የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau @aabols Channel on Telegram

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

@aabols


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄዎ
+251118124566

Promotional Article for Labor and Skill Bureau- Addis Ababa Telegram Channel (Amharic)

በየቀኑ፣ ሉባቸውና አስተዳደር ሠራዊት በአዲስ አበባ የተሞላችሁ የታክስ እና አገልግሎቶች ማብራሪያ ቴሌግራም ቻናሎችን መምጣታችሁ አጋር፡፡ 'Labor and Skill Bureau- Addis Ababa' በርዕዮት መተግበሪያ ቴሌግራም ከእነሱ ጋር እያለው በመሆኑ ታክስ እና ስልኩት አገልግሎቶች የሆነውን ማብራሪያ መድሃኒት ስላደረጋችሁ ቅርብ አስተዋፅኦቶች እና ስክዳውስ ተመልከቱ፡፡ በዚህ ቡሕ ቦታ በአማርኛ እና በEnglish እንዲሆኑ እናስታህላለን፡፡ የታክስ እና ስልኩት አገልግሎቶች በአሲዳስ በትምህርት፣ በዘርፍ፣ በመፍትሄ ወይም በከሁም ድርጅታ ለምንደርስ ነው፡፡ ለማህበርበህልም አማካኝ አና ማናፍርሀ እንዲሆኑ እንገልጻለን፡፡ በሌላ ቦታ ትኩረት አማራኝን በመቃወማ እንዲቀጥለን እናም እንጨመርላለን፡፡

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

05 Feb, 14:39


ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የሀብት አጠቃቀማቸውን ከብልሹ አሰራር የፀደ ለማድረግ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።

ጥር 28/2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የሀብት አጠቃቀማቸውን ከብልሹ አሰራር የፀዳ ለማድረግ ያለመ ስልጠና ከ15ቱ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች ለተውጣቱ የፋይናንስ እና የሰው ሀብት ዳይሬክተሮች ስልጠና ተሰጥቷል።

በስልጠናው የውስጥ ኦዲት መመሪያ ቁጥር 08/2003 እና የአፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 01/2011 እንዲሁም የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 56/2010 ላይ ግንዛቤ በመፍጠር ሰራተኞች መብትና ግዴታቸውን አውቀው ተግባራትን በውጤታማነት ለመስራት ያስችላል ተብሏል።

ስልጠናው ከዚህ ቀደም ሲደረጉ ከነሩ መሰል ስልጠናዎች በተለየ  መልኩ ሰልጣኞች ስለ ስልጠና ርዕሶች ምን አይነት ግንዛቤ እንዳላቸው  በመግቢያ ፈተና በመፈተሽ ከስልጠና በኃላ የመውጫ ፈተና በመስጠት የስልጠናውን ፋይዳ መገምገም እንደተቻለ በሥራና ክህሎት ቢሮ የውስጥ የውስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ዘቢደሩ ሸዋረጋ ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

04 Feb, 17:21


Channel name was changed to «የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau»

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

04 Feb, 17:17


የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሄደ።

ጥር 27/2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀሙን ከ11ዱም ክፍለከተሞችና ከ119 ወረዳዎች ከተውጣጡ የኢንተርፕራይዝ ቡድን መሪዎች እና ከ15 የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አስተባባሪዎች ጋር በጋራ ገምግሟል።

በግምገማ መድረኩ በዘርፉ የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች ባለፉት ስድስት ወራት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ተደጋጋሚ መድረኮች መዘጋጀታቸው ስራዎችን ተቀራርቦ እና በባለቤትነት ለመስራት እንደሚችል ተናግረዋል።

የውይይት መድረኩን የመሩት በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ኃላፊ #አቶ መሀመድ ልጋኒ መድረኩ ባለፉት ስድስት ወራት የተመዘገቡ ውጤቶችን በማላቅ በቀሪዎቹ ስድስት ወራት ቀሪ ተግባራትን በተሻለ መነሳሳት እና አቅም ለመፈጸም ያስችላል ብለዋል።

ዘመናዊ የአሰራር ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዘርፉ የሚሰጠውን አገልግሎት ከብልሹ አሰራር የፀዳ በማድረግ ሂደት ኢንተርፕራይዞች በኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት E-LMIS እንዲመዘገቡ በማድረግ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

በቀጣይ ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለሚከናወኑ ተግባራት የባለሙያዎችን አቅም መገንባት የሚያስል ተከታታይነት ያላቸው ስልጠናዎች እና ውይይቶች እንደሚካሄዱ ተጠቁሟል።

Labor and Skill Bureau- Addis Ababa

02 Feb, 12:53


የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት  ቢሮ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮን 3ለ2 በሆነ ውጤት አሸነፈ።

ጥር  25 / 2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ ስፓርት ለሁሉም  ኮሚቴ የሚያካሂደው ስፓርታዊ ውድድሮች በተያዘው ዓመት ለ15ኛ ጊዜ በድምቀት በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የዚሁ ስፓርታዊ ውድድሮች አንዱ አካል የሆነው የወንዶች እግር ኳስ ውድድር በሶስት ዲቪዝዮን እና በተለያየ ምድብ እየተካሄደ ነው።

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት   ቢሮ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አቻውን 3ለ2 በሆነ ውጤት  አሸንፏል።

ቡድኑ ትላንት በምስራቅ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባካሄደው የመጀመሪያ ጨዋታ ነው ድል የቀናው።

Labor and Skill Bureau- Addis Ababa

24 Dec, 17:49


በሥራ ዕድል ፈጠራና ሌማት ቱሩፋት የንቅናቄ ሥራዎች የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑ ተገለፀ።

ታህሳስ 15/2017 ዓ ም

የከተማ አስተዳደሩ የሥራ እድል ፈጠራ እና የሌማት ቱሩፋት የንቅናቄ ሥራዎች የ42 ቀናት አፈፃፀምን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጧል።

በከተማ ግብርና ዘርፍም ሆነ በሥራ ዕድል ፈጠራ የንቅናቄ ሥራዎች የተሻለ አፈፃፀም መመዝገቡ ከመድረክ ተገልጿል።

መድረኩን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ እና የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ ክቡር አቶ አለማየሁ እጅጉ በጋራ መርተውቷል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ሀሳብ የሰጡት ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ በቀጣይ የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ከቅጥር ባሻገር ኢንተርፕራይዞችን በማደራጀት ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል።

አቶ ጥራቱ አያይዘውም ከሌማት ቱሩፋት ስራ ጋር ተያይዞ ነባር ተቋማትን ማስቀጠል እና አዳዲስ የፋሚሊ ቢዝነሶችን አጠናክሮ ወደ ስራ ማስገባት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ምክትል ኃላፊ በሰጡት ሀሳብ በሥራ እድል ፈጠራ እና በሌማት ቱሩፋት ስራዎች ውጤት ማስመዝገብ የብልፅግና ፓርቲ ዋና ዕሴት የሆነውን ሰው ተኮርነት ማስፈፀም መሆኑን ገልፀው ከዚህም በላይ የላቀ አፈፃፀም ለማስመዝገብ አመራሩ ስራውን ከመቼውም ጊዜ በላይ በጥብቅ ዲሲፒሊን ሊመራ ይገባል ብለዋል።

Labor and Skill Bureau- Addis Ababa

21 Dec, 19:03


ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ የሥራ ዕድል ፈጠራና የሌማት ቱሩፋት የንቅናቄ ሥራዎችን እና የምግብ ዋስትና ተጠቃሚ ልየታ አፈፃፀምን በመገምገም ቀጣይ ሥራዎች ላይ አቅጣጫ አስቀመጡ።

ታህሳስ 12/2017 ዓ ም

በመድረኩ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ የልማት ትሩፋት የንቅናቄ የሱፐርቪዥን ስራ እና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ቀጣይ በሚተገበረው የምግብ ዋስትና ፕሮግራም የተጠቃሚዎች ልየታ፣ የደራጃ ፍረጃ እና የ2ኛ ዙር ተጠቃሚዎች ምርቃት ተገምግሞ የቀጣይ ስራ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ከሥራ ዕድል ፈጠራና ከሌማት ቱሩፋት የንቅናቄ ሥራዎች አንፃር የአፈፃፀም ሂደቱን ሱፐርቫይዝ የማድረግ ሥራው ከድጋፍ ጋር ተሳስሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ተግባራዊ በሚደረገው የከተማ ምግብ ዋስትና እና ልማታዊ ሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ለመለየት የምዝገባ ሥራው መጠናቀቁ በመድረኩ በጠንካራ ጎን የተነሳ ሲሆን በቀጣዮቹ ቀናት ተመዝጋቢዎችን በደረጃ የመፈረጅ ሥራውን በማጠናቀቅ ለማህበረሰቡ ማስተቸት እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

Labor and Skill Bureau- Addis Ababa

06 Dec, 09:38


ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ የአርባ ምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማትን የአፈፃፀም ሂደት በመስክ ተገኝተው በመመልከት ተመለከቱ።

ህዳር 28/2017 ዓ ም

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ክቡር ጠቅላይ ሚንስቴር ዶክተር አብይ አህመድ በተሰጣቸው ኃላፊነት መሠረት በአርባ ምንጭ ከተማ ተገኝተው የኮሪደር ልማቱን በመደገፍ ላይ ይገኛሉ።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር በከተማው የተሰሩ እና በተሻሻለው ስታንዳርድ መሠረት የተጠናቀቁና እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎችን እያስጎበኘ ይገኛል።

Labor and Skill Bureau- Addis Ababa

06 Dec, 09:33


በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ የተመራ ልዑካን ቡድን በአርባምንጭ ከተማ የተሰማሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን የመስክ ምልከታ እያደረገ ይገኛል

