💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️ @ethiomerejaa Channel on Telegram

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

@ethiomerejaa


24 Hour News

💚💛❤️ ዮቶራዊያን 💚💛❤️ (Amharic)

ህወሓት እና ምንጮች ፖስት የአማርኛ ዜና ለመጠቀም፣ ተጨማሪ በሚሠራው ቢሮ ጤና እና ተመሳሳይ ጉዳይ ያግኙ። በስልክ ወደ '💚💛❤️ ዮቶራዊያን 💚💛❤️' ተወሰነ። ይህ ፖስት ከ 'ethiomerejaa' እንደተገኘ ጉዳይ ነው፣ ለመለየት፣ ለመከታተል፣ በተጨማሪም ዜናን ለመምረጥ ሆነው የዜና ጉዳይን ተጠቅመው እንደሚረዳ ነው። በአገር እና በአዘጋጅ ልዩ በሆኑ አርእስቶች በየአመት ለመላኩ ስባት አጋለጠው ነው።

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

12 Feb, 18:02


https://youtu.be/JrgRJzN_g5U

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

10 Feb, 22:07


https://youtube.com/live/XdloaxknTrA?feature=share

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

10 Feb, 18:32


https://youtu.be/jWi0KIHgNts

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

10 Feb, 13:55


ጣና ግንባር፦ የዐርበኞች መስመር…

ኮማንዶ ሻለቃ ያለው አዱኛ|

ልዩ ቆይታ ከዘመቻ መምሪያ ኃላፊው ጋር|

በጎንደር ፋኖ አንድነት ጉዳይ
👇
https://youtu.be/4P7ids2TJt4?si=uiIFpN_NU1ndPVwh

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

09 Feb, 14:20


ውድ የጣና ቴቪ ቤተሰቦች

ዩቲዩብ ቻናላችን ተደጋጋሚ ጥቃት ያጋጠመው በመሆኑ አማራጭ ቻናል መክፈት አስፈልጓል።

በመሆኑም አዲሱን የጣቢያችን አማራጭ እንድትቀላቀሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን🙏

ጣና ሳተላይት ቴሊቪዥን ቻናል 2
Tana Satellite Tv Channel 2

በማለት ተቀላቀሉ።

Youtube👇

https://www.youtube.com/@TanaSatelliteTvChannel2

ጣና ሳተላይት ቴሌቪዥን
ከሀቅ ጋር  …!

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

07 Feb, 14:29


https://www.youtube.com/watch?v=5mTHdf_ged8

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

06 Feb, 21:40


https://youtube.com/live/l_lJ3JB6wuY?feature=share

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

03 Feb, 18:55


https://youtu.be/nfNWxZlQzQ0

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

03 Feb, 07:03


https://www.youtube.com/live/2uimzXn0_Sg?si=z5OsNaR2cTvm9guY

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

31 Jan, 18:07


https://youtu.be/oChe43HkzWk

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

30 Jan, 10:21


https://youtu.be/bCQBv6kEWPo?si=YBzoaLh1G0VoJHnx

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

29 Jan, 22:28


https://youtube.com/live/eBLc8B4oleM?feature=share

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

29 Jan, 15:39


https://youtu.be/aApVK3pHMLA?si=zGBXp-kV0I_fo1CX

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

24 Jan, 01:03


https://youtu.be/tYG4Sus71b0

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

21 Jan, 19:32


ጣና ዜና፦ ጥር 13/2017

በፋኖ ከለላ ከካንፕ ያመለጡ የሰራዊቱ አባላት

"ትግሉ መገምገም አለበት" ምሁራን

የባህርዳር-ጎንደር መንገድ ያዘጋ ከባድ ውጊያ

👇

https://youtu.be/91TeznZg2ZI?si=FfeMHKnHRw78XdFX

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

28 Dec, 18:26


https://youtu.be/xxg-BFjbG8E

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

25 Dec, 16:08


💚💛 "60 ወታደር እና 200 መሳሪያ ሲማረክ ከ150 በላይ ሙት ሆኗል'' የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ።

3 ክፍለጦር፣ 3 ጀንበር እልፍ ድል በጎንደር ምድር !

