Biruh @dailybiruh Channel on Telegram

Biruh

@dailybiruh


“የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው፥ ልብንም ደስ ያሰኛል፤ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፥ ዓይንንም ያበራል።”
— መዝሙር 19፥8
📬📬📬 ለማንኛውም አስተያየት ጥያቄ 📬📬📬
@Biruhfeedback_bot

Biruh (Amharic)

በቅና ተማሪዎች እና በመላእክት ላይ ቅጣት እና ስለ መንግሥት ችግር እስማማለው Biruh ተይዞ ከማበረታታቶች እና መንስኤት መሰመር ማህበረሰብም ከሞት የሞት የመንአኤል አገርና ድርጅት አመታት ያገኘን ስለሆነን። የሴቶችና ወንድምሽን በቅና እሳት አክሱምንና መስተዋድር ላይ አይገቡም። ብሏል እያለ አመታትም የሚገኙ ስፖርቶች ከተቋማቸውን ለመስክ ወደ በጣም ትክክለኛው ታከለ እና ስለ ተጽባበት መከላከያም በአፍሪካ ምእራፍ ለመስክ አቅምጣቸው። ስለህገወሩም ለሆስላም በህልው ምግብ አዊ።

Biruh

23 Dec, 11:14


ክርስቲያን፣በጌታ ቤት ያደጋችሁ አልፎ ተርፎም አገልጋዮች ከሆናችሁ በተለይ ደግሞ አድቬንቲስት ሆናችሁ እግዚአብሔር በሰጣችሁ መልክ ተማምናችሁ አሻንጉሊት ሳትመስሉ ልክ እንደነዚህ የሠርግ ፕሮግራማችሁን አድርጉ!

እናመሰግናለን!

Biruh

22 Dec, 13:03


https://youtu.be/qEmKDPAF-Xk?si=37QD8SlhfCev2n0P

Biruh

18 Dec, 15:28


https://youtu.be/omvwRlMeBLk?si=qFNHFC903GZTf66G

Biruh

13 Dec, 06:58


እንደፈለግነው አልታሸገም

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል:- “ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም
(ኤርምያስ 29:11)

ስዩም ከዩኒቨርሲቲ ለመመረቅ በዝግጅት ላይ ነው፤ ለብዙ ወራት አንድ እጅግ የሚያምር የስፖርት መወዳደርያ ሚመስል መኪና በመኪና መሸጫ ቦታ ቆሞ ተመልክቶት ሲመኘው ቆይቷል። አባቱም ያንን ለመግዛት አቅም እንዳለው ስለሚያውቅ ሁሉ ነገር ቀርቶበት ይህንን መኪና ብቻ እንደሚፈልግ ነግሮታል። የምርቃት ቀኑ እየተቃረበ ሲመጣ ይህ ወጣት አባቱ ያንን መኪና መግዛቱን የሚያሳዩ ምልክቶችን መፈለግ ጀመረ። በመጨረሻ የምርቃቱ ቀን ማለዳ አባቱ ወደ ጥናት ክፍሉ ጠራው። ምን ያህል እንደኮራበትና እንዳስደሰተው የእርሱ ልጅ በመሆኑም ደስተኛ እንደሆነ እና እጅግ እንደሚወደው ከነገረው በኋላ በሚያምር ማሸግያ የታሸገ አነስተኛ የካርቶን ሳጥን ሰጠው። በጉጉት፣ ነገር ግን በጥቂቱም ቢሆን እየከፋው ሲከፍተው፤ ... የሚያምር በቆዳ የተለበደና የልጁ ስም በወርቃማ የተጻፈበት መጽሐፍ ቅዱስ በውስጡ አገኘ። በጣም ተናደደ፤ እየተቆጣም አባቱ ላይ ጮኸበት:- “እጅግ ብዙ ገንዘብ እያለህ ይህንን መጽሐፍ ቅዱስ ነው ምትሰጠኝ?" ብሎ መጽሐፍ ቅዱሱን ትቶ በሩጫ ከቤት ወጥቶ ሄደ።

ብዙ አመታት አለፉ ይህ ወጣት የተዋጣለት የንግድ ሰው ሆነ፤ የሚያምር ቤት እና መኪና ግሩም ቤተሰብንም አፈራ። ነገር ግን አባቱ እጅግ ማርጀቱን በማሰብ እርሱን ሄዶ ማየት እንዳለበት ተሰማው። ከምርቃቱ ቀን በኋላ አባቱን አይቶት አያውቅም ነበር። ነገሮችን አስተካክሎ ከመጓዙ በፊት አባቱ እንዳረፈ እና ሙሉ ንብረቱን ለእርሱ ማውረሱን የሚገልጽ መልዕክት ደረሰው። በፍጥነት ወደቤቱ ገብቶ እቃውን ሰብስቦ ወደ አባቱ ቤት ለመሄድ ተነሳ። አባቱ ቤት ሲደርስ ልቡ በድንገት በሃዘንና በጸጸት ተሞላ፤ አርፍዷል በጣምም ዘግይቷል። የአባቱን አስፈላጊ ሚባሉ ዶክመንቶች ሁሉ መፈታተሽ ጀመረ፤ እስካሁን ድረስ አዲስነቱን ያለቀቀውን መጽሐፍ ቅዱስ ከአመታት በፊት እንደተወው አገኘው። በእንባ አይኖቹ እያነባ መጽሐፉን መግለጥ ጀመረ። ምንም እንኳን ጥሩ ትዝታም ባይሆን አባቱን ሊያስታውስ የሚችልበት ብቸኛው ማስታወሻ እርሱ ነበር። ማንበቡን ሲጀምር ከመጽሐፍ ቅዱሱ የኋላ ገፅ አንድ ቁልፍ ወደቀ፤ የመኪና ቁልፍ፤ በላዩ ላይ የተንጠለጠለው ማንጠልጠያ ያ ሲመኘው የነበረውን የስፖርት መኪና መሸጫ ቤት ስም ተጽፎበታል። በዚያው ማንጠልጠያ ላይ የምርቃቱ ቀን እና “ሙሉ በሙሉ ተከፍሏል" የሚል ጽሁፍ ነበረበት።

እኛስ፣ ምን ያህል ጊዜ ነው እኛ እንደምንፈልገው ያልታሸጉ ስጦታዎቻችንን አልፈናቸው የሄድነው? እግዚአብሔር እንዲህ ይላል:- “ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም” (ኤር 29:11)

👉 በማስተዋል አንብቡ በዚህ ታሪክ ውስጥ ማን ነው ተጎጂው? አባት ወይስ ስዩም?
👉 የስዩም ችኮላ ምን አስከተለው?
👉 ከዚህ ታሪክ ምን ተማርን?

የዕለት እንጀራ (ገጽ 166)
@MesayD

Biruh

11 Dec, 00:35


https://youtu.be/LQaj3LGVMuo?si=snznGNx4bZTYP-59

Biruh

09 Dec, 11:59


ጃኬቴን ልደርብልሽ !

