Hawassa University @hucommunicationsoffice Channel on Telegram

Hawassa University

@hucommunicationsoffice


One of the top ranking first generation Universities in Ethiopia.

Hawassa University Telegram Channel Promotion (English)

Are you a student, alumni, or simply interested in one of the top ranking first generation Universities in Ethiopia? Look no further than the Hawassa University Telegram channel, with the username @hucommunicationsoffice. This channel is your go-to source for all the latest news, updates, and events happening at Hawassa University. Whether you want to stay informed about academic achievements, research breakthroughs, or upcoming seminars and workshops, this channel has got you covered. Connect with fellow students, alumni, and faculty members to stay engaged with the vibrant community that makes Hawassa University so special. Don't miss out on important announcements or opportunities - join the Hawassa University Telegram channel today! Stay connected, stay informed, and be a part of the Hawassa University family.

Hawassa University

19 Feb, 10:40


ዩኒቨርሲቲዉ የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ
//
12/6/2017 ዓም
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በወንዶ ገነት የደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ አካሂዷል።

ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታዉ አየለ በመክፈቻዉ ላይ እንደገለፁት የዘንድሮዉ የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ሲገመገም ዩኒቨርሲቲው በሁሉም ዘርፍ መጠነ ሰፊ የሪፎርም ሥራዎች እያካሄደ ባለበት ወቅት እንደመሆኑ አሁን ላይ ለውይይት የሚቀርቡ ነጥቦች ከቁልፍ ዉጤት አመላካቾች አንፃር ብቻ ሊሆን ይገባዋል::

ራስገዝ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ለመሆን የሚያስፈልገውን ወሳኝ ሽግግር ለማድረግ ከልምድ ልውውጥ ጀምሮ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ችሮታው ኮሌጆችና ኢንስቲትዩቶችም ዕቅድና አፈፃፀማቸዉን ከዚሁ ግብ አንፃር በመናበብ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።

በመድረኩ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር፣ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር፣ የዳዬ ካምፓስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር እና የሰባቱ ኮሌጆች ዲኖች በግማሽ ዓመት ያከናወኗቸዉን ተግባራት ከቁልፍ ዉጤት አመላካቾች አንፃር አቅርበው በዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት ጥያቄና አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል::

በተጨማሪም ሶስቱም ምክትል ፕሬዝዳንቶች በየዘርፉ የተነሱት ጉዳዮች ላይ ግብረመልስ እና መስተካከል ባለባቸው ጉዳዮች ላይ የሥራ መመሪያዎችን ሰጥተዋል::

በውይይቱ ማጠቃለያ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታዉ በአፈፃፀም ሪፖርቱ ላይ የታዩ ክፍተቶች ታርመዉ በቀጣይ የተሻለ አፈፃፀም መመዝገብ እንዳለበት እንዲሁም በቀጣይ አጭር ግዜ ውስጥ የሚኖሩ የለውጥ ሥራዎችና ውጤቶች እውን እንዲሆኑ ለሁሉም ባለድርሻ አካል ጠንካራ የሥራ መመሪያ ሰጥተዉ መድረኩ ተጠናቋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

18 Feb, 09:19


Internal Vacancy Announcement for Associate Dean's Position at Daye Campus
**//***
To All Interested HU Academic Staff,

You may apply for the Associate Dean for RTT vacancy at the Bensa Daye Campus.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

18 Feb, 07:18


Internal Vacancy Announcement for Continuing & Distance Education Director's Position
**//***
To All Interested HU Academic Staff,

You may apply for the Director for Continuing & Distance Education Directorate vacancy at Hawassa university.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

18 Feb, 07:05


Internal Vacancy Announcement for Collaborative Projects Coordination Director's Position
****//*****
To All Interested HU Academic Staff,

You may apply for the Director for Collaborative Projects Coordination Directorate vacancy at Hawassa university.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

18 Feb, 07:01


Internal Vacancy Announcement for Research Programs Director's Position
**//***
To All Interested HU Academic Staff,

You may apply for the Director for Research Affairs Directorate vacancy at Hawassa university.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

18 Feb, 06:41


Internal Vacancy Announcement for Associate Dean's Position at CoEBS
****//*****
To All Interested HU Academic Staff,

You may apply for the Associate Dean for RTT vacancy at the College of Education and Behavioral Science.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

18 Feb, 06:34


Internal Vacancy Announcement for Scientific Director's Position at IOT
****//*****
To All Interested HU Academic Staff,

You may apply for the Scientific Director's position vacancy at the Institute of Technology.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

18 Feb, 06:31


Internal Vacancy Announcement for College Dean's Position
****//*****
To All Interested HU Academic Staff,

You may apply for the vacancy at the College of Law and Governance.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

18 Feb, 06:17


Internal Vacancy Announcement for College Dean's Position
****//*****
To All Interested HU Academic Staff,

You may apply for the vacancy at the College of Agriculture.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

18 Feb, 04:40


Internal Vacancy Announcement for College Dean's Position
**//***
To All Interested HU Academic Staff,

You may apply for the vacancy at the College of Business and Economics.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

17 Feb, 18:13


Dr. Eng. Fisiha Getachew, Vice President for Academic Affairs, also underscored that digital education is no longer an optional but a necessity, and he urged the university staff and academic leadership to embrace digital learning for effective implementation.
The meeting has featured insightful presentations by: Dr. Getahun Mekonnen, a consultant of e-SHE Project at the Ministry of Education, on who has discussed Digitalization for Quality Education in Ethiopian HEIs; Dr. Tesfaye Bayu, Director for Electronic Education at HU, on the progress and challenges of e-education at HU; and Dr. Zufan Bedewi, Dean of CNCS at HU, on Inclusive and Equitable Digital Education.

The workshop involved leaders in the academic wing: college deans, associate deans, department/school heads, and directors for interactive and clear action plans for implementation.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

15 Feb, 18:32


ኮሌጁ ለተመራቂ ተማሪዎች የክህሎት ስልጠና መስጠት ጀመረ::
**//**
የካቲት 8 ቀን 2017 ዓም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የወንዶገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ከዩኒቨርሲቲው የሙያ ማበልጸጊያ ማዕከል ጋር በመተባበር ለ130 ተመራቂ ተማሪዎች "ለተመራቂ ተማሪዎቻችን እናስባለን" በሚል መሪ ቃል ከዛሬ ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቅዳሜዎች የሚቆይ የስራ ፈጠራ ክህሎትና የመቀጠር ዝግጁነት ስልጠና መስጠት ጀምሯል።

የተማረ የሰው ኃይል ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገትና የኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና ከሚጫወቱ አካላት መካከል ግንባር ቀደም ሆነው መሆኑን የገለጹት የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ተሻለ ወ/አማኑኤል በየሙያ ዘርፉ ሳይንሳዊ እውቀት ገብይተው የሚወጡ ተማሪዎች እውቀታቸው እንዳይባክን ለማድረግ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ላይ ተሰማርተው ሀገራቸውን እንዲጠቅሙ ማስቻል ይገባል ብለዋል።

ዶ/ር ተሻለ አክለውም ባለፉት ጥቂት አመታት ውስጥ በሀገራችን ለወጣቶች ስራ አጥነት መጨመር ምክንያቶችን ለማወቅ በተደረጉ ጥናቶች ከተለዩት ችግሮች መካከል አዳዲስ ተመራቂ ተማሪዎች ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት አለሟሟላታቸው አንዱ መሆኑን ጠቁመው ይህንን ክፍተት ለመቀነስ መሰል ስልጠናዎች ማስፈለጋቸውን ተናግረዋል::

የስልጠናው አስተባባሪ መ/ር አባይ አስረስ በበኩላቸው ስልጠናው በተመራቂ ተማሪዎች አዕምሮ ውስጥ ስለ ስራ ፈጠራም ሆነ የቅጥር ስራ ማፈላለግ ተነሳሽነት እና ዝግጁነትን መነቃቃትን የሚፈጥር እና አዲስ አስተሳሰብን የሚያጭር መሆኑን ገልፀዋል::

ስልጠናው ከግንዛቤ ማስጨበጫነቱ ባሻገር በዓመቱ መጨረሻ ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር የማገናኘት እድልን እንደሚያካትት በሀ/ዩ /የሙያ ማበልጸጊያ ማዕከል አስተባባሪ የሆኑት አቶ ከብረት ፍቃዱ ተናግረዋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

15 Feb, 15:57


CMHS Conducts Internal Curriculum Review to launch 6 PhD & 3 MPH programs
***
15, 02, 2025
The College of Medicine & Health Sciences (CMHS) at Hawassa University has conducted an internal curriculum review workshop to launch six PhD & three masters programs.

Mr. Amanuel  Ejeso, Director for Public Health academic & service directorate at the college in his opening speech mentioned that the aim of the workshop is to enhance the ongoing research & publication activities of the college staff through upgrading academic programs that increase visibility in health sector as part of a research university.
Mr. Berhan Meshesha, organizer of the event l, also mentioned that the college is aggressively working towards boosting its role and visibility in health related researches through opening additional PhD and MPH programs.

Dr. Alemu Tamiso, Chief Executive Director (CED) of the college, concluded the workshop where he remarked that the college has plans to launch post-doctoral programs in addition to the PhD.

Hawassa University

15 Feb, 14:38


For Your Information

Hawassa University

15 Feb, 14:10


strengthening the capacity of academic staff in supporting entrepreneurship, incubation, and innovation; and equipping students with essential entrepreneurial skills to develop innovative business ideas thereby enhancing the university’s role in fostering job creation and economic development.
Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

15 Feb, 14:09


VPRC Conducts Capacity Building Training at Daye Campus
*//**
February 15, 2025
Hawassa University's Office of the Vice President for Research & Collaboration (VPRC), in collaboration with the Entrepreneurship Development Institute (EDI), conducted a capacity-building training on Entrepreneurship, Incubation, and Innovation for academic staff and Youth Entrepreneurship for students at Daye Campus on February 14, 2025.

Mr. Yoseph Yohanes, Managing Director of Daye Campus, shared his experience attending the Public Entrepreneurship training organized by HU's Entrepreneurship & Technology Incubation Directorate while opening the training. He described it as an eye-opening experience for leaders and expressed gratitude to the VPRC for organizing this training for the academic staff and students, emphasizing the importance of fostering an entrepreneurial mindset at the moment.

According to Eng.Tigist Assefa, Coordinator of HU’s Entrepreneurship Development Center, the training was aimed at:

Hawassa University

07 Feb, 14:06


የህግና ገቨርናንስ ኮሌጅ ለተመራቂ ተማሪዎች የክህሎት ስልጠና ሰጠ።
**//**
ጥር 30 ቀን 2017 ዓም

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህግና ገቨርናንስ ኮሌጅ ለተመራቂ ተማሪዎቹ የራሳቸውን ስራ ለመፍጠርም ሆነ የሚፈጠሩ የስራ እድሎችን በአግባቡ መጠቀም እንዲችሉ የሚረዷቸውን ክህሎቶች እንዲላበሱና ለስራ ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያስትችላቸውን የሁለት ቀናት ስልጠና በመቀጠር ምጣኔና ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል አማካኝነት ዛሬ መስጠት ጀምሯል።

የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ደብረወርቅ ደበበ ኮሌጁ የመጀመሪያው ኃላፊነቱ ከሆነው የመማር ማስተማር ስራ ባሻገር ተማሪዎች ወደ ስራው አለም ገብተው ውጤታማ መሆን እንዲችሉ የተለያዩ የክህሎት ማሳደግያና የሙያ ማጎልበቻ ስልጠናዎች በተለይም ለተመራቂ ተማሪዎች ሲያዘጋጅና ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው በዚህም የሚጨበጥ ውጤት ማስመዝገቡን ገልፀዋል።

ስልጠናውን የሰጡት መ/ር አብነት ወንድሙ በበኩላቸው ተመራቂዎች በተለይም የራስን አቅም የማወቅ፣ የስራ ዶክመንትና የግል ማህደር ዝግጅት፣ የፈተና ቃለ መጠይቅ ዝግጅት እና ውጤታማ የስራ አፈላለግ ክህሎቶች ላይ ስልጠና እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በሀገራችን የሚገኘው የስራ እድልና የስራ ፈላጊው ቁጥር ተመጣጣኝ ባለመሆኑ የመቀጠር ምጣኔው በእጅጉ ያነሰ ሆኗል ያሉት የሀ/ዩ የመቀጠር ምጣኔና ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል ኃላፊ መ/ር ክብረት ፈቃዱ ለዚህ እንደ አንድ ምክንያት የሚቆጠረውን የተመራቂ ተማሪዎች አጠቃላይ የተግባቦት እና የሙያ ክህሎት ብሎም የሥራ ፈጠራን አቅም ለማሳደግ ብዙ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!
           
በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL

Hawassa University

07 Feb, 12:53


Summer Exit Exam Yekait 1Morining Sesstion 1.pdf

Hawassa University

07 Feb, 11:42


Main campus Summer_EXIT_EXAM Room Placement.pdf

Hawassa University

07 Feb, 11:41


Summer Exit Exam Yekait 1Morining Sesstion 1.pdf

Hawassa University

07 Feb, 10:55


በተ/ቀ/ሳ/ኮ በጥራት ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ።
*
30/5/17

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በመማር ማስተማሩና በምርምር ዘርፍ ጥራትን በማሳደግና በማስጠበቅ የአፈጻጸም ደረጃውንና የአክሬዲቴሽን ሂደቱን ሊያፋጥኑ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናና የውይይት መድረክ አካሂዷል።

የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ዙፋን በደዊ መድረኩን ባስጀመሩበት ንግግራቸው የኮሌጅ እና የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች በትምህርት ጥራት ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ ጨብጠው የትምህርት ሚኒስቴር በውል ስምምነቱ ያስቀመጣቸውን ቁልፍ ውጤት መለኪያዎች ለማሟላት የሚያስችሉ ስትራቴጂካዊ ዝግጅቶች ላይ በመወያየት ወደ ተግባር ለመግባት መድረኩ የጎላ ሚና እንደሚኖረው ገልፀዋል::

ዶ/ር ዙፋን ኮሌጁ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚያስችሉት ላብራቶሪዎች አጠናክሮ እያደራጀ እንደሚገኝ ጠቁመው በተለይም ከላብራቶሪ አክሬዲቴሽን ጋር ተያይዘው እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በቅርብ ጊዜ ውጤት ማስገኘት የሚችሉበትን አሰራር በመዘርጋት ወደ እንቅስቃሴ ተገብቷል ብለዋል።

የኮሌጁ ትምህርት ጥራት ማስጠበቂያና ማሻሻያ ኃላፊ ዶ/ር መቅደስ ማሞ በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚረዱ ግብአቶች ዘርፈ ብዙ መሆናቸውንና ከእነዚህም ውስጥ የትምህርት ክፍለ ጊዜዎችን በውጤታማነት መጠቀም፣ የመማሪያ ግብአቶችን ደረጃ ማሻሻል ብሎም የመምህራንንና የትምህርት አመራሩን ግንዛቤ ማሳደግ ዋነኞቹ መሆናቸውን ገልጸዋል። በኮሌጁ ስር የሚገኙ አብዛኛዎቹ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች አዳዲስ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ቀዳሚ ባለድርሻ ከሆኑት መምህራን ጋር በሚኖራቸው ግንኙነት ሊኖራቸው የሚገባውን እውቀትና ከህሎት የሚጨብጡበትን ስልጠና እየወሰዱ እንደሚገኝ ዶ/ር መቅደስ አክለዋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

07 Feb, 07:46


Her Excellency underscored that Most of the Swiss universities are known for top innovation capacity, so they invite a lot of international students and innovators who are vibrant and commited. "A country like Ethiopia is seen as a very capable country as an equal partner we're looking for, so I'm very happy to strengthen the already established cooperation among academic institutions in boPresident ies," she added. The experience in autonomy, she said, is also different from Ethiopia's experience as most Swiss universities are cantonal, not centrally governed.

