የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

@stphk


ይህ የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት የቴሌግራም ቻናል ሲሆን የሰንበት ት/ቤቱ መልዕክት : ትምህርት እና ወቅታዊ መረጃዎችን ማስተላለፊያ ነው

መልዕክትም ካሎት በዚህ ሊንክ ይላኩልን
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@Kibrehaymanot

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

23 Oct, 22:26


14/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 19:26-ፍጻሜ


ኢየሱስም እነርሱን ተመልክቶ ይህ በሰው ዘንድ አይቻልም በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሁሉ ይቻላል አላቸው። በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ መልሶ እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ፤ እንኪያስ ምን እናገኝ ይሆን? አለው። ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ እውነት እላችኋለሁ፥ እናንተስ የተከተላችሁኝ፥ በዳግመኛ ልደት የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን በሚቀመጥበት ጊዜ፥ እናንተ ደግሞ በአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ ስትፈርዱ በአሥራ ሁለት ዙፋን ትቀመጣላችሁ። ስለ ስሜም ቤቶችን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል። ነገር ግን ብዙዎቹ ፊተኞች ኋለኞች፥ ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ..........

1 ቆሮንጦስ 7:36-ፍጻሜ
1 ጴጥሮስ 2:18-21
ሐዋ.ሥራ 8:26-ፍጻሜ

የጌታም መልአክ ፊልጶስን ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው። ተነሥቶም ሄደ። እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘብዋም ሁሉ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር..................ፊልጶስም አፉን ከፈተ፥ ከዚህም መጽሐፍ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌልን ሰበከለት.......................ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም። ከውኃውም ከወጡ በኋላ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጠቀው፤ ጃንደረባውም ሁለተኛ አላየውም፥ ደስ ብሎት መንገዱን ይሄድ ነበርና.......................

ቅዳሴ  ዘሐዋርያት

ምስባክ
                           መዝሙር 18:4-5


አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ

ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ

ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

23 Oct, 22:26


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 14 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አቡነ ዘሚካኤል (አረጋዊ)
2.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
3.ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ
4.ቅዱስ ሙሴ መርዓዊ
5.ቅድስት እድና (የአረጋዊ እናት)
6.አባ ማትያስ (የአረጋዊ ረድዕ)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

23 Oct, 12:23


ፊልጶስ ሆይ በስብከትህ አብርተሀልና ኮከብ ብለን ሰየምንህ ... !

እንኳን አደረሳችሁ !

#ማኅበራዊ_ድህረገፅና_መረጃና_ሚዲያ_ክፍል
#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

23 Oct, 08:02


ፊልጶስ አባታችን ...

ለጥቅምት 14 እየዘጋጀን ነው ። በክብረሃይማኖት የቲክቶክ ገፅ ...

https://vm.tiktok.com/ZMhmCGkod/

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

22 Oct, 17:42


13/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 12:27-32

አበቦችን እንዴት እንዲያድጉ ተመልከቱ፤ አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከእነዚህ እንደ አንዲቱ አለበሰም። እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን በሜዳ የሆነውን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ፥ እናንተ እምነት የጐደላችሁ፥ እናንተንማ ይልቁን እንዴት? እናንተም የምትበሉትን የምትጠጡትንም አትፈልጉ፥ አታወላውሉም፤ ይህንስ ሁሉ በዓለም ያሉ አሕዛብ ይፈልጉታልና፤ የእናንተም አባት ይህ እንዲያስፈልጋችሁ ያውቃል። ዳሩ ግን መንግሥቱን ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል............

2 ቆሮንጦስ 9:1-10
ያዕቆብ 1:9-17
ሐዋ.ሥራ 20:16-28


ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ (ናሁ ንዜኑ)

ምስባክ
መዝሙር 91:12-13

ጸድቅሰ ከመ በቀልት ይፈረ

ወይበዝን ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ

ትኩላን እሙንቱ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

22 Oct, 17:42


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 13 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
2.አባ ዘካርያስ ገዳማዊ
3.አባ ማርዳሪ ጻድቅ
4.ቅዱስ አብጥማዎስ ሰማዕት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