“ወዳጅ በዘመኑ ሁሉ ይወድዳል”
(ምሳሌ 17:17)

እውነተኛ ፍቅር ጊዜና ሁኔታ አይለውጠውም። ዛሬ ወይም በአንድ ወቅት ነፍስ እስከማይቀርልን ድረስ የወደድናቸውን ሰዎች እጃችን ከገቡ በኋላ ፍቅራችን መቀዝቀዝ የለበትም። እውነተኛ ፍቅር ጊዜ አይለውጠውም፡፡

በእጮኝነት ዘመናቸው በጣም የሚዋደዱ ፍቅረኛሞች ነበሩ። ወንዱ ነፍሱ እስከትወጣ ይወዳታል። አብረው እየሄዱ ከበረዳት የኔ ፍቅር ጃኬቴን ልደርብልሽ ይልና ይደርብላታል፤ እንቅፋት ከመታትም እኔን ይድፋኝ እኔ ልደፋ' ይላል ። እንዲህ እንዲህ እያለ ተጋብተው አንድ አስር አመት ከቆዩ በኋላ ሁኔታዎች እየተለወጡ መጡ። ያ የድሮ እንስፍስፍነቱ ቀዘቀዘና ከእለታት አንድ ቀን ወዳጅ ዘመድ ለመጠየቅ አብረው ሲሄዱ በርዷት “በረደኝ ስትለው በጎርናና ድምፁ:- ደርበሽ አትመጭም ነበር? ይላታል። እንቅፋት ሲያደናቅፋትም:- “ እያየሽ አትሄጂም? ” ይላታል። አጃኢብ ነው ጎበዝ! ለምን ብትሉ “ የቀደመውን ፍቅር ትቷልና ”። ዳሩ ግን የምነቅፍብህ ነገር አለኝ የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃልና” ብለን ይህን ሰው እንገስፀዋለን።

ወዳጅ በዘመኑ ሁሉ ይወድዳልና '' ብሎ ይመክራል ጠቢቡ። እውነት ለመናገር በጣም የሚዋደዱ ወዳጆች አሁንም አሉ፣ ባይበዙም ቅሉ፤ በማይቀዘቅዝ ፍቅር የሚዋደዱ ጥንዶች አሉ፤ በንፁህ ፍቅር የሚዋደዱ አብሮ አደጎች ጓደኞች አሉ። ይሄም ይበል የሚያሰኝ እና ልንከተለው የሚገባ ግብር ነው፤ ምንም እንኳን አንዳንዶች “ ፍቅር ድሮ ቀረ ” ቢሉም።

አንድ ሰው ነበረ ይባላል፤ ስለ ትምህርት ሲነሳ “ውይ ትምህርት እኮ ድሮ ቀረ” ይላል። ስለ አገልግሎት ሲነሳ ውይ እሱማ ድሮ በእኛ ጊዜ ቀረ” ይላል። ብቻ ምን አለፋችሁ በሱ ቤት ሁሉ ነገር ድሮ የቀረ ነው። አንድ ቀን እንደ ልማዱ ከወጣቶች ጋር እያወራ ሳለ አንዱ ጎበዝ ለጓደኞቹ “የሚገርም ኮምፒዩተር ተገዛልኝ” አለ። ይሄኔ ያ ሰውዬ ቀበል አድርጎ “ውይ ኮምፒዩተር ድሮ ቀረ” አለ። ይገርማል ለመሆኑ ኮምፒዩተር ድሮ ነበር ግን? መልሱን ለእናንተ ትቻለሁ። አንድ ልብ ማለት ያለብን ነገር ዛሬም እንደ ድሮው መሆን እንደምንችል መዘንጋት የለብንም ። ለምሳሌ ድሮ የሰፈሩ ሰው በአንድ ላይ ቡና ይጠጣ ነበር ፤ አረም በደቦ ያርም ነበር ፤ ከብት ተራ በተራ ይጠብቅ ነበር። ይህ የፍቅሩ መገለጫ ሁነኛ ማሳያ ነው። ስለዚህም የድሮ ቀረ” መፈክርን ትተን ይልቁንስ “ ዘመኑን ዋጁት ” የሚለውን አስታውሰን ይሄን የጥላቻ ዘመን በፍቅር እንድንፈውሰው ያስፈልገናል። ልብ ማለት ያለብን፣ የፍቅር መገለጫ ሁሌ ደቦ ብቻ፣ ተራ ቡና መጠራራት ብቻ መገለጫው ላይሆን ይችላል። ነገር ግን ወረት ያልነካው ፍቅር ጊዜው የሚሻው ነው፤ ምክንያቱም ይህ ዘመን በዘረኝነት ጥላቻ የቆረፈደ የፍቅርን ሸማ ገፎ የጣለ ጉደኛ ዘመን ነው። ስለዚህ ዘመናችንን፤ እንደ ጓደኛ፣ እንደ ቤተሰብ፣ እንደ ፍቅር አጋር፣ እንደ ክርስቲያን፣ በእውነተኛ ፍቅር እንድንጨርሰው ፈጣሪ ይርዳን አሜን! ወዳጅ በዘመኑ ሁሉ ይወድዳል ። እጸልያለሁ፡፡ ይህንንም በማድረግ እለት እለት አንተን በማምለክ እንዳድግ እርዳኝ። አሜን!

የዕለት እንጀራ (ገጽ 290)
@MesayD

Biruh

09 Dec, 01:12


https://youtu.be/xww_k4E1YK4?si=X1KzyW2DRkKBb7kj

Biruh

04 Dec, 13:03


የጽጌረዳዋ ምሳሌ

ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም መቀደሳችሁ ነውና፤ ከዝሙት እንድትርቁ፥ እግዚአብሔርን እንደማያውቁ አሕዛብ በፍትወት ምኞት አይደለም እንጂ፥ ከእናንተ እያንዳንዱ የራሱን ዕቃ በቅድስናና በክብር ያገኝ ዘንድ እንዲያውቅ
(1ኛ ተሰሎንቄ 4:3-5)

አንድ ወጣት ከዕለታት አንድ ቀን የአጎቱን የአበባ እርሻ ለመጎብኘት ወደዚያ አመራ። የአበባ እርሻው በተለያዩ የሚያማምሩ ጽጌረዳ አበቦች ተሞልቷል። ከዛም እየዞረ መጎብኘት ጀመረ፤ ሁሉም በጣም ያምሩ ነበር። ከዛ መሀል ግን አንዲት ጽጌረዳ ቀልቡን ሳበችው፤ እጅግ በጣም ታምራለች። ነገር ግን አልፈነዳችም፤ ገና እንቡጥ ነበረች። ፈንድታ መዓዛዋን እስኪያሸት ጓጓ፤ ነገር ግን መታገስ ስላልቻለ ጉብኝቱን ቀጠለ። ሌሎች የማረኩትን ጽጌረዳዎች እየዞረ ማሸተት ጀመረ። እጅግ ብዙ ጽጌረዳዎችን ጎንበስ ብሎ መዓዛቸውን አሸተተ። እንዳንዶቹንም እንዲያውም በቸልታ እየቀጠፈ ይጥል ነበር። በዚህ መሀል ዞር ሲል ቅድም ያያት እንቡጥ ጽጌረዳ ፈንድታለች። በደስታ እየሮጠ ሄደና ለማሽተት ሞከረ፤ ነገር ግን ምንም ልዩ መዓዛዋን ማሽተት አልቻለም፤ ምክንያቱም ቀድሞ ሌሎች ብዙ ጽጌረዳዎችን በማሽተት የማሽተት ስሜቱን ገድሎት ነበር፤ ወይም ሽታውን ተላምዶት ነበረ። በመሆኑም ምንም ማድረግ ስላልቻለ አዘነ።

