✞የካቲት 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ስምዖን አረጋዊ
2.ቅድስት ሐና ነቢይት (የፋኑኤል ልጅ)
3.ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ እግዝእት
4.አባ ኤልያስ ገዳማዊ (በትህትና ያጌጠ ቅዱስ ሰው)
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእነዚህ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን
የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ክብረ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ቴሌግራም ቻናል ነን፣ የሰንበት ት/ቤቱ መልዕክትን በትምህርት እና ወቅታዊ መረጃዎችን ማስተላለፊያ ይገኛል። በመልዕክትም ካሎት በዚህ ሊንክ ይላኩልን። ስለዚህ በመልኩ ያስተካክለውን @Kibrehaymanot የሚከተሉትን የወጪዎችን መረጃዎችን በማግኘት እና በተለያዩ መረጃዎችን በተለያዩ የሰነዳን ደረጃዎችን ይረዳል።
14 Feb, 18:13
14 Feb, 18:13
የመንጻታቸውም ወራት በተፈጸመ ጊዜ እንደ ሙሴ ሕግ በእግዚአብሔር ፊት ያቆሙት ዘንድ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት። "በኵር ሆኖ የሚወለድ ወንድ ልጅ ሁሉ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ይባላል” ተብሎ በእግዚአብሔር ሕግ እንደ ተጻፈ፥ በእግዚአብሔርም ሕግ እንደታዘዘ ሁለት ዋኖስ ወይም ሁለት የርግብ ግልገሎች ስለ እርሱ መሥዋዕት አድርገው ያቀርቡለት ዘንድ።
በኢየሩሳሌምም ስሙ ስምዖን የሚባል አንድ ሰው ነበር፤ እርሱም ጻድቅና ደግ ሰው ነበር፤ እርሱም የእስራኤልን ደስታቸውን ያይ ዘንድ ተስፋ ያደርግ ነበር፤ መንፈስቅዱስም ያደረበት ነበር። የእግዚአብሔርንም መሲሕ ሳያይ እንደማይሞት መንፈስ ቅዱስ ገልጦለት ነበር። መንፈስም ወደ ቤተ መቅደስ ወሰደው ዘመዶቹም በሕግ የተጻፈውን ያደርጉለት ዘንድ ሕፃኑን ጌታችን ኢየሱስን ወደ ቤተ መቅደስ በአገቡት ጊዜ።እርሱ ደግሞ ተቀብሎ በክንዱ ታቀፈው፤ እግዚአብሔርንም አመሰገነው። እንዲህም አለ፣ “አቤቱ፥ እንደ አዘዝህ ዛሬ ባርያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ። ዐይኖቼ ትድግናህን አይተዋልና። “በወገንህ ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን፥ "ለአሕዛብ ብርሃንን፥ ለወገንህ ለእስራኤልም ክብርን ትገልጥ ዘንድ።” “ዮሴፍና እናቱ ግን በእርሱ ላይስለሚናገረው ያደንቁ ነበር። ስምዖንም ባረካቸው፤ እናቱን ማርያምንም እንዲህ አላት፤ “እነሆ፥ ይህ ሕፃን ከእስራኤል መካከል ለብዙዎች ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው፥ ለሚቃወሙትም ምልክት ይሆን ዘንድ የተሠየመ ነው.......
ጎሥዐ ልብየ ቃለ ሰናየ
ወአነ አየድዕ ግብርየ ለንጉሥ
ከመ ቀለመ ጸሐፊ ዘጠበጠበ ይጽሕፍ ልሳን
የልቤ መልካም ነገርን ተናገረ
እኔም ሥራዬን ለንጉሥ እናገራለሁ
አንደበቴ እንደ ፈጣን ጸሓፊ ብዕር ነው
13 Feb, 18:36
ይህንም ሲሰሙ ምሳሌ መስሎ ነገራቸው፤ ወደ ኢየሩሳሌም ቀርቦ ነበርና፤ እነርሱም የእግዚአብሔር መንግሥት ወዲያውኑ የምትገለጥ መስሎአቸው ነበርና። "እንዲህም አለ፥ “አንድ የከበረ ሰው መንግሥት ይዞ ሊመለስ ወደ ሩቅ ሀገር ሄደ። "ዐሥሩን አገልጋዮቹንም ጠርቶ ዐሥር ምናን ሰጣቸውና፦ እንግዲህ እስክመለስ ድረስ ነግዱ አላቸው። "የሀገሩ ሰዎች ግን ይጠሉት ነበርና፥ ይህ በእኛ ላይ ሊነግሥ አንሻም ብለው አከታትለው መልእክተኞችን ላኩ። ከዚህም በኋላ፤ መንግሥትን ይዞ በተመለሰ ጊዜ እንደ አተረፉ ያውቅ ዘንድ ምናን የሰጣቸውን ብላቴኖቹን እን ዲያመጡአቸው አዘዘ። አንደኛውም መጥቶ፦ አቤቱ፥ ምናንህ ዐሥር ነበር፤ እነሆ ዐሥር ምናን አትርፌአለሁ አለው። "ጌታውም፦ መልካም፥ አንተ በጎ አገልጋይ በጥቂት የታመንህ ስለሆንህ በብዙ ላይ እሾምሃለሁ፤ በዐሥሩ ከተሞች ላይ ተሾም አለው። ሁለተኛውም መጥቶ፦ አቤቱ፥ ምናንህ አምስት ነበር ፤ አምስት አትርፌአለሁ አለው። “እርሱንም፦ አንተም በአምስት ከተሞች ተሾም አለው። ሦስተኛውም መጥቶ እንዲህ አለው፦ አቤቱ፥ በእኔ ዘንድ የነበረቺው ምናንህ እነኋት፤ በጨርቅ ጠቅልዬ አኑሬአት ነበር። አንተ ያላኖርኸውን የምትወስድ፥ ያልዘራኽውን የምታጭድ፥ ያልበተንኸውንም የምትሰበስብ፡ ጨካኝ ሰው እንደ ሆንህ ስለማውቅህ ፈርቼሃለሁና። ጌታውም እንዲህ አለው፦ አንተ ክፉ ሰነፍ አገልጋይ፥ እኔ ያላስቀመጥሁትን የምወስድ፥ ያልዘራሁትን የማጭድ፥ ያልበተንሁትንም የምሰበስብ ጨካኝ ሰው እንደሆንሁ ታውቃለህን? እንደ ቃልህ እፈርድብሃለሁ። “ለምን ገንዘቤን ወደ ለዋጮች አላስገባህም? እኔም መጥቼ ከትርፉ ጋር በወሰድሁት ነበር። ከዚያ የቆሙትንም፦ ይህን ምናን ከእርሱ ተቀብላችሁ ዐሥር ምናን ላለው ስጡት አላቸው። እነርሱም አቤቱ፥ ዐሥር ምናን ያለው አይደለምን? አሉት። “እርሱም እንዲህ አላቸው:- ላለው ሁሉ ይሰጡታል፤ ይጨምሩለታልም፤ የሌለውን ግን ያን ያለውንም ቢሆን ይወስዱበታል። ነገር ግን እነዚያን ልነግሥባቸው ያልወደዱትን ጠላቶቼን ወደዚህ አምጡና በፊቴ ውጉአቸው”.........
13 Feb, 18:36
11 Feb, 18:53
ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያንም ከሰማይምልክትን ያሳያቸው ዘንድ ሊፈትኑት መጡ። ፤ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፥ “በመሸ ጊዜ ሰማዩ ቀልትዋልና ጊዜው ብራ ነው ትላላችሁ። ፤በነጋም ጊዜ ሰማዩ ደምኖ ቀልቶአልና ዛሬስ ይዘንማል ትላላችሁ፤ እናንተ ግብዞች፥ የሰማዩን ፊት መተርጐም ታውቃላችሁ፤ የዘመኑንስ ምል ክት እንዴት አታውቁም? ክፉና፤ አመን ዝራ ትውልድ ምልክትን ትሻለች፤ ምልክት ግን ከነቢዩ ከዮናስ ምልክት በቀር አይሰጣ ትም” ከዚህም በኋላ ትቶአቸው ሄደ......
ኵሉ ማዕበልከ ወሞገድክ እንተ ላእሌየ ኀለፈ
መዓልተ ይኤዝዝ እግዚአብሔር ሣህሎ ወሌሊተ ይነግር
እምኀቤየ ብዕዐተ ሕይወትየ ለእግዚአብሔር
11 Feb, 18:53
10 Feb, 19:19
ብዙ ሕዝብም በተሰበሰቡ ጊዜ እንዲህ ይል ጀመር፦ይህ ትውልድ ክፉ ነው ምልክት ይፈልጋል ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም፡፡ ዮናስ ለነነዌ ሰዎች ምልክት እንደ ሆናቸው እንዲሁ ደግሞ የሰው ልጅ ለዚህ ትውልድ ምልክት ይሆናል፡፡ ንግሥተ አዜብ በፍርድ ከዚህ ትውልድ ሰዎች ጋራ ተነሥታ ትፈርድባቸዋለች የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና እንሆም ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ.......