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ 3 ክፍለጦሮች 72 ሰዓታትን ከጠላት ጋር እያደረጉት ባለው እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ ከፍተኛ ድልና ጀብዱ አስመዝግበዋል።

እስካሁን ተጠናክሮ በቀጠለው  ይህ ትንቅንቅ የአገዛዙን 68ኛ ክፍለጦር በጥራሂናና ወገዳ ቀጣናዎች በመግጠም ከፍተኛ የመሳሪያና ወታደር ምርኮ ያገኙበትና ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የአገዛዙን ሀይል ሙትና ቁስለኛ አድርገው ድል ያስመዘገቡበት፤ አሁንም እየተፋለሙበት ያለ ሆኗል።

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ድብ ጠለምት ተከዜ ክፍለጦር፣ ጭና ክፍለጦርና ሰሜን አምባራስ ክፍለጦሮች እያደረጉት ባለው ትንቅንቅና ድል በተጎናፀፉበት ተጋድሎ ከ200 በላይ የነፍስ ወከፍ መሳሪያና ከ60 በላይ የአገዛዙ ወታደሮች እንደዚሁም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የብሬንና ስናይፐር ምርኮም በወገን ሀይል ተገኝቷል።

በትንቅንቁ እድል የቀናቸው የአገዛዙ ሀይሎች በቀላልና ከባድ ቁስለትም ውስጥ ሆነው ለሽሽት ሲበቁ ከ150 በላይ የሚሆኑት በውጊያው ተገድለዋል ሲል የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ዮሀንስ ንጉሱ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጧል።

ይህ የመረጃ ቅብብል ቃለምልልስ እየተደረገ ባለበት ጊዜም ውጊያው በከፍተኛ ሁነት ተጠናክሮ መቀጠሉን ፋኖ ዮሀንስ አንስቷል።

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

07 Dec, 19:55


...ገጥመናል ገጥመናል 💪

አሁንም ዘግተውታል    በሉ ገጥመን መስሎኝ በፍጥነት 1000 SUBSCRIBE  ትግላችን እስከቀራኒዮ ነው..‼️


     አዲስ ድምፅ Channel  179 የዛሬ  መግብያ ነው።
👇
https://youtube.com/channel/UCGuiq-K-30oo4jyWHUnv9TQ?si=RdpH82s-hHyJCwlN
አድርጋችሁ ስትመለሱ     Done ፈጣን ምላሽ
በየግሩፑ  ሼር አድርጉት በውስጥ ተላላኩ

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

07 Dec, 18:45


ክብር ለህዝባቸው ዋጋ ለማከፍሉ ጀግኖቻችን ....💪💪💪💪

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

07 Dec, 15:10


የጫካውንም የከተማውንም ፕሮጀክት እጅ ከአልሰጠ ስትገረፍ እጅህን ተሰጣለህ አፈር ከደሜ ትደባለቃለህ::
😁😁

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

07 Dec, 13:52


🔥#አማራው_ተራራው_ተገፍቶ_ማይወድቀው‼️

የአማራ ፋኖ በጎጃም መብረቁ ብርጌድ ከሕዝብና ከአሽከርካሪዎች በቀረበ ጥያቄ መሠረት   የመብረቁ ብርጌድ ፋኖዎች በሞጣ ቀጠና የተበላሹ መንገዶችን እየጠገኑ  ይገኛሉ።

28/3/2017 ዓ.ም

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

07 Dec, 13:52


ጠላት ገብቶ የማይወጣበት ጮቄ !!

🔥የጮቄ ቀጠና ሕዝብ ምሳር መጥረቢያ  ገጀራ  ያለውን መሳሪያ ሁሉ እየያዘ ከሕጻን እስከ አዋቂ  ከደጁ የመጣለትን ጠላት ለመደም*ስስ  በጋራ ወጥቷል።

የብልጽግና ሰራዊት  በሁለት አቅጣጫ በሰዴ_ከርነዋሪ  እና ከድጎጽዮን በኩል ወደ ጮቄ ዋብር ለመግባት ቢሞክርም አልማ ከተባለው ቦታ ሆኖ ሞርተር እየተኮሰ ንጹሐንን ከማሸ*በር ውጭ ሊሳካለት አልቻለም።

ጠላት ሙሉ በሙሉ መደም*ሰሻ ጊዜው አሁን ከምሽግ እንደወጣ ነው።

አይጥን ከጉድጓዷ እንደወጣች !!

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

07 Dec, 13:37


https://t.me/abathageramhara

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

15 Nov, 17:03


https://www.youtube.com/watch?v=K7ZUE2Jb5TI

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

14 Nov, 21:04


https://youtu.be/3-BfzjoUuJc?si=ztkKMa5BGNBdrv-8

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

14 Nov, 15:27


https://youtu.be/PKN4cPq43lc?si=LuZCLPx550nmYLNX

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

13 Nov, 18:54


https://www.youtube.com/watch?v=iPb-qCgZPBo

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

07 Nov, 14:22


ሰበር ዜና!