Hawassa University has a longstanding collaboration with University of Applied Sciences & Arts of Southern Switzerland (SUPSI) through its Institute of Technology.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

07 Feb, 07:45


Swiss Ambassador to Ethiopia and South Sudan Visits Hawassa University
//
February 7, 2025

Her Excellency Tamara Mona, Ambassador of Switzerland to Ethiopia and South Sudan, has visited Hawassa University and discussed potential areas of further academic collaboration with the President, February 6, 2025.

President of Hawassa University, Dr. Chirotaw Ayele, warmly welcomed the delegation and spoke on the university’s commitment to forging additional international partnerships with Swiss universities. The President highlighted the need for collaborations in research and innovation, education, student and staff exchanges, and income-generating initiatives to support the university’s long-term goals to be an autonomous research university.

Ambassador Mona also expressed Switzerland’s strong interest in working with Hawassa University, as one of the most distinguished Ethiopian universities. She mentioned that, "Ethiopia is the only African country with MoU for academic cooperation with Switzerland."

Hawassa University

07 Feb, 03:34


ከሶስት ወራት በፊት ጥያቄ ማቅረቡን አስታውሰዋል። ጥያቄውን ተከትሎ የችግሩን ምንጭ መርምሮ መፍትሄ ላይ ለመድረስ እና በአጭር ጊዜ ስራውን ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሆነ የገለጹት ዶ/ር ታፈሰ ስራውን ቀልጣፋ ከማድረግ አንጻር ከኢንዱስትሪ ፓርኩ በተጨማሪ ከሲዳማ ክልል ውሀ ስራዎች ድርጅት ጋርም በትብብር ይሰራል ብለዋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

07 Feb, 03:33


ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጋር የሥራ ውል ስምምነት ተፈራረመ
*
30/5/17
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተደጋጋሚ የሚከሰተውን የውሃ ፓምፕ ችግር በምርምር ታግዞ ለመቅረፍ የሚያስችለው የሥራ ውል ከሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጋር ጥር 29/2017 ዓ.ም ተፈራርሟል።
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ በስምምነቱ ወቅት እንደተናገሩት በዩኒቨርሲቲዎች የሚመነጨው እውቀት ያለ ኢንዱስትሪዎች ተሳትፎ እንዲሁም የኢንዱስትሪዎች ውጤታማነት ያለ ምርምር ስራዎች ከግብ ስለማይደርሱ መሰል ትስስሮች የሀገራችንን እድገት በጽኑ መሰረት ላይ ለመገንባት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ አፅንኦት ሰጥተዋል። ፕሬዚደንቱ ኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚገጥመውን የትኛውም የቴክኖሎጂ እውቀት የሚፈልግ ችግር በጋራ ለመፍታት ዩኒቨርሲቲው ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል::

የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዋና ሰራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አሸናፊ በበኩላቸው እስካሁን ባላቸው ተሞክሮ ፓርኩ ከፍተኛ ትብብር ከሚያደርግባቸው ተቋማት መካከል ዋነኛው ችግር ፈቺ አጋር ሀዋሳ  ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ትብብር ቀደም ሲል በተከናወኑ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች፣ የጋራ የምርምር ስራዎችና የልምድ ልውውጦች የታየ ነው ብለዋል። ሥራ አስኪያጁ ፓርኩ ተደጋጋሚ የሆነ የውሃ ፓምፕ ብልሽቶች ሲገጥሙት መቆየቱንና ይህም በስሩ ባሉ ኢንዱስትሪዎች አጠቃላይ አፈጻጸም ላይ አሉታዊ ጫና በማሳደሩ ዘላቂና አስተማማኝ መፍትሔ ለማግኘት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ሚና በእጅጉ ተስፋ የተጣለበት እንደሆነ ተናግረዋል።
የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር ታፈሰ ማቴዎስ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ለከርሰምድር ውሀ ምንጭ ከሚጠቀምባቸው አራት ጉድጓዶች መካከል በሶስቱ ላይ ተደጋጋሚ የሆነ የፓምፕ ብልሽት ችግር የሚገጥመው መሆኑን በመጥቀስ የምርምር ቡድን ተቋቁሞ መፍትሔ እንዲያበጅለት

Hawassa University

23 Jan, 19:05


ኮሌጁ ለዶ/ር ፀጋዬ አነመ ጎዴቦ የምስጋናና የክብር ሽኝት አደረገ::
*//*
ጥር 15 ቀን 2017 ዓም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ በጡረታ ለተገለሉት የቀድሞ ባልደረባው ዶ/ር ፀጋዬ አነመ ጎዴቦ ልዩ የምስጋናና የክብር ሽኝት አድርጎላቸዋል::

ኮሌጁ በዛሬው ዕለት የኮሌጁን የግማሽ ዓመት አፈፃፀም ለመገምገም ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ በተገኘበት መድረክ የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የሆኑትንና በመምህርነት፣ በተመራማሪነትና በተለያዩ ደረጃዎች በኃላፊነት ለረጅም ዓመታት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲንና የማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅን ሲያገለግሉ የቆዩትን ዶ/ር ጸጋዬ አነመ በክብርና በምስጋና ሸኝቷቸዋል።

በክብር የተሸኙት ዶክተር ጸጋዬ የተዘጋጀላቸውን የምስጋና የምስክር ወረቀት እና ስጦታዎች ከዩኒቨርሲቲው የአካደሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ዶክተር ኢንጂነር ፍስሃ ጌታቸው እጅ ተቀብለዋል።

በምስጋና ስነስርዓቱ ላይ ዶ/ር ፀጋዬን በመምህርነታቸውና በሥራ ኃላፊነት ዘመናቸው በቅንነትና በታጋሽነት: ሰዎችንም በመልካምነት መንገድ ስለመምራታቸው በተማሪነት ጭምር አብረዋቸው የቆዩት የኮሌጁ ባልደረቦች ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል::

ዶ/ር ፀጋዬ በተደረገላቸው የክብር ሽኝትና ስጦታ እጅግ መደሰታቸውን ገልፀው ሁሉንም ስለ መልካም ሃሳባቸው ከልብ አመስግነዋል::

በመጨረሻም የዕለቱ መርሃግብር በደም ልገሳ እና በጋራ ምሳ በመብላት ተጠናቋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!
           
በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et
Telegram: https://t.me/HUCommunicationsoffice

Hawassa University

23 Jan, 18:19


የማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ::
*//*
ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብ ኮሌጅ የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወራት አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ መድረክ የኮሌጁ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም የሚመለከታቸው ስራ አስፈጻሚዎች፣ ዳይሬክተሮች፣ ቡድን መሪዎችና አስተባባሪዎች በተገኙበት በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ቀርቦ ተገምግሟል።

የኮሌጁ ዲን ፕሮፌሰር ዘለቀ አርፊጮ በመድረኩ መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት ኮሌጁ በዩኒቨርሲቲው ስትራቴጂክ ዕቅድ የተመራ የራሱ ዓመታዊ ዕቅድ በቁልፍ ውጤት አመላካቾች መዝኖ ማዘጋጀቱን አስታውሰው በተጋመሰው የ2017 በጀት ዓመት ምን አሳክተን ምን እንደቀረን በጋራ መገምገም ለቀጣይ ስራችን ወሳኝ መሰረት ይጥላል ብለዋል::
የኮሌጁ ዕቅድና ዳታ ማኔጅመንት አስተባባሪ ዶ/ር ሲቢሎ ጋሹሬ የኮለጁን አጠቃላይ የአፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ፕ/ር ዘለቀ ደግሞ በቅርቡ ከምክትል ፕሬዝዳንቶች ጋር የገቡትን ለኮለጁ ተለይተው የተቀመጡ ቁልፍ አመላካች ተግባራትን ለመፈጸም የሚያስችል የተልዕኮ ዉል ስምምነት (KPI Performance Contracting Agreement) በተመለከተ ገለፃ አድርገዋል።

በቀረቡት ሪፖርትና ማብራሪያ ዙርያ ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና ገንቢ አስተያየቶች የተሰነዘሩ ሲሆን ኃላፊዎቹም በጥያቄዎቹ ላይ ግብረመልስ ሰጥተውበታል::

ፕሮፌሰር ዘለቀ በውይይቱ ማጠቃለያ በሰጡት የሥራ መመሪያ ሁሉም የኮሌጁ ባልደረባ የየራሱን ኃላፊነት በተጠያቂነት ስሜት እንዲወጣና በሥራ ስነምግባር አርአያ መሆን እንጂ ጥራትንና ተቋማዊ ራዕይን ማስተጓጎል ፈፅሞ ተቀባይነት እንደሌላቸው አሳስበዋል::
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

20 Jan, 16:14


ይሄንን ተረፈ ምርት ወደ እጅግ ጠቃሚ ምርቶች ለመቀየር የዩኒቨርሲቲው ምሁራን እገዛ ማስፈለጉን ገልፀዋል::

በፓርኩ አንዱ ፋብሪካ ብቻውን በቀን ከ1 ቶን በላይ የአቦካዶ ምርት ከአርሶአደሩ ይረከባል ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው እስካሁን ሥራ ላይ ከነበሩት ሌሎች ሁለት ተጨማሪ አምራች ፋብሪካዎች ወደ ሥራ ሊገቡ መሆኑን ተከትሎ ለአካባቢው አርሶ አደር ከፍተኛ የገበያ ዕድል ቢፈጠር መልካም ስለሆነ ስራውን ለማገዝ ይሄ ፕሮጀክት ትልቅ ተስፋ የተጣለበት መሆኑን ተናግረዋል::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ዛሬ የተፈራረምነው ስምምነት ለኛ እንደ ፕሮጀክት ብቻ የሚታይ ሳይሆን መንግስት ለዩንቨርስቲዎች ባስቀመጠው የዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስር የትኩረት አቅጣጫ ላይ የራሳችን ሚና የምናጎለብትበት ትልቅ ዕድል ነው ብለዋል::

ፕሬዝዳንቱ ይሄንን እንደ ጅማሮ በጣም አድንቀው ተመራማሪዎችም ይሄንን ዕድል እንደምርምር ብቻ ሳታዩ ከፍ ባለ የኃላፊነት ስሜት ስራችሁን በተቀመጠው ግዜ ፈፅማችሁ የላቀ አስተዋፅኦ እንድታደርጉ ሲሉ የስራ መመሪያ ሰጥተዋል::

ዶ/ር ችሮታው "እኛ ወደ ኢንዱስትሪው ቀርበን ሌሎች ትላልቅ ስራዎችን በጋራ መስራት እንፈልጋለንም" ብለዋል::

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

20 Jan, 16:13


ዩኒቨርሲቲው ከሲ/ኢ/ፓ/ል/ኮ ጋር የ8 ሚልዮን ብር የትብብር ፕሮጀክቶች የስራ ውል ተፈራረመ::
**//**
ጥር 12 ቀን 2017 ዓም

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር የኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶችን ወደ ጠቃሚ ምርቶች ለመለወጥ ያለሙ ሁለት የትብብር ፕሮጀክቶችን ለማሳካት የስምንት ሚልዮን ብር የሥራ ውል ስምምነት ዛሬ በሴኔት መሰብሰብያ አዳራሽ ተፈራርሟል::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቴዎስ ስለ ፕሮጀክት ሥራዎቹ ሲያብራሩ የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪዎች ከይርጋለም የተቀናጀ አግሮ ኢንዳስትሪ በተለይም ከአቦካዶ ፕሮሰሲንግ የሚወጣውን ተረፈ ምርት በመጠቀም የአፈር አሲዳማነትን የሚቀነስ የተፈጥሮ ማዳበሪያ እና የዶሮና ዓሣ መኖዎች የሚያዘጋጁ ወደ አራት አይነት በምርምር የታገዙ ምርቶች ለመቀየር አንዱን በ5 ሚልዮን ብር ሌላኛውን ደግሞ በ3 ሚልዮን ብር የሚሰሩ ሁለት የጋራ ፕሮጀክቶች ላይ ለመስራት ስምምነት ላይ መደረሱን አብራርተዋል::

ዶ/ር ታፈሰ እንዳሉት የትብብር ስራው ባለፈው ዓመት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጥያቄ መነሻነት ተጀምሮ የተለያዩ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክረሃሳቦች ቀርበው በተደጋጋሚ የተገመገሙ መሆኑን ጠቅሰው የበለጠ አሳማኝና አዋጭ የተባሉት ለዚህ ትብብር መመረጣቸውን ገልፀዋል::

የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኃይሉ የተራ በበኩላቸው ኮርፖሬሽኑ በስሩ ካሉት ፋብሪካዎች የይርጋለም የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከሌሎቹ ሁሉ ቀደም ብሎ ወደስራ የገባ መሆኑን አውስተው ሆኖም ግን በተለይ በአቦካዶ ተረፈምርት ከፍተኛ መጠን ያለው በመሆኑ በሳይንሳዊ ዘዴ ማስወገድ ካልተቻለ አካባቢውን በከፍተኛ ደረጃ ሊበክል ስለሚችል

Hawassa University

19 Jan, 17:20


የግብርና ኮሌጅ የጸባይ ዋንጫ ተሸላሚ መሆናቸውን ዶ/ር ሲሳይ ገልጸዋል።

በማጠቃለያ ፕሮግራሙ ለአሸናፊዎች የዋንጫ ሽልማት ስነስርዓት የተካሄደ ሲሆን ዩኒቨርሲቲውን የሚወክሉ ተጫዋቾች እና ተወዳዳሪዎች ቀጣይ ሳምንት በሚጀምረው የዩኒቨርሲቲዎች ሀገር አቀፍ ውድድር ላይ የሚወዳደሩ መሆኑ ተመላክቷል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

19 Jan, 17:19


በካምፓሶች መካከል ሲካሄድ የቆየው ስፖርታዊ ውድድር ተጠናቀቀ ።
**//**
ጥር 11/2017 ዓ.ም.
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በስሩ በሚገኙ ስድስት ግቢዎች መካከል በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች ዩኒቨርሲቲውን የሚወክሉ ስፖርተኞችን ለመመልመል ታስቦ ሲካሄድ የነበረው ኢንተር-ካምፓስ ስፖርታዊ ውድድር ጥር 10/2017 ዓ/ም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ማጠቃለያውን አግኝቷል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ችሮታው አየለ በማጠቃለያው መርሃግብር ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ሁሉም ተወዳዳሪዎች የውድድር ስሜትን ብሎም የእርስበርስ መግባባትን በመፍጠር ረገድ በውድድሩ ቆይታ ላሳዩት መልካም ስነ-ምግባር ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ስፖርት በእውቀትና በአካል ብቃት የተገነቡ ወጣቶችን ለማፍራት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት የገለጹት ፕሬዚደንቱ ዩኒቨርሲቲውን በሀገር አቀፉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውድድር ላይ የሚወክሉ ተማሪዎች ውድድሩ ላይ ከመሳተፍ ባሻገር ውጤት በማስመዝገብና ዩኒቨርሲቲውን በመልካም በማስተዋወቅ የአምባሳደርነት ድርሻቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

በተ/ቀ/ሳ ኮሌጅ የስፖርት ሳይንስ ት/ክፍል ኃላፊ ዶ/ር ሲሳይ መንግሰቱ የውድድር መድረኩ በሰላምና በስኬት መጠናቀቁ እንዳስደሰታቸው ገልጸው በርካታ ተተኪ ስፖርተኞች የተመለመሉበት ስለመሆኑም ተናግረዋል።

የውድድር ዘርፉ አሸናፊዎች የተለዩ ሲሆን በአትሌቲክስ በወንዶች አዋዳ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ እንዲሁም በሴቶች ዋናው ግቢ፣ በቼዝ ውድድር በወንዶች ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሴቶች ደግሞ አዋዳ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ፣ በባህል ስፖርት በወንዶች ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እንዲሁም በሴቶች የአዋዳ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ፣ በቴኳንዶ እና በእግር ኳስ ውድድሮች ደግሞ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሲያሸንፍ

Hawassa University

18 Jan, 09:53


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች
**//***
እንኳን ለከተራና ጥምቀት በዓላት በሰላም አደረሳችሁ!

በዓሉ የሰላም: የበረከትና የደስታ ይሁንላችሁ!