ይህን ምሳሌ ወደ እኛ ሕይወት ስናመጣው እግዚአብሔር ባዘዘው የጋብቻ ሕይወት የተከለለ የግብረ ስጋ ግንኙነት ታግሶ ከመጠበቅ ይልቅ ከጋብቻ በፊት ብዙዎች ልክ እንደ ባለጽጌረዳው ወጣት የእነርሱ ያልሆኑትን ያልተፈቀደውን ግንኙነት በማድረግ እግዚአብሔር በጋብቻ የከለለውን ልዩ መዓዛ የመደሰት እድላቸውን ያባክናሉ። ስለዚህ ሰሪው እግዚአብሔር የሆነውን ተግባር 100% መደሰት ከፈለግክ/ሽ እርሱ እንዳዘዘው የራሳችሁን ጽጌረዳ የሆነ ወንድ ወይም ሴት በጋብቻ ብቻ እስክታገኙ መታገስ ጥቅሙ ለራስ ነው። አስቀድመን በምሳሌ እንዳነሳነው ወጣት አይነት ሕይወት ውስጥ ያላችሁም ጊዜው አልረፈደምና አቁማችሁ ወደ ጌታ መንገድ መመለስ ያዋጣል።

ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም መቀደሳችሁ ነውና፤ ከዝሙት እንድትርቁ፥ እግዚአብሔርን እንደማያውቁ አሕዛብ በፍትወት ምኞት አይደለም እንጂ፥ ከእናንተ እያንዳንዱ የራሱን ዕቃ በቅድስናና በክብር ያገኝ ዘንድ እንዲያውቅ፤” (1ኛ. ተሰ. 4:3-5 )

የዕለት እንጀራ (ገጽ 251)
@MesayD

👉 በተለይ ትዳር ሕይወት ውስጥ ያልገባን ወይም ለመግባት እየተዘጋጀን ያለን ወጣቶች ልብ ልንል የሚገባን ነገር ነውና በደንብ እናስብበት!!! (በትዳር ሕይወት ውስጥ ያላችሁም ብትሆኑ አስቡበት)

Biruh

28 Nov, 14:11


https://youtu.be/pPY9yl1tBqM?si=PECsgmYdDc-WRqli

Biruh

27 Nov, 14:00


እንዳያመልጣችሁ!
ማህበራዊ ሚዲያን ለቀልድ ሳይሆን ለወንጌል

Biruh

26 Nov, 13:35


አስገራሚ ጥያቄ

"...የእምነታችንን ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን..."
(ዕብራውያን 12:1)

አንዲት ጠና ያለች ሴት የቤተክርስቲያኑ ፓስተር ጋር በመሄድ “ከዛሬ ጀምሮ ለአምልኮ ወደ ቸርች አልመጣም አለችው። ፓስተሩም ደንገጥ ብሎ “ለም?" ብሎ ጠየቃት። እርሷም እንዲ አለች “ለአምልኮ የሚመጡት ሰዎች በስብከት ሰዓት ስልካቸው ላይ አፍጠው ፌስቡክና ሌሎች ሶሻል ሚድያዎችን ያያሉ፣ አንዳንዶቹ አፍ ለአፍ ገጥመው ያንሾካሽካሉ፣ ሰውን ያማሉ፣ ሌሎቹ በሃሳብ ሄደዋል። ሁሉም አሰመሳዮች ናቸው፤ ስለዚህ ሁለተኛ አልመጣም አለች። ፓስተሩ ዝም እለ። ከዚያ ትንሽ ቆይቶ "ውሳኔ ላይ ከመድረስሽ በፊት ላንቺ የሚሆን አንድ ጥያቄ አለኝ አላት ። አርሷም " ጠይቀኝ " አለችው። “አንድ ብርጭቆ ሙሉ ውሃ ይዘሸ ምንም ጠብ ሳይል በጉባኤው መሐል አቋርጥሽ መምጣት ትችያለሽ? እርሷም "በሚገባ እችላለው!" አለች ከዚያም በቀጣዩ የጉባኤ ቀን እንዳለችው አደረገች።

ፓስተሩም ጥያቄ አቀረበላት ዛሬ ጉባኤ ውሰጥ ስልክ የሚመለከት ወይም የሚያንሾካሽክ ሰው አይተሻል ወይ? አላት ሴትየዋም “አረ በፍፁም አላየሁም የብርጭቆው ውሃ እንዳይፈስ ሃሳቤን በሙሉ እዛ ላይ አድርጌ ነበር" አለች ፓስተሩም እንዲህ አለ:- "አየሸ መሉ ትኩረትሽ ብርጭቆው ላይ ሰለነበር ማንንም አላየሸም። ወደ ቤተከርስቲያን ስትመጪ ማድረግ ያለብሽ ነገር ይህ ነው፤ ሙሉ ትኩረትሽ እግዚአብሔር ላይ መሆን አለበት፥ ያለበለዝያ ትወድቂያለሽ። አይኖችሽን ከሰዎች ላይ አንስተሽ ክርስቶስ ላይ አድርጊ። ኢየሱስ እኔን ተከተሉኝ አለ እንጂ ክርስቲያኖችን ተከተሉ አላለም። አእምሮአችን ክርስቶስ የተናገረውን፣ ያደረገውን፣ ያሰበውን ምን አንደነበር እንዲያሰላስል እናድርግ፤ ከሰው ላይ ዓይናችን ይነሳ" አላት።

እኛም አይናችንን በሰዎች ላይ ከማድረግ ይልቅ በኢየሱስ ላይ አድርገን ጉዟችንን እስከመጨረሻው መቀጠል እንድንችል እግዚአብሔር ይርዳን።


የዕለት እንጀራ (ገጽ 159)
@MesayD

Biruh

21 Nov, 08:33


https://youtu.be/eg9oDFiUZ2M?si=qSReni5ufbNyYNG6

አድሜ ተባረክ አሁንም ጸጋው ይብዛልህ 🙏

እንዲህ አይነት ፀጋ ያላቸውን አገልጋዮቻችንን በሚያስፈልጋቸው ነገር ሁሉ ማበረታታት አለብን ይህ ዘማሪ በአንድ Single Track ብቻ መቅረት የለበትም 20 ሰዎች 5ሺህ ብር እያንዳንዳችን ቢናዋጣ 100,000 ብር ሆኖ ኮራ ብሎ አንድ ሙሉ አልበም እንዲያወጣ ያደርጋል ስለዚህ ይህንን ሥራ እንስራ እኔም አንዱ ነኝ ብቻ በጹሑፍ ማበረታታት አይደለም በሀሳቡ የምትስማሙ በውስጥ መስማር አናግሩኝ🙏 ይህም ከወንጌል ሥራዎች አንዱ ነውና!

Biruh

20 Nov, 19:18


👋ሰላም ውድ የ አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ወጣቶች

👉በአድቬንቲስት የመጀመሪያው የወጣቶች የውይይት እና የትምህርት መድረክ በ ኤ ዋይ የደቀመዝሙርነት ትምህርት ቤት!!!


🌼ከህዳር 12 ጀምሮ በ https://t.me/AYBCLUB ቴሌግራም ግሩፕ በቀጥታ ስርጭት በ ተመረጡ ርዕሶች የትምህርት እና የጥያቄ እና የውይይት ፕሮግራም ይኖረናል።

👉ግሩፑን በመቀላቀል በብዙ ይጠቀሙ።

📚ህዳር 12 እና 16 በመጽሐፍ ቅዱስ እና በትንቢት መንፈስ ዙርያ ጥልቅ ጥናት እና ውይይት ይኖረናል።

📅ህዳር 12
🕐ከምሽቱ 3:00-4:00
በቀጥታ ስርጭት( Live stream)

🔖  ያላችሁን መንፈሳዊ ጥያቄዎች ሁሉ ጻፉልን!! 👉@Kidist_Desalegn

👉ቀጠሯችሁ ከእኛ ጋር ይሁን

https://t.me/AYBCLUB

ተባረኩ!!!
ለአድቬንቲስት ወጣቶች ብቻ!!