                                                                                                                                                                                                                                                       ሰሜን ምስራቅ እዝ ሁለተኛ ኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ጣዕመ በጀግኖቹ ተጋድሎ ተደመሰሰ::

የአማራ ፋኖ በወሎ በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ የቃሊሙ ታላቅ ድል በዛሬው እለትም ተደግሟል::

የበላጎው ባለታሪኮች ዞብል አምባ ክፍለጦርና አሳምነው ክፍለጦር ታጠቅ ክፍለጦርን ተጠባባቂ አድርገው በጋራ በፈፀሙት ታላቅ ተጋድሎ ከወልድያ ከተማ በቅርብ ርቀት የምትገኘው የራያ ቆቦዋ ቃሊም ከተማን ለመቆጣጠር የመጣው ጠላት በጀግኖቹ በርካታ ሙትና ቁስለኛ እንዲሁም ምርኮኛ ሆኗል::

ከበላጎ ተራራ ስር የምትገኘዉን ቃሊም ከተማ ለመቆጣጠር አስቦ የመጣው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ አዲስ ምልምል ሰራዊት በጀግኖቹ የዋርካው ምሬ ወዳጆ ልጆች አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ 48ኛ ክፍለጦር 5ኛ እና 2ኛ ሻለቆች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ተደምስሰዋል:: በአዲሱ አመት 2017 አ.ም መባቻ ቃሊም ከተማና አካባቢው ላይ 48ኛ ክፍለጦር 4ኛ ሻለቃ በብ/ጀ አሳምነው ፅጌ ክፍለጦር ሙሉ ለሙሉ መማረኳና መደምሰሷ የሚታወቅ ነው::

በጀኔራል አሰፋ ቸኮል የሚመራው ሰሜን ምስራቅ እዝ ሁለተኛ ኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ጣእመ በጀግኖቹ ተጋድሎ የተደመሰሰ ሲሆን ሁሉም አጃቢዎቹ እጅ ሰጥተው ይገኛሉ::

በተጋድሎው በርካታ የጠላት ሃይል ሙትና ቁስለኛ የሆነ ሲሆን ከምርኮ የተረፈዉም ፈርጥጦ ወልድያ ከተማ ገብቷል:: በርካታ ቁጥር ያለው ምርኮኛ በእጃችን ያለ ሲሆን በቀጣይ ይፋ የምናደርግም ይሆናል ሲሉ የዞብል አምባ ክፍለጦርና የአሳምነው ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነቶች ፋኖ ሃብተማርያም መንበሩ እና ፋኖ ንጉስ አበራ ገልፀዋል::

በምርኮ የተገኙ ድሎች

-ስናይፐርና ብሬን
-ለጊዜው ቁጥሩ በዉል ያልታወቀ ነፍስ ወከፍ ክላሽ
-ለጊዜው ቁጥሩ በዉል ያልታወቀ የብሬንና የክላሽ ተተኳሽና የዲሽቃ ተተኳሽ

የህልዉና ተጋድሎው እስከ ነፃነት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ አበበ ፈንታው  ገልጿል።

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

28 Oct, 17:46


"28 ሰዓት በፈጀው ውጊያ የአገዛዙ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሁኗል፤ ከፋኖ ጉዳት አልተመዘገበም።" አርበኛ ከፍያለው ደሴ

የአማራ ፋኖ በጎንደር የዘመቻ መምሪያ ኃላፊና የገብርዬ ክፍለጦር ዋና አዛዥ አርበኛ ከፍያለው ደሴ በደቡባዊ ጎንደር እየተደረጉ ባሉ ውጊያዎች ዙሪያ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ጥቅምት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጧት 12 ሰዓት የጀመረው ውጊያ እስከ ዛሬው ዕለት ረፋድ 4 ሰዓት የተደረገ ሲሆን በዚህ ውጊያ አገዛዙ ከባድ መሳሪያዎችን የተጠቀመ ሲሆን በከባድ መሳሪያም የመምህራን ቤትና የአርሶ አደሮችን ቤት አቃጥሏል፤ በአየር ኃይሉም ድብደባ ፈጽሟል፤ ሶስት ቦታዎች ላይም የድሮን ጥቃት በንጹሃን ላይ ፈጽሟል፣ የፋኖ ሰራዊት አንድም ጉዳት ሳይደርስበት በገብርዬ ክፍለጦር ብቻ 7 አምቡላንስ ሬሳ ጭኖ ወጥቷል፤ አሁንም ያልተነሳ ሬሳ አለ ሲል አርበኛ ከፍያለው ደሴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

