኛ፤ እሳት በጨርቅ ተጠቀለለ፤ ወተትን ጠባ፤ ሱራፌል በክንፍ የሚሸከሙት ዛሬ በሆድ አደረ፤ የባሕርን ማዕበል ከፍ የሚያደርግው ወተትን ጠባ፤ እርሱን መክበብ / መድረስ ፣ መረዳት/ አንችልምና በዝምታ እናክብረው ለ ክርስቶስ እንስገድለት፡፡)
➥• ይትፌሳሕ ሰማይ ወትትሃሰይ ምድር በብዙኅ ሰላም በእንተ ልደቱ ለ ክርስቶስ ዮም ሠረቀ ለነ ብርሃን፡፡ (በክርስቶስ ልደት ሰማይና ምድር በብዙ ሰላም እጀግ ደስ ይበላቸው)
➥• አንፈረዓፁ ሰብአ ሰገል ረኪቦሙ ሕፃነ፤ ለመድኃኒትነ መንክር ግርማሁ እምድኅረ ተወልደ ድንግልናሃ ተረክበ፤ እውነ ኮነ ልደቱ፤ ብርሃነ ኮነ ምጽአቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ (ሰብአ ሰገል ሕጻኑን እግኝተው በደስታ ዘለሉ፤ የመድኃኒታችን ግርማው ድንቅ ነው፡፡ ከተወለደ በኋላ / የእናቱ ድንግልናዋ አልጠፋም፤ የመድኃኒታችን ልደቱ እውነት፤ መምጣቱም ብርሃን ሆነ፡፡)

✤• ፫ ቅዱስ ኤፍሬም
ቅዱስ ኤፍሬም በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሶርያ የነበረ የቤተ ክርስቲያን አባት ነው፡፡ በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ከነበሩት ታላላቅ የነገረ መለኮት ምሁራን እና ጸሐፊዎች አንዱ ነው፡፡ የሶርያ ቤተ ክርስቲያን ዛሬም ድረስ የምትጠቀምበትን ዜማ የደረሰውም ቅዱስ ኤፍሬም ነው፡፡

ቅዱስ ኤፍሬም እጅግ በርካታ ድርሰቶችን የደረሰ ሲሆን ከእነዚህ መካከል ስለ ጌታችን ልደት የደረሳቸው ከ4ዐ በላይ መዝሙራት /Hymns on nativity/ ይገኙባቸዋል፡፡ AT YEGITW 1140 I OD NUGT /Hymns on navitY/INIT\..

በእነዚህ መዝሙራቱ የጌታችንን ልደትና በልደቱ የተገለጠውን የጌታችንን ትህትና እና የእመቤታችንን ክብር አጉልቶ ይጽፋል፡፡ ከእነዚህ መካከል ጥቂቶቹ ቀጥለው ቀርበዋል፤ የአባታችን በረከቱ ይደርብን፡፡

በእንተ ልደት /17ኛ መዝሙር/
➥1. እመቤታችን እንዲህ አለች፣ «የምሸከመው ሕጻን ተሸከመኝ፤ ዝቅ ብሎ በክንፎቹ መካከል አስቀመጠኝና ወደ ላይ /ወደ አየር/ በረረ፡፡ «ከፍታው እና ጥልቁ ሁሉ የልጅሽ ነው» ብሎ ቃል ገባልኝ፡፡
➥2. «ጌታ» ብሎ የጠራውን ገብርኤልን እና በትህትና ያቀፈውን አረጋዊ አገልጋይ /ስምዖንን/ ዐየሁ፡፡ ሰብአ ሰገል ሲሰግዱ እና ሄሮድስም ንጉሱ መጥቷል ብሎ ሲሸበርም አየሁ፡፡ 
ይቆየን...ይቀጥላል

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

03 Jan, 13:51


+++ አባ በግዑ +++

[ታኅሣሥ 27 ዝክራቸውን በመዘከር ፤ በጸሎታቸው በመማጸን ብዙ ሰው የማያውቃቸውን ጻድቅ እንወቅ እናስተዋውቅ!]

+ አባ በግዑ በቀደመ ሕይወቱ ሽፍታ የነበረ ፤ ዕድሜውን በማታለል እና በመስረቅ ያሳለፈ ሰው ነበረ፡፡ ይህ ጻድቅ አባት በጉልምስናው ላይ ኀይለኛ እና ብርቱ ነበረና ፤ በጎዳናዎች እየሸመቀ ገንዘብ የያዙ ሰዎችን አስፈራርቶ ይቀማ ነበረ፡፡ በእጁ ጦርና ሰይፍ ይዞ ሰዎችን ያስጨንቅ ነበረ፡፡ የቀደመ ዘመኑን በተለያዩ ምግቦችና መጠጦች ራሱን በማስደሰት የኖረ ነበረ፡፡ ይህም አባት እንዲህ ባለ ሕይወት ይኑር እንጂ በስም ክርስቲያን ነበረ፡፡

+ ይህ ጻድቅ አባት በአንድ ወቅት ወደ ቤተ ክርስቲያን በሄደ ጊዜ አንድ ካህን አግኝቶት ‹‹በዘመንህ ፍጻሜ እግዚአብሔር ይጎበኝሃል ፤ መንፈስ ቅዱስም ያድርብሃል ፤ ፍጹም መነኩሴ ትሆናለህ ፤ ሚስትህን ቤትህን ርስትህንም ትተህ ከሀገርህ ትወጣለህ ፤ ከፍ ወደአለ ቤተ ክርስቲያን ትደርሳለህ በጾም በጸሎት በብዙም መከራም በዚያ ትኖራለህ፡፡›› በማለት ስለ ነገ ሕይወቱ ነገረው፡፡ ከዚህ በኋላ ቤተሰቦቹን ትቶ ወደ ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም ገብቶ አባቶችን እያገለገለ ከአንድ አረጋዊ መነኩሴ ጋር መኖር ጀመረ፡፡ የዐቢይ ጾም በሆነ ጊዜ በትንሽ በዓት ብቻውን ሆኖ በኅብስትና በውኃ ብቻ ይጋደል ነበረ፡፡

+ የሕማማት ሳምንት በሆነ ጊዜ ከመነኮሳቱ ጋር በጋራ ሆኖ አገልግሎቱን ይሳተፍ ነበረ፡፡ በአንድ ወቅት በዚህ በሰሙነ ሕማማት በዕለተ አርብ የስቅለት ዕለት ‹‹ሁሉ ከንቱ ነው ፤ ሁሉ ብላሽ ነው ፤ የዚህ ዓለም አኗኗር ኃላፊ ነው›› የሚል የመጽሐፍ ቃል ሰማ፡፡ ይህን ቃል ከሰማበት ጊዜ ጀምሮ ፍጹም ልቅሶን ያለቅስ ነበረ፡፡ ከዚህ ጊዜም በኋላ ሥጋዊ ሥራን ተወ ፤ እስከሞተበት ጊዜ ድረስ እህል አልበላም ውኃ አልጠጣም፡፡ እጆቹንና እግሮቹን በሰንሰለት በማሰር በጸሎት በጾም የተጋ ሆነ፡፡ ከቅጠል በቀር አንች ሌላ ነገር ስለማይመገብ ከብዙ ረኃብና ጽም የተነሣ ሥጋው እያለቀ ሄደ፡፡

+ ከእጅ ማስገቢያ ቀዳዳ በቀር በጭቃ ተመርጎ ከተዘጋው በዓቱ ውስጥ ቁርባን ለመቀበል በቅዱስ ሚካኤል በዓል በ12 ፤ በጌታችን ልደት በታኅሣሥ 29 ፤ በጌታችን ጥምቀት በጥር 11 እና በጌታችን ትንሣኤ ዕለት ካልሆነ በቀር ፈጽሞ ከበዓቱ አይወጣም ነበረ፡፡ ብዙ መነኮሳትን በምንኩስና ቆብ የወለደ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ እስኪደነቅ ድረስ ሥጋው አልቆ አጥንቱ ብቻ ቀርቶ ፤ ቆዳው ከአጥንቱ ጋር ተጣብቆ እንደ እንጨት እስኪደርቅ ድረስ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ረዳትነት ለ7 ዓመታት ውኃ ሳይጠጣ በጽኑ ተጋድሎ ኖረ፡፡

+ በዚህ ተጋድሎ ውስጥ ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምን ዘወትር በሌሊት ይመለከታት ነበረ፡፡ እርስዋም ዘወትር ታጽናናው ታረጋጋው ነበረ፡፡ በመጨረሻም ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ንጽሕት እናቱ ጋር ተገልጦ ፤ ‹‹ወዳጄ አባ በግዑ ሰላምታ ይገባሃል! ስምህን ለጠራ ፤ መታሰቢያህን ላደረገ ፤ ወደ ተቀበርክበት ቦታ ሄዶ ለተሳለመ ፤ በበዓልህ ቀን ምጽዋት ለሰጠ እስከ ሰባት ትውልድ እምርልሃለሁ ፤ በጸሎትህ አምኖ ከመልካም ሥራ የሠራ የገድልህን መጽሐፍ የሰማ ሁሉ የእሳቱን ባሕር በግልጽ ይለፍ ፤ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይግባ›› አለው፡፡ ከዚህም በኋላ ይህን ታላቅ ቃልኪዳን ተቀብሎ የገዳሙን አባቶች ተሰናብቶ ታኅሣሥ 27 ቀን በክብር አረፈ፡፡

[ጻድቁ የተቀበሩበት ቦታ ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ ነው] በረከቱ ከሁላችን ጋር ትኑር ፤ በጸሎቱ ሀገራችንን ኢትዮጵያን ይጠብቅልን!!!

"በዚህች ዕለት(ታኅሣሥ ፳፯) የአባ በግዑና የአባ ፊልጶስ የሰማዕታት ፍጻሜ የሆነ የኖላዊ መታሰቢያቸው ነው። የመድኃኒታችንም የስቅለቱ መታሰቢያ ነው።" (ስንክሳር ዘወርኃ ታኅሣሥ)

ምንጭ፡
- ‹‹ገድለ አቡነ ኪሮስ ወአባ በግዑ በግእዝና በአማርኛ›› (በሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ አንድነት ገዳም 1996 ዓ.ም የታተመ)

ስብሐት ለእግዚአብሔር
ከዲያቆን ደረጀ ድንቁ

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

01 Jan, 22:28


አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቡልጋ ደብረ ጽላልሽ ወይም ዞረሬ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰበካ ክልል ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ቅድስት እግዚእ ኃረያ መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው፤ በ፲፩፻፺፯ ዓ.ም ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስት ቀናቸው ከእናታቸው እቅፍ ወርደው «አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ» ብለው ሥላሴን አመስግነዋል፡፡ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ትርጓሜውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ 

ስም ፍስሐ ጽዮን በኋላ ተክለሃይማኖት፤ የተወለዱበት ቀን ታኅሣሥ ፳፬ ፲፩፻፺፯፤ የትውልድ ቦታ ቡልጋ፤ የአባት ስም ጸጋዘአብ፤ የእናት ስም ቅድስት እግዚእ ኃርያ፤ ያረፉበት ነሐሴ ፳፬[1]፤ ንግሥ ነሐሴ ፳፬፤ የሚከበሩት በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በኮፕት ቤተክርስቲያን በየኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥንክሳር።

‹ተክል› ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣ የሚበላ፣ የሚሸተት፣ ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ፤ ሥርዓት ማለት ነው [ማቴ.፲፭፥፲፫]፡፡ ‹ሃይማኖት› ማለት ደግሞ በሀልዎተ እግዚአብሔር፣ እግዚአብሔር የሁሉ አስገኚ መሆኑን፣ በሥላሴ አንድነትና ሦስትነት፣ በቅዱሳን ተራዳኢነት ማመን አምኖም መመስከር ማለት ሲሆን ‹ተክለ ሃይማኖት› የሚለው ሐረግም የሃይማኖት ተክል፣ ይኸውም የጽድቅ ፍሬን ያፈራ፣ ከኃጢአት ሐሩር ማምለጫ ዛፍ፣ ምእመናንን በቃለ ወንጌል ያጣፈጠ ቅመም፣ መዓዛ ሕይወቱ የሚማርክ፣ ቢመገቡት ረኃበ ነፍስን የሚያስወግድ ቅጠል፣ የጻድቃን መጠለያ ዕፅ የሚል ትርጕም አለው፡፡‹‹ተክለ ሃይማኖት ማለት የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል ማለት ነው›› ሲል የጻድቁን ስም ይተረጕመዋል፡፡

በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በዐሥራ አምስት ዓመታቸው ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ /ጌርሎስ/ ዲቁናን ተቀብለዋል፡፡ በዚህም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡

ከዕለታት በአንዱ ቀን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከጓደኞቻቸው ጋር ወደ ዱር አደን ሄደው ሳለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ለኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ መረጣቸው። ስማቸውንም «ተክለ ሃይማኖት» አለው፡፡ ትርጓሜውም በሃይማኖት ፍሬ ማለት ነው፡፡

አባታችንም ሐዋርያዊ ጉዟቸውን ሲጀምሩ
«አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደተከፈተ ተውኩልህ . . . ደካማ ለሆንኩ ለእኔ ያለ አንተ የሚያፀናኝ የለም። ለምፍገመገም ለእኔ ያለ አንተ ደጋፊ የለኝም። ለወደቅሁ ለእኔ ያለአንተ የሚያነሳኝ የለም። ለአዘንኩ ለእኔ ያለአንተ የሚያረጋጋኝ የለም። ለድሀው ለእኔ ያለ አንተ መጠጊያ የለኝም፡፡» [ገድለ ተክለ ሃይማኖት ምዕ ፳፰ ቁ ፪ - ፫] ይህን ብለው ትሕትና በተሞላበትና በተሰበረ ልብ ወደ ፈጣሪያቸው ከለመኑ በኋላ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገራት ከኀጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ሃይማኖት መልሰዋል፡፡ በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ፀሐይ ተብለዋል፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን ክታቡ ስለ ቅዱሳን መንፈሳዊ ተጋድሎ ሲገልፅ:-
«እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሱ» [ዕብ. ምዕ ፲፩ ቁ ፴፫ ] እንዳለ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖትም በመንፈሳዊ ተጋድሎ እንዲሁም በትህትና በተአምራት አላዊ የነበረውን ንጉሥ ሞቶሎሚን ወደ ክርስትና መልሰዋል፡፡
«ጽድቅን አደረጉ» እንዳለው አባታችን ወንጌልን በተጋድሎ ሕይወታቸው ተርጉመዋል፡፡
«የአንበሶችን አፍ ዘጉ» [ምዕ ፲፩ ቁ ፴፫ /ምዕ ፲፩ ቁ ፴፬] እንዳለው አባታችንም የአውሬውን፥ የዘንዶውን ራስ ቀጥቅጠዋል።
«ከሰይፍ ስለት አመለጡ» እንዳለው አባታችንም ሞቶሎሚ ከወረወረው ጦር በተአምራት ድነዋል፡፡
«ከድካማቸው በረቱ» እንዳለው አባታችንም ያለ ዕረፍት በብዙ ተጋድሎ በጾምና በስግደት በብዙ መከራ በርትተዋል፡፡
ይህን ሁሉ ገድልና ትሩፋት እየፈጸሙ ዕረፍታቸውም በደረሰ ጊዜ ደቀመዝሙሮቻቸውን «ልጆቼ ሆይ ሁሉም መነኮስ መንግሥተ ሰማይ ይገባል ማለት አይደለም፤ ዓለምን በሚገባ የናቀ ብቻ ይገባል እንጂ መጀመሪያ የእግዚአብሔርን ጽድቁን ብቻ ፈልጉ፤ ጾምና ጸሎትን አዘውትሩ፤ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ ትእዛዛቱንም አጥብቃችሁ ጠብቁ እያሉ ይመክሯቸው ነበር. . .» በኋላም «ለዓለም ጨው ለራሴ አልጫ ሆንኩ፤ ለዓለም ብርሃን ለራሴ ጨለማ ሆንኩ፣ ከእውነተኛው ዳኛ ከጌታዬ ፊት ስቆም ምን እመልሳለሁ?» እያሉ በፍጹም ትህትና እና በልዩ መንፈሳዊ ተመስጦ ይጸልዩ ነበር፡፡