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

18 Jan, 07:17


የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በስሩ የህክምና ዶክትሬትን ጨምሮ በነርሲንግ: በሚድዋይፈሪ: አንስቴዥያ: ራድዮሎጂ: ኦፕታልሞሎጂና ኦፕቶሜትሪ (የዓይን ሕክምና) እና በህብረተሰብ ጤና ትምህርት ክፍሎች ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ስፔሻሊቲና ሰብ ስፔሻሊቲ ትምህርትና ስልጠና የሚሰጥ ኮሌጅ ሲሆን አጠቃላይ ስፔሻለይዝድ ሪፈራል ሆስፒታልና የካንሰር ሕክምና ማዕከልን በስሩ ያስተዳድራል::

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

18 Jan, 07:16


የህ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ቺፍ ኤግዘክዩቲቭ ዳይሬክተር ከሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር የአፈጻጸም ውል ስምምነት ተፈራረሙ::
**//***
ጥር 10 ቀን 2017 ዓ.ም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ  የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤግዘክዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር አለሙ ጣሚሶ ከኮሌጁ የተለያዩ የስራ ክፊል ኃላፊዎች ጋር የስራ አፈጻጸም ውል ስምምነት ጥር 9/2017 ዓም ተፈራርመዋል።

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት  ዶ/ር ኢ/ር  ፍስሃ ጌታቸው እንደተናገሩት በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትና የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ዩኒቨርሲቲው ሊያስፈፅም የሚገባው ግብ አመላካች ውል መፈረሙን አስታውሰው ይሄንኑ ቁልፍ የውጤት አመላካቾች የያዘ ውል ትግበራ ወደ ፈፃሚ ክፍሎች ማውረድ  ተገቢ መሆኑን አብራርተዋል።

በዚህም መሠረት እያንዳንዱ ፈጻሚ  ዓመታዊ  እቅዶቹን በመከለስ ውጤት አመላካቾችን በማስተያየት እንዲሰራ አመቺ ሁኔታዎችን የሚፈጥር መሆኑን ዶ/ር ፍስሃ አስገንዝበዋል።

የኮሌጁ ቺ/ኤ/ ዳይሬክተር ዶ/ር አለሙ ጣሚሶ በበኩላቸው ኮሌጁ በጤናው መስክ ከፍተኛ ልምድ ባካበቱ ባለሙያዎቹ አማካይነት በሀገር አቀፍ ደረጃ እውቅና ያተረፈበት ዘርፈ ብዙ ስራዎች ሲያከናውን መቆየቱን አውስተው ልምዶቹን በመቀመርና አዳዲድስ ምክረ - ሀሳቦችን  የሚያቀርቡ ባለሙያዎችን በማበረታታት ከመስራት ባሻገር በዓመቱ መጨረሻ የተሻለ የስራ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ሁሉም ባለሙያና የሥራ ኃላፊ በታማኝነትና በትብብር መንፈስ እንዲሰራ አሳስበዋል።

Hawassa University

18 Jan, 05:29


የማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ በስሩ የአንትሮፖሎጂ፣ የኢንግሊዝኛ ቋንቋና ስነ-ጽሁፍ፣ የቻይንኛ ቋንቋና ስነ-ጽሁፍ፣ የጂኦግራፊና አካባቢ ጥናት፣ የጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን፣ የሲዳሙ አፎና ስነ-ጽሁፍ፣ የሶሺዮሎጂ እንዲሁም የቲአትር ጥናት ትምህርት ክፍሎችን የያዘና በርካታ ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ ኮሌጅ መሆኑ ይታወቃል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

18 Jan, 05:28


የማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ዲን ከትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ጋር የአፈፃፀም ውል ስምምነት ተፈራረሙ።
**//**
ጥር 10 ቀን 2017 ዓም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ያለው በቁልፍ የውጤት አመላካቾች ልኬት የተዘጋጀ የአፈጻጸም ውል ስምምነት የፊርማ ስነ-ስርአትን ተከትሎ የማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ዲን ፕሮፌሰር ዘለቀ አርፊጮ በኮሌጁ ስር ከሚገኙ ትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ጋር ጥር 9/2017 ዓ.ም ተፈራርመዋል።

የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር ኢ/ር ፍሰሐ ጌታቸው በስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው የሥራ መመሪያ የሰጡ ሲሆን የአፈጻጸም ውል ስምምነቱ ውጤት የዩኒቨርሲቲውን ብሎም የኃላፊዎችን እጣ ፈንታ የሚወስን እንደመሆኑ ስራውን የራስ አድርጎ መስራት ይገባል ብለዋል። ም/ፕሬዚደንቱ ማንኛውም ስራ በጥሩ የስራ መንፈስና በቡድን በጋራ አላማ ከተሰራ የመሳካት እድሉ ከፍተኛ ስለሚሆን ይህንን ስሜት በእያንዳንዱ ትምህርት ክፍል ውስጥ ማጋባት እንደሚገባ ተናግረዋል።

የኮሌጁ ዲን ፕ/ር ዘለቀ አርፍጮ በበኩላቸው የ2017 በጀት አመት የስራ አፈጻጸም የመጀመሪያው አጋማሽ የተጠናቀቀ ቢሆንም በቀሩት ስድስት ወራት ውስጥ በውል ስምምነቱ ላይ የተጠቀሱ ግቦችን ለማሳካት ርብርብ ሊደረግ እንደሚገባው አሳስበዋል። የተቀመጡት እቅዶች በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረዥም ጊዜ የሚሳኩ ሆነው የተቀመጡ በመሆኑ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡትን የመለየትና ወደስራ የማስገባት ተግባር እንደሚከናወን የገለጹት ፕ/ር ዘለቀ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች የተሰጣቸውን ስራ ለእያንዳንዱ መምህር በመደልደል እንዲያስረክቡ ይጠበቃል ብለዋል::

Hawassa University

11 Jan, 19:06


የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ መደበኛ ስብሰባ አካሄደ።
*//*
ጥር 3 ቀን 2017 ዓም
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሰብሳቢነት የሚመራው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ 66ኛውን መደበኛ ስብሰባ ከጥር 2-3/2017 አካሂዷል::

በቅርቡ የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው የተመደቡት ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ ስብሰባውን ሲያስጀምሩ እንደተናገሩት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ እርሳቸውን ጨምሮ ሌሎች በሀገርና በአለምአቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ የፈጠሩ ምሁራንን ማፍራት የቻለ ትልቅ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ጠቁመው ይህንን አንጋፋ ተቋም የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ለመምራት በመመረጣቸው ክብርና ደስታ እንደተሰማቸው እና ከቦርድ አባላቱ ጋር በመሆን ውጤታማ ስራዎችን ለመስራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

ቦርዱ የተጠናቀቀውን የ2016 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲውን ዕቅድ አፈጻጸም እና በትግበራ ላይ የሚገኘውን የ2017 ዓ.ም ዕቅድ ገምግሞ ማጽደቅ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን ገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዝ የመመስረቻ ሰነድ እንደሚገመግምና እንደሚያፀድቅ ከተያዙት አጀንዳዎች ዋናዎቹ መሆናቸው ታውቋል።

በተጨማሪም የሥራ አመራር ቦርዱ የገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዝ የ2016 አፈፃፀም እና የ2017 ዕቅድ ገምግሞ ማፅደቅ: የገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዝ የቁጥጥር ኮሚቴ መሰየም: የ2017 ዓም የዩኒቨርሲቲ ውስጥ ገቢና ወጪ ዕቅድ ገምግሞ ማፅደቅ: እና ሌሎች የቦርድ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ መምከር የስብሰባው አጀንዳዎች መሆናቸውን ማወቅ ተችሏል::

በስብሰባው ማጠቃለያ ዕለትም የቦርድ አባላት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማስተማሪያ ኮ/ስ/ሪፈራል ሆስፒታል እና በገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዝ የተለያዩ ማዕከላት ተገኝተው አካላዊ ጉብኝት አድርገዋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

11 Jan, 14:43


Call for Applications for 22nd ICES @ HU
*//*
January 11, 2025

We are excited to announce that Hawassa University is hosting the 22nd International Conference of Ethiopian Studies in September 2025.

Hence, we would like to suggest to all potential participants in the 22ICES from Hawassa University and other Ethiopian Universities or Research Institutes to apply timely.

When and how?

Please, open this link to the conference website for all the information you need to know. 👇👇👇

https://ices22.hu.edu.et/

Hawassa University
Ever to Excel!

Follow us @
**
Website: https://www.hu.edu.et
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Telegram: https://t.me/HUCommunicationsoffice

Hawassa University

10 Jan, 12:30


ከተጠናከሩ የዩኒቨርሲቲዎችን ራስገዝነት እንደሚያግዙ አብራርተዋል::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አሰፋ በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ አምስት ቅርንጫፎች እንዳሉት ጠቁመው ቅርንጫፎቹ በተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች አስተባባሪነት በመታገዝ ኢንዱስትሪውን የማላቅ ኃላፊነት እንደተሰጣቸው ገልጸዋል።

ዶ/ር ቴዎድሮስ የደቡብ ቅርንጫፍ የዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትብብር የውይይት መድረክ ያስፈለገው ሁሉም የትስስሩ አባል ዩኒቨርሲቲዎች እኩልና ተመሳሳይ ተሞክሮ ስለማይኖራቸው የሥራውን ሂደት በተመለከተ የጋራ ግንዛቤ እንዲጨብጡ የማድረግና በየወሩ ቀጥለው በሚካሄዱ ስብሰባዎች ላይ አጀንዳ ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ በጸደቀው የከፍተኛ ትምህርት፣ ቴክኒክና ሙያ፣ የምርምር ተቋማት እና ኢንዱስትሪዎች ትስስር አዋጅ 1298/15 መሰረት የደቡባዊ ቅርንጫፍን የሚያስተባብረው ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን የዲላ: አርባምንጭ: ቦረና: ወላይታ ሶዶ: ዋቸሞ: ቡሌ ሆራ: ጂንካ: ወራቤና መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲዎችን ያጠቃለለ ትስስር መሆኑ ታውቋል::

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

10 Jan, 12:30


በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የደቡብ ቅርጫፍ የዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስር የምክክር መድረክ ተካሄደ
*
1/5/2017
በሀገር አቀፍ ደረጃ በትምህርት ሚኒስቴር የተዋቀረው የዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስር የደቡብ ቅርጫፍ ሰብሳቢ በሆነው ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የትስስሩ አባል ዩኒቨርሲቲዎች ተወካዮችን ያሰባሰበ የሥራ ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ ጥር 1/2017 ተካሂዷል::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዚደንት እና የትስስሩ ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ታፈሰ ማቴዎስ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት የትስስሩ ዋና ዓላማ በትብብር ሰርቶ ሁለንተናዊ ሀገራዊ ለውጥ ማስመዝገብ እንዲቻል መሆኑን ጠቁመው በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በውጤታማነት ለማስቀጠል ዩኒቨርሲቲዎችን ከቴክኒክና ሙያ ተቋማት፣ ከምርምር ተቋማት እንዲሁም ከኢንዱስትሪዎች ጋር የሚያስተሳስር አዋጅ ጸድቆ ወደ ትግበራ መገባቱ መልካም ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።

ዶ/ር ታፈሰ እንዳሉት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በስሩ ዘጠኝ ዩኒቨርሲቲዎችን አቅፎ የደቡብ ቅርንጫፍን የማስተባበር ሚና እንደመጫወቱ በተፈጠረው ትብብር የጋራ ችግሮች ላይ ያተኮሩ ምርምሮች፣ የስልጠናና የማማከር አገልግሎት፣ የተማሪዎች ኢንተርንሺፕ እና የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች ኤክስተርንሺፕ ብሎም የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎችን ማዕከል አድርጎ ይሰራል ብለዋል።

ም/ፕሬዝዳንቱ ለአባል ዩኒቨርሲቲዎች ተወካዮች ባቀረቡት ፅሁፍ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ እስካሁን በአቅራቢያው ካሉት የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ: የይርጋለም የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ: የተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት: ሌሎች የሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም ዓለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር ያለውን ሰፊ የትብብር: የምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ተሞክሮዎች አቅርበው እነዚህ ተሞክሮዎች

Hawassa University

09 Jan, 16:25


ምክትል ፕሬዝዳንቶችና የኮሌጅ አመራሮች የአፈፃፀም ውል ኮንትራት ተፈራረሙ::
*//*
ጥር 1 ቀን 2017 ዓም
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶችና የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ከኮሌጅ ዲኖች: የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር: የህ/ጤ/ሣ/ኮ ቺፍ ኤግዘኪዩቲቭ ዳይሬክተር እና ከዳዬ ካምፓስ ኤግዘኪዩቲቭ ዳይሬክተር ጋር ቁልፍ የአፈፃፀም አመላካቾችን የያዘውን የአፈፃፀም ውል ኮንትራት ዛሬ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት በተገኙበት ተፈራርመዋል::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ስለ ውሉ አስፈላጊነት ባስረዱበት ንግግራቸው ሁሉም የሥራ ክፍሎች የየድርሻቸውን ኃላፊነት ቆጥረው ተረክበው ውጤቱንም እንዲያመጡ የወረደና ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑን ገልፀዋል::

በዚህም መሰረት ዛሬ ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ውል የገቡት የየኮሌጁ አመራሮች በሚቀጥለው ሳምንት ደግሞ በተዋረድ ከየትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ጋር ውል ገብተው አፈፃፀሙን የመምራት ግዴታ እንደተጣለባቸው እንዲረዱ መመሪያ የሰጡት ፕሬዝዳንቱ ከፍተኛ አመራሩም ሁሉንም የሥራ ሂደቶች የመከታተልና አስፈላጊውን ሁሉ አስተዳደራዊ ድጋፍ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ተናግረዋል::

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!
           
በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et
Telegram: https://t.me/HUCommunicationsoffice

Hawassa University

08 Jan, 08:55


ጉብኝቱ በተካሄደባቸው በዋናው ግቢ የመርከብ፣ ሲኒየርና ጁኒየር ካፍቴሪያዎች የተገኙ ተማሪዎች ከፍተኛ አመራሩ ለተማሪዎች የተዘጋጁትን ምግቦች ተገኝተው በመመልከታቸውና አብረው በመካፈላቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው የዘንድሮው በዓል ለየት ያለ ድባብ ያለበት መሆኑን ገልጸዋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

08 Jan, 08:55


የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች የበዓል ምሣ ከተማሪዎች ጋር ተጋሩ::
*//****
ታህሳስ 30/2017 ዓም
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንትን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች፣ የተማሪዎች አገልግሎት ኃላፊዎች እና የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝደንት ተማሪ እሰይ ጴጥሮስ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በዓሉን ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ለሚያከብሩ ተማሪዎች በልዩ ሁኔታ የተሰናዳውን ምግብ በየምግብ አዳራሾቹ ተዘዋውረው ከተማሪዎች ተጋርተዋል።

ፕሬዚደንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ስለ ጉብኝቱ ሲያብራሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለረጅም አመታት ሲተገበር የነበረው የተማሪዎች የምግብ ሜኑ በበጀት ጫና ምክንያት አቅርቦት ላይ የነበረውን ችግር ለመቅረፍና ለማሻሻል ሌት ተቀን እየሰራን ነው ብለዋል:: የዛሬውን ዓመት በዓል ምክንያት  በማድረግ ዩኒቨርሲቲው በልዩ ሁኔታ ግብዓት ጨምሮ ተማሪዎቻችን የተሻለ እንዲመገቡ አድርገናል ያሉት ዶ/ር ችሮታው ተማሪዎች አብዛኛውን በዓላት ከወላጅ ቤተሰቦቻቸው ርቀው ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ጋር የሚያሳልፉ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ቤተሰባዊ ስሜትን ለመፍጠር ዕለቱን አስመልክቶ ለየት ያለ የምግብ አይነት በማዘጋጀት ማቅረቡን እና እነሱም ከልጆቹ ጋር ምሣ መጋራታቸው ጥሩ የቤተሰብነት ስሜት እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

የአስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ በበኩላቸው የጉብኝቱ ዋነኛ አላማ በዓሉን ከተማሪዎች ጋር በጋራ የማሳለፍና ቅርርብ የመፍጠር መሆኑን አንስተው ዩኒቨርሲቲው ሁሉም ሀገራዊ በዓላት በሚከበሩበት ወቅት ተመሳሳይ ዝግጅቶችን በማካሄድ በዓሉን የሚያከብሩ ተማሪዎች ባይተዋር እንዳይሆኑ ማድረግ ችሏል ብለዋል።

Hawassa University

07 Jan, 02:58


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች:-
*//**

እንኳን ለ2017 ዓ.ም. የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት መታሰቢያ (የገና በዓል) በሰላም አደረሳችሁ!