አርበኛ ከፍያለው ደሴ አገዛዙ ጀነራል መሐመድ ተሰማ፣ ጀነራል አለምሸት ደግፌን የጦር መሪ አድርጎ በርካታ ጀነራሎችንና ኮሎኔሎችን አሰልፎ ቢመጣም አብዛኛው ሰራዊቱ በምርኮ አስቀርተነዋል፣ ለሁለቱ ያቀደውን እቅድ በ28 ሰዓት ውስጥ እቅዱን መና አድርገንበታል፤ ተጋድሏችን አሁንም ይቀጥላል ብሏል።

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

22 Oct, 12:40


Tana Tv - ጣና ቴቪ  

ጣና ሳተላይት ቴሌቪዥን ከሀቅ ጋር ስራውን ጀምሯል  !!


መሬት ላይ የፋኖዎቻችን እለታዊ ዜና የዐማራ ሕዝባዊ ትግል ስትራቴጂካዊ አመራር ማረጋገጥ ይችል ዘንድ በሚዲያው ግንባር የትግሉን ክፍተቶች በመገምገም  ዕውነት እና ዕውቀት ይዞ  ከተፍ ብሏል፡፡

           ቴሌግራም  ቻናላችን  በፍጥነት ይቀላቀሉ
በየግዜው የምንለቃቸውን የምስል እንዲሁም የፁሑፍ መረጃዎችን ይከታተሉ ፡፡

Telegram

👇

https://t.me/+B_GvW2ylisY3Zjhk

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

21 Oct, 17:58


🔥የጥቅምት ሰማዕት - ፋኖ አርበኛ ሞላ ደስዬ‼️

ጀንበሯ መጥለቅ እያማራት ነበር ወደ ምዕራብ አዘቅዝቃለች፤ የቦሩ ስላሴ ቅዝቃዜ አይሏል፥ ዝናብ እና ብርድ አድሮባቸው ከሀይቅ (ሂትቻ) ተነስተው ቦሩ ስላሴ የገቡት የምስራቅ አማራ ፋኖዎች ለ6 ሰአት ያህል ትንቅንቅ ላይ ናቸው፤ በዚህ ሂደት 3 የሚሆኑ ጓዶች ተሰውተዋል።

ዕለቱ ጥቅምት 11 ቀን 2014 ዓ/ም ምሽት ነው። ይህ ዕለት አርበኛ እና ምሁሩ ያ ለሰማይ ለምድር የከበደው በአማራነት ልቡ የመነነው ጀግናው ሰማዕት ፋኖ ሞላ ደስዬ የተሰዋበት ዕለት ነው።

በወቅቱ ጠላት ሙሉ ለሙሉ ተሁለደሬ ወረዳን ማለትም ሀይቅና ዙሪያውን መያዝ ስላልቻለ በምትኩ የአምባሰል ተራሮችን በመቆጣጠር በቦሩ ስላሴ አድርጎ ደሴን የመቆጣጠር ዕቅድ ነበረው፤  ያኔ ዝናብ እና ብርድ ለተከታታይ ቀናት ያለፈበት የምስራቅ አማራ ፋኖ ወደ ኋላ በማፈግፈግ ሂቲቻ እኩለ ሌሊት ላይ ደረሰ:: እዛው በማደር በጧት 12 ሰአት ስብሰባ ተብሎ ተጠራ:: ጠላት በቦሩ ስላሴ አድርጎ ደሴን ሊቆጣጠር ነው ተብሎ ተነገረ። በእግር ጉዞ ተጀመረ:: ትንሽ መንገድ እንደተጓዝን አንድ ካሶኒ እና አይሱዚ ከፓትሮል ጋር ተላከ::

በጢጣ ሚካኤል አልፈን በደሴ ዳንዲ ቦሩ ትምህርት ቤት አድርገን ወደ ቦሩ ስላሴ በሰልፍ ጉዞ ተጀመረ። ጠላት በዲሽቃ እና በስናይፐር ተኩስ ከፈተ:: ቦታ ቦታ ተያዘ:: ከወገን በኩል የዲሽቃውን በዲሽቃ የክላሹን በክላሽ ምላሽ ተሰጠ። ዲሽቃውን ሙሉጌታ ዲሽቃ ያስጎራው ጀመረ:: ብሬኖችን እነ ራምቦ፥ ጋሻው እና ሌሎች ጀግኖች አቅለበለቡት።