ስለዚህም ቤተ ክርስቲያናችን ጻድቃንን እንድናስባቸው፣ በስማቸውም ለድሆች እንድንመጸውት፣ መታሰቢያቸውን እንድናደርግ የምትመክረን፤ የምታስተምረን [ማቴ.፲፥፵፩-፵፪]፡፡ ቅዱሳን ጻድቃን በሕይወተ ሥጋ ሳሉም ሆነ ከሞቱ በኋላ በዐጸደ ነፍስ ሆነው በጸሎታቸው ለሚታመኑ፣ በቃል ኪዳናቸው ለሚማጸኑ ምእመናን በመጸለይና ወደ እግዚአብሔር በማማለድ ድኅነተ ሥጋ፣ የድኅነት ነፍስን የሚያስገኙልን የችግር ጊዜ አማላጆቻችንና አስታራቂዎቻን ናቸው፤ ከእነዚህ ቅዱሳን መካከል ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንደኛው ናቸው፡፡

አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው፣ በብሕትውና ኖረዋል፡፡ በተጨማሪም እንደቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ የሰበኩ፣ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሐዋርያ ናቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከሚታወሱባቸው በዓላት መካከልም ታኅሣሥ ፳፬ ቀን የሚከብረው በዓለ ልደታቸው አንደኛው ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ዜና ልደታቸውን ሲናገር ‹‹ሐዲስ ሐዋርያ›› በማለት በክብር ጠርቷቸዋል፡፡
                                            
                                           ✥••┈••●◉  ✞  ◉●••┈••✥

ምንጭ፡– ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፤ መጽሐፈ ስንክሳር (ታኅሣሥ ፳፬፣ ጥር ፳፬፣ መጋቢት ፳፬፣ ግንቦት ፲፪ እና ነሐሴ ፳፬ ቀን)፤ መለከት መጽሔት ፲፰ኛ ዓመት፣ ቍጥር ፱፡፡

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

30 Dec, 01:32


ዲያቆን ኤስሮም ተሾመ የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት ፍሬ ነው እነሆ በዐዲስ ዝማሬ መቷል አካውንቱንም ሰብስክራይብ ሼር ላይክ በማድረግ እድናበረታታውና ከጎኑ እንድንሆን እላለሁ።
ዝማሬ መላእክት ያሰማልን ያጉልግሎት ዘመንህንም ያርዝምልህ።


https://youtu.be/zTzd-itwqNA?si=w5PesIzr7XfGZNto

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

27 Dec, 21:02


ምንጭ:- ብሥራት ዘአንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት 6ኛ ዓመት 9ኛ እትም

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

26 Dec, 22:45


꧁ ብርሃን ገላጭ ሰላማ ꧂
ፍሬምናጦስ በእንግሊዘኛ Frumentius የተወለዱት ታይር በምትባል ቦታ በምሥራቃዊ የሮማ ነገሥት በ፬ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያዎቹ ሲሆን ማንም መርምሮ ሊደርስበት በማይችለው በእግዚአብሔር ሀሳብ ወደ ኢትዮጵያ መተው ክርስትናን ከመሠረቱት ዋነኛው አባት ሆኖ በመቆጠር፣ አገራችንን ከሌሎች ክርስቲያን አገሮች ጋር ያስተዋወቁ፣ ያስተካከሉ፣ በአክሱም ዘመነ መንግሥትና መንግሥት የተወደዱና የተከበሩ ፣ በመላው ኢትዮጵያ የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች የተከበሩ ታላቅ አባት ናቸው።

ስም መጀመሪያ ፍሬምናጦስ በኋላ አቡነ ሰላማ ክሳቴ ብርሃን፤ የተወለዱት በ፬ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ፤ የትውልድ ቦታ ሶርያ፤ ኖረው ያረፉት በአክሱም ኢትዮጵያ በ፫፻፸፭ ዓ.ም.፤ ዓመታዊ በዓላቸው የሚከበረው ታኅሣሥ ፲፰ ቀን በኢትዮጵያ አቆጣጠር ዲሴምበር 14 በጁሊያን ካላንደር ኦክቶበር 27 በጌሬጎሪያን አቆጣጠር፤ የሚከበሩት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በኮፕት ቤተ ክርስቲያንና በኦርየንታል ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን

“ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጒድጓድ ተቅበዘበዙ።” [ዕብ. 11፥38]። በእርግጥ ዓለም ለእገሌ ይገባል ለእገሌ አይገባም የምትባል አይደለችም። ቅዱሳን መናንያን ግን በራሳቸው ፈቃደ ዓለምን አንፈልግሽም ስላሏት ዓለም አልተገባቸውም ተባሉ። እንደ ማንኛውም ሰው በዓለም መኖር ሲችሉ ዓለምን ንቀው መኖሪያቸውን በተራራና በዋሻ አደረጉ። ያላቸውን ንቀው እንደ ሌላቸው በመሆን ስለ ሰማያዊ ፍቅር መከራን ተቀበሉ። “ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ” [ዕብ. 11፥37]

ወዳጄ ሆይ! ለመሆኑ ቅዱሳን አባቶቻችን የሞቀ ቤታቸውን ጥለው በዱር በጫካ ከአራዊት ጋራ መኖርን መምረጣቸው እንደ ሞኝነት ይቆጠር ይሆን? ወይስ እውቀት ያነሳቸው ይመስልሃል? አይደለም። በሳይንሱ ዓለም ትምህርት ተምረው ዲፕሎም፣ ዲግሪ፣ ማስትሬት የጨረሱ ዶክትሬትም ጨብጠው ወደ ገዳም የገቡ ብዙዎች ናቸው። እነዚህ ቅዱሳን በዓለም ላይ ሳሉ ብዙ ነገር ቢኖራቸውም እንኳን የሚበልጠውን ሰማያዊ ፍቅር ፈልገው ሁሉንም ትተው ወደ ምናኔ ገቡ።
      
“እውነት እላችኋለሁ እናንተስ የተከተላችሁኝ፥ በዳግመኛ ልደት የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን በሚቀመጥበት ጊዜ፥ እናንተ ደግሞ በአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ ስትፈርዱ በአሥራ ሁለት ዙፋን ትቀመጣላችሁ።” [ማቴ. 19፥28]።

ወዳጄ ሆይ! የቅዱሳን ገዳማውያን ገድል የሕይወታቸው ኑሮ ለሁሉም መልካም ምሳሌና አርአያ ሊሆን ይችላል። ከምንም በላይ ደግሞ እምነታችን ለማጠንከርም ይረዳናል። ምክንያቱም ጠንካራ እምነት ማምጣት የምንችለው የእምነት ጀግኖች አባቶቻችንን የሰሩትን አብነት በማድረግ ነው። አዎ! የቅዱሳንን ሕይወት ማጥናት ለእኛም ከይስሙላ ወይም ከታይታ ኑሮ ወጥተን በትክክል የተቀየረ ሕይወት እንዲኖረን ያግዘናል። ስለሆነም ቅዱሳን በየዕለቱ ሥራቸውን እንድናስታውስና ሕይወታቸው የመንፈስ ምግብ ማድረግ ይገባናል። እንግዲህ ወዳጄ የቅዱሳን ገዳማውያን በረከታቸው ለማግኘትና ከሕይወታቸው ተምረን ብርሃን የሆነውን መንገዳቸውን እንድንከተል ወደ ታሪካቸው እንሻገር። “የጻድቃን መንገድ ግን እንደ ንጋት ብርሃን ነው።” [ምሳ. 4፥18]

ወዳጄ ሆይ! ˝ባሕርን በጭልፋ˝ እንደሚባለው በዚህች ብጣሽ ወረቀት የሁሉንም ቅዱሳን መናንያን ታሪክ መዘርዘር ባይቻልም ከቅዱሳን ታሪክ የዚሁ ቅዱስ ጻድቅ ራሱ እንደ ሻማ እየቀለጠ ለእኛ ብርሃን የሆነ የታላቁ አባታችን አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ፍቅሩን እንመልከት። አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን በሦስተኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ በኅዳር 26/ 245 ዓ.ም ከአባቱ ቅዱስ ምናጦስና ከእናቱ ቅድስት ማርያም ሰናይት በጢሮስ /ግሪክ/ ተወለደ። የመጀመሪያ ስሙ ፍሬምናጦስ ይባላል።

አባታችን አቡነ ሰላማ የ12 ዓመት ልጅ እያለ ሜሮጵዮስ የተባለ ነጋዴ /ፈላስፋ/ ይዞት ወደ አገራችን በእግዚአብሔር ፈቃድ መጣ። ከእርሱም ጋር ኤድስዮስ የተባለም አብሮት እንደነበረ ይታወቃል። እነዚህን ሁለት ወጣቶች አስከትሎ የመጣው ሜሮጵዮስ በቀይ ባሕር አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች በጣሉለት አደጋ በዚሁ እንደ ሞተ ታሪክ ይነግረናል። ፍሬምናጦስና ኤድስዮስ ግን በወቅቱ የአክሱም ንጉሥ የነበረው ንጉሥ ታዜር ጋር አድገዋል። ንጉሡ በአእምሮ መብሰላቸውን ተመልክቶ ፍሬምናጦስ በጅሮንድ ኤድስዮስም ጋሻ ጃግሬው አድርጎ ሾማቸው።

ከዚያ በኋላ ንጉሥ ታዜር ሲያርፍ ወደ ፈለጉበት እንድሄዱ ነፃ ስለተለቀቁ ኤድስዮስ ወደ አገሩ ተመልሶ ሄዷል። አባታችን አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ግን በጨለማ የሚኖረውን ሕዝብ ትቼ ወደ አገሬ አልመለስም በማለት እኛን በማፍቀር እንደቀረ ታሪክ ያስረዳናል። ወዳጄ! የቅዱሳን ፍቅራቸው እውነትም ልብ ይነካል።

በዚያን ጊዜ በአገራችን ኢትዮጵያ ሥርዓተ ንስሐ፣ ሥርዓተ ጥምቀት፣ ሥርዓተ ቅዳሴ፣ ሥርዓተ ቅዱስ ቊርባን የሚያከናውን ጳጳስ ስላልነበረ ይህን የተመለከቱ ነገሥታት ኢዛናና ሳይዛና ጵጵስና እንዲያመጣ አባታችን አቡነ ሰላማን ወደ ግብጽ ላኩት። አባታችንም ወደ ግብጽ በመሄድ ሥርዓቶቹን በመማር በቅዱስ አትናትዮስ አንብሮተ እድ ˝ኤዽስ ቆጶስ ዘአክሱም ወዘኩላ ኢትዮጵያ” ተብሎ ጵጵስና ተቀበለ። ወደ አገራችን ከተመለሰ በኋላ መጀመሪያ ነገሥታት ኢዛናና ሳይዛናን አጥምቆና አቁርቦ አብርሃ ወአጽበሃ በማለት ስመ ክርስትና ሰጣቸው። በመቀጠልም በመላው አገራችን እየተዘዋወረ በማስተማር ሥርዓቱን ፈጽሟል። ከዚህም የተነሳ ጨለማን አስወግዶ ብርሃንን የገለጠ ቀዳሚ የምድረ ሐበሻ ታላቅ ሐዋርያ ነው። የቀናች ሃይማኖትን በማስተማር ጨለማውን ብርሃን በማድረጉ “ብርሃን ገላጭ ሰላማ” ተብሏል። የሓምሌ ወር ስንክሳር።

አባታችን አቡነ ሰላማ በኢትዮጵያና ኤርትራ በእግራቸው ተመላልሰው ወንጌል እንዳስተማሩ ስፍር ቊጥር የሌላቸው ድውያንን ፈውሰው ሙታንን እንዳስነሡ ገድላቸው ያስረዳናል። በተለያዩ ባዕድ አምልኮ ያመልክ የነበረ ሕዝብም በጣፋጭ ስብከቱ እግዚአብሔርን ወደ ማመን መልሰዋል። በጸሎታቸው አጋንንትን ጠራርገው ከአገራችን በማስወጣት ሰላም የሰጡን የሰላም አባት ናቸው። ˝ሰላማ˝ ማለት ˝ሰውና እግዚአብሔርን የሚያስታርቅ˝ ማለት ነው።

አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን በ 350 ዓ.ም ክርስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ሆኖ እንዲታወጅ አድርጓል። ቅዱስ ያሬድ “ዝንቱ ብእሲ መምህርነ ዘተፈነወ ውስተ ምድርነ ይከሰተ ብርሃነ” በማለት አመስግኖታል። ብርሃንን ለመግለጥ ወደ አገራችን የተላከ መምህራችን ማለቱ ነው። በልጅነታቸው የመጡት አባታችን አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን የአገራችን ፍቅር አስገድዷቸው እስከ ዕለተ ዕረፍታቸው በአገራችን የኖሩ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያቶች ውስጥ የሠሯቸው የተለያዩ ድንቅ ሥራዎች መቼም የማይረሱ ናቸው።

ድንቅ ሥራዎቻቸው
➥ ወንጌል የሚያስተምሩና የሚያጠምቁ የሚያቆርቡ ካህናትና ዲያቆናት ሾመ።
➥ ለምእመናን መካሪ የንስሐ አባት እንዲኖራቸው አድርጓል።
➥ ከአብርሃ ወአጽብሃ ጋር በመሆን አብያተ ክርስቲያን አንጸዋል።
➥ ቅዱሳት መጻሕፍት ከሱርስት፣ እብራይስጥና ከግሪክ ወደ ግእዝ ቋንቋ እንዲተረጎሙ አድርጓል።
➥ የሳባውያን ፊደል አቀማመጥ በማስተካከል ከግራ ወደ ቀኝ የመጻፍንና የማንበብን ዘዴ በማስተማር በተጨማሪ ፊደላችን ➥ የተለያየ ድምፅ ኢንዲኖረው (ቯዬል፡voyelle) በመጨመር ብዙ ውለታ የዋሉልን ታላቅ አባት ናቸው።

 የአባታችን ረድኤት በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን።
➥ይቆየን

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

25 Dec, 20:19


ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕት
ክርስትናን በሰማዕትነት በማሳደግ የመጀመሪያ ምሳሌ የሆነ ሊቀ መምህር