Biruh

20 Nov, 15:13


ጭንቀታችን ለምን ይሁን?

ለየትኛው ዓለም ነው ሁልጊዜ የምንጨነቀው? መጽሐፍ ቅዱስ ("ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ ደግሜ እላለሁ ደስ ይበላችሁ"። ፊል 4:4) እያለን የኛ ጭንቀት ለምንድነው? ተጨንቀን በቁመታችን ላይ ስንዝር እንጨምር ይሁንን? ቃሉ እንደምለው... (ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው? ማቴ. 6:27 እና ሉቃ. 12:25) እናም ጌታ አምላካችን የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእኔ ላይ ጣሉ እያለን የእኛ የጭንቀትን መዓት ተሸክመን የምንገዳገደው ለምን ይሁን? (እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት። 1ጴጥ. 5:7) እንዲሁም (ትካዜህን በእግዚአብሔር ላይ ጣል እርሱ ይደግፍሃል ለጻድቁም ለዘላለም ሁከትን አይሰጠውም። መዝ. 55:22)

ሌላው ደግሞ በምድር ላይ ምን ያክል እንደምንኖር እኛ አናውቅም ግን በእግዚአብሔር የተወሰነ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው ("የዘመኖቻችንም ዕድሜ ሰባ ዓመት ቢበረታም ሰማንያ ዓመት ነው ቢበዛ ግን ድካምና መከራ ነው"... መዝ. 90:10) ።

ስለዚህ ለየትኛው ዓለም ነው ጭንቀታችን????

መልዕክቴ እግዚአብሔር በሰጠን በዚህች በጥቂት ጊዜ ደስተኞች ሆነን እንኑር! ከዚያም መልካም መልካሙን እንስራ! የጌታን ዱካ እንከተል! የሚያስፈልገንን ሁሉ እርሱ ያውቃልና በእርሱ እንታመን!

እርሱን አስከብረን ማለፍ እንድንችል ጌታ አምላክ በጸጋው ይርዳን!

ወንድማችሁ @MesayD

Biruh

17 Nov, 12:04


በአባታችን መተማመን

አምላኬ መልአኩን ልኮ የአንበሶችን አፍ ዘጋ እነርሱም አልጎዱኝም"
(ዳንኤል 6፡22)

በጣም ከሚደንቁኝ የሃይማኖት አባቶች ታሪክ አንዱ የዳንኤል ወደ አንበሳ አስኪጣል ድረስ የነበረው እምነት ነው። ዳንኤል በባቢሎን ከዚያም በሜዶንና ፋርስ መግንስት ጊዜ ትልቅ ስልጣ ነበረው። ስልጣን ቢኖረውም በእግዚአብሐር ላይ ሙሉ በሙሉ በመታመን እስከሞት ድረስ ታማኝ ሆነ። እንዲህ አይነት የእምነት ታሪኮች ሊያበታቱንና እኛም በምናልፈው ችግርና መከራ ሁሉ ድል እንድናገኝ፣ በእግዚአብሔርም ላይ ሙሉ በሙሉ የምንታመን እንድንህን ያደፋፍሩናል። ያኔ ከነ ዳንኤል ጋር የነበረው አምላክ አሁንም ከእኛ ጋር ነው። እግዚአብሔር ሳያውቅ በሕይወታችን የሚሆን ነገር እንደሌለ እርግጠኞች ልንሆን ይገባናል። ዳንኤልን በሰማይ አባቱ ሙሉ በሙሉ እንዲታመን ያደረገው አምላኩን በሚገባ ለለሚያውቀው ነበር። ዳንኤል በቀን ሶስት ጊዜ በመንበርከክ ራሱን ዝቅ በማድረግ ከልብ የሆነውን ጸሎቱን ወደ ሰማይ አባቱ ያቀርብ ነበር። ዳንኤል የሰማይ አባቱን ሳያነጋግር ቀኑን አይጀምርም ነበር።

አንድ ፓስተር ወደ እሩቅ አገር በአይሮፕላን ሲጓዝ ሳለ ፓይለቱ አስደንጋጭ የሆን መልዕክት አስተላለፈ። በዚያን ጊዜ በአውሮፕላን ውስጥ የነበሩት በሙሉ በድንጋጤ ሲርበደበዱ፤ እንድ ትንሽ ልጅ ግን በተረጋጋ መንፈስ ተኝታ ነበር። ይህ ፓስተር በጣም በመገረም ወደዚህች ልጅ ጠጋ ብሎ እየሆነ ያለውን ነገር ሲነግራት የመለሰችለት መልስ በጣም የሚያስደንቅ ነበር:- ፓይለቱ አባቴ ነው ፤ ዛሬ እቤታችን እንደሚወስደኝ ነግሮኛል ብላ ለዚህ ፓስተር መለሰችለት ፤ ከዚያም ወደ መኝታዋ ተመለሰች። እኛስ ዛሬ ምድርን በቃሉ የፈጠረና ለእኛ እስትንፋስን ካለማቋረጥ ለሚሰጠን ለታላቁ እግዚአብሔር ያለን አምነት እንዴት ነው? በነገሮች ሁሉ ልባችን በተስፋው ቃል ላይ ያርፋል? ልክ እንደትንሽዋ ልጅ አይሮፕላኑ በችግር ላይ ቢሆንም ፓይለቱ አባትዋ ስለነበረ ተረጋግታ እንደነበረ እኛም ሁሉን ቻይ በሆነው አምላካችን ላይ ተስፋችንን እንድናደርግና በአርሱ ብቻ እንድንታመን እንደ ዳንኤል በጸሎት መትጋት አለብን።

እግዚአብሔር የቃሉን እውነታነትና የተስፋውን እርግጠኝነት ራሳችን ሞክረን እንድንለማመደው አንዲህ በማለት ያድመናል:- “ እግዚአብሔር ቸር አንደሆነ ቅመሱ እዩም (መዝ. 34:8)። " ጠይቁ ይሰጣችኋል " በማለትም ያደፋፍረናል (ዮሐንስ 16:24)። የተስፋው ቃሎች ይፈጸማሉ። ሳይፈጸሙ የቀሩበት ጊዜ የለም፣ ለወደፊትም አይኖርም። ወደ ኢየሱስ ስንቀርብና በፍቅሩ ሙላት ስንደሰት ጥርጣሬያችንና ጨለማችን ሁሉ በመገኘቱ ብርሃን ይገፈፋሉ። (ወደ ከርስቶስ የሚያደርስ መንገድ ገጽ 108)