የጨበጣ ውጊያውን እነ በለጠ ሸጋው፥ ይታገሱ አራጋው እና አማን ባረኩት። ዳንኤል አለሙ ኢንፎርቲውን ጥሎ ስናይፐር ይዞ ጠላትን መጣል ጀመረ። ተኩሱ ተባባሰ፤ ምድር ቃጤ ሆነች::  50 አለቃ ሻምበል ጦሩን ጥሩ አድርጎ እያዋጋው ነው። ዋርካው ምሬ የጠላትን ሁኔታ እያዬ የጦር አሰላለፉን ይቀያይራል::

የደሴ ወጣት ምግብ እና ውሀ በማቅረብ ደጀን ሆኗል። 3 የሚሆኑ ጓዶች መስዋዕትነት ከፈሉ:: በዚህ መሀል 50 አለቃ ሻምበል ክፉኛ ቆሰለ::

ጠላት የከባድ መሳሪያ ጫና በጨበጣ ዉጊያ መሀዲሱቹ ላይ ለማሳረፍ እየሞከረ ነው ። 50 አለቃ ሻምበል ከወደቀበት አልተነሳም። ጠላት በቀላሉ ሊያስጠጋ አልቻለም ግን በለጠ ሸጋው እና አማን 50 አለቃ ሻምበልን ጥለን አንወጣም አብረነው እንሞታለን ብለው በተኩስ መአት መሀል አልፈው ደረሱለት።

አልተፍርም እዚሁ ጨርሳችሁኝ ውጡ ብሎ ለመናቸው፤ እነሱ ግን ፍጹም አናደርገውም ይልቁንስ ተፋልመን እናወጣሀለን አሉት ተሳካላቸውም።  ጫኔና አንድ ሳይጠረነፍ ከደሴ በራሱ ውሳኔ የመጣ ክብሮም የሚባል ወንድም እንደተሰው ተኩሱ ጋብ ብሎ የነበረ ሲሆን ትንሽ ቆይቶ ድጋሜ ተኩስ ፋኖ ከፈተ። ፋኖ መልሶ ማጥቃቱ ላይ በርትቶ ውጊያው ቀጠለ። የዲሽቃ ምድብተኛው በደንብ የጠላት ገዥ መሬት ላይ አነጣጥሮ መምታትን ተያይዞታል።

በጎጃም፥ በጎንደር እና በሸዋ ከ 2008 ዓ/ም ጀምሮ በፋኖ አደረጃጀት ውስጥ ትልቅ ሚና የነበረውና የዘመናችን ልዩ ክስተት ሆኖ ብዙዎችን ያስደመመው የዘመናዊው የፋኖ አደረጃጀት ፈር ቀዳጅ የሆነው የምስራቅ አማራ ፋኖ ምክትል አዛዥ የሆነው ፋኖ ሞላ ደስዬ  ጦርነቱ እየከበደ መምጣቱን ቢያስተውልም "እኛ ቆመን ደሴ በጠላት አትያዝም" ብሎ ሽርጡን ከጭንቅላቱ እንዳሰረ በግራ እጁ ባለ ሁለት እግር ክላሹን እንደጨበጠ ወደ ውጊያ ገባ። በግ እና ወሎ ካመረረ አይመለስም ነውና ያ ድምጽ አልባ ሚሳኤል የሀውጃኖ ወንድም ወንዱ ሞላ ደስዬ ጠላትን አነባበረው፤ ውጊያው ረገብ ሲል አሸነፍን ብለው ፋኖዎች ሲንጎባለሉ ያ አረንጓዴ ለባሹ የቦሩ ሜዳ መልከአምድር ጠላትን በሳር በቅጠል ደብቆ አስቀርቶ ነበርና ፋኖ ሞላ ደስዬ የጠላትን ቅሪት በማጽዳት ላይ ሳለ የተረገመች ጥይት እሱ ላይ አነጣጠረች::

ጨለማው ለአይን ነስቷል። ወዳጅ እና ጠላት መለየት አይቻልም ነበር። የአሸዋ ገበታው ተበላሽቷል። ፋኖ ሞላ ደስዬ የት እንደወደቀም አልታወቀም። ለካስ ሳር ውስጥ ከሁለት ወንድሞች ጋር  ሰማዕትነትን ተቀብሏል። ጠላት የቦሩ ስላሴን ዙሪያ አጥሮት ስለነበር ከከባድ ፍልሚያ በኃላ  አስከሬናቸው ተነስቶ ደሴ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን በክብር አረፈ።