እስጢፋኖስ (በግሪክ: Στέφανος ሲነበብ ፡ Stéphanos ስቴፋኖስ፤ በዕብራይስጥ ፡ הקדוש סטפנוס ፤ በእንግሊዘኛ ፡ Stephen ሲነበብ ፡ ስቴፈን) በሕገ ወንጌል (በክርስትና) የመጀመሪያው ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳሚው ሰማዕት ይህ ቅዱስ ነው።

የተወለደው በ፩ኛው ክፍለ ዘመን፤ የትውልድ ቦታ ኢየሩሳሌም፤ የእናት ስም ማርያም፤ የአባት ስም ስምዖን፤ የሚከበረው በመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ሥንክሳር፤ በዓለ ንግሥ ሲመቱ ጥቅምት ፲፯ ቀን፣ ዕረፍቱ ጥር ፩ ቀን ፍልሰቱ መስከረም ፲፯ ቀን
በግብፅ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን ቶቢ ፩ ቀን በምዕራባውያን ዲሴምበር ፳፮ ቀን፤ ያረፈበት ቀን ጥር ፩ ቀን በመናፍቃን በድንጋይ ተወግሮ

ቅዱሱ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር። ይህም በወጣትነት ያለፈችው ሕይወቱ ስትሠራ የነበረው ታላቅ መንፈሳዊ ሥራ ይመሠክራል።

የቅዱስ እስጢፋኖስ ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም ይባላሉ። (ሌሎች ናቸው የሚሉም አሉ) ገና ከልጅነቱ ቁም ነገር ወዳድ የነበረው ቅዱስ በሥርዓተ ኦሪት አድጐ እድሜው ሲደርስ ወደ ት/ቤት ገባ። የወቅቱ ታላቅ መምህር ገማልያል ይባል ነበር። ይህ ሰው [በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፭፥፴፫] ላይ ተጠቅሷል። በትውፊት ትምህርት ደግሞ ይህ ደግ (ትልቅ) ሰው በርካታ ቅዱሳንን (እስጢፋኖስን፣ ጳውሎስን፣ ናትናኤልን፣ ኒቆዲሞስን...) አስተምሯል። በጌታችን መዋዕለ ስብከት ጊዜም ከፈጣሪያችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ እየቀረበ ይጨዋወት ነበር ፤ በፍጻሜውም አምኗል ። ቅዱስ እስጢፋኖስም ከዚህ ምሑር ዘንድ ተምሮ ኦሪቱን ነቢያቱን ጠንቅቆ ወጣ። ወቅቱ አስቸጋሪና ለኃጢአት ሕይወት የተመቸ ቢሆንም ቅዱሱ ግን የመሲህን መምጣት በጸሎትና በተስፋ ይጠባበቅ ነበር።

ከቅዱስ ዮሐንስ መጥምቁ ጋር
በወቅቱ ደግሞ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ የንስሐ ጥምቀትን እየሰበከ መምጣቱን የተመለከተ ቅዱስ እስጢፋኖስ ነገሩን መረመረ። ከእግዚአብሔር ሆኖ ቢያገኘው የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆነ። ለስድስት ወራትም በትጋት ቅዱስ ዮሐንስን አገለገለ። ለስድስት ወራት ከቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ ከተማረ በኋላ ለስም አጠራሩ ስግደት ይድረሰውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠመቀ። በወቅቱ የተደረገውን ታላቅ ተአምር ልብ ያለው ቅዱስ እስጢፋኖስ መምህሩን ቅዱስ ዮሐንስን እንዲያስረዳው ጠየቀው። "ከእኔ ይልቅ ከፈጣሪው አንደበት ይስማው።" በሚል ላከው። ቅዱሱም ከጌታ ዘንድ ሔዶ እጅ ነስቶ ተማረ። [ሉቃ. ፯፥፲፰] በዚያውም የጌታ ደቀ መዝሙር ሆኖ ቀረ።

ወንጌል ስለማጥናቱ
ጌታም ከሰባ ኹለቱ አርድእት አንዱ አድርጐት ለአገልግሎት ላከው፤ አጋንንትም ተገዙለት። [ሉቃ. ፲፥፲፯] ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታችን መድኃኔ ዓለም ከዋለበት እየዋለ ካደረበት እያደረ ወንጌልን ተማረ፤ ምስጢር አስተረጐመ። ጌታ በፈቃዱ ስለ እኛ ሙቶ ከተነሳ በኋላ ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን በአንብሮ እድ ባርኳል። በዚህ ጊዜም ቅዱሱ እንደ ወንድሞቹ ሐዋርያት ቅስናን (ጵጵስናን) ተሹሟል። በበዓለ ሃምሳም መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከሰባ ኹለቱ አርድእት የእርሱን ያህል ልሳን የበዛለት፣ ምሥጢርን የተገለጠለት የለም። በፍጹም ድፍረትም ወንጌልን ይሰብክ ገባ።

በመጀመሪያይቱ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከማዕድ ሥርዓት ጋር በተያያዘ ፈተና ሲመጣ በመንፈስ ቅዱስ ምርጫ ሰባቱ ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር። አልፎም የስድስቱ ዲያቆናት አለቃ እና የስምንት ሺው ማኅበር መሪ(አስተዳዳሪ) ሆኑዋል። ስምንት ሺህ ሰውን ከአጋንንት መጠበቅ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ አባቶቻችን መጠየቅ ነው። አንድን ሰው ተቆጣጥሮ ለደኅንነት ማብቃት እንኳን እጅግ ፈተና ነው። መጸሐፍ እንደሚል ግን መንፈስ ቅዱስ የሞላበት ማኅደር እግዚአብሔር ነውና ለርሱ ተቻለው። [ሐዋር፣ሥ፡፮ ቁ፡፭] አንዳንዶቻችን ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ሲባል እንደዘመኑ ይመስለን ይሆናል። እርሱ በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነው። ዲቁና ለእርሱ " በራት ላይ ዳርጎት" እንጂ እንዲሁ ድቁና አይደለም።

ከጌታችን ዕርገት በኋላ
ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በኋላ ለአንድ ዓመት ያህል ስምንት ሺውን ማኅበር እየመራ ወንጌልን እየሰበከ ቢጋደል ኦሪት "እጠፋ እጠፋ" አለች። በዚህ ጊዜ "ክርስትናን ለማጥፋት መፍትሔው  ቅዱስ እስጢፋኖስን መግደል ነው " ብለው አይሁድ በማመናቸው አልቀረም ገደሉት። እርሱ ግን ፊቱ እንደ እግዚአብሔር መልአክ እያበራ ፈጣሪውን በብዙ ነገር መሰለው። በመጨረሻውም ስለ እነሱ ምሕረትን እየለመነ በድንጋይ ወገሩት። ደቀ መዝሙርቱም ታላቅ ለቅሶን እያለቀሱ ቀበሩት።

ከአረፈ በኋላ 
ቅዱስ እስጢፋኖስ ከአረፈ ከሦስት መቶ ዓመት በኋላ በኢየሩሳሌም የሚኖር አንድ ደግ ሰው ነበረ ስሙም ሉኪያኖስ ይባላል። በተደጋጋሚ በራዕዪ ቅዱሱ እየተገለጠለት "ሥጋዬን አውጣ" ይለው ነበርና ሒዶ ለጳጳሱ ነገረው። ጳጳሱም ደስ ብሎት ካህናትና ምዕመናንን ሰብስቦ ወደ አፀደ ገማልያል ማለት ወደ መምህሩ ሄደ። ቦታውንም በቆፈሩ ጊዜ ታላቅ መነዋወጥ ሆነ። መላዕክት ሲያጥኑም በጎ መዓዛ ሸተተ። ዝማሬ መላዕክትም ተሰማ። ሕዝቡና ጳጳሱም በቅዱስ እስጢፋኖስ ፊት ሰግደው በታላቅ ዝማሬና በሐሴት ዐፅሙን ከዚያ አውጥተው በጽርሐ ጽዮን (በተቀደሰችው ቤት) አኖሩት። እለ እስክንድሮስ የተባለ ደግ ሰውም ቤተክርስቲያን አነጸለት ወደዚያ  አገቡት።
ከአምስት ዓመታት በኋላም እስክንድሮስ ሲያርፍ በሳጥን አድርገው በቅዱሱ ጎን አኖሩት። የእስክንድሮስ ባለቤት ግን ወደ ሀገሩዋ ቁስጥንጥኒያ ስትመለስ የባሏ ሥጋ መስሉዋት የእስጢፋኖስን ቅዱስ ሥጋ በመርከብ ጭና ወሰደችው። መንገድላይም ከሳጥኑ ውስጥ ዝማሬ ሰምታ ብታየው ያመጣችው የቅዱሱን ሥጋ ነው። እጅግም ደስ አላት አምላክ ለዚህ አድሉዋታልና። እርሷም ወስዳ ለታላቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆስጥንጢኖስ አስረከበችው። በከተማው ታላቅ ሐሴት ተደረገ። ሥጋውን ሊያኖሩት በበቅሎ ጭነው ሲወስዱትም በቅሎዋ በሰው ልሳን ተናግራ ማረፊያውን አሳወቀች። በዚያም ላይ ትልቅ ቤተክርስቲያን ታንጾለታል።[1]

ማጣቀሻ
* ሲመቱ ጥቅምት ፲፯ ቀን፤ ዕረፍቱ ጥር ፩ ቀን ፍልሰቱ መስከረም ፲፭ ቀን ነው ።
^ ከስንክሳር የተገኘ መረጃ
* መጽሐፍ ቅዱስ (የሐዋርያት ሥራ አንድምታ)
* መዝገበ ቅዱሳን

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

17 Dec, 19:38


#ተጀመረ #ለጥያቄዎ? #መልስ! ፤ ይግቡ፣ ያጋሩ
ሰዎችን ይቅርታ መጠየቅ ከበደኝ! ምን ላድርግ? ፤
https://youtu.be/RtTSQqMDQ-M?feature=shared
#Subscribe #Share #like
የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሀገረ ስብከት ሚድያ

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

16 Dec, 21:02


https://youtu.be/MPOUiGcOaJo?si=Ot6O2oYbEXnjIc95

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

15 Dec, 21:15


https://youtu.be/dhdEkVzE_x4?si=cBoO5HDEceVjdxar

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

12 Dec, 07:12


 “ልጄ ሆይ ስሚ፣ ጆሮሽንም አዘንቢዪ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፤ እርሱ ጌታሽ ነውና፡፡” [መዝ.44፡10] የሚለው ቃል መፈጸሙን እናስተውላለን፡፡

የጌታን መወለድ በተስፋ ሲጠባበቁ ለነበሩ ቅዱሳን አበው ይህች ቀን እጅግ ታላቅ እለት ነበረች፤ ምክንያቱም የመዳናቸው ቀን መቃረቧን የምታበሥር ቀን ነበረችና፡፡ ለእኛም ለክርስቲያኖች ይህች ቀን ታላቅ የሆነ በረከት ያላት ናት፡፡ ሙሴ የመገናኛ ድንኳኗንና በውስጡ ያሉትን ነዋያተ ቅዱሳት የጥጃና የፍየሎች ደምን ከውኃ ጋር በመቀላቅል በቀይ የበግ ጠጉርና በሂሶጵ በመንከር ረጭቶ ቀድሶአት ነበር፡፡[ዘጸ.24፡7-8፤ ዕብ.9፡18-22] ንጉሥ ሰሎሞንም እርሱ ያሠራውን ቤተመቅደስ እርሱና ሕዝቡ ባቀረቡት የእንስሳት መሥዋዕት ቀደሷት ነበር፡፡(1ነገሥ.8፡23) እነዚህ ሥርዐታት ግን ክርስቶስ በደሙ ለሚዋጃት ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ነበሩ፡፡

በዚህች ቀን ቅድስት እናታችን ራሱዋን የጌታ ቤተ መቅደስ በማድረግ የብሉዩዋ ቤተመቅደስ ክርስቶስ በደሙ በዋጃት ቤተክርስቲያን ልትተካ መቃረቡዋን ለማብሠር ወደ ቤተ መቅደስ ያመራችበት ቀን ነው፡፡ ጌታችንም ከእርሱዋ የነሳውን ሥጋና ነፍስ በተዋሕዶ የራሱ ቤተመቅደስ በማድረግና እኛንም በጥምቀት የአካሉ ሕዋሳት እንድንሆን በማብቃት ሥጋችንን የመንፈስ ቅዱስ ቤተመቅደስ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ስለዚህም እኛ ክርስቲያኖች የቅድስት ድንግል ማርያምን ወደ ቤተመቅደስ መግባት ባሰብን ቊጥር እግዚአብሔር ቃል ከእርሱዋ በሥጋ በመወለዱ ያገኘነውን ድኅነትና ብዙ ጸጋዎችን እናስባለን፡፡ አሁን እኛ ክርስቲያኖች በጥምቀት ከእርሱዋ የተወለደውን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ለብሰነዋል፤ (ገላ.3፡27) ከእርሱዋ በነሣው ተፈጥሮ በኩል ሞትን በመስቀሉ ገድሎ ሲያስወግደው፣ እኛም በጥምቀት ከእርሱ ሞት ጋር በመተባበራችን ሞትን ድል የምንነሣበትን ኃይልን ታጥቀናል፡፡ በጥምቀት ያገኘነውን ጸጋ ሠርተንበትና አብዝተነው ብንገኝ ከትንሣኤው ተካፋዮች መሆንን እናገኛለን፡፡ ይህ ሁሉ የተፈጸመልን እግዚአብሔር ቃል ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ በመወለዱ ምክንያት ነው፡፡

ቅድስት ድንግል ማርያም ብሉይን ከሐዲስ ያገኛኘች መንፈሳዊት ድልድይ ናት፡፡ በብሉይ ያሉት ቅዱሳን በሐዲስ ኪዳን ካለነው ጋር አንድ ማኅበር የፈጠሩትና ከቅዱሳን መላእክትም ጋር እርቅ የወረደው ከእርሱዋ በነሳው ሰውነት በኩል ነው፡፡ ስለዚህም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “እንግዲህስ ወዲህ እናንተ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም”[ኤፌ.2፡19] ብሎ አስተማረ፡፡ ራሷን የጌታ ቤተ መቅደስ በማድረግ እኛንም በልጁዋ በኩል የመንፈሱ ቤተ መቅደስ እንድንሆን ምክንያት ሆናልናለችና የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተመቅደስ መግባት ለእኛ ክርስቲያኖች ልዩ ትርጉም አለው፤ ስለዚህም ይህቺን እለት በታላቅ ድምቀት እናከብራታለን፡፡

                           ✥••┈••●◉ ይቆየን ◉●••┈••✥
እግዚአብሔር አምላክ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም
ረድኤትና በረከት ያሳትፈን
ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

10 Dec, 20:20


https://youtu.be/eWoqa2SZeLw?si=d4vksEUXhugIyOo1

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

10 Dec, 15:02


https://youtu.be/hGciNxI_tk4?si=z7aA9031briOaDuK

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

10 Dec, 12:49


https://youtu.be/09ljJZMpvTw?si=4W1RelXW0C5JDa7Y&sfnsn=scwspmo

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

30 Nov, 11:57


‼️‼️ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን አዲስ ስብከት‼️‼️

"ለምን እንጾማለን....... ይህንን ሳትረዱ አትጹሙ"

በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን በተዘጋጀው ልዩ ጉባኤ ላይ ያስተመሩት እጅግ ድንቅ የሆነ ትምህርት ከታች ባለው የ youtube link ከፍተው ያድምጡ!!