ልክ ህጻን ልጅ በአባቱ እንደሚተማመን፣ እኛም በሰማይ አባታችን በሁሉ ነገር ልንተማመንበት ይገባናል



የዕለት እንጀራ (ገጽ 186)
@MesayD

Biruh

15 Nov, 08:14


https://www.youtube.com/live/JECG0ExsL9A?si=g8OM9_0KOim-xSNw

Biruh

14 Nov, 14:06


https://youtu.be/2IpgWhAFqjU?si=arMjImFvU6mz7OzT

Biruh

13 Nov, 19:56


እግዚአብሔር እውነቱን ከሰዎች ደብቆ አያውቅም ። ሰዎች ግን በራሳቸው ድርጊት ቃሉ ግልጽ እንዳይሆንላቸው ያደርጋሉ። ክርስቶስ መሲሕ ስለመሆኑ ለአይሁድ በቂ ማስረጃ ተሰጥቷቸው ነበር፤ ሆኖም ትምህርቱ ወሳኝ የሕይወት ለውጥ የሚጠይቅ ነበር። በመሆኑም ክርስቶስን ከተቀበሉ ለዘመናት ሲደሰቱበት የነበረውን ወግ፣ ሥርዓት ራስ ወዳድና አምላካዊ ያልሆኑ ልምምዶችን በሙሉ መተው እንዳለባቸው ተረዱ። የማይለወጠውን ዘላለማዊ እውነት ለመቀበል መስዋዕትነት ይጠይቃል። በመሆኑም በክርስቶስ እምነት ለመመሥረት እግዚአብሔር በማያዳግም መልኩ የሰጠውን ማስረጃ ለመቀበል አልወደዱም። በብሉይ ኪዳን የተጻፈውን እንደሚያምኑ ሲናገሩ የነበረ ቢሆንም በዚያ ውስጥ ግን ስለ ክርስቶስ ሕይወትና ባህሪይ የተነገረውን ምስክርነት ተቃወሙ። ከተለወጡ አስቀድመው ያከማቹትን አመለካከትና ሃሰብ ለመተው ስለሚገደዱ ለመለወጥ ፈሩ። መንገድ፣ እውነትና ሕይወት የሆነውን የወንጌል ሃብት ከእነርሱ ጋር የነበረ ቢሆንም ከሰማይ ሊሰጥ የሚችለውን ታላቁን ስጦታ እምቢ አሉ” (ኤለን ጂ ዋይት፣ የክርስቶስ ምሳሌያዊ ትምህርቶች፣ ገጽ 55)።

Biruh

12 Nov, 20:25


ሀይማኖቱን ብሎ በ 22 አመቱ ጫማውን የሰቀለው ተጨዋች

ስዊዘርላንዳዊው እግርኳስ ተጨዋች ሲልቫን ዋልነር ሃይማኖቴ ቅዳሜ እንድጫወት አይፈቅድም በሚል ገና በ22 አመቱ ጫማውን መስቀሉን አስታውቋል::

ተጨዋቹ የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን እምነት ተከታይ መሆኑን የገለፀ ሲሆን በሚከተለው እምነት ቅዳሜ ሰዎች ምንም ስራ እንዲሰሩ አይፈቀድም ብሏል::

''እኔ የእየሱስ ክርስቶስ ተከታይ ነኝ ሀይማኖታዊ የበዓል ቀናት ለእኔ ከምንም በላይ ነው ስለዚህ ቅዳሜ አልጫወትም እግርኳስ ለማቆም ወስኛለሁ '' ብሏል ተጨዋቹ::

ሲልቫን ዋልነር የስዊዘርላንድ ከ 21 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን ተጨዋችም ነበር::

Biruh

10 Nov, 12:43


https://www.youtube.com/live/zv2847kJvnc?si=oVpl65LmMfqsz_ce

Biruh

10 Nov, 09:22


ከፀሐይ በታች

“... ከፀሐይ በታች የተሠራውን ሥራ ሁሉ አየሁ፤ እነሆም፥ ሁሉ ከንቱ ነው፥ ነፋስንም እንደ መከተል ነው”
(መክብብ 1:14)

ጠቢቡ ሰለሞን “ስኬት ናቸው” ተብለው የሚታሰቡትን ብዙ ነገሮች በመክብብ ምዕራፍ 2 ውስጥ ከዘረዘረ በኋላ ሁሉንም አንድ ላይ ሰብስቦ “ ከንቱ ናቸው ” በማለት ይደመድማል። ምንድነው ከንቱ ያደረጋቸው? የሚለውን ሲገልጽ “ ከፀሐይ በታች " መሆናቸው ነው ይለናል። ይህንንም በመክብብ መጽሐፍ ብቻ 29 ጊዜ ጠቅሶታል። እውነትም ከፀሐይ ማዶ ያለውን ነገር ታሳቢ ያላደረገ ማንኛውም ነገር ከንቱ ነው። ከሰማያዊ ነገር የተለየ ሁሉ ከንቱ ነው። ከዘለዓለማዊነት የተለየ ጉዳይ ከንቱ ነው። ከእግዚአብሔር የተለየ ነገር ሁሉ ከንቱ ነው።

ብዙ ፈላስፋዎች እና ሳይንቲስቶች “ እግዚአብሔርን ገድለናል” በማለት ተናግረዋል፤ በመጽሐፍም ጽፈውታል። ይህንን መስማትም ሆነ ማንበብ በእጅጉ ያስደነግጣል። እነዚህ ሰዎች የተሳካላቸው እና ደስተኞች ይመስላሉ። ነገር ግን ሕይወታቸው ትርጉም የለውም። ምክንያቱም ከፀሐይ በታች ናቸው። በእርግጥ እግዚአብሔር ሟች ባይሆንም፣ እነርሱ ግን ከጥበባቸው ውስጥ ገድለውታል፤ ከስኬታቸው ውስጥ ገድለውታል፤ ከሕይወታቸው ውስጥም እንዲሁ።

ውድ አንባቢ ፡- ነገሮችህ “ ከፀሐይ በታች " ከሆኑብህ የእግዚአብሔር ነገር ከውስጥህ እየሞተ ይሄዳል። ከፀሐይ ማዶ ያለው ከውስጥህ እየሞተ ይሄዳል። ያ ደግሞ ከንቱ ነው፤ የከንቱ ከንቱ። “ ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ፣ ነፍሱንም ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል? ” ይለናል በማርቆስ 8፡36 ላይ። አብዛኛውን ጊዜያችንን እና ጉልበታችንን የምናባክነው ከንቱ በሆነው የዚህ ምድር ኑሮ ላይ ነው። ዛሬ ግን ቆም ብለን ልናስብ ይገባል። የምናደርጋቸው ማናቸውም ነገሮች ከፀሐይ ማዶ ያለውን ታሳቢ ያደረገ መሆን አለበት።

ከከንቱ ነገር ተላቀን የዘለዓለም ሕይወትን ያማከለ ኑሮ መኖር እንድንችል ፈጣሪ ራሱ ይርዳን

የዕለት እንጀራ (ገጽ 239)

@MesayD

Biruh

08 Nov, 13:28


https://www.youtube.com/live/coUeZvKhkRA?si=bDY2_2zHiwxdMj69

Biruh

08 Nov, 08:56


https://www.youtube.com/live/_c4dGo01o00?si=2oLUA_IIncCEj9l1

Biruh

07 Nov, 12:05


https://www.youtube.com/live/lt6Fx2Zsl5E?si=mQqID2maR7Z-jIuP

Biruh

07 Nov, 07:10


የምላስ ጉልበት

አቤቱ፥ ለአፌ ጠባቂ አኑር፥ የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ ''
(መዝሙር 141:3)

በዚህ ምድር ሰውን ከሚያሰናክሉ በርካታ ነገሮች አንዱ ምላስ ነው ። ጌታ ኢየሱስ ሰዎች ስለሚናገሩት ስለ ከንቱ ነገር ሁሉ በፍርድ ቀን መልስ ይሰጡበታል ብሎአል (ማቴ. 12:36–37)። ጠቢቡ ሰለሞንም ስለ ምላስ ጉልበት እንዲህ ብሎአል: “ የለዘበች ምላስ ቁጣን ትመልሳለች፣ ሸካራ ቃል ግን ቁጣን ታነሳለች ' (ምሳሌ 15:1)። " ፈዋሽ ምላስ የሕይወት ዛፍ ነው፣ ጠማማ ምላስ ግን ነፍስን ይሰብራል ” (ምሳሌ 15:4)።

