የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት @stphk Channel on Telegram

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

@stphk


ይህ የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት የቴሌግራም ቻናል ሲሆን የሰንበት ት/ቤቱ መልዕክት : ትምህርት እና ወቅታዊ መረጃዎችን ማስተላለፊያ ነው

መልዕክትም ካሎት በዚህ ሊንክ ይላኩልን
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@Kibrehaymanot

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት (Amharic)

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ቴሌግራም ቻናል ነን፣ የሰንበት ት/ቤቱ መልዕክትን በትምህርት እና ወቅታዊ መረጃዎችን ማስተላለፊያ ይገኛል። በመልዕክትም ካሎት በዚህ ሊንክ ይላኩልን። ስለዚህ በመልኩ ያስተካክለውን @Kibrehaymanot የሚከተሉትን የወጪዎችን መረጃዎችን በማግኘት እና በተለያዩ መረጃዎችን በተለያዩ የሰነዳን ደረጃዎችን ይረዳል።

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

14 Feb, 18:13


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞የካቲት 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ስምዖን አረጋዊ
2.ቅድስት ሐና ነቢይት (የፋኑኤል ልጅ)
3.ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ እግዝእት
4.አባ ኤልያስ ገዳማዊ (በትህትና ያጌጠ ቅዱስ ሰው)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

14 Feb, 18:13


8/06/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 2:22-35

የመንጻታቸውም ወራት በተፈጸመ ጊዜ እንደ ሙሴ ሕግ በእግዚአብሔር ፊት ያቆሙት ዘንድ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት። "በኵር ሆኖ የሚወለድ ወንድ ልጅ ሁሉ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ይባላል” ተብሎ በእግዚአብሔር ሕግ እንደ ተጻፈ፥ በእግዚአብሔርም ሕግ እንደታዘዘ ሁለት ዋኖስ ወይም ሁለት የርግብ ግልገሎች ስለ እርሱ መሥዋዕት አድርገው ያቀርቡለት ዘንድ።

በኢየሩሳሌምም ስሙ ስምዖን የሚባል አንድ ሰው ነበር፤ እርሱም ጻድቅና ደግ ሰው ነበር፤ እርሱም የእስራኤልን ደስታቸውን ያይ ዘንድ ተስፋ ያደርግ ነበር፤ መንፈስቅዱስም ያደረበት ነበር። የእግዚአብሔርንም መሲሕ ሳያይ እንደማይሞት መንፈስ ቅዱስ ገልጦለት ነበር። መንፈስም ወደ ቤተ መቅደስ ወሰደው ዘመዶቹም በሕግ የተጻፈውን ያደርጉለት ዘንድ ሕፃኑን ጌታችን ኢየሱስን ወደ ቤተ መቅደስ በአገቡት ጊዜ።እርሱ ደግሞ ተቀብሎ በክንዱ ታቀፈው፤ እግዚአብሔርንም አመሰገነው። እንዲህም አለ፣ “አቤቱ፥ እንደ አዘዝህ ዛሬ ባርያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ። ዐይኖቼ ትድግናህን አይተዋልና። “በወገንህ ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን፥ "ለአሕዛብ ብርሃንን፥ ለወገንህ ለእስራኤልም ክብርን ትገልጥ ዘንድ።” “ዮሴፍና እናቱ ግን በእርሱ ላይስለሚናገረው ያደንቁ ነበር። ስምዖንም ባረካቸው፤ እናቱን ማርያምንም እንዲህ አላት፤ “እነሆ፥ ይህ ሕፃን ከእስራኤል መካከል ለብዙዎች ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው፥ ለሚቃወሙትም ምልክት ይሆን ዘንድ የተሠየመ ነው.......


1 ጢሞ 5:5-11
ያዕቆብ 5:13-ፍጻሜ
ግብ፡ ሐዋ፡ሥራ 3:17-ፍጻሜ


ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ

                           ምስባክ
                   መዝሙር ፵፬:፩-፪


ጎሥዐ ልብየ ቃለ ሰናየ

ወአነ አየድዕ ግብርየ ለንጉሥ

ከመ ቀለመ ጸሐፊ ዘጠበጠበ ይጽሕፍ ልሳን


ትርጉም

ልቤ መልካም ነገርን ተናገረ

እኔም ሥራዬን ለንጉሥ እናገራለሁ

አንደበቴ እንደ ፈጣን ጸሓፊ ብዕር ነው

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

13 Feb, 18:36


07/06/2017
                     የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                         ሉቃስ 19:11-28

     ይህንም ሲሰሙ ምሳሌ መስሎ ነገራቸው፤ ወደ ኢየሩሳሌም ቀርቦ ነበርና፤ እነርሱም የእግዚአብሔር መንግሥት ወዲያውኑ የምትገለጥ መስሎአቸው ነበርና። "እንዲህም አለ፥ “አንድ የከበረ ሰው መንግሥት ይዞ ሊመለስ ወደ ሩቅ ሀገር ሄደ። "ዐሥሩን አገልጋዮቹንም ጠርቶ ዐሥር ምናን ሰጣቸውና፦ እንግዲህ እስክመለስ ድረስ ነግዱ አላቸው። "የሀገሩ ሰዎች ግን ይጠሉት ነበርና፥ ይህ በእኛ ላይ ሊነግሥ አንሻም ብለው አከታትለው መልእክተኞችን ላኩ። ከዚህም በኋላ፤ መንግሥትን ይዞ በተመለሰ ጊዜ እንደ አተረፉ ያውቅ ዘንድ ምናን የሰጣቸውን ብላቴኖቹን እን ዲያመጡአቸው አዘዘ። አንደኛውም መጥቶ፦ አቤቱ፥ ምናንህ ዐሥር ነበር፤ እነሆ ዐሥር ምናን አትርፌአለሁ አለው። "ጌታውም፦ መልካም፥ አንተ በጎ አገልጋይ በጥቂት የታመንህ ስለሆንህ በብዙ ላይ እሾምሃለሁ፤ በዐሥሩ ከተሞች ላይ ተሾም አለው። ሁለተኛውም መጥቶ፦ አቤቱ፥ ምናንህ አምስት ነበር ፤ አምስት አትርፌአለሁ አለው። “እርሱንም፦ አንተም በአምስት ከተሞች ተሾም አለው። ሦስተኛውም መጥቶ እንዲህ አለው፦ አቤቱ፥ በእኔ ዘንድ የነበረቺው ምናንህ እነኋት፤ በጨርቅ ጠቅልዬ አኑሬአት ነበር። አንተ ያላኖርኸውን የምትወስድ፥ ያልዘራኽውን የምታጭድ፥ ያልበተንኸውንም የምትሰበስብ፡ ጨካኝ ሰው እንደ ሆንህ ስለማውቅህ ፈርቼሃለሁና። ጌታውም እንዲህ አለው፦ አንተ ክፉ ሰነፍ አገልጋይ፥ እኔ ያላስቀመጥሁትን የምወስድ፥ ያልዘራሁትን የማጭድ፥ ያልበተንሁትንም የምሰበስብ ጨካኝ ሰው እንደሆንሁ ታውቃለህን? እንደ ቃልህ እፈርድብሃለሁ። “ለምን ገንዘቤን ወደ ለዋጮች አላስገባህም? እኔም መጥቼ ከትርፉ ጋር በወሰድሁት ነበር። ከዚያ የቆሙትንም፦ ይህን ምናን ከእርሱ ተቀብላችሁ ዐሥር ምናን ላለው ስጡት አላቸው። እነርሱም አቤቱ፥ ዐሥር ምናን ያለው አይደለምን? አሉት። “እርሱም እንዲህ አላቸው:- ላለው ሁሉ ይሰጡታል፤ ይጨምሩለታልም፤ የሌለውን ግን ያን ያለውንም ቢሆን ይወስዱበታል። ነገር ግን እነዚያን ልነግሥባቸው ያልወደዱትን ጠላቶቼን ወደዚህ አምጡና በፊቴ ውጉአቸው”.........

ኤፌሶን 6:10-19
ዮሐ.ራእይ 13:11-ፍጻሜ
ሐዋ፡ሥራ 20:20-31


ቅዳሴ ዘባስልዮስ

ምስባክ
መዝሙር ፵፫ :፭ - ፮


ብከ ንወግዖሙ ለኵሎሙ ፀርነ

ወበስምከ ናኀሥሮሙ ለእለ ቆሙ ላዕሌነ

ዘአኮ በቀሥትየ እትአመን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

13 Feb, 18:36


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† የካቲት 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አባ አብዱልማዎስ ገዳማዊ
2.አባ ቴዎድሮስ ሊቀ ጳጳሳት
3.አባ እለ እስክንድሮስ ሊቀ ጳጳሳት
4.ቅዱስ አባዲር

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

11 Feb, 18:53


ዘነነዌ ረቡዕ
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 16:1-5

ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያንም ከሰማይምልክትን ያሳያቸው ዘንድ ሊፈትኑት መጡ። ፤ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፥ “በመሸ ጊዜ ሰማዩ ቀልትዋልና ጊዜው ብራ ነው ትላላችሁ። ፤በነጋም ጊዜ ሰማዩ ደምኖ ቀልቶአልና ዛሬስ ይዘንማል ትላላችሁ፤ እናንተ ግብዞች፥ የሰማዩን ፊት መተርጐም ታውቃላችሁ፤ የዘመኑንስ ምል ክት እንዴት አታውቁም? ክፉና፤ አመን ዝራ ትውልድ ምልክትን ትሻለች፤ ምልክት ግን ከነቢዩ ከዮናስ ምልክት በቀር አይሰጣ ትም” ከዚህም በኋላ ትቶአቸው ሄደ......

👉ሮሜ 5:1-7
👉ይሁዳ 1:20-ፍጻሜ
👉ሐዋ፡ሥራ 14:21-23

👉ቅዳሴ ዘእግዚእነ


ምስባክ
                  መዝሙር ፵፩ : ፯ – ፰


ኵሉ ማዕበልከ ወሞገድክ እንተ ላእሌየ ኀለፈ

መዓልተ ይኤዝዝ እግዚአብሔር ሣህሎ ወሌሊተ ይነግር

እምኀቤየ ብዕዐተ ሕይወትየ ለእግዚአብሔር

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

11 Feb, 18:53


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† የካቲት 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አባ ዕብሎይ ገዳማዊ
2.ቅዱስ አባ ብሶይ ጻድቅ
3.አባ አክርዽዮስ
4."49" አረጋውያን ሰማዕታት (ፍልሠታቸው)
5.ቅዱስ አሞኒና ሚስቱ ቅድስት ሙስያ (የታላቁ ዕብሎይ ወላጆች)
6.አባ ኖብ ጻድቅ : መነሳንሱ ዘወርቅ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

10 Feb, 19:19


ዘነነዌ ሠሉስ
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 11:29-23

ብዙ ሕዝብም በተሰበሰቡ ጊዜ እንዲህ ይል ጀመር፦ይህ ትውልድ ክፉ ነው ምልክት ይፈልጋል ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም፡፡ ዮናስ ለነነዌ ሰዎች ምልክት እንደ ሆናቸው እንዲሁ ደግሞ የሰው ልጅ ለዚህ ትውልድ ምልክት ይሆናል፡፡ ንግሥተ አዜብ በፍርድ ከዚህ ትውልድ ሰዎች ጋራ ተነሥታ ትፈርድባቸዋለች የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና እንሆም ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ.......

👉ቆሮንጦስ 4:2-6
👉1 ጴጥሮስ 1:10-13
👉ሐዋ.ሥራ 8:18-25

👉ቅዳሴ ዘእግዚእነ


ምስባክ
መዝሙር 63:9-10


ወፈርሃ ኵሉ ሰብእ

ወነገሩ ግብረ እግዚአብሔር

ወአዕመሩ ምግባሮ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

10 Feb, 19:19


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† የካቲት 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አጋቦስ ነቢይ: ሐዋርያና ሰማዕት
2.አባ ዘካርያስ ትሩፈ ምግባር

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን



በዓመት ውስጥ ጸሎት የሚያርግባቸው የተለዩ (የተመረጡ) ቀናት አሉ።
ርኅወተ ሰማይ አንዱ ሲሆን ነገ ወይም በቤተክርስቲያን አቆጣጠር ዛሬ የካቲት 4 ነው።
ስለዚህ በነዚህ ቀናት በርትተን በቀና ልቦና ልንፀልይ ያስፈልጋል። ከቻልን (ከበረታን) ሌሊት ተነስተን እንዲሁም ቤተክርስቲያን መጥተን ብንፀልይ የበለጠ ጥሩ ነው።

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

09 Feb, 19:04


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞የካቲት 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (አፈ በረከት-በዓለ ፍልሠቱ)
2.ቅዱስ አባ ዕብሎይ ገዳማዊ (ሕይወቱ መላዕክትን
የመሰለ ግብፃዊ አባት)
3.አባ ያዕቆብ መስተጋድል

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

09 Feb, 19:04


ዘነነዌ ሰኑይ
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 12:38-43

በዚያን ጊዜ ከጻፊዎችና ከፈሪሳውያን አንዳንዶቹ መለሱና፦መምህር ሆይ ከአንተ ምልክት እንድናይእንወዳለን አሉ። እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው፦ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም፡፡ ዮናስ በዓሣ ዐንበሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል። የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋራ ተነሥተው ይፈርዱበታል በዮናስ ስብከት ንስሓ ገብተዋልና እንሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ፡፡ ንግሥተ አዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋራ ተነሥታ ትፈርድበታለች የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና እንሆም ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ........

👉ቆሮንጦስ 6:1-11
👉1 ጴጥ1:13-21
👉ሐዋ፡ሥራ 2:37-40

👉ቅዳሴ ዘእግዚእነ


                             ምስባክ
                       መዝሙር ፪ ቍ. ፲፪


አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዓዕ እግዚአብሔር

ወኢትትኀጐሉ እምፍኖተ ጽድቅ

ሶበ ነደት ፍጡነ መዓቱ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

07 Feb, 18:45


1/06/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ዮሐንስ 15:26-17

እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ ጰራቅሊጦስ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመስክራል። “እናንተም ትመሰክራላችሁ፤ ከጥንት ጀምሮ ከእኔ ጋር ኑራችኋልና።

“እንዳትሰናከሉ ይህን ነገርኋችሁ። "ከምኵራባቸው ያስወጡአችኋል፤ ደግሞም እናንተን የሚገድላችሁ ሁሉ ለእግዚአብሔር አገልግሎት የሚያቀርብ የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል። 'ይህንም የሚያደርጉባችሁ አብንም፥ እኔንም ስላላወቁ ነው። ነገር ግን ጊዜው ሲደርስ እኔ እንደ ነገርኋችሁ ታስቡ ዘንድ ይህን ነገርኋችሁ አስቀድሜ ግን ይህን አልነገርክኋችሁም ነበር ከእናንተ ጋር ነበርሁና አሁን ግን ወደ ላከኝ ወደ አብ እሄዳለሁ፤ ከእናንተ አንዱ እንኳ ወዴት ትሄዳለህ?” ብሎ አይጠይቀኝም። ነገር ግን ይህን ስለነገርኋችሁ በልባችሁ ኀዘን ሞላ።

"እኔ በእውነት የሚሆነውን እነግራችኋለሁ፤ እኔ ብሄድ ይሻላችኋል፤ እኔ ካልሄድሁ ጰራቅሊጦስ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ከሄድሁ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ። እርሱም በመጣ ጊዜ ዓለምን ስለ ኀጢአትና ስለ ጽድቅ፡ ስለ ፍርድም ይዘልፈዋል። “ስለ ኅጢኣት፡ በእኔ አላመኑምና ነው፣ 'ስለ ጽድቅ፥ እኔ ወደ ኣብ እሄዳለሁና፤ እንግዲህ ወዲህም አታዩምኝምና ነው ስለ ፍርድም፥ የዚህ ዓለም ገዢ ይፈረድበታልና ነው።

“የምነግራችሁ ብዙ ነገር ነበረኝ፣ ነገርግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም። "ያ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ግን ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ እርሱ ከራሱ አይናገርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል። እርሱም እኔን ያከብረኛል፤ ከእኔ ወስዶ ይነግራችኋልና። ለአብ ያለው ሁሉ የእኔ ነው፤ ስለዚህም ከእኔ ወስዶ ይነግራችኋል አልኋችሁ።

“ጥቂት ጊዜ አለ፤ አታዩኝምም፤ ደግሞም ጥቂት ጊዜ አለ፤ እንደገናም ታዩኛላችሁ፤ ወደ አብ እሄዳለሁና”......


👉ኤፌሶን 4:17-ፍጻሜ
👉ይሁዳ 1:17-23
👉ሐዋ፡ሥራ 20:28-31

👉ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)

 
                                 ምስባክ
                          መዝሙር ፴፪ : ፭ - ፮


ሣህሉ ለእግዚአብሔር መልዐ ምድረ

ወበቃለ እግዚአብሔር ጸንዐ ሰማያት

ወእምእስትንፋሰ አፉሁ ኵሉ ኃይሎሙ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

07 Feb, 18:45


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† የካቲት 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1."150"ቅዱሳን ሊቃውንት ዻዻሳት (በቁስጥንጥንያ ተሠብሥበው መናፍቃንን ያወገዙበት: ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን ያፀኑበት /ጉባዔ ቁስጥንጥንያ/ በ381 ዓ/ም::
ከወቅቱ ቅዱሳን ሊቃውንት እነዚህ ይጠቀሳሉ:-
*ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ
*ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘእንዚናዙ
*ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘአልቦ ጥሪት
*ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም)
2.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት (ቅዳሴ ቤቱ)
3.ታላቁ ቴዎዶስዮስ ጻድቅ (ንጉሠ ቁስጥንጥንያ)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

06 Feb, 19:44


30/05/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 22:26-31

በወሰዱትም ጊዜ የቀሬና ሰው ስምዖንን ከዱር ሲመለስ ያዙት፤ ከጌታችን ከኢየሱስም በስተኋላ መስቀሉን አሸከሙት። ብዙ ሰዎችም ተከተሉት፤ ሴቶችም “ዋይ ዋይ” እያሉ ያዝኑለትና ያለቅሱለት ነበሩ። ጌታችን ኢየሱስም መለስ ብሎ እንዲህ አላቸው፥ “እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች ሆይ፥ ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ እንጂ ለእኔስ አታልቅሱልኝ። መካኖች፥ ያልወለዱ ማኅፀኖችና ያላጠቡ ጡቶችም የተመሰገኑ ናቸው የሚሉበት ወራት ይመጣልና። ያንጊዜም ተራሮችን በላያችን ውደቁ፤ ኮረብቶችንም ሰውሩን ይሉአቸዋል........