የዩቱዩብ ገፃችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁን ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ።

https://youtu.be/te-t8jxjSjo?si=r9aHVQasj0rqthtb&sfnsn=scwspmo

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

29 Nov, 16:27


እመቤታችን ሆይ፣ የቅዱሳንና የምእመናንን ኹሉ ጸሎት በማዕጠንታቸው ከምድር ወደ ሰማይ በሚያሳርጉ በሰማያውያን የካህናት አለቆች አጆች ውስጥ ባለ የወርቅ ማዕጠንት እንመስልሻለን። እንዲኹም ስምሽን በመጥራት የሰው ልጆችን ልመና ወደ ልዩ ሦስትነት አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያሳርጋሉ። የወገኖችሽንም ኅጢአት ታስተሠርዪ ዘንድ ከአብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ተፈቅዶልሻልና። ለሰዎች ልጆች የዘለዓለም ሕይወት ድልድይ ትሆኝ ዘንድ የዓለም ኹሉ መድኃኒት ሆይ፣ ለምእመናን ወገኖችሽ መድኃኒታቸው ልትባይ ይገባል። ቅድስት ሆይ ልጅሽ ይቅርታውን ያድለን ዘንድ ለምኝልን።

አንቀጸ ብርሃን

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

28 Nov, 07:16


በሠራዊት ሁሉ ላይ የተሾመ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው። [ሄኖ.10:14]
ሰላም ለሰኰናከ
ገብርኤል ሆይ፥ በዚያ ድብቅልቅና ሽብር በሆነበት ዕለት ከጌታ እግረ መስቀል ሥር ለቆሙት ተረከዞችህና ጫማዎችህ ሰላም እላለሁ፤ ገብርኤል ሆይ የጌታን ትዕግሥት የአይሁድን ግፍ ተመልክተህ በታላቅ ዐደባባይ ላይ ሰይፈ ቁጣህን አምዘገዘግኸው ቅዱሳት አንስት ግን ክርስቶስ ተነሥቷል ስላልካቸው የትንሣኤውን ምሥራች ይነግሩ ዘንድ ወደ ሐዋርያት ሄዱ።

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

26 Nov, 08:29


በአንድ ወቅት በብዛትና በአንድነት ሲጠፉ ለምን ጠፍ ምክንያቱ ምንድን ነው ሳንል ራሳችንን አገልግሎታችንን ሳንፈትሽ ጸጥ ብለን በሆነ ወቅት ደሞ እነዛው የጠፉት መመለስ ሲጀምሮ የምን ማንጎራጎር ማብዛት ነው። አገልግሎት ምንድን ነው
አገልግሎት ማለት በፍቃደኝነት በተሰጠን ጸጋ(ስጦታ ) ልዑል እግዚአብሔርን ማገልገል ማለት አይደለምን? ለዚህ ደግሞ ሁሉም ተጠርቷል፡፡

አገልግሎት በእግዚአብሔር ጥሪ የሚጀመር መንፈሳዊ ተልዕኮ ነው፤ 
እግዚአብሔር ሰዎችን ያገለግሉት ዘንድና የፍቅሩ ተሳታፊዎች ይሆኑ ዘንድ ይጠራል፡፡
አግልግሎት በእግዚአብሔር እና በሰው ልጆች መካከል ያለ የፍቅር መግለጫ ነው፡፡
አግልግሎት ከእግዚአብሔር የተደረገልንን ውለታ ማሰብ ነው፡፡
አንድ አባት ”ቤተ ክርስቲያን አምጥታናለች፤ አስተምራናለች ለጌታችንም አንድንገዛ አድርጋናለች“ ብለዋል፡፡

አገልግሎት ማለት ያዩትን እና የሰሙትን የእግዚአብሔርን ቸርነት መመስከር ያወቁትን መንፈሳዊ ዕውቀት ላላወቀ ማሳወቅ ማለት ነው፡፡

የቤተ ክርስቲያን አገለግሎት ዋና ዓላማው የጠፋውን የሰው ልጅ ለድኀነት ማብቃት ነው፡፡ ሰው ለድኀነት የሚበቃው አዕማደ ምስጢራትን አምኖ ሲፈጽም በአመነበት እምነት ጸንቶ ከኃጢአት በመጠበቅ እግዚአብሔርን ሲያገልግል ነው፡፡ [2ኛ ጢሞ 2፤15 ”የእውነት ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍርም ሠራተኛ ኾነኽ፥ የተፈተነውን ራስኽን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ።"
ለመጣችሁም በመምጣት ሂደት ላይ ያላችሁም የምትመጡም እንኩዋን ወደ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖታችሁ ተመለሳችሁ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን ደግሞም ያጽናችሁ።

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

23 Nov, 21:38


ለምን ያህል ሰዓት ምግብ ከመብላት እንቆጠብ? 
አንድ ሰው በጾም ወቅት ምግብ ከመብላት የሚቆጠብበት ጊዜ እንደ እድሜ፣ አቅም፣ የጤና ኹኔታ እና የሥራጫና የሚወሰን ነው፡፡ እነዚህን መሠረታዊ መስፈርቶች እንመልከታቸው፡፡
1. መንፈሳዊ አቅም/ብስለት [Spiritual Maturity] - አንድ ሰው ከፍተኛ የሆነ መንፈሳዊ አቅም/ብስለት ካለው፤ ለረጅም ሰዓት ምግብ ሳይበላ መቆየት ይችላል፡፡ ለምሳሌ ያህል፡- አንዳንድ ገዳማውያን እና ባህታዊያን በሦስት እና በአራት ቀን አንድ ጊዜ ብቻ በጥቂቱ እየተመገቡ መቆየት ይችላሉ፡፡ ዝቅተኛ የሆነ መንፈሳዊ አቅም ያለን ግን በአቅማችን መጾም መቻል አለብን፡፡ ሌሎችን ዐይተን ‘ለምን ይበልጡናል’ በሚል ስሜት ብንንጠራራ ግን ራሳችንን እንጎዳለንእንጂ፤ መንፈሳዊ በረከትን አናገኝበትም፡፡

2. እድሜ [Age] - በጾም ወቅት የምናየው ኹለተኛ መስፈርት እድሜ ነው፡፡ አንድ ጾምን በመለማመድላይ ያለ የስምነት ዓመት ልጅ፣ ወደ ወጣትነት እየተሸጋገረ ያለ የዐሥራ ስድስት ዓመት ልጅ፣ የሃያ አራት ዓመት ወጣት፣ የአርባ ዓመት ጎልማሳ እና የሰባ ዓመት አዛውንት እኩል የሆነ የመጾም አቅም አይኖራቸውም፡፡ በመሆኑም የጾም ሰዓት ከእድሜ ጋር መገናዘብ አለበት፡፡ አንድን የስምንት ዓመት ልጅ እስከ ዐሥራ አንድ ካልጾምክ ብሎ ማስገደዱ ጾምን በልኩ እንዳይለማመድ ከማድረጉም በተጨማሪ፣ እየተሰላቸ እና እየተማረረ እንዲጾመው በማድረግ መንፈሳዊ በረከቱን እንዳያገኝ ሊያደርገው ይችላል፡፡

3. የጤና ኹኔታ [Status of Health] - ሌላው አጽንኦት የሚሰጠው ጉዳይ ደግሞ የጤና ኹኔታ ነው፡፡ በሕመም ከደከሙ ሰዎች ይልቅ ሲነጻጸር ፍጹም ጤናማ የሆነ ሰው በተሻለ ኹኔታ የመጾም ችሎታ ይኖረዋል፡፡ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ አስቸጋሪ የሆነ ሕመም ያለባቸው ሰዎች ከንስሐ አባቶቻቸው ጋር በመመካከር ለአጭር ሰዓት ብቻ ከጸሎት ጋር መጾም ይችላሉ፡፡ ሆኖም ግን ‘አንድ ጊዜ እንዲህ አሞኝ ነበር፤ አሁንም ብጾም ሊያመኝ ይችላል’ በሚል ፍራቻብቻ ደግሞ ከጾም መሸሽ እንደማይገባ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡

4.የሥራ ክብደት [Heaviness of Work] - አንድ ሰው የሚሠራው የሥራ ዓይነትም ግምት ውስጥ ይገባል፡፡አንዳንድ ሰዎች ከፍተኛ የሆነ አካላዊ አቅም የሚጠይቅ ሥራ ሊሠሩ ይችላሉ፤ ሌሎች ደግሞ ብዙ አካላዊ እንቅስቃሴ የማያስፈልገውእና ቢሮ ውስጥ ቁጭ ተብሎ የሚሠራ ሥራ ሊሠሩ ይችላሉ፡፡በዚህ ዓይነት ያሉ ኹለት ሰዎች እኩል ላይጾሙ ይችላሉ፡፡ የመጾም አቅማቸውም ከሥራቸው አኳያ ሊለያይ ይችላል፡፡

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

20 Nov, 22:29


✥••┈••●◉ ቅዱስ ሚካኤል ◉●••┈••✥
ሚካኤል (በዕብራይስጥ: מִיכָאֵל‎, ሲነበብ፡ ሚካኤል, ሲተረጎም፡ 'ማንነው እንደ እግዚአብሔር?'; በግሪክ: Μιχαήλ, ሲነበብ፡ Mikhaḗl; በላቲን: Michahel-ሲነበብ፡ ሚካኤል; በአረቢኛ: ميخائيل‎, ሲነበብ፡ ሚካኤል) በክርስትና በአይሁድ በእስልምና እንዲሁም በመላዕክት አማላጅነት በሚያምኑ ሃይማኖቶች የመላዕክት ሁሉ አለቃ ሊቀ መላዕክት ተብሎ ይጠራል።

በኅዳር ወር በዐሥራ ኹለተኛው ቀን ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ሲመት በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች፡፡ እንደ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምህሮ ኅዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በኢዮር ባለችው በአራተኛይቷ ከተማ በሚኖሩት ኃይላት እና በዐሥሩ ነገደ መላእክት ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት ቀን ነው፡፡ እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ ገፍፎ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል፡፡ (ይህን ኹለተኛውን ሹመት ያገኘው በሚያዚያ 2 እንደሆነ አክሲማሮስ በሚባለው የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ላይ ሰፍሮ አናገኛለን፡፡)

መላእክት ቊጥራቸው እጅግ ብዙ ቢሆንም በ 99ኙ ነገደ መላእክት የተከፈሉና አለቆችም ያሏቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ሁሉ መላእክት አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ በትህትናው ልዕልናን ያገኘው ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠው ክብር ከማንኛውም መልአክ የበለጠ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡

በተጨማሪም ስለ መላእክት ከመጽሐፍ ቅዱስ ለመረዳት እነዚህን ጥቅሶች ይመለከቱ:-

• ሰውን ይረዳሉ [ዘፍ.16፡7፤ ዘፍ.18፡15፤ ዘጸ.23፡20፤ መሳ6፡11፤ 1ኛነገ.19፡5፤ 2ኛነገ 6፡15፤ ዳን.8፡15-19፤ ዳን.3፡17፤ ት.ዘካ.1፡12፤ ማቴ.18፡10፤ሉቃ. 1፡26፤ ሉቃ.13፡6፤ ዩሐ.20፡11፤ ሐዋ.12፡6፤ ራዕይ 12፡7፤]

• ስግደት ይገባቸዋል [ዘፍ.19፡1-2፤ ዘኁ.22፡31፤ ኢያሱ 5፡12፤ መሳ.13፡2፤ 1ኛ ዜና 21፡1-7፤ ዳን.8፡15]

የቅዱስ ሚካኤል ስሞች
ሚካኤል ማለት "መኑ ከመ አምላክ (እግዚአብሔር) እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው" ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት ነው እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ ንጹሕ ርህሩህ ኃይል ረቂቅ ማነው መልሱ የለም ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ዘርፍ ሆነው የሚጨመሩ መጠሪያዎች አሉት እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነት ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡ ይኸውም መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ፣…ናቸው፡፡
መልአከ ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸ - ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡
መጋቤ ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡
መልአከ ምክር ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታል በሱም አማካኝነት ይሠራል።

ሰላም ለርእስከ
ሚካኤል ሆይ፣ መብረቅን ለተጎናጸፈ መልአካዊ ረቂቅ ርእስህ ሰላም እላለሁ።
ተፈጥሮአቸው ከእሳት የሆነ የሰማያውያን የመላእክት ሠራዊት አለቃቸው የምትሆን ሚካኤል ሆይ፣ በኃጢአት ተሰናክዬ ወድቄ እንዳልፍገመገም አንተን ድጋፌ አድርጌአለሁና ፍጹም የማዳንህን ትድግና በኔ ላይ ትገልጽ ዘንድ በስተቀኜ ቁመህ አለሁልህ በለኝ እንጂ በሩቅ ሆነህ አትመልከተኝ። [መልክአ ሚካኤል አንቀጽ ፫]
መልካም በዓል ይሁንላችኹ።

✥••┈••●◉ ይቆየን ◉●••┈••✥

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

13 Nov, 10:10


አንዳንድ ጊዜ ኃጢአት የሠሩ፣ ነገር ግን ንስሐ ያልገቡ፣ እና ሌሎች ኃጢአት የሠሩ እና ንስሐ የገቡ ሰዎችን እናገኛለን…

ላልሠሩት ኃጢአት ንስሐ የገቡ ሰዎች እና ሌሎች ስህተታቸውን በሌሎች ላይ ያደረጉ...

ምንም ኃጢአትን ላለማድረግ የታገሉ ሰዎች አሉ፤ ሌሎችም ኃጢአትን ለመሥራት የጸኑ አሉ።…

ስለሌሎች ኃጢአት የሚያስብ አለ፥ ስለ ራሱም ኃጢአት የሚጨነቅ...

ለኃጢአተኞች ንስሐ እንዲገቡ የሚጸልይ ሰው አለ፣ ሌሎችም የሚኮንኑአቸው...