በዓሉ የሰላም: የፍቅር: የአንድነት ይሁንላችሁ!

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

06 Jan, 10:29


Call for Application: PhD Supervision Training
*//*
January 6, 2025
Dear PhD Supervisors of Hawassa University,

We are pleased to announce an upcoming training program designed specifically for Female PhD Supervisors.
This training is a crucial step towards enhancing your supervisory skills, ensuring the success of your PhD students, and maintaining the high standards of our academic programs.

As a supervisor, your role is pivotal in guiding our students to achieve their full potential, and this training will provide you with valuable tools and insights to facilitate that process.

We strongly encourage all current and prospective Female PhD Supervisors to apply for this training. Your participation is essential in fostering an environment of excellence and support within our academic community.

Please, find the application form attached here.

Kindly complete and return it within 5 days to secure your place in the training program.

School of Graduate Studies
Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

06 Jan, 10:18


የመውጫ ምዘና ከየካቲት 10 - 12 /2017 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ ተገለጸ።
*//**
ታህሳስ 28/2017 ዓም
በክረምት በመምህርነት ሙያ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ድግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ሲከታተሉ ቆይተው የመውጫ ምዘና (Exit Exam) ለመውሰድ ለሚጠባበቁ መምህራን የመውጫ ምዘናው የሚሰጥበትን ቀን ትምህርት ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል።

በዚህም የመውጫ ምዘናው ከየካቲት 10 እስከ የካቲት 12/2017 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን መምህራኑ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉና በየአቅራቢያቸው ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ለመፈተን እንዲችሉ በቀጣይ በክልል ወይም የከተማ አስተዳደር ት/ቢሮዎች በኩል እንደሚያሳውቃችሁ ትምህርት ሚኒስቴር ገልፅዋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

03 Jan, 18:01


የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ አሳየኸኝ ግርማ እንደገለፁት በተደረሰው የውል ስምምነት መሰረት የሰው ሀብት መረጃ አያያዝ ሲስተም/ Human Resource Management System ፣ የንብረት አስተዳደር ሲስተም/ Property Management System፣ የፕሮጀክትና ኮንትራት አስተዳደር ሲስተም/ Project and Contract Administration Management System፣ የፋይናንስ አስተዳደር ሲስተም/ Finance Management System፣ የሰነድ አያያዝ ሲስተም/ Document Management System እና የደንበኛ መረጃ አስተዳደር ሲስተም/ Customer information management system በአንድ ላይ የተቀናጀ ሶፍትዌር ሲስተም/ Enterprise Resource Planning Software/ የማልማትና እና ሲስተሞቹን ለመጠቀም ከሚያስችል የዕውቀት ሽግግር የማከናወን ስራን በመስጠት ሁሉንም የስራ ዘርፎች ውጤታማ የማድረግ ስራ ይሰራል ብለዋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et
Telegram: https://t.me/HUCommunicationsoffice

Hawassa University

03 Jan, 18:00


ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ ያለማውን የERP ሶፍትዌር ሲስተም ለመሸጥ ተፈራረመ::
*//**
ታህሳስ 25/2017 ዓም

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ከሲዳማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ ጋር በዩኒቨርሲቲው የአይ ሲ ቲ ባለሙያዎች የበለፀገውን ERP ሶፍትዌር ሲስተም ልማትና ትግበራ እንዲሁም የእውቀት ሽግግር ለማድረግ የሚረዳውን ስምምነት ታህሳስ 24/2017 ዓም ተፈራርሟል::

የሀ/ዩ ምርምርና ትብብር /ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር ታፈሰ ማቴዎስ ዩኒቨርሲቲው ከኢትዮጵያ አልፎ ዓለም አቀፍ ተቋማት ውስጥ እየሰሩ ያሉ የሶፍትዌር ባለሙያዎች እንዳሉት ገልጸው የሲዳማ ክልል ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ ሲስተም አውቶሜት ለማድረግ በጠየቀው መሰረት የሚሰራው ስራ ደረጃውን ጠብቆ እንዲካሄድ ክትትልና ድጋፍ ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው ተናግረዋል።

ዶ/ር ታፈሰ ዩኒቨርሲቲው በሶፍትዌር ልማት ስራው የሀገራችንን ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ዕቅድ እውን ለማድረግ ሰፋፊ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን አውስተው ኢንተርፕራይዙ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር ለመስራት በመምጣቱ አመስግነዋል::

የሲዳማ ክልል ዲዛይንና ቁጥጥር ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢ/ር ይርጉ ታደሰ በስምምነቱ ወቅት እንዳሉት ኢንተርፕራይዙ ሁሉንም ሥራዎች ዲጅታይዝ ለማድረግና ለደንበኞቹ የተቀላጠፈና በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት ሰጥቶ ትርፋማ ለመሆን ሶፍትዌሩ እንደሚያስፈልገው ተናግረዋል:: ኢንተርፕራይዙ እንደ ተቋም የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት፣ የደንበኞችን ፍላጎት ለሟሟላትም ሆነ ትርፍ ለማመንጨት ዲጂታላይዜሽን ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ሆኖ መገኘቱንም አክለዋል።

Hawassa University

03 Jan, 13:11


ዶ/ር ዳዊት ሐዋሪያ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ ባካሄደው ጥናት በሲዳማና አጎራባች ክልሎች ያለው የወባ በሽታ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ጠቅሰው በአንጻሩ የአጠቃላይ ማህበረሰቡ ግንዛቤ እምብዛም ለውጥ እንዳላሳየ ተናግረዋል። የውይይት መድረኩ ዋነኛ አላማ ለወባ በሽታ ስርጭት አጋላጭ የሆኑ ምክንያቶችን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመለየት ውጤቶቹን ቀምሮ መፍትሔ ለማስቀመጥ መሆኑን በመጠቆም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ እንደ ምርምር ዩኒቨርሲቲነቱ የሚጠበቅበትን ድርሻ ለመወጣት አዲስ የምርምር ማዕከል በማቋቋም እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ችሮታው አየለ በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚገኝበት አካባቢ የወባ አምጪ ትንኞች ለመራባት አመቺ በሆነው የስምጥ ሸለቆ አካባቢ እንደመሆኑ እንደ አዲስ ያገረሸውን ወረርሽኝ ለመቆጣጠርና አዳዲስ የመከላከያ መንገዶችን ለማስተዋወቅ የሚረዳውን የወባ ምርምር ማዕከል አቋቁሞ ሥራ መጀመሩ አንድ ነገር ሆኖ ማዕከሉን ወደ ልህቀት ማዕከል ለማሳደግ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል::

የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ እንዲሁ የማዕከሉ መጠናከር ላይ ሁሉንም ባለድርሻ አስተባብሮ ሳይንሳዊ የሆነ መፍትሄ ማመንጫ ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ ቃል ገብተዋል::

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

03 Jan, 13:10


የወባ በሽታ ስርጭት አሁናዊ ሁኔታን የሚዳስስ ሴሚናር ተካሄደ።
**
25/4/2017

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት እንደ አዲስ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየጨመረ በመጣው የወባ በሽታ ስርጭት እና ዩኒቨርሲቲው በዚህ ዙርያ እያከናወነ ስላላቸው ሥራዎች እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ቀጣይ ሚና ላይ ለመመካከር ያለመ ሴሚናር አዘጋጅቷል::

ታህሳስ 24/2017 ዓም በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በተካሄደው ሴሚናር ላይ ከአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የተጋበዙት የዘርፉ ከፍተኛ ተመራማሪ ሳይንቲስት ዶ/ር ሰለሞን ክብረት እና ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህ/ጤ/ሣ/ኮ ተመራማሪው ዶ/ር ዳዊት ሐዋርያ ለውይይት መነሻ የሚሆን ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን በመድረኩ ላይ ከተለያዩ ክልሎች የተወከሉ የዘርፉ ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ተመራማሪዎችና ሚድያዎች ተሳትፈዋል።

ዶ/ር ሰለሞን ክብረት የወባ በሽታ በዓለም ላይ በገዳይነታቸው ከሚጠቀሱት መካከል ግንባር ቀደም ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው በተለይ በአፍሪካ አህጉር ከባድ የማህበረሰብ ጤና እክልና የኢኮኖሚ ተግዳሮት እንደሆነ ገልፀዋል:: በሽታው ባለፉት ዓመታት በቅንጅት በተሰሩ በርካታ ስራዎች የተሻለ ቁጥጥርና የመከላከል አቅም ተገንብቶ እንደነበር ያነሱት ዶ/ር ሰለሞን ይሁን እንጂ ከጥቂት አመታት ወዲህ የወባ በሽታ ስርጭት ዳግም ማገርሸቱን፣ በሀገራችን አዲስ የወባ አስተላላፊ ትንኝ ዝርያ መገኘቱን፣ በየአካባቢው የሚከሰቱ ግጭቶች መበራከት፣ በህብረተሰቡና በጤና ተቋማት የተፈጠሩ ዝንጉነቶች እንዲሁም በኮቪድ ምክንያት የተፈጠረው የጤናው ሥርዓት መዳከም ዋነኞቹ ባለድርሻዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል::

የወባ በሽታ ዳግም ስጋት ወደማይሆንበት ደረጃ ለማድረስ በአዳዲስ ምርምሮች የተደገፈ ስትራቴጂካዊ እቅድ ተዘጋጅቶ መተግበር እንደሚገባውም ዶ/ር ሰለሞን አሳስበዋል።

Hawassa University

03 Jan, 07:12


የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፋካሊቲዎች ስፖርታዊ ውድድር ተጠናቀቀ
**
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በስሩ በሚገኙ 5 ፋካሊቲዎች መካከል በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች ኢንስቲትዩቱን የሚወክሉ ስፖርተኞችን ለመመልመል ሲያካሂድ የነበረው ስፖርታዊ ውድድር ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም ተጠናቋል።

የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ኢ/ር ፋሲካ ቤተ በማጠቃለያው መርሃግብር ላይ እንደተናገሩት ስፖርት ለሰላም ግንባታና መግባባት ለመፍጠር መልካም እድል የሚፈጥር መሆኑንና በፋካሊቲዎቹ የእግር ኳስ፣ ሩጫ፣ ቴኳንዶና ቼዝ ውድድሮችን ያካተተው ውድድር በኢንስቲትዩቱ ማህበረሰብ ዘንድ የተሻለ ቅርርብ መፍጠሩን ገልጸዋል። በውድድሩ የታዩ ጠንካራ ስፖርተኞችም ኢንስቲትዩቱን ወክለው ዩኒቨርሲቲ አቀፍ (Inter campus) ውድድር ላይ እንደሚቀርቡና በመቀጠልም በአዲስአበባ በሚካሄደው ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲዎች ውድድር ላይ በመሳተፍ ዩኒቨርሲቲውን እንደሚያስጠሩ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።

ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ አቶ ተመስገን ከበደ በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ በትልልቅ መድረኮች ላይ ተሳታፊ መሆን የቻሉ ስፖርተኞችን ያፈራው ሀገር አቀፉ የዩኒቨርሲቲዎች ስፖርታዊ ውድድር ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ሳይካሄድ ቆይቶ ዘንድሮ ዳግም መጀመሩን አስታውቀዋል። ስፖርት በባህሪው የፉክክር ስሜትን የሚፈጥር ቢሆንም መሰል የአቻ ተቋማት ውድድሮች ዋና ግባቸው አንድነት መፍጠር በመሆኑ ውድድሮቹን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን አቶ ተመስገን አክለዋል።

በኢንስቲትዩቱ የራሱ እግር ኳስ ሜዳ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የእግር ኳስ ውድድር የኢንፎርማቲክስ እና ሲቪል ፋካሊቲዎች ለፍጻሜ የደረሱ ሲሆን በጨዋታውም የሲቪል ፋካሊቲ አሸናፊ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

26 Dec, 07:20


EXTENDED CALL FOR PAPERS

Hawassa University

25 Dec, 18:30


የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአገሪቱን እድገትና የህዝቡን ህይወት ለማሻሻል ቅድሚያ ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስገነዘቡ።
**

ትምህርት ሚኒስቴር ከአርባ ሰባት (47) የመንግስተት ዩኒቨርስቲዎች ጋር በ2017 የሚተገበር ቁልፍ የአፈጻጸመም ውል ተፈራርሟል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በስምምነቱ ወቅተት እንደገለጹት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሯቸው ምርምሮችና የሚያፈሯቸው ዜጎች አገር የሚለውጡና ከዓለም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል። የተፈረመው ውል ሃላፊነትና ተጠያቂነትን በማስፈን የትምህርት፣ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ጥራት ለማስጠበቅ እንደሚያስችልም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ ስምምነቱ መሠረት ውጤት የሚያስመዘግቡ ተቋማት በበጀት ጭምር የበለጠ የሚደገፉበት፣ ወደ ኋላ የሚቀሩና ዝቅተኛ አፈጻጸም የሚያስመዘግቡት ደግሞ ተጠያቂ የሚሆኑበት እንደሆነ ጠቁመዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የቁልፍ ስራዎች አፈጻጸም ውሉ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሳይንሳዊና ዓለም አቀፋዊ መለኪያዎች ላይ ያተኮረ እድገት እንዲኖራቸው እንደሚያስችል ገልጸዋል። ስምምነቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የክትትልና ግምገማ ስርዓት እንዲኖርና ዩኒቨርስቲዎች በተልዕኳቸው ላይ አትኩረው እንዲሰሩ እንደሚያደርግም ጠቅሰዋል።
ተቋማቱ በገቡት ስምምነት መሠረት ስራዎቻቸውን በየደረጃው በማውረድና ጠንክሮ በመስራት ቀጣይነት ያለው ውጤት ለማስመዝገብ መረባረብ እንዳለባቸው ተናግረዋል።

ስምምነቱን የትምህርት ሚኒስትሩን በመወከል የከፍተኛ ትምህርቶ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አት ኮራ ጡሹኔ ዩኒቨርስቲዎቹን በመወከል ደግሞ የየዩኒቨርስቲዎቹ ቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዚዳንቶች ፈርመዋል።

Hawassa University

25 Dec, 13:52


https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0N7qXrLbuUgz81N2WXiJrx8VCCvKGtXfeU7sQHNEzpLPQ3ZxaAbU9HMiJGZTH5GJsl&id=100064777722828&mibextid=kFxxJD

Hawassa University

24 Dec, 06:52


Call for Registration for NGAT Tutorials
*//*
December 24, 2024

Dear Graduate Studies Applicants,

Hawassa University, School of Graduate Studies, is pleased to announce plans to offer tutorials for the National Graduate Admission Test (NGAT) preparation. This tutorial will be delivered by experienced experts and is scheduled to take place one week before the actual exam.

To register, please send Your full name and field of study you're applying for graduate program via email at [ [email protected] ]

NB:
• Registration is free at this stage.
• Tutorials will only be conducted if a sufficient number of applicants register in advance.
• Payment will be required for the tutorial only after confirmation that it will proceed based on the number of registered applicants.

Therefore, we encourage interested applicants to register early. Your prompt registration will enable us to assess demand and determine whether the tutorial can be held.

       Hawassa University
               Ever to Excel!