በገዥው መንግስት ሴራና ተንኮል አንድ ቀን እንኳ የወር ደመወዙን  አሟልቶ ሳይቀበል ለአመነበት አላማ ለታመነለት ህዝብ መስዋዕትነትን ተቀበለ።
ሞት አይፈሬው ጀግና ለማንነቱ እና ለእርስቱ ግንባሩን ለጥይት ደረቱን ለሳንጃ ሰጥቶ  አስፈሪውን ምሽግ ተረማምዶት በክብር አረፈ::

ለማንነት እና ለታሪክ መስዋዕትነት የመክፈል የኩሩ ሰው ገድል ይህ ነው። ባርነትን የመጸየፍ እና የአልበገር ባይነት ተምሳሌት ይህ ነው። በጥቅሉ አማራነት እንዲህ ነው።

አርበኛ ፋኖ መምህር ሞላ ደስየ የተሰዋህለትን አላማ ከግብ ለማድረስ የመጨረሻው ትንቅንቅ ላይ ነን:: ቃልህን ጠብቀን በድል ዋዜማ ላይ እንገኛለን! ለድልም እንበቃለን::

ክብር ዉድ ህይወታቸዉን ገብረው ለዛሬ ላደረሱን ሰማእቶቻች

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

14 Oct, 18:31


ጎንደር አርማጭሆ በማር ዘንብ እና ሟታድጊ አካባቢ   የሚደረገው ዉጊያ ለ3ኛ ቀን የቀጥለ ሲሆን ዛሬ ተጨማሪ በማሰሮ ደንብ ሌላ የጦርነት ግባር ተከፍቶ  ጠላት እየተቀጠቀጠ ነው።                                                                                                         

አርማጭሆ ከሶረቃ እና ከሳንጃ ውጭ በሁሉም አካባቢ የሰልክ ግንኙነት ተቋርጦል። ድል ለፋኖ

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

09 Oct, 16:07


ሳስበው ሳስበው የጎንደር አማራ ጀርመን ሀገር እሚኖሩ አይመስለኝም እንጂማ ...............🤔

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

05 Oct, 08:31


"ልጄ የሞተው መጠጥ ቤት በሴት ተጣልቶ አይደለም"
ደቡብ ጎንደር ጋይንት አከባቢ ተወልዶ ያደገ አንድ ጀግና ከወሎ ወንድሞቹ ጋር በመሆን ከወራት በፊት በአምባሰል ተራሮች ላይ ባደረገው ትንቅንቅ  በክብር ይሰዋል።አስከሬኑም ግሸን ደብረ ከርቤ ቅጥር ግቢ ውስጥ ያርፋል።

የዚህ ጀግና እናት፡ "የልጄ አስከሬን ያረፈበትን ቦታ ልይ" ብላ ከጎንደር ተነስታ ወሎ አምባሰል ደረሰች። እለቱ የግሸን ንግስ በዓል የሚከበርበት እለት ነበር።

አብረዋት የነበሩ ሰዎች እና የበዓሉ ታዳሚዎች እንዲሁም የፋኖ አባላቱ ሃዘኗን ለመካፈል አጅበዋት ወደ መቃብሩ ቦታ አመሩ።

እናት እንዲህ ስትል ታለቅስ ነበር፦

"ልጄ የሞተው መጠጥ ቤት በተነሳ ግጭት አይደለም።"

ልጄ የሞተው በሴት ተጣልቶ ከሰው ጋር ሲደባደብ አይደለም።

ልጄ የሞተው ስለ አማራ ነጣነት ሲፋለም እንጂ።"

"ብቻውን አልወደቀም ልጄ
ባዶውን አልወደቀም ልጄ
ሺ ጥሎ ነው የወደቀው።"

"ልጄ እንደማጣህ ያወኩት አንተን የመሰለ ጀግና የወለድኩ ቀን ነው"

"ጓደኛየ ልጄ፣ ጀግናየ ልጄ፣ መኩሪያየ ልጄ፣ የመቃብርህ ግርማ መጎስ በቁም ካሉ ባንዳዎች ይበልጥ ያስፈራል"   እያለች ወገቧን በሟች ልጇ ወታደራዊ መልዮ ልብስ ጥብቅ አድርጋ አስራ አንዳንዴም ታለቅሳለች አንዳንዴም ትፎክራለች።

ንግስ በዓሉን ለማክበር ከመጡና የሟቹን እናት ሃዘን ለመካፈል ወደ መቃብሩ ስፍራ ካቀኑ ሰዎች መካከል ከጎጃም መርጦ ለማርያም አከባቢ የመጣች አንዲት እናት ደግሞ፦
"የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ
ልጅሽን አሞራ እንጂ አይቀብረውም ዘመድ" እያለች በማንጎራጎር የጀግናውን እናት ሃዘን ስትጋራ፡ የፋኖ አባላቱ ደግሞ "ዘራፍ አካኪ ዘራፍ!" እያሉ ለጀግናው ጓዳቸው መፈክር ያሰሙ ነበር።
#መረብ ሚዲያ



ሞቶም እንኳን ....ስኳድ ነው ወሎን ሊከፋፍል ሄዶ ካላሉት እነ ዘመድ ኩን ህዝባችን እንዲህ ዋጋ እየከፈለ ነው ለአማራነት .......! .....!