እና “በኹለት ሀሳብ መካከል የሚንኮታኮት ሰው አለ” [1ኛ ነገ 18፡21] በትሩን ከመካከላቸው ሊይዙት ይፈልጋሉ፣ እሱ ንስሃ የገባ ወይም ኃጢአተኛ አይደለም፣ ከእግዚአብሔር ጋር ወይም ከዲያብሎስ ጋር…

እናም በንስሃ ህይወት የኖሩ ሰዎች አሉ እናም የመጽናኛ ስርአተ ትምህርት ሆነ በእርሱም የዘላለምን ሕይወት አሸንፈዋል…

ከላይ ከተዘረዘሩት ውስጥ አንዱ እርስዎን የሚመለከት የግል ልምምድ ያድርጉት…

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

12 Nov, 00:25


https://youtu.be/CB5_EfXd1Ks?si=w6B6LOsgORPPFyk1&sfnsn=scwspmo

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

08 Nov, 05:53


የሰናፍጭ ቅንጣት [ማቴ. 13÷31]
ታላቅነትን በታናሽነት ሰውራ የያዘች እንከን የለሽ፤ ዙሪያዋን ቢመለከቷት ነቅ የማይገኝባት አስደናቂ ፍጥረት ናት፡፡ የሰናፍጭ ቅንጣት፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን በምሳሌ ካስተማረባቸው መንገዶች አንዱ ሰናፍጭ ነው፡፡ ስትዘራ ታናሽነቷ ስትበቅል ግን ታላቅነቷ የገዘፈ ምስጢር ያለው በመሆኑ ለዚህ ተመርጣለች በመጽሐፍ እንደተባለ ሰናፍጭ ስትዘራ እጅግ ታናሽናት ስትበቅል ግን ባለብዙ ቅርንጫፍ እስከመሆን ደርሳ ታላቅ ትሆናለች ከታላቅነቷ የተነሳ እጅግ ብዙ አእዋፍ መጥተው መጠጊያ እንደሚያደርጓትም አብሮ ተገልጿል አሁን ታናሽነቷን በታላቅነት መሰወር ችላለችና ብዙዎችን ልታስገርም ትችላለች፡፡

ይህ ምሳሌ ታላቅነትን በታናሽነት ሰውራ ይዛ የኖረችውን የክርስቶስ ቤተ ክርሰቲያን ነው እንጅ ሌላ ምንን ያመለክታል? የሰናፍጭ ቅንጣት ብሎ የጠራት አካሉ የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ምክንያቱም እንደ ሰናፍጭ ሁሉ ሲዘራት ትንሽ ነበረች፡፡ በመቶ ሃያ ቤተሰብ ብቻ የተዘራች ዘር ናት፡፡ የእግዚአብሔርን ምስጢር ልብ አድርጉ ኦሪትን ሲመሰርት እንዲህ ነበርን? በሙሴ ምክንያት በስድስት መቶ ሺህ ሕዝብ መካከል የሠራት አይደለምን? ወንጌልን ግን እንዲህ አይደለም ከመቶ ሃያ በማይበልጡ ሰዎች መካከል ሠራት እንጅ፡፡ ወደ ሕይወት የሚወስደው መንገድ የጥቂቶች ብቻ መሆኑን ሲያሳየን ይህን አደረገ፡፡

ሰናፍጭ ካደገች በኋላ ለብዙዎች መጠጊያ እስኪሆን ድረስ ብዙ ቅርንጫፍ እንድታወጣ ቤተ ክርስቲያንም የዓለም መጠጊያ የሰው ልጆች መጠለያ ናት፡፡ ኦሪት በብዙዎች መካከል የተሰበከች ብትሆንም ቅሉ ቅርንጫፏ ከቤተ እስራኤል ወጥቶ ለሞዓብና ለአሞን ስንኳን መጠጊያ ሊሆን አልቻለም፡፡ ቤተክርስቲያን ግን ቅርንጫፏ ከምድር እስከ ሰማይ ደርሶ ሰማያውያኑንና መሬታውያኑን ባንድ ማስጠለል ይችላል ሙታን ሳይቀር መጠለያቸው ቤተክርስቲያን ናት እንጅ ሌላ ምን አላቸው፡፡ ከዚህም የተነሳ "ሰናይ ለብዕሲ መቅበርቱ ውስተ ርስቱ፤ ለሰው በርስቱ ቦታ መቀበሩ መልካም ነው" እያሉ ሥጋቸውን በቤተክርስቲያን ነፍሳቸውን በገነት እንዲያኖርላቸው ይማጸናሉ፡፡

ቤተ ክርስቲያን እንደ ሰናፍጭ ካልቀመሷት በቀር ጣዕሟ የማይታወቅ ታናሽ የምትመስል የሰናፍጭ ቅንጣት ናት ለቀመሷት ሁሉ ደግሞ ጣዕሟ በአፍ ሳይሆን በልብ የሚመላለስ ከደዌ የሚፈውስ ነውና ቀርባችሁ ጣዕመ ስብከቷን፣ ጣዕመ ዜማዋን፤ ጣዕመ ቅዳሴዋን እንድትቀምሱ አደራ እላችኋለሁ፡፡ ከዚሁሉ ጋራ ርስታችሁ ናትና ከአባቶቻችሁ በጥንቃቄ እንደ ተረከባችሁ ለቀጣዩ ትውልድ እስክታስረክቡ ድረስ የተጋችሁ እንድትሆኑና የጀመራችሁን መንፈሳዊ ተጋድሎ በትጋት እንድትፈጽሙ መንፈስ ቅዱስን ዳኛ አድርጌ አሳስባችኋለሁ፡፡

ኃያሉ አምላክ ልዑለ ባሕርይ እግዚአብሔር በቸርነቱ የሀገራችን ኢትዮጵያን አንድነት የኦርቶዶክስ ተዋህዶቤተ ክርስቲያናችንን ዕድገት ለዘለዓለሙ ይባርክ፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

06 Nov, 08:30


https://youtu.be/VGg-_G-OVkI?si=2On7XrRr24Q34K1d

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

04 Nov, 20:18


https://youtu.be/9nApb7b4h8Y?si=qzybRLJL6yx7ZFXp

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

02 Nov, 18:39


https://youtu.be/sw8-h-aXIwc?si=Rqxz1Em_Xk92zi84

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

26 Oct, 21:16


ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕት
ክርስትናን በሰማዕትነት በማሳደግ የመጀመሪያ ምሳሌ የሆነ ሊቀ መምህር

እስጢፋኖስ (በግሪክ: Στέφανος ሲነበብ ፡ Stéphanos ስቴፋኖስ፤ በዕብራይስጥ ፡ הקדוש סטפנוס ፤ በእንግሊዘኛ ፡ Stephen ሲነበብ ፡ ስቴፈን) በሕገ ወንጌል (በክርስትና) የመጀመሪያው ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳሚው ሰማዕት ይህ ቅዱስ ነው።

የተወለደው በ፩ኛው ክፍለ ዘመን፤ የትውልድ ቦታ ኢየሩሳሌም፤ የእናት ስም ማርያም፤ የአባት ስም ስምዖን፤ የሚከበረው በመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ሥንክሳር፤ በዓለ ንግሥ ሲመቱ ጥቅምት ፲፯ ቀን፣ ዕረፍቱ ጥር ፩ ቀን ፍልሰቱ መስከረም ፲፯ ቀን
በግብፅ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን ቶቢ ፩ ቀን በምዕራባውያን ዲሴምበር ፳፮ ቀን፤ ያረፈበት ቀን ጥር ፩ ቀን በመናፍቃን በድንጋይ ተወግሮ

ቅዱሱ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር። ይህም በወጣትነት ያለፈችው ሕይወቱ ስትሠራ የነበረው ታላቅ መንፈሳዊ ሥራ ይመሠክራል።

የቅዱስ እስጢፋኖስ ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም ይባላሉ። (ሌሎች ናቸው የሚሉም አሉ) ገና ከልጅነቱ ቁም ነገር ወዳድ የነበረው ቅዱስ በሥርዓተ ኦሪት አድጐ እድሜው ሲደርስ ወደ ት/ቤት ገባ። የወቅቱ ታላቅ መምህር ገማልያል ይባል ነበር። ይህ ሰው [በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፭፥፴፫] ላይ ተጠቅሷል። በትውፊት ትምህርት ደግሞ ይህ ደግ (ትልቅ) ሰው በርካታ ቅዱሳንን (እስጢፋኖስን፣ ጳውሎስን፣ ናትናኤልን፣ ኒቆዲሞስን...) አስተምሯል። በጌታችን መዋዕለ ስብከት ጊዜም ከፈጣሪያችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ እየቀረበ ይጨዋወት ነበር ፤ በፍጻሜውም አምኗል ። ቅዱስ እስጢፋኖስም ከዚህ ምሑር ዘንድ ተምሮ ኦሪቱን ነቢያቱን ጠንቅቆ ወጣ። ወቅቱ አስቸጋሪና ለኃጢአት ሕይወት የተመቸ ቢሆንም ቅዱሱ ግን የመሲህን መምጣት በጸሎትና በተስፋ ይጠባበቅ ነበር።

ከቅዱስ ዮሐንስ መጥምቁ ጋር
በወቅቱ ደግሞ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ የንስሐ ጥምቀትን እየሰበከ መምጣቱን የተመለከተ ቅዱስ እስጢፋኖስ ነገሩን መረመረ። ከእግዚአብሔር ሆኖ ቢያገኘው የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆነ። ለስድስት ወራትም በትጋት ቅዱስ ዮሐንስን አገለገለ። ለስድስት ወራት ከቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ ከተማረ በኋላ ለስም አጠራሩ ስግደት ይድረሰውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠመቀ። በወቅቱ የተደረገውን ታላቅ ተአምር ልብ ያለው ቅዱስ እስጢፋኖስ መምህሩን ቅዱስ ዮሐንስን እንዲያስረዳው ጠየቀው። "ከእኔ ይልቅ ከፈጣሪው አንደበት ይስማው።" በሚል ላከው። ቅዱሱም ከጌታ ዘንድ ሔዶ እጅ ነስቶ ተማረ። [ሉቃ. ፯፥፲፰] በዚያውም የጌታ ደቀ መዝሙር ሆኖ ቀረ።

ወንጌል ስለማጥናቱ
ጌታም ከሰባ ኹለቱ አርድእት አንዱ አድርጐት ለአገልግሎት ላከው፤ አጋንንትም ተገዙለት። [ሉቃ. ፲፥፲፯] ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታችን መድኃኔ ዓለም ከዋለበት እየዋለ ካደረበት እያደረ ወንጌልን ተማረ፤ ምስጢር አስተረጐመ። ጌታ በፈቃዱ ስለ እኛ ሙቶ ከተነሳ በኋላ ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን በአንብሮ እድ ባርኳል። በዚህ ጊዜም ቅዱሱ እንደ ወንድሞቹ ሐዋርያት ቅስናን (ጵጵስናን) ተሹሟል። በበዓለ ሃምሳም መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከሰባ ኹለቱ አርድእት የእርሱን ያህል ልሳን የበዛለት፣ ምሥጢርን የተገለጠለት የለም። በፍጹም ድፍረትም ወንጌልን ይሰብክ ገባ።

በመጀመሪያይቱ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከማዕድ ሥርዓት ጋር በተያያዘ ፈተና ሲመጣ በመንፈስ ቅዱስ ምርጫ ሰባቱ ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር። አልፎም የስድስቱ ዲያቆናት አለቃ እና የስምንት ሺው ማኅበር መሪ(አስተዳዳሪ) ሆኑዋል። ስምንት ሺህ ሰውን ከአጋንንት መጠበቅ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ አባቶቻችን መጠየቅ ነው። አንድን ሰው ተቆጣጥሮ ለደኅንነት ማብቃት እንኳን እጅግ ፈተና ነው። መጸሐፍ እንደሚል ግን መንፈስ ቅዱስ የሞላበት ማኅደር እግዚአብሔር ነውና ለርሱ ተቻለው። [ሐዋር፣ሥ፡፮ ቁ፡፭] አንዳንዶቻችን ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ሲባል እንደዘመኑ ይመስለን ይሆናል። እርሱ በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነው። ዲቁና ለእርሱ " በራት ላይ ዳርጎት" እንጂ እንዲሁ ድቁና አይደለም።

ከጌታችን ዕርገት በኋላ
ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በኋላ ለአንድ ዓመት ያህል ስምንት ሺውን ማኅበር እየመራ ወንጌልን እየሰበከ ቢጋደል ኦሪት "እጠፋ እጠፋ" አለች። በዚህ ጊዜ "ክርስትናን ለማጥፋት መፍትሔው  ቅዱስ እስጢፋኖስን መግደል ነው " ብለው አይሁድ በማመናቸው አልቀረም ገደሉት። እርሱ ግን ፊቱ እንደ እግዚአብሔር መልአክ እያበራ ፈጣሪውን በብዙ ነገር መሰለው። በመጨረሻውም ስለ እነሱ ምሕረትን እየለመነ በድንጋይ ወገሩት። ደቀ መዝሙርቱም ታላቅ ለቅሶን እያለቀሱ ቀበሩት።

ከአረፈ በኋላ 
ቅዱስ እስጢፋኖስ ከአረፈ ከሦስት መቶ ዓመት በኋላ በኢየሩሳሌም የሚኖር አንድ ደግ ሰው ነበረ ስሙም ሉኪያኖስ ይባላል። በተደጋጋሚ በራዕዪ ቅዱሱ እየተገለጠለት "ሥጋዬን አውጣ" ይለው ነበርና ሒዶ ለጳጳሱ ነገረው። ጳጳሱም ደስ ብሎት ካህናትና ምዕመናንን ሰብስቦ ወደ አፀደ ገማልያል ማለት ወደ መምህሩ ሄደ። ቦታውንም በቆፈሩ ጊዜ ታላቅ መነዋወጥ ሆነ። መላዕክት ሲያጥኑም በጎ መዓዛ ሸተተ። ዝማሬ መላዕክትም ተሰማ። ሕዝቡና ጳጳሱም በቅዱስ እስጢፋኖስ ፊት ሰግደው በታላቅ ዝማሬና በሐሴት ዐፅሙን ከዚያ አውጥተው በጽርሐ ጽዮን (በተቀደሰችው ቤት) አኖሩት። እለ እስክንድሮስ የተባለ ደግ ሰውም ቤተክርስቲያን አነጸለት ወደዚያ  አገቡት።
ከአምስት ዓመታት በኋላም እስክንድሮስ ሲያርፍ በሳጥን አድርገው በቅዱሱ ጎን አኖሩት። የእስክንድሮስ ባለቤት ግን ወደ ሀገሩዋ ቁስጥንጥኒያ ስትመለስ የባሏ ሥጋ መስሉዋት የእስጢፋኖስን ቅዱስ ሥጋ በመርከብ ጭና ወሰደችው። መንገድላይም ከሳጥኑ ውስጥ ዝማሬ ሰምታ ብታየው ያመጣችው የቅዱሱን ሥጋ ነው። እጅግም ደስ አላት አምላክ ለዚህ አድሉዋታልና። እርሷም ወስዳ ለታላቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆስጥንጢኖስ አስረከበችው። በከተማው ታላቅ ሐሴት ተደረገ። ሥጋውን ሊያኖሩት በበቅሎ ጭነው ሲወስዱትም በቅሎዋ በሰው ልሳን ተናግራ ማረፊያውን አሳወቀች። በዚያም ላይ ትልቅ ቤተክርስቲያን ታንጾለታል።[1]

ማጣቀሻ
* ሲመቱ ጥቅምት ፲፯ ቀን፤ ዕረፍቱ ጥር ፩ ቀን ፍልሰቱ መስከረም ፲፭ ቀን ነው ።
^ ከስንክሳር የተገኘ መረጃ
* መጽሐፍ ቅዱስ (የሐዋርያት ሥራ አንድምታ)
* መዝገበ ቅዱሳን