Hawassa University

22 Dec, 19:12


በሚል ርዕስ የተሰጠው የቴማቲክ ፕሮጀክት ተንተርሶ ሙሉ በሙሉ ወርክሾፓችን pilot prototype አምርቶ በመጨረስ ለሙከራ አዘጋጅቷል ብለዋል።

የእነዚህ ማሽኖች የፈጠራ ባለቤትነት እውቅና ያላቸው ሁለት መሀንዲሶችን በዎርክሾፕ ውስጥ ተገኝተን ያነጋገርናቸው ሲሆን የማሽን ማምረት ስራውን እስከ 16 ሰዎች እንደሚሳተፉበትና በዋጋም ሆነ በጥራት ከውጭ አገር ከሚገዙት ማሽኖች እጅግ የተሻሉትን ማምረት እንደቻሉ አስረድተውናል::

ኢንጂነር ፍሬው ስለሺ ማሽኖቹ ከእንግሊዝና ከጀርመን የሚገቡትን የሚተኩ እንደሆነ ጠቅሶ በውሃ ምህንድስና ቤተ ሙከራዎች ውስጥ ሲሙሌተር: የውሃ ስነ ባህሪ መመርመርያ: የግድብ አሰራር መቆጣጠርያና የመሳሰሉትን ተግባር ተኮር ትምህርት ለመስጠት እጅግ አስፈላጊ ግብዓት መሆናቸውን አስረድቶናል:: ከስድስት ዓመታት በፊት የጀመሩት የፈጠራ ስራ አሁን ላይ ሰባት ማሽኖች ላይ መድረሱን የጠቀሰው መ/ር ፍሬው ድጋፍ ከተደረገላቸው ብዙ መስራት እንደሚችሉ ገልጽዋል::

ኢንጂነር መኮንን በቀለ በበኩሉ እስካሁን ከሰሩት ሰባት ማሽኖች በተጨማሪ ሙሉ የሃይድሮሊክስ ላብራቶሪን ማቋቋም ደረጃ መድረሳቸውን ጠቅሶ ከውጪ የሚመጣውን ማሽን ዋጋ በብዙ እጥፍ ባነሰ ዋጋ ለዩኒቨርሲቲዎች አስረክበው መተው ሳይሆን ከ100 ገፅ በላይ ያለው ማኑዋል አዘጋጅተው አብረው እንደሚያስረክቡና ለላብራቶሪ ባለሙያዎችም ስልጠና እንደሚሰጡ ተናግሯል::

የማኑፋክቸሪንግ ምህንስና ፋካልቲ ማሽን ዎርክሾፕን ሥራ የጎበኙት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ባዩት ነገር እጅግ መደሰታቸውን ገልፀው ከዩኒቨርሲቲው ጋር በመተባበር ለመስራት የሚፈልጉ ማንኛውም ተቋማት አብሮ ለመስራትና መሃንዲሶቹንም በአስፈላጊው ነገር ሁሉ ለመደገፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት አሳውቀዋል::
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

22 Dec, 19:11


ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሃይድሮሊክስ ምህንድስና ላብራቶሪ ማሽኖች እያመረተ ነው::
*//****
ታህሳስ 13 ቀን 2017 ዓም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ስር የሚገኘው የማኑፋክቸሪንግ ምህንድስና ፋካልቲ በራሱ መምህራን ያሰራቸውን ለሀይድሮሊክስ ቤተሙከራ የሚያገለግሉ ማሽኖች ከ24 በላይ ለሚሆኑ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ሠርቶ አስረክቧል።

የፋካሊቲው ዲን ዶ/ር ካሳሁን ጋሹ እንዳሉት የማኑፋክቸሪንግ ፋካሊቲ በስሩ ስድስት የትምህርት ክፍሎች ሲኖሩት በስራቸው ባሉ ወርክሾፕ ላቦራቶሪዎች ውስጥ የተለያዩ ሥራዎችን በመሥራት ላይ ይገኛሉ። በተለይ ከ2014 ዓ.ም በኋላ የዩኒቨርስቲያችንን የትኩረት አቅጣጫ ልየታ ተከትሎ ፋካሊቲው የተለያዩ ገቢ የሚያመነጩ ሥራዎችን መሥራት መጀመሩን የጠቆሙት ዶ/ር ካሳሁን የማሽን ሾፕ ውስጥ ከሰባት ዓመታት በላይ ካለ ሥራ የተቀመጡ ከ15 በላይ ቀላልና ከባድ ማሽኖችን የፌደራል ኦዲተር በ2014 ከላከልን በኃላ  በራሣችን መምህራን በመጠገን ወደ ምርት አስገብተናቸዋል ብለዋል። 
ከዚህ በተጨማሪ በውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ይገቡ የነበሩ ለሀይድሮሊክስ ላቦራቶሪ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ማሽኖች በፋካሊቲው መምህራን በተሻለ ጥራት ተሰርተው እና የአእምሯዊ ንብረት ባለቤትነት እውቅና ተሰጥቷቸው እስካሁን ለ24 የሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች ማስረከብ እንደቻሉ ዲኑ ገልፀዋል::
በቀጣይም ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ባደረግናቸው የመሥክ ዳሰሳ ጥናት ፍላጎቶችን ስላየን ወደሥራ ለመግባት የመግባቢያ ሠነዶችን ለመፈራረም በሒደት ላይ እንገኛለንም ብለዋል።
ዶ/ር ካሳሁን በሀዋሳ ዩኒቨርስቲና በሀዋሳ እንዳስትሪ ፓርክ በጋራ እየተሠራ ያለውን "Experimental Investigation and Implementation Automantion and Sludge Mangement System"

Hawassa University

22 Dec, 09:13


The panelists, Dr. Emebet Bekele, Ass. Professor of English Language, Literature & Linguistics and Executive of Public & International Relations at HU; Mahteme Feleke, a Lecturer of International Relations, Political Science & Law at CLG; and Addis Zena, Ass. Professor of Sociology at CSSH, delved into the essence of international relations, the role of technology in contemporary IR, most pressing challenges of IR in the 21st century, and strategies of overcoming those challenges from different perspectives.

Chekolech Neshru, a lecturer at CLG facilitated the panel discussion, and students raised questions to the panelists and they explained different issues in the complex nature of international relations and cooperation.

A scholarship student from South Sudan and an exchange student from Germany shared their experiences in Hawassa University with the beauty of differences in culture, language and food beyond being away from home. They both attested to the kindness and hospitality of Ethiopians which made them feel at home away from home.

The dean of CLG and the PIR executive both wished international students at Hawassa university a very pleasant holiday season with the upcoming Christmas and new year, and the session was concluded by certification.

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

22 Dec, 09:12


HUGaDSSA organizes a panel discussion on "Navigating the complexity of modern International relations"
*//****
December 22, 2024
Hawassa University Governance & Development Studies Students Association (HUGaDSSA) has organized a panel discussion under the theme "Navigating the complexity of modern International relations" on December 21, 2024 at Africa Union hall.

The Dean of College of Law & Governance, Dr. Debrework Debebe, stated in his opening speech that such a platform is very important to exchange culture, ideas and knowledge among scholars and to clarify confusions about international relations. He appreciated the students for organizing the event on a scholarly discussion and inviting international students to attend.

Feven Mekonnen, President of HUGaDSSA, also expressed her deepest gratitude for the CLG, the panelist academics, and her club members for making the panel discussion happen with their commitment and dedication.

Hawassa University

02 Dec, 18:44


የሴቶችና ማህ/ጉ/አ/ት/ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ምህረት ገነነ የዓለም የኤድስ ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ37ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ36ኛ ጊዜ እየተከበረ እንደሚገኝ እና የተለያዩ ሁነቶችን በማሰናዳት የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግና ውይይቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚመቻችበት ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በዕለቱ ከሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የኤች.አይ.ቪ መከላከልና መቆጣጠር ጽ/ቤት በመጡ ባለሙያ በወቅታዊው የሀገራችን የበሽታው ስርጭት ላይ ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et

Hawassa University

02 Dec, 18:43


የዓለም የኤድስ ቀን እና ዓለምአቀፉ የአካል ጉዳተኞች ቀን በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተከበረ::
**//**
ህዳር 23 ቀን 2017 ዓም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ "ሰብአዊ መብትን ያከበረ የኤች.አይ.ቪ አገልግሎት ለሁሉም" እና "የአካል ጉዳተኞችን የመሪነት ሚና በማጠናከር አካታችና ዘላቂ ልማት እናረጋግጥ" በሚሉ መሪ ቃሎች በጥምር ባከበረው በዓላት ላይ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው በዕለቱ ተሳታፊዎች ውይይት ተካሂዶባቸዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ አዳቶ መርሐ ግብሩን ባስጀመሩበት ንግግራቸው ከጥቂት ዓመታት በፊት ኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚደረግበት በሽታ ሆኖ የተሳለ የነበር ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በሰዎች ውስጥ በተፈጠረው ቸልተኝነት የተነሳ በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን አንስተዋል። ኃላፊው ይህንን መዘናጋት በመቅረፍ የቫይረሱን ስርጭት መግታት እንደሚገባ ገልጸው በዕለቱ በጥምረት እየተከበረ ስላለው የአካል ጉዳተኞች ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የትምህርትና ስነ-ባህሪ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ሳሙኤል አሰፋ ስለአለምአቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን ባስተላለፉት መልዕክት ከሀገራችን ህዝብ ውስጥ 2.4% የሚሆኑት የአካል ጉዳት ያለባቸው መሆኑን ጠቅሰው ይህንን ትልቅ ቁጥር ይዘው የሚገኙትን የህብረተሰብ ክፍሎች በሁሉም አገልግሎቶችና ማህበራዊ ኡደቶች ላይ ተደራሽና ዋነኛ ተሳታፊ በማድረግ ዘላቂ እድገትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህንጻዎቹን ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ከማድረግ አኳያ ራንች በማሰገንባት ውጤታማ ስራ መስራቱን የጠቆሙት ዲኑ በተጨማሪም በልዩ ፍላጎት የትምህርት ክፍል በርካታ ተማሪዎችን አቅፎ እያስተማረ እንደሆነ ተናግረዋል::

Hawassa University

02 Dec, 07:04


Information related to IELTS exam at Hawassa University can be obtained through the following email address: [email protected] or mobile phone: 0925629589, and by visiting the British Council’s official website.

Take IELTS at Hawassa University!
Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

02 Dec, 07:03


HU hosts its fifth round of IELTS Exam
**//**
December 2, 2024
Hawassa University, in partnership with the British Council Ethiopia, has successfully hosted the fifth round of IELTS (International English Language Testing System) exam session on November 28-30, 2024 where 29 individuals sat for the paper-based IELTS exam (both IELTS Academic and IELTS General).

According to Dr. Mihireteab Abraham, Coordinator of the Centre at HU, individuals are taking the advantage of geographical proximity and other factors which make it convenient for them when deciding to take the exam at Hawassa University, and the figure shows growing demand among the community to take the IELTS exam at HU. Dr. Mihireteab mentioned that the next round of IELTS exam session at Hawassa University will be conducted in February, 2025 and the registration is already being undertaken, and IELTS exam preparation is also part of the service that the Center provides through its British Council certified trainers.

Hawassa University

30 Nov, 12:45


በኢትዮጵያ ሰላም ተቋም የፕሮግራም ኃላፊ አቶ ካሳሁን አብደታ ተቋሙ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ አካባቢዎች ላይ የሰላም እሴቶች ግንባታና ግጭት አፍታት ዙሪያ አመራሩንና አጠቃላይ ማህበረሰቡን ዝግጁ በማድረግ ረገድ የተጣለበትን ሀገራዊ ግዴታ ሲወጣ መቆየቱን አስረድተዋል። ሰላም ለአንድ አካል የሚሰጥ የአንድ ጊዜ ስራ አለመሆኑን የገለጹት አቶ ካሳሁን ሰላማዊ የዩኒቨርሲቲ ከባቢን መፍጠርም የሁሉም ባለድርሻ አካላት የጋራ ውጤት ስለሆነ ከፍተኛ አመራሩን በብቃት ለማስታጠቅ ስልጠናው መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et

Hawassa University

30 Nov, 12:44


የግጭት አፈታትና ሰላም አጠባበቅ ክህሎት ላይ ለከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ።
**
ህዳር 21 ቀን 2017 ዓም
ሰላማዊ የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብን ለመፍጠር ላለፉት ሶስት አመታት ለተለያዩ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አካላት ስልጠናዎችን ሲሰጥ የቆየው የኢትዮጵያ ሰላም ተቋም ለዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በግጭት ጥንቁቅነትና ዝግጁነት ላይ ያተኮረ ሁለት ቀናት ስልጠናዊ ውይይት በሮሪ ሆቴል እየሰጠ ነው::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዚደንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ውይይቱን ባስጀመሩበት ንግግራቸው የዩኒቨርሲቲ ሰላም ሊስተጓጎል የሚችለው የመማር ማስተማር ሂደቱ በአግባቡ ሳይመራ ሲቀር፣ የተቋም ህግና ሰላም ተጠብቆ ጥያቄዎች በአግባቡ ሳይስተናገዱ ሲቀሩ፣ ተማሪው የሚጠቀማቸው አገልግሎቶች ተሟልተው አለመቅረብ እንዲሁም ከዩኒቨርሲቲ ውጪ ያሉ አላስፈላጊ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ አካላት ተጋላጭነት ሲኖር ዋና ዋናዎቹ በመሆናቸው በእነዚህ ዘርፎች ላይ ውጤታማ ስራ መስራት ሰላምን ለማስጠበቅ የራሱ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። ሰላምን ማረጋገጥ ለአንድ ወገን የሚሰጥ ኃላፊነት ሳይሆን ሁሉም አካላት አስፈላጊውን ክህሎት ተላብሰውና እጅ ለእጅ ተያይዘው የሚያስቀጥሉት በመሆኑ ስልጠናው በሁሉም ክፍሎች ላይ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ፕሬዝዳንቱ አክለዋል።

የሀ/ዩ/ፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ አዳቶ በበኩላቸው ከኢትዮጵያ ሰላም ተቋም ጋር በትብብር ከተሰሩ ዋነኛ ስራዎች መካከል የሰላም አምባሳደሮችን በማሰልጠን የግቢውንና የአካባቢውን ሰላም ማስጠበቅ በሚችሉበት ቦታ ማሰማራት ዋነኛው መሆኑን አስታውሰው ስልጠናው ከጥቂት በቅርቡ በዩኒቨርሲቲው በተደረገው የከፍተኛ አመራር ለውጥ ምክንያት ም/ፕሬዚደንቶች፣ ዲኖችና ማኔጂንግ ዳይሬክተሮችን ጨምሮ በሥራ ላይ የጋራ መግባባት እንዲኖር ታስቦ በድጋሚ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

Hawassa University

18 Nov, 13:16


ቋሚ ኮሚቴው የገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዝ ሥራዎች ተዘዋውሮ ጎበኘ::
**//**
ህዳር 9/2017 ዓም
በኢፌዲሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ፣ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዝ ስራዎችን ከህዳር 7-8/2017 ዓም በየካምፓሱ በአካል ተገኝቶ ጎብኝቷል።

የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢና የቡድኑ አስተባባሪ የተከበሩ ወ/ሮ አራሬ ሞሲሳ በጉብኝቱ ወቅት ቋሚ ኮሚቴው ኢንተርፕራይዙ የነበረበትን የኦዲት ግኝት አስመልክቶ ያስቀመጣቸው አቅጣጫዎች መኖራቸውን አስታውሰዋል።

በዚሁ መሠረት ኢንተርፕራይዙ መውሰድ ያለበትን ማሻሻያዎች ተግባራዊ በማድረግ ተቋሙ የታለመለትን ዓላማ ለማሳካት ደንብና መመሪያን ተከትሎ በመስራት የራሱን ገቢ ማመንጨት እና የተሻለ ስራ በመስራት የዩኒቨርስቲውን የውስጥ አቅም ሊያሳድግ እንደሚገባ አመላክተዋል።

ማሻሻያውን በተመለከተ በርካታ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን፣ ማሻሻያ ያልተደረገባቸው ግኝቶችን ለመፍታት የተዘጋጀ የአሰራር ስርዓት ስለመኖሩ ቋሚ ኮሚቴው በጉብኝቱ ወቅት ካነሳው ውስጥ የሚጠቀስ ነው።

ቋሚ ኮሚቴው በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዝ የወንዶ ገነት ደንና ተፈጥሮ ሃብት ኮሌጅ እና በሀዋሳ ግብርና ኮሌጅ ዕደ ጥበብ ማዕከላት እንዲሁም በዋናው ግቢ የሚገኙ የገቢ ማመንጫ ስራዎችን አሁናዊ ይዞታ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

                    ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
                    ሁሌም ለልህቀት!
           
በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et

Hawassa University

18 Nov, 11:50


የ2017 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎች እየገቡ ነው

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከ4,500 በላይ የሚሆኑ የ2017 ዓም አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎቹን ከዛሬ ጀምሮ እየተቀበለ ነው::

የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ህብረት ከተማሪዎች አገልግሎት ዲን ፅ/ቤት እንዲሁም ከካምፓስ ፀጥታና ደህንነት አካላት ጋር በመቀናጀት ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች አቀባበል እያደረጉ ነው::

የአስ/ል/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ አዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል ከጸጥታና ደህንነት እንዲሁም ከምግብና መኝታ አገልግሎት ጋር የተያያዘ ሰፊ ዝግጅት በዩኒቨርሲቲው ሲካሄድ መቆየቱን ገልጸው ተማሪዎቹ በዋናው ግቢና በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እንደተመደቡ ተናግረዋል:: ም/ፕሬዝዳንቱ ልጆቻቸውን ወደ ዩኒቨርሲቲው ይዘው የመጡ ወላጆችም ሆነ ተማሪዎች ያለምንም ስጋት በአቀባበል ኮሚቴው አባላት የሚሰጣቸውን መመሪያ በመከተል አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የተማሪዎች አገልግሎት ም/ዲን መ/ር ዳሞት ተስፋዬ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የብዙ አዳዲስ ተማሪዎች የቅድሚያ ምርጫ ከሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ እንደመሆኑ ከመማር ማስተማሩ ጎን ለጎን አጠቃላይ የተማሪዎች አገልግሎቱና የካምፓስ ቆይታው የተሻለና ሰላማዊ  እንዲሆን በትጋት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
ሀሳባቸውን የሰጡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከመምጣታቸው በፊት የቀድሞ ተማሪዎችን መረጃ መጠየቃቸውን ገልጸው ጥሩ ግብረ መልስ በማግኘታቸው ዩኒቨርሲቲውን መርጠው መምጣታቸውን ተናግረዋል:: እስከአሁን ያለው አቀባበልም አስደሳች ሆኖ እንዳገኙት ገልፀዋል።

አዲስ የዩኒቨርሲቲያችን ተማሪዎች እንኳን ወደ ልህቀት ማዕከሉ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ እንኳን ደህና መጣችሁ እያልን መልካም የትምህርትና የስኬት ዘመን እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን!
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ

Hawassa University

15 Nov, 11:02


China and Africa through nnurturing skilled talents and diversified exchanges in the words of the Jiangsu province's governor.

Being one of the pioneering universities to run academic and research programs in forestry and natural resources management, Hawassa University is the right place to collaborate with NUIST on establishing joint academic and research programs related to climate change and building resilient environment.

Hawassa University
Ever to Excel!

Follow us @
**
Website: https://www.hu.edu.et
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Telegram: https://t.me/HUCommunicationsoffice

Hawassa University

15 Nov, 11:02


HU, NUIST ink MoU for Collaboration
**//**
November 15, 2024
Hawassa University has signed a memorandum of Understanding for collaboration with Nanjing University of Information Science and Technology (NUIST), China, on November 14, 2024 at the Adwa Memorial Museum, Addis Ababa.

Hawassa University's Interim President Dr. Chirotaw Ayele and CHEN Haishan, President of Nanjing University of Information Science and Technology, signed the agreement at the China- Africa Vocational Education Cooperation and Exchange Conference organized by Jiangsu Provincial Department of Education and Nanjing Vocational University of Industry Technology, and hosted by Jiangsu Provincial People's Government, the Ethiopian Ministry of Labor and Skills, and Department of Higher Education and Training of South Africa.

The signing of MoU between the two universities is believed to be a starting point for Cooperation for Win-Win Results with an opportunity to contribute more wisdom and strength towards the modernization of

Hawassa University

13 Nov, 11:04


ክህሎት ማሻሻያ እድሎች ላይ የበለጠ ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባ ም/ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር ኢ/ር ፍስሃ ጌታቸው ተናግረዋል::

በተመሳሳይ በምርምር: የማህበረሰብ አገልግሎትና ዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስር ዘርፎች ላይ የበለጠ መስራት የሚጠበቀው በጭብጥ-ተኮር ምርምሮችና የድህረምረቃ ተማሪዎችን ያካተቱ ፕሮጀክቶች ላይ ማትኮር: በዓለምአቀፍ ጆርናሎች ላይ ያለውን ህትመት መጨመር: የተጀመሩ ጆርናሎችን እውቅና እንዲያገኙ ማጠናከር: ራስን ለመቻል የሚረዱ ጠንካራ የትብብር ፕሮጀክቶችን ማምጣት: ከኢንዱስትሪው ጋር ጠንካራ ትስስር መፍጠር: የምርምርና ልህቀት ማዕከላትን ማዘመንና አለማቀፍ ስታንዳርድ ማሰጠት: ከማህበረሰቡ ጋር ትርጉም ያለው ትስስርና ትብብር መፍጠር: ያለንን ተፈጥሯዊና አካባቢያዊ ፀጋ ለይቶ ፈጠራ የታከለበት ችግር ፈቺ ምርምር መስራት እንደሚገኙበት ም/ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ ገልፀዋል::

በመጨረሻም በአስተዳደርና ልማት ዘርፉ ዩኒቨርሲቲው ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራው በሰው ኃይልና የመሰረተ ልማት አቅም ግንባታ ላይ ሆኖ ከዚህ በኃላ እንደበፊቱ ወደጎን መስፋት ሳይሆን ጥራትና አግባብነት ላይ የበለጠ እንደሚሰራ: ካለው የበጀትና የገበያ ሁኔታ ጋር የተናበበ ቅድሚያ ሊሰጣቸው በሚገባቸው ጉዳዮች ልየታ ላይ የተመሰረተ የግዥ: የጥገናና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ሥራዎች ላይ ብሎም ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን ተጠቅሞ አገልግሎቶችን በሙሉ አውቶሜት ማድረግ ላይ መሆኑን ም/ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ አብራርተዋል::
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et

Hawassa University

13 Nov, 11:03


የ2017 በጀት ዓመት አንደኛ ሩብ አመት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
ህዳር 4/2017 ዓም
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የ2017 በጀት ዓመት አንደኛው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የገመገመበት መድረክ አካሂዷል::

የዩኒቨርሲቲው ተ/ፕሬዚደንት ዶ/ር ችሮታው አየለ መድረኩን ባስጀመሩበት ንግግራቸው ዘንድሮ የግምገማ መድረኩን ለየት የሚያደርገው በቅርቡ በማኔጅመንት ውሳኔ ካውንስሉ ከዚህ ዓመት ጀምሮ በነበረው የአባላት ስብጥር ላይ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎችን ማካተቱ አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ ሩብ ዓመት ግዜ ውስጥ በየኮሌጆችና ትምህርት ክፍሎች ደረጃ ምን ታቅዶ ምን እንደተከናወነ እንዲሁም ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና በቀጣይ ትኩረት የሚፈልጉ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቅጣጫ ለመያዝ መድረኩ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ተ/ፕሬዝዳንቱ አክለዋል።

በግምገማ መድረኩ ከስምንት ኮሌጆች: የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እና በንሳ ዳዬ ካምፓስ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ካውንስሉ በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ሰፊ ውይይት አድርጓል::

ውይይቱን የመሩት ሶስቱም ምክትል ፕሬዝዳንቶች ዩኒቨርሲቲው አሁን በሚጠበቅበት የራስገዝነት እና የምርምር ዩኒቨርሲቲ የመሆን የሽግግር ወቅት ላይ እንደመሆኑ በየዘርፋቸው በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ያላቸውን ግብረመልስ ሲሰጡ አስሩም የዩኒቨርሲቲው ቅርንጫፎች በቀሪዎቹ የዓመቱ ወራት ውስጥ በአጠቃላይ የዩኒቨርሲቲው መፃኢ ዕድል ላይ ወሳኝ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል::

በአካዳሚክ ዘርፍ ላይ ድጅታላይዜሽን: የድህረምረቃ ፕሮግራሞችን ማጠናከር: የፕሮግራሞች ክለሳና አለማቀፍ እውቅና ማግኘት: ፕሮግራሞችን ከዩኒቨርሲቲው ልዩ የትኩረት መስክ ጋር ማጣጣም: ቤተሙከራዎችንና ቤተመፃህፍትን በቴክኖሎጂ ግብዓቶች ማሳደግ እንዲሁም የተማሪዎች ተግባር-ተኮር ትምህርትና ክህሎት

Hawassa University

12 Nov, 18:18


የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶ/ር መቅደስ ሺፈታ ስለ SLL360 ፕሮጀክት ዓላማና ይዘት ሲያብራሩ ፕሮጀክቱ የጨቅላ ሕፃናት ሕክምናን በማዘመንና ተደራሽ በማድረግ በኢትዮጵያ ደረጃ አምስት ክልሎች ውስጥ የሚገኙ 16 ሆስፒታሎች ላይ በምርምር: በአቅም ግንባታ: በቴክኖሎጂ ሽግግርና በማህበረሰብ ጤና አገልግሎት ዘርፎች ላይ የሚሰራና ከዓለም ጤና ድርጅት ጀምሮ በርካታ ዩኒቨርሲቲዎችንና ሌሎች አጋሮችን ያቀፈ አለማቀፍ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀዋል:: በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስር በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የሚሆኑት የዩኒቨርሲቲው ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል: አዳሬ ጠ/ሆስፒታል: ቱላ ጠ/ሆስፒታል እና ዶሬ ባፋና የመ/ደ/ሆስፒታል መሆናቸውን ዶ/ር መቅደስ አክለዋል:: በዕለቱ በክሊኒካል: በቴክኖሎጂ: በጥራት ማሻሻያና በዳታ ዘርፎች ላይ ያለውን ሥራ የሚመሩት የፕሮጀክቱ አባላት የየዘርፋቸውን ዕቅድና አፈፃፀም አቅርበዋል::

የሀ/ዩ/ምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዮስ በመርሃግብሩ ላይ ከተጋበዙት ባለድርሻ አካላት የተነሱ አስተያየትና ጥያቄዎችን ላይ የፕሮጀክቱ አባላት ምላሽ እንዲሰጡ አድርገዋል:: ም/ፕሬዝዳንቱ በማጠቃለያ ንግግራቸው ፕሮጀክቱ የመሰረተ ልማትና የሰው የአቅም ግንባታ: የምርምር: የቴክኖሎጂ ሽግግርና የማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፎችን አካትቶ የያዘ ካለፉት ተሞክሮዎች ብዙ ትምህርት ወስዶ የተቀረፀ ሁለገብ በመሆኑ ለዩንቨርሲቲያችንና ለዚህ አካባቢ ብቻ ሳይሆን እንደሀገር በጨቅላ ሕፃናት ሕክምና ዘርፍ ወርቃማ ዕድል ይዞ የመጣ መሆኑን በመረዳት የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ሙሉ ድግፍና ክትትል እንደሚያደርግ ገልፀዋል::

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et

Hawassa University

12 Nov, 18:17


በጨቅላ ሕፃናት ሕክምና ላይ የሚሰራው "SLL360" ፕሮጀክት የማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሄደ::
*//*
ህዳር 3 ቀን 2017 ዓም
በሀዋሳ ዩኒቨሪሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ስር በጨቅላ ህጻናት ህክምናና ሕይወት የማዳን ሥራ ላይ የሚያተኩረው Saving Little Lives (SLL 360) የተሰኘ አለማቀፍ የትብብር ፕሮጀክት የማስጀመሪያ መርሃግብር ህዳር 2/2017 ዓም በሮሪ ሆቴል ተካሂዷል::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታዉ አየለ መርሃግብሩን ሲያስጀምሩ በሀገራችን የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ጤናና ህክምና በየትኛዉም ደረጃ የሚገኝ ተቋምና ማህበረሰብን በእጅጉ ሊያሳስብና ልዩ ትኩረት ሊሰጠዉ የሚገባ አጀንዳ መሆኑን ጠቅሰዉ ዩኒቨሪሲቲው ይህንን ከግምት በማስገባት የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ህክምናን በማሻሻል መጠነ-ሞትን ለመቀነስ እንደሀገር በሚደረገው እንቅስቃሴ ላይ የጎላ አስተዋፅዖ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል:: ዶ/ር ችሮታው የ"SLL 360" ፕሮጀክትን ቀርፀው ያለግዜያቸው የሚወለዱ ጨቅላ ሕፃናትን ሕይወት ለመታደግ በልዩ ትጋት እየሰሩ ያሉትን ሴት ስፔሻሊስት ሐኪሞችና አብረዋቸው የሚሰሩትን ባለሙያዎች በሙሉ ላልተቆጠበው ድንቅ ሃገራዊ አበርክቷቸው ከልብ አመስግነው የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ለፕሮጀክቱ ስኬታማ አፈፃፀም ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል::

የሲዳማ ብ/ክ/መ/ጤና ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንደ ፕሮጀክቱ ተጠቃሚና ዋና አጋር በክልሉ ያለውን የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት መጠነ ሞት ቅነሳ ላይ እስካሁን በርካታ ዉጤታማ ስራዎች ከዩኒቨርሲቲው ጋር እንደተሰሩ ገልፀዉ የክልሉ ጤና ቢሮ ለSLL360 ፕሮጀክት የተሳካ ተፈፃሚነት ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል::

Hawassa University

04 Nov, 19:16


ማስታወቂያ
*********
ጥቅምት 25/2017 ዓም

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች   የምዝገባ  ጊዜ ኀዳር 09-10/2017 ዓ.ም መሆኑን ይገልጻል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
• የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ
• የማህበራዊ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት

ማሳሰቢያ፤
ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲመጡ የሚከተሉትን ይዘው መምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡
• የ12ኛ ክፍል ፈተና ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
• ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው
• አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
• አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣
• የስፖርት ትጥቅ

ማሳሰቢያ:-

ከተጠቀሰው ቀን በፊትም ሆነ በኃላ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡
     
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ጽ/ቤት

                    ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
                    ሁሌም ለልህቀት!
           