ወፈርሃ ኵሉ ሰብእ
ወነገሩ ግብረ እግዚአብሔር
ወአዕመሩ ምግባሮ
10 Feb, 19:19
09 Feb, 19:04
09 Feb, 19:04
በዚያን ጊዜ ከጻፊዎችና ከፈሪሳውያን አንዳንዶቹ መለሱና፦መምህር ሆይ ከአንተ ምልክት እንድናይእንወዳለን አሉ። እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው፦ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም፡፡ ዮናስ በዓሣ ዐንበሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል። የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋራ ተነሥተው ይፈርዱበታል በዮናስ ስብከት ንስሓ ገብተዋልና እንሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ፡፡ ንግሥተ አዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋራ ተነሥታ ትፈርድበታለች የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና እንሆም ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ
አለ
........
አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዓዕ እግዚአብሔር
ወኢትትኀጐሉ እምፍኖተ ጽድቅ
ሶበ ነደት ፍጡነ መዓቱ
07 Feb, 18:45
እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ ጰራቅሊጦስ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመስክራል። “እናንተም ትመሰክራላችሁ፤ ከጥንት ጀምሮ ከእኔ ጋር ኑራችኋልና።
“እንዳትሰናከሉ ይህን ነገርኋችሁ። "ከምኵራባቸው ያስወጡአችኋል፤ ደግሞም እናንተን የሚገድላችሁ ሁሉ ለእግዚአብሔር አገልግሎት የሚያቀርብ የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል። 'ይህንም የሚያደርጉባችሁ አብንም፥ እኔንም ስላላወቁ ነው። ነገር ግን ጊዜው ሲደርስ እኔ እንደ ነገርኋችሁ ታስቡ ዘንድ ይህን ነገርኋችሁ አስቀድሜ ግን ይህን አልነገርክኋችሁም ነበር ከእናንተ ጋር ነበርሁና አሁን ግን ወደ ላከኝ ወደ አብ እሄዳለሁ፤ ከእናንተ አንዱ እንኳ ወዴት ትሄዳለህ?” ብሎ አይጠይቀኝም። ነገር ግን ይህን ስለነገርኋችሁ በልባችሁ ኀዘን ሞላ።
"እኔ በእውነት የሚሆነውን እነግራችኋለሁ፤ እኔ ብሄድ ይሻላችኋል፤ እኔ ካልሄድሁ ጰራቅሊጦስ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ከሄድሁ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ። እርሱም በመጣ ጊዜ ዓለምን ስለ ኀጢአትና ስለ ጽድቅ፡ ስለ ፍርድም ይዘልፈዋል። “ስለ ኅጢኣት፡ በእኔ አላመኑምና ነው፣ 'ስለ ጽድቅ፥ እኔ ወደ ኣብ እሄዳለሁና፤ እንግዲህ ወዲህም አታዩምኝምና ነው ስለ ፍርድም፥ የዚህ ዓለም ገዢ ይፈረድበታልና ነው።
“የምነግራችሁ ብዙ ነገር ነበረኝ፣ ነገርግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም። "ያ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ግን ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ እርሱ ከራሱ አይናገርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል። እርሱም እኔን ያከብረኛል፤ ከእኔ ወስዶ ይነግራችኋልና። ለአብ ያለው ሁሉ የእኔ ነው፤ ስለዚህም ከእኔ ወስዶ ይነግራችኋል አልኋችሁ።
“ጥቂት ጊዜ አለ፤ አታዩኝምም፤ ደግሞም ጥቂት ጊዜ አለ፤ እንደገናም ታዩኛላችሁ፤ ወደ አብ እሄዳለሁና”......
ሣህሉ ለእግዚአብሔር መልዐ ምድረ
ወበቃለ እግዚአብሔር ጸንዐ ሰማያት
ወእምእስትንፋሰ አፉሁ ኵሉ ኃይሎሙ
07 Feb, 18:45
06 Feb, 19:44
በወሰዱትም ጊዜ የቀሬና ሰው ስምዖንን ከዱር ሲመለስ ያዙት፤ ከጌታችን ከኢየሱስም በስተኋላ መስቀሉን አሸከሙት። ብዙ ሰዎችም ተከተሉት፤ ሴቶችም “ዋይ ዋይ” እያሉ ያዝኑለትና ያለቅሱለት ነበሩ። ጌታችን ኢየሱስም መለስ ብሎ እንዲህ አላቸው፥ “እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች ሆይ፥ ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ እንጂ ለእኔስ አታልቅሱልኝ። መካኖች፥ ያልወለዱ ማኅፀኖችና ያላጠቡ ጡቶችም የተመሰገኑ ናቸው የሚሉበት ወራት ይመጣልና። ያንጊዜም ተራሮችን በላያችን ውደቁ፤ ኮረብቶችንም ሰውሩን ይሉአቸዋል........
ወይወስዱ ለንጉሥ ደናግለ ድኅሬሃ
ወቢጻሂ ይወስዱ ለከ
ወይወስድዎን በትፍሥሕት ወበሐሤት
06 Feb, 19:44
05 Feb, 16:34
05 Feb, 16:34
እርሱም ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምን ስለ ብርሃን ይመሰክር ዘንድ ለምስክርነት መጣ። ስለ ብርሃን ምስክር ሊሆን መጣ እንጂ እርሱ ራሱ ብርሃን አልነበረም።
"ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃንስ ወደ ዓለም የመጣው ነው። በዓለም ነበረ፤ ዓለሙም በእርሱ ሆነ፤ ዓለሙ ግን አላወቀውም። “ወደ ወገኖቹ መጣ፤ ወገኖቹ ግን አልተ ቀበሉትም። ለተቀበሉት ሁሉ ግን በስሙ ለሚያምኑ የእግዚአብሔር ልጆች እንዲሆኑ ሥልጣንን ሰጣቸው። "እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከሥጋዊና ከደማዊ ግብር ወይም ከወንድና ከሴት፤ ፈቃድ አልተወለዱም።
ያም ቃል ሥጋ ሆነ፤ በእኛም አደረ፤ ለአ ባቱ አንድ እንደ ሆነ ልጅ ክብር ያለ ክብሩን አየን፤ ጸጋንና እውነትን የተመላ ነው........
እስመ ፈላሲ አነ ውስተ ምድር
ወነግድ ከመ ኵሉ አበውየ
ስሕተኒ ከመ አዕርፍ
04 Feb, 18:07
04 Feb, 18:07
ጌታችን ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ጠርቶ፥ “እነዚህ ሰዎች ያሳዝኑኛል፤ በዚህ ከእኔ ጋር ከዋሉ ሦስት ቀን ነውና፤ የሚበሉትም የላቸውም፤ በመንገድ እንዳይደክሙ ጦማቸውን ላሰናብታቸው አልወድም” አላቸው። ደቀ መዛሙርቱም፥ “ይህን ያህል ሕዝብ የሚያጠግብ እንጀራ በምድረበዳ ከወዴት እናገኛለን?” አሉት። "ጌታችን ኢየሱስም፥ “ስንት እንጀራ አላችሁ?” አላቸው፤ እነርሱም፥ “ሰባት እንጀራ፥ ጥቂትም ዓሣ” አሉት። ሕዝቡንም በምድር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፤ ሰባቱን እንጀራና ዓሣውን ይዞ አመሰገነ፤ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው፤ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ አቀረቡ። ሁሉም በልተው ጠገቡ፤ የተረፈውንም ቍርስራሽ ሰባት ቅርጫት ሙሉ አነሡ። የበሉት ሰዎችም ከሴቶችና ከልጆች በቀር አራት ሺህ ወንዶች ነበሩ። ሕዝቡንም አሰናብቶ ወደ ታንኳው ገባ፤ ወደ መጌዶል አገርም ሄደ........
አዝነመ ሎሙ መና ይብልዑ
ወወሀቦሙ ኅብስተ ሰማይ
ወኅብስተ መላእክቲሁ በልዑ እጓለ እመሕያው
ጸገብነ እግዚኦ እምበረከተ ቤትከ
ቅዱስ ጽርሕከ ወመንክር በጽድቅ
ስምዐነ አምላክነ ወመድኃኒነ
03 Feb, 19:23
እነዚያም ከሄዱ በኋላ፥ ጌታችን ኢየሱስ ስለ ዮሐንስ ለሕዝቡ እንዲህ ይላቸው ጀመረ፥ “ምን ልታዩ ወደ ምድረ በዳ ወጥታችኋል? ከነፋስ የተነሣ የሚወዛወዘውን ሸንበቆ ነውን? ፤ወይስ ምን ልታዩ ወጥታችኋል? ቀጭን ልብስ የለበሰ ሰውን ነውን? እነሆ፥ ቀጭን ልብስ የሚ ለብሱስ በነገሥታት ቤቶች አሉ። ምን ልታዩ ወጥታችኋል? ነቢይን ነውን? አዎን፤ እሱ ከነቢይ እጅግ ይበልጣል እላችኋለሁ። እነሆ፥ እኔ በፊትህ መንገድህን የሚጠርግ መልእክተኛዬን በአንተ ፊት እልካለሁ ተብሎ ስለ እርሱ የተጻፈለት ይህ ነውና። “እውነት እላችኋለሁ፤ ሴቶች ከወለዱአቸው ወገን ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም፤ በመንግሥተ ሰማያት ግን የሚያንሰው ይበልጠዋል። «ከመጥምቁ ከዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ መንግሥተ ሰማያት ትገፋለች፤ የተገፉትም ይናጠቁአታል። "ነቢያትም ሁሉ፥ ኦሪትም እስከ ዮሐንስ ትንቢትን ተናግረዋልና። ልትቀበሉትስ ብትወድዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይህ ነው......
እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኵሎ ዓሚረ
ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ
ንቃሕ እግዚኦ ለምንት ትነውም
03 Feb, 19:23
03 Feb, 06:00
03 Feb, 06:00
ከዚህም በኋላ በአንዲት ቦታ ጸለየ፤ ጸሎቱን በጨረሰ ጊዜም ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ፥ “ጌታ ሆይ፥ ዮሐንስ ለደቀ መዛሙርቱ እንደ አስተማራቸው ጸሎት አስተምረን” አለው። 'እርሱም እንዲህ አላቸው፥ “በምትጸልዩበት ጊዜ እንዲህ በሉ፦ በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፥ ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነ እንዲሁም በምድር ይሁን። 'የዕለት ምግባችንን በየዕለቱ ስጠን። "እኛም የበደለንን ሁሉ ይቅር እንድንል በደላችንን ይቅር በለን፤ አቤቱ፥ ወደ ፈተና አታግባን፤ ከክፉ ሁሉ አድነን እንጂ።”
እንዲህም አላቸው፥ “ከመካከላችሁ ወዳጅ ያለው ሰው ቢኖር በመንፈቀ ሌሊትም ወደ እርሱ ሄዶ እንዲህ ቢለው:- “ወዳጄ ሆይ ሦስት እንጀራ አበድረኝ። 'ወዳጄ ከመንገድ መጥቶብኛልና የማቀርብለት የለኝም። ያ ወዳጁም ከውስጥ ሆኖ፦ “አትዘብዝበኝ፤ ደጁን አጥብቀን ዘግተናል፤ ልጆችም ከእኔ ጋር በአልጋ ላይ ተኝተዋል እሰጥህ ዘንድ መነሳት አልችልም” ይለዋልን? ወዳጁ ስለሆነ ሊሰጠው ባይነሣ እንኳ እንዳይዘበዝበው ተነሥቶ የወደደውን ያህል ይሰጠዋል። እኔም እላችኋለሁ:-ለምኑ፥ ይሰጣችኋልም፤ ፈልጉ፥ ታገኛላች ሁም፣ ደጅ ምቱ፥ ይከፈትላችኋልም። የሚለምን ሁሉ ይሰጠዋልና፤ የሚፈልግም ያገኛ ልና፤ ደጅ ለሚመታም ይከፈትለታልና። “ከአናንተ መካከል ልጁ ዳቦ የሚለምነው አባት ቢኖር ድንጋይ ይሰጠዋልን? ዓሣ ቢለምነውስ በዓሣ ፋንታ እባብን ይሰጠዋልን? “ወይስ ዕንቍላል ቢለምነው በዕንቍላል ፋንታ ጊንጥ ይሰጠዋልን? “እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታን መስጠትን የምታውቁ ከሆነ፥ የሰማይ አባታችሁማ ለሚለምኑት መልካሙን ሀብተ መንፈስ ቅዱስ፤ እንዴት አብዝቶ ይሰጣቸው ይሆን?”
"ዲዳና ደንቆሮ፤ ጋኔንንም ያወጣ ነበር፤ ጋኔኑም በወጣ ጊዜ ዲዳና ደንቆሮ የነበረው ተና ገረ፤ ሰዎችም አደነቁ። ነገር ግን ከመካከላቸው፥ “በአጋንንት አለቃ በብዔል ዜቡል አጋንንትን ያወጣቸዋል” ያሉ ነበሩ፤ እርሱም መልሶ፥ “ሰይጣን ሰይጣንን ማውጣት እንደ ምን ይቻለዋል?” አላቸው። "ሌሎችም ሊፈትኑት ከእርሱ ዘንድ ከሰማይ ምልክትን ይፈልጉ ነበር። “እርሱ ግን የሚያስቡትን ዐወቀባቸውና እንዲህ አላቸው፥ “እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁሉ ትጠፋለች፤ ቤትም እርስ በርሱ ቢለያይ ያ ቤት ይወድቃል። ።ሰይጣንስ እርስ በርሱ ከተለያየ መንግሥቱ እንዴት ይጸናል? በአጋንንት አለቃ በብዔል ዜቡል አጋንንትን ያወጣል ትላላችሁና.........
እበውዕ ቤተከ ምስለ መባዕየ
ወእሁብ ብፅዓትየ ዘነበብኩ በአፉየ
ዘእቤ በከናፍርየ አመ ምንዳቤየ
01 Feb, 18:02
01 Feb, 18:02
ዐሥራ ሁለት ዓመትም በሞላው ጊዜ እንደ አስለመዱ ወደ ኢየሩሳሌም ለበዓል ወጡ። ሥራቸውንም ጨርሰው ተመለሱ፤ ሕፃኑ ጌታችን ኢየሱስ ግን በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፤ ዮሴፍና እናቱም አላወቁም ነበር። በመንገድም ከሰዎች ጋር ያለ መስሎአቸው ነበር፤ ያንድ ቀን መንገድንም ከሄዱ በኋላ ዕለቱን ከዘመዶቹ፥ ከሚያውቁትም ዘንድ ፈለጉት። ባላገኙትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። " ከዚህም በኋላ በሦስተኛው ቀን በቤተ መቅደስ በሊቃውንት መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውና ሲጠይቃቸው አገኙት። "የሰሙትም ሁሉ አስተዋይነቱንና አመላለሱን ያደንቁ ነበር። በአዩትም ጊዜ ደነገጡ፤ እናቱም፡ “ልጄ፥ ለምን እንዲህ አደረግኸን? እነሆ አባትህም፥ እኔም ስንፈልግህ ደከምን” አለችው። "እርሱም፥ “ለምን ትፈልጉኛላችሁ? በአባቴ ቤት ልኖር እንደሚገባኝ አላወቃችሁምን?” አላቸው። እነርሱ ግን የነገራቸውን ቃል አላስተዋሉም። "ከእነርሱም ጋር ሂዶ ወደ ናዝሬት ወረደ፤ ይታዘዝላቸውም ነበር፤ እናቱ ግን ይህን ሁሉ ነገር ትጠብቀው፥ በልብዋም ታኖረው፤ ነበር። ጌታችን ኢየሱስም በእግዚአብሔር ዘንድ፥ በሰውም ዘንድ፥ በጥበብና በአካል በሞገስም አደገ.........
እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ
ግበሩ በዐለ በትፍሥሕት በኀበ እለ ያስተሐምምዎ
እስከ አቅርንቲሁ ለምሥዋዕ
31 Jan, 19:01
13 Jan, 18:10
12 Jan, 17:40
ጲላጦስም እንደገና ወደ ፍርድ አደባባይ ገብቶ ጌታችን ኢየሱስን ጠራና፥ “የአይሁድ ንጉሥ አንተ ነህን?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም፥ “ይህን የምትናገር ከራስህ ነውን? ወይስ ስለ እኔ የነገረህ ሌላ አለን?” ብሎ መለሰለት። ጲላጦስም መልሶ፥ “እኔ አይሁዳዊ ነኝን? ለእኔ አሳልፈው የሰጡህ ወገኖችህና ሊቃነ ካህናት አይደሉምን? ኧረ ምን አድርገሃል?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም፥ “የእኔ መንግሥት ከዚህ ዓለም አይደለችም፤ መንግሥቴስ በዚህ ዓለም ብትሆን ኖሮ ለአይሁድ እንዳልሰጥ አሽከሮቼ በተዋጉልኝ ነበር፤ አሁንም መንግሥቴ ከዚህ አይደለችም” ብሎ መለሰለት። ጲላጦስም፥ “እንግዲያ አንተ ንጉሥ ነህን?” አለው፤ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፥
“እኔ ንጉሥ እንደ ሆንሁ አንተ ራስህ ትላለህ፤ እኔ ስለዚህ ተወለድሁ፤ ስለዚህም ለእውነት ልመሰክር ወደ ዓለም መጣሁ፤ ከእውነት የሆነ ሁሉ ቃሌን ይሰማኛል” አለው............
12 Jan, 17:40
12 Jan, 11:19
12 Jan, 03:08
11 Jan, 18:02
በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በይሁዳ ክፍል በቤተ ልሔም ጌታችን ኢየሱስ በተወለደ ጊዜ፥ እነሆ፥ ሰብአ ሰገል ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ። ፤እንዲህ ሲሉ፥ “ኮከቡን በምሥራቅ አይተን እንሰግድለት ዘንድ መጥተናልና፥ የተወ ለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው?” ፤ንጉሥ ሄሮድስም በሰማ ጊዜ ደነገጠ፤ ኢየሩሳሌምም በመላዋ ከእርሱ ጋር ደነገጠች። ፤የካህናት አለ ቆችንና የሕዝቡን ጻፎች ሁሉ ሰብስቦ “ክርስቶስ በየት ይወለዳል?” ብሎ ጠየቃቸው። እንዲህም አሉት፤ “በይሁዳ ክፍል በቤተ ልሔም ነው፤ በነቢይ እንዲህ ተብሎ ተጽፎአ ልና። የይሁዳ ምድር አንቺ ቤተ ልሔም ከይ ሁዳ አለቆች፤ ከቶ አታንሽም፤ ሕዝቤን እስራ ኤልን የሚጠብቅ ንጉሥ ከአንቺ ይወጣልና።” ከዚህም በኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገልን በስውር ጠራቸው፤ ኮከቡ የታየበትንም ዘመን ከእነርሱ ተረዳ። “ሂዳችሁ የዚያን ሕፃን ነገር ርግ ጡን መርምሩ፤ ያገኛችሁትም እንደ ሆነ እኔም መጥቼ እሰግድለት ዘንድ በእኔ በኩል ተመልሳችሁ ንገሩኝ” ብሎ ወደ ቤተ ልሔም ሰደዳቸው። እነርሱም ከንጉሡ ሰምተው ሄዱ፤ እነሆ፥ በምሥራቅ ያዩት ኮከብ ሕፃኑ በአለበት ቦታ ላይ ደርሶ እስኪቆም ድረስ ይመራቸው ነበር። ፤ኮከቡንም አይተው ታላቅ ደስታ ደስ አላቸው።ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አገኙት፤ ወድቀውም ሰገዱለት፤ ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው ወርቅና ዕጣን፥ ከርቤም፥ እጅ መንሻ አቀረቡለት። ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ነገራ ቸው፤ በሌላ መንገድም ወደ ሀገራቸው ሄዱ........
ወአነሂ በኵርየ እሬስዮ
ወልዑል ውእቱ እምነገሥተ ምድር
ወለዓለም አዐቀብ ሎቱ ሣህልየ
11 Jan, 18:02
10 Jan, 17:31
እነርሱም ከሄዱ በኋላ እነሆ፥ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ፥ “ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይሻዋልና ተነሣ፤ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ምድረ ግብፅ ሽሽ፤ እስክነግርህም ድረስ በዚያ ኑር” አለው፤ "እርሱም በሌሊት ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ ግብፅ ሄደ። ።ከእግዚአብሔር ዘንድ “ልጄን ከግብፅ ጠራሁት” ተብሎ በነቢይ የተ ነገረው ይፈጸም ዘንድ፣ ሄሮድስም እስኪሞት ድረስ በዚያ ኖረ።
ከዚህም በኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገል እንደ ተዘባበቱበት ባየ ጊዜ እጅግ ተቈጣና ጭፍራዎቹን ልኮ ከሰብአ ሰገል እንደ ተረዳው ዘመን ልክ ሁለት ዓመት የሆናቸውን፥ ከዚያም የሚያንሱትን፥ በቤተ ልሔምና በአውራጃዎችዋ ሁሉ የነበሩትን ሕፃናት አስገደለ። "ያንጊዜ፥ በነቢዩ በኤርምያስ የተነገረው ተፈጸመ፤ እንዲህ ሲል፦ “ራሔል ስለ ልጆችዋ ስታለቅስ ብዙ ልቅሶና ዋይታ በራማ ተሰማ፣ መጽናናትንም እንቢ አለች፤ ልጆችዋ የሉምና።”
“ሄሮድስም በሞተ ጊዜ እነሆ፥ የእግዚእ ብሔር መልአክ በግብፅ ሀገር ለዮሴፍ በሕ ልም ታየው። እንዲህ ሲል፡ “የሕፃኑን ነፍስ የሚሹ ሙተዋልና፥ ተነሥተህ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ እስራኤል ሀገር ሂድ።” እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ እስራኤል ምድር ገባ። “አርኬላኦስም በአባቱ በሄሮድስ ፋንታ በይሁዳ እንደ ነገሠ በሰማ ጊዜ፥ ወደዚያ ለመሄድ ፈራ፤ በሕልምም ተገልጦለት ወደ ገሊላ አውራጃ ሄደ። በነቢያት “ልጄ ናዝራዊ ይባላል” የተባለው ይፈጸም ዘንድ ናዝሬት ወደ ምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ.........
10 Jan, 17:20
10 Jan, 04:44
09 Jan, 19:54
09 Jan, 19:54
እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ ጸሎታችሁን በማብዛት ምክንያት የመበለቶችን ገንዘብ ስለምትበሉ ወዮላችሁ! ስለዚህ ጽኑ ፍርድን ትቀበላላችሁ። እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ መንግሥተ ሰማያትን በሰው ፊት ስለምትዘጉ ወዮላችሁ! እናንተም አትገቡም፤ የሚገቡትንም ከመግባት ትከለክሉአቸዋላችሁ። እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳው ያን፥ አንድን ሰው ለማሳመን ባሕሩንና የብሱን ስለምትዞሩ ወዮላችሁ! ካመነም በኋላ ከእናንተ ይልቅ ሁለት እጥፍ የገሃነም ልጅ ታደርጉታላችሁ። "በቤተ መቅደስ የሚምል ኀጢአት የለበትም፤ በቤተ-መቅደስ ወርቅ የሚምል ግን ይበድላል የምትሉ ዕውራን መሪዎች እናንተ ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ ወዮላችሁ! ”እናንተ ደንቆሮዎችና ዕውሮች፥ የትኛው ይበልጣል? ወርቁ ነውን? ወይስ ወርቁን የሚቀድ ሰው ቤተ መቅደስ? ፤ደግማችሁም በመሠዊ ያው የሚምል አይበድልም፤ በላዩ በአለው በመ ሥዋዕቱ የሚምል ግን ይበድላል ትላላችሁ። "እናንተ ሰነፎችና ዕውራን፥ የትኛው ይበልጣል? መሥዋዕቱ ነውን? ወይንስ መሥዋዕቱን የሚቀድሰው መሠዊያው? በመሠዊያው የሚምል በእርሱ ይምላል፤ በእርሱ ላይም ባለው ሁሉ ይምላል። “በቤተ መቅደስም የሚምል በእርሱና በውስጡ በሚኖረው ሁሉ ይምላል
.....
09 Jan, 18:16
08 Jan, 17:23
“ሌላ ምሳሌ ስሙ፤ ባለቤት ሰው ወይንን ተክለ፡ ቅጥርም ቀጠረለት፤ መጭመቂያም አስቆፈረለት ግንብም ሠራለት፤ ለገባሮችም ሰጥቷአየው ሄደ የሚያፈራበት ወራት በደረሰ ጊዜም፥ ከወይኑ ፍሬ ያመጡለት ዘንድ አገልጋዮችን ወደ ገባሮቹ ላከ። ገባሮቹም አገልጋዮ ቹን ይዘው፥ አንዱን በበትር ደበደቡት፤ አንዱንም ገደሉት፤ ሌላውንም በድንጋይ መቱት። ከዚያም በኋላ ከቀደሙት የሚበዙ ሌሎች አገልጋዮችን ላከ፤ እነርሱንም እንዲሁ አደረጉባቸው። በኋላም ልጄንስ ይፈሩት ይሆናል ብሎ ልጁን ላከ። ገባሮቹም ልጁን ባዩት ጊዜ እርስ በርሳቸው፦ እነሆ፥ ወራሹ ይህ ነው፤ ኑ እንግደለውና ርስቱን እንውረስ ተባባሉ። ይዘውም ከወይኑ ቦታ ወደ ውጭ አውጥተው ገደሉት። “እንግዲህ የወይኑ ቦታ ባለቤት በመጣ ጊዜ እነዚህን ገባሮች ምን ያደርጋቸዋል?” እነርሱም፥ “ክፉዎችን በክፉ ያጠ ፋቸዋል፤ ወይኑንም በየጊዜው ፍሬውን ለሚሰ ጡት ለሌሎች ገባሮች ይሰጣል” አሉት።
ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፡ “በመጻሕፍት ያለውን ያነበባችሁበት ጊዜ የለ ምን? ግንበኞች የናቁአት ድንጋይ የማዕዘን ራስ ሆነች፤ ይህቺም ከእግዚአብሔር ዘንድ ሆነች፤ ለዐይኖቻችንም ድንቅ ናት። "ስለዚህም እላ ችኋለሁ፤
የእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ትወሰዳለች፤ ፍሬዋንም ለሚያደርጉ ለአሕዛብ ትሰጣለች። በዚያችም ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ይቀጠቀጣል፤ በላዩ የምትወድቅበትንም ትፈጨዋለች።የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያንም ምሳሌዎቹን በሰሙ ጊዜ፥ ስለ እነርሱ እንደተናገረ ዐወቁ። ሊይዙትም ሲፈልጉ ሕዝቡን ፈሩአቸው፤ በእነርሱ ዘንድ እንደ ነቢይ ነበርና.........
08 Jan, 17:23
07 Jan, 22:31
05 Jan, 17:54
የዳዊት ልጅ፥ የአብርሃም ልጅ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ መጽሐፍ፤ ፤አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ። 'ይሁዳም ከትእማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ፤ ፋሬስም ኤስሮምን ወለደ፤ ኤስሮምም አራምን ወለደ። አራምም አሚናዳብን ወለደ፤ አሚናዳብም ነአሶንን ወለደ፤ ነአሶንም ሰልሞንን ወለደ። ሰልሞንም ከራኬብ ቦኤዝን ወለደ፤ ቦኤዝም ከሩት ኢዮቤድን ወለደ፤ ኢዮቤድም እሴይን ወለደ። ፤እሴይም ንጉሥ ዳዊትን ወለደ።
፤ንጉሥ ዳዊትም ከኦርዮ ሚስት ሰሎሞንን ወለደ፤ ሰሎሞንም ሮብዓምን ወለደ፤ ሮብዓ ምም አብያን ወለደ፤ አብያም አሳፍን ወለደ። አሳፍም ኢዮሳፍጥን ወለደ፤ ኢዮሳፍጥም ኢዮ ራምን ወለደ፤ ኢዮራምም ዖዝያንን ወለደ። ፤ዖዝያንም ኢዮአታምን ወለደ፤ ኢዮአታምም አካዝን ወለደ፤ አካዝም ሕዝቅያስን ወለደ። ፤ሕዝቅያስም ምናሴን ወለደ፤ ምናሴም አሞጽን ወለደ፤ አሞጽም፤ ኢዮስያስን ወለደ። “ኢዮስ ያስም በባቢሎን ምርኮ ጊዜ ኢኮንያንንና ወንድሞቹን ወለደ።
ከባቢሎን ምርኮም በኋላ ኢኮንያን ሰላትያልን ወለደ፤ ሰላትያልም ዘሩባቤልን ወለደ። “ዘሩባቤልም አብዩድን ወለደ፤ አብዩድም ኤልያቄምን ወለደ፤ ኤልያቄምም አዛርን ወለደ። አዛርም ሳዶቅን ወለደ፤ ሳዶቅም አኪምን ወለደ፤ አኪምም ኤልዩድን ወለደ። ኤልዩድም አልዓዛርን ወለደ፤ አልዓዛርም ማትያንን ወለደ፤ ማትያንም ያዕቆብን ወለደ። ያዕቆብም ክርስቶስ የተባለ ጌታ ኢየሱስ ከእርስዋ የተወለደ የማርያምን እጮኛ ዮሴፍን ወለደ።
እንግዲህ ትውልድ ሁሉ ከአብርሃም እስከ ዳዊት ዐሥራ አራት ትውልድ፥ ከዳዊትም እስከ ባቢሎን ምርኮ ዐሥራ አራት ትውልድ፥ ከባቢሎንም ምርኮ እስከ ክርስቶስ ዐሥራ አራት ትውልድ ነው። ትውልድም ሁሉ ከአ ብርሃም እስከ ክርስቶስ ዐርባ ሁለት ትውልድ ነው.........
05 Jan, 17:54
04 Jan, 16:53
“እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ ወደ በጎች ስፍራ በበሩ የማይገባ፥ በሌላም በኩል የሚ ገባ ሌባ፥ ወንበዴም ነው። በበሩ የሚገባ ግን የበጎች ጠባቂ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍ ትለታል፤ በጎቹም ቃሉን ይሰሙታል፤ እር ሱም በጎቹን በየስማቸው ይጠራቸዋል፤ አው ጥቶም ያሰማራቸዋል። 'ሁሉንም አውጥቶ ባሰ ማራቸው ጊዜ በፊት በፊታቸው ይሄዳል፤ በጎ ቹም ይከተሉታል፤ ቃሉን ያውቃሉና። *ሌላ ውን ግን ይሸሹታል እንጂ አይከተሉትም፤ የሌ ላውን ቃሉን አያውቁምና።” ጌታችን ኢየሱ ስም ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ እነርሱ ግን የነገ ራቸውን አላወቁም። "ዳግመኛም ጌታችን ኢየሱስ እንዲህ አላ ቸው፥ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ የበጎች በር እኔ ነኝ። #ከእኔ በፊት የመጡ ሁሉ ሌቦ ችና ወንበዴዎች ናቸው፤ ነገር ግን፣ በጎች አልሰሙአቸውም። እውነተኛዉ የበጎች በር እኔ ነኝ፤ በእኔ በኩልም የሚገባ ይድናል፤ ይገ ባልም ይወጣልም፤ መሰማርያም ያገኛል። ፤ሌባ ግን ሊሰርቅና ሊያርድ፥ ሊያጠፋም ካልሆነ በቀር አይመጣም፤ እኔ ግን የዘለዓለም፤ ሕይ ወትን እንዲያገኙ፥ እጅግም እንዲበዛላቸው መጣሁ። “ቸር ጠባቂ እኔ ነኝ፤ ቸር ጠባቂ ስለ በጎቹ ነፍሱን ይሰጣል። "ጠባቂ ያይደለ፥ በጎ ቹም ገንዘቡ ያይደሉ ምንደኛ ግን፥ ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵ ላም መጥቶ በጎቹን ይነጥቃቸዋል፥ ይበትናቸዋ ልም። "ምንደኛስ ይሸሻል፤ ስለ በጎቹም አያ ዝንም፤ ምንደኛ ነውና። "ቸር ጠባቂ እኔ ነኝ፤ የእኔ የሆኑትን መንጋዎቼን አውቃለሁ፤ የእኔ የሆኑትም ያውቁኛል። አብ እኔን እንደሚያው ቀኝ እኔም አብን አውቀዋለሁ፤ ለበጎችም ቤዛ አድርጌ ሰውነቴን አሳልፌ እሰጣለሁ። "ከዚህ ቦታ ያይደሉ ሌሎች በጎችም አሉኝ፤ እነር ሱንም ወደዚህ አመጣቸው ዘንድ ይገባኛል፤ ቃሌንም ይሰሙኛል፤ ለአንድ እረኛም አንድ መንጋ ይሆናሉ። ”ስለዚህም፤ አብ ይወድደ ኛል፥ እንደ ገና አስነሣት ዘንድ እኔ ነፍሴን እሰ ጣለሁና። *ከእኔ ማንም አይወስዳትም፤ ነገር ግን እኔ በፈቃዴ እሰጣታለሁ፤ እኔ ላኖራት ሥልጣን አለኝ፤ መልሼ እወስዳት ዘንድ ሥልጣን አለኝና፤ ይህንም ትእዛዝ ከአባቴ ተቀበ ልሁ።” አይሁድ ለሁለተኛ ጊዜ ስለ መለያየታቸው "ስለዚህም ነገር አይሁድ እንደገና እርስ በር ሳቸው ተለያዩ። “ከእነርሱም ብዙዎች፥ “ጋኔን ይዞት ያብዳል፤ ለምንስ ታዳምጡታላችሁ?” አሉ። ሌሎችም ይህ ነገር ጋኔን ከያዘው ሰው የሚገኝ አይደለም፤ ጋኔን የዕዉሮችን ዐይን ማብራት ይችላልን?” አሉ..........
ኖላዊሆሙ ለእስራኤል ለእስራኤል አጽምዕ
ዘይርዕዮሙ ከመ አባግዐ ዮሴፍ
ዘይነብር ላዕለ ኪሩቤል አስተርእየ
04 Jan, 16:10
04 Jan, 06:39
03 Jan, 20:05
ያንጊዜም መንግሥተ ሰማያት መብራታቸውን ይዘው ሙሽራውን ለመቀበል የወጡ ዐሥሩን ደናግል ትመስላለች። ከእነርሱም ውስጥ አምስቱ ሰነፎች፥ አምስቱም ልባሞች ነበሩ። ሰነፎቹ መብራታቸውን ይዘው ዘይት አልያዙም ነበር። ልባሞቹ ግን ከመብራታቸው ጋር በማሰሮቻቸው ዘይት ይዘው ነበር። ሙሽራውም በዘገየ ጊዜ ሁሉም አንቀላፉና ተኙ። መንፈቀ ሌሊት በሆነም ጊዜ “እነሆ ሙሽራ መጣ፤ ልትቀበሉት ውጡ” የሚል ጩኸት ሆነ። ያንጊዜ እነዚያ ደናግል ሁሉ ነቁና መብራታቸውን አዘጋጁ። እነዚያ ሰነፎችም ልባሞችን፦ መብራታችን ሊጠፋብን ነውና ከዘይታችሁ ስጡን አሉአቸው። ልባሞ ችም፦ ለእኛና ለእናንተ የሚበቃ የለም፤ ነገር ግን ወደሚሸጡ ሂዱና ለራሳችሁ ግዙ ብለው መለሱላቸው። ሊገዙም እንደ ሄዱ ሙሽራው መጣ፤ እነዚያም የተዘጋጁት ከእርሱ ጋር ወደ ሰርጉ ገቡ፤ ደጁም ተዘጋ። በኋላም እነዚያ ደናግል መጥተው፦ አቤቱ አቤቱ ክፈትልን አሉ። እርሱ ግን መልሶ፦
እውነት እላች ጓለሁ፤ አላውቃችሁም አላቸው። "እንግዲህ ትጉ፤ የሰው ልጅ የሚመጣባትን ቀኒቱንና ሰዓ ቲቱን አታውቁምና.........
03 Jan, 20:05
02 Jan, 18:53
02 Jan, 18:53
ከዚህም በኋላ ሕዝቡን ትቶ ወደ ቤት ገባ፤ ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ ቀርበው “የእርሻውን እንክርዳድ ምሳሌ ተርጒምልን” አሉት። እርሱም መልሶ አላቸው፤ “መልካም ዘርን የዘራ የሰው ልጅ ነው። እርሻውም ዓለም ነው፤ መልካሙም ዘር የመንግሥት ልጆች ናቸው፤ እንክርዳዱም የክፉው ልጆች ናቸው። የዘራውም ጠላት ዲያብሎስ ነው፤ መከሩም የዓለም ፍጻሜ ነው፤ አጫጆ ቹም መላእክት ናቸው። “እንግዲህ አስቀድሞ እንክርዳዱን እንደሚለቅሙት፥ በእሳትም እንደሚያቃጥሉት በዚህ ዓለም ፍጻሜም እንዲሁ ይሆናል። የሰው ልጅም መላእክቱን ይልካል፤ ከመንግሥቱም ዐላውያንንና በደልን የሚያደርጉትን ሁሉ ይሰበስባሉ። ወደ እሳት ጒድጓድም ይጥሉአቸዋል፤ በዚያም ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።
ያንጊዜም ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ፤ ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ......
ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም
ወከዐዉ ደሞሙ ከመ ማይ ዐውዳ ለኢየሩሳሌም
ወኀጥኡ ዘይቀብሮሙ
02 Jan, 07:16
በዚያች ሰዓት ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ ቀርበው በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ የሚበልጥ ማን ይሆን? አሉት። ሕፃንም ጠርቶ በመካከላቸው አቆመ፡ እንዲህም አለ እውነት እላችኋለሁ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም። እንግዲህ እንደዚህ ሕፃን ራሱን የሚያዋርድ ሁሉ፥ በመንግሥተ ሰማያት የሚበልጥ እርሱ ነው። እንደዚህም ያለውን አንድ ሕፃን በስሜ የሚቀበል ሁሉ እኔን ይቀበላል፤ በእኔም ከሚያምኑ ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ሁሉ፥ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር። ወዮ ለዓለም ስለ ማሰናከያ፤ ማሰናከያ ሳይመጣ አይቀርምና፥ ነገር ግን በእርሱ ጠንቅ ማሰናከያ ለሚመጣበት ለዚያ ሰው ወዮለት። እጅህ ወይም እግርህ ብታሰናክልህ፥ ቈርጠህ ከአንተ ጣላት፤ ሁለት እጅ ወይም ሁለት እግር ኖሮህ ወደ ዘላለም እሳት ከምትጣል ይልቅ አንካሳ ወይም ጉንድሽ ሆነህ ወደ ህይወት መግባት ይሻልሀል። ዓይንህ ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት፤ ሁለት ዓይን ኖሮህ ወደ ገሃነመ እሳት ከምትጣል ይልቅ አንዲት ዓይን ኖራህ ወደ ሕይወት መግባት ይሻልሃል። ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁና። የሰው ልጅ የጠፋውን ለማዳን መጥቶአልና........
02 Jan, 07:16
01 Jan, 08:30
01 Jan, 08:30
ስለ ሙታን መነሣት ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእናንተ እንዲህ ተብሎ የተነገረውን አላነበባችሁምን? እኔ እግዚአብሔር የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ እንግዲህ
የሕያዋን አምላክ እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም።” ሕዝቡም ሰምተው ትምህርቱን አደነቁ። ፈሪሳውያንም ሰዱቃውያንን ምላሽ እንዳሳ ጣቸው በሰሙ ጊዜ በአንድነት ወደ እሱ ተሰ በሰቡ። ከመካከላቸውም አንድ ሕግ ዐዋቂ ሊፈትነው ጠየቀው። “መምህር ሆይ፥ ከኦሪት ማንኛይቱ ትእዛዝ ትበልጣለች?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አለው፥ “አምላክህ እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ፥ በፍጹም ነፍስህ፥ በፍጹም ኀይልህ ውደደው። ታላቂቱና የመጀመሪያይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። የምትመስላት ሁለተኛይቱም ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትለው ናት። “ኦሪትና ነቢያት ሁሉ በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ጸን ተዋል።”
ፈሪሳውያንም ተሰብስበው ሳሉ ጌታችን ኢየሱስ እንዲህ ብሎ ጠየቃቸው፦ “ስለ ክርስቶስ ምን ትላላችሁ? የማን ልጅ ነው?” እነርሱም፥ “የዳዊት ልጅ ነው” አሉት። ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፥ “እንግዲያ እርሱ ራሱ ዳዊት በመንፈስ ቅዱስ እንዴት እንዲህ አለ? “ጌታ ጌታዬን፦ ጠላቶችህን ከእግርህ በታች እስከ አደርጋቸው ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው። እርሱ ራሱ ዳዊት “ጌታዬ” ያለው፥ እንግዲህ እንዴት ልጁ ይሆነዋል?” አንድም ቃል እንኳ ሊመልስለት የቻለ የለም፤ ከዚያች ቀንም ጀምሮ ማንም ሊጠይቀው
አልደፈረም
.......
ለስሒት መኑ ይሌብዋ
እምኅቡዓትየ አንጽሐኒ
ወእምነኪር መሐኮ ለገብርከ
31 Dec, 09:22
ማርያምም በዚያ ወራት ተነሥታ ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ከተማ ፈጥና ወጣች፥ ወደ ዘካርያስም ቤት ገብታ ኤልሳቤጥን ተሳለመቻት። ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥ በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው። የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና። ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት። ማርያምም እንዲህ አለች ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፥ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤ የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤ ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጎአልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው። ምሕረቱም ለሚፈሩት እስከ ትውልድና ትውልድ ይኖራል። በክንዱ ኃይል አድርጎአል፤ ትዕቢተኞችን በልባቸው አሳብ በትኖአል፤ ገዥዎችን ከዙፋናቸው አዋርዶአል፤ ትሑታንንም ከፍ አድርጎአል፤ የተራቡትን በበጎ ነገር አጥግቦአል፤ ባለ ጠጎችንም ባዶአቸውን ሰዶአቸዋል። ለአባቶቻችን እንደ ተናገረ፥ ለአብርሃምና ለዘሩ ለዘላለም ምሕረቱ ትዝ እያለው እስራኤልን ብላቴናውን ረድቶአል። ማርያምም ሦስት ወር የሚያህል በእርስዋ ዘንድ ተቀመጠች ወደ ቤትዋም ተመለሰች......
ህየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ
ወትሰይሚዮሙ መላእክት ለኵሉ ምድር
ወይዘክሩ ስመኪ በኵሉ ትውልደ ትውልድ
31 Dec, 09:22
29 Dec, 18:46
እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ፥ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል። ዘካርያስም መልአኩን እኔ ሽማግሌ ነኝ ምስቴም በዕድሜዋ አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ? አለው። መልአኩም መልሶ እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፤ እነሆም፥ በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ፥ ይህ ነገር እስከሚሆን ቀን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ መናገርም አትችልም አለው። ሕዝቡም ዘካርያስን ይጠብቁት ነበር፤ በቤተ መቅደስም ውስጥ ስለ ዘገየ ይደነቁ ነበር። በወጣም ጊዜ ሊነግራቸው አልቻለም፥ በቤተ መቅደስም ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፤ እርሱም ይጠቅሳቸው ነበር፤ ድዳም ሆኖ ኖረ። የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሄደ። ከዚህም ወራት በኋላ ሚስቱ ኤልሳቤጥ ፀነሰችና ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ በተመለከተበት ወራት እንዲህ አድርጎልኛል፡ ስትል ራስዋን አምስት ወር ሰወረች። በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ፥ ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ። መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት። እርስዋም ባየችው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው? ብላ አሰበች። መልአኩም እንዲህ አላት ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ። እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ። እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘላለም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም.
.
..
29 Dec, 16:17
29 Dec, 10:53
29 Dec, 10:53
29 Dec, 07:47
28 Dec, 18:26
በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ። ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። በእርሱ ሕይወት ነበረች፥ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረች። ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም።
ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምኑ ይህ ስለ ብርሃን ይመሰክር ዘንድ ለምስክር መጣ። ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ እንጂ፥ እርሱ ብርሃን አልነበረም። ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ይመጣ ነበር። በዓለም ነበረ፥ ዓለሙም በእርሱ ሆነ፥ ዓለሙም አላወቀውም። የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።
ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን። ዮሐንስ ስለ እርሱ መሰከረ እንዲህም ብሎ ጮኸ ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ከእኔ በፊት ነበረና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል፤ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነበረ።
እኛ ሁላችን ከሙላቱ ተቀብለን በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጥቶናልና፤ ሕግ በሙሴ ተሰጥቶ ነበርና ጸጋና እውነት ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ሆነ።
መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ
ተረከው
...........
ፈኑ ብርሃነከ ወጽድቀከ
እማንቱ ይምርሓኒ ወይሰዳኒ ደብረ መቅደስከ
ወውስተ አብያቲከ እግዚእ
28 Dec, 18:25
28 Dec, 11:00
06 Dec, 18:19
ከሙታንስ ሲነሡ በሰማያት እንዳሉ መላእክት ይሆናሉ እንጂ አያገቡም፥ አይጋቡምም። ስለ ሙታን ግን እንዲነሡ እግዚአብሔር እኔ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ እንዳለው በሙሴ መጽሐፍ በቍጥቋጦው ዘንድ የተጻፈውን አላነበባችሁምን?
የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም። እንግዲህ እጅግ ትስታላችሁ.......
06 Dec, 18:19
05 Dec, 17:51
ከዚህም በኋላ ጌታ ሌሎቹን ሰብዓ ሾመ፥ ሁለት ሁለትም አድርጎ እርሱ ሊሄድበት ወዳለው ከተማና ስፍራ ሁሉ በፊቱ ላካቸው።አላቸውም መከሩስ ብዙ ነው፥ቀ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዴህ የመከሩን ጌታ ለመከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት። ሂዱ፤ እነሆ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ። ኮረጆም ከረጢትም ጫማም አትያዙ፤ በመንገድም ለማንም እጅ አትንሡ። ወደምትገቡበት ቤት ሁሉ አስቀድማችሁ ሰላም ለዚህ ቤት ይሁን በሉ። በዚያም የሰላም ልጅ ቢኖር፥ ሰላማችሁ ያድርበታል፤ አለዚያም ይመለስላችኋል። በዚያም ቤት ከእነርሱ ዘንድ ካለው እየበላችሁና እየጠጣችሁ ተቀመጡ፤ ለሠራተኛ ደመወዙ ይገባዋልና። ከቤት ወደ ቤት አትተላለፉ። ወደምትገቡባትም ከተማ ሁሉ ቢቀበሉአችሁ፥ ያቀረቡላችሁን ብሉ በእርስዋም ያሉትን ድውዮችን ፈውሱና የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ቀረበች፡ በሉአቸው። ነገር ግን ወደምትገቡባት ከተማ ሁሉ ባይቀበሉአችሁ፥ ወደ አደባባይዋ ወጥታችሁ ከከተማችሁ የተጣበቀብንን ትቢያ እንኳን እናራግፍላችኋለን፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ግን ወደ እናንተ እንደ ቀረበች ይህን እወቁ በሉ እላችኋለሁ፥ በዚያን ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶም ይቀልላታል.....
05 Dec, 17:51
04 Dec, 18:03
ከዚህም ሁሉ በፊት እጃቸውን በላያችሁ ይጭናሉ ያሳድዱአችሁማል፤ ስለ ስሜም ወደ ምኵራብና ወደ ወኅኒ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ወደ ነገሥታትና ወደ ገዥዎችም ይወስዱአችኋል፤ ይህም ለምስክርነት ይሆንላችኋል። ሰለዚህ እንዴት እንድትመልሱ አስቀድማችሁ እንዳታስቡ በልባችሁ አኑሩት፤ ወደረኞቻችሁ ሁሉ ሊቃወሙና ሊከራከሩ የማይችሉትን አፍና ጥበብ እሰጣችኋለሁና። ወላጆችም ስንኳ ወንድሞችም ዘመዶችም ወዳጆችም አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ከእናንተም አንዳንዱን ይገድላሉ፤ በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ። ከራሳችሁም አንዲት ጠጉር ስንኳ አትጠፋም፤ በመታገሣችሁም ነፍሳችሁን ታገኛላችሁ። ኢየሩሳሌም ግን በጭፍራ ተከባ ስታዩ በዚያን ጊዜ ጥፋትዋ እንደ ቀረበ እወቁ.............
04 Dec, 18:03
04 Dec, 04:41
04 Dec, 04:41
ወንድምም ወንድሙን፥ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ ይገድሉአቸውማል። በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። በአንዲቱ ከተማም መከራ ቢያሳዩአችሁ ወደ ሌላይቱ ሽሹ፤ እውነት እላችኋለሁና፥ የሰው ልጅ እስኪመጣ ድረስ የእስራኤልን ከተማዎች አትዘልቁም። ደቀ መዝሙር ከመምህሩ፥ ባሪያም ከጌታው አይበልጥም። ደቀ መዝሙር እንደ መምህሩ፥ ባሪያም እንደ ጌታው መሆኑ ይበቃዋል። ባለቤቱን ብዔል ዜቡል ካሉት፥ ቤተሰዎቹንማ እንዴት አብዝተው አይሉአቸው እንግዲህ አትፍሩአቸው፤
ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም። የእናንተስ የራሳችሁ ጠጉር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል።
እንግዲህ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ..........02 Dec, 16:29
በዚያን ጊዜ ሕዝቡን ትቶ ወደ ቤት ገባ። ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ ቀርበውየእርሻውን እንክርዳድ ምሳሌ ተርጕምልን አሉት። እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው መልካምን ዘር የዘራው የሰው ልጅ ነው፤ እርሻውም ዓለም ነው፤ መልካሙም ዘር የመንግሥት ልጆች ናቸው፤ እንክርዳዱም የክፉው ልጆች ናቸው፥ የዘራውም ጠላት ዲያብሎስ ነው፤ መከሩም የዓለም መጨረሻ ነው፥ አጫጆችም መላእክት ናቸው። እንግዲህ እንክርዳድ ተለቅሞ በእሳት እንደሚቃጠል፥ በዓለም መጨረሻ እንዲሁ ይሆናል። የሰው ልጅ መላእክቱን ይልካል፥ ከመንግሥቱም እንቅፋትን ሁሉ ዓመፃንም የሚያደርጉትን ይለቅማሉ፥ ወደ እቶነ እሳትም ይጥሉአቸዋል፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል.....
02 Dec, 16:21
01 Dec, 18:43
ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ። በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም።
ሰውን ከአባቱ፥ ሴት ልጅንም ከእናትዋ፥ ምራትንም ከአማትዋ እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና፤ ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል። ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።
......
01 Dec, 18:43
30 Nov, 10:30
24 Nov, 17:48
የታደሙትንም የከበሬታ ስፍራ እንደ መረጡ ተመልክቶ ምሳሌ ነገራቸው እንዲህ ሲል ማንም ለሰርግ ቢጠራህ በከበሬታ ስፍራ አትቀመጥ፤ ምናልባት ከአንተ ይልቅ የከበረ ተጠርቶ ይሆናልና፡ አንተን እርሱንም የጠራ መጥቶ ለዚህ ስፍራ ተውለት ይልሃል፥ በዚያን ጊዜም እያፈርህ በዝቅተኛው ስፍራ ልትሆን ትጀምራለህ። ነገር ግን በተጠራህ ጊዜ፥ የጠራህ መጥቶ ወዳጄ ሆይ፥ ወደ ላይ ውጣ እንዲልህ፥ ሄደህ በዝቅተኛው ስፍራ ተቀመጥ፤ ያን ጊዜም ከአንተ ጋር በተቀመጡት ሁሉ ፊት ክብር ይሆንልሃል።
የጠራውንም ደግሞ እንዲህ አለው ምሳ ወይም እራት ባደረግህ ጊዜ፥ እነርሱ ደግሞ በተራቸው ምናልባት እንዳይጠሩህ ብድራትም እንዳይመልሱልህ፥ ወዳጆችህንና ወንድሞችህን ዘመዶችህንም ባለ ጠጎች ጎረቤቶችህንም አትጥራ። ነገር ግን ግብዣ ባደረግህ ጊዜ ድሆችንና ጕንድሾችን አንካሶችንም ዕውሮችንም ጥራ፤ የሚመልሱት ብድራት የላቸውምና ብፁዕ ትሆናለህ፤ በጻድቃን ትንሣኤ ይመለስልሃልና። ከተቀመጡትም አንዱ ይህን ሰምቶ በእግዚአብሔር መንግሥት እንጀራ የሚበላ ብፁዕ ነው አለው። እርሱ ግን እንዲህ አለው አንድ ሰው ታላቅ እራት አድርጎ ብዙዎችን ጠራ....
እግዚኦ በኃይልከ ይትፌሣሕ ንጉሥ
ወብዙኃ ይትሐሠይ በአድኅኖትከ
ፍትወተ ነፍሱ ወሀብኮ
24 Nov, 17:48
24 Nov, 17:47
22 Nov, 18:24
22 Nov, 18:24
እርሱም ኢየሱስ ከይሁዳ ወደ ገሊላ እንደ መጣ ሰምቶ ልጁ ሊሞት ስላለው ወደ እርሱ ሄደ ወርዶም እንዲፈውስለት ለመነው። ስለዚህም ኢየሱስ ምልክትና ድንቅ ነገር ካላያችሁ ከቶ አታምኑም አለው። ሹሙም ጌታ ሆይ፥ ብላቴናዬ ሳይሞት ውረድ አለው። ኢየሱስም ሂድ፤ ልጅህ በሕይወት አለ አለው። ሰውዬውም ኢየሱስ የነገረውን ቃል አምኖ ሄደ። እርሱም ሲወርድ ሳለ ባሮቹ ተገናኙትና ብላቴናህ በሕይወት አለ ብለው ነገሩት። እርሱም በጎ የሆነበትን ሰዓት ጠየቃቸው፤ እነርሱም ትናንት በሰባት ሰዓት ንዳዱ ለቀቀው አሉት። አባቱም ኢየሱስ ልጅህ በሕይወት አለ ባለው በዚያ ሰዓት እንደ ሆነ አወቀ፤ እርሱም ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር አመነ። ይህም ደግሞ ኢየሱስ ከይሁዳ ወደ ገሊላ መጥቶ ያደረገው ሁለተኛ ምልክት ነው.........
እስመ አቡየ ወእምየ ገደፉኒ
ወእግዚአብሔር ተወክፈኒ
ምርሀኒ እግዚኦ ፍኖተከ
21 Nov, 17:59
የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ፥ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል፤ አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ፤ እረኛም በጎቹን ከፍየሎች እንደሚለይ እርስ በርሳቸው ይለያቸዋል፥ በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል።
ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።
ጻድቃንም መልሰው ይሉታል ጌታ ሆይ፥ ተርበህ አይተን መቼ አበላንህስ? ወይስ ተጠምተህ አይተን መቼ አጠጣንህ? እንግዳ ሆነህስ አይተን መቼ ተቀበልንህ? ወይስ ታርዘህ አይተን መቼ አለበስንህ? ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ አይተን መቼ ወደ አንተ መጣን? ንጉሡም መልሶ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ
ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል።
በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ። ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥ ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና።
እነርሱ ደግሞ ይመልሱና ጌታ ሆይ፥ ተርበህ ወይስ ተጠምተህ ወይስ እንግዳ ሆነህ ወይስ ታርዘህ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ መቼ አይተን አላገለገልንህም? ይሉታል።
ያን ጊዜ
እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም ብሎ ይመልስላቸዋል። እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ......
21 Nov, 17:58
20 Nov, 20:58
ወንድምህም ቢበድልህ፥ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፥ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው፤ ባይሰማህ ግን፥ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር አፍ ነገር ሁሉ እንዲጸና፥ ዳግመኛ አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ፤ እነርሱንም ባይሰማ፥ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፥ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ።
ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል
። ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና........
20 Nov, 20:58
17 Nov, 17:13
ኢየሱስም መለሰላቸው፥ እንዲህ ሲል ነገርኋችሁ፡ አታምኑምም፡ እኔ በአባቴ ስም የማደርገው ሥራ ይህ ስለ እኔ ይመሰክራል፤ እናንተ ግን እንደ ነገርኋችሁ ከበጎቼ ስላልሆናችሁ አታምኑም። በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ ይከተሉኝማል፤ እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።
አይሁድ ሊወግሩት ደግመው ድንጋይ አነሡ። ኢየሱስ ከአባቴ ብዙ መልካም ሥራ አሳየኋችሁ፤ ከእነርሱ ስለ ማናቸው ሥራ ትወግሩኛላችሁ? ብሎ መለሰላቸው።አይሁድም ስለ መልካም ሥራ አንወግርህም፤ ስለ ስድብ፤ አንተም ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለ ማድረግህ ነው እንጂ ብለው መለሱለት።
ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው እኔ አማልክት ናችሁ አልሁ ተብሎ በሕጋችሁ የተጻፈ አይደለምን? መጽሐፉ ሊሻር አይቻልምና እነዚያን የእግዚአብሔር ቃል የመጣላቸውን አማልክት ካላቸው፥ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ፡ ስላልሁ እናንተ አብ የቀደሰውን ወደ ዓለምም የላከውን ትሳደባለህ ትሉታላችሁን? እኔ የአባቴን ሥራ ባላደርግ አትመኑኝ፤ ባደርገው ግን፥ እኔን ስንኳ ባታምኑ አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ።
እንግዲህ ደግመው ሊይዙት ፈለጉ፤ ከእጃቸውም ወጣ። ዮሐንስም በመጀመሪያ ያጠምቅበት ወደ ነበረው ስፍራ ወደ ዮርዳኖስ ማዶ እንደ ገና ሄደ በዚያም ኖረ። ብዙ ሰዎችም ወደ እርሱ መጥተው ዮሐንስ አንድ ምልክት ስንኳ አላደረገም፥ ነገር ግን ዮሐንስ ስለዚህ ሰው የተናገረው ሁሉ እውነት ነበረ፡ አሉ። በዚያም ብዙዎች በእርሱ አመኑ............
17 Nov, 17:12
17 Nov, 09:25
16 Nov, 19:11
15 Nov, 18:17
15 Nov, 18:17
14 Nov, 18:44
14 Nov, 18:44
12 Nov, 18:50
12 Nov, 18:50
11 Nov, 18:51
11 Nov, 18:15
10 Nov, 17:58
10 Nov, 17:39
10 Nov, 17:39
10 Nov, 03:01
09 Nov, 18:33
08 Nov, 18:39
08 Nov, 18:39
07 Nov, 18:10
07 Nov, 18:10
06 Nov, 19:01
06 Nov, 19:01
05 Nov, 18:35
05 Nov, 18:35
04 Nov, 19:09
04 Nov, 19:09
03 Nov, 20:12
03 Nov, 20:12
03 Nov, 20:12
01 Nov, 18:40
01 Nov, 18:40
31 Oct, 19:21
31 Oct, 19:20
29 Oct, 17:10
29 Oct, 17:10
29 Oct, 17:10
28 Oct, 19:06
28 Oct, 19:06
27 Oct, 19:18
27 Oct, 19:18
27 Oct, 06:09
25 Oct, 18:15
25 Oct, 18:14
24 Oct, 18:31
24 Oct, 18:31
23 Oct, 22:26
23 Oct, 22:26
23 Oct, 12:23
23 Oct, 08:02
22 Oct, 17:42
22 Oct, 17:42
21 Oct, 19:39
21 Oct, 19:39