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

24 Oct, 07:02


በዓለ ልደቱ ለአቡነ አረጋዊ

የጻድቁ የአቡነ አረጋዊ አባት ይስሐቅ እናቱም እድና ይባላሉ፡፡ ሁለቱም እግዚአብሔርን የሚፈሩና የሚያከብሩ ነበሩ፡፡ እግዚአብሔር አምላክም የተባረከውን ልጅ ሰጣቸው፤ይህም የሆነው በጥር ፲፬ ቀን ነው፡፡ እግዚአብሔርን መፍራት፣ ሕገ ኦሪትን ትምህርተ ነቢያትንና ቅዱሳት መፃሕፍትን እያስተማሩ አሳደጉት፡፡ እርሱም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እየጸና እየበረታ አደገ፡፡ ሚስት ያገባ ዘንድ አጩለት፡፡ ጻድቁ አባታችን አቡነ ዘሚካኤል(አረጋዊ) ፈጽሞ እምቢ አለ፡፡ ከብዙ ዘመን በኋላ ከሮም ወደ ግሪክ ሀገር አባ ጳኩሚስ የሚኖርበት ደውናስ ወደምትባል ገዳም የምንኩስናን ልብስ ይለብስ ዘንድ ሄደ፡፡ አባ ጳኩሚስንም አገኘው፡፡ አባ ጳኩሚስም ‹‹ልጄ ሆይ፥  አንተ የንጉሥ ልጅ እንደ መሆንህ መጠን የመንግሥቱ ወራሽ ነህና መንኰሰህ ለመኖር ይቻልሃልን?›› አለው፡፡ ብፁዕ አባታችንም ‹‹አባቴ ሆይ፥ የምድር መንግሥት ኃላፊ ጠፊ ነው፤ ነገር ግን የማታልፈውን የማትጠፋውን ዘለዓለማዊት መንግሥት እወርስ ዘንድ እፈልጋለሁ›› አለው፡፡ በፈተናም ከጸና በኋላ በዐሥራ ዐራት ዓመቱ በአባ ጳኩሚስ እጅ የምንኩስናውን ልብስ ለበሰ፡፡ ከአመነኮሰውም በኋላ ስሙን ዘሚካኤል ብሎ ሰየመው፡፡

ከአባ እንጦንስ ዐራተኛው የቆብ ልጅ ሲሆን እርሱን በቆብ የሚወልደው ደገኛውን የገዳም ሥርዓትን ከሠሩልን አበው አንዱ የሆነው ታላቁ ቅዱስ ጳኲሚስ ነው። ቀድሞም በአባ ጳኲሚስ ዘንድ መንኲሶ ለመኖር ሲመጣ የመጣው ከንጉሥ ቤት ነበርና አባ ጳኲሚስ ከማመንኰሱ በፊት ብዙ ፈትኖታል። በኋላም ገና ልጅ ሳለ በዐሥራ ዐራት ዓመቱ አመነኰሰው። የምንኲስና ስሙንም አባ ዘሚካኤል ብሎ ሰየመው። አረጋዊ የተባለው ገና ወጣ ሁኖ ሳለ ልባዌውና ግብሩ ሁሉ እንደሚያስተውል አረጋዊ ነውና ‹‹አንተስ አባታችን አረጋዊ ነህ›› ብለው ጠሩት።
በገድልም ተጸምዶ የሚኖር ሆነ። በኋላም ከሁለት ደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ከተመለከታት በኋላ ወደ ሮም ተመልሶ ለወንድሞቹ ለስምንቱ ቅዱሳን ነገራቸውና እየመራ አብረው መጥተው በኢትዮጵያ መኖር ጀመሩ። በኋላ እነርሱ በአንድነት መኖራቸው ለወንጌልና ለምንኲስና መስፋት አይሆንም ነበርና ሀገሪቱን ተከፋፈሏት። በዚህም አባታችን አቡነ አረጋዊ ወደ ትግራይ በተለይም ወደ ደብረ ዳሞ መጦና በዚያ በዓታቸው ወሰኑ። በእሊህ ዘጠኝ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ መምጣት እጅግ ብዙ የሐዋርያዊ አገልግሎት እንዲሰፋ ሆኗል።፣

አባ አረጋዊም ወደ ደብረ ዳሞ ለመውጣት በአደዱ ጊዜ የታዘዘ ዘንዶ ከወገባቸው ይዞ አውጥቷቸዋል። በዚያም ሲጋደሉ ከኖሩ በኋላ ያማረች ቤተ ክርስቲያንን ሠሩና መወጣጫውን ‹‹ዳህምሞ-አፍርሰው›› ብለው አስፈረሱት። በዚህም ዳሞ ተብላ እንደተጠራች ይነገራል። እርሳቸውም በገድል ተጸምደው ከኖሩ በኋላ በዚያችው ገዳማቸው ሳሉ ወደ ብሔረ ሕያዋን ተሠውረው ሄደዋል። እኒህ ደግ ጻድቅ ከቅዱስ ያሬድም ጋር የሚነገርላቸው ግሩም ዜና አላቸው።
የጻድቁ በረከት በሁላችንም ይደርብን። እግዚአብሔርም በጸሎታቸው ይማረን፤ ለዘላለሙ አሜን።
ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ጥቅምት፣ ገድለ አቡነ አረጋዊ

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

22 Oct, 19:59


ሚካኤል (በዕብራይስጥ: מִיכָאֵל‎, ሲነበብ፡ ሚካኤል, ሲተረጎም፡ 'ማንነው እንደ እግዚአብሔር?'; በግሪክ: Μιχαήλ, ሲነበብ፡ Mikhaḗl; በላቲን: Michahel-ሲነበብ፡ ሚካኤል; በአረቢኛ: ميخائيل‎, ሲነበብ፡ ሚካኤል) በክርስትና በአይሁድ በእስልምና እንዲሁም በመላዕክት አማላጅነት በሚያምኑ ሃይማኖቶች የመላዕክት ሁሉ አለቃ ሊቀ መላዕክት ተብሎ ይጠራል።

መላእክት ቊጥራቸው እጅግ ብዙ ቢሆንም በ 99ኙ ነገደ መላእክት የተከፈሉና አለቆችም ያሏቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ሁሉ መላእክት አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ በትህትናው ልዕልናን ያገኘው ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠው ክብር ከማንኛውም መልአክ የበለጠ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡

በተጨማሪም ስለ መላእክት ከመጽሐፍ ቅዱስ ለመረዳት እነዚህን ጥቅሶች ይመለከቱ:-

• ሰውን ይረዳሉ [ዘፍ.16፡7፤ ዘፍ.18፡15፤ ዘጸ.23፡20፤ መሳ6፡11፤ 1ኛነገ.19፡5፤ 2ኛነገ 6፡15፤ ዳን.8፡15-19፤ ዳን.3፡17፤ ት.ዘካ.1፡12፤ ማቴ.18፡10፤ሉቃ. 1፡26፤ ሉቃ.13፡6፤ ዩሐ.20፡11፤ ሐዋ.12፡6፤ ራዕይ 12፡7፤]

• ስግደት ይገባቸዋል [ዘፍ.19፡1-2፤ ዘኁ.22፡31፤ ኢያሱ 5፡12፤ መሳ.13፡2፤ 1ኛ ዜና 21፡1-7፤ ዳን.8፡15]

የቅዱስ ሚካኤል ስሞች
ሚካኤል ማለት << መኑ ከመ አምላክ (እግዚአብሔር) እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው>> ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት ነው እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ ንጹሕ ርህሩህ ኃይል ረቂቅ ማነው መልሱ የለም ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ዘርፍ ሆነው የሚጨመሩ መጠሪያዎች አሉት እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነት ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡ ይኸውም መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ፣…ናቸው፡፡ 

• መልአከ ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸ - ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡ 
• መጋቤ ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡
• መልአከ ምክር ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታል በሱም አማካኝነት ይሠራል 

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

18 Oct, 12:54


ዘመነ ጽጌ ካለፈው የቀጠለ

በጊዜ እንደመወሰን ⇛ ፈጣሪያችን ቅድመ ዘመናት ሰው በማይቆጥረው ፍጥረት በማይሰፍረው በራሱ ዘመን የነበረና ሁሉ ሲቋጭና ሲያበቃ የእርሱ  ዓመታት ግን ሳያልቅ ድኅረ ዘመናት የሚኖር ነውና እርሱ ብቻውን ሳይለወጥ ሌላውን የሚለውጥ ሆኖ ይጸናል። " አቤቱ፥ አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ፥ ሰማያትም የእጅህ ሥራ ናቸው። እነርሱ ይጠፋሉ፥ አንተ ግን ትኖራለህ ሁላቸው እንደ ልብስ ያረጃሉ፥ እንደ መጐናጸፊያም ትለውጣቸዋለህ፥ ይለወጡማል ::  አንተ ግን ያው አንተ ነህ፥ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም።" [መዝ101:26] በኢየሩሳሌም የነገሠው ሰባኪው የዳዊትም ልጅ እንዲህ ይላል "ለሁሉ ዘመን አለው፥ ከሰማይ በታችም ለሆነ ነገር ሁሉ ጊዜ አለው። " [መክ. 3:1]

አበባ በዘመነ ጽጌ ወቅትን ጠብቆ የሚተርፍ ጊዜው ሲያልፍ የሚረግፍ  ዘር ለፍሬ መብቃቱን እንደምልክት የሚያስረዳ ለኑሮውም የወራት እድሜ ብቻ የተቸረው ነው ፍጥረት ነው:: " ጽጌ ገዳምኒ በጊዜሁ የኃልፍ ኩሉ በጊዜሁ የሐልፍ ወዘኢየሐልፍ አልቦ ዘይመጽእ ... የምድረበዳ አበባ በጊዜው ያልፋል ሁሉም በጊዜው ያልፋል ላያልፍ የሚመጣ አንዳች የለም " ይለናል ቅዱስ ያሬድ።

እንግዲህ ይህን ወደኛ ሕይወት ስናዞረው  ቅዱስ ዳዊት
" ዘመናችን ሁሉ አልፎአልና፥ እኛም በመዓትህ አልቀናልና ዘመኖቻችንም እንደ ሸረሪት ድር ይሆናሉ። የዘመኖቻችንም ዕድሜ ሰባ ዓመት፥ ቢበረታም ሰማንያ ዓመት ነው ቢበዛ ግን ድካምና መከራ ነው ከእኛ ቶሎ ያልፋልና፥ " አለ  መልሶም " ሰውከንቱን ነገር ይመስላል ዘመኑ እንደ ጥላ ያልፋል። " [መዝ .89:10,143:4] ይለናል:: 

ማጠቃለያ 
በሚያልፍ ዘመኑ የማያልፍ ሥራ የሚሰራ በተወሰነለት መዋዕሉ ፈቃደ ሥጋውን ወስኖ ለነፍሱ ሥምረት ያደረ የሰማይ አእዋፋትን ያጠገበ የምድር አበቦችን ያደመቀ ያስሸበረቀ ፈጣሪ " እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን ?" ሲለን በቅዱስ መጽሐፍ እናነባለን 

"የሜዳ አበቦች እንዴት እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ"  የሚለውን የጌታችንን ቃል ይዘን ጊዜው ዘመነ ጽጌ ከምድር አበቦችየምንማርበት ወቅት ነው አበባ ለአንክሮ ለተዘክሮ ተፈጥሯልና [ማቴ .6:28]:: 

ሰው ራሱ  የእግዚአብሔር አበባ ነው! ጽጌ ባለ ብዙ መዓዛና መልክእ ነው፤ ከአቃፊው ወጥቶ ለዓይን የሚማርከው እምቡጥ አበባ ሲፈነዳም ለአፍንጫ የሚያውደው መልካም መአዛ ለዓይን የሚስበው የቀለም ለዛ በሰው ልጆች ዘንድ ያለው ቦታ ልዩ ነው! የአበባ መዓዛና ቀለም መለያየቱና መብዛቱ እኛ ባለ ልሳነ ብዙኅ ፣ ባለ ኅብረ መልክእ መሆናችንን የሚያሳይ ነው! 

ምን አበባ በህጹጽ መገለጫው በጊዜ የሚወሰንእና ፈጥኖ የሚጠወልግ ሆኖ ለደካማው የሰው ልጅ የሥጋ ጠባይ መገለጫ ሆኖ ትምህርት ቢሰጥ ይህን እያየን በነፍስ ደርቀን ወደማንጠወልግበት ተቀብረን ወደማንቀርበት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት ለመሻገር የሚሰራው ሁሉ ለሚከናወንለት ምሳሌ የተገለጸውን ዕለት ዕለት በደጁ እየተጋ ከህይወት ምንጭ ቅዱስ ቃሉ እየጠጣ አበባነቱ ሲያልፍ የሃይማኖት ቅጠሉ ሳይረግፍ የምግባር ፍሬን እየሰጠ በዘመናት ሳያፍ ዘመናትን የሚያሳልፍ መልካሙን ዕፅ መስሎ መኖር ይገባል "... ከመ ዕፅ እንተ ትክልት ሀበ ሙኃዘ ማይ እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ ወቆጽላኒ ኢይትነገፍ ወኩሎ ዘገብረ ይፌጽም = ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ ቅጠሏም እንደማይረግፍ በፈሳሽ ውኃ ዳር እንደ ተከለች ዛፍ የሚሰራው ሁሉ ይከናወንለታል " [መዝ1:3]፡፡ በቸርነቱ የምናስብ የምንናገረውን የምንሠራውን ሁሉ የሠመረ የተከናወነ ያድርግልን!
ይቆየን...

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

15 Oct, 22:46


ዘመነ ጽጌ ካለፈው የቀጠለ.  …†… ስለ ነገረ ክርስቶስ …†…
ሊቃውንቱ " ቡሩክ እጽ ዘሰናየ ይፈሪ ወኃጢዓተ ይሰሪ " እያሉ መልካም ፍሬን የሚያፈራ ኃጢዓትን የሚደመስስ ቡሩክ እጽ ( የበረከት ተክል/እንጨት ) ክርስቶስ መሆኑን ከሊቁ የማኅሌት ምንጭ ቅዱስ ያሬድ ድጓ ጠቅሰው ይመሰክራሉ።
መልሰውም ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ " ትወጽእ በትር እምስርወ እሴይ ወየአርግ ጽጌ " [ኢሳ.11:1] ያለውን ምስጢራዊ የትንቢት ፍጻሜይዘው እንዲህ ይላሉ " ይእቲ በትር አምሳለ ማርያም ቅድስት ወጽጌ ዘወጽአ እምኔሃ አምሳሉ ለወልድ = ይህችውም በትር የቅድስት እናቱ የድንግል ማርያም ምሳሌ ናት ከእርሷ የተገኘው አበባም የወልድ አምሳል ነው ":: 
በዚህም ላይ የድንግል አበባ ክርስቶስ "የእግዚአብሔር ጸጋ ለማንም እንዳይጎድለው፥ ብዙዎቹም የሚረክሱበት አንድ መራራ ሥር ወደ ላይ በቅሎ እንዳያስጨንቅ " በበጎ መአዛው የመላውን ዓለም ክፉ ጠረን ለውጦ በመልካም ጣዕም ከህዝብና ከአህዛብ መራራነትን አጥፍቶ ህዝቡን ሁሉ ስለማዳኑ ይነገራል [ዕብ 12:15]:: 
በጥልቀትም ናዝራዊ የነበረው ብርቱ ሰው ሶምሶን "ምአፈ በላኢ ተረክበ መብልዕ ወእምአፈ ህሱም ተረክበ ጥዑም" ብሎ ለጠየቀው እንቆቅልሽ ፍቺ በፍፃሜው ከበላተኛ የተገኘ ምግብ ከመራራው የሰው ልጅ ግንድ የተገኘ ጣፋጭ ፍሬ ክርስቶስ ሁሉን አጽንቶ ለአበባና ለፍሬ እንዳበቃ ምስክርነት ይሰጣል [መሳ . 14:14]:: 