በዚህ ይከታተሉን:-
*************
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et
Telegram: https://t.me/HUCommunicationsoffice

Hawassa University

03 Nov, 13:03


ዶ/ር ችሮታው በንግግራቸው "የማህበረሰብ አገልግሎት ሲባል ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠው ማህበረሰብ ደግሞ ዝም ብሎ የሚቀበለው አገልግሎት ሳይሆን ሁለቱም በአጋርነት ስሜት የማህበረሰቡን ችግር በሳይንሳዊ እውቀት ላይ የተመሰረተ መፍትሄ የሚያፈላልጉበት ትብብር" መሆኑን አስምረውበታል:: እስካሁን በተለምዶ ዩኒቨርሲቲው ወደ ማህበረሰቡ በመቅረብ ይሄንን ችግር በጥናት ስለደረስንበት እንፍታው ማለት ብቻ እንደማይበቃ የጠቀሱት ተ/ፕሬዝዳንቱ የማህበረሰብ መሪዎችም ወደ ዩኒቨርሲቲው ቀርበው የቸገራቸውን ጉዳይ አብሮ ለመፍታት የሚተባበሩበት አሰራር መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል:: በዚህም ዩኒቨርሲቲው ከማህበረሰቡ አመራር ጋር የልማት አጋር መሆኑን በመረዳት ዩኒቨርሲቲዉ በጥሩ ሁኔታ እንዲያገለግል እና የህብረተሰቡን ፍላጎትና ችግር ገብቶት እንዲያግዝ አጋርነታችን እንዲጠናከር መሰል የምክክር መድረኮች ቢያንስ በዓመት ሁለት ግዜ ይኖረናል ብለዋል።

የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ማርቆስ ፍስሐ ላለፉት ሦስት ዓመታት በዳይሬክቶረቱ የተሰሩ ስራዎች ሪፖርት እንዲሁም የ2017 ዓ.ም የክንውን ዕቅድ ለተሳታፊዎች ካቀረቡ በኃላ በቀረበው ገለፃ ላይ ግብረመልስ እና ውይይት ተደርግጓል::

በባለድርሻ ውይይት መድረኩ ላይ ከሲዳማ ብሔራዊ ክልል ሁሉም ክላስተር ቢሮዎች፣ ከ4ቱም ዞኖች፣ ከ26 ወረዳዎች እና ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሁሉም መምሪያዎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች የተጋበዙ ሲሆን በተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዉ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et

Hawassa University

03 Nov, 13:02


የማህበረሰብ አገልግሎት ማጠናከሪያ የምክክር አዉደጥናት ተካሄደ።
**//**
ጥቅምት 24 ቀን 2017 ዓ.ም

በሀዋሳ ዩኒቨርሰቲ የምር/ቴ/ሽ/ም/ፕ/ጽ/ቤት ስር የሚሰራው የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ሥራዎቹን ለማጠናከር ያለመ የባለድርሻ አካላት የምክክር አዉደጥናት ጥቅምት 23/2017 ዓም በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ አካሂዷል።

የም/ቴ/ሽ/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸዉ የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት እንደስራ ክፍል ከተመሰረተበት ጀምሮ ላለፉት 13 ዓመታት በተመረጡ 6 ዘርፎች ማለትም በሰብል ልማት፣ በእንስሳት እርባታ፣ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ፣ በትምህርት፣ በጤና እና በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዘርፎች ከ6 የቴክኖሎጂ መንደሮች አንስቶ በአሁኑ ሰዓት በ19 ወረዳዎች የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎቹን ማስፋቱን ገልፀዋል። ም/ፕሬዝዳንቱ የመድረኩ ዓላማ እስካሁን ምን እንደተሰራ እና ምን መጠናከር እንዳለበት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት አገልግሎቱን በጋራ አጠናክሮ ለመቀጠል መሆኑን ተናግረዋል።

ተ/ፕሬዝዳንት ክቡር ችሮታዉ አየለ (ዶ/ር) በመክፈቻ ንግግራቸው ዩኒቨርሲቲዉ በመማር ማስተማር፣  በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎቹ ለሀገር እድገት ብሎም ለአካባቢው ማህበረሰብ እስካሁን የቻለውን በጎ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንዳለ ጠቅሰው በተለምዶ የማህበረሰብ አገልግሎት ላይ ካለው ሰፊ የግንዛቤ ማነስ የተነሳ የሚጠበቀውን ያህል ርቀት አለመጓዙን ተናግረዋል::

Hawassa University

02 Nov, 19:08


Last day of Internship celebration at Hawassa University, 2024
**//**
November 2, 2024

You remember the feeling of joy, almost to tears, the day you discharged your first patient from the hospital and the tears that you can never hold back during the miracle of birth.

That feeling is a reward for your hard work here [in medical school] and in years that follow. You can't imagine being a doctor without it.

We ask you to recall the vigor and happiness of your youths and then, imagine the beauty of that energy channeled into the care of another human being.

Congratulations 👏👏👏🎉🎉🎉

From obstetrics and gynecology residents!!!

Hawassa University
Ever to Excel!

Hawassa University

01 Nov, 15:22


ለምርምር ስነምግባር ገምጋሚ ኮሚቴ አባላት ስልጠና ተሰጠ::
ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ፕሮግራሞች ዳይሬክቶሬት በዩኒቨርሲቲው በሁሉም ኮሌጆችና ኢንስቲትዩቶች ለሚሰሩ የምርምር ስነምግባር ገምጋሚ ኮሚቴ አባላት በምርምር ስነምግባር መመሪያ ላይ ያተኮረ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

የምርምር ፕሮግራሞች ዳይሬክተር ዶ/ር ራህመቶ አበበ በመክፈቻው ንግግራቸው እንደገለፁት በዳሰሳ ጥናት በተገኘ ውጤት መሰረት በሁሉም ኮሌጆች ወጥ የሆነ የምርምር ግምገማ አሰራር ስርዓት ላይ ክፍተት በመታየቱ፣ በምርምር ገምጋሚ ኮሚቴውና ተመራማሪዎች መካከል አለመግባባት በመከሰቱ እና የኮሚቴው አባላትም በየጊዜው ስለሚቀያየሩ አዲስ ለሚመጡት አባላት ግንዛቤ እንዲጨብጡ ለማድረግ አስፈላጊ ስልጠና መሆኑን ጠቅሰው ስልጠናው አባላቱ በምርምር ስነምግባር ግምገማ አሰራር ላይ ወጥነት ያለው ሥርዓት እንዲከተሉ ለማስቻል ነው ብለዋል፡፡ ስልጠናው በዩኒቨርሲቲው የሚካሄደውን ምርምር በስነምግባር እንዲሚያሳድግና የምርምር ምክረሃሳቦች በጥንቃቄ እንዲመረጡ ይረዳል የሚል እምነት አላቸው፡፡

የምርምር ስነምግባር መመሪያው በየዓመቱ የሚፀድቁ ምርምሮች ወደ ተግባር ከመግባታቸው በፊት ማሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶች ማሟላታቸውን ለማረጋገጥ፣ የምርምሩን ዓላማ፣ ሂደት፣ ጥቅምና ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመረዳት፣ በምርምር የሚሳተፉ ሰዎች ፈቃደኝነታቸው የተረጋገጠ መሆኑን ለማወቅ፣ የመረጃ ሰጭዎችን ወይም ተቋማትን ማንነትና የሰጡትን መረጃ አይነት ሚስጥር በጠበቀ ሁኔታ መሰራት እንዳለበት እና የሚሰሩ ምርምሮች መረጃ ሰጭዎች ላይ ጉዳት የማያደርስና ምቾት የማያሳጣ መሆኑን ለማረጋገጥ እንዲሁም የሚሰራው ምርምር ሳይንሳዊ ታዕማኒነት ያለው መሆኑን ለማረጋገጥ የሚረዳ መሆኑን ዶ/ር ራህመቶ ተናግረዋል፡፡
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ

Hawassa University

31 Oct, 17:24


የትኩረት መስኮች ላይ ጥራትን መሰረት ያደረገ ልየታ ማድረጉን አስታውሰው አሁን ግዜውን የዋጀ አሰራር ለመዘርጋት ያሉትን ሁሉ የትምህርት ፕሮግራሞች ይዘን መቀጠል ስለማንችል በአጭር ግዜ ውስጥ በጥናት ላይ የተመረኮዘ የፕሮግራም ክለሳ ይደረጋል ብለዋል:: እንደተባለው ዩኒቨርሲቲ መምሰል: ራሳችንን ለመቻል ከፍተኛ ጥረት ማድረግና ተወዳዳሪ ሆኖ ፈተናውን ለማለፍ እጅ ለእጅ ተያይዘን በጥንቃቄ መስራት አለብን ሲሉ ጥሪ አድርገዋል::

ስለራስገዝነት ስናስብ ማወቅ ያለብን መንግስት ማንንም ያለአግባብ ሥራ የማሳጣት ዓላማ ኖሮት ሳይሆን ሁሉም ብቁና ተወዳዳሪ ሆኖ በተቀመጠበት የስራ መስክ ውጤታማ መሆን ካልቻለ ከውድድር የሚወጣበት አሰራር መዘርጋት ላይ እያተኮረ ነው ያሉት ተ/ፕሬዝዳንቱ አሁን የአስተዳደር ሰራተኛ ብቻ ሳይሆን በአግባቡ ማስተማር ያልቻለ መምህር: ውጤታማ ያልሆነ ማንኛውም ሰው በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ቦታ አይኖረውምና ሁሉም ኃላፊነቱን አውቆ በየደረጃው በህግ ተጠያቂነት ስሜት ስራውን ካልሰራ ከሲስተም እንዲወጣ እናደርጋለን ብለዋል:: እጁ ንፁህ ሆኖ ሕጋዊ አሰራርን ብቻ ተከትሎ ካልሰራ ማንኛውም ሰው ከተጠያቂነት እንደማይድን አስተዳደሩም ህገወጥነትን እንደማይታገስ ተ/ፕሬዝዳንቱ አስምረውበታል::

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et

Hawassa University

31 Oct, 17:24


የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች የአዋዳ ካምፓስን ጎበኙ::
**//**
ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም
በተ/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ የተመራው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራር ቡድን ዛሬ በአዋዳ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የጉብኝትና ውይይት መርሃግብር አካሂደዋል::

የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ወገኔ ማርቆስ አመራሮቹን ሲቀበሉ ስለ ኮሌጁ ታሪካዊ ዳራ: አሁናዊ ቁመናና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን ከሌሎች ኮሌጆች ለየት የሚያደርገው ደግሞ ኮሌጁ ሦስት ቦታዎች ላይ ማለትም ሀዋሳ ዋናው ግቢ: አዋዳና አለታወንዶ ላይ የሚሰራ በመሆኑ ለአስተዳደር ትኩረት የማጣት ብሎም ለክትትልና ድጋፍ የማያመች መሆኑን ጠቁመዋል:: እንደ መልካም ዕድል ከተነሱ ነጥቦች መካከል ደግሞ የሚሰጣቸው የትምህርት መስኮች በጣም ተፈላጊ መሆናቸው እና በዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተማሪ የሚያስተናግድ መሆኑን አንስተዋል::

የከፍተኛ አመራር ቡድኑ በግቢው ውስጥ ያሉ የተለያዩ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በአካል ከጎበኙ በኃላ ከኮሌጁ አመራሮች ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከኮሌጁ አመራሮችና መምህራን ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎች ሦስቱም ምክትል ፕሬዝዳንቶች በየዘርፉ ምላሽ ሰጥተዋል::

በመጨረሻም ተ/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ በኮሌጁ ለተደረገላቸው መልካም አቀባበል ከልብ አመስግነው ኮሌጁ ለዩኒቨርሲቲው የራስገዝነት ጉዞ ትልቅ ድርሻ ከሚወስዱት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው የማጠቃለያ ሃሳብና የስራ መመሪያ ሰጥተዋል::

ዶ/ር ችሮታው መንግስት ለዩኒቨርሲቲዎች በየዓመቱ እጅግ ከፍተኛ በጀት መድቦ ቢያስፋፋም ብቁና ተወዳዳሪ ምሩቃን ከማፍራትና ችግር ፈቺ ምርምሮች ሰርቶ ስር ነቀል ሃገራዊ ለውጥ ከማምጣት አንፃር የሚጠበቀውን ውጤት ሊያመጡ ስላልቻሉ በትክክል እንዲያመጡ የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት በተወሰኑ

Hawassa University

30 Oct, 20:23


various studies on Frailty in PLHV, Lung function study, NCDs study and STI. Additionally, he mentioned that the project has financially supported two MPH students in their thesis work and established a large dataset.

During the workshop, two professionals from the public health department, Mr. Netsanet Abera and Mr. Abreham Abate, addressed participants on policy issues, challenges, and opportunities related to dual HIV/syphilis testing. Mr. Netsanet emphasized that syphilis poses significant risks at global, continental, and national levels. Meanwhile, Mr. Abreham provided insights into what syphilis is,  the algorithm for HIV/syphilis testing, and strategies for addressing the challenges faced by the health sector in improving HIV/syphilis rapid diagnostic testing in antenatal care settings.

Participants also raised their concerns on implementing dual HIV/syphilis testing in their health centers as well as mitigating mechanisms of challenges hindering the enactment.  

Finally, Mr. Alemu Tamiso, Chief Executive Director of the CMHS gave a closing remark where he stated that HIV/AIDS is spreading alarmingly and such platforms are very important to solve related societal problems calling for stronger coalitions.

Hawassa University
Ever to Excel!

Follow us @
**
Website: https://www.hu.edu.et
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Telegram: https://t.me/HUCommunicationsoffice

Hawassa University

30 Oct, 20:23


HU holds Stakeholders’ Workshop on enhancing HIV/Syphilis RDT in Antenatal Care in Southern Ethiopia
**//***
October 30, 2024
Department of Public Health at Hawassa University, in collaboration with Frailty Study Project, has conducted a stakeholders' workshop on dual HIV/syphilis testing during antenatal care in Southern Ethiopia at Rori International Hotel.

Prof. Mebratu Mulatu, Director of Collaborative Projects' Coordination at HU, officated the workshop where he emphasized the essence of the project on mothers' and infants' care.

Prof. Jaime Vera, the principal investigator from Brighton and Sussex Medical School, UK, virtually addressed the ultimate importance of dual HIV/Syphilis testing to the participants.

Dr. Endrias Markos, the focal person for the dual RDT testing project at HU, also provided a comprehensive overview of the initiative. Dr. Endrias underscored that the Frailty study project has made significant contributions at Hawassa University since 2021 which includes

Hawassa University

30 Oct, 15:31


ማስታወቂያ
ለአዲስ የድህረምረቃ ትምህርት አመልካቾች በሙሉ:-

በ2017 ዓም የትምህርት ዘመን በቂ አመልካች ላለባቸው ፕሮግራሞች የመጀመሪያ ሴሚስተር ምዝገባ የሚከናወነው ከጥቅምት 25 - 27/2017 ዓም ብቻ መሆኑን እናሳውቃለን::

ማሳሰቢያ:-
በምዝገባ ወቅት ከዩኒቨርሲቲው የድህረምረቃ ት/ቤት "Acceptance Letter እንዲሁም Official Transcript ለማስመጣት ከሬጂስትራር ቢሮ የAdmission Letter እና የትምህርት ማስረጃችሁን መያዝ የሚጠበቅባችሁ መሆኑን እናሳውቃለን!

ሬጅስትራርና አሉምናይ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

30 Oct, 07:52


ፕ/ር ብርሃኑ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ "ዛሬ እዚህ የተገኘሁት ምንም እንኳን በኢኮኖሚ ጫና ብሎም በተለያዩ አካባቢያዊና ወቅታዊ ችግሮች ብትፈተኑም በተቻለ መጠን በችሎታችሁና በእውቀታችሁ የምትተማመኑ ምሁራን: የእውቀት ጥማት ያላችሁ እና ቀጣይ ትውልድን በመቅረፅ ሀገርን የማሻገር አደራ የተጣለባችሁ እንደሆናችሁ ለማሳሰብና ልማፀናችሁ ነው!" ብለዋል::

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አስተዳደርና ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ክቡር ዶ/ር ሰለሞን አበርሃ በሰጡት ምላሽ እንደሀገር የትምህርት ሴክተሩ ሪፎርም በሰፊው እየተሰራበት መሆኑን ጠቁመው አሁን ያለው የሲቪል ሰርቪስ አሰራር ሁሉም ሴክተር ተመሳሳይ ቅርፅ እንዲኖራቸው ተደርጎ ስለሆነ ይሄንን የሚቀይርና ትምህርት-ተኮር የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት እንዳለበት በማሳወቅ መዋቅሩ ምን መምሰል እንዳለበት ለማመላከት በሰፊው እየተሰራበት እንደሆነ ገልፀዋል::

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው የተጀመረው የትምህርት ሪፎርም ቀጣይነት እንዲኖረው ሥርዓቱ የሚቀየረው ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ባሳተፈ መልኩ ባለው አጠቃላይ ኢኮ ሲስተም ይወሰናል እንጂ ትምህርት ሚኒስቴር ብቻውን የሚሰራው እንዳልሆነ ገልፀው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለይ ወደ ራስገዝነት በሚያደርጉት ሽግግር ከምርምር አንፃር: ከባለድርሻ ሴክተሮች ጋር ባላቸው ትስስርና ተመራጭነት: ከደንበኛ እርካታ አንፃር ምን ቅርፅ ሊኖራቸው ይገባል በሚለዉ ላይ በዝርዝር እየተሰራ በመሆኑ ሪፎርሙ ይቀጥላል ብለዋል::

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

በዚህ ይከታተሉን:-
*****
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et
Telegram: https://t.me/HUCommunicationsoffice

Hawassa University

30 Oct, 07:51


የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ጋር ተወያዩ::
**//**
ጥቅምት 20/2017 ዓ.ም
በክቡር ሚኒስትሩ የተመራው የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ቡድን ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላትና መምህራን ጋር ጥቅምት 19/2017 ዓ.ም በዋናው ግቢ አፍሪካ ህብረት አዳራሽ ውይይት አካሂዷል::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ እንግዶቹንና የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ እንኳን ደህና መጣችሁ ካሉ በኃላ ክቡር ሚኒስትሩ የውይይቱን ማስጀምሪያ ንግግር አድርገዋል::

ክቡር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ እንዳሉት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እውነትና ዕውቅት ብቻ የሚፈልቅባቸው እንዲሆኑና ምሁራን በጎታችና ኋላ ቀር አስተሳሰብ ሳይሸነፉ ነፃና ገለልተኛ በሆነ መልኩ የምርምር ስራዎቻቸውን እንድያካሄዱ በግልጽነት መስራት  ይጠበቅባቸዋል ። የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጨምሮ አሁናዊ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያላቸው: በእውቀት የተደገፈ ክርክርና ውሳኔ በሚፈልጉ ወሳኝ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምርምር መስራት: የውይይትና ክርክር መድረኮችን ማዘጋጀት: ፖሊሲ አውጭዎች ከግንዛቤ እንዲያስገቧቸው ምሁራዊ አቅጣጫ መስጠት: እንዲሁም ለአከባቢው ማህበረሰብ በየጊዜው የተሻለ ሃሳብ በማቅረብና በማወያየት ሕዝቡን ማንቃት የከ/ት/ተቋማት ዋነኛ አጀንዳ እንዲሆን ሁሉም ተግቶ እንዲሠራ ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።

የኑሮ ውድነትና የደመወዝ ጭማሪውን አለመጣጣም ጨምሮ የትምህርት ዘርፉን እየተፈታተኑ ነው በተባሉ የተለያዩ አስተዳደራዊና የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ከተሳታፊዎች ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቷል::

Hawassa University

29 Oct, 06:42


ለሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላትና አካዳሚክ ሰራተኞች በሙሉ
*
ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓም

ዛሬ ከቀኑ 10:00 ሰዓት ላይ ከኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎች የሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር የውይይት ፕሮግራም ስለሚኖር በዋናው ግቢ አፍሪካ ህብረት አዳራሽ እንድትገኙና በውይይቱ እንድትካፈሉ ጥሪ እናደርጋለን::

ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ

ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

28 Oct, 18:07


ያላቸው አስተዋጽኦ በተመለከተ ለ693 አርሶአደሮች እንዲሁም የቀበሌና ወረዳ ግብርና ባለሙያች ግንዛቤ የማስጨበጥ ስልጠና እየተሰጠ እንደሚገኝ ዶ/ር ቴዎድሮስ አክለዋል።

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

25 Oct, 11:41


በአፈጻጸም ውል ዝግጅት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ባለሙያዎች ዩኒቨርሲቲዎች የመነሻ መረጃ በማሰባሰብና የእርካታ ዳሰሳ ጥናት በማድረግ በሚያዘጋጁትና ውል በሚፈጽሙበት "Performance contracting agreement" ላይ መረጃ ለማሰባሰብና ወደስራ ለመግባት በሚያስችለው ዝግጅት ዙሪያ ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስራ ኃላፊዎች ጋር ጥቅምት 14/2017 ዓ.ም ውይይት አካሂደዋል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አካ/ጉ/ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር ፍሰሀ ጌታቸው በውይይቱ ወቅት ባነሱት ሀሳብ ት/ሚ/ር የከ/ት/ተቋማትን ለመገምገምና ያሰበበት የመግባቢያ ሰነድ ለማዘጋጀት ጥራት ያለውና ያልተዛባ መሰረታዊ መረጃን ለማግኘት ዋነኛው መሳሪያ መሆኑን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው ቀደም ብሎ መሰረታዊ የመነሻ መረጃ የሰበሰበ መሆኑን የጠቆሙት ም/ፕሬዚደንቱ ከአሁን በኋላ ከትምህርት ሚኒስቴር ባለሙያዎች ጋር በመሆን መረጃዎቹን የማጥራትና የማሟላት ስራ እንደሚከናወን በመጨረሻም ዩኒቨርሲቲውና ትምህርት ሚኒስቴር በጋራ በሚገቡት ስምምነት መሰረት ይፈራረማሉ ብለዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የቴክኖሎጂ ሽግግርና ተቋማት ትስስር ዴስክ ኃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ዳንኤል በበኩላቸው የብቃት መመዘኛ ኮንትራቱ በዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ አገልግሎት ላይ የተማሪዎች፣ የመምህራን፣ የአስተዳደር ሰራተኞችና የማህበረሰቡን እርካታ ዳሰሳ ጥናት በማካሄድ የሚዘጋጅ እንደመሆኑ ተሳታፊዎች እውነተኛ መረጃን በመስጠትና ቀና ትብብር በማድረግ ተግባራዊነቱን ሊያግዙ እንደሚገባ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት መረጃ ኃይል የሆነበት ጊዜ ላይ እንደምንገኝ የገለጹት አቶ ተሾመ የዩኒቨርሲቲዎችን አቅምና አፈጻጸም ለማሳደግ ብሎም በሚዘጋጁ ዓመታዊና ስትራቴጂክ እቅዶች ላይ በማካተት ለመጠቀም የሚያስችል ነባራዊ ሁኔታውን የሚገልጽ መረጃ መሰብሰብ እንደሚገባው አሳስበዋል።

Hawassa University

24 Oct, 19:05


ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር የትብብር ሰነድ ተፈራረመ::
**//**
ጥቅምት 14 ቀን 2017 ዓም
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ ሃይቆች ተፋሰስ ውስጥ በፍሎራይድ በተጎዱ አካባቢዎች የፍሎራይድ ቅነሳ ቴክኒኮችንና ቴክኖሎጂዎችን ዲዛይን፣ ሙከራና ማስፋፊያ ፕሮጀክት (FLUORIDE MITIGATION IN THE RIFT VALLEY [FMRV]: PROJECT DESIGN AND PILOTING) በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ በአዲስ አበባ ተፈራርሟል::

በስምምነቱ መሰረት የሁለቱ ተቋማት ትብብር በፍሎራይድ ቅነሳ ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና፣ ምርምርና ስርፀት፣ የአዋጭነት ጥናት፣ በቤተሰብ ደረጃ ጥቅም ላይ የሚውል የፍሎራይድ ቅነሳ ቴክኖሎጂዎች ዲዛይንና የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም በአጠቃላይ በስምጥ ሸለቆ ሃይቆች ተፋሰስ ውሃ ላይ የሚስተዋለውን ከፍተኛ የፍሎራይድ መጠን በመቀነስና በህብረተሰቡ ጤና ላይ አደጋ የማያስከትል ንፁህ ውሃ አቅርቦትን በማሻሻል የአካባቢውን ማህበረሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሕይወት ማሻሻል ላይ ያተኩራል ተብሏል:: የዳሰሳ ጥናቱም በሶስት የተመረጡ የፍሎራይድ ተጠቂ አካባቢዎች ላይ እንደሚሰራ ለማወቅ ተችሏል::

ስምምነቱን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ተፈራርመዋል::

                    ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
                    ሁሌም ለልህቀት!
           
በዚህ ይከታተሉን:-

Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Website: https://www.hu.edu.et

Hawassa University

24 Oct, 17:22


ከጉብኝቱ ተንስተውም ኮሌጁ በጣም ብዙ እድሎች ያሉት ትልቅ ተቋም መሆኑ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል:: በቀጣይም ወንዶገነት ኮሌጅ እንደስሙ ገነት የሚመስል መሆኑን በበቂ ሁኔታ ማስተዋወቅ፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ላይ ማትኮር፣ አለምዓቀፍና የሀገር ውስጥ አጋርነት ላይ የበለጠ መስራት፣ በተመረጡ የትኩረት ዘርፎች ላይ የልህቀት ማዕከል መሆን፣ በተማሪዎች ዘንድ ተመራጭ ለመሆን ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ መመሪያ ሰጥተዋል:: ግብርናና የተፈጥሮ ሀብት ጉዳይ የሀገራችንም የዩኒቨርሲቲያችንም ልዩ የትኩረት መስክ እንደመሆናቸው ፈተናዎችን ወደ ዕድል መቀየር ያስፈልጋልም ብለዋል::

የአካ/ጉ/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኢ/ር ፍስሃ ጌታቸው ራስገዝ ለመሆን በተያዘው ዕቅድ ልዩ ትኩረት የሚፈልጉ ጉዳዮች ዲጂታላይዜሽን: የፕሮግራሞች አክሪዲቴሽን: የመምህራን አጫጭር ስልጠናዎች: የፕሮግራም ትኩረት አቅጣጫ ላይ ጥራት ያለው ሥራ መስራት ናቸው ያሉ ሲሆን የምር/ቴ/ሽ/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ በበኩላቸው የኮሌጁ አቅም በሰውም ሆነ በተፈጥሮ ሀብት የካበተ እንደመሆኑ የራሱ የምርምር ጆርናል ላይ ሥራ እንደሚቀረው፣ ግን ደግሞ ራስገዝ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ለመሆን የሚደረገውን ጉዞ ለማገዝ ብዙ ተስፋ የሚጣልበት መሆኑን: የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችል ጠንካራ ከባቢ ለመፍጠር ግንባር ቀደም የልህቀት ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል:: ዶ/ር ታፈሰ ራስገዝነት የመጣው ዕድልም ፈተናም ይዞ ስለሆነ በምርምር የተደገፈና ጥራት ያለው ተወዳዳሪ አሰራር በመዘርጋት: ከግዜው ጋር የተናበበ የትምህርት መስክ ላይ አትኩሮ በመስራት ኮሌጁ ከሀገር አልፎ በአፍሪካ ደረጃ የሚጠራ የልህቀት ማዕከል በመሆን በርካታ ፈተናዎችን ወደ ዕድል መቀየር የሚያስችለው ከፍተኛ አቅም እንዳለው ያላቸውን እምነት ገልፀዋል::

የአስ/ል/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ጂሎ ዩኒቨርሲቲው ካሉት ኮሌጆች ባሉት አንጋፋና ወጣት ምሁራን በርካታ የትብብር ፕሮጀክቶችን በማምጣት ኮሌጁን ራሱን ለማስቻል የሚያደርጉት አስተዋፅኦ ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዉ አሁን ያለውን መሰረተልማት እያደሱ መጠቀምና በአይሲቲ መደገፍ የዩኒቨርሲቲው ትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልፀዋል::

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ሁሌም ለልህቀት!

Hawassa University

24 Oct, 17:22


የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች የወንዶገነት ደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅን ጎበኙ::
*
ጥቅምት 14 ቀን 2017 ዓም
በዩኒቨርሲቲው ተ/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ የተመራው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራር ቡድን ጥቅምት 13/2017 ዓ.ም በወንዶገነት የደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ጉብኝት አድርገዋል::

የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ተሻለ ወ/አማኑኤል ስለኮሌጁ አመሰራረትና ወቅታዊ ቁመና፣ ስለአዲሱ አመት የመማር ማስተማር ጅማሮ፣ ዕድልና ፈተናዎችና ልዩ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በጉብኝቱ የመማሪያ ክፍሎች፣ የተማሪዎች የምግብ ግብዓት ማከማቻና የመመገቢያ አዳራሽ፣ የተማሪዎች ማደሪያ ህንፃዎች፣ የአይ.ሲ.ቲና ዳታ ማዕከል፣ የደህንነት ጥበቃ ማዕከል፣ የአፈር ጥናት ቤተሙከራና ቤተ-መጽሐፍትን ጨምሮ ሌሎች የስራ ክፍሎች የታዩ ሲሆን አሁን ያሉበት የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና የአስተዳደሩን ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተለይተዋል::

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለና ምክትል ፕሬዝዳንቶቹ ከጉብኝት መልስ ከኮሌጁ አስተዳደርና መምህራን ጋር በሲዳ አዳራሽ ተወያይተዋል::

ዶ/ር ችሮታው አሁን ላይ እንደሀገር የመንግስት አቅጣጫ ዩኒቨርሲቲዎችን ማስፋፋትና ሙሉ ወጪያቸውን መሸፈን ሳይሆን በትኩረት የተለዩትን ወደ ራስገዝ የመለወጥ እንደሆነ ጠቅሰው ቀደም ሲል በማስፋፋት ስራው ወቅት የተሰሩ አብዛኛዎቹ ህንፃዎች በተለይ የፍሳሽ ማስወገጃ ሥርዓት ላይ የሚታየው መጠነሰፊ ችግር እንደሀገር እንደሚያሳስባቸው ትዝብታቸውን ገልፀዋል:: የህንፃዎቹ እድሳትም ከማስፋፊያ ወጪ በላይ የሆነ አቅም ይጠይቃልና ራሳችንን ለመቻል የምናደርገው ጉዞ ላይ ከፍተኛ ጫና ይፈጥራል ካሉ በኃላ ጥራት ላይ በማትኮር ያለንን አቅም ሁሉ ተጠቅሞ ተመራጭና ተወዳዳሪ መሆን ምርጫ እንዳልሆነ ገልፀዋል::

Hawassa University

23 Oct, 13:43


CALL FOR PITCH
*//**
October 23, 2024
Dereja (Africa Jobs Network) in partnership with the Mastercard Foundation and Hawassa University is running a pilot entrepreneurship support program dedicated to fostering innovation and entrepreneurship. We are committed to providing resources, mentorship, and support to early-stage startups.

We are thrilled to announce an opportunity for startups being incubated in university centers to showcase their innovative ideas and secure invaluable mentorship. We are committed to fostering the growth of early-stage ventures and providing them with the support they need to succeed.

Opportunity
**
Five selected startups will be given the opportunity to receive a comprehensive 2-3 month technical and business mentorship program. This program is designed to equip entrepreneurs with the skills and knowledge necessary to take their ventures to the next level.

Requirements
========
To be eligible for this opportunity, startups must:
• Be currently incubated in a university center
• Prepare a pitch presentation that is no longer than 30 minutes and 15 slides
• Clearly outline the current stage of their startup and the specific support they require to progress to the next stage

Pitch Presentation Guidelines
*
The pitch presentation should cover the following key areas:
• Startup Idea: Clearly articulate your unique value proposition and the problem your startup solves.
• Market Analysis: Demonstrate your understanding of the market landscape, target audience, and competitive environment.
• Team: Highlight the skills, experience, and passion of your team members.
• Progress and Challenges: Discuss your startup's current stage of development, key achievements, and the challenges you are facing.
• Mentorship Needs: Specify the areas where you seek mentorship, such as technical development, business strategy, or fundraising.

Selection Criteria
***
The selection of startups will be based on the following criteria:
• Innovation and Potential: The originality and potential impact of the startup idea.
• Market Opportunity: The size and growth potential of the target market.
• Team Strength: The quality and experience of the founding team.
• Pitch Quality: The clarity, persuasiveness, and professionalism of the pitch presentation.
• Mentorship Needs Alignment: The match between the startup's needs and the expertise of the mentors.

Pitching Event
Startups should prepare their pitch within the next 5 working dates (October 28) and send a confirmation email to this address ([email protected] and [email protected] ) to schedule their pitch and pitching event details will be notified through the incubation center team.

We look forward to receiving your pitches and supporting the next generation of successful entrepreneur Pitch.

        Hawassa University
               Ever to Excel!

Follow us @
**
Website: https://www.hu.edu.et
Facebook: https://www.facebook.com/Hawassa.University?mibextid=ZbWKwL
Telegram: https://t.me/HUCommunicationsoffice