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

03 Oct, 16:15


ውጊያ ለመዘገብ ቀጠና እሚመረጥበት ጎጥ የገነነበት ጊዜ ላይ መድረሳችን የትግሉ አሳዛኙ ክፍል ነው ።

ድል ለአማራ ፋኖ
ጎጠኝነት ይውደም 💪

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

03 Oct, 14:32


ጎንደር መተማ ከፍተኛ ዉጊያ ሲደረግ የዋለ ሲሆን አሁን ሽንፋ ከተማላይ ድሮን በመጣል በርካታ ንፁሀኖችን ገሏል💔

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

03 Oct, 13:09


በር ዜና

የአገዛዙ ጦር በጣለው ሞርታር አራት የአንድ ቤተሰብ አባላት ላይ ጉዳት ደረሰ

ኤቢሲ ዜና ፥ መስከረም 23/2017፤

የአገዛዙ ጦር ዛሬ መስከረም 23 በጎጃም ውጊያዎች በጣለው ሞርታር የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑ አራት ንፁሐን ላይ የአካል ጉዳት አደረሰ።

ኮሶበር  ሆኖ ወደመኖሪያ መንደሮች በተጣለው ሞርተር  ሳትማ ዳንጊያ በተባለ ስፍራ በንፁሀን ቤት ላይ በማረፉ የአንድ ቤተሠብ አባላት አባላት የሆኑ አራት ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል።
ጉዳቱ የደረሰባቸው መሠንበት ተስፋው ፣ሙሉነህ ተስፋው ፣ ተስፋው ጌታሁን እና ቀኑ ፈቃዱ የተባሉ የአንድ ቤተሰብ አባላት ናቸው።
በአገዛዙ ሠራዊት በተፈፀመው ጥቃት አንድ ፈረስ እና 13 የቀንድ ከብቶች ተጎድተዋል።
የአገዛዙ ሠራዊት ከፋኖ የገጠመውን ደፈጣ መቋቋም ሲያቅተው የቡድን መሣሪያዎችን ወደ መኖሪያ መንደሮች እየተኮሰ መሆኑን ከስፍራው ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

የኤቢሲ ቴቪ

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

03 Oct, 13:00


የአየር ጥቃት !

አገዛዙ የአየር ጥቃት ፈፅሞ ከፍተኛ ከፍተኛ የንፁሀን ፍጅትና ቁሳዊ ውድመት አደረሰ። በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር በቋራ ወረዳ ሽንፋ ላይ ልዩ ቦታዉ ዘዉደ ባድማ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ረፋዱን የአየር ጥቃት ተፈፅሞ ንፁሀን ላይ በርካታ ውድመት መድረሱን ሰምተናል ።

ስለደረሰው ጉዳት አሁን ላይ በግልፅና በአሀዝ የተለየና የታወቀ ነገር ባይኖርም አገዛዙ በንፁሀንና በሀብትና ንብረት ላይ ያደረሰው ጉዳት ግን ቀላል አይደለም ተብሏል።

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

03 Oct, 08:36


መረጃ!

የፋኖ ኃይሎች ማንኩሳ ከተማ ገብተዋል። የዞን ከተማ የሆነችው ፍኖተ ሰላም ውስጥ ሁሉም እንቅስቃሴ ቆሟል (ትራንስፖርት እንቅስቃሴ የለም፣ ሱቆችና ሆቴሎች ዝግ ናቸው፣ የሰዎች እንቅስቃሴም ተገድቧል)።