ስለ ነገረ ማርያም 
" መዝገቡ ለቃል ጽጌ እንተ ኢትትነገፍ " ይህችን ለቅዱሳን አበው የህሊናቸው እረፍት ..... ለፍሬ ሕይወት ክርስቶስ የማረፊያው ሙዳይ የሆነች አበባ ድንግል ማርያምን " የቃል ማደርያ የሆነች የማትረግፍ አበባ " እያለ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ያወድሳታል ሊቃውንቱም በምስጋናው ይተባበሩታል :: 

ይልቁንም ዘመኑ ዘመነ ጽጌ የሌሊቱ ምስጋና ማኅሌተ ጽጌ የምስጋናውም ደራሲ አባ ጽጌድንግል እየተባለ ድንግል የተወደደ ልጇንይዛ ወደ ግብጽ በረሃ መሰደድዋን በማሰብ መፍቀሬ ጥበብ ሰሎሞን " በእሾህ መካከል እንዳለ የሱፍ አበባ፥ እንዲሁ ወዳጄ በቈነጃጅት መካከል ናት።" ያለውን ምስጢራዊ ፍቺ እሾህ ከሆኑ አይሁድ መካከል ተገኝታ በሃይማኖት አብባ ፍሬ ትሩፋት ሰርታ የተገኘች የቆላ የሱፍ አበባ ድንግል ማርያም መሆኗን እየገለጡ  " ሌቱን" የንጋትዋን ምስራቅ ፣ የማለዳዋን ፀሐይ መውጫ ፣ አጥቢያ ኮከቡን መገኛ ሲያመስግኗት ያድራሉ :: [መኃ 2:2]

ስለ ነገረ መስቀል 
ቀድሞ በዘመነ መስቀል [ከመስከረም 17 እስከ መስከረም 25] ለዘጠኝ ቀናት ሲነገር የቆየው ምስጢር መስቀል አበባ ተብሎ እየተዘመረ ከዚህም ይሻገራል :: ልብ በሉ አዳም ወደ ሞት እንጨት ( እጸ በለስ )እጆቹን ዘርግቶ ሞቱን ቢያቀብለን ከማዕረጋችን ተዋርደን ወደ ምድርም ወረድን ክርስቶስ ግን ወደ ሕይወትእንጨት ( እጸ መስቀል ) እጆቹን ዘርግቶ ሕይወቱን ቢያቀብለን ወደ ቀደመ ክብራችን ተሻገርን :: ምንም እንኳ ጢቢቡ በማኅሌቱ "እነሆ፥ ክረምት አለፈ፥ ዝናቡም አልፎሄደ። አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ፥ የዜማም ጊዜ ደረሰ "( መኃ2:11) እንዳለው ዘመነ ክረምቱም ቢያልፍ ዘመነ መጸው ቢተርፍ ዜና መስቀሉ ግን ዓመቱን ሁሉ ይሰበካል :: ለዚህም የመንፈሳዊው ዜማ አባት ቅዱስ ያሬድ " በከመ ይቤ ሰሎሞን በእንተ ማርያም ንዑ ንትፈጋዕ ወኢይኅልፈነ ጽጌ ደመና መስቀል ዘዮም አብርሃ በስነ ማርያም = ሰሎሞን ስለማርያም እንደተናገረው ኑ ደስ ይበለን የበረከቱ አበባ አይለፈን ይኸውም ዛሬ በማርያም ውበት ( በድንግል ባህሪ በክርስቶስ ሥጋ ) መስቀሉ አብርቷልና " (ድጓ ዘዘመነ ጽጌ ) 

ስለ ነገረ ቤተ ክርስቲያን 
ሥሯ በምድር ላይ ቅርንጫፎቿ በሰማይ ያለውን ኆኅተ ሰማይ ቤተክርስቲያንን ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ አስቀድሞ ስለ አማናዊቷ የክርስቶስ መርዓት ስለቅድስት ቤተክርስቲያን ይኽን ይናገራል  "እነሆ፥ ድንጋዮችሽን ሸላልሜ እገነባለሁ፥ በሰንፔርም እመሠርትሻለሁ። የግንብሽንም ጕልላት በቀይ ዕንቍ፥ በሮችሽንም በሚያብረቀርቅ ዕንቍ፥ ዳርቻሽንም ሁሉ በከበሩ ድንጋዮች እሠራለሁ። ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል። ... በአንቺ ላይ የተሠራ መሣሪያ ሁሉ አይከናወንም በፍርድም በሚነሣብሽ ምላስ ሁሉ ትፈርጂበታለሽ። የእግዚአብሔር ባሪያዎች ርስት ይህ ነው፥ " [ኢሳ 54:11] ሊቁም ከዚህ አያይዞ የቤተ ክርስቲያንን ውበት እንዲህ እያለ ያደንቃል " በከመ አሰርገዎሙ ለሰማይ በከዋክብት ወለምድርኒ በሥነ ጽጌያት ከማሁ አሰርገዋ ለቤተ ክርስቲያን በደመ ሰማዕታት = ሰማያትን በከዋክብት ያስጌጠ ምድርንም በአበባ የሸለመ ቤተክርስቲያንንም በሰማዕታቱ ደም አሸበረቃት" 

መሠረተ ዜማ ቅዱስ ያሬድም ጨምሮ በዚህ መንገድ ለቤተክርስቲያን የመወደድ ጌጧ የሰማዕታት ገድል መሆኑን እንዲህ እያለ አስረድቷል "ሰማዕትኒ ያሰረግዋ ለቤተ ክርስቲያን በገድሎሙ " / ድጓ ዘቴዎቅርጦስ / 

ጽጌን ( አበባን ) በጠንካራ ጎንና መልካም ምሳሌው ከላይ ያየነውን ጥልቅ የነገረ ሃይማኖት ማብራርያ ከዚህ እናቆየውና ወደኛ ከሚሻገረው የክርስቲያናዊ ሕይወት ምክር እንፃር ደግሞ ለሰው ደካማ ባህሪያት አብነት የሚሆኑ የጽጌን ደካማ ባህሪ የሚመለከቱ ጥቂት ነጥቦችን እንደ ማጠቃለያ ለመመልከት እንሞክር :: 

ሁላችን እንደምናውቀው  ከአቃፊው ወጥቶ ለዓይን የሚማርከው እምቡጥ አበባ ሲፈነዳም ለአፍንጫ የሚያውደው መልካም መአዛ ዘላቂ ሳይሆን አላቂ ቋሚም ሳይሆን ጊዜአዊ ነው :: 

ልብ እናድርግ ለአበባ ህጹጽነቱ ፈጥኖ መጠውለጉና በጊዜ መወሰኑ ነው እኛም ሥጋ ለባሾቹ የሰው ልጆች በምድር ላለን ቆይታ ህያው ሆኖ ነዋሪ በምድር ላይ ሞትን ሳያይ ቀሪ ማንም የለምና እንደዚሁ ነን :: 

★ ፈጥኖ እንደ መጠውለግ ⇛  ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ይላል
" ሰውስ ዘመኑ እንደ ሣር ነው እንደ ዱር አበባ እንዲሁ ያብባል ነፋስ በነፈሰበት ጊዜ ያልፋልና፥ ስፍራውንም ደግሞ አያውቀውምና። "( መዝ. 102:15)
ቅዱስ ያሬድም በዘመነ ጽጌ ድጓው እንዲህ ሲል ከነቢዩን ቃል እያጣቀሰ ነገሩን ያጸናዋል " ተዘከር እግዚኦ ከመ መሬት ንህነ ዘለሐኮ በእዴከ ኢታማስን ህዝበከ ከመጽጌ ገዳም ዘይፀመሂ ፍጡነ ከማሁ መዋዕሊነ .... አቤቱ እኛ እኛ እንደ አፈር መሆናችንን አስብ የምድረ በዳ አበባ ፈጥኖ እንደሚጠወልገው የእኛም ዘመን እንደዚያው ነውና በእጅህ ያበጀኸውን ህዝብህን አታጥፋ ":: 
እንግዲህ በአምላኩ ፊት ሰው ምን ያህል ደካማ እንደሆነ እናስተውል ::  
ታዲያ ስለምነው በሚያልፍ እውቀቱ የሚታበይ ?  
  በሚጠፋ ጉልበቱ  የሚመካ? 
በሚረግፍ ውበቱ የሚመጻደቅ? 
በሚያልቅ ሀብቱ ሲተማመን የሚኖር ? 
ቅዱስ ያሬድ ግን እንዲህ እያለ ይዘልፈናል "ብዕሉሰ ለሰብዕ ከመጽጌ ገዳም ወኃይሉሰ ለሰብዕ ከመ ሳዕር ድኩም ... የሰው ንብረቱ እንደምድረ በዳ አበባ ኃይሉም እንደ ደረቅ ሳር ነው " አዎ የምንመካበት ክብራችን ታይቶ ጠፊ ፈጥኖ አላፊ ነው :: ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስም " ሥጋ ለባሽ ሁሉ ሣር ነው፥ ክብሩም ሁሉ እንደ ምድረ በዳ አበባ ነው። " ሲል የተናገረው መልእክት የተነሳንበትን ፍሬ ሃሳብ የሚያጠናክር ነው [ኢሳ . 40:6]:: 
ይቆየን...

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

11 Oct, 15:06


 …†… ዘመነ ጽጌ  …†…
ከላይኛው መንበር ከሰማይ በላይ ካለው ሰማይ በምድር ወዳለችው ዙፋን ዳግሚት አርያም ወርዶ፣ መለኮታዊ እሳትነቱን በደመ ድንግልናዋ አብርዶ፣ ደካማውን የሰውነት ባህሪ ከመለኮትነቱ ጋር አዋሕዶ  … የሕይወት ፍሬ መገኛ አበባ እናቱን ድል ከምንነሳበት ከመስቀሉ ሥር ዋጋ ከሚገኝበት መከራ ጋር   የሰጠን አምላካችን የተመሰገነ ይሁን። 

ክኅሎቱ ከፍጡራን ኅሊና በላይ የሆነ የቅዱሳን አምላክ የመላው ዓለም ፈጣሪ "ይህን " የሚታየውንና " ያን " የማይታየውን ሁሉ መልካም አድርጎ ፈጥሮታል። በዚህም ሁሉ ውስጥ ፍጥረታቱን በሦስት መንገዶች ለሦስት ዓላማ መሆኑን የሥነ ፍጥረት መጻሕፍትና ሊቃውንት ያስረዳሉ። 

ከአፈጣጠር መንገዶቹም
በኃልዮ (በማሰብ) የተፈጠሩ አሉ እንደመላእክት ያሉት ለዚህ ምሳሌ ሆነው ይቀርባሉ።
  ደግሞም በነቢብ (በመናገር ) የተፈጠሩ አሉ እንደ ብርሃን ያሉትን ለአብነት መጥቀስ የሚቻል ሲሆን። 
በሦስተኛው መንገድ በገቢር ( በመሥራት ) የተፈጠረ አለ። በዚህ መንገድ  የሰውን ልጅ ብቻ ፈጥሮታል።

ፍጥረታቱ ከተፈጠሩበት ዓላማ አንጻር ደግሞ 

ለአንክሮና ለተዘክሮ (ለመደነቅና ለማስታወስ ለማሰብ)  የተፈጠረ አለ :- ይህ ለመጠቀሚያ ነው። የዚህ ዓይነት ፍጡር መኖሩ ለፈጣሪ ሃለዎት ማስረጃነት እርባና (ጥቅም) ያለው ነው። ቅዱስ መጽሐፍ ይህን ሲያስረዳን 
☞  " የማይታየው ባሕርይ እርሱም የዘላለም ኃይሉ ደግሞም አምላክነቱ ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ ከተሠሩት ታውቆ ግልጥ ሆኖ ይታያልና" ፣ 
“ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል።”
  " ተፈጥሮ እንኳ አያስተምራችሁምን ?" 

[ሮሜ .1:20,  መዝ 19፥1, 1ኛ. ቆሮ. 11:15] 

ለምግብነት የተፈጠሩም አሉ :- እነዚህ ጉልበትን ያጠነክራሉ የኑሮ መሰረትይሆናሉ " እክል ያጸንዕ ኃይለ ሰብዕ ....እህልም የሰውን ጕልበት ያጠነክራል።"~~" የኑሮህ መጀመርያ የምትበላው እህል... ነው " [መዝ .103:15, ሲራ 29:21] ይላልና :: 

ሦስተኛው ወገን መላእክትንና የሰው ልጆችን የያዘ ሲሆን እነዚህም ጥንቱን ፈጣሪያቸውን አመስግነውት ክብሩን ለሚወርሱበት ዓላማ የተፈጠሩ ናቸው ::

በዚህ የሥነ ፍጥረት ጥልቅ ፍልስፍና ውስጥ ሊቃውንቱ የመጀመርያው ፍጥረትጊዜ ነው ይላሉ። ሊቀ ነቢያት ሙሴ የዘልደት መጀመርያ ባደረገው መነሻ እንዲህ ይለናል 
" በቀዳሚ ገብረ እግዚአብሔር ሰማየ ወምድረ " [ዘፍ 1:1] «በመጀመርያ» ብሎ ጊዜ ቀዳሚ ግኝት የግኝቶችም ልኬት ቀመር መሆኑን ይጠቁመናል :: የአልዓዛር ልጅ ሲራክ የተባለ ኢያሱ በመጽሐፉ እግዚአብሔር ከምድር በአርአያውና በአምሳሉ ለፈጠራቸው ለሰው ልጆች ከሰጠው ገጸ - በረከት ቀዳሚው ጊዜ ነው ይለናል።
"(ለሰው ልጆች) ዘመንን ቀንን በቍጥር ሰጣቸው "[ሲራ 17:2] በዚህ የጊዜ ምህዋር ውስጥ ደግሞ የአዝማናትን ኡደት የወቅቶችን መፈራረቅ የሚቆጣጠር ምድርን በዳርቻው የሚያጸናው እርሱ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ነው። ነቢዩ ዳዊት " አንተ የምድርን ዳርቻሁሉ ሠራህ በጋንም ክረምትንም አንተአደረግህ። "  ይለዋል። [መዝ . 75:17]:: 

በጊዜአቱ ቀመር ውስጥ አንድ ዓመት በአራት ወቅቶች (አዝማናት ) የተከፋፈለ ነው :: እነዚህም፡-
  ዘመነ መጸው
  ዘመነ ሐጋይ
  ዘመነ ጸደይና
  ዘመነ ክረምት ይባላሉ ::  (የዘጠኝ ወር በጋ
የዐሥራ ሦሥት ወር ጸጋ የሚል ብኂል በማኅበረሰባችን ዘንድ መገኘቱ ከወቅቱ ርቦው  (አንድ አራተኛ) ውጪ ሌላው በጋ መሆኑን ያሳያል) አሁን ያለነው ከመስከረም 26 እስከ ታኅሣሥ 25 ድረስ ለ 90 ዕለታት በሚታሰበው ዘመነ መጸው ወርኃ ነፋስ ውስጥ ነው። በሥሩም አምስት ንዑሳን ክፍላት ያካትታል ዘመነ ጽጌ : ዘመነ አስተምሕሮ : ዘመነ ስብከት : ዘመነ ብርሃንና ዘመነ ኖላዊ የሚባሉትን ::
ለዚህም እንዲህ የሚል አብነት ይገኛል " ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ክፍለ ዘመኑ ለመጸው ትዌጥን እምዕሥራ ወሰዱሱ ለመስከረም ወትፌጽም እምዕሥራ ወሐሙሱ ለታህሳስ ወኁልቆ ዕለቱ ተስአ ውእቱ ወእምዝ ኢታህፅፅ ወኢትወስክ :: በውስቴቱ ሐለዉ ሐምስቱ ንዑሳት ክፍላት ዘውእቶሙ ዘመነ ጽጌ : ዘመነ አስተምሕሮ : ዘመነ ስብከት :ዘመነብርሃን ዘመና ኖላዊ " 

በዚሁ ዘመን ሥር የመጀመርያው ንዑስ ክፍል ዘመነ ጽጌ ( የአበባ ጊዜ) ከመስከረም 26 እስከ ህዳር 5 ያለውን 40 ዕለታት አካቶ የያዘው ነው። በጊዜውም ለምዕመናን የነፍስ ቀለብ የሰማይ ፍኖት ስንቅ በዜማ ቢሉ በንባብ በብዙ ህብረ አምሳል ስለ አበባ በቤተክርስቲያናችን ወንጌል ይሰበካል በነገረ ሃይማኖትና በክርስቲያናዊ ሕይወት ዙርያ ሰፊ ትምህርት ይሰጣል።

እስኪ በጣም በጥቂቱ በአበባው ወቅት  በቤተ ክርስቲያናችን ዘመነ ጽጌ ለነገረ ሃይማኖት አስተምሮ  እንዴት ጥቅም ላይ እንደሚውል እንመልከት።
ይቆየን.. .