21 Oct, 19:39


12/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 9:9-32


ኢየሱስም ከዚያ አልፎ በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረ ማቴዎስ የሚባል አንድ ሰው አየና ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው። በቤቱም በማዕድ ተቀምጦ ሳለ፥ እነሆ፥ ብዙ ቀራጮችና ኃጢአተኞች መጥተው ከኢየሱስና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አብረው ተቀመጡ። ፈሪሳውያንም አይተው ደቀ መዛሙርቱን መምህራችሁ ከቀራጮችና ከኃጢአተኞች ጋር አብሮ ስለ ምን ይበላል? አሉአቸው። ኢየሱስም ሰምቶ ሕመምተኞች እንጂ ባለ ጤናዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም፤ ነገር ግን ሄዳችሁ፦ ምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም፡ ያለው ምን እንደ ሆነ ተማሩ፤ ኃጢአተኞችን ወደ ንስሐ እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁምና አላቸው። በዚያን ጊዜ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው እኛና ፈሪሳውያን፥ ብዙ ጊዜ የምንጦመው፥ ደቀ መዛሙርትህ ግን የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው? አሉት። ኢየሱስም እንዲህ አላቸው ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ። በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፥ መቀደዱም የባሰ ይሆናል። በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን፥ አቁማዳው ይፈነዳል፥ የወይን ጠጁም ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል፤ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል፥ ሁለቱም ይጠባበቃሉ። ይህንም ሲነግራቸው፥ አንድ መኰንን መጥቶ ልጄ አሁን ሞተች፤ ነገር ግን መጥተህ እጅህን ጫንባት፥ በሕይወትም ትኖራለች እያለ ሰገደለት። ኢየሱስም ተነሥቶ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተከተለው። እነሆም፥ ከአሥራ ሁለት ዓመት ጀምሮ ደም የሚፈስሳት ሴት በኋላው ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች፤ በልብዋ ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ፥ እድናለሁ ትል ነበረችና። ኢየሱስም ዘወር ብሎ አያትና ልጄ ሆይ፥ አይዞሽ፤ እምነትሽ አድኖሻል አላት። ሴቲቱም ከዚያች ሰዓት ጀምራ ዳነች። ኢየሱስም ወደ መኰንኑ ቤት በደረሰ ጊዜ፥ እምቢልተኞችንና የሚንጫጫውን ሕዝብ አይቶ ብላቴናይቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችምና ፈቀቅ በሉ አላቸው። በጣምም ሳቁበት። ሕዝቡን ግን ከአስወጡ በኋላ ገብቶ እጅዋን ያዛት፥ ብላቴናይቱም ተነሣች። ያም ዝና ወደዚያ አገር ሁሉ ወጣ። ኢየሱስም ከዚያ ሲያልፍ ሁለት ዕውሮች የዳዊት ልጅ ሆይ፥ ማረን ብለው እየጮሁ ተከተሉት። ወደ ቤትም በገባ ጊዜ ዕውሮቹ ወደ እርሱ ቀረቡ፥ ኢየሱስም ይህን ማድረግ እንድችል ታምናላችሁን? አላቸው። አዎን፥ ጌታ ሆይ አሉት። በዚያን ጊዜ እንደ እምነታችሁ ይሁንላችሁ ብሎ ዓይኖቻቸውን ዳሰሰ። ዓይኖቻቸውም ተከፈቱ። ኢየሱስም ማንም እንዳያውቅ ተጠንቀቁ ብሎ በብርቱ አዘዛቸው። እነርሱ ግን ወጥተው በዚያ አገር ሁሉ ስለ እርሱ አወሩ...............

1 ጢሞቴዎስ 5:19-ፍጻሜ
ይሁዳ 1:9-14
ሐዋ.ሥራ 13:22-29


ቅዳሴ        ዘጎርጎሪዮስ ዘኑሲስ

ምስባክ
                            መዝሙር 83:6-7


እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ

ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል

ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

21 Oct, 19:39


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ዳዊት ልበ አምላክ (የነገሠበት)
2.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ድሜጥሮስ ሊቅ
4.ቅድስት ልዕልተ ወይን
5.ቅዱስ ሳሙኤል ነቢይ
6.ጻድቃን ዼጥሮስ ወዻውሎስ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን