Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

@ethiomine2


ይህ ቻናል የሀገራችን የማዕድን ሀብቶች ትኩረት እንዲሰጣቸውና አነዚህን የተፈጥሮ ሀብቶች ወደ ልማት አንዲውለ ለማድረግ መረጃዎች ለህዝቡ ተደረሽ ማድረግ ነው!
ሀሳብ አስተያየት ከፈለጉ በ @tirunehgeo ይጠቀሙ!!!

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

21 Oct, 18:04


ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ የሁለተኛ ዙር 30 ከባድ ተሸከርካሪዎችን ወደ ሳይት የማስገባት ሥራ አከናወነ!!

ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ወደሀገር ውስጥ እያስገባቸው ከሚገኙት 330 ገልባጭና የጭነት ከባድ ተሸከርካሪዎች መካከል 36 ገልባጭ ተሸከርካሪዎች መስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም. የሳይት ቦታ ወደሚገኝበት ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ መግባታቸው ይታወቃል፡፡

ይህን ተከትሎ የሁለተኛ ዙር ወደ ሀገር ውስጥ የማስገባት ሂደት ዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም. 30 ተጨማሪ ገልባጭ ከባድ ተሸከርካሪዎች ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ በመግባት ላይ ይገኛሉ፡፡

እነዚህ ከባድ ተሽከርካሪዎች የሲሚንቶ ምርት ግብዓት የሆነውን ማዕድን ከማምረቻ ጣቢያው - ማከማቻ ቦታ የሚያጓጉዙ እጅግ ግዙፍና ዘመናዊ የሆኑ ገልባጭ ከባድ ተሸከርካሪዎች ሲሆኑ፣ የግብዓት ምርቱ የሚመረተው በፕሮጀክቱ አካባቢ በሚገኘው ጀማ ወንዝ ሸለቆ ውስጥ በመሆኑ የቦታው መልክዓ-ምድር አስቸጋሪ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለሥራው የሚመጥንና ደረጃውን የጠበቀ ገልባጭ ከባድ ተሸከርካሪዎችን ለማሰማራት ከፍተኛ ዋጋ የተከፈለበት ትልቅ ሥራ ነው፡፡

በሳይት ላይ የሚሰማሩትን ከባድ ተሸከርካሪዎች ታሳቢ በማድረግ በለሚ ከተማና አጎራባች ወረዳዎች ከሚገኙ የአካባቢው ነዋሪዎች መስፈርቱን የሚያሟሉ 61 አሽከርካሪዎች በቋሚነት የተቀጠሩ ሲሆን በዚህም ለአካበቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ጋር ተያይዞ ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ ነው፡፡
join👉https://t.me/Ethiomine2

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

21 Oct, 10:22


The world's largest uncut gem-quality emerald has been discovered in Zambia's Copperbelt Province. The emerald weighs a staggering 7,525 carats .
https://www.geologyin.com/2024/02/worlds-largest-uncut-emerald-discovered.html?

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

20 Oct, 06:21


በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚገኙ  የከበሩ እና ከፊል የከበሩ ድንጋዮች :-
👉መረገድ/ኦፓል#opal
👉በሉር/ኤምራልድ#Emerald
👉ሩቢ/Rub/
👉ቶጳዝዮን/ቶፓዝ#Topaz
👉ፔረዶት/perdo
👉ጋርኔት/Garnet/
👉ኳርትዝ/Quartz/
👉ሞሳናይት/moissanite/
👉ሰንፔር/ሳፋየር/Sapphire
👉ኦፕሲዲያን/Obsidian/
👉አሜቴስት/Amethyst/
👉አጌት/Agate/
👉ጃስፐር/Jasper/
👉ፋናካይት/Fanacit/
👉ጎሸናይት/Goshenit/
👉ሲትሪን/citrine/
👉ክራይሶክራስ/Chrysocrase/
👉ቶረማሊን/Tourmaline /
👉አምበር/Amber/
👉አሜትሪን/Ametrin/
👉አማዞናይት/Amazonit/
👉አኳማሪን/Aquamarine/
👉ፍሎራይት/Fluorit/
👉ላፒስ ላዞሊ/Lapis lazuli/
👉ኳንዛይት/kunzite/
👉ሞርጋናይት/morganite/
👉ኦኔክስ/Onyx/
👉የነብር አይን/Tiger eye/
👉ቶርኮይስ/Turquoise  እና ሌሎች ማዕድናት በሀገራችን ይገኛሉ።
ቻናላችን ይቀላቀሉ ለሌሎች forward ያድርጉ!!
https://t.me/Ethiomine2

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

19 Oct, 17:04


የኢትዮጵያ ምርት ገቢያ የከበሩ ማዕድናትን ሊያገበያይ መሆኑ ተገለፀ።
============================
የኢትዮጵያ ምርት ገቢያ የከበሩ ማዕድናትን ሊያገበያይ መሆኑ ተገለፀ።ምርት ገቢያው ሳፋየር ኤምራልድ እና ኦፓል የተባሉ የከበሩ ማዕድናትን እንደሚያገበያይ ገልጿል።

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

19 Oct, 06:28


#አፋር

በአፋር ክልል ንዝረቱ እስከ አዲስ አበባ የደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ እየተከሰተ መሆኑ ይታወቃል።

በቦታው የባለሙያ ቲም አዋቅሮ የላከው ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ ትላንት እና ከትላንት በስቲያ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋው እንደተከሰተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጦ ለአካባቢው ማህበረሰብ ልዩ ትኩረት እንዲደረግ በአጽንኦት አሳስቧል።

ህዝቡ ላይ የከፋ ከደጋ እንዳይደርስ የሚመለከታቸው አካላት ሊያደርጉት የሚገባው ርብርብ ምንድን ነው ? ስንል የጠየቅናቸው ዩኒቨርሲቲው የጂኦሎጂ ትምህርት ክፍል ተመራማሪና መምህር ኖራ ያኒሚኦ ምላሽ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

“ የአደጋው ምክንያት ምንነት አሁን ታውቋል። አደጋው የተፈጠረው የቀለጠ አለት በሚያደርገው እንስቃሴ ነው። 

ስለዚህ የከሰም ግድብ የሚባል ስኳር ፋብሪካ አካበቢ አለ። አደጋው እዛ አካባቢ ላይ የሚከሰት ከሆነ የከፋ ጉዳት ሊያከተል ይችላል። ምክንያቱም የመሬት መንቀጥቀጡ በተከታታይ እየተፈጠረ ነው።

አደጋው ካልቆመና የግድቡ አካል የሚነካ ከሆነ ከግድቡ ቁልቁለት አካባቢ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የከፋ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል። 

ስለዚህ በተለይ የአዋሽ ፈንታሌ የወረዳ ካቢኔዎች፣ የዞን አስተዳዳሪዎች ህብረተሰቡን ከቁልቁለታማው ቦታ የውሃ ፍስት ወደማይደርስበት ወደ ሌላ ቦታ ያውርዱ።

ተራራ ስር አካባቢ የሚኖሩ ሰዎችን ታዝበናልና እነዛ ሰዎች ወደ ሜዳ የሚመጡበት መንገድ ቢፈጠር ሊከሰት የሚችለውን ጉዳት ሊቀንስ ይችላል ”
ሲሉ አስገንዝበዋል።

የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ተጠባባቂ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም አሊ በበኩላቸው፣ ወደ ቦታው ባለሙዎችን እንደላኩ ገልጸው፣ “ በአካባቢው የግድብ ስራዎች አሉ። አደጋው ከጨመረ ቀፈን ቀበና ያለው ግድብ ትልቅ ፋክተር ተደርጎ ተፈርቷል ” ብለዋል።

“ ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ ሊደረግለት ይገባል ግድቡ። አንዴ ጉዳት ከደረሰበት ህዝቡን ጠራርጎ ነው የሚወስደው። ከፍተኛ ቦታ ላይ ነው ያለው። በጣም ብዙ መሬትን ሊያካልል የሚችልም ነው ” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

አደጋው የሚጨምር ነው የሚቀንስ ? ምን እየተሰራ ነው ? አደጋው ሊያስከትለው የሚችለው ጉዳትስ በምን ደረጃ ነው ? ስንል የጠየቅናቸው ተመራማሪና መምህር ኖራ በበኩላቸው ተከታዩ ማብራሪያ ችረዋል።

“ የመሬት መንቀጥቀጡ እየተፈጠረ ያለው በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ነው። ከሦስት ሳምንታት ወዲህ የትላንት ስድስት ሰዓቱን ጨምሮ አደጋው ሦስት ጊዜ ተከስቷል።

መነሻው በክልሉ ሳቡሪ ቀበሌ ነው። ከዛ ተነስቶ ነው እስከ አዲስ አበባ፣ አዳማ፣ አዋሽ አካባቢዎች ላይ ንዝረቱ የሚሰማው።

በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አማካኝነት አንድ ቲም ተዋቅሮ ለሁለት ሳምንታት በቦታው ተገኝተን ምልከታዎችን እያደረግን ነው። ሙያዊ ሥራዎችን እየሰራን ነው። ለህዝቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ እየሰጠንም ነው።

የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የሚከሰትበትን ቦታ መለየት ይቻላል። በዚህ ሰዓት ሊከሰት ይችላል ተብሎ የሚገመት ግን አይደለም። አሁን ባለን ቴክኖሎጂና እውቀት ቦታዎቹን መለየት ብቻ ነው የሚቻለው።

የመሬት መንቀጥቀጥ ዋናው ምክንያቱ ከሥር የቀለጠው አለት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ነው። ስለዚህ ማግማው ወደላይ ሰንጥቆ መውጣት እስከሚያቆም ድረስ አደጋው ቀጣይነት ሊኖረው ይችላል።