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

04 Oct, 11:14


በቤተክርስቲያን የጽጌ ማኅሌት እንጂ የጽጌ ጾም የሚባል ነገር የለም¡
━━━━━━━✦༒🌻 ༒✦━━━━━━━ 

የደብረ ሊባኖስ አገልጋይ የሆኑ አንድ አባት ከወንድሞች ጋር ሆነን ቅድመ ቅዳሴ ተምረን፣ ተመክረንና አድምጠን እንወጣበት በነበረበት ጉባኤ ቤት በተለየ መልክ በመጪው "የጽጌ ጾም" ስለሚገኘው በረከት እየነገሩን  አባቶች በልዩ ፍቅር ተጠብቀው እንዴት እንደተጠቀሙባት እየነገሩን እንድንዘጋጅ  ይመክሩን ጀመር ። በቸኮለ ማቅኛ (ድፍረት በነዳው አንደበት) ድንገት ማረም አማረኝና  «በቤተክርስቲያን ወርኃ ጽጌ ፣ ዘመነ ጽጌ ፣ ማኅሌተ ጽጌ  እንጂ የጽጌ ጾም የሚባል ነገርኮ የለም አባታችን!» አልኳቸው። 

አልተናደዱም ግን አዘኑ። በትካዜ እጅጉን ዝግ ባለ ድምጽ "እንዲያ እያላችሁ ነው ምታስተምሩት? " አሉኝ። "ለምን መሰልዎት አባታችን… " ብዬ ለማስረዳት እኔ የጽጌን ጾም ንቄና አጥቅቼ ሳይሆን የፈቃድ ጾም ስለሆነ እያልኩ ላብራራ ስንደረደር በከንቱ መውተርተሬን ገትተው እንዲህ አሉ "ተወው የኔ ልጅ አባቴ ቅዱስ ያሬድ እንዲህ ብሎሃል «ጾም ታጸምም ኵሎ ፍትወታት ዘሥጋ ትሜህሮሙ ለወራዙት ጽሙና» #ጾም_የሚባል_የሌለው_በዓለ_ሃምሳ_ብቻ_ነው። ቀንበር አለዘብን ብላችሁ ሸክም አታክብዱ፤ መብል ሥጋን ያገዝፋል ጾም ግን ሰውነትን ያቀላል …  ዛሬማ ፍቅር በራቀበት፣ ተስፋ በመነመነበት፤ ትውልድ እያለቀ ፣ እምነት እየደረቀ  ያለጊዜዋ ምድርን ልታሳልፉ  ጾም የለም እያላችሁ መስበክ ጀምራችኋላ? " ተግሳጹ ከጅራፍ በላይ የሚያም ነበር!  ያኔ  ኅሊናውን ዋሻ፣ አንደበቱን ጋሻ አድርጎ ራሱን የሚከላከል «ሰው» በተፈለገው ልክና በተገቢው መንገድ መጥፋቱ እያስጨነቃቸው  «ምላሱ የሰላ አእምሮው የላላ» ከልክ በላይ የሚፈነጭ የኔቢጤው በየቦታው "ጾመ ጽጌን" ማውገዙ  እጅጉን ሕመም እንደሆነባቸው አስረድተው በአላዋቂነት ስለሰጠሁት ማቅኛ ይቅርታዬን ተቀብለው አለፉኝ። 

ከቅዱስ ያሬድ የነገሩኝን እያሰላሰልኩ 
ጾመ … ጻመወ …  ጸመወ … (ጾመ፣ መከራ ተቀበለ፣ ዝም አለ) የሚለውን ዘር እየቆጠርኩና እያዛመድኩ   ጿሚ፣ ጸማዊ፣ ጽምው ለመሆን በመጣር ከጽሙና መንደር ደርሶ መቆጠብ ያለውን ዋጋ እየመዘንኩ ተመለስኩ።

ባለ ብዙ መልእክት ሆኖ "«ጾም ታጸምም ኵሎ ፍትወታት ዘሥጋ ትሜህሮሙ ለወራዙት ጽሙና» አለ አባቴ ቅዱስ ያሬድ" ያሉት በውስጤ ተመላለሰ። 

ጾም የሥጋን ፍላጎቶች ሁሉ ጸጥ ታደርጋለች። ለወጣቶችም ዝምታን ታስተምራቸዋለች።  (እውነት ነው እርጋታ፣ ዝምታ፣ ጽሙና…  የጾም ውጤት ነው) 

በቤተክርስቲያናችን የበዙ የጾም ቀናት አሉን፤ በዓመት ውስጥ በአጠቃላይ ወደ ፪፻፷ ገደማ ይደርሳሉ ከእነዚህ ውስጥ ወደ ፩፻፹ የሚጠጉ ቀናት ለሁሉም አማንያን እንደ ግዴታ በአዋጅ አጽዋማት ውስጥ ተካትተዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በካህናቱ እና ሌሎች  ምዕመናን በቀኖና፣ በፈቃድ…  የሚጾሟቸው ናቸው። መናንያኑ ግን ከዓመት እስከ ዓመት የዱር ዕፀው ቅጠላ ቅጠል ከውኃ ጋር ሰንበትና በዓለ ፶ እየቀመሱ ከዓመት እስከ ዓመት ይጾማሉ። 

【 Ethiopian Christians observe an extraordinary number of fast days, generally reckoned to be about 250. Of these approximately 180 are obligatory for all believers, while the rest are observed by the clergy and other particularly devout individuals. In addition to the organized calendric fasts, throughout the history of the Ethiopian Church there were ascetics renowned for their extreme fasting, often subsisting on little more than wild plants and water.】  ⇝ Sergew Hable Selassie “Worship in the Ethiopian Orthodox Church” & "The Church of Ethiopia: a Panorama of History and Spiritual Life" 

ቅዱስ ያሬድ ሌላ ምክርም አለው ፦ 

"በፍኖተ ጽድቅ ፍትሑ ለእጓለ ማውታ ወአነሂ እትመየጥ ኀቤክሙ ለሣህል ከመ ፈለገ ሰላም ዛቲ ጾም በቍዔት  ባቲ ትፈሪ ጽድቅ ትሜህሮሙ ለወራዙት ጽሙና ወታበጽሕ ውስተ አዕምሮ ዚአሁ" 

በእውነት መንገድ ለድሃ-አደግ ፍረዱ (የተቸገረውን እርዱ)  እኔም ወደእናንተ ለይቅርታ እንደ ሰላም ወንዝ እመለሳለሁ፤  ጥቅም የሚገኝባት  ይህች ጾም ጽድቅን የምናፈራባት ለወጣቶች እርጋታን የምታስተምር እርሱን ወደማወቅ የምታደርስ ናት ። 

የተዋህዶ ዓይን የኢትዮጵያ ብርሃን ቅዱስ ያሬድ ሌላም ምዕዳን ይጨምራል 

ጾም ቅድስት ትሜህሮሙ ለወራዙት ጽሙና ዛቲ ጾም ቅድስት ወበይእቲ ጾም ተመጠወ ሙሴ ሕገ እግዚአብሔር ጾም ቅድስት ወበይእቲ ጾም ኤልያስ ዓርገ ውስተ ሰማያት ጾም ቅድስት ወበይእቲ ጾም ዳንኤል ድኅነ እምአፈ አናብስት ጾም ቅድስት ሶስና ድኅነት እምዕደ ረበናት ጾም ቅድስት ዓቀመ ኢያሱ ፀሐየ በገባዖን ጾም ቅድስት ጳውሎስኒ ይቤ ትግሁ እንከ አኃውየ በጾም ወበጸሎት ዛቲ ጾም ቅድስት ወበይእቲ ጾም ጾም ቅድስት ትሚህሮሙ ለወራዙት ጽሙና። 

ቅድስት ጾም ለወጣቶች እርጋታ ዝምታን ታስተምራቸዋለች።  ጾም የተለየችና  የተቀደሰች ናት። በዚህች በተቀደሰችዋ ጾም  ሙሴ የአምላኩን ሕግ ተቀበለባት፤  ጾም የተለየችና  የተቀደሰች ናት። በዚህች ቅድስት ጾም ኤልያስ ወደ ሰማይ ዐረገባት ፤  ጾም የተለየችና  የተቀደሰች ናት። በዚህች ቅድስት ጾም ዳንኤል ከአንበሶች አፍ ዳነባት በዚህች ቅድስት ጾም ሶስና ከመምህራኑ ክስ ተርፋለች በዚህች ቅድስት ጾም ኢያሱ በገባዖን ፀሐይን አቆመ ። ጾም የተለየችና  የተቀደሰች ናት! ጳውሎስ እንዲህ አለ ‘ እንግዲህ ወንደረሞቼ በጾምና በጸሎት ትጉ’ ጾም የተለየችና  የተቀደሰች ናት። በዚህች በተቀደሰችዋ ጾም … ቅድስት ጾም ለወጣቶች እርጋታ ዝምታን ታስተምራቸዋለች። 

ደራሲውም እንዲህ ሲል መክሮናል 

… ማርያም ታቦት ጽላተ ኪዳን ሐዲስ፣ 
ቅብዕኒ ርጢነ ጾም እስከ ሰኮና እግር ወርእስ፣ 
እስመ ጾም ትፌውስ ሕማማ ለነፍስ። 

ለሐዲስ ኪዳን ጽላት ታቦቱ ፡ ማርያም አንቺ ነሽና
የጾም መድኃኒቱን ቀቢኝ ፡ ከራስጠጉር እስከ እግር ሰኮና
የነፍስ ሕመም የሚፈወስ ፡ በጾም «በጸሎት» ነውና። 

እንግዲህ ከአባቴ ይኼን ያዝኩላቸው በቤተክርስቲያናችን ጾም የሌለው ለበዓለ ሃምሳ ብቻ ነው። ይልቅ ሰውን በማንጠቅምበት አልፎም ለማያድንም ምክንያት ጾመ ጽጌን አንንቀፋት።

"ወዝኬ ዘሰ ዘይሜህር ዘእንበለ ይኅሥሡ እምኔሁ ወዘእንበለ ምክንያተ ድልወት ለበቁዔተ ሰማእያን ውእቱኬ አብድ ወአኮ ጠቢብ ➺ ይኸውም አስተምረን ሳይሉት እና ሰሚዎቹን የሚጠቅምበት ምክንያት ሳይኖረው ላስተምራችሁ የሚል ሰው አላዋቂ ነው እንጂ አዋቂ አይባልም፡፡ ሰነፍ እንጂ ጠቢብ አይባልም" (ፊልክስዩስ) 

እንኳን ለጽጌ ጾም አደረሰን አደረሳችሁ። በማኅሌት የታጀበውን ተወዳጁን ዘመነ ጽጌ ወርኃ ጾም ተደርቦበት የበረከት ዋጋና በጎ ምላሽ የሚያሰጠን ያድርግልን። 
ከቴዎድሮስ በለጠ

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

02 Oct, 08:48


በ14ኛው መ/ክ/ዘ የኢትዮጵያ መሪ የነበረውን ታላቁን ንጉሥ አጼ ዳዊትን ያወሳና በንግሥና ቆይታቸው ስላጋጠሙት ጉዳዮች ፣ ስለ ዘመኑ ስነጽሑፍ ፣ ስለ አባይ ወንዝና ከግብጽ ጋር ስለነበረው ግጭት እንዲሁም ሌሎች ጉዳዮች የተሰናዳበት ዝግጅት ነው።
ወንድማችን ዲያቆን ዳዊት ናሁሰናይ ጥሩ ወግ ነው በርታልን።
SUBSCRIBE በማድረግ ይከታተሉ።


https://youtu.be/8bCBSXP1KjA?si=8-lFCJ2jrdS6M4tf

꧁༒꧂ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ꧁༒꧂

01 Oct, 18:43


የክርስቶስ ከኹለት ባህሪ አንድ ባህርይ ከክርስትና ቁልፍ እምነቶች አንዱ ነው 
ሥጋ ካልሆነ በግርግም ተኝቶ የነበረው ማን ነው?  
እርሱ አምላክ ካልሆነ መላእክት ወርደው ያከበሩት ማንን ነው?
እርሱ ሥጋ ካልሆነ ማን ነው በመጠቅለል ተጠቅልሎ የነበረው?  
እርሱ አምላክ ካልሆነ እረኞቹ ያመለኩት ማንን ነው?
ሥጋ ባይሆን ዮሴፍ የገረዘው ማንን ነው? 
እርሱ አምላክ ካልሆነስ ኮከቡ በማን ክብር በሰማያት የሮጠ?
ሥጋ ካልሆነ ማርያም ማንን አጠባች? 
እርሱ አምላክ ካልሆነስ ሰብአ ሰገል ለማን ስጦታ አቀረቡ?
ሥጋ ካልሆነ ስምዖን ማንን በእቅፉ ተሸከመ?  አምላክ ካልሆነ ደግሞ “በሰላም ልሂድ” ያለው ለማን ነው?
ሥጋ ካልሆነ ዮሴፍ ማንን ወስዶ ወደ ግብፅ ሸሸ?  
አምላክ ካልሆነ ደግሞ “ልጄን ከግብፅ ጠራሁት” የሚለው ቃል የተፈጸመው በማን ነው?
እርሱ ሥጋ ካልሆነ ዮሐንስ ያጠመቀው ማንን ነው?  
እርሱ አምላክ ካልሆነ ደግሞ ከሰማይ ያለው አብ “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው” ያለው ለማን ነው?
ሥጋ ካልሆነ በበረሃ የጾመና የተራበ ማን ነው?  
እርሱ አምላክ ካልሆነ መላእክት ወርደው ያገለገሉት ማንን ነው?
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

9,254

subscribers

198

photos

2

videos