አርባምንጭ፡ህዳር 27/2017 ዓ/ም (አርባምንጭ ከተማ መ/ኮሚዩኒኬሽን)

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር በከተማው የተሰሩ፣ በተሻሻለው ስታንዳርድ መሠረት የተጠናቀቁና እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎችን እያስጎበኘ ይገኛል

Labor and Skill Bureau- Addis Ababa

05 Dec, 16:12


በከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት እና የሥራ ፕሮጀክት አዲስ ተጠቃሚዎችን ለመለየት በተዘጋጀ ማስፈፀሚያ ዕቅድ ዙሪያ የባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሄደ።

ህዳር 26 ቀን ፤ 2017 ዓ.ም

በከተማ ልማታዊ ሴፍት ኔትና የስራ ፕሮጀክት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የገንዘብ ድጋፍ እና ተጨማሪ ፋይናንስ አዲስ ተጠቃሚዎች ልየታ ለማካሄድ ከዘርፉ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።

ፕሮጀክቱ በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና ተጨማሪ ፋይናንስ-2 RHSIN በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በከተማ ልማታዊ ሴፍት ኔትና የስራ ፕሮጀክት የሚታቀፉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ቤተሰቦችን በመለየት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

በተያዘው ዕቅድ መሠረት ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ስደተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ፣ በቀጥታ ድጋፍ የሚጠቀሙ፣ በብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የሚታቀፉ እና በ2014 ዓ ም በኑሮ ምዘና ስርአት አልፈው በተጠባባቂነት የተያዙ 128, 560 ተጠቃሚዎችን በማካተት በአጠቃላይ 178ሺ 258 ተጠቃሚዎችን ለማጥራት እና ለመለየት በማዕከል እና በክፍለ ከተሞች ስራውን የሚያከናውን አደረጃጀት በመፍጠር ወደ ተግባር ይገባል።

የውይይት መድረኩን የመሩት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር #አቶ ጥራቱ በየነ የፕሮጀክቱን ተጠቃሚዎች በሚገባ ለይቶ በቀጣይ ወደ ዘላቂየኑሮ ማሻሻያ እንዲገቡ ለማድረግ የተጠቃሚዎች ልየታ በጥንቃቄ እንዲካሄድ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።

Labor and Skill Bureau- Addis Ababa

05 Sep, 13:33


ከተለያዩ የአፍሪካ እና የአለም ሀገራት የመጀመሪያው የአፍሪካ ከተሞች ፎረም ላይ ለመሳተፍ ወደ ከተማችን የመጡ እንግዶች በመዲናችን የተሰሩ ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የነዋሪውን የኑሮ ጫና ለማቅለል የተሰሩ ስራዎች እጅግ እንዳስደሰታቸው የተናገሩ ሲሆን ተሞክሮዎቹንም ወደየመጡበት ሀገር እንደሚወስዱ ገልጸዋል።

Labor and Skill Bureau- Addis Ababa

22 Aug, 20:57


የ2016 ትምህርትና ስልጠና ዘመን የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች የምረቃ ስነ-ስርዓት በድምቀት ተካሄደ።

ነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2016 ትምህርትና ስልጠና ዘመን የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች የምረቃ ስነ-ስርዓት በዛሬው ዕለት በሚሊኒየም አዳራሽ በድምቀት ተካሂዷል።

በምረቃ ሥነ-ሥርአቱ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ #ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ባስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት የሀገራችንን ብልፅግና ለማረጋገጥ በክህሎት የበለፀገ ትውልድ ያስፈልጋል ለዚህም የከተማ አስተዳደሩ ለቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ተብለዋል።

ክብርት ከንቲባዋ በመልዕክታቸው የስራን ክቡርነት በመገንዘብ በቀጣይ የስራ ህይወታቸው ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር #አቶ ጥራቱ በበኩላቸው ዛሬ ላይ ከአለማችን አገራት መካከል በቴክኖሎጂ አቅማቸው እና በኢኮኖሚ እድገታቸው ከፊተኛው ረድፍ ላይ የሚገኙ የአለማችን አገራት የእድገታቸውና የጥንካሬያቸው ምንጭ ለሰው ሀብት ስልጠና በተለይም ለቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ልዩ ትኩረት ሰጥተው በመስራታቸው ነው፡፡

ተመራቂ ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው የጨበጡትን ሙያ በራሳቸው ጥረት እያሳደጉ በመሄድ ከአገራቸው አልፈው በአለም ገበያ ተወዳዳሪ መሆን ይገባቸዋል ብለዋል።

ቢሮው በዛሬው ዕለት ባካሄደው የምረቃ ስነ-ስርአት ከደረጃ ሁለት እስከ ደረጃ አምስት ስልጠናቸውን የተከታተሉ እና ሙያዊ ብቃታቸው የተረጋገጠ 5180 ሰልጣኞች ተመርቀዋል።