ምላስ መጠኑ ትንሽ ይሁን እንጂ መገንባት ይሁን ማፍረስ የሚችል ጉልበት አለው። ያዕቆብ ከፈረሶች ልጓም፣ ከመርከቦች መቅዘፊያ፣ እንዲሁም ከእሳት ጋር ያነፃፅረዋል። ምላስ መጠኑ ትንሽ ቢሆንም በሰው ሕይወት ውስጥ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው መቅዘፊያ በግዙፉ መርከብ፣ ልጓም በትልቁ ፈረስ፣ እንዲሁም ትንሽ እሳት በትልቁ ጫካ ላይ የሚጫወቱትን አይነት ሚና ይጫወታል። በምላስ ምክንያት በሁለት አገሮች መካከል ግጭት ሊፈጠር በሺህዎች የሚቆጠሩ ሊሞቱ ይችላሉ። በምላስ ምክንያት ወህኒ ቤቶች ሙሉ ናቸው። በምላስ ምክንያት ትዳራቸው የፈረሰ ብዙ ናቸው። ያዕቆብ “ምላስ መጥፎ ጉዳት ስለሚያስከትል ዝም በሉ' እያለን አይደለም፤ ነገር ግን ትክክለኝውን ነገር በትክክለኛ ጊዜ ተናገሩ” እያለን ነው

ምላስ የሚያስከትለው ጉዳት በጫካ ውስጥ ከሚነሳው እሳት ጋር ተመሳሳይ ነው። የእሳትን አጥፊነት ማንም ሰው ያውቀዋል። እሳትና ምላስን ከሚያመሳስሏቸው ነገሮች አንዱ ፍጥነታቸው ነው። ምላስ በሺዎች የሚቆጠሩ ኪሎሜትሮችን ተጉዞ ሊጎዳ ይችላል። አንድ በአገሪቱ በምስራቅ አቅጣጫ ከብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተለቀቀ የቃል ሚሳኤል በአጭር ጊዜ በሌላኛው ጥግ በሚኖሩ ላይ ትልቅ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል። ምላስ እጅ የለውም፣ ነገር ግን እጅ እንደሚገል ምላስም ይገድላል። እጅ በቅርብ ያለውን ሲገድል ምላስ ግን በሩቅ የሚኖረውንም ሊገድል ይችላል። ዳዊት ስለ ምላስ ከተናገረው አንዱን ልጥቀስላችሁ:- አፋቸውን በሰማይ አኖሩ፣ አንዳበታቸው በምድር ውስጥ ተመላለሰ ” (መዝ. 73:9)።

ምላስ በምድር ሁሉ የመመላለስ ኃይል አለው። ከዚያም አልፎ ወደ ሰማይም ይደርሳል። በአጠገቡ ያለውን ብቻ ሳይሆን የማያውቀውን እንግዳ ጭምር ሊያጠቃ ይችላል። ያዕቆብ ምላስን hመፀኛ አለም' ብሎ ይጠራዋል (ያዕቆብ 3:6)። አመፀኛ አለም ማለት ለእግዚአብሔር የማይታዘዝ አለም' ማለት ነው። ያልተቆጣጠሩት ምላስ ለእግዚአብሔር ፈቃድ እንዳማይታዘዝ አለም ነው። አንድ የማይታዘዝ አመፀኛ አለም በውስጣችን አለ ማለት ነው። ምላስን ለመቆጣጠር ከሰው ውጪ የሆነ ኃይል ያስፈልጋል: " አቤቱ፥ ለአፌ ጠባቂ አኑር፥ የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ ” (መዝሙር 141:3)

የዕለት እንጀራ (ገጽ 137)
@MesayD

Biruh

06 Nov, 13:00


https://www.youtube.com/live/LiC5pEW1jG8?si=hw9fAU5nio_r7UmH

Biruh

05 Nov, 14:59


https://www.youtube.com/live/cH0II8XN8Zo?si=Y9dRr3apSHTkn9ky

እስራኤል በመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት ክፍል 1

Biruh

04 Nov, 17:02


https://youtu.be/2eeiA81GXt4?si=lwwU43GI7mWhNz0g

Biruh

03 Nov, 08:08


የፈተና ደስታ

ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት
(ያዕቆብ 1፡2)

ብዙዎቻችን በፈተና ወይም በመከራ ምክንያት የሚገኝ ደስታን ለማጣጣም አልታደልንም። የዚህ ምክንያቱ ብዙ ነው። ከብዙ በጥቂቱ:-

1 . የሚደርሱብን ፈተናዎች ያዕቆብ እንዳለው በእምነታችን ምክንያት ሳይሆን በሥጋዊ ምኞታችን ምክንያት የሚመጡ ስለሆኑ ነው። *አመጋገብ ላይ ባለመጠንቀቅ በሽታዎች፣ ኑሮ ላይ ባለመጠንቀቅ እዳዎችና ሌሎች ብዙ ችግሮች ይመጣሉ* ።

2 . ብዙ ጊዜ ችግርና መከራ ሲመጣ ክፉ ሰዎች፣ ኃጢአተኞች ስለሆንን የመጣብን ስለሚመስለን በጥፋተኛነት እየተቸገርን የመከራውን መንፈሳዊ በረከት ማጣጣም አንችልም።

3 . የሚደርስብን ችግር ለመንፈሳዊ እድገታችን የሚበጅ ሳይሆን “ *ሰይጣን እኛን ለመጉዳት ያመጣብን ነው* ” ብለን በማሰብ በአምላካችን ላይ ያለው እምነታችን ይሸረሸራል። የመከራ እሳቱ እኛን ለማጥፋት ሳይሆን ለማጽዳት የመጣ መሆኑን ማመን ይከብደናል። በዚህ ምክንያት የፈተናን ደስታ አናውቀውም።

4 . ለፈተና የሚበቃም እምነት ስለማይኖረን በትንሹ ኮሽታ በመደንገጥ ጸሎትን እግዚአብሔርን ለመምሰል ሳይሆን ከፈተናና ከችግር ማምለጫ መንገድ እናደርገዋለን።

በእምነታችን ምክንያት ግን በሥራ፣ በትምህርት፣ በትዳር እና በተለያዩ የኑሮአችን ክፍሎች እንፈተናለን!! ይህን አይነት ፈተና የተፈተነ ሰው በትእግስት የሚበልጥ በረከትን መቀበሉ አይቀርም። አንዳንዶቻችን በትምህርት ቤት በሰንበት ምክንያት እሳት ውስጥ ገብተን እናውቃለን። በእምነታችን በቤተሰብ ውስጥ ችግር ውስጥ ገብተን እናውቅ ይሆናል። ከወዳጅ ዘመድ መሳደድ ይመጣብን ይሆናል። ይህ መከራ መጨረሻው በረከት ነው። ጌታን የሰቀሉት እኛን ቢደበድቡን ስለስሙ ስለሆነ ደስ ይበለን!!

የመከራ በረከቶች ብዙ ናቸው። ከሁሉ በላይ ግን ጠንካራ የሆነ ሕይወት፣ የእግዚአብሔርን እጅ ያየ እምነት ይኖረናል!!