👉1 ጢሞቴዎስ 5:1-7
👉1 ጴጥሮስ 5:2-5
👉ሐዋ.ሥራ 9:36-ፍጻሜ

👉ቅዳሴ ዘእግዝእትነ  (ጐሥዓ)



                         መዝ· ፵፬ : ፲፬ – ፲፭

ወይወስዱ ለንጉሥ ደናግለ ድኅሬሃ

ወቢጻሂ ይወስዱ ለከ

ወይወስድዎን በትፍሥሕት ወበሐሤት

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

06 Feb, 19:44


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ጥር 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅድስት ሶፍያና ሦስቱ ሰማዕታት ልጆቿ (ጲስጢስ አላጲስና አጋጲስ)
2.ቅድስት ኦርኒ ሰማዕት ( (በ5 ነገሥታት እጅ የተሰቃየች : የሐዋርያው ጢሞቴዎስ ተከታይና ወደ ብሔረ ሕያዋን የተነጠቀች እናት)
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
4.አባ አክርስጥሮስ
5.አምስቱ ደናግል ሰማዕታት (ጤቅላ: ማርያ: ማርታ: አበያ: ዓመታ)
6.ጻድቃነ ዴጌ (የተሠወሩበት)
7.አባ ሚናስ ሊቀ ጳጳሳት
8."130,000" ሰማዕታት (የቅድስት ኦርኒ ማኅበር)


ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

05 Feb, 16:34


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ጥር 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ጻድቃን ቅዱሳን ማሕበረ ዶጌ (ዴጌ ጻድቃን)
(አክሱም አካባቢ በቁጥር ወደ 3,000 ሲሆኑ ከመድኃኔ ዓለም ጋር ማሕበር ይጠጡ የነበሩና በአንድ ላይ የተሠወሩ ቅዱሳን ናቸው)
2.አባ ገብረ ናዝራዊ ዘቃውንት (ኢትዮዽያዊ)
3.ቅድስት አክሳኒ ፈላሲት
4.ቅዱስ ሰርያኮስ ሰማዕት
5.አባ እስጢፋኖስ ገዳማዊ
6.ከድሮዋ ሮም የተነሱ ቅዱሳት አንስት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

05 Feb, 16:34


29/05/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ዮሐንስ 1:7-15

እርሱም ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምን ስለ ብርሃን ይመሰክር ዘንድ ለምስክርነት መጣ። ስለ ብርሃን ምስክር ሊሆን መጣ እንጂ እርሱ ራሱ ብርሃን አልነበረም።

"ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃንስ ወደ ዓለም የመጣው ነው። በዓለም ነበረ፤ ዓለሙም በእርሱ ሆነ፤ ዓለሙ ግን አላወቀውም። “ወደ ወገኖቹ መጣ፤ ወገኖቹ ግን አልተ ቀበሉትም። ለተቀበሉት ሁሉ ግን በስሙ ለሚያምኑ የእግዚአብሔር ልጆች እንዲሆኑ ሥልጣንን ሰጣቸው። "እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከሥጋዊና ከደማዊ ግብር ወይም ከወንድና ከሴት፤ ፈቃድ አልተወለዱም።

ያም ቃል ሥጋ ሆነ፤ በእኛም አደረ፤ ለአ ባቱ አንድ እንደ ሆነ ልጅ ክብር ያለ ክብሩን አየን፤ ጸጋንና እውነትን የተመላ ነው........


👉1 ጢሞ 3:14-ፍጻሜ
👉1 ዮሐ 1:9-ፍጻሜ ዓዲ 4:9-18
👉ሐዋ፡ሥራ 3:12-17

👉ቅዳሴ ዘእግዝእትነ

ምስባክ
መዝ· ፴፪ ቍ. ፲፪ - ፲፫


እስመ ፈላሲ አነ ውስተ ምድር

ወነግድ ከመ ኵሉ አበውየ

ስሕተኒ ከመ አዕርፍ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Feb, 18:07


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ጥር 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ቀሌምንጦስ ሰማዕት (ስለ ሃይማኖት 7 ጊዜ ሙቶ የተነሳ, 7 አክሊል የወረደለት)
2.ቅዱስ አካውህ መነኮስ
3."800" ሰማዕታት
4.ቅዱስ ዮሴፍ አይሁዳዊ (የእመቤታችን ወዳጅ)
5.ቅድስት ሳቤላ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Feb, 18:07


28/05/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 15:32-ፍጻሜ

ጌታችን ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ጠርቶ፥ “እነዚህ ሰዎች ያሳዝኑኛል፤ በዚህ ከእኔ ጋር ከዋሉ ሦስት ቀን ነውና፤ የሚበሉትም የላቸውም፤ በመንገድ እንዳይደክሙ ጦማቸውን ላሰናብታቸው አልወድም” አላቸው። ደቀ መዛሙርቱም፥ “ይህን ያህል ሕዝብ የሚያጠግብ እንጀራ በምድረበዳ ከወዴት እናገኛለን?” አሉት። "ጌታችን ኢየሱስም፥ “ስንት እንጀራ አላችሁ?” አላቸው፤ እነርሱም፥ “ሰባት እንጀራ፥ ጥቂትም ዓሣ” አሉት። ሕዝቡንም በምድር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፤ ሰባቱን እንጀራና ዓሣውን ይዞ አመሰገነ፤ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው፤ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ አቀረቡ። ሁሉም በልተው ጠገቡ፤ የተረፈውንም ቍርስራሽ ሰባት ቅርጫት ሙሉ አነሡ። የበሉት ሰዎችም ከሴቶችና ከልጆች በቀር አራት ሺህ ወንዶች ነበሩ። ሕዝቡንም አሰናብቶ ወደ ታንኳው ገባ፤ ወደ መጌዶል አገርም ሄደ........

👉ዕብራውያን 11:8-17
👉1 ጴጥሮስ 4:12-ፍጻሜ
👉ሐዋ.ሥራ 2:32-40

👉ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)


ምስባክ
መዝ ፸፯ : ፳፬ – ፳፭

አዝነመ ሎሙ መና ይብልዑ

ወወሀቦሙ ኅብስተ ሰማይ

ወኅብስተ መላእክቲሁ በልዑ እጓለ እመሕያው



ዓዲ መዝሙር ፷፬ :፬ – ፭


ጸገብነ እግዚኦ እምበረከተ ቤትከ

ቅዱስ ጽርሕከ ወመንክር በጽድቅ

ስምዐነ አምላክነ ወመድኃኒነ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

03 Feb, 19:23


27/05/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 11:7-15

እነዚያም ከሄዱ በኋላ፥ ጌታችን ኢየሱስ ስለ ዮሐንስ ለሕዝቡ እንዲህ ይላቸው ጀመረ፥ “ምን ልታዩ ወደ ምድረ በዳ ወጥታችኋል? ከነፋስ የተነሣ የሚወዛወዘውን ሸንበቆ ነውን? ፤ወይስ ምን ልታዩ ወጥታችኋል? ቀጭን ልብስ የለበሰ ሰውን ነውን? እነሆ፥ ቀጭን ልብስ የሚ ለብሱስ በነገሥታት ቤቶች አሉ። ምን ልታዩ ወጥታችኋል? ነቢይን ነውን? አዎን፤ እሱ ከነቢይ እጅግ ይበልጣል እላችኋለሁ። እነሆ፥ እኔ በፊትህ መንገድህን የሚጠርግ መልእክተኛዬን በአንተ ፊት እልካለሁ ተብሎ ስለ እርሱ የተጻፈለት ይህ ነውና። “እውነት እላችኋለሁ፤ ሴቶች ከወለዱአቸው ወገን ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም፤ በመንግሥተ ሰማያት ግን የሚያንሰው ይበልጠዋል። «ከመጥምቁ ከዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ መንግሥተ ሰማያት ትገፋለች፤ የተገፉትም ይናጠቁአታል። "ነቢያትም ሁሉ፥ ኦሪትም እስከ ዮሐንስ ትንቢትን ተናግረዋልና። ልትቀበሉትስ ብትወድዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይህ ነው......

👉ዕብራውያን 11:5-8
👉ይሁዳ 1:11-17
👉ሐዋ.ሥራ 17:14-22

👉ቅዳሴ ዘያዕቆብ ዘሥሩግ (ተንሥኡ)


ምስባክ
መዝሙር 45:22-23

እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኵሎ ዓሚረ

ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ

ንቃሕ እግዚኦ ለምንት ትነውም

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

03 Feb, 19:23


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ጥር 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ኄኖክ ነቢይ (ወደ ብሔረ ሕያዋን ያረገበት)
2.ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ (ፍልሠቱ)
3.ቅዱስ አባ ቢፋሞን ሰማዕት
4.ቅዱስ ሰራብዮን ሰማዕት
5.ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት (ከሰባቱ ሊቃናት አንዱ)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

03 Feb, 06:00


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ጥር 26 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አርባ ዘጠኝ አረጋውያን ሰማዕታት (ግብጽ ገዳመ አስቄጥስ ውስጥ)
2.ቅድስት አንስጣስያ (በ5ኛው መቶ ክ/ዘ ከቁስጥንጥንያ ወደ ግብጽ ወርዳ ፡ ንግሥናን ንቃ በበርሃ ስትጋደል የኖረች ቅድስት
እናት ናት::)
3.ቅዱስ ዮሴፍ (መፍቀሬ ነዳያን)
4.አባ ጽሕማ (ከተስዓቱ ቅዱሳን)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

03 Feb, 06:00


26/05/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 11:1-19

ከዚህም በኋላ በአንዲት ቦታ ጸለየ፤ ጸሎቱን በጨረሰ ጊዜም ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ፥ “ጌታ ሆይ፥ ዮሐንስ ለደቀ መዛሙርቱ እንደ አስተማራቸው ጸሎት አስተምረን” አለው። 'እርሱም እንዲህ አላቸው፥ “በምትጸልዩበት ጊዜ እንዲህ በሉ፦ በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፥ ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነ እንዲሁም በምድር ይሁን። 'የዕለት ምግባችንን በየዕለቱ ስጠን። "እኛም የበደለንን ሁሉ ይቅር እንድንል በደላችንን ይቅር በለን፤ አቤቱ፥ ወደ ፈተና አታግባን፤ ከክፉ ሁሉ አድነን እንጂ።”

እንዲህም አላቸው፥ “ከመካከላችሁ ወዳጅ ያለው ሰው ቢኖር በመንፈቀ ሌሊትም ወደ እርሱ ሄዶ እንዲህ ቢለው:- “ወዳጄ ሆይ ሦስት እንጀራ አበድረኝ። 'ወዳጄ ከመንገድ መጥቶብኛልና የማቀርብለት የለኝም። ያ ወዳጁም ከውስጥ ሆኖ፦ “አትዘብዝበኝ፤ ደጁን አጥብቀን ዘግተናል፤ ልጆችም ከእኔ ጋር በአልጋ ላይ ተኝተዋል እሰጥህ ዘንድ መነሳት አልችልም” ይለዋልን? ወዳጁ ስለሆነ ሊሰጠው ባይነሣ እንኳ እንዳይዘበዝበው ተነሥቶ የወደደውን ያህል ይሰጠዋል። እኔም እላችኋለሁ:-ለምኑ፥ ይሰጣችኋልም፤ ፈልጉ፥ ታገኛላች ሁም፣ ደጅ ምቱ፥ ይከፈትላችኋልም። የሚለምን ሁሉ ይሰጠዋልና፤ የሚፈልግም ያገኛ ልና፤ ደጅ ለሚመታም ይከፈትለታልና። “ከአናንተ መካከል ልጁ ዳቦ የሚለምነው አባት ቢኖር ድንጋይ ይሰጠዋልን? ዓሣ ቢለምነውስ በዓሣ ፋንታ እባብን ይሰጠዋልን? “ወይስ ዕንቍላል ቢለምነው በዕንቍላል ፋንታ ጊንጥ ይሰጠዋልን? “እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታን መስጠትን የምታውቁ ከሆነ፥ የሰማይ አባታችሁማ ለሚለምኑት መልካሙን ሀብተ መንፈስ ቅዱስ፤ እንዴት አብዝቶ ይሰጣቸው ይሆን?”

"ዲዳና ደንቆሮ፤ ጋኔንንም ያወጣ ነበር፤ ጋኔኑም በወጣ ጊዜ ዲዳና ደንቆሮ የነበረው ተና ገረ፤ ሰዎችም አደነቁ። ነገር ግን ከመካከላቸው፥ “በአጋንንት አለቃ በብዔል ዜቡል አጋንንትን ያወጣቸዋል” ያሉ ነበሩ፤ እርሱም መልሶ፥ “ሰይጣን ሰይጣንን ማውጣት እንደ ምን ይቻለዋል?” አላቸው። "ሌሎችም ሊፈትኑት ከእርሱ ዘንድ ከሰማይ ምልክትን ይፈልጉ ነበር። “እርሱ ግን የሚያስቡትን ዐወቀባቸውና እንዲህ አላቸው፥ “እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁሉ ትጠፋለች፤ ቤትም እርስ በርሱ ቢለያይ ያ ቤት ይወድቃል። ።ሰይጣንስ እርስ በርሱ ከተለያየ መንግሥቱ እንዴት ይጸናል? በአጋንንት አለቃ በብዔል ዜቡል አጋንንትን ያወጣል ትላላችሁና.........


👉2 ቆሮንጦስ 2:1-8
👉1 ጴጥሮስ 5:9-ፍጻሜ
👉ሐዋ.ሥራ 16:14-16


👉ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ (እምቅድመ ዓለም)

ምስባክ
መዝሙር 65:13-14


እበውዕ ቤተከ ምስለ መባዕየ

ወእሁብ ብፅዓትየ ዘነበብኩ በአፉየ

ዘእቤ በከናፍርየ አመ ምንዳቤየ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

01 Feb, 18:02


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ጥር 25 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕተ ሮሜ
2.ቅዱሳን ባስልዮስና ጎርጎርዮስ
3.ብፁዕ አባ ዼጥሮስ ጽሙድ (ለምጽዋት ራሱን የሸጠ አባት)
4.ቅዱስ ሰብስትያኖስ ሰማዕት
5.ቅዱስ አስኪላ ሰማዕት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

01 Feb, 18:02


ዘሰንበተ ክርስቲያን
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 2:42-ፍጻሜ

ዐሥራ ሁለት ዓመትም በሞላው ጊዜ እንደ አስለመዱ ወደ ኢየሩሳሌም ለበዓል ወጡ። ሥራቸውንም ጨርሰው ተመለሱ፤ ሕፃኑ ጌታችን ኢየሱስ ግን በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፤ ዮሴፍና እናቱም አላወቁም ነበር። በመንገድም ከሰዎች ጋር ያለ መስሎአቸው ነበር፤ ያንድ ቀን መንገድንም ከሄዱ በኋላ ዕለቱን ከዘመዶቹ፥ ከሚያውቁትም ዘንድ ፈለጉት። ባላገኙትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። " ከዚህም በኋላ በሦስተኛው ቀን በቤተ መቅደስ በሊቃውንት መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውና ሲጠይቃቸው አገኙት። "የሰሙትም ሁሉ አስተዋይነቱንና አመላለሱን ያደንቁ ነበር። በአዩትም ጊዜ ደነገጡ፤ እናቱም፡ “ልጄ፥ ለምን እንዲህ አደረግኸን? እነሆ አባትህም፥ እኔም ስንፈልግህ ደከምን” አለችው። "እርሱም፥ “ለምን ትፈልጉኛላችሁ? በአባቴ ቤት ልኖር እንደሚገባኝ አላወቃችሁምን?” አላቸው። እነርሱ ግን የነገራቸውን ቃል አላስተዋሉም። "ከእነርሱም ጋር ሂዶ ወደ ናዝሬት ወረደ፤ ይታዘዝላቸውም ነበር፤ እናቱ ግን ይህን ሁሉ ነገር ትጠብቀው፥ በልብዋም ታኖረው፤ ነበር። ጌታችን ኢየሱስም በእግዚአብሔር ዘንድ፥ በሰውም ዘንድ፥ በጥበብና በአካል በሞገስም አደገ.........

👉2 ቆሮንጦስ 1:13-ፍጻሜ
👉1 ዮሐንስ 2:22-ፍጻሜ
👉ሐዋ.ሥራ 13:20-28

👉ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ


ምስባክ
መዝሙር 117:27-28

እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ

ግበሩ በዐለ በትፍሥሕት በኀበ እለ ያስተሐምምዎ

እስከ አቅርንቲሁ ለምሥዋዕ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

31 Jan, 19:01


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ጥር 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1አቡነ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት
2.ቅድስት ማርያ ግብጻዊት
3.ታላቁ አባ ቢፋ
4.አባ አብሳዲ ቀሲስ
5.ቅዱሳን ጻድቃነ ሐውዚን

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

13 Jan, 18:10


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ጥር 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.በዓለ ግዝረቱ ለክርስቶስ
2.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
3.ቅዱስ ኖኅ ጻድቅ
4.ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
5.አባ ሙሴ ገዳማዊ
6.አባ ወርክያኖስ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

12 Jan, 17:40


05/05/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ዮሐንስ 18:23-28

ጲላጦስም እንደገና ወደ ፍርድ አደባባይ ገብቶ ጌታችን ኢየሱስን ጠራና፥ “የአይሁድ ንጉሥ አንተ ነህን?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም፥ “ይህን የምትናገር ከራስህ ነውን? ወይስ ስለ እኔ የነገረህ ሌላ አለን?” ብሎ መለሰለት። ጲላጦስም መልሶ፥ “እኔ አይሁዳዊ ነኝን? ለእኔ አሳልፈው የሰጡህ ወገኖችህና ሊቃነ ካህናት አይደሉምን? ኧረ ምን አድርገሃል?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም፥ “የእኔ መንግሥት ከዚህ ዓለም አይደለችም፤ መንግሥቴስ በዚህ ዓለም ብትሆን ኖሮ ለአይሁድ እንዳልሰጥ አሽከሮቼ በተዋጉልኝ ነበር፤ አሁንም መንግሥቴ ከዚህ አይደለችም” ብሎ መለሰለት። ጲላጦስም፥ “እንግዲያ አንተ ንጉሥ ነህን?” አለው፤ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፥እኔ ንጉሥ እንደ ሆንሁ አንተ ራስህ ትላለህ፤ እኔ ስለዚህ ተወለድሁ፤ ስለዚህም ለእውነት ልመሰክር ወደ ዓለም መጣሁ፤ ከእውነት የሆነ ሁሉ ቃሌን ይሰማኛል” አለው............

👉ዕብራውያን 2:11-ፍጻሜ
👉ያዕቆብ 3:5-13
👉ሐዋ.ሥራ 7:55-ፍጻሜ


👉ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ ካልእ

ምስባክ
                    መዝሙር 83:6

እስመ መምህረ ህግ ይሁብ በረከተ

ወየኃውር እምኃይል ውስተ ኃይል

ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን

               ትርጉም

የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና

ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ

የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

12 Jan, 17:40


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥር 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አባ ማቴዎስ
2.ቅዱስ አውስግንዮስ አረጋዊ (ሰማዕት)
3.ቅድስት እስክንድርያ
4.ቅድስት አውስያ ሰማዕት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

12 Jan, 11:19


🛑 ለጥምቀት መዝሙር ተሰላፊዎች በሙሉ እሑድ እና ሰኞ የመጨረሻ ሰልፍ ስለሚሰራ ሁላችሁም ግዴታ መገኘት አለባችሁ።

መዝሙር ክፍል ‼️

#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

12 Jan, 03:08


የገና ትኬት የወሰዳችሁ አባላት ዛሬ ለትምህርት ስትመጡ አደራ ይዛችሁ እንድትመጡ ። እስካሁን ሰብስበን ስላልጨረስን ተግዳሮቶች እየገጠሙን ነው ስለዚህ ሁላችሁም ይዛችሁ እንድትመጡ ።

ከመምህራኖቻችሁ የተቀበላችሁ ለመምህሩ ወይም ለክፍል ተወካይ ከኤልሳ የወሰዳችሁ ለራሷ እና ለዳግም ወንድወሰን ፣ ለዮሴፍ ደምስስ መስጠት ትችላላችሁ ።

#ማህበራዊ_አገልግሎት_ክፍል ( በጎ አድራጎት )
#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

11 Jan, 18:02


፩ መዝሙር ዘልደት
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 2:1-13

በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በይሁዳ ክፍል በቤተ ልሔም ጌታችን ኢየሱስ በተወለደ ጊዜ፥ እነሆ፥ ሰብአ ሰገል ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ። ፤እንዲህ ሲሉ፥ “ኮከቡን በምሥራቅ አይተን እንሰግድለት ዘንድ መጥተናልና፥ የተወ ለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው?” ፤ንጉሥ ሄሮድስም በሰማ ጊዜ ደነገጠ፤ ኢየሩሳሌምም በመላዋ ከእርሱ ጋር ደነገጠች። ፤የካህናት አለ ቆችንና የሕዝቡን ጻፎች ሁሉ ሰብስቦ “ክርስቶስ በየት ይወለዳል?” ብሎ ጠየቃቸው። እንዲህም አሉት፤ “በይሁዳ ክፍል በቤተ ልሔም ነው፤ በነቢይ እንዲህ ተብሎ ተጽፎአ ልና። የይሁዳ ምድር አንቺ ቤተ ልሔም ከይ ሁዳ አለቆች፤ ከቶ አታንሽም፤ ሕዝቤን እስራ ኤልን የሚጠብቅ ንጉሥ ከአንቺ ይወጣልና።” ከዚህም በኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገልን በስውር ጠራቸው፤ ኮከቡ የታየበትንም ዘመን ከእነርሱ ተረዳ። “ሂዳችሁ የዚያን ሕፃን ነገር ርግ ጡን መርምሩ፤ ያገኛችሁትም እንደ ሆነ እኔም መጥቼ እሰግድለት ዘንድ በእኔ በኩል ተመልሳችሁ ንገሩኝ” ብሎ ወደ ቤተ ልሔም ሰደዳቸው። እነርሱም ከንጉሡ ሰምተው ሄዱ፤ እነሆ፥ በምሥራቅ ያዩት ኮከብ ሕፃኑ በአለበት ቦታ ላይ ደርሶ እስኪቆም ድረስ ይመራቸው ነበር። ፤ኮከቡንም አይተው ታላቅ ደስታ ደስ አላቸው።ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አገኙት፤ ወድቀውም ሰገዱለት፤ ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው ወርቅና ዕጣን፥ ከርቤም፥ እጅ መንሻ አቀረቡለት። ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ነገራ ቸው፤ በሌላ መንገድም ወደ ሀገራቸው ሄዱ........

👉ሮሜ 11:25-ፍጻሜ
👉1 ዮሐንስ 2:1-9
👉ሐዋ.ሥራ 7:17-23

👉ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ


ምስባክ
መዝሙር 88:27-28

ወአነሂ በኵርየ እሬስዮ

ወልዑል ውእቱ እምነገሥተ ምድር

ወለዓለም አዐቀብ ሎቱ ሣህልየ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

11 Jan, 18:02


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥር 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ
(ፍቁረ እግዚእ)
2.አባ ናርዶስ ጻድቅ (ዘደብረ ቢዘን)
3.ቅዱስ ጊዮርጊስ
4.ቅዱስ ማርቴና

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

10 Jan, 17:31


03/05/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 2:13-ፍጻሜ

እነርሱም ከሄዱ በኋላ እነሆ፥ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ፥ “ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይሻዋልና ተነሣ፤ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ምድረ ግብፅ ሽሽ፤ እስክነግርህም ድረስ በዚያ ኑር” አለው፤ "እርሱም በሌሊት ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ ግብፅ ሄደ። ።ከእግዚአብሔር ዘንድ “ልጄን ከግብፅ ጠራሁት” ተብሎ በነቢይ የተ ነገረው ይፈጸም ዘንድ፣ ሄሮድስም እስኪሞት ድረስ በዚያ ኖረ።

ከዚህም በኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገል እንደ ተዘባበቱበት ባየ ጊዜ እጅግ ተቈጣና ጭፍራዎቹን ልኮ ከሰብአ ሰገል እንደ ተረዳው ዘመን ልክ ሁለት ዓመት የሆናቸውን፥ ከዚያም የሚያንሱትን፥ በቤተ ልሔምና በአውራጃዎችዋ ሁሉ የነበሩትን ሕፃናት አስገደለ። "ያንጊዜ፥ በነቢዩ በኤርምያስ የተነገረው ተፈጸመ፤ እንዲህ ሲል፦ “ራሔል ስለ ልጆችዋ ስታለቅስ ብዙ ልቅሶና ዋይታ በራማ ተሰማ፣ መጽናናትንም እንቢ አለች፤ ልጆችዋ የሉምና።”

“ሄሮድስም በሞተ ጊዜ እነሆ፥ የእግዚእ ብሔር መልአክ በግብፅ ሀገር ለዮሴፍ በሕ ልም ታየው። እንዲህ ሲል፡ “የሕፃኑን ነፍስ የሚሹ ሙተዋልና፥ ተነሥተህ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ እስራኤል ሀገር ሂድ።” እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ እስራኤል ምድር ገባ። “አርኬላኦስም በአባቱ በሄሮድስ ፋንታ በይሁዳ እንደ ነገሠ በሰማ ጊዜ፥ ወደዚያ ለመሄድ ፈራ፤ በሕልምም ተገልጦለት ወደ ገሊላ አውራጃ ሄደ። በነቢያት “ልጄ ናዝራዊ ይባላል” የተባለው ይፈጸም ዘንድ ናዝሬት ወደ ምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ.........


👉ሮሜ 11:25-ፍጻሜ
👉1 ጴጥሮስ 2:1-11
👉ሐዋ.ሥራ 28:17-ፍጻሜ


👉ቅዳሴ  ዘእግዝእትነ ማርያም  (ጐሥዓ) 
 

                                    ምስባክ
                            መዝሙር 43:22-23

እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኩሎ አሚረ

ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ

ንቃዕ እግዚኦ ለምንት ትነውም

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

10 Jan, 17:20


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥር 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1."144 ሺ" ቅዱሳን ሕጻናት
2.አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
3.አባ አሞን መስተጋድል

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

10 Jan, 04:44


ከሞት በኋላ ነፍስ እስከፍርድ ቀን ድረስ ትሞታለችን/ትጠፋለችን? – Telegraph

ከላይ ያለውን ሊንክ ነክታችሁ ሙሉውን ታነቡት ዘንድ ጋበዝናችሁ

#ወቅታዊ_ትምህርት_ክፍል
#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

09 Jan, 19:54


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥር 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አቤል ጻድቅ
2.ቅዱስ ቴዎናስ ሊቀ ዻዻሳት
3.ቅዱስ አላኒቆስ ሰማዕት
4.ቅድስት ሳቤላ ነቢዪት
5.ቅዳሴ ቤቷ ለድንግል (በደብረ አባ ሲኖዳ)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

09 Jan, 19:54


02/05/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 23:13-23

እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ ጸሎታችሁን በማብዛት ምክንያት የመበለቶችን ገንዘብ ስለምትበሉ ወዮላችሁ! ስለዚህ ጽኑ ፍርድን ትቀበላላችሁ። እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ መንግሥተ ሰማያትን በሰው ፊት ስለምትዘጉ ወዮላችሁ! እናንተም አትገቡም፤ የሚገቡትንም ከመግባት ትከለክሉአቸዋላችሁ። እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳው ያን፥ አንድን ሰው ለማሳመን ባሕሩንና የብሱን ስለምትዞሩ ወዮላችሁ! ካመነም በኋላ ከእናንተ ይልቅ ሁለት እጥፍ የገሃነም ልጅ ታደርጉታላችሁ። "በቤተ መቅደስ የሚምል ኀጢአት የለበትም፤ በቤተ-መቅደስ ወርቅ የሚምል ግን ይበድላል የምትሉ ዕውራን መሪዎች እናንተ ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ ወዮላችሁ! ”እናንተ ደንቆሮዎችና ዕውሮች፥ የትኛው ይበልጣል? ወርቁ ነውን? ወይስ ወርቁን የሚቀድ ሰው ቤተ መቅደስ? ፤ደግማችሁም በመሠዊ ያው የሚምል አይበድልም፤ በላዩ በአለው በመ ሥዋዕቱ የሚምል ግን ይበድላል ትላላችሁ። "እናንተ ሰነፎችና ዕውራን፥ የትኛው ይበልጣል? መሥዋዕቱ ነውን? ወይንስ መሥዋዕቱን የሚቀድሰው መሠዊያው? በመሠዊያው የሚምል በእርሱ ይምላል፤ በእርሱ ላይም ባለው ሁሉ ይምላል። “በቤተ መቅደስም የሚምል በእርሱና በውስጡ በሚኖረው ሁሉ ይምላል.....

👉ዕብራውያን 11:1-8
👉1 ዮሐንስ 3:6-13
👉ሐዋ.ሥራ 12:18-ፍጻሜ

👉ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)


ምስባክ
መዝሙር 93:21-22

ወይንዕዋ ለነፍሰ ጻድቅ

ወይኴንን ደመ ንጹሐ

ወኮነኒ እግዚአብሔር ፀወንየ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

09 Jan, 18:16


🛑 የልብስ ስፌት ሙያ ኖሯችሁ ሰንበት ትምህርት ቤታችሁን በሙያ ማገዝ የምትፈልጉ ወንድም እና እህቶች በሙሉ በውስጥ መስመር አናግሩን ‼️

👉 @Yeenatuhab

#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

08 Jan, 17:23


01/05/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 21:33-ፍጻሜ

“ሌላ ምሳሌ ስሙ፤ ባለቤት ሰው ወይንን ተክለ፡ ቅጥርም ቀጠረለት፤ መጭመቂያም አስቆፈረለት ግንብም ሠራለት፤ ለገባሮችም ሰጥቷአየው ሄደ የሚያፈራበት ወራት በደረሰ ጊዜም፥ ከወይኑ ፍሬ ያመጡለት ዘንድ አገልጋዮችን ወደ ገባሮቹ ላከ። ገባሮቹም አገልጋዮ ቹን ይዘው፥ አንዱን በበትር ደበደቡት፤ አንዱንም ገደሉት፤ ሌላውንም በድንጋይ መቱት። ከዚያም በኋላ ከቀደሙት የሚበዙ ሌሎች አገልጋዮችን ላከ፤ እነርሱንም እንዲሁ አደረጉባቸው። በኋላም ልጄንስ ይፈሩት ይሆናል ብሎ ልጁን ላከ። ገባሮቹም ልጁን ባዩት ጊዜ እርስ በርሳቸው፦ እነሆ፥ ወራሹ ይህ ነው፤ ኑ እንግደለውና ርስቱን እንውረስ ተባባሉ። ይዘውም ከወይኑ ቦታ ወደ ውጭ አውጥተው ገደሉት። “እንግዲህ የወይኑ ቦታ ባለቤት በመጣ ጊዜ እነዚህን ገባሮች ምን ያደርጋቸዋል?” እነርሱም፥ “ክፉዎችን በክፉ ያጠ ፋቸዋል፤ ወይኑንም በየጊዜው ፍሬውን ለሚሰ ጡት ለሌሎች ገባሮች ይሰጣል” አሉት።

ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፡ “በመጻሕፍት ያለውን ያነበባችሁበት ጊዜ የለ ምን? ግንበኞች የናቁአት ድንጋይ የማዕዘን ራስ ሆነች፤ ይህቺም ከእግዚአብሔር ዘንድ ሆነች፤ ለዐይኖቻችንም ድንቅ ናት። "ስለዚህም እላ ችኋለሁ፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ትወሰዳለች፤ ፍሬዋንም ለሚያደርጉ ለአሕዛብ ትሰጣለችበዚያችም ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ይቀጠቀጣል፤ በላዩ የምትወድቅበትንም ትፈጨዋለች።

የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያንም ምሳሌዎቹን በሰሙ ጊዜ፥ ስለ እነርሱ እንደተናገረ ዐወቁ። ሊይዙትም ሲፈልጉ ሕዝቡን ፈሩአቸው፤ በእነርሱ ዘንድ እንደ ነቢይ ነበርና.........

👉ዕብራውያን 11:32-ፍጻሜ
👉1 ጼጥሮስ 4:12-ፍጻሜ
👉ሐዋ.ሥራ 7:51  አዲ 8:3


👉ቅዳሴ  ዘወልደ ነጎድጓድ ( ኀቤከ )

ምስባክ
መዝሙር 20:3-4

እስመ በጻሕኮ በበረከት ሠናይ

ወአንበርከ አክሊለ ዲበ ርእሱ ዘእምዕንቍ ክቡር

ሐይወ ሰአለከ ወወሀብኮ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

08 Jan, 17:23


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥር 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ እስጢፋኖስ ቀዳሜ ሰማዕት (ሊቀ ዲያቆናት)
2.ቅዱሳን ሰማዕታተ አክሚም
3.ቅዱሳን ዲዮስቆሮስ ወሰከላብዮስ
4.ቅዱስ ለውንድዮስ ሰማዕት
5.አባ መቃርስ ሊቀ ዻዻሳት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

07 Jan, 22:31


የጌታችን የልደት የበዓል መርሐ ግብር በክብረ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ተካሔደ

#ማኅበራዊ_ድህረገፅና_መረጃና_ሚዲያ_ክፍል
#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

05 Jan, 17:54


28/04/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 1:1-18

የዳዊት ልጅ፥ የአብርሃም ልጅ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ መጽሐፍ፤ ፤አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ። 'ይሁዳም ከትእማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ፤ ፋሬስም ኤስሮምን ወለደ፤ ኤስሮምም አራምን ወለደ። አራምም አሚናዳብን ወለደ፤ አሚናዳብም ነአሶንን ወለደ፤ ነአሶንም ሰልሞንን ወለደ። ሰልሞንም ከራኬብ ቦኤዝን ወለደ፤ ቦኤዝም ከሩት ኢዮቤድን ወለደ፤ ኢዮቤድም እሴይን ወለደ። ፤እሴይም ንጉሥ ዳዊትን ወለደ።

፤ንጉሥ ዳዊትም ከኦርዮ ሚስት ሰሎሞንን ወለደ፤ ሰሎሞንም ሮብዓምን ወለደ፤ ሮብዓ ምም አብያን ወለደ፤ አብያም አሳፍን ወለደ። አሳፍም ኢዮሳፍጥን ወለደ፤ ኢዮሳፍጥም ኢዮ ራምን ወለደ፤ ኢዮራምም ዖዝያንን ወለደ። ፤ዖዝያንም ኢዮአታምን ወለደ፤ ኢዮአታምም አካዝን ወለደ፤ አካዝም ሕዝቅያስን ወለደ። ፤ሕዝቅያስም ምናሴን ወለደ፤ ምናሴም አሞጽን ወለደ፤ አሞጽም፤ ኢዮስያስን ወለደ። “ኢዮስ ያስም በባቢሎን ምርኮ ጊዜ ኢኮንያንንና ወንድሞቹን ወለደ።

ከባቢሎን ምርኮም በኋላ ኢኮንያን ሰላትያልን ወለደ፤ ሰላትያልም ዘሩባቤልን ወለደ። “ዘሩባቤልም አብዩድን ወለደ፤ አብዩድም ኤልያቄምን ወለደ፤ ኤልያቄምም አዛርን ወለደ። አዛርም ሳዶቅን ወለደ፤ ሳዶቅም አኪምን ወለደ፤ አኪምም ኤልዩድን ወለደ። ኤልዩድም አልዓዛርን ወለደ፤ አልዓዛርም ማትያንን ወለደ፤ ማትያንም ያዕቆብን ወለደ። ያዕቆብም ክርስቶስ የተባለ ጌታ ኢየሱስ ከእርስዋ የተወለደ የማርያምን እጮኛ ዮሴፍን ወለደ።

እንግዲህ ትውልድ ሁሉ ከአብርሃም እስከ ዳዊት ዐሥራ አራት ትውልድ፥ ከዳዊትም እስከ ባቢሎን ምርኮ ዐሥራ አራት ትውልድ፥ ከባቢሎንም ምርኮ እስከ ክርስቶስ ዐሥራ አራት ትውልድ ነው። ትውልድም ሁሉ ከአ ብርሃም እስከ ክርስቶስ ዐርባ ሁለት ትውልድ ነው.........


👉ሮሜ 8:3-18
👉1 ዮሐንስ 4:1-9
👉ሐዋ.ሥራ 3:22-ፍጻሜ


👉ቅዳሴ  ዘእግዝእትነ  (ጐሥዓ) 

                                ምስባክ
                        መዝሙር 75:15-16

የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቀ ዓረብ

ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ

ወኵሎ ዓሚረ ይድኅርዎ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

05 Jan, 17:54


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ታሕሳስ 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አማኑኤል አምላካችን
2.በዓለ ጌና ስቡሕ
3.ዕለተ ማርያም ድንግል
4."174" ሰማዕታት (የቅዱስ ዻውሎስ ማሕበር)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Jan, 16:53


ግጻዌ ዘኖላዊ
                    
  የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                          ዮሐንስ 10:1-22

    “እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ ወደ በጎች ስፍራ በበሩ የማይገባ፥ በሌላም በኩል የሚ ገባ ሌባ፥ ወንበዴም ነው። በበሩ የሚገባ ግን የበጎች ጠባቂ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍ ትለታል፤ በጎቹም ቃሉን ይሰሙታል፤ እር ሱም በጎቹን በየስማቸው ይጠራቸዋል፤ አው ጥቶም ያሰማራቸዋል። 'ሁሉንም አውጥቶ ባሰ ማራቸው ጊዜ በፊት በፊታቸው ይሄዳል፤ በጎ ቹም ይከተሉታል፤ ቃሉን ያውቃሉና። *ሌላ ውን ግን ይሸሹታል እንጂ አይከተሉትም፤ የሌ ላውን ቃሉን አያውቁምና።” ጌታችን ኢየሱ ስም ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ እነርሱ ግን የነገ ራቸውን አላወቁም። "ዳግመኛም ጌታችን ኢየሱስ እንዲህ አላ ቸው፥ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ የበጎች በር እኔ ነኝ። #ከእኔ በፊት የመጡ ሁሉ ሌቦ ችና ወንበዴዎች ናቸው፤ ነገር ግን፣ በጎች አልሰሙአቸውም። እውነተኛዉ የበጎች በር እኔ ነኝ፤ በእኔ በኩልም የሚገባ ይድናል፤ ይገ ባልም ይወጣልም፤ መሰማርያም ያገኛል። ፤ሌባ ግን ሊሰርቅና ሊያርድ፥ ሊያጠፋም ካልሆነ በቀር አይመጣም፤ እኔ ግን የዘለዓለም፤ ሕይ ወትን እንዲያገኙ፥ እጅግም እንዲበዛላቸው መጣሁ። “ቸር ጠባቂ እኔ ነኝ፤ ቸር ጠባቂ ስለ በጎቹ ነፍሱን ይሰጣል። "ጠባቂ ያይደለ፥ በጎ ቹም ገንዘቡ ያይደሉ ምንደኛ ግን፥ ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵ ላም መጥቶ በጎቹን ይነጥቃቸዋል፥ ይበትናቸዋ ልም። "ምንደኛስ ይሸሻል፤ ስለ በጎቹም አያ ዝንም፤ ምንደኛ ነውና። "ቸር ጠባቂ እኔ ነኝ፤ የእኔ የሆኑትን መንጋዎቼን አውቃለሁ፤ የእኔ የሆኑትም ያውቁኛል። አብ እኔን እንደሚያው ቀኝ እኔም አብን አውቀዋለሁ፤ ለበጎችም ቤዛ አድርጌ ሰውነቴን አሳልፌ እሰጣለሁ። "ከዚህ ቦታ ያይደሉ ሌሎች በጎችም አሉኝ፤ እነር ሱንም ወደዚህ አመጣቸው ዘንድ ይገባኛል፤ ቃሌንም ይሰሙኛል፤ ለአንድ እረኛም አንድ መንጋ ይሆናሉ። ”ስለዚህም፤ አብ ይወድደ ኛል፥ እንደ ገና አስነሣት ዘንድ እኔ ነፍሴን እሰ ጣለሁና። *ከእኔ ማንም አይወስዳትም፤ ነገር ግን እኔ በፈቃዴ እሰጣታለሁ፤ እኔ ላኖራት ሥልጣን አለኝ፤ መልሼ እወስዳት ዘንድ ሥልጣን አለኝና፤ ይህንም ትእዛዝ ከአባቴ ተቀበ ልሁ።” አይሁድ ለሁለተኛ ጊዜ ስለ መለያየታቸው "ስለዚህም ነገር አይሁድ እንደገና እርስ በር ሳቸው ተለያዩ። “ከእነርሱም ብዙዎች፥ “ጋኔን ይዞት ያብዳል፤ ለምንስ ታዳምጡታላችሁ?” አሉ። ሌሎችም ይህ ነገር ጋኔን ከያዘው ሰው የሚገኝ አይደለም፤ ጋኔን የዕዉሮችን ዐይን ማብራት ይችላልን?” አሉ..........

👉ዕብራውያን 13:16-ፍጻሜ
👉1 ጴጥሮስ 2:21-ፍጻሜ
👉ሐዋ.ሥራ 11:22-ፍጻሜ


👉ቅዳሴ ዘእግዚእነ

ምስባክ
መዝሙር 78:1-2

ኖላዊሆሙ ለእስራኤል ለእስራኤል አጽምዕ

ዘይርዕዮሙ ከመ አባግዐ ዮሴፍ


ዘይነብር ላዕለ ኪሩቤል አስተርእየ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Jan, 16:10


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ታሕሳስ 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አብሳዲ ሰማዕት
2.አባ አላኒቆስ ሰማዕት
3.አባ በግዑ ጻድቅ
4.አባ ፊልዾስ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Jan, 06:39


የገና ትኬት የወሰዳችሁ አባላት ዛሬና ነገ ለትምህርት ስትመጡ አደራ ይዛችሁ እንድትመጡ ። የልደት በዓል ማክሰኞ እንደመሁኑ ያለን ሁለት ቀን ነው ።በዚህች ሁለት ቀን ሁላችሁም ይዛችሁ እንድትመጡ !!

ከመምህራኖቻችሁ የተቀበላችሁ ለመምህሩ ወይም ለክፍል ተወካይ ከኤልሳ የወሰዳችሁ ለራሷ እና ለዳግም ወንድወሰን ፣ ለዮሴፍ ደምስስ መስጠት ትችላላችሁ ።

#ማህበራዊ_አገልግሎት_ክፍል ( በጎ አድራጎት )
#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

03 Jan, 20:05


26/04/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 25:1-14

ያንጊዜም መንግሥተ ሰማያት መብራታቸውን ይዘው ሙሽራውን ለመቀበል የወጡ ዐሥሩን ደናግል ትመስላለች። ከእነርሱም ውስጥ አምስቱ ሰነፎች፥ አምስቱም ልባሞች ነበሩ። ሰነፎቹ መብራታቸውን ይዘው ዘይት አልያዙም ነበር። ልባሞቹ ግን ከመብራታቸው ጋር በማሰሮቻቸው ዘይት ይዘው ነበር። ሙሽራውም በዘገየ ጊዜ ሁሉም አንቀላፉና ተኙ። መንፈቀ ሌሊት በሆነም ጊዜ “እነሆ ሙሽራ መጣ፤ ልትቀበሉት ውጡ” የሚል ጩኸት ሆነ። ያንጊዜ እነዚያ ደናግል ሁሉ ነቁና መብራታቸውን አዘጋጁ። እነዚያ ሰነፎችም ልባሞችን፦ መብራታችን ሊጠፋብን ነውና ከዘይታችሁ ስጡን አሉአቸው። ልባሞ ችም፦ ለእኛና ለእናንተ የሚበቃ የለም፤ ነገር ግን ወደሚሸጡ ሂዱና ለራሳችሁ ግዙ ብለው መለሱላቸው። ሊገዙም እንደ ሄዱ ሙሽራው መጣ፤ እነዚያም የተዘጋጁት ከእርሱ ጋር ወደ ሰርጉ ገቡ፤ ደጁም ተዘጋ። በኋላም እነዚያ ደናግል መጥተው፦ አቤቱ አቤቱ ክፈትልን አሉ። እርሱ ግን መልሶ፦ እውነት እላች ጓለሁ፤ አላውቃችሁም አላቸው። "እንግዲህ ትጉ፤ የሰው ልጅ የሚመጣባትን ቀኒቱንና ሰዓ ቲቱን አታውቁምና.........

👉1 ቆሮንጦስ 7:34-ፍጻሜ
👉1 ዮሐንስ 5:14-ፍጻሜ
👉ሐዋ.ሥራ 16:14-16


👉ቅዳሴ  ዘወልደ ነጎድጓድ ( ኀቤከ )

                ምስባክ
            መዝሙር 44:9-10

አዋልደ ንግሥት ለክብርከ

ወትቀውም ንግሥት በየማንከ

በአልባሰ ወርቅ ዑፅፍት ወኁብርት

              ትርጉም

የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው

በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና፡

ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

03 Jan, 20:05


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ታሕሳስ 26 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅድስት አንስጣስያ ሰማዕት
2.ቅዱስ አቦሊ ጻድቅ
3.ቅድሰት ዮልያና ሰማዕት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

02 Jan, 18:53


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ታሕሳስ 25 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱሳን 5ቱ መቃብያን
2.ቅዱስ ዮሐንስ ከማ (እና የተቀደሰች ሚስቱ)
3.ቅዱስ ዳንኤል መነኮስ
4.ቅዱስ ኒቆላዎስ መኮንን

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

02 Jan, 18:53


25/04/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 13:36-44

ከዚህም በኋላ ሕዝቡን ትቶ ወደ ቤት ገባ፤ ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ ቀርበው “የእርሻውን እንክርዳድ ምሳሌ ተርጒምልን” አሉት። እርሱም መልሶ አላቸው፤ “መልካም ዘርን የዘራ የሰው ልጅ ነው። እርሻውም ዓለም ነው፤ መልካሙም ዘር የመንግሥት ልጆች ናቸው፤ እንክርዳዱም የክፉው ልጆች ናቸው። የዘራውም ጠላት ዲያብሎስ ነው፤ መከሩም የዓለም ፍጻሜ ነው፤ አጫጆ ቹም መላእክት ናቸው። “እንግዲህ አስቀድሞ እንክርዳዱን እንደሚለቅሙት፥ በእሳትም እንደሚያቃጥሉት በዚህ ዓለም ፍጻሜም እንዲሁ ይሆናል። የሰው ልጅም መላእክቱን ይልካል፤ ከመንግሥቱም ዐላውያንንና በደልን የሚያደርጉትን ሁሉ ይሰበስባሉ። ወደ እሳት ጒድጓድም ይጥሉአቸዋል፤ በዚያም ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል። ያንጊዜም ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ፤ ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ......

👉ቲቶ 2:13-ፍጻሜ
👉1 ዮሐንስ 2:12-18
👉ሐዋ.ሥራ 4:31-ፍጻሜ


👉ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)

ምስባክ
መዝሙር 78:2-3


ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም

ወከዐዉ ደሞሙ ከመ ማይ ዐውዳ ለኢየሩሳሌም

ወኀጥኡ ዘይቀብሮሙ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

02 Jan, 07:16


24/04/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 18:1-12

      በዚያች ሰዓት ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ ቀርበው በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ የሚበልጥ ማን ይሆን? አሉት። ሕፃንም ጠርቶ በመካከላቸው አቆመ፡ እንዲህም አለ እውነት እላችኋለሁ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም። እንግዲህ እንደዚህ ሕፃን ራሱን የሚያዋርድ ሁሉ፥ በመንግሥተ ሰማያት የሚበልጥ እርሱ ነው። እንደዚህም ያለውን አንድ ሕፃን በስሜ የሚቀበል ሁሉ እኔን ይቀበላል፤ በእኔም ከሚያምኑ ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ሁሉ፥ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር። ወዮ ለዓለም ስለ ማሰናከያ፤ ማሰናከያ ሳይመጣ አይቀርምና፥ ነገር ግን በእርሱ ጠንቅ ማሰናከያ ለሚመጣበት ለዚያ ሰው ወዮለት። እጅህ ወይም እግርህ ብታሰናክልህ፥ ቈርጠህ ከአንተ ጣላት፤ ሁለት እጅ ወይም ሁለት እግር ኖሮህ ወደ ዘላለም እሳት ከምትጣል ይልቅ አንካሳ ወይም ጉንድሽ ሆነህ ወደ ህይወት መግባት ይሻልሀል። ዓይንህ ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት፤ ሁለት ዓይን ኖሮህ ወደ ገሃነመ እሳት ከምትጣል ይልቅ አንዲት ዓይን ኖራህ ወደ ሕይወት መግባት ይሻልሃል። ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁና። የሰው ልጅ የጠፋውን ለማዳን መጥቶአልና........


👉ኤፌሶን 4:11-ፍጻሜ
👉1 ጴጥሮስ 1: 13-17
👉ሐዋ.ሥራ 19:11-ፍጻሜ


👉ቅዳሴ ዘሐዋርያት

ምስባክ
መዝሙር 8:2-3

እም አፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሓተ

በእንተ ጸላኢ

ከመትንስቶ ለጸላኢ ወለገፋኢ

           ትርጉም

ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ

ስለ ጠላትህ

ጠላትንና ቂመኛን ለማጥፋት

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

02 Jan, 07:16


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


✞✞✞ ታኅሣሥ 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
2.ቅዱሳን ጸጋ ዘአብና እግዚእ ኃረያ
3.ቅዱስ አግናጥዮስ ሐዋርያ
4.ቅድስት አስቴር
5.አባ ፊሎንጐስ ሊቀ ዻዻሳት
6.አባ ዻውሊ ጻድቅ
7.ጻድቃን ቅዱሳን ዘከዲህ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

01 Jan, 08:30


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ ታሕሳስ 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ዳዊት ልበ አምላክ
2.አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
3.አባ ሳሙኤል ጻድቅ
4.አባ ስምዖን ጻድቅ
5.አባ ገብርኤል ጻድቅ
6.አባ ይስሐቅ ጻድቅ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

01 Jan, 08:30


23/04/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 22:31-ፍጻሜ


ስለ ሙታን መነሣት ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ እንዲህ ተብሎ የተነገረውን አላነበባችሁምን? እኔ እግዚአብሔር የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ እንግዲህ የሕያዋን አምላክ እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም።”

ሕዝቡም ሰምተው ትምህርቱን አደነቁ። ፈሪሳውያንም ሰዱቃውያንን ምላሽ እንዳሳ ጣቸው በሰሙ ጊዜ በአንድነት ወደ እሱ ተሰ በሰቡ። ከመካከላቸውም አንድ ሕግ ዐዋቂ ሊፈትነው ጠየቀው። “መምህር ሆይ፥ ከኦሪት ማንኛይቱ ትእዛዝ ትበልጣለች?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አለው፥ “አምላክህ እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ፥ በፍጹም ነፍስህ፥ በፍጹም ኀይልህ ውደደው። ታላቂቱና የመጀመሪያይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። የምትመስላት ሁለተኛይቱም ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትለው ናት። “ኦሪትና ነቢያት ሁሉ በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ጸን ተዋል።”

ፈሪሳውያንም ተሰብስበው ሳሉ ጌታችን ኢየሱስ እንዲህ ብሎ ጠየቃቸው፦ “ስለ ክርስቶስ ምን ትላላችሁ? የማን ልጅ ነው?” እነርሱም፥ “የዳዊት ልጅ ነው” አሉት። ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፥ “እንግዲያ እርሱ ራሱ ዳዊት በመንፈስ ቅዱስ እንዴት እንዲህ አለ? “ጌታ ጌታዬን፦ ጠላቶችህን ከእግርህ በታች እስከ አደርጋቸው ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው። እርሱ ራሱ ዳዊት “ጌታዬ” ያለው፥ እንግዲህ እንዴት ልጁ ይሆነዋል?” አንድም ቃል እንኳ ሊመልስለት የቻለ የለም፤ ከዚያች ቀንም ጀምሮ ማንም ሊጠይቀው አልደፈረም.......

👉2 ጢሞቶዎስ 2:8-12
👉1 ጴጥሮስ 5:2-8
👉ሐዋ.ሥራ 13:30-44

👉ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)

                                 ምስባክ
                         መዝሙር 18:12-13

ለስሒት መኑ ይሌብዋ

እምኅቡዓትየ አንጽሐኒ

ወእምነኪር መሐኮ ለገብርከ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

31 Dec, 09:22


22/04/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 1:3-57

ማርያምም በዚያ ወራት ተነሥታ ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ከተማ ፈጥና ወጣች፥ ወደ ዘካርያስም ቤት ገብታ ኤልሳቤጥን ተሳለመቻት። ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥ በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው። የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና። ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት። ማርያምም እንዲህ አለች ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፥ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤ የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤ ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጎአልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው። ምሕረቱም ለሚፈሩት እስከ ትውልድና ትውልድ ይኖራል። በክንዱ ኃይል አድርጎአል፤ ትዕቢተኞችን በልባቸው አሳብ በትኖአል፤ ገዥዎችን ከዙፋናቸው አዋርዶአል፤ ትሑታንንም ከፍ አድርጎአል፤ የተራቡትን በበጎ ነገር አጥግቦአል፤ ባለ ጠጎችንም ባዶአቸውን ሰዶአቸዋል። ለአባቶቻችን እንደ ተናገረ፥ ለአብርሃምና ለዘሩ ለዘላለም ምሕረቱ ትዝ እያለው እስራኤልን ብላቴናውን ረድቶአል። ማርያምም ሦስት ወር የሚያህል በእርስዋ ዘንድ ተቀመጠች ወደ ቤትዋም ተመለሰች......

👉2 ጢሞቴዎስ 1:8-ፍጻሜ
👉1 ዮሐንስ 4:9-18
👉ሐዋ.ሥራ 12:6-18


👉ቅዳሴ  ዘእግዝእትነ  (ጐሥዓ)  

ምስባክ
                        መዝ 44:16-17

ህየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ

ወትሰይሚዮሙ መላእክት ለኵሉ ምድር

ወይዘክሩ ስመኪ በኵሉ ትውልደ ትውልድ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

31 Dec, 09:22


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ታኅሣሥ 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ተአምረ ማርያም
2.ቅዱስ ደቅስዮስ ጻድቅ
3.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
4.ቅዱስ አንስጣስዮስ ሊቅ
5.አባ አርኬላዎስ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

29 Dec, 18:46


21/04/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 1:17-34

እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ፥ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል። ዘካርያስም መልአኩን እኔ ሽማግሌ ነኝ ምስቴም በዕድሜዋ አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ? አለው። መልአኩም መልሶ እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፤ እነሆም፥ በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ፥ ይህ ነገር እስከሚሆን ቀን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ መናገርም አትችልም አለው። ሕዝቡም ዘካርያስን ይጠብቁት ነበር፤ በቤተ መቅደስም ውስጥ ስለ ዘገየ ይደነቁ ነበር። በወጣም ጊዜ ሊነግራቸው አልቻለም፥ በቤተ መቅደስም ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፤ እርሱም ይጠቅሳቸው ነበር፤ ድዳም ሆኖ ኖረ። የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሄደ። ከዚህም ወራት በኋላ ሚስቱ ኤልሳቤጥ ፀነሰችና ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ በተመለከተበት ወራት እንዲህ አድርጎልኛል፡ ስትል ራስዋን አምስት ወር ሰወረች። በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ፥ ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ። መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት። እርስዋም ባየችው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው? ብላ አሰበች። መልአኩም እንዲህ አላት ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ። እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ። እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘላለም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም....

👉ገላትያ 2:1-14 አዲ ቆላስያሴ 4:1-ፍጻሜ
👉ይሁዳ 1:17-ፍጻሜ
👉ሐዋ.ሥራ 11:23-ፍጻሜ


👉ቅዳሴ  ዘእግዝእትነ  (ጐሥዓ)  

ምስባክ
                      መዝሙር 44:9


ወትቀውም ንግስት በየማንከ

በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኅብርት

ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ እዝነኪ

               ትርጉም

ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች

በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋ ተሸፋፍና

ልጄ ሆይ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

29 Dec, 16:17


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ታሕሳስ 21 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ኖላዊ ሔር
2.ቅዱስ በርናባስ ሐዋርያ
3.አባ ይስሐቅ ጻድቅ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

29 Dec, 10:53


በዛሬው ዕለት በሰ/ት/ቤታችን የተካሄደው የዝክረ አኃው መርሃ ግብር ይህንን ይመስል ነበር

#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

29 Dec, 10:53


በተጨማሪ ፕሮግራሙ በሰ/ት/ቤታችን የቲክቶክ ገፅ በቀጥታ ስርጭት ሲተላለፍ ነበር በዚህም በአጠቃላይ ዕይታ ከ 600 በላይ ሰው ተመልክቷል ።

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

29 Dec, 07:47


https://vm.tiktok.com/ZMkBHs3Ga/

የዛሬውን ፕሮግራም በሰ/ት/ቤታችን የቲክቶክ ገፅ በቀጥታ ስርጭት መከታተል ትችላላችሁ 👆

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

28 Dec, 18:26


ግጻዌ ዘብርሃን
                    
  የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                          ዮሐንስ 1:1-19

    በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ። ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። በእርሱ ሕይወት ነበረች፥ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረች። ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም።

ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምኑ ይህ ስለ ብርሃን ይመሰክር ዘንድ ለምስክር መጣ። ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ እንጂ፥ እርሱ ብርሃን አልነበረም። ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ይመጣ ነበር። በዓለም ነበረ፥ ዓለሙም በእርሱ ሆነ፥ ዓለሙም አላወቀውም። የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።

ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን። ዮሐንስ ስለ እርሱ መሰከረ እንዲህም ብሎ ጮኸ ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ከእኔ በፊት ነበረና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል፤ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነበረ።
እኛ ሁላችን ከሙላቱ ተቀብለን በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጥቶናልና፤ ሕግ በሙሴ ተሰጥቶ ነበርና ጸጋና እውነት ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ሆነ። መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው...........

👉ሮሜ 13:11-ፍጻሜ
👉1 ዮሐንስ 1:1-ፍጻሜ
👉ሐዋ.ሥራ 26:12-19


👉ቅዳሴ ዘአትናቴዎስ

ምስባክ
መዝሙር 42:3-4

ፈኑ ብርሃነከ ወጽድቀከ

እማንቱ ይምርሓኒ ወይሰዳኒ ደብረ መቅደስከ

ወውስተ አብያቲከ እግዚእ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

28 Dec, 18:25


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ታሕሳስ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ሐጌ ነቢይ
2.አባ አውጋንዮስ
3.ታውፊና ንግሥት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

28 Dec, 11:00


ቪዲዮውን በቲክቶክ ገፅ ይመልከቱ

https://vm.tiktok.com/ZMkkEYuXK/

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

28 Dec, 10:59


#ክብረ_ሃይማኖት
ታኅሳስ 19

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

06 Dec, 18:19


28/03/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማርቆስ 12:25-28


ከሙታንስ ሲነሡ በሰማያት እንዳሉ መላእክት ይሆናሉ እንጂ አያገቡም፥ አይጋቡምም። ስለ ሙታን ግን እንዲነሡ እግዚአብሔር እኔ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ እንዳለው በሙሴ መጽሐፍ በቍጥቋጦው ዘንድ የተጻፈውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም። እንግዲህ እጅግ ትስታላችሁ.......


👉ገላትያ 3:5-15  ዓዲ 2 ቆሮንጦስ 4:1-7
👉ያዕቆብ 2:21-ፍጻሜ
👉ሐዋ.ሥራ 3:12-17


👉ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)

ምስባክ
መዝሙር 96:11-12

በርህ ሠረቀ ለጻድቃን

ወለርቱዓነ ልብ ትፍሥሕት

ይትፌሥሑ ጻድቃን በእግዚአብሔር

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

06 Dec, 18:19


በስመ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ኅዳር 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አባ ሊቃኖስ ጻድቅ (ከተስዓቱ ቅዱሳን)
2.ቅዱስ ሰረባሞን ሰማዕት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

05 Dec, 17:51


27/03/2017
                    የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                          ሉቃስ 10:1-12

    ከዚህም በኋላ ጌታ ሌሎቹን ሰብዓ ሾመ፥ ሁለት ሁለትም አድርጎ እርሱ ሊሄድበት ወዳለው ከተማና ስፍራ ሁሉ በፊቱ ላካቸው።አላቸውም መከሩስ ብዙ ነው፥ቀ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዴህ የመከሩን ጌታ ለመከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት። ሂዱ፤ እነሆ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ። ኮረጆም ከረጢትም ጫማም አትያዙ፤ በመንገድም ለማንም እጅ አትንሡ። ወደምትገቡበት ቤት ሁሉ አስቀድማችሁ ሰላም ለዚህ ቤት ይሁን በሉ። በዚያም የሰላም ልጅ ቢኖር፥ ሰላማችሁ ያድርበታል፤ አለዚያም ይመለስላችኋል። በዚያም ቤት ከእነርሱ ዘንድ ካለው እየበላችሁና እየጠጣችሁ ተቀመጡ፤ ለሠራተኛ ደመወዙ ይገባዋልና። ከቤት ወደ ቤት አትተላለፉ። ወደምትገቡባትም ከተማ ሁሉ ቢቀበሉአችሁ፥ ያቀረቡላችሁን ብሉ በእርስዋም ያሉትን ድውዮችን ፈውሱና የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ቀረበች፡ በሉአቸው። ነገር ግን ወደምትገቡባት ከተማ ሁሉ ባይቀበሉአችሁ፥ ወደ አደባባይዋ ወጥታችሁ ከከተማችሁ የተጣበቀብንን ትቢያ እንኳን እናራግፍላችኋለን፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ግን ወደ እናንተ እንደ ቀረበች ይህን እወቁ በሉ እላችኋለሁ፥ በዚያን ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶም ይቀልላታል.....

ፊልሞና 1:1-ፍጻሜ
1 ጴጥሮስ 5:9-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 11:25-ፍጻሜ


ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም) አው ዮሐንስ አፈወርቅ (ናሁ ንዜኑ)

ምስባክ
መዝሙር 39:1-12


ጸኒሐ ጸናሕክዎ ለእግዚአብሔር

ሰምዐኒ ወተመይጠኒ

ወስምዐኒ ቃለ ስእለትየ

ትርጉም

ቆይቼ እግዚአብሔር ደጅ ጠናሁት

እርሱም ዘንበል አለልኝ

ጩኽቴንም ሰማኝ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

05 Dec, 17:51


በስመ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ኅዳር 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
2.አቡነ ተክለ ሐዋርያት ጻድቅ
3.ቅዱስ ፊልሞና ሐዋርያ
4.ቅዱስ ቀሌምንጦስ ሰማዕት
5.ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሰማዕት
6.አባ ገብረ ዮሐንስ ጻድቅ


ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Dec, 18:03


26/03/2017
                  የዕለቱ የወንጌል ክፍል

                    ሉቃስ 21:12-21

       ከዚህም ሁሉ በፊት እጃቸውን በላያችሁ ይጭናሉ ያሳድዱአችሁማል፤ ስለ ስሜም ወደ ምኵራብና ወደ ወኅኒ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ወደ ነገሥታትና ወደ ገዥዎችም ይወስዱአችኋል፤ ይህም ለምስክርነት ይሆንላችኋል። ሰለዚህ እንዴት እንድትመልሱ አስቀድማችሁ እንዳታስቡ በልባችሁ አኑሩት፤ ወደረኞቻችሁ ሁሉ ሊቃወሙና ሊከራከሩ የማይችሉትን አፍና ጥበብ እሰጣችኋለሁና። ወላጆችም ስንኳ ወንድሞችም ዘመዶችም ወዳጆችም አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ከእናንተም አንዳንዱን ይገድላሉ፤ በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ። ከራሳችሁም አንዲት ጠጉር ስንኳ አትጠፋም፤ በመታገሣችሁም ነፍሳችሁን ታገኛላችሁ። ኢየሩሳሌም ግን በጭፍራ ተከባ ስታዩ በዚያን ጊዜ ጥፋትዋ እንደ ቀረበ እወቁ.............

👉2 ቆሮንቶስ 6:1-12
👉1 ጴጥሮስ 1:7-9
👉ሐዋ.ሥራ 20:28-31


👉ቅዳሴ  ዘወልደ ነጎድጓድ ( ኀቤከ )

ምስባክ
መዝሙር 9:12-13

እስመ ተዘከረ ዘይትኀሠሥ ደሞሙ

ወኢረሥዐ ዐውያቶሙ ለነዳያን

ተሣሃለኒ እግዚኦ ወርኢ ዘከመ የሐሙኒ ጸላእትየ

ትርጉም

ደማቸውን የሚመራመር እርሱ አስቦአልና

የድሆችንም ጩኸት አልረሳምና

አቤቱ እዘንልኝ ጠላቶቼም የሚያመጡብኝን መከራ እይ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Dec, 18:03


በስመ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ኅዳር 26 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ
2.አቡነ ሃብተ ማርያም ንጹሕ
3.ቅዱሳን ሰማዕታተ ናግራን
4.ቅዱስ ሒሩት አረጋዊ
5.ቅዱሳን ቢላርያኖስ: ኪልቅያና ታቱስብያ (ሰማዕታት)
6.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘደሴተ ሰንሲላ
7.ቅድስት ዮስቴና ቡርክት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Dec, 04:41


በስመ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ኅዳር 25 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
2.ቅዱሳን ታቦትና ኖኅ (ወላጆቹ)
3.ቅዱስ ሮማኖስ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Dec, 04:41


25/03/2017
                        የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                           ማቴዎስ 10:16-32


      እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ። ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤ ለእነርሱና ለአሕዛብም ምስክር እንዲሆን፥ ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና።

ወንድምም ወንድሙን፥ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ ይገድሉአቸውማል። በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። በአንዲቱ ከተማም መከራ ቢያሳዩአችሁ ወደ ሌላይቱ ሽሹ፤ እውነት እላችኋለሁና፥ የሰው ልጅ እስኪመጣ ድረስ የእስራኤልን ከተማዎች አትዘልቁም። ደቀ መዝሙር ከመምህሩ፥ ባሪያም ከጌታው አይበልጥም። ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ፥ ባሪያም እንደ ጌታው መሆኑ ይበቃዋል። ባለቤቱን ብዔል ዜቡል ካሉት፥ ቤተሰዎቹንማ እንዴት አብዝተው አይሉአቸው እንግዲህ አትፍሩአቸው፤

የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለምና። በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ፤ በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ። ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ።

ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም። የእናንተስ የራሳችሁ ጠጉር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል። እንግዲህ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ..........

👉2 ቆሮንጦስ 7:4-12
👉1 ጴጥሮስ  4:12-ፍጻሜ
👉ሐዋ.ሥራ 5:11-17


👉ቅዳሴ  ዘወልደ ነጎድጓድ ( ኀቤከ )

                           ምስባክ
                   መዝሙር 67:23-24

ልሳነ ከለባቲከ ላዕለ ጸላዕቱ

አስተርአየ ፍናዊከ እግዚኦ

ፍናዊሁ ለአምላክነ ለንጉሥ ዘውስተ መቅደስ

                           ትርጉም

የውሾችህ ምላስ በጠላቶች ላይ ይሆን ዘንድ

የአምላኬ የንጉሥ መንገድ በመቅደሱ

አቤቱ መንገድህ ተገለጠ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

03 Dec, 08:59


https://vm.tiktok.com/ZMk1grh3o/

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

02 Dec, 16:29


24/03/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 13:36-43


በዚያን ጊዜ ሕዝቡን ትቶ ወደ ቤት ገባ። ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ ቀርበውየእርሻውን እንክርዳድ ምሳሌ ተርጕምልን አሉት። እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው መልካምን ዘር የዘራው የሰው ልጅ ነው፤ እርሻውም ዓለም ነው፤ መልካሙም ዘር የመንግሥት ልጆች ናቸው፤ እንክርዳዱም የክፉው ልጆች ናቸው፥ የዘራውም ጠላት ዲያብሎስ ነው፤ መከሩም የዓለም መጨረሻ ነው፥ አጫጆችም መላእክት ናቸው። እንግዲህ እንክርዳድ ተለቅሞ በእሳት እንደሚቃጠል፥ በዓለም መጨረሻ እንዲሁ ይሆናል። የሰው ልጅ መላእክቱን ይልካል፥ ከመንግሥቱም እንቅፋትን ሁሉ ዓመፃንም የሚያደርጉትን ይለቅማሉ፥ ወደ እቶነ እሳትም ይጥሉአቸዋል፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል.....

1 ጢሞቴዎስ 5:17-ፍጻሜ
ያዕቆብ 5:12-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 22:18-22  ዓዲ 12:6-12


ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)

ምስባክ
                        መዝሙር 102:20-22


ባርክዎ ለእግዚአብሔር ኵልክሙ መላእክቲሁ

ጽኑዓን ወኃያላን እለ ትገብሩ ቃሎ

ወእለ ትሰምዑ ቃለ ነገሩ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

02 Dec, 16:21


በስመ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ኅዳር 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1."24ቱ" ቅዱሳን ካህናተ ሰማይ (ሱራፌል)
2.ቅዱስ አዝቂር ሰማዕት
3."48" ሰማዕታት (ማሕበሩ)
4.አባ ዮሴፍ ዘሃገረ ጻን
5.ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጥዑመ ዜና
6.ቅዱስ ኪርያቅ ሰማዕት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

01 Dec, 18:43


23/03/2017
                      የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                      ማቴዎስ 10:32-ፍጻሜ


     ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ። በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም።

ሰውን ከአባቱ፥ ሴት ልጅንም ከእናትዋ፥ ምራትንም ከአማትዋ እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና፤ ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል። ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።

ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም ስለ እኔ የሚያጠፋ ያገኛታል። እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም......

ዕብራውያን 11:32-ፍጻሜ
2 ጴጥሮስ 1:19-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 10:23-32

ቅዳሴ  ዘወልደ ነጎድጓድ ( ኀቤከ )

                                    ምስባክ
                            መዝሙር 43:22-23


ወበኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አዕርክቲከ እግዚኦ

ወፈድፋደ ጸንዑ እምቀደምቶሙ

እኌልቆሙ ወእምኆፃ ይበዝኁ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

01 Dec, 18:43


በስመ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ኅዳር 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ቆርኔሌዎስ (ሐዋርያዊ ጻድቅ)
2.ቅዱስ አብድዩ ነቢይ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

30 Nov, 10:30


ቤተክርስቲያንን አንተውም ከቶ

ኅዳር 21 በደብረ ምጥማቅ …

https://vm.tiktok.com/ZMhKvuvFj/
https://vm.tiktok.com/ZMhKvjnK5/

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

30 Nov, 09:13


#ክብረ_ሃይማኖት

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

30 Nov, 09:13


#ክብረ_ሃይማኖት

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

30 Nov, 09:13


#ክብረ_ሃይማኖት

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

24 Nov, 17:48


16/03/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 14:7-17


የታደሙትንም የከበሬታ ስፍራ እንደ መረጡ ተመልክቶ ምሳሌ ነገራቸው እንዲህ ሲል ማንም ለሰርግ ቢጠራህ በከበሬታ ስፍራ አትቀመጥ፤ ምናልባት ከአንተ ይልቅ የከበረ ተጠርቶ ይሆናልና፡ አንተን እርሱንም የጠራ መጥቶ ለዚህ ስፍራ ተውለት ይልሃል፥ በዚያን ጊዜም እያፈርህ በዝቅተኛው ስፍራ ልትሆን ትጀምራለህ። ነገር ግን በተጠራህ ጊዜ፥ የጠራህ መጥቶ ወዳጄ ሆይ፥ ወደ ላይ ውጣ እንዲልህ፥ ሄደህ በዝቅተኛው ስፍራ ተቀመጥ፤ ያን ጊዜም ከአንተ ጋር በተቀመጡት ሁሉ ፊት ክብር ይሆንልሃል።

ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱንም የሚያዋርድ ከፍ ይላል።

የጠራውንም ደግሞ እንዲህ አለው ምሳ ወይም እራት ባደረግህ ጊዜ፥ እነርሱ ደግሞ በተራቸው ምናልባት እንዳይጠሩህ ብድራትም እንዳይመልሱልህ፥ ወዳጆችህንና ወንድሞችህን ዘመዶችህንም ባለ ጠጎች ጎረቤቶችህንም አትጥራ። ነገር ግን ግብዣ ባደረግህ ጊዜ ድሆችንና ጕንድሾችን አንካሶችንም ዕውሮችንም ጥራ፤ የሚመልሱት ብድራት የላቸውምና ብፁዕ ትሆናለህ፤ በጻድቃን ትንሣኤ ይመለስልሃልና። ከተቀመጡትም አንዱ ይህን ሰምቶ በእግዚአብሔር መንግሥት እንጀራ የሚበላ ብፁዕ ነው አለው። እርሱ ግን እንዲህ አለው አንድ ሰው ታላቅ እራት አድርጎ ብዙዎችን ጠራ....

👉2 ቆሮንጦስ 9:5-ፍጻሜ
👉1 ጴጥሮስ 5:2-12
👉ሐዋ.ሥራ 14:23-ፍጻሜ


👉ቅዳሴ ዘቄርሎስ

ምስባክ
                             መዝሙር 20:1-2


👉እግዚኦ በኃይልከ ይትፌሣሕ ንጉሥ

ወብዙኃ ይትሐሠይ በአድኅኖትከ

ፍትወተ ነፍሱ ወሀብኮ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

24 Nov, 17:48


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን!!!

†††ኅዳር 16ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አኖሬዎስ ጻድቅ (ንጉሠ ሮም)
2.አባ ዳንኤል ገዳማዊ
3.ቅዱስ አውሎጊስ መነኮስ
4.ቅድስት ጣጡስ ሰማዕት
5.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
6.ቅዱስ ኪስጦስ ሰማዕት
7.ቅዱስ ፊቅጦር ምዑዝ
8.አባ ዮሐንስ መሐሪ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

24 Nov, 17:47


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን!!!

†††ኅዳር 15 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ሚናስ ሰማዕት
2.ልደተ ቅዱስ ቂርቆስ
3.ብጽዕት ኢየሉጣ
4.አባ ሚናስ ዳግማይ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

22 Nov, 18:24


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን!!!

†††ኅዳር 14 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አባ ዳንኤል ገዳማዊ
2.አባ መርትያኖስ ካልዕ (ዘጠራክያ)
3.አባ ዮሐንስ ዘደብረ ቢዘን (ኤርትራ)
4.ቅድስት ደብረ ቀልሞን

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

22 Nov, 18:24


14/03/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ዮሐንስ 4:47-ፍጻሜ

እርሱም ኢየሱስ ከይሁዳ ወደ ገሊላ እንደ መጣ ሰምቶ ልጁ ሊሞት ስላለው ወደ እርሱ ሄደ ወርዶም እንዲፈውስለት ለመነው። ስለዚህም ኢየሱስ ምልክትና ድንቅ ነገር ካላያችሁ ከቶ አታምኑም አለው። ሹሙም ጌታ ሆይ፥ ብላቴናዬ ሳይሞት ውረድ አለው። ኢየሱስም ሂድ፤ ልጅህ በሕይወት አለ አለው። ሰውዬውም ኢየሱስ የነገረውን ቃል አምኖ ሄደ። እርሱም ሲወርድ ሳለ ባሮቹ ተገናኙትና ብላቴናህ በሕይወት አለ ብለው ነገሩት። እርሱም በጎ የሆነበትን ሰዓት ጠየቃቸው፤ እነርሱም ትናንት በሰባት ሰዓት ንዳዱ ለቀቀው አሉት። አባቱም ኢየሱስ ልጅህ በሕይወት አለ ባለው በዚያ ሰዓት እንደ ሆነ አወቀ፤ እርሱም ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር አመነ። ይህም ደግሞ ኢየሱስ ከይሁዳ ወደ ገሊላ መጥቶ ያደረገው ሁለተኛ ምልክት ነው.........

1ቆሮንጦስ 15:12-24
1 ጴጥሮስ 5:6-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 23:6-10


ቅዳሴ ዘባስልዮስ (እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ)

ምስባክ
መዝሙር 26:10-11

እስመ አቡየ ወእምየ ገደፉኒ

ወእግዚአብሔር ተወክፈኒ

ምርሀኒ እግዚኦ ፍኖተከ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

21 Nov, 17:59


13/03/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 25:31-ፍጻሜ

የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ፥ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል፤ አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ፤ እረኛም በጎቹን ከፍየሎች እንደሚለይ እርስ በርሳቸው ይለያቸዋል፥ በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል።

ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።


ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና።

ጻድቃንም መልሰው ይሉታል ጌታ ሆይ፥ ተርበህ አይተን መቼ አበላንህስ? ወይስ ተጠምተህ አይተን መቼ አጠጣንህ? እንግዳ ሆነህስ አይተን መቼ ተቀበልንህ? ወይስ ታርዘህ አይተን መቼ አለበስንህ? ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ አይተን መቼ ወደ አንተ መጣን? ንጉሡም መልሶ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ
ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል።

በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ። ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥ ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና።

እነርሱ ደግሞ ይመልሱና ጌታ ሆይ፥ ተርበህ ወይስ ተጠምተህ ወይስ እንግዳ ሆነህ ወይስ ታርዘህ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ መቼ አይተን አላገለገልንህም? ይሉታል።

ያን ጊዜ
እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም ብሎ ይመልስላቸዋልእነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ......

👉ዕብራውያን 12:22-25
👉ይሁዳ 1:14-17
👉ሐዋ.ሥራ 12:6-12


👉ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)

ምስባክ
መዝሙር 102:20-22


👉ባርክዎ ለእግዚአብሔር ኵልክሙ መላእክቲሁ

ጽኑዓን ወኃያላን እለ ትገብሩ ቃሎ

ወእለ ትሰምዑ ቃለ ነገሩ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

21 Nov, 17:58


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ኅዳር 13 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አእላፍ (99ኙ) ነገደ መላእክት
2.ቅዱስ አስከናፍር ሮማዊ
3."13ቱ" ግኁሳን አበው (ሽፍቶች የነበሩ)
4.ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘእንጽና
5.አባ ዘካርያስ ሊቀ ዻዻሳት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

20 Nov, 20:58


12/03/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 18:15-21


ወንድምህም ቢበድልህ፥ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፥ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው፤ ባይሰማህ ግን፥ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር አፍ ነገር ሁሉ እንዲጸና፥ ዳግመኛ አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ፤ እነርሱንም ባይሰማ፥ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፥ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ።

እውነት እላችኋለሁ፥ በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል። ደግሞ እላችኋለሁ

ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋልሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና........

ሮሜ 9:17-24
ይሁዳ 1:9-14
ሐዋ.ሥራ 20:28-31


ቅዳሴ ያዕቆብ ዘሥሩግ (ተንሥኡ) አው ዘባስልዮስ (እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ)
ምስባክ
መዝሙር 33:7-8

ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዐውዶሙ

ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖሙ

ጠዐሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

20 Nov, 20:58


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ኅዳር 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ኢያሱ ነቢይ
3.ቅዱሳን ዱራታኦስና ቴዎብስታ
4.አፄ በዕደ ማርያም ጻድቅ
5.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
6.ቅዱስ ባሕራን ቀሲስ
7.አባ ፊላታዎስ ሊቀ ዻዻሳት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

18 Nov, 13:05


#ዝማሬ

እንተ ክርስቶስ መሠረት ...

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

17 Nov, 17:13


09/03/2017
                     የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                      ዮሐንስ 10:25-ፍጻሜ


   ኢየሱስም መለሰላቸው፥ እንዲህ ሲል ነገርኋችሁ፡ አታምኑምም፡ እኔ በአባቴ ስም የማደርገው ሥራ ይህ ስለ እኔ ይመሰክራል፤ እናንተ ግን እንደ ነገርኋችሁ ከበጎቼ ስላልሆናችሁ አታምኑም። በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ ይከተሉኝማል፤ እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።

የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ ከአባቴም እጅ ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም። እኔና አብ አንድ ነን።

አይሁድ ሊወግሩት ደግመው ድንጋይ አነሡ። ኢየሱስ ከአባቴ ብዙ መልካም ሥራ አሳየኋችሁ፤ ከእነርሱ ስለ ማናቸው ሥራ ትወግሩኛላችሁ? ብሎ መለሰላቸው።አይሁድም ስለ መልካም ሥራ አንወግርህም፤ ስለ ስድብ፤ አንተም ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለ ማድረግህ ነው እንጂ ብለው መለሱለት።

ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው እኔ አማልክት ናችሁ አልሁ ተብሎ በሕጋችሁ የተጻፈ አይደለምን? መጽሐፉ ሊሻር አይቻልምና እነዚያን የእግዚአብሔር ቃል የመጣላቸውን አማልክት ካላቸው፥ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ፡ ስላልሁ እናንተ አብ የቀደሰውን ወደ ዓለምም የላከውን ትሳደባለህ ትሉታላችሁን? እኔ የአባቴን ሥራ ባላደርግ አትመኑኝ፤ ባደርገው ግን፥ እኔን ስንኳ ባታምኑ አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ።

እንግዲህ ደግመው ሊይዙት ፈለጉ፤ ከእጃቸውም ወጣ። ዮሐንስም በመጀመሪያ ያጠምቅበት ወደ ነበረው ስፍራ ወደ ዮርዳኖስ ማዶ እንደ ገና ሄደ በዚያም ኖረ። ብዙ ሰዎችም ወደ እርሱ መጥተው ዮሐንስ አንድ ምልክት ስንኳ አላደረገም፥ ነገር ግን ዮሐንስ ስለዚህ ሰው የተናገረው ሁሉ እውነት ነበረ፡ አሉ። በዚያም ብዙዎች በእርሱ አመኑ............


👉ቆላስያስ 2:5-13
👉2 ዮሐንስ 1:6-12
👉ሐዋ.ሥራ 15:22-30


👉ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)

                              ምስባክ
                        መዝሙር 72:8-9


👉ወነበቡ ዓመፃ ውስተ ዓርያም

     ወአንበሩ ውስተ ሰማይ አፉሆሙ

     ወአንሶሰወ ውስተ ምድር ልሳኖሙ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

17 Nov, 17:12


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ኅዳር 9 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱሳን 318ቱ ሊቃውንት
2.ቅዱስ እለእስክንድሮስ ሊቅ
3.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
4.አባ ይስሐቅ ሊቀ ጳጳሳት
5.ሊቁ አካለ ወልድ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

17 Nov, 09:25


ውድ ሙሽሮቻችን ከክብረ ሃይማኖት ዘማርያን ጋር ...

#ክብረ_ሃይማኖት

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

16 Nov, 19:11


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ኅዳር 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱሳን 4ቱ እንስሳ (ኪሩቤል)
2.ቅዱስ አፍኒን ሊቀ መላእክት
3.አባ ቅፍሮንያ ጻድቅ
4.ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ንጉሥ (ዘምስለ ቅዱስ መስቀል)
5.ቅድስት እግዚእ ክብራ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

15 Nov, 18:17


07/03/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 10:16-ፍጻሜ


እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ። ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤ ለእነርሱና ለአሕዛብም ምስክር እንዲሆን፥ ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ወንድምም ወንድሙን፥ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ ይገድሉአቸውማል። በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። በአንዲቱ ከተማም መከራ ቢያሳዩአችሁ ወደ ሌላይቱ ሽሹ፤ እውነት እላችኋለሁና፥ የሰው ልጅ እስኪመጣ ድረስ የእስራኤልን ከተማዎች አትዘልቁም። ደቀ መዝሙር ከመምህሩ፥ ባሪያም ከጌታው አይበልጥም። ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ፥ ባሪያም እንደ ጌታው መሆኑ ይበቃዋል። ባለቤቱን ብዔል ዜቡል ካሉት፥ ቤተሰዎቹንማ እንዴት አብዝተው አይሉአቸው! እንግዲህ አትፍሩአቸው፤ የማይገለጥ የተከደነ፥ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለምና። በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ፤ በጆሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ። ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ። ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም። የእናንተስ የራሳችሁ ጠጉር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል። እንግዲህ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ። ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ። በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም። ሰውን ከአባቱ፥ ሴት ልጅንም ከእናትዋ፥ ምራትንም ከአማትዋ እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና፤ ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል። ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም። ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም ስለ እኔ የሚያጠፋ ያገኛታል። እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም............

ኤፌሶን 5:23-28  ዓዲ  1ቆሮንጦስ 7:25-ፍጻሜ
1 ጴጥሮስ 4:12-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 28:1-11  ዓዲ 27:21-27


ቅዳሴ ዘባስልዮስ

ምስባክ
                                 መዝሙር 78:10-11


ወይርአዪ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ

በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ

ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

15 Nov, 18:17


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ኅዳር 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት (ቅዳሴ ቤቱ)
2.ቅዱስ ጊዮርጊስ እስክንድርያዊ
3.ቅዱሳን ዘኖቢስና ዘኖብያ (ሰማዕታት)
4.ቅዱስ ሚናስ ዘተመይ
5.ቅዱሳን መርቆሬዎስና ዮሐንስ (ጻድቃን ወሰማዕት)
6.አባ ናሕርው ሰማዕት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

14 Nov, 18:44


05/03/2017
                      የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                       ዮሐንስ 19:31-ፍጻሜ


      አይሁድም የማዘጋጀት ቀን ስለ ሆነ ያ ሰንበት ትልቅ ነበረና ሥጋቸው በሰንበት በመስቀል ላይ እንዳይኖር፥ ጭናቸውን ሰብረው እንዲያወርዱአቸው ጲላጦስን ለመኑት። ጭፍሮችም መጥተው የፊተኛውን ጭን ከእርሱም ጋር የተሰቀለውን የሌላውን ጭን ሰበሩ፤ ወደ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን እርሱ ፈጽሞ እንደ ሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም፤ ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጎኑን በጦር ወጋው፤ ወዲያውም ደምና ውኃ ወጣ። ያየውም መስክሮአል፤ ምስክሩም እውነት ነው፤ እናንተም ደግሞ ታምኑ ዘንድ እርሱ እውነት እንዲናገር ያውቃል። ይህ የሆነ ከእርሱ አጥንት አይሰበርም የሚል የመጽሐፉ ቃል እንዲፈጸም ነው። ደግሞም ሌላው መጽሐፍ የወጉትን ያዩታል ይላል። ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ። ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ። የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት። በተሰቀለበትም ስፍራ አትክልት ነበረ፥ በአትክልቱም ማንም ገና ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበረ። ስለዚህ መቃብሩ ቅርብ ነበረና ስለ አይሁድ ማዘጋጀት ቀን ኢየሱስን በዚያ አኖሩት.........

ሮሜ 5:8-ፍጻሜ
1 ጴጥሮስ 2:9-13
ሐዋ.ሥራ 26 :12-19


ቅዳሴ  ዘእግዝእትነ  (ጐሥዓ)  

                                          ምስባክ
                                    መዝሙር 24:7-8

ኃጢአትየ ዘበንዕስየ ወዕበድየ ኢትዝክር ሊተ

ወበከመ ሣህልከ ተዘከረኒ

በእንተ ምሕረትከ እግዚኦ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

14 Nov, 18:44


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ ኅዳር 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም (ሚጠታ ለማርያም)
2.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
3.ቅድስት ሰሎሜ ቡርክት
4.ቅዱስ ዮሳ (ወልደ ዮሴፍ)
5.ቅዱስ ቴዎፍሎስ ሊቅ
6.አባ ጽጌ ድንግል ዘወለቃ
7.አባ ፊልክስ ዘሮሜ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

12 Nov, 18:50


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ኅዳር 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ቶማስ ዘደማስቆ
2.ቅዱሳን ያዕቆብና ዮሐንስ
3.ቅዱሳን አቢማኮስ ወአዛርያኖስ
4.አባ አበጊዶ ዘትግራይ
5.ታላቁ አባ ዘካርያስ
6.ጉባኤ ቅዱሳን ሰማዕታት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

12 Nov, 18:50


04/03/2017
                      የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                      ማቴዎስ 10:32-ፍጻሜ


     ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ። በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም። ሰውን ከአባቱ፥ ሴት ልጅንም ከእናትዋ፥ ምራትንም ከአማትዋ እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና፤ ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል። ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም። ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም ስለ እኔ የሚያጠፋ ያገኛታል። እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም......

2 ቆሮንጦስ 11:29-ፍጻሜ
1 ጴጥሮስ 5:9-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 9:22-28

ቅዳሴ  ዘወልደ ነጎድጓድ ( ኀቤከ )

                                    ምስባክ
                            መዝሙር 43:22-23


እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኩሎ አሚረ

ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ

ንቃዕ እግዚኦ ለምንት ትነውም

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

11 Nov, 18:51


03/03/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 12:9-14


ከዚያም አልፎ ወደ ምኩራባቸው ገባ። እነሆም፥ እጁ የሰለለች ሰው ነበረ፤ ይከሱትም ዘንድ በሰንበት መፈወስ ተፈቅዶአልን? ብለው ጠየቁት። እርሱ ግን ከእናንተ አንድ በግ ያለው በሰንበት በጉድጓድ ቢወድቅበት፥ ይዞ የማያወጣው ሰው ማን ነው? እንግዲህ ሰው ከበግ ይልቅ እንደምን አይበልጥም! ስለዚህ በሰንበት መልካም መሥራት ተፈቅዶአል አላቸው። ከዚያም በኋላ ሰውየውን እጅህን ዘርጋ አለው። ዘረጋትም፥ እንደ ሁለተኛይቱም ደህና ሆነች......

1 ጢሞቴዎስ 4:6-ፍጻሜ
1 ዮሐንስ 2:15-22
ሐዋ.ሥራ 19:8-11


ቅዳሴ  ዘእግዝእትነ  (ጐሥዓ)  

ምስባክ
መዝሙር 1:2-3

ወዘሕጎ ያነብብ መዓልተ ወሌሊተ

ወይከውን ከመ ዕፅ እንተ ትክልት ኀበ ሙኀዘ ማይ

እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

11 Nov, 18:15


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ኅዳር 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ጻድቅ (ዘደብረ በንኮል)
2.ቅዱስ ዓምደ ሚካኤል ጻድቅ (የሠራዊት አለቃ)
3.ቅዱስ ኪርያቆስ ሊቅ
4.ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ ንጉሥ (ልደቱ)
5.ቅዱሳን አትናቴዎስና እህቱ ኢራኢ (ሰማዕታት)
6.አቡነ ፍሬ ካህን

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

10 Nov, 17:58


እምነት ብቻውን ያድናልን?

ከላይ ያለውን ሊንክ ነክታችሁ ሙሉውን ታነቡት ዘንድ ጋበዝናችሁ

#ወቅታዊ_ትምህርት_ክፍል
#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

10 Nov, 17:39


02/03/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ዮሐንስ 10:1-22


እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና። ኢየሱስ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ እነርሱ ግን የነገራቸው ምን እንደ ሆነ አላስተዋሉም። ኢየሱስም ደግሞ አላቸው እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እኔ የበጎች በር ነኝ። ከእኔ በፊት የመጡ ሁሉ ሌቦችና ወንበዴዎች ናቸው፤ ዳሩ ግን በጎቹ አልሰሙአቸውም። በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማሪያም ያገኛል። ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል። እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል በጎቹንም ይበትናቸዋል። ሞያተኛ ስለ ሆነ ለበጎቹም ስለማይገደው ሞያተኛው ይሸሻል። መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች ያውቁኛል፤ ነፍሴንም ስለ በጎች አኖራለሁ። ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ። ነፍሴን ደግሞ አነሣት ዘንድ አኖራለሁና ስለዚህ አብ ይወደኛል። እኔ በፈቃዴ አኖራታለሁ እንጂ ከእኔ ማንም አይወስዳትም። ላኖራት ሥልጣን አለኝ ደግሞም ላነሣት ሥልጣን አለኝ ይህችን ትእዛዝ ከአባቴ ተቀበልሁ። እንግዲህ ከዚህ ቃል የተነሣ በአይሁድ መካከል እንደ ገና መለያየት ሆነ። ከእነርሱም ብዙዎች ጋኔን አለበት፡ አብዶአልም፤ ስለ ምንስ ትሰሙታላችሁ? አሉ። ሌሎችም ይህ ጋኔን ያለበት ሰው ቃል አይደለም፤ ጋኔን የዕውሮችን ዓይኖች ሊከፍት ይችላልን? አሉ....

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

10 Nov, 17:39


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ኅዳር 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አባ ዼጥሮስ ሊቀ ዻዻሳት ሣልስ
2.አባ ሱንቱዩ ሊቀ ዻዻሳት
3.ቅድስት ሴቴንዋ ነቢይት
4.ቅድስት አንስጣስያ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

10 Nov, 03:01


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ኅዳር 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
2.ቅዱሳን መክሲሞስና ባልንጀሮቹ (ሰማዕታት)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

09 Nov, 18:33


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን።

ለበጎ አድራጎት ስራ የሚሆን መዝገበ ሰማይ ሳጥን የወሰዳችሁ በሙሉ ነገ ህዳር 1 ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ ሳጥኑን በማምጣት እንድትመልሱ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።

ማህበራዊ ሙያ ተራድኦ ክፍል

#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

08 Nov, 18:39


30/02/2017
                    የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                    ማቴዎስ 16:24-ፍጻሜ


    በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አለ እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታል፤ ስለ እኔ ግን ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ያገኛታል። ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል? ወይስ ሰው ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል? የሰው ልጅ ከመላእክቱ ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንድ አለውና፤ ያን ጊዜም ለሁሉ እንደ ሥራው ያስረክበዋል። እውነት እላችኋለሁ፥ የሰው ልጅ በመንግሥቱ ሲመጣ እስኪያዩ ድረስ እዚህ ከሚቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ....

2 ጢሞቴዎስ 4:11-ፍጻሜ
ያዕቆብ 1:2-6
ሐዋ.ሥራ 10:37-43


ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)

  ምስባክ
                                 መዝሙር 26:6-7

ናሁ ይእዜ አልዐለ እግዚአብሔር ርእስየ ዲበ ጸላእትየ

ዖድኩ ወሦዕኩ ውስተ ደብተራሁ መሥዋዕተ

ወየበብኩ ሎቱ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

08 Nov, 18:39


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ጥቅምት 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ
2.ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ)
3.ቅድስት ማርያም (እናቱ)
4.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
5.አባ አብርሃም ገዳማዊ
6 ቅዱስ ይስሐቅ ንጉሥ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

07 Nov, 18:10


29/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማርቆስ 8:34-ፍጻሜ---9:1-2


ሕዝቡንም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ጠርቶ እንዲህ አላቸው በኋላዬ ሊመጣ የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታልና፥ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ግን ያድናታል። ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል? ሰውስ ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል? በዚህም በዘማዊና በኃጢአተኛ ትውልድ መካከል በእኔና በቃሌ የሚያፍር ሁሉ፥ የሰው ልጅ ደግሞ በአባቱ ክብር ከቅዱሳን መላእክት ጋር በመጣ ጊዜ በእርሱ ያፍርበታል............ ..
......እውነት እላችኋለሁ፥ በዚህ ከቆሙት ሰዎች የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል ስትመጣ እስኪያዩ ድረስ፥ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች አሉ፡ አላቸው። ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ዮሐንስንም ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። በፊታቸውም ተለወጠ፥ ልብሱም አንጸባረቀ.........

2 ቆሮንጦስ 6:1-12
1 ዮሐንስ 3:7-12
ሐዋ.ሥራ 9:20-23


ቅዳሴ  ዘእግዝእትነ  (ጐሥዓ)  

ምስባክ
መዝሙር 17:39-40

ወታቀንተኒ ኃይለ በፀብዕ

አዕቀፅኮሙ ለኵሎሙ እለ ቆሙ ላዕሌየ በመትሕቴየ

ወመጠውከኒ ዘባኖሙ ለፀርየ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

07 Nov, 18:10


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

†††ጥቅምት 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አቡነ ሳሙኤል ጻድቅ (ዘደብረ ወገግ)
2.አባ ጸቃውዐ ድንግል (ዘደብረ ዘኸኝ)
3.ቅዱስ ድሜጥሮስ ሰማዕት
4.ቅዱስ ስቅጣር ሰማዕት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

06 Nov, 19:01


28/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 20:37-41


ሙታን እንዲነሡ ግን ሙሴ ደግሞ በቍጥቋጦው ዘንድ ጌታን የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ በማለቱ አስታወቀ፤ ሁሉ ለእርሱ ሕያዋን ስለ ሆኑ፥ የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም። ከጻፎችም አንዳንዶቹ መልሰው መምህር ሆይ፥ መልካም ተናገርህ አሉት። ወደ ፊትም አንድ ነገር ስንኳ ሊጠይቁት አልደፈሩም.....

የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት
ዕብራውያን 6:9-15

ስለ እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ ምንም እንኳ እንዲሁ ብንናገር፥ አብልጦ የሚሻለውና ለመዳን የሚሆነው እንዲሆንላችሁ ተረድተናል። እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና። በእምነትና በትዕግሥትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ፥ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን። እግዚአብሔርም ለአብርሃም ተስፋ በሰጠው ጊዜ በእውነት እየባረክሁ እባርክሃለሁ እያበዛሁም አበዛሃለሁ ብሎ፥ ከእርሱ በሚበልጥ በማንም ሊምል ስላልቻለ፥ በራሱ ማለ....

1 ጴጥሮስ 4:12-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 3:12-17


ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)

ምስባክ
መዝሙር 111:2-3

ትውልደ ጻድቃን ይትባረኩ

ክብር ወብዕል ውስተ ቤቱ

ወጽድቁኒ ይነብር ለዓለም

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

06 Nov, 19:01


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

††† ጥቅምት 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አባ ይምዓታ ጻድቅ (ከተስዓቱ ቅዱሳን)
2.ቅዱሳን መርትያኖስ ወመርቆሬዎስ (ሰማዕታት)
3.አባታችን ያፌት (የኖኅ ልጅ)


ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

05 Nov, 18:35


27/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ዮሐንስ 3:11-25

እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ምስክራችንንም አትቀበሉትም። ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ? ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው። ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል። በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና። ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና። በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፤ በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል። ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው። ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፤ እውነትን የሚያደርግ ግን ሥራው በእግዚአብሔር ተደርጎ እንደ ሆነ ይገለጥ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ይሁዳ አገር መጣ፥ በዚያም ከእነርሱ ጋር ተቀምጦ ያጠምቅ ነበር። ዮሐንስም ደግሞ በሳሌም አቅራቢያ በሄኖን በዚያ ብዙ ውኃ ነበርና ያጠምቅ ነበር፥ እየመጡም ይጠመቁ ነበር ዮሐንስ ገና ወደ ወኅኒ አልተጨመረም ነበርና። ስለዚህም በዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና በአይሁድ መካከል ስለ ማንጻት ክርክር ሆነ.....

1 ቆሮንጦስ 12:22-28
1 ጴጥሮስ 2:21-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 5:12-17


ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ (ናሁ ንዜኑ)

ምስባክ
መዝሙር 55:1-2

ተሣሃለኒ እግዚኦ እስመ ኬደኒ ሰብእ

ወኵሎ ዓሚረ አሥርሐኒ ቀትል

ወኬዱኒ ፀርየ ኵሎ ዓሚረ በኑኀ ዕለት

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

05 Nov, 18:35


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥቅምት 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት

1.ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
2.ቅዱስ መቃርስ ብጹዓዊ
3.አቡነ መብዓ ጽዮን ጻድቅ
4.አባ ጽጌ ድንግል ዘወለቃ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Nov, 19:09


26/02/2017
                    የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                          ሉቃስ 10:1-12

    ከዚህም በኋላ ጌታ ሌሎቹን ሰብዓ ሾመ፥ ሁለት ሁለትም አድርጎ እርሱ ሊሄድበት ወዳለው ከተማና ስፍራ ሁሉ በፊቱ ላካቸው።አላቸውም መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዴህ የመከሩን ጌታ ለመከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት። ሂዱ፤ እነሆ፥ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ። ኮረጆም ከረጢትም ጫማም አትያዙ፤ በመንገድም ለማንም እጅ አትንሡ። ወደምትገቡበት ቤት ሁሉ አስቀድማችሁ ሰላም ለዚህ ቤት ይሁን በሉ። በዚያም የሰላም ልጅ ቢኖር፥ ሰላማችሁ ያድርበታል፤ አለዚያም ይመለስላችኋል። በዚያም ቤት ከእነርሱ ዘንድ ካለው እየበላችሁና እየጠጣችሁ ተቀመጡ፤ ለሠራተኛ ደመወዙ ይገባዋልና። ከቤት ወደ ቤት አትተላለፉ። ወደምትገቡባትም ከተማ ሁሉ ቢቀበሉአችሁ፥ ያቀረቡላችሁን ብሉ በእርስዋም ያሉትን ድውዮችን ፈውሱና የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ቀረበች፡’ በሉአቸው። ነገር ግን ወደምትገቡባት ከተማ ሁሉ ባይቀበሉአችሁ፥ ወደ አደባባይዋ ወጥታችሁ፦ ከከተማችሁ የተጣበቀብንን ትቢያ እንኳን እናራግፍላችኋለን፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ግን ወደ እናንተ እንደ ቀረበች ይህን እወቁ በሉ እላችኋለሁ፥ በዚያን ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶም ይቀልላታል.....

ገላትያ 1:15-ፍጻሜ
1 ዮሐንስ 2:28-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 6:1-8


ቅዳሴ  ዘእግዝእትነ  (ጐሥዓ)   

ምስባክ
መዝሙር 113:22-23


ይዌስክ እግዚአብሔር ላዕሌክሙ

ላዕሌክሙ ወላዕለ ውሉድክሙ

ቡሩካኑ አንትሙ ለእግዚአብሔር

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Nov, 19:09


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥቅምት 26 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት

1.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ ዮሴፍ)
2.ቅዱስ ጢሞና ሐዋርያ ወዲያቆን
3.ቅዱስ አግናጥዮስ
4.ቅዱስ ፊልዾስ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

03 Nov, 20:12


25/02/2017
                      የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                          ማቴዎስ 5:1-17

       ሕዝቡንም አይቶ ወደ ተራራ ወጣ፤ በተቀመጠም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀረቡ፤ አፉንም ከፍቶ አስተማራቸው እንዲህም አለ በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና። የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና። ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና። የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና። ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና። የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና። ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና። እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም። እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም። መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል። መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ........

ኤፌሶን 7:14-ፍጻሜ
1 ጴጥሮስ 3:1-18
ሐዋ.ሥራ 11:23-27


ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)

       ምስባክ
                   መዝሙር 91:12-13

ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ

ወይበዝኅ ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ

ትኩላን እሙንቱ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

03 Nov, 20:12


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥቅምት 25 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አቡነ አቢብ (አባ ቡላ)
2.አባ ዕብሎይ ገዳማዊ
3.ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት
4.ቅዱሳን አብርሃምና ሐሪክ
5.ቅዱሳን አሞኒና ሙስያ (የታላቁ ዕብሎ ወላጆች)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

03 Nov, 20:12


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥቅምት ፳፬ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አብላርዮስ ገዳማዊ
2.ቅድስት ጸበለ ማርያም
3.ቅድስት አውስያ
4.አባ ዻውሎስ ሊቀ ዻዻሳት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

01 Nov, 18:40


23/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ6:36-ፍጻሜ


አባታችሁ ርኅሩኅ እንደ ሆነ ርኅሩኆች ሁኑ። አትፍረዱ አይፈረድባችሁምም፤ አትኰንኑ አትኰነኑምም። ይቅር በሉ ይቅርም ትባላላችሁ። ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል። ምሳሌም አላቸው ዕውር ዕውርን ሊመራ ይችላልን? ሁለቱ በጕድጓድ አይወድቁምን? ደቀ መዝሙር ከመምህሩ አይበልጥም፤ ፈጽሞ የተማረ ሁሉ ግን እንደ መምህሩ ይሆናል። በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለ ምን ታያለህ፥ በራስህ ዓይን ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም? በዓይንህ ያለውን ምሰሶ ራስህ ሳታይ፥ እንዴት ወንድምህን፦ ወንድሜ ሆይ፥ በዓይንህ ያለውን ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ ልትል ትችላለህ? አንተ ግብዝ፥ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ ከዚያም በኋላ በወንድምህ ዓይን ያለውን ጉድፍ ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ። ክፉ ፍሬ የሚያደርግ መልካም ዛፍ የለምና፥ እንዲሁም መልካም ፍሬ የሚያደርግ ክፉ ዛፍ የለም። ዛፍ ሁሉ ከፍሬው ይታወቃልና፤ ከእሾህ በለስ አይለቅሙም፥ ከአጣጥ ቍጥቋጦም ወይን አይቈርጡም። በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፉ ይናገራልና መልካም ሰው ከልብ መልካም መዝገብ መልካሙን ያወጣል፥ ክፉ ሰውም ከልብ ክፉ መዝገብ ክፉውን ያወጣል። ስለ ምን ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ ትሉኛላችሁ፥ የምለውንም አታደርጉም? ወደ እኔ የሚመጣ ሁሉ ቃሌንም ሰምቶ የሚያደርገው፥ ማንን እንዲመስል አሳያችኋለሁ። ቤት ሲሠራ አጥልቆ የቆፈረ በዓለት ላይም የመሠረተ ሰውን ይመስላል፤ ጐርፍም በመጣ ጊዜ ወንዙ ያን ቤት ገፋው፥ በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ ሊያናውጠው አልቻለም። ሰምቶ የማያደርገው ግን ያለ መሠረት በምድር ላይ ቤቱን የሠራ ሰውን ይመስላል፤ ወንዙም ገፋው ወዲያውም ወደቀ የዚያ ቤት አወዳደቅም ታላቅ ሆነ.......

1 ጢሞቴዎስ 6:17-ፍጻሜ
ያዕቆብ 1:12-19
ሐዋ. ሥራ 15:1-9

ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)


    ምስባክ
                            መዝሙር 83:6-7


እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ

ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል

ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

01 Nov, 18:40


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥቅምት 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አባ ዮሴፍ ጻድቅ ሊቀ ዻዻሳት
2.ቅዱስ ዲዮናስዮስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ኢላርዮስ
4.ቅድስት እለእስክንድርያ ሰማዕት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

31 Oct, 19:21


22/02/2016
የዕለቱ የወንጌል ክፍል

ሉቃስ 1:1-5

የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ....

ቆላስያስ 4:12-ፍጻሜ

1 ዮሐንስ 1:4-ፍጻሜ


ደስታችሁም እንዲፈጸም ይህን እንጽፍላችኋለን። ከእርሱም የሰማናት ለእናንተም የምናወራላችሁ መልእክት እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም የምትል ይህች ናት። ከእርሱ ጋር ኅብረት አለን ብንል በጨለማም ብንመላለስ እንዋሻለን እውነትንም አናደርግም፤ ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን፥ የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል። ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም። በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው። ኃጢአትን አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም...


ሐዋ.ሥራ 1:1-6

ቅዳሴ ዘሐዋርያት


ምስባክ
                           መዝሙር 18:4-5


አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ

ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ

ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

31 Oct, 19:20


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥቅምት 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ሐዋርያ
2.ቅዱስ ሲላስ አረጋዊ (የቅዱስ ሉቃስ ረድእ)
3.ቅዱስ ታኦፊላ
4."477" ሰማዕታት (የቅዱስ ሉቃስ ማሕበር)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

29 Oct, 17:10


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጥቅምት 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር
2.ቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ
3.አባ ባይሞይ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

29 Oct, 17:10


20/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 4:27-32


በነቢዩ በኤልሳዕ ዘመንም በእስራኤል ብዙ ለምጻሞች ነበሩ፥ ከሶርያዊው ከንዕማን በቀር ከእነርሱ አንድ ስንኳ አልነጻም። በምኵራብም የነበሩ ሁሉ ይህን ሰምተው ቍጣ ሞላባቸው፥ ተነሥተውም ከከተማ ወደ ውጭ አወጡት፥ ይጥሉትም ዘንድ ከተማቸው ተሠርታባት ወደ ነበረች ወደ ተራራው አፋፍ ወሰዱት፤ እርሱ ግን በመካከላቸው አልፎ ሄደ። ወደ ገሊላ ከተማም ወደ ቅፍርናሆም ወረደ። በሰንበትም ያስተምራቸው ነበር፤ ቃሉ በሥልጣን ነበርና በትምህርቱ ተገረሙ.........

ዕብራውያን 12:11-25
1 ጴጥሮስ 4:6-11
ሐዋ.ሥራ 20:31-ፍጻሜ


ቅዳሴ  ዘወልደ ነጎድጓድ ( ኀቤከ )

ምስባክ
መዝሙር 64:10-11

አርውዮ ለትለሚሃ

ወአሥምሮ ለማዕረራ

ወነጠብጣብከ ትበቁል ተፈሢሓ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

29 Oct, 17:10


ከዕለታት በአንድ ቀንም ቅዱስ ዮሐንስ ወደ መምህሩ ቀርቦ ‹‹አባቴ ጅብ ካገኘሁ ምን ላድርግ?›› በማለት ጠየቀው:: አባ ባይሞይ ሊፈትነው በማሰብ ‹‹ይዘህልኝ ና›› አለው:: ትእዛዝ ነውና ቅዱሱ ወደ በርኃ ወርዶ ጅብ አልምዶ ይዞለት መጥቷል:: ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር የመታዘዝ ጸጋ በእጅጉ የተሰጠው እንደሆነም በአባ ባይሞይ ዘንድ የተመሠከረለት ነው፤ ስለዚህ ነገር ዐውቆ በድጋሜ ሊፈትነው ደረቅ ዕንጨት ለቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር ከሰጠው በኋላ ‹‹ይህነን ዕንጨት ትከለውና እስከሚያፈራ ድረስ ውኃን አጠጣው›› በማለት አዘዘው፤ ቅዱስም በመታዛዝ ወስዶ ተከለው፤ ዐሥራ ሁለት ምዕራፍ ወደሚርቀው የውኃ ጒድጓድ እየተመላለሰም በየቀኑ ሁለት ሁለት ጊዜ  ያጠጣው ጀመረ፤ ከሦስት ዓመትም በኋላ ያ ዕንጨት አቈጥቊጦ በቀለ፤ አበበ፤ አፈራ፤ ቅዱሱም ካፈራው በኩረ ሎሚ ወስዶ ለመምህሩ ‹‹አባቴ! እንካ ብላ›› ብሎ ሰጠው፤ አባ ባይሞይ ግን ማመን ተስኖት እጅግ አደነቀ፤ አለቀሰም:: ወዲያውም ያን ፍሬ ታቅፎ ወስዶ ለገዳሙ መነኮሳትና ለቅዱሳን አረጋውያን ‹‹የታዛዡንና የትሑቱን ፍሬ እነሆ ብሉ፤ በረከትንም አግኙ:: ይህ የዛፍ ሳይሆን የመታዘዝ ፍሬ ነው›› ብለው ሰጥተዋቸዋል፤ እነርሱም እግዚአብሔርን አመስግነዋል፡፡
የቅዱስ አባታችን ምልጃና ጸሎት እንዲሁም በረከት አይለየን፤ አሜን፡፡

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

28 Oct, 19:06


19/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 10:15-21


እውነት እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ይቀልላቸዋል። እነሆ፥ እኔ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ ስለዚህ እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ። ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ በምኩራቦቻቸውም ይገርፉአችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ፤ ለእነርሱና ለአሕዛብም ምስክር እንዲሆን፥ ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና.............

ቲቶ 3:8-12
1 ዮሐንስ 2:22-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 20:28-31


ቅዳሴ  ዘእግዝእትነ  (ጐሥዓ)   

ምስባክ
መዝሙር 108:6-7

ወሶበሂ ይትዋቀሥ ይፃእ ተመዊዖ

ወጸሎቱሂ ትኩኖ ጌጋየ

ወይኩና መዋዕሊሁ ኅዳጠ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

28 Oct, 19:06


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ (ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ)
2.ቅዱስ ዮሐንስ ዘጸይለም
3.አባ ስምኦን ገዳማዊ
4.ቅዱሳን በርተሎሜዎስና ሚስቱ (ሰማዕታት)
5.አበው ኤዺስ ቆዾሳት (ሳምሳጢን ያወገዙ)
6.ጻድቃን እለ መጥራ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

27 Oct, 19:18


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 18 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ቴዎፍሎስ ሊቅ
2.ቅዱስ ሮማኖስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ዮሐንስ ሰማዕት
4.ቅድስት አስማኒትና 7ቱ ልጆቿ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

27 Oct, 19:18


18/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማርቆስ 12:13-18


በንግግርም ሊያጠምዱት ከፈሪሳውያንና ከሄሮድስ ወገን የሆኑትን ወደ እርሱ ላኩ። መጥተውም መምህር ሆይ፥ የሰውን ፊት ሳትመለከት በእውነት የእግዚአብሔር መንገድ ታስተምራለህና እውነተኛ እንደ ሆንህ ለማንምም እንዳታደላ እናውቃለን፤ ለቄሣር ግብር መስጠት ተፈቅዶአልን ወይስ አልተፈቀደም? እንስጥን ወይስ አንስጥ? አሉት። እርሱ ግን ግብዝነታቸውን አውቆ ለምን ትፈትኑኛላችሁ? አየው ዘንድ አንድ ዲናር አምጡልኝ አላቸው እነርሱም አመጡለት ይህች መልክ ጽሕፈቲቱስ የማን ናት? አላቸው እነርሱም የቄሣር ናት አሉት ኢየሱስም መልሶ የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር አስረክቡ አላቸው በእርሱም ተደነቁ............

ቲቶ 1:7-12
1 ጴጥሮስ 1:6-10
ሐዋ.ሥራ 20:31-ፍጻሜ


ቅዳሴ ዘባስልዮስ

                                  ምስባክ   
                             መዝሙር 35:8-9


ወይረውዩ እምጠለ ቤትከ

ወትሠቅዮሙ እምፈለገ ትፍሥሕትከ

እስመ እምኀቤከ ነቅዐ ሕይወት

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

27 Oct, 06:09


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 17 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት (ወቀዳሜ ሰማዕት)
2.ቅዱስ ፊልያስ ሰማዕት
3.ቅድስት ሐና ነቢይት
4.ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ
5.የደብረ ሊባኖስ ሰማዕታት (ካቶሊካውያን የገደሏቸው)
6.ቅዱሳን ሔራን ሰማዕታት
7.አባ ዲዮስቆሮስ ካልዕ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

25 Oct, 18:15


16/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 5:1-16


ሕዝቡንም አይቶ ወደ ተራራ ወጣ፤ በተቀመጠም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀረቡ፤ አፉንም ከፍቶ አስተማራቸው እንዲህም አለ በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና። የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና። ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና። የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና። ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና። የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና። ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና። እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም። እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም። መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል......

ኤፌሶን 6:13-19
1 ጴጥሮስ 3:10-18
ሐዋ.ሥራ 20:28-31


ቅዳሴ  ዘእግዝእትነ  (ጐሥዓ)    

ምስባክ
መዝሙር 21:4-5


ኪያከ ተወከሉ አበዊነ

ተወከሉከኒ ወአድኀንኮሙ

ኀቤከ ጸርሑ ወድኅኑ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

25 Oct, 18:14


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 16 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት
1.አባ ያቃቱ ሊቀ ዻዻሳት
2.ጻድቃን እለ ድርቂ
3.አባ ዻውሊ ገዳማዊ
4.አባ ማርቆስ መስተጋድል
5.አባ አሮን መስተጋድል

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

24 Oct, 18:31


15/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 18:12-21


ምን ይመስላችኋል? ለአንድ ሰው መቶ በጎች ቢኖሩት ከእነርሱም አንዱ ቢባዝን፥ ዘጠና ዘጠኙን በተራራ ትቶ ሄዶም የባዘነውን አይፈልግምን? ቢያገኘውም፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ካልባዘኑቱ ከዘጠና ዘጠኙ ይልቅ በእርሱ ደስ ይለዋል። እንደዚሁ ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱ እንዲጠፋ በሰማያት ያለው አባታችሁ ፈቃድ አይደለም። ወንድምህም ቢበድልህ፥ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፥ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው፤ ባይሰማህ ግን፥ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር አፍ ነገር ሁሉ እንዲጸና፥ ዳግመኛ አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ፤ እነርሱንም ባይሰማ፥ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፥ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ። እውነት እላችኋለሁ፥ በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል። ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል። ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና..........

ሮሜ 8:31-35
ይሁዳ 1:17-22
ሐዋ.ሥራ 15:22-30

ቅዳሴ  ዘወልደ ነጎድጓድ ( ኀቤከ )


ምስባክ
መዝሙር 21:22-23


እነግሮሙ ስመከ ለአኀውየ

በማዕከለ ማኅበር እሴብሐከ

እለ ትፈርኅዎ ለእግዚአብሔር ሰብሕዎ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

24 Oct, 18:31


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 15 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1."12ቱ" ቅዱሳን ሐዋርያት
2.ቅዱስ ቢላሞን ሰማዕት
3."158" ሰማዕታት (የቅዱስ ቢላሞን ማሕበር)
4.ቅዱስ ሲላስ ሐዋርያ
5.ቅድስት ጾመታ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

23 Oct, 22:26


14/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 19:26-ፍጻሜ


ኢየሱስም እነርሱን ተመልክቶ ይህ በሰው ዘንድ አይቻልም በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሁሉ ይቻላል አላቸው። በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ መልሶ እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ፤ እንኪያስ ምን እናገኝ ይሆን? አለው። ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ እውነት እላችኋለሁ፥ እናንተስ የተከተላችሁኝ፥ በዳግመኛ ልደት የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን በሚቀመጥበት ጊዜ፥ እናንተ ደግሞ በአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ ስትፈርዱ በአሥራ ሁለት ዙፋን ትቀመጣላችሁ። ስለ ስሜም ቤቶችን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል። ነገር ግን ብዙዎቹ ፊተኞች ኋለኞች፥ ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ..........

1 ቆሮንጦስ 7:36-ፍጻሜ
1 ጴጥሮስ 2:18-21
ሐዋ.ሥራ 8:26-ፍጻሜ

የጌታም መልአክ ፊልጶስን ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው። ተነሥቶም ሄደ። እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘብዋም ሁሉ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር..................ፊልጶስም አፉን ከፈተ፥ ከዚህም መጽሐፍ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌልን ሰበከለት.......................ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም። ከውኃውም ከወጡ በኋላ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጠቀው፤ ጃንደረባውም ሁለተኛ አላየውም፥ ደስ ብሎት መንገዱን ይሄድ ነበርና.......................

ቅዳሴ  ዘሐዋርያት

ምስባክ
                           መዝሙር 18:4-5


አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ

ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ

ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

23 Oct, 22:26


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 14 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አቡነ ዘሚካኤል (አረጋዊ)
2.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
3.ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ
4.ቅዱስ ሙሴ መርዓዊ
5.ቅድስት እድና (የአረጋዊ እናት)
6.አባ ማትያስ (የአረጋዊ ረድዕ)

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

23 Oct, 12:23


ፊልጶስ ሆይ በስብከትህ አብርተሀልና ኮከብ ብለን ሰየምንህ ... !

እንኳን አደረሳችሁ !

#ማኅበራዊ_ድህረገፅና_መረጃና_ሚዲያ_ክፍል
#ክብረ_ሃይማኖት 

📌 የቲክቶክ ገፅ
👉 ይህን ይጫኑ 
ቲክቶክ 

📌 የቴሌግራም አድራሻ
👉 ይህን ይጫኑ
ቴሌግራም

📌 የፌስቡክ አድራሻ         
👉 ይህን ይጫኑ
ፌስቡክ

📌 የዩቲዩብ ቻናል   
👉 ይህን ይጫኑ
ዩቲዩቡ

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

23 Oct, 08:02


ፊልጶስ አባታችን ...

ለጥቅምት 14 እየዘጋጀን ነው ። በክብረሃይማኖት የቲክቶክ ገፅ ...

https://vm.tiktok.com/ZMhmCGkod/

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

22 Oct, 17:42


13/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 12:27-32

አበቦችን እንዴት እንዲያድጉ ተመልከቱ፤ አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከእነዚህ እንደ አንዲቱ አለበሰም። እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን በሜዳ የሆነውን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ፥ እናንተ እምነት የጐደላችሁ፥ እናንተንማ ይልቁን እንዴት? እናንተም የምትበሉትን የምትጠጡትንም አትፈልጉ፥ አታወላውሉም፤ ይህንስ ሁሉ በዓለም ያሉ አሕዛብ ይፈልጉታልና፤ የእናንተም አባት ይህ እንዲያስፈልጋችሁ ያውቃል። ዳሩ ግን መንግሥቱን ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል............

2 ቆሮንጦስ 9:1-10
ያዕቆብ 1:9-17
ሐዋ.ሥራ 20:16-28


ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ (ናሁ ንዜኑ)

ምስባክ
መዝሙር 91:12-13

ጸድቅሰ ከመ በቀልት ይፈረ

ወይበዝን ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ

ትኩላን እሙንቱ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

22 Oct, 17:42


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 13 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
2.አባ ዘካርያስ ገዳማዊ
3.አባ ማርዳሪ ጻድቅ
4.ቅዱስ አብጥማዎስ ሰማዕት

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

21 Oct, 19:39


12/02/2017
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 9:9-32


ኢየሱስም ከዚያ አልፎ በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረ ማቴዎስ የሚባል አንድ ሰው አየና ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው። በቤቱም በማዕድ ተቀምጦ ሳለ፥ እነሆ፥ ብዙ ቀራጮችና ኃጢአተኞች መጥተው ከኢየሱስና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አብረው ተቀመጡ። ፈሪሳውያንም አይተው ደቀ መዛሙርቱን መምህራችሁ ከቀራጮችና ከኃጢአተኞች ጋር አብሮ ስለ ምን ይበላል? አሉአቸው። ኢየሱስም ሰምቶ ሕመምተኞች እንጂ ባለ ጤናዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም፤ ነገር ግን ሄዳችሁ፦ ምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም፡ ያለው ምን እንደ ሆነ ተማሩ፤ ኃጢአተኞችን ወደ ንስሐ እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁምና አላቸው። በዚያን ጊዜ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው እኛና ፈሪሳውያን፥ ብዙ ጊዜ የምንጦመው፥ ደቀ መዛሙርትህ ግን የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው? አሉት። ኢየሱስም እንዲህ አላቸው ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ። በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፥ መቀደዱም የባሰ ይሆናል። በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን፥ አቁማዳው ይፈነዳል፥ የወይን ጠጁም ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል፤ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል፥ ሁለቱም ይጠባበቃሉ። ይህንም ሲነግራቸው፥ አንድ መኰንን መጥቶ ልጄ አሁን ሞተች፤ ነገር ግን መጥተህ እጅህን ጫንባት፥ በሕይወትም ትኖራለች እያለ ሰገደለት። ኢየሱስም ተነሥቶ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተከተለው። እነሆም፥ ከአሥራ ሁለት ዓመት ጀምሮ ደም የሚፈስሳት ሴት በኋላው ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች፤ በልብዋ ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ፥ እድናለሁ ትል ነበረችና። ኢየሱስም ዘወር ብሎ አያትና ልጄ ሆይ፥ አይዞሽ፤ እምነትሽ አድኖሻል አላት። ሴቲቱም ከዚያች ሰዓት ጀምራ ዳነች። ኢየሱስም ወደ መኰንኑ ቤት በደረሰ ጊዜ፥ እምቢልተኞችንና የሚንጫጫውን ሕዝብ አይቶ ብላቴናይቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችምና ፈቀቅ በሉ አላቸው። በጣምም ሳቁበት። ሕዝቡን ግን ከአስወጡ በኋላ ገብቶ እጅዋን ያዛት፥ ብላቴናይቱም ተነሣች። ያም ዝና ወደዚያ አገር ሁሉ ወጣ። ኢየሱስም ከዚያ ሲያልፍ ሁለት ዕውሮች የዳዊት ልጅ ሆይ፥ ማረን ብለው እየጮሁ ተከተሉት። ወደ ቤትም በገባ ጊዜ ዕውሮቹ ወደ እርሱ ቀረቡ፥ ኢየሱስም ይህን ማድረግ እንድችል ታምናላችሁን? አላቸው። አዎን፥ ጌታ ሆይ አሉት። በዚያን ጊዜ እንደ እምነታችሁ ይሁንላችሁ ብሎ ዓይኖቻቸውን ዳሰሰ። ዓይኖቻቸውም ተከፈቱ። ኢየሱስም ማንም እንዳያውቅ ተጠንቀቁ ብሎ በብርቱ አዘዛቸው። እነርሱ ግን ወጥተው በዚያ አገር ሁሉ ስለ እርሱ አወሩ...............

1 ጢሞቴዎስ 5:19-ፍጻሜ
ይሁዳ 1:9-14
ሐዋ.ሥራ 13:22-29


ቅዳሴ        ዘጎርጎሪዮስ ዘኑሲስ

ምስባክ
                            መዝሙር 83:6-7


እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ

ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል

ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን

የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

21 Oct, 19:39


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

✞✞✞ጥቅምት 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ ዳዊት ልበ አምላክ (የነገሠበት)
2.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ድሜጥሮስ ሊቅ
4.ቅድስት ልዕልተ ወይን
5.ቅዱስ ሳሙኤል ነቢይ
6.ጻድቃን ዼጥሮስ ወዻውሎስ

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን

1,213

subscribers

2,188

photos

26

videos