ጥር 28/2017 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የሀብት አጠቃቀማቸውን ከብልሹ አሰራር የፀዳ ለማድረግ ያለመ ስልጠና ከ15ቱ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች ለተውጣቱ የፋይናንስ እና የሰው ሀብት ዳይሬክተሮች ስልጠና ተሰጥቷል።
በስልጠናው የውስጥ ኦዲት መመሪያ ቁጥር 08/2003 እና የአፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 01/2011 እንዲሁም የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 56/2010 ላይ ግንዛቤ በመፍጠር ሰራተኞች መብትና ግዴታቸውን አውቀው ተግባራትን በውጤታማነት ለመስራት ያስችላል ተብሏል።
ስልጠናው ከዚህ ቀደም ሲደረጉ ከነሩ መሰል ስልጠናዎች በተለየ መልኩ ሰልጣኞች ስለ ስልጠና ርዕሶች ምን አይነት ግንዛቤ እንዳላቸው በመግቢያ ፈተና በመፈተሽ ከስልጠና በኃላ የመውጫ ፈተና በመስጠት የስልጠናውን ፋይዳ መገምገም እንደተቻለ በሥራና ክህሎት ቢሮ የውስጥ የውስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ዘቢደሩ ሸዋረጋ ተናግረዋል።