እስካሁን ድረስ እየተመዘገበ ያለው ከ4.5 እስከ 4.9 ሬክተር ስኬል አካባቢ ነው፤ ይሄም ያን ያክል ጉዳት የሚያደርስ አይደለም መካከለኛ ስኬል ነው። 7 እና ከዚያ በላይ ከሆነ ነው አደጋው ከፍተኛ ሊሆን የሚችለው ”
ብለዋል።

በመጀመሪያ የመሬት መንቀጥቀጥ በተከሰተበት ቦታ ፍል ውሃ መፍለቁ፤ ነዋሪውም ውሃውን ከመጠቀም እንዲቆጠብ ማሳሰቢያ መሰጠቱ ይታወሳል፤ የተገኘ የምርምር ውጤት አለ እንዴ ? ለሚለው ጥያቄ ምላሻቸው፣ “ አሰስመንት ላይ ነን። ካጠናቀቅን በኋላ ሙሉ መረጃ እናጋራለን ” የሚል ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

18 Oct, 11:55


በመላ የሀገሪቱ የሚገኙ የማዕድን መረጃዎችን ለህዝብ እንዲደርሱ በማድረግና የማዕድን ሀብትን እሴት በመጨመር  እንዲለማ በማድረግ ከማዕድን ዘርፉ ተጠቃሚ መሆን ይቻላል ።ሰለሆነም ይህን የቴሌግራም ቻናል  join and forward ያድርጉ።
https://t.me/Ethiomine2
https://t.me/Ethiomine2
https://t.me/Ethiomine2

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

17 Oct, 11:10


ዛሬ ከቀኑ 6 ሰዓት አካባቢ በአዋሽ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ በአዲስ አበባ ተሰማ

በዛሬው ዕለት ከቀኑ 6 ሰዓት አከባቢ በአዋሽ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ተሰምቷል፡፡

ትናንት ምሽት የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በመዲናዋ አሁንም ዳግም መከሰቱን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶ/ር ኤሊያስ ሌዊ ለኢቢሲ ሳይበር አረጋግጠዋል።

ከቀኑ 6 ሰዓት ከ10 ደቂቃ ከ9 ሰኮንድ በአዋሽ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.6 አካባቢ እነደሆነም ዶ/ር ኤሊያስ ገልጸዋል።

የመሬት መንቀጥቀጡ የተከሰተው ባለፈው በተከሰተበት አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ሲሆን በአካባቢው ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ እንቅስቃሴ አሁንም እንዳልቆመ ዶ/ር ኤሊያስ ተናግረዋል።

አሁን የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት መጠኑ አነስተኛ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ኤሊያስ፤ በአዋሽ ፈንታሌ እና ሳቡሬ ከተማ መካከል ላይ ያለው የቅልጥ ዓለት እንቅስቀሴ እስከቀጠለ ድረስ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቱ የመቀጠል እድል እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

16 Oct, 23:48


ዛሬ ምሽት ከደቂቃዎች በፊት 5:12 ደቂቃ በደብረዘይት፣ በአዲስ አበባ፣ጀሞ፣መካኒሳ፣አያት፣፣ጣፎ፣22፣ሸጎሌ፣መካኒሳ፣ገርጂ፣ቱሉዲምቱ፣አዳማ....ጠንከር ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት መሰማቱን ነዋሪዎቹ ገልፀውልኛል። በአዲስ አበባ ከተሰማው ንዝረት ቀደም ብሎ በአፋር አዋሽ 5:11 ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። አዋሽ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.6 መመዝገቡን ከ Volcano discovery ማረጋገጥ ተችሏል።
06/02/2017

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

15 Oct, 12:02


ጥራት ያለው calcite እንፈልጋለን!!
👇👇👇
https://t.me/Ethiomine2
https://t.me/Ethiomine2
አድራሻ:አዲስ አበባ

📞📞251 910488478

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

15 Oct, 06:53


ጥራት ያለው እና ጥሩ grain size ያለው ሲሊካ እንፈልጋለን!!
👇👇👇
https://t.me/Ethiomine2
https://t.me/Ethiomine2
አድራሻ:አዲስ አበባ

📞📞251 910488478

Tiruneh Bekele Ethiopian Gemstones trade

14 Oct, 22:29


ሀገራችን ኢትዮጵያ ከተፈጥሮ የተቸራት የማዕድን ሀብት ውስጥ ምን  ያህል ያውቃሉ?
===========================

👉ከአንድ ቢሊዮን ቶን በላይ የሚገመት የብረትና ብረት ነክ የማዕድናት ክምችት አላት።
👉ከግማሽ ቢሊዮን ቶን በላይ የድንጋይ ከሰል ክምችት በሀገሪቱ ይገኛል።
👉ከዓለም ግዙፉ ያለማ የፖታሽ ክምችት ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ  ናት።
👉በደናክል ተፋሰስ ውስጥ ከ26 ቢሊዮን ቶን በላይ የፖታሽ ሃብት አላት።
👉የጂኦተርማል አቅሟም እስከ 10ሺ ሜጋ ዋት ይደርሳል ተብሎ ይገመታል።
👇👇👇
https://t.me/Ethiomine2