ፍኖተ ሰላም ከተማ አቅራቢያ ወደ ገራይ መስመር ከባድ ውጊያ አለ።

ቀደም ሲል የፋኖ አደረጃጀቶች ጥሪ ማድረጋቸውን ተከትሎ በአማራ ክልሉ በርካታ አካባቢዎች መንገዶች ዝግ መሆናቸው ታውቋል።

Belay Manaye

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

02 Oct, 11:42


ሰበር ዜና ከጎንደር ሰማይ ስር ከጉና ተራራ አናት 15 ወታደር፣ አንድ ዲሽቃና 70 ክላሽ ምርኮ ሆኗል።

የአማራ ፋኖ በጎንደር ዛሬ መስከረም 22/2017 ዓ.ም ክምር ድንጋይ ላይ የብልጽግና ሠራዊትን ድባቅ መቶታል።

ሶስት ክፍለ ጦሮች ባደረጉት የቅንጅት ውጊያ አንድ ዲሽቃ፣ አንድ  መትረየስ፣ ስናይፐር፣ ብሬን እና ሰባ ክላሽንኮቭ መሣሪያን መማረካቸውን የጉና ክፍለጦር ዋና አዛዥ ሻምበል አምሳሉ ማዘንጊያ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ተናግሯል።
ሻምበል አምሳሉ አክሎም፤ 15 የብልጽግና ሠራዊት በምርኮ ገቢ መሆኑን ገልጿል። ታሪካዊው ጉና ተራራ በርካታ አውደ ውጊያዎች የሚካሄዱበት ተራራ ነው።

ይህ በእዲህ እንዳለ የአማራ ፋኖ በጎንደር ገብርዬ ክፍለ ጦር ከትናንት እስከ ዛሬ ከጠላት የብልጽግና ሠራዊትና፤ በአረጋ ከበደ ስምሪት ተሰጥቷቸው ለጭፍጨፋ የዐቢይን ጦር ከሚመሩት አድማ ብተናና ሚሊሻ ጋር ከፍተኛ ትንቅንቅ እያደረገ ነው።
የብልጽግና መንግስት፤ "ታች ጋይንት ያለውን የፋኖ መሪ ከፍያለው ደሴን መያዝ ወይም መደምሰስ አለብን" ብሎ በወታደራዊ ካውንስሉ ጭምር ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል።

በዚህ እቅዱ መሠረትም ያለ የሌለ ሀይሉን ይዞ ደቡብ ጎንደር የገባው የጠላት ብልጽግና ሠራዊት ከትናንት እስከዛሬ ድረስ፤ በራስ ጋይንት ምድር በፋኖ እየተለበለበ ነው ።

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

30 Sep, 08:53


ወሎ ...!

ከወሎ ዩኒቨርስቲ  አቶ ተመስገን ተሰማ ፣ ዶ/ር ብርሃኑ ፣ ዶ/ር አያሌው ታለማ ፣ አቶ ፀጋ ዘአብ ፣ የግዕዝ መምህርቷ ሰዋሰውን ጨምሮ በርካቶች ታስረዋል ።

በደሴ በዘመቻ እየታደኑ በመታሠር ላይ ካሉት የዩኒቨርስቲ መምህራን ፣ አመራሮችና ተማሪዎች ባሻገር የዮሐንስ ቤተክርስቲያን አብዛኞቹ አገልጋዮች ፣ የባንክ ማናጀሮችና ነዋሪዎችም ለእስር መዳረጋቸውን የመረጃ ምንጮች አመልክተዋ ።

መጨረሻው የደረሰ ስርአት ....!

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

30 Sep, 08:49


ምስራቅ ደንቢያ አይምባ ላይ አገዛዙ የድሮን ጥቃት እና የከባድ መሳሪያ ድብደባ በማድረግ በርካታ ንፁሃን ተገድለዋል።
ጥቃቱ ቤተክርስቲያን የተጠጉትን ሰዎችም አልማረም። አማራን ማጥፋት ዕቅዱ የሆነው ይሄን ስርዓት አቅም በፈቀደው ሁሉ መታገል የዚህ ትውልድ ግዴታ ነው።

ድል ለአማራ ፋኖ ....

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

29 Sep, 13:41


ንስሮቹ .....💪💪💪💪

💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

29 Sep, 11:50


ምእራብ ጎንደር !!!!!!!!

ጎንደር በዚህ ሰዓት በአይንባ በመተማ ኮኪት፣ በአማጭሆ በደቡባዊ ጎንደር ደግሞ በአፈርዋናት አካባቢ ከፍተኛ የሆነ ውጊያ እየተካሄደ ነው።

መናበብ እና መቀናጀት የግድ ይላል። የተጠና ደፈጣ የፋኖ የዘመኑ የውጊያ ብራድ መሆኑን ማስመስከር ነው።

ሁሉም የአማራ ወጣት መረጃ በመለዋወጥ ጠላት መንቀሳቀሻ እንዲያጣ ማድረግ አለብን ። ውጊያው በመሳሪያ  ብቻ አይደለም ...!


ድል ለአማራ ህዝብ #