የዕለት እንጀራ (ገጽ 134)
@MesayD

Biruh

02 Nov, 17:27


https://www.youtube.com/live/mFqPxlZj4F4?si=Es_MW3uKRH6mLnot

ተጽፏል የቀጥታ ስርጭት

Biruh

02 Nov, 06:01


በማንኛውም ጊዜና በየትኛውም ቦታ፣ በማንኛውም ስቃይና መከራ፣ ነገሮች ሁሉ ሲጨላልሙና የወደፊቱ ሁኔታም በጭንቀት ሲሞላን፣ ከዚህም የተነሳ ረዳተ ቢስና ብቸኛች እንደሆንን ሲሰማን፣ በእምነት ወደ እርሱ ለምንጸልየው ጸሎት ምላሽ ይሆን ዘንድ አጽናኙ ይላክልናል፡፡

መልካም ሰንበት

Happy Sabbath


@DailyBiruh

Biruh

01 Nov, 08:11


https://www.youtube.com/live/AVRjLXrQfJ0?si=yXBW3X2uAcpXsFmI

5ኛ ሰንበት ትምህርት

Biruh

01 Nov, 07:34


https://youtu.be/OEmaJUNSvBA?si=VKYugIGOHHWW6n-R

Biruh

01 Nov, 06:41


https://youtube.com/@alamurasdachurch?si=weWY7I5wKlTCapoF

ይህንን የአላሙራ SDA YouTube ቻናል Subscribe አድርጉ ሌላው ደግሞ በጣም ግሩም የሆኑ ዝማሬዎች አሉ ሰምታችሁ ተባረኩበት ለሌሎችም ሼር አድርጉ የበረከቱ ተካፋዮች ይሁኑ🙏

Biruh

31 Oct, 16:03


ስምንቱ ሐኪሞች

"ወዳጅ ሆይ፥ ነፍስህ እንደሚከናወን፥ በነገር ሁሉ እንዲከናወንልህና ጤና እንዲኖርህ እጸልያለሁ"
3ኛ ዮሐንስ 1:2

1.ምግብ

ነገ የሚናገረው፤ የሚሰራው፤ የሚራመደው ዛሬ የተመገብነው ምግብ ነው። ስለዚህ ገንቢ ገንቢውን ብላው! የሚጎዳውን ሁሉ ተወው።

2.እንቅስቃሴ

የአካል እንቅስቃሴ ከሚታሰበው የበለጠ አስፈላጊ ነው፤ ስለዚህ ለነፍስህ ድረስ፣ ተነሳ! ተንቀሳቀስ!

3.ውኃ

አካላችን ከመቶ ሰባ ውኃ ነው። ሲነጋ በውኃ ጀምር፤ ቀኑን ሙሉ ቀጥል። ውኃ ለደፈረው መድኃኒት ነው።

4.ጸሐይ

በአግባቡ ከተጠቀሙበት ጸሐይ ፈውስና በረከት ናት። የጸሐይ ሙቀትና ብርሃን ባይኖር ኖሮ ምን ይውጠን ነበር!!

5.ራስን መግዛት

ራሱን የሚገዛ አገርን ከሚገዛ ይበልጣል። ለሰውነትህ የማይስማማውን እምቢ በል፣ ጠቃሚውን በልክ ተጠቀምበት"

6.አየር

መስኮቱን ከፈት ከፈት አድርገው አየር ይግባ፡፡ ክክርስቶስ ጸጋ ቀጥሎ ታላቁ ስጦታ አየር መሆኑን አትርሳ።

7.ዕረፍት

የዛሬ ዓመት ወይም ጡረታ ስገባ አርፋለሁ አትበል። በየቀኑ እፎይ በል፤ ተዝናና። ለሚያልፍ ዓለም ይህን ያህል አትጨነቅ።

8.እምነት በመለኮት

ባለቤቷን የምታምን በግ ላቷን ከውጭ ታሳድራለች። እግዚአብሔርን እመነው፤ አትጠራጠረው። ከእናት የበለጠ ያፈቅርሃል ፤ከእረኛም የበለጠ ይጠነቀቅልሃል።

“አንተ የእምላክህን የእግዚአብሔርን ቃል አጥብቀህ ብትሰማ በፊቱም የሚበጀውን ብታደርግ፥ ትእዛዙንም ብታደምጥ፥ ሥርዓቱንም ሁሉ ብትጠብቅ በግብፃውያን ላይ ያመጣሁትን በሽታ አላደርስብህም እኔ ፈዋሽህ እግዚአብሔር ነኝና አለ።" ዘጸ 15:26

የዕለት እንጀራ (ገጽ 272)
@MesayD

Biruh

30 Oct, 14:52


https://www.youtube.com/live/Zth7QxHhnBE?si=OkL9ZbSoSaIyiHs4

5ኛ ሰንበት ትምህርት

Biruh

30 Oct, 13:42


የዕለት እንጀራ (ገጽ 279)



                ክፉ ለማድረግ ጊዜ የለም

"ይህ ሁሉ እንዲህ የሚቀልጥ ከሆነ የእግዚአብሔርን ቀን መምጣት እየጠበቃችሁና እያስቸኮላችሁ በቅዱስ ኑሮ እግዚአብሔርንም በመምሰል እንደምን ልትሆኑ ይገባችኋል”
               (2 ጴጥሮስ 3፡11-12)

የጽድቅ ጠላት ከሆነው ጋር እየሰሩ ያሉ፣ ሳያውቁም የእርሱን ሥራ የሚሠሩ እንዲሁም ከክርስቶስ ጋር ሆነው የእርሱን ሥራ እየሠሩ ያሉ ሁሉ ነፍሳቸውን የከበበው ከባቢ አየር ወደ ምን እየወሰዳቸው እንደሆነ ሊያውቁ ይገባል።

ሰይጣን እውነቱን ባመኑት መካከል አለመስማማትን የሚያመጡትን፤ በወንድማማቾች መካከል መተማመን እንዲሳሳ ከሚያደርጉት ከማናቸውም ጋር በመተባበር ይደሰታል።

ይህ ለጌታ የምንዘጋጅበት ቀን ነው። አለማመንን ለመነጋገርና የሰይጣንን ስራ ለመስራት አሁን ጊዜ የለንም ። እየንዳንዱ የቅናትን፤የምቀኝነትንና የመከፋፈልን ዘር በመዝራት የሌሎችን እምነት እንዳይንድ ይጠንቀቅ፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ቃሎቻችንን ስለሚሰማና ሲፈርድም አንድ ድርጊት ባመጣቸው ውጤቶች ልክም ጭምር ስለሚፈርድ ነው።

ደግሞም እራቱ ነፋሳት ሳይለቀቁ የተያዙት የእግዚአብሔር ባርያዎች ግንባሮች እስኪታተሙ ድረስ ነው። ከዚያ የምድር ኃይላት ወደ መጨረሻውና ታላቁ ጦርነት ኃይላቸውን ያሰፋሉ። በምህረት የተሰጠንን ጊዜ በጥንቃቄ ልናሻሽለው ይገባል፤ ተግተን ራሳችንን ልንመረምር ይገባናል።

የሚያስፈልገን የተገራ መንፈስ፣ የነፃ ልብና ሃሳብ ነው። ይህ ከችሎታ፣ ከብልሃት ወይም ከእውቀት የበለጠ ዋጋ ያለው ነው። ችሎታው ኖሯቸው በትክክል ከማይተገብሩት ሰዎች ይልቅ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል” *የሚለውን ለመታዘዝ የሰለጠነ ብዙም ችሎታ የሌለው ሰው አእምሮ ለእግዚአብሔር ሥራ በተሻለ ብቁ ነው። ሰዎች ዓለማዊ ነገሮችን በማወቃቸው ሊኩራሩ ይችላሉ። ነገር ግን እውነት፣ ሕይወትና መንገድ የሆነውን ክርስቶስን ካላውቁ አላዋቂዎች ሆነው እውቀታቸውም ከእነርሱ ጋር አብሮ የሚጠፋ ይሆናል። አለማዊ እውቀት ኃይል ቢሆንም እዕምሮን መለወጥ የሚችለውን ቃል ማወቅ ግን የማይጠፋ ነው።

              📝 ኤለን ኋይት፥ማራናታ 53

       @MesayD                     

Biruh

29 Oct, 11:30


HTML

ዛሬ ማታ 3:00 ላይ ለዌብሳይት መሰረት የሆነውን HTMLን በስፋት እና ጠቀመታውን እንመለከታለን ። እስከዛው ሼር በማድረግ ይሄንን እድል ለሁሉም ያድርሱ ። 400 MEMBERS እንድናልፍ ያጋሩ ።


@DinkTech

Biruh

28 Oct, 07:30


https://www.youtube.com/live/58IWegkfXnU?si=rKAtH00hSDi_NSyQ

ታላቁ ተጋድሎ
ምዕራፍ ሁለት

Biruh

27 Oct, 12:20


https://www.youtube.com/live/vjCR6hGfw14?si=RBJhIkzJQWMF_c1N

Biruh

26 Oct, 04:04


"ሕያው ተስፋ ያለኝ ኃጢአተኛ ስላልሆንኩ አይደለም፤ ነገር ግን ለእኔ ኃጢአት ክርስቶስ ስለ ሞተ ነው።

እርካታዬ ቅዱስ በመሆኔ የተገኘ አይደለም፤ ነገር ግን ለእኔ ለእርኩሱ እርሱ ጽድቄ ሆኖ ነው።

እምነቴም በእኔነቴ ላይ፣ ሊሆኑ ይችላሉ በምላቸው ነገሮች ወይም በሚሰማኝ ስሜት ወይም ደሞ በማውቀው እውቀት ያረፈ አይደለም፤ ነገር ግን ክርስቶስ ባደረገው እና አሁን በእኔ እያደረገ ባለው ነገር ላይ ያረፈ ነው።"

Biruh

25 Oct, 18:36


ምሪት ያስፈልጋችኋል?

ከእናንተ ማንም ጥበብ ቢጎድለው!ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉም የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፤ ለእርሱም ይሰጠዋል።ያዕ 1፡5
አስተምርሃለሁ፤ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ!እመክርሃለሁ በአይኔም እከታተልሃለሁ፡፡መዝ 32፡8
ፈቃዳችንን ለእግዚአብሔር እስካስረከብንና በብርታቱና በጥበቡም እስከታመንን ድረስ፣ በእርሱ ትልቅ እቅድ ውስጥ የተዘጋጀልንን ዓላማ ለመፈጸም ሰደህንነት መንገድ ይመራናል፡፡
እግዚአብሔርን የሚያሳዝን ነገር በምንም መንገድ ላለማድረግ የወሰኑ ሰዎች፣ ጉዳያቸውን ሰእግዚብአብሔር ፊት ካቀረቡ በኋላ የትኛውን መንገድ መከተል እንዳለባቸው እርሱ ያሳውቃቸዋል፡፡እናም ጥበብን ብቻ ሳይሆን ብርታትንም ይቀበላሉ፡፡


መልካም ሰንበት

Biruh

25 Oct, 06:22


https://www.youtube.com/live/mkhaV7-cflM?si=42DaS3NldOyNOJsi

4ኛ ሰንበት ትምህርት

Biruh

24 Oct, 06:50


https://www.youtube.com/live/bWDjCyUm7zQ?si=c_539QNLHlx3MZVs

Biruh

23 Oct, 15:33


https://www.facebook.com/share/v/gedhewn7YTU7V6G1/

የቀጥታ ስርጭት ከሀላባ ቁሊቶ

የመጨረሻ ዘመን መልዕክት

Biruh

23 Oct, 08:04


በYouTube

https://www.youtube.com/live/hsgSkmLuelk?si=a1s2juSkUpZUZxNb

Biruh

23 Oct, 07:59


የኃይማኖት አባቶችና ነቢያት
በዘማሪ ማሞ ጴጥሮስ

https://www.facebook.com/share/v/C9WtvpuC6E2UkKNq/

Biruh

21 Oct, 17:17


ከማክሰኞ ጀምሮ በሀላባ ቁሊቶ የሚደረገውን ታላቅ መንፈሳዊ ኮንፈረንስ ከቦታው በቀጥታ ስርጭት በFacebook እና በYouTube ቻናል ከHope Channel Ethiopia በተጨማሪ ለማስተላለፍ ዝግጅቴን አጠናቅቄያለሁ! መልካም የበረከት ጊዜ እንደሚሆን ተስፋ አድርጋለሁ።

እስከዛው Facebookን follow እና YouTubeን Subscribe አድርጉ 🙏

Facebook Link 👇👇

https://www.facebook.com/dubushe?mibextid=ZbWKwL

YouTube👇👇

https://youtube.com/@mesayadventist1984?si=xDYXn5-fDvI_OHJb

Biruh

20 Oct, 14:40


https://youtu.be/SBG1sWE0lwg?si=UGFJEvsdkRooaA10

Biruh

18 Oct, 15:48


" እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤... " ኤር 6: 16።


መልካም ሰንበት
Happy Sabbath

        sʜᴀʀᴇ ◈ Join ◈ sʜᴀʀᴇ
    👇JOIN OUR CHANNEL👇
          ▷ @DailyBiruh ◁
            ▷ @DinkTech ◁
 
 
         👇👇Inbox Chat 👇👇
              ▷  @TattyA7  ◁

Biruh

16 Oct, 18:42


የባካፋ 7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን መዘምራን አዲሱ አልበም

ተባረኩበት ።

        sʜᴀʀᴇ ◈ Join ◈ sʜᴀʀᴇ
    👇JOIN OUR CHANNEL👇
          ▷ @DailyBiruh ◁
            ▷ @DinkTech ◁
 
 
         👇👇Inbox Chat 👇👇
              ▷  @TattyA7  ◁

Biruh

12 Oct, 16:19


አዲሱ ሰንበት ትምህርት እንዴት ነው ።  ብዙ ተጠቃም አለ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።

sʜᴀʀᴇ ◈ Join ◈ sʜᴀʀᴇ
    👇JOIN OUR CHANNEL👇
          ▷ @DailyBiruh ◁
            ▷ @DinkTech ◁
 
 
         👇👇Inbox Chat 👇👇
              ▷  @TattyA7  ◁

Biruh

12 Oct, 10:49


https://t.me/Nehemiahchristian

Biruh

11 Oct, 10:43


🎉🎉🎊ተለቀቀ ተለቀቀ 🎊🎉🎉

ሶስት ቋንቋ የያዘው አዲሱ ሰንበት ትምህርት ተለቀቀ ።  ተባረኩበት

BIRUH 🤝 DINK TECH


Manni barumsaa Wiixataa haaraan afaan sadii gadhiifame.    Inni eebbifame

  BIRUH 🤝 DINK TECH

ሓድሽ ናይ ስሉስ ቋንቋታት ቤት ትምህርቲ ሰንበት ተዘርጊሑ።    ተባሪኹ

  BIRUH 🤝